Professional Documents
Culture Documents
መፍጠንና_መፍጠር_የወል_እውነቶችን_ማፅናት
መፍጠንና_መፍጠር_የወል_እውነቶችን_ማፅናት
ሰኔ 2015 ዓ.ም
ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት
አዲስ አበባ
ማውጫ
መግቢያ ...................................................................................................................................... 1
ክፍል አንድ...................................................................................................................... 3
I. ተለዋዋጭ ዓለም፤ሥር የሰደዱ ሀገራዊ ችግሮች ..................................................................... 3
1.1 ከባለ አንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ ዋልታ እየተቀየረ ያለ የዓለም የኃይል አሰላለፍ ........... 3
1.2 የመንግሥታት ኃይል መሸርሸር.................................................................................. 5
1.3 የድኅረ እውነት ፖለቲካዊ ሐሳዊነት ........................................................................... 7
1.4 የሃይማኖት፣ የብሔርና የፖለቲካ ጽንፈኝነት ጥምረት አደጋ ..................................... 11
1.5 ድህነት እንደ ታላቁ ተግዳሮት ................................................................................. 14
1.6 በእንጥልጥል ላይ ያለ የሀገር ግንባታ........................................................................ 17
ክፍል ሁለት ................................................................................................................... 20
II. የፈጠራና ፍጥነት አስፈላጊነት ............................................................................................ 20
2.1 ኋላ ከቀረንበት ወጥተን ከፊት ለመገኘት .................................................................. 20
2.2 ጊዜና የምርጫ ቃል ኪዳን ....................................................................................... 22
2.3 ቃልን ማጠፍ እና ቃልን ማክበር ............................................................................. 23
ክፍል ሦስት ................................................................................................................... 24
III. የመፍጠን ጅማሮ ስኬቶች ............................................................................................... 24
3.1 ብልጽግናዊ መንግሥት እና ኢኮኖሚያዊ ፍጥነት ..................................................... 24
3.2 ከተናጠል ወደ ወል እውነት ..................................................................................... 30
3.3 የታደሰው የዓለም አቀፍ ግኑኘነትና ዲፕሎማሲ ........................................................ 44
ክፍል አራት ................................................................................................................... 48
IV. ከፍጥነት የሚገቱን .......................................................................................................... 48
4.1 የሠርጎ ገብ ፖለቲካ፡ ራእይን መንጠቅ፤ ዕይታን መስረቅ ......................................... 50
4.2 የተናጠል እውነት እና አንጻራዊ ጥቅም .................................................................... 51
4.3 ያልተገባ ክብርና ሀብት ፍለጋ .................................................................................. 52
4.4 ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን አለመላመድ፡ ጠባቂነት እና መርሕ አልባነት .................. 53
