Professional Documents
Culture Documents
አዲስ አበባ
ማውጫ
ይዘቶች ገጽ
መግቢያ………………………………………………………………………………………… .7
1. አጠቃላይ ሁኔታዎች....................................................................................................................................9
1.1. ስያሜ................................................................................................................................................9
1.2. የማንዋሉ ዓላማ..................................................................................................................................9
1.3 የማንዋሉ ግብ......................................................................................................................................9
1.4. የማንዋሉ አስፈላጊነት፤........................................................................................................................9
1.5. የማንዋሉ ወሰንና ተጠቃሚዎች..........................................................................................................10
1.6. ከማንዋሉ የሚጠበቅ ውጤት፤.............................................................................................................10
0
1.7. በማንዋሉ ውስጥ የተካተቱ ዋና ዋና ተግባራት.......................................................................................10
2. የቃላትና የጽንሰ ሃሳቦች ማብራሪያ፤............................................................................................................10
11.1. የንግድ ምዝገባ፤ የንግድ ፍቃድና እድሳት፤ የንግድ አሰራርና ሸማቾች ጥበቃ ዙሪያ የሚፈጸሙ የኢንስፔክሽን
ተግባራት.......................................................................................................................................28
12. የውጭ ኢንስፔክሽን ለማከናወን የምንከተላቸው የአሰራር ቅደም ተከተሎች...................................................29
12.1. ሕገ-ወጥ ንግድ ሥራ ተፈጽሟል የሚያሰኙ ተግባራት፣........................................................................29
13. የንግድ ህጋዊነትን ስለማስከበር...............................................................................................................30
1
13.2.6. የንግድ አድራሻ ጋር በተያያዘ-፡...................................................................................................34
14. የደረሰኝ ግብይትና መረጃ አያያዝ፣...........................................................................................................35
16.1. በንግድ ምዝገባና ፍቃድ ዙሪያ የሚፈጸሙ ተገቢ ያልሆኑ አሰራሮችን መከላከልና ስርዓት
ማስያዝ………………………………………………………………………………………..39
17.1. የህብረተሰቡን ደህንነትና ጤንነት የሚጎዱ፣ የአካባቢ ብክለት የሚያስከትሉ የንግድ ተቋማትን ተከታትሎ ህግ
የማስከበር አሰራር፣.........................................................................................................................44
17.2. ቢሮዉ የንግድ ፈቃድ የማይሰጥባቸዉ መጤ ባህሎችን ስለመከላከል፣......................................................45
18. የምርት ጥራትን ስለመከታተል፣.............................................................................................................45
2
19.2. የመስፈሪያ መሳሪያዎች ላይ የሚፈፀም ህገ-ወጥነትን ስለመከላከል፣........................................................49
19.3. ምርመራ የሚካሄደባቸው የሚዛን ዓይነቶች እና አሰራራቸው................................................................51
19.4. የመሥፈሪያ መሣሪዎች እደገና ማረጋገጥ...................................................................................................55
19.5. የመሥፈሪያ መሣሪያዎች ትክከለኝነታቸው ሳይረጋገጥ ገበያ ላይ እንዳይወሉ መቆጣጠር..........................................56
19.6. ልኬት አዛብቶ በተገኘ ድርጅት ላይ ስለሚወሰድ እርምጃ፣.....................................................................57
20. የምርት ወይም ዋጋ ክትትል………………………………………………………………………57
3
መግቢያ
መንግስት በሀገሪቱ መልካም አስተዳደርን እና ፈጣን ልማት ለማምጣት የተለያዩ ስትራቴጂ እና የአሰራር ስልቶች በመቀየስ ተግባራዊ
እንቅቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በተለይም ነፃ የገበያ ኢኮኖሚ ፖሊሲን መሠረት በማድረግ በማንኛውም የንግድ ሥራ መስክ
ለሚደረገው እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር፣ ህጋዊ ሆኖ የተሰማራውን የንግዱን ማህበረሰብ ለማገዝ፤ በህገወጥ ነጋዴው ላይ
ደግሞ አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ የህግ ማስከበር ስራውን የተጠናከረ ለማድረግ፤ የሸማቹን ህብረተሰብ ጤንነትና
ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ የንግድ እቃዎችንና አገልግሎቶችን መስፋፋት ለመግታት እንዲቻል፤ እንዲሁም ተጠቃሚው ለከፈለው ዋጋ
ተመጣጣኝ የሆኑ የንግድ ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን ማግኘት የሚችሉበትን ሁኔታ ለማመቻቸትና፤ የንግዱ ሕብረተሰብም ከጸረ -
ውድድርና ተገቢ ካልሆነ የገበያ ተግባራት የሚከላከልና ለነጻ ውድድር አመችነት ያለው የገበያ ሥርዓት ለማስፈን የሚያስችሉ ህጎችን
በማውጣትና አሰራሮችን በመቅረጽ ለንግዱ ማደግ ወሳኝ የሆኑ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ከነዚህም መካከል የንግድ ምዝገባና
ፈቃደ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 ወጥተው ሥራ ላይ
በዚሁ መነሻነትም በከተማችን የሚካሄደው የንግድ እንቅስቃሴ የተሳለጠ ለማድረግ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በንግድ ኢንስፔክሽንና
ሬጉላቶሪ ስራ ሂደት አማካኝነት የንግድ ክትትል፤ ቁጥጥርና የህግ ማስከበር ስራዎችን ለማስፈጸም የሚረዳ የአሰራር ማንዋል የንግድ
ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ 686/2002 እና የንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ አዋጅ 813/2006 ን መነሻ በማድረግ አዘጋጅቶ
4
ይሁንና የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ 686/2002 የተሻሻለና በመሆኑና አሁን በስራ ላይ ባለው የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር
980/2008 እና አሱን ለማስፈጸም በሚኒስትሮች ምክር ቤት በወጣው የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ደንብ ቁጥር 392/2009
የተተካ በመሆኑ ይህንኑ ተከትሎ የተሻሻሉትንና እንደ አዲስ የገቡ ጉዳዮችን በማካተት የክትትልና ቁጥጥር አሰራር ማንዋሉን በማሻሻል
ከአዋጁና ደንቡ ጋር ተናባቢ የማድረግንና እና የአሰራር ግልጽነትን የመፍጠር አስፈላጊነት በማመን የማስፈጸሚያ ማንዋል ማሻሻያ
በተጨማሪም በንግዱ፣ በሸማቹ፣ በመንግስት መዋቅር ዘንድ የሚታየዉን የአመለካከት እና የክህሎት እጥረት መፍታት፣
የመረጃ ስርዓታችንን የበለጠ ግልጽ ማድረግ እና የንግድ ህግ ማስከበር ስራን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማረጋገጥ
በሚያስችል መልኩ መመራት ያለበት ከመሆኑም ባሻገር በተለይ ህገ -ወጦች ላይ የሚወሰደዉ እርምጃ ፍትሃዊ፤
አስተማሪ እና ጤናማ መሆኑን ማረጋገጥ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ከዚህ በፊት በ 2007 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣውና
ተግባራዊ እየተደረገ የነበረው የንግድ ክትትልና ቁጥጥር አሰራር ማንዋል የነበረበትን እጥረት በመፈተሽ ማስተካከያ
1. አጠቃላይ ሁኔታዎች
1.1. ስያሜ
ይህ ማንዋል በአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት
የንግድ አሰራር እና ህጋዊነት ማንዋል” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
5
1.3 የማንዋሉ ግብ
የዚህ ማንዋል ግብ በንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት የንግድ አሰራሩ ህግን ተከትሎ እንዲከናወን
በማስቻል ፍትሃዊ፤ ፈጣን፤ ውጤታማ፤ ጥራትና ምቹነት ያለው አሰራር እንዲኖር በማድረግ
ደንበኛውን/ተገልጋዩን/ ማርካት ነው፡፡
6
1.7.5. የህጋዊ ስነ-ልክ ካሊበሬሽንና ኢንስፔክሽን፣
1.7.6. የክትትልና ድጋፍ ተግባራት
1.7.7. የሸማቾች ቅሬታና አቤቱታ መቀበል፤ ማጣራትና ምላሽ መስጠት፤
1.7.8. ለኢንስፔክሽን የሚያገለግሉ ልዩ-ልዩ ቅጻ-ቅጾች ማዘጋጀት
1.7.9. የክስ መረጃዎችን የማደራጀትና ክስ እንዲመሰረት ማድረግና መከታተል ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
7
2.14. የንግድ ድርጅት ማሸግ/መዝጋት ማለት፡-የንግድ ሥራው የሚፈጽምበትን መደብር ሥራውን ለማስቆም
መስኰቶችንና በሮቹን በባለ ድርጅቱ እንዲዘጋ አድርጐ መቆለፉን በማረጋገጥ የመስሪያ ቤቱ ማህተም ባለበት
ስለመታሸጉ የሚገልጽ ደብዳቤ በማጣበቂያ በበሩ/ በመስኮቱ መክፈቻ ወይም መገጣጠሚያ ላይ እንደተዘጋ
መለጠፍ ነው፤
2.15. የንግድ ድርጅት ማገድ፡- ማለት የንግድ ድርጅቱ በሮችና መስኮቶች ሳይታሽጉ /ሳይዘጉ ነጋዴው ሥራውን
እንዲያቆም ፈቃዱ ለጊዜው የታገደ መሆኑን በደብዳቤ/ በጽሁፍ መግለጽ ማለት ነው፤
2.16. መደበኛ ክትትል፡- ማለት እቅድና ፕሮግራም ተይዞ የሚከናወን የንግድ ስራ ክትትልና ቁጥጥር ነው፤
2.17. ድንገተኛ ክትትል፡- ማለት ጥቆማ ደርሶ ድርጊቱን ለማስቆም፣ ለመቆጣጠር የሚፈጸም ሲሆን ሕገወጥ ንግድ
ድርጊቱ ይሰወራል፤ ይጠፋል፤ ይደበቃል ተብሎ ሲገመት ከአካባቢው የፖሊስ ሃይል ጋር በመሆን ፍተሻ
የማድረግና ተገቢ ሆኖ ሲገኘ የማሸግ ተግባር ነው፡፡
2.18. ሕጋዊ ስነ - ልክ፡- ማለት በሕግ የተቀመጡ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ ልኬትና የልኬት አሐዶችን
፤የመለኪያ መሣሪያዎችን ፤የልኬት ዘዴዎችን ከማረጋገጥ ጋር በተያያዘ በሕግ ስልጣን በተሰጣቸው የመንግስት
አስፈፃሚ አካለት የሚከናወን ተግባር ነው፡፡
2.19. የመስፈሪያ መሳሪያ፡- ማለት የክብደት፤ የርዝመት፤ የይዘት፤ ጉልበት፤ የጊዜ፤ የሙቀት ልክ መሣሪያ ነው፡፡
2.20. የማመሰካሪያ መደበኛ መሳሪያዎች፡- ማለት ቢሮው የሚኖሩትና የሚጠብቃቸው መደበኛ መሥፈሪያዎች ወይም
የመስፈሪያ መሣሪያዎች ናቸው፡፡
2.21. የመቆጣጠሪያ መደበኛ መሣሪያዎች፡- ማለት ለመገበያያ የሚያገለገሎትን የመሥፈሪያ መሣሪያዎች ትክክለኝነት
ለመርመርና ለማረጋገጥ የህጋዊ ስነ-ልክ ኦፊሰሮቹ የሚጠቀሙባቸው መደበኛ መሣሪያዎች ናቸው፡፡
2.22. የመሥፈሪያ መሣሪያዎች ሻጭ፡- ማለት ትርፍ ለማግኘት በሳይንሣዊ ሥነ-ልክ የመሥፈሪያ መሣሪያዎችን
ለተጠቃሚዋች የሚሸጥ ወይም በሌላ አኳኋን የሚያስተላለፍ ሰው ነው፡፡
2.23. ተጠቃሚ፡- ማለት በንግድ ሥራ ላይ በመሥፈሪያ መሳሪያ የሚጠቀም ወይም ለዚሁ ጉዳይ የሚያገለግል
የመሥፈሪያ መሣሪያ በቁጥጥሩ ሥር ያለ ማናቸውም ሰው ነው፡፤ነገር ግን ለግል ቤት አገልግሎት ጉዳይ በመስፈሪያ
መሣሪያ የሚጠቀመውን ሰው አይጨመርም፡፡
