Professional Documents
Culture Documents
ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት
የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ጥናትና ምርምር
ዳይሬክቶሬት
አዲስ አበባ
ም ስ ጋ ና
ይህንን ጥናት እንድናከናውን ርዕስ በመምረጥና ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን እንዲሟሉ
በማድረግ እንዲሁም ጥናቱን ሚያግዙ ስልጠናዎችን እንድንወስድ ሙሉ ድጋፍ ያደረገልንን
ተቋማችንና አመራሩን ማመስገን እፈልጋለን፡፡ በተጨማሪም የጥናትና ምርምር ጠቅላላ
ባለሙያዎችና ዳይሬክተራችንን ከጎናችን በመሆን የሀሳብ ድጋፍና አቅጣጫ ስለሰጡን
እናመሰግናለን፡፡ በመጨረሻም መረጃ በመስጠት የተባበሩን የ40/60 ቤቶች ልማት ኤጀንሲ፤
20/80 ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ፤ ቂርቆስ ክ/ከተማ፤ ቦሌ ክ/ከተማ፤ አራዳ ክ/ከተማ፤
አዲስ ከተማ ክ/ከተማ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ፤ የባህርና ትራንዚት ሎጂስቲክ አገልግሎት
ድርጅት፤ የባህልና ቱሪዝም፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፤ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን፤
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከልና መቆጣጠር፤
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ፤ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ሚኒሊክ
ሆስፒታል፤ የካቲት 12 ሆስፒታል፤ ዘውዲቱ ሆስፒታል፤ ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል፤
የራስ ደስታ ሆስፒታል፤ ቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታልን እናመስግናለን፡፡
i
ማውጫ
የሠንጠረዥ ዝርዝር ............................................................................................................................................. vi
ማጠቃለያ (Abstract) ................................................................................................................................ viii
ክፍል አንድ ................................................................................................................................................... 1
መግቢያ.......................................................................................................................................................... 1
1.1. ዳራ (Back ground of the study) ........................................................................................... 1
1.2. ሰበበ ጥናት (Statement of the problem) ............................................................................... 2
1.3. የጥናቱ አስፈላጊነት፣ ..................................................................................................................... 3
1.4. የጥናቱ ዓላማ ................................................................................................................................ 3
1.4.1. ጥቅል አላማ .......................................................................................................................... 3
1.4.2. ዝርዝር አላማ ........................................................................................................................ 4
1.5. የጥናቱ ወሰን ................................................................................................................................. 4
1.6. የሚጠበቅ ውጤት፣ ....................................................................................................................... 4
1.7. የጥናቱ ዘዴ፣ ................................................................................................................................. 5
1.7.1. የናሙና አመራረጥ ዘዴ ........................................................................................................ 5
1.7.2. የመረጃ ማሰባሰቢያ መሳሪያዎች (Data gathering tools) ................................................ 8
1.7.3. የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ..................................................................................................... 11
1.8. የጥናቱ ውስንነት (Limitation) ................................................................................................... 11
1.9. ያጋጠሙ ችግሮች (Challenges of the study)...................................................................... 11
ክፍል ሁለት ................................................................................................................................................ 12
2. የቀደምት ጥናቶች ዳሰሳ (Literature review) .................................................................................. 12
2.1. ትርጉም........................................................................................................................................ 12
2.1.1. ደህንነት................................................................................................................................ 12
2.1.2. የግንባታ አካባቢ ደህንነት ትርጉም ..................................................................................... 12
2.2. የስራ ላይ ደህንነት ፕሮግራም ክፍሎች/ Elements of safety program.............................. 12
2.3. የደህንነት ልምድን አስቀድሞ በፕሮጀክት ላይ ማቀድ ያለው ጠቀሜታ ................................... 12
2.4. የግንባታ ቦታ ላይ አደጋዎች ...................................................................................................... 13
2.5. በግንባታ አካባቢ የአዳጋና የጉዳት መንስኤዎች .......................................................................... 14
2.6. የግንባታ ደህንነትን የሚጎዱ ሁኔታዎች .................................................................................... 16
2.7. የግንባታ ደህንነትን የተመለከቱ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ህጎች ........................................ 16
2.7.1. የግንባታ ደህንነት የተመለከቱ ህጎች ...................................................................................... 16
2.7.2. የግንባታ ደህንነትን የተመለከቱ ደንቦች.............................................................................. 19
ii
2.8. የውጪ ሀገር ተሞክሮዎች ......................................................................................................... 33
2.8.1. የብራዚል ተሞክሮ ............................................................................................................... 33
2.8.2. የሲንጋፖር ተሞክሮ ............................................................................................................ 35
2.9. ከዚህ በፊት የተደረጉ ጥናቶች (Case study) .......................................................................... 37
2.10. የሀገር ውስጥ ተሞክሮ ............................................................................................................ 38
2.10.1 የስራ ላይ ደህንነትና ጤንነት በኢትዮጵያ የግንባታ ዘርፍ በአዲስ አበባና በወልቂጤ በ2014
እ.ኤ.አ የተደረገ ጥናት ........................................................................................................................ 38
2.10.2 በደህንነትና ጤንነት ላይ ያለው አፈጻጸም ማሳያ በአዲስ አበባ በመንገድና ቤት ግንባታ
እ.ኤ.አ በ2014 የተደረገ ጥናት ........................................................................................................... 39
ክፍል ሶስት ................................................................................................................................................. 41
3. ትንታኔ እና የጥናቱ ግኝቶች .............................................................................................................. 41
3.1. ከመጠይቅ የተገኙ ትንታኔዎች ................................................................................................... 41
3.1.1. ከህንጻ ግንባታ የተገኙ ትንታኔዎች .................................................................................... 41
3.1.2. ከመንገድ ፕሮጀክቶች የተገኙ መጠይቆች ትንታኔ ............................................................ 62
3.1.3. የደህንነት ዕቃ አቅራቢዎችን የተመለከተ መጠይቅ ትንተና .............................................. 83
3.2. የጥናቱ ግኝቶች ........................................................................................................................... 87
3.2.1. ደህንነት በውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ ............................................................................. 87
3.2.2. ደህንነትን የተመለከቱ ህጎች እና አፈጻጸማቸው................................................................. 88
3.2.3. የደህንነት አስተዳደር ........................................................................................................... 88
3.2.4. በግንባታ ቦታ ላይ በደህንነት መጓደል ምክንያት የሚፈጠሩ አደጋዎች ............................ 91
3.2.5. በኮንስትራክሽን ስራ ምክንያት የደረሱ አደጋዎችን የመመዝገብ ልምድ እና የተመዘገቡ
አደጋዎች 100
3.2.6. የስራ ደህንነት ተግባራዊ እንዳይሆን የሚጠቀሱ ምክንያቶች .......................................... 102
3.2.7. የስራ ላይ ደህንነት መጓደል ያለው ተጽእኖ ..................................................................... 103
3.2.8. ከመንገድ ፕሮጀክቶች ጋር የተያያዙ ግኝቶች ................................................................... 104
4. የጥናቱ ድምዳሜ ............................................................................................................................... 110
5. የመፍትሄ ሀሳቦች (Recommendation) ......................................................................................... 114
6. ዋቢ .................................................................................................................................................... 119
7. አባሪ ................................................................................................................................................... 120
7.1. መጠይቆች ................................................................................................................................. 120
7.2. ቼክ ሊስት .................................................................................................................................. 120
7.3. ከተለያዩ የግንባታ ቦታዎች የተወሰዱ ፎቶ ግራፎች ............................................................. 120
iii
የምስል ዝርዝር
ምሰል 2.1፡ የአዳጋ ድግግሞሽ መጠን እና የአደጋው ክብደት መጠን ................................................................................. 37
ምስል 3-7፡ በሴፍቲ ጉድለት ምክንያት አደጋ ሲያጋጥም ተጠያቂው አካል ማን ነው............................................................ 50
መስል 3-12፡ የግንባታ ደህንነት ባለመተግበሩ ምክንያት ከስራው ውጪ የሆኑ የማህበረሰብ ከፍሎች ላይ የደረሱ አደጋዎች............ 56
ምስል 3-17፡ ለደህንነት የሚወጣው ወጪ በውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ ስለመካተቱ ......................................................... 64
iv
ምስል 3-28፡ ስልጠና በቋሚነት ስለመሰጠቱ ........................................................................................................... 79
ምስል 3-29፡ ደህንነት ባለመተግበሩ ምክንያት ከስራ ውጪ የሆኑ ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰው ጉዳት..................................... 82
ምስል 3-32፡ የደህንነት ዕቃዎቹ ደረጃቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸው የሚያረጋግጥ አካል ...................................................... 85
ምስል 3-33፡ በግባ ዘርፍ የተሰማሩ ተቋምት የደህንነት አልባሳትን የመግዛት ልምድ ............................................................ 85
ምስል 3-36፡ ዕድሜያቸው የገፋ የቀን ሰራተኞች እና የደህንነት አልባሳት ያልተሟላላቸው ሰራተኞች ....................................... 90
ምስል 3-45 ግንባቸው ሳይጠናቀቅ ለተጠቃሚ ክፍት የሆኑ መንገዶች ........................................................................... 105
ምስል 3-48፡ የወሰን ማስከበር ሂደቱ ሳይጠናቀቅ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች ............................................................ 109
v
የሠንጠረዥ ዝርዝር