ክፍል አምስት ................................................................................................................ 54
V. ይበልጥ መፍጠር፤ ይበልጥ መፍጠን................................................................................... 54
5.1 “የብልጽግና አጣዳፊነት” ዕሳቤ ................................................................................. 54
5.2 ነገርን ከሥሩ ........................................................................................................... 55
5.3 አዳዲሶቹን ወደ ትግበራ ነባሮቹን ወደ ሥራ ገበታ _ ለትውልድ .............................. 56
5.4 በክረምት፣ እራትና መብራት .................................................................................... 57
5.5 የወል እውነትን የማጽናት ቀጣይ የፖለቲካ አቅጣጫ ................................................ 58
VI. ማጠቃለያ ....................................................................................................................... 62
መግቢያ
ብልጽግናን ማረጋገጥ ፈጣን እና ቀጣይነት ያለው ጉዞንና ጥረትን የሚጠይቅ ነው። ለውጡ
የነበረውን ሁኔታ በመለወጥ በመለወጥ ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚያስችል መደላድል
ወይም ምሕዋር ውስጥ እየተጓዘ ነው።
ፍጥነት ማለት በቶሎ በቶሎ ነገሮችን በመማርና በማሻሻል፣ ነገሮች በተፈጥሯዊ መንገድ
ከሚወስዱት ጊዜ በተሻለ ጊዜ፣ በወቅቱ የተፈጠሩ ዕድሎችን በቶሎና አማጥጦ በመጠቀም፣
ነገሮችን ከግብ ለማድረስ መቻል ነው። በለውጥ ያመጣናቸውን ስኬቶች ለማላቅ፣ የተፈጠሩ
እንከኖችን ለማረም ጥራት ያለው ፍጥነት ወሳኝ ነው። ጥራት ያለው ፍጥነት ማለት ‹የነ
ቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ› ከሚለው የተለየ፤ ለፍጥነት ሲባል ጥራትን፣ ለጥራትም
ሲባል ፍጥነትን ሳያስተጓጉሉ፣ ለውጥን መምራት ነው። ብልጽግና ለማረጋገጥ ጥራት ያለው
ፍጥነትን መጨመር ያስፈልገናል።
የብልጽግና መነሻችን ወለል ዝቅተኛ ነው:: በዕድገትም ከኋላ ቀርተናል። ስለዚህም ውድድር
በበዛበት ዓለም ለማሸነፍ አንዱ መሣሪያችን ፍጥነት ነው። ወደ ኋላ መቅረት ለተለያዩ
ጫናዎች ይዳርጋል። ከዚህ ጫና ተላቅቆ ከሌሎቹ ጋር በእኩል ደረጃ ለመታየት መፍጠን
አለብን። ከመነሻ እስከ መዳረሻችን ያለው ጉዞ ሩቅ ስለሆነ፣ በለውጥ ጎዳና ላይ መጓዝ ብቻ
1
ሳይሆን የግድ ፍጥነት መጨመር ያስፈልጋል። ከዚህም በተጨማሪ መፍጠን ነገሮችን በቶሎ
ለማጠናቀቅ እና ሌሎች ሥራዎችን ለመጀመር ዕድል ይሰጣል። እንጦጦን በቶሎ
መጨረሳችን፣ ኮይሻን እንድንጅምር አድርጎናል። ኮይሻን መጨረሳችን ገበታ ለትውልድን
እንድንጀምር አድርጎናል። ሌሎች ተጨማሪ ነገሮችን እንድንሠራ የጊዜ ነጻነት ሰጥቶናል።
በመሆኑም የፍጥነትን ዋጋ ተገንዝበን ለመፍጠን የሚያስፈልገውን ሥርዓታዊ ጥንካሬ
ማምጣት ይኖርብናል።
2
ክፍል አንድ
1.1 ከባለ አንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ ዋልታ እየተቀየረ ያለ የዓለም የኃይል አሰላለፍ
የአፍሪካ ቀንድን ሰላም፣ ደኅንነትና ብልጽግና ከቀይ ባሕርና ከመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት
ጋር አጣምሮ ማየት ይገባል። የኃያላኑ ዕይታም በዚህ ልክ በመሆኑ፣ የቀንዱ ሀገራትን ጥቅምና
ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚያስችለው በዚህ ልክ መመልከትና መረዳት ስንችል ነው። በርግጥ
የቀንዱ ሀገራት ቀጥታ ግንኙነት በዚህ ክበብ ሳይወሰን ሰሜን አፍሪካ ድረስ ይደርሳል።
አውታረ ሰፊ ግንኙነቶች ቀጣናውን ተለዋዋጭ ክሥተቶችን የሚያስተናግድ አድርገውታል።
በመሆኑም በንቃት መከታተልና ዝግጁነትን ማረገገጥ የሠርክ ተግባር መሆን ይገባዋል።
3
የየሀገራቱ የውስጥ ጉዳይ አለመርጋትና ጣልቃ የሚገቡ ሀገራት ፍላጎት መበራከት፣ በድንበር
ተገድቦ የሚቀር የውስጥ ጉዳይ እንደሌለ ያሳያል።
የእርስ በርስ ጦርነት ሳይበቃን የቀንዱ ሀገራትን ተፈጥሮ ትፈትነናለች። የኮቪድ ወረርሽኝ
ያቀዛቀዘው ኢኮኖሚ እያገገመ ሳለ የአየር ንብረት ለውጥ በምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ድርቅ
አስከተለ፤ ከዚህ ጋር እየታገልን የአንበጣ ወረርሽኝ መጣ። እርሱንም ስንቋቋመው ዩክሬን
ጦርነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችን የሩሲያ እንድናስተናግድ አደረገን። በቀጣናው
ጂኦፖለቲካዊ ውድድር ውስጥ ታላላቆቹ ኃያላን አሜሪካ፣ ቻይና፣ የአውሮፓ ኅብረትና ሩሲያ
እየተፎካከሩ ናቸው። እንዲሁም ወደ ኃያልነት የሚንደረደሩት ቱርክ፣ ጃፓንና የባሕረ
ሰላጤው ሀገራት በአካባቢው እያማተሩ ይገኛሉ።
