Professional Documents
Culture Documents
Biodiversity Institute Biodiversity Conservation Usage Ef
Biodiversity Institute Biodiversity Conservation Usage Ef
መ/ቤት
የብዝሀ ሕይወት ሀብት አጠባበቅ
እና አጠቃቀምን በተመለከተ
የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት
0
የአርዕስት ማውጫ
ክፍል አንድ ................................................................................. 1
መግቢያ..................................................................................... 1
የኢንስቲትዩቱ ዓላማ፣ ሥልጣን እና ተግባር......................................................... 5
ኢንስቲትዩቱ የተቋቋመበት ዓላማ ........................................................................... 5
የኢንስቲትዩቱ ሥልጣን እና ተግባር ......................................................................... 5
የኢንስቲትዩቱ ድርጅታዊ መዋቅር እና የሰው ኃይል ............................................... 6
የኢንስቲትዩቱ የፋይናንስ ምንጭ .................................................................... 7
1
በተደረጉት የዘረመል ሀብት የሽያጭ ውሎች መሠረት ክፍያዎች መፈፀማቸውን በተመለከተ........... 35
የዘረመል (genetical) ሀብቶች ሽያጭ ውሎቹ ላይ የሀብቱ ባለቤት፣ መፍለቂያ ሀገርና ቦታ በግልጽ
መቀመጡን በተመለከተ ...................................................................................... 36
የዘረመል (genetical) ሀብት ሽያጭ ውሎች እና መረጃዎች የሚዘጋጁበትን ቋንቋ በተመለከተ ........ 37
የብዝሀ ሕይወት ሀብት ዝርያዎች አለአግባብ ከሀገር እንዳይወጡ ለማድረግ ያለውን አሠራር
በተመለከተ .................................................................................................... 37
ከዘረመል (genetical) ሀብት ሽያጭ የአካባቢው ማኅበረሰ ተጠቃሚ መሆኑን በተመለከተ ............. 39
በኢንስቲትዩቱ በሕግ ሊያዙ የሚገቡ የብዝሀ ሕይወት ጉዳዮችን የሚከታተል አካል መኖሩን
በተመለከተ .................................................................................................... 39
መ. ኢንስቲትዩቱ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሊያሠራ የሚያስችል
የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን በተመለከተ .................................................... 40
በክልል በሚገኙ ባለድርሻ አካላት ውስጥ ከብዝሀ ህይወት ጋር ተያያዥ የሆኑ ተግባራትን
የሚያከናውን አደረጃጀት መኖሩን በተመለከተ ............................................................. 40
ብዝሀ ሕይወትን በተመለከተ የሚደረጉ የመረጃ ልውውጦችን በተመለከተ ........................ 41
ከባለድርሻ አካላት ጋር ብዝሀ ሕይወትን በተመለከተ መደበኛ የመረጃ ልውውጥ
የሚደረግበት ሥርዓት መዘርጋቱን በተመለከተ ....................................................... 41
የዓለም አቀፍ ስምምነት አፈጻጸምን በሚመለከት ዓመታዊ ሪፖርት ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
የሚቀርብ መሆኑን በተመለከተ .......................................................................... 42
ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ መደበኛ የግንኙነት መድረክ፣ ቅንጅታዊ አሠራር እና
ግምገማዎች መኖራቸውን በተመለከተ ................................................................. 43
አባሪዎች .....................................................................................I