ሠንጠረዥ 2-1፡ የሳይት ምልከታ ድግግሞሽ .............................................................................................................. 37
ሠንጠረዥ 3-7፡ ሰዓት እላፊና ትራፊክ በሚበዛበት የሚከናወኑ ሥራዎች ለአደጋ መፈጠር ያላቸው አስተዋጽኦ............................ 53
ሠንጠረዥ 3-11፡ ደህንነት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቢሰጥ ያለው አስተዋጽኦ ............................................................... 61
Table 3-18 ሠንጠረዥ 3-18፡ ሰዓት እላፊና የትrፊክ ፍሰት ለአደጋ መፈጠር ያላቸው አስተዋጽኦ .......................................... 73
ሠንጠረዥ 3-21፡ ደህንነት በከፍተና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ቢሰጥ ያለው ጠቀሜታ ....................................................... 78
ሠንጠረዥ 3-23፡ በርክክብ ወቅት ከደህንነት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሥራዎች ስለመጠናቀቃቸው ......................................... 80
vi
ሠንጠረዥ 3-28፡ ደህንነትን ውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ መግባ አለበት ብለው የሚያምኑ እና ያስገቡ ..................................... 87
vii
ማጠቃለያ (Abstract)
ጥናቱ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሚገኙ የህንጻ እና የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ
ያለውን የደህንነት ሁኔታ ምን ደረጃ ላይ እዳለ ለመለየት የተደረገ የዳሰሳ ጥናት ሲሆን
አላማውም በግንባታ አካባቢ ደህንነት ዙሪያ ያለውን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ በማጤን በስራ
በደህንነት ባለመተግበሩ ምክንያት የተፈጠሩ የአደጋ አይነቶችንና መንስኤያቸውን መለየት፣
የአደጋ መረጀ አያያዝ ስርዓቱ ምን እንደሚመስል መቃኘት እንዲሁም በግንባታ አካባቢ
ደህንነት ስላሉ ህጎችና የአፈጻጸም ደረጃቸውን ማጥናት ነው፡፡
viii
ክፍል አንድ
መግቢያ
የሙያ ደህንነት አጠባበቅ አለማቀፋዊ ገፅታ ስንመለከት እ.ኤ.አ 2013 የዓለም ስራ ድርጅት
ባወጣው ጥናታዊ ሪፖርት መሰረት በዓለማችን በየዓመቱ 331.5 ሚሊዮን የሚገመቱ የሥራ
ላይ አደጋዎችና 168.1 ሚሊዮን በስራ ምክንያት የሚከሰቱ በሽታዎች በሁሉም የኢንዱስትሪ
ዘርፎች ሰራተኞች ላይ እንደሚደርሱ ታውቋል፡፡ በዚህም የተነሳ 2.34 ሚለዮን ሠራተኞች
በስራ ላይ አደጋዎች ሳቢያ እንደሚያጡ ያለመከተው የድርጅቱ ሪፖርት በአማካይ በየአስራ
አምስት ሰከንድ አንድ ሰራተኛ ህይወት በስራ ላይ በሚደርስ አደጋ ሳቢያ እንደሚቀጠፍ
አስገንዝቧል፡፡
1
የስራ ላይ አደጋዎችና በስራ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በአሳሳቢ ደረጃ
እየጨመሩ መምጣታቸውን የጠቆመው ይህ ሪፖርት በተለይ አደገኛ የስራ ባህሪ ባላቸው
/ኮንስትራክሽ፣ ማዕድን፣, እርሻ/ የተሰማሩ የታዳጊ ሀገር ሰራተኞች የጉዳቱ ዋነኛ ተጠቂዎች
መሆናችን አመልክቷል፡፡ በስራ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችና የጤና ጉዳቶች በህይወት፣ በአካልና
በንብረት ላይ ያስከተሉት ውድመት በወጪ ሲሰላ የሀገሪቱን አጠቃላይ ብሄራዊ ገቢ እስከ 4%
እንደሚሸፍን ሪፖርቱ አሰታውቆ መንግስታት ይህን አሳሳቢ የልማት ችግር ትኩረት ሰጥተው
የተጠናከረ የመከላከልና የመቆጣጠር እንቅሰስቃሴ ሊያደርጉ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡[14]
አደጋ ማለት ማንኛውም በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል ማለት ነው፡፡[3]
ይህም በሰው ሕይወት ላይ እስከ ሞት ሊያደርስ ይችላል፡፡ በንብረት ላይ የሚደርሰው ጉዳት
በኢኮኖሚ እድገት ላይ ክፍተኛ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡ ይህ ሁኔታ በተመሳሳይ የሚቀጥል ከሆነ
በሀገራችን ያለውን የኮንስትራክሽኑን ኢንዱስትሪ ክፉኛ ይጎዳል በመሆኑም ይህ ጉዳይ ትኩረት
ይሻል፡፡ እንደ ILO መረጃ መሰረት 160 million አደጋዎች በየአመቱ እና 6,000 የሞት አደጋ
በየቀኑ በአለማችን ይከሰታል፡፡ የአለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (International Labour
Organization) ዘገባ በየቀኑ በአለም ዙሪያ ቢያንስ 6,000 አደጋዎች በኮንስትራክሽን ስራ
አከባቢ ይፈጠራል ብሏል፡፡ በተለይ ባደጉት ሀገራት በስራ አከባቢ ከሚፈጠሩት የሞት አደጋዎች
ውስጥ ከ25-40% ያለው የሞት አደጋ የሚፈጠረው በኮንስትራክሽን ስራ አከባቢ ነው፡፡
እንዲሁም እንደ አለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት በአንዳንድ ሀገራት 30%ቱ የኮንስትራክሽን
ሰራተኞች በጀርባ ህመምና በጡንቻ መሸማቀቅ ህመም እየተሰቃዩ እንደሚገኙ ገልጿል፡፡ በተለይ
በሀገራችን በኢትዮጵያ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ እየደረሰ ያለው አደጋን የሚያሳይ
መረጃ ባይኖርም ነገር ግን በኮንስትራክሽን ስራ አከባቢ ብዙዎች በደረሰባቸው አደጋ
ሕይወታቸውን አጥተዋል ብዙዎች የአካል ጉዳተኛ ሆነዋል በተለይ ደግሞ እጅግ የሚሳዝነው
ለዚህ አደጋ የተጋለጡት በስራው ላይ ያሉት ብቻ ሳይሆኑ በስራው ላይ ተሳታፊ ያልሆኑ
አዋቂዎችና ህፃናትም ጭምር ነው፡፡ [4]
2
ከኢንደስትሪው እድገት ጋር አብሮ የሚጨምር ይሆናል፡፡ ለዚህም ስለ ግንባታ አካባቢ ደህንነት
የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን እንደ ምክንያትነት ይጠቀሳል፡፡ በግንባታ አካባቢ ደህንነት
መጓደል ምክንያት የሰውን ህይወት አደጋ ላይ እሰከመጣልና ለሞት እስከ ማድረስ የሚደርስ
አደጋ ሲደርስ ይስተዋላል፡፡ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ በመሆኑ የተነሳ አደጋው በሰው ህይወት
ላይ ብቻ ሳይሆን በንብረት ላይ እንዲሁም አንድ ስራ በተያዘለት ወጪ፣ ጥራትና ጊዜ መሰረት
እንዳይጠናቀቅ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደረ ነው፡፡ ይህም የግንባታውን ጊዜ፤ ገንዘብና የሰው ሀይል
የታለመለትን ግብ እንዳይመታ ትልቅ እንቅፋት ከመሆኑም ባሻገር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ
ያዳክማል፡፡
3
1.4.2. ዝርዝር አላማ
በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የግንባታ አካባቢ ደህንነትን በተመለከተ የተቀመጡ ህጎቸችና
ደንቦች እና ተፈጻሚነታቸውን መለየት እንዲሁም በውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ
መካተታቸውን ማረጋገጥ
4
ሀ) በአሁኑ ጊዜ በአገራችን በተጨባጭ ያለው የግንባታ ስራ ደህንነት ሁኔታ
ሐ) የመፍትሄ ሀሳቦች፣
5
የግንባታ ቦታ አመራረጥን በተመለከተ ናሙና ለመውሰድ እንደ መመዘኛነት የተጠቀምናቸው
መስፈርቶች፤ በመንግስት ባለቤትነት እየተሰሩ ያሉ የግንባታ ስራዎች( የጋራ መኖሪያ ቤቶች
እና ሌሎች ግንባታዎች)፣ የግል ፕሮጀክቶች እና የመንገድ ፕሮጀክቶች ሆነው ከደህንነት ጋር
ተያያዥነት ያላቸውን ጉዳዮች ለማየት በግንባታ ላይ የሚገኙ ወይም ግንባታቸው ወደ
መጠናቀቅ የደረሱ የተመረጡ ሲሆኑ በነዚህ የግንባታ ቦታዎች በአካል በመገኘት መረጃ
ለመሰብሰብ ተችሏል፡፡ በዚህም መሰረት የአዲስ አበባ መንንዶች ባለስልጣን በባለቤትነት
እያስገነባቸው ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶችን፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እየተገነቡ ያሉ የግል
ፕሮጀክቶችን እንዲሁም መንግስት እያስገነባቸው ያሉ የፌደራል መንግስት ህንፃዎች፣
የኮንስትራክሽን እና አስተዳደር ቢሮዎች፣ የክፍለ ከተማ ግንባታዎች፣ ሌሎች የመንግስት
ድርጅቶች እንዲሁም በ20/80 እና በ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክቶች
በናሙናነት ተመርጠዋል፡፡ እነዚህንም የግንባታ ቦታዎች ሙሉ ለመሉ ተደራሽ ለማድረግ
ተችሏል፡፡
6
የጥናቱን የናሙና አወሳሰድ ዘዴ የሚያሳይ ሠንጠረዥ
ተ በአዲስ አበባ በመንግስት ባለቤትነት የሚሰሩ የፕሮጀክት በጥናቱ ተደራሽ በጥናቱ ተደራሽ ምርመራ
በቁጥር በቁጥር
1 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት 13 የናሙና መጠኑም 90% ትክክል ቢሆንን
(Level of confidenece) 10% ደግሞ
ቢሮ
ሥህተት ቢኖረዉ (possible/megin of
2 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽን 49 Errors) በሚለዉ አግባብ የተሠላ ነዉ
ቢሮ
3 በከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር 5
4 በአዲስ አበባ ቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ 7
5 በተለያዩ የመንግስት ድርጅቶች የሚገነቡ 6
48 52
6 በተለያዩ የግል የግንባታ ፕሮጀክቶች 80
ድምር 160
7 በአዲስ አበባ ከተማ ግንባታቸው እየተካሄደ ያለ 21 18 18
የመንገድ ፕሮጀክቶች
በ2008 ህንፃ ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚሣተፉ ብዛት በጥናቱ ተደራሽ በጥናቱ በጥናቱ የናሙና መጠኑም 95% ትክክል ቢሆንን
መደረግ ተደራሽ (Level of confidenece) 5% ደግሞ ሥህተት
የተቋራጭና የግንባታ አማካሪወች ብዛት በቁጥር ያለበት ተደራሽ
ናሙና ብዛት በቁጥር ተደርገው ቢኖረዉ (possible/margin of Errors)
የተደረገ
ምላሽ የሰጡ በሚለዉ አግባብ የተሠላ ነዉ
በቁጥር
1 የሥራ ተቋራጮች 1462 323 359 217
2 የግንባታ አማካሪዎች 60 53 53 31
በ2008 ግንባታቸው እየተከናወኑ ላሉ የመንገድ
ፕሮጀክቶቹ ላይ የሚሣተፉ የተቋራጭና
የግንባታ አማካሪወች ብዛት
የሥራ ተቋራጮች 21 18 18 17
የግንባታ አማካሪዎች 13 13 12 11
በዚህም መሰረት በድምሩ በመንገድና በህንፃ ግንባታ 377 የሥራ ተቋራጮችን ተደራሽ
ተደርገው ነገርግን 234 ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ 65 አማካሪዎች ተደራሽ ተደርገው 42 ምላሽ
ሰጥተዋል፣ 34 የግንባታ ባለቤቶቸ ተደራሽተደርገው 34 ምላሽ ሰጥተዋል በተጨማሪም 812
የግንባታ ሰራተኞች ተደራሽ ተደርገው 474 ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
7
1.7.2. የመረጃ ማሰባሰቢያ መሳሪያዎች (Data gathering tools)
ይህን የዳሰሳ ጥናት ዓላማ ከግብ ለማድረስ በኮንስትራክሽን ስራ ደህንነት (work zone safety)
በሚገባ ባለመተግበሩ ምክንያት የሚፈጠሩ በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን
መንስኤቸውንና መደረግ የሚገባውን ጥንቃቄ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን መረጃዎች ከስራ
ተቋራጭ፣ አማካሪ፣ ከግንባታ ባለቤት ፣ስራውን ከሚያከናውኑት የግንባታ ሰራተኞች፣
ከሆስፒታል፣ ከትራፊክ ማኔጂመንት ኤጀንሲ፣ ከእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከያና
መቆጣጠር፤ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ከሰራተኛና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ከመንገዶች
ባለስልጣን እና የመሳሰሉት መረጃ ለማሰባሰብ የሚያስፈልጉ የአጠናን ስልቶች እንደሚከተለው
ተገልጿል፡፡
ሣይት ፎርማን
9
ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተር ፕራይዝ (40/60)፣ በአዲስ አበባ ቤቶች
ልማት ኘሮጀክት ጽ/ቤት (20/80)፣ የግል የግንባታ ፕሮጀክቶች እንዲሁም የመንገድ
ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ምልከታ በማካሄድ አጠቃላይ የደህንነት ሁኔታው ምን
እንደሚመስል በፎቶግራፍ እና በቪዲዮ ማስረጃ በማከል መረጃ ተሰብስቧል፡፡
1 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ (ዋና መስሪያ ቤት) 13 ስድስት ኪሎ
2 የአዲስ አባባ ከተማ የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ 40/60 ዋና መስሪያ ቤት 8 አራት ኪሎ
2 የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት ተቋራጭ፤አማካሪና ሣይት
መሃንዲስ
10
11 ሪፈራል ሆስፒታሎች የሆስፒታሉ ሜዲካል
ዳይሬክተሮች
11
ክፍል ሁለት
2. የቀደምት ጥናቶች ዳሰሳ (Literature review)
2.1. ትርጉም
2.1.1. ደህንነት
ዉጤታማትን ይጨምራል
12
ያልታሰቡ ወጪዎችን ይቀንሳል
13
መሆን አለበት፡፡ ሠራተኞቹ አደጋ በሚደርስ ጊዜ ማድረግ ስላለባቸው ድርጊቶች መሰልጠን
አለባቸው፡፡
7. አደጋን አለመመዝገብ እና አለማስቀመጥ
ማንኛውንም ሠራተኛ ላይ የደረሰን አደጋን፣ የተወሰደውን ህክምና አለመመዝገብ ለወደፊት
ሊደርሱ ለሚችሉ አደጋዎች መፍትሄ እንዳይኖር ያረጋል፡፡ ከሌሎች ተሞክሮ እንዳየነው
የግንባታ ቦታ ድህረ-ገፅ መፅሀፍ ስለ ተከናወኑት ስራዎች ሁሉ የሚተርክ እና አንድ ችግር
ሲፈጠር መፍትሄ የካተተ መፅሀፍ ማዘጋጀት አመዘጋገቡን ቀላል ያደርገዋል፡፡
8. ብየዳ
መበየድ የተለመደ የግንባታ ቦታ ላይ ስራ ሲሆን አብዛኛው በያጅ ስራውን አቅልሎ በማየት
እና የደህንነት መሳሪያ መጠቀም አመቺ ስላልሆን ቸልተኛ ይሆናል፡፡ ምንም ቸልተኛ
ቢሆንም በሚበየድበት ወቅት የብረት ፍንጣቂዎች አይን ውስጥ እንዳይገባ ግዴታ የአየን
መከላከያ መነፅር መጠቀም አለበት፡፡
9. ስልጠና አለመኖር
የስራ ቦታ ላይ አደጋዎች ለመቀነስ በየጊዜው ስልጠና መስጠት ዋናው ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡
የግንባታ ቦታ ተቆጣጣሪው ሠራተኞቹ በየጊዜው ስልጠና አንደሚወስዱ እነ ስለ ስራ ቦታ
ደህንነት በቂ አውቀት እንዳላቸው የማወቅ ገዴታ አለበት፡፡ ሠራተኛው የስራውን ህግ
ማወቅ እና እራሱን ብሎም በአካባቢው ላለው ማህበረሰብ ደህንነትን ስለ መጠበቅ ስልጠና
መውሰድ አለበት፡፡
14
1. የፖሊሲ/ የህግ ክፍተት
2. የአደረጃጀት ክፍተት
3. የግንዛቤ ክፍተት
4. የመረጃ ክፍተት
5. የቅንጅት ክፍተት
6. የህግ አፈጻጸም ክፍተት
7. የጥናትና ምርምር ክፍተት
8. የክትትልና ግምገማ ክፍተት
16
1. ሰራተኛው በአንድ በተወሰነለት መሬት ወይም ቦታ ውስጥ የስራውን አገልግሎት
ሲፈጽም የሆነ እደሆነ በስራው ጊዜና ቦታ በሰራተኛው ለሚደርሱበት አደጋዎች አሰሪው
ኃላፊ ነው፡፡
2. በሥራ ሰዓት የሚፈቀደው የእረፍት ጊዜ እንደ ስራ ጊዜ ሆኖ ይቆጠራል፡፡
3. በነዚሁ የእረፍት ጊዜ የሰራተኞች ማረፊያ የተዘጋጁ ቦታዎች እንደ ስራ ቦታ ክፍል
ሆነው ይቆጠራሉ፡፡
1. አደጋ ወይም በሽታው የደረሰበት ሰው አስቦ ባደረገው ጥፋረ መሆኑ አሰሪው ካስረዳ
ከዚህ በፊት ባሉት ቁጥሮች ከተወሰነው ኃላፊነት አሰሪው ነጻ ይሆናል፡፡
2. እንዲሁም አደጋው ወይም በሽታው የደረሰበት ሰራተኛ በግልጽ በጽሁፍ የተሰጠውን
ትእዛዝ በመተላለፍ መሆኑን ካስረዳ አሰሪው ነፃ ይሆናል፡፡
17
1. አሰሪው ስለ ህክምና መድሀኒቶች፣ ሆስፒታልና ሌሎችም አደጋ ወይም በሽታው
ሰራተኛውን የሚያስገድዱትንና በሚገባ አኳኋን የተደረጉትን ወጪዎች ሁሉ መክፈል
አለበት፡፡
2. በአደጋው ወይም በበሽታው ጠንቅ ሰራተኛው የሞተ እንደሆነ በዚሁ አኳኋን ለመቃብር
ሥርአቶች አስፈላጊ የሆኑትን ወጪዎች አሰሪው መክፈል አለበት፡፡
1. ማንኛውም ህንፃ ሲገነባ ወይም ሲፈርስ በሕዝብ ላይ አደጋ ወይም ከፍተኛ መጉላላት
ሊያስከትል የሚችል ከሆነ የግንባታ ቦታው ባለቤት ሥራውን ከመጀመሩ በፊት አስፈላ
18
ጊውን የመከላከያ ሥራ እንዲያከናውን በከተማው አስተደደር ወይም በተሰየመው አካል
ሊጠየቅ ይችላል፡
2. አንድን ህንፃ ከመገንባት ወይም ከማፍረስ ጋር የተያያዘ ሥራ የከተማው አስተደደር
ወይም የተሰየመው አካል ንብረት በሆነ ወይም በእርሱ ቁጥጥር ሥር ባለ ንብረት
ጥንካሬ፣ ደረጃ፣ ደህንነት፣ ጥራት ወይም አቀማመጥ ላይ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ
የከተማው አስተደደር ካመነ ባለቤቱ በሥራው ምክንያት ለሚያደርሰው ጉዳት መጠገኛ
የሚውል ማስያዣ ወይም ዋስትና እንዲሰጥ ሊጠይቀው ይችላል፡፡
3. ከግንባታ ቦታ ክልል ውጪ የግንባታ ቁሳቁስ ወይም ተረፈ ግንባታ የተጠራቀመ ከሆነ
የከተማው አስተዳደር ወይም የተሰየመው አካል በጽሑፍ ማስታወቂያ በሚገለጽ የጊዜ
ገደብ ውስጥ ባለቤቱ እንዲያነሳ ሊያዝ ይችላል፡፡
4. ማኛውም የግንባታ ቦታ ባለቤት ወይም ከህንፃ ግንባታ ወይም ማፍረስ ጋር የተያያዘ
ስራ የሚሰሩ ሰዎች ሥራውን በሚያከናውኑበት ጊዜ በሥራው ቦታ ላይ እንደ
አስፈላጊነቱ ጊዜያዊ መጠለያ ሊያሰሩ ይችላሉ፡፡
5. ማንኛውም የግንባታ ቦታ ባለቤት ወይም የህንፃ ግንባታ ወይም ማፍረስ ስራ የሚሰራ
ሰው በሥራው ላይ ለሚሰማሩ ሰዎች የሚሆን ተቀባይነት ያለው የንጽህና ቦታ በግንባታ
ሥፍራው ላይ ወይም በከተማው አስተዳደር ወይም በተሰየመው አካል ፈቃድ በሌላ ቦታ
ላይ ሳያዘጋጅ የግንባታም ሆነ የማፈረስ ሥራውን መጀመርም ሆነ መቀጠል
አይችልም፡፡ እንዲህ ያለው ዝግጅት እስኪደረግ ድረስ ሥራው እንዲቆም ይደረጋል፡፡
19
በንዑስ አንቀጽ 45.7 "የተቋራጩ ሠራተኞች ተቋራጩ በቀረጸው የአደጋ አያያዝ
ሥርዓት መሰረት ሂደቱን ተከትለው አደጋን ሪፖርት ማድረግ አለባቸው"፡፡
በንዑስ አንቀጽ 45.9 "ተቋራጩ የእሳት፣ ወይም ሌላ ማንኛውም አደጋ ላይ የተነደፉ
የመከላከያ እርምጃዎች ላይ በሰራተኞች መካከል አብሮ መስራትን ማረጋገጥ እንዲሁም
የተቋራጩ የስራ ልምዶች ወይም ሌሎች ክስተቶች ላይ ማንኛውም ለውጥ ሲኖር እና
ከላይ የተጠቀሱ አደጋዎችን የሚጨምሩ ወይም የአዲስ አደጋ ምክንያቶችን ለሕዝብ
አካል ማሳወቅ አለበት፡፡
ንዑስ አንቀጽ 45.10 "ተቋራጩ የመጀመሪያ እርዳታ መገልገያዎችን ማቅረብ እና
የህዝቡ አካል እንደሚፈልገው ሰራተኞች ለመጀመሪያ እርዳታ ሂደት መገዛታቸውን
ማረጋገጥ አለበት"፡፡
በንዑስ አንቀጽ 34.2 " ተቋራጩ በውሉ መሠረት ለሚከናወኑት የግንባታ ሥራዎች
እና ዘዴዎች መረጋጋት እና ደህንነት ሙሉ ኃላፊነት ይወስዳል."
