You are on page 1of 42

በሰው መነገድና ሰውን በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር

ወንጀልን ለመከላከል
ለሀይማኖት አባቶች፤ ለሀገር ሽማግሌዎችና ለሚመለከታቸው
አካላት ግንዛቤ ለመፍጠር የተዘጋጀ ሰነድ

መጋቢት -----/2016 ዓ.ም


ወልቂጤ
እ”"D” ÅI“ S׋G<
የሰነዱ ይዘት
 መግቢያ
 የፍልሰት ዳራ
 መነሻ ሁኔታዎች
 አጠቃላይ ሀገራዊ ሁኔታ፣
 የክልላችን የኢ-መደበኛ ፍልሰት አጠቃላይ ገጽታና መንስኤዎቹ
 የዞናችን የኢ-መደበኛ ፍልሰት አጠቃላይ ገጽታና መንስኤዎቹ
 ወቅታዊ የፍልሰት መረጃዎች ትንተና እንደ ማሳያ
 ህገወጥ ስደት ለመከላከል መወያያ ነጥቦች
 በሰዎች መነገድን፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀሎችንና ኢ-
መደበኛ ፍልሰትን ለመከላከል የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች፣
መግቢያ
• በሠ/ማ/ጉ/ መምሪያ ተቋም ካሉት ሶስቱ(3) ግዙፍ ፖሊሲዎች
ውስጥ አንዱ ብሔራዊ የስራ ስምሪት ፖሊሲና እስትራቴጂ ሲሆን
የስራ ስምሪት ዘርፍ፣ ፖሊሲው መነሻ ተደርጎ የወጣ የአሰሪና
ሰራተኛ አዋጅ 1156/2011፣የህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና
ድንበር ማሻገር ወንጀል ለመከላከል የወጣ አዋጅ 909/2007
( አሁን የተሻሻለው 1178/2012 )፣የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት
አዋጅ 923/2008 (የተሻሽለው 1246/2013)፣ እንዲሁም
የሀገር ውስጥ ስራና ሰራተኛ ለማገናኘት የወጣ አዋጅ 632/-----
እና እነዚህ አዋጆች ለማስፈጸም የወጡ መሪያዎች ተግባራዊ
ለማድረግ በተሠጠው ሃላፊነት መሰረት ዕለት ተዕለት ከሚስተዋሉ
ውስብስብ የህብረተሰብ ችግሮች ደረጃ በደረጃ ለመቅረፍ
በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡
የቀጠለ
• በመሆኑም እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ ፖሊሲዎች፤አዋጆችና
መመሪያዎች መነሻ በማድረግ በዘርፉ ከሚከናወኑ በርካታ ተግባራት
መካከል የተለያዩ ስልቶችና አደረጃጀቶች በመጠቀም የህገ-ወጥ
የሰዎች ዝውውር መከላከል፣ከስደት ተመላሾች መረጃ በማደራጀት
ለድጋፍ ማስተባበር፣በልማት ድርጅቶች ከፍት የስራ ቦታዎች
በመመዝገብ ስራ ፈላጊዎችን እንደየፍላጎታቸው በመመዝገብና
ለስልጠና ተቋማት በመላክ ወደ ስራ በማሰማራት የዞኑን የሰው ሀይል
ፍላጎትና አቅርቦት ማጣጣም ፣ዜጎች በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ዘርፍ
ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል፣ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ስራ
ስምሪት በወጡ አዋጆችና መመሪያዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የግሉ
ዘርፍ ወደ ስራ ስምሪት እንዲመጡ በማድረግ የሥ/ሰ/አ/ኤጀንሲዎች
ፍቃድ መስጠትና ቁጥጥር ማድረግ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የፍልሰት ዳራ

