Professional Documents
Culture Documents
የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር አፈፃፀም ሞዴል መመሪያ ቁጥር …… ../2010
.
ዓ ም
/የተሻሻለ/
u²=IU መሠረት በተለያዩ የምርትና የአገልግሎት ሙያዎች K}WT\ u`ካታ ኢንተርፕራይዞች አስፈላጊው
የማደራጀት፣ የማሰልጠን፣ የፋይናንስና እንዲሁም የማምረቻና የመሸጫ x ታ ›p`x„‹ እ“ የገበያ ƒee` ድጋፎች
እንዲያገኙ በማድረግ ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጠርና ለድህነት p’d ፕሮግራሙ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረከተ
በመሆኑ፣ የተሰጡት ድጋፎች ኢንተርፕራይዞቹ በየዕድገት ደረጃቸው ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች መፍትሄ በመስጠት
ረገድ ዉስንነት ታይቶባቸዋል:: እንዲሁም ለኢንዱስትሪ MTƒ SW[~ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች MTƒ“
መስፋፋት እንደሆነ በኢንዱስትሪ MTƒ ሥትራቴጂ ሠነድ ላይ በግልጽ የተቀመጠ ቢሆንም እስከ አሁን ተግባራዊ
በማድረግ ሂደት እንደታየው ለኢንተርፕራይዞቹ ሲደረግ የነበረው ድጋፍ ከአንድ የዕድገት ደረጃ ¨ደ ሌላ የዕድገት ደረጃ
ለመሸጋገር የሚያደርጉትን ጥ[ት በ T በረታ ƒ ረገድ የተሟላ አፈጻጸም ያልነበረው በመሆኑ ምክንያት በ 2003 ዓ.ም
የወጣው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ሥትራቴጂ የድጋፍ ማዕቀፍና የአፈፃፀም ሥ M„‹ ሠድን
SW[ƒ በማድረግ ኢንተርፕራይዞችን እንደየዕድገት ደረጃቸው በመክፈል የተቀመጡ c=J”& እ’`c<U Ue[ታ ወይም
ጀማሪ/Start-Up/ ደረጃ፣ ታዳጊ> ወይም መስፋፋት/Growth/ ደረጃ እ“ Swnƒ /Maturity/ ደረጃ “†¨<::
በመሆኑም ይህንን የኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ክፍፍል SW[ƒ በማድረግ ኢንተርፕራይዞቹ በየዕድገት
ደረጃቸው የሚያስፈልጓቸው ድጋፎች ለመስጠት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ መመሪያዎችና ማኑዋሎች ተዘጋጅተው ሥራ
ላይ ከዋሉ የቆዩ ቢሆንም ኤጄንሲው ከተሰጠው ተልዕኮ እና ካለው ወቅታዊ አደረጃጀት አንፃር የነበሩ ችግሮችን
በመፈተሽ ከኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳ፣ አሳታፊ፣ ፍትሃዊና ውጤታማ በሆነ መልኩ ድጋፉን ለማቅረብ
እንዲሁም ይበልጥ ለአሰራር በሚያመች መልኩ ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ
ቁጥር 374/2008 አንቀጽ 14 መሠረት ይህ የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር
ሞዴል መመሪያ ተሸሽሎ ተዘጋጅቷል::
1
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ ሞዴል መመሪያ “የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ሽግግር አፈፃፀም ሞዴል
መመሪያ ቁጥር ……. /2010” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል::
2. ትርጓሜ
በዚህ ሞዴል መመሪያ ውስጥ የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር፤
1) ”ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ” ማለት የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞችን
ጨምሮ እስከ አምስት ሰዎች ቀጥሮ የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር
በአገልግሎት ዘርፍ ከብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ወይም በኢንዱስትሪ ዘርፍ ከብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ)
ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው:፡