20
በንዑስ አንቀጽ 45.3 "ተቋራጩ በራሱ ኃላፊነትና ወጪ አስፈላጊ እርምጃዎችን
በመውሰድ ያሉቱን ስትራክቸሮችና ዝርጋታዎችን መጠበቅ እና ሲበላሹም ማስተካከል
አለበት፡፡ ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ወይም በመሀንዲሱ አስፈላጊ የሆኑ እንደ
መብራት፣ ጥበቃ፣ አጥር እና የደህንነት መሣሪያዎችን በራሱ ወጪ የማቅረብና
የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡"
በንዑስ አንቀጽ 45.9 "ተቋራጩ የእሳት፣ ወይም ሌላ ማንኛውም አደጋ ላይ የተነደፉ
የመከላከያ እርምጃዎች ላይ በሰራተኞች መካከል አብሮ መስራትን ማረጋገጥ እንዲሁም
የተቋራጩ የስራ ልምዶች ወይም ሌሎች ክስተቶች ላይ ማንኛውም ለውጥ ሲኖር እና
ከላይ የተጠቀሱ አደጋዎችን የሚጨምሩ ወይም የአዲስ አደጋ ምክንያቶችን ለሕዝብ
አካል ማሳወቅ አለበት፡፡"
21
35.2.8. ከብረት የተሰሩ መሰላሎች ወይም በእንጨት ተሰርተው በሽቦ የተጠናከሩ መሰላሎች
በሃይል የተሞላ የኤሌክትሪክ መሣሪያ ባለበት ቦታ ላይ መጠቀም የተከለከለ ነው፣
35.2.9. የመሰላሎች ርዝመት ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት መሆን ይኖርበታል፣
ሀ) ለባለድጋፍ መሰላሎች ወይም ተቀጣይ ለሆኑ ባለድጋፍ መሰላሎች 4.8 ሜትር፣
ለ) ከመሰላሉ የታችኛው ክፍል ከ2.5 ሜትር በላይ ለሆነ ከፍታ ሠራተኞች
እንዳይወድቁ ለመከላከል የሚስችል የደህንነት መጠበቂያ አጥር (ኬጅ) ሊኖረው
ይገባል፣
35.2.11. የማይንቀሳቀሱ መሰላሎች መተከል ያለባቸው በየመሐከላቸው የ3 ሜትር ርቀት
እንዲኖር ተደርጎ ሆኖ ከላይ እስከታች ያለው አካላቸው ይህን ርቀት መጠበቅ
ይኖርበታል፣
35.2.12. በተተከሉ መሰላሎች ላይ ከሚገኙ መወጣጫዎች በስተጀርባ በትንሹ 1.75 ሜትር
ስፋት ያለው ቦታ በቋሚነት እንዲኖር ማድረግ ይገባል፣
35.2.13. ከመሰላሎቹ በላይ መወጣጫዎች እንዳይኖሩ ሆኖ የጎን ቋሚዎቹ ከመሰላሎቹ
ማረፊያ በላይ 90 ሳ.ሜ እስከሚቀረው ድረስ መቀጠል ይኖርባቸዋል፣
37. ስለ ከፍታ እና የጣሪያ ላይ ሥራዎች
37.1. የከፍታ ላይ ሥራዎች
37.1.1. ሠራተኞች ከወለል ከ3 ሜትር በላይ ከፍታ ላይ የሚሰሩ ሆኖ ሲገኝ የመጠንጠልጠያ
ገመዶች፣ የደህንነት መጠበቂያ ቀበቶዎች ወይም የአደጋ መከላከያ መረቦች መቅረብ
ይኖርበታል፣
37.1.2. ሠራተኞች ሊወድቁ ወይም ሊንሸራተቱ የሚችሉበት በወለል ላይ የሚገኝ ክፍት ቦታ
በከለላ ድጋፍ እና በእግር መደገፊያ ጣውላ መሸፈን ወይም መከደን ይኖርበታል፣
37.1.3. በማንኛውም በከፍታ ቦታ ላይ የመገንባት ወይም የማፍረስ ሥራ የሚሰራ ሠራተኛ
ከአደጋ መከላከል የሚያስችሉ የጭንቅላት፣ የእጅ እና የእግር መጠበቂያ ማቴሪያሎችን
መጠቀም ይኖርበታል፣
37.2. የጣሪያ ላይ ሥራዎች
37.2.1. ማንኛውም የጣሪያ ሥራ በቅድሚያ የታቀደና ተገቢው ቁጥጥር ሊደረግለት ይገባል፣
37.2.2. በጣሪያ ሥራ ላይ የሚሰማራ ማንኛውም ሠራተኛ የፊዚካላዊ እና ሳይኮሎጂካዊ ብቃት
ያለው፣ በጣሪያ ሥራ ላይ በቂ እውቀት እና የሥራ ልምድ ያለው መሆን ይገባዋል፣
22
37.2.3. የጣሪያ ሥራ የሠራተኞችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል የአየር ሁኔታ በሚኖርበት
ጊዜ መቋረጥ ይኖርበታል፣
37.2.4. ለጣሪያ ሥራ የሚውሉ የመንፏቀቂያ እንጨቶች፣ መረማመጃዎች እና የጣሪያ
መሰላሎች ከቋሚ ግንብ ጋር በአስተማማኝ ሁኔታ መታሰር ይኖርባቸዋል፣
37.2.5. የጣሪያ ተሸካሚዎች ወይም ድጋፎች ከጣሪያው ቁልቁለማነት/ዝቅዝቃት ጋር
እንዲገጥሙ እና በእስተማማኝ ሁኔታ የተደገፉ መሆን ይገባቸዋል፣
37.2.6. በጣሪያው ጠርዝ ዙሪያ መንበርከክ ወይም ቁጢጥ ማለት ሲያስፈልግ ሠራተኛው
በደህንነት መጠበቂያ ገመድ መጠቀም ይኖርበታል፣ ይህ ካልሆነ ደግሞ በመካከሉ
ድጋፍ መኖር አለበት፣
37.2.7. በጣሪያ ላይ ለሚገኙ ክፍት ቦታዎች መዝጊያ ክዳኖች በሙሉ ጠንካራ ከሆነ ቁሳቁስ
የተሰሩ ሆነው በትክክል መገጠም ይኖርባቸዋል፣
37.2.8. በቁልቁለታማ ጣሪያዎች ላይ ለሚከናወኑ ሥራዎች አስተማማኝ እና ተስማሚ
የመንፏቀቂያ ጣውላዎች ወይም የጣሪያ መሰላሎች ተዘጋጅተው በተገቢው ቦታ
እንዲቀመጡ መደረግ ይኖርበታል፣
37.2.9. ረዥም ጊዜ ለሚወስዱ የጣሪያ ሥራዎች ሠራተኛውን ከአደጋ መከላከል የሚያስችሉ
ጠንካራ የሆኑ ማገጃዎች ወይም ከለላ ድጋፎች እና እግር እንዳይንሸራተት የሚከላከሉ
ጣውላዎች መዘጋጀት ይኖርባቸዋል፣
37.2.10. አደጋ ሊያስከትሉ በሚችሉ ጣሪያዎች ወይም ተሰባሪ ጣሪያዎች ባሏቸው ሕንፃዎች
ላይ ወደ ጣሪያው መውጫ አካባቢ የማስጠንቀቂያ ጽሁፍ በግልጽ በሚታይ መልኩ
እንዲኖር መደረግ ይኖርበታል፣
38. የመሬት ውስጥ ሥራዎች
38.1. ጠቅላላ
38.1.1. ማንኛውም የቁፋሮ እና የመሬት ውስጥ ሥራዎች በሚከናወኑበት ወቅት በሠራተኞች
ላይ የመውደቅ፣ የአፈር መናድ፣ የውሃ ሙላት እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ
አደጋዎች እንዳይደርሱ ተገቢው ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፣
38.1.2. ከመሬት በታች ለሚከናወኑ የቁፋሮ ሥራዎች ብርሃን እና አየር ለማስገባት የሚስችሉ
ክፍተቶች መኖራቸውን እና የአደጋ ጊዜ መውጫ መንገድ መዘጋጀቱ መረጋገጥ
ይኖርበታል፣
23
38.1.3. በመሬት ውስጥ የሚዘረጉ የኤሌክትሪክ መሥመሮች በኢትዮጵያ የሕንፃ ኮድ እና
ስታንዳርድ በተቀመጡት የአሠራር ሥርዓቶች መሠረት ይሆናል፣
38.1.4. ትላልቅ የቁፋሮ እና የመሬት ውስጥ ሥራዎች ሲከናወኑ የእለት ከእለት ቁጥጥር እና
ክትትል በተቆጣጣሪ መሐንዲሱ መደረግ ይኖርበታል፣
38.2. የቁፋሮ ሥራ
38.2.1. ማንኛውም የቁፋሮ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ከዚህ በታች የተመለከቱት ሁኔታዎች
መረጋገጥ አለባቸው፣
ሀ) የሚፈለገው የቁፋሮ ሥራ በሚገባ የታቀደ እና የአቆፋፈር ዘዴው በግልጽ ተለይቶ
የተቀመጠ መሆን ይኖርበታል፣
ለ) የመሬቱ የተፈጥሮ ሁኔታ በተገቢው ባለሙያ ተመርምሮ መታወቅ ይኖርበታል፣
ሐ) የሚካሄደው የቁፋሮ ሥራ በአካባቢው ላይ የሚገኙትን ሕንፃዎች፣ መንገዶችእና
ሌሎች የመሠረተ ልማት አውታሮችን የማይጎዳ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፣
መ) በቁፋሮ ወቅት አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ የውሃ መስመሮች፣ ከመሬት በታች
የቆሻሻ መውረጃ መስመሮች ወይም ቱቦዎች፣ እና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያዎች
በሚመለከተው አካል ቁጥጥር እና ክትትል የሚደረግባቸው መሆኑን ማረጋገጥ
ይገባል፣
ሠ) ቁፋሮ የሚካሄድበት ቦታ በጎጂ ኬሚካሎች ወይም ጉዳት ሊያመጡ በሚችሉ
አደገኛ ቁሶች ያለመበከሉ በሚመለከተው አካል መረጋገጥ ይኖርበታል፣
ረ) የተቆፈሩ ጉድጓዶች ጎን በሠራተኞች ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ ከከባድ ዝናብ፣
ከመሬት መንሸራተት እና ከፈንጂዎች መፈንዳት በኋላ በተገቢው ባለሙያ
ቁጥጥር እና ክትትል ሊደረግላቸው ይገባል፣
ሰ) የተቆፈረውን ጉድጓድ እንዲናድ ወይም እንዲንሸራተት የሚያደርጉ ከባድ
መሣሪያዎች እና ማሽነሪዎች እንዲሁም የማምረቻ ተቋማት በአካባቢው መቀመጥ
ወይም መተከል አይኖርባቸውም፣
ሸ) እግረኞች እና ተሸከርካሪዎች የተቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ እንዳይገቡ የመከለያ
አጥሮች እና የማስጠንቀቂያ ማስታወቂያዎች ተዘጋጅተው መተከል ይኖርባቸዋል፣
38.3.2. ማንኛውም በቁፋሮ ሥራ ላይ የተሰማራ ሠራተኛ ከቁፋሮው የወጣውን ማቴሪል
ከተቆፈሩ ጉድጓዶች ጠርዝ ጀምሮ በ1.2 ሜትር ርቀት ውስጥ ማከማቸት
አይኖርበትም፣
24
38.3.3. ከተቆፈሩ ጉድጓዶች ውስጥ የወጡትን ማቴሪሎች ለማስወገድ ጥቅም ላይ የሚውሉ
የማዘለያ እቃዎች ወይም ባልዲዎች የመደገፊያ አካላቸውእንዳይነቀሉ ተገቢው ጥንቃቄ
መደረግ ይኖርበታል፣
42. ስለ የመጀመሪያ እርዳታ አሠጣጥ
42.1. በማንኛውም የሥራ ቦታ ላይ የመጀመሪያ የእርዳታ አገልግሎት መስጫ ቁሳቁስ ክፍል
በአሰሪው መደራጀት ይኖርበታል፣
42.2. በሥራ ቦታ ውስጥ የመጀመሪያ የህክምና መስጫ ቦታን የሚያመለክቱ ምልክቶች በግልፅ
በሚታዩ ቦታዎች መለጠፍ ወይም መተከል ይኖርበታል፣
42.3. በሥራ ቦታ ላይ ጉዳት የደረሰበት ማኝኛውም ሠራተኛ በሥራ ላይ የደረሰበትን አደጋ
ወይም ጉዳት በተመለከተ አግባብ ባለው መ/ቤት ተዘጋጅቶ በተፈቀደ ፎርም መመዝገብ
ይኖርበታል፣ አሠሪውም በሠራተኛው ላይ የደረሰው ጉዳት መመዝገቡን የማረጋገጥ
እና የምዝገባ ዝርዝሩን ወደ ሚመለከተው አካል የማስተላለፍ ግዴታ አለበት፣
42.4. ማንኛውም አሠሪ በሥራ ቦታ ላይ በከባድ ሕመም ወይም አደጋ የተጎዳን ሠራተኛ ወደ
ሕክምና ተቋም የመውሰድ ሃላፊነት አለበት፣
42.5. በግንባታ ቦታዎች ለድንገተኛ አደጋ አገልግሎት የሚሠጡ የሕክምናና የአምቡላንስ
አገልግሎት ተቋማት አድራሻው መመልከት አለባቸው፣
44. ስለ ሠራተኞች እና የሥራ ቦታዎች ደህንነት አጠባበቅ
44.1. የሠራተኞች ደህንነት
44.1.1. የታወቀ አካላዊ ወይም አእምሯዊ ችግር ያለበት ሰው በግንባታ ሥራ ላይ እንዲመደብ
መደረግ የለበትም፣
44.1.2. ማንኛውም የግንባታ አሰሪ ወይም ተቆጣጣሪ ወይም ሠራተኛ በሰዎች ጤንነት እና
ደህንነት ላይ አደጋ በሚያስከትል ሁኔታ አስካሪ መጠጦች ጠጥቶ ከተገኘ ወደ ሥራ
ቦታ መግባት ወይም ሥራው ወደ ሚገኝበት ቦት ላይ መቆየት አይፈቀድም፣
44.1.3. ማንኛውም በሥራ ቦታ ላይ የሚገኝ ሠራተኛ በሠራተኞች ላይ አደጋ ሊያስከትል
በሚችል መልኩ እንደ ግብግብ፣ አላስፈላጊ ሩጫ እና ዝላይ እንዲሁም ቀልዶችን
በሰዎች ላይ መሞከር ወይም በሌላ ተመሳሳይ ረብሻ ላይ መሳተፍ የለበትም፣
44.1.4. ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ቦታው ላይ ደህንነቱን እና ጤንነቱን ለመጠበቅ
የተሰጡትን መሣሪያዎች በአግባቡ መያዝ እና መጠቀም ይኖርበታል፣
25
44.1.5. አሠሪው የሠራተኞቹ ደህንነት እና ጤንነት ሊያስጠብቁ የሚችሉ የመከላከያ
መሣሪያዎች እና ሌሎች አልባሳት እንዲያገኙ ማድረግ እና በስራ ላይ መዋላቸውን
ማረጋገጥ ይገባዋል፣
44.2. የሥራ ቦታዎች ደህንነት
44.2.1. ማንኛውም አሠሪ የሥራ ቦታዎች በሠራተኞች ደህንነት እና ጤንነት እንዲሁም
በሕብረተሰቡ እና በአካባቢው ላይ ጉዳት እንዳያስከትሉ ማድረግ ይኖርበታል፣
44.2.2. አሠሪው በሁሉም የሥራ ቦታዎች የደህንነት መጠበቂያ ሥነ-ስርኣቶች በሥራ ላይ
መዋላቸውን በየጊዜው ማረጋገጥ ይኖርበታል፣