2.24 . ምርመራ፡- ማለት ማናቸውም የመሥፈሪያ መሣሪያዎች ትክከለነታቸውና ሌሎችም ግዴታዎች ሁሉ ከተገቢዎች
የኢትዩጵያ ደረጃዎች ጋር ለመስማማታቸው በአፊሰር የሚመረመርበት ሥርዓት ነው፡፡
2.2.5 ካሊብሬሽን/ማመሳከር፡- ማለት የመለኪያ መሣሪያውን የተመለከቱ የልኬታ እሴት /value/ መጠን ወይም
የመለኪያ ሰርዓት ወይም የማመሳከሪያ ስሪት የልኬታ ደረጃዎች ላይ በተገለጸው ዕሴት ጋር ያለውን አንድነት
ወይም ልዩነት ለማወቅ የሚደረግ ንጽጽር ነው፡፡
2.26. የመለኪያ መሣሪያን ትክክለኝነት ማረጋገጥ /verfiction/፡- ማለት የመለኪያ መሣሪያ በሕግና በአስገዳጅ የኢትዩጵያ
ደረጃዎች የተቀመጡ መስፈርቶችን ማሟላቱን ለማረጋገጥ የሚደረግ ምርመራን ፈትሸን ምልክት ማድረግንና
የትክክለኛነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መስጠትን የሚጨምር ተግባር ነው
8
2.27. ልኬት፡- የአንድን የተወሰነ መጠን ለማከናወን የተሟላ፣ የመለኪያ መሣሪያ እና ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውን
መሣሪያዎችን በማቀናጀት የሚገኝ ውጤት ማለት ነው፡፡
3.1 . የአሰራር ማንዋሉ መነሻ ያደረጋቸዉ ዋና ዋና ጉዳዮች
3.1.1. ከዚህ በፊት መጋቢት 2007 ተዘጋጅቶ በስራ ላይ የነበረዉ የንግድ ክትትልና ቁጥጥር አሰራር ማንዋል
ነባሩን አዋጅ ቁጥር 686/2002 መነሻ ያደረገ ነበር፡፡ ነገር ግን አዲስ የወጣው የንግድ ምዝገባና ፍቃድ
አዋጅ ቁጥር 980/2008፤ ደንብ ቁጥር 392/2009 እና የንግድ ምዝገባ፣ ፍቃድ እና ድህረ ፍቃድ
ኢንስፔክሽን መመሪያ ቁጥር 10/2009 በርካታ አዳዲስ ድንጋጌዎች የያዘ በመሆኑ እና በንግድ
ውድድርና የሸማቾች መብት ጥበቃ አዋጅ 813/2006 በመጠቀም ይህን ማሻሻያ ለማድረግ እንደ
መነሻ ተወስዷል፤
3.1.2. በነባሩ የአሰራር ማንዋል ላይ የነበረውን የግልፀኝነት ችግር እና በሁሉም ተግባሮቻችን ላይ ተደራሽ
የመሆን እጥረቶችን የመፍታትና አሰራሩን በሁሉም ክ/ከተሞችና ወረዳዎች ወጥ በማድረግ ህገ-
ወጥነቱን የመከላከል ለዉጥ የማምጣት አስፈላጊነት፣
3.1.3. የግብርናና የኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂዎች ዉስጥ የንግድ እና ግብይት ስርዓታችንን ስርዓት
ለማስያዝ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ለማሳካት፣
3.1.4. በቢሮዉ ተዘጋጅቶ በከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የፀደቀዉን የንግድ አሰራር ማሻሻያ ፕሮግራም ተግባራዊ
ማድረግ፣
3.1.5. በህገ-ወጦች ላይ በሚወሰዱ አስተዳዳራዊ እና ህጋዊ እርምጃዎች ፍትሃዊነት እና አስተማሪነት ጋር
ተያይዞ የሚነሱ መልካም አስተዳደር ችግሮች፣ በንግድ ህግ ማስከበር ሂደት በሚወሰዱ እርምጃዎች
ላይ የንግዱ አደረጃጀትና ሸማች ማህበረሰብ የሚያነሳውን ቅሬታና የመልካም አስተዳደር መጓደል
ጉድለቶችን ለማረም፣ እና
3.1.6. አሁን ባለንበት ወቅት በከተማችን ዉስጥ የሚስተዋሉ የንግድ ህገ-ወጥነቶች ለሰነዱ ዝግጅት መነሻ
የተደረጉ ዋና ዋና ጉዳዮች ናቸዉ፡፡
3.2 . ዳይሬክቶሬቱ ከሌሎች ዳይሬክቶሬቶች ጋር ያለው ግንኙነትና ተመጋጋቢነት
3.2.1. ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በዘመኑ ያልታደሱት ንግድ ፈቃዶች በአድራሻቸው መረጃ መቀበል እንዲሁም በተለያዩ
ጥፋቶች የታገዱ የተዘጉና የተሰረዙ ፈቃዶችንና ምዝገባዎች መረጃ ማግኘት፤
3.2.2. ከሴክተር መ/ቤቶች የሙያ ብቃት የሌላቸውን ድርጅቶች መረጃ መቀበልና ሙያዊ እገዛ ማግኘት፤
3.2.3. ከፍትህ አካላት ጋር ጥፋተኞች አስተማሪ የሆነ ቅጣት እንዲያገኝ ማድረግ፤
3.2.4. ከፌደራል የንግድ ውድድርና ሸማች ጥበቃ ባለስልጣን ጋር ጸረ -ውድድርና ሸማቾች መብት ጥሰት ተግባራትን መከላከልና
የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት፤
3.2.5. ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስለዘርፉ ሥራ የሚሰጡ መመሪያዎችና አሠራሮች መቀበልና መተግበር ወዘተ…
3.2.6. ስለህገ-ወጡና ህጋዊው ከማንኛውም ህዝባዊና መንግስታዊ አካላትም ሆነ ከግለሰብ አስፈላጊውን መረጃ መለዋወጥ፡፡
9
4. የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ቡድን ኃላፊነት እና ተግባር
በቡድኑ የሚከናወኑ የክትትልና ቁጥጥር፣ መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ስርጭት መረጃ አያያዝ፣ ስነ ልኬት ሜትሮሎጂ ሥራ፣ ቅሬታና
አቤቱታዎችን ማጣራትና ምላሽ መስጠት እና በክስ ምርመራ በህገ ወጦች ላይ የማጣራት ስራ ዋና ዋና ተግባራት ናቸው፡፡
10
4.1.23. ስለ ህገወጥ ንግድ ለባለድርሻ አካላትና ለንግድ ህብረተሰብ ግንዛቤ መፍጠር፤
4.1.24. ጥፋት ሰርተው ወደ ህግ ላቀረባቸው ነጋዴዎች የህግ ምስክር ሆኖ ይቀርባል መረጃውንም ያጠናቅራል ለሚመለከተውም
ያቀርባል፣
4.1.25. ማኑዋልና መመሪያ ማዘጋጀት ሲፈቀድ መተግበር፤
4.1.26. የክትትልና ቁጥጥሩን ሥራ ላይ የድጋፍና ክትትል ሥራ መሰራት፤
4.1.27. በሥራ ላይ በሚያጋጥም ችግሮች ላይ በጥናት የተደገፈ መፍትሄ መስጠት፤
4.1.28. ለባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ይሰጣል፤
4.1.29. የንግድ ሥራ ፈቃድ ለሌላ ሰው በኪራይ በሽያጭ በሌላ በአዋጁ በተከለከሉ ተግባሮች ለ 3 ኛ ወገን አለመተላለፉን
ማረጋገጥ፤
4.1.30. አገልግሎትና የሸቀጦች ዝውውር በደረሰኝ መሆኑን ማረጋገጥ፤
4.1.31. ማንኛውም የንግድ ግብይቱ ከመጨረሻ ተጠቃሚ በስተቀር በቲን ሰርተፊኬት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ማረጋገጥ፤
4.1.32. ጥፋት የተገኙበት ነጋዴ መጠራት ያለበት በቃል ሣይሆን በመጥሪያ መሆን አለበት፤
4.1.33. ማንኛውንም አስተዳደራዊ እርምጃ ሲወሰድ የሚበላሽ ምርት ወይም አገልግሎት የሚኖር ከሆነ በመጀመሪያ የ 24 ሰዓት
ማስጠንቀቂያ በአድራሻ መስጠት ይገባል፣ ነገር ግን የሚያሣግድና የሚያሰርዝ ሆኖ ከተገኘ ሪፖርቱን ለንግድ ምዝገባና
ፈቃድ ዳይሬክቶሬት በማስተላለፍ እርምጃው እንዲወሰድ ይደረጋል፤
4.1.34. በትክክል በመስክ የተገኘውን ነጋዴ ከምዝገባና ፍቃድ ሥራሂደት ካለው መረጃ ጋር /ማናበብ/ ማገናዘብ፤
4.1.35. ስለ ሕገወጥ ንግድ መንስዔዎችን በማጥናት መረጃዎችን የመሰብሰብና የመፍትሄ ሃሳቦችን ማመንጨት፤
4.1.36. በአጠቃላይ በአዲሶቹ አዋጅ መሠረት የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት የሥራ እንቅስቃሴውን በማዕከል
በክፍለ ከተማና በወረዳ ተግባራዊ ማድረግ ነው፤
4.2. የህጋዊ ስነ-ልክ ዋና ዋና ተግባርና ኃላፊነቶች
11
4.2.5. በትክክል የማይሰሩ ነገር ግን ተስተካክለዉ በትክክል መስራት የሚችሉ የመለኪያና የመስፈሪያ
መሳሪያዎች እንዲጠገኑ ያዛል፣መሳሪያዎቹ ተጠግነዉ ሲመጡ በትክክል ልኬት የሚሰጡ መሆኑን
በማረጋገጥ አገልግሎት ላይ እንዲዉሉ ያደርጋል፤
4.2.6. ትክክለኛ ሆነው ያልተገኙ የመለኪያና የመስፈሪያ መሳሪያዎችን ይቆጣጠራል፣ አገልግሎት
እንዳይሰጡ ይደረጋል፤
4.2.7. የንግድ ስነ-ምግባር በሚጎድላቸዉ ነጋዴዎች አማካኝነት የመለኪያና የመስፈሪያ መሳሪያዎች ላይ
የሚፈፀም የማጭበርበር ድርጊትን ለመከላከል ድንገተኛ ፍተሻ እና ክትትል ያደርጋል፡፡ ችግር
ያለባቸው መስፈሪያዎችን ያስወግዳል፡፡ አጥፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል፡፡
መረጃዎችንም አጠናቅሮ ለህግ ክፍል በማቅረብ ክስ እንዲመሰረት ያደርጋል፤
4.2.8. የልኬት ወይም የመስፈሪያ መሳሪያዎችን መዛባትን በተመለከተ የጥቆማ ስልኮችን በየንግድ ተቋማት
በመለጠፍ በማስተዋወቅ የጥቆማ አሰጣጥ ስርዓት ይዘረጋል፤
4.2.9. ከህብረተሰቡ የሚቀርቡ ጥቆማዎችን ይቀበላል፣ድንገተኛ ፍተሻ እና ክትትል በመለኪያና መስፈሪያ
መሳሪያዎች ላይ ያካሂዳል፣ አጥፊዎች ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል፣ ያስወስዳል፣
ዉጤቱንም ለጠቋሚዉ ያሳዉቃል፤
4.2.10. የመስፈሪያ መሳሪያዎችን በማዛባት የማጭበርበር ጥፋት አጥፍተዉ የተገኙ ነጋዴዎችን ዝርዝር እና
መረጃ አደራጅቶ ለፖሊስ ያቀርባሉ፣ በፍ/ቤት ተገኝተዉ በጥፋተኞች ላይ የምስክርነት ቃል
ይሰጣሉ፤
4.2.11. በሚዛንና መስፈሪያ መሳሪያዎች የሚለኩ ወይም የሚመዘኑ ቁሶች መጠናቸው ከተከፈለባቸው ዋጋ
እኩል ሆነው ካልተገኙ እርምጃ ይወሰዳል፤
4.2.12. በክፍለ ከተማውና በወረዳው ለልኬት ስራ የሚውሉ የመለኪያና መስፈሪያ መሳሪያዎችን በጀት
በማስያዝ በኢትዮጵያ ደረጃዎች አጀንሲ የካሊብሬሽን ስራ ያሰራል፤
12
4.3.6. ሸቀጦች ለህብረተሰቡ ከሚያቀርቡ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጋር ቅንጅታዊ አሰራር ይፈጥራል፣
በየእለቱ መረጃ ይለዋወጣል፣ የአሰራር ግልጽነትን በመፍጠር አላስፈላጊ ብክነትን ይከላከላል፤
4.3.7. የመሰረታዊ ሸቀጦች ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ቸርቻሪ ነጋዴዎችንና ሸማቹን ለማስተሳሰር የሚያስችል
የኩፖን ስርዓት መፈጠሩን ያረጋግጣል፤ በተፈጠረው ስርዓትም ለህ/ቡ ምርቱ እየደረሰ መሆኑን
ያረጋግጣል፤
13
6.3. የፋይል ምርመራ ስራውን በሙሉ ኃላፊነትና ተጠያቂነት በማካሄድ ወቅታዊ ሪፖርቶችን ያዘጋጃል፤
ለሚመለከተው ስራ ኃላፊም ለውሳኔ ያቀርባል፤
6.4. የፋይል ምርመራ ስራ ሲካሄድ የተዘጋጁ ቼክ-ሊስቶችን በመጠቀምና በፋይል ውስጥ የተያያዙ
መረጃዎችን ብቻ መሠረት በማድረግ ይፈጽማል፤
6.5. የውስጥ ኢንስፔክሽን ህጎችንና አሰራሮችን የተመለከቱ የሥልጠና ፕሮግራሞችን ያዘጋጃል፤
ስልጠናዎችን ይሰጣል፤
6.6. የውስጥ ኢንስፔክሽን አሰራርን ለማሻሻልና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ ጥናቶችን ያካሂዳል፤
ምክረ-ሃሳቦችን ይሰጣል፤ ጥናቶችን ተግባራዊ ያደርጋል፤
6.7. በፋይል ምርመራ ትግበራ የተገኙ መረጃዎችን ይመዘግባል፤ መረጃዎችም ያደራጃል፤
6.8. በየወቅቱ በሚካሄድ የውስጥ ኢንስፔክሽን ትግበራን ተከትሎ በተገኙ ነጥቦች ላይ የተደራጀ ግብረ
መልስ በባለሙያና በስራ ክፍል ደረጃ ያዘጋጃል፤ ግብረ-መልስ ይሰጣል፤
14
7.1.13. በከተማው መሠረታዊ ሸቀጦች በኩፖን ስርኣት መሠረት እየተሰራጨ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ከዚህ የስርጭት መስመር
ውጪ ምርት በሚያሰራጩና ብክነት በሚፈጥሩ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል፡፡
7.1.14. የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች አፈፃፀምና ሪፖርት በየወቅቱ ማዘጋጀት ለሚመለከታቸው አካላት ያሰራጫል፤
7.1.15. ለንግዱ ህብረተሰብና ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ይሰጣል፡፡
7.2. በክፍለ ከተማ የሚሠሩ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች
7.2.1. የክፍለ ከተማው የንግድ ኢንስፔክሽንና ሪጉላቶሪ ቡድን ዕቅድና የሚያስፈልገውን በጀት ያዘጋጃል፤
7.2.2. በቡድኑ የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ላይ ለወረዳዎች ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል፤
7.2.3. በትግበራ ማኑዋሉ ላይ ለወረዳዎች ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራና አስፈላጊ ቁሣቁሶችን ያሰራጫል፤
7.2.4. በወረዳ ደረጃ በቋሚ መዝገብ የሚመዘገበው ነጋዴ መረጃ በአግባቡ መያዙን ይከታተላል፤ መረጃውንም ያጠናቅራል፤
7.2.5. ለወረዳ ኦፊሰሮችና ለህብረተሰቡ በየወቅቱ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ ይሠራል፡፡
7.2.6. የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች በተባለላቸው ጊዜ፣ ጥራት መጠን መሠራታቸውንና ውጤታቸውን ይገመግማል፡፡
7.2.7. በክፍለ ከተማ ደረጃ የተለዩ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች የንግድ ምዝገባና ፈቃድ መረጃ ለወረዳዎች ለሥራ አመቺ አድርጐ ይሰጣል
፡፡
7.2.8. አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በመስክ ሥራ ላይ ወረዳዎችን ያግዛል፤
7.2.9. የህገወጥ ንግድ መንስዔዎች ላይ የዳሰሳ ጥናት ያደርጋል፡፤
7.2.10. በንግድ አዋጆችና በክፍለ ከተማው ውስጥ ስለሚታየው ህገ-ወጥነት ከነጋዴውና ከነዋሪው ጋር ይወያያል ግንዛቤ ይሰጣል፡፡
7.2.11. ወረዳዎች በህገ-ወጦች ላይ በሚወስዱት ዕርምጃ የሚቀርብ ቅሬታ አይቶ በአዋጅ መሠረት መሆኑን ያረጋግጣል፤
ለቅሬታውም መልስ ይሰጣል፡፡
7.2.12. በክፍለ ከተማው የሚሰራጩትን መሠረታዊ ሸቀጦች ስርጭት ይመዘግባል፤ መረጃውንም ይይዛል፤ ለሚመለከተውም
ያስተላልፋል፤
7.2.13. የመሰረታዊ ሸቀጦች ተደራሽነትን ለማረጋጥ የሚያስችል የኩፖን ስርዓት በችርቻሪ ነጋዴዎችና በሸማቾች መካከል
መፈጠሩንና መተግበሩን ያረጋግጣል፤
7.2.14. የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች አፈፃፀም ሪፖርት በየወቅቱ ያቀርባል፤