2) ”አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ” ማለት የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞችን
ጨምሮ ከስድስት እስከ ሰላሳ ሰዎች የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር በአገልግሎት
ዘርፍ ከብር 50,001 (ሃምሳ ሺህ አንድ) እስከ 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ወይም በከተማ ግብርና፣
በባህላዊ ማዕድን ማምረት ሥራና በግንባታ ዘርፍ ከብር 100,001 (አንድ መቶ ሺህ አንድ) እስከ 1,500,000
(አንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሺ) ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው::
3) “የኢንተርፕራይዝ ደረጃ ሽግግር” ማለት አንድ ኢንተርፕራይዝ ባለበት የዕድገት ደረጃ የሚሰጠውን ድጋፍ
ተጠቅሞ በገበያ ላይ በዋጋ፣ በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳሪ ሆኖ የቀጣይ የዕድገት ደረጃ የሽግግር
መስፈርቶቹን በማሟላት መሸጋገር ሲችል ነው::
4) “የምሥረታ/ጀማሪ ደረጃ” ማለት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ለመመሥረት ፍላጎት ያላቸው
ሰዎች እና ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት በየደረጃው የሚጠበቅባቸውን ትምህርት በማጠናቀቅና በማህበር
እና በግለሰብ በሕግ አግባብ ተደራጅተው የራሳቸውን ቁጠባና ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ብድር በመውሰድ
ወደ ሥራ የገቡትን የሚያካትት ነው:: የምሥረታ /ጀማሪ ደረጃ ኢንተርፕራይዝ ሕጋዊ አቋም ይዞ
የማምረትና አገልግሎት የመስጠት ተግባር የሚጀምርበት ነው::
5) “የታዳጊ/መስፋፋት ደረጃ” ማለት አንድ ኢንተርፕራይዝ የሚሰጠውን ድጋፍ ተጠቅሞ በገበያ ላይ በዋጋ፣
በጥራትና በአቅርቦት ተወዳዳሪ ሲሆንና ትርፋማነቱ በቀጣይነት ሲረጋገጥ ነው:: በዚህ ደረጃ ያለ
ኢንተርፕራይዝ በምሥረታ ደረጃ ከነበረው ቀጥሮ የሚያሠራው የሰው ኃይል ቁጥርና የጠቅላላ ሀብት መጠን
ዕድገት ይኖረዋል:: በተጨማሪም ኢንተርፕራይዙ የሂሳብ አያያዝ ሥርዓት የሚጠቀም ይሆናል::
6) “የመብቃት ደረጃ” ማለት አንድ ኢንተርፕራይዝ የሚሰጠውን ድጋፍ ተጠቅሞ በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪና
ትርፋማ ሆኖ የገበያ ድርሻውን ለማሳደግ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት በሥራ ላይ ካዋለና ለዘርፉ
የተቀመጠውን ትርጓሜ መሥፈርት በማሟላት ወደ ታዳጊ መካከለኛ ሲሸጋገር ወይንም በአለበት ደረጃ
በመሆን በገበያ ውስጥ ተወዳዳሪና ትርፋማ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን ነው::
2
7) “ታዳጊ መካከለኛ ደረጃ” ማለት ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የተቀመጠውን የሰው ሃይልና ጠቅላላ ሃብት
መጠን የመብቃት የዕድገት ደረጃ በማለፍ ወደ ኩባንያ ደረጃ የተሸጋገረ የኢንተርፕራይዝ የዕድገት ደረጃ
ነው::
8) “ቋሚ የሥራ ዕድል” ማለት የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ ፈጥረው የሚሰሩ ወይም በሌሎች ድርጅቶች
ውስጥ ከአንድ ዓመት ላላነሰ ጊዜ በቋሚነት ተቀጥረው በፔይሮል ክፍያ በማግኘት የሥራ ዕድል
የተፈጠረላቸው ማለት ነው::
9) “ጊዜያዊ የሥራ ዕድል” ማለት በጥሪት ማፍሪያ ፕሮጀክቶች የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ በጊዜያዊነት
በማቋቋም ወይም በፔይሮል ክፍያ በማግኘት ከአንድ ዓመት ላነሰ ጊዜ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ማለት
ነው::
10) "የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት" ማለት የኢንተርፕራይዞቹን ችግር የለየና በፍላጎት ላይ
የተመሠረተ የተሟላ መረጃ ማደራጀትና የመስጠት፣ ሥልጠና ድጋፍ፣ የቴክኖሎጂ ልማት፣ ግብይት፣ ምርጥ
ተሞክሮ ቅመራና ማስተላለፍን የሚያካትት ድጋፍ ነው፡፡