44.2.3. ማንኛውም የሥራ ቦታ ከቆሻሻ የፀዳ እና በጽዳት የሚጠበቅ መሆን ይኖርበታል፣
44.2.4. ማንኛውም የሥራ ቦታ ለወንዶች እና ሴት ሠራተኞች መገልገያ የሚሆኑ እና በተለያየ
ቦታ የተገነቡ ጊዜያዊ የመታጠቢያ እና የንፅህና መጠበቂያ አገልግሎት መስጠት
የሚችሉ ክፍሎች ሊኖሩት ይገባል፣
44.2.5. ማንኛውም የሥራ ቦታ ከመንግስት ዋና ምንጭ ወይም በሚመለከተው አካል ፍቃድ
ካገኘ ሌላ የተለየ ምንጭ የተገኘ በቂ እና ለጤና ተስማሚ የሆነ የመጠጥ ውሃ
ሊኖረው ይገባል፣
44.2.6. በሥራ ቦታዎች የሚገኙ ለእሣት አደጋ እና ለበሽታ የሚያጋልጡ ደረቅ ቆሻሻዎች
በወቅቱ መወገድ አለባቸው፣
44.2.7. በግንባታው አካባቢ ብክለት እንዳይከሰት ጊዜያዊ የፍሳሽ ማከማቻ እና ማስወገጃ
መዘጋጀት አለበት፣
44.2.8. ህዝብ በሚተላለፍበት መንገድ የሚከማች የግንባታ ቁሳቁስ ከከተማው አስተዳደር
ፈቃድ ካልተሠጠ በስተቀር ማከማቸት አይፈቀድም፣
44.2.9. ከሀምሣ እና ከዚያ በላይ ቁጥር ያላቸው ሠራተኞች በሚሠሩባቸው ማናቸውም የሥራ
ቦታዎች የደህንነት እና የጤንነት ሁኔታዎችን የሚከታተል የደህንነት መኮንን ሊኖር
ይገባል፣ የደህንነት መኮንኑ፣
ሀ) የሥራ ቦታ የደህንነት እና ጤንነት አጠባበቅ የሙያ ሥልጠና የተሰጠው ሊሆን ይገባል፣
ለ) ከሥራ ተቆጣጣሪዎች ጋር በመመካከር በአሠሪው የተቀመጡትን የደህንነት እና ጤንነት
ተግባራትን ያከናውናል፣ በሠራተኞች መተግበሩንም ይቆጣጠራል፣
45. የሚደርሱ አደጋዎችን ስለ መመዝገብ እና ማሳወቅ
26
45.1. ማንኛውም ሠራተኛ በሥራ ቦታ ላይ የደረሰበትን አደጋ ወይም የደረሰበትን አደገኛ
ሁኔታ ለአሰሪው ወይም ለተቆጣጣሪው ወዲያውኑ ማሳወቅ ይኖርበታል፣
45.2. በሥራ ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎች እና በሥራ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎች
እንዲሁም አደገኛ ክስተቶች ተመዝግበው ለዚሁ ሥራ በተመደበ ሰው በአግባቡ መያዝ
ይኖርባቸዋል፣
45.3. በሥራ ቦታ ላይ ተመዝግበው የተያዙ መረጃዎች ተጠብቀው የሚቆዩበት ጊዜ ቢያንስ
ከ10 ዓመት ቢበዛ ደግሞ ከ20 ዓመት መብለጥ የለበትም፣
45.4. ማንኛውም በሥራ ቦታ ላይ የሚደርስ አደጋ በ3 ቀናት ውስጥ ለሚመለከተው አካል
ሪፖርት መደረግ አለበት፣ ሪፖርቱ የሚከተሉትን የሚካትት ይሆናል፣
45.5.5 አደጋው የሞት አደጋን የሚስከትል ሆኖ ሲገኝ በስልክ ወይም በማናቸውም ሌሎች
የመገናኛ ዘዴዎች አደጋው ለሚመለከተው አካል ሪፖርት መደረግ ይኖርበታል፣
27
ለ) አደጋ በሚደርስበት ጊዜ መወሰድ ስላለባቸው መመሪያዎች፣ እና ለስራው ተጠሪ የሆነውን
ሰው ስምና ዝርዝር አድራሻ
ለ/የማስጠንቀቅያ ምልክቶች
28
መውጣት (exit) ምልክቶች- እነዚ ምልክቶችን ስንጠቀም በነጭ መስክ ላይ በቀይ
ቀለም የተፃፈ፤ ፊደሉ ርዝመት ከ 6 ኢንች (15 ሴ.ሜ) ያላነሰ ስፋቱ ቢያንስ ቢያንስ
ሦስት አራተኛ ኢንች (2 ሴንቲሜትር) መሆን አለበት፡፡
29
ፍላግሜን፡ ከሀይዌይ ወይም ከመንገድ ጎን ለጎን ምልክቶችን ማስቀመጥ ከአደጋ
ለመከላከል በቂ ሳይሆን ሲቀር፣ ፍላግሜን ወይም ሌላ ጠቋሚዎች ተገቢ የትራፊክ
መቆጣጠሪያዎች መቅረብ አለባቸው ፍላግሜን ጠቋሚዎች በሚውሉበት ጊዜ ቀይ
ወይም ብርቱኳናማ የማስጠንቀቂያ ልብስ ማልበስ አለብን፡፡ በምሽት ላይ
የምንጠቀማቸው ፈላግሜኖች የሚየንፀባርቁ መሆን አለባቸው፡፡
ሐ/ የአደጋዎች አያያዝ
1. የመጀመሪያ እርዳታ
30
አሰሪዎች ለሰራተኞቻቸው የመጀመሪያ መሳሪያዎችን፣ የመሣሪያው ቦታንና ተቋማት
እና ሠራተኞች ጨምሮ ማሳወቅ አለባቸው፡፡
ሁሉም ጉዳት በሂደቱ መሰረት ሪፖርት መደረግ፣ መያዝ እና መመዝገብ አለበት፡፡
በማንኛውም የግንባታ ቦታ ላይ ቢያንስ አንድ የእርዳታ ሳጥን ሊኖር ይገባል፡፡
2. የሕክምና እንክብካቤ
አሰሪ የድንገተኛ ድርጊት መርሃ ግብር ሊኖረው ይገባል፡፡ የድንገተኛ አደጋ ድርጊት
መርሃ ግብር በጽሁፍ ስራ ቦታ ላይ መቀመጥ እና ሠራተኞች መገምገ አለባቸው::
ይሁን እንጂ 10 ወይም ከዚያ በታች ሠራተኞች ያለው አሠሪ እቅዱን ለሠራተኞች
በቃል ማነጋገር ይችላል፡፡
4. ሥልጠና
31
በኮንስትራክሽን ሥራ ላይ አሰሪው ተገቢውን መመሪያ እና ስልጠና መስጠት
ይኖርበታል ይህም የሠራተኞቹን ጤና እና ደህንነት ለማረጋገጥ አስፈላጊ ነው፡፡
እንዲህ ዓይነቱ ሥልጠና አካላዊ ሎጂስቲክስ ያካትታል፡፡
ቀጣሪው አካል ለአዲስ ሠራተኞች የድርጅቱ አደረጃጀት እና አስተዳደርን፣
የሰራተኞችና የደህንነት እቅድ፣ ጤና እና ደህንነት እና የሰራተኞች መገልገያዎች
ዝርዝር ያካትታል አጫጭር ኮርሶችን መሰጣት አለበት፡፡
32
መሣሪያዎች] ላይ ከተጠቀሱት ነገሮች በስተቀር) ወይም ማንኛውም ሰራተኛ (ንዐስ
አንቀጽ 18.4 [ለተቋራጩ ሠራተኞች ኢንሹራንስ] ላይ ከተጠቀሱት ሰራተኞች በስተቀር)
ተጠያቂ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
በብራዚል ኢኮኖሚ ውስጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ትልቅ የሆነ ድርሻ አለው፡፡ በሁሉም
ደረጃ ለሚገኙት የህብረተሰብ ክፍሎች የሀብት እና የስራ ዕድል ምንጭ ነው፡፡ የመንግስት
የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች እና የሪል እስቴቶች ቁጥር መጨመር ኢንዱስትሪው እንዲስፋፋና
ትርፋማ እንዲሆን አድርገውታል፡፡ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው 2.6 ሚሊዮን መደበኛ የስራ
መደብን በመያዝ ከሀገሪቱ ጠቅላላ የስራ ድርሻ 7.1% ይሸፍናል፡፡
33
ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ምንም እንኳን የሞት አደጋው እየቀነሰ ቢመጣም በአለም ላይ
ተሻለ ልምድ ካላቸው ሀገራት እንደ አሜሪካ፣ እንግሊዝ እና ፊንላንድ ጋር ሲነፃፀር ለአደጋ
የመጋለጡ አዝማሚያ ከፍተኛ ነው፡፡ የግንባታ ስራው በጤና ላይ የሚያደርሰውን አደጋ በመረጃ
እጥረት ምክንያት ለመገመት አዳጋች ቢሆንም በስራ ቦታ ላይ በሚደርሱ አደጋዎች ምክንያት
ጊዜያዊ የህመም ፍቃድ ከ15 ቀን በላይ የሚወስዱ ሰራተኞችን ከግምት ውስጥ በማስገባት
በአመት ወደ 1 ሚሊዮን የሚደርስ የስራ ሰአታትን የብራዚል የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ
ያጣል፡፡
34
አራተኛ ደረጃ፡- የቡድኑን አጠቃላይ ተግባራት መቆጣጠርና መገምገም፡፡ የመቆጣጠርና
የመገምገም ሂደት የሚከናውነው ቢያንስ በሁለት ወር ውስጥ ሶስት ጊዜ በግንባታ
ቦታው ላይ የመስክ ምልከታ በማካሄድ ነው፡፡ በግምገማ ወቅት የቡድኑ አባላት በግንባታ
ቦታ ላይ የተፈጠሩትን አደጋ፣ ሊፈጥሩ የሚችሉ ሁኔታዎችን እና የተወሰዱ
መፍትሄዎችን በፎቶግራፍ በተደገፈ መረጃ ያቀርባሉ፡፡
35
የተለዩ ርእሶች መሰረት በማድረግ ጥልቀት ያለው ስልጠና በመስጠት፡
ጥሩ ተሞክሮ በማምጣትና በማስፋፋት፡
በየ3ወሩ በሚታተመው የተቋሙ የውስጥ ጋዜጣ ስለግንባታ የስራ ላይ ደህንነት
ትኩረት ተሰጥቶት በስፋት በመተንተን እንዲነበብ በማድረግ፡
የግንባታ የስራ ደህንነት በተመለከተ በዉስጥ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተለያዩ ፅሁፎች
በመለጠፍና እንዲነበቡ በማድረግ የግንዛቤ ለዉጥ እንዲኖር አድርጓል፡፡
36
ሠንጠረዥ 2-1፡ የሳይት ምልከታ ድግግሞሽ
የሳይት ምርመራ/ምልከታ የሚካሄድነት ድግግሞሽ
አይነት ድግግሞሽ ምልከታውን የሚያካሂደው አካል
የደህንነት ጉብኝት በየ 6 ወር ፕሮጀክት ዳይሬክተር
የደህንነት ክትትል በየ 3 ወር ፕሮጀክት ማናጀር
አጠቃላይ የታቀደ የደህንነት በየወሩ/ በየሳምንቱ ሲኒየር ፕሮጀክት መሀንዲሰ
ምርመራ
37
በጥናቱ ከተሸፈኑ 216 የኮንስትራክሽን ድርጅቶች የተጠናቀረው የስራ ላይ አደጋ መረጃ
የመለከተው ሌላ እውነታ በሥራ ቦታዎች የተከሰቱ የስራ ላይ አደጋዎች እና የጤና ጉዳቶች
እንዳይደርሱ በቅደሚያ መደረግ የነበረባቸው የመከላከል ስራዎች አጠቃላይ ወጪ ከግባታው
ጠቅላላ ወጪ 0.54%-3.1% ድርሻ ነበራቸው፤ ይህ የመከላከል ወጪ ከአደጋ ወጪ ጋር
ሲነጻጸር ከ81.5%-83.2% ዝቅተኛ ከመሆኑም በተጨማሪም በቀጣይ ለሚከናወን የአደጋ
መከላከል እርምጃ ኢንቨስትመንት ከመሆኑም በተጨማሪ የመከላል ስራ ወጪ ቆጣቢ፣ ተቋማዊ
የሴፍቲ አቅምን ደረጃ በደረጃ የሚያጠናክርና ውጤታማ አሠራርን የሚዘረጋ መሆኑን
አመልክቷል፡፡ በመሆኑም በብሄራዊ ደረጃ የሚነደፍና ተግባራዊ የሚደረጉ ሙያ ደህንነትና
ጤንነት ፕሮግራሞች ለኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ትኩረት እንዲሰጡ አስገንዝቧል፡፡[14]
2.10.1 የስራ ላይ ደህንነትና ጤንነት በኢትዮጵያ የግንባታ ዘርፍ በአዲስ አበባና በወልቂጤ
በ2014 እ.ኤ.አ የተደረገ ጥናት
በሀገራችን የግንባታ አካባቢ ደህንነት ላይ የተደረጉ ብዙ ጥናቶች ባይኖሩም ከተደረጉት
የተወሰኑ ጥናቶች ውስጥ በሰይፈዲን ሰርሞሎ በኢትዮጵያ የግንባታ ቦታ ደህንነት እና ጤና
በሚል ርዕስ የተደረገው ጥናት እንደሚያሳየው፡-[10]
38
ይሰጣሉ:: በተጨማሪም ዋና ዋናዎቹ የኩባንያው ክፍሎች አስፈላጊ የሆኑ የመጀመሪያ
ደረጃ ዕርዳታዎችን እና የጤና ባለሙያዎችን ይይዛሉ፡፡
2.10.2 በደህንነትና ጤንነት ላይ ያለው አፈጻጸም ማሳያ በአዲስ አበባ በመንገድና ቤት ግንባታ
እ.ኤ.አ በ2014 የተደረገ ጥናት
በ2014 እኤአ በዘሩ ታሪኩ በተደረገው ጥናት እንደሚያመለክተው [9]
በአዲስ አበባ የመንገድና ህንጻ ግንባታ ላይ በጣም አነስተኛ የሆነ የደህንነት ሁኔታ
እንዳለ ሲያመላክት ለዚህም እንደማስረጃነት ያስቀመጠው በመስክ ምልከታ ወቅት ለስራ
የተሰማሩ ሰራተኞች ምንም አይነት የደህንነት መጠበቅያ ቁሳቁሶችና አልባሳትን
አለመጠቀማቸዉን ገልጻል፡፡
የግንባታ ዘርፉ እያደረሰ ያለው አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሆነና ይህም
ከሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ መሆኑ ያሳያል፡፡ በተጨማሪም
በግንባታ ቦታ ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን መዝግቦ የመያዝ ስርአቱ በቂና በተደራጀ
መልኩ አለመሆኑ ተገልጸል፡፡ በተጨማሪም በጣም ከፍተኛ የሆነና ወደ ሆሰፒታል
ለህክምና የሚሄዱት ላይ የደረሱ አደጋዎችን እንጂ ሌሎች ቀለል ያሉት
39
እንደማይመዘገቡም ያሳያል፡፡ እንዲሁም በከተማው ጤና ቢሮም ሆነ በሆስፒታል
ከግንባታ ስራ ጋር ተያያዥነት በሆነ ምክንያት አደጋ ደርሶባቸው ለህክምና
የሚመጡትን የመመዝገቢያ ስርአት አለመኖሩን ጠቁሟል፡፡
40
ክፍል ሶስት
ድርጅቱ ስለግንባታ ደህንነት (Safety and healthy) የተፃፈ ህግ አለው ወይ ለሚለው ጥያቄ
በአማካሪ፣ በስራ ተቋራጭ እንዲሁም በግንባታ ባለቤት የተሰጠው ምላሽ እንደሚያመለክተው
