Professional Documents
Culture Documents
ዐማርኛ
ዐማርኛ
“በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ መረዳት ችሎታ ተዛምዶ፤ በዳባት ሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት በዘጠነኛ ክፍልተ ማሪዎች ተተኳሪነት” በሚል ርእስ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ በማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብዕ
ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ቋንቋ(ዎች)ና ስነጽሁፍ አማርኛ ትምህርት ክፍል በተግባራዊ ስነ-ልሳን አማርኛን ማስተማር
ለማስተርስ ዲግሪ ማሟያነት ያቀረብኩት ይህ ጥናት ከዚህ በፊት በማንኛውም አካል ያልተሰራ የራሴ ወጥስራ መሆኑንና
የተጠቀምኩባቸው ድርሳናትም በትክክል ዋቢዎች የሆኑና ጎንደር ዩኒቨርሲቲም የጥናቱ ህጋዊ ባለቤትነት ያለው መሆኑን
በፊርማዬ አረጋግጣለሁ፡፡
ስም ----------------------------------------------
ፊርማ -------------------------------------------
ቀን--------------------------------------------------
ምዕራፍ አንድ
መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
ማንበብ የተጻፈን ነገር ቀጥተኛ ትርጉም መረዳት ብቻ ሳይሆን፣ በጽሁፍ ውስጥ በተዘዋዋሪ መንገድ የተገለጸን
ሃሳብንም የመረዳት ሂደት ነው (ቤከር፣ 2008)፡፡ እንደቲየርኔይ (2005) ገለጻ ለማንበብ መማር ቃላትን ለማወቅ ወይም
ለማስታወስ መማር ብቻ ሳይሆን የምንባብን አጠቃላይ ትርጉም ለመረዳት መማርንም ያካትታል፡፡ ማንበብ የአራት
ጉዳዮች መስተጋብር ውጤት ነው፡፡ አንደርሰን (2003) እንደገለጹት ማንበብ የአንባቢ፣ የውህድአሃድ፣ የአቀላጥፎ
ማንበብ (በተገቢ ፍጥነት በትክክል አንብቦ የመረዳት ችሎታ) እና የብልሃታዊ ማንብበ (የማንበብ አላማ ለማሳካት
የአንባቢው የተለያዩ የማንበብ ብልሃቶችን የመጠቀም ችሎታ) መስተጋብር ያካትታል፡፡ይሁን እንጂ በተለያዩ ጊዜያት
በተለያዩ ንድፈሃሳቦች ስለማንበብ የተለያዩ ዕይታዎች ሲንጸባረቁ ቆይቷል፡፡ ከ 1950 ዎቹ እስከ 1960 ዎቹ የነበረውና
የባህርያውያን ንድፈሃሳብ ስነ-ልቦና ተጽዕኖ ያረፈበት የማንበብ ትምህርት ዕይታ ታህታይ-ላዕላይ ዕይታ ነው፡፡ በዚህ
ዘመን የነበሩት ተመራማሪዎችና የትምህርት ባለሙያዎች ማንበብን እንደታህታይ-ላዕላይ ሂደት አድርገው ያስቡ ነበር፡፡
ታህታይ-ላዕላይ የማንበብ ሂደትን ያስተዋወቁት ጎፍ (1972)፣ ላበርግና ሳሙኤልስ (1974) ናቸው፡፡ ይህ የማንበብ ዕይታ
የልየታ (decoding) ንድፈሃሳብ በመባልም ይታወቃል፡፡ በዚህ የማንበብ ዕይታ ለማንበብ አስፈላጊው ነገር ውህድአሃዱ
ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም በዚህ ዕይታ ትርጉም ያለው በተጻፈው ነገር ወይም በወረቀት ላይ ብቻነው፤ ተብሎ ይታሰባል፡፡
ማካርቲ (1999) እንደሚሉት ይህ ዕይታ ከውጭ ወደውስጥ ሂደት (Outside-in processing) ነው፤ ምክንያቱም
ትርጉም ያለው በተጻፈው ነገር ላይ እንደሆነና በአንባቢው እንደሚተረጎም ስለሚታሰብ ነው፡፡ ኑናን (1991)
እንደሚያስረዱት አንብቦ መረዳት በጽሁፍ ውስጥ ያሉ ምልክቶችን በተናጠል የመለየት ጉዳይ ሲሆን፣ አንባቢው
ውህድአሃዱን በመመልከት መጀመሪያ በቃል ውስጥ የሚገኙ ፊደላትን በተናጠል ከለየ በኋላ ወደ ውስብስብ ቅንጣቶች
ይሸጋገራል፡፡ በሌላ አገላለጽ በመጀመሪያ ፊደላቱን ይለያል፣ ከዚያም ከፊደላት የተዋቀሩትን ቃላት ይለያል፤ ከቃላት ወደ
ሃረጋት ልየታ ይሸጋገራል፤ ከዚያም ወደ ዐረፍተነገር ልየታ ይሸጋገራል፤ በእነዚህ ሁሉ ሂደቶች ትርጉም ይረዳል፡፡ አንባቢው
የውህድአሃዱን ትርጉም የሚረዳው ግን የልየታ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ነው(ሃሪስ፣ 2005)፡፡ በአጠቃላይ በዚህ የማንብብ ዕይታ
ማንበብ አንድ አቅጣጫን የሚከተል (ከውህድአሃዱ ወደአንባቢው የሆነ) ሂደት ነው፡፡ ውጤታማ ማንበብ ማለት
አንባቢው ጸሃፊው በውህድአሃዱ ያሰፈረውን መልዕክት የመረዳት ችሎታ ካለው የማንበብ ተግባሩ ውጤታማ ይሆናል
ተብሎ የሚታሰብበት ነው፡፡ አንባቢው የቀረበውን ውህድአሃድ በመገንዘብ ብቻ እንዲገደብ የሚያደርግ ነው፡፡ አንባቢው
በማንበብ ሂደቱ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ የማይሆንበት የማንበብ ሂደት ስለሆነ፣ አመለካከቱ አሉዊይሆናል፡፡ በ 1970 ዎቹ
የነበረውና በአዕምሯውያን ንድፈሃሳብ ላይ የተመሰረተው የማንበብ ትምህርት እይታ ደግሞ ላዕላይ-ታህታይ ሂደትነው፡፡
ይህንን የማንበብ ሂደት ያስተዋወቁት ስሚዝ (1978) እና ጉድማን (1976) ናቸው፡፡ ይህ የማንበብ ሂደት በ 1970 ዎቹ
በአዕምሯዊ ሳይንስ ረገድ የአመለካከት ለውጥ ከመከሰቱ ጋር ተያይዞ የመጣ ነው፡፡ ዘመኑም የባህርያውያን የማንበብ
ዕይታ በአዕምሯውያን የማንበብ ዕይታ የተተካበት ነው፡፡ ይህ ዘመን መማር እንዲከሰት የአዕምሮ አስተዋጽኦ ከፍተኛ
እንደሆነ የታሰበበት ጊዜ ነበር፡፡ የታህታይ-ላዕላይ የማንበብ ሂደት በላዕላይ-ታህታይ ሂደት የተተካበት ነበር፡፡ የማንበብ
ሂደቱመሰረት ድምጸልሳናትን ማደራጀት ወይም የፊደላትና የቃላት ልየታ አስፈላጊ ቢሆንም ለተሳካ ማንባብ ግን በቂ
አይሆንም የሚል ነበር፡፡ በመሆኑም በላዕላይ-ታህታይ ሂደት አንብቦ መረዳት ሁልጊዜም ቢሆን አንባቢው ስለውህድአሃዱ
ርዕስ በሚኖረው የቀደመ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ መሆን አለበት፡፡ የማንበብ ሂደት የሚጀምረው በአንባቢው ጭንቅላት
ውስጥ ነው፡፡ በመሆኑም በላዕላይ-ታህታይ ዕይታ ትኩረት የሚሰጠው ለትርጉም ምስረታ የአንባቢው ዳራዊ ዕውቀትና
የውህድአሃድ መስተጋብር ነው (ሀሪስ፣ 2005)፡፡ ላዕላይ-ታህታይ ሂደት ተማሪዎች ለማንበብ የሚማሩባቸውን መንገዶች
ጽንሰ ሃሳብ አሳይቷል (ስሚዝ፣ 1994)፡፡ በማንበብ ሂደት ዳራዊ ዕውቀት መጠቀም፣ ከመረጃ በመነሳት የራስ ውሳኔ ላይ
ወይም ማጠቃለያ ላይ መድረስ፣ አንብቦ መረዳትን መቆጣጠር፣ ለመሳሰሉት ጉዳዮች ትኩረት ይሰጣል፡፡ ላዕላይ-ታህተይ
ሂደት ተማሪው ዝም ብሎ መረጃ ተቀባይ ሳይሆን፣ በትርጉምና በዕውቀት ምስረታ ሂደት ውስጥ በንቃት ሲሳተፍ ነው
መማር የሚከሰተው የሚለውን የግንባታውያን ዕይታ ይቀበላል፡፡ የግንባታውያን ዕይታ ተማሪው አዲስ መረጃን ወይም
ተመክሮን ለመረዳት የማሰብና የአዕምሮ ሂደቶችን ይጠቀማል፤ አዳዲስ ነገሮችንም ይማራል (ሮቢንሰን
ሞሌንዳናሬዛቤክ፣ 2008)፡፡ በቅድመ ማንበብ፣ በማንበብና በድህረ ማንበብ አንባቢው በጭንቅላቱ ውስጥ የሚያስበውን