የኦዲት መመዘኛ መስፈርት ........................................................................... I
የኢትዮጵያ የብዝሀ ሕይወት ሀብት ብዛት እና አይነት .............................................. IV
GLOSSARY /የቃላት መፍቻ/ ....................................................................... IV
2
ክፍል አንድ
መግቢያ
1. በዓለም አቀፍ ደረጃ በጸደቀው ዓለም አቀፍ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት (CBD)
1
መገኛ ማዕከላት አንዷ እንድትሆን ያደረጋት ሲሆን፣ ከአፍሪካም አልፎ በዓለም
የጎላ የብዝሃ ህይወት ሀብት ካላቸው እና ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጥቂት ሀገሮች
ጋር ለመቆጠር አስችሏታል::
i
www.iucn.org/; www.iucnredlist.org/
2
ዕድገት ጋር ያልተመጣጠነ የህዝብ ቁጥር መጨመር ወዘተ ምክንያት በዓለም
አቀፍ ደረጃ በተለይም የብዝሀ ሕይወት ክምችት በስፋት በሚገኝበት በምድር
ወገብ አካባቢ ባሉ ሀገራት የጎላ ጠቀሜታ ያላቸው የብዝሀ ሕይወት ሀብቶች
በከፍተኛ ፍጥነት በመመናመን እና በመጥፋት ላይ እንደሚገኙ በየጊዜው
የሚወጡ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ii
ii
http://www.globalstewards.org/issues.htm
iii
The 2010 Nagoya COP10 Biodiversity summit in Japan
3
10.በተለይ የሀገሪቱን 84 ከመቶ የሕዝብ ቁጥር በሚይዘው የገጠሩ አካባቢ እነዚህ
4
የኢንስቲትዩቱ ዓላማ፣ ሥልጣን እና ተግባር
ኢንስቲትዩቱ የተቋቋመበት ዓላማ
13.ኢንስቲትዩቱ የተቋቋመው ሀገሪቱ ያላትን የብዝሀ ህይወት ሀብት እና ይህን
iv
"ዘቦታ ጥበቃ" ማለት በተፈጥሮ የአኗኗር ሁኔታ ውስጥ በሚገኙበት አኳሆን እንዳሉ የሚፈጸም
የእንስሳት፣ የእጸዋት እና የጥቃቅን ህዋሳት አጠባበቅ ነው፡፡
v
"ኢዘቦታ ጥበቃ" ማለት በተፈጥሮ የአኗኗር ሁኔታ ውጭ በማኖር የሚካሄድ የእንስሳት፣ የእጸዋት
እና የጥቃቅን ህዋሳት አጠባበቅ ነው፡፡
5
በተለያዩ ሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ ችግሮች ምክንያት የብዝሀ ሕይወት
ሀብት የተመናመነባቸው አካባቢዎች በማጥናት እና በመለየት ቀደም ሲል
ከተሰበሰበው እና በኢዘቦታ ጥበቃ የሚገኘው ዘረመልን በመጠቀም መልሶ
እንዲተካ ለሚመለከታቸው አካላት ሃሳብ በማቅረብ እና ተቀባይነት
ሲያገኝም ሥራ ላይ የሚውልበትን ሁኔታ ማመቻቸት እና ድጋፍ
መስጠት፤
ናቸው::
6
ከነዚህም ውስጥ 13 (8 %) የዶክትሬት ድግሪ፣ 12 (7.4%) ሁለተኛ ድግሪ፣
7
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ሁለት ማኅበራዊ ዘር ባንኮች
(community gene banks) በናሙና ተለይተው በኦዲቱ ተዳሰዋል፡፡
8
ለክዋኔ ኦዲቱ የተለየው የኦዲት አካባቢ
(Potential Audit Area)
21.ከላይ የተመለከቱትን የኦዲት ዘዴዎች በመጠቀም የኦዲት ቡድኑ አንድ
9
2.1 ኢንስቲትዩቱ የሀገሪቱን የብዝሀ ሕይወት ሀብት በብቃት እና
ኢኮኖሚያዊ በሆነ መልኩ ለመጠበቅና ዘላቂነት ባለው
ሁኔታ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ በፌዴራል ደረጃ
ከሚገኙ መንግስታዊ ከሆኑ መ/ቤቶች እና በክልል ደረጃ
ከሚገኙ መንግስታዊ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት
እየሠራ መሆኑን መገምገም፡፡
10
የአሠራር ሂደት መግለጫ (Process
Description)
24.ኢንስቲትዩዩ በብዝሀ ሕይወት ዙሪያ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ሊያከናውን
11
28.በስተመጨረሻም የተጠበቀና ባህሪው የታወቀ ብዝሀ ሕይወት ሀብት ማቅረብ
12
ስምምነቶችን መሠረት በማድረግ ከሚገኘው ጥቅም 50% የሚሆነው የብዝሀ
ህይወት ሀብቱ ከተገኘበት ወይም ከተወሰደበት ቦታ ለሚገኝው ማህበረሰብ
ይሰጣል፡፡ በመጨረሻም ከብዝሀ ህይወት ዝውውር የተገኘ ጥቅም ፍትሀዊነትን
በተከተለ ሁኔታ የሚከፋፈልበትን መንገድ በማመቻቸት የብዝሀ ህይወት
ደህንነትን ያረጋገጠ ሁኔታን መፍጠር ከብዝሀ ሕይወት ሀብት ዝውውር፣ ፈቃድ
እና ቁጥጥር የሚጠበቅ ውጤት ነው፡፡
13
ክፍል ሁለት
የኦዲት ግኝቶች
ሀ. የብዝሀ ሕይወት አጠባበቅን በተመለከተ
የሀገሪቱን የተፈጥሮ ደን ሽፋን የሚያሳይ ካርታ መዘጋጀቱን
በተመለከተ
31.ወቅታዊ የሆነ እና የሀገሪቱን የተፈጥሮ ደን ሽፋን እና በየጊዜው የሚታየውን
14
34.የሀገሪቱን የደን ሽፋን የሚያሳይ ካርታ አለመዘጋጀቱ የሀገሪቱ የተፈጥሮ ደን
vi
http//rainforest.mongoby.com/20Ethiopia.htm.
