Professional Documents
Culture Documents
4
4
Written by
Author's Name
Draft
information
Contact
information
ምህረት
ክፍል - 4
ደራሲ ዳይሬክተር
Teaser
አማን ክለቡ ፊት ለፊት መኪናው ውስጥ ተቀምጦ ሲብሰለሰል ስልኩ ይጮሀል በፍጥነት ያነሳውና ከስልኩ ውስጥ
የሚነገረውን መረጃ ካዳመጠ በኋላ፡-
አማን
እርግጠኛ ነህ ምንም አልሆነችም?.....ጥሩ የሚፈጠረውን ሁሉ በትኩረት
ተከታተል...ታውቃለህ ጫፏ እንዲነካ አልፈልግም
አማን ስልኩን እያወራ ቤቲ ከክለቡ ወጥታ ዙሪያዋን ታማትርና ወደ እሱ መኪና ፈጠን እያለች ስትመጣ አማን
ስልኩን ይዘጋል ቤቲም የጋቢናውን በር ከፍታ ትገባና በንዴት እየተቀመጠች፡-
ቤቲ
ምን ማድረግህ ነው?
አማን
አንበሲት ተረጋጊና ሲት ቤልትሽን እሰሪ?
ቤቲ
ጓደኛዬን የት እንዳደረካት ሳትነግረኝ ከዚ ንቅንቅ አንልም!
አማን
ደህነቷን ካወቅሽ አይበቃሽም!...ደርሶ ለጓደኛሽ ተቆርቋሪ አትምሰይ!!
ቤቲ
ቆይ ደህና መሆኗን በምን እርግጠኛ መሆን እችላለሁ?
አማን
ቤቴልሄም....አድርጊ የምልሽን ከማድረግ ውጭ ነገሮች ለማወቅ
የምታደርጊውን ጥረት አቁሚ! ይሄን ማድረግ የማትችይ ከሆነ አደጋ
ውስጥ ትወድቂያለሽ! ከዚህ በኋላ ደግሜ አልነግርሽም!!!
ቤቲ
(በፍርሀት)
እሺ እሺ...
አማን
ይልቅ ሲነጋ ሰናይት ፖሊስ ጣቢያ ማመልከቷ ስለማይቀር አንቺ ማለት
ያለብሽን ብጠይቂኝ ይሻላል!
ቤቲ ምንም መልስ ሳትሰጠው ታየዋለች አማንም የመኪናውን ሞተር ያስነሳና ከአካባቢው መንቀሳቀስ ይጀምራሉ።
End of teaser
ምህረት ቀስ እያለች አይኗን ትገልጥና ራሷን ከሳተችበት ስትነቃ ቴዲ ከፊት ለፊቷ ቆሞ የዘውትር ፀሎት ሲያነብ
ታየውና በድንጋጤ ተስፈንጥራ ትነሳለች ቴዲም ደንግጦ እያማተበ፡-
ቴዲ
በስመ አብ ወወልድ...በስመ አብ ወወልድ...አይዞሽ እሺ ሲስቱ አይዞሽ
ምህረት
የት ነኝ...ምን ሆኜ ነው...ማነህ አንተ
ቴዲ
እኔ ቴዲ እባላለሁ የዚህ ቤት ባሉካ ነኝ...መንገድ ላይ ላቦሮዎች
ሲተናኮሉሽ አስጥዬሽ ነው እራስሽን ስትስቺብኝ ግራ ገብቶኝ ወደዚህ
ያመጣሁሽ
ምህረት
ስለረዳኸኝ አመሰግናለሁ አሁን ግን ወደ ቤቴ መሄድ አለብኝ
ቴዲ
አረ አረጋጊው ነፍሴ ሰአቱን አይተሸዋል ከለሊቱ 8 ሰአት እኮ ነው በዚህ
ሰአት በምንሽ ነው የምትሄጂው
ምህረት
ወይኔ ምህረት ምን ውስጥ ነው የገባሁት
ምህረት ተመልሳ ሶፋው ላይ የምትቀመጥ ሲሆን ቴዲ ከሻንጣ ውስጥ ልብስ መፈለግ ሲጀምር እሷ ደግሞ የቤቱን
ዙርያ ታያለች ቴዲ ከሻንጣው ሺቲ ያወጣና ወደ ምህረት እየወረወረላት፡-
ቴዲ
ሲስቱ እንኳን ነቃሽልኝ እንጂ ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም እኔ መኪና
ስጠብቅ ስለማድር ልወጣ ነው ስለዚህ በሩን ከውስጥ ቆልፈሽ ደቅሺና
ጠዋት ወደ ቤትሽ ትነኪዋለሽ
ቴዲ (CONT'D)
ምግብ ምናምን መፈወስ ትፈልጊያለሽ?
