Professional Documents
Culture Documents
ቤተልሄም ተፈራ
2016 EC
የምናብ መንገድ
እገስፅሃለው ..................................................................................4
አደራዎቼ .....................................................................................6
ልክ ግን ምንድን ነው....................................................................9
የማይነጋ ለሊት...................................................................... 15
እ ኔ ነኝ.................................................................................... 16
ሀሳብ ነኝ .................................................................................. 20
ሰውነት ..................................................................................... 23
ዝም ፀጥ ረጭ ወደ ውስጥ መኮብለል
ራስን ማበርታት ራስን ማባለል
ከልብ መመካከር ደግሞም ማሰላሰል
ከመንፍስ ትባብሮ ነፍስን ማደላደል
1
የውጪውን ሙግት ባልብት ሲትውት
የህይውትን ጥሪ ያኔ ነው ሚሰሙት
ከራስ ጋር ሲስማሙ የእወነት ይጀገናል
ይቻላል ይቻላል መልሳችን ይሆናል
2
የዝምታ ውበት….
3
ራሴን ይበላኛል ግን እኔ አላከውም
ከህሊናዬ ቤት ከአእምሮዬ ጓዳ
ዝም ጭጭ ብዬ ብርሀን ናፍቃለው
ብቻ ዝም ጭጭ አላይም አልሰማ
4
ያልፋል እንደተራ?
5
እኔን ደካማዋን በብዙ ብታምነኝ
እንዲህም ሆነና
ሰው ነኝና
6
ብርታትም ድካምም ነው ልበል?
7
ብርሃን በተሞላው መንገድ እንደ አደይ አበባ ፍክት ብለው
እንዲሮጡ እመኛለው፡፡
8
የሰውነት ሚዛን የሰውነት ልኩ
የሰውነት ስሪት የሰውነት መልኩ
ከመንፈስ ከስጋ ፍፁም አንድ የሆነ
የሁለቱ ውህድ የተመጣጠነ
ስህተት እርማት የየቀን ህይወቱ
ዘላለማዊ ነው ደግሞ ሀላፊ ከንቱ
ስጋው ሲጎትተው መንፈስ ሲመልሰው
ገላውን ሲያስደስት ነፍስያው ሲወቅሰው
እንዲሁ ማህል ቤት ልቡ እንደባዘነ
ለምድርም ለሰማይ ፀንቶ አልታመነ
አለምን ሲመስል ነፍሱ ስትከፋ
አካሉ ሲበድል ደስታ ሳቁ ጠፋ
የሰውነት ጥጉ ልኩ ግን መንድነው?
የስጋን ሲያደርሱ ነፍስን ማሳዘን ነው?
ያዳም ዘር ተልኮ የአለም ህይወቱ
ብፁዕ እንዲሆን አካሉን መጉዳቱ
የቱ ያስብለው ብርቱ ጉዞውም አሳካ?
የምድር ቆይታው በፍሬ ሲለካ
9
ስህተት ወይ ትክክል....
10
አባቴ አያቴ ከተወለዱበት መንደር ግዛታቸው
ካደጉበት ሀገር ከሜዳው ቦርቀው ከወንዙ ተራጭተው
ሰፈሩን ቆርቁረው ካቀኑት ሀገር
እንግዳ ቢያደርጉን መጤ ባይተዋር
ሹሙም ዝም ካለ ቤታችን ሲደፈር
ወዴት እንሰደድ ከየትስ እንደር
ግፍ እንዲህ ሲዛመት ሁሉን ሲያዳርስ
በልጆች ደም እንባ መሬቷ ሲርስ
መሰደጃ ጠፍቶን ክፉን ምናልፍበት
ቀንን ስንጠብቅ በተስፋ እና እምነት
ሊነጋ ሲል ይመሽ እያልን እያልን
ስንት ምሽት አለፍን እኛም እያለፍን
ግፉን እንገፋ ተስፋችን አያልቅም
ደጃፍ እንቆማለን የትም አንሄድም
በፈረሰው ምትክ ቤትም እንሰራለን
ካልሆነም ካልሆነም ከመሬቷ ገብተን ሰላም እናርፋለን
11
አንዲት ሀገር አለን….