የእኛ አፍሪካውያን የችግሮቻችን ምንጭ፣ የጸና ሰላም ማጣታችን ነው። የጸና ሰላም ማለት
ለረዥም ዓመታት የዘለቀ፣ ሁለንተናዊ የሆነ፣ ከውስጥና ከውጭ ግጭት የጸዳ ሰላም ማለት
ነው። በአራቱም የአፍሪካ ማዕዘናት መትረየስ _ ያጓራል። የአፍሪካ ኅብረት በ2060 በአፍሪካ
የመሣሪያ አርምሞን ለማሳካት እየሠራ ቢሆንም፣ ያስቀመጠውን ግብ እውን ማድረግ ከባድ
እንደሆነ በርካታ አመላካቾች ይታያሉ። በ2022/2023 ከ54 ሀገራት ውስጥ ከ35 በላይ
የሚሆኑት በጦርነት ውስጥ ይገኛሉ። ይሄንን መሰል ችግሮቻችንን ተሸክመን ኃያላኑ ይዘውት
የመጡትን ዕድል በአግባብ ልንጠቀም አንችልም። ኬክን በጥይት፣ ፍቅርን በግጭት እየቀየርን
ትውልድ የማይገፋውን ድህነት መሻገር ፈጽሞ አይቻልም።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ምልክት ናት። ከቀንዱ ሀገራት መካከል ሰፊ የቆዳ ስፋት አላት፤
በሕዝብ ብዛት ትልቋ ናት ፤ በታሪክ፣ በኢኮኖሚ ዕድገት፣ በሰላም ማስከበር ትታወቃለች፤
የአፍረካ ኅብረት መቀመጫ ናት። ከዐሥሩ የቀንዱ ሀገራት መካከል ከሰባቱ ጋር ድንበር
ትጋራለች። ይህ ሁሉ ስለ ቀንዱ ሲነሣ የኢትዮጵያን ድርሻ እንዲገዝፍ አድርጎታል። ድንበር
ከምንጋራቸው ሀገራት በዘለለ መነሻውን ኢትዮጵያ ያደረገው ዓባይ ከዐሥር ሀገራት ጋር
ያገናኘናል። ከዐሥሩ ሀገራት መካከል ከአራቱ ጋር ድንበር ስንጋራ፣ ከተቀሩት ስድስቱ ጋር
ደግሞ ድንበር ሳይሆን ውኃ እንጋራለን። በድምሩ ከኢትዮጵያ ጋር በድንበርና በውኃ
ግንኙነት ያላቸው 13 አፍሪካ ሀገራት ናቸው። ሀገራችን ከእነዚህ ሀገራት ጋር ጂኦፖለቲዊና
የጂኦ ኢኮኖሚያዊ ትሥሥሮች አሏት።
ኢትዮጵያ የምትገኝበት የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና የቀይ ባሕር አዋሳኝ መሆኑና ቀጣናው የብዙ
ዓለም አቀፍ ኃይሎች መሻኮቻ መሆኑ፣ ቀይ ባሕርን ከኢትዮጵያ ህልውናና ጥቅም ጋር
4
በእጅጉ የተቆራኘ አድርጎታል። ቀይ ባሕር የዓለም ወሳኝ የንግድ ማሳለጫ መሥመር ነው።
ከዚያም ባሻገር ውቅያኖሶችን አቋርጦ ለሚደረግ ማናቸውም ዓይነት የባሕር ኃይል
እንቅስቃሴ እጅግ አስፈላጊ ሥፍራ ነው። በሀገራት መካከል የሚደረጉ ኢኮኖሚያዊም ሆነ
ወታደራዊ ግብግቦች በቀይ ባሕርና በቀጣናው በሚኖረው የኃይል ሚዛን ላይ የተመሠረተ
ነው።
ኢትዮጵያና የቀንዱ ሀገራት በአጠቃላይ ባላቸው የጂኦ ፖለቲካ ሥፍራ፣ በለም መሬታቸው
እና በሕዝብ ብዛታቸው ብቻ ሰፊ ተጽዕኖ ማሳደር የሚችሉበት ዕድል በፊትም አሁንም
ክፍት ነው። ሆኖም ቀጣናው ለብዙ ኃያላን ሀገራት መናኸሪያ በመሆኑ በቀጣናው ሀገራት
ውስጣዊ ፖለቲካ እጁን ሰድዶ የሚፈተፍተውና ሀገራቱ ጠንክረው እንዳይወጡ የሚያሤረው
ኃይል ብዛት የትየለሌ ነው። ይህን ሤራና የጂኦፖለቲካ ግብግብ መቋቋምና ብሔራዊ ጥቅምን
ማስከበር የሚቻለው ውስጣዊ አንድነታችንን አጠንክረን ከጎረቤቶቻችን ጋር ያለንን ግንኙነት
በማሣለጥ ከቀጣናው የሚገኘውን ጥቅም ለማረጋገጥ ስንችል ነው። የቀጣናው ሽኩቻ
ውስብስብ፣ ብዙ ኃይሎች ያሉበት፣ ተለዋዋጭ፣ እና በሥጋት የተከበበ ነው። ይህን ሁኔታ
አልፎ በብቃት ዘላቂ ጥቅምን ለማስከበር ውስጣዊ የፖለቲካ መረጋጋትና ጠንካራ አንድነት
ያስፈልጋል። ሌላው ቀርቶ ጊዜያዊ የኢኮኖሚ ማስተንፈሻ ድጋፎችን ከፋርስ ባሕረ ሰላጤ
ሀገራት ለማግኘት እንኳን፣ በቀጣናው ያለን ይዞታ መጠንከር፣ በቀይ ባሕር ላይ የሚኖረን
ሚናም መጨመር አለበት።
አፍሪካ ብሎም ሀገራችን ያለችበት የአፍሪካ ቀንድ የኃያላኑ ትኩረት ማረፊያ መሆኑን ወደ
ጥቅም ለመቀየር የቀንዱ ሀገራት ትብርርና ሰላም በእጅጉ አስፈላጊ ነው። ይሄን ማድረግ
አለመቻል ውሻ በቀደደው ጅብ እንዲገባ ያደርገዋል። ቀዳዳችንን ደፍነን የግንኙነት
ሚዛናችንን ጠብቀን መጓዝ እስከቻልን ዕድሉ መልካም ነው። ይሁንና ዕድሉን በፍጥነትና
ፈጠራ አክለን ወደጥቅም ካልቀየርነው፣ ዕድሉ በተለዋዋጭ ክሥተቶች ምክንያት
ያመልጠናል።
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከመቶ ዓመት በፊት የነበረ አንድ መንግሥት እና በዚህ በ21ኛው
ክፍለ ዘመን ያለ መንግሥት ያላቸው ኃይልና ሥልጣን ሲወዳደር፣ የዚህ ዘመን መንግሥታት
ኃይልና ሥልጣን እጅጉን ቀንሷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ሥርዓት የተሣሠረ
ሆኗል፤ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጽዕኖ ፈጣሪ ነው ፤ የዲጂታል ሉዓላዊነት
5
ትርጉም አልባ ሆኗ፤ የትላልቅ ኩባንያዎች ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ አይሏል፤ የዴሞክራሲ
ሥርዓት ያልተማከለ ኃይልና ሥልጣንን እየፈጠረ ነው፤ እነዚህ ሁሉ ተደምረው በፈጠሩት
ጫና የሀገረ መንግሥታት ኃይልና ሥልጣን እጅጉን አሽቆልቁሏል።
በዚህ ኑባሬ ውስጥ የወል እውነት መገንባት ታላቅ ፈተና ነው። የተለያዩ ቡድኖች
የየራሳቸውን እውነት በማራገብ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅ፣ ከመደጋገፍ ይልቅ መገፋፋትን
6
የህልውናቸው መሠረት አድርገው ስለሚወስዱ የውጥረት ፖለቲካ መለያቸው ነው። በዚህ
ውጥረት መካከል የወል እውነትን ግንባታ በፈተና ውስጥ የሚከወን ይሆናል።
