You are on page 1of 19

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ

ጥር/2015 ዓ.ም

ጎንደር
ምስጋና

ይህን ተሞክሮ እንዲደራጅ በርካታ ግለሰቦች ድጋፍ አድርገዋል፡፡ በቅድሚያ ደከምኝ ሰለችኝ ሳይሉ በጽሁፍ እና በአርትኦት ትልቅ ድጋፍ
ለዳረጉልን ወ/ሮ ሙሉቀን አጣናውና አቶ ደርሶልኝ አበበ በቀጠል ኮሚቴው ውን በመላላክ እንዲሁም ሪፍሬሽመነት በማቅረብ ለተባበሩን
ወ/ሮ አበበች፣ ከቦታ ቦታ በሚደረገው እንቅስቃሴ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ያመላለስን ሹፌራችን አቶ ዘውዱ አድማሱ፣ በቃለ መጠይቅን
እና የቡድን ውይይት የተሳተፉ የቁሳቋም፣ የደብረብርሐን ስላሴ እና የተጠዳ እንግዚአብሔር አብ ኗሪዎች፣ የክ /ከተማና ቀበሌ
አስተዳደሮች ከልብ የመነጨ ምስጋናችን ይድረሳችሁ! ያለ እናንተ ድጋፍ የትም አይደርሰም ነበር እና!
ማውጫ
01. መግቢያ.....................................................................................................................................................1

02. የችግር ትንተና.............................................................................................................................................2

03. ዓላማ........................................................................................................................................................3

04. ወሰን........................................................................................................................................................3

05. ዘዴዎች.....................................................................................................................................................4

06. አስፈላጊነት.................................................................................................................................................4

1. አጠቃላይ ተግባራት እና ውጤት......................................................................................................................5

ተግባር አንድ የህ/ሰብ ተሳትፎና ቅርስ ጥገና..........................................................................................................5

ተግባር ሁለት የአጋር አካለት ተሳትፎና መዳረሻ ልማት.........................................................................................5

ተግባር ሶስት የወዳደቁ ቁሳቁሶችን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል................................................................................5

2. በተግባር እና ውጤት በዝርዝር........................................................................................................................5

2.1.1. ከውጤት በፊት የነበሩ ሁኔታዎች....................................................................................................5

2.1.3. ደብር ብርሃን ሰላሴ ከለውጥ በፊት የበረበት ሁኔታ............................................................................7

2.1.4. ለውጡት ሁለት ደብር ብርሃን ሰላሴ ጥገና የተከናወኑ ተግባራት..........................................................8

2.1.5. ጠዳ እግዚአብሔር አብ ከለውጥ በፊት የበረበት ሁኔታ..........................................................................8

2.1.6. ለውጥ ሶስት ጠዳ እግዚአብሔር አብ ጥገና የተከናወኑ ተግባራት.........................................................9

3. በአጋር አካላት ተሳትፎ የፋይናንስ አቅም መጨመር..............................................................................................9

ውጤት 1. ፋሲል አብያ ተመንግስት ኢንስታሌሽ..............................................................................................9

ውጤት 2. .ፋሲል አብያ ተመንግስት ትራንሰፈርመር ተከላ..............................................................................10

4. የአጋር አካት ተሳትፎ ተሳትፎን ለማሳደግ የራስ ግንብ ሙዚየምን መልሶ የማልማት የተሰሩ ዝርዝር ተግባራት......................10

5. የወዳደቁ ቁሳቁሶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል የተከናወኑ ዝርዝር ተግባት................................................................11

የአጋር ኣካላት ተሳትፎ.................................................................................................................................11

6.1. የተገኘ ኢኮኖሚ ጥቅም ስሌት....................................................................................................................12

6.2. ማህበራዊ ፋይዳ....................................................................................................................................13

7. የነበሩ ጥንካራ፣ ደካማ ጎኖች፣ መልካም እድሎች እንዲሁም ተግዳሮቶች ትንተና (SWOC)............................................14

8. የቀረቡ አስተያየቶ (Recommendations).....................................................................................................15

9. ማጠቃለያ.............................................................................................................................................15
አጠቃሎ
በቱሪዘም ገቢያ ተወደዳሪ በመሆን ከፍተኛ ጎብኝ ለመሳብ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን መስራት ይጠበቃል፡፡ ከእነዚህም የመዳረሻ
ልማት ስራዎች እና የቅርስ እንክብካቤ እና ጥገና ቅድሚያ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ተግባራት በአንዴ ተጀምረው አንዴ
የሚያልቁ ስራዎች ሳይሆነ የመዳረሻ ባለቤት የሆኑ አገራት ወይም መንግስታት ሁልጊዜ የሚሰሯቸው ተግራት ናቸው፡፡ ካለው
የዋጋ ግሽበት እንዲሁም ካላቸው ኢኮኖሚ አቅም አኳያ በተለይ በማድግ ላይ ያሉ አገራት ይህ ተግባር በብቃት
አያካነውኑትም፡፡ ይህን ጉድለት ለመሙላት የተለያዩ ዘዴዎች ይቀየሳሉ፡፡ በዚህ ወረቀት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባህልና
ቱሪዝም መምሪያ ያለበተን የፋይና አቅም ውስንነት በማህረሰብ ድጋፍና አጋር አካለት አስተዋጽኦ እንዲሸፍን ሰፊ የህዝብ
ንቅናቄ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ በመሆሙም በቅርስ ጥበቃ እንክብካቤ ስራ ያመጣውን ለውጥ፣ ለለውጡ መምጣት የተካናወኑ
ዝርዝር ተግበራት እንዲሁም ማን ምን ፈጸመ የሚሉ ዝርዝር ጉዳዮችን አደራጅቶ እንደ ምርጥ ተመክሮ አደራጅቷል፣
አሰራጭቷል፡፡