7.2.15. ከክፍለ ከተማው የንግዱ ህብረተሰብና ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ይሰጣል፡፡
7.2.16. የንግድና የመለኪያ መሳሪያዎች ደንቦችን ከወረዳዎች ጋር በመሆን ተግባራዊ መሆናቸው ያረጋግጣል
7.2.17. ድንገተኛ ጥቆማ ሲደርሰው ከወረዳዎች ጋር በመሆን አፋጣኝ እርምጃ ይወስዳል፤ ያስወስዳል፤
7.2.18. እያንዳንዱ ወረዳ የልኬት መሣሪያዎች እንዲኖረው ወይም ያለውን በኘሮግራም እንዲጠቀሙበት ያደርጋል፤
7.2.19. ህገወጦች ላይ የሚወሰደውን አስተዳደራዊ እርምጃዎችን አካሄድ በህጉ መሠረት መሆኑን ይከታተላል፤ ክስ እንዲመሰረት
ከወረዳዎች እንዲላኩ ያስተባብራል ፤መረጃ አደራጅቶ ክስ ይመሰርታል፡ ውሳኔዎችን ይከታተላል፡፡ ይግባኝ
በሚያስፈልጋቸው ላይ ይግባኝ እንዲጠየቅ ያደርጋል፡፡
7.2.20. በክፍለ ከተማ አስተዳደር ክልል ውስጥ ህገ-ወጥ ሥራ በተደጋጋሚ በሚሠሩ ነጋዴዎች በንግድ ፈቃዳቸው ላይ ሪከርድ
የሚሆን ደብዳቤ ይጽፋል፤
15
7.2.21. ዋስትና ያለባቸውን የንግድ ድርጅቶች ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ ሥራ ሂደት መረጃ በመውሰድ እንዲከታተሉት ለወረዳዎች
ሪፖርቱን ያደርጋል፤ መረጃ ይቀበላል፤ መረጃውንም መዝግቦ ይይዛል፤
7.2.22. መሠረታዊ ሸቀጥ የተመደበላቸው ድርጅቶች የተመደበውን ኮታ በተገቢው መንገድ ማሰራጨታቸውን ይከታተላል፤
7.2.23. የመሠረታዊ ሸቀጦች አቅርቦት በፍላጐት ላይ ተመስርቶ እየተፈጸመ መሆኑን መረጃ ይሰበሰባል፡፡
7.2.24. በህገወጦች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ ቡድን ሪፖርት መረጃ ይወስዳል፤
16
7.3.19. ህገ ወጥ በመሆኑ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድበት ስለተወሰነበት የንግድ ድርጅት መረጃ ለንግድ ምዝገባና ፈቃድ ቡድን
በጽሁፍ ያሳውቃል፡፡ ቡድኑም በፈቃዱ ላይ የተጠየቀውን እርምጃ ይወስዳል፤
7.3.20. በወረዳው ያልታደሱ የንግድ ስራ ፈቃድ መረጃ ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ ቡድን በመውሰድ እርምጃ ይወስዳል፤ ከቋሚ
መዝገቡም ላይ ያለውን መረጃ ወቅታዊነት በእርማት ያስተካክላል፤
7.3.21. አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከኃላፊው በሚሰጥ ፍቃድ ከሥራ ስዓት ውጭ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ በራሱ ወይም ከሌሎች ሴክተር
መ/ቤቶች ጋር በመሆን ያካሂዳል፤
7.3.22. ህገ ወጦችን ለክስ ለማቅረብ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ለክፍለ ከተማ አደራጅተው ይሰጣል፤
7.3.23. በጥፋቱ ምክንያት የተሰረዘበት የንግድ ፈቃዱ የተሰረዘበት ሰው በዚያ መስክ ለአንድ ዓመት የንግድ ሥራ ማቆሙን
ይቆጣጠራል፡፡
7.3.24. በህዝብ ማስታወቂያ ዋጋቸው የተወሰነ ሸቀጦች በተባለው ዋጋ መሸጣቸውን ያረጋግጣል፤
7.3.25. መሠረታዊ የሆኑ ሸቀጦች የተመደበላቸው ቸርቻሪ ድርጅቶች የተመደበውን ኮታ በተገቢው መንገድ በኩፖን ስርኣት
ለህብረተሰቡ ማሰራጨታቸውን ይከታተላል፤ ያረጋግጣል፤
8. የንግድ ኢንስፔክሽን ባለሙያ ስምሪት
የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች ነጋዴዉን ማስተማር፣ መደገፍ፣ ህገ-ወጦች ላይ ከአድርባይነት የፀዳ
እርምት በመዉሰድ ልማታዊ አስተሳሰብ እና አሰራር ማጎልበትን ማዕከል ያደረገ የንግድ ህግ ማስከበር ስራ ላይ
ትኩረት ያደርጋሉ፡፡
9.1. የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ስራዎች የንግድ ህግ የማስከበር ተግባር በወር፣ በሳምንትና በእለት ተመንዝሮ
በሚዘጋጅ ፕሮግራም ይመራል፣ ፕሮግራሞቹን በዳይሬክቶሬቱ/ቡድኑ አጸድቀዉ ወደ ተግባር ይገባሉ፡፡
9.2. ነጋዴዉ በክትትልና ቁጥጥር ወቅት ተላልፎ የተደረሰበትን የደንብ ጥሰት ሳያዛባ በቃለ ጉባኤ አስደግፎ
ሪፖርት ማቅረብና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እዉነታዉን ማእከል ያደረገ የምስክርነት ቃል በፍ/ቤት ተገኝቶ
ይሰጣል፣
9.3. በሃሰት ነጋዴዉን መወንጀል ወይም በሃሰት የምስክርነት ቃል መስጠት ተገቢ ያልሆነ ተግባር ነው፤
በዲስፕሊንም ያስጠይቃል፡፡
9.4. በማናቸውም ደረጃ የሚገኙ ማንኛውም የክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች በማንኛዉም ሰዓት ወደ ንግድ
መደብር ሲገቡ ማንነታቸዉን የሚገልፅ ባጅና ማንነታቸዉን ለነጋዴዉ በአግባቡ አስረድተዉ የድጋፍ፣
ክትትልና ቁጥጥር ስራቸዉን ያከናዉናሉ፡፡
9.5. የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ኦፊሰሮች በንግድ ቤት ተገኝተዉ ክትትልና ድጋፍ አካሂደዉ
ከመዉጣታቸዉ በፊት በንግድ ቤቱ የተመለከቷቸዉን መጥፎም ሆነ መልካም አሰራሮችን በቃለ-ጉባኤ
በማረጋገጥ ለነጋዴዉም ግልፅ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
9.6. በክትትልና ቁጥጥር የተያዙ ቃለ-ጉባኤዎች በየእለቱ ለዳይሬክቶሮቱ/ቡድኑ በማቅረብ መወሰድ ያለበት
እርምት በጋራ ዉሳኔ ማስተላለፍ እና በዚህ አግባብ እርምጃ ይወስዳሉ፣
9.7. ከዳይሬክተሩ/ቡድን መሪው ወይም በሌለበት ከጽ/ቤት ኃላፊ ጋር የጋራ ዉሳኔ ሳይተላለፍ ማንኛዉንም
አስተዳደራዊ ሆነ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ ተገቢ አይደለም፡፡
9.8. የሚወሰደዉ እርምጃ ለነጋዴዉ በጽሁፍ ይገለፃል፡፡ ለነጋዴዉ የሚሰጠዉ መግለጫ ጥፋቱን በመግለፅ
የሚያስረዳና የተላለፈዉን የህግ ድንጋጌ ያካተተ መሆን አለበት፡፡
9.9. ደንብ ተላልፎ የተገኘ ንግድ ድርጅት ላይ የተወሰደ እርምጃ እሽግ ሲነሳ የቡድን መሪው ወይም ጽ/ቤት
ኃላፊ ማወቅ ይኖርበታል፡፡ የቡድን መሪው ወይም የጽ/ቤት ኃላፊዉ ሳያዉቅ አስተዳደራዊ እርምጃ
መነሳት የለበትም፡፡
9.10. ተመሳሳይ የደንብ ጥሰት ፈፅመዉ የተገኙ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰደዉ አስተዳደራዊም ሆነ ህጋዊ እርምጃ
ተመሳሳይ መሆን አለበት፡፡
18
9.11. ነጋዴዎች የሚተላለፏቸዉ የህግ ጥሰቶች በየወቅቱ በነጋዴዉ ስም እና የንግድ ፋይል ሪከርድ ይመዘገባል፡፡
9.12. ማንኛዉንም ነጋዴ ማመናጨቅ፣ ማስፈራራት፣ መደለያ መጠየቅ፣ መቀበል ፈፅሞ የተከለከለ ነዉ፡፡
9.13. የደንብ ጥሰት ፈጽሞ በተገኘ ነጋዴ ላይ እንደጥፋቱ አይነት ተመጣጣኝ እና አስተማሪ እርምጃ
ይወስዳል፣ የደንብ ጥሰት ፈጽሞ የተገኘን ነጋዴ አይቶ ማለፍ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ህገ-
ወጥነትን ማስፋፋት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
9.14. አንድ የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ወይም የህጋዊ ስነ-ልክ ባለሙያ ለብቻው በንግድ ቤት ተገኝቶ
መቆጣጠር አይችልም፡፡
10. የውስጥ ኢስፔከሽን በሚከናወንበት ወቅት የሚከተሉት ቅድመ ሁኔታዎችን መከተል ይገባል፤
10.1. የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008፣ የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር
813/2006 እና የንግድ ሕግ አዋጅ በጥልቀት መረዳት ይገባል፤
10.2. የውስጥ ኢንስፔክሽን እቅድ መዘጋጀት ይኖርበታል፤
10.3. ለምርመራ የሚፈለገውን መዝገብ ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ ዳይሬክቶሬት/ቡድን መረከብ፤
10.4. ከላይ በዝርዝር የተቀመጡ የምዝገባና የፈቃድ አሰጣጥ ተግባራት በአዋጁና በአሰራር ማንዋሎች
መሠረት መሆኑን የኢንስፔክሽን ስራ ማከናወን፤
10.5. ምርመራው ከአበቃ በኋላ ከሚያስመረምረው አፊሰር በምርመራው ውጤት መሠረት መተማመኛ
መቀበልና አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን ለመረጃነት ፎቶ ኮፒ አደርጎ መያዝ፤
10.6. መርማሪው አፊሰር ምርመራውን ከአጠናቀቀ በኋላ የተረከባቸውን መዝገቦች ለአስመርማሪው ይመልሳል፤
10.7. ምርመራው ከተጠናቀቀ በኋላ በምርመራው ውጤት ላይ ተመርኩዞ የመውጫ ስብሰባ በማድረግ
ሊስተካከሉ በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ የሃሳብ ልውውጥ ይደረጋል /ከቢሮ/ጽ/ቤት ኃላፊው
ከአስመርማሪውና ከተመርማሪው የዳይሬቶሬት/ቡድን መሪዎችጋር/፤
10.8. የምርመራ ሪፖርቱን ለድህረ-ፍቃድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት/ቡድን ከአስተያየት ጋር ያቀርባል፤
19
11. የውጭ ኢንስፔክሽን
11.1. የንግድ ምዝገባ፤ የንግድ ፍቃድና እድሳት፤ የንግድ አሰራርና ሸማቾች ጥበቃ ዙሪያ የሚፈጸሙ
የኢንስፔክሽን ተግባራት
በቢሮው የሚሰጡ የንግድ ምዝገባ ፈቃድና አገልግሎቶች እንዲሁም የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ ህግች
በአግባቡ ስራ ላይ ስለመዋላቸው በንግድ ድርጅቶች /መደብሮች/ የኢንስፔክሽን ስራ በሚከናወንበት ወቅት
የሚታዩ ዋና ዋና ተግባሮች የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡
20
11.1.20. ተገቢ ያልሆኑ የንግድ ውድድር ተግባራት ስለመፈጸሙ፤
11.1.21. ስለንግድ እቃዎች የሚያመለክት መግለጫ ስለመለጠፉ፤
11.1.22. የንግድ እቃዎችን መደበቅና ያለአግባብ ስለማከማቸት፤
11.1.23. የመሰረታዊ ፍጆታ እቃዎች የአቅርቦትና የስርጭት አፈጻጸምን፤እና
11.1.24. በሌሎች ህገ-ወጥ የንግድ አሰራሮች ላይ በመደበኛም ሆነ በድንገተኛ የኢንስፔክሽን ሥራ ይከናወናል፡፡
12.1. የውጭ ኢንስፔክሽን ለማከናወን የምንከተላቸው የአሰራር ቅደም ተከተሎች
12.1.1.የኢንስፔክሽን ፕሮግራም ማዘጋጀት፤
12.1.2.ለኢንስፔክሽን ስራ የሚያሰፈልጉ ቅጻ ቅፆች (ፎርማቶች) ማዘጋጀት፤
12.1.3. የኢንስፔክሽን ሥራ ማካሄድ፤በኢንሥፔክሽን እንቅስቃሴ ላይ የተገኘውን መረጃ ማደራጀትና መተንተን፤
12.1.4.በዳይሬክቶሬቱ የሥልጣን ክልል ስር በሆኑት ጥፋቶች ላይ ተጠያቂ የሆኑት ግለሰቦች ወይም የንግድ ድርጅቶች
ለይቶ አስተማሪ የሆነ እርምጃ መውሰድና ክስ ለመመስረት የሚያስችሉ መረጃዎች ማደራጀት፤
12.1.5.ከዳይሬክቶሬቱ የሥልጣን ክልል ውጪ በሆኑ ጥፋቶች ላይ ተሠማርተው የተገኙ ጥፋት ፈጻሚዎች ተገቢውን
ቅጣት /ውሣኔ/ እንዲያገኙ ለቢሮው ወይም ጽ/ቤቱ ማስረጃዎችን ማቅረብና ውሳኔዎችን መከታተል፡፡
12.2. ሕገ-ወጥ ንግድ ሥራ ተፈጽሟል የሚያሰኙ ተግባራት፣
12.2.1. አዲስ የተሰጠ ወይም የታደስ ንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የሌለው፤
12.2.2. የፀና የንግድ ሥራ ፈቃድ ሳይዙ መነገድ ወይም በሌላ ክልል ወይም በፌዴራል የተሰጠን ፈቃድ ቅርንጫፍ
ሳያስመዘግቡ መነገድ፤
12.2.3. ሐሰተኛ መረጃ በመስጠት ፈቃድ ያገኘ ወይም ለሌላ ተግባር የፈፀመ/አገልግሎት ያገኘ፤
12.2.4.በበላይነት የተያዘን ገበያ አለአግባብ የመጠቀም ድርጊት ተፈጽሞ ሲገኝ፤
12.2.5. የንግድ ውድድርን የሚያግድ፤ የሚገድብ ወይም የሚያዛባ ዓላማ ወይም ውጤት ያለው ስምምነት ማድረግ፤
በሕብረት አቋም መያዝ ወይም በማህበር ውሳኔ ተላልፎ ሲገኝ፤
12.2.6.የንግድ እቃዎችንና አገልግሎቶቹን ዋጋ ዝርዝር በድርጅቱ ውስጥ የማይለጥፍ ከሆነ፤
12.2.7. የንግድ እቃዎችንና አገልግሎቶቹን በድርጅቱ ውስጥ በተለጠፈው የዋጋ ዝርዝር መሰረት የማይሸጥ ከሆነ፤
12.2.8. ለገዛው እቃ ደረሰኝ ማቅረብ የማይችል ለሸጠው እቃ ደረሰኝ የማይሰጥና ቀሪ የማይዝ ከሆነ፤
12.2.9. በሕዝብ ማስታወቂያ/በመመሪያ ሥርጭታቸውና የመሸጫ ዋጋቸው የተወሰኑ ሸቀጦች፤ የትርፍ ጣሪያቸው
የተወሰኑ የንግድ ዕቃዎችና አገልግሎቶችን ዋጋ አለማክበር፤
12.2.10. በአዋጅ ወይም በሌላ ምክንያት በተሰረዘ፤ በተመለሰ፤ በታገደ ንግድ ፈቃድ መነገድ፤
12.2.11. ፈቃዱ ከተሰጠበት ዓላማ ውጭ ሲገለገልበትና ተገቢ ያልሆነ ሥራ ሲሰራበት ከተገኘ ወይም ከተረጋገጠ፤
12.2.12. የንግድ ሥራ ፈቃድ በተሰጠበት የሥራ መስክ የተለያዩ ሥራዎችን በአንድ ቤት ውስጥ አጣምሮ በመስራቱ
ምክንያት በተጠቃሚው ህዝብ ጤንነትና ደህንነት ወይም በንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ ከሆነ፤
21
12.2.13. በተጠቃሚው ወይም በደንበኛው ላይ ጉዳት ማስከተል፣
12.2.14. የጥቅም ግጭት ሊፈጥሩ የሚችሉ የተለያዩ ሥራዎችን አጣምሮ መስራት፤
12.2.15. ደረጃውን ባልጠበቀ መለኪያ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ሲረጋገጥ፤
12.2.16. ከምርት ጋር ባዕድ ነገሮችን ደባለቆ /ቀላቅሎ መሸጡ ሲታወቅ፤
12.2.17. ሌሎች በንግድ ምዝገባ ፍቃድና በንግድ አሰራር በሸማቾች ጥበቃ አዋጆችአሰራሮች ላይ የተከለከሉ ጉዳዩች
ሕገወጥ ንግድ ሥራ የተፈጠመ መሆኑን ሲረጋገጥ፤፡
በነጻ ገበያ ስርዓት በሚከተሉ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት መንግስት የንግድ ስርዓቱን የሚያዛቡ ህገ-ወጥ