የህግ አፈጻጸማቸው ከ50% በታች መሆኑን ነው፡፡ እንዲሁም ምንም ምላሽ ያልሰጡም
ይገኛሉ፡፡ይህም እንደሚያለክተው ምንም ግንዛቤ የሌላቸው በግንባታ ዉስጥ እየሰሩ ያሉ ቁልፍ
ተዋናዮች መኖራቸው ነው፡፡ በተለይም ለግንባታው ዋና የስራ ባለቤት የሆነው ስለግንባታ
ደህንነት ያለው የህግ እውቀት በጣም ዝቅተኛ መሆኑ ያሳያል፡፡ ይህም አንድን ስራ ለጨረታ
በሚያወጡበት ጊዜ የግንባታ ደህንነትን በተመለከተ ትኩረት ከመስጠት ይልቅ በዝቅተኛ ዋጋ
የሚሰራለትን የመምረጥ አዝማምያ እንዲኖራቸው ያደርጋል፡፡
41
ሴፍቲን በተመለከተ ያለው የውል ስምምነት ሁኔታ
ሠንጠረዝ 3-1፡ ደህንነት በውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ
አማካሪ ተቋራጭ ባለቤት
ሴፍቲ የውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ መካተት አለበት ወይ ለሚለው አማካሪ፣ የስራ ተቋራጭ
እንዲሁም የግንባታ ባለቤት በአማካኝ 94% አዎ የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ይህም
እንደሚያሳየው በዉል ስምምነቱ ዉስጥ መካተቱን ሁሉም በከፍተኛ ደረጃ መስማማታቸውን
ያመለክታል፡፡ይሁን እንጂ በቃለመጠይቅና በትኩረት ቡድን ዉይይት እንደተገለጸው በአማካሪ
በኩል ሴፍቲን በተመለከተ በዝርዝር የተቀመጠ የስራ ዉል ስምምነት አለመኖሩ በበጎ
ፈቃደኝነት ከሚያሟሉት ዉጭ ህጉን ለማስፈጸም አስቸጋሪ መሆኑን ሲገልፁ በተቋራጮች
በኩል የስራ ውል የሚገቡበት ዝቅተኛ ዋጋ በመሆኑ፣ በዉል ስምምነት አለመካተቱ እንዲሁም
ወጭን በመፍራት የሴፍቲ አልባሳትን ያለማሟላት በጣም ጎልቶ የሚታይ ችግር ነው፡፡ ለዚህም
እንደምክንያት የሚያስቀምጡት እንኳንስ ለቅድመ ጥንቃቄ ደህንነት ለማውጣት ያላቸው
ትርፍ አናሳ እንዲሁም ኪሳራ ውስጥ ስለሆነ ይህንን ጉዳይ ማንም ቦታ አይሰጠውም፡፡
በአሰሪው አካል በኩል ዝቅተኛ ዋጋን የመምረጥ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ለደህንነት
መጠበቂያ አሰፈላጊ የሆኑ ነገሮችን በማካተት ዋጋ የሚያቀርቡ የስራ ተቋራጮችን
አያበረታታም፡፡ ይህም በተደጋጋሚ በሁሉም ባለድርሻ አካላት በዉል ስምምነት ዉስጥ መካተት
አለበት የሚል የመደምደምያ ሃሳብ መኖሩን ተገንዝበናል፡፡
42
ምስል 3-2፡ የደህንነት ወጪ በውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ ስለመካተቱ
43
ሠንጠረዥ 3-2፡ ስለ ግንባታ ደህንነት ያለው ግንዛቤ
አማካሪ ተቋራጭ ባለቤት ሠራተኛ
ምላሽ ያልሰጡ 0 0 0 0 0 0 2 .5
ስለ ግንባታ አካባቢ ደህንነት (work zone Safety) ከዚህ በፊት ያውቃሉ ወይ ለሚለው
በአማካሪ፣ በስራ ተቋራጭ፣ በግንባታ ባለቤት እንዲሁም በጉልበት ሰራተኛ በአማካይ 91%
እንደሚያዉቁ ገልጸዋል፡፡ በአማካሪ በኩል ሙሉ ለሙሉ ግንዛቤው ሲያመለክት በጉልበት
ሰራተኛ በኩል ያለዉ ከሌሎቹ ዝቅ ያለ መሆኑ ይስተዋላል፡፡ ባደረግነው ዉይይትም ያስተዋነው
በሁሉም አካላት የግንዛቤ ማነስ አለመኖሩን ሲሆን ትኩረት ሰጥቶ ተግባራዊ ማድረግ ላይ
ከፍተኛ ችግር መኖሩን ነው፡፡
በሀገራችን ከ Safety ጋር ተያያዥነት ያለው ህግ/አዋጅ/ደንብ/ በተመለከተ
የህግ/አዋጅ/ደንብ/ ተፈፃሚነት
45
የደህንነት አስተዳደር
ድርጅቱ ለሰራተኞቹ የጥንቃቄ ዕቃዎችን አሟልቷል ለሚለው አማካሪ 29% አሟልቷል 65%
አላሟላም ሲሉ ተቋራጭ ደግሞ 48% አሟልቷል 49% አለማሟላታቸውን ገልጸዋል፡፡
እንዲሁም በሁለቱም በኩል ምላሽ ያልሰጡት ዝቅተኛዉን ፐርሰንት ይይዛሉ፡፡ነገር ግን
በተቋራጭ የተገለጸው ዉጤት እንደሚያሳየው ግማሽ በግማሽ የተሟላና ያልተሟላ ሲሆን
በተጨባጭ ያለዉ ግን የደህንነት እቃዎች አለማሟላታቸዉንና በአማካሪዎቹም በኩል
አልተሟላም የሚለው ከፍተኛ ሲሆን ተቋራጭ በበጎ ፈቃደኝነት ካላሟላ በስተቀር ማስገደድ
እንደማይችሉና አሁን ያለዉ ነባራዊ ሁኔታ ዝቅተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በመስክ
በተዘዋወርንባቸው የግንባታ ቦታዎች አብዛኛዎቹ የድህንት አላባሳትም ሆነ የጥንቃቄ
ምልክቶቹን ምንም የማይጠቀሙ ሲሆን በቁጥር እጅግ አናሳ የሆኑ በተሻለ መልኩ ከደህንነት
ባለሙያ እስከ አስፈላጊዉን ቁሳቁስ ያሟሉና ለሌሎችም ምሳሌ መሆን የሚችሉ ተቋማት
መኖራቸዉን ተረድተናል፡፡
46
የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና (First aid)
ሠንጠረዥ 3-4፡ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና ስለመኖሩ
ተቋራጭ ሠራተኛ
47
የተሟሉ የደህንነት ዕቃዎች
19.00% ሄልሜት
20.00% 17.50%
16.20%
14.90% የደህንነት ጫማ
15.00% 11.70%
10.50% 9.90% መነፀር
10.00%
የአቧራ መከላከያ
5.00% 3.50%
1.10% ሁሉንም
0.00%
አማካሪ ተቋራጭ ሰራተኛ
በናንተ በኩል የተሟሉ የደህንነት ዕቃዎች የትኞቹ ናቸው ለሚለው በአማካሪ፣ ተቋራጭ
እንዲሁም የግንባታ ስራተኛ የተሰጠው ምላሽ የደህንነት ዕቃዎችን በሚገባ አለመሟላታቸዉን
ያመለክታል፡፡ በተጨማሪም በሁሉም ወገን በኩል ሄልሜት በተወሰነ መልኩ የተሟላ ሲሆን
አንጻባራቂ ልብስ ደግሞ ሁለተኛዉን ደረጃ ይይዛል፡፡ በእየአንዳንዱ የግንባታ ባለድርሻ አካላት
አልፎ አልፎ በስብጥር አንዳንድ እቃዎችን ከማሟላት የዘለለ ለደህንት አስፈላጊ የሆኑት
አልባሳት በተሟላ መልኩ የሌለ መሆኑን በግልጽ ይታያል፡፡እኛም በመስክ ምልከታችን
ያረጋገጥነው ይህንኑ ነው፡፡
ማንኛውም ጎብኝ ወደ ግንባታ ቦታ (construction site) በሚመጣበት ጌዜ ስላለው ቅድመ
ጥንቃቄ
አለ 11 35.5 82 37.8
48
ከላይ በሰንጠረዝ እንደተገለፀው ማንኛውም ጎብኝ ወደ ግንባታ ቦታ (construction site)
በሚመጣበት ጌዜ ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ተቋሙ ያለው የአሰራር ሁኔታ አለ ወይ
ለሚለው አማካሪና የስራ ተቋራጭ በአማካይ 62% ጥንቃቄ እንደማያደርጉ ገልፀዋል፡፡ይህም
ጥንቃቄ ያለማድረጉ ሁኔታ ከፍተኛ መሆኑን ያለው የመቶኛ ውጤት ያሳያል፡፡በመሆኑም
ለሰራተኛው ሆነ ከሰራተኛው ውጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚደረገው ጥንቃቄ አናሳ
ነው፡፡ እኛም ባደረግው የመስክ ምልከታ እንዳሰተዋልነው እንኳን ከስራው ዉጭ ለሆኑት
የህብረተሰብ ክፍሎች ይቅርና በግንባታ ስራ ላይ ለተሰማሩትም ቢሆን አሰፈላጊውን የደህንነት
አልባሳት እንዲሁም የቅድመጥንቃቄ ምልክቶች አለመሟላታቸውን ነው፡፡
የደህንነት ባለሙያ
49
ባይኖርም በሌላ የምህንድሰና ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎች እንደ ደህንነት ባለሙያ ሆነው
እንዲሰሩ የተደረገበት ሁኔታ በቁጥር እጅግ አናሳ የግንባታ ተቋማት መኖሩን አስተዉለናል፡፡
አለ 5 16.1 46 21.2
በsafetyጉድለትአደጋሲያጋጥመውስላለውተጠያቂነት
60 አሰሪው መስሪያቤት
ተቋራጭ
40
ሌላ አካል
ምላሽ ያልሰጡ
16.1 17.1
20 12.5 9.8
6 4.2
0.51.4 0 0 1.30.5
0
ተቋራጭ ባለቤት ሰራተኛው
50
አንድ ሰራተኛ በsafety ጉድለት አደጋ ሲያጋጥመው ተጠያቂው አካል ማን ነው ለሚለው
በተቋራጭ፣ በአሰሪው መ/ቤት እንዲሁም በጉልበት ሰራተኛው በአማካይ 77% ያክሉ የስራ
ተቋራጭ መሆኑን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ይህም እንደሚያመለክተው ማንኛዉም በስራ ምክንያት
በስውም ሆነ በንብረት ላይ ለሚደርስ አደጋ ከፍተኛውን የተጠያቂነት ድርሻ የሚወስደው የስራ
ተቋራጩ መሆኑ ያሳያል፡፡
ከላይ በሰንጠረዥ እንደሚታየው ስለስራ ቦታ ደህንነት ከአሰሪ መስሪያ ቤትዎ ተገቢው ስልጠና
(training) በቋሚነት ይሰጣል ወይ ለሚለው በሰራተኛ፣ በተቋራጭ፣ በአማካሪ በአማካይ 79%
አይሰጥም በማለት መልሰዋል፡፡ እኛም ባደረግነው የመስክ ምልከታና ውይይት እንደተረዳነው
አብዛኛው የጉልበት ሰራተኛው ከማንበብና መጻፍ የዘለለ የእዉቀት ደረጃ የሌለዉ መሆኑ፣
እንዲሁም የመግባብያ ቋንቋ እንኳ በቅጡ ለመናገር የማይችሉ ከተለያየ የአገሪቱ አካባቢ
የመጡ የጉልበት ሰራተኞች ባለበት ሁኔታ በተጨማሪም ስለግንባታ ደህንነት ምንም ስልጠና
አለመሰጠቱ በኢንዱስትሪዉ የሚደርሰው አደጋ ዉስብስብና ከፍተኛ እንደሚያደርገው
አስተውለናል፡፡
51
በግንባታ ቦታ ላይ በደህንነት መጓደል ምክንያት የሚፈጠሩ አደጋዎች
በግንባታ አካባቢ አስፈላጊው የደህንነት ጥንቃቄ ባለመደረጉ ምክንያት አደጋ ሲያጋጥም ያለውን
የሪፖርት አደራረግ በተመለከተ የግንባታ አማካሪ 61%፣ ተቋራጭ 34%፣ ስራተኛ 34%
ሪፖርት አለመደረጉን ገልፀዋል፡፡ በሰራተኛና በተቋራጭ መካከል ያለው አስተያየት ተመሳሳይ
ሲሆን አማካሪው አጠቃላይ በግንታው ላይ ያለዉን ሁኔታ የሚቆጣጠረው አካል የሰጠው ምላሽ
ግን ከነሱ ፍጹም የተለየና የሪፖርት አደራረግ ሰርአቱ ዝቅተኛ መሆኑን ነው፡፡ ይህም
የሚያመለክተው በተቋራጭ በኩል ሪፖርት ይደረጋል ማለቱ ተጠያቂነትን ከመሸሽ አንጻር
ሲሆን እኛም ባደረግነው ውይይት የተገነዘብነው አደጋ ሲያጋጥም በተደራጀ መልኩ ሪፖርት
አለመደረጉን ነው፡፡
52
ሰአት እላፊና ትራፊክ ፍሰት በሚበዛበት የሚከናወኑ ስራዎች ለአደጋ መፈጠር ያላቸው
አስተዋጸኦ
Table 3-1 ሠንጠረዥ 3-7፡ ሰዓት እላፊና ትራፊክ በሚበዛበት የሚከናወኑ ሥራዎች ለአደጋ መፈጠር ያላቸው አስተዋጽኦ
ተቋራጭ ሰራተኛው
የድግግሽ የመቶኛ የድግግሽ መጠን የመቶኛ ሰስሌት
መጠን ሰስሌት
ከፍተኛ 146 67.3 203 51.0
መካከለኛ 52 24.0 117 29.4
ዝቅተኛ 19 8.8 70 17.6
ምላሽ ያልሰጡ 0 0 8 2.0
ጠቅለላ 217 100.0 398 100.0
ሰአት እላፊና ትራፊክ ፍሰት በሚበዛበት ሰአት የሚከናውኑ ስራዎች ለአደጋ መፈጠር ያላቸው
አስተዋፅኦ ምን ያክል ይሆናል ለሚለው ተቋራጭና የግንባታ ሰራተኛ በአማካይ 59% ከፍተኛ
መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከዚህ መረዳት እንደሚቻለው በምሽትና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛበት ወቅት
ለሚከናወኑ ስራዎች ከሌሎች በተለየ ሁኔታ ግልጽና ማንኛዉም በቀላሉ ሊረዳው የሚችል
የቅድመ ጥንቃቄ ምልክቶች መቀመጥ እንዳለባቸው ነው፡፡ ይህ ባልሆነበት ሁኔታ ለሚፈጠረው
አደጋ ያለው አስተዋጾ በቀላሉ የሚታይ አለመሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሰራተኛው ተቋራጭ
የድግግሞሽ የመቶኛ የድግግሞሽ የመቶኛ ሰስሌት
መጠን ሰስሌት መጠን
54
በተደጋጋሚ የሚደርሱ የአደጋ አይነቶች
55
በግንባታ ስራ ደህንነት (work zone Safety) አለመተግበር ከስራው ውጭ የሆኑ