1
01. መግቢያ
የባህልና የቱሪዝም ስራዎች ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቁ ሁለት የተለያዩ ሴክተሮች ናቸው፡፡ (Luodolf, 1991)
የባህል ዘርፍ ውሰጥ የፈጠራ ስራን ለማጉልበት በብዙ ሚሊየኖች የሚቆጠር ከፍተኛ ካፒታል ይጠይቃል፡፡ በተለያዩ አለም
ሀገራት ያለዉ የፈጠራ ኢንዱስትሪ ወስደን ብንመለከት የአገርን ኢኮኖሚን ግንባታ ከፍተኛ ሚና እዲኖረው ለማድረግ
መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደቡ ዘርፉን ሲያንቀሳቅስው ይሰተዋላል (Kadile, 2012)፡፡ ለምሳሌ ከአሜሪካ ሆሊውድ
የደቡብ አፍርካ የፊልም ኢንዱስትሪ እና ናይጀሪያ “ኖሊ ውድ” የፊልም ኢንዱስትሪ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ መንግስት በዉጭ
ከፍተኛ ድርሻዉን ወሰዶ ሲያንቀሳቅሰው ዘርፍ በራሱ ገቢ ማመንጨት ይጀምራል፡፡ ከዚህ አኳያ ዘርፍ በሙሉ አቅም
እንዲያድግ በማድረግ ረገድ የመንግስት ተሳትፎ በእጅጉ ሲታከልበት ውጤታማና ለኢኮኖሚ የሚያደርገው አስተዋጽኦም
ከፍተኛ ይሆናል (Kin, 2014)፡፡ ነገር ግን በማደግ ላይ ያሉ አገራት ግን ከፋይናስ አኳያ የመንግስት አሰተዋጽኦ እድግ ደካማ
ነዉ፡፡ በመሆኑም ዘርፍ እምብዛም አድጎ ለኢኮኖሚ ያለዉ አበረክቶ ጎልቶ አይታይም፡፡
በባህል ዘርፍ ይህን ለማሳያ ካልን በቱሪዝም ዘርፍ በተመሳሳይ ገቢያ ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ግብዓት የሚሆኑ በርከታ
ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይጠይቃል፡፡ ለአብነት ፕሮሞሽን, የማህበረሰቡ ህሴቶችን መጠበቅ (Authenticty)
አካባቢን ወይም (environement) ማልማት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
መዳራሻ ስፍራ ልማቶችንና አቅርቦቶች የማልማት ጉዳይ በገቢያ ተዋዳዳሪ ከሚያደርጉና ከፍተኛ ካፒታል ከሚጠይቁ
ጉዳች የሚመከደብ ነው፡፡ ይህ ሲባል አንድ መዳረሻ በተሟላበት ሁኔታ ምንም የተፈጥሮ እና ሰዉስራሽ ሀብቶች ቢኖሩም
የቱሪዝም ገቢያ ዉስጥ ገብተዉ በብቃት ለማሸነፍ ስለማይችል ተጨማሪ የመዳረሻ ልማት ስራዎች መስራት እና
አቅርቦቶችን ሟሟላት ይጠይቃል ማለት ነው፡፡ ይህን ኃላፊነት ደግሞ በአብዛኛው የሚወስደው መንግስት ነው፡፡ ስለሆነም
መንግስት መዳረሻዎች በቱሪዝም ገቢያ እንዲቀርቡ ለማድረግ ከፍተኛ መዋለ ንዋይን ወደ ልማት ስራ መርጨት ይኖርበታል
(Luodolf, 1991)፡፡ ይህን ማድረግ የቻሉ አገራት ከፍተኛ የገቢያ ድርሻ ይዘው ይሰዋላል፡፡ በዚህ ረገድ ቀዳሚዉን ቻይና
ከፍተኛ ስፋራን እየተቆናጠጠች ትገኛለች (ben, 2014) ለቱሪዝም ኢንዱስትሪ ማድረግ የቻይና መንግስት የሚዉስደዉ
ድርሻ ከፍተኛ ነዉ፡፡ የደቡብ አሜሪካዋ ብራዚልም ይህን በሁለተኛነት ተግባራዊ ስታደርገ ይታያል፡፡ ከአህጉራችን ሞሮኮ እና
አልጀሪያ የልማት ስራዎች ላይ መንግስት ደርሻ ከማንም በላይ ነው፡፡ በታዳጊ አገራት በተለይም ዝቅተኛ የኢኮኖሚ እድገት
ያለዉ አገራት ከገቢያዉ ተጠቃሚ ሲሆን አይስተዋልም ምንም የመስህብ ሀብት ሞልቶ ቢተረፈረፍባቸወም (Luodolf,
1991)፡፡ ለዚህም ቻድ እንደ ምሳሌ ትጠቀሳለች፡፡ በዋናነት ከድህነት ጋር ወይም ከፋይናስ አቅም ማነስ ጋር በቀጥታ
የሚያያዝ ሲሆን አገራዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ሌላው ምክኒያት ሊሆን እንደሚችል ይታወቃል፡፡
እንደ ቻድ ያሉ አገራት በርከታ ሲሆኑ ባለሙያዎች የሚያሰጡት ምክር የገቢያ ጉድለ ትሸፍኖ የቱሪዝም ገቢያውን ለማሸነፍ
የፋይናስ አቅም የሌላቸው አገራት ከፍተኛ የገቢ ማመነጫ ዘዴዎች ቀይሰው መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው ነው፡፡
በየትኛውም ጉዳይ ላይ የሚፈጠር የፋይናንስ ጉድለት (financial short fall) መሙላት ብዙ ገቢ ማመንጫ ዘዴዎች
እንዳሉ ይታወቃል፡፡ በአብዛኛዉ አጋር አካላትን አካቶ መስራት በሁሉም አካባቢዎች የተለመደ ተግባር ( (Dawning,
2015)፡፡ የከፍ ሲል የጠቀስናቸው የአፍሪካ አገራት ሞሮኮ አን ቱኒዚያ አብዛኛውን በቱሪዝም ልማት ስራዎች የአየር መንገድ፣
ባንኮች እና ፕራይቬት ቱሪስት ሳይት ኦነሮች ጋር ተቀራርቦ መስራት የበጀት ምንጭ ሆኖ እንደገዛቸው ይጠቅሳሉ (Sales
@exploring moroco travel, 2023)

