Professional Documents
Culture Documents
ግንቦት/ 2010
አዲስ አበባ
መግቢያ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍ ከግብርናው ቀጥሎ ሠፊ የስራ ዕድል የሚፈጠርባቸው
በመሆናቸው ድህነትን ከመቅረፍ እና ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ
0
አላቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር በማመቻቸት፣ ለመካከለኛና ከፍተኛ
ኢንዱስትሪዎች ዕድገት ሰፊ መደላደል በመፍጠር ረገድ ለቀጣይ የኢኮኖሚ ዕድገት አይነተኛ መሳሪያ
መሆናቸው ጋር ተያይዞ በመንግስት ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ
በመሆናቸው፣ በጥቃቅን አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ መሰረት የከተማ ቁጠባና ብድር አገልግሎት
አሰጣጥ የኢንተርፕራይዞችን የደረጃ ዕድገት እና የተሻሻለውን የኤጀንሲውን ተልዕኮ ታሳቢ ያደረገ ወጥነት ያለው
ሞዴል መመሪያ ማዘጋጀት በማስፈለጉ እንዲሁም በዘርፉ የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን ልማት ለማስፋፋትና
ለማጠናከር የዕድገት ደረጃቸውን መሰረት ያደረገና ቁጠባ መር የብድር አገልግሎት የሚያገኙበትን ሥርዓት ማሻሻል
በማስፈለጉ እና የፌደራል ኤጀንሲውን መነሻ በማድረግ ሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች እንደ ክልሎች
ተጨባጭ ሁኔታ ከኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳ፣ አሳታፊ፣ ፍትሃዊና ውጤታማ በሆነ መልኩ ድጋፉን ለማቅረብ ቁጠባ መር
የብድር አገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ለማሻሻል በማስፈለጉ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 374/2008 አንቀጽ
14 መሠረት ይህ ሞዴል መመሪያ ተሻሽሎ ተዘጋጅቷል፡፡
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የተሻሻለ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ መሰረት ያደረገ የከተማ
ቁጠባና ብድር አገልግሎት አሰጣጥ ሞዴል መመሪያ ቁጥር ---------2010 ›› ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2. ትርጓሜ
1
"ቡድን”” ማለት የፋይናንስ አቅርቦት ለኢንተርፕራይዞች ለማመቻቸት በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ባላቸው
1) "ቡድን
የስራ ዘርፎች የተሰማሩ የጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች እና ቁጥራቸው ከ 3 እስከ 7 የሚደርሱ
የቡድን ብድር አባላትን ይገልፃል፡፡
2) "የቡድን ዋስትና"
ዋስትና" ማለት የቡድን ተበዳሪዎች ከመካከላቸው አንደኛው ፈቃድ ከተሰጠው አበዳሪ ተቋም
የተበደረውን ብድር ያልከፈለ እንደሆነ ብድሩን መልሶ ለመክፈል በአንድነት ባልተነጣጠለ ኃላፊነት
የሚወስዱበት የዋስትና አሰራር ነው፡፡
3) "የብድር ዋስትና"
ዋስትና" ማለት ለሚወሰድ ብድር በዋስትና የሚቀርብ የቡድን፣ የከተማ አስተዳደር፣ የደመወዝ ወይም
የንብረት መያዣ ነው፡፡
4) "የግዴታ ቁጠባ"
ቁጠባ" ማለት በተቋሙ የብድር ደንበኞች የሚያስቀምጡትና ያለባቸውን የብድር ዕዳ ከፍለው
እስከሚያጠናቅቁ ድረስ ሊወጣ የማይችል የግዴታ ቁጠባ ሲሆን የቅድመ ብድር ቁጠባና መደበኛ ቁጠባ ተብሎ
በሁለት ይከፈላል፡፡
5) "የውዴታ ቁጠባ"
ቁጠባ" ማለት በተቋሙ የብድር ደንበኞችና ሌሎች፣ የህብረተሰብ ክፍሎች ወይም በተቋሞች ፍላጎት
ላይ ተመስርቶ የሚቀመጥ የቁጠባ ዓይነት ሲሆን አስቀማጮቹ በፈለጉ ጊዜ ወጪ ሊያደርጉት የሚችሉት
የውዴታ ቁጠባ ነው፡፡
6) "ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ"
" ማለት የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሠራተኞች ጨምሮ
እስከ አምስት ሰዎች ቀጥሮ የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር በአገልግሎት ዘርፍ
ከብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) ወይም በኢንዱስትሪ ዘርፍ ከብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ) ያልበለጠ
ኢንተርፕራይዝ ነው:፡
7) "አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ"
" ማለት የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞችን
ጨምሮ ከስድስት እስከ ሰላሳ ሰዎች የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር በአገልግሎት
ዘርፍ ከብር 50,001.00 (ሃምሳ ሺህ አንድ) እስከ 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ) ወይም በከተማ ግብርና ፣
ባሕላዊ ማዕድን ማምረት እና ግንባታ ዘርፍ ከብር 100,001.00 (አንድ መቶ ሺህ አንድ) እስከ 1,500,000.00
(አንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሺ) ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው::
2
የሚጠቀም ማለት ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ላይ ኢንተርፕራይዝ በምስረታ ደረጃ ከነበረው ቀጥሮ የሚያሰራው የሰው
ሀይል ቁጥርና ጠቅላላ ሀብት መጠን ዕድገት ይኖረዋል፡፡
3. የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ ሞዴል መመሪያ በኢትዮጵያ ከተሞች በሚገኙ የከተማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ ተፈጻሚ
ይሆናል፡፡
4. ዓላማ
5. መርሆዎች
ክፍል ሁለት
ዋና ዋና አገልግሎቶች
6. በአነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
1) የቁጠባ አገልግሎት
2) የብድር አገልግሎት
3) የመሳሪያ ሊዝ
3
4) የማይክሮ ኢንሹራንስ
5) የሃዋላ አገልግሎት
6) የሶስተኛ ወገን ገንዘብ ማስተዳደር
7) ሌሎች ፋይናንስ አገልግሎቶች ናቸው::
አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለማበደር በዕቅድ ከሚያዘው ጠቅላላ
የገንዘብ መጠን ውስጥ 80 በመቶ ከቁጠባ መሸፈን አለባቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በከተማው አስተዳደር ውስጥ ለተወሰነ
ጊዜ ያለስራ የሚቀመጥ ገንዘብ ከየተቋማቱ ተለይቶ በአነስተኛ የፋይናስ አቅራቢ ተቋማት እንዲቀመጥና አውት ሶርስ
ሊደረጉ የሚችሉ ፋይናንሻል ስራዎች በአበዳሪ ተቋማቱ እንዲሰሩ በማድረግ የማበደር አቅማቸው እንዲጎለብት
ይደረጋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም ፈፃሚ እና ባለድርሻ አካላት የታቀደውን የቁጠባን ባህል ለማሳደግና ለዘርፉ የሚያስፈልገውን ያህል
የገንዘብ መጠን ለማሰባሰብ ትኩረት ሰጥተው መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. የቁጠባ አይነቶች
2) ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች
ሀ) ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች ለብድር አገልግሎት ብቁ ለመሆን ከሚበደሩት የብድር መጠን 20 በመቶ
አስቀድመው መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
4
ለ) ሆኖም በመንግስት ፕሮጀክት በቀጥታ ወደ ስራ ለሚገቡ ኢንተርፕራይዞች ለግብአትና መሳሪያ ግዢ
የሚሆን ብድር በሶስትዮሽ ውል ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ከገቡ በኋላ 20 በመቶ ቁጠባውን እንዲቆጥቡ
ይደረጋል፡፡
3) ታዳጊ ኢንተርፕራይዞች
ሀ) የኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት የሚያመርቱና በእድገት ተኮር ዘርፍ የሚሰማሩ ታዳጊ ኢንተርፕራይዞች
ለብድር አገልግሎት ብቁ ለመሆን ለመበደር ያቀዱትን 15 በመቶ አስቀድመው መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
ለ) በስትራቴጂው ቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸው የሥራ ዘርፎች ላይ የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ለብድር
አገልግሎት ብቁ ለመሆን ከሚበደሩት የብድር መጠን 20 በመቶ አስቀድመው መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
ሐ) የኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት ከሚያመርቱና ከዕድገት ተኮር የስራ ዘርፍ ከተሰማሩ ውጭ ያሉ ታዳጊ
ኢንተርፕራይዞች ለብድር አገልግሎት ብቁ ለመሆን ለመበደር ያቀዱትን 25 በመቶ አስቀድመው
መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
4) የበቃ ኢንተርፕራይዞች
ሀ) የኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት የሚያመርቱና በእድገት ተኮር ዘርፍ የሚሰማሩ የበቁ ኢንተርፕራይዞች
ለብድር አገልግሎት ብቁ ለመሆን ለመበደር ያቀዱትን 15 በመቶ አስቀድመው መቆጠብ ይኖርባቸዋል፡፡
ሐ) የኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት ከሚያመርቱና በዕድገት ተኮር የስራ ዘርፍ ከተሰማሩ ውጭ ያሉ የበቁ
ኢንተርፕራይዞች ለብድር አገልግሎት ብቁ ለመሆን ለመበደር ያቀዱትን 30 በመቶ አስቀድመው መቆጠብ
ይኖርባቸዋል፡፡
የተበደሩትን ብድር ከፍለው እስከሚያጠናቅቁ ጊዜ ድረስ የግዴታ መደበኛ ቁጠባ እንዲቆጥቡ ይደረጋሉ፡፡
ለ) በዚህም መሰረት እያንዳንዱ ተበዳሪ ኢንተርፕራይዝ ብድሩን ከፍሎ እስከሚያጠናቅቅ ጊዜ ድረስ የብድሩን
መጠን 2 በመቶ በየወሩ እንዲቆጥቡ ይደረጋል፡፡ በብድር ቆይታ ጊዜ ውስጥ የሚሰበሰብ የግዴታ ቁጠባ ብድሩ
በተሰጠ በወሩ መሰብሰብ ይጀምራል፡፡
5
9. የውዴታ ቁጠባ አይነቶች
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች፣ ተማሪዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች የሚያገኙትን ገቢ በማብቃቃት
እንዲሁም ወጪን በመቀነስ ለስራ የሚያስፈልጋቸውን ካፒታል ለማሳደግና ለተለያዩ ወጪዎች የሚያስፈልጋቸውን
ገንዘብ በብድር አስቀድሞ ለማግኘት ዝግጁ ለመሆን፤ እንዲሁም ጥሪት ለመያዝ ቁጠባን እንደ ባህል በመርህ ደረጃ
መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ለህብረተሰቡ የቀረበ አደረጃጀት ያላቸው ቢሆኑም ተደራሽነታቸውን ይበልጥ
በማስፋትና በማሳደግ ከዚህ በታች በተጠቀሱትና ሌሎችንም ተጨማሪ የውዴታ የቁጠባ አይነቶችን ለህብረተሰቡ
በማስተዋወቅ የገንዘብ አቅርቦትንና የብድር ፍላጎትን ክፍተት መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡ እነሱም፡-
የደብተር ቁጠባ /Pass book saving/ ማለት ደንበኞች በብር 10 መነሻ የቁጠባ አካውንት በመክፈት ቁጠባ
ሊያጠራቅሙት የሚችሉበት የቁጠባ አገልግሎት ነው፡፡
በዚህ የቁጠባ ዓይነት የተቀመጠ ገንዘብ በአነስተኛ የፋይናንስ ተ ቋማት ውስጥ የሚቆይበትን የጊዜ ገደብ አስቀማጩ
ደንበኛ ከተቋሙ ጋር በሚደረገው የውል ስምምነት መሰረት የሚወሰን ሲሆን የወለድ ምጣኔውም/interest rate/
በተቋሙ ውስጥ በሚቆይበት የውል ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተሰልቶ የሚከፈል ይሆናል፡፡ ቁጠባው ከውል
ስምምነቱ በፊት ወጪ የሚደረግ ከሆነ አስቀማጩ ወለዱን እንዲያጣ ተደርጎ ዋናውን ገንዘብ ወጪ እንዲያደርግ
ይደረጋል፡፡
ይህ የቁጠባ ዓይነት ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ገንዘባቸውን በአደራ የሚያስቀምጡበት አሰራር ሲሆን ተቋሙ
ለሚሰጠው አገልግሎት ደንበኞች የኮሚሽን ክፍያ እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
በጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ስራዎች ላይ የተሰማራ/ች ማህበራት እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ
ድርጅት ሰራተኞች የተቋሙ የብድር ደንበኞች የሆኑና ማንኛውም ግለሰብ መጠቀም የሚችልበት ከአበዳው
በሽያጭ፤በስፖንሰር ወይም አበዳው ለዚሁ ተግባር በሚያቀርበው የቁጠባ ሳጥን የሚቆጠብ የቁጠባ ዓይነት ነው፡፡
6
5) የቤት ለቤት/ተንቀሳቃሽ ቁጠባ /Mobile saving Service/
ይህ የቁጠባ አይነት በተቋሙ ቁጠባ ለመቆጠብ ፍላጎት ያላቸው ነገር ግን በሥራ ባህሪያቸው ምክንያት ወደ ተቋሙ
ጽ/ቤት በአካል ቀርበው መቆጠብ ለማይችሉ የህብረተሰብ ክፍሎች በስራ ገበታቸው፣በገበያና በመኖሪያ ቦታቸው ድረስ
በመዘዋወር ቁጠባ ለማሰባሰብ የሚያስችል ስርዓት ነው፡፡
3) የቁጠባ ምንጮች
የአነስተኛ ብድር አቅራቢ ተቋማት በየደረጃው ከሚገኙ የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲ፣
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት፣ የከተማ አስተዳደር፣ የወረዳ አስተዳደር፣ የዞን መስተዳደርና የክልል መስተዳደር አካላት ጋር
በጋራ በመስራት ያሉትን የቁጠባ ምንጮች አሟጠው መጠቀም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከቁጠባ ምንጮች መካከል ዋና
ዋናዎቹ ከዚህ በታች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
ቀ) የግል ባለሀብቶች
በ) የክላስተር ማዕከላትና
ካለው ውስን የብድር አቅርቦት አኳያ፤ ሰፊ የስራ ዕድል ከመፍጠር፣ እሴት (value) የሚጨምሩ ኢንተርፕራይዞችን
ከማስፋፋት፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ቴክኖሎጂዎችን ወደ መካከለኛና ከፍተኛ ቴክኖሎጂ ለማሸጋገርና የተያዘውን ዕቅድ
እውን ለማድረግ በሌላም በኩል ሴክተሩ የኢንዱስትሪውን ቴክኖሎጂ ሊሸከም የሚችል የሰው ኃይል ማፍራት ይችል
ዘንድ የብድር ስርዓቱ በሚከተሉት የሥራ ዘርፎች ለሚሰማሩት በቅድሚያ ትኩረት ይሰጣል::
8
ከላይ የተጠቀሱትን ትኩረት የሚሰጣቸው ዘርፎች ግምት ውስጥ በማስገባትበየዘርፎቹ ሊካተቱ የሚችሉ ንዑስ