አሰራሮችን በመከላከል የነጋዴዉንና የሸማቹን ሚዛናዊ ጥቅም የማስጠበቅ ሚና አለዉ፡፡ በንግድ ሪፎርሙ
የንግድና የግብይት ስርዓታችን ቁልፍ ችግሮች ተብለዉ ከተለዩ እጥረቶች መካከል አንዱና ዋናዉ የመንግስት
ህግ የማስከበር አቅምና አሰራር ደካማ ሆኖ መገኘት ነዉ፡፡ በንግድ ህግ ማስከበር አሰራራችን ላይ የሚታየዉን
እጥረት በመፍታት መሰረታዊ ለዉጥ ለማምጣት በመረጃ ስርዓታችን፣ በንግዱና በሸማቹ ማህበረሰብ ዘንድ
የሚታየዉን የግንዛቤ እጥረትና የአመለካከት ችግሮችን በክትትል፣ ቁጥጥርና እርምት አወሳሰድ ላይ የሚታዩ
የክህሎት፣ የአመለካከትና የአሰራር እጥረቶችን ፈትሾ ለማስተካከል ግልፀኝነት ያለው ወጥ አሰራር መፍጠር
ይገባል፡፡
22
ለ. በየብሎኩ የሚገኘዉ ነጋዴ ማንነት፣ በአድራሻ፣ በንግድ ዘርፉ፣ በንግድ መስኩ፣ በንግድ ምዝገባና ንግድ
ፈቃዱ፣ በግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩ መዝግቦ ለድጋፍና ክትትል ስራዎቻችን ምቹ በሚሆን መንገድ
እንዲደራጅ ይደረጋል፡
ሐ. በእያንዳንዱ ብሎክ የሚገኘዉ ነጋዴ በዚህ አግባብ ከተለየ በኋላ ከንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ
ባለሙያዎች በቋሚነት ለድጋፍና ክትትል ስራዎች ባለቤት ይመደባል፡፡
መ. ከየብሎኩ በአመለካከታቸዉ የተለዩ ልማታዊነት ዝንባሌ ያላቸዉ ግንባር ቀደም ነጋዴዎችን እየፈጠሩ
መሄድ በምናካሂደዉ የፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ትግሉ ከቁጥጥር ሰራተኞች ጋር ሆኖ ድጋፍ እንዲሰጥ
መለየት፣ ማብቃትና ማሳተፍ አስፈላጊ ይሆናል፡፡
ሀ. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የንግድ ምዝገባ ቁጥር፣ አድራሻ፣ የንግድ ፈቃድ ቁጥር የአንድ ነጋዴ ልዩ
(Unique) መለያዎቹ ናቸዉ፡፡
ለ. በየብሎኩ ነጋዴዉን በእነዚህ መለያ ቁጥሮቹ ለይቶ ማወቅ ለነጋዴዉ ለምናደርጋቸዉ ድጋፎችና ህገ-
ወጥነትን ለመከላከል ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ትኩረት ሊሰጥበት የሚገባው
የመረጃ አያያዝ ስርዓት ሊዘረጋ ይገባል፡፡
23
መ. ተቆጣጣሪውም ይህን የነጋዴውን ልዩ መለያ ቁጥር ነጋዴው ባስመዘገበው አድራሻ ስለ ትክክለኛነቱ
ከመረጃ መረብ ውስጥ አመሳክሮ ማረጋገጥ፣ መረጃውን መያዝና ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡
ሀ. በንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ የሚገኝ ማንኛዉም ነጋዴ የንግድ ስራ ፈቃድ አዉጥቶ ስራ መጀመርና በንግድ
ፈቃዱ ላይ ባስመዘገበዉ መሰረት የንግድ ስራዉን ማከናወን አለበት፡፡
ለ. አንድ ነጋዴ በተለያዩ የንግድ ዘርፎችና የንግድ መስኮች ከአንድ በላይ የንግድ ፈቃድ ሊኖረዉ ይችላል፡፡
ሐ. የእያንዳንዱ የንግድ ፈቃድ ቁጥር ተመሳሳይ ላይሆን ይችላል፡፡
መ. በአንድ ወረዳ ዉስጥ በአንድ የንግድ ዘርፍ ከአንድ በላይ የንግድ ድርጅት ከፍቶ ለመስራት እድል ሊኖረዉ
ስለሚችል ቅርንጫፎቹን በግልጽ ለወረዳዉ የንግድ ጽ/ቤት አስመዝግቦና አሳዉቆ መነገድ
ይጠበቅበታል፡፡
ሠ. በተመሳሳይ የንግድ ዘርፍ በአንድ የንግድ ፈቃድ ከአንድ በላይ ቅርንጫፍ ያለዉ ነጋዴ በንግድ ምዝገባ
ሰርተፍኬት ጀርባ ላይ ቅርንጫፎቹን ያስመዘግባል ፡፡
ረ. የንግድ ምዝገባውና የንግድ ፍቃዱ ኮፒ ላይ በህጋዊ ማህተም አረጋግጦ በቅርንጫፍ የንግድ መደብሮቹ
ላይ መሰቀሉን ተቆጣጣሪው ተከታትሎ ማረጋገጥና የነጋዴዉን ትክክለኛና የተደራጀ መረጃ መያዝ
ይኖርበታል፡፡ለምሳሌ፡- ABC ኃ/የተ/የግል ተቋም በአዲስ አበባ ዉስጥ በተለያዩ ክ/ከተሞችና
ወረዳዎች በተመሳሳይ ዘርፍና መስክ ከአንድ በላይ ቅርንጫፎች ሊኖሩት ይችላል፡፡
ሰ. ተቋሙ ቅርንጫፎቹን ንግድ ፈቃድ ለሰጠዉ ክ/ከተማና ወረዳ አሳዉቆና ዝርዝሮቹን በንግድ ምዝገባ
ጀርባ ላይ አስመዝግቦ የንግድ ስራዉን መስራት ይችላል፡፡
ሸ. በሌላ መልኩ በአንድ የንግድ ዘርፍ በወጣ የንግድ ስራ ፈቃድ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ላይ ተሰማርቶ
መስራት አይቻልም፡፡
ቀ. ለእያንዳንዱ የንግድ ዘርፍ የተለያያ የንግድ ፈቃድ መዉጣት አለበት ማለት ነው፡፡
በ. የአስመጪነት የንግድ ፈቃድ ያለዉ አንድ ነጋዴ በአስመጪነት የንግድ ፈቃድ የኢንዱስትሪ ማምረት ስራ
ላይ መሰማራት አይችልም፡፡
ተ. ከዉጪ ያስመጣዉን ሸቀጥ በጅምላ ለማከፋፈል የጅምላ ንግድ ፍቃድ ማዉጣት ግን አይጠበቅበትም፡፡
ቸ. በመሆኑም የንግድ ተቆጣጣሪዉ ከንግድ ፈቃድ ጋር ተያይዞ አንድ ነጋዴ ስንት የንግድ ፈቃድ እንዳለዉ፣
ነጋዴዉ በንግድ ፍቃዱ ላይ ያስመዘገበዉ የንግድ ዘርፍና ነጋዴዉ እየሰራዉ የሚገኘዉ የንግድ ስራ
ተመሳሳይ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅበታል፡፡
24
ነ. የችርቻሮ የንግድ ፈቃድ ይዘዉ በጅምላ ስራ ላይ ጅምላ ፍቃድ ይዞ ችርቻሮ ንግድ ላይ ፤ የማምረት ስራ
ላይ ተሰማርቶ ችርቻሮ ንግድ ላይ መሳተፍ አይቻልም፡፡
ኘ. ነገር ግን የማምረት ንግድ ፍቃድ ያለው የጅምላ ፍቃድ ሳያስፈልገው በማምረቻው አለያም
ለማከፋፈል ባስመዘገበው ቅርንጫፍ አድራሻ በጅምላ ማከፋፈል ይችላል፡፡
ሀ. ነጋዴዉ ወደ ንግድ ስርዓት ዉስጥ ከመግባቱ በፊት ለንግድ ስራ የሚጠቀምበት ቤት የራሱ ከሆነ የባለ
ይዞታነት ካርታ፣ የኪራይ ከሆነ በሰነድ አረጋጋጭ የተረጋገጠ የኪራይ ውል ወይም ይህን ማቅረብ
ይኖርበታል፡፡
ለ. የነጋዴዉን አድራሻ የቤት ቁጥር በንግድ ምዝገባና ፈቃድ ሰርተፊኬት ላይ የሚገለጽ ሲሆን
ተቆጣጣሪው የነጋዴዉን አድራሻ በንግድ ፈቃዱ ላይ ከሰፈረዉ የንግድ አድራሻ ጋር በማመሳከር
ትክክኛነቱን ተከታትሎ ማረጋገጥ ይጠበቅበታል፡፡
ሐ. ነጋዴዉ ካስመዘገበዉና በንግድ ፈቃዱ ላይ ከሰፈረዉ አድራሻ ዉጪ ንግድ ማካሄድ የለበትም፡፡
መ. ያስመዘገበዉንና እየሰራ ያለበትን ቦታ መቀየር ሲፈልግ አዲሱን አድራሻ በቅድሚያ ማሳወቅና
በንግድ ፈቃዱ ላይ የአድራሻ ማስተካከያ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
ሠ. ተቆጣጣሪዉ ይህንን መረጃ ትክክለኛነት ሊያረጋግጥ የሚችለዉ ነጋዴዉ በንግድ መደብሩ በግልጽ
በሚታይ ቦታ ካኖረዉ የንግድ ፈቃዱ ላይ ነው
ረ. ንግድ የሚካሄድበትና በንግድ ፈቃዱ ላይ ያለዉ አድራሻ የማይገናኝ ከሆነ በንግድ ቤቱ ዉስጥ የንግድ
ፈቃድ እንደወጣበት አድርጎ መዉሰድ አይቻልም፡፡
የአንድ ነጋዴ ህጋዊነት መገለጫዎች መካከል በህጋዊ ደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ግብይት ማካሄዱ ነዉ፡፡
በንግድ ውድድርና የሸማቾች መብት ጥበቃ አዋጅ አንቀጽ 17 መሰረት ማንኛውም ነጋዴ ስለሸጠው እቃ
ወይም አገልግሎት ለሸማቹ ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ እንዳለበት ያስቀምጣል፡፡ በግልጽና በህጋዊ ደረሰኝ
ላይ የተመሰረተ ግብይት ማካሄድ የነጋዴዉን የመንግስትንና የሸማቹን ሚዛናዊ ጥቅምና ደህንነት
ለማስጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለዉ፡፡ በመሆኑም በአዋጁ መሰረት ሸማቹን መብት ማስከበር እንዲቻል
ማንኛውም ነጋዴ ለሸማቾች ስለሚሸጠው እቃ ወይም አገልግሎት ህጋዊ ደረሰኝ የመስጠት ግዴታውን
እንዲያከብር ጠንካራ የቁጥጥር ተግባር ማካሄድ ይጠበቅብናል፡፡
25
14.1. ህጋዊ የደረሰኝ ግብይት አሰራር፡-
ሀ. በነጋዴና በሸማቹ መካከል የሚካሄድ ግብይት በገቢዎች ሚኒስቴር ወይም በአዲስ አበባ ገቢዎች ባለስልጣን
ወይም በጉምሩክ ኮሚሽን እዉቅና ባለዉ ደረሰኝ ላይ መሰረት መፈፀም አለበት፣
ለ. የነጋዴዉ ደረሰኝ፡- የነጋዴዉን ስም፣የንግድ ስም፣ አድራሻ፣ ልዩ ቦታ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የያዘ
መሆን አለበት፡፡
ሐ› በመሆኑም ማንኛውም ሸማች በነጋዴ የንግድ መደብር የተለጠፉ የጥቆማ ስልኮች በመጠቀም
መብቱን እንዲያስከብርና በጉዳዩ ላይ ነጋዴዉን ግንዛቤ ማስጨበጥና ጥቅሙን በማስጠበቅ ህገ-ወጥነትን
እንዲከላከል ማድረግ ይገባል፡፡
መ. ቸርቻሪ ነጋዴዎች ሽያጭ ማካሄድ የሚችሉት በቀጥታ ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ ነዉ፡፡ በችርቻሮ
የንግድ ስራ ፍቃድ ጅምላ ንግድ መነገድ አይቻልም፡፡
ሠ. በመሆኑም ማንኛዉም ለሌላ ነጋዴ ሽያጭ የሚያካሂድ ነጋዴ የጅምላ ንግድ ፈቃድ እንዲያወጣና
በደረሰኝ ላይ የተመሰረተ ሽያጭ እንዲያከናዉን ማድረግ ይገባል፡፡
ረ. አምራች፣ አስመጪና ጅምላ ነጋዴ በተዋረድ ለሚገኘዉ ነጋዴ ሽያጭ ሲያካሄድ ህጋዊ የንግድ ፈቃድና
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት ላለዉ ነጋዴ መሆን አለበት፡፡ ሽያጭ የተደረገላቸዉ ነጋዴዎችን
ስም፣ የንግድ ምዝገባ ቁጥር፣ የንግድ ፈቃድ ቁጥርና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እየመዘገበ ሽያጭ
ማካሄድ አለበት፡፡
ሸ. ማንኛውም ነጋዴ ወይም የንግድ ድርጅት ስለሚሸጠው እቃ ወይም አገልግሎት ደረሰኝ እንዲያቀርብ
በተጠየቀ ጊዜ የማቅርብና የማስረዳት ኃላፊነት አለበት፡፡
26
ሰ. ቸርቻሪ ነጋዴዎች ለህብረተሰቡ ለመቸርቸር የገዙትን ሸቀጥ ከህጋዊ ነጋዴ/ምንጭ ስለመግዛታቸዉና
ከህጋዊ ነጋዴ ግዥ መፈጸማቸዉን ደረሰኝ እንዲያቀርቡ በማድረግ ትክክለኛነቱን ማረጋገጥ፣
ሸ. የግብርና ምርቶችን ከአርሶ አደር በቀጥታ በመግዛት ለሽያጭ የሚያቀርብ ነጋዴ ከአርሶ አደሩ ደረሰኝ
የማያገኝበት ሁኔታ ካለ የመግዣ ደረሰኝ (payment vouchure) በመቁረጥ ግዥ መፈጸም ይገባዋል፡፡
ቀ. ከላይ በተቀመጠው አሰራር መሰረት ወደ ደረሰኝ ግብይት ያልገቡ ነጋዴዎችን/ድርጅቶችን ለ 7 ቀናት
ድርጅቱ እንዲታሸግ ማድረግና በዚህ ያልታረሙትን ግድፈታቸውን እስከሚያርሙ የንግድ ፈቃዳቸዉ
መታገድ አለበት፤
በ. ለነጋዴ ደረሰኝ ለመስጠት ፈቃደኛ የማይሆን ወይም የተጭበረበረ ደረሰኝ ለነጋዴ የሚሰጥ አምራች፣
አስመጪ ወይም ጅምላ ነጋዴ ድርጅቱ 15 ቀን ታሽጎ የንግድ ስራ ፍቃዱ ይታገዳል፤ መረጃ ተጣርቶም
ክስ እንዲመሰረትበት ይደረጋል፡፡ መረጃዉ ለአ/አበባ ገቢዎች ባለስልጣን እንዲደርስ ማድረግ ይገባል፡፡
15. ለንግዱ፣ ለሸማቹ ማህበረሰብ ስልጠና መስጠትና ግንዛቤ ማስጨበጥ
የነጻ ገበያ ስርዓትን እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ መርህ ስንከተል የግሉ ዘርፍ ለሃገሪቷ እድገት የማይተካ ሚና
ያለዉ መሆኑን በመገንዘብ ሲሆን ዘርፉ በልማታዊ አስተሳሰብ ዉስጥ ዘመናዊ አሰራርን ተከትሎ በውድድር
ላይ ተመስርቶ እንዲመራና በዚህ ማዕቀፍ ዉስጥ እንዲያድግ ማድረግ ይገባል፡፡የንግድ ሪፎርሙን ማዕከል
አድርገን ስንቀሳቀስ በነጻ ገበያ ስርዓት ዉስጥ ህጋዊ ሆኖ መስራት ያለዉ ሃገራዊ ፋይዳ ዙሪያ ለግብይት
ስርዓቱ ተዋናይ አካላት በቂ ግንዛቤ መፍጠርና የአመለካከት ቀረጻ ስራ ላይ ርብርብ ማድረግ ይገባል፡፡
የንግድ ኢንስፔክሽንና ህግ የማስከበር ስራዎች ጎን ለጎን በንግድ ስርዓቱ ዉስጥ ያሉትን ችግሮች
በመሰረታዊነት ለመፍታት በንግዱ ማህበረሰብ ዘንድ በሚታዩ የአመለካከትና የክህሎት ግንባታ ስራዎች
ላይ ሰፊ ጊዜ ተወስዶ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ ነዉ፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫና የስልጠና ስራዎቻችን በንግዱ ማህበረሰብ በነፃ ገበያ ስርዓቱ ዉስጥ ሊከተለዉ
በሚገባ ህጋዊ የንግድ አሰራር በዚህ ሂደት ዉስጥ በነጋዴዎች መካከል በሚፈጠር ፍትሃዊ ያልሆነ የንግድ
አሰራርና ተጽእኖ መከላከል በሚቻልበት አግባብየሸማቹ ማህበረሰብ በነጻ ገበያ ስርዓቱ ደህንነቱንና
ሚዛናዊ ጥቅሙን ሊያስጠብቅ በሚችልበት አግባብ ላይ ያተኮረ ስልጠናና ግንዛቤ ሊፈጠር በሚችልበት
አግባብ ላይ ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነዉ፡፡
27
ሠ. የመድረኩ ተሳታፊ አካላት ማንነት(ስብስብ)፣
ረ. መድረኩ የሚካሄድበት እለትና ቦታ፣
ሰ. መድረኩን የሚመሩና የሚያወያዩ ኃላፊዎች/ፈፃሚዎች፣
ሸ. ለመድረኩ የሚያስፈልግ ወጪ፣
ቀ. መድረኩ የሚመራበት የድርጊት መርሃ ግብር በእቅዱ ዉስጥ በዝርዝር እንዲካተት ይደረጋል፡፡
15.2. የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ዝግጅት፣
ሀ. የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ከዉይይት መድረኩ በፊት አስቀድሞ ይዘጋጃል፣
ለ. የሚዘጋጀዉ ሰነድ መነሻ የንግድ ህግና አዋጆች፣የንግድ ሪፎርም ሰነዶች፣ወቅታዊ
ጉዳዮች፣እንደየአካባቢዉ የሚታዩ የንግድ ስርዓቱ እጥረቶች፣የጥናት ሰነዶች፣ዘመናዊ የግብይት አሰራር
ወዘተ ማእከል ያደረገ ሊሆን ይችላል፣
ሐ. የተዘጋጀዉን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ ይዘትና አጠቃለይ ሁኔታ መገምገምና ለመድረኩ የሚመጥን
መሆኑን ማረጋገጥ፣
መ. የመወያያ ሰነዱን ፍሬ ነገሮች ዘርዝሮ በብሮሸር መልኩ ማዘጋጀትና በተጨማሪነት ለተወያዩ ማደል፣
28
በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ላይ የክልል ንግድ ቢሮዎች አዲስ አበባና ድሬደዋ መስተዳድሮችን ጨምሮ
በየክልላቸዉ የንግድ ፈቃድ የሚሰጥባቸዉና ፈቃድ የተሰጣቸዉ የንግድ ድርጅቶች በንግድ ህጉና አዋጆች
መሰረት በህጋዊ መስመር ጤናማ የንግድ እንቅስቃሴ እያካሄዱ መሆኑን ተከታትለዉ ስርዓት እንዲያስጠብቁ