11) "የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና" ማለት በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፎች ለተሠማሩና
ለሚሠማሩ የኀብረተሰብ ክፍሎች፣ ባለሙያዎች አንድን ምርት ወይም አገልግሎት በብቃት ለማቅረብ፣
ጥራትና ምርታማነትን በቀጣይነት ለማሻሻል፣ የፈጠራ ሥራዎችን ለማበረታታት አመለካከት፣ ዕውቀትና
ክህሎት በማሳደግ በተሰማሩበት ወይም በሚሰማሩበት መስክ ላይ ዕሴትን በመጨመር ልማትን ለማፋጠን
እንዲያስችል የሚሰጥ ሙያዊ ሥልጠና ነው፣
12) "የንግድ ሥራ አመራር ሥልጠና" ማለት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አዋጪ የንግድ መስክን
በመምረጥ፣ በማቋቋምና በመምራት ሂደት ውስጥ በማቀድ፣ በማደራጀት፣ በመምራት፣ በማስተባበርና
በመቆጣጠር ውጤታማ እንዲሆኑ የሚሰጥ ሥልጠና ነው፣
13) “የገበያ ትስስር” ማለት ለአንድ ኢንተርፕራይዝ የገበያ ዕድል ለመፍጠር ከመንግስት ተቋማት ፕሮግራሞችና
ፕሮጀክቶች በአገር ውስጥ ከሚገኙ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ጋር በግብዓት፣ በምርትና
አገልግሎት አቅርቦት በጎንዮሽና በተዋረድ ግንኙነት የሚፈጠር የግብይት ወይም የሥራ ትስስር ነው::
14) “ጠቅላላ ሃብት” ማለት የአንድ ኢንተርፕራይዝ የተከፈለ እና በብድር የተገኘ ሀብት ነው::
15) ”ጠቅላላ ካፒታል” ማለት ህንፃን ሳይጨምር ከኢንተርፕራይዙ ጠቅላላ የቢዝነሱ ሀብት ላይ ዕዳው ተቀንሶ
የሚገኝው ካፒታል ማለት ነው፡፡
16) “የምርት ወይም የአገልግሎት ማስተዋወቂያ ዘዴዎች” ማለት ምርትን ወይም አገልግሎትን ለማስተዋወቅ
የመገናኛ ብዙሃን፣ ንግድ ትርዒትና ባዛር፣ ድረ-ገፅ፣ በራሪ ወረቀት፣ ቢዝነስ ካርድ፣ ቋሚ የማስታወቂያ ሰሌዳ፣
ማሸጊያ እና የመሳሰሉትን ያካትታል::
17) “ኢንዱስትሪ ዘርፍ” ማለት ማኑፋክቸሪንግ (በጥቃቅን ብቻ)፣ ከተማ ግብርና፣ ባህላዊ ማዕድን እና ግንባታ
ዘርፎችን ያካትታል፡፡
18) “አገልግሎት ዘርፍ” ማለት ከኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጪ ሆኖ አገልግሎት በመስጠትና በ ሀገር ውስጥ ምርቶች
ንግድና ጥሬ ዕቃ አቅርቦት ሥራ ላይ የሚሰራ የሥራ ዘርፍ ነው::
3
19) "የሙያ ብቃት ምዘና" ማለት አንድ ባለሙያ በተዘጋጀው የሙያ ደረጃ መስፈርት መሰረት የሚጠበቅበትን
ብቃት መያዙ የሚረጋገጥበት ሥርዓት ነው።
20) "ቴክኖሎጂ” ማለት ዕውቀትን፣ ክህሎትን፣ መሣሪያዎችን እና እነዚህኑ ለመጠቀም የሚያስችሉ
ማኑዋሎችን፣ የአሰራር መመሪያዎችና አደረጃጀትን ያጠቃልላል፡፡
21) በዚህ መመሪያ ውስጥ በወንድ ፆታ የተገለፀው የሴትንም ፆታ ያካትታል፡፡
3. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ ሞዴል መመሪያ በኢትዮጵያ ከተሞች በሚገኙ የከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ
ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
4. ዓላማ
በዘርፍ ልማት ለተሰማሩ የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ለመወሰን፣ ለማሸጋገርና
የኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃን ታሳቢ ያደረጉ ድጋፎች ለመስጠት ነው፡፡
5. መርሆዎች
ክፍል ሁለት
4
(1) የጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ 3
እስከ 5 ሰዎች እንዲሁም በዓመት ውስጥ በጊዜያዊ እስከ 3 ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ መሆን
አለበት፣
(2) የአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ 6-
10 ሰዎች እንዲሁም በዓመት ውስጥ በጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከ 4 እስከ 6 ሰዎች የሥራ ዕድል
የፈጠረ መሆን አለበት::
2) በካፒታል መጠን
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
(1) የካፒታል መጠኑ ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከብር 50,001 እስከ 75,000 መሆን አለበት፣