እንደ GTZ ባሉ ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶች ባለሙያዎች የሕዋ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀደም ብለው በ1990
የተጠኑ ጥናቶች 163600 ሄክታር ደን በዓመት እንደሚወድም ያሳያሉ፡፡ (CHANGE DETECTION OF
NATURAL HIGH FORESTS IN ETHIOPIA USING REMOTE SENSING AND GIS
TECHNIQUES: Matthias REUSING-Land Use Planner
German Technical Cooperation (GTZ), Ethiopia
German Development Service (DED), Ethiopia
Land Use Planning and Resource Management Project in Oromia Region (LUPO)
atomatthias@hotmail.com)
15
37.ኢንስቲትዩቱ በአራት ክልሎች 12 የማህበራዊ የዘር ባንኮችን በማቋቋም ሀገር
16
የተተከሉ ብዛት ያላቸው የፈረንጅ ጽድ ችግኞች በበሽታ በመጠቃቸው
እየደረቁ መሆኑን እና ለመከላከል የሚደረገውም ጥረት የተፈለገውን ያህል
ውጤታማ አለመሆኑን ከጥብቅ ደኑ ኃላፊ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል (ፎቶ-2)፡፡
መድረቅ
የጀመሩ
የፈረንጅ ጽዶች
17
የሆነ እና ሕግን መሠረት ያደረገ ጥበቃ እየተደረገላቸው ባለመሆኑ ለእንስሳት
ግጦሽ፣ ለሕዝብ መኖሪያነት፤ ለእርሻ አገልግሎት እንዲሁም የደን ሽፋናቸው
የሚመነጠርበት ሁኔታ ይታያል፡፡
42.የሀገሪቱን ሥርዓተ ምህዳሮች ወካይ በሆነ ደረጃ ሀገር በቀል የሆኑ የብዝሀ
18
45.ስለ ጉዳዩ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ
19
ሀገር አቀፍ የብዝሀ ሕይወት ስራቴጂክ ዕቅድን ለመተግበር
የሚያስፈልጉ አካላት መቋቋምን በተመለከተ
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚመራና የሚያስተባብር ስትሪንግ ኮሚቴ
(steering committee) መቋቋሙን በተመለከተ
50.የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ተግባራትን የሚመራና የሚያስተባብር ሶስት
ከመንግስት መ/ቤቶች አንድ ከግል ተቋማት አንድ መንግስታዊ ካልሆኑ
ድርጅቶች ባጠቃላይ አምስት አባላት ያሉት አስፈፃሚ ኮሚቴ (steering
committee) በፌዴራል ደረጃ ሊቋቋምና በዓለም አቀፍ የብዝሀ ሕይወት
ስምምነት እና ሀገሪ ባዘጋጀችው የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ስትራቴጂክ ዕቅድ
መሠረት ሥራውን ሊያከናውን ይገባል::
20
ከኢንስቲትዩቱም ሆነ ከሌላ አካል ወደ ክልሎቹ የወረደ ነገር እንደሌለ
ለመረዳት ተችሏል፡፡
21
59.ከዚሁ ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃ እና
22
የብዝሀ ሕይወት ዝውውር የሥነ-ምግባር ሰነድ ተዘጋጅቶ እና የሀዝቦት ሥራ
ተካሂዶ ወደተግባር መተርጎሙ ጊዜ የማይሰጠው አስፈላጊ ጉዳይ እንደሆነ
ለመገንዘብ ተችሏል::
23
68.በሀገሪቷ የብዝሀ ሕይወትን ሀብት በተመለከተ ለሚከናወኑ አስራ አንድ
24
የብዝሀ ሕይወት ሀብት ያለውን ጠቀሜታ እና ዋጋ መለኪያ
አሠራር መኖሩን በተመለከተ
71.የሀገሪቱን የብዝሀ ሕይወት ሀብት ጠቀሜታ እና ዋጋ ለመለካት፣ ለመተመን
እና ለማወቅ የሚያስችል ግልጽ የአሠራር ሥርዓት ሊኖር ይገባል፡፡
72. የሀገሪቱ የብዝሀ ሕይወት ስትራቴጄክ ዕቅድ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የብዝሀ
25
የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ
(environmental impact assessment) ደረጃውን ጠብቆ
መከናወኑን በተመለከተ
የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ መከናወንን እና ክትትልን በተመለከተ
75.በፈዴራልም ሆነ በክልሎች የሚተገበሩ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ለብዝሀ
77.ስለ ጉዳዩ ከፌዴራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የአካባቢ አሀዶች መርሀ ግብር
26
እንደተቻለው የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ በቅድሚያ ሳይካሄድ የልማት
ሥራዎች ወደ ትግበራ የሚገባበት ሁኔታ እንዳለ ለመረዳት ተችሏል፡፡
27
ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት በተመለከተ ጥናት ያልተደረገ እና የማይደረግ
መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
28
በመቶ እንዲጠፉ፤ የእርሻ መሬቶችም ምርታማነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንስ
እያደረጉ ይገኛል /ፎቶ-3፣4 እና 5/፡፡
29
ፎቶ-5 ረቨርቪያን የሚባለው መጤ ወራሪ ዝርያ
በአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ የግራር ዛፎትን እያጠፋ ያለ
30
ባለመሆኑ እነዚህ መጤ ወራሪ ዝርያዎች በአርብቶ አደሩ እና በአርሶ አደሩ ላይ
ከፍተኛ ጉዳት እያስከተሉ ይገኛሉ፡፡
ፎቶ-6፤ በአዋሽ ፓርክ ውስጥ በአካባቢው ህብረተሰብ የቤት እንስሳት የግጦሽ ስምሪት
31
ጥቃት እያደረሰ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን፣ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተርም
ስለጉዳዩ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ኢንስቲትዩቱ በተለያየ ጊዜ በተለይ
መንግስታዊ ለሆኑ መ/ቤቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መሥራቱን ነገር ግን
የግንዛቤ ማስጨበጫው ኅብረተሰቡንና ገበሬውን መሠረት ያደረገ እንዳልሆነ
ገልጸዋል፡፡
32
የሚገኘው የማኅበረሰብ ዘር ባንክ ህንፃው እየፈራረሰ በመሆኑ በውስጡ
የሚገኙት ሀገር በቀል ዝርያዎችን በአግባቡ ለመጠበቅ የማይችሉበት ሁኔታ
በመፈጠሩ በአፋጣኝ መፍትሔ እንደሚያሻው ቦታው ድረስ በመሄድ
ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከትግራይ፤ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤
ከአማራ እና ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስታት
የአካባቢ ጥበቃ ቢሮዎች መጠይቅ በመላክ ከተሰበሰቡት መረጃዎች አልፎ
አልፎ ሥልጠና ከመስጠት በዘለለ ከኢንስቲትዩቱ የሚደረግ ድጋፍ አለመኖሩን
ለማወቅ ተችሏል፡፡
33
ሐ. የብዝሀ ሕይወት ሀብት የጥቅም ተጋሪነትን
በተመለከተ
እራሱን የቻለ የጀኔቲክ አርክቦትvii ፈንድ የባንክ አካውንት
መኖሩን በተመለከተ
100. ከእያንዳንዱ የብዝሀ ህይወት የአርክቦት ውል የሚገኝ ገንዘብ በተለየ የአርክቦት
vii
አርክቦት ማለት የጄኔቲክ ሀብትን ወይም የማኅበረሰብ ዕውቀትን ማሰባሰብ፣ መውሰድ፣ ማስተላለፍ
ወይም መጠቀም ነው፡፡
34
በተደረጉት የዘረመል ሀብት አርክቦት ውሎች መሠረት
ክፍያዎች መፈፀማቸውን በተመለከተ
104. ዘረመል ሀብት እና ማኅበረሰብ ዕውቀትን በመጋራት ሊገኝ የሚገባ የፈቃድ፣
35
የዘረመል (genetical) ሀብቶች ሽያጭ ውሎቹ ላይ የሀብቱ