ስልጣን ይሰጣቸዋል፡፡ በመሆኑም በከተማ አስተዳደሩ የሚካሄዱ የንግድ እንቅስቃሴዎችን መከታተልና ስርዓት
የማስያዝ እንቅስቃሴዉን በሁሉም ክ/ከተሞችና ወረዳዎች ወጥ ማድረግ በጥፋተኞች ላይ የሚወሰዱ
እርምጃዎች ከአድሎአዊነትና ከሌሎች ኢፍትሃዊ ከሆኑ ድርጊቶች በፀዳ መልኩ መተግበር አለበት፡፡
16.1. ከንግድ ምዝገባና ፈቃድ ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ተገቢ ያልሆኑ የንግድ አሰራሮችን መከላከልና ስርዓት
ማስያዝ፤
16.1.1. የንግድ ምዝገባ፣
በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 980/2008 ነጋዴዉ በንግድ መዝገብ መመዝገብ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡
በንግድ ምዝገባ አሰራር ነጋዴዉ የተረጋገጠ የንግድ አድራሻ እና በጣት አሻራ የተረጋገጠ የግብር ከፋይነት መለያ
ቁጥር ይዞ በንግድ መዝገብ እንዲመዘገብ ይደረጋል፡፡ የነጋዴ አድራሻ፣በጣት አሻራ የተረጋገጠ የግብር ከፋይ
መለያ ቁጥር፣የንግድ ምዝገባ ቁጥር የአንድ ነጋዴ መለያዎች ናቸዉ፡፡አንድ ነጋዴ አንድ የግብር ከፋይ መለያ
ቁጥርና አንድ የንግድ ምዝገባ ቁጥር ብቻ ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም የክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ ከንግድ ምዝገባ
ጋር በተያያዘ ማረጋገጥ የሚገባዉ፤-
ሀ. ነጋዴዉ በጣት አሻራ የተረጋገጠ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለዉ መሆኑን፣
ለ. ነጋዴዉ የንግድ ምዝገባ ማካሄዱንና ለዚህም ሰርተፊኬት ያለዉ መሆኑን፣
መ. በምዝገባ ሰርተፍኬቱ ላይ የተጠቀሰው አድራሻ ከንግድ መደብሩ አድራሻ ጋር ተመሳሳይ መሆኑን
ማረጋገጥ ቅርንጫፍም ከሆነ በኮፒው ላይ ማህተም ከመዝጋቢው አካል የተደረገበትን ማረጋገጥ፤
ማንኛዉም ነጋዴ የንግድ ፈቃድ ሳያወጣ የንግድ ስራ መስራት እንደማይችል በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ
ዉስጥ በግልጽ ተደንግጓል፡፡አንድ ነጋዴ የንግድ ስራ ፈቃድ ሲያወጣ በግብር ስርዓቱ ዉስጥ ገብቶ የንግድ ምዝገባ
ማካሄዱን ለሚሰራዉ የንግድ ስራ ብቃት ማረጋገጫ ከሚመለከተዉ አካል አቅርቦ የንግድ ፈቃድ ያወጣል፡፡አንድ
ነጋዴ በተለያዩ ዘርፎች የተለያዩ የንግድ ፈቃድ ሊያወጣ ይችላል፡፡በተመሳሳይ መልኩ በተመሳሳይ መስክ
በተለያዩ ቦታዎች ቅርንጫፍ ከፍቶ ሊሰራ ይችላል፡፡ነጋዴዉ የንግድ ስራ ፈቃዱን በበጀት ዓመቱ እስከ ታህሳስ
ወር መጨረሻ ድረስ ማደስ ይኖርበታል፡፡ ከንግድ ፈቃድ አንጻር የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ ማረጋገጥ
የሚገባዉ፡-
ሀ. ነጋዴዉ ለሚሰራዉ የንግድ ስራ የንግድ ፈቃድ ያለዉ መሆኑን፣
ለ. የንግድ ስራ ፈቃዱ የተሰጠበት ወይም የታደሰበት የበጀት ዓመት ካበቃ በኋላ ባሉት ስድስት ወራት
ጊዜ ዉስጥ ማሳደሱን፣
29
ሐ. ንግድ ፈቃድ የወጣበትና ንግድ ስራ የሚካሄድበት ቤት ተመሳሳይ መሆኑን ከንግድ ፈቃዱና
ከአድራሻዉ ማረጋገጥ፣
መ. በተመሳሳይ መስክ የተለያየ ቅርንጫፍ ከፍቶ የሚነግድ ነጋዴ አድራሻዎቹን አሳዉቆ በንግድ
ምዝገባ ሰርተፊኬት ጀርባ ላይ አስመዝግቦ ማረጋገጫ መያዙን፣
ሠ. በንግድ ፈቃድ ላይ ባስመዘገበዉ ዘርፍ ብቻ ንግድ እያካሄደ መሆኑን ተከታትሎ ማረጋገጥ አለበት፡፡
ለምሳሌ፡-የችርቻሮ የንግድ ፈቃድ ይዞ በጅምላ የማከፋፈል ስራ መስራት፣የአገልግሎት መስጠት
የንግድ ፈቃድ ይዞ የማምረት ወይም ሌላ ከዘርፉ ጋር የማይመሳሰል የንግድ ስራ መስራት
ስለማይቻል የንግድ ተቆጣጣሪዉ ይህ አለመሆኑን ተከታትሎ ማስተካከያ ማድረግ
ይጠበቅበታል፡፡
ረ. ኦሪጅናል የንግድ ፈቃዱን መደብሩ ውስጥ በሚታይ ቦታ መስቀል ወይም በአንድ የንግድ መስክ
ቅርንጫፍ ያለው ነጋዴ በንግድ ፈቃዱ ጀርባ ላይ የጽ/ቤቱን ማህተም በማስደረግ በቅርንጫፉ
ንግድ መደብሩ ውስጥ መስቀል አለበት፡፡
16.1.3. ህጋዊ አሰራር ተላልፈዋል የሚያሰኙ ተግባራት እና እርምጃ አወሳሰዳችን
ማንኛውም ሰው በአዋጅ ቁጥር 980/2008 መሰረት
ሀ. የፀና የንግድ ስራ ፈቃድ ሳይኖረው በንግድ ስራ ተሰማርቶ ከተገኘ፣
ለ. ሀሰተኛ መረጃ በማቅረብ በንግድ ምዝገባ የተመዘገበ ወይም የንግድ ስሙን ያስመዘገበ ወይም
የንግድ ፍቃድ የምስክር ወረቀት ያወጣ ወይም የንግድ ምዝገባውን ወይም የንግድ ፍቃዱን
የምስክር ወረቀት ያሳደሰ እንደሆነ፣
ሐ. የሕጉን፣አዋጅን ወይም የደንቡን ድንጋጌዎች ወይም ሚኒስትሩ የሚያወጣውን የህዝብ
ማስታወቂያ ተላልፎ የተገኘ እንደሆነ
16.2. እርምጃ አወሳሰድ በተመለከተ
የእሳት አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ማንኛውም ነገር በማስወገድ የአሌክትሪክ ሶኬቶችን እንዲነቅሉ፣
የሚበላሹ ነገሮችን፣መገልገያ ሰነዶችን የመሳሰሉትን እንዲያወጡ በማድረግ የንግድ መደብሩ ይታሸጋል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 980/2008 መሰረት ቢሮው ወይም ጽ/ቤቱ የሚወስደው አስተዳደራዊ እርምጃ እንደተጠበቀ
ሆኖ ጉዳዩ ለፖሊስ ጣቢያ ቀርቦና ምርመራው ተጣርቶ ለአቃቤ ህግ እንዲተላለፍ በማድረግ በወንጀል ክስ
ተመስርቶ በፍ/ቤት ሲረጋገጥ ቅጣቱ የሚፈፀም ይሆናል፡፡ በፍርድ ቤት ክስ የተመሰረተበት እና እሸጋ
የተፈፀመበት ነጋዴ ወደህጋዊነት ሲመለስ የንግድ ድርጅቱ ይከፈታል ህገ ወጥ እስከነበረበት ጊዜ ባለው
የተመሰረተው ክስ ግን ይቀጥላል፡፡
ከመታሸጉ በፊት-፡
30
ሀ.በድርጅቱ ውስጥ የተገኘውን ንብረት ተቆጣጣሪዎች በቃለ-ጉባኤ በመመዝገብ የድርጅቱን ባለቤት
ወይም ተወካይ በማስፈረም መያዝና ንብረቱ እንዳይወጣ ወይም እንዳይሸሽ በፖሊስ አማካኝነት
ጥበቃ እንዲደረግለት በደብዳቤ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
ለ. የንግድ ምዝገባና ፍቃድ ሳይኖረው ሲነግድ የተደረሰበትና የንግድ ድርጅቱ የታሸገበት ነጋዴ የንግድ
ድርጅቱ በታሸገበት ዕለት መረጃዎች ተደራጅተው ቢበዛ በሁለት ቀናት ውስጥ ክስ እንዲመሰረት
ለክፍለ ከተማ ክስ ምርመራ መላክ አለበት፡፡
ሐ. ክፍለ ከተማ የደረሱትን መረጃዎች በ 3 ቀናት ውስጥ ለፖሊስ ክስ እንዲመሰረት የክስ ማመልከቻ
እና ምስክሮቹን በመያዝ ቃል እንዲሰጡ ያደርጋል፡፡
መ. ህገ ወጥ ሆነው አስተዳደራዊ እርምጃ የተወሰደባቸው የንግድ ድርጅቶች ላይ ክስ ሳይመሰርት
ያቆየው ባለሙያ ተጠያቂ ይሆናል፡፡
16.3. ከጥር 1 እስከ ሰኔ 30 ባልተደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ ሲነግድ የተገኘ ነጋዴ በተመለከተ
የንግድ ስራ ፍቃድ ከጥር 1 እስከ ሰኔ 30 ባለው ጊዜ ከፍቃድ ማሳደሻ በተጨማሪ ፈቃድ ማሳደሱ ለዘገየበት
ለጥር ወር ብር 2500/ሁለት ሺህ አምስት መቶ/ እና ለሚቀጥለው ለእያንዳንዱ ወር ብር 1500/አንድ ሺህ
አምስት መቶ/ ቅጣት በመክፈል ፍቃዱ ይታደሳል፡፡ በዚሁ መሰረት የንግድ ስራ ፈቃዱን ያላሳደሰ ማለትም
የንግድ ስራ ፍቃዱ የተሰጠበት ወይም የታደሰበት የበጀት አመት ካበቃ ከጥር 1 በኋላ ባልታደሰ የንግድ ስራ
ፈቃድ ሲነግድ በክትትልና ቁጥጥር ባለሙያዎች የተደረሰበት ማንኛዉም ሰዉ
ሀ. የ 24 ሰዓት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰዉ በማድረግ የንግድ ድርጅቱን ለእሸጋ ዝግጁ
እንዲያደርግ ይደረጋል፡፡
ለ. ነጋዴውም ፈርሞ እንዲቀበል ይደረጋል ፍቃደኛ ካልሆነ በንግድ መደብሩ በር ላይ ይለጠፋል፡፡
ሐ. የ 24 ሰዓት የማስጠንቀቂያ ጊዜው እንዳበቃ በ 12 ሰዓት ጊዜ ዉስጥ የንግድ ድርጅቱ ይታሸጋል፣
መ. የፀና ንግድ ስራ ፈቃድ ሳይኖረው በንግድ ስራ ላይ ተሰማርቶ በመገኘቱ መረጃው ተደራጅቶ በወንጀል
ክስ ተመስርቶበት በአዋጁ 980/2008 መሰረት እንዲቀጣ ይደረጋል፡፡
16.4. ከሰኔ 30 በኋላ ያልታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ በአዋጁ መሰረት የተሰረዘ ስለሆነ
ሀ. ለነጋዴዉ የ 24 ሰዓት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰዉ ይደረጋል፣
ለ. ነጋዴውም ፈርሞ እንዲቀበል ይደረጋል ፍቃደኛ ካልሆነ በንግድ መደብሩ በር ላይ ይለጠፋል፡፡
ሐ. 24 ሰዓት እንደሞላ በ 12 ሰዓት ዉስጥ የንግድ ድርጅቱ ይታሸጋል፣
መ. መረጃ ተደራጅቶ ክስ ይመሰረታል፣
ሠ. በፍ/ቤት ዉሳኔ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል፣
31
ረ. ፈቃዱን በወቅቱ ስላለማደሱ ያቀረበው ምክንያት በቢሮው፣ በፅ/ቤቱ ኃላፊ ተቀባይነት ካገኘ በቅጣት
ሊከፍል የሚገባውን ገንዘብ 10 ሺህ ብር ከፍሎ አዲስ ንግድ ፈቃድ አውጥቶ እንደመጣ የንግድ
መደብሩ ይከፈትለታል፡፡ የተመሰረተው ክስ ግን ቀጣይነት ይኖረዋል፡፡
16.5. ካስመዘገበዉ የንግድ ዘርፍ ዉጪ ሲነግድ/ሲያመርት/አገልግሎ ሲሰጥ የተደረሰበት ነጋዴ፤
ሀ. ከተሰጠው ፍቃድ ውጪ መስራቱ ተገልጾለት በ 30 ቀናት ውስጥ ዘርፉን እንዲያስተካክል የጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፣
ለ. በ 30 ቀናት ውስጥ ማስተካከያዉን አድርጎ ሪፖርት ማድረጉን በመስክ ክትትል ጭምር ማረጋገጥ፣
ሐ. በተሰጠው 30 ቀናት ውስጥ ማስተካያ ያላደረገ ነጋዴ በቀጥታ የንግድ ድርጅቱ ለ 15 ቀን እንዲታሸግ
ይደረጋል፣
ሠ. መረጃ ተደራጅቶ ክስ ይመሰረታል፣
ረ. በፍ/ቤት ዉሳኔ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል፣
ሠ. ዘርፉን አስተካክሎ ሲቀርብ የ 15 ቀን እሸጋ ጊዜ ሲያበቃ እሽጉ እንዲነሳ ይደረጋል፣
16.6. ኦሪጅናል የንግድ ፈቃዱን በንግድ መደብሩ በሚታይ ቦታ ያልሰቀለ ነጋዴ፣
ሀ. የንግድ ፈቃዱን እንዲሰቅል የሚበላሽ ምርት ወይም አገልግሎት የ 24 ሰዓት የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
በመስጠት የንግድ ድርጅቱ ለ 7/ሰባት/ ቀናት ታሽጎ ይቆያል፣
ለ. ከእሸጋዉ በኋላ ያልታረመ ወይም ተመሳሳይ ጥፋት ላይ ተሰማርቶ ከተገኘ የንግድ ስራ ፍቃዱ ለ 1
ወር ታግዶ በወንጀል ክስ ይመሰረትበታል፡፡
16.7. የዋጋ ዝርዝር በንግድ መደብሩ በሚታይ ቦታ ያልሰቀለ/ያልለጠፈ/ ወይም በተለጠፈው የዋጋ
ዝርዝር መሠረት ሽያጭ የማያካሂድ ነጋዴ
32
ለ. ማስጠንቀቂያውን ነጋዴው ፈርሞ እንዲቀበል ይደረጋል፡፡ ፍቃደኛ ካልሆነ በንግድ መደብሩ በር ላይ
ይለጠፋል፡፡
ሐ. በማስጠንቀቂያዉ ያላስተካከለ የሚበላሽ ምርት ወይም አገልግሎት የሚኖር ከሆነ የ 24 ሰዓት
ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶት የንግድ ድርጅቱ ለ 15 ቀናት እንዲታሸግ ይደረጋል፣
መ. የአድራሻ ለዉጥ ማስተካከያ አድርጎ ሪፖርት ካደረገ የእሸጋ ጊዜው በተጠናቀቀ በ 12 ሰዓት ዉስጥ
እሸጋዉ ይነሳል፣
17. የህብረተሰቡን ጤንነት፣ደህንነት፣ ባህልና ፀጥታ የሚያውኩ ህገ-ወጥ የንግድ ተግባር ስለመከላከል፣
ቢሮዉ የንግድ ፍቃድ በሚሰጥባቸዉ የንግድ ዘርፎችና መስኮች የንግድ ስራ ፈቃድ አዉጥቶ የሚሰራ
ማንኛዉም ነጋዴ የህብረተሰቡን ጤንነትና የአካባቢ ደህንነቱን ጠብቆ መስራት ይጠበቅበታል፡፡ በሌላ መልኩ
ቢሮዉ የንግድ ስራ ፈቃድ የማይሰጥባቸዉ የህብረተሰቡን ባህልና ኃይማኖት የሚጻረሩ፤ መጤ ባህሎችን እንደ
ሺሻና ጫት የማስቃም አገልግሎቶች ንግድ ማካሄድ አይቻልም፡፡ የንግድ ተቆጣጣሪ ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ
ሴክተር መስሪያ ቤቶች ፖሊስ፣ደንብ ማስከበር አገልግሎት ት/ቤት፣ ጤና ቢሮ፣ አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን …
ወዘተ ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር እነዚህን ህገ-ወጥ ተግባራት መከላከል ይጠበቅበታል፡፡
16.1. የህብረተሰቡን ደህንነትና ጤንነት የሚጎዱ፣ የአካባቢ ብክለት የሚያስከትሉ የንግድ ተቋማትን ተከታትሎ
ህግ የማስከበር አሰራር፣
ሀ. ከማእከል እስከ ወረዳ ከላይ ከተጠቀሱና ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ ሴክተር መ/ቤቶች ጋር
ቅንጅታዊ አሰራር መፍጠር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረም፡፡
ለ. የህብረተሰቡን ደህንነት እና ጤንነት ይጎዳሉ በሚል ህብረተሰቡ ካቀረበዉ ቅሬታ አንጻር ጉዳዩ
ለሚመለከታቸዉ ተቋማት በማሳወቅ ቅሬታ የቀረበባቸዉን ተቋማት አሰራር አጣርተዉ 30 ቀናት
ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ በጽሁፍ እንዲያሳዉቁ ማድረግ፤
ሐ. ቅሬታ በቀረበበት የንግድ ተቋም ላይ ጉዳዩ የሚመለከተዉ ተቋም ያቀረበዉ የፅሁፍ ሪፖርት
የህብረተሰቡን ጤንነትና ደህንነት የሚያዉክ መሆኑ ከተረጋገጠ ቅሬታ የቀረበበት ተቋም ግድፈቶቹ
33
ተገልጸዉለት በ 15 ቀናት ዉስጥ ግድፈቶቹን አርሞ ብቃት ከሚያረጋግጠዉ ተቋም ማረጋገጫ
እንዲያመጣ በፅሁፍ ተገልፆለት የንግድ ፍቃዱ እንዲታገድ ተደርጎ ድርጅቱ ይታሸጋል፡፡
መ. ቅሬታ የቀረበበት ተቋም የንግድ አድራሻውን የሚያስቀይር እንደሆነ ከብቃት አረጋጋጭ ተቋም
ማረጋገጫ ከቀረበ በ 30 ቀናት ዉስጥ የአድራሻ ለዉጥ አድርጎ እንዲሰራ ተገልፆለት ማስተካከያ
እስኪያደርግ ድረስ የንግድ ስራ ድርጅቱ እንዲታሸግ በማድረግ ፍቃዱ ይታገዳል፡፡
በምንከተለዉ የነፃ ገበያ ስርዓት በጥራት ላይ የተመሰረተ ዉድድር ለኢኮኖሚ እድገቱ መሰረታዊ የገበይት