• በዓለማችን የሰዎች ፍልሰት ወይም ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ


የሚደረግ ዝዉዉር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከኢኮኖሚያዊ፤
ማህበራዊ፤ ፖለቲካዊና ቴክኖሎጂ ሽግግሮችና እዉነታዎች ጋር
ያለዉ ቁርኝት ከፍተኛ ነው፡፡
• በ2017 (እ.አ.አ) የነበረው የአለም አቀፍ የፍልሰተኞች ቁጥር 258
ሚሊዩን ሲሆን በ2019 (እ.አ.አ) ይህ ቁጥር ወደ 272 ሚሊዮን
ከፍ እንዳለ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
• ዞናችንን ጨምሮ በክልላችንና በአገራችን የሚደረግ የፍልሰት
ሁኔታንም ስንመለከት እንደ አጠቃላይ ሁለት መልክ ያለው ነው፡-
በአገር ዉስጥ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በተለያየ ምክንያት
የሚደረግ ፍልሰት እና ድንበር ተሻጋሪ ፍልሰት ናቸው፡፡
መነሻ ሁኔታዎች
አጠቃላይ ሀገራዊ ሁኔታ
 ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መገኛ፣ የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላትና
ህዝቦቿ በተለያዩ ስርዓቶች የነበራቸዉን የዉስጥ ልዩነት ጭምር ወደ ጎን
በመተዉ በከፍተኛ መስዋዕትነት ለዘመናት ድንበሯን ያላስደፈረች ሀገር
መሆኗ በእኛ ብቻ የሚዘከር ታሪክ ሳይሆን ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡
 ይሁንና ይህንን ወርቃማ ዕድል ባለመረዳትና በሀገር ውስጥ እየተፈጠሩ
ያሉ የስራ ዕድሎችን አሳንሶ በማየት፣ በደላሎች ግፊት፣ በግንዛቤ እጥረት
ችግሮችና በአቋራጭ ሀብት ለማግኘት ሰዎች ባላቸው የተሳሳተ አስተሳሰብ
በርካታ ዜጎቻችን በኢ-መደበኛ መንገድ እየተሰደዱ ለአውሬ ሲሳይ
እየሆኑ፣ በኮንቴይነሮች ታፍነው እየሞቱና በተለያዩ ሀገራት እስር ቤቶች
እየታጎሩ፣ አለፍ ሲልም ከፎቆች ጭምር እየተወረወሩ ህይወታቸውን
እያጡና ለአካል ጉዳት እየተጋለጡ መሆናቸውን መስማትና ማየት
እየተለመደ መጥቷል፡፡
የክልላችን የኢ-መደበኛ ፍልሰት አጠቃላይ ገጽታና መንስኤዎቹ
 በክልላችን በሁሉም አካባቢዎች በሰዎች መነገድ፣ በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር
ወንጀልና መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት የሚስተዋል ቢሆንም በተለይ ወደ ዉጪ በሚደረገዉ
ፍልሰት የሀዲያ፣ የከምባታ-ጠምባሮ፣ የስልጤ፣ የጉራጌ፣ የሀላባ፣ የወላይታ፣ የጋሞና የጎፋ
ዞኖች የኢ-መደበኛ ፍልሰቱ ሰለባ የሆኑ መዋቅሮች ናቸው፡፡

 የመጀመሪያዎቹ ስድስት መዋቅሮች (ማለትም ሀዲያ፣ ከምባታ-ጣምባሮ፣ ስልጤ፣ ጉራጌ፣


ሀላባ እና ወላይታ) የኢ-መደበኛ ፍልሰቱ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡

 በአገር ዉስጥም በተለይ ህጻናት እና ወጣት ሴቶች ትምህርታቸዉን እያቋረጡ ከገጠር ወደ


ክልላችን ዞን ከተሞች፣ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ወደ ሌሎች ክልሎች ከተሞች በመፍለስ
በተለያዩ መደበኛ ባልሆኑ የሥራ ዘርፎች (በሽመና፣ በሎተሪ አዟሪነት፣ በእርሻ፣ በማዕድን
ቁፋሮ፣ በልመና፣ በጀብሎ፣ በቆሻሻ ማጓጓዝ፣ በሱቅ በደረቴ፣ በሊስትሮ፣ በሆቴሎች እና
በመንገድ ላይ ሴተኛ አዳሪነት) ተሰማርተው ለጉልበት ብዝበዛና ለተለያዩ ጉዳቶች ሰለባ
ሆነዋል፡፡ የተሻለ ኑሮ እና ህይወት ይገኛል በሚል ቀቢጸ ተስፋና ሰበብ ለሰዎች መነገድ
ወንጀል ተጋላጭም እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
የዞናችን የኢ-መደበኛ ፍልሰት አጠቃላይ ገጽታና መንስኤዎቹ

 በዞናችን በሁሉም አካባቢዎች በሰዎች መነገድ፣ በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልና
መደበኛ ያልሆነ ፍልሰት የሚስተዋል ቢሆንም በተለይ ወደ ዉጪ በሚደረገዉ ፍልሰት
ከፍተኛ ዝውውር ያለባቸው ወልቂጤ፤ አበሽጌ፤ እኖር፤ቸሀ፤ጌታ፤እንደጋኝ፤ ገ/ጉ/ወለኔ፤
እ/ኤ/መገር፤ ጉንችሬ ሲሆኑ ይብዛ ይነስ እንጂ ፤በሌሎችም የዞናችን ወረዳዎችና ከተማዎች
ዝውውሩ እንዳለ በተለያየ ጊዜ በምንቀበላቸው መረጃዎች ማረጋገጥ ችለናል፡፡

 የመጀመሪያዎቹ አራት መዋቅሮች(ወልቂጤ፤ አበሽጌ፤ እኖር፤ቸሀ; ገ/ጉ/ወለኔ)፤ የኢ-መደበኛ


ፍልሰቱ ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ሲሆን ጌታ፤እንደጋኝ፤እ/ኤ/መገር እና ጉመር ከነሱ
የሚቀጥሉ ናቸው፤