(2) የካፒታል መጠኑ ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከብር 120,001 እስከ 500,000 መሆን አለበት::
(3) ጥቃቅን ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ በብድር ካገኘው ገንዘብ 40% እና በላይ ወይም ከጠቅላላ
የሃብት ውስጥ 20% እና በላይ ለቋሚ ንብረት ያዋለው መሆን አለበት::
3) በገበያ መጠን
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
(1) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 120,001 እስከ 200,000 መሆን
አለበት፣
(2) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 200,001 እስከ 300,000 መሆን
አለበት፣
(3) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ከዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 30% በላይ፣ በብረታ ብረትና እንጨት ንዑስ ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 50% በላይ እና በተቀሩት ዕድገት ተኮር ንዑሳን ዘርፎች የተሰማሩ
5
ኢንተርፕራይዞች ከ 70% በላይ የተገኘው ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ መሆን
አለበት፣
(4) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 30% በላይ እና በተቀሩት የዕድገት ተኮር ንዑሳን ዘርፎች የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ከ 70% በላይ የተገኘው ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ መሆን
አለበት፣
(5) ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ ለሌሎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ
ኮንትራት ቢያንስ 1 ጊዜ የገበያ ትስስር የፈጠረ መሆን አለበት፣
(6) ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ ምርት ለማስተዋወቅ ቢያንስ ሦስት ዓይነት ውጤታማ
የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን መጠቀም አለበት፣
(7) ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ በየደረጃው በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ቢያንስ
አንድ ጊዜ የተሳተፈ መሆን አለበት::
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
(1) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 80,001 እስከ ብር 120,000 መሆን
አለበት፣
(2) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 120,001 እስከ 200,000 መሆን
አለበት፣
(3) የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ ከ 70% በላይ የተገኘው
ሽያጭ ከመንግሥት የገበያ ትስስር ውጪ መሆን አለበት፣
(4) ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ ለሌሎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ
ኮንትራት ቢያንስ 1 ጊዜ የገበያ ትስስር የፈጠረ መሆን አለበት፣
(5) ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ ምርትና አገልግሎቱን ለማስተዋወቅ ቢያንስ ሦስት
ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን መጠቀም አለበት::
4) በትርፋማነት
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፤
(1) በዓመቱ ካደረገው ሽያጭ ቢያንስ 10 በመቶ የትርፍ መጠን መሆን አለበት፣
(2) ሥራውን ለማስፋፋት ያዋለው ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እና/ ወይም የቁጠባ መጠን ከተጣራው