2
ይህም ስልት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገራችንም በስፋት ጥቅም ላይ ሲዉል ይስተዋላል የኮይሻ፣ የሃላላ ኬላ እና የጎርጎራ
ፕሮጅክቶች ጥቂት ማሳያዎች ናቸዉ፡፡ በከተማችንም የመንግስት ያለበትን የፋይናስ ጉድል ሞልቶ በቂ የመሰረተ ልማት
አቅርቦት ያለበት የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ለመገንባት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ የስራ ድርሻ የወሰደዉ ደግሞ የከተማ
አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ነዉ ፡፡
ሴክተሩ መንግስት ያለበትን የገንዘብ ጉድለት እንዲሟላ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህ በመነሳት
ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ለማዳረሻዎች ማሟላት ተችሏል ይህን አስመልክቶ ዉጤቶች፣ ለዉጤቶች ምክንያት የሆኑ
የተቀናጁ ስራዎች እና ተግባራትን ለመቀመር ኮሚቴ ተደራጅተዉ ወደ ስራ ገብቷል ነበር፡፡ ከተደረገ መለስተኛ የማህበራዊና
ኢከኮኖሚያዊ እዲሁም አሰራር ወይም አተጋበር ልምዶች ጥናት በኋላ የገኘውን ተሞክሮ በሚከተለው መንገድ ተቀምሯል፡፡
ስለሆነም ይህ ተሞክሮ ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡

02. የችግር ትንተና


ሰዉ ስራሽና ተፈጥሯዊ የቱሪዝም ጸጋዎች የተለያዩ መሰረተ ልማቶችና አቅርቦቶች ቢሟሉላቸው መድረሻው በገቢያ
የመወዳር አቅሙ ከፍተኛ ያደርገዋል (Peterson, 2015)፡፡ በገቢያ ጸንቶ ለመቆየት እዲዚህን ሐብቶች መንከባከብ
ማልማትና ከፍተኛ ትኩረት የሚጠው ተግበራ ነው፡፡ (Luodolf, 1991)
የጎንደር ከተማ በዓለም የቱሪዝም ገቢያ የሚታወቁ የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ቅርሶች ባለቤት ሰከተማ ነዉ፡፡ ስለሆነም
ቱሪዝም ለከተማው ብሎም ለአገር ኢኮኖሚ ያለው አበርክቶ ከፍተኛ ነው፡፡ ሆኖም ከፍተኛ ፉክክር በሚታይበት በቱሪዝም
ገቢያ በማሸነፍ ሆነ ጸንቶ ለመቆየት ከፍኛ የመዳረሻዎ የመሰረተ ልማት ማሟላት ተግባረን በአግባቡ መከውን ሚጠበቅባት
ከተማ ናት፡፡ በመንገስት ወጭ ይህን ማድረግ የምትችል ከተማ ግን አይደለችም፡፡
ለዚህ እንደዋነኛ ምክኒያት የመንግስት ገቢ አቅም አነስተኛ መሆን እና ለዘርፉ የሚመድበው በጀት አስተኛ መሆን ይጠቐሳል፡፡
በመሆኑም ለመድረሻ ግብአት የሚሆኑ መሰረተ ልማቶችን ለመሟላት ሳይቻል ቆይቷል፡፡ እንደ መሳያ በርከታ ጥኝታዊ
አብያተክርስቲያናት እነደ በድረፀሀይ ቁስቋም፣ ጠዳ እግዚአብሄር አብና ደብረ ብርሐን ስላሴ ጥገና እያሻቸው ሳይጠገኑ
ቆይዋል፡፡ ሌላው መሰረተ ልማት እንዲሟላላቸው የሚጠይቁ መደራሻዎች ለአብነት አንደ ራስ ግንብ ሙዚየም ያሉ
ስራፍራዎች መሰረተ ልማት ሳይሟላላቸው በመቆየቱ እዚህ ግባ የማይባል ጎብኝ የሚያስተናግዱ ማዳረሻዎች ሆነው
አመታትን አሳልፈዋል፡፡ ከ 2013 ዓ.ም መገባደጃ ወዲህ የዓለም ቱሪዝም በኮረና ምክኒያት ከነበረበት ድብርት ወጥቶ እጅግ
ተነቃቅቶ በላበት በዚህ ወቅት ሀብቶቻችን ጥግነን፣ እና ዘላቂነታቸውን አረጋግጠን ወደ ገቢያ ልናስባቸው እንደሚገባ
ልብይሏል፡፡
ዛሬ ይህን ግምት ውስጥ አስግተው ናይሮቢ፣ ማራካሽ እና ቱኒዝ እየሲሩ ባሉበት ወቅት የከተማች አስተዳደር መዳረሻዎችን
ለመከባከብ ሆነ ለመጠገን አቅሙ እጅግ ውሱን ሆኖ ይስተዋላል፡፡ ዋናው ማነቆ በጀት ነው፡፡ ነገርግን መንግስት የበጀት አቅሙ
ደካማ ነው በማለት እስከመቼ እንዲሁ እንቀጥላል? የችግሩ ዋና ዋና ጥያቄ ነው፡፡

03. ዓላማ
የአጋር አካላት ተሳትፎ በማሳደግ የቱሪዝም መዳረሻ የሆነዉን ሀብቶችን ለመጠገን፣ ለመንከባከብና ለማስተዋወቅ
የሚጠየቀዉ ከፍተኛ ገንዘብ በመሸፈን የቱሪዝም ገቢያ የተሟላ ምርትን ለማቅረብ እንዲሁም ይህን አሰራር ቀምሮ ለሌሎች
እንዲዳረስ ማድረግ ዋናዉ ዓላማ፡፡

3
04. ወሰን
የጎንደር ከተማና አካባቢዋ ባሉ 11 ገጠር ቀበሌዎች ክልል ዉስጥ ነዉ የመንግስት የቱሪስት መዳረሻ አካባቢዎችን
ለመንከባከብና ለማልማት ያለበትን የገንዘብ እጥረት ለመቅረፍ የአጋር አካላትን አካቶ በመስራት እና ልዩ ልዩ ገቢ መሰብሰቢያ
ስልቶችን ተቀይሶ ተግባራዊ በማድረግ የመጣዉን ዉጤት፣ ለውጤቱ መገኘት የተከናወኑ ተግበራንት የሚዳስስ ሰነድ ነዉ፡፡
በዋናነት በሶሰት ጉዳዮች ያተኩራል እነዚህም፡-