በአዲሱ ዓለም የሚዲያ ዓይነቶችና ባለቤቶቹ በዝተዋል። ይህም ‹ሚዲያን የያዘ ኃይልን ያዘ
የሚለውን አባባል ከአንድ ኃይል እጅ አውጥቶ ወደ ብዙዎች እጅ እንዲገባ አደረገው። በዚህ
የተነሣም የአንድ ኃይል የበላይነት እያከተመ የኃይል መከፋፈል ተፈጥሯል። በመሆኑም ዛሬ
የሕዝብን አስተሳስብ የሚቀርጹ ብዙ ኃይሎች አሉ። ነገሩ እንደ መንግሥት የኃይል መሸርሸር
ሲፈጥር፣ እንደ ሕዝብ ደግሞ ግራ መጋባት የፈጠረ ዘመን ሆኗል። የመንግሥት ሥልጣን
ከሕዝብ በሚመነጭበት ሥርዓት ውስጥ፣ የሕዝቡን ሐሳብ የሚቀርጹ ኃይሎች መብዛታቸው፣
የወል እውነቶችን መገንባት እጅግ ከባድ እንዲሆን ያደርገዋል።
የድኅረ እውነት ፖለቲካ ሰዎች ከሐቅ ይልቅ በስሜት የሚመሩበት፣ ከእውነትና ከማስረጃ
ይልቅ ወሬን ማናፈስና ስሜትን መያዝ የበላይነት የያዘበት፣ እንዲሁም የሤራ ትንተና
የብዙዎችን ቀልብና አስተሳሰብ የሚገራበት ጊዜ ነው። በመሆኑም የድኅረ እውነት ፖለቲካ
እውነትን በውሸት የቀየረ ብቻ ተብሎ ሊበየን የሚችል ሳይሆን፣ ውስብስብ የአመለካከት፣
የአስተሳሰብና የባህሪ ለውጥን ያመጣ ኑባሬ ሆኗል። ይህ ኑባሬ እውነትንና ምክንያታዊነትን
7
በመያዝ ብቻ የሰውን ሐሳብና ዕይታ መቅረጽ የማይቻልበት፣ ከሐሳብ ጥራት ይልቅ
የሥርጭት ዐቅሙና ስሜት ኮርኳሪነቱ የበለጠ ተጽዕኖ የሚፈጥርበት ዓለም ነው።
ድኅረ እውነት ስንል የውሸት ዜና (fake news) ማለትም ያልተከሠተን ነገር ተከሥቷል ብሎ
መዘገብ፣ ፈጥሮ ማውራት እና ማጋነን፣ ሆን ተብሎ የተዛባ መረጃ ማቅረብ (dis-information)
የተለመደበትን ዘመን ነው። ሰዎች እውነታዉን እንዳያውቁ በማድረግ ውሸት፣ ሤራ እና
ፕሮፖጋንዳ በመንዛት በሌሎች ላይ ጉዳት እንዲደርስባቸው ማድረግ፣ የተሳሳተ መረጃ (mis-
information) ሆን ተብሎ ጉዳት ለማድረስ ሳይሆን ባለ ማወቅ የሚተላለፍ የሐሰት መረጃ
መልቀቅ፤ እንዲሁም ያልተገባ መረጃ( mal- infommation) ማለትም ሆን ተብሎ የሆነን
አካል ስም ለማጥፋት እውነትን ከውሸት ጋር እንደ መርዝ በመቀላቀል የሚደረግ ጎጂ ድርጊት
የሚካሄድበትን ዘመን ነው።
ዘመንን እንደ ዘመን ‹ድኅረ እውነት› ብሎ መፈረጅ በጣም አስደንጋጭ ነው። በዙሪያችንን
ያለውን ሁሉ ነገር እንድንጠራጠር የሚያደርግ እና ለትውልዱም አእምሮ እጅግ ከባድ አባባል
ነው። ይህ ማለት ግን በዘመናችን ምንም ዓይነት እውነት የለም፤ ወይም እውነትን የሚናገሩ
አካላት የሉም ለማለት ተፈልጎ አይደለም። ነገር ግን እንደ ማዕበል ከዓለም ጫፍ ወደ
ሌላኛው ጫፍ እውነትን እየደፈጠጠ ያለው ውሸት እና የሤራ ዜና መበራከት፣ ጊዜውን ድኅረ
እውነት አስብሎታል። ይህ የፈጠረው ደግሞ ብዙ የመረጃ ምንጮች በመኖራቸው ምክንያት
ሰዎች የትኛውን መረጃ ማመን እንዳለባቸው ስለሚቸገሩ ነው።
በድኅረ እውነት - ዓለም ውስጥ፣ ስለ እውነት የጋራ መሥፈሪያ፣ ልኬትና ብያኔ ማግኘት
አዳጋች ሆኗል። በእውነትና በአማራጭ እውነት፣ በዕውቀትና በአስተያየት፣ በእምነትና በሐቅ
መካከል ያሉ ዕይታዎች ዓለምን ግራ መጋባትና ወዥንብር ውስጥ ጥሏታል። በድኅረ እውነት
በተጠየቅ ያልተፈተሹና በሳይንሳዊ ሂደት ያልተረጋገጡ እውነቶች የሚሠራጩበትና በቀላሉ
የሰፊውን ሕዝብ አእምሮና ልቡና የሚማርኩበት ዕድል አግኝተዋል። በድኅረ እውነት
ከተጨባጭ እውነቶች ይልቅ የሰዎችን ስሜት የሚኮረኩሩ ንግግሮችና መረጃዎች ገዥና
ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆነዋል።
8
ምክንያት የጠፉ ሕዝቦች ታሪክ በብዛት ተጽፎ ይገኛል። ከጆን ኤፍ. ኬኔዲ እስከ ሩዋንዳ
የዘር ማጥፋት ወንጀል በዓለም ላይ የውሸት ዘገባ ብዙ ጉዳት አስከትሏል።
9
በዚህ ጉዳይ የተከናወኑ በርካታ ጥናቶች መፍትሔውን በአጭር ጊዜ እና በረጅም ጊዜ
ከፋፍሎ ማየት ጠቃሚ እንደሆነ ይገልጻሉ። አሠራጮች የሚያደርሱትን ጉዳት
የመጀመሪያው የአጭር ጊዜ የመፍትሔ መንገድ የሐሰት መረጃ በመመዘን፣ አስቸኳይ እና
አሳሳቢዎችን ቅድሚያ በመስጠት፣ አስፈላጊውን የመመከት እና የመልሶ ማጥቃት
ርምጃዎችን መውሰድ ነው። እንደ ዘለፋ፣ ቁም ነገር አዘል ቀልዶች፣ የተፈበረኩ መረጃዎች፣
ግነት የታከለበት መረጃ፤ የተዛባ ሪፖርት ፤ የዘር ማጥፋት፣ ብጥብጥ፣ ወደ ፀብ የሚገፋፉ
ሚዲያዎችን እና የሚዲያ ውጤቶችን በመለየት እንደየ ችግሩ አሳሳቢነት ደረጃ መስጠት
እና ፈጣን ርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል።
የሀገራችን ፖለቲካ አንዱ ጉድለት የጋራ አጀንዳን በመፍጠር ሕዝብን ለጋራ ግብ ማሰባሰብ
አለመቻሉ ነው። ከዚያ ይልቅ ዋልታ ረገጥነት እና እስከ ታችኛው ቅንጣት ድረስ መከፋፋል
የፖለቲካችን አንዱ ገጽታ ነው። ሁሉም ራሱን የእውነት ብቸኛ ባለቤት አድርጎ
ስለሚመለከት በተለያዩ አስተሳሰቦች፣ አመለካከቶችና ማንነቶች መካከል መስተጋብርን
አለመፍጠር እና የጋራ አጀንዳን ይዞ መታገል የፖለቲካችን አንዱ ትልቅ ክፍተት ሆኖ
ሲፈትነን ቆይቷል።
በሀገራት ፖለቲካ ዕድገት ውስጥ አንዱና ትልቁ ጥያቄ ልዩነት የሚስተናገድበት መንገድ
ምን ያህል የሠለጠነ ነው? የሚለው ነው። በየሀገራቱ የተለያዩ የአመለካከትና የማንነት
ልዩነቶች አሉ። ልዩነቶቹ የሚታዩበትና የሚስተናገዱበት መንገድ ለሀገራት ፖለቲካዊ
መረጋጋት እጅግ አስፈላጊ ነው። የሀገራችን የፖለቲካ ባህል ልዩነትን ከልክ በላይ ለጥጦ
የሚያይ እና ለማቀራረብም ምን ዓይነት በር ለመክፈት የማይሞክር ነው። አክራሪነት