ነገር ያካትታል (ኦርምሮድ፣ 2008)፡፡ በግንባታውያን ንድፈሃሳብ አንባቢው በመማር ሂደት ውስጥ እንደንቁ ተሳታፊ
የሚታይበት ብቻ ሳይሆን የአንባቢው ውህድአሃድን መረዳትም እንደትርጉም ምስረታ ሂደት የሚታይበት ነው(ግሬቭና
ሌሎች፣ 1998)፡፡ ይህም ማለት ተማሪው ከውህድአሃዱ ዝምብሎ ትርጉም የሚቀበልበት ወይም የሚያገኝበት ሳይሆን
እያነበበ እያለ ትርጉም የሚመሰርትበት ሂደት ነው፡፡ አንድ አንባቢ ከውህድአሃዱ የሚመሰርተው ትርጉም በንባብ አውዱ፣
በአንባቢው ተመክሮ፣ በአንባቢው ችሎታና በሌሎችም ምክንያቶች ተጽዕኖ ስለሚደርስበት ሌላው አንባቢ
ከሚመሰርተው ትርጉም ይለያል (ካምቦርኔ፣ 2004)፡፡ ስለሆነም ሁለት አንባቢዎች ከአንድ ውህድአሃድ አንድ አይነት
ትርጉም ይመሰርታሉ ማለት አይቻልም(ግሬቭና ሌሎች፣ 1998) ፡፡ ምክንያቱም አንባቢዎች በማንበብ ሂደቱ ውስጥ ንቁ
ተሳታፊዎች ስለሚሆኑ በራሳቸው ትርጉም ስለሚመሰርቱ ነው፡፡ ንድፈሃሳቦቹ እንዳሉ ሆነው ሰለንባብ ልምድና አንብቦ
መረዳት ችሎታ በተለያየ ጊዜ የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን የራሳቸውን ብያኔ ሰጥተዋል፡፡ ቴንድል(2003) ማንበብ ከተፃፈ
ነገር ላይ ትርጉምን መረዳትና መረጃን በአግባቡ የመውሰድ ደረጃና ከቋንቋ ክሂሎች ውስጥ በመማር ብቻ የሚገኝ
ከማዳመጥና ከመናገር ቀጥሎ የሚመጣ ክሂል ነው፤ ሲሉ አያይዘውም ስለንባብ ማንበብ ከዝቅተኛ የክፍል ደረጃ ጀምሮ
ወደከፍተኛ የክፍል ደረጃ በሚሄድበት ጊዜ ልምዱም ሆነ የመረዳት ችሎታው አብሮ እያደገ እንደሚመጣ ያሰረዳሉ፡፡
በሌላ በኩል አልደርሰን (2003) ማንበብ ከተፃፈ ጹሁፍ ላይ መረጃ መውሰድ ብቻ ነው ብሎ ወስኖ ማስቀመጥ
ያስቸግራል፡፡ ይኽውም አንድ አንባቢ የሚያነበው ለተለያየ አላማ በመሆኑ ከአላማው አንፃርም የተለያዩ ውህድ
ክሂሎችንና ብልሀቶችን ሊጠቀም ይችላል፡፡ ሰለዚህ ንባብ ለእውቀት (ለመረዳት) ተብሎ ብቻ የሚተገበር ሳይሆን እንደ
አንባቢው አላማ ለተለያዩ ተግባራት የሚፈፀም በመሆኑ በውስጡ ሌሎች ንዑሳን ክሂሎችን አካቶ የያዘ ክሂል ነው
በማለት ይገልጻሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ኒልሰን (1963) ንባብ በየእለቱ በሚደረግ ተከታታይነት ያለው ልምምድ እያደገና
እየጎለበተ የሚመጣ ክሂል መሆኑን ገልፀው ለተማሪዎች ያለውን ጠቀሜታ ሲያስረዱ ንባብ በተማሪዎች ውጤት ላይ
በየጊዜው የሚታይ የራሱ አሻራ ያለው የቋንቋ ክህሎት ነውይላሉ፡፡ እንደስሚዝ (1978)፣ ኑናን (1982) እና ኮንሌፍ
(1992) አገላለጽ ደግሞ፣ ማንበብ ማለት ደራሲው ለተደራሲው ሊያስተላልፍ የፈለገውን መልዕክት የመረዳት ሂደት
ነው፡፡ በሌላ በኩል ንባብ የደራሲውና የአንባቢው የሁለት ወገን ግንኙነት እንደሆነና ግንኙነቱም ቀስ በቀስ እያደገ
እንደሚሄድ ሚች (1997) ይገልጻሉ፡፡ ብራነስ (1984) የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ለሁለተኛ ቋንቋም
ሆነ ለአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት አስፈላጊና ወሳኝ እንደሆነ ያሰረዳሉ፡፡ ኦሁሹ አችዋ (2014) በበኩላቸው የማንበብ
ልምድ ተማሪዎች ፊደል መቁጠር ከሚጀምሩበት ጊዜ ጀምሮ እየሰፋና እየጎለበተ የሚመጣ ችሎታ እንደሆነና ተማሪዎች
አንድን ርዕሰ ጉዳይ ወይም የትምህርት ይዘት አንብበው ከተረዱ በኋላ ለመመለስ፣ አካባቢያቸውን ተረድተው እንዲኖሩ፣
የእውቀት አድማሳቸው እንዲሰፋ ከክፍል ወደ ክፍል እንዲዘዋወሩ ለማድረግ ቁልፍ ሚና የሚጫዎት፡፡ የተማሪዎችን
የትምህርት ውጤት በመወሰን በኩልም ትልቅ ሚና ያለው እንደሆነ ያሰረዳሉ፡፡ በመሆኑም አንብቦ የመረዳት ችሎታ
ለአንድ ለተወሰነ የክፍል ደረጃ የሚዘጋጅ ንባብን በክፍል ደረጃው የተመደቡ ተማሪዎች ያለምንም ችግር ማንበብና
የምንባቡን ሀሳብ መረዳት መቻልን ያመለክታል፡፡ በድሉ(1988) ጋሪሌት (1981)ን በመጥቀስ እንደገለፁት አንድን ምንባብ
መረዳት ማለት ምንባቡ የያዘውን አስፈላጊ መረጃ በሚቻለው መጠን መገንዘብ ነው፡፡ በምንባቡ ውስጥ ተፈላጊውን
መረጃ የመገንዘብ ሂደት የተለያየ ሲሆን ልዩነቱ የሚመነጨው ከሚነበበው የጹሑፍ ይዘት ፣ ከሚነበብበት አላማና
ከማንበቢያ ዘዴው የተነሳ ነው፡፡ ሃይማኖት (በ 2005) ለሁለተኛ ድግሪ መመረቂያ በሰራችው ጥናት ተማሪዎች በክፍል
ውስጥ ከሚሰጧቸው ምንባቦች በተጨማሪ በሕይዎት ዘመናቸው ሊያውቋቸውና ሊረዷቸው የሚፈልጉ የምርምር
ስራዎችንም ጭምር ሊያስቡ የሚችሉት በቀደመ የማንበብ ልምዳቸውና አረዳዳቸው ነው በማለት ገልፃለች፡፡
በመሆኑም አንድን ርእሰ ጉዳይ በውል ለመረዳት ማንበብና የማንበብ ልምድን ማዳበር በጣም አስፈላጊ እንደሆነ አያይዛ
ታስረዳለች፡፡ ግሪን (2001) በበኩላቸው የማንበብ ልምድ የሰው ልጆችን አዕምሮ ሚዛናዊ በማድረግ አንባቢዎች
በሕይዎት ዘመናቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ያደርጋል በማለት ይገልፃሉ፡፡ ባሸርናማቶ (2012) ፓላኒ (2012)ን በመጥቀስ
የማንበብ ልምድ ተማሪዎች ለወደፊቱ የሰነጽሁፍ ጸሐፊዎች እንዲሆኑ ከማድርጉም በላይ አንባቢዎች በመረጃ
ተመስርተው የተደራጀ ሀሳብ እንዲይዙና እንዲያፈልቁ ይረዳቸዋል ይላሉ፡፡ ምሁራኑ አያይዘውም የማንበብ ልምድና
አንብቦ የመረዳት ችሎታ አብዛኛውን ጊዜ የማይለያዩ ሲሆን የማንበብ ልምድ ያላቸው ተማሪዎች በትምህርታቸውም
ውጤታማ ሲሆኑ የማንበብ ልምድ የሌላቸው ተማሪዎች በትምህርታቸው የሚያሰመዘግቡት ወጤትም ዝቅተኛ መሆኑ
የተለመደ እንደሆነ ያሰረዳሉ፡፡ ግርሃም (1987) ተማሪዎች በትምህርት አለም የተሻለ ውጤት አስመዝግበው ለመቀጠል
ከሚያስችሏቸው የትምህርት ሂደቶች ውስጥ የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ዋናው ነው ይላሉ::
ኒልስን (1984) እና ሃይላንድ (1990) በበኩላቸው ስለማንበብ ልምድ ሲያሰረዱ የማንበብ ልምድና አንብቦ
የመረዳት ችሎታ ከሌሎቹ ችሎታዎች ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ምክንያቱም በትምህርት አለም ያሉ ሰዎች
በየእለቱ ከሚነበቡ በርካታ ነገሮች ጋር የመገናኘት ዕድል አላቸው፡፡ ነገር ግን የማንበብ ልምዳቸውና አንብቦ የመረዳት
ችሎታቸው በአግባቡ ከጽሁፎች ተገቢውን እውቀት ለመቅሰም ያስችላቸዋል ለማለት አያስደፍርም ይላሉ፡፡ ቪክቶሪያ
እና ሌሎች (1989) በትምህርት ቤትም ይሁን ከትምህርት ቤት ውጪ ትምህርት የሚገኘው ተማሪዎች ባላቸው
የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ መጠን ነው፡፡ እውቀታቸውም የሚጐለብተው በጽሁፍ በቀረበ ሃሳብ
አማካኝነት ነው፡፡ የትምህርቱም ዋና ግብ ተማሪዎች ከንባብ በቂ የሆነሃሳብና መረጃ እንዲያገኙ መርዳት ነው፡፡