 ከክልሉ በተለይ ዞናችን በተመሳሳይ በአገር ዉስጥም በተለይ ህጻናት እና ወጣት ሴቶች
ትምህርታቸዉን እያቋረጡ ከገጠር ወደ ከተሞች፣ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ወደ ሌሎች
የክልሎች ከተማ በመፍለስ በተለያዩ መደበኛ ባልሆኑ የሥራ ዘርፎች ( በሎተሪ አዟሪነት፣
በእርሻ፣ በማዕድን ቁፋሮ፣ በልመና፣ በጀብሎ፣ በቆሻሻ ማጓጓዝ፣ በሱቅ በደረቴ፣ በሊስትሮ፣
በሆቴሎች እና በመንገድ ላይ ሴተኛ አዳሪነት) ተሰማርተው ለጉልበት ብዝበዛና ለተለያዩ
ጉዳቶች ሰለባ ሆነዋል፡፡
…… የቀጠለ (ገጽታና መንስኤዎቹ)
• የተሻለ ኑሮ እና ህይወት ይገኛል በሚል ቀቢጸ ተስፋና ሰበብ ለሰዎች
መነገድ ወንጀል ተጋላጭም እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
• ይህ ተግባር ለጥቂቶች የብልጽግና ምንጭ፣ ለብዙሀኑ ህዝባችን መርዶና
ሃዘን እንዲሁም ለዞናችን የማንነት ገጽታ ችግር ወደ መሆን ደረጃ
ደርሷል፡፡
• የዞናችን ተወላጆች በኢ-መደበኛ መንገድ ወደ ውጭ ሀገራት
የሚሰደዱባቸው መስመሮችና መነሻ አካባቢዎች ተለይተው
ይታወቃሉ፡፡ እነዚህም፡-
• በደቡባዊ መስመር፡-በዚህ መስመር እንደዞናችን በጣም ውስን የሆኑ
ከሃድያ ድበር አካባቢ ያሉና በተለያየ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው በሌላ ዞን
የሚኖሩ በቁጥር የሚፈልሱ ካልሆነ በስተቀረ በትክክል ከዞናችን
ተነስተው የሚሄዱ መረጃ ማግኘት አልተቻለም፡፡
…… የቀጠለ (ገጽታና መንስኤዎቹ)
• በምስራቃዊና ሰሜን ምዕራብ መስመር፡- ከዞናችን በአብዛኛው
ወልቂጤ እና አበሽጌ ወረዳዎች (በተለይም ሴቶች) መነሻ አድርገው
ወደ አረብ ሀገራት፣ ሱዳን፤ ሊቢያና አውሮፓ መዳረሻ
የሚያደርጉበት መስመር ነው፡፡
• አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ፡- በዚህ መስመር
እንደ ዞናችን በአብዛኛው ደቡብ አፍሪካና አረብ ሀገራትን መዳረሻ
የሚያደርጉ የኢ-መደበኛ ፍልሰተኞች የሚሄዱበት መስመር ሲሆን
በዚህ መስመር ሰለባ የሆኑ መዋቅሮች በወረዳዎች ተለይተው
ሲታዩ የሚከተለውን ገጽታ እናገኛልን፡፡
የቀጠለ
• አበሽጌ፣ ቸሃ፣ ወልቂጤ ከተማ፤ገ/ጉ/ወለኔ፤እኖር፤ ጉመር፤ጌታ፤
እንደጋኝ እና እዣ ወረዳዎች ሲሆኑ በተወሰነ መልኩ ሌሎችም
ወረዳዎች ላይ መኖሩ መረጃዎች ያሳያሉ ፡፡
• በዞናችን የስደቱ ገጽታና እያስከተለ ያለው ጉዳት ለመረዳት ያስችለን
ዘንድ ከወንጀሉ ውስብስብነት አንጻር የተሟላ ዞናዊ መረጃ ማቅረብ
አዳጋች ቢሆንም በተለያዩ ጊዜያት ከክልሉ፤መንግስታዊና መንግስታዊ
ካልሆኑ ተቋማት እና በራሳቸው መንገድ የመጡትን የተሰበሰቡ የህገ-
ወጥ የሰዎች ዝውውር ተጋላጮች የተገኘው መረጃ እንደሚከተለው
ለመዳሰስ ተሞክራል፡፡
የቀጠለ

 ከ2014 በጀት አመት መጋቢት ጀምሮ እስከ 2015 በጀት አመት


ታህሳስ ማጠቃለያ ድረስ ብቻ ከሳውዲ አረቢያ እስር ቤት ከስደት
የተመለሱ ዜጎች መረጃ ስንመለከት ከክልል መረጃቸው የተላከልን
ድምር.71 ሲሆኑ ታስረው ቆይተው ከመንግስት ውጪ
በራሳቸው ጊዜ አምልጠው የመጡ ድምር 10 በጥቅሉ
ድምር.81 ወደ ዞናችን ገብተዋል፡፡ እነዚህም ከታች በዝርዝር
ተቀምጣል
በ2014 ከሳዉዲ አረቢያ እስር ቤቶች ወደ ዞናችን የተመለሱ
መረጃ በወረዳ ሲታይ
የወረዳ ስም የተመላሽ ብዛት የወረዳ ስም የተመላሽ ብዛት
 እኖር 5
 ቸሀ 6
 እዣ 4
 ጌታ 3
• ወልቂጤ 15
 ገ/ጉ/ወለኔ 15 ም/አክሊል 1
• ጉመር 8
• አበሽጌ 2
• እንደጋኝ 2
• ወረዳቸው ለይቶ ማወቅ ያልተቻለ 10
በ2014 በጀት ዓመት አጠቃላይ የዞኑ የፍልሰተኞች መረጃ (ምንጭ:-
ከወረዳ መዋቅሮች የተሰበሰበ ሪፖርት)