ምህረት
አይ ምንም አልፈልግም
ቴዲ
ጎሽ እንኳንም አልፈለክሽ በድንጋጤ ወንጌል መድገሜ ሳያንስ በዚህ ደረቅ
ለሊት ምግብ ልታሰሪኝ ነው ብዬ ሀሳብ ይዞኝ ነበር.
ምህረት ምንም ምላሽ ሳትሰጠው ስትቀር ስልኩን ከኪሱ አውጥቶ ፊት ለፊቷ እያስቀመጠው፡-
ቴዲ (CONT'D)
ስልኬ ባትሪ ስለዘጋ ቻርጅ አርጊውና የምትፈልጊው ቦታ
ደውይ....ፓተርን ምናምን የለውም...ደህና እደሪ በቃ...እና ደግሞ ሸኖ
ምናምን ካስቸገረሽ እዛ ላይ መጠቃቀም ትችያለሽ
ምህረት ወደ ሚጠቁማት ቦታ ስታይ ማስታጠቢያ በማየቷ እንደ መገረም ትላለች ቴዲም ፈገግታውን ያሳያትና ቤቱን
ለቆ ሲወጣ ምህረት በፍጥነት ትነሳና በሩን ከቆለፈች በኋላ እዛው በሩን ተደግፋ ተንሸራታ መሬት ላይ ትቀመጥና
በረጅሙ ትተነፍሳለች፡፡
ሰናይት በፈገግታ ተሞልታ ቁርስ አቀራርባ እንደጨረሰች ምህረትን ለመቀስቀስ ወደ መኝታ ቤቷ ትሄድና በሩን
ስትከፍት ታጣታለች ግራ እየተጋባች በሩን ትዘጋና ወደ ስእል ስቱዲዮዋ በማምራት በሩን ከፍታ ስታይ እዛም
ታጣታለች ግራ እየተጋባች ወደ መመገቢያ ጠረቤዛው ትመለስና ከተቀመጠች በኋላ ከጠረቤዛው ላይ ስልኳን
አንስታ ‹‹ትንሿ›› ብላ ሴቭ ወዳደረገችው ቁጥር ትደውልና ስልኩ በተደጋጋሚ ከጠራ በኋላ ሲነሳ፡-
ሰናይት
አንቺ በጠዋት ወዴት ሄደሽ ነው?
ዌይተር (V.O)
ይቅርታ የኔ እህት የዚህ ስልክ ባለቤት ትላንት ክለባችን ውስጥ ስልኳን
እና ቦርሳዋን ጥላ ወጥታ ነው ምናልት.......
ምህረት
ማ..ማ...ማነው?
ቲጂ
እ? ማነሽ?...አንቺ ራስሽ ማነሽ ባክሽ?....
ምህረት
እረ እናት እኔ ?....
ቲጂ
እናት አትበይኝ አንቺ ውሻ ነይ ውጩ ብዬሻለሁ ዛሬ? እሱንም ውጣ
በይው!
ምህረት የምትመልሰው ጠፍቷት ዝም ትላለች ቲጂ ግን ይበልጡን ተናዳ ድንጋይ ታነሳና በሩን በሀይል መደብደብ
ስትጀምር ቴዲ ደግሞ ዳቦና እንቁላል ይዞ ወደ ግቢው ሲገባ የቲጂን ሁኔታ ሲያይ ተደናግጦ፡-
ቴዲ
ቲጂ...ምንድን ነው ምን ሆነሻል?
ቲጂ
ማናባህን ነው አስተኝተህ የወጣህልኝ ባክህ
ቴዲ ቲጂ ነገሩን በሌላ መልኩ እንደተረዳችው ይገባውና መሳቅ ይጀምራል ቲጂም ይበልጥ ግራ ይገባታል፡፡
ቤቲና ሰናይት አብርሀም ቢሮ ውስጥ ተቀምጠው ለፍራኦል ቃላቸውን እየሰጡ ሲሆን አብርሀም ፈንጠር ብሎ ቆሞ
የሚወራውን በትኩረት ይሰማል፡-
ፍራኦል
ይሄ ጉዳይ ከአቶ አማን ጋር ግንኙነት ይኖረዋል ብለሽ ታስቢያለሽ?