ዘርፎች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል::
1) ሥራ ተቋራጭነት
2) ንዑስ ሥራ ተቋራጭነት
3) የጥሬ ዕቃ አቅርቦት
9
2) ካፌና ሬስቶራንቶች
3) የማከማቻ አገልግሎት
4) የማሸጊያ አገልግሎት
13) የዲኮር ስራ
14) ኢንተርኔት ካፌ
2) የንብ ማንባት
3) የዶሮ እርባታ
6) አትክልትና ፍራፍሬ
7) ዘመናዊ የመስኖ ስራ
8) የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ
9) እንጉዳይ ማምረት
10
የማደራጀት ስራ እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና በመለየት ወደ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ተቋማት የመላክ ሥራ የዘርፍ ፈጻሚዎችና ባለድርሻ አካላት በአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚያከናውኑት ሆኖ
የብድር አገልግሎት ተጠቃሚዎች ከዚህ በታች የተቀመጡትን የመመልመያ መስፈርቶች ማሟላት የሚጠበቅባቸው
ሲሆን የሚመለምለውና የሚያደራጀው አካል መስፈርቶቹ መሟላታቸውን ያረጋግጣል፡፡ እንዲሁም የተበዳሪዎችን
ሙሉ ዝርዝር መረጃ ለአበዳሪ ተቋሙ አስቀድሞ እንዲላክ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
1) ለቡድን ተበዳሪዎች
ሀ) የመሥራት አቅምና ችሎታ ያላቸው አቅማቸውን ተጠቅመውና ሰርተው ለመለወጥ ዝግጁ የሆኑ፤
ሐ) በጥቃቅንና አነስተኛ የስራ ዘርፎች የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች በተደራጁበት ቀበሌ ቋሚ ነዋሪ ካልሆኑ
በቋሚነት ይኖሩበት ከነበረው ቀበሌ ቋሚ ነዋሪነታቸውን እና ከአነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ብድር
እንደሌለባቸው የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
መ) ኢንተርፕራይዞች ከብድር በፊት አነስተኛ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋም ባወጣው መስፈርት መሠረት ቅድሚያ
ቁጠባ ማሟላት አለባቸው፡፡
ሠ) ሁሉም የቡድኑ አባላት ወይም የተወሰኑት አባላት በሚሰማሩበት የስራ ዘርፍ ከዩንቨርስቲ፣ ቴክኒክና ሙያ
ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የተመረቁ ወይም ስልጠና የወሰዱ ወይም በልምድ ያገኙት ዕውቀት
ስለመኖራቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
ቀ) የታደሰ ንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ ወይም ቁጥሩ ያልተሰጣቸው ቢሆኑም
ለግብር ከፋይነት የተመዘገቡ ለመሆናቸው ከሚኖሩበት ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ
የሚችሉ፣
በ) ነባር ከሆኑ ሂሳባቸውን በአግባቡ እየሰሩ መሆናቸውን ከፈጻሚ አካላት ማረጋገጥ ከቻሉ፣
ተ) የጋብቻ ምስክር ወረቀት ወይም ትዳር አለመኖሩን የሚያስረዳ ሥልጣን ከተሰጠው አካል ህጋዊ ማስረጃ
ማቅረብ የሚችል፣
11
2) የንግድ ማህበራት ወይም የግል ተበዳሪዎች
ሐ) ሁሉም የማህበሩ አባላት ወይም የተወሰኑት አባላት በሚሰማሩበት የስራ ዘርፍ ከዩንቨርስቲ፤ ኢንስቲቲዩት
እና ሙያና ቴክኒክ ማሰልጠኛ ተቋማት የተመረቁ ወይም ስልጠና የወሰዱ፣ወይም በልምድ ያገኙት
ዕውቀት ስለመኖራቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፤
ሠ) ነባር ከሆኑ ሂሳባቸውን በአግባቡ እየሰሩ መሆናቸውን የፈጻሚ አካላት ማረጋገጥ ከቻሉ፣
ረ) ለነባር ኢንተርፕራይዞች ሂሳባቸውን በየዓመቱ ኦዲት ያስደረጉና ከቢዝነስ ፕላኑ ጋር ማቅረብ የሚችሉ፣
ሰ) በንግድ ማህበራት ተደራጅተው ብድር ለመበደር የሚፈልጉ ተበዳሪዎች በማህበራት ማደራጃ በህጋዊ መንገድ
የተደራጁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ፣የመተዳደሪያና የመመስረቻ ጽሁፍ ማቅረብ
ይጠበቅባቸዋል፣
ቀ) የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማቅረብ የሚችሉ ወይም ቁጥሩ ያልተሰጣቸው
ቢሆኑም ለግብር ከፋይነት የተመዘገቡ ለመሆናቸው ከሚኖሩበት ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ህጋዊ ማስረጃ
ማቅረብ የሚችሉ፣
ተ) የተሰማሩበት የስራ መስክ ህጋዊና በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው እና የጋብቻ ምስክር ወረቀት ወይም
ትዳር አለመኖሩን የሚያስረዳ ሥልጣን ከተሰጠው አካል ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
1) የማስተዋወቅ ሥራ
አበዳሪ ተቋማት ከላይ የተዘረዘሩትን አገልግሎቶች በአግባቡ በመስጠት ወጤታማና ትርፋማ የሆኑ
ኢንተርፕራይዞችን ለመሳብ የሚከተሉትን የማስታወቂያና የመቀስቀሻ ዘዴዎች ይከናወናሉ፡፡
ሀ) የሰው በሰው ቅስቀሳ
12
ለ) በየአካባቢው በሚደረጉ ህዝባዊ መድረኮች
ሐ) ውይይቶችና ኮንፈረንሶች በማዘጋጀት
መ) በኤግዚቢሽኖችና ባዛሮች
ሠ) በአካባቢ ባሉት የኤሌክትሮኒክስና የህትመት ሚዲያዎች
ረ) በአካባቢ ባሉት ሌሎች የህዝብ መገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም ይሆናል፡፡
ሐ) ስለቁጠባ ምንነት፣ ስለቁጠባ ዓላማና አስፈላጊነት፣ ስለ ቁጠባ ዓይነቶችና ስለሚያስገኙት ጠቀሜታ ግንዛቤ
ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት
ሰ) ስለሂሳብ መዝገብ አያያዝ እና የሥራ ዕቅድ ጠቀሜታ እንዲሁም አዘገጃጀት ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ፤
3) አደረጃጀት
በአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ፋይናንስ ስራ አዋጅ ቁጥር 626/2001 አንቀጽ 16 በተመለከተ መሰረት ፈቃድ የተሰጠው
ተቋም ለቡድኖችም ሆነ ለግለሰቦች ብድር መስጠት ይችላል፡፡ ተቋሙ እንደ አግባብነቱ በራሱ ውሳኔ ያለመያዣ፣
በመያዣ፣ በንብረት ወይም በቡድን ወይም በግለሰብ ዋስትና ብደር መስጠት እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ በዚህም መሰረት
ቀጥሎ በተቀመጡት አደረጃጀት አይነቶች ብድር ማግኝት እንዲችሉ ይደረጋል፡፡
ሀ) የቡድን አደረጃጀት
13
ቁጥራቸው ከ 3 እስከ 7 ህጋዊ ዕውቅና ያላቸው የግል ወይም የማህበር ኢንተርፕራይዞች በአነስተኛ የፋይናንስ ተቋሙ
የቡድን አደረጃጀት መመሪያ መሰረት የሚፈጸም ሆኖ አባላቱም በአግባቡ የሚተዋወቁና የሚግባቡ፣በራሳቸው ፍላጎት
ያለማንም ጣልቃ ገብነት የሥጋ ዝምድና እና የጾታ ልዩነት ሳይደረግባቸው በቡድን ተደራጅተው በቡድን ዋስትና
የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
በንግድ ማህበራት አደረጃጀት መሠረት (በህብረት ሽርክና ማህበር እና ኃላፊነቱ የተወሰነ የግልማህበር) በህጋዊ መንገድ
የተደራጁ መሆናቸውን የሚያስረዳ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ ኢንተርፕራይዞችን እንደየተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ባህሪ
በብድር ዋስትና ፈንድ ዋስትና፣ በከተማ አስተዳደር/ወረዳ ዋስትና እና ሌሎች የዋስትና አማራጮችን በማቅረብ
ሐ) የግል ተበዳሪዎች