12
የመረጥሽን ስለፈለግንሽ ብቻ ሳይሆን ስለምናስፈልግሽም ጭምር
ነው፡፡ ያለ ምክንያት የሚሆን ምንም ነገር የለም ሁሉ የሚሆነ
አንድና ትልቁን አላማ ለማሳካት ብቻ፡፡
13
የማይነጋ ለሊት የማይመሽ ቀን የለም
ያለ የሚረሳባት ቅዠት ናት ይቺ አለም
እልፍ ሂድት ጥፍት መሰወር መረሳት
ከከንቱ ድካሟ ለዘላለም መጥፉት
ግራ ግብት ሲል ሁሉ ትርጉም ሲያጣ
እርፍ በእንቅልፍ ፀሀይ እስክትወጣ
በሰው ቅዠት አለም ግብቶ ከመገኘት
በሞት ታናሽ ወንድ በእንቅልፍ መረታት
እስቲ ሁሉን ልርሳ ልተወው ልሽሸው
የዛለ መንፈሴን በእንቅልፍ ላድሰውው
14
የማይነጋ ለሊት
15
አልገኝም ብዬ ምዬ ተገዝቼ
ንቄ ረግሜ ተፀይፌ ትቼ
ገና ከመውጣቴ እግሬን ከማንሳቴ
ጠልፎ ይጥለኛል ክፉው ማንነቴ
ሰውነትን ይዤ ስጋዬን ለብሼ
ስህተትን ስደግም መልሼ መልሼ
ታጥቦ ጭቃ ብለህ አልተፀየከኝም
ሽንፈቴ ሰልችቶህ ዛሬም አልተውከኝም
እኔ ነኝ አላፍርም ፊትህ እቆማለው
ከፈጠርከኝ ጌታ ወዴት እሸሻለው?
ስታውቀኝ መርምረህ ከስር መሰረቴ
እንዲሁ ፈራለው ላይደንቅህ ስህተቴ
ዛሬም መጥቻለው ከፊትህ ቆሜያለው
እኔ ነኝ ልጅህ አንፃኝ ቆሽሼያለው
16
ስህተት እና ፍፁምነት
17
ያልበሰለ ሀሳቤ ባልተገራ አንደበት
ድንገት ይወጣና ተገፍቶ በስሜት
ከቀልቤ ስመለስ ፀፀት ያለብሰኛል
ዝምታ ሰላሜን ደግሞ ያስመኘኛል
ሀሳብ ልቤን ይሙላ ይብሰልሰል መንፈሴ
ይሻግት ይበስብስ ሳይወጣ ከራሴ
ከንቱ ተናግሬ ስህተቴን አልቁጠር
እውነቴ አይሰማ ከውስጤ ይቀበር
ዝምታዬ ይንገስ በዘመን ህይወቴ
ከኔው ይክረምልኝ ድካሜ ብርታቴ
18
ከአንደበት የወጣ ቃል
19
ምትሰሙት አንደበት መንፈስ የሚያድሰው
የምታነቡት ቃል ልብን የሚያክመው
ሀሳብ ነው ረቂቅ ሀሳብ የወለደው
አመታት ቀልቦ ደግሞም ያሳደገው
የሰው ልጅ የሰው ሰው
ስንኞችን ቋጥሮ ቅኔን የሚያፈሰው
ልብን የሚሞላለው ነፍስን የሚያርሰው
መንፈስ ተቆጣጥሮ ስሜት የሚያሞቀው
አይደል በሽፋኑ ከላይ በደረበው
ሲደላው አብቦ ከርሞ በሚደርቀው