ሰናይት
ያለምንም ጥርጥር እሱ ነው ሌላ ሊያስጠፋት የሚችል ምክንያት የለም!
ፍራኦል
ሰናይት አቶ አማን ከተፈታ በኋላ በተፈጠረው ነገር እህትሽ መረበሽ
ውስጥ ገብታ ስለነበር ምናልባት በጭንቀት ምክንያት ለመጥፋት አስባ
ቢሆንስ ብዙ ሰዎች እንደዚህ ያደርጋሉ ብዬ ነው።
ሰናይት
እህቴ በጣም ጤነኛ ልጅ ናት! በጭራሽ እንደዚህ አይነት ተራ ነገር
አታደርግም።
ፍራኦል
ምን ያህል እርግጠኛ ነሽ?
ሰናይት
በጣም እርግጠኛ ነኝ!
ፍራኦል
ስንት ሰዓት ላይ ነበር ከቤት የወጣችሁት?
ቤቲ
በግምት ወደ 4 ሰዓት አካባቢ።
ፍራኦል
ምክንያታችሁ ምን ነበር?
ቤቲ
በጣም ተጨንቃ እንቅልፍ እንቢ ብሏት ነበር ከዛም ደወለችልኝና ወጥተን
እንድንጠጣና ከጭንቀቷ መገላገል እንደምትፈልግ ነገረችኝ በጣም
የደከመኝ ቢሆንም ሁኔታዋ ስላሳዘነኝ እሺ አልኳት!
ፍራኦል
ምን እንዳስጨነቃት አልነገረችሽም?
ቤቲ
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆና ስሜቷን ከመጠበቅ ውጪ ልጠይቃት አልፈለኩም
ፍራኦል
ስትገምቺው ግን ምን ያስጨነቃት ይመስልሻል!
ቤቲ
እኔንጃ መገመት ይከብደኛል።
ፍራኦል
መጨረሻ እንዴት ነው የተለያያችሁት?
ቤቲ
ሁለታችንም በጣም ጠጥተንና ሰክረን ነበር በመሀል ከዚ በፊት
የማውቀው የረጅም ጊዜ ጓደኛዬ የነበረን ሰው አገኘሁ ከሱ ጋር ብዙ
ጠጣን እስከዛ ሰዓት ድረስ አብረን እንደነበርን አስታውሳለሁ...ከራሴ
ይልቅ ለሷ ትኩረት ልሰጥ ይገባ ነበር.....ወይኔ ጓደኛዬ
ፍራኦል
አይዞሽ....መለያያታችሁን ያወቅሽው መቼ ነው።
ቤቲ
ጠዋት ያልኩህ ሰው ቤት ራሴን አገኘሁት ከዛ ሰኒ ደውላ መጥፋቷን
ነገረቺኝ እዚህ አገር ከመጣሁ በኋላ እንደዚህ አይነት ምሽት አሳልፌ
ስለማላውቅ ራሴን እስክረሳ ነው ነገሮችን ሳደርግ የነበረው እባካችሁ
ጓደኛዬን አግኙልኝ አለዛ ፀፀቱን አልችለውም!
ቤቲ መልሳ ማልቀስ ስትጀምር አብርሀም በንዴት ተሞልቶ ክፍሉን ለቆ ይወጣል፡፡
አብርሀም በንዴት ተሞልቶ ከክፍሉ ከወጣ በኋላ ኮሪደሩ ላይ ቆሞ ሲብሰለሰል ሰናይት ከምርመራው ክፍል ትወጣና
ወደ አብርሀም ተጠግታ እየቆመች፡-
ሰናይት
አብርሽ ለምን አታምነኝም ከእሱ ውጪ ማንም እንደዚህ ሊያደርግ
አይችልም!
አብርሀም
እኔም እንዳንቺ ነው የማስበው ግን ከዚህ በኋላ ይሄን ሰው
የምንታገልበትን መንገድ መቀየር ይኖርብናል እጁ ረጅም ስለሆነ ፊት
ለፊት ልንፋለመው አንችልም
ሰናይት
(በንዴት ተሞልታ)
እኛ ነን ፊት እየሰጠን የሌለውን አቅም አለው እያልን እዚህ
ያደረስነው...ወይኔ ሰናይት!...እውነቴን ነው የምልህ ጫፏን ነክቷት ከሆነ
የመጨረሻው ነው የሚሆነው ለእህቴማ መሆን ካቃተኝ የውብዳር ተፈሪ
አልወለደችኝም!