ማህበረሰብ ላይ ስለሚደርሰው ጉዳት
መስል 3-12፡ የግንባታ ደህንነት ባለመተግበሩ ምክንያት ከስራው ውጪ የሆኑ የማህበረሰብ ከፍሎች ላይ የደረሱ አደጋዎች
56
በንብረትም ሆነ በሰው ላይ ለሚደርስ አደጋ የኢንሹራንስ ዋስትና ስለመስጠቱ
57
በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ የሚደርሱ የአደጋ መንስኤዎች
በግንባታ ስፍራ ለደህንነት አስጊ የሆኑ የስራ አይነቶች 54% በግልፅ ተለይተዋል ሲሉ 43%
አለመለየታቸውን ገልጸዋል፡፡ 2% ደግሞ ምንም አይነት ምላሽ አልሰጡም፡፡ ከዚህም መረዳት
እንደሚቻለው 46% አካባቢ የሚሆነው ለአደጋ በሚያጋልጡ ሁኔታዎች የግንታ ስራ
እየተከናወነ መሆኑን ነው፡፡ይህም በስራተኛው በስራ መንፈስ ላይ ከፍተኛ የስጋት ስሜት
ስለሚፈጥር የሚጠበቅበትን ስራ እንዳያከናዉን እንቅፋት ይሆናል፡፡
58
በዋናነት የሚጠቀሱ የአደጋ መንስኤዎች
59
የደህንነት መጓደል በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪው ላይ ያለው ተጽእኖ
60
የአደጋዎች መቀነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው አስተዋፅኦ
Table 3-2 ሠንጠረዥ 3-10፡ የአደጋዎች መቀነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው አስተዋጽኦ
61
አሁን ካለዉ የሃገራችን ኮንስትራክሽን ነባራዊ ሁኔታ Safety professional እንደ አንድ
አይነት በከፍተኛ የትምህርት ተቋም ቢሰጥ ያለው ጠቀሜታ ለሚለው ተቋራጭ፣ የግንባታ
ባለቤት፣ አማካሪ እንዲሁም የግንባታ ሰራተኛ በአማካይ 88 በከፍተኛ ደረጃ ጠቀሜታ እንዳለው
አመላክተዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ለኢንዱስትሪዉ በሴፍቲ ሙያ የተመረቀ ባለሙያ በጣም
አስፈላጊ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን በአብዛኛው የግንባታ ቦታ የሴፍቲ ባለሙያ ተብሎ ይህንን
ጉዳይ የሚከታተል የለም በተመሳሳይ ይህንን በተግባር ሊያከናዉኑ የሞከሩት በቁጥር እጅግ
ኣናሳ የሆኑ ተቋማትም በዘርፉ የተመረቀ ባለሙያ ገበያ ላይ የማግኘት ሁኔታ አስቸጋሪ
ሆኖባቸዋል፡፡ በቁጥር እጅግ ዉስን በሆኑ የግንባታ ቦታዎች እንደ ደህንነት ባለሙያ ሆነዉ
ቢሰሩም የራሳቸውን ስራ ወደጎን በመተው በሌሎች ሙያዎች የመሳብ አዝማምያ ስለሚየሳዩ
ዉጤቱ እንደተፈለገው አይደለም፡፡ በመሆኑም እነዚህንና መሰል ችግሮች ከመቅረፍ አንጻር
የSafety professional እንደ አንድ የሙያ ዘርፍ በከፍተኛ የትምህርት ተቋምት ቢሰጥ
ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡
ስለግንባታ ደህንነት (Safety and healthy) የተፃፈ ህግ አለው ወይ ለሚለው አማካሪ 46%
ተቋራጭ 71% እንዲሁም ባለቤት 30% አለ ሲሉ አማካሪ 55% ተቋራጭ 29% እንዲሁም
ባለቤት 50% የተፃፈ ህግ አለመኖሩን ገልጸዋል፡፡ ይህም የሚያመለክተው በተቋራጭ በኩል
62
የተሻለ የህግ ግንዛቤ መኖሩን እንዲሁም በግንባታ ባለቤት በኩል ግማሽ የሚሆኑት ስለህጉ
መኖር እውቀት የሌላቸው ሲሆኑ 20% የሆኑት ደግሞ ህጉ መኖሩና አለመኖሩ የማያውቁት
ናቸው፡፡ በጥናት ቡድኑ በኩል በቃለመጠይቅና በትኩረት ዉይይት ለማየት እንደሞከረው
አብዛኛው ህግ መኖሩን የማያዉቁ ሲሆን የተወሰኑት ደግሞ ህጉ ቢኖሩም ተግባራዊ
አለመደረጉን ገልፀዋል፡፡
የስራ ደህንነት (Safety) የውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ መካተት አለበት ወይ ለሚለው
አማካሪ፣ ተቋራጭ፣ እንዲሁም የግንባታ ባለቤት በአማካይ 98% በዉል ስምምነት መካተት
አለበት ብለው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ከዚህም መረዳት እንደሚቻለው ሁሉም ስራው
የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች (Safety) በዉል ስምምነት መካተት እንዳበት ቢያምኑም እንኳን
በተግባር ግን እየተሰራበት አለመሆኑን ባደረግነው ዉይይት እንዲሁም በቃለ መጠይቅ
ለመገንዘብ ችለናል፡፡
63
ለግንባታ ስራ ደህንነት (work zone Safety) የሚወጣ ወጪ (በcontract agreement)
የሚካተትበት ሁኔታ በተመለከተ
64
ስለግንባታ አካባቢ ደህንነት (work zone Safety) ያለዉ እውቀት
ስለ ግንባታ አካባቢ ደህንነት (work zone Safety) ከዚህ በፊት ያውቃሉ ወይ ለሚለው
አማካሪ፣ የስራ ተቋራጭ እና የግንባታ ባለቤት 100% እንደሚያዉቁ ሲገልጹ ነገር ግን
የግንባታ ሰራተኛ 63% አዎ በማለት መልሰዋል፡፡ ይህም የስራው ቁልፍ ተዋናኞች ሙሉ
ለሙሉ ስለ ደህንነት (Safety) ከዚህ በፊት ግንዛቤው እንዳላቸው ነገር ግን በዋናነት ስራውን
የሚያከናውነው የጉልበት ሰራተኛው የእውቀት ማነስ እንዳለበት ያመላክታል፡፡ እንደአጠቃላይ
ከጉልበት ሰራተኛ ውጭ የግንዛቤ ማነስ ሳይሆን ትኩረት ያለመስጠት ጉዳይ መሆኑን ባደረገነው
ውይይት ለመረዳት ችለናል፡
65
ደህንነት ጋር የተያያዙ ህግና ደንቦች ቢኖሩም በኢንዱስትሪው ተዋናኞች ግን ህግና ደንቦችን
መኖራቸዉን የማያውቀው ከፍተኛውን ቦታ ይይዛል፡፡ ባደረግነው ውይይትም የተረዳነው
ይህንኑ ነው፡፡
የህግ/አዋጅ/ደንብ/ ተፈፃሚነት
66
ስለ ደህንነት ዕቃዎችና ምልክቶች (safety equipment, signs and signals)
የጥንቃቄ ዕቃዎችን ስለመሟላታቸው
67
በግንባታ ቦታ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና (First aid) አለ ወይ ለሚለው በተቋራጭ 77%
እንዳለ ሲገልጹ በግንባታ ሰራተኛ በኩል ግን ምንም እንኳን 57% እንዳለ ቢገልጹም ከሱ
ባልተናነሰ 43% አለመኖሩን በማስመልከት መልሰዋል፡፡ በግንባታ ሰራተኞች እንደተገለጸው
የስራ ተቋራጩ አሟልቻለሁ ቢልም ሁሉም ሰራተኛ ምቹና ተጠቃሚ ሊያደርግ በሚችል
መልኩ አለመሆኑ ነው፡፡ በዉይይት ያስተዋልነውም ይህንኑ ነው፡፡ የህንጻ ግንባታ ከመንገድ
ግንባታ አንጻር ሲታይ በተሻለ መልኩ የመጀመርያ ደረጃ የህክምና እርዳታ አሰጣጥ ያለው
ሲሆን በመንገድ ግንባታ ላይ ያለው ከስራው ባህሪው የተነሳ የግንባታ ቦታው ከጊዜያዊ ግንባታ
ፅ/ቤት (project office) የራቀ መሆኑ በተጠቃሚዎች ላይ ምቹ እንዳይሆን አድርጎታል፡፡
የተሟሉ የደህንነት ዕቃዎች
የተሟሉ የደህንነት ዕቃዎች የትኞቹ እንደሆኑ ሲጠቅሱ በሁሉም ወገን አንጻባራቂ ልብስ
በአንደኛ ደረጃ ሲያስቀምጡ ቀጥሎ የእጅ ጓንት፣ በሶስተኛ ደረጃ ሄልሜት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሌሎቹ አልፎ አልፎና በከፊል እንደሚሟላ አመላክተዋል፡፡በመስክ ምልከታ እንደተመለከትነው
በአብዛኛው ቦታ አንጸባራቂ በተሻለ መልኩ ይገኛል፡፡
68
ስለ ደህንነት ባለሙያ (safety officer)
ጥንቃቄ
69
በግንባታ አካባቢ አስፈላጊው የደህንነት ጥንቃቄ ባለመደረጉ ምክንያት አደጋ ሲያጋጥም
ያለው የሪፖርት አደራረግን በተመለከተ
70
አጠቃላይ ከደህንነት (Safety) ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ስራዎች የሚያከነውን Safety
60 50 አለ
40 የለም
40
መልስ ያልሰጡ
23.5
18.2
20 11.8 10
0
0
አማካሪ ተቋራጭ ባለቤት
71
59% የለም ብለዋል፡፡ በአማካሪው የተሰጠው ጥራታቸው የሚያረጋግጥ አካል አለመኖሩ ከስራ
ተቋራጭ ከተሰጠው ምላሽ አንጻር ከፍተኛ መሆኑ የቁጥጥር ስርአቱ ልልና ደካማነቱን ያሳያል
፡፡
በsafety ጉድለት አደጋ ሲያጋጥመው ስላለው ተጠያቂነት
60
60 ሰራተኛው
40 አሰሪው መስሪያቤት
40
ተቋራጭ
20 11.811.8 9.2 6.6
0
0
ተቋራጭ ባለቤት ሰራተኛው
72
ሰአት እላፊና ትራፊክ ፍሰት በሚበዛበት የሚከናወኑ ስራዎች ለአደጋ መፈጠር ያላቸው
አስተዋጸኦ
ሠንጠረዥ 3-18፡ ሰዓት እላፊና የትrፊክ ፍሰት ለአደጋ መፈጠር ያላቸው አስተዋጽኦ
ተቋራጭ ሰራተኛው
የድግግሽ የመቶኛ የድግግሽ የመቶኛ
መጠን ሰስሌት መጠን ሰስሌት
14 82.4 25 32.9
ከፍተኛ
2 11.8 36 47.4
መካከለኛ
1 5.9 13 17.1
ዝቅተኛ
0 0 2 2.6
ምላሽ ያልሰጡ
17 100.0 76 100
ጠቅለላ
ሰአት እላፊና ትራፊክ ፍሰት በሚበዛበት ሰአት የሚከናውኑ ስራዎች ለአደጋ መፈጠር ያለው
አስተዋፅኦ ምን ያህል እንደሆነ ሲያስቀምጡ ተቋራጭ 82% ከፍተኛ መሆኑ ሲገልጹ ሰራተኛው
ደግሞ 47%ቱ መካከለኛ ነው ብለዋል፡፡ በተለይም በመዲናችን አዲስ አበባ በቀኑ የስራ ሰአት
የመንገድ ግንባታ ማከናወን አስቸጋሪ በመሆኑ በአብዛኛው የምሽትን ሰአት ለግንባታ ስራ
ማዋል በሰፊው የተለመደ ነው፡፡ይህም ለአደጋ መፈጠር አስተዋጽኦ ከሚያደርጉት ዉስጥ
በዋናነት የሚጠቀስ ነው፡፡ በትኩረት ቡድን ዉይይት እንደተገለጸው በምሽት ለሚከናወኑ
ስራዎች አደጋ ለመቀነስ ሰራተኞችን በፈረቃ የማሰራት ሁኔታ መኖሩን ተገንዝበናል፡፡
የደህንነት (Safety) ምልክቶችን ባለማስቀመጥ የተፈጠሩ አደጋዎች
ሰራተኛው ተቋራጭ
የድግግሞሽ የመቶኛ ሰስሌት የድግግሞሽ የመቶኛ ሰስሌት
መጠን መጠን
አዎ 29 38.2 11 64.7
73
አስፈላጊ የሆኑ የደህንነት (Safety) ምልክቶችን በአግባቡ ባለማስቀመጥ የተፈጠሩ አደጋዎች
እንዳሉ ለቀረበው ጥያቄ ሰራተኛው 59% የለም ሲሉ በተቋራጩ በኩል ግን 65% መኖሩን
ያሳያል፡፡ ለዚህም ተቋራጩ እንደምክንያትነት ያስቀመጠው አስፈላጊ የደህንነት ምልክቶች
በተለያዩ አካላት መወሰዳቸውና በጉልበት ሰራተኛው በቂ ግንዛቤ ባለመኖሩ ከጥንቃቄ ጉድለት
የተነሳ መሆኑ ነው፡፡
በመጠጥ ወይም ለስራ ብቁ ሳይሆኑ ስራ በማከናወናቸው የተፈጠረ አደጋ
74
በተደጋጋሚ የሚደርሱ የአደጋ አይነቶች
75
በግንባታ ስፍራ ለደህንነት አስጊ የሆኑ የስራ አይነቶች
ተቋራጭ
12%
አዎ
አይደለም
88%
በግንባታ ስፍራ ለደህንነት አስጊ የሆኑ የስራ አይነቶች በግልፅ ተለይተዋል ለሚለው 88% አዎ
የሚል መልስ ሰጥተዋል፡፡ ይህም የአደጋ መንስኤዎች ከህንጻ ግንባታ በተሻለ መልኩ በቅድምያ
ተለይተው አስፈላጊው ጥንቃቄ እንደሚደረግባቸው ያመለክታል፡፡ ነገር ግን ባደረግነው ዉይይት
በተጨባጭ ያስተዋልነው ሪስክ አሳስመንት (risk assessment) ቀድሞ ሰርቶ ወደ ፕሮጀክት
የሚገባ ተቋራጭ በቁጥር እጅግ አናሳ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
በዋናነት የሚጠቀሱ የአደጋ መንስኤዎች
? ? ? ? ? ?? ? ? ? ? ?
? ? ? ? ??
12% ?? ???? ?? ? ? ? ?? ? ? ?
19%
12%
? ? ?? ?? ? ? ??? ? ?? ? ? ??
20%
19% ? ? ?? ? ? ?? ? ? ?
18%
? ?? ? ? ? ? ? ? ? ? ? ? ?
? ??