ልዩነትን ያለ አግባብ ለጥጦ በመመልከት፣ ማናቸውንም ዓይነት ሌሎች ሐሳቦችን
ለማድመጥም ይሁን ለማክበር ፍላጎት የሌለው የፖለቲካ አካሄድ ነው።
አክራሪነት ሰፍኗል ልንል የምንችለው ሁለት ጉዳዮች መንታ ሆነው ሲመጡ ነው። አንዱ
ልዩነቶችን አላግባብ በመለጠጥ እውነት የእኔ ብቻ ነው በሚል ስለሌላው ያለው ዕይታ
ማቻቻል የሌለበት፤ የበላይነትን መፍጠር እና ማጥፋት የሚተልም ሲሆን ነው። ሁለተኛው
ደግሞ ሐሰት የሚሉትን ከእነርሱ ውጭ ያለውን አመለካከት ለማጥፋት ማንኛውንም ዓይነት
ኃይል እና ማጥቃትን እንደ መንገድ የሚጠቀም ሲሆን ነው። የእኛ እና የእነርሱ ወገን ብሎ
በመለየት የአንዱን ወገን በሌላው ላይ መቀስቀስ፣ ማነሣሣት እና ማስጠቃት እንደ
ማስፈጸሚያ መንገድ ይጠቀማል።
11
በሀገራችን አክራሪነት ዋነኛው የፖለቲካ ችግር እንደሆነ ለመጥቀስ ሁለቱ መገለጫዎችን
እንመለከታቸው። የሀገራችን ፖለቲካ ‹እውነት የእኔ ብቻ ነው› የሚል ዋልታ ረገጥ
አመለካከቶች የሰፈነበት ነው፡ ጫፍና ጫፍ ያሉ አመለካከቶችን ወደ አማካይና ወደ
አስታራቂው መሥመር ለመምጣት ፍላጎት የሌለው የፖለቲካ ምልከታና እና አካሄድ
የሀገራችን ፖለቲካ መገለጫ ነው። የማይታረቁ ልዩነቶች አሉ የሚለው ገዥ መርሑ ነው።
ለውይይት፣ ለክርክር እና ለመቀራረብ ቦታ አይሰጥም። የኔን ብቻ የሚተልም በመሆኑ
ጥቃቅን የቃላት ልዩነቶች ሳይቀሩ ጎልተው ይታያሉ። ይህን ተከተሎም መጠፋፋትን
መሠረት ያደረጉ ደም አፋሳሽ ግጭቶች ሀገራችንን ሲያቆራቁዙ ኖረዋል።
12
እየጨመረ የመጣው አክራሪነት ሁሉንም ነገር በማንነት መነጽር ውስጥ የሚዳኝ አድርጎታል።
ሁሉንም ነገር በብሔርና በሃይማኖት ሚዛን የሚያስቀምጠው ፖለቲካ፣ ለሐሳብ ውድድር
ክፍተትን አይሰጥም᎓᎓
የወል እውነት (የጋራ ግብ) መላላት፡- የጋራ ግብ የሕዝብን የጋራ ዕጣ ፈንታ የተሻለ ማድረግ
ነው። በአንድ ሀገር ውስጥ የሚኖር ሕዝብ የጋራ ዕጣ ፈንታ ይኖረዋል። ይህ የጋራ ዕጣ
ፈንታ በአንድ ሀገር ውስጥ የሚኖር ሕዝብ ባስቀመጠው ግብ እና በግቡ ዙሪያ ተሰባስቦ
ለስኬቱ በሠራው ሥራ ላይ ይንጠላጠላል። በኅብረትና በጥንካሬ በጋራ ግብ ዙሪያ የሠራ
ሕዝብ ነገውን የተሻለ ያደርጋል። ከዚህ በተቃራኒ ለጋራ ግብ በጋራ መቆም ካልተቻለ ዕጣ
ፈንታችን የከፋ ይሆናል።
አግላይ የሆነ የልዩነት ፖለቲካ በሰፈነበት ሥርዓት ውስጥ፣ ፖለቲካኞች ራሳቸውን በተናጠል
የአንድ ማንነት ተወካይ አድርገው ይቆጥራሉ። ሥልጣን የሚታየው የአንድ ብሔር፣
ሃይማኖት ወይም የሌሎች ማንነቶች ጉዳይ ማስፈጸሚያ ተደርጎ ነው። በመሆኑም ሁሉም
እወክለዋለሁ የሚሉትን አካል ተናጠላዊ ፍላጎት አስጠባቂ አድርጎ በሚወስድበት የፖለቲካ
ሥርዓት ውስጥ የጋራ ግብ ቦታ እያጣ ይመጣል። ሁሉም አነስ ሲል ግለሰባዊ ፍላጎቱን፣ ከፍ
ሲል ቡድናዊ ፍላጎቶችን የሚያስፈጽም እንጂ ለሀገራዊ ጉዳዮች ቁብ የሚስጥ አይሆንም።
ይልቁንም በሌሎች ፍላጎቶች ወይም በጋራ ፍላጎት ላይ ተንተርሶ ግለሰባዊና ቡድናዊ
ፍላጎትን ለማርካት ሩጫዎች ይበዛሉ።
13
ማኅበረሰባዊ ትሥሥር መላላትና አለመረጋጋት፡- አንድ የፖለቲካ ስርዓት የተለያዩ
የማህበረሰብ ክፍሎች ውቅር ነው። ጥቁር ነጭ፣ሀብታም ድኻው፣ ሴት ወንዱ፣ የተለያየ ብሔር
በአንድ ላይ የሚኖሩበት ነው። አንድን ሥርዓት ሥርዓት የሚያደርገውም በእነዚህ
ማኅበረሰቦች መካከል የሚኖር ትሥሥር ነው። አክራሪነት ልዩነትን በማጉላት በአንድ
ማኅበረሰብ ውስጥ ያለን ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ያናጋዋል።
ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በር መክፈት፡- እጅግ አደገኛው ውጤት ሀገራችንን ለውጭ
የፖለቲካ ነጋዴዎች አሳልፎ መስጠቱ ነው። በኢኮኖሚያዊም ይሁን በፖለቲካዊ ዐቅም
ጠንካራ የሆኑ ሀገራት በሀገራችን ፖለቲካ ውስጥ በረቀቀ መንገድ ገብተው የፖለቲካ ገበያውን
ለመዘወር ዕድል ያገኛሉ።
15
የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ዋነኛ ፈተና ሥር የሰደደ ድህነት ከሚፈጥረው አዙሪት
የሚመነጭ ነው። ድህነት የሀገራችንን ህልውና ለሚፈትኑ ከውስጥና ከውጪ ለሚነሡ
ጫናዎች ይዳርጋል። በሀገራችን የውጭ ተጽዕኖዎች እንዲያይሉ፣ የብሔርና የሃይማኖት
ግጭት ዘላቂ መፍትሔ እንዳያገኝ እንዲሁም የተረጋጋ የሀገር ግንባታ እንዳይኖር ትልቅ
ተግዳሮት ሆኖ ለዘመናት የዘለቀው ድህነትና ኋላ ቀርነት ነው። ኢትዮጵያ ከዓለም ድኻ
ሀገሮች ተርታ የምትሰለፍ ናት። ይህ ድህነት ጠንካራ ተቋማትን ለመገንባት እንዳትችል
አድርጓታል። ድህነት፣ ሥራ አጥነት እና በቂ የመሠረተ ልማት አውታሮች አለመሟላት
በሀገራችን በቂ የመንግሥት ሥርዓት ግንባታ እንዳይኖር አስተዋጽዖ የሚያደርጉ ናቸው።
ሕዝቡ ካለበት ድህነት ወጥቶ ወደ ዕድገት እንዳያመራ ራሱን ችሎ የሚቆም መንግሥት
ያስፈልገዋል። ድህነት ተደጋፊ መንግሥት እንዲኖር የበኩሉን ድርሻ ይወስዳል።
16
ሥራዎች ካልተሠሩና ወጣቶች ተስፋቸው ካልለመለመ ወደ ጥፋት ኃይልነት ለመቀየር
ቅርብ ናቸው።
ያለፉት አራት እና አምስት ዓመታት በኮቪድ ወረርሽኝ፣ በዓለም አቀፉ ውጥረት፣ እንዲሁም
በሰሜኑ ጦርነት ውስጥ ብታልፍም፣ ኢትዮጵያ ከየትኞቹም የአፍሪካ ሀገራት የተሻለ
የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግባለች። በዚህ የዕድገት ጉዞ ውስጥ ወጣቶችን ፈጠራ በታከለበት