አብርሀም
ሰኒ ተረጋጊ አንቺ ራስሽን መጉዳት የለብሽም
ምህረትና ቲጂን በቤቱ ውስጥ የምንመለከት ሲሆን ቲጂ ቡና እያፈላች ምህረትን አፈር ብላ በማየት፡-
ቲጂ
እንዴት ብዬ ይቅርታ እንደምጠይቅሽ አላውቅም?
ምህረት
እረ ምንም አላጠፋሽም
ቲጂ
እርሜን ቤተሰቦቼ ጋር ላድር ብሄድ ሌላ ሴት ደርቦ ጠበቀኝ ብዬ እኮ ነው
እንደዛ ላብድ የደረስኩት...ታውቂያለሽ ቴዲን ከልክ በላይ ነው
የማፈቅረው በሱ የመጣ ምንም ነገር ቢሆን መቋቋም አልችልም!
ምህረት
ደስ ይላል!
ቲጂ
የሚገርምሽ ነገር ግን በፊት እንደዚህ አልነበርኩም....አሁን ሳስበው
በጣም ይገርመኛል!
ምህረት
እንዴት?
ቲጂ
በፊት የሰፈሩ ጉልበተኛ ስለነበር በጡንቻው ብቻ የሚያስብ አድርጌ
ስለማስበው በጣም ነበር የምጠላው...አቤት እኔን ለማግኘት የከፈለው
ዋጋ....ህንድ ፊልም ታያለሽ?
ምህረት
አይ አይቼ አላውቅም።
ቲጂ
ውይ ተበድለሻላ የምታይ ቢሆን ኖሮ የምልሽ ይገባሽ ነበር ብቻ ግን ምን
አለፋሽ ባጭሩ የኔ እና የሱ ህይወት የህንድ ፊልም ነበር የሚመስለው!
ምህረት
እንዴት?
ቲጂ
ከስንት ጎረምሳ እ...ከወንድሞቼ...ከፖሊሶች ሳይቀር እየተፋለመ ነው
የራሱ ሊይደርገኝ ሲሞክር የነበረው።
ምህረት
በጉልበት? ይሄ እኮ ልክ አይደለም? እውነት ለመናገር መብትሽን መጣስ
ነው!
ቲጂ
ልክ ነሽ! እኔም ፍቅር በጉልበት እንደማይሆን እንዲያውቅ እፈልግ
ስለነበር ጭራሽ እልህ ውስጥ እየከተትኩ እንደ እብድ ነበር የማደርገው
ምህረት
እና እንዴት አብራችሁ ሆናችሁ!
ቲጂ
ነገሮች ሲባባሱ እራሱን መጉዳት ጀመረ ያኔ ቀርቤ ላረጋጋው ሞከርኩ
ታውቂያለሽ ሴት ልጅ ብልሀተኛ ናት የሚባለው እውነት ነው ስፈልግ
ውሀ ስፈልግ እሳት አደርገው ጀመር ከዛ አሳዘነኝ ጉልበት ብቻ እንዳልሆነ
ገባኝ የሆነ የማላውቀውን ነገሩን አገኘሁት ከዛ ቅድም እንዳየሽው
እስክሆን ድረስ ከንፌልሽ ቁጭ
ቴዲ
ቡናውን ትታችሁ ቀደዳ ጀመራችሁ አይደል?
ቲጂ
ትንሽ ፈታ ላርጋት ብዬ እኮ ነው
ቴዲ
በይ ቶሎ አጠጪንና ወደ ቤቷ እንሸኛት
አብርሀም ከጎኑ ሰናይትን ከጀርባ ደግሞ ቤቲን አስቀምጦ መኪናውን እያሽከረከረ ሲሆን ሰናይት መንገድ መንገዱን
እያየች ሀሳብ ውስጥ ትገባና ንግስትን ያገኘቻት ቀን ያወሩትን ማስታወስ ትጀምራለች፡-
Flash back start
የሰናይት ስልኳ እየጠራ ቢሆንም እሷ ግን ሀሳብ ውስጥ በመሆኗ አትሰማውም አብርሀምም ሁኔታዋ ግራ አጋብቶት
ነካ በማድረግ ከነበረችበት ሀሳብ ያነቃትና ስልኳን ያሳያታል ሰናይትም ስልኳ እየጠራ መሆኑን ስታውቅ ፈጠን ብላ
ታነሳውና፡-
ሰናይት
ሄሎ
ምህረት V.O
ሄሎ ሰኒ!