በመሆኑም በመለስተኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በንባብ ፕሮግራም ለተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ
የመረዳት ችሎታ ማደግ ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል ይላሉ፡፡ ምክንያቱም በአብዛኛው የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ
ተማሪዎች እውቀትን የሚያገኙት በማንበብ አማካኝነት ነው፡፡ ውጤታማ የሆነ የአንብቦ መረዳት ችሎታ ያላቸው
ተማሪዎች በማንበብ ሂደት መሠረታቸውን የሚጥሉት አንብቦ ለመረዳት በሚያደርጉት ጥረት፣ በንባብ ዳራቸውና
ሃሳቡን ከቀዳሚ እውቀታቸው ጋር በማዛመድ ነው (አርምብሩስተር፣ አንደርሰን፣ አስታርግ 1987፣ ቪክቶሪያ እና ሌሎች
1989፣ ካሬል 1984፣ ኤጅ 1994፣ ናታል 1996)፡፡ ይሁንና ኮንለይ (1992) እና ዳይሞክስ (2007) እንደሚያስረዱት
ዘወትር እንደሚታየው ተማሪዎች ከንባብ ጋር ሳይተዋወቁ፣ የማንበብ ልምድ አናሳ በሆነበትና አንብቦ የመረዳት ችሎታ
ሳይኖራቸው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቅቃሉ፡፡ በመሆኑም በርካታ ተማሪዎች የማንበብ ልምዳቸውና
አንብቦ የመረዳት ችሎታቸው ደካማ ነው፡፡ የዳበረ አንብቦ የመረዳት ችሎታና ልምድ ስለሌላቸው የሚያነቡትን ምንባብ
በሰፊው እንዳይመለከቱ ከማድረግ ባለፈ በትምህርት ውጤታቸው ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ያሳድራል ይላሉ፡፡ ከዚህ ጋር
በተያያዘ ቤንትዝ (1997) በአንብቦ መረዳት ዙሪያ ከመቶ በላይ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ የሚያስተምሩ 6 መምህራንን
ጠይቀው በሰበሰቡት መረጃ መሠረት ሁሉም መምህራን የተማሪዎቻቸው አንብቦ የመረዳት ችሎታ ያልዳበረ መሆኑን
መግለፃቸውን በጥናታቸው አመላክተዋል፡፡ አርምቢስተርና ሊሎች (1987፣1989) በሁለተኛ ደረጃ ያሉ ተማሪዎች ብዙ
ጊዜ የሚገጥማቸው ችግር ለትምህርት የሚቀርቡ ጽሁፎችን አንብቦ መረዳት አለመቻል ነው፡፡ ችግሮቹ በየትኛውም
ጊዜ እና ቦታ ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ ጽሁፉን ካነበቡ በኋላ ጠቃሚ ነጥቦችን የመለየት ዋናውን ሃሳብ የማውጣትና
የማጠቃለያ ሃሳብን የመጻፍ ችግሮች ይገጥማቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በጽሁፍ ውስጥ ስላለው ሃሳብ የቀደመ እውቀት
አለመኖር፣ ፍላጐት ማጣት፣ አለመነሳሳት በጥቅሉ የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታቸው አናሳ የመሆን
ችግሮች ይታይባቸዋል፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት የዳበረ የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ አለመኖር
እንደሆነ አመላክተዋል፡፡
1. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ተዛምዶ አለ? 2. የተማሪዎች የማንበብ
ልምድ የአንብቦ መረዳት ችሎታቸውን የመተንበይ ድርሻው ምን ያህል ነው?
3. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ ልዩነት ያሳያለል?
1. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ተዛምዶ መኖር አለመኖሩን መመርመር፤
2. የተማሪዎች የማንበብ ልምድ የአንብቦ መረዳት ችሎታቸውን የመተንበይ ድርሻው ምን ያህል እንደሆነ መላከት፣
3. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና የአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ ልዩነት እንዳለው መመርመር
የሚሉ ናቸው፡፡
1.4 የጥናቱ አስፈላጊነት
ይህ ጥናት በተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋ የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ተዛምዶ የሚያተኩር
በመሆኑ ከጥናቱ የሚገኘው ውጤት ለመምህራን፣ ለተማሪዎች እና ለስርዓተ ትምህርት አዘጋጆች የሚከተሉት
ጠቀሜታዎች ያስገኛል ተብሎ ይታመናል፤
1. ለመምህራንና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ተዛምዶ
ምን እንደሚመስል መረጃ ይሰጣል ፡፡ 2. በአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች የማንበብ
ልምድበአንብቦ የመረዳት ችሎታቸው ላይ ይተነብይ እንደሆን ፍንጭ በመስጠት የቋንቋ ትምህርቱ በተማሪዎች
የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ላይ እንዲያተኩር ያደርጋል፡፡
3. የተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋ የማንበብ ልምድ በአንብቦ መረዳት ችሎታቸውላይ ያለውን ጠቀሜታ ያመላክታል፡፡
የተማሪዎች የማንበብ ልምድ በአንብቦ የመረዳት ችሎታ ያለውን የትንበያ መጠን ለመገንዘብ ስለሚያስችል፤ ይህንን
መሠረት በማድረግ የመማሪያ ክፍል የትምህርት አቀራረብ የማንበብ ልምድን እንዲሚያጎለብት መምህራን
እንዲገነዘቡት ያደርጋል፡፡ 4. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና የአንብቦ መረዳት ችሎታ
መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ ልዩነት እንዳለውና እንደሌለው ስለሚያሳይ ወላጆች የልጆቻቸውን የማንበብ ልምድ
አንብቦ የመረዳት ችሎታቸውን በመገንዘብ ለችግሮቻቸው ከመምህራን ጋር በመተባበር መፍትሄ እንዲፈልጉ ያግዛል፡፡
5. የትምህርት ባለሙያዎች በጥናቱ ግኝቶች መረጃ መሠረት የተማሪዎችን የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት
ችሎታን በመገንዘብ መምህራን የትምህርት ዕቅድ፣ መርሐትምህርትና የንባብ ትምህርት መርሐግብር ሲያዘጋጁ
የተማሪዎቹን የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ከማጎልበት አንፃር እንዲመለከቱት ይረዳቸዋል፡፡
ምዕራፍ ሁለት
ክለሳ ድርሳናት
በአንድ ጉዳይ ዙሪያ የቀደመ የንባብ ዳራ፣ ግንዛቤ፣ ዕውቀት፣ ወ.ዘ.ተ. መኖር ያለው ጠቀሜታ በቀላል የሚገመት
አይደለም፡፡ ተማሪዎች ሰለሚያነቡት ቴክስት የቆየ የንባብ ልምድ ሲኖራቸው በቀላሉ አንብበው መረዳት ይችላሉ፡፡
በመሆኑም አንድን ምንባብ ውጤታማ በሆነ መልኩ አንብቦ ለመረዳት የንባብ ልምድን መጠቀም ግድ ይላል፡፡ ለዚህም