ስትራቴጂ ነዉ፡፡ በተለያየ የኢንዱስትሪ እድገት ደረጃ የሚመረቱ የሃገር ቤት ምርቶች ከዉጪ ወደ ሃገር ቤት
ከሚገቡ ምርቶች እንዲሁም ወደ ሌሎች ሃገሮችም ኤክስፖርት ተደርጎ ተወዳዳሪና ተቀባይነት ሊያገኝ
የሚችለዉ በጥራትና በዋጋ ተወዳዳሪ መሆን ሲችል ብቻ ነዉ፡፡ በሌላ መልኩ ሸማቹ ማህበረሰብ ጥራት ያለዉ
ምርት የማግኘት መብት አለዉ፡፡ ይሁንና በከተማችን ከምርት ጥራት ጋር ተያይዞ በንግዱ ማህበረሰብ ዘንድ
የሚታየዉ አስተሳሰብ በጣም የተዛባ ነዉ፡፡ ጥራትና ደረጃቸዉን ያልጠበቁ ምርቶች በስፋት ተመርተዉ ወደ
ገበያ ሲገቡ ይታያል፡፡ ከባዕድ ነገሮች ጋር የተደባለቀ ምርት፣ የአገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸዉና የተበላሹ
የኢንዱስትሪ ምርቶች፣ በኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ የተቀመጡ አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃዎችን
የማያሟሉ ምርቶችን አምርቶ ወደ ገበያ ማቅረብ በአንዳንድ አምራች ኢንዱስትሪና የንግድ ማህበረሰብ ዘንድ
ከሚታዩ ብልሹ አሰራሮች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ የሸማቹን ማህበረሰብ ጤንነት፣ ደህንነትና የሀገር
ኢኮኖሚን የሚጎዱ ድርጊቶች ናቸዉ፡፡ በመሆኑም በንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006
ከምርት ጥራት መጓደል ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ ግድፈቶች ለመከላከል የሚያስችል ድንጋጌዎች ተመላክተዋል፡፡
34
18.1. ከምርት ጥራት መጓደል ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥነትን የምንከላከልበት አግባብ፣
ሀ. በኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና የጥራት ጉድለት ሪፖርት የቀረበበት ነጋዴ የንግድ ፍቃዱ ታግዶ ጉድለቱን
አስተካክሎ ማረጋገጫ ከተቋሙ እንዲያቀርብ ይደረጋል፡፡ ማረጋገጫዉ እንደቀረበ የንግድ ፈቃድ
እገዳዉ ይነሳል፣ እገዳው እሰኪነሳ የንግድ ስራው እንዲያቆም ይደረጋል፡፡
ለ. አስገዳጅ የኢትዮጵያ ደረጃ የወጣለት ምርት እያመረቱ ነገር ግን የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት
የሌላቸዉ ወይንም የጥራት ማህተም የማይጠቀሙ ድርጅቶች በቁጥጥር ሲደረስባቸዉ የንግድ
ፈቃዳቸዉ ይታገድና ከላይ በተገለጸዉ አግባብ ማረጋገጫ እንዲያመጣ ይደረጋል፡፡
35
ሐ. በሚያመርተዉ የኢንዱስትሪ ምርት ላይ የምርት መግለጫ ሳያደርግ አምርቶ የሚሸጥ ባለኢንዱስትሪ
የንግድ ፈቃዱ ለ 2 ወራት ታግዶ ከላይ በተገለጸዉ መሰረት ማረጋገጫ አቅርቦ የምርት መግለጫ
ማድረግ ሲጀምር እግዱ ይነሳል፣
መ. ሆኖም የተፈፀመው ጥፋት ቀጣይነት ኖሮት አስተዳደራዊ እርምጃ የተወሰደ በሆነ ጊዜ መረጃ
ተደራጅቶ ተቋሙ ላይ ክስ ይመሰረታል፡፡
ሠ. የአገልግሎት ጊዜ ያለፈበትን የኢንዱስትሪ ምርት ለሽያጭ ሲያቀርብ የተገኘ የንግድ ድርጅት ለ 30
ቀናት ታሽጎ መረጃ ተደራጅቶ ክስ እንዲመሰረትበት ይደረጋል፡፡
ረ. አገልግሎት ጊዜ ያለፈባቸዉ ምርቶች ምርቱ በተገኘበት ነጋዴ ወጪ ተሰብስቦ ከአባባቢ ጥበቃ፣ ከጤና
ጽ/ቤት፣ ከንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት፣ ከፖሊስ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እንዲወገድ ይደረጋል፡፡
ሰ. ባዕድ ነገር ተቀላቅሎ በምርቶች ላይ ሲሸጥ ወይም ምርቱ ችግር አለበት ተብሎ በሚጠረጠርበት ጊዜ ናሙና
በመውሰድ ለሚመለከተው አካል ማሰመርመር ይገባል፡፡ አካሂዱም የህጋዊ ስነልክ ኦፊሰር፤ ፖሊስ የተጠርጣሪው
ደርጅት ባለቤት በጋራ ናሙናውን በሁለት መያዣ ይወስዳሉ ለዚሁም ይፈራረሙበታል፡፡ በተለይ የደርጅቱ ባለቤት
የተወሰደው ናሙና የራሱ መሆኑን በፊርማው ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ በዚሁ መሰረት አንዱን ጽ/ቤቱ ላይ
ማሰቀመጥ ሌላውን በላቦራቶሪ በተቀመጠ እስታንደርድ እንዲመረመር ለሚመለከተው አካል በግንባር ወስዶ
ማስረከብ ያስፈልጋል፡፡
ሸ. ባእድ ነገር በመቀላቀል የሚፈፀም የወንጀል ድረጊት ያለበት ጥፋት የፈፀመ የንግድ ድርጅት መረጃ
እንዲደራጅበት ተደርጎ ክስ ይመሰረትበታል፡፡ የንግድ ስራ ፈቃዱ የወንጀል ድርጊቱ እስኪረጋገጥ
ታግዶና ድርጅቱም ታሽጎ ይቆያል፡፡ ተግባሩ በፍርድ ቤት ውሳኔ ከተሰጠው የንግድ ፍቃዱ ይሰረዛል፡፡
የመስፈሪያ መሳሪዎችን ለማረጋገጥ በመጀመሪያ በአይነትና በጥቅማቸዉ መለይት አለበት፡፡በዚሁ መሰረት መስፈሪያ
መሳሪዎችን በሶስት መንገድ ከፍሎ ማየት ጠቃሚ ይሆናል፡፡እነሱም
በአለካክ ሕግ መሠረት
በአሰራር ስልት መሠረት
በሚጠቅሙበት መስክ መሠረት ናቸው፡፡
19.1. በአለካክ ሕግ መሠረት የሚረጋገጡትን መስፈሪያ መሳሪያዎች በሁለት መልኩ ክፍለን ማየት ይቻላል፡፡
19.1.1. በቀጥታ ሁለት መጠነ ቁሶችን በማወዳደር፤
ምሳሌ ፡-
36
ሀ. የጠረጴዛ ሚዛን፤
ለ. ግዝፈትን በማወዳደር ለምሣሌ የምድር ሚዛን፤
19.1.2. በአሰራር ስልት መሠረት
ሀ. በአንድ ዘንግ አመልካች ያልሆን መለኪያ. ለምሣሌ የወርቅ ሚዛን ቢም ባለንስ
ለ. የባለ ጥምር ዘንግ አመልካች ያልሆነ መለኪያ. ምሣሌ የምድር ሚዛን
ሐ. በክፍል አመልካች የመለኪያ ዘዴ ይህ ያለምንም መጠነቁስ መጨመር እስከተወሰነ መጠነቁስ ያነባል፡
መ. አመልካች የመለኪያ ዘዴ፤ይህ መለኪያ መጠነ ቁስ ሲጨመርበት የመጠነቁሱን መጠን በቁጥር ያነባል ለምሣሌ
የሰው ክብደት ለመለካት የሥጋ መጠን ለማወቅ በሆስፒታል እና ሥጋ ቤት አካባቢ ይገኛል፡፡
ሠ. ባለ ስፕሪንግ የሆነ አመልካች የመለኪያ ዘዴ ይህ የአላካክ ዘዴ በብዛት ፍራፍሬና አትክልትን ለመለካት
ይጠቅማል ፡፡
ረ. ዲጅታላዊ የሆነ እራሱን ችሎ የሚያመለክት ያለካክ ዘዴ፤ይህ የመለኪያ ዘዴ ትንንሽ መጠን ያላቸዉን ለሁሉም
ኣይነት መለኪያ የሚጠቅም ሲሆን በሁሉም የመለኪያ መስክ ይገኛል፡፡
19.1.3. የመለኪያ መሣሪያዎች በሚጠቅሙበት መስክ መሠረት
የልኬት መሳሪያዎች በእርጅና ወይም በተፈጥሮአዊ ብልሽትና በሰዉ ሰራሽ ችግሮች ወይም የንግድ ስነ-ምግባር
በሚጎድላቸዉ ነጋዴዎች በሚፈጸም የማጭበርበር ድርጊት ምክንያት ትክክለኛዉን ልኬት ላይሰጡ ይችላሉ፡፡
በመሆኑም በልኬት መሳሪያዎች ክትትል ላይ ሁለት ስራዎች ይሰራሉ፤ የመጀመሪያዉ የመሳሪያዎቹን
ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የሚደረግ ምርመራ ሲሆን ይህ በመሳሪያዉ እርጅና ወይንም ብልሽት ምክንያት
የሚከሰት የልኬት መዛባትን ለመከላከል ያግዛል፡፡ ሁለተኛዉ ስራ ሰዉ ሰራሽ ወይንም የንግድ ስነ-ምግባር
የሚጎድላቸዉ ነጋዴዎች የሚፈጽሙትን የልኬት ማጭበርበር ድርጊትን ለመከላከል የሚደረግ ድንገተኛ ፍተሻ
ስራ ነዉ፡፡
19.2.1. የመስፈሪያ መሳሪያዎች ላይ የሚደረግ ፍተሻ አካሄድ
19.2.1.1. ቅድመ ምርመራ
ሀ. የምናነፃፅረውን መለኪያ መሣሪያ ክፍሎችንና አስፈላጊ እቃዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ፤
37
ለ. መሣሪያው በመስራት ላይ መሆኑን ማረጋገጥ፤
ሐ. የመለኪያ መሣሪያው በተደላደለ ወለል ማረፋንና አመልካቾቹም የፀዱ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤
19.2.1.2. ዜሮ ላይ ማስቀመጥ፤
ሀ.የመለኪያ መሣሪያው ምንም ክብደት ሣይጨመርበት አመልካቹ ዜሮ ማንበቡን ማረጋገጥ
ለ. አመልካቹ ዜሮ ካላነበበ መሣሪያው የተሠራበትን ፋብሪካ ማንዋል በመከተል ወደ ዜሮ ማምጣት
19.2.1.3. ምርመራ ማድረግ
ሠ. ከአሠላነው ግድፈት ውስጥ ትልቁን ግድፈት መምረጥ ከዚህ ግድፈት ተነስተን ለመሣሪያው የተፈቀደለትንት
ግድፈት በማወቅ ይህ መለኪያ መሣሪያ ወይም ሚዛን መስራት አለመስራቱን እናረጋግጣለን፡፡
19.2.1.4. የምርመራ ምስክር ወረቀት ስለመስጠት
ሀ. የስነ ልክ ባለሙያው የመረመራቸውንና ያረጋገጣቸውን የመስፈሪያ መሣሪዎች ተጠቃሚዎች ሰምና
አድራሻ፣ምርመራና ማረጋገጫ የተከነወነበትን ቀንና እነዲሁም የተመረመሩትን የመሥፈሪያ መሣሪዎች
ዓይነትና ብዛት የሚመዘግብበት የምርመራና ማረጋገጫ መዝገብ ይይዝና ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ
የሚሰፈረውን ማስረጃ ሁሉ በፊርማው ያረጋግጣል፡፡
ለ. የኢትዩጵያን ስታንዳርድ ቅድመ ሁኔታ ከአረጋገጥን በኃላ የምስክር ወረቀት ይሰጣል ወይም አስቲከር
ይለጠፋል ፡፡ ለእያንዳንዱ የመለኪያ መሣሪያ ግድፈት መጠንና የመረጃ መሰበሰቢያ ቅጽ ከዚህ ማንዋል
በአባሪነት ተያይዟል፡፡
19.3. ምርመራ የሚካሄደባቸው የሚዛን ዓይነቶች እና አሰራራቸው
19.3.1. ባለ አንድ ዘንግ በራሱ አመልካች ያልሆነ ሚዛንን የመመርመር አካሄድ
(የጠረጴዛ ሚዛን) ቅድመ ምርመራ
ሀ. መሣሪያው የማይዋዥቅ እና ወለል ላይ ማረፉን ማረጋገጥ
ለ. የመሣሪያው የተሟሉ ክፍሎች መኖራቸዉን ማረጋገጥ (ሁሉም ክፍሎች በቦታ ላይ መሟላታቸውን ማየት)
ሐ. መሣሪያው በስራ ላይ መሆኑን ትንሽ ሲነካ ወደ ላይና ወደ ታች መሆኑን ማረጋገጥ (The Instrument is
sensitive)
መ. የሚዛኑ ሳህኖች ንፁህ መሆናቸውን ማረጋገጥ
19.3.2. ዜሮ ላይ ማስቀመጥ
38
ሀ. አመልካቹ ዜሮ ላይ ማንበቡን (የግራና የቀኝ አመልካች ትይዩ በሆነ መልኩ መቀመጣቸውን ማረጋገጥ) ይህ
የሚሆነው ምንም ክብደት ሣይጨመርበት ነው
ለ. ዜሮ ካልሆነ የመሣሪያውን የተሰራበትን ፋብሪካ በመጠቀም ወደ ዜሮ ማምጣት፤
ሐ. በሚዛኑ የኋላ ኪስ ወይም ጐኑ ላይ የተቀመጠ ትንሽ ክፍል አለ ይህ ክፍል ሣንቲም ወይም ሌላ ነገር
በመጨመር የሚዛኑን ትይዩነት ወይም ዜሮ ለማንበብ የሚጠቅም ህጋዊ ኪስ ነው፤
19.3.3. ምርመራ ማድረግ
(የምድር ሚዛን)
39
ሀ. ምንም ክብደት ሣይጨመርበት አመልካቹ ዜሮ ላይ ማንበቡን ማየት ወይም የግራና የቀኙ አመልካች ትይዩ
መሆኑን፣ ዜሮ ካልሆነ ደግሞ ካቻ ቪቴ በመጠቀም ማነፃፀሪያውን ወደ ፊትና ወደ ኋላ በማስኬድ
ማስተካከል፤
19.3.4.3. ምርመራ ማካሄድ
ሀ. በመሣሪያው በተቀመጡ ክፍልፋዮች እኩል 10 ነጥቦችን መምረጥ፤
ለ. ደረጃ በደረጀ መደበኛ ክብደቶችን በመጠቀም ከሚዛኑ ወለል ማህል ላይ ማስቀመጥ፤
ሐ. የእያንዳንዱን አመልካች ዋጋ መመዝገብ፤
መ. ለተመዘገበው ዋጋ ግድፈቱን ማስላት፤
ሠ. ከፍተኛውን ግድፈት ማግኘት ይህም ከፍተኛ ግድፈት ወስዶ የተፈቀደውን ግድፈት ማወቅና ከኢትዩጵያ ደረጃ
አንፃር የዚህን ሚዛን መስራትና አለመስራት ማረጋገጥ፤
(የወርቅ ሚዛን)
19.3.5.2. ዜሮ ላይ ማስቀመጥ
ሀ. አመልካቹ ዜሮ ላይ ማንበቡን (ምንም ክብደት ሳይጨመርበት ዜሮ ላይ ማንበቡን)
ለ. ዜሮ ካልሆነ መሣሪያው የተሰራበትን የፋብሪካ ማንዋል በመጠቀም ወደ ዜሮ ማምጣት
ሐ. በሚዛኑ የኋላ ኪስ ወይም ጐኑ ላይ የተቀመጠ ትንሽ ክፍል አለ ይህ ክፍል ሣንቲም ወይም ሌላ ነገር
በመጨመር የሚዛኑን ትይዩነት ወይም ዜሮ ለማንበብ የሚጠቅም ህጋዊ ኪስ ነው፡፡
19.3.5.3. ምርመራ ማድረግ
40
ሀ. ከመሣሪያው ባሉት ክፍልፋዬች ላይ አስር ነጥቦችን እንመርጣለን፡፡
ለ. ደረጃ በደረጃ (መደባዊ ክብደቶችን ከመለኪያ ሣህኑ መሀል ላይ በማስቀመጥ የመለኪያ አመልካቹ
እስከሚያቆም ድረስ ማየት) ለሌሎቹ ክብደቶች የማነፃፀር ሂደት የምንጨምረውን ክብደት ዋጋ
ከአመልካቹ ዋጋ ጋር በማነፃፀር እናሠላለን
ሐ. በእያንዳንድ ክብደት ላይ ያለውን ዋጋ ስለመመዝገብ
መ. ለእያንዳንዱ አመልካች ግድፈት ማስላት
ሠ. ትልቁን ግድፈት መውሰድ ከዚህ ግድፈት ተነስቶ የተፈቀደውን ግድፈት በማስላት ከኢትዩጵያ ደረጃ አንፃር
የሚዛኑን ትክክለኛነት ማረጋገጥ፡፡
(የስጋ ሚዛን)
41
እያንዳንዱ የምንጠቀምባቸውን ወይም የምንገለገልባቸውን ጌጣጌጦች እንዲሁም መሣሪያዎች ከምን ንጥረ ነገር እንደተሠሩ
የምናውቅበት መንገድ እፍጋት (density) ይባላል፡፡ /the amount per unit size
ቅድመ ምርመራ
ሀ. የመስፈሪያ መሳሪያዎችን እንደገና ለማረጋግጥ ከላይ በዝርዝር የተጠቀሱትን የምርመራ አከሄዶች መከተል
ይገባል፡፡
42
መ. የመስፈሪያ መሳሪያ እንደገና በሚመመረበት ገዜ ትክክለኛ ሁኖ የተገኘ እንደሆነ ባለሙያው አስፈለጊዉን
መረጃ ከያዘ በኋላ የመሥፈሪያ መሣሪውን እንደገና ያረጋግጣል፡፡
ሠ. የመስፈሪያ መሳሪያ እንደገና በሚመረመረበት ገዜ ትክክለኛ ሣይሆን የተገኘ እንደሆነ ባለሙያው ከዚህ
ቀደም የተደረጉትን የማረጋጋጫ ማኀተሞች ሁሉ ከመስፈሪያ መሳሪዉ ላይ ያነሳና እንደይሰራበት
ያደርጋል፡፡
የመሥፈሪያ መሣሪዎች ለንግድ ሥራ አገልግሎት ለማዋል በየደረጃው ተመርምረውና ተረጋገጠው ትክለኝነታቸው ተረጋግጦ
ወደ ገብያ መውጣት ያለባቸው ስለሆነ ተከታታይ ቁጥጥር ማደረግ ያስፈልጋል በዚሁ መሰረት
መ. ተገቢው ማስረጃ ከሌላቸው በመቆጣጠሪያ መሣሪያ ከላይ በተጠቀሰው አካሄድ መሰረት የምርመራ ስራ
ማከናወን
ረ. በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ወሰጥ ካላስተካከሉ የመሥፈሪያ መሳሪያውን በሚዛንና መሥፈሪያ ደንብ ቁጥር
431/1965 መሰረት በህግ መጠየቅ ውሳኔውንም መከታተል
ሀ. የልኬት አዛብቶ ወይም አሳንሶ ሲሸጥ የተገኘ የንግድ ድርጅት የሚበላሽ ምርት ካለ የ 24
ሰዓት ማስጠንቀቂያ በመስጠት 7 ቀን እንዲታሸግ ይደረጋል፣ ድርጅቱ የሚያቀርበው ምርት
መሰረታዊ ሸቀጥ ከሆነ በመሰረታዊ ሸቀጥ መመሪያው መሠረት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ለ. የታሸገዉ ድርጅት መለኪያ መሳሪያ መስተካከል የሚችል ከሆነ ነጋዴዉ አስጠግኖና