ከውጪ ብታየው ብትመረምር ከንቱ
ገላውን ብታውቀው ላይገባህ ስሪቱ
ይልቅ ብናስተውል ከስር መሰረቱ
የሰው ልጅ ሰውነት መጠኑ ልኬቱ
ማሰላሰሉ ነው ጥበብ ብልሀቱ
ወሰን ገደብ አለባ መገለጫ ዉበቱ
የሰውነት ሞገስ ሀይሉ ጉልበቱ
ረቂቅ እውቀቱ የልቦና እምነቱ
ዝንታለም የሚኖር የአዳም እሱነቱ
ሀሳቡ ብቻ ነው ማይሻር እውነቱ
20
መርጦ ማሰብ
21
መርጦ ማሰብ ይቻላል በደንብ ይቻላል፡፡ ክፉውን ከሰውነታችን
ከነፍሳችን እናርቅ፡፡ አንደበታችን ጥሩውን ይመስክር ለክፉ ነገር
ጊዜ አይኑረን፡፡ ሰዎች ያላቸውን መልካም ነገር እንመልከት፡፡
መኞታችን ሁሉ መልካም ይሁን፡፡ ይሁን ብለን ያሰብነውን
እንናገር እንመን እንጠብቅ እንቀበል፡፡
22
በፈጠረው ጌታ ያለው ትልቅ ዋጋ
የሰው ልጅ ክቡር ነው የለበሰ ፀጋ
አምላክ የወደደው ደግሞም የሞተለት
የጠራው ደጋግሞ ሊያድነው በምህረት
ሰውነት ሚስጥር ነው እጅግ የረቀቀ
ከስጋና ከደም ከአካልም የላቀ
ያለም ልብሱን ለብሶ ከአለም ሲመላለስ
ሲወድቅ ሲነሳ የልቡን ለማድረስ
የስጋ የነፍሱ ሙግት ሚያስጨንቀው
ከቁስ የጠጠረ የሰው ልጅ ክቡር ነው
የአካል ህመሙ የመንፈሱ ሁካታ
ሌተቀን ሚያከንፈው ተጠምቶ ለርካታ
እንዲሁ ሚባትል ረፍት የሚርበው
ተፈጥሮው የረቀቀ ያዳም ዘር ድንቅ ነው
ምንም ልብሱ ጎድፎ ለእይታ ቢሸክክ
በበሽታ ማቆ ዝሎ ቢንበረከክ
ከሚታየው መልኩ ቁስ አካሉ ገዝፎ
መንፈሱ ይኖራል ከዚች አለም አልፎ
ሰው መልኩ ያምላክ ነው ረቂቅ ነው ስሪቱ
ከሀሳቡ ነው ያለው የእሱ እሱነቱ
ምንም ደክሞ ቢዝል
ቢታመም ቢቆስል
ባረጀ ድሪቶ ቆሽሾ ባደፈው
ዋጋ አታውጣለት ንቀህ አታራክሰው
23
በደም ተገዝተሀል
24
አቤቱ የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ የሆንክ ፍፁም ፍቅር የሆን አባት
መጀመሪያም መጨረሻም የሌለህ ጌታ ስምህ የህይወት ምንጭ ነው
ሁል ጊዜ ተባረክ፡፡
25
እንደምን አለፍኩት በየቱ ብርታቴ?
እንዴት እዚህ ደረስኩ በየቱ ጉልበቴ?