ሲልበስትሪንና(1994) እና ኡር (1999) ተማሪዎች በሚያነቡበት ወቅት የሚያነቡት ቴክስት ከአሁን በፊት የሚያውቁት
ከሆነ ያለምንም ድካም በቀላሉ ሊረዱት ይችላሉ፡፡ይህም እውቀት በተለያየ መንገድ ለምሳሌ በመምህራን፣ በወላጅ፣
በመማሪያ ቴክስቶች እና በተማሪዎች የማንበብ ልምድ ሊገኝ እንደሚችል ጥናቶች እንደሚያመለክቱ ካሬ (1983)
ያስገነዝባሉ፡፡ የንባብ ልምድ በተማሪዎች ኑሮ ደረጃ የተለያየ ከሆነ አንብቦ የመረዳት ችሎታም በዚያው መጠን ሊለያይ
ይችላል፡፡ ይህም ሲባል ሰለሚነበበው ቴክስትትንሽ እውቀት ካላቸው ተማሪዎች ወይም አንባቢያን ይልቅ ሰፊ የማንበብ
ልምድ ያላቸው ተማሪዎች ወይም አንባቢያን ቴክስቱን በተሻለ መልኩ ይረዳሉ፡፡ ከዚህ በመነሳት ጆንሰን (2000) የንባብ
ልምድ ያለቸው ተማሪዎች የንባብ ልምድ ከሌላቸው ተማሪዎች በተሻለ የሚያነቡትን ቴክስት ይዘትና ቅንጅት መረዳት
እንደሚችሉ ያብራሩት፡፡ ይህን ሀሳብ ፍሎይድና ሌሎች (1987) ሁለት ምርምሮችን ሰርተው ባገኙት ውጤት የማንበብ
ልምድ ያላቸው ተማሪዎች የንባብ ልምድ ከሌላቸው ተማሪዎች ጋር ሲነፃፀሩ የማንበብ ልምድ ያላቸው ተማሪዎች
ሰለሚነቡት ቴክስት በተሻለ ሁኔታ መረጃውን ለማጠናከር ለመተርጎምና ለመረዳት እንደቻሉ በጥናት ውጤታቸው
ታይቷል፡፡ ንባብ ውስብስብ ሂደት ሲሆን አንብቦ መረዳት ደግሞ አንዱ የንባብ ችሎታ መገለጫ ነው፡፡ የተለያዩ ምሁራን
በስነ ልቦና አንደ ብሉም(1963) እንዲሁም በቋንቋ ስነ ትምህርት መስክ የሚሰሩ እንደ ፐርፊት(1985) ያሉት አንብቦ
መረዳት አዕምሯዊ ሂደት መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ በትምህርት አላማዎች አመዳደብ ብሉም(1963)፣ ቻለሀምና
ክላርክ(1988) አንብቦ መረዳት በአዕምሮታዊ ምድብ ከዕውቀት ቀጥሎ የሚመጣው ዋናው የአዕምሮታዊ
ክፍል(cognitive domains) መሆኑን ይገልፃሉ፡ ፕርፊት (1985) እንዲሁ ሲገልፅ ‹‹ንባብ የበርካታ አዕምሮታዊ ሂደት
ውጤት ነው፡፡ በተለይም አንብቦ መረዳት በአዕምሮታዊ ተግባር ውስጥ፣ ማንበብን የሚወሰነው በአንባቢው እውቀትና
የሚነበበውን ነገር ከመረዳት ጋር በተያያዘ ነው፡፡ ሲል፣ ቢችና ኮል(1987) ይህንን ሃሳብ ሲገልፁ ማንበብ፣ የተለያዩ ቃላትና
ሐረጋትን መገንዘብና መረዳትን ያካትታል፡፡ዋናው የጥሩ አንባቢ ችሎታ በቃላትመደበኛ ትርጉምና አግባባዊ ትርጉም
መካከል ያለውን ግንኙነት ከአሀዱ በመነሳት አስቦ መድረስ ወይም መረዳት 16 ነው፡፡ በሌላ በኩል ጋርሌት(1996)
እንደሚያብራሩት አንብቦ መረዳት ውህድአሃድ የያዘውን መልዕክት በአግባቡ መርምሮ መገንዘብ የሚለውን ፅንሰ ሃሳብ
የሚያመለክት ነው፡፡ አንብቦ መረዳት ማለት በተቻለ መጠን በጽሁፉ ውስጥ ያለውን መረጃ በአግባቡ መገንዘብ መቻል
ማለት ነው፡፡ እንደፓንግና ሌሎች(2003) የምናነበው ነገር ማስታወቂያ፣ የጋዜጣ ርዕስ አንቀፅ፣ የሳይንሳዊ ጆርናል
መጣጥፍ ወዘተ.ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም አንድን ማስታወቂያ ማንበብና አንድን የሳይንስ ጆርናል መጣጥፍ ማንበብ
አላማው ይለያያል፡፡ይሁን እንጅ አንደ አላማው መለያየት ሁሉንም በተገቢው መንገድ አንብቦ ውጤታማ መረጃ ማግኘት
ወይም ግንዛቤ መውሰድ መቻል አንብቦ መረዳት ነው፡፡ ሌላው ከዚህ ጋር የምናየው አንደኛው ነገር ውጤታማ አንባቢ
በፍጥነት በማንበብ በአሀዱ ውስጥ ያለውን ጠቃሚውንና የማይጠቅመውን መረጃ ይለያል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ፣
ጠቃሚውን መለየት ብቻ በራሱ በቂ ስላልሆነ በጥልቀት ገብቶ በመመርመር ትልቅ ግንዛቤ ይወስዳል፡፡ ይህም አንብቦ
መረዳት ይባላል፤ በማለት ይገልፃሉ፡፡ አንቶኒና ሌሎች (2004) ማሶን(1984)ን ጠቅሰው እንደሚያስረዱት አንብቦ
መረዳት የአንባቢው በቴክስት መልክ የቀረበ መረጃን ከቀደመ እውቀቱ ጋር ውጤታማና ትርጉም አዘል በሆነ መልኩ
የማቀናጀት ችሎታ ነው፡፡ ኮንልን (1990) ጠቅሰው አንቶኒና ሌሎች (2004) እንደሚያሰረዱት አንብቦ መረዳት ቃላዊ
ከሆነ ክሂል በተፃራሪ መልኩ የቃላቱን ትርጉም የመረዳት፣ ከዳራዊ እውቀትና ተማሪው ከተማረው ትምህርት ጋር
የማያያዝ አይነት በርካታ ችሎታዎች ይጠይቃል፡፡ ጃኔትና ቤቲ (1988) ስፒሮ(1980)ን ጠቅሰው እንደሚገልፁት አንብቦ
መረዳት አንባቢው ያገኘውን አዲስ መረጃ በውስጡ ካለው ዳራዊ እውቀት ጋር እንዲያስተሳሰር የሚያግዘው ገንቢ
ተግባር ነው ተግባሩን እንዲያከናውን የሚያስችለው ደግሞ የማንበብ ልምዱ ነው፡፡ በአንብቦ መረዳት ሂደት የቃላት
ትርጉም እውቀት አረፍተ ነገርና የቴክስት መዋቅር እውቀት እንዲሁም የህይዎት ልምድ (ዳራዊ እውቀት) የየራሳቸው
አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ ዋግነር፣ መሴና ታነንቡዋ (2007) እንደሚያሰረዱትም አንብቦ መረዳት አንድ ሰው የሚያነበውን
ፅሁፍ የመተርጎምና የመረዳት ችሎታ ውጤት ነው፡፡ እንደፓንግና ሌሎች (2003) የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት
ችሎታ ተማሪዎች አካባቢያቸውን በሚገባ እንዲያውቁና ቀጣይ እድላቸውን እንዲተነብዪ በር ይከፍትላቸዋል፡፡ ከዚህም
በተጨማሪ አዲስ እውቀት እንዲገበዩ፣ በሰነፅሁፍ ራሳቸውን እንዲያዝናኑና ከዘመናዊው ሕይዎት ጋር የተያያዙ የእለት
ከእለት ተግባራትን በልበ ሙሉነት እንዲፈፅሙ ያስችላቸዋል፡፡ ባለሙያዎቹ እንደሚያስረዱት ማንበብ በፁሁፍ የቀረበን
አሀድ መረዳት ነው፡፡ የማንበብ ኪሂል ውስጣዊ ግንዛቤን እና እሳቤን የሚጠይቅ ውስብስብ ተግባር ነው፡፡ ኪሂሉ ሁለት
የተያያዙ ሂደቶችን ቃላትን መለየትንና መረዳትን ያካትታል፡፡ቃላትን መለየት የሚባለው የፅሁፉ ወኪል የሆኑ ቃላት
እንዴት ከንግግር ቋንቋ ጋር እንደሚገናኙ መለየት ሂደት ሲሆን ቃላትን መረዳት ደግሞ ቃላቱ ስሜት እንዲሰጡ የማድረግ
ሂደት ነው ይህ ደግሞ በዳበረ የማንበብ ልምድ ተግባራዊ የሚደረግ ነው፡፡ አልደርሰን ናፒርሶንን (1988) ጠቅሶ ኮንለይ
(1992) እንደሚያብራሩት የማንበብ ልምድ አንብቦ ለመረዳት የተለያዩ ቅድመ እውቀቶች ከአዲሱ ንባብ ጋር
የሚዋሃዱበትን ሂደት የሚያፋጥን ነው፡፡ ይኸውም የተማሪው ቅድመ ዕውቀት፣የሚነበበው ነገር ዕውቀት (የርዕሰ ጉዳዩ
ዕውቀት)፣ ለቋንቋው ያለው ቀረቤታ፣ ስለርዕሰ ጉዳዩ ያለው አስተሳሰብና የሚነበበው ፅንሰ ሐሳብ አንድ ላይ
የሚገናኙበትን ሂደት ተግባራዊ ለማድረግ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በተጨማሪም በማንበብ ልምድ የዳበረ አንብቦ የመረዳት
ችሎታ በርካታ ክሂሎችንና ዕውቀቶችን ባንድ ላይ በማዋሃድ አንድን ጹሁፍ ለመገንዘብም እንደሚያስችል ይገልጻሉ፡፡
በተመሳሳይ ሂትልማን(1988) ሲገልፁ፤ በንባብ ጊዜ መረዳት የሚባለው በአውድ ውስጥ ያሉትንና ከአውድ ውጭ ያሉትን