ሰናይት
ምሩ!...የኔ እናት አለሽ? ምን ሆነሽ ነው ግን?...ቆይ የት ሆነሽ ነው?
አስጨነቅሽኝ እኮ! ደህና ነሽ ግን አይደል?
ምህረት
ደህና ነኝ እህቴ ተረጋጊ ......
አማን ፋይል እያገላበጠ በሚመለከትበት ግዜ አብይ ሌላ ፋይል ይዞ በሩን ያንኳኳና ይገባል አማንም በፈገግታ
ተሞልቶ እያየው፡-
አማን
እንኳን ደህና መጣህ?
አብይ
እንኳን ደህና ቆየህኝ!!
አማን
አረፍ በል!
አብይ
(ፋይሉን ሰጥቶት እየተቀመጠ)
ይሄ ባለፉት 6 ወራት ውስጥ ለተከናወኑ ግዢዎችን የወጣውን ወጪ
የሚያሳይ ዝርዝር ነው
አማን
በጣም ጥሩ በኋላ በደንብ አያቸዋለሁ።
አብይ
እንቅልፍ አጥቼ ነው ያደርኩት።
አማን
በሰላም?
አብይ
ትላንት ብዙ ጥያቄ ነው የፈጠርክብኝ እ…ጊዜ ካለህ አንዳንድ ነገሮችን
ብናወራ ብዬ ነበር
አማን
እምነት ብቻ አይበቃም? ለሁሉም ጥያቄዎችህ መልስ ልሰጥህ አልችልም!
አማን (CONT'D)
እሺ በቃ ማታ ላይ ተረጋግተን እናወራለን!...ግን
ብዙ ነገር ይነግረኛል ብለህ እንዳጠብቅ።
አብይ
(በፈገግታ ከተቀመጠበት ይነሳና)
እኔም ብዙ ማወቅ አልፈልግም ማታ እንገናኝ መልካም ስራ
ሰናይት አብርሀምና ቤቲን በግቢው ውስጥ የምንመለከታቸው ሲሆን ሰናይት አላስችል ብሏት ወዲህ ወድያ ትላለች
ድንገት ግን የግቢው በር ሲንኳኳ ሰናይት በፍጥነት ሮጣ ሄዳ በሩን ስትከፍት ምህረት ሺቲ እንደለበሰች ቴዲና ቲጂን
አስከትላ ወደ ግቢው ትገባለች። ሰናይትም በደስታ ተሞልታ ትጠመጠምባትና አገላብጣ በስስት እያየቻት፡-
ሰናይት
ደህና ነሽልኝ አይደል...እውነት ምንም አላደረጉሽም?
ምህረት
አዎ ደህና ነኝ ምንም አልሆንኩም!
ሰናይት
እርግጠኛ ነሽ ምሩዬ? ወይ ሀኪም ቤት እንሂድ?
ምህረት
ደህና ነኝ አልኩሽ እኮ ሰኒ ይልቅ ተዋወቂያቸው
(ወደ ቴዲ ዞራ እየጠቆመች)
ቴዲ ይባላል እሱ ነው ማታ ከብዙ ነገር አድኖኝ ቤቱ ያሳደረኝ እሷ ደግሞ
ቲጂ ትባላለች ሚስቱ ናት
ሰናይት
ሰናይት እባላለሁ የምህረት እህት ነኝ ስላደረጋችሁላት ነገር ሁሉ
እግዚአብሔር ውለታችሁን ይክፈለው
በዘመናዊው ባር ውስጥ አብይ አማንን በጥያቄ አይን እየተመለከተው ሲሆን አማን እየጠጡት ካለው ውስኪ ላይ
አይኑን ሳያነሳ፡-
አማን
ተጨማሪ ማወቅ የምትፈልገው ነገር ምንድን ነው?
አብይ
መጀመሪያስ ምን ያወኩት ነገር አለ? ጭንቅላቴን እንደሆነ በጥያቄ
ሞልተህዋል!