መልኩ በማሳተፍ፣ የዕድገት ምጣኔውንና ፍጥነቱን እንዲጨምሩት በማድረግ፣ ወጣቶችን
ከጥፋት ጎዳና ማዳን ይገባናል። የመንግሥትና የግል ዘርፉን ትብብር በማሳደግ በበለጸገች
ኢትዮጵያ ውስጥ የወጣቶች ቦታ እንደቁጥራቸው መጠን እንዲሆን መሥራት ይገባናል።
የተጀመሩ ልማቶችን በየክልሉ በማስፋፋት እና አንዱን ክልል ከሌላኛው ጋር የጥቅም
ትሥሥር እንዲፈጥር በማስቻል፣ ሁሉም ክልሎች ተቀራራቢ የሆነ ዕድገት እንዲኖራቸው
መሥራት ይገባል።
ይህም ሲባል ነጻ፣ ገለልተኛና ጠንካራ ተቋማት ለመገንባት አሁንም ሰፊ ሥራን ይጠይቃል
ማለት ነው። በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያሉ መግባባቶች፣ መጻኢውን ትውልድ
17
በኢትዮጵያዊነት የመቀረጽና የማነጽ እንዲሁም የጋራ ማንነትን የመፍጠር ሥራ አሁንም
ትልቅ ጥያቄ ነው። በተጨማሪም የፖለቲካ ሥርዓቱን የጨዋታ ሕግጋት ሰላማዊ፣ መርሕ
ተኮር፣ በሐሳብ የበላይነት ላይ የተመሠረተ እና ዴሞክራሲያዊ የማድረግ ሥራ ገና በጅምር
ላይ የሚገኝ ነው። ከድህነት ተላቅቀን ትርጉም ያለው ሕይወትን የሚያጣጥም የበለጸገ
ማኅበረሰብ የመፍጠር ትልማችን ብዙ ርቀት መጓዝን ይጠይቃል።
በሀገራችን የፖለቲካ ኃይሎች መካከል በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ማለትም በታሪክ፣ በሕገ
መንግሥት፣ በሰንደቅ ዓላማ፣ በፌደራሊዝም፣ በወሰንና በማንነት፣ ወዘተ. ጉዳዮች ዙሪያ
መግባባት የለም። በመሆኑም ጠንካራ የፖለቲካ ሥርዓት በሀገራችን ዘላቂ፣ አስተማማኝና
አለመገንባቱ ብቻ ሳይሆን የሀገራችን ህልውናም አደጋ ውስጥ እንዲገባ ሆኗል። ስለዚህም
ይሄንን መሠረታዊ ችግር ለመፍታት ዕርቀ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር
መንግሥትና ፓርቲያችን በድኅረ ምርጫ ለእነዚህ ጉዳዮች ትኩረት በመስጠት እንደሚሠራ
አቅጣጫ ተቀምጧል።
18
በጥቅሉ የሀገር ግንባታ እና መጠናከር የብዙ ነገሮች ድምር ውጤት ነው። ሀገርን ለማጠናከር
የሚደረገው ጥረት ለዘመናት ሥር የሰደዱ ችግሮችን እና ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም አቀፍ
ሁኔታ የሚፈጠሩ ፈተናዎችን መመከትን ይጠይቃል። ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ
አዝማሚዎች የሚፈጥሩትን ዕድል ለመጠቀምና ተግዳሮቶችን ለመግታት፣ ተቋማትን
ለመገንባት፣ ብሔራዊ መግባባትን ለማስፈን፣ ዴሞክራሲን ለማጎልበትና ብልጽግናን
ለማረጋግጥ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል።
19
ክፍል ሁለት
በሀገራችን እንዴት ይሄ ኖሮን እንዴት በዚህ ችግር ውስጥ ልንገኝ እንችላለን? የሚሉ
ጥያቄዎች በዝተው ይነሣሉ። ለዚህም ዋነኛው ችግር ዐቅሞቻችንን የምንጠቀምባቸውና እና
ችግሮቻችን የምንፈታባቸው አዳዲስ ሐሳቦችን የማመንጨት እና የማደረግ ክፍተት መኖሩ
ነው። ችግሮችንን የምንፈታበት መንገድ አዲስነት እና ፍጥነት የሚጎድለው በመሆኑ ለረዥም
ጊዜ ከችግሮች ሳንላቀቅ ኖረናል። ከችግር ለመላቀቅና የሕዝብን ሐሴት የሚፈጠር ዕሴት
ለመፍጠር ያደረግነው ጥረት ፈጠራና ፍጥነት የሚጎድለው ሲሆን ችግር ፈቺ አዳዲስ
ሐሳቦችን ባለማምጣታችን እና ችግሮቻችንን ለመፍታት በፍጥነት ባለመጓዛችን ወደ ኋላ
ቀርተናል። ችግሮች በችግሮች ላይ እየተደራረቡ ከአንድ የዕድገት ደረጃ ወደ ሌላ የዕድገት
ደረጃ ሳንሸጋገር ከችግሮቻችን እና ከዓለም ኋላ ቀርተናል።
20
በአንድ በኩል ተደራራቢ የሆኑ ችግሮችን እየመለሱ፣ በሌላ በኩል ከዓለም የፖለቲካ እና
የኢኮኖሚ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ እየሆኑ ለመሄድ የሚያስችል ፍጥነት ያስፈልገናል።
ፈጠራ ፈጠራ ከችግሮቻችን መላቀቅ እንድንችል የሚያደረግ መሻሻል ለማምጣት እንዲሁም
በዓለም ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት የሚያስችል ዕድል ይሰጠናል። ፈጠራና ፍጥነት
ውዝፍ ችግሮችን ለመቅረፍ እና በለውጥ ውስጥ የሚፈጠሩ አዳዲስ ፈተናዎችን ለመቋቋም፤
ዕምቅ ዐቅሞችን እና በነባራዊ ሁኔታ ውስጥ የሚከፈቱ ዕድሎችን መጠቀም የሚያስችል ነው።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ መዘግየት ብልጽግናን ለማረጋገጥ ያለንን ውሱን ሀብትና ጊዜ እንዲባክን
እና ዓለም አቀፍ ጫናዎች እንዲበረቱ ያደርጋል። በመዘግየታችን ሀገራችንን ለመለወጥ እና
የተሻለ የብልጽግና ደረጃ ላይ ለማስቀመጥ የሚያስችሉ ብዙ ዕድሎች መክነዋል። በዚያው
ልክ ብዙ ችግሮች እየተወሳሰቡ እና እየጠነከሩ መጥተዋል። ጫናዎችም በርትተዋል።
አንዳንዴ በሀገራችን ትልልቅ ሐሳቦች እና አጓጊ ውጥኖች ቢነሡም እነዚህን ውጥኖች
ለማሳካት አንፈጥንም። ይህ አዝጋሚ ጉዟችን ከሐሳቦቹ ውጤት እና ከጅምሮቹ ፍጻሜ
ሳንደርስ ባክነን እንድንቀር ያደርገናል። አልያም ብዙ ፈተና ይበዛብናል።
ለአዝጋሚ ጉዟችን አንዱ ማሳያ የሕዳሴ ግድብ ግንባታችን ነው። የሕዳሴ ግድብ ትልቅ
ውጥን እና ሐሳብ ቢሆንም በአዝጋሚ ጉዟችን ምክንያት ብዙ ፈተናዎች ውስጥ ገብቷል።
የሕዳሴ ግድብ ከተጀመረ _ ጀምሮ ያሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች በግድቡ ላይ ያሳረፉት ጫና