የግል ተበዳሪዎች የምንላቸው የንብረት፣ የደመወዝ ወይም የፈጠራ የፕሮጀክት ሀሳብ የያዘ የንግድ ስራ ዕቅድ ዋስትና
በማቅረብ ብድር ለመበደር ፍላ¯ት ያላቸው ኢንተርፕራይዞች ማለት ነው፡፡
የንግድ ዕቅድ 5 ዋና ዋና ክፍሎች ሲኖሩት የመጀመሪያው ክፍል አጠቃላይ መረጃ፣ሁለተኛው ክፍል የገበያ ዕቅድ፣
ሶስተኛው የምርት ዕቅድ፣ አራተኛው የአደረጃጀትና የሰው ኃይል ዕቅድ እና አምስተኛው የፋይናንስ ዕቅድ መያዝ
ይኖርበታል፡፡
14
3) በቅድመ ብድር የቁጠባ ሥርዓት መሰረት ቁጠባ መቆጠቡን የሚያስረዳ ማስረጃ፣
4) የግል ተበዳሪ ወይም የበቃ ኢንተርፕራይዝ ከሆነ በዋስትና የሚቀርበው ንብረት (የስራ መሳሪያ፣ የቤት ካርታ፣
የተሸከርካሪ ሊብሬ) ወይም የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ፣
8) የጋብቻ የምስክር ወረቀት ወይም ትዳር አለመኖሩን የሚያስረዳ ስልጣን ከተሰጠው አካል ማስረጃ፣
በተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርቡ ዋስትናዎች አነስተኛ የፋይናንስ አቅራቢ ድርጅቶች የሚሰጡት ብድር በወቅቱ
እንዲመለስ ከማድረጉ በተጨማሪ ተቋሞቹ የሚሰጡትን አገልግሎት ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ፣ በብድር
የሚቀርበው ገንዘብ ከተለያዩ የቁጠባ ምንጭ የተሰባሰቡ በመሆናቸውና የብድር መመለስና አለመመለስ ከፋይናንስ
ተቋሙ ሕልውና ጋር በቀጥታ ተያያዥነት ያለው መሆኑ እና ኢንተርፕራይዞች ባጠቃላይም የማህበረሰቡን በብድር
የመጠቀም፣ ብድር ወስዶ በጊዜው የመመለስ ባህልን ለማዳበር ያግዛል፡፡ በመሆኑም የተሰጡ ብድሮች በአግባቡ
እንዲመለሱ ከማድረግ አኳያ ማንኛውም ተበዳሪ ለሚወስደው ብድር ተመጣጣኝ የሆነ ዋስትና እንደ እድገት ደረጃው
ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
ለ) የሚቋቋመው የዋስትና ፈንድ በአነስተኛ የፋይናንስ አቅራቢ ተቋም ዋና መ/ቤት በዝግ ሂሳብ ውስጥ
በሚከፈት የተቀማጭ ቁጠባ ሂሳብ ገቢ የሚደረግ ሲሆን በተቀማጩ ገንዘብ ላይ የፋይናንስ አቅራቢ
ተቋሙ 5 በመቶ ወለድ ይከፍልበታል::
ሐ) የዋስትና ፈንዱ በየዓመቱ አዲስ የበጀት ዓመት እንደገባ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተወስኖ ወደ ፋይናንስ
አቅራቢ ተቋሙ ሂሳብ ገቢ ይደረጋል::
መ) የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ጽ/ቤቶች ኢንተርፕራይዞች በአበዳሪ ተቋሙ
የተፈቀደላቸውን የብድር መጠን እና የዕድገት ደረጃቸውን ታሳቢ በማድረግ ከብድር ዋስትና ፈንዱ
15
የብድር ዋስትና ሽፋን እንዲያገኙ ለአበዳሪው የፋይናንስ ተቋም በአድራሻ በሚጻፍ ደብዳቤ
ያሳውቃሉ::
ረ) በዋስትና ፈንዱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ኢንተርፕራይዞች የብድሩን 1.5 በመቶ ለዋስትና ፈንዱ ማጠናከሪያ
ይከፍላሉ፡፡
(1) ጀማሪ በንግድ ማህበር የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ቅድመ ቁጠባ 20 በመቶ ሲያሟሉ 70 በመቶ
ከብድር ዋሰትና ፈንድ የዋስትና ሽፋን በማግኘት ብድር እንዲበደሩ ይደረጋል::
(1) በኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት በማምረት የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ቅድመ ብድር ቁጠባ 15
በመቶ ሲያሟሉ 75 በመቶ፣ ትኩረት በሚሰጣቸው የስራ ዘርፍ የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ቅድመ
ብድር ቁጠባ 20 በመቶ ሲያሟሉ 70 በመቶ የብድር ዋስትና ሽፋን ያገኛሉ፡፡
(1) በኤክስፖርት ወይም ተኪ ምርት በማምረት የሚሰማሩ ኢንተርራይዞች ቅድመ ብድር ቁጠባ 15
በመቶ ሲያሟሉ 75 በመቶ፣ ትኩረት በሚሰጣቸው የሥራ ዘርፍ የሚሰማሩ ኢንተርፐራይዞች ቅድመ
ብድር ቁጠባ 20 በመቶ ሲያሟሉ 70 በመቶ የብድር ዋስትና ሽፋን ያገኛሉ፡፡
ሠ) በብድር ዋስትና ሽፋን የተመለሰ ብድር ለአነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ገቢ ቢደረግም ከተበዳሪ
ኢንተርፕራይዞቹ ቀጣይ ክትትል ተደርጎ ተመላሽ ሊሆን ይገባል፡፡ ለዚህም በየደረጃው ያለ አቃቤ ህግ
እንዲከታተለውና እንዲያስፈጽም ይደረጋል፡፡
2) ሶስትዮሽ ውል ስምምነት
በምርት ገዢ፣አቅራቢና አበዳሪ ድርጅት መካከል በሚደረግ የሦስትዮሽ ውል በመጠቀም በማንኛውም ደረጃ
ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ከአነስተኛ የፋይናስ ተቋም ብድር ሊበደሩ ይችላሉ:: በዚህም መሰረት፡-
16
ሀ) የተመረተውን የኢንተርፕራይዞች ምርት ወይንም አገልግሎት ግዢ የሚፈፅመው ሁለተኛ ወገን
ምርቱን/አገልግሎቱን ለመግዛት መስማማቱን፣ የግዢውን ዋጋ የሚገልፅ እና ለአቅራቢ ኢንተርፕራይዞች
ክፍያውን ከመፈጸሙ በፊት ለአበዳሪ የፋይናንስ ተቋሙ ብድሩን ቀንሶ ለመክፈል መስማማቱን የሚያረጋግጥ
ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል::
ለ) በማንኛውም ደረጃ ላይ የሚገኙ የግል ፣ የቡድን እና የንግድ ማህበር ተበዳሪ ኢንተርፕራይዝ በቅድመ ብድር
መቆጠብ ያለባቸው ቁጠባ እንዳለ ሆኖ ሌላ የግል ዋስትና ማቅረብ ሳያስፈልግ ከብድር ዋስትና ፈንድ
የብድሩን 50 በመቶ የዋስትና ሽፋን ብቻ በማቅረብ ብድር እንዲሰጣቸው ይደረጋል::
3) የንብረት/የደመወዝ ዋስትና
ከብድር ዋስትና ፈንድ (Credit guarantee fund) የዋስትና ሽፋን ማግኘት ለማይገባቸው በማንኛውም ደረጃ ላይ የሚገኙ በንግድ
ማህበር የተደራጁ እና የግል ተበዳሪዎች በቅድመ ብድር መቆጠብ ያለባቸው ቁጠባ እንዳለ ሆኖ ልዩነቱን የዋስትና ሽፋን በግል
በሚያቀርቡት የንብረት/የደሞወዝ ዋስትና ብድር እንዲሰጣቸው ይደረጋል::
ከብድር ዋስትና ፈንድ የዋስትና ሽፋን ማግኘት የማይገባቸውን ኢንተርፕራይዞች የማጣራቱ ስራ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጪያ
ጣቢያ ተግባር ይሆናል፡፡
አነስተኛ የፋይናንስ አቅራቢ ተቋማቱ ከላይ ከተቀመጡት የብድር ዋስትና አይነቶች በተጨማሪ ሌሎችንም የዋስትና
አማራጮች መጠቀም ይችላሉ፡፡
አበዳሪው ተቋም በአካባቢው ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመዳሰስ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን
የመገምገሚያ ነጥቦችን መሰረት በማድረግ የቀረበውን የንግድ ሥራ ዕቅድ የአዋጭነት ትንተና ያካሄዳል፡፡
ሀ) በተሰማሩበት የምርት፣ የንግድ ወይም የአገልግሎት ሥራ አስመልክቶ የክህሎትና ሥልጠና የወሰዱ መሆናቸውን
ማረጋገጥ ፣
ለ) ደንበኛው የተሰማራበት የሥራ መስክ ያለው የገበያ አዋጭነት፣ የግብአት አቅርቦት፣ በሥራው ላይ ያለው ልምድ ፣
ያደረገው ቅድመ ዝግጅት፣ በአካባቢው ያሉ ተፎካካሪዎችና የገንዘብ እንቅስቃሴውን ይገመግማል፣
17
ሐ) ለምርቱ/ለአገልግሎቱ አስፈላጊ የሆኑ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት መገኘቱን፤ ዘላቂነት ያለው መሆኑን ምርቱ/ አገልግሎቱ
በቂ ገበያ መኖሩን፤ እንዲሁም ከትርፋማነት አንፃር እና ከንግዱ የሚገኘው ትርፍ ብድሩን የመመለስ አቅሙን
መገምገም፣
መ) ንግዱ የሚካሄድበት የማምረቻና የመሸጫ ቦታ ለስራው ምቹና ተስማሚ እንዲሁም ህጋዊ መሆኑን ያረጋግጣል ፣