ትክክለኛነቱን አስፈትሾ የእሸጋው ቀን ሲያበቃ ስራ ላይ እንዲዉል ማድረግ ይቻላል፣
ሐ. የታሸገዉ መሳሪያ የማይስተካከል ከሆነ እንዲወገድ ይደረጋል፣
43
መ. አገልግሎት ለመስጠት ብቁ ያልሆነ መስፈሪያ መሳሪያን ሳያስጠግንና በባለሙያ ትክክለኛነቱ
ተረጋግጦ ስቲከር ሳይለጠፍበት ሲጠቀምበት የተገኘ ነጋዴ የንግድ ድርጅቱ ለ 15 ይታሸግና
ክስ እንዲመሰረት ይደረጋል፡፡
ሠ. ድርጅቱ ተመሳሳይ ጥፋት ለሁለተኛ ጊዜ ከደገመ ለ 30 ቀን ይታሸጋል፡፡
ሰ. ለሶስተኛ ጊዜ ከሆነ የንግድ ድርጅቱ 3 ወራት ይታገዳል ፣
44
ሠ. ህብረተሰቡ ለሚያቀርበዉ ጥቆማ ፈጣን ምላሽ መስጠት፣ህገ-ወጥ ድርጊት ፈፅመዉ
በተገኙት ላይ በቢሮዉ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ በሚገኘዉ ሸቀጦች ስርጭት
መመሪያ መሰረት አስተማሪ እርምጃ መዉሰድ ልንከተላቸዉ ከሚገቡ አሰራሮች ናቸዉ፡፡
ድህረ ሽያጭ የዋጋ ቁጥጥር ለማካሄድ በዋናነት የሸቀጦችን ዋጋ በየጊዜዉ በትኩረት መከታተልና ግልጽ መረጃ
መያዝ ያስፈልጋል፡፡በዚህ አግባብ በየወቅቱ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ የሚታይባቸዉ ሸቀጦች ከመነሻቸዉ
ጀምሮ የዋጋ ጭማሪዉ መንስኤ መታወቅ ይኖርበታል፡፤
ሀ. የሸቀጦችን ዋጋ በየወቅቱ መከታተልና በሸቀጦች ዋጋ ላይ የሚታየዉን የዋጋ ሁኔታ በትኩረት
መከታተል፣
ለ. ነጋዴዎች ለገበያ የሚያቀርቧቸዉን የዋጋ ሸቀጦች የዋጋ ዝርዝር በየንግድ መደብራቸዉ
እንዲለጥፉ ማድረግና ምክንያታዊ ያልሆነ ዋጋ ጭማሪ ሲታይ ለየወረዳዉ ንግድጽ/ቤት
እንዲያሳዉቁ ማድረግ፣
ሐ. በሸቀጦች ላይ የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ሲከሰት ነጋዴዉ የዋጋ ጭማሪዉን መንስኤ በማስረጃ
አስደግፎ በጽሁፍ ሪፖርት እንዲያቀርብ በማድረግ የዋጋ ግንባታ በማስላት በየደረጃው
ያለዉ የግብይት ተዋናይ(አስመጪ፣አምራች፣ጅምላ፣ቸርቻሪ ነጋዴ) በእያንዳንዱ
መለኪያ(ኪሎ፣ ሊትር ወዘተ…)የተያዘዉን ትርፍ መለየት(በ 24 ሰዓት ዉስጥ ነጋዴዉ
ማስረጃዎቹን ማቅረብ ይጠበቅበታል)፣
መ. ነጋዴዉ የዋጋ ግንባታዉን ሲያቀርብ ምርቱን ከየት እንደገዛ ህጋዊ ማስረጃ(ደረሰኝ)
ማቅረቡን ማረጋገጥ፣
ሠ. በዋጋ ግንባታው ምክንያታዊ የሆነ የዋጋ ጭማሪ ሳይኖር የተጋነነ የዋጋ ጭምሪ አድርጎ የታየ
ነጋዴ ከዋጋ ጭማሪው በፊት ይሸጥ ወደ ነበረዉ ዋጋ መልሶና አስተካክሎ የዋጋ ዝርዝር
ለጥፎ በዚሁ አግባብ ሽያጭ እንዲያካሄድ ይደረጋል፣
ረ. የዋጋ ግንባታዉን በተሰጠዉ ጊዜ ገደብ ዉስጥ ያላቀረበ ነጋዴ የንግድ ድርጅቱ ታሽጎ
እንዲያቀርብ ይደረጋል፣ማስረጃዉን እንዳቀረበ እሽጉ ይነሳል፣
ሰ. ምክንያታዊ ያልሆነ ዋጋ ጭማሪ አድርጎ የተገኘ ነጋዴ ዳግም ተመሳሳይ ድርጊት ላይ
እንዳይሰማራ ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፣
ሸ. የተጋነነ ዋጋ ጭማሪ አድርጎ የተገኘው ነጋዴ ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ ካልቻለ ሸቀጡን
በህጋዊ መስመር እንዳልገዛዉ ወይም ሆን ብሎ የዋጋ ንረት እየፈጸመ የሚገኝ ተደርጎ
ስለሚወሰድ የንግድ ፈቃዱ እንዲሰረዝ ይደረጋል፡፡
45
21. በጥፋተኞች ላይ ክስ ስለመመስረት
ጥፋተኛ ሆነዉ የተገኙ ነጋዴዎችን ፍ/ቤት በማቅረብ ሌሎች ነጋዴዎችን ሊያስተምር የሚችል የጥፋተኝነት
ዉሳኔ ማስወሰድ ሌላዉና ዋናዉ በንግድ ሪፎርሙ ትኩረት የሚያሻዉ የንግድ ስርዓታችን ችግር ፈቺ መሳሪያ
ነዉ፡፡ ጥፋተኞችን ለፍርድ አቅርቦ የጥፋተኝነት ዉሳኔ ለማስወሰን የተደራጀ ግልጽና ተጠያቂነትን ሊያመጣ
የሚችል ማስረጃ ማደራጀት ወሳኝ ጉዳይ ነዉ፡፡የተደራጀ መረጃ ባለመያዛችንና ለፍ/ቤት ለምናቀርበዉ ክስ በቂ
ማስረጃ አደራጅተን ባለማቅረባችን ጥፋተኞች በነፃ እንዲለቀቁና ኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር
ጉልበት እንዲያገኝ ምቹ ሁኔታ ሲፈጥርለት ይታያል፡፡
የችግሩ መንስኤ በፈጻሚያችንና በህብረተሰቡ ዘንድ የሚታይ የአመለካከት ችግር ዋነኛዉን ድርሻ የሚወስድ
ነዉ፡፡ በህብረተሰቡ ዘንድ ፍ/ቤት ሄዶ የምስክርነት ቃል ለመስጠት እንግልት አለዉ፡፡ህገ-ወጡ የምስክርነት ቃል
በሚሰጠዉ አካል ላይ ተጽእኖ ሊያመጣ ይችላል ከሚል ስጋት መነሻነት መብቱ በህገ-ወጦች እየተወሰደ ዝም
ብሎ የሚያልፍበትና መንግስት ላይ ቅሬታ የሚያቀርብበት ሁኔታ በስፋት የሚስተዋል ጉዳይ ነዉ፡፡በተመሳሳይ
መልኩ ተቆጣጣሪዎቻችን ጥፋተኛን ለህግ ከማቅረብ ይልቅ በአስተዳደራዊ እርምጃ ማለፍ በዚህም መደራደር
አንዱ ችግር ሲሆን በሌላ በኩል ፍ/ቤት የሄደ ጉዳይ ስለሚያመላልስና ስለሚያደክም ህገ-ወጦች የንግድ ህጉን
እየጣሱ የሸማቹንና የመንግስትን ጥቅም ለጉዳት እየዳረጉ የሚታለፉበትን አግባብ ፈጥነን ማረም ካልቻልን
ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ ይሄዳል፡፡ ሌላዉ ጉዳይ በመረጃ አያያዝ ላይ በፈጻሚያችን ዘንድ የሚታይ
የክህሎት እጥረት ችግር ነዉ፡፡ በመሆኑም የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ በክትትል ወቅት መረጃ አያያዝ
ላይ ልዩ ትኩረት ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ለክስ ምርመራና ክትትል ኬዝ ቲም የሚያቀርበዉ መረጃ በአግባቡ
የተደራጀና በግልጽ ነጋዴዉ የተላለፈዉን ጥፋት በዝርዝር የሚያመላክት መሆን አለበት፡፡
21.1. ደንብ ተላልፈዉ በተገኙ ነጋዴዎች ላይ ክስ ለመመስረት መያዝ ያለባቸዉ ማስረጃዎች፤
46
ቀ. የሸማቹን ደህንነትና ጥቅም የሚጎዱ ተግባራት ተፈጽሞ ከተገኘ ቢቻል ድርጊቱ
የተፈጸመበት ሸማች ስም፣አድራሻ(ስልክ መኖሪያ ቦታ) ቢያዝ፣
በ. የዶክመንት ማስረጃ ከተቻለ ኦርጅናሉን አለበለዚያ ኮፒዉን(ባለቤቱ በማህተሙና
በፊርማዉ ያረጋገጠዉ)፣
ተ. ቢቻል የኤሌክትሮኒክስ ቅጂ ማስረጃዎችን መያዝ፣/በሞባይል፤በካሜራ፤ በቪዲዮ
ወዘተ…./
ቸ. ኢግዚቢት መያዝ የሚያስፈልግ ከሆነ በፖሊስ እንዲያዝ ማድረግ፣ ለምንመሰርተዉ ክስ
ዉጤታማነት ከፍተኛ ሚና ያለዉ ሲሆን መረጃዉ የቀረበለት የክስ ምርመራና ክትትል ባለሙያ
ማስረጃዉን አደራጅቶ ከህግ ጋር አጣቅሶ ለፖሊስ የክስ አቤቱታ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
በቂ ማስረጃ ተደራጅቶ ክስ ከተመሰረተ በኋላ በቂ ክትትል ማድረግ የክስ ምርመራና ክትትል የስራ ድርሻ
ነዉ፡፡ ያቀረብናቸዉን ክሶች በአግባቡ ባለመከታተላችን ህገ-ወጦች በነጻ ሊለቀቁ ይችላል፡፡ ምንም እንኳን
ክስ የሚመሰረተዉ በፖሊስና በአቃቢ ህግ ቢሆንም የተመሰረተውን ክስ በባለቤትነት ዉጤታማነት በጥብቅ
ዲሲፕሊን መከታተል ያስፈልጋል፡፡ በአቃቢ ህግም ሆነ በፍ/ቤት ዉሳኔ ላይ የሚታይ ግድፈት ካለ በጥብቅ
ዲሲፕሊን በመከታተል በተዋረድ ላለዉ የፍትህ አካል ይግባኝ የሚባልበትን ሁኔታ ማመቻቸትና
የመጨረሻዉን ዉሳኔ መከታተል ይገባል፡፡
21.2. ክስ የሚያስቀርቡ ጥፋቶች፤
የሂደቱን ተግባራት ዕቅድ አፈፃፀም አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች መረጃዎችን የመለዋወጡ ሁኔታ እንዳለ ሆኖ በመስክ
በመዘዋወር የመደጋገፍና መረጃዎችን የመለዋወጥ ሥራ በታቀደ አግባብ ሊከናወኑ ይገባል፡፡ የመስክ ክትትልና ድጋፍ
ሥራዎች የሚሠሩት በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደረጃ ባሉ የሂደቱ ባለሙያዎች ሲሆን፤ የማእከል ባለሙያዎች በክፍለ
ከተማዎች እንደ አስፈላጊነቱ ደግሞ በወረዳዎች በሩብ ዓመት /3 ጊዜ/ የክፍለ ከተማ ባለሙያዎች ደግሞ በሥራቸው ባሉ
ወረዳዎች በሩብ ዓመት /3 ጊዜ/ በመገኘት ድጋፍና ክትትል ያደርጋሉ፡፡ በመጨረሻም ስለመስክ ክትትልና ድጋፍ አሰጣጥ
የአፈፃፀም ሪፖርት በታቀደው ዕቅድ መሠረት በማድረግ ተዘጋጅቶ የድጋፍና ክትትሉ ውጤታማነት በክልልም ሆነ በክፍለ
ከተማ ደረጃ መገምገም አለበት እያንዳንዱ ክፍለ ከተማና ወረዳ የውጭና የውስጥ ኢንስፔክሽን ሥራው ያለበት ደረጃና
በተለይም ህገወጥ ነጋዴዎችን ወደ ህጋዊነት በመመለስ ባልተመለሱት ላይ ደግሞ እየተወሰደ ያለው ህጋዊ እርምጃ ምን ላይ
እንዳለ ሊያሳይ በሚችል በማነፃፀር መገምገም ይገባል፡፡ ከመስክ መልስ ግምገማው ላይ ለሌላውም ተሞክሮ ሊያስተላልፍ
በሚችል መልኩ በመስክ የተሳተፈውም ሆነ ያልተሳተፈው በተገኘበት መገምገም ይገባዋል፡፡ ከግምገማው በኋላም በየደረጃው
የመስክና የአፈፃፀም ሪፖርቱን ግብረ-መልስ መስጠትና ትምህርትና ተሞክር የሚገኝበትን ሁኔታ መፍጠር፡፡
48
ረ. በመስክ ክትትልና ድጋፍ የቆይታ ጊዜ
ሰ. የሚያስፈልግ የሰው ሀይል ፤ በጀትና ተሽከርካሪ ካለ ወዘተ --- የመሣሰሉትን ጠቅሶና የጋራ አዱርጐ
ስምሪት ማድረግና ሥራችንን በተደራጀና በተቀናጀ በመስራት ውጤታማ ማድረግ ይገባናል፡፡
22.2. የመስክ አፈጻጸም ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብና የክትትልና ድጋፍ አግባብ
የእለቱ፣ የሳምንቱ፣የወሩ የመስክ ክትትልና ቁጥጥር ሪፖርት በጥብቅ ዲሲፕሊን ጊዜዉን ጠብቆ ሳይቆራረጥ
ይዘጋጃል፡፡ በየልማት ቀጠናዉ ያለዉ አፈጻፀም እና ለዉጡ ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ የቀጣይ አቅጣጫ
እየተቀመጠ ይሄዳል፡፡
22.2.1. የመስክ አፈጻጸም ሪፖርቱ፡-
49
22.2.3. አፈጻፀም መገምገም፣
ቅፅ 01
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት
በዳቦ ግራሞች ላይ ለሚደረግ ቁጥጥር መከታተያ ቅፅ
50
5
6
7
8
አማካኝ
ከኦፊሰሩ ለባለ ዳቦ ቤቱ የተሰጠው
ምክር-------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
-------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
------፡፡
የተሰጠ
ውሳኔ-------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
-------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
---------------------------፡፡
የተሰጠውን አስተያየት ድርጅቱ ስለመቀበሉ የሰጠው
አስተያየት--------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
------------------------------------------------------------------------------------------------------------- ፡፡
የድርጅቱ ባለቤት ወይም ተወካይ ስም------------------------------ፊርማ-------------- ቀን------------
የተቆጣጣሪዎች ስም---------------------------- ፊርማ-------------------
ስም--------------------------- ፊርማ-----------------
ስም---------------------------- ፊርማ----------------
51
ቅፅ 02
በንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬቶሬት በየወሩ በሚፈጠረው የነዳጅ ስርጭት ቁጥጥር ላይ የመስክ ምልከታ ቅፅ
የባለማደያው ፊርማ
የድፕ ስቲክ ንባብ
የተገኘ ሊትር
ተ.ቁ ነዳጁ ጥያቄ የተከፈለ
የካምፓኒው ልዩ ቤንዚን ናፍጣ ነጭ ጋዝ የታዘዘበት የደረሰኝ የተወሰደ እርምጃ
የታየ ማደያ ስም ያለቀበት የቀረበበት ክፍያ
ወረዳ በሊትር
ስም ቦታ በሊትር በሊትር ቁጥር ቁጥር
ቀን ቀን መጠን
ማስጠንቀቂያ እሸጋ
ቅጽ 03
በ 2007 ዓ.ም በንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ንግድና ኢንስፔክሽንና ሬጉላቶሪ ዳይሬክቶሬት የልኬት መሳሪያዎች እና የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎች በየወሩ ሪፖርት ማድረጊያ
ህጋዊ ምስክር
የዓመቱ
በድንገ
ተ.ቁ የንግድ ቤቱ ስም በክ/ከተማው የመስፈሪያ መሳሪያዎች የተወሰደ ህጋዊ ቬሪፋይ
ዕቅድ
ንግድ
የማረጋገጥ ስራ
በእስራ
ክስ
የተሰበሰቡ. ወይም
ማስጠን
መስፈሪያዎች ብዛት የተወገዱ
የተሰራባቸው ብዛት የታሸጉ
52
ብዛትወረቀት/ስቲከር/ የተለጠፈባቸ
የተመሰረተባቸው
ፍቃድ የተሰረዘባቸው
በገንዘብ የተቀጡ
ት የተቀጡ
የተሰበሰቡ ስታንደርዶች
ፍቃድ የተሰረዘባቸው
የተሰበሰቡ ሚዛኖች
የታሸጉ ሚዛኖች
ማነፃፀሪያዎች
ማነፃፀሪያዎች
ማነፃፀሪያ
ማነፃፀሪያ
ሚዛኖች
ሚዛኖች
ሚዛን
ሚዛን
ቀቂያ
ማነፃፀሪያ
ሚዛን
1 ስጋ ቤቶች
2 ዳቦ ቤቶች
3 አትክልት ቤቶች
4 ወርቅ/ብር/ ቤት
5 እህል በረንዳ
6 ወፍጮ ቤት
7 ሸቀጣ ሸቀጥ ሱቅ
8 ነዳጅ ማደያ
9 ዱቄት ፋብሪካ
10 ኢትፍሩት ኮንቲነሮች
11 ሌሎች ይጠቀሱ
የተሟላ ግብዓት
12 ሚዛን
13 የተሟላ ስታንደርድ
ድምር
53
ቅፅ 04
ቀን---------------------------
ቃለ ጉባኤ
የስብሰባ ቦታ-------------------------------
የስብሰባ ሰዓት-----------------------------
የተሰብሳቢ አባላት
1. ሰብሳቢ አቶ/ወ/ሮ-------------------የ----------------ስራ ሂደት አስ/መሪ/ኦፊሰር
2. ፀሀፊ አቶ/ወ/ሮ------------------- የ---------------- ኦፊሰር
3. አባል አቶ/ወ/ሮ------------------- የ---------------- ኦፊሰር
ሆነን በመሰብሰብ በሚከተለው አጀንዳ ላይ ተወያይተናል፡፡
የመወያያ አጀንዳ
አጀንዳ 1 .