ቀላል አይደለም። ከሚገባው በላይ በመዘግየቱ የተነሣ የዋጋ ጭማሪ ፈትኖናል፤ ዓለም አቀፍ
ፖለቲካው ተቀያይሯል፤ ለዲፕሎማሲያዊ ጫና እንድንጋለጥ አድርጎናል፤ የዓለም የኢኮኖሚ
ፈተና ጨምሯል።
ፈጠራና ፍጥነት በሰው ልጆች ውስጥ ያሉ ዕምቅ ዐቅሞች ናቸው። በየተሠማራንበት መስክ
እነዚህን ዕምቅ ዐቅሞችን ወደ ተግባር ከቀየርን ዕጣ ፈንታችንን ራሳችን እንድንጽፍ
21
ያስችሉናል። በፓርቲና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ፈጠራና ፍጥነት እንደ ግልና እንደ
ቡድን ምን ያክል አለን? ለአንድ ራእይ የተሰለፉ ባለ ራእዮች ወደ ራእያቸው ለመድረስ
ፍጥነትና ፈጠራ ያስፈልጋቸዋል። ፍጥነት በውስጡ ጊዜና ርቀትን ይይዛል። ከታለመው
ርቀት(ራእይ) በጊዜ ለመድረስ ፈጠራ ያስፈልጋል። ፈጠራ በእግር ከመሄድ በፈረስ፤ ከፈረስ
ወደ ሳይክል፣ ከሳይክል ወደ መኪና፣ ከመኪና ወደ ፈጣን ባቡር፣ ከእነዚህ በበለጠ ፍጥነት
ለመጓዝና ካሰብንበት ለመድረስ አውሮፕላን የበለጠ አማራጭ ነው::
ፈጠራ ከራእያችን ለመድረስ አማራጭ የሚያቀርብ መሣሪያ ነው። በርካታ የፈጠራ ሐሳብ
ኖሮ የአድራሹ ፍጥነት ከዘገየ ፈጠራዎቹ ከመዳረሻቸው ሳይደርሱ በሌላ ይተካሉ። እያዘገሙ
ፈጠራን መተግበር በጦርነት መሐል ፈረስን እንደ መቀየር ነው። የሚያስከትለው አደጋ
የሕይወት እንደሆነ ሁሉ መዘግየት ከመድረስ ጋር ፍጹም የራቀ እንደገና እንደ መጀመር
ነው። ለዚህ ነው እንደ ግለሰብም እንደ ሀገርም አንድ ጊዜ ያደናቀፈን ድንጋይ፣ ሺ ጊዜ
የሚደጋግመን።
ቃልን ማጠፍ በማንኛውም ኅብረተሰብ ውስጥ እምነትን የሚሸረሽር፣ እንደ ከሐዲ የሚያስቆጥርና
የፖለቲካ ባሕልን የሚጎዳ ጉዳይ ነው። ቃላቸውን የሚያጥፉ ፖለቲከኞች በበዙበት ሀገር _ ውስጥ፣
ዜጎች _ እምነታቸውን ሰጥተው የሚያዳምጡት፣ የሚመርጡትና የሚደግፉት ፖለቲከኛ ወይም
የፖለቲካ ፓርቲ ማግኘት ፈታኝ ነው። በዚህ ሁኔታ ደግሞ የውክልና ዴሞክራሲን መገንባትና
ማጽናት ዴሞክራሲን የተላመጠ የሸንኮራ አገዳ ያደርገዋል፤ ጣዕሙን ያጣ ባዶ እንጨት።
ዴሞክራሲ ማለት የሕዝብ አስተዳደር በመሆኑ የሕዝብን ቃል የሚበሉ ፖለቲከኞች ባለበትና
የውክልና ውሉ በፈረሰበት ሁኔታ ሕዝብ ራሱን በራሱ አስተዳደረ ሊባል አይችልም።
የምርጫ ቃል ኪዳንን በመጠበቅ ረገድ አራት የቢሆን ሁኔታዎች ሊከሠቱ ይችላሉ። አንደኛው
የቢሆን ሁኔታ ቃልን ጠብቆ በአፈጻጸም ግን ዝቅተኛ መሆን ነው። ይህ ሁኔታ የፖለቲከኞችን
የመፈጸም ፍላጎትና ለቃላቸው ያላቸውን ታማኝነት የሚያሳይ ቢሆንም ቃላቸውን ግን መፈጸም
አለመቻላቸውን ያመለክታል። ለሕዝቡ የገቡትን ቃልና የፖሊሲ አቅጣጫ ቢከተሉም በውጤቱ
ግን አስፈላጊውን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ግብ ማሳካት ሳይችሉ ሲቀሩ የሚከሠት የቢሆን ሁኔታ
ነው። ሁለተኛው የቢሆን ሁኔታ ቃላቸውን አጥፈውና ከቃላቸው ውጭ ሌላ የፖሊሲ አቅጣጫና
አስተሳሰብ ተከትለው፣ ነገር ግን በተግባራዊ አፈጻጸማቸው ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ስኬት
ሲያስመዘግቡ የሚከሠት ነው። በዚህኛው የቢሆን ሁኔታ፣ ፖለቲከኞች በእነርሱ ጥንካሬም ይሁን
በተለያዩ ውጫዊ ምክንያቶች ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዕድገት ቢያስመዘግቡም፣ የተከተሉት
መንገድ ግን ለሕዝቡ ከገቡት ቃል የተለየ ነው። ሦስተኛው የቢሆን ሁኔታ ቃላቸውን አጥፈው፣
በአፈጻጸማቸውም ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማስመዝገብ ሳይችሉ ሲቀሩ የሚከሠት ነው።
23
ክፍል ሦስት
የአንድ ማኅበረሰብ ዕድገትና ለውጥ ማኅበረሰቡ ባለው ዕምቅ ዐቅምና በፈጠረው ሥርዓት
ላይ ይመሠረታል። ትላልቅ ሥልጣኔዎች የተፈጠሩት እነዚህ ዕምቅ ዐቅሞች ባሉበት አካባቢ
ሰዎች ተሰባስበው ዕምቅ ዐቅሞችን በሰላም እና የራሳቸውን ፍላጎት ለማሳካት በሚያስችል
መልኩ ለመጠቀም በፈጠሩት ሥርዓት ነው። ማኅበረሰቦች ለማደግና ለመለወጥ ሁለቱ ድምር
ነገሮች እጅግ አስፈላጊ ሲሆን ከሁለት አንዱ በተጓደሉባቸው አካባቢዎች ዕድገት ፈታኝ
ነው። አያሌ የአፍሪካ ሀገሮች ብዙ ዕምቅ ዐቅም አሏቸው። ነገር ግን የፈጠሩት ሥርዓት
ዕምቅ ዐቅሞቹን ተጠቅሞ ፈጣን እና ቀጣይነት ያለው ዕድገት እንዲሁም ፍትሐዊ
ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አልቻለም። በመሆኑም የአፍሪካ ሕዝቦች በሀብት ላይ ተኝተው
የሚራቡ እና በብዙ ችግሮች ውስጥ የሚሰቃዩ ናቸው። በሌላ በኩል ዕምቅ ዐቅም እምብዛም
የሌላቸው ወይም ለዕድገት ምቹ ባልሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ ማኅበረሰቦች ለማደግ እጅግ
ፈታኝ ሁኔታ እንደሚያጋጥማቸው የታወቀ ነው።
ሁለተኛው ለውጥ ፍጥነት ነው። በፍጥነት ማሰብ፣ በቶሎ መተግበር እና ማጠናቀቅ የሥራዎች
ዋና ገጽታ ነው። ትላልቅ ሐሳቦች በፍጥነት ተተግብረው እና እውን ሆነው ሀብት ማመንጨት
ሲጀምሩ ማየት እየተለመደ ነው። ይህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ውጤቶችን ለማስመዝግብ