 ህብረተሰብ ተሳትፎና ቅርስ ጥገና

 የአጋር አካለት ተሳትፎና መዳረሻ ልማት

 የወዳደቁ ቁሳቁሶችን ምልሶ ጥቅም ላይ ማዋልና አቅርቦ ልማት (Facilities development) ናቸው፡፡

05. ዘዴዎች
ይህን ተሞክሮ ለመቀመር የተጠቀምንባቸው ዘዴዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

 የተሞክሮ ቀማሪ ቡድን በማዋቀር ተሞክሮውን እንዲያደራጅ ሁኗል

 ኮሚቴው የመጀመሪያና 2 ኛ ደረጃ የጥናት መረጃዎችን ማሰባሰብና መተንተኑ

 የቡድን ቃለ መጠይቅ መጠቀም፣መጠይቆችን በማስሞላት

 /የተወሰኑ የቡድን ውይይቶች/ ተደርገዋል

 የመስክ ምልከታ ተደርጓል፡፡

06. አስፈላጊነት
 በጎንደርከተማ ተከስቶ የቆየውን የኢኮኖሚ ማሽቆልቆልና ማህበራዊ መስተጋብርን ለማነቃቃት ስላገዘ

 የማ/ሰቡ ባህል ፣ወግ፣ታሪኮች ተጠብቀው ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ አበርክቶ ስላለው፣

 ተደራሽ ያልሆኑ የቱሪስት መዳረሻዎች መሰረተ-ልማት እንዲሟላላቸው በማድረግ ተደራሽ እንዲሆኑ ስላስቻለ

 ግለሰቦችና ድርጅቶች እንዲማሩባቸው ለፖሊሲና ስትራቴጅ አዘጋጆች (ግብዓት) መነሻ ሆነው እንዲያገለግሉና
እንዲሰፋ ለማድረግ ተሞክሮውን መቀመር አስፈላጊ ሆኗል፡፡

4
1. አጠቃላይ ተግባራት እና ውጤት

ተግባር አንድ የህ/ሰብ ተሳትፎና ቅርስ ጥገና


የመጣ ውጤት1. ደብረ ፀሐይ ቁስቋም በህ/ሰብ ተሳትፎ መጠገ
የመጣ ውጤት2. ደብረብርሃን ስላሴ በህ/ሰብ ተሳትፎ መጠገኑ

የመጣ ውጤት3. ጠዳ እግዚአብሔር አብ መጠገኔ

ተግባር ሁለት የአጋር አካለት ተሳትፎና መዳረሻ ልማት


የመጣ ውጤት1. ፋሲል አብያ ተመንግስት በመብራት እና በኃይል ሙሉ አቅርቦት እንዲኖረዉ
የትራንስፈር እና ተከላ ስራ መስራቱ
የመጣ ውጤት2. ፋሲል አብያተ መንግስት የማታጉብኝት ለማስጀመር የኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽን
የመጣ ውጤት3. እራስ ግንብ የመዳረሻ የልማት ስራ መጠናቀቁ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተሰራ ስራ በዝርዝር

ተግባር ሶስት የወዳደቁ ቁሳቁሶችን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል


የመጣ ውጤት1. የሽንት ቤት ግንባታ
የመጣ ውጤት2. የፓኔሎች ግንባታ እና ወክ ወይዮች ጥርዝ ግንባታ
የመጣ ውጤት3. እና የአካባቢ ጽዳት እና ውበት ማስጠበቅ

2. በተግባር እና ውጤት በዝርዝር


2.1.1. ከውጤት በፊት የነበሩ ሁኔታዎች

የደብረጸሀይ ቁስቋ ቤተክርስቲያ የተገነባችው በእቴጌ ምንትዋብ በ 1878 ዓ.ም አካበቢ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በ 1979 ዓ.ም
በተባበሩት መንግስታት በትምህርት፣ በሳይንስ እና ባህል ተቋም በሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት ከተመዘገቡ የጎንደር ቅርሶች
ውስጥ ትካተታለች፡፡ ሆኖም በተለያዩ ጊዜያት በተፈጥሮ እና ሰውሳራሽ ችግሮች የመፈራረስ ኣዳጋ ተጋርጦባት ቆይቷል፡፡
በመሆኑ ጣራው እንዲሁም ግድግዳና ፈራርሶ የነበረበት ሁኔታ ይስተዋል ነበር፡፡ በተለይም የአዋፍት ኩስ፣ አልጌና ሌሎች በካይ
ቁሶች በህንጻው ላይ የነበሩ በመሆኑ ጉዳቱን ይበልጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደግ መጥቶ ነበር፡፡ በመሆኑም የማህበረሰቡ የቅሬታ
ምንጭ ሆኖ የይጠገንልን ጥያቄ በተደጋጋሚ የሚቀርበብት ታሪካዊ ቅርስ እና ስፍራ ነበር፡፡

5
2.1.2. ለ ውጤት አንድ. ደብረ ፀሀይ ቁስቋምን በህ/ሰብ ተሳትፎን ለማጠገን የተሰሩ ዝርዝር ተግባራት
 ዝርዝር የአተገባበር ሂደትን የሚያሳይ ፕሮጀክቶች ፕሮፖዛል ተቀርጻል

 አ




ስልጠና ለተመለመሉ ወጣቶች ተሰጠዋል

 ይህ በማስፈፀም የኮሚቴ አደረጃጀት ተመስርቷል፡፡

ይህም 1 ኛ/ ዓብይ አሰራር ኮሚቴ


2 ኛ/ 3 ንዑሳን ኮሚቴዎች
3 ኛ/ የስትሪባን ኮሚቴ ተደራጁቷል
 አሰልጣኝ ወጣቶች ወደ ቁስቋም እና አካባቢዉ በመሄድ በጎጥ
እንዲሁም በቀበሌ ስለ ቁስቋም ቅርስ ይዘት እና አሁን ያለበትን
ሁኔታ አስመልክቶ ዉይይት ጥገናና የህብረተሰብ ተሳትፎ እንዴት
ሊከወን እንደሚች በፕሮፖዛሉ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በዚህም 120,000
ህዝብ ግንዛቤ እዲይዝ ተደርጓል፡፡