አማን
አሁን መስማት የምትፈልገውን ብቻ ጠይቀኝ ከዚህ በኋላ ስለዚህ ጉዳይ
አንስተን ማውራት የለብንም
አብይ
መጀመሪያ እንደማትዋሸኝ ቃል ግባልኝ!!
አማን
መመለስ የማልችለውን ጥያቄ አንስተህ እንድነግርህ ልታስገድደኝ
እንዳትሞክር እንጂ አልዋሽህም
አብይ
እሺ!....የመጀሪያው ጥያቄ ከምህረት የምትፈልገው ነገር ምንድን ነው?
አማን
(ፈገግ ይልና)
ከከባዱ ጀመርክ....እሱን ባታውቀው ይሻላል።
አብይ
(ኮስተር ብሎ)
አማን...ይሄንን እንድትደብቀኝ አልፈልግም...ምህረትን የቀረብካት ከሷ
ለምትፈልገው ጥቅምህ ብቻ ብለህ ነው? እውነት ምንም አይነት ፍቅር
ውስጥህ የለም?
አማን ስሜቱ እጅግ ይለወጣል ምን መገናገር እንዳለበት ግራ ይጋባል አብይም ስሜቱን አስተውሎ፡-
አብይ (CONT'D)
ለምን አልወዳትም ብለህ ዋሸኸኝ?
አማን
ምክንያቱም ልቀበለውና ልታረቀው የምፈልገው እውነት እሱ ስለሆነ
ምህረትን በማፍቀሬ ብዙ የማጣው ነገር አለ...አብይ ከራሴ እና ከአላማዬ
ጎትቶ ያስቀረኝ የእሷ ፍቅር ነው
አብይ
ምን ማለት ነው?
አማን
የመጀመሪያ ሰሞን ፍላጎቴ ፍቅር አልነበረም ከዛ ይልቅ ከሷ የምፈልገውን
ማግኘት ላይ ነበር ትኩረቴ...ቅርርባችን በጨመረ ቁጥር ነገሮች
እየተለወጡ ሄዱ!
አብይ
ቆይ ግልፅ አርግልኝ...አውነቱ የትኛው ነው ትላንት የነገርከኝ ወይስ?...
አማን
እውነቱ ምህረትን አሁንም ድረስ አፈቅራታለሁ። ፍቅሯ ግን ከራሴ
እያጣላኝ ልተካው የማልችለውን ነገር እያሳጣኝ ነው!
አብይ
ምንድን ነው እሱ ልትተካው የማትችለው ነገር?
አማን
ብነግርህ ሚስጥር መጠበቅ ትችላለህ!
አብይ
አማን!!...እኔ እኮ ጓደኛህ ብቻ አይደለሁም ወንድምህ ነኝ! ይሄን ሁሉ
ነገር የምጠይቅህ ያንተን ሚስጥር የማወቅ ጉጉት ኖሮኝ ሳይሆን ችግርህን
ለመካፈልና በቻልኩት አቅም አንተን ለማገዝ ስለምፈልግ ነው! አንተ
እንደዚህ እየሆንክ ደስተኛ የምሆን ይመስልሀል?
አማን
(ትኩር ብሎ አይቶት)
ደግመህ አስብ ይሄን ነገር ከነገርኩህ በኋላ ከጎኔ ከመቆም ውጭ አማራጭ
አይኖርህም!
አብይ
ከጎንህ ለመቆም ሁለቴ ማሰብ አይጠበቅብኝም!
አማን
ወላጅ አባቴ አልሞተም በህይወት አለ!
አብይ
(በድንጋጤ ፈጦ)
ምን?
አማን
(አይኑ እንባ እያቀረረ)
አዎ መኖር ከተባለ በህይወት አለ...በከፋ ህመም እየተሰቃየ አይኑ
ውጪውን ሳያይ የፀሀይን ብርሃን እንደናፈቀ ብቻውን ቤት ውስጥ
ተዘግቶ በህይወት አለ
አማን አይኑ እንባ ያቀርና ከተቀመጠበት ተነስቶ እራሱን ለማረጋጋት እየሞከረ ወደ መታጠቢያ ቤት ያመራል፡፡
በሳሎኑ ሶፋ ላይ ሰናይት ምህረትን እግሯ ላይ ጋደም እንድትል አድርጋት ፀጉሯን እየደባበሰቻት ፊልም የሚያዩ ሲሆን
ምህረት አይኗ ቴሌብዥኑ ላይ ቢሆንም ሀሳቧ ግን እነቴዲ ቤት በነበረችበት ግዜ ከቲጂ ጋር ያወሯቸው ነገሮች
ያስታውሳል፡-
ቲጂ
ከስንት ጎረምሳ እ...ከወንድሞቼ...ከፖሊሶች ሳይቀር እየተፋለመ ነው
የራሱ ሊይደርገኝ ሲሞክር የነበረው።
ምህረት
በጉልበት? ይሄ እኮ ልክ አይደለም? እውነት ለመናገር መብትሽን መጣስ
ነው!