ተላውጦች መሰረት አድርጎ የቃላትንና የአርፍተ ነገርን ሃሳብ መገንዘብ መቻል ሲሆን፣ የሚነበበውን ቴክስት ፅንሰ ሐሳብ
ለማደራጀት፣ ለመተርጎምና ለማጠቃለል ልምድ ከፈተኛ ሚና አለው፡፡ በተጨማሪም አንብቦ መረዳት፣ ተማሪዎች
የሚያነቡትን ጽሁፍ ካላቸው ዕውቀትና ልምድ ጋር በማስተሳሰር በማደራጀት፣ በመተርጎምና በማጠቃለል እንዲሁም
ከደራሲው ሃሳብ ጋር በማዋሃድ የራሳቸውን ግላዊ ግንዘቤ የሚያጠናክሩበት(የሚፈጥሩበት) ክሂል ነው፡፡ ቢችና
ኮል(1987)፣ ሆሪባ(1996) እና ሻንግ (2000) በአጠቃላይ እንደሚስማሙበት አንብቦ መረዳት አንዱ ከሌላውጋር
የተዛመዱና ደረጃቸውን የጠበቁ በዙ አዕምሯታዊ ሂደቶች(multiple cognitive processes) ይካተቱበታል፡፡ ምሁራን
ይህንን ሃሳብ ሲያረጋግጡ አንብቦ መረዳት መረጃን በተለያየ መንገድ ማቀነባበርና መረዳት ይፈልጋል፡፡ ይህ መረጃን
የማቀነባበር ሂደት በአንባቢው የቀደመ የማንበብ ልምድ እያንዳንዱን ቃል ከመረዳት ጀምሮ በአንባቢው ዳራዊ እውቀት
መሰረት አወድፍችተኮር(ከምናነበው ፀሁፍ) ወይም አውድፍች ተኮር ያልሆነ(ከቅድመ ዕውቀታችን) ስርፀተ ሃሰብ
ተጠቅሞ አስከ መተርጎም የሚደርስ ሂደት በውስጡ ያካትታል፡፡ ስለዚህ በማንበብ ልምዳችን የታገዘ አንብቦ መረዳት
የተሰጠንን ጹሁፍ በማንበብ በግልፅ የቀረበውንና ያልቀረበውን መረጃ መረዳት የሚያስችል ነው በማለት ያብራራሉ፡፡
ይሁን እንጅ እንደሻንግ(2000) ገለጻየ ተወሰኑ ትምህርት ቤቶች አንብቦ መረዳትን የማስተማር የምንባቡ ላዕላይ መዋቅር
ላይ ብቻ ላይ የተመሰረተና ልምድን የዘነጋ በመሆኑ፣ አንባቢው ግልብ በሆነ መልኩ የጹሁፉን ላዕላይ ትርጉም ከማንበብ
በሰተቀር በደራሲው ወይም በጻሐፊው ሐሳብ ላይ የመመራመርና ከልምዱ ጋር የማስተሳሰር ክፍተት ይታይበታል፡፡
ይህም ልምዱን መሰረት አድረጎ በፅሁፉ ውስጥ ሊተላለፉ የተፈለጉትን ቀጥተኛና ተጓዳኝ መልዕከቶች የመተርጎም ስራ
ላይ ትኩረት አይሰጡም፡፡ በተለይእንደኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የተማሪዎች የንባብ ልምዳቸውን ተጠቅሞ አንብቦ
መረዳትን የመማር ችግር መኖሩን አስረስ (2008) በጥናታቸው ጠቁመዋል፡፡ ተማሪዎች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን
የሚያጠናቅቁት የማንበብ ልምዳቸው ዝቅተኛ ሆኖና በክፍል ደረጃቸው ሰለንባብ የሚገባቸውን ያህል እውቀት ሰይዙ
በክፍል ደረጃቸው የቀረበውን ምንባብ ሀሳብ ለመረዳት፣ ለመተርጎምና ፀሀፊው ሊያስተላልፍ የፈለገውን ሀሳብ
ለመረዳት ተቸግረው እንደሆነ የአገር ውስጥ ጥናቶች (ለምሳሌ፣ ገደፈው፣ 1993፤ ሀሰን፣2004) ጠቁመዋል፡፡ እንደናታል
(1982) የተማሪዎችን የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታን ለመገምገም(ለመፈተን) የችሎታው
መገለጫዎችን በተለይም የንባብ ፍጥነትን በሚከተለውመንገድ መለካት ይቻላል፡፡ ፍጥነታቸውን ስንለካ የምንመርጠው
ምንባብ ለተማሪዎች እንግዳ የሆነና አስቸጋሪ መሆን የለበትም፤በመቀጠልም የተመረጠው ምንባብ የያዘውን የቃላት
ቁጥር መቁጠር፤ አስከትሎም ለእያንዳንዱ ተማሪ የምንባቡን አንዳንድ ቅጅ ማዘጋጀት፤ ቀጥሎም ምንባቡ ምንም
ግድፈት የሌለውና በግልፅ የሚነበብ መሆኑን ማረጋገጥ፤ ከዚህ በኋላ ለተማሪዎች በራሳቸው ችሎታና አቅም እንዲያነቡ
ገለፃ ማድረግ፤ የማታለል ስራ እንዳይሰሩ በግልፅ መንገርና፤በመጨረሻም የንባቡን አተገባበር በሚከተለው መልኩ
ማደራጀት ያስፈልጋል፡፡ የተማሪዎችን አንብቦ መረዳት ለመለካት የተለያዩ የጥያቄ አይነቶችን በማዘጋጀት መለካት
ይቻላል፡፡ አንብቦ መረዳትን ለመለካት የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች ሲዘጋጁ ለተማሪው በቀላሉ የሚረዱና የተለያዩ
አይነት መሆን አለባቸው፡፡ ጥያቄዎችም ከተዘጋጀው ጽሁፍ ጋር ጥበቅ ዝምድና ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡ ይህ ትልቅ
ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ጥያቄው ሲዘጋጅ የደራሲው አመለካከት፣ትኩረትና ድምፀት ሙሉ
ግንዛቤ ሊሰጠው ይገባል፡፡ ጥያቄውም በሚከተሉት አይነቶች ማለትም በክፍት ጥያቄዎች፣ በምርጫ፣ በእውነት ሐሰት፣
ወዘተ. ሊዘጋጅ ይችላል፡፡ በሌላ መልኩም ጽሁፋዊ ያልሆኑ አጠያየቆችም መጠየቅ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ካርታዎችን
ማገናኘት፣ ፎቶግራፎችን ማዛመድና በአንቀፅ (ከተለያየ ፅሁፍ ላይ የተወሰዱ ፅሁፎችን በታትኖ በመስጠት እንዲያገናኙ
በማድረግ) ሊዘጋጅ ይችላል (ጋርሌት፣1996)፡፡
የአጠናን ዘዴ
3.3.2 ፈተና
ሁለተኛው የመረጃ መሰብሰቢያ አንብቦ የመረዳት ፈተና ነው፡፡ ፈተናው አጥኝዋ ለተመረጡ ተጠኝ ተማሪዎች
አንብቦ የመረዳት ፈተና አዘጋጅታለች፡፡ ለአንብቦ መረዳት ፈተና የሚያገለገሉ ምንባቦች ሂተን (1990) እና
ማድሰን(1983) ከተማሪዎች ማህበረ ባህላዊ አውድ ጋር የሚጣጣም ይዘት ያላቸው፣ የደራሲውን አመለካከት ከራሳቸው
እንዲያወዳድሩ የሚያግዝ፣ አንድን ጉዳይ በጥልቀት ለመመርመር እንዲነሳሱ የሚገፋፋ፣ የድምር ሀሳቦችን ፍጻሜ
ለማዎቅ የሚያጓጉ (ለምሳሌ፣ ከልቦለዶች ጋር የተቀነጨቡ)፣ ከእውቀት አድማሳቸውጋር የሚጣጣም ይዘት ያላቸው፣
ለየደረጃው የሚመጥኑ የተወሰኑ እንግዳ ቃላት ያካተቱና ፍቻቸውንም ከአውድ ለመገመት የሚያስችሉና መሆን
አለባቸው፤ በሚሉት መሰረት የተዘጋጀ ነው፡፡ በተጨማሪ ማረው (1998) እንደሚገልጹት ከንበብ በኋላ የሚጠየቁ
ጥያቄዎች የተማሪዎችን ግንዛቤ ለመረዳት የሚረዱ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለምሰሌ፣ ተማሪዎች ያላቸውን ክፍተት
ለመሙላት፣ ያነበቡትን ለማጠቃለል፣ ያነበቡትን አዲስ መረጃ ከነበራቸው እውቀት ጋር ለማዛመድ የሚያስችሉ፣
ምክኒያታቸውን የሚገልፁበት፣ የንባቦችን ይዘት የሚተነትኑበት፣ ትርጉምና ማጠቃለያ የሚሰጡበት፣ ሊሆኑ ይገባል፤
ያሉትንና ናታል (1996) እና ማድሰን (1983) የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች በማዛመድ፣ ትንበያ እንዲሰጡ በማድረግ፣
በአጭር መልስ ስጥ፣ በፃፍ፣ በክፍት ቦታ ሙላ መጠየቅ እንደሚቻል የሚያሰረዱትን ግምት ውሰጥ በማሰገባት ሁለት
ምንባቦችን በመጠቀም ፈተና ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ሆኗል የመጀመሪያው ምንባብ ከሲሳይ ንጉሱ (1999፣1-2) ሲዎሰድ
ሁለተኛው ምንባብ ከከበደ ሚካኤል (ዓ.ም ያልተጠቀሰ፣ 23-25) ተወስዷል፡፡ በመጀመሪያው ምንባብ ከተካተቱት ሀያ
ሁለት ጥያቄዎች አስራ ሁለቱ የባለብዙ ምርጫ ጥያቄዎች፣ አምስቱ የአዛምድ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ ሁሉም መልስ