 በተዘጋጀው ፕሮዛልና ይህን ግንዛቤ መሰረት ያደረገ የገቢ ማሰባሰቢያ


መርሃግብር ተዘጋጅቶ ወደስራ ተግበቷል፡፡ ቤት ለቤት የገንዘብ መዋጮ መሰብሰብ ስራ፣ በሰንቤቴ፣ እድርእና
በንግሰ ክብረ በዓላት ተሰርቷል፡፡ በት/ቤት በመንግስት መሰሪያ ቤቶች ገቢ የሚሰበሰብ ስራ ተሰርቷል

 ወደ 6 ሚሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ 6.5 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል

በኮሚቴ የተደራጁ አካላት ከምንግሰት፣ ከታዋቂ ግለሰቦች፣ ሽማገሌዎች፣ ምሁራን እንዲሁም ነጋዴዎችና የቤተ
ክርስቲያኗ መሪዎች የተውጣጣ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
 የጎንደር ከተማ ዓማቀፍ ቅርስ አስተዳደር ዋና ስበሳቢ

6
 የቤተ ክርሰቲያኗ አስተዳዳረ ምክትል ሰብሳቢና የሰበካ ጉባኤ ተወካይ ጸሐፊ በውስጡ 25 አባላት ያሉት ዓብይ
ኮሚቴ ተቋቋመ በስሩ
3 ንዑሳት ኮሚቴዎች አደረጃጀት
1 ኛ. ገንዘብ አሠባስብ ኮሚቴ
2 ኛ. የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ
3 ኛ. የስትሪንግ ኮሚቴ
ተደራጀቶ በየዘርፍ በተናጠል እና በቡድን ከፍተኛ ርብርብ ተደርጓል
መሰረት ከማህበረሰቡ በአንድ ጊዜ ብቻ 2.6 ሚሊዬን ብር ለስራ ማስጀመሪያ ተብስቦ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡
በሂደት 6.5 ሚሊዬን ብር ወጭ የተደረገበት የደብረ ፀሀይ ቁስቋም ቤቱ ክርስቲያን ጥገና ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ
ጥር 6/2015 ዓ.ም ተመርቆ ወደ ስራ ገብቷል፡፡

2.1.3. ደብር ብርሃን ሰላሴ ከለውጥ በፊት የበረበት ሁኔታ


የደብረ ብርሐን ስላሴ ቤተ ክርስቲያን በአፄ እያሱ መንግስት 16 ኛ ክፍለ ዘመን መገባደጃ እንደተሰራ ይነገራል፡፡ ይህ
ቤተክርስቲያን በአሰራሩ ከሁሉም ቤተ ክርስቲያኖች ለየት ያለ ሲሆን ከጥንታዊነቱ በሻገር የጎንደር ስዕል ጥበብን የሚያሳዩ
የግድግዳ ላይ ስዕሎች በውስጡ የያዘ ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ሆኖም እንደ ቁስቋም ሁሉ በተለያዩ ተፈጥሮዊ
ችግሮች የመፈራረስ ኣዳጋ ተጋርጦባት ቆይቷል፡፡ በመሆኑ ጣራው እንዲሁም ግድግዳ ማዕዘን ድንጋዮች፣ የኖራ መርከስ እና
የጣራ መፈራረስና ውሃ የማስገባት ችገር ነበረበት፡፡ በመሆኑም ህንጻውን ጉዳት ከመጨመር በላይ በውስጡ ያሉ አይተኬ
የሥዕል ስራዎች ላይ አደጋ ጋርጦ ቆይቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የአዋፍት ኩስ፣ አልጌና ሌሎች በካይ ቁሶች በህንጻው ላይ የነበሩ
በመሆኑ ጉዳቱን ይበልጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደግ መጥቶ ነበር፡፡ በመሆኑም የማህበረሰቡ የቅሬታ ምንጭ ሆኖ ይጠገንልን
ጥያቄ በተደጋጋሚ የሚቀርበብት ታሪካዊ ቅርስ እና ስፍራ ነበር፡፡

2.1.4. ለውጡት ሁለት ደብር ብርሃን ሰላሴ ጥገና የተከናወኑ ተግባራት

7
የቁስቋምን መርሐ ግብር ተከትለን የተፈፀመ ሲሆን በዚህ
በደ/ብርሃን ስላሴ ቤተክርስቲያን ጥገና ላይ ተመሳሳይ ተግባርት
በመፈጽም ከፍተኛ ውጤት ተገኝቷል፡፡
በመጀመሪያው አካባቢያ በተደረገ ጥረት 124 ሺ ሰዎችን ላይ
በተፈጠረሰ ግንዛቤ ስራ እና ከግንዘቤ ፈጠራ በኋላ በተደረገው ገቢ
ማሰባሰቢያ ስልት መሰረት ከማህበረሰቡ 2.8 ሚሊዮን ብር ተሰብሰብ
ወደስራ የተገባ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደስራ ገብቷል፡፡

2.1.5. ጠዳ እግዚአብሔር አብ ከለውጥ በፊት የበረበት ሁኔታ


የጠዳ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን 15 ኛ ክፍለ ዘመን ከተገነቡ አብያተ ክርስቲያንት አንዱ ሲሆን በአጼ ሱሲንዮስ ዘመን
መንግስት እንደ ተገነባ ይነገራል፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌሎ ጥንታዊ ቤተክስርሰቲያኖች ምንም ዓይነት ጥገና ተደርጎለት
ሰለማያውቅ የጉዳት መጠኑ እጅግ ከፍተኛ ነበር፡፡ በመሆኑ በርከታ የህንጻው ከፍሎች በተለይም ኖራዎቹ ተፈነቃቅለው ይታዩ
ነበር፡፡ ከፍተኛ የሚባሉ ስንጥኮች በህጻው ዙሪያ ይታዩ ነበር፡፡ አካበቢውም በአረሞና መሰል ችገሮች ተዎ ይስተዋል ነበር፡፡