ባለቤት፣ መፍለቂያ ሀገርና ቦታ በግልጽ መቀመጡን
በተመለከተ
108. የሀገሪቱ የዘረመል (genetical) ሀብት ወደ ሌላ አካል ሲተላለፍ የሀብቱ
36
የዘረመል ሀብት አርክቦት ውሎች እና መረጃዎች
የሚዘጋጁበትን ቋንቋ በተመለከተ
112. የዘረመል ሀብት አርክቦት ጥቅም ተጋሪነት የስምምነት ሰነድ እና የሪፖርት
115. የዘረመል Gwት ዝውውር eUUነት ሲካሄድ ሁለቱም ወገኖች በሚግባቡበት ቋንቋ
37
117. የውጭ ተመራማሪዎች ፈቃድ አግኝተው በብዝሀ ሕይወት ሀብት ዙሪያ ጥናት
38
የብዝሀ ሕይወት ሀብቶች አቅምን በማጠናከር፣ በመለየት እና በማወቅ ተጠቀሚ
የምትሆንበትን ዕድል በጎላ ሁኔታ እንዲጠብ ያደርገዋል፡፡
125. ኢንስቲትዩቱ በመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት ከያዛቸው ዕቅዶች አንዱ
39
በኢንስቲትዩቱ ብዝሀ ሕይወትን የሚመለከቱ የሕግ ጉዳዮችን የሚከታተል
አካል አለመኖሩን ለማረጋገጥ ተችሏል::
40
በክልሎች የተጠናከረ የብዝሀ ሕይወት አደረጃጀት ባለመኖሩ ኢንስቲትዩቱ
ከክልሎች ጋር በተቀናጀ ሆኔታ ለመስራት እንቅፋት እንደሆነበት ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር ተጠይቀው በሰጡት
ምላሽ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአብዛኛው ክልሎች ብዝሀ ሕይወትን የሚመለከቱ
ተግባራትን የሚያከናውን አካል ለማደራጀት ጥረት የተደረገ መሆኑን፤ ሆኖም
አደረጃጀት ያላቸውም ክልሎችም ቢሆኑ በበቂ ባለሙያና የሰው ኃይል
የተደራጁ ባለመሆናቸው በትብብር ስራዎችን ለመሥራት እንዳላስቻለ
ገልጸዋል፡፡
41
እና የክትትል ሥርዓት ወይም አሠራር ከባለድርሻ አካላት ጋር አለመኖሩ
ዕቅዱ እንዳይሳካ ካደረጉ ችግሮች መካከል ዋነኛው እንደሆነ አራተኛው ዓለም
አቀፍ የብዝሀ ሕይወት ስምምነት አፈፃፀም ሪፖርት ያሳያል፡፡
ለአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሊቀርብ ይገባል የሚል ዕምነት ያለን ሲሆን፤ በሌላ
በኩል ደግሞ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣንን ጨምሮ ለሌሎች ዋነኛ ባለድርሻ
42
አካላት የሀገሪቱን የብዝሀ ህይወት ሀብት አጠባበቅ በሚመለከት የሚዘጋጁ
ሪፖርቶች እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው መረጃዎች እንዲደርሳቸው
አለማድረጉ የተሻለ የመረጃ ልውውጥ እንዳይኖር በማድረግ የባለድርሻ አካላቱ
የሚጠበቅባቸውን ተግባር ተረድተው እንዳይወጡ እና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃን
ዕቅድ ለማሳካት እና የተሻለ ውጤት ለማግኘት እንዳይቻል ተፅዕኖ ይኖረዋል፡፡
140. ሀገራዊ የብዝሀ ሕይወት ስትራቴጂክ ዕቅዱን ለማስፈፀም ተቋማዊ በሆነ መልኩ
43
142. ይህን ጉዳይ በተመለከተ የኢንስቲትዩቱ የእንስሳት ጀኔቲክ ሀብት ጥበቃና
44
ክፍል ሦስት
መደምደሚያ
144. ሀገራችን ተግባራዊ ለማድረግ በፈረመችው ዓለም አቀፍ የብዝሀ ሕይወት
45
የመጠቀም ልምድን ለማዳበር የሚያግዝ ተገቢ አደረጃጀት አለመኖሩ እና
የብዝሀ ህይወት ምንነትና ጥቅምን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ከብዝሀ
ሕይወት ሀብቱ ጋር የዕለት ተዕለት ግንኙነት ኖሮት በአብዛኛው ከግንዛቤ
እጥረት የተነሳ በሀብቱ ላይ ጥፋት እያደረሰ ያለውን የአካባቢው ኅብረተብ
መሠረት ያደረገ አለመሆኑ ሀብቱ ለከፍተኛ ጉዳት የመጋለጥ ዕድሉ ሰፊ
እንዲሆን ያደርጋል፡፡
46
ክፍል አራት
የማሻሻያ ሀሳብ
በአይነትም ሆነ በብዛት ከፍተኛ የብዝሀ ሕይወት ክምችት የያዙትን