ዕድል የሰጠ ነው። አረንጓዴ ዐሻራ፣ ሸገርን ማስዋብ፣ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር፣ የሕዳሴ
ግድብ እና መሰል ስኬቶች ከፍ ያለ ሐሳብን በፍጥነት የመከወን ውጤቶች ናቸው።
25
ከነበረበት 2.2 ትሪልዮን ብር በ2014 በጀት ዓመት ወደ 6.2 ትሪልዮን ብር እንዲያድግ
ለማድረግ ተችሏል።
ለጠቅላላ የምርት ዕድገቱ የግብርና ዘርፍ በአማካይ የ33 በመቶ ድርሻ ነበረው። ከዚህም
ውስጥ የዋና ዋና ሰብሎች ንዑስ ዘርፍ 65.4 በመቶ የሚሆነውን ድርሻ ይይዛል። የኢንዱስትሪ
ዘርፉም በአማካይ የ28 _ በመቶ ድርሻ አለው። ለዚህም የኮንስትራክሽን እና የማኑፋክቸሪንግ
ንዑስ ዘርፎች በቅደም ተከተል የ66 በመቶ እና የ19 በመቶ ድርሻ ነበራቸው። በሌላ በኩል
የአገልግሎት ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት የ39 በመቶ ድርሻ ያለው ሲሆን፣ ከዚህም
ውስጥ የጅምላና የችርቻሮ ንግድ ንዑስ ዘርፍ 35 በመቶ ድርሻ ይይዛል። ይህም ማለት
የምርት ዕድገታችን በሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች እንደተመዘገበ ያመለክታል። በውሱን
ዘርፎች ጥገኛ ከመሆን ወደ ብዝኃ ዘርፍ ያደረገነው ሽግግር ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ
እንደሆነም ያሳየናል።
ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ ግብር ዋና ዋና የማክሮ
ኢኮኖሚ ማነቆዎቹን ለመለየት ተችሏል። ማነቆዎቹን ለመፍታት የሚያስፈልጉ የፖሊሲ
አቅጣጫዎችን በማመላከት ሰፊ ርብርቦች ሲደረጉ ቆይቷል። በተጨማሪም በዐሥር ዓመቱ
የልማት ዕቅድ ኢኮኖሚውን ከረዥም ጊዜ ዕይታ አኳያ በመቃኘት ብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ
ዕድገት ስትራቴጂን ተከትለናል። የግብርናና የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪን ጨምሮ ማዕድን፣
ቱሪዝምና የከተማን ዕድገት መሠረት ያደረገ የአይ.ሲ.ቲ. ዘርፍ እንደ ተጨማሪ የዕድገት እና
የሥራ ዕድል ምንጮች ተለይተዋል። በዚህም የኢኮኖሚ ዕድገቱን ከአንድ የገቢና የዕድገት
ምንጭ ይልቅ በብዝኃ ዘርፍ የዕድገት ምንጮች ላይ የተመሠረተ እንዲሆን አቅጣጫ ተቀምጦ
ሥራዎች ተሠርተዋል፤ እየተሠሩም ይገኛሉ።
በዚህም እንደ ሀገር ከገጠሙን በተጨማሪ እንደ አንድ የዓለም ማኅበረሰብ የተጋፈጥናቸውን
የተለያዩ ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ ኢኮኖሚው ባለፉት አራት ዓመታት በአማካይ በ7.1
በመቶ ዕድገት አስመዝገቧል። ለዚህም ዕድገት ግብርና በ4.6 በመቶ የኢንዱስትሪ ዘርፍ
በ9.4 በመቶ እንዲሁም የአገልግሎት ዘርፉ በ7.8 በመቶ በአማካይ አድጓል። ከግብርናው
ክፍለ ኢኮኖሚ ንዑስ ዘርፎች መካከል የዋና ዋና ሰብል ምርትና ምርታማነት ለዘርፉ ዕድገት
ከፍ ያለ አስተዋጽዖ አበርክቷል። _ በባለፉት አምስት ዓመታት አጠቃላይ ኢኮኖሚው
ላስመዘገበው ዕድገት በአማካይ ግብርና የ16.2 በመቶ ድርሻ ነበረው። ሌላው ከግብርና
ዘርፎች ውስጥ የሚጠቀሰው የእንስሳት ልማት ንዑስ ዘርፍ ሲሆን ይህም ለአጠቃላይ
ኢኮኖሚው ዕድገት የ5.2 በመቶ ድርሻ አስተዋጽዖ አድርጓል።
26
የኢኮኖሚ ሥርዓታችን ወደ ብዝኃ ዘርፍ በመቀየሩ ሁሉንም የምርታማነት ዘርፎች
የኢኮኖሚው ጥቅል ምርታማት እና የኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት እንዲሆኑ አድርገናል። ይህ
የአስተሳሰብ ለውጥ ቀላል አይደለም። በነጠላ ቡድናዊ ተጠቃሚነት የበላይነት ሲዘወር
የነበረን ኢኮኖሚ፣ ለሁሉም ፍትሐዊ እና እኩል ተጠቃሚነትን እንዲያረጋግጥ ለማድረግ
ታግለናል።
ፓርቲያችን ይህን የአስተሳሰብ ፓራዳይም የሚቀይር አዲስ ታሪክ ጽፏል። ከገጠመን ችግር
ተነሥተን ችግርን እንደ ዕድል ተጠቅመን በአምስት ዓመት ውስጥ ጥቅል ሀገራዊ የምርት
ዕድገትን 6.2 ትሪልዮን ብር ለማድረስ ተችሏል። ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት በአማካይ 7.1
በመቶ ዕድገት ተመዝግቧል። በዓመት ለሁለት ጊዜ ከማምረት በላይ ስንዴን ወደ ወጭ
መላክ ተችሏል። ከሃምሳ ዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ምንም ዓይነት የውጭ ምንዛሬ
ለስንዴ ግዢ ሳናውል ቀርተናል። እንዲያውም በተቃራኒው ከስንዴ ምርት የውጭ ምንዛሬ
ወዳገኘንበት አዲስ ምእራፍ ላይ ደርሰናል።
የኢኮኖሚ ዕድገታችን በቀጣዮቹ ዐሥር ዓመታት ውስጥ ከአፍሪካ አምስት ጠንካራ ኢኮኖሚ
ካላቸው ሀገራት ተርታ የሚሰለፍ እንዲሆን ፓርቲያችን በመሥራት ላይ ነው። ዓለም አቀፉ
የገንዘብ ተቋም አይ.ኤም.ኤፍ. ባወጣው የ2023 የኢኮኖሚ ምጣኔያዊ ሪፖርት መሠረት
የሀገራችን GDP 156.08 ቢልዮን ዶላር ይሆናል። በዚህም ከአፍሪካ አምስተኛ ከፍተኛ
ኢኮኖሚ፤ ከምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚው ኢኮኖሚ፤ እንዲሁም ከዓለም ሃምሳ ዘጠኛ ደረጃ ያየዘ
ግዙፍ ኢኮኖሚ ሆኗል። ይህ ውጤት በውስጣዊ እና በውጫዊ ጫናዎች፤ በሰው ሠራሽ እና
በተፈጥሯዊ ፈተናዎች ሳንበገር በጽናት በመትጋት ፓርቲያችን ያስመዘገበው ውጤት ነው።
የአስተሳሰብ ውጤታችንንም ፍሬ ያየንበት ድል ነው።