2.1.6. ለውጥ ሶስት ጠዳ እግዚአብሔር አብ ጥገና የተከናወኑ ተግባራት

የቁስቋምንና የደብረብርሐን ስላሴን ተሞክሮ በተመሳሳይ ወስደን ለዚህ ጥናታ በተክርስቲያን ጥገና ተግበራዊ
አድርገነዋል፡፡ በመሆኑ በመጀመሪያው አካበቢያ በተደረገ ጥረት ከግንዘቤ ፈጠራ በኋላ በተደረገው ገቢ ማሰባሰቢያ
ስልት መሰረት ከማህበረሰቡ 3 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ፕሮጅቱ ለቅርስ ጥበቃ በላስልጣን ቀርቦ 3.8 ሚሊዮን
ብር ድጋፍ እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ በድመሩ 6.8 ሚሊዮን ብር ተሰብሰቦ ወደስራ የተገባ ሲሆን አሁን ሰዓት
ጥገናው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ወደስራ ገብቷል፡፡

3. በአጋር አካላት ተሳትፎ የፋይናንስ አቅም መጨመር


3.1. ፋሲል አብያ ተመንግስት ትራንሰፈርመር ተከላ በፊት የነበረ ሁኔታ
የጎንደር አብያተ መንግስታት ቅጥር ግብ ከ 70 ሺ ካሬ ሜትር ስኩዌር የሚሆን ስፋት ላይ ያረፉ 7 ነገስታት ቤተ መንግስቶች
እና ሌሎች አገልግሎት ሚሰጡ የነበሩ ጥንታዊ ግብረ ህንጻዎችና በርከታ ፍርስራሾችን በውስጡ የያዘ ታሪካ ስፋራ ነው፡፡
8
በርከታ ጎብኝዎችን ሚያስተናግድ ሲሆን ከአንድ ቆጣሪ ውጭ ምንም ዓይነት የሀይል አቅርቦት አልነበረውም፡፡ ስለሆነም
ለተለያዩ ስራዎች የሚውል ኃይል ባለመኖሩ አካበቢውን ማልማት ሳይቻል ቆይቷል፡፡ በተለይ መዝናኛዎችን እንዲሁም
ምሽት ጉብኝትን በቦታ ማከሄድ አይቻልም ነበር፡፡

ውጤት 1. ፋሲል አብያ ተመንግስት ኢንስታሌሽ


በመብራት እና በኃይል ሙሉ አቅርቦት እንዲኖረዉና የመምሽ ጉብኝት እንዲጀምር ለማስቻል የትራንስፈር እና
ተከላ ስራ መስራቱ እንዱ የዚህ ፕሮጀክት ተግባር ሲሆ ይህን ተከትሎ ኢንስታሌሽን ሌላ ፌዝ ነበር፡፡ በመሆኑም
የጎንደር ዩኒቨሲቲ በዚህ ፌዝ ብቻ ከመምሪያችን ኃላፊዎች ጋር በማድረግ ኢንስታሌሽኑን ወሰድ እንደሚፈጽም
ቃል ገባ፡፡ ይህ በአሁነ ወቅት ተግበራዊ እየተደረገ ያለ ሲሆን ሲጠናቀቅ የ 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት ሙያዊ እና
ቁሳዊ ድጋፍ ነው፡፡

ውጤት 2. .ፋሲል አብያ ተመንግስት ትራንሰፈርመር ተከላ


በዚህ ፕሮጅት ላይ የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ኃይል ፕሮጅቱን እንዲደግፍ ሰፊ ውይይት

ከአመራሩ ጋር ተደርጓል፡፡ መግባት ላይ ተደርሶ ጥር 2013 ዓ.ም ይን ተግበራዊ ለማድረግ ስራ ተጀምሯል፡፡

በመሆኑም ጥር 6 ትራንስፈርመር ወደ 6 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ለመምያችን አስረክቧል፡፡

4. የአጋር አካት ተሳትፎ ተሳትፎን ለማሳደግ የራስ ግንብ ሙዚየምን መልሶ የማልማት የተሰሩ ዝርዝር
ተግባራት
4.1. የማልማት ስራ ከመሰራቱ በፊት
ራስ ግንብ በአጼ ፋሲል ዘመነ መንስት ከተገነቡ ቀደምት ታዊካዊ ህንጻች አንዱ ሲሆን አጼ ፋሲል ለጦር አበጋዛቸው
ለራስ ወልደ ጊዎርጊ መኖሪያ ቤት ይሆን ዘንድ የተገነባ ህንጻ ነው፡፡ ይህ ህንጻ ምንም ዓይነት ጥገና ተደርጎለት
የማያውቅ ከመሆኑም በላይ በተለያዩ ጊዜያት አላስፈላጊ ሚበሉ ጣልቃ ገብነቶች ሲዳርጉበት የቆየና ትኩረት ተነፍጎ
የኖረ ታሪካ ሐብት ነው፡፡ በመሆኑም በስመንቶ የተለጠፈ፣
በአልጌ የተወረረ፣ በወፎች ኩስ ተወረራ እና በስጥቆች
የተሸሞነሞነ የነበ ህንጻ ነው፡፡ ቅጥር ግቢውም በአረሞ
እንዲሁም በተለያ አላፋስላጊ ህጻዎች ግንባታ ይዘቱ
የተረበሸ ግቢ ነው የነበረው፡፡ ልዕየታ ያመይስብ ነው
የነበረው፡፡
4.2. የመጣ ለውጥ
 ገጽ ምድር የማስዋብ ስራ
 የመዝናኛ፣ የባህል ምግብ በመጠጥ ማቅረቢያ ጎጆ
ቤት ስራ ተከናውኗል፡፡

9
 በዚህ ስራ ከ 4 ሚሊዮን ገደማ የሚገመት ወጭ የጠየቀን ሲሆን ይህም የተሰበሰበው

 ፕሮፖዛል በመቅረጽ በዚህ ላይ ከሀበሻ ቢራ ጋር መግባባት ላይ በመድረስ የተቻለ ሲሆን ታላቅ የሙዚቃ
ኮንስርት በማዘጋጀት ወደ 780,000 ብር ተገኝቷል፡፡
 ከተቋማት ድጋፍ 2 ሚሊዮን የሚገመት ብር በዓይነት ድጋፍ ተገኝቷል፡፡