የሀገሪቱን የተፈጥሮ የደን ይዞታዎች ክትትል በማድረግ በየጊዜው
የሚደርስባቸውን ጫና በአይነት፣ በስፋት እና በቦታ በመለየት ለመጠበቅ
እና ለማስፋፋት ይቻል ዘንድ የተደራጀ ዘመናዊ የመረጃ ማግኛ
ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ለማሰባሰብ የሚችሉ ብቃት
ያላቸውን መ/ቤቶቸን (የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ኤጀንሲ፣ የደን ጥናትና እና
ምርምር ተቋምን እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ትብብር የሚያደርጉ እና
በደን ሀብት ጥበቃ እና ማስፋፋት ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን)
በማሳተፍ የሀገሪቱን ወቅታዊ የደን ሽፋንን የሚያሳይ ካርታ ሊዘጋጅ
በየጊዜው ወቅታዊ በማድረገ አገልግሎት ላይ ሊውል የሚችልበት ሁኔታ
ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡
ከፌዴራል ጀምሮ በየደረጃው እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ድረስ ያሉ
እንዲሁም ዋነኛ ባለድርሻ አካላት ሀገር በቀል የሆኑ በተለይም በኢትዮጵያ
ብቻ የሚገኙ እና በመጥፋት አደጋ ላይ ያሉ ዕጸዋቶችን በመጠበቁ ረገድ
ሊያከናውኑት የሚገባቸው ድርሻ በግልጽ ሊለይ፣ እንዲያውቁት ሊደረግ እና
ኃላፊነታቸውን መወጣታቸውን በተመለከተ ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሠራር
በመዘርጋት ተግባራዊ ሊሆን የሚችልበት እንዲሁም የኅብረተሰቡን ግንዛቤ
በማሳደግ በጥበቃው ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ የሚሆንበት ሁኔታ ሊመቻች
ይገባል፡፡
በዓለም አቀፍ የብዝሀ ህይወት ስምምነት መሠረት እያደጉ ያሉ ሀገሮች
ከአደጉ አገሮች ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ስምምነት የተደረሰ
ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ይህን ተገባር ለማስፈጸም ከተቋቋመው ዓለም አቀፍ
የአካባቢ ፋሲሊቲ (GEF) በሀገሪቱ ለሚከናወኑ የብዝሀ ሕይወት ተግባራት
ማስፈፀሚያ የሚሆን የተሻለ ድጋፍ ለማግኘት እንዲቻል ተቀባይነት
ያላቸውን ፕሮጀክቶች ለመቅረጽ የሚችል አካል ሊደራጅ ጥረት ሊደረግ፤
የሚገኘውን ድጋፍ የሚያስፈጽሙ አካላት በትክክል ለተባለው ዓላማ
47
ለማዋላቸው ተጠያቂነት ያለው አሠራር እንዲጠናከር ጥረት ሊደረግ
ይገባል፡፡
በሀገሪቱ የብዝሀ ሕይወት ሀብት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የልማት
ተግባራትን ለመተግባር የሚወሰዱ እርምጃዎች ሚዛናዊነትን የጠበቁ
እንዲሆኑ ለማድረግ ስለሚረዳ የሌሎች የተሻለ ተሞክሮ ያላቸውን ሀገራት
እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዝሀ ሕይወትን ጠቀሜታ በኢኮኖሚያዊ ምዘና
በዋጋ ለማስቀመጥ ጥናት በማድረግ ላይ ከሚገኘው አካል ልምድ እና
መረጃ በመውሰድ የሀገሪቱ የብዝሀ ህይወት ሀብቶች በአሉበት የተፈጥሮ
ሁኔታ ሊያስገኙ የሚችሉት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን በገንዘብ መጠን
ለማወቅ ጥረት ሊደረግ ይገባል፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተሰብስበው በናሙና ተይዘው የሚጠበቁ
የዕጽዋት ዝርያዎች በእሳት በጎርፍና በሌሎች አደጋዎች ሊፈጠር
የሚችለውን የጉዳት ስጋት ለመቀነስ እና በድንገት ጉዳት ቢደርስ
ለመተካትና ለመጠበቅ እንዲቻል ቢያንስ በኢንስቲትይቱ ውስጥ በኢዘቦታ