76
ግንባታ ቦታ ላይ ለሚፈጠሩ አደጋዎች በዋናነት የሚጠቀሱ መንስኤዎች የትኞቹ እንደሆኑ
ለተጠየቀው የደህንነት እቃዎች አለመሟላት የመጀመርያ ደረጃ ሲሆን ቸልተኝነት በሁለተኛ
እንዲሁም ምቹ ያልሆነ የሰራ ቦታና ስለ ስራ ቦታ ደህንነት ግንዛቤ ማነስ በሶሰተኛነት
ተጠቅሰዋል፡፡ ብዙ ወጪ የማይጠይቅ ነገር ግን አደጋ ከተከሰተ በኋላ የሚያስከትለዉን ተጽእኖ
በቀላሉ መታደግ ሲቻል አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ይህ እየተተገበረ አይደለም፡፡
አንድ ስራ በታቀደለት ጊዜ፣ ወጪ እና ጥራት ለማጠናቀቅ የግንባታ ቦታ ደህንነትን
(work zone Safety) ያለው አስተዋፅኦ
77
ከኮንስትራክሽን ነባራዊ ሁኔታ የSafety profession በከፍተኛ የትምህርት ተቋም
ቢሰጥ ስላለው ጠቀሜታ
ሠንጠረዥ 3-21፡ ደህንነት በከፍተና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ቢሰጥ ያለው ጠቀሜታ
ተቋራጭ አሰሪው መስሪያቤት አማካሪ ሰራተኛው
የድግግሞሽ የመቶኛ የድግግሞሽ የመቶኛ የድግግሞሽ የመቶኛ የድግግሞሽ የመቶኛ
መጠን ስሌት መጠን ስሌት መጠን ሰስሌት መጠን ስሌት
ከፍተኛ 11 64.7 9 81.8 7 70.0 64 84.2
መካከለኛ 10 35.3 2 18.2 3 30.0 6 7.9
ዝቅተኛ 0 0.0 0 0.0 0 0.0 3 3.9
ምላሽ ያልሰጡ 0 0.0 0 0.0 0 0.0 3 3.9
ጠቅለላ 17 100.0 11 100.0 10 100.0 76 100.0
አሁን ካለዉ የሃገራችን ኮንስትራክሽን ነባራዊ ሁኔታ Safety professional እንደ አንድ
የትምህርት አይነት በከፍተኛ የትምህርት ተቋም ቢሰጥ ያለው ጠቀሜታ ለሚለው
ተቋራጭ፣ የግንባታ ባለቤት፣ አማካሪ እንዲሁም ሰራተኛ በአማካይ 75% በከፍተኛ ደረጃ
ጠቀሜታ እንዳለው አመላክተዋል፡፡ ከዚህም መረዳት የሚቸለው የSafety profession
መኖር አሁን ያለውን የስራ ላይ አደጋ ከመቀነሱም ባሻገር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን
የላቀ ደረጃ ለማድረስ ያለው ሚና በቀላሉ የሚታይ አለመሆኑን ነው፡፡
የአደጋዎች መቀነስ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ያለው አስተዋፅኦ
78
የተሰጠው ምላሽ የሚያሳየው አስፈላጊዉን ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ አደጋ በሚከሰት ወቅት
የሚወጣን ወጪ እንዲሁም ተተኪ ያልሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት በማትረፍ በሃገራችን
የኢኮኖሚ እድገት ላይ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማበርከት በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ አገራችን
ወደተሻለ ደረጃ እንድትራመድ ያደርጋል፡፡ ባደረግነዉም ዉይይት ያስተዋልነው ይህንኑ ነው፡፡
ስለግንባታ ቦታ ደህንነት ስልጠና (training) በቋሚነት ስልጠና ስለመሰጠት
ስለስራ ቦታ ደህንነት ከአሰሪ መስሪያ ቤትዎ ተገቢው ስልጠና (training) በቋሚነት ይሰጣል
ለሚለው ሰራተኛው፣ ተቋራጭ እንዲሁም አማካሪ በአማካይ 77% አይሰጥም በማለት
መልሰዋል፡፡ ሁሉም የግንባታው ባለድርሻ አካላት ስልጠና በመሰጠት ዙርያ ያለው የአሰራር
ስርኣት ዝቅተኛ መሆኑን አምነዉበታል፡፡ ይህ መሆኑ በግንባታ ቦታ ላይ የግንባታ ሰራተኛው
በየጊዜው የሚቀያየርበት፣ አብዛኛው ማንበብ አለመቻሉ እንዲሁም የሚቀመጡ የቅድመ
ጥንቃቄ ምልክቶችም ሆነ የአሰራር ማንዋሎችን አለመረዳቱ ስለደህንነት ስልጠና ካለመሰጠቱ
ጋር ተዳምሮ በግንባታ ቦታ ላይ የሚደርሰዉን አደጋ የከፋ ያደርገዋል፡፡
79
ስራ (project) ተጠናቆ በርክክብ ወቅት ከሴፍቲ ጋር ተያያዥ የሆኑ ስራዎች
ስለመጠናቀቃቸው
በግንባታ ስራ ደህንነት (work zone Safety) የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ የሚበረታቱበት ሁኔታ
አለ ወይ ለሚለው 47% የሚሆኑት ተቋራጮች በስራ የተሻለ አፈጻጸም ያሳዩ ሰራተኞችን
80
እንደሚያበራታቱ ሲገልፁ አሰሪው መስሪያቤትና አማካሪው በአማካይ 85% የማበረታቻ
ስርአት እንደሌለ ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው በስራቸው የተለያዩ ጥቅማ
ጥቅሞችን የማያገኙ ከሆነ እንዲሁም በተደጋጋሚ በደህንነት ዙሪያ የአሰራር ስርአት
የሌላቸውና በዚህም ምክንያት ብዙ ጊዜ አደጋ የሚያደርሱ ተቋማት አስፈላጊው እርምጀ
የማይወሰድባቸው ከሆነ በግንባታ ዙሪያ ላይ የሚደርሱ አደጋዎች መባባስ ከፍተኛ ምክንያት
እንደሚሆን ባደረግነው ዉይይት ተረድተናል፡፡
ተቋራጭ
የድግግሽ መጠን የመቶኛ ሰስሌት
ከፍተኛ 3 17.6
መካከለኛ 7 41.2
ዝቅተኛ 7 41.2
ምላሽ ያልሰጡ 0 0
ጠቅለላ 17 100.0
81
በግንባታ ስራ ደህንነት (work zone Safety) አለመተግበር ከስራው ውጭ የሆኑ
ማህበረሰብ ላይ ስለሚደርሰው ጉዳት
ምስል 3-29፡ ደህንነት ባለመተግበሩ ምክንያት ከስራ ውጪ የሆኑ ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰው ጉዳት
ሰራተኛው
የድግግሽ መጠን የመቶኛ ሰስሌት
ከፍተኛ 61 80.3
መካከለኛ 9 11.8
ዝቅተኛ 3 3.9
ምላሽ ያልሰጡ 3 3.9
ጠቅለላ 76 100.0
82
የደህንነት (safety) በአግባቡ መተግበሩ በሰራተኞች የስራ ተነሳሽነት ላይ ያለው ሚና ለሚለው
80%ቱ ከፍተኛ ብለዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን
የግንባታ ደህንነት (safety) በሚገባ ባለመተግበሩ አንድን ስራ በተሳካ መልኩ ለማከናወን
የሰራተኛው ሚና ከፍተኛ ከመሆኑ አኳያ ስራው የታለመለትን ግብ እንዳይመታ ያደርገዋል፡፡
ይህ ደግሞ ለኢንዱስትሪው እድገት እንቅፋት ይሆናል፡፡
በንብረትም ሆነ በሰው ላይ ለሚደርስ አደጋ የኢንሹራንስ ዋስትና ስለመስጠቱ
9%
አዎ
የለም
91%
83
ከላይ በሰንጠረዥ እንደተገለፀው ስለግንባታ አካባቢ ደህንነት መጠበቅያ አልባሳት (Safety
equipment) በቂ እዉቀት አለዎት ለሚለው 90% የሚሆኑት መላሾች አዎ በማለት ምላሽ
ሰጥተዋል፡፡ይህም የሚያመለክተው የእቃ አቅራቢዎች ስለደህንት መጠበቅያ አልባሳት በቂ
ግንዛቤ ያላቸው መሆኑን ነው፡፡
በድርጅታችሁ የሚገኙት የደህንነት መጠበቂያ አልባሳት (Safety equipment) ምርቶች
20%
ዩሮፕ
የሌላ ሀገር
80%
84
ደረጃቸውን የጠበቁ የደህንነት መጠበቂያ አልባሳት (Safety equipment)
የመቶኛ ስሌት
30%
አለ
የለም
70%
የመቶኛ ስሌት
0% 20%
ከፍተኛ
መካከለኛ
ዝቅተኛ
80%
ምስል 3-33፡ በግባ ዘርፍ የተሰማሩ ተቋምት የደህንነት አልባሳትን የመግዛት ልምድ
85
በሀገራችን ውስጥ በግንባታ (construction) ዘርፍ የተሰማሩ ተቋማት የደህንነት አልባሳትን
የመግዛት ልምዳቸው ምን ይመስላል ለሚለው 20% መካከለኛ ሲሉ 80% ግን ዝቅተኛ ሲሆን
ከፍተኛ የሚለው 0% መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ይህም የሚያመለክተው የሴፍቲ አልባሳትን
የመጠቀም ልምድ አለመኖሩን ሲሆን ይህም በዘርፉ ለሚፈጠሩ አደጋዎች ትልቁን ድርሻ
ይወስዳል፡፡ ምንም እንኳን በምስል 3-33 እንደተጠቀሰው የደህንነት እቃ አቅራቢዎች
ስለደህንነት አጠባበቅ በቂ ግንዛቤ ያላቸውም ቢሆንም ተጠቃሚዉን ከማሳወቅና ግንዛቤ
ከመፍጠር አንጻር ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት መስራት እየሰሩ አይደለም፡፡
ዋጋ ወይንስ ጥራቱ ለደህንነት (safety) አልባሳት
የመቶኛ ስሌት
20%
አዎ
አይደለም
80%
86
3.2. የጥናቱ ግኝቶች
ሠንጠረዥ 3-28፡ ደህንነትን ውል ስምምነት ሰነድ ውስጥ መግባ አለበት ብለው የሚያምኑ እና ያስገቡ
አሰሪው መስሪያቤት ተቋራጭ አማካሪ
ለግንባታ ስራ ደህንነት የሚወጣ ወጭ ለግንባታ ስራ ደህንነት የሚወጣ ወጭ ለግንባታ ስራ ደህንነት የሚወጣ ወጭ
(በcontract agreement) ይካተታል (በcontract agreement)ይካተታል (በcontract agreement) ይካተታል
ከላይ በሰንጠረዡ እንደሚታየው ደህንነት በውል ስምነቱ ውስጥ መግባት አለበት ብለው
የሚያምኑት ባለድርሻ አካላት(ተቋራጭ፣ አማካሪ እና አሰሪው መስሪያ ቤት) ቁጥር ትልቅ
ቢሆንም በውሉ ውስጥ ያካተቱት በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡ ይህም የሚያሳየው የግንዛቤ እጥረት
እንደሌለ እና ግን ተግባራዊ ማድረጉ ላይ ከፍተኛ ክፍተት እንዳለ ነው፡፡
በስራ ተቋራጮች በኩል የጉልበት ሰራተኛው ዛሬ ስርቶ ነገ ወደሌላ ስፍራ ሊቀይር ስለሚችል
የደህንነት አልባሳት ማሟላት ችግር እንደሆነባቸው ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የጨረታ ስርአቱ(
87
Bidding process) ያነሰ ዋጋ (Least price) መሆኑ የደህንት ጥንቃቄ የበለጠ እንዲቀጭጭ
አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ይህም የስራ ተቋራጩ የሚከፈለው ዋጋ በጣም አናሳ በመሆኑ
ለሚያከናዉናቸው ስራዎች እንኳን በአግባቡ የማይሸፍንለት ስለሆነ የደህንነት ሁኔታን
ለመተግበር ተግዳሮት ሆኖበታል፡፡
88
ምስል 3-35፡ ሰራተኞች የደህንነት ዕቃዎች ሳይሟላላቸው
የቀን ሰራተኛው የእለት ጉርሱን ሰርቶ መዋሉን እንጅ ለወደፊት ስለሚፈጠረው አደጋ
እምብዛም ግድ የለውም፡፡ ስለሚሰራው ስራና ማሽነሪዎች እንኳን በቅጡ ሳያውቅ ወደ ስራ
የሚገባበት ሁኔታ የተለመደ ነው፡፡ በአሰሪዎችም በኩል በሙያው ጠለቅ ያለ እውቀት ያለውና
89
ስልጠና የወሰደ የቀን ሰራተኛ ስለማያገኙና አልፎ አልፎ ቢገኙም ክፍያቸው ስለሚወደድ
ማንኛውንም ያገኙትን ለመቅጠር መገደዳቸው ይህም ለአደጋ መፈጠር ትልቅ አስተዋፅኦ
እንደሚኖረው አስተውለናል፡፡
ምስል 3-36፡ ዕድሜያቸው የገፋ የቀን ሰራተኞች እና የደህንነት አልባሳት ያልተሟላላቸው ሰራተኞች
90
ምስል 3-37፡ ምቹ የስራ ቦታ
91
ስላልተሰራ ተመሳሳይ አደጋ በተደጋጋሚ ሲደርስ ይስተዋላል፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ሰአት
በተጨባጭ የደህንት ጥንቃቄን በተመለከተ በአገራችን ያለዉ ሁኔታ ምንም የለም ለማለት
ያስችላል፡፡ በአጠቃላይ ትኩረት ያልተሰጠዉ በልምድና በዘፈቀደ እየተሰራ ያለ የተረሳ ጉዳይ
ነው፡፡ እንዲያዉም እንደተጠቃሚዉ ቸልተኝነትና ትኩረት እንደማጣቱ የአደጋው መጠን አሁን
ካለው ሊብስ ይገባ ነበር፡፡
92
ምስል 3-39፡ ሰራተኞች የደህንነት አልባሳት ሳይሟላላቸው የማጠናቀቂያ ስራ በመስራት ላይ
በመዲናችን አዲስ አበባ ካለው የቦታ ጥበት አንጻር በሰፊው እየተገነቡ ያሉ ህንጻዎች ከወለል
በላይ ያላቸው ከፍታ ብዙ ስለሆነ እንዲሁም ለመኪና ማቆሚያና መሰል ስራዎች በሚል
ከወለል በታች ሁለትና ሶስት ቤዝመንት ስለሚገነባ በከፍታው ምክንያት የመዉደቅ አደጋዎች
በብዛት ሲከሰቱ፣ በቤዝመንት ቁፋሮ ምክንያት የአፈር መደርመስ አደጋ በብዛት ሲደርስ
ይስተዋላል፡፡
93
ምሰል 3-40፡ ደህንነቱ ባልተጠበቀ የቁፋሮ ሰራ ላይ
2002 ዓ.ም 1 3 0 0 0 0 0 0
2003 ዓ.ም 7 3 1 5 1 3 0 0
2004 ዓ.ም 4 3 0 0 0 2 0 0
2005 ዓ.ም 4 4 0 0 0 5 10 0
2006 ዓ.ም 6 5 0 0 0 7 0 0
2007 ዓ.ም 3 12 0 2 0 1 0 0
2008 ዓ.ም 3 14 0 1 0 1 5 3
ጠቅላላ 28 44 1 8 1 37 15 3
95
ከአካል ጉዳተኞች ፌዴሬሽን በወሰድነው መረጃ መሰረት በ 2009 ዓ.ም በ አዲስ አበባ በ ኮንስትራክሽን
ምክንያት የደረሰ አካል ጉዳት የሚያሳይ ሰንጠረዥ
96
በህንጻ ግንባታ ላይ በተደጋጋሚ የጉልበት ሰራተኞችን ለአደጋ ከሚያጋልጡት አንዱ የእንጨት
ስካፎልዲንግ ነው፡፡ ይህም የግንባታ ጊዜው በሚራዘምበት ሰአት ፀሃይና ዝናብ የሚፈራረቅበትና
ግንባታው ሲቀጥል በነበረው ስለሚጠቀሙ ከሰካፎልዲንግ በመወደቅ ለከባድ የአካል ጉዳትና
ለህልፈተ ህይወት ይዳረጋሉ፡፡ ምንም እንኳን ህጉ ከ4ኛ ፎቅ በላይ ለሆኑ ህንጻዎች የብረት
ሰካፎልዲንግ መጠቀም እንዳለበት ቢያስቀምጥም በሳይት ምልከታችን በተዘዋወርንባቸው የጋራ
መኖርያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ በእንጨት የሚሰሩ ናቸው፡፡ አልፎ አልፎ ግን ዉስን የግንባታ
ቦታዎች ላይ የብረት ሰካፎልድኒግ የሚጠቀሙ አሉ፡፡ ይህ አጠቃላይ ካለው የኮንስትራክሽን ስራ
ጋር ሲነጻጸር እጅግ አናሳ ነው፡፡
97
ምሰል 3-44፡ የእንጨት እስካፎልዲንግ
98
ምስል 3-45፡ ሰራተኞች ለአደጋ በሚያጋልጥ የሥራ ሁኔታ ላይ
99
አሉ፡፡ አብዛኛው የጉልበት ሰራተኛም ከተለያየ ክፍለ ሀገር የሚመጣ በመሆኑ ለሚደርስበት
ጉዳት ተጠሪ የሚሆን ቤተሰብ እንኳን የላቸውም፡፡ ይህም ችግሩን የበለጠ ያባብሰዋል፡፡
በተለይም በአሁኑ ሰዓት የሴት ጉልበት ሰራተኞች ወደ ግንባታው ስራ በከፍተኛ ደረጃ እየገቡ
እና በስራው ላይ ተሳታፊ እየሆኑ ያለበት ሁኔታ በገልጽ የሚታይ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ
የደህንነት እቃዎች እና ምቹ የስራ ሁኔታ ባልተመቻቸበት ሁኔታ እንዲሁም የሚያከናውኑት
ስራ የበለጠ ጉልበትን የሚጠይቅ እና ከባድ ሸክሞችን የማንሳት ስራዎች ስለሚበዙበት ሴቶች
ለጉዳቱ ተጋላጭ ከመሆናቸውም በላይ ለወደፊቱ ከወሊድ ጋር በተገናኘ ሁኔታ
የሚያጋጥማቸውን ችግር እንዲባባስ ያደርገዋል፡፡ በተጨማሪም ሴት ሰራተኞች የግንባታ
ስራቸውን በሚያከናውኑበት አካባቢ ልብስ መቀየሪያ ቦታ፣ ጾታን የለየ የመጻዳጃ ቦታ ባለመኖሩ
ምክንያት ጾታዊ ትንኮሳ እና ሌሎችም ጉዳቶች ሲደርስባቸው ይስተዋላል፡፡