ቲጂ
ልክ ነሽ! እኔም ፍቅር በጉልበት እንደማይሆን እንዲያውቅ እፈልግ
ስለነበር ጭራሽ እልህ ውስጥ እየከተትኩ እንደ እብድ ነበር የማደርገው
ሰናይት
ሄሎ...እሺ አሁኑኑ መጣሁ
ምህረት
ወዴት ልትሄጂ ነው?
ሰናይት
እዚሁ ነኝ መጣሁ
የአማን መኪና የአብይ ቤት አካባቢ መጥቶ ይቆማል ሁለቱም ለጥቂት ቆይታ ዝም ተባብለው ይቆዩና አማን በረጅሙ
ተንፍሶ፡-
አማን
ቆይ አንተ ብትሆን የቱን ትመርጣለህ?
አብይ
(አሰብ አድርጎ)
ምርጫው ከባድ ነው ግን ሁለቱንም ማግኘት የምችልበትን መንገድ
እፈልጋለሁ!
አማን
እሱን ለማድረግ ስሞክር ነው ራሴን ያጣሁት!
አብይ
ያልሞከርከው ነገር እንዳለ ይሰማኛል።
አማን
ምን?
አብይ
ለምህረት ግልጽ ሁንላት! ከሷ የምትፈልገውን ነገር ምንም ይሁን ምን
ፊት ለፊት ጠይቀህ ለማግኘት ሞክር! ላደረስከው ጥፋት ለሄድክበት
መንገድ ሁሉ ይቅርታ በል! ያኔ እሷንም ማግኘት አባትህንም ማትረፍ
የምትችል ይመስለኛል
አማን
ይሄን አድርጌ ነገሮች ባይሆኑስ?
አብይ
ቢያንስ ራስህን አታጣም!
ሰናይት ፊቷን በሻሽ ሸፋፍና አንድ ሳምሶናይት ነገር ይዛ አስፋልቱ ዳር ቆማ የምንመለከታት ሲሆን ከዚህ በፊት
ንግስትን ያገኘችበት Rava4 መኪና እሷ ወዳለችበት መጥቶ ይቆምና የኋላው በር ይከፈትላታል ሰናይትም ፈራ ተባ
ብላ ስትገባ መኪናው መንቀሳቀስ ይጀምራል።
ሰናይት ይዛው የነበረውን ሳምሶናይት ጋቢና ያለው ሹፌር ማንነቱ ሳይታይ ከፍቶ እያየው ሲሆን ውስጡ በገንዘብ
ተሞልቷል ፊቱን ሳያዞር ብሩን እያየ፡-
ሰውየው
አለቃ ገንዘቡ ልክ ነው።
ንግስት
(ለሰናይት እጇን ዘርግታላት)
ስራው ተጀምሯል በአጭር ጊዜ አማን የሚባል ሰው ከመኖር ወዳለመኖር
እንቀይረዋለን
ቤቲ
እንደዚህ በአደባባይ መገናኘቱ ጥሩ ነው ትላለህ? የምትፈልገውን ነገር
በስልክ ልትነግረኝ ትችል ነበር እኮ!
አማን
ከዚህ በኋላ ካንቺ ምንም አልፈልግም።
ቤቲ
ምን?...ማለት?...ምን አጠፋሁ?
አማን
ምንም አላጠፋሽም...ግን ምህረትን ምን ያህል እንደማፈቅራት
ታውቂያለሽ! ስለዚህ ከዚህ በላይ ላስጨንቃት አልፈልግም የሚሆን ከሆነ
የምፈልገውን ነገር በፍቃዷ ለመውሰድ ወስኛለሁ።
CLIFF HANGER
አብርሀም ቤቲና አማን መኪና ውስጥ ሲያወሩ በማየቱ ሲገረም ይቆይና ስልኩን አውጥቶ ፎቶ ሲያነሳቸው ይታያል።