5. የወዳደቁ ቁሳቁሶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል የተከናወኑ ዝርዝር ተግባት


የመጣ ውጤት1. የሽንት ቤት ግንባታ
የመጣ ውጤት2. የፓኔሎች ግንባታ እና ወክ ወይዮች ጥርዝ ግንባታ የተከናወኑ ተግባራት

የተለያዩ ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ የወሉ ቁሳቁሶች ማለትም፡-


 ቁርጥራጭ ብረቶችን
 እንጨቶች
 የደረቁ የኖራ ግግሮች
 ፕላተኮች

የአጋር ኣካላት ተሳትፎ


በተቀረጸው ፕሮጅከቱ መተማመን ላይ በመድረስ ሁሉም አጋር አካለት ማለትም ክ /ከተሞች የፈረሱ ቤቶች እንጨት
በመስጠት ግብዓት እንዲሆኑን ግምቱ 61400 ብር የሚሆን እንጨር አበርክተዋል፡፡ የመንገድ ስራዎች ባለስልጣን ትርፍ ሆነው
በሳይቶች ላይ የወዳደቁ 7 ሜትር ኩብ ድንጋዮን ግምታቸው 21000 ብር እንዲሁም ቁርጥራጭ ቴንዲኖ በረቶች እና
ስታፋዎችን ግምታቸው 31205 ብር የሚሆኑ ንብረቶችን በስጦታ በማበርከት ከፍተኛ አጋርነታቸውን አሳይተዋል፡፡ የጎንደር
ከተማ አካበቢ ጥበቃ ተቋም የተለያ ገጽ ምድር ማስዋቢያ የሚሆኑ የአረንጓዴ ሳር ዘሮ፣ የአትክል ፈሎች በማበርከትና ሙያዊ
ድጋፍ በመስጠት ድጋፍ አድገዋል፡፡
ከተማ ልማት መምሪያ ንረቶችን ካሉበት ወደ ቅርስ ሳይት በመጓጓዝ ትልቅ ድጋፍ አደርገውልና፡፡

ከዚህ ውጭ ያሉ ቀረ የወዳደቁ ንብረቶችን በቅርስ ጥገባ ፕሮጅክት ተገዝተው የተጣሉንት በቅጥር ግቢያችን በማስበሳሰቡ
ጥቅም ላይ እንዲውሉ በማደረግ ነው፡፡

 እነዚህን ግብአቶች በልሶ ጠቅም ላይ በመዋል ወደ 820,000 ብር የሚገመት ግብዓት እንዲሆኑን በማስቻል በፋሲል

አብያተ መንግስትና በራስ ግንብ ሙዚየም 2 ደረጃቸውን የጠበቁ ሽንት ቤቶች ተግንብተው ለጎብኝ አገልግሎት
እንዲሰጡ ተደርጓል

 የደረቁ የኖራ ግግሮች የራስ ግንብ ሙዚም የእግር ምገድ እና ከርብ ስቶን ስራ እንዲሰራ ተደርጓል

10
 ከወዳደቁ ብረቶች ለጎብኝው መረጃ ሚሰጡ ከ 220 በላይ ፓኔሎች

ተሰርተው በራስ ግብ ሙዚየም እና በአብያተ ምገስቱ ተቀምጠው አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል፡፡

 በዚህ ምክኒያት ተልከስክሰው አካበቢን ያበላሹ የነበሩ አላፋለጊ ቁሳቁሶች ጥቅም ላይ እንዲወሉ ተድርጎ ወጭን
ከመቀነስ በላይ የአካበቢው ውበት እንዲጠበቅ በማድረግ ከፍተኛ ጠቅም አስገኝቷል፡፡

6. በህዘብ ተሳትፎና በአጋር አካለት ድጋፍ የመጣ ኢኮኖሚና የማህበራዊ ፋይዳ

6.1. የተገኘ ኢኮኖሚ ጥቅም ስሌት


ተ.ቁ የገቢ ርዕስ መለኪያ ገቢ መጠን ምርመራ
1 ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ከ በህ/ሰብ በብር 6,500,000
ተሳትፎ
2 ደብረብርሃን ስላሴ በህ/ሰብ ተሳትፎ በብር 2,800,000
መጠገኑ
3 ጠዳ እግዚአብሔር አብ መጠገ በብር 3,000,000

4 ፋሲል አብያ ተመንግስት በመብራት እና በብር 6,000,000


በኃይል ሙሉ አቅርቦት እንዲኖረዉ
የትራንስፈር እና ተከላ ስራ
5 ፋሲል አብያተ መንግስት የማታጉብኝት በብር 2,000,000
ለማስጀመር የኤሌክትሪክ ኢንስታሌሽን
6 እራስ ግንብ የመዳረሻ የልማት ስራ በብር 2,000,000
መጠናቀቁ በህብረተሰብ ተሳትፎ የተሰራ ስራ
በዝርዝር

11
7 ከወዳደቁ ቁሳቀሱች በገንዘብ የሚገመት በብር 820,000
ግብዓት
8 ጠቅላላ ድምር በብር 23,120,000

በዚህ ሰንጠረዥ እንደሚታየው 23,120,000 ብር መንግስት ለጥገና የጎደለውን ከአጋር አካለት እንዲም ከማሀብረሰቡ
በማሰባሰብ ጉድለቱን በብቃት መልቶ ሊሰሩ የሚችሉትን የጥገናና እንክብካቤ ስራ በቅሶቻችን ላይ መስራት መቻላት ትልቅ
አቅም በገቢየ ላይ ልንፈጥር ከሚያስችሉን አንዱን እና ዋነኛው ደረጃ አሟልተና ተበሎ ይገመታል፡፡