ረ) የቀረቡትን አጠቃላይ የብድር ሂደት ሰነዶች ከተቋሙ የብድር አሰራር አንጻር ይተነትናል፣
ቀ) ንግዱ ሊፈጥር የሚችለውን የሥራ ዕድልና ለህብረተሰቡ የሚሰጠው ማህበራዊ ጠቀሜታ ይገመግማል፣
ነ) ያለፈ ብድር አመላላስ ታሪካቸው ጥሩ የሆነና ቁጠባ ለማስቀመጥ ያደረጉትን ጥረት ማረጋገጥና ግብር
ስለመክፈላቸው ማስረጃ ያቀረቡ መሆናቸውን ማረጋገጥ፣
ኘ)ነባር ኢንተርፕራይዞች ከሆኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ እና ዓመታዊ የሂሳብ መግለጫና የተመረመረ የሒሳብ ሰነድ
ያቀረቡ መሆነቸውን ማረጋገጥ::
3) የብድር መጠን
በመንግስት የትኩረት አቅጣጫ እንደ ሌሎች መንግስታዊ ድጋፎች ሁሉ ለኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው የብድር መጠን
እንደተሰማሩበት የስራ አይነት፣ ቢዝነሱ ብድሩን ለመክፈል ያለው አቅም እና የወሰዱትን ብድር በአግባቡ ለመጠቀም
የሚያስችል የገንዘብ አጠቃቀም አስተዳደር ብቃት በየእድገት ደረጃቸውና በንግድ ስራ እቅዱ መሰረት ይወሰናል፡፡
በዚህ መሰረት በየስራ ዘርፎቹ እንደየዕድገት ደረጃቸው ሊቀርብ የሚገባው የፋይናንስ /ብድር/ አቅርቦት መጠን
የወቅቱን የገንዘብ ግሽበት፣የተለያዩ የአነስተኛ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋማት ከሚሰጡት ብድር በመነሳትና የወቅቱን
የስራ እንቅስቃሴ ግምት ውስጥ በማስገባት በአባሪው ላይ በግልጽ ቀርቧል፡፡ የብድር አሰጣጥ አገልግሎት
የኢንተርፕራይዞችን የዕድገት ደረጃ ያገናዘበ፣በየደረጃው ሊጠቀሙ ይችላሉ ተብሎ የተገመተውን የመስሪያ መሳሪያ
ከግምት ውስጥ ያስገባና የኢንተርፕራይዞችን የደረጃ ትርጉም ማለትም የሚያንቀሳቅሱትን ካፒታል እና የሰው ኃይል
18
ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ይህ የእድገት ደረጃን መሰረት ያደረገ የብድር አገልግሎት ኢንተርፕራይዞቹ ከሚያዘጋጁት የተጠና
የንግድ ስራ እቅድ ጋር የተጣጣመ መሆን ይኖርበታል፡፡ በተለይም ጀማሪ ኢንተርፕራይዞች ስራ ሲጀምሩ በአነስተኛ
ካፒታል የሚጀመሩ ስራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉና ደረጃ በደረጃ የገበያውን የውድድር ሜዳ እየተለማመዱ
ውጤት እንዲያሳዩ በዘርፍ አስፈፃሚ ባለሞያዎች ምክር ማግኘትና መታገዝ ይኖርባቸዋል፡፡
1). የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጪያ ጣቢያ በውክልና የተሰጠውን የብድር መጠን በመገምገም ያጸድቃል፡፡
2). ከአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጪያ ጣቢያ ውክልና በላይ የሆነ የብድር መጠን አስተያየቱን በመስጠት
በሚቀጥለው ደረጃ ባለው የአነስተኛ ፋይናንስ ተቋም አቅርቦ ያጸድቃል፡፡
3). የሥራ ዕቅዱ የቀረበለት አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ጽ/ቤት የስራ ዕቅዱን አዋጭነት ግምገማ በአግባቡ
በማካሄድ ከ 5 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ብድሩ በየደረጃው እንዲጸድቅ ያደርጋል፡፡
4). በዚህ መሰረት የአነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት በተዋረድ ብድር የማጽደቅ ሥልጣንና የብድር ውል መፈጸም
እንደ አበዳሪ ተቋም አደረጃጀትና አሰራር ይወሰናል፡
22. በዋስትና የተያዘን ንብረትና ብድርን የኢንሹራንስ ሽፋን እንዲያገኝ ማድረግ የማይክሮ ኢንሹራንስ አገልግሎት
ሀ) የግል ተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች ለተፈቀደላቸው ብድር የቀረበው ማስያዣ የንብረት ዋስትና ከሆነ ብድሩ
ተከፍሎ እስኪጠናቀቅ ከአበዳሪ ተቋሙ ወይም ከሁለተኛ ወገን የመድህን አገልግሎት ድርጅት (insurance
company) በየዓመቱ የሚታደስ የመድህን ዋስትና እንዲገቡ ይደረጋል:፡ ይህ የመድህን ዋስትና ሽፋን
የሚያገለግለው በዋሰትና ለቀረበው ንብረት ብቻ ይሆናል፡፡
ለ) የበቁ ኢንተርፐራይዞች ለሚበደሩት ብድር የብድር ዋስትና ፈንድ ሽፋን የማያገኙ በመሆናቸው ለሚበደሩት
ብድር የንብረት ዋስትና የሚያቀርቡ ከሆኑ በዋስትና የሚያዘው ንብረት በተጠቀሰው መሰረት የመድን ዋስትና
ሽፋን ሊደረግለት ይገባል፡፡ አፈጻጸሙም ለግል ኢንተርፕራይዝ ተበዳሪዎች በተጠቀሰው መስረት ይሆናል፡፡
ሐ) የብድሩ መመለሻ ጊዜ ከአንድ ዓመት በላይ ከሆነ ተበዳሪው ግለሰብ የመድህን ሽፋኑን ማሳደስ ይኖርበታል፡፡
በግንባር ቀርቦ የማያሳድስ ከሆነ አበዳሪው የፋይናንስ ተቋም ከራሱ ወጪ በማድረግ የሚያሳድስ ሲሆን
በማሳደስ ሂደቱ ወጪ የተደረጉትን ሂሳቦች በሙሉ በቀሪው ብድር ላይ በመጨመር ያስከፍላል፡፡
19
መ) የመድን ሽፋን አገልግሎቱ በአበዳሪ ተቋሙ የሚሰጥ ከሆነና የብድሩ መመለሻ ጊዜ ከአንድ ዓመት በላይ ከሆነ
በየዓመቱ ከቀሪው የብድር ባላንስ ላይ አረቦን የሚታሰብ ሲሆን ተበዳሪው የመጀመሪያ ዓመት ላይ ሆኖ
ለሚቀጥለው ዓመት የአረቦን ክፍያ የሚውል የአረቦን ቁጠባ (Insurance saving) እንዲቆጥቡ ይደረጋል፡፡
በዓመቱ መጨረሻ የቁጠባው ባላንስ ወደ መድሕን አረቦን ክፍያ ይተላለፋል፡፡
ሀ) በቡድን የጠለፋ የብድር ዋስትና ሥርዓት የተደራጁ ተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች እያንዳንዳቸው በግል የህይወት
መድህን ዋስትና (Micro life insurance) ከአበዳሪው የፋይናንስ ተቋም መግዛት ግዴታ ይሆናል::
ለ) ለዚህ አገልግሎት በእያንዳንዳቸው የብድር ድርሻ በአነስተኛ ፋይናንስ አቅራቢ ተቋማት በሚወሰነው
መሠረት አረቦን የሚከፈሉ ሲሆን ተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች የራስን ሕይወት በራስ እጅ ከማጥፋት ውጭ
በሌላ በማናቸውም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩ በሟች ስም ተመዝግቦ የሚገኘው ቀሪ የብድር
ባላንስ ይሰረዛል፤ በጠለፋ ዋስትና ያስያዙት ንብረትም ሆነ ሌላ ዋስትና ከእዳው ነፃ ይደረጋል::
መ) የብድሩ መመለሻ ጊዜ ከአንድ ዓመት በላይ ከሆነ በየዓመቱ ከቀሪው የብድር ባላንስ ላይ አረቦን ሚታሰብ
ሲሆን ተበዳሪው የመጀመሪያ ዓመት ላይ ሆኖ ለሚቀጥለው ዓመት የአረቦን ክፍያ የሚውል የአረቦን ቁጠባ
(Insurance saving) እንዲቆጥቡ ይደረጋል፡፡ በዓመቱ መጨረሻ የቁጠባው ባላንስ ወደ መድሕን አረቦን ክፍያ
ይተላለፋል፡፡
የብድር ውል ስምምነት መፈጸም እንደ አበዳሪ ተቋም አደረጃጀትና አሰራር የሚወሰን ይሆናል፡፡
ቅድመ ብድር መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች ከተሟሉ በኋላ ለብድር የጸደቀው ገንዘብ ወደ ተበዳሪዎች የቁጠባ
ሂሳብ ገቢ ይደረጋል፡፡ ወይም በጥሬ ገንዘብ ይሰጣቸዋል፡፡ እንደሚሰማሩበት የስራ ዘርፍና የግዢ ዕቅድ በተለያየ ጊዜ
ይለቀቅላቸዋል፡፡
አበዳሪ ተቋማት ለሚሰጡት አጠቃላይ የብድር አገልግሎት እያንዳንዱ ተበዳሪ ኢንተርፕራይዝ ከፀደቀለት ብድር ላይ
የሚከፍለው ክፍያ እንደ አበዳሪ ተቋሙ አደረጃጀትና አሰራር የሚወሰን ይሆናል፡፡
20
2) ለዋስትና ፈንድ ማሳደጊያ የሚውል የአገልግሎት ክፍያ
ኢንተርፕራይዞችን የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ በክልል መንግስታት በሚመቻችና በልማት አጋሮች ድጋፍ