• በ2014 በጀት አመት በተወሰኑ ቀበሌዎች በተደረገ አሰሳ ወደ ውጭ ሀገር የፈለሱ


የዞናችን ወጣቶች ከ297 ቀበሌዎች ውስጥ በ63 ቀበሌ ወ.154 ሴ.549 ድ.703
መፍለሳቸው መረጃው ያመላክታል
• ፈልሰው የተመለሱ፤በፍልሰት የሞቱ፤የአካል ጉዳት የደረሰባቸው፤የት እንዳሉ
የማይታወቅ መረጃው ለማጠናቀር ቢሞከርም ለጊዜው ከመጀመርያው የዞናችን
ወረዳዎች ጋር አንድ ላይ በመሆኑ ለመለየት ጊዜ ወሰወዶብናል በቀጣይ የመለየት
ስራ እንሰራለን፡፡
• እንደ ዞናችን ወደ ውጭ ሲፈልሱ በአብዛኛው መነሻቸው አዲስ አበባና ሌሎች
የክልል ከተሞች ስለሆነ ለመረጃ አሰባሰብ ምቹ ባለመሆኑ እንጂ ፍልሰተኞች ከዚህ
እጥፍ በላይ መሆናቸው የሚያሳዩ አመላካቾች ነገሮች አሉ፡ ሲመለሱም
በተመሳሳይ ቁጥሩ ከዚህ በላይ ነው፡፡
… የቀጠለ(ወቅታዊ የፍልሰት መረጃ)
 የሀገር ውስጥ የሰዎች ዝውውር ሁኔታን በሚመለከት በኢትዮጵያ ዉስጥ በህገ-ወጥ
መንገድ የሚዘዋወሩት እና በአገር ዉስጥ በሰዉ የመነገድ ወንጀል ተጠቂ የሚሆኑት
በአመዛኙ ከ8-24 የዕድሜ ክልል የሚገኙ ህጻናትና ወጣቶች ናቸዉ፡፡

 ህጻናትንና ወጣት ሴቶችን በህገወጥ መንገድ ከገጠር ወደ ከተማ እንዲፈልሱ ከሚያደርጉ


ምክንያቶች መካከል ሰዎች ርካሽ ጉልበት መፈለጋቸዉ እና ሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት
ተጠቃሽ እንደሆኑ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡

 ለዚህም አዲስ አበባን ጨምሮ ወደ ሌሎች አጎራባች ክልሎች በደላላ ግፊት፣ በግንዛቤ
ችግርና በመሳሰሉት ምክንያቶች የሚፈልሱ የህጻናት ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መሆኑን
በየከተሞቹ በጎዳና ተዳዳሪነትና በሴተኛ አዳሪነት ህይወት እየገፉ ያሉትን ህፃናትን ብቻ
ማየት ለጉዳዩ በቂ አስረጂ ነው፡፡
የኢ-መደበኛ ፍልሰት መንስዔዎች

የፍልሰት ሳቢ (Pulling) ምክንያቶች የፍልሰት ገፊ (Pushing) ምክንያቶች

 የተቀባይ አገራት ሰፊ የሰው ኃይል ፍላጎት  የተሳሳተ ግንዛቤ እና የአመለካከት ችግር


 በተቀባይ አገራት ያለው በዝቅተኛ ደረጃ  ድህነት፣ ሥራ አጥነትና የተሻለ ሕይወት
የሚገኙ የስራ ዕድልና የተሸለ ክፍያ ፍለጋ
 የተቀባይ አገራት የዕድገት ደረጃ ከእኛ  የቤተሰብና የአቻ ግፊት
የተሻለ መሆን  በአገር ውስጥ ያለውን የሥራ ዕድል
 በተቀባይ አገራ የሚታዩ አማላይ ተገንዝቦ አለመጠቀም ወይም ሥራ መናቅ
ህንጻዎችና መኪኖች  የሕገ-ወጥ ድርጊቱ ተዋናዮች መበራከት
 የተቀባይ አገራት ዜጎች ለአነስተኛ ሥራ  ሕገ-ወጥ ደላሎች
ያላቸው ፍላጎት አናሳ መሆን
 በሕጋዊነት ሽፋን ህገ-ወጥ ድርጊት
የሚፈጽሙ ሥራና ሠራተኛ አገናኝ
ኤጄንሲዎች
የኢ- መደበኛ ፍልሰት ጉዳቶች
 ኢ-መደበኛ ፍልሰትና በሰዎች መነገድና በህገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀሎች እያስከተሉት
ያሉ ጉዳቶች፡-
 ሰብአዊ ቀውስ
 ማህበራዊ ቀውስ
 ፖለቲካዊ ቀውስና
 ኢኮኖሚያዊ ቀውስ