100
ያለው ባለሙያ የሚጠይቅ በመሆኑ መረጃዉን በተፈለገው መልክ ለመስጠት አስቸጋሪ
ሆኖብናል ብለው በደብዳቤ ገለፀዋል፡፡ በቀሪዎች ሁለት ሪፈራል ሆስፒታሎች ዉስጥ አንዱ
በሶስት ወራት ዉስጥ 125 በግንባታ ስራ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ታካሚዎችን ዝርዝር
የገለፀ ሲሆን የአደጋዉ አይነት በጥቅሉ የተቀመጠ በመሆኑ በተደጋጋሚ የሚደርሰዉን አደጋ
የትኛዉ መሆኑ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ ሌላኛው ሆስፒታል ደግሞ በ2008 ውስጥ 531
በመውደቅ 79 በኤሌክትሪክ 27 በማሽን መቆረጥ 122 በኬሚካል ሲሆን በ2009 ደግሞ 681
በመውደቅ 63 በኤሌክትሪክ 47 በማሽን መቆረጥ 176 በኬሚካል ምክንያት መሆኑን
ገልጸዋል፡፡ ከዚህም መረዳት የሚቻለው በኮንስትራክሽን ስራ ምክንያት እየደረሰ ያለው አደጋ
ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሆኑን ያሳያል፡፡ እንደ አጠቃላይ ምንም እንኳን ሁለቱ
ሆሰፒታሎች ከላይ የተገለፀዉን መረጃ ቢሰጡንም ያለው የመረጃ አያያዝ ስርአት
ኮምፒውተራይዝድ በሆነና በተደራጀ መልኩ አለመሆኑን ሁሉም ይስማሙበታል፡፡ በመሆኑም
በቀጣይ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶት የተደራጀ የመረጃ ቋት እና ራሱ የቻለ ባለሙያ ተመድቦለት
ቢሰራ በተደጋጋሚ አደጋ የሚከሰትባቸው የኮንስትራክሽን ተቋማትን አስፈላጊዉን ማስተካከያ
እንዲያደርጉና ጥሩ አፈጻጸም ያላቸዉንም የሚበረታቱበትን ሁኔታ በመፍጠር የኮንስትራክሽኑን
ኢንዱስትሪ ወደ ተሻለ የአሰራር ስርአት ለማድረስ ጠቀሜታዉ የጎላ ነወ፡፡
101
እንደ አጠቃላይ ከ 2005 እስከ 2009 ዓ.ም በግንባታ ስራ ምክንያት የደረሱ አደጋዎች ከተለያዩ
ተቋማት የተገኘው መረጃ በሚከተለው ሰንጠረዥ ተቀምጧል፡፡
102
የተለያዩ ህጎች እና ደንቦች ቢኖሩም ህጉን የተላለፉት ላይ የሚወሰድ እርምጃ
አለመኖር፡፡
በግንባታ ባለቤት፣ አማካሪና የስራ ተቋራጭ በኩል የግንዛቤ ማነስ አለ ብሎ ማለት
አይቻልም ነገር ግን ትኩረት አለመስጠት በትልቁ የሚታይ ችግር ነው፡፡ በጣም ቀላልና
ብዙ ወጪን የማይጠይቁ የሴፍቲ ምልክቶችን እንኳን የመጠቀም ልምዱ በጣም አናሳ
ነው፡፡ ለሚሰሩት ስራዎች የቅድመ ማስጠንቀቅያ ምልክት በማስቀመጥ ብቻ ህይወትና
ንብረት መታደግ ሲቻል ነገር ግን ለጉዳዩ አስፈላጊዉን ትኩረት ባለመሰጠቱ ምክንያት
በርካቶችን አካል ጉዳተኛ እንዲሁም ህይወት እስከመንጠቅ እና ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ
የወጣባቸዉን ንብረቶች ሲወድሙ ማየት እየተለመደ የመጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡ በግንባታ
ሰራተኛ በኩል ደግሞ የእውቀትና የትምህርት ደረጃ ዝቅ ከማለት ጀምሮ በሚሰሩት ስራ
ላይ ያላቸው ግንዛቤ በጣም አናሳ መሆኑ ይጠቀሳል፡፡
የግንባታ ደህንነትን የሚቆጣጠረው አካል ስራው በህጉና በደንቡ መሰረት
የሚከታተልበት አግባብ ልል መሆኑ
በተወሰነ መልኩ ሴፍቲን የተገበሩ አንዳንድ ፕሮጀክቶች አለማበረታታቱ እንዲሁም
ያልተገበሩ ተከታትሎ እርምጃ አለመወሰዱ
በደህንነት ራሱ የቻለ ሙያ የተመረቀ ባለሙያ አለመኖሩ በራሱ በመንግስትም ትኩረት
አለመሰጠቱ ያሳያል፡
103
እንደ አጠቃላይ የግንባታው ዘርፍ ከግብርና ዘርፍ ቀጥሎ ክፍተኛውን የሀገሪቱን እኮኖሚ
የሚያንቀሳቅስ እንደመሆኑ መጠን በግንባታ ቦታ ላይ የደህንነት መጓደል ዘርፉ የሚጠበቅበትን
ድርሻ እንዳያበረክት ከማድረጉም በላይ የኢንደስትሪ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡
በተጨማሪም ይህ ዘርፍ ለበርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች ከፍተኛ የስራ እድል የፈጠረና
እየፈጠረም ያለ በመሆኑ የግንባታው ደህንነት ካልጠጠበቀ በስራው ላይ የተሰማራውን ከፍተኛ
የሰው ሀይል ጉዳት ከማድረስም አልፎ በሞት እንዲቀጠፉ ምክንያት ይሆናል፡፡
104
ምስል 3-46 ግንባቸው ሳይጠናቀቅ ለተጠቃሚ ክፍት የሆኑ መንገዶች
105
ምስል 3-47፡ ሠራተኞች የደህንነት አልባሳት ሳይሟላላቸው በመንገድ ስራ ላይ
ስፔስፊኬሽን በተመለከተ
የሴፍቲ ግንዛቤ በተመለከተ የምንመራበት ሰታንዳርድ ስፔሲፊኬሽን ግርድፍ በሆነ
መልኩ አለ፡፡ ለእያንዳንዱ ፕሮጀክት በተለየ መልኩ (ስፔስፊክ) ግን አይደለም፡፡ ጉድለት
የለበትም ባይባልም በአመዛኙ ስራ ላይ ስለማይተገበር ግንዛቤው አናሳ ነው፡፡ ሙሉ
ለሙሉ ግን የለም ማለት አይደለም፡፡
የስራ ውል ስምምነት
በስራ ውል ስምምነት ላይ ሴፍቲን በተመለከተ አለ ነገር ግን ትኩረት በማጣቱና
አስፈፃሚው አካል የሚወስደው እርምጃ ልል በመሆኑ ተግባራዊ እየተደረገ አይደለም፡፡
በመንገድ ስራ ላይ የሚስተዋሉ አደጋዎችና የአደጋ መንስኤዎች
ከመንገድ ግንባታ ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ የአደጋ አይነቶች የሚከተሉትን ይመስላሉ፡፡
የአደጋው አይነት
106
ባልተከደኑ ማንሆሎች ማየት የተሳናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እና የአቅመ ደካሞች
በመግባት ለከፋ አካል ጉዳት መዳረግ
ተሸከርካሪዎች በመንገድ መረጣ ሳቢያ በሌላ ተሸከርካረ ላይ አደጋ ማድረስ
የራሳቸው ተሸከርካሪ መሰበር
በግንባታ ወቅት በሚፈጠረው የመንገድ መዘጋት ተሸከርካሪዎች ተሳስረው ለረጅም ጊዜ
በመቆመም እርስ በርስ መኮራከም
የአደጋ መንስኤዎች
107
ምስል 3-48፡ ምልክት ሳይቀመጥላቸው እየተገነቡ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶች
108
ለመንገድ ግንባታ በግብአትነት የሚውሉ ማቴሪያሎችን ከኳሪ ሳይት ከተወሰደ በኋላ
ቦታውን ቀድሞ ወደነበረበት ስለማይመለስ ከዚህ ጋር ተያይዞ በሰው ላይ የአካል ጉዳት
ብሎም የሞት አደጋ እያስከተለ ይገኛል፡፡ምንም እንኳን በህጉ ላይ የተቀመጠ ቢሆንም
ተግባራዊ እየተደረገ አይደለም፡፡
4. የጥናቱ ድምዳሜ
በሀገራችን የኮንሰትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ በደህንነት መጓደል ምክንያት በስራው ውስጥ ያሉ
እና ከስራው ውጪ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጎጂ የሚሆኑበት ሁኔታ እየተበራከተ ነው፡፡
ለዚህም ደግሞ በግንባታ ቦታ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ቁልፍ ተዋንያኖች ማለትም ተቋራጮች፣
አማካሪዎች፣ የግንባታ ባለቤቶች እና ሰራተኞች በግንባታ ቦታ ላይ ለሚከሰቱ አደጋዎች
ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡ በአጠቃላይ ከዚህ ጥናት የተገኙ የማጠቃለያ ሀሳቦች
እነደሚከተለው ተቀምጠዋል፤
110
የማበረታቻ ስርአት የለም፡፡ ይህም የሆነው ህጉን ተከታለው በሚያስፈጽሙት አካላት
ላይ ተጠያቂነት ባለመኖሩ ነው፡፡
አንድ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት በዕቅድ ዉስጥ አደጋ እንዳይደርስ ቅድመ ዝግጅት
ማድረግ ብሎም የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመቀነስ እንዲሁም ከተከሰቱ በኋላ
የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ በቅድሚ risk assessment ተሰርቶ ወደ ስራ
አይገባም፡፡
111
በህንፃ ግንባታ ላይ በተደጋጋሚ የሚደርሱ አደጋዎች የሚጠቀሱት ከላይ በመውደቅ፣
ከስካፎልዲንግ መውደቅ እና የአፈር መናድ ሲሆን በመንገድ ግንባታ በኩል ለኳሪ
የተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ መግባት፣ ባልተከደኑ ማንሆሎች ውስጥ መግባት እና የጎረፍ
አደጋ ከፍተኛውን ደርሻ ይወስዳሉ፡፡ ለዚህም በዋናነት ከሚጠቀሱ ምክንያቶች የቅድመ
ጥንቃቄ ዕቃዎች አለመሟላት፣ በአሰሪውም በሰራተኛውም በኩል የሚታይ ቸልተኝነት፣
ምቹ ያልሆነ የስራ ቦታ እና የግንዛቤ ማነስ በቅደም ተከተል ከፍተኛውን ቦታ ይይዛሉ፡፡
112
በመግባት፣ የጎርፍ አዳጋ እንዲሁም ለመንገድ ግንባታ የሚውሉ ማቴሪያሎች
ከተገለበጡ በኋላ ግንባታው ሲጠናቀቅ የተረፉት ግብአቶች አለመነሳታቸው ከመንገድ
ጋር ተያይዘው ለሚከሰቱ አደጋዎች መፈጠር ትልቅ አስተጽኦ አላቸው፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቶች በሚከናወኑበት ጊዜ ከሌሎች ዘርፎች ጋር ያለው ቅንጅታዊ
የአሰራር ስርአት አናሳ ነው፡፡
113
5. የመፍትሄ ሀሳቦች (Recommendation)
የውል ስምምነት ሰነድን በተመለከተ
ህግን በተመለከተ
114
የሥራ ተቋራጮችም ሆነ የአማካሪዎች የስራ ፈቃድ በሚሰጥበት ወቅት እንደማንኛዉም
ሌሎች ፕሮፌሽን የደህንነት ባለሙያ (safety profession) በመስፈርቱ ዉስጥ ተካቶ
የሚጠየቅበት ሁኔታ ቢመቻች፤
በተደጋጋሚ አደጋ የሚከሰትባቸው የኮንስትራክሽን ተቋማትን አስፈላጊዉን ማስተካከያ
እንዲያደርጉና የቅጣት እርኮኖችን በማስቀመጥ በተዋረድ ውለታን ማቋረጥና ከዚያም
ሲብስ የስራ ፈቃዱን እስከመሰረዝ የሚያደርስ እርምጃ ቢወሰድ፤
እንዲሁም የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ተቋማት ከሌሎች ተነጥለው ተጨማሪ ሥራን
በመስጠት፣ የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት እንዲሁም የኢንሹራንስ ተቋማት ቅናሽ
እእዲያደርጉ በማድረግ የሚበረታቱበት ሁኔታ ቢፈጠር፤
115
የሴፍቲ እቅድን በተመለከተ
116
ደህንነትን (Safety) በተመለከተ አስፈላጊ የሆኑ ትምህርቶች እንደየትምህርት ደረጃቸው
ከዝቅተኛ የትምህርት ክፍል ጀምሮ እየተሰጠ ቢመጣ እና ወደ ከፍተኛ የትምህርት
ተቋማትም በሚደርሱበት ጊዜ ከግንባታ ስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው
የደህንነት ኮርሶች በጥልቀት የሚሰጡበት ሁኔታ ቢመቻች
እንደ አጠቃላይ ከግንባታ ደህንነት ጋር ተያያዥ የሆኑ ችግሮችን በዘለቄታዊ ሁኔታ
ከመቅረፍ አንጻር ግንባታ ደህንነት ሥልጠና ማዕከል (Safety excellency center)
ቢቋቋም
ሰራተኞች ወደ ግንባታ ቦታ ላይ ስራ በያከናውኑበት ጊዜ በተለያዩ ሱሶች ምክንያት
እየደረሰ ያለው አደጋ እየጨመረ ስለሆነ በሰራተኞች ላይ ተገቢው የሆነ ቁጥጥር
የሚደረግት ሁኔታ ቢመቻች
117
የኢንሹራንስ ሽፋንን በተመለከተ
ይህ ጥናት የተካሄደው በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ብቻ ስለሆነ እንደ አጠቃላይ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ተግባራዊ ለማድረግ ተጨማሪ
ጥናቶች በደህንነት ዙሪያ ቢካሄዱ እና የሚገኘውንም መረጃ እንደየ ቦተው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግበት ሁኔታ በመቻች
የተሻለ ውጤትን ያስገኛል፡፡
118
6. ዋቢ
1. J.K.Tan, Dr. Stolz and S.Mijan,(2003), Safet to build and safe to use- A total safety
management system, land transport authority, Singapore
2. S.Wiliiams, (2006), Health and safety in construction, London
3. Cheng, (2004), Safety management assessment framework
4. Mr.chappeu,(2016), Hazzards in construction, Canada
5. የፍትሀብሄር ህግ
8. Ministry of urban development and construction, (August 2013), Ethiopian building code
standards (EBCS 14), Ethiopia
10. study of occupational safety and health in ethiopian construction industry: a case study on
addis ababa and welkiteby Seifedin sermolo,(jan. 2014)
11. Ann Herbert, (March 2012); National profile report on occupational safety and health in
China, China
12. John Kreps, Workzone safety in Europe
13. Journal of construction in developing countries, Penerbit university Saris Malaysia (2013);
14. የሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡ 2008/2009ዓ.ም፡፡ የኮንስትራክሽን ዘርፍ የሙያ ደህንነት፣ ጤንነት
ፖሊሲና ስትራቲጂ ረቂቅ ሰነድ፡፡ አዲስ አበባ
15. Site C Clean energy project, june 2015, Construction safety management plan
16. Land transport authority, September 2012, Construction safety handbook
17. Takele.T & Mengesha. A, 2006, Occupational health and safety, Gondar university
18. J.K Tan, D.R Stolz, S. Mijan, 2003, Safet to build and safe to use/ Atotal safety management system,
RTS conference, Singapore
ፕሮፌሰር አበበ ድንቁ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ እና ማኔጅመንት ቼር
ዶ/ር አብረሀም
119
7. አባሪ
7.1. መጠይቆች
7.2. ቼክ ሊስት
120