አስመራጭ እንዲሆኑ የተደረገበት ምክንያትም ለአስተማማኝነት ትከረት ለመስጠት ነው፡፡ በተጨማረሪም በአብዛኛው
ተማሪዎች የለመዷቸው በመሆናቸው አስቸጋሪ ሁኔታን ሰለማይፈጥሩባቸው ነው፡፡ እንዲሁም ሂተን (1990) እና
ማድሰን (1983) ባለብዙ ምርጫ ጥያቄዎች በበርካታ ተፈታኞች ዘንድ በማንኛውም የክፍል ደረጃ የሚመረጡና
የሚሰሩባቸው ከመሆኑ ባሻገር በተለያየ መንገድ ከምንባቡ ውስጥ በተካተቱ ቃላት አንብቦ የመረዳት ችሎታቸውን
ለመለካት የተሻሉ መሆናቸውን ሰለሚመሰክሩ ነው፡፡ ሁለተኛው ምንባብ ደግሞ ስምንት ጥያቄዎችን የያዘ ነው
በአንቀፅ(ምንባቡ) ውስጥ ገብተው የተሟላ ትርጓሜ የሚሰጡ አማራጮች ቀድመው ተካተዋል፡፡ እነዚህ አማራጮች
በምንባቡ ውስጥ በቁጥር በተወከሉት ቦታዎች እንዲያስገቡ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡ ይህ የፈተና ክፍል ተማሪዎች
አጠቃላይ የምንባቡን ሀሳብ እንዲተነብዩ ብሎም በቅርብና በሩቅ አውድ በመታገዝ መልሱን እንዲገምቱ የማድረግ ብቃቱ
ከፍተኛ ነው፡፡ እያንዳንዱ መልስ በቅርብና በሩቅ አውድ የታገዘ በመሆኑ በጥንቃቄ አንብቦ የተረዳን ተማሪ ለመለየት
ያስችላል፡፡ ሂተን (1990) እና ማድሰን (1983) ዝግ ጥያቄዎች ተማሪዎች ከግላቸው ሰሜት ተነሳስተው በትክክል
እንዲመልሱ የሚደረግበት ሂደት ሳይሆን ቃላቱ ወይም ሀረጋቱ የሚተውት ሰልታዊ በሆነ መንገድ ነው፡፡ ተማሪዎች
በስልት ታግዘው እንዲንደረደሩ ይረዳቸዋል፤ በሚሉት መሰረት የተዘጋጀ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ሁለቱም ምንባቦች ከተዘጋጁ
በኋላ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሚያሰተምሩና ለጥናቱ በተመረጠው
የክፍል ደረጃ በሚያሰተምሩ የቋንቋ መምህራን ተገምግሞና አስተያየታቸው ተካቶ የጥያቄዎችን አመላለስ
የሚያመለክት መመሪያ ታክሎበት ፈተናው በጥናቱ ሌላ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሚማሩ የዘጠነኛ ክፍል
ተማሪዎች የሙከራ ጥናት ተካሂዷል፡፡ አስተማማኝነቱም በክሮንባህ አልፍ (cronbach alpha) ቀመር ተሰልቶ የተገኘው
ወጤት 0.74 ሆኗል፡፡ በሙከራ ጥናቱ የፈተናው አስተማማኝነት በመረጋገጡ ለዋናው ጥናት ፈተናው በተጠኝዎች ቁጥር
ልክ ተባዝቶና ለተማሪዎች ኮድ ተሰጥቶ የመረጃዎችን አስተማማኝነት ለመጠበቅ በአንድ ትልቀ አዳራሽ በሶስት
የአማርኛ ቋንቋ መምህራን ተራርቀው በአንድ ጠረጵዛና ወንበር አንድ ተማሪ በማሰቀመጥ ፈተናውን እንዲሰሩ
ተደርጓል፡፡ ለፈተና የተሰጠው ሰአት ሲያልቅ የፈተና ወረቀቶቹ በአጥኝዋና በረዳቶቿ ተሰብስበዋል፡፡
ምዕራፍ አራት
የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የማንበብ ልምድና አንብቦ መረዳት ችሎታ
መካከል ያለውን ተዛምዶ መመርመር ነበር፡፡ ለዚህም እንዲረዳ በፅሁፍ መጠይቅና በፈተና አማካይነት የተማሪዎች
የማንበብ ልምድና የአንብቦ መረዳት ችሎታ ውጤት በመረጃነት ተሰብስቧል፡፡ በዚህ ምዕራፍ በፅሁፍ መጠይቅና በፈተና
የተገኙትን መረጃዎች መሠረት በማድረግ የጥናቱ ውጤት ትንተናና ማብራሪያ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ምዕራፍ አምስት
ማጠቃለያ
5.1 የጥናቱ ዐቢይ አላማ
የጥናቱ ዐቢይ አላማ በተማሪዎች የማንበብ ልምድና የአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ያለውን ተዛምዶ
መመርመር ነበር፡፡ በዚህ መሰረትምበጥናቱ በቀዳሚነት መልስ እንዲገኝባቸው የተነሱት መሰረታዊጥያቄዎች
የሚከተሉት ነበሩ፡፡
የጥናቱን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ እንዲቻልም የፅሁፍ መጠይቅና ፈተና ለመረጃ መሰብበሰቢያነት
ውለዋል፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎችም በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ በዳባት አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
በ 2010 ዓ.ም በዘጠነኛ ክፍል ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ያሉ ተማሪዎች ናቸው፡፡ በዚህ የክፍል ደረጃ ከሚማሩ
(ወንድ =56፣ ሴት =60) ተማሪዎች መካከል በእድል ሰጭ የንሙና ዘዴ የተመረጡ 116 ተማሪዎች የጥናቱ ተሳታፊዎች
ሆነዋል፡፡ የጥናቱ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ የፅሁፍ መጠይቅ ሲሆን፣ የተማሪዎቹ የአንብቦ መረዳት ችሎታ ውጤትም
በፈተና አማካይነት ተሰብስቧል፡፡ በፅሁፍ መጠይቁና በአንብቦ መረዳት ፈተና የተሰበሰቡት መረጃዎች ገላጭና ተንባይ
ስታትስቲካዊ የቅመራ ዘዴዎችን በመጠቀም ተተንትነዋል፡፡ በውጤት ትንተናው መሰረትም የተማሪዎችን የማንበብ
ልምድና የአንብቦ መረዳት ችሎታ ተዛምዶን ለማየት ተሞክሯል፡፡ በዚህም የተማሪዎች የማንበብ ልምድ ከአንብቦ
መረዳት ችሎታ ጋር ጉልህ አዎንታዊ ተዛምዶ እንዳላቸው የጥናቱ ውጤት አመልክቷል፡፡
የተማሪዎች የማንበብ ልምድ አንብቦ የመረዳት ችሎታቸውን መተንበይ አለመተንበዩን መመርመር ሲሆን፣
ለዚህም ትንተና ይረዳ ዘንድ የድህረት ትንተና ተከናውኗል፡፡ ውጤቱም የማንበብ ልምድ የአንብቦ መረዳት ችሎታን
በማጎልበት ረገድ ጉልህ ድርሻ መኖሩን አሳይቷል፡፡ ይህም ማለት የማንበብ ልምድ ከዳበረ የአንብቦ መረዳት ችሎታቸውን
በጉልህ ደረጃ ይተነብያል፡፡ የማንበብ ልምድ አንብቦ መረዳት ችሎታን የቀጥታ ተጽእኖ በቤታ ቀመር(beta coefficient)
ሲለካ ከፍተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ይህም የሚያሳየዉ የማንበብ ሲጨምር አንብቦ የመረዳት ችሎታ አብሮ ይጨምራል፡፡
በተማሪዎች የማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ ያለውን ልዩነት ለመፈተሸ
ተሞክሯል፡፡ በሴትና በወንድ ተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ በመረዳት ችሎታ መካከል ልዩነት እንደሌለ የውጤት
ትንተናው አሳይቷል፡፡ በመሆኑም በማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታቸው መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ
ተመሳሳይ መሆኑ ውጤቱ አሳይቷል፡፡
5.2 መደምደሚያ
የጥናቱን ውጤትና ማብራሪያ መሰረት በማድረግ ከሚከተሉት መደምደሚዎች ላይ ተደርሷል፡፡
1. በተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ በመረዳት ችሎታ መካከል ጉልህ ዝምድና አለ፡ 2.