 ሰብአዊ ቀውስ
 ሞት (በባህር ላይ፣ በየበረሀው)፣
 ከፍተኛ የአካል እና የሰውነት ክፍል ጉዳት፣
 ስነ-ልቦናዊ ቀውስ

 ማህበራዊ ቀውስ
 የልማት ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን ይፈታተናል፤
 ተዘዋውሮ በመሥራት ላይ የተዛባ አስተሳሰብ እንዲያዝ የሚያደርግ ወንጀል መሆኑ፣
የቀጠለ
 እንደ አገር ያለንን የሰው ኃይል ተጠቅመን የፀረ-ድህነት ትግላችንን በማጠናከር ልማታችንን
እንዳናረጋግጥ የሚፈታተን መሆኑ፣
 የትምህርትና ሥልጠናን እሴት በማሳነስ የማስፈፀም አቅማችንን በሂደት የሚያዳክምና የልማትና
የመልካም አስተዳደር ሥራችንን የሚያደናቅፍ መሆኑ፣

 ፖለቲካዊ ቀውስ
 በሄዱባቸው አገራት በሕገወጥ ተግባራት (በአሸባሪነት፣ በአደንዛዥ ዕፅና የጦር መሣሪያ
አዘዋዋሪነት፣ በሴተኛ አዳሪነት…ወ.ዘ.ተ) በመሳተፍ
 የአገር ገጽታን የሚያጠፉ
 በህገዊ መንገድ ለሚሄዱ ዜጎች እንቅፋት መሆን
 በአገር ውስጥ ከሕጋዊነት ይልቅ ሕገ-ወጥነትን ማስፋፋት፤ የሕግ የበላይነትን መናድ፣ የዴሞክራሲ
ሥርዓት ግንባታን ለመሸርሸር አመቺ ሁኔታ መፍጠር፣
 ዜጎች በአገሪቱ ውስጥ ባሉት ሕጋዊ ተቋማት ላይ እምነት እንዲያጡ በማድረግ ሥርዓት
አልበኝነትን ማስፈን፣
 ከውጭ አገር ተቋማት ጋር በመሻረክ ዜጎች በሌሎች አገሮች ላይ እምነት እንዲጥሉ ማድረግ፣
 በአጠቃላይ ዜጎች ብሔራዊ ስሜት እንዲያጡ የሚያደርግ መሆኑ
የቀጠለ
 ኢኮኖሚያዊ ቀውስ
 ከህጋዊ ኤጀንሲዎች መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ግብርና ታክስ በመደበቅ
የግል ጥቅም ላይ ማዋልና የልማት ሥራዎችን መጉዳት፣
 አምራች የሆነው ወጣት ክፍል (Youth Labour Force) መፍለሱ
በኢኮኖሚ ዕድገታችን ያለዉ አሉታዊ ተጽእኖ፣
 ፍልሰተኞችና ቤተሰቦቻቸው ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ኪሣራና ውድቀት
እያደረሰ መሆኑ፣
 ከፍተኛ የጉልበት ብዝበዛ (ለረጅም ሰዓታት መሥራት)
እንደ አገር ዋና ዋና የፍልሰት መውጫ በሮች (Major migration routes)

ሀ. ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ

ለ. ሞያሌ መውጫ በር

ሐ. መተማ መውጫ በር

መ. ጅጅጋ መውጫ በር

ሠ. ሚሌ/ጋላፊ መውጫ በር

ረ. ኩምሩክ መውጫ በር
ዜጎች መደበኛ ባልሆነ መንገድ ወደ ዉጭ ሲፈልሱ የሚያወጡት ወጪ

ወደ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ


ለሚደረገው ጉዞ በአማካይ ወደ
364,000 ብር ያህል ፍልሰተኞች
ያወጣሉ፡፡
በሞያሌ፣ በኩል ወደ ኬንያ ቀጥሎም
በታንዛኒያ፣ ማላዊ፣ ዚምባብዌ በኩል
ዛምቢያን አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ
ለሚደረገው ጉዞ በአማካይ ወደ
450,000 ብር ያህል ፍልሰተኞች
ያወጣሉ፡፡