ብዬ ጠይቅና ራሴው መልሳለው
አቅሜ ስለሆንክ ምሰግና አፈሳለው
ከአይምሮዬ በላይ ገዝፈው የፈተኑኝ
ያስጨነቁኝ ለሊት አልነጋ ብለውኝ
ማያልቁ የመሰሉ እነዛ እለታት
እንደምን አለፉ? ሆኑ ታሪክ ትናንት
ስጋ ነው አካሌ ድካም ነው ልማዴ
ዛሬ ላይ ያቆመኝ አይደል ሀይሌ ክንዴ
መቻሌ አንተ ነህ ማለፌ መቆሜ
የሆንኩት ባንተ ነው የተሳካው ህልሜ
ከእጆችህ አልወጣም ጠብቀኝ ሸሽገኝ
ከምድር ፈተና በጥበብህ አድነኝ
በእጆችህ ስከለል መልኬ ደምቆ አበራ
ምሳሌም ተደረኩ ወድቆም ለሚጣራ
26
ሀይላችን ነህ
27
በኩር አንድ ልጅ ምትክ የሌለውን
እስከ መስጠት ድረስ ልታድን ወደኸን
የፍቅር ቀለም የፍቅር ምስል
ምህረትህ ማያልቅ ሁሉን የምትችል
የማታንቀላፋ ማደክም ማትዝል
ከአይምሮ በላይ ነው ሁሉ ያንስሀል
ሰው ሆነን ዳካማ አፈር ልብሳችን
ከንቱ ምኞታችን ግብር ስራችን
እንዲሁ መረጥከን እንዲሁ ወደድከን
በትኩሱ ደመህ ዋጀኸን አዳንከን
ተገለጠ ለአለም ፍቅር ስጋ ለብሶ
አይሆኑትን ሆኖ ተዋርዶ ኮስሶ
ተርቦ ታርዞ የሾህ አክሊል ለብሶ
የደም ላብ አልቦት አዳነን መልሶ
እጅግ በከበረ በሚደንቅ ጥበብ
ልጅ ያደረከን አምላክን ሳስብ
አልፈራም ህይወትን የስጋን መከራ
መንፈስህ ነውና ሁሌ ከኛ ጋራ
28
ፍቅር ምን ይመስላል?
እናት ልጇን ወደደች የእሱን ስቃይ ሁሉ ለእኔ ያድርገው አለች እኔ
ልቅደም አለች፡፡ ህይወቷን በሙሉ እሱን ስታስቀድምጥ መንገዱን
ስታሳምር ትኖራለች ፡፡ አባትም እንዲሁ ልጁን ባይኑ ካየቀን ጀምሮ
ስለልጁ ብዙ ያልማል ያግዘዋል ያበረታዋል፡፡
29
በዋጋ ገዝተኸው ንብረት ያረከውን
30
አዎ ወድታለው ብዬ ፈርሜያለው
አዲስ ነገር የለም ዛሬም ቃሌ ያው ነው
ያየኝ የታዘበኝ ይጠራጠረኛል
በፍቅርሽ መያዜን ፍራት ነው ይለኛል
እውነት ፈራለው እስክትወጣ ነፍሴ
ስጋ እኮ አይደለም ስጋት ነው ልባሴ
ውስጤ ተብረክርኮ እግሮቼ እስኪክዱኝ
ፈርቼ ወደድኳት እናንተው ፍረዱኝ
እኔን ያሸነፈኝ ውበቷ መስሏቸው
ምኗ ቢማርክህ ብለው ማሾፋቸው
ተሸነፍኩ ተረታው አፈቀርኳት ያልኩት
ጦሯን ሰግቼ ነው እጄን የሰጠሁት
ከጉያዋ ሆኜ ከቅፏ ሳልወጣ
ስራዋን እያየው ሀይሏን ለባላንጣ
እንዴት እኔን ልሁን ማንነት ምርጫዬን
ህመሟ ነኝና ላፍቅራት ስጋቴን
31
ፍርሀት አርግዞ ፍርሀት የወለደው ፍቅር
አፈቅራታለው ነፍሴን ስለምወድ መኖር ስላልጠገብኩ
አፈቅራታለው፡፡ ህይወቴን በወደድኩት ልክ ወዳታለው
እታዘዛታለው ራሴን እሰጣታለው፡፡ ማንነቴን የካድኩት ለእሷ
ነው፡፡ የምወደውን የጠላውት የምናገረውን የመረጥኩት እምነቴን
እውነቴን የካድኩት ለእሷ ነው፡፡
32