ለሚቋቋመው የዋስትና ፈንድ ብድሩ የተፈቀደላቸው ኢንተርፕራይዞች በጸደቀላቸው ብድር ላይ 1.5 በመቶ
የአገልግሎት ክፍያ እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
ተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች ለሚበደሩት ብድር የብድር ወለድ ምጣኔን በተመለከተ አበዳሪ ተቋማቱ እንደየአካባቢው
ተጨባጭ ሁኔታ የሚወስኑት ይሆናል፡፡ ሆኖም የአነስተኛ ፋይናንስ ተቋማቱ የማህበራዊ አላማቸውንና
ቀጣይነታቸውን በሚያረጋግጥ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ ወለድ ምጣኔ ይወስናሉ፡፡
27. የእፎይታ ጊዜ
ተበዳሪ ኢንተርፕራይዞች ብድር ወስደው ወደ ተግባር ከመግባታቸው በፊት ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ
ሁኔታዎችን ለማዘጋጀት በቀጥታ ወደ ምርት አቅርቦት የማይገቡበት ሁኔታ ስለሚኖር፣
1) እንደስራው ባህሪ እየታየ እስከ 4 ወር ድረስ የእፎይታ ጊዜ የሚሰጥበት ሁኔታ ይኖራል፡፡ ይሁን እንጂ ተበዳሪዎቹ
ብድሩን ከተበደሩበት ቀን ጀምሮ አበዳሪ ተቋሙ በተፈቀደው ብድር ላይ ወለድ ያሰላል ፡፡
3) በአመት አንድ ጊዜ፣ በአመት ሁለት ጊዜ ወይም በአመት አራት ጊዜ ተጠቃለው ለሚመለሱ ብድሮች የእፎይታ
ጊዜ አይሰጣቸውም፡፡
ክፍል ሶስት
አበዳሪው የፋይናንስ አቅራቢ ተቋም እና የከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲ መደበኛ የጊዜ
ሰሌዳ በማውጣት ያልተቋረጠ ድጋፍና ክትትል ያደርጋሉ:: በዚህም
21
1) ብድሩ በየትኛውም የተቋሙ መዋቅር ቢፀድቅም ለደንበኛው ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ እንዲሆን
ማስቻል እና ሌሎች ሥራዎች በሙሉ የሚከናወኑት ብድሩ በተጠየቀበት ጽ/ቤት ባሉ ሠራተኞች ይሆናል፡፡
2) ሁሉም ደንበኞች ብድሩን በወሰዱ ከ 15 እስከ 30 ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ብድሩን በተባለው ተግባር ላይ
ማዋላቸውን በአካል ያረጋግጣሉ፣
3) ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አቅርበውት በነበረው የሥራ ዕቅድ መሠረት እየተጓዙ መሆኑን
ማረጋገጥ፣
4) ኢንተርፕራይዞች ከካፒታላቸው ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የስቶክ ወይንም የማሽነሪ ንብረት መኖሩን ማረጋገጥ፣
6) የኢንተርፕራይዞቹ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን ማረጋገጥና ድጋፍና ምክር
መስጠት፣
10) ኢንተርፕራይዞች መደበኛና የውዴታ ቁጠባቸውን በአግባቡ እየፈፀሙ መሆኑን ማረጋገጥና በውዴታ ቁጠባም
የበለጠ እንዲጠናከሩ ማበረታታት፣
11) ሁሉም የማህበሩ አባላት በሚፈለገው ደረጃ በሥራው ላይ ሙሉ ጊዜያቸውን እያዋሉ መሆናቸውን፣
በአካልም መኖራቸውን እንዲሁም በማህበሩ ውስጥ የጥቂት ግለሰቦች ተፅዕኖ ያልተስፋፋ መሆኑን ማረጋገጥ፣
12) የወጪ መዝገባቸውን በመገምገም የተጋነኑና ቁጥጥር ሊደረግባቸው የሚገባቸውን የወጪ አይነቶች
በመለየት የማስተካከያ እርምጃ እንዲወስዱ ምክር መስጠት፣
13) የሥራ መስካቸውን የቀየሩ ካሉም ምክንያቱን ማጥናትና የስራ መስኩም የማያዋጣ መሆኑ ከተረጋገጠ
ብድሩን እንዲመልሱ ማድረግ፡፡ ይህንንም ተግባራዊ ማድረግ እንዲቻል በብድር ውል ስምምነቱ እንዲካተት
ይደረጋል፡፡
14) ብድሩን በተጠየቀበት የሥራ መስክ ያላዋሉትን መለየትና በመፍትሔው ዙሪያ ደንበኛውን ማማከርና
አቅጣጫ መስጠት፣
15) የሌሎች አካላትን ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን መለየትና ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፣
22
16) ደንበኞች በተበደሩት የስራ መስክ ውጤታማ የሚሆኑበትንና ብድሩን መመለስ የሚያስችላቸው የገበያ ሁኔታ
መኖሩን ማረጋገጥና እንደ አስፈላጊነቱ የገበያ ትስስር የሚፈጠርበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣
20) ደንበኞች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ላይሆኑ እንደሚችሉ ከተገመተና በብድር አመላለሱም ላይ
ችግር ያስከትላሉ ተብሎ ከታሰበ ከመፍትሄ ሃሳብ ጋር ሪፖርት ማድረግ፣
21) አካላዊ ጉብኝት የተደረገበትን ዝርዝር ሁኔታ የያዘ የድጋፍ አሰጣጥ መዝገብ ማዘጋጀት፣ በድጋፍ መዝገቡ ላይ
ጉብኝት የተደረገላቸው ደንበኞች እንዲፈርሙ ይደረጋል፡፡ ቢዝነሱ ላይ ለየት ያለነገር ሲያጋጥም ለሌሎች
ኢንተርፕራይዞች በተሞክሮነት እንዲያገለግል በተንቀሳቃሽ ምስልና ፎቶግራፍ እንዲነሳ ይደረጋል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን ዋና ዋና ተግባራትንና ሌሎችንም ዘላቂና ቋሚ በሆነ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በመገምገም የከተሞች
የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲና የፋይናንስ አቅራቢው ተቋም ድጋፍ መስጠት ዋነኛ መደበኛ
ተግባራቸው ይሆናል::
ሀ) በምርት ጥራት
ሐ) በቴክኒክና ማኔጅመንት
ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚሰማሩበትን የስራ መስክ ግምት ውስጥ ያስገባ ከፍተኛው የብድር የቆይታ
ጊዜ 36 ወር ወይም 3 ዓመት ብቻ ይሆናል፡፡ በዚህም መሰረት እንደተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሚወሰን
1) በየወሩ የሚመለስ
2) በየሶስት ወሩ የሚመለስ
23
5) በየወሩ ብድር የሚመልሱ ኢንተርፕራይዞች የምንላቸው ኢንተርፕራይዞቹ ብድር ከወሰዱበት ጊዜ ጀምሮ ወይም
የእፎይታ ጊዜያቸው ከተጠናቀቀ በኋላ በየጊዜው ገቢ ያገኛሉ ተብለው የሚገመቱ የሥራ መስኮች ላይ
የሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በዚህ የብድር አመላለስ ሥርዓት ውስጥ እንዲካተቱ ይደረጋል፡፡
6) ምርታቸው ወይም አገልግሎታቸው በየጊዜው እየተሸጠ ገቢ የማያስገኝላቸው እንደ ከተማ ግብርና የመሳሰሉት
የሥራ መሥኮች ላይ የሚሰማሩ የብድር ተጠቃሚዎች በዓመት በአንድ ጊዜ ተጠቃሎ በሚመለስ ፤በዓመት
በሁለት ጊዜ ወይም አራት ጊዜ ተጠቃሎ በሚመለስ የብድር አመላለስ ሥርዓት ውስጥ እንዲካተቱ ይደረጋል፡፡
ተበዳሪዎች ብድሩን ለመመለስ በገቡት የውል ስምምነት መሰረትና በአበዳሪው ተቋም የብድር አመላለስ ሥርዓት
መሠረት የሚፈጸም ይሆናል፡፡
1) ማበረታቻ (incentives)
የፋይናንስ አቅራቢ ተቋማት በቁጠባ፣በብድር አመላለስና አጠቃቀም እና በመሳሰሉት የደምበኞችን አፈፃፀም
እየገመገመ የወለድ ማሻሻያና የልዩ ልዩ ማበረታቻ ያደርጋል:: አፈጻጸሙም በአበዳሪ ተቋም የውስጥ አሰራር
መሠረት የሚፈጸም ይሆናል፡፡
ለ) ያለውን የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት ችግር ለመቅረፍና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማሳደግ ሁሉም ፈፃሚ እና
ባለ ድርሻ አካላት ለብድር ማስመለስ ሥራ ቅድሚያ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል::
ሐ) በአነስተኛ የብድር አቅራቢው ቅ/ጽ/ቤት ወይም ንዑስ ቅ/ጽ/ቤት አማካይነት በየሦስት ወሩ የጥቃቅንና