ወደ መካከለኛ ምስራቅ አገራትና ደቡብ ሱዳን


ለሚደረግ ጉዞ በአማካኝ ወደ 31,200 ብር
ያህል ፍልሰተኞች ያወጣሉ፡፡
ህገ-ወጥ ስደት ለመከላከል የቀረበ ዋና ዋና ነጥቦች

• 1. በሰዎች መነገድና ህገ-ወጥ ድንበር ማሻገር ወንጀል ወይም በሌላ ስያሜው ህገ-ወጥ
የሰዎች ዝውውር መከላከል ተግባር ስንመለከት በአሁኑ ወቅት እጅግ በተራቀቀና
በተደራጀ መልክ የሚከናወን ዓለም አቀፋዊ ወንጀል በመሆኑ የችግሩ ውስብስብነትና
አሳሳቢነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ዜጐች ከሀገር ሀገር በመዘዋወር
መስራት ህጋዊ መብት ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች በተለይም በህገ-ወጥና በአቋራጭ
መንገድ ለመክበር በሚሯሯጡ ስግብግብ ደላሎች በመታለል በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር
ለመውጣት በሚደረግ እንቅስቃሴ በርካታ ዜጐች ለከፋ ችግር እንግልትና ሞት
ተዳርገዋል፤ሴት እህቶቻችን ተደፍረዋል፣ ጉልበታቸው ተበዝብዘዋል ፣ የጤነኛ
ወጣቶችን ብልታቸው ወጥቶ ተሸጠዋል፣ወላጅ እናት አባት ለዘመናት ደክመው ያፈሩት
ቋሚ ሀብት ንብረታቸው ተዘርፈዋል፣ ሰብዓዊ መብታቸውና ክብራቸው
ተጥሰዋል፤በበረሀ በረሃብና በጥም ወድቀዋል፤በርካታ ዜጎቻችን በዚህ ህገ-ወጥ ስደት
ይኑሩ ወይም ይሙቱ ጭምር የደረሱበት አይታወቅም፡፡
የቀጠለ
• ችግሩ በዚህ አያበቃም ገንዘብ ይልክልኛል በሚል ባልተጨበጠ ተስፋ ያለውን
ጥሪት ሀብትና ንብረት አወድመው የላኩ ቤተሰቦች ያልጠበቁት ነገር ይከሰትና
አጠቃላይ ቤተሰብ ለክፍተኛ ማህበራዊ ተጋላጭነት ለቤተሰብ መፍረስና
መበታተን ምክነያት እየሆነ ይገኛል፡፡ ከብዙ መከራና ስቃይ በኋላ ወደ መዳረሻ
ሀገር የገቡትም ቢሆን ህጋዊው መስመር ተከትለው ባለመውጣታቸው ወደ
ውጭ ሳይወጡ ከአንድ ቤት በላይ በዘመድ አዝማድ ጉልበታቸው
እየተበዘበዙና ከአቅም በላይ የሆነ ስራ እየሰሩ የፈለጉትን ሳያሳኩ የሄዱበትን
የደላላውን ብር እየከፈሉ ለከፍተኛ የአእምሮ ጭንቀትና ህመም የሚጋለጡም
ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡ከአቅም በላይ ስራ ሰርተው ከቆይታ በኋላ ደምና
ስጋቸው አልቆ፤ብዙዎቹ መውለድ የማይችሉ ሆነው ስለሚመለሱ ትዳር
አጥተው ያለ ዘር አና የአእምሮ ዘገምተኛ ሆነው ህይወታቸው ከንቱ ሆኖ
ይቀራል፡፡ ታድያ ለዚህ ሁሉ ችግር በቀጥታ ሰለባ የሚሆኑት ወጣቶች
በመሆናቸው ህገ-ወጥ ድርጊቱን ለመከላከል ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም
ከችግሩ አሳሳቢነትና ስፋት አንጻር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ፡፡
የቀጠለ
• እስካሁን ድረስ በዞኑ ፣በክልሉና ከአለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት
(IOM) ጋር በመቀናጀት በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች 108
ቀበሌያት ላይ ስልጠና በመስጠት የማ/ሰብ ውይይት
በማቋቋም ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን ከኮቪድ መምጣት ጋር
ተያይዞ በአሁን ወቅት የተቀዛቀዘ ቢሆንም በቀበሌ የማ/ሰብ
ውይይት በማድረግ ስደት የሚጸየፍ ማህበረሰብ በመፍጠር
ከክልሉ አንደኛ በመውጣት በፌደራል ደረጃ ምርጥ ተሞክሮ
የተቀመረበት እንደነበርም አይተናል፡፡
የቀጠለ
• ሌላው ችግሩ በከፋባቸው አካባቢዎች ከተማሪዎች መጠነ-
ማቋረጥ ጋር በቀጥታ ስለሚያያዝ ስደት በሚበዛባቸው
አካባቢዎች ባሉ በ30-ት/ቤቶች አመቻቾች በማሰልጠን የአቻ
ለአቻ ክበብ በማቋቋም የውይይት ፕሮግራሞችን በማስጀመር
በሰለጠኑ አመቻቾች አማካይነት ከት/ቤቱ ተማሪዎች በማቀፍ
በክበቡ፣ በወመህ፣ በት/ቤቱ ሚኒሚዲያ በበዓላትና በሰልፍ
ፕሮግራሞች ሰፋፊ የግንዛቤ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፤ በዚህም
ድጋፍና ክትትል ተደርጎ ግብረ-መልስ ሲወርድ የነበረና እምርታዊ
ለውጥ የታየበት እንደነበር የሚታወቅ ቢሆንም አሁን ባለው
ሁኔታ ከኮቪድ መከሰት በኋላ ባብዛኛው ት/ት ቤት ውይይቱ
ተቃርጦና በከፍተኛ ሁኔታ ተቀዛቅዞ ይገኛል፡፡
በሰዎች መነገድን፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀሎችንና ኢ-መደበኛ ፍልሰትን
ለመከላከል የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች

 በዞናችን እስከ 2015 ግማሽ የበጀት ዓመት ድረስ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ
ኢ-መደበኛ የሰዎች ፍልሰት ተጋላጭ መዋቅሮች ውስጥ በአለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት
(IOM)፤በክልሉ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና በዞን ሠ/ማ/ጉ/መምሪያ በጥቅሉ
108 ተጋላጭ ቀበሌያት በማህበረሰብ ዉይይት ፕሮግራም እንዲታቀፉ ተደርጓል፡፡

 በ30 ትምህርት ቤቶች የአቻ ለአቻ ዉይይት ክበባት ተቋቁመዉ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ
ተደርጓል፡፡

 በወልቂጤ FM 89.2 የሬዲዮ የአየር ሰዓት በቋሚነት በመከራየት አስተማሪ ፕሮግራሞች


እየተዘጋጁ እንዲሰራጩ ተደርጓል፡፡

 ትላልቅ መድረኮችንና አዝናኝ ኩነቶችን በማዘጋጀት የንቅናቄና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን


በመስራት ጥረት ተደርጓል፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 የወንጀሉን አስከፊነት አስመልክቶ የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና


ወስደዉ ፕሮግራሙን በከፊል ዉጤታማ ያደረጉ ቀበሌያት እና
ትምህርት ቤቶች ከኢ-መደበኛ ፍልሰት ነጻ ያደረጉ አመቻቾችንና
መዋቅሮችን ተሞክሮዎቻቸዉን በማስፋት፤ የልምድ ልውውጥ
በማድረግ የተለያዩ ጥረቶች ለማድረግ ተሞክሯል፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 ሆኖም ግን እነዚህን የግንዛቤ ፈጠራና የባህሪይ ለዉጥ ማምጫ


ፕሮግራሞች በየቀበሌዉ እና በየትምህርት ቤት ደረጃ ስልጠናዎች
ተሰጥተዉ ወደ ስራ ከገቡ በኋላ የዉይይት መርሃ ግብሩን ጠብቆ
ዉይይቱን በማስቀጠል ረገድ፣ የተሰጡ ሞጁሎችን ጠብቆ
አጀንዳዎችን ከማወያየት እና የሚፈለገዉን ዉጤት ከማስመገብ
አንጻር ያለዉ አፈጻጸም ሲታይ በአመዛኙ ክፍተት የታየበት ነዉ፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 የኢ-መደበኛ ወንጀሉን አስከፊነት ለመከላከል እንዲቻል የተፈጠሩ


አደረጃጀቶቹ ክትትል ባለማድረጋቸው ምክንያት የማህበረሰብ
ውይይትና የት/ቤቶች አመቻቾች ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ
በቀጣይነት በየ15 ቀን ኢ-መደበኛ ፍልሰቱን ከመቆጣጠር አንጻር
ቀበሌው ያለበትን ሁኔታ እየገመገሙና ለማህበረሰቡ የተወያዩበትን
ጉዳይ ግንዛቤ እያስጨበጡ ስደቱን የሚቋቋም ማህበረሰብ
ከመፍጠር ይልቅ ሰልጥነው በአብዛኛው ምንም እንቅስቃሴ
የማያደርጉበት ሁኔታ መኖሩንና ለችግሩም በየደረጃዉ ያለዉ
አመራር እና ፈጻሚ የክትትል እና ድጋፍ ሥራዉ የላላ መሆኑን
የሚያሳይ ሲሆን የዉይይት አመቻቾችም የሚጠበቅባቸዉን ሚና
በአግባቡ አለመወጣታቸዉ ዉጤታማነታቸዉ ዥንጉርጉር መሆኑ
በየጊዜው በሚመጡ ሪፖርቶችና መረጃዎች ያሳያል፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 ሌላው እንደ ዞን በኢ-መደበኛ ፍልሰቱ ወንጀል አስከፊነት ዙሪያ


