Professional Documents
Culture Documents
ከአበራ ሣህሌ
እንደመግቢያ
ማሞ ውድነህ በሞት የተለዩን የካቲት 23 ቀን 2004 ዓ.ም ነው። ታዲያ ይህ ፅሑፍ አሁን
ሲቀርብ “ምነው ከረፈደ?” የሚል ጥያቄ ያስከትል ይሆናል። በርግጥ ፅሑፉ ወረቀት ላይ
ከሰፈረ ቆይቷል። ለሁለት ሳምንታዊ ጋዜጦችም ልኬው ነበር። አንዱ እገኝበታለሁ ያለው
አድራሻ ልክ ባለመሆኑ መልዕክቱ ለላኪው ተመልሷል። ሌላኛው ደግሞ አላወጣውም።
በጋዜጦቹ ማሳበቤ እንዳለ ሆኖ ስንፍናም ድርሻ ነበረው። ይሁንና አሁንም ቢሆን ፅሑፉ
ስለአንድ ትልቅ የሃያኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊ የብዕር ሰው ግንዛቤ ያስጨብጣል
በሚል እምነት ለተለያዩ ድረ ገፆች ልኬዋለሁ።
እነሆ ታሪክ
በልጅነቴ ጊዜያት ከእኛ ጋር ትኖር የነበረችው ከገጠር የመጣች ዘመዳችን በድብቅ ከአንድ
መጽሐፍ ላይ ገፆችን እየገነጠለች ለእሳት ማቀጣጠያነት ታውላቸው ነበር። መፅሐፉ
በየጊዜው እየተገነጣጠለ ገፆቹ ሳስተው ሽፋኑ ብቻ ቀርቷል። ይህንን ነገር አባቴ ቢያውቅ
ቤቱ በአንድ እግሩ እንደሚቆም ግልጽ ነው። በእስራኤሎች ተዓምረኛነት የሚያምነውና
ከአይሁዶች ጋር የተያያዘ ርዕስ ጉዳዬ የሚለው አቶ ሣህሌ ያንን ሥራ እንደጸሎት
መጽሐፍቱ ነበር የሚያየው። ያንብበው አያንብበው በእርግጠኛነት መናገር አልችልም።
1
ከሚገኘው አበጀ የመጻሕፍት አከፋፋይ መደብር ነበር። ያ አከፋፋይ መፃሕፍቶቹን
ያሳትም ወይ ከሳቸው ጋር ውል ይግባ የሚያሳስበኝ ጉዳይ አልነበረም።
በገበያ ዘንድ ተወዳጅነት ከነበራቸው መካከል “የካይሮው ጆሮ ጠቢ” ፣ “ጊለን የክፍለ ዘመኑ
ሰላይ” ፣ እንዲሁም “የበረሃው ተኩላ” ዋነኞቹ ናቸው። የነዚህ መፃሕፍት የሽፋን ስዕልና
ወረቀት፣ መጠናቸው እንዲሁም ገፆቻቸው ተመሳሳይ ነበር። ከነዛ ቀደም ብለው የወጡት
“ዘጠና ደቂቃ በኢንቴቤ” እና “የኦዴሳ ማህደር”ም እንደዛው። “ኦዴሳ”- ያኔ ባጭሩ
እንደምንጠራው - ፈላጊው ብዙ ነበር። በቀላሉም የሚገኝ አልነበረም። ሽፋኑ ላይ የግብጹ
ናስር፣ የዩኤሱ ኬኔዲ፣ የእስራኤሉ ዴቪድ ቤንጎሪዮን፣ እንዲሁም አንድ እስካሁን
የማላውቀው ሰው አንገቶች ነበሩ።
2
ኧርቪንግ ዋለስ ጋር በእንግሊዝኛ መፃሕፍት አንባቢያን ዘንድ ተፈላጊነት ከነበራቸው
ደራሲያን አንዱ ነበር (በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ አብዛኞቹ በእነ ኤፍሬም እንዳለ ፣
ፋንታሁን ዮሴፍ ፣ አውግቸው ተረፈ ፣ ታደሰ መለሰና በሌሎችም በአማርኛ
ተተርጉመዋል።) ቀጥሎ የሳበኝ “የእኛ ሰው በደማስቆ” ሲሆን ትንሽ መጽሐፍ ከመሆኑ
በተጨማሪ “የዘመኑ ምርጫ”ም ነበር። መጽሐፉን ማግኘት አይደለም ለአንባቢ ለእኛም