የተማሪዎች የማንበብ ልምድ አንብቦ የመረዳት ችሎታቸውን በጉልህ ይተነብያል፡፡ ይህም የማንበብ ልምዳቸው
ሲጨምር አንብቦ የመረዳት ችሎታቸውም በተመሳሳይ ይጨምራል፡፡ የተማሪዎች የማንበብ ልምድ ከዳበረ አንብቦ
የመረዳት ችሎታቸውን ውጤት በጉልህ ደረጃ ስለሚጨምር፣ የማንበብ ልምድ የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታ
ይተነብያል፡፡ 3. ፆታ በማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ ምንም ልዩነት የለውም፡፡ ወይም
በሴትና በወንድ ተማሪዎች መካከል ያለው የማንበብ ልምድ ተመሳሳይ ነው፤ የሚል አንድምታ አለው፡፡
1. መምህራን በተማሪዎች የማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታቸው መካከል ዝምድና መኖሩን ተገንዝበው
የበለጠ የተማሪዎችን የማንበብ ልምድ የሚያዳብሩ የትምህርት ዘዴዎችን ተጠቅመው የቋንቋ ትምህርቱን ቢሰጡ
በጥናቱ ውጤት የታየው አበረታች የተማሪዎች ማንበብ ልምድ የበለጠ ሊዳብር ይችላል፡፡
2. ሁሉም ባለድርሻ አካላት በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የማንበብ ልምድና አንብቦ መረዳት ላይ ትኩረት አድረገው ቢሰሩ
በተማሪዎች የማንበብ ልምድና አንብቦ መረደት ላይ የሚታየውን አበረታች ለውጥ ማሳደግ ይቻላል፡፡
3. የስርዓተትምህርት ቀራጮች፣ ተመራማሪዎች፣ የትምህርት ፖሊሲና ዕቅድ አውጭዎች የአንብቦ መረዳትን
ትምህርት መርሀግብር ሲያዘጋጁ የተማሪዎችን የማንበብ ልምድ የሚያዳብሩ የተለያዩ ስልቶችን ተጠቅመው የበለጠ
ልምዱን ለማሳደግ ቢሰሩ፡፡ የሚሉት በአጥኝዋ የቀረቡ የመፍትሄ ሀሳቦች ናቸው፡፡
4. በጥናቱ በማንበብ ልምድና በአንብቦ መረዳት ችሎታ መካከል ያለው ተዛምዶ በፆታ ልዩነት አላሳየም፡፡ መምህራን
ይህን ከግምት በማስገባት ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ተማሪዎች በአንብቦ መረዳት ችሎታቸው ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ፤
የማንበብ ልምዳቸውን ሊያዳብሩ በሚችሉ ልዩ ልዩ ክበቦች (ለምሳሌ፣ በቤተመፅሐፍት፣ የስነጽሁፍ ክበባት) ቢሳተፉ፡፡
5. የትምህርት ባለሙያዎች በጥናቱ ግኝቶች መረጃ መሠረት የተማሪዎችን የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ
በመገንዘብ መምህራን የትምህርት ዕቅድ፣ መርሐ ትምህርትና የንባብ ትምህርት መርሐግብር ሲያዘጋጁ የተማሪዎቹን
የማንበብ ልምድና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ከማጎልበት አንፃር እንዲመለከቱት ቢጠቁሙ፡፡
6. በርዕሱ ዙሪያ ተጨማሪ ጥናት የሚያደርጉ ተመራማሪዎች ይህንን ጥናት እንደመነሻ በማድረግ ከዚህ የተሻለ ጥናት
ለማካሄድ ጥረት ቢያደርጉ፤ የሚሉት በአጥኝዋ የቀረቡ የመፍትሄ ሐሳቦች ናቸው፡፡
ዋቢዎች
በህርዳር ከተማ በፋሲሎ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ 10 ኛ ክፍልተማሪዎች የማንበብ አመለካከትና
የአንብቦ መረዳት ችሎታ ተዛምዶ፡፡
ለ 2 ኛ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ጽሁፍ ባህርዳር ዩኒበርስቲ (ያልታተመ) ሀይማኖት ደመላሽ (2005)፡፡
የቃላት እውቀት ችሎታና አንብቦ መረዳት ውጤት ተዛምዶ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለድህረ ምረቃ የቀረበ ያልታተመ
መሐመድ ዓሊ (1992 )፡፡
‘‘በባሕርዳር ከተማ የግዩን ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ 10 ኛ ክፍል ተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋን ለመማር
ያላቸው አመለካከት፡፡''
ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ፣ ባሕርዳር ዩኒቨርስቲ፡፡ (ያልታተመ)፡፡ መሐመድ ዓሊ፡፡ (1992 ዓ.ም)፡፡
‘‘በባሕር ዳር ከተማ የግዩን ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ 10 ኛ ክፍል ተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋን ለመማር
ያላቸው አመለካከት፡፡'' ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ፣ ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ፡፡ (ያልታተመ)፡፡ መስፍን
ኃብተማሪያም(2001)፡፡
ኤማይ ፕሪንተርስ ኃ.የተ.የግ.ማ፡፡ አዲስ አበባ፡፡ማረው ዓለሙ (1998)፡፡ የአማርኛ ቋንቋ ማሰተማሪያ ዘዴ፡፡ አዲስአበባ፤
ንግድ ማተሚያ ቤት፡፡
የተማሪዎች የስብዕና አይነትና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ተዛምዶ፤ ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ፣ ባሕርዳር
ዩኒቨርስቲ፡፡ (ያልታተመ) ፡፡ በድሉ ዋቅጅራ (1988)፡፡
ተሳታፊነት፣ ጭምትነት፣ ስብዕና አይነት ከድርሰት መጻፍከ አንብቦ መረዳት ችሎታ ጋር ያለው ተዛምዶ፡፡ አዲስ አበባ
ዩኒቨርሲቲ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ቤት አዲስአበባ፣ ያልታተመ፡፡ ታዛሽ ሰይፉ (1992 ዓ.ም)፡፡
የ 11 ኛ ክፍል ተማሪዎች የአንብቦ መረዳትችሎታ፡፡'' ለመጀመሪያ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ፣ ባሕርዳር ዩኒቨርስቲ፡፡
(ያልታተመ)፡፡ ታፈረ ወርቁ (2000)፡፡
በዳንግላ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ 9 ኛ ክፍልተማሪዎች የንባብ ዳራና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ተዛምዶ፡፡
ለሁለተኛ ድግሪ ማሟያ የቀረበ ፅሁፍ፣ ባህርዳር ዩንቨርሲቲ (ያልታተመ)፡፡ያለው እንግዳወርቅ (1998)፡፡
የ 10 ኛ ክፍል የአማርኛ መማሪያ መጽሀፍ ውስጥ የሚገኙምንባቦች የተማሪዎችን የማንበብ ፍላጎት ለመያዝ ያላቸው
ብቃት፡፡ለመጀመሪያ ዲግሪ ማሟያ የቀረበ ጽሁፍ፡፡ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ (ያልታተመ) ገደፈው አምሳሉ (1993)፡፡
የ 11 ኛ ክፍል ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን ለመማር ያላቸው ተነሳሽነትና የትምህርት ውጤት ተዛምዶ፡፡ ባህርዳር
ዩኒበርስቲ (ያልታተመ)፡
Abu-Rabia, S. (1996). Attitudes and cultural background and their relationship to reading comprehension
in a second language: a comparison of three different social contexts.
1996.tb00090.x Aebersold, J.A., and Field, M.A. (1997). From Reader to Reading Teacher: Issues and
strategies for second language classrooms.Cambridge Universty Press.
Alexander, J.E., and Filler, R.C. (1976). Attitudes and Reading. Newark., DE. International Reading
Association.
Ambrusster, B.B. Anderson. T.H. And Osterag.j.(1987) Dase Test Structral Sammarization Institution
Facilitate learning from Exposi Tory Text? ReadingResearch Quarterly.22.331.346.
Anderson, N.J. (2003). Metacognitive reading strategies increase L2 performance. The Language Teacher
Online, 27(7).
Anderson, V. (1992).A teacher development project in Transactional Strategy Instruction for teachers of
severely reading-disabled adolescents.Teaching and Teacher Education,8, 391-403.
Appllegate, A.J. and Appllegate, M.D. (2004). The Peter Effect: Reading Habits and Attitudes of
Preservice Teachers. The Reading teacher, 57, 554-563.
Appllegate, A.j.and Appllegate, M.D. (2004). The peter effect Reading Habits and Attitudes of preservice
Teachers.The Reading Teachers the Reading Teacher, (57). 554_563.
Bas, G. (2012). Correlation between elementary students’ reading attitudes and their writing dispositions.
IJGE: International Journal of Global Education - 2012, volume 1 issue 2. Konya University.Graduate
School of Education Sciences. Konya, Turkey
Bas, G (2012). Coreiation between.elementry studntes reading attitude and their writing dispositions.
IJGE; International Jornal of Giobal of Global Education Science.Konya, Jurkey.
Basir, I. Mattoo, N.H. (2012) A study on study Habits and AcademicPerformance among Adolescent (14-
19) year. International Journal of social Sciencetomorrow. Vol.1, No.5, pp.1-5.
Benjamin, p(ed.) (2010). “Ethiopian Elementry Scool Grad Reding assessment” Data Ll Task
Number7.Publication USAID/ETHIOPA.
Blackb, A. (2006) << Attitudes to Readnge: An Inyestigation across the Primary years.>>this Master of
education. School of Education, Australlan CatholicUniversty.
Block, C.C. (1997), Teaching the Language Arits: Expanding Thinking Through student Centerd
Instruction, Boston Allyn and Bacon.
Bloom, B.S.(ed.) (1963). Taxonomy of Educatinal Objecitve: The Classification of Educational Goals.
New York Longman, Green and co.
Doi: 10.1111/j.1467-9817.2008. 00369.x Burns, p.c. (1984) Teaching) Reading in Todays Elementary
school Boston: Houghton, Mifflin company.
Kothar C.R. (2004) Resarch MItedologe-Methdes and Techiques Former Principals, College of
commerce University of Raiasthan, jaipur (india).
Christina, (2011).young people Reading and Writing: An-Depth study Focusingon Enjoyment, Behavior,
Attitudes and Attaimhent.2011-00-00.
Christina, C. and Jonathan D. (2011). Young People's Reading and Writing: An In-Depth Study Focusing
on Enjoyment, Behavior, Attitudes and Attainment. 2011-00-00.
Conely, m.w. (1992). Content Reading Instruction: A communicative Approach. New York:
Cramer, M. (1994). Fosternig the Love of reading: The Affective Domain in Reading Education (PP.74-
87). Newyork, DE: International reading Association.
Day, R and Bamford. (1998), Eytensive Reading in the second language Classroom U.S.A.:
Day, R. and Bamford. (1998). Extensive Readng and in The Second Language Classroom. U.S.A:
Cambridge Universty Press.
Dishiner.E.K. et.al.(1980) Readinge Strategies and practice: Guide for Improving Instruction.
Dubin, B.V, and Zorkaia, N.A (2010). The changes in the attitude of Russia's Reading public interms of
frequency and intensiveness. Russian Education and Society, v52n7 P16-51 Jul. 2010.
Eiser, J. R., (1994). Social Psychology.Attitudes, cognition and social behavior. Cambridge University
Press.
Estes, T. H. (1971). A Scale to Measure Attitudes Toward Reading. Journal of reading. 15, 135-138.
Evans, K.M., (1965). Attitudes and Interests in Education. Routlege and Kegan private limited.
Flood J., and Lapp, D., (1983). Teaching Reading to Every Child (2ed ed). Macmillan Publishing Co.,
Inc.
Frankel, J.R., and Wallen.(2000). How to design and Evaluate Research in education. (4th Ed).Mcgraw
Hill. Gambrell, l.B., (1996). Creating Classroom cuitures that Foster ReadingMotivation, the Reading
Teachers 50,14.25.
Gambrell, L.B., (1996). Creating Classroom Cultures That Foster Reading Motivation. The Reading
Teacher, 50, 14-25.
Graves, MF., Laberge, M.J.and Cooke c. (1983). Efects of previeng difficults short Stories on low ability
junior higy school students Compration, realland Attitudes,18(3), Greaney, V. and Hegarty, M. (1987).