ግንዛቤ ከመፍጠር ጎን ለጎን ስራ አጥ ዜጎች በዞኑ ውስጥ በከተማ
በአነስተኛና ጥቃቅን ዘርፍ፣ በገጠር ስራ እድል ፈጠራ፣ በመንግስትና
የግል ኢንቨስትመንቶች በየጊዜው በርካታ ቋሚና ጊዜያዊ የስራ
ዕድሎች እየተፈጠሩ ቢሆንም በተለይም ለፍልሰት በይበልጥ ተጋላጭ
በሆኑ መዋቅሮቻች አካባቢ ያሉ ወጣቶች እነዚህን ዕድሎች
ተጠቅመው ከመለወጥ ይልቅ አሳንሶ የማየትና በአቋራጭ የመክበር
አመለካከት በስፋት የሚንጸባረቅ በመሆኑ በአብዛኛው በአገር ውስጥ
ሰርቶ ከመቀየር ይልቅ ከደቡብ አፍሪካና አረብ ሀገራት ስደት ውጭ
መለወጥ እንደማይችሉ ራሳቸውን አሳምነው እስከ አሁን ድረስ
መደበኛ ባልሆነ መንገድ በከፍተኛ ቁጥር እየፈለሱ ይገኛሉ፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 በሰዎች መነገድ፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል


እንዲባባስ ዋና ተዋናይ የሆኑ ህገወጥ ደላሎችንና ተባባሪዎቻቸውን
በማህበረሰቡ ተሳትፎ እንዲጋለጡና ህጋዊ እርምጃ
እንዲወሰድባቸው በማድረግ ረገድ መንግስት ጥፋተኞች እንደ
ወንጀላቸው ሁኔታ ተገቢዉ ቅጣት በፍርድ ውሳኔ የሚያገኙበትን
ሁኔታ የደነገገ አዋጅን ከማጽደቅ ጀምሮ በአዋጁ ዙሪያ ግንዛቤ
የማስጨበጥና ህገወጥ ደላሎች አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ሰፊ
ጥረት ተደርጋል፡፡
 በየአካባቢው ደላሎችን ከማጋለጥ እና ተመጣጣኝ ቅጣት
በመወሰን ጭምር ጠንካራ ትግል እየተደረገ ቢሆንም አብዛኞቹ
አካባቢዎች በቂ ማስረጃ በማቅረብ ውሳኔ ከማሰጠት አንጻር ሰፊ
ክፍተት የሚታይበት ነው፡፡
… የቀጠለ (የተደረጉ ጥረቶችና ተግዳሮቶች)

 በህገወጥ መንገድ የሌሎች ሀገራትን ድንበር ሲሻገሩ ተይዘው


ማረሚያ ቤት ፍርዳቸውን ጨርሰውና በተለያዩ ሀገራት በስደት
ቆይተው ወደ ዞናችን የሚመለሱትን መልሶ ማቋቋም አንዱ
ትኩረት የተሰጠው ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ የተመላሾችን መረጃ
በአግባቡ የመሰብሰብ፣ የስነልቦና ድጋፎችን በመስጠት ወደ
ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ከማድረግና የብድር አገልግሎት
ከማመቻቸት አንጻር ጅምር ስራዎች አሉ ቢባልም በአብዛኞቹ
ተጋላጭ ወረዳዎች ወደታች ተወርዶ ሲፈለግ አለማግኘትና
ተግባሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ አለመሆኑን በተለያየ ጊዜ
በተደረጉ የድጋፍ እና ክትትል ማወቅ የተቻለ በመሆኑ በቀጣይ
በትኩረት መስራት የሚገባን ተግባር መሆኑ ተለይቷል፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በቂ የሆነ ለውጥ ያላመጡበት ዋና ችግሮች

 የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም በሰው የመነገድና ሰውን በሕገ-ወጥ


መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል አስከፊነት ለህብረተሱ ግንዛቤ
የማስጨበጥ ሥራ ቢሰራም ከተለያዩ ሎጂስቲክና በጀት እጥረት
ተደራሽ አለማድረግ እና በወቅቱ አለመገምገም፣
 በአገር ውስጥ የሚገኙ እንዲሁም ከውጭ አገር የተመለሱ
ተጎጂዎች ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ
እንዲያገኙ ከማድረግ አካያ ውስንነቶች መኖራቸው፤፣
 ወረዳ ከተማ የሚመለከታቸው አካላት ለጉዳዩ ትኩረት
አለመስጠት፡፡
 የሰለጠኑ አመቻቾች በየጊዜው አበልና ጥቅማጥቅም መፈለጋቸው፤
የቀጠለ

• የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ቀበሌዎች ምርጥ ተሞክሮ


በመቀመር አለማስፋት፤
• ድጋፍና ክትትል በተገቢው አለማድረግና ከፍተኛ የሆነ
የበጀት እጥረት መኖር፤
• ለአወያዩች ወይም ለአመቻቾች የማነቃቂያ ፕሮግራሞች
አለማዘጋጀት…ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉ ተግዳሮቶች ገጥመዋል፡፡
በሰዎች የመነገድ አደጋዎች እና ጉዳቶች
በበረሀ ሲጋዙ ውሀ ጥምና ረሀብ
የአውሬ እና የአሞራ እራት መሆንና ያለቀባሪ በየጢሻው መቅረት
የቀጠለ
አመሰግናለሁ!!!

You might also like