የሚጠበቁ ናሙናዎች በተመሳሳይ በሌላ ኢዘቦታ (duplicate gene
bank) እንዲጠበቁ አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባል ፡፡
በከፍተኛ ሁኔታ ብዝሀ ሕይወትን እንዲጠፉና እንዲመናመኑ እያደረጉ
የመጡትን መጤ ወራሪ ዝርያዎች ዘላቂነት ባለው መንገድ ለሌላ
ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ሊውሉ የሚችሉነትን እና ኅብረተሰቡም ተጠቃሚ
የሚሆንበት ሁኔታን ለማመቻቸት ሀገር አቀፋዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ ጥረት
ሊጠናከር የሚችልበት ሁኔታ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡
የአካባቢው የዘረመል ሀብቶች (genetiaL resources) ሕጋዊ ባልሆነ
ሁኔታ እንዳይወሰዱ ከክልል እስከ ታችኛው ማኅበረሰብ ድርስ የግንዛቤ
ማስጨበጫ መርሐ ግብር ሊከናወኑ፣ ለመቆጣጠር የሚያስችል አሠራር
ሁሉንም ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ በጥናት ሊዘጋጅ እና ተግባራዊ
እንዲሆን ጥረት ሊደረግ ይገባል:: በተለይም በውጪ አካል
የተወሰዱየዘረመል ሀብቶችን ለማስመለስና ጥቅም ለማግኘት እንዲቻል
ለማስፈጸም የሚረዳ እና የህግ ጉዳዮችን የሚከታተል አካል በኢንስቲትዩቱ
እንዲደራጅ ከማድረግ በተጨማሪ የፍትህ እና የውጪ ግንኙነት ጉዳዮች
የሚመለከቷቸው ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ቀደም ብለው ከወጡም ሆነ
ለወደፊት በተመሳሳይ ሁኔታ የሚያጋጥሙ ሁኔታዎች በብቃት
48
በመከታተል ሀገሪቷ ከብዝሀ ሕይወት ሀብቷ የተሻለ ተጠቃሚ ልትሆን
የምትችልበት ሁኔታ እንዲፈጠር ጥረት ሊደረግ ይገባል፡፡
49
የጀኔቲክ ሀብት አርክቦት ውል ሽያጭ በሚካሄድበት ጊዜ መገኝት ያለበትን
የተለየዩ ጥቅሞች ለማግኝት የሚያስችል አሠራር መኖር አለበት፡፡
50
ሀገሪ ባዘጋጀችው የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ዕቅድ መሠረት ስራቸውን
ሊያከናውኑ የሚችሉበት ሁኔታ ሊመቻች ይገባል::
51
መንግስታዊ ከሆኑም ሆነ ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የተሠሩ
ተግባራትን መገምገም እና በግምገማውም መሠረት ምላሽ መሰጠት
አለበት፡፡
52
አባሪዎች
አባሪ 1
ii
ኃይል (biodiversity task force) በፌዴራል እና በክልል ደረጃ ሊቋቋም
ይገባል፡፡
24. የሀገሪቱን የብዝሀ ህይወት ሀብት ይዘው የሚገኙት የክልል መንግስታዊ
መስሪያ ቤቶች የብዝሀ ህይወት ሀብትን ለመጠበቅና ዘለቄታዊ በሆነ
መንገድ የመጠቀም ልምድ ለማዳበር የሚያግዝ አደረጃጀት ሊኖርአቸው
ይገባል፡፡
25. ›=”e+ƒ¿~ የብዝሀ ህይወት አለም አቀፍ ስምምነት አፈጻጸምን
በሚመለከት ¯መታዊ ሪፖርት ለአከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሊያቀርብ
ይገባል፡፡
26. የሀገሪቱን የብዝሀ ሕይወት ሀብት ለመጠበቅ እና ዘለቄታዊ በሆነ መንገድ
የመጠቀም ልምድ የማዳበር ክንውንን በተመለከተ መደበኛ (formal)
የሆነ ክትትል፣ የሪፖርት አቀራረብ •“ ¾S[Í M¨<¨<Ø Y`¯ƒ Ñ<Ç¿
uT>SKŸ†¨< ¾ôÅ^M' ¾¡MM S”Óe© S/u?„‹ “
u›=”e+ƒ¿~ S"ŸM K=²[Ò ÃÑvM፡፡
27. ›=”e+ƒ¿~ በ}cÖ¨< eM×”“ Lò’ƒ መሰረት ›Óvw’ƒ ÁL†¨<”
S”Óe© ›"Lƒ uTe}vu` K¡MKA‹ ¾‚¡’>¡ ÉÒõ SeÖƒ
Õ`u•M::
28. በብዝሀ ህይወት ዙርያ ከሚንቀሳቀሱ S”Óe© "MJ’< ሀገር በቀል
ከሆኑም ሆነ ካልሆኑ vKÉ`h ›"Lƒ ጋር በመወያየት የጋራ ሰነድ