Correlates of leisure-time reading. Journal of Research in Reading, 10: 3–20. Doi: 10.1111/j.1467-9817.
1987.tb00278.x Greene, B. (2001) “Testing Reading Comprehension of Theoretical Discourse with
Close” Journal of Research in Reading. Owusu-Acheaw, Micheal, ‘’Reading Habits Among Students and
its Effect On Academic Performance A study of students.
Heatan, J.B. (1990) writing English anguge Tests, Landon: Long man Heathington, B.S. and Alexander,
J.E. (1984). Do Classroom Teachers Emphasize Attitudes Toward Reading? The Reading Teacher, 37,
484-488.
Heilman, A.W. Blair, T.R., and Ruphley W.H. (1998). Principles and Practices of Teacing Reading.(9th
Ed.). New Jersy prints Hall Inc.
Hittle man, D.R. (1988) Developmntal Reading.k-8; Teaching from a Whole Language Prespective.
Columbus: Merrill publishing company.
http://digital commons.unl.edu/libphilpral/1130.
Issa. A. O., Aliyu, M. B., Akangbel, R.B.& Adedeji, A.F. (2012) Reading Interest and Habits of the
Federal Polytechnic Students, International of Learninge & Development.vol.2, No.1.pp 470-486.
Kulik, A.J. and Kulik C.C. (1982). Effects of Ability Grouping on Secondary School Students: A Meta-
analysis of Evaluation Findings.American Educational Research Journalaer.sagepub.com. Doi:
10.3102/00028312019003415. Am Educ Res J September 21, 1982 vol. 19 no. 3 415-428 University of
Michigan.
Kush, J.C, and Watkins, M.W. (1996). Long –Term Stability of Children's Attitudes Toward Reading.
[Eelectronic Version]. The Journal of Educational Reserch.
Lena S.and, Karin T. ( 2007). Influences of Family Based Prerequisites, Reading Attitudes, and Self-
Regulation onReading Ability.Contemporary Educational Psychology, v32 n2 p206-230 Apr 2007
Journal of Atricles; Reports – Research.
Lenas.s.and T. (2007). Infiuences of family Based prerequisites, Reading Attitudes, and Self-Regulation
on Reading Ability. Contemporary Educational psychology,32 (2),206-230 JOrnal of Atricels; Reports-
Research.
Logna, S., and Johnston, R. (2009). Gender Differences in Reading Ability and Attitudes:
Examining where these differences Lie. Jornal of Research in Reading, V32 n2 P199-214 May 2009.
Lorene, W.C., (2010). ‘‘Secondary Students' Reading Attitudes and Achievement in a scaffold Silent
Reading Program Versus Traditional Sustained Silent Reading.’’ProQuest LLC, Ph.D. Dsessertaion,
Auburn University.
Lynn, H.W. (2010). Difference between third, forth, and fifth Grade students' attitudes to ward reading in
relation to community size. Master of education (MED), Bowling Green state Universty, reading 2010.
Martinez, R.S., Tolga, A.o, and Jermy, J. (2008). Influence of Reading Attitude on Reading Achievement:
A Test of the Temporal Interaction Model. Psychology in the schools, v45 n10 P1010-1022.Dec.2008.
May, B.F. (1990). Reading as Communication: An Interactive Approach. (3rd Ed.). U.S.A:
McCarthy, C. (1999). Reading theory as a microcosm of the four skills.The Internet TESL Journal, 5(5).
Mckenna, M.C., Kear, D.J., and Ellsworth, R.A., (1995). Children’s attitudes to woard reading.A national
survey.Reading research quarterly.Retrieved on 01/08/2011 09:59.From http:// WWW.jstor.Org
/stable/748205.
Muller, D.L., (1973). Teacher Attitude Towards reading.Journal of Reading. 17, 202-205.
Nancy, W. (1989).Developmental relationships between Students’ attitudes Toward reading and Reading
Achivement in Grades 1 through 8. Page 95, Education Specialist Thesis, Universty of Northen Iowa.
Norton, D.E. (1997). The Effective Teaching of Language Arts. (5th Ed.). New Jersy: Prentice Hall Inc.
Nunan, D. (1991). Language teaching methodology: A textbook for teachers. Prentice Hall Nuttall, c
(1982).Teaching Reading skill in foreign language London: Heinemann Educational Book Ltd.
Ormrod, J.E. (2008). Human learning.Fifth Edition. New Jersey: Upper Saddle River.
OWUSU-Achewa, Micheal<<Reading Habits Among Students and its Effecton Acadeic Performance:
AstudyOf Students of Konforidua poly technic>> /2014/. Library Philosophy and Practice (e-
Journal).paper 1130.
Palani, K.K. (2012) Promising Reading Habits and Creating Literate Social.International Reference
Research Journal.vol. (1) Issue2(1) pp1.
Roe, B.D., and Smith, S.H., (2005). Teaching reading in today's middle schools, Houghton Mifflin
Company.
Rrowell, G.C., (1972). An Investigation of Factors Related to Change in Attitude Toward Reading. 972-
73* Vol.5, No.4, Fall.
Sallabas, M.E., (2008). Relationship between 8th Grade Secondary School Students' Reading Attitudes
and Reading Comprehension skills. Journal of the Faculty of Education.V01, 9, Issue.16 (fall 2008).141-
155. Retrived on http://WWW.web. Inonu. Edu.tr/ efdergi/ sayi 16/08-Rn.pdf.
Schmitt, E. (2009). ‘‘Four Case studies: The reading Attituds and Practices of Teachers and students
Grade’’.Thesis, Master of Education in Reading, The graduate College of Bowling Green State Universty.
Sheng, H.S. (2000). ``Acognitive Model for Teaching Reading comprehension`` English Teaching
forum.Vol.38, No.4, October.
Spiegel, D.L. (1994). A Portrait of Parents of successful readers. In E.H. NewYork, DE:
Teremotit, J. (1995) ‘’Improving Junior College Reading Programs.’’ Theodore S.K. (2010). Reading
Achievement, Attitudes towards, Reading and Reading Self-Esteem of Historically Low Achieving
Students Journal of Instructional Psychology, v37 n2 p184-188 Jun 2010.Journal Articls; Reports –
Research.
Thraves, P., (2010). "An Investigation into Students' Reading Attitudes and Habits Using a Children's
Literature Intervention Programme" CPUT Thesis and Dissertations.Paper 296.
http://dk.cput.ac.za/td_cput/296 Tindale j.c. (2003) Assessing Reading.cambridge Unviersity Cambridge
university press.
Vacca, R.T. And Vacca, J.L., (1999). Content Area Reading Literacy and Learning across the
Curriculum. (6th Ed). Long Man.
Webb, H.L., (2009). The Relationship between African American Middle School Students' attitudes
toward Reading and their Reading Comprehension Level’’. Proquest LLC, Ed.D. Unpublished
Dissertation, the University of Memphis.
Wie (2006) Gender Difference in Reading Comprehension for Chinese Secondary School Students.
Aseminar Paper Resarch Retraved on 20-05-2012, fromhttp://mindsMaster of science in
education.unpublisher theis, the faculityUniversity of wis consin-piatteville.
Wie (Veronica) (2009). Gender Difference in Reading Comprehension for Chinese Secondary School
Students.A Seminar Paper Research.Master of Science in Education.Unpublished Thesis.The Graduate
Faculty Universty of Wisconsin-Platteville.
Wigfield, A., Guthrie, J. T., Tonks, S., & Perencevich, K. C. (2004). Children's motivation forreading:
Domain specificity and instructional influences. Journalof Educational Research, 97, 299-309.
Yaacov, P. (2010). A Meta- Analysis of the Relationship between Student Attitudes towards Reading and
Achievement in Reading. Journal of Research in Reading, v33 n4 P335-355 Nov 2010.
Zelalem Berhanu. (2010). The Reading Attitudes Preferences and Habits of First Year Bahir Dar
Universty Studentes with Particular Reference to The faculty of Humanities.Unpublished Master’s
Thesis. Humanities Faculty, Bahir Dar Universty.
Zoitan Dorney. (2001). Resrch methods Applied Linguistics. Oxford Universty press.
አባሪ
ውድ ተማሪዎች፤ የዚህ መጠይቅ ዋና አላማ በአማርኛ ቋንቋ የማንበብ ልምድና አንብቦ መረዳት ችሎታ
መካከል ያለውን ተዛምዶ በመርመር ለሚሰራ ጥናት መረጃ ማስገኘት ነው፡፡ በመሆኑም ከመጠይቁ የሚገኘው መረጃ
ለጥናቱ ግብ መምታትወሳኝ በመሆኑ መጠይቁን በጥንቃቄ በመሙላት እንድትተባበሩኝ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡
ሰለትብብራቸሁ ከልብ አመሰግናለሁ!
መመሪያ፣ ከዚህ በታች የተሰጡት ዓረፍተ-ነገሮች እያንዳንዳቸው አራት አራት አማራጮች አሏቸው፡፡ ከተሰጡት
አማራጮች መካከል የምትስማሙበትን የ(X) ምልክት በማድረግ አመልክቱ፡፡ መግለጫዎቹ ከ 1-5 ባሉ ቁጥሮች
ተወክለዋል፡፡ የማንበብ ልምድን የሚመለከቱ መግለጫዎችን ታገኛላችሁ የቀረቡትን ዝርዝር መግለጫዎች
አንብባችሁየምትስማሙበትን ከቀረቡት አማራጭ መልሶች ግርጌ ይህን (X) ምልክት በማድረግ አመልክቱ፡፡ ከ 1-5
የተመለከቱት ቁጥሮች ውክልና ቀጥሎ በቀረበው መሰረት አማራጮቹም፤