ካፒታል ከ 15% በላይ መሆን አለበት፡፡
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፤
(1) በዓመቱ ካደረገው ሽያጭ ቢያንስ 10 በመቶ የትርፍ መጠን መሆን አለበት፣
(2) ሥራውን ለማስፋፋት ያዋለው ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እና/ ወይም የቁጠባ መጠን ከተጣራ
ካፒታል ከ 15% በላይ መሆን አለበት::
5) የኢንተርፕራይዙ ምርታማነት
6
(ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ካለው ሙሉ
የማምረት አቅም 70% እና በላይ መጠቀም አለበት፣
(ለ) ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ አባላት ወይም ቋሚ ሰራተኞች መካከል ቢያንስ 50% የሙያ
ብቃት ምዘና ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ያላቸው መሆና አለባቸው::
8) በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
ለጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፡-
ሀ) ኢንተርፕራይዙ ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና
ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና
አዋጭ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ ለመሆን ቅድመ ዝግጅት ያደረገ መሆን አለበት::
ለ) ኢንተርፕራይዙ ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም አገልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ
50% በኢነርጂ ብቻ የሚንቀሳቀስ መሆን አለበት::
9) ግዴታን ስለመወጣት
ለጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፡-
7
ሀ) ኢንተርፕራይዙ የሚጠበቅበትን ዓመታዊ ግብር መክፈል አለበት፣
ለ) ኢንተርፕራይዙ ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ዕድሳት ማካሄድ አለበት::
2) በካፒታል መጠን
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
(1) የካፒታል መጠኑ ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከብር 75,001 እስከ 100,000 መሆን አለበት፣
(2) የካፒታል መጠኑ በከተማ ግብርና፣ በባህላዊ ማዕድን ማምረት ሥራ ወይም በግንባታ ዘርፍ
የተሰማራ አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከብር 500,001 እስከ 1,500,000 መሆን አለበት፣
(3) ጥቃቅን ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ በብድር ካገኘው ገንዘብ 50% እና በላይ ወይም ከጠቅላላ
የሃብት ውስጥ 25% እና በላይ ለቋሚ ንብረት ያዋለ መሆን አለበት፣
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፣
(1) የካፒታል መጠኑ ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ከብር 40,001 እስከ ብር 50,000 መሆን አለበት፣
(2) የካፒታል መጠኑ ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ከብር 200,001 እሰከ ብር 500,000 መሆን አለበት፣
(3) ጥቃቅን ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዙ በብድር ካገኘው ገንዘብ 30% እና በላይ ወይም ከጠቅላላ
የሃብት ውስጥ 15% እና በላይ ለቋሚ ንብረት ያዋለው መሆን አለበት::
3) በገበያ መጠን
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
8
(1) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 200,001 እስከ 300,000 መሆን አለበት፣
(2) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 1,000,001 እስከ 2,000,000 መሆን
አለበት፣