አስቸጋሪ እንደነበር አስታውሳለሁ። ለእኔ ሶስተኛ መጽሐፍ “አሉላ አባ ነጋ” ነበር። ጥቅጥቅ
ብለው የተጻፉ መፃሕፍትን ለማንበብ ካለኝ ስልቹነት አንፃር ያንን አንብቤ መጨረሴ
ይገርመኛል። ስለጽሁፉ ጥቅጥቅነት ከወሬ ባላለፈ እንደሰማሁት የገፆቹን ብዛት በዛውም
የሕትመት ወጪውን ለመቀነስ ታስቦ በዛ መልኩ እንደወጣ ነው። በንጉሱ ዘመን አሉላ አባ
ነጋ በቴአትር ተሰርቶ ቀርቧል።
3
ፕሮግራም በተጀመረበት ወቅት ከአዘጋጆች አንዱ ነበርኩ። እያንዳንዳችን የቡድኑ አባላት
በዝግጅቱ ለመስራት የምናስባቸውን ሰዎች ከአሳማኝ ምክንያት ጋር በጽሑፍ ማቅረብ
ነበረብን። እኔ ማሞ ውድነህን ለመስራት ያቀረብኩት ዕቅድ ተቀባይነት በማግኘቱ
እሳቸውን በቅርበት ለማወቅ መንገድ ከፍቶልኛል።
ማሞና ባለቤታቸው በትዳር ህይወት የቆዩት ከአንድ ኢትዮጵያዊ አማካይ የሕይወት ዘመን
አይተናነስም። ለአምሳ ሁለት ዓመት አብረው በመኖራቸው በርካታ የልጅ ልጆችን
ለማየት ታድለዋል። ባለትዳሮቹ ግን ከባልና ሚስትነት ይልቅ ጓደኝነት አልፎ አልፎም
የወንድምና እህት ፉክክር ይታይባቸዋል። በወቅቱ ያደረግነው ቃለ ምልልስ ሕልፈታቸውን
አስመልክቶ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከሳምንታት በፊት ባስተላለፈው ዝግጅት ላይ
በቅንጭብ ቀርቧል።
አንጋፋው የብዕር ሰው ከ60 በላይ መጻሕፍትን ጽፈዋል። አሁን ባለው መረጃ መሰረት 54
መጻሕፍትን አ-ሳ-ት-መ-ዋ-ል። ይህ ኢትዮጵያ ውስጥ ክብረወሰን ነው። ሁለተኛ የሚወጣ
ካለ የዚህን ግማሽ ማሳተሙን እጠራጠራለሁ። ማሳተም ቀላል ቋንቋ ነው። ነገር ግን
4
መጽሐፍ ቀርቶ መጽሔት እና ጋዜጣ ለማሳተም ያለው ውጣ ውረድ ስስ ቆዳ ላላቸው
የሚታዘዝ አይደለም።
5
ከማሞ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኘነው በጀርመን ኤምባሲ በተደረገ የምሳ ግብዣ ላይ
ነው። ወ/ሮ አልማዝ የሃገር ልብሳቸውንና ሳቃቸውን ይዘው መጥተዋል። ጋሽ ማሞም
ከእንግዶች ጋር መጫወታቸውን ይዘዋል። ለእኔም የአቅሜን ያህል የአየር ሰዓት
አልነፈጉኝም። በማሞ ውድነህ ስራዎች ላይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋሟት የመመረቂያ
ሥራ(thesis) የሰሩ እንዳሉ አውቃለሁ። ለሙያዊ ትንታኔ እነሱን ደጅ መጥናት
ያስፈልጋል። እኔ ግን ይህን ያህል አውቃቸዋለው።
ሀዘኑ እጅግ መራር ለሚሆንባቸው ባለቤታቸው ወ/ሮ አልማዝ ገብሩ እንዲሁም በሃገር
ውስጥና በውጭ ሃገር ለሚኖሩ ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ።
እግዜር ይስጥልኝ ጋሽ ማሞ!