6.2. ማህበራዊ ፋይዳ


በቃለ መጠይቅ እና በቡድን ውይይት ከተገኙ ውጤቶች

 በቅርስ ባለቤትነት እና የኔ ባይነት ስሜት በማህበረሰቡ ዘንድ ስር እንዲሰድ ትልቅ ፋይዳ መኖሩ
ተረጋግጧል
 በመንግሰት እና ማህበረሰቡ እንዲሁም በማህረሰቡ መካከል ከፍተኛ መቀራረብን የፈጠረ ተግባራ
መሆኑ ተረጋጧል
 ቅርሶች እንዲሁም ሌሎች አካባቢያችን ጸጋዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ተለይተው እንዲታወቁ የማደረግ
እድልን በመፍጠር የጋራ ግንዘቤ ያደገበት ሁኔታ ፈጥሯል፡፡
 በራስ የሚተማመን ማህረሰብ በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሚና እደነበረው ተረጋግጧል፡፡

7. የነበሩ ጥንካራ፣ ደካማ ጎኖች፣ መልካም እድሎች እንዲሁም ተግዳሮቶች ትንተና (SWOC)

7.1. ጠንካራ ጎን

 ጠንካራ ማህበረሰባዊ አደረጃጀት ያልን በመሆኑ

 በመምሪያው ያሉ ባሙያዎች ከፍተኛ የእውቅት እና ክህሎት ያላቸው መሆኑና ችግሩን ተረድቶ ወጭ ቆጣቢ በመሆነ
መንገድ ተግባራትን ለመፈጽም ያለው ዝግጁነት

 የሀሳብ አፍለቂነት ባህሪ የተቋማችን መገለጫ መሆኑ

 ከአጋር አካላት ጋር ያለን ቅርርብ ከፍተኛ መሆኑ

12
 ከሁኔታው ጋር የሚሄዱ ፕሮጅከት ፕሮዛሎችን በጥራት ቅረጽና ተግባዊ ላድረግ ያለው ጥረት

7.2. ደካማ ጎን

 የበጀት እጥረት በተቋማችን ያለብን መሆኑ

7.3. መልካም እድሎች

 መንግስት በህዝብ ተሳትፎ የልማት ስራዎች እንዲሰሩ የሚፈጥረው ንቅናቄ

 ይህን ተግባር የሚደግፉ መመሪያዎች ፖሊሲዎች በመንገስት ተቀርጸው ተግባራዊ መደረጋቸው

 የማህበረሰባችን ቀናኢነት እና ተሳታፊነት የዳበረ ሆኖ መቆየቱ

 የአጋር አካላት በቅርስ ዙሪያ ከመምሪያችን ጋር ለመስራት የነበራቸው ከፍተኛ ፍላጎት

7.4. የነበሩ ተግዳሮቶች

 የኮረና ወረርሽኝ

 በሰሜን የአገራን ከፍል ተቀስቅሶ የነበረው ጦርነት

 በከተማችን የነበረው የዕምነት ግጭት

 የፖለቲካ አለመረጋጋት

8. የቀረቡ አስተያየቶ (Recommendations)


 ይህን ተሞልሮ በተደራጀ መንገድ ስለተከወኑ ለአጠቃለይ ማህበረሰቡ በውይይት ቢቀርብ ለቀጣይ ስራ ውጤት
እንዲያድግ ያስቻላል

 በሰነድ ደረጃ ተዘጋጅቶ ቢታትም እና ለአንባቢያን በመረጃ መስጫ ማዕከላት በቤተ-መጻሀፍት እንዲቀመጥ ቢደረግ
 ለአስተዋጽኦ ላደረጉ አጋር አካለት ቢሰራጭ
 በኢንተርኔት ወይም በዌብ ሳይት ለሁለም ተደራሽ እንዲሆን ቢለቀቅ መልካም ነው

13
9. ማጠቃለያ
የገንዘብ እጥረት በመንግስት ተቋማት የመግጠሙ ሁኔታ ዛሬም እንዲሁም ለቀጣይ አመታት ሊቀጥል
የሚችል ችግር በመሆኑ ይህን ጉድለት ሊሞላ የሚችል ደግሞ የማህረሰቡ ተሳትፎ መሆኑን ያየናቸው
ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ስለሆነም ከአጋር አካለት ጋር ተቀራርቦ መስራት፣ ኪነ ጥበብን መስረት ያደረገ የገቢ
ማሰባሰቢያ ስልቶችን ተግራበዊ ማድረግና ማህረሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ለማኝኛውም አይነት ልማት ስራ
ተጨማሪ ሀብትን ፈጥሮ ተግባራዊ በማድረግ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግርች መፍታት ይቻላል፡፡

የጎንደር ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ በመንግስት በጀት የማይሸፈኑ የቅርስ ጥገና ጉዳዮችን የከወነው በዚህ
መንገድ እንደሆነ ይህ ተሞከሮ ያስረዳል፡፡ በተለይም ፕሮጅክቶችን በመቅረጽ፣ ከማህበረሰቡ ጋር በአደረጃጀት
ውይይት በማድረግ፣ አጋር አካላትን ጋር በተመረጡ ስራዎች ላይ አብሮ ለመስራት ሰምምነት ላይ በመድረስና
የኪነ ጥበብ ስራዎን ለገቢ ማመንጫነት አደርጎ በመጠቀም እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ ሰለሆነም ይህን ተሞክሮ
ሊያሰፋ የሚፈልግ አካል እዚህ ላይ አተኮሮ እንደ አካባቢው ነባራዊ ሁኔታ ቃኝቶ ተግራባዊ ቢያደርግ መሰል
ውጤቶችን በአካባቢው ሊያጣ እንዲችል እሙን ነው፡፡

14
ማጣቀሻ

ben, M. (2014, sept 24). wolrdtourism. Retrieved ju ne 02, 2023, from www.wto.com:
hh://www.wto.com
Dawning, A. (2015). information. Retrieved june 07, 2023, from Newsights:
www.newsight.com
Kadile. (2012). in creative world: who shoulder the role. Abuja: Abjua publishing.
Kin, L. (2014, july 06). creative world. Retrieved june 08, 2023, from cinima Host:
http://www.cinimahost.com
Luodolf, S. (1991). effectiive community based tourism Development . London: London
pulishing.
Peterson, A. (2015). community based ecotourism. Easian Tourism , 78-81.
Sales @exploring moroco travel. (2023). home. Retrieved from Exploring morocco travel:
Exploringmoroccotravel.com

15

You might also like