(3) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ከዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 35% በላይ፣ በብረታ ብረትና እንጨት ንዑስ ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 60% በላይ እና በተቀሩት ዕድገት ተኮር ንዑሳን ዘርፎች የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ከ 70% በላይ የተገኘው ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የተገኘ መሆን
አለበት፣
(4) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ቢያንስ ከ 35% በላይ በተቀሩት የዕድገት ተኮር ንዑሳን ዘርፎች የተሰማሩ
ኢንተርፕራይዞች ከ 70% በላይ የተገኘው ሽያጭ ከመንግስት የገበያ ትስስር ውጪ የተገኘ መሆን
አለበት፣
(5) ኢንተርፕራይዙ ለሌሎች ኢንተርፕራይዞች በንዑስ ኮንትራት በዓመት ቢያንስ 2 ጊዜ የገበያ ትስስር
የፈጠረ መሆን አለበት፣
(6) ኢንተርፕራይዙ ምርት ለማስተዋወቅ ቢያንስ አምስት ዓይነት ውጤታማ የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን
መጠቀም አለበት፣
(7) ኢንተርፕራይዙ ለደረጃው በተዘጋጀ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ሁለት ጊዜ የተሳተፈ መሆን አለበት፡፡
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
(1) ለጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 120,001 እስከ ብር 200,000 መሆን
አለበት፣
(2) ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ከብር 600,001 እስከ ብር 1,200,000 መሆን
አለበት፣
(3) ከኢንተርፕራይዙ ዓመታዊ የሽያጭ መጠን ውስጥ ኢንተርፕራይዞች ከ 70% በላይ የተገኘው ሽያጭ
ከመንግሥት የገበያ ትስስር ውጪ መሆን አለበት፣
(4) ኢንተርፕራይዙ ለሌሎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በንዑስ ኮንትራት ቢያንስ 1 ጊዜ
የገበያ ትስስር የፈጠረ መሆን አለበት፣
(5) ኢንተርፕራይዙ ምርትና አገልግሎቱን ለማስተዋወቅ ቢያንስ ሦስት ዓይነት ውጤታማ
የማስተዋወቂያ ዘዴዎችን መጠቀም አለበት፡፡
4) በትርፋማነት
ሀ) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
(1) በዓመቱ ካከናወነው ሽያጭ ቢያንስ 15 በመቶ የትርፍ መጠን መሆን አለበት፣
(2) ሥራውን ለማስፋፋት ያዋለው ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እና/ ወይም የቁጠባ መጠን ከተጣራ
ካፒታል ከ 20% በላይ መሆን አለበት፣
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
9
(1) በዓመቱ ካከናወነው ሽያጭ ቢያንስ 15 በመቶ የትርፍ መጠን መሆን አለበት፣
(2) ሥራውን ለማስፋፋት ያዋለው ተጨማሪ ኢንቨስትመንት እና/ ወይም የቁጠባ መጠን ከተጣራ
ካፒታል ከ 20% በላይ መሆን አለበት::
5) የኢንተርፕራይዙ ምርታማነት
ጥቃቅንም ሆነ አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፡-
(1) በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ ካለው ሙሉ
የማምረት አቅም ቢያንስ 80% መጠቀም አለበት፣
(2) ለሚያመርታቸው ምርቶችና ለሚያቀርባቸው አገልግሎቶች ዘመናዊ የሥራ አመራርን የተከተለ
የጥራት ቁጥጥር ሥርዓት የዘረጋ መሆን አለበት፣
(3) ለገቢ ወይም ለወጪ ምርቶች የሚውሉ ግብዓቶችን ወይም ገቢ ምርቶችን የሚተካ ምርት
ማምረት አለበት፣
(4) ከአባላት ወይም ቋሚ ሠራተኞች መካከል ቢያንስ 60% የሙያ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ የምስክር
ወረቀት ያላቸው መሆን አለባቸው::
10
(4) የማምረቻ ማዕከል ተጠቃሚ ከሆነ የኪራይ ውዝፍ ዕዳ የሌለበትና ከማዕከሉ ከመውጣቱ በፊት
አስፈላጊውን የፋይናንስና የማምረቻ ቦታ ቅድመ ዝግጅት ያደረገ መሆን አለበት፣
(5) የተፈጠረለትን የገበያ ትስስር ዕድል በልማታዊ መንገድ የሚጠቀም መሆን አለበት፣