አነስተኛ ተቋማት የብድር የማስመለስ ምጣኔ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የሶስት ወሩ
በአደጋ ላይ ያለ የብድር ምጣኔ (Portifolio At Risk) 3% በታች ሆኖ ከተገኘ የአበዳሪው ተቋም የገንዘብ
አስተዳደር(liquidity) ጤናማ ለማድረግና ከበላይ ተቆጣጣሪው የብሔራዊ ባንከ የብድር አመላለስ መመሪያ
ጋር ተጣጥሞ እንዲጓዝ ለማስቻል የጥቃቅንና አነስተኛ የብድር አገልግሎቱ በአካባቢው /በከተማው ለጊዜው
እንዲቆም ተደርጎ ሁሉም ፈፃሚና ባለድርሻ አካላት በወቅቱ ሳይከፈል በቀረው ብድር ላይ በመረባረብ
ያስመልሳሉ::
መ) የአካባቢው የብድር አመላለስ ምጣኔ ከ 97% በላይ ሆኖ ሲገኝ የብድር አሰጣጥ ሥራው እንዲቀጥል
ይደረጋል::
24
ሠ)ብድሩ ጤናማ በሆነ መልኩ ተመላሽ ሆነ የሚባለው ተበዳሪው ከስራ እንቅስቃሴው ካገኘው ሽያጭ/ገቢ ላይ
ሲመልስ እንጂ ከዋስትና መያዣ ወይንም ከብድር ዋስትና ፈንድ ተመላሽ የተደረገ ብድር አለመሆኑ
ሊታወቅ ይገባል::
ረ) ደንበኞች ብድሩን በመመለሻ ቀናቸው ካልመለሱ የአበዳሪ ተቋሙ ጽ/ቤት በቀበሌ ደረጃ ካለው ኮሚቴ ጋር
በመሆን የተፈጠረውን ውዝፍ እንዲመለስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ ውዝፉ በዚህ ኮሚቴ የጋራ ጥረት
በ 7 ቀናት ውስጥ ካልተመለሰ የእያንዳንዱ ደንበኛ ዝርዝር፣ የውዝፍን መጠንና ምክንያት ያካተተ ሪፖርት
በ 5 ቀናት ውስጥ ለከንቲባ ጽ/ቤት ወይም ለወረዳ አስተዳደር ያሳውቃሉ፡፡
ሰ) የከተማ አስተዳደር ወይም የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት በሪፖርቱ መሰረት ደንበኞች ውዝፍ ከፈጠሩበት ጊዜ
ጀምሮ ደንበኛውን በማወያየት በ 30 ቀናት ውስጥ እንዲመልሱ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል በማድረግ
ውዝፉ እንዲመለስ ያደርጋል፡፡
ሸ) ከላይ በተቀመጠው አግባብ ብድሩን በወቅቱ ያልከፈሉትን በፎርክሎዠር ህግ (626/2001) መሰረት ለዋስትና
ያስያዙትን ንብረት በመሸጥ እንዲመለስ ማድረግ ወይም ለክስ የሚያበቁ መረጃዎችን በማደራጀት ክስ
እንዲመሰረትባቸው ይደረግባቸዋል፡፡
ቀ) በክስ ብድራቸውን የሚመልሱ ደንበኞች በጥቁር መዝገብ ተለይተው ይያዛሉ፡፡ መረጃውም በየደረጃው
እንዲያዝ ይደረጋል፡፡
በ) በጥቁር መዝገብ የተመዘገበ ደንበኛ በተቋሙ በየትኛውም ጽ/ቤት ብድር እንዳያገኝ ይደረጋል፡፡
ተ) ከላይ በተዘረዘሩት መንገዶች ብድሩ በ 180 ቀናት ውስጥ ተጠቃሎ የማይመለስ ከሆነ ውዝፉን ከነወለዱ
ከዋስትና ፈንዱ ገንዘብ እንዲተካ ይደረጋል፡፡
ቸ) በፎርክሎዠርም ሆነ በክስ ውዝፉ ሳይመለስ ቀርቶ ከብድር ዋስትና ፈንዱ ውዝፉ ለአበዳሪ ተቋማት ከተተካ
በኋላ ከተበዳሪዎች የሚመለሰው ብድር ወደ ዋስትና ፈንዱ የተቀማጭ ሂሳብ ገቢ ይደረጋል፡፡
ኀ) ከዋስትና መያዣ ወይንም ከብድር ዋስትና ፈንድ የሚተካ ብድር የመጨረሻው አማራጭ ሆኖ በተለይ ከብድር
ዋስትና ፈንድ እንዲተካ የሚደረገው ብድር በየስድስት ወሩ (Semi annually) የሚከናወን በመሆኑ ፈፃሚ
አካላት ከዋስትና መያዣ እና ከብድር ዋስትና ፈንድ ሊመለስ የሚችለውን ብድር የአመላለስ ምጣኔ ግምገማ
ላይ ከግምት ውስጥ አይገባም::
ተበዳሪዎች የወሰዱትን ብድር በአግባቡ በሥራ ላይ ካዋሉ በኋላ በወቅቱ የመመለስ ግዴታና ኃላፊነት አለባቸው::
ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች ውዝፍ ከተከሰተ ይህን ውዝፍ የማስመለስ ሥራ የአነስተኛ ፋይናንስ አቅራቢ
ተቋማት፣ የከተማ የስራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ኤጀንሲዎች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች ተግባር
ይሆናል::
25
በክልል መንግስታት ከተቋቋመውና በተቋሙ ከተቀመጠው የዋስትና ፈንድ ላይ ያለተጨማሪ የህግ ድጋፍ 6 ወራት
ያሳላፉ ውዝፍ ብድሮች ለተቋሙ ገቢ ይደረጋሉ:: ሆኖም ውዝፍ ብድሩ እንዲመለሰ ለሚመለከተው አቃቤ ህግ
የተሟላ መረጃ በመስጠት ብድሩ እንዲመለስ ከፈጻሚ አካላት ጋር ተቀናጅቶ ይሰራል፡፡
31. ቅጣት
በማንኛውም የዕድገት ደረጃ ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች፣ የግልና የቡድን ተበዳሪዎች፣ አስቀድሞ በተስማሙበትና
በተሰጣቸው የብድር መክፈያ ሰሌዳ (Repayment schedule) መሠረት ብድራቸውን የመከፈል ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡
ብድርን በወቅቱ መክፈልና ያለመክፈል በሚቀጥሉት ዙር ብድሮች ላይ አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ ከማስከተሉም
በላይ በአበዳሪው ተቋም የገንዘብ ማኔጅመንት (liquidity management) እና የገንዘብ አቅርቦት ላይ ችግር
የሚያስከትል ይሆናል፡፡ በመሆኑም አበዳሪው ተቋም ገንዘቡን በወቅቱ ቢሰበስብ እና መልሶ ቢያበድረው ሊያገኘው
የሚችለውን ገቢ ታሳቢ በማድረግ በእያንዳንዳቸው ባለፉት ቀናት ሳይከፈል በቆየው የብድር ገንዝብ ላይ በአበዳሪው
ተቋም መመሪያ መሰረት እንዲቀጣ ይደረጋል፡፡
ሀ) ደንበኞች ምን ያህል ውጤታማ እንደሆኑ ወይም እንዳልሆኑ ለማጥናት እንዲቻል ብድር ከመለሱ በኋላ
ያላቸውን ሀብት መጠን በዝርዝር የሚያሳይ ጥሬ መረጃ ይሰበስባል
ሐ) እንዲረጋገጥ ይደረጋል
ለ) ውጤት ይለካል፣
ሠ) የውጤት ትንተናው በአንድ ማዕከል አገልገሎት መስጪያ ጣቢያ በፈጻሚ አካላት ይከናወናል፡፡
26
ክፍል አራት
የባለድርሻ አካላት ተግባርና ኃላፊነት
ለ) የቁጠባን ባህል የሚያሳድጉ ስራዎችን ከሌሎች የልማት እቅዶች ጋር በማቀናጀት እንዲከናወኑ በበላይነት
በማስተባበር አፈጻጻሙን መከታተልና መደገፍ፤
መ) በትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችና የትምህርት ተቋማት የአነስተኛ የቁጠባ እና ብድር ተቋማት ቅርንጫፍ
ጽ/ቤት ከፍተው አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ መፍጠር፤
ረ) ከአበዳሪና አደራጅ ተቋማት በሚደርሳቸው ዝርዝር መረጃ መሰረት ውዝፍ ውስጥ የገቡ
ኢንተርፕራይዞችን በማሰባሰብና በማነጋገር ውዝፍ ብድር እንዲመለስ አመራር ይሰጣሉ፤
ሸ) የቁጠባ አሰባሰብ፣ የብድር ስርጭት፣ የብድር አመላለስና የውዝፍ ብድር አመላለስን ለመምራት በየደራጀው
መቋቋም የሚገባቸውን ኮሚቴዎች በማቋቋም በኃላፊነትና በተጠያቂነት መንፈስ እንዲሰሩ ያደርጋሉ፡፡
ለ) የቁጠባ ዕቅዱን አፈፃፀም ከሚመለከታቸው ፈፃሚ አካላት ጋር በመሆን በየጊዜው በመገምገም አስፈላጊውን
የማስተካከያ እርምጃ በማድረግ የገንዘብ አቅርቦትን ቅድሚያ ለትኩረት በሚሰጣቸው ዘርፎች በመስጠት
ካለው የብድር ፍላጎት ጋር የማጣጣም ኃላፊነት አለባቸው::
27
ሐ) የአንቀሳቃሽ ቤተሰቦች ለልጆቻቸው የስራ ባህል እንዲያስተምሩና የቅድመ ብድር ቁጠባ እገዛ በማድረግ፤
ዋስትና በመግባት፤የተበደሩትን ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ እንዲያውሉ በመከታታል፤በብድር አመላለስና
ቁጠባ እንዲሁም በአጠቃላይ በኢንተርፕራይዞቹ ሁለንተናዊ ድጋፍ ላይ የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ
ተከታታይ ግንዛቤ ማስጨበጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡
መ) በግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችና በትምህርት ተቋማት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን በመክፈት ሰራተኞች በቀጣይ
የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ ለማቋቋም የሚያስችላቸውን መነሻ ገንዘብ እንዲቆጥቡ ማድረግ፤
ሠ) በአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ገብቶ የፋይናንስ ድጋፍ አገልግሎት የሚሰጥ ባለሙያ መመደብ፤
ረ) ለተመለመሉ ደንበኞች ስለ ብድርና ቁጠባ ጠቀሜታ እንዲሁም ስለ ብድር አሰጣጡና ብድር አመላለስ ሂደቱ
ማሰልጠን፤
በ) በአንድ ማዕከላት ባለሙያዎች ቴክኒካል ድጋፍ ኢንተርፕራይዙ አዘጋጅቶ የሚያቀርበውን የንግድ ስራ ዕቅድ
ገምግሞ ማጽደቅ፤
ቸ) ውዝፍ እንዳይከሰት አስቀድሞ መከላከል እንዲቻል የተበዳሪዎችን የብድር አመላላስ ሁኔታ በሚገባ
መከታተልና ተበዳሪው ብድሩን በወቅቱ እንዲመልስ ግንዛቤ እንዲይዝ ያደረጋሉ፣
ኀ) ውዝፍ ብድር አደገኛ መሆኑን ሠራተኛው ተረድቶ እንዲንቀሳቀስ የአቅም ግንባታ ሥራ በቅድሚያ
ያከናውናሉ፣
ኘ) የውዝፍ መንስኤዎችን በመለየትና ተከታታይነት ያለው ትንተና በመስራት ውዝፍ ከመበራከቱ በፊት
በየደረጃው ያለው አመራር በቂ መረጃ አግኝቶ የተከሰተውን ውዝፍ ለማስመለስ እንደየአካበቢው ተጨባጭ
ሁኔታ ወቅታዊ እርምጃ እንዲወስድ በወቅቱ በማሳወቅ ተቀናጅተው ይሰራሉ፡፡
ሀ) አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ቁጠባን ለማሰባሰብ የሚያደርጉትን ጥረት በዋነኛነት መደገፍና ማስተባባር
ሐ) የአነስተኛ የፋይናንስ ተቋማትን የማበደር አቅም ለማጠናከር በሚደረገው የሥራ እንቅስቃሴ ውስጥ
ኃላፊነት በመውሰድ በአካባቢያቸው የሚገኙትን የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላትን ማስተባበርና፤
28
መ) የሕዝብ ንቅናቄ በመፍጠርና ግንዛቤን በማስጨበጥ አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት የሚያደርጉትን የቁጠባ
እንቅስቃሴ በግንባር ቀደምነት መደገፍ አለባቸው ::
ሰ) ስለሂሳብ መዝገብ አያያዝ እና የሥራ ዕቅድ ጠቀሜታ እንዲሁም አዘገጃጀት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ
መስራትና ቴክኒካል ድጋፍ ማድረግ
ሸ) የተሰጠ ብድር በወቅቱ መመለስ ሳይችል ሲቀር ከአበዳሪ ተቋም ጋር በመነጋገር የጋራ መፍትሄ በእንጭጩ
ይፈልጋሉ፣
ቀ) ውዝፍ የሆነውን የብድር መጠን መረጃ በየጊዜው መያዝና መንስኤዎቹን በመለየት መተንተንና
ለሚመለከተው አካል እንዲተላላፍ በማደረግ ቀጣይ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ተቀናጅተው ይሰራሉ፣
በ) በየደረጃው ያሉ የአመራር አካላት የውዝፍን መረጃ እንዲያገኙ በማድረግ ከፈፃሚ አካላትና ባለድርሻ አካላት
ጋር ተቀናጅተው ውዝፍ በማስመልሱ ተግባር እንዲሳተፉ ያደርጋሉ፣
ኢንተርፕራይዞች የስራ ፈጣሪነት ፣ ታታሪነት ፣ ስለ ቁጠባ ምንነት ስለቁጠባ አላማ እና አስፈላጊነት፣ ስለ ቁጠባ
አይነቶችና ስለሚያስገኙት ጠቀሜታ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት
29
34. የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጣቢያ ኃላፊነትና ተግባር
1) ስለቁጠባና ብድር ጠቀሜታና የአሰራር ሂደት ለማህበረሰቡ ፣ ለአንቀሳቃሾችና ለስራ ፈላጊዎች ግንዛቤ
ማስጨበጥ፣
3) ተበዳሪዎች በሚሰማሩበት የስራ መስክ ላይ የንግድ ስራ ዕቅድ እንዲያዘጋጁ ቴክኒካል ድጋፍ መስጠት፣
4) የተዘጋጀውን የስራ ዕቅድ በአግባቡ የተዘጋጀ መሆኑን የአነስተኛ የፋይናንስ ተቋም ተወካይ ሰራተኛ
ይገመግማል፣
6) የተስተካከለውን የንግድ ስራ ዕቅድ መሰረት በማድረግ የአነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ተወካይ ሰራተኛ
ኢንተርፕራይዙ ሊበደር የሚችለውን የገንዘብ መጠንና የራሱን አስተያየት በማካተት ለማጽደቅ የሚያስችሉ
ሰነዶችን አሟልቶ በአንድ ማዕከል አገልግሎት ጣቢያ ብድሩን እንዲያገኙ ያደርጋል፡፡
7) ከአንድ ማዕከል አገልግሎት ጣቢያ ውክልና በላይ የሆኑ የብድር መጠን በሚቀጥለው አካል እንዲጸድቅ
የሚያስችሉ ሰነዶችን አሟልቶ በመላክ ያስፈጽማል፡፡
8) ተበዳሪዎች የወሰዱትን የገንዘብ መጠን፣ ብድሩን የሚመልሱበት የጊዜ ሠሌዳ፣ ብድሩ ተከፍሎ
የሚጠናቀቅበት ጊዜና ሌሎችን መረጃዎች በአንድ ማዕከል ጣቢያ ተጠናቅሮ እንዲያዝ ከማድረግ በተጨማሪ
ድህረ ብድር ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ብድሩ ተጠቃሎ እስከሚመለስ ድረስ ትኩረት ሰጥተው ይንቀሳቀሳሉ፣
9) ውዝፍ እንዳይከሰት ከመከላከል ጀምሮ የተወዘፈንና በብድር ዋስትና ፈንድ የተሸፈነ ብድርን
ከሚመለከታቸው ፈጻሚና ባድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ማስመለስ ዋና ዋና ተግባሮቻቸው ናቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ፈፃሚ እና ባለድርሻ አካላት ከቁጠባ አሰባሰብ ፣ ከብድር አቅርቦት እና ከብድር ማስመለስ ጋር የተያያዙ
እና ሌሎች ተዛማጅ ስራዎችን በኃላፊነት መንፈስ መወጣት ኃላፊነት እና ግዴታ ያለባቸው ሲሆን ኃላፊነትን በአግባቡ
ባለመወጣት ምክንያት በሚያጋጥሙ የአፈፃፀም ጉድለቶች በግልና የጋራ ተጠያቂ ይሆናሉ፡፡
ክፍል አምስት
ለ) በክልል ደረጃ የሚዋቀር የጋራ ኮሚቴ የጋራ ዕቅድ ያዘጋጃል፡፡ አጠቃላይ አፈጻጸሙን በየ 3 ወሩ የመስክ
ጉብኝት በማድረግ ይገመግማል፣ ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ በጋራ መክሮ የጋራ አቅጣጫ
ያስቅምጣል፣
የዘርፉ ፈጻሚዎች በየሳምንቱ አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋሉ፣ የብድር ቁጠባ እንቅስቃሴው ሪፖርት ያዳምጣሉ፣
ሁኔታዎችን ይገመግማሉ፣ ለተከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ይሰጣሉ፡፡
ለ) በሁለቱም አካላት የተያዙ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ አንድ ወጥ የሆነ ሪፖርት በየወሩ ከቀበሌ እስከ ክልል ላሉ
ፈፃሚና ባለድርሻ አካላት ወጥነት ባለው የሪፖርት ፎርማት መሰረት መላክ ይኖርበታል፡፡
ሐ) የመረጃ ልውውጡና አያያዙም ጊዜንና ወጪን ለመቆጠብ እንዲቻል ከማኑዋል አሰራር ወጥቶ በሲስተምና
ዘመናዊ በሆነ አሰራር ተደግፎ እንዲሰራ እና እንዲያዝ መደረግ አለበት፡፡
31
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
ይህ ሞዴል መመሪያ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንዲሁም ከአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር ለማጣጣም
መሰረታዊ ይዘቱን ሳይለቅ እንደ አስፈላጊነቱ በክልሉ/ከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ወይም በፌዴራል ከተማ ልማትና ቤቶች
ሚኒስቴር አማካኝነት ሊሻሻል ይችላል፡፡
አቶ ጃንጥራር ዓባይ
የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር
32