Professional Documents
Culture Documents
ስራ ፍለጋ
ስራ ፍለጋ
በዚያም ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ
ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ። ልትድን ትወዳለህን? አለው።
ድውዩም። ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም
ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት። ኢየሱስ፦ ተነሣና
አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።
አንድ ቤተክርስትያን ቁጭ ብዬ በስብከት ሰዓት የዕለቱ ተረኛ ሰባኪ ይህን ክፍል ሲናገር
እንዴት እንደሆነ ባላውቅም ከስራ ፍለጋ ጋር ተያያዘብኝ፡፡ እስኪ ክፍሉን የታመመውን ሰውዬ
አውጥተን ስራ ፈላጊ ሰውዬ እናስገባበት፡፡ ምናልባት ግን ሌላ ወንጌል እየሰበኩ ከሆነ መልሱኝ፡
፡
“በዚያም ከሆነ ጊዜ ጀምሮ ስራ ያልያዘ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥
እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ። “ስራ ልትይዝ ትወዳለህን? አለው” ።
ስራ ዕጡም “ጌታ ሆይ፥ መንግስትና የግል ድርጅቶች የስራ ማስታወቂያ በሀገሪቱ ላይ ባናወጡ
ጊዜ በድርጅታቸው ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው (ዘመድ) የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ
ሌላው ቀድሞኝ ይቀጠራል” ብሎ መለሰለት። ኢየሱስ፦ ተነሣና ሲቪህን ተሸክመህ ሂድ አለው።
ወዲያውም ሰውዬው ተነሳ ሲቪውንም ተሸክሞ ሄደ።”