2.
3.
የተደረገ ውይይት
አጀንዳ 1.
አጀንዳ 2.
አጀንዳ 3.
የተደረሰበት ስምምነት(ማጠቃለያ)
---------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
-------------------------------------------------------------------፡፡
የተሰብሳቢ አባላት
ስም------------------ ፊርማ----------------
ስም -----------------------ፊርማ---------------
የጽ/ቤቱ ወይም ሰራ ሂደቱ አስ/ የውሳኔ
ሀሳብ---------------------------------------------------------------------------------------------------------------
--------------------------------------------------፡፡
ስም-------------------------------ፊርማ---------------------ቀን------------------------------
ቅፅ 05
54
በአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ግልባጭ፡-
ለ-----------------------------
ለ------------------------------
አዲስ አበባ
ቅጽ ዐ 6
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
55
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- ምርመራ እንዲጣራና ክስ እንዲመሠረት ስለመጠየቅ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ------------- ክፍለ ከተማ -------------- ወረዳ --------------የቤት
ቁጥር------------------ልዩ ቦታ----የንግድ ምዝገባ ቁጥር ---------------የንግድ ሥራ ፈቃድ ------------------
የተሰማሩት አቶ/ወ/ሮ --------------------------------------በ----------------ቀን-------ዓ.ም የወረዳው
የቁጥጥርና ክትትል ኦፊሰሮች በተደረገ
1.--------------------------------------------
2.-------------------------------------------
3.-------------------------------------------
4.-------------------------------------------
5.-------------------------------------------
አግባብነት የሌላቸውን የንግድ ሥራዎች ሲያካሂዱ ተደርሶባቸዋል፡፡ በመሆኑም ይህ ህገወጥ ተግባር ተጣርቶ
በንግድ ምዝባና ፍቃድ በአዋጁ ------ እና በንግድ ውድድርና ሸማቾች ጥበቃ እዋጅ ቁጥር ------- መሠረት ክስ
ተመስርቶ አቃቢ ህግ እንዲተላለፍለን እንጠይቃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ግልባጭ፣
ለ------------------------------
ለ------------------------------
አዲስ አበባ
56
ቅፅ 07
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
በ----------------------------------- ክፍለ ከተማ
መሰረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች ስርጭት ተደራሽነት መከታተያ ፎርማት
የታየበት ቀን------------------------------
ለቸርቻሪ ሱቅ
የተሰራጨ በመጋዘን ያለ ምርመራ
ምርቱ
የገባው ምርት መጠን
የተቋሙ ምርት ለቸርቻሪ ሱቅ የታዩ ሱቆች
ተ.ቁ ወረዳ የገባበት
ስም የተሰራጨበት
ቀን
ቀን
‹
ዘይት ስኳር ስኳር ዘይት
ዱቄት ዘይት ስኳር ዘይት ስኳር ዱቄት ብዛት
በሊትር በኩ/ል ያላቸው ያላቸው
ቅፅ 08
57
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ተ. የድርጅቱ/ግለሰቡ መለያ የሚሰራበት አድራሻ የንግድ የንግድ የግብር ሲመዘገብ ጉድለት ሲመዘገብ የተደረገ ምርመራ
ቁ ስም ኮድ ዘርፍ/መስክ ም/ቁጥር ፍ/ቁጥር ከፋይ ቁጥር ያልተገኘባቸው ጉድለት ለውጥ
ቤት.ቁ ስልክ ቁ የተገኘባቸው
ቅጽ 9
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
በ----------------------------------- ክፍለ ከተማ ------------ ወረዳ---------- ቀጠና------------
በብሎክ ማኔጅመንት በሳምንት ሊጐበኙ የታቀዱ የንግድ ድርጅቶች ብዛት
በ-------- በጀት ዓመት ሊጐበኙ የታቀዱ የንግድ ድርጅቶች
ጠቅላላ
1 ኛ ሩብ ዓመት 2 ኛ ሩብ ዓመት
ዘርፍ ድምር
ሐምሌ ነሃሴ መስከረም ድምር ጥቅምት ህዳር ታህሳስ ድምር
58
1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4 2 3 4 1 2 3 4 4
ድ ድ ድ 1ኛ ድ ድ 1ኛ 2ኛ 3ኛ ድ
ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ
ቅጽ 10
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
በ----------------------------------- ክፍለ ከተማ ------------ ወረዳ---------ቀጣና-----------
በብሎክ ማኔጅመንት በሳምንት ሊጐበኙ የታቀዱ የንግድ ድርጅቶች ብዛት
በ-------- በጀት ዓመት ሊጐበኙ የታቀዱ የንግድ ድርጅቶች
ጠቅላ
3 ኛ ሩብ ዓመት 4 ኛ ሩብ ዓመት ላ
ዘርፍ ድምር
ጥር የካቲት መጋቢት ድምር ሚያዚያ ግንቦት ሰኔ ድምር
59
1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4
ድ ድ ድ ድ ድ ድ
ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ ኛ
ቅፅ 11
60
የባለሙያው ስም --------------------------ፊርማ--------------ቀን---------------------------
ያፀደቀው ሃላፊ ስም-----------------------ፊርማ-----------------ቀን--------------------------
ቅፅ 12
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ክፍለ ከተማ ------------- ወረዳ-------------ቀጣና -------
በንግድ ክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች የተጎበኙ የንግድ ድርጅቶች መመዝገቢያ ቅፅ
ድርጅቱ የፈፀመው የጥፋት ዓይነት
ምርመራ
ደረሰኝ አለመስጠት
ከአድራሻ ውጪ መነገድ
የንግድ ም/ፈ/ በተገቢ ቦታ አለመለጠፍ
የን
አለንግድ ፈቃድ መነገድ
ከቅጣት የተገኘ ገቢ
ከዋጋ በላይ መሸጥ
በነፃ የተለ ቀቀ
ምርት መደበቅ
ጥፋት የለውም
እሽግ መክፍት
ተ. የድርጅቱ/ ግለሰቡ ግድ
ከመስክ ውጭ
ከዘርፉ ውጭ
የቤት
ቀጣና
የተቀጣ
ሌሎች
ቁጥር
ቁ ስም ዘር
ፍ
61
የተቆጣጣሪዎች ስም
1. ------------------------------------ ፊርማ --------------------------- ቀን-------------------
2. ----------------------------------- ፊርማ ---------------------------- ቀን--------------------
ማሳሰቢያ፡- ድርጅቱ/ግለሰቡ የፈፀመው ጥፋት በ” “ አሳይ
የጉብኝቱ ዓይነት በጥቆማ ከሆነ ይህንኑ ምርመራ በሚለው አለም ላይ የደረጅቱ /ግለሰቡ ስም አንፃር ይገለጽ፡፡
ቅፅ 13
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ክፍለ ከተማ ------------- ወረዳ-------------
በንግድ ክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች የተጎበኙ የንግድ ድርጅቶች ውጤት ማጠናቀሪያ ቅፅ
ድርጅቱ የፈፀመው የጥፋት ዓይነት
ምርመራ
ደረሰኝ አለመስጠት
ከአድራሻ ውጪ መነገድ
ከቅጣት የተገኘ ገቢ
ከዋጋ በላይ መሸጥ
በነፃ የተለ ቀቀ
ምርት መደበቅ
ጥፋት የለውም
እሽግ መክፍት
በር
ከመስክ ውጭ
ከዘርፉ ውጭ
የተቀጣ
ሌሎች
ለበር
ብዛት
62
በአሰራር ላይ ያጋጠሙ ችግሮች
፡፡
የመፍትሄ ሀሳቦች
፡፡
ሪፖርቱን ያዘጋጁ ተቆጣጣሪዎች
1. ስም ------------------------------------ ፊርማ --------------------------- ቀን-------------------
2. ስም----------------------------------- ፊርማ ---------------------------- ቀን--------------------
ማሳሰቢያ፡- ድርጅቱ/ግለሰቡ የፈፀመው ጥፋት በ” “ አሳይ
63
የጉብኝቱ ዓይነት በጥቆማ ከሆነ ይህንኑ ምርመራ በሚለው አለም ላይ የደረጅቱ /ግለሰቡ ስም አንፃር ይገለጽ፡፡
ቅጽ 14
ማስጠንቀቂያ
ይህን ሕጋዊ መጥሪያ ፈርሞ ያለመቀበልና በቀጠሮ ቀን ያለመቅረብ በሕግ የሚያስቀጣ መሆኑን በቅድሚያ
እናስገነዝባለን፡፡
ቅጽ 15
64
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ማሳሰቢያ-፡
ይህ ፎርም በሁለት ኮፒ ተዘጋጅቶ አንዱ ለነጋዴው ሁለተኛው ኮፒ ለወረዳው/ክ/ከተማው ንግድ ፅ/ቤት ፋይል
ተደርጎ ይቀመጣል፡፡
ቅጽ 16
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
65
የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ሥራዎች ክንውን ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
66
ቅጽ 17
የድርጅቱ ስም ----------------------------------------------------
የድርጅቱ ባለቤት/ወኪል/ስም --------------------------------------------
አድራሻ ክፍለ ከተማ--------------ወረዳ-----------የቤት ቁ.----------------ስልክ ቁ.-----------------የንግድ
ምዝገባ ቁጥር --------------------------- የንግድ ፈቃድ ቁጥር ------------------------------- ድርጅቱ
የሚሸጣቸው ዕቃዎች /የሚሰጣቸው አገልግሎቶች/ ዓይነት ዋጋ መግለጫ
የዕቃው /አገልግሎት/ ዓይነት መሸጫ/የአገልግሎት/ ዋጋው
-------------------------------------------- --------------------------------------
-------------------------------------------- --------------------------------------
------------------------------------------- --------------------------------------
------------------------------------------ -------------------------------------
------------------------------------------ -------------------------------------
------------------------------------------ -------------------------------------
------------------------------------------ -------------------------------------
------------------------------------------- -------------------------------------
እኔ ስምና አድራሻዬ ከላይ የተጠቀሰው በድርጅቱ ውስጥ ለምሸጣቸው ዕቃዎች/ለምሰጣቸው አገልግሎቶች/
መሸጫ ዋጋ ከዚህ በላይ በዝርዝር የተመለከተው መሆኑን እያረጋገጥኩ ሳላስፈቅድ/ሳላሳውቅ/ ከተጠቀሰው
ዋጋ በላይ ስሸጥ ወይም አገልግሎት ስሰጥ ብገኝ ግን ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድብኝ መሆኑን ተነግሮኝ
ተረድቻለሁ፡፡
የድርጅቱ ባለቤት /ወኪል/ ፊርማ------------------------------ቀን------------------------
ቅጽ 18
67
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
ቁጥር----------------------------------
ቀን ----------------------------------
ለ----------------------------------------------
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- ማስጠንቀቂያ መስጠትን ይመለከታል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ ------------ ክፍለ ከተማ በወረዳ--------ቀጣና -------የቤት ቁጥር-----------
የንግድ ምዝገባ ቁጥር -----------------የንግድ ፈቃድ ቁጥር-----------------ተመዝግቦ በተሰጠዎት የንግድ ሥራ
ፈቃድ ከዘርፉ /ከመስክ/ ካስመዘገቡት አድራሻ --------------፣-------------------፣------------- ውጭ
ተሰማርተው በሚገኘው የክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች ተጣርተው ቢሮ ቀርበው በገቡት ግዴታ መሠረት
ሊያስተካክሉ ባለመቻሉ ይህ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሊሰጠዎት ተወስኖአል፡፡
በመሆኑም ይህ ማስጠንቀቂያ በተሰጠዎት በ-----------------ቀን ውስጥ ጉድለትዎን አስተካክለው ለጽ/ቤቱ
በጽሁፍ እንዲያሣውቁ እያሳሰብን ይህ ሳይሆን ግን -------- አዋጅ ቁጥር ------ አንቀጽ ------ መሠረት
ያለምንም ተጨማሪ ማስጠንቀቂያ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
ግልባጭ፣
ለ--------------ክፍለ ከተማ ን/ኢ/ል/ጽ/ቤት
ለ-------------ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ
አዲስ አበባ
ቅጽ 19
68
ቁጥር----------------------------------
ቀን ----------------------------------
ለ-----------------------------------------
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠትን ይመለከታል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ---------------------ክ/ከተማ ------------ወረዳ---------ቀጣና-------የቤት ቁጥር ውስጥ
በንግድ ምዝገባ ቁጥር ------------------- በንግድ ፈቃድ ቁጥር ------------------ ተመዝግቦ ፈቃድ መስጠትዎ
ይታወሳል፡፡
ሆኖም በመ/ቤቱ ክትትልና ቁጥጥር ኦፊሰሮች ተጣርቶ በተገኘው መረጃ መሠረት የንግድ ምዝገባ የንግድ
ፈቃዱ ሳያሣድሱ የንግድ ሥራ ሲሰሩ መገኘትዎ ተረጋግጧል፡፡
ይህም ሥራ በአዋጁ ቁጥር ------ አንቀጽ ----- መሠረት በተሠረዘ የንግድ ሥራ ፈቃድ ሲሰሩ በመገኘትዎ ይህ
የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ በደረሰዎት በ 24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ እንዲታሸግ ስለተወሰነ በድርጅቱ ውስጥ ሊበላሹ
የሚችሉትንና የግል መጠቀሚያ ቁሣቁሶችን አውጥተው እንዲጠብቁ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ከሠላምታጋር
69
ቅፅ 20
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
የጥቆማ ማቅረቢያ ስልክና ስልት
1. ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ጥቆማ ለመስጠት
ነፃ የስልክ መስመር 8588
2. ጥቆማ ሲያቀርቡ መሟላት የሚገባቸው ጉዳዮች
1.1 ጥቆማ የሚቀርብበት ግለሰብ/ድርጅት/ስም/
1.2 የጥቆማው ምክንያት
በህወጥ የንግድ ፍቃድ ተግባር ላይ
ካለንግድ ፈቃድ መነገድ
ባልታደሰ ፈቃድ መነገድ
የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን ምርቶች መሸጥ
ደረሰኝ ካለማግኘት አንፃር
የመሰረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች በህገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር፣ ማከማቸት እያለ የለም
ማለት፣ ከዋጋ በላይ መሸጥ፣ አየር ባየር መሸጥ
ሚዛን/ግራም/ ማጉደል
በአገልግሎት አሰጣጥ የተፈጠሩ ችግሮች ለማሳወቅ
ሌሎች ህገ-ወጥ ድጊቶች ካሉ
1.3 ጥቆማ የቀረበበት ግለሰብ ድርጅት የሚገኝበት ቦታ
ክፍለ ከተማ
ወረዳ
ልዩ ቦታ
የንግድ መለያ ኮድ
በመጥቀስ ጥቆማ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ልብ ይበሉ መሰረታዊ የድጎማ ምርቶች ማለትም ስኳር፣ የፓልም ዘይት እና የድጎማ ስንዴ በህገወጥ
መንገድ ሲያዘዋውር፣ ሲያከማች ለጠቆመ ምርቱ ተሸጦ 30% ለጠቋሚው የሚከፈል መሆኑን
እንገልፃለን፡፡
የጥቆማ ስልክ
ማዕከል ክፍለ ከተማ የጥቆማ ስልክ ወረዳ የነጋዴ ብዛት ቁጥር ምርመራ
ንግድና 8588 1
ኢንዱስትሪ
ልማት ቢሮ
2
3
4
5
ድምር
70
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር CITY GOVERNMENT OF
ADDIS ABABA
ንግድ ቢሮ
1. የነጋዴው/የድርጅቱ ስም––––––––––––––––––––––––––
2. የንግድ ስም––––––––––––––––––––––––––
3. አድራሻው፡-ክ/ከተማ–––---––– ወረዳ–––––ነባር ቀበሌ––––– ቀጠና------- ብሎክ------- ኮድ-----------
ቁ-----------ስ.ቁ-----------
የንግድ ምዝገባ ቁጥር --------------------------------------------------- የንግድ ፈቃድ ቁጥር-------------------------------------
የግ.ከ.መለያ ቁጥር/TIN/------------------------------------- የንግድ መስክ--------------------------------
ዘርፍ---------------------------
4. የተገኘበት የጥፋት ዓይነት፡-
1. ----------------------------------------------- 3.-------------------------------------------------------5.---------------------------------------------
2. ----------------------------------------------- 4--------------------------------------------------------6.--------------------------------------------
5. የተወሰደ የእርምጃ ዓይነት፡---------------------------------------------------------
6. እርምጃው የተወሰደበት ቦታ------------------------------------- ሰዓት--------------- ቀን---------------ወር--------------ዓ.ም------------------
7. ከዚህ በፊት ጥፋት ካለበት፡- የጥፋት ዓይነት፡---------------------------------- የተወሰደ እርምጃ----------------------------
ቁጥር-------------
8. ተቆጣጣሪዎች፡-1 ስም----------------------ፊርማ---------------------- ቀን----------/--------------/------------- ዓ.ም
2.ስም----------------------ፊርማ---------------------- ቀን----------/--------------/------------- ዓ.ም
3. ስም----------------------ፊርማ---------------------- ቀን----------/--------------/------------- ዓ.ም
71
ቅፅ 22
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
በ––––––––––ክ/ከተማ----------- ወረዳ –––––ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት
0
ቅፅ 23
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ
የ------------------------- ክፍለ ከተማ ወረዳ--------------- ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት
የታሸገበት ቀን----------------
ምክንያት
ታ ሽ ጓ ል!!
የተቆጣጣሪው ስም የስራ ድርሻ ፊርማ የታዛቢዎች ሙሉ ስም ፊርማ
1.
2.