8) በቴክኖሎጂ አጠቃቀም
(ሀ) ኢንተርፕራይዙ ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማሻሻል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ተቋማት፣ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ተቋማት የሚሰራጩ ተፈላጊና አዋጭ
ቴክኖሎጂዎችን ተጠቃሚ መሆን አለበት፣
(ለ) የምርትና አገልግሎት ጥራትን ለመቆጣጠር የሚያስችል ወቅታዊና የተሻሻለ አሠራር ተጠቃሚ መሆን
አለበት፣
(ሐ) ኢንተርፕራይዙ ከሚጠቀምባቸው የማምረቻ ወይም አገልግሎት መስጫ መሣሪያዎች ውስጥ ቢያንስ
75% በኢነርጂ ብቻ የሚንቀሳቀስ መሆን አለበት::
9) ግዴታን ስለመወጣት
ሀ) ኢንተርፕራይዙ የሚጠበቅበትን ዓመታዊ የገቢ ግብር መክፈል አለበት፣
ለ) ኢንተርፕራይዙ ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ዕድሳት ማካሄድ አለበት፣
ሐ) የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ የሚጠበቅባቸው ኢንተርፕራይዞች የተመዘገቡ መሆን አለባቸው፡፡
8. ከመብቃት ወደ ታዳጊ መካከለኛ ደረጃ የሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች ሊያሟሉዋቸው የሚገቡ
ዝርዝር መስፈርቶች
1) በሥራ ዕድል ፈጠራ
ሀ) በከተማ ግብርና፣ በባህላዊ ማዕድን ማምረት ሥራ እና በግንባታ ዘርፎች የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ
የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን ጨምሮ ከ 30 በላይ ሰዎች መሆን አለበት፣
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ የፈጠረው ቋሚ የሥራ ዕድል የኢንተርፕራይዝ አባላቱን
ጨምሮ ከ 30 በላይ ሰዎች መሆን አለበት፣
ሐ) በዓመት ውስጥ በጊዜያዊነት የፈጠረው የሥራ ዕድል በከተማ ግብርና፣ በባህላዊ ማዕድን ማምረት ሥራ
ወይም በግንባታ ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ ከ 8 ሰዎች በላይ፣ በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ
ኢንተርፕራይዝ ደግሞ ከ 5 ሰዎች በላይ መሆን አለበት::
2) በካፒታል መጠን
ሀ) በከተማ ግብርና፣ በባህላዊ ማዕድን ማምረት ሥራ፣ በግንባታ ዘርፍ የተሰማራ
ኢንተርፕራይዝ፤
(1) የካፒታል መጠኑ ከብር 1.5 ሚሊየን በላይ መሆን ይኖርበታል::
(2) ኢንተርፕራይዙ በብድር ካገኘው ገንዘብ ለቋሚ ንብረት ያዋለው 70% እና በላይ ወይም ከጠቅላላ
የሃብት መጠን ውስጥ 50% እና በላይ መሆን ይኖርበታል::
ለ) በአገልግሎት ዘርፍ የተሰማራ ኢንተርፕራይዝ፤
11
(1) የካፒታል መጠኑ ከብር 500,000 በላይ መሆን ይኖርበታል::
(2) ኢንተርፕራይዙ በብድር ካገኘው ገንዘብ ለቋሚ ንብረት ያዋለው ከ 40% በላይ ወይም ከጠቅላላ
የሃብት መጠን ውስጥ 30% እና በላይ መሆን ይኖርበታል::
4) ግዴታን ስለመወጣት
ሀ) ኢንተርፕራይዙ የሚጠበቅበትን ዓመታዊ የገቢ ግብር መክፈል አለበት፣
ለ) ኢንተርፕራይዙ ዓመታዊ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ ዕድሳት ማካሄድ አለበት፣
ሐ) አስፈላጊውን የደረጃና የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ያገኘ መሆን አለበት፡፡
ለ) ሕጋዊ አቋም እንዲኖራቸው ማድረግ፡ ህጋዊ አደረጃጀት፣ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር
እንዲኖራቸው መደገፍ አለባቸው፣
ሐ) የቢዝነስ ሥራ አመራር (የኢንተርፕርነርሽፕና ሂሳብ አያያዝ) ብቃት እንዲኖራቸው ሥልጠና መስጠት፣
የተለያዩ የሂሳብ ማኑዋሎችና ሠነዶች እንዲኖሩዋቸው መደረግ አለበት፣
መ) ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንዲችሉ የክህሎትና የቴክኒክ ሥልጠናዎችን መሠጠት አለበት፣
12
ሠ) የአካባቢ ገበያን በሰፊው እንዲጠቀሙ መደገፍ አለባቸው፡፡
ክፍል ሦስት
13
ሀ) ኢንተርፕራይዞችን እንደየዕድገት ደረጃቸው የድጋፍ ማዕቀፎች አፈፃፀም መከታተልና በሂደትም
እንዲሻሻል ማድረግ፣
ለ) የድጋፍ ማዕቀፎችን ለማስፈፀም የሚረዱ መመሪያዎች እና ማኑዋሎች አተገባበር ላይ ክትትል
ማድረግና አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት አለበት፣
ሐ) የኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ የተመለከቱ መረጃዎችን የማሰባሰብ፣ የማጠናቀርና የማሰራጨት
ሥራ ያከናውናል፣
መ) በዚህ መመሪያ መሰረት ከየክልሉ የተመረጡ የላቀ አፈጻጸም ያላቸውን ወደ ታዳጊ መካከለኛ የተሸጋገሩ
ኢንተርፕራይዞች ዕውቅና እና የምስክር ወረቀት ይሰጣል፣
ሠ) ወደ ታዳጊ መካከለኛ የተሸጋገሩ የላቁ ኢንተርፕራይዞች በፌደራል ደረጃ እውቅና እና የምስክር ወረቀት
ይሰጣል፣
ረ) ወደ አነስተኛ ማኑፋክቸሪግ የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞችን ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዳስትሪዎች
አጀንሲ ወይም በየደረጃው ላሉ መዋቅሮች ፕሮፋይላቸውን በማስተላለፍ የተሻለ ድጋፍ እንዲያገኙ
ያደርጋል፡፡
14
ለ) የኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ አፈፃፀም መከታተልና በወረዳ እና ከተማ አስተዳደር ለሚገኘው
መዋቅር ድጋፍ ያደርጋሉ፣
ሐ) የኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ለመወሰን አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ያሰባስባሉ፣ ያደራጃሉ፣
መ) ከታዳጊ ወደ መብቃት ለሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ የምስክር ወረቀት ይሰጣሉ፡፡
6) የከተማ/ወረዳ/1 ማዕከል የከተሞች ሥራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤቶች
ሀ) ለኢንተርፕራይዞች እንደየዕድገት ደረጃቸው አስፈላጊ ድጋፎችን ይሰጣሉ፣ ወይም እንዲያገኙ
ያመቻቻሉ፣
ለ) የኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ ለመወሰን አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ያሰባበስባሉ፣ ያደራጃሉ፣
ሐ) ለጀማሪ እና ከጀማሪ ወደ ታዳጊ የእድገት ደረጃ ለሚሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ደረጃ የምስክር
ወረቀት ይሰጣሉ፡፡
የአፈፃፀም አመልካቾች
በዕድገት ደረጃ ሽግግር በተገኘ ውጤት የሚኖሩ የአፈፃፀም አመልካቾች፦
ክፍል አራት
መብትና ግዴታ
2) ግዴታ
ሀ) ኢንተርፕራይዙ ለዕድገት ደረጃ አሰጣጥ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች በሚመለከተው አካል ሲጠየቅ
ሳይደብቅ በግልጽ የመስጠት ግዴታ አለባቸው፣
ለ) መንግስታዊ ድጋፎችን ለማግኘት ሲወዳደር ወይም ሲጫረት የተሰጠውን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት
ይዞ የመቅረብ ግዴታ አለባቸው፣
ሐ) የእድገት ደረጃ ሽግግር ሲያደርግ በፊት የተሰጠውን የእድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት እንዲመልስ ይደረጋል፡፡
13. የፈፃሚ አካላት መብትና ግዴታ
1) የፈጻሚ አካላት መብት
ሀ) የዕድገት ደረጃ ለመስጠት የሚያስችሉ መረጃዎችን ከኢንተርፕራይዙና ከሌሎች አጋዥ ሴክተሮች
መጠየቅና መውሰድ ይችላል፣
ለ) ሰብዓዊና ሙያዊ ክብሩ የመከበር፡፡
16
2) የዘርፉ ፈጻሚ ግዴታ
ሀ) በደረጃ እድገት መስፈርቶች እና በአሰራሩ ዙሪያ ለኢንተርፕራይዞች መረጃ መስጠትና ግንዛቤ
የመፍጠር፣
ለ) ለሚሰጠው የእድገት ደረጃ የሚሰበሰቡ መረጃዎችን የማጥራት፣
ሐ) ኢንተርፕራይዞች በመስፈርቶችና ባቀረቡት መረጃ መሠረት የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ ሰርቲፊኬት
የመስጠት፡፡
ክፍል አምስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
አንድ ኢንተርፕራይዝ ወደ ታዳጊ መካከለኛ ተሸጋግሮ ከመመረቁ በፊት በየደረጃው ድጋፍ ተደርጎለት በሌሎች
የዕድገት ደረጃዎች ያለፈ መሆን አለበት፡፡
ጃንጥራር ዓባይ
የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር
17
18