መፈራረም የሀገሪቱን የብዝሀ ህይወት ሀብት ለመጠበቅ እና ዘለቄታዊነት
ያለው አጠቃቀምን ለማዳበር አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉበት ሁኔታ
K=S‰‹ Ãገባል፡፡
29. የS<Á ማህበራት እና ሲቪል መህበራት የሀገሪቱን የብዝሀ ህይወት ሀብት
ለመጠበቅ እና ዘለቄታዊነት ያለው አጠቃቀምን ለማዳበር የሚሳተፉበት
መድረክ ሊመቻች ይገባል፡፡
30. ማህበረሰቡ ስለ ብዝሀ ሕይወት በሂደት ያካበተው አካባቢያዊ እውቀት
በጥናት ሊለይ እና ተመዝግቦ ሊያዝ ይገባል፡፡
31. በሀገሪቱ የብዝሀ ህይወት ሀብት ዙሪያ በሚከናወኑ ሴሚናሮች ውይይቶች
ወይም መደበኛ የሆኑ ስብሰባዎች በሚዘጋጁበት ወቅት መንግስታዊ
ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት እንዲሳተፉ በማድረግ ›=”e+ƒ¿~ Ó”–<’~”
TÖ“Ÿ` ÃÑvªM፡፡
32. መንግስታዊ ከሆኑ እና ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ¾T>Ÿ“¨’<
ስራዎች” ›=”e+ƒ¿~ በየጊዜው መገምገምና በግምገማው ውጤት
መሠረት አስፈላጊውን ምላሽ እና እርምጃ መውሰድ አለበት፡፡
iii
አባሪ 2
የብርቅዬ
የዝርያ ብዛት በመቶኛ
የዝርያ አይነት ዝርያዎች
(Number of (~ % of
(Group) (Number of
Species) Endemics)
Endemics)
አጥቢዎች (Mammals) 278 31 11
አዕዋፍት (Birds) 861 28 3
ተሳቢ እና ተራማጅ
201 14 7
(Reptiles)
አምፊቢያንስ Amphibians 63 24 38
አሳ (Freshwater fish) 200 40 20
ነፍሳት (Insects) 1250 7 0.6
ዕፀዋት (Plants) 6,000 600 10
ሌማዳ ተግብርና እንስሳት 102 - -
ድምር 8853 744 8
iv
አባሪ 3
Glossary /የቃላት መፍቻ/
v
characteristics of a micro-organism, plant or animal by inserting a
modified gene or a gene from another variety or species.)
የመኖሪያ አካባቢ መለወጥ /Habitat change/: የመኖሪያ አካባቢ ለረጂም ጊዜ ከነበረው
ባሕርይ እና ይዘት መለወጥ፤
ነባር የማኅበረሰብዕውቀት /Indigenous knowledge/: በረጂም ጊዜ በማኅበረሰብ ውስጥ
ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲወራረስ የቆየ እና ተፈትሾ የዳበረ አካባቢያዊ ዕውቀት
- (information and learning processes developed over many years
and passed down from one generation to the next. Traditional
knowledge is not static; it evolves or changes over time.)
ወራሪ መጤ ዝርያዎች /Invasive species/ ፤ ከነበረበት አካባቢ ወጥቶ በአንድ አዲስ
አካባቢ የገባ ዝርያ (an introduced species which invades natural
habitats.
ብክለት /Pollution/፣ አካባቢ ለአካባቢው ባዕድ በሆኑ ወይም በቆሻሻ ነገሮች መበከል፡፡
የማኅበረሰብ ባህሎች /Social culture/: ማኅበረሰባዊ ልምዶች፣ ወጎች፣ የአኗኗር
ዘይቤዎች ወዘተ…
ዝርያዎች /Species/: እርስ በእርስ ሊዋለዱ የሚችሉ ዝርያዎች (a species is a group
of morphologically similar organisms that are able to interbreed
and produce fertile offspring.)
አርክቦት፤ የጄኔቲክ ሀብትን ወይም የማኅበረሰብ ዕውቀትን ማሰባሰብ፣ መውሰድ፣
ማስተላለፍ ወይም መጠቀም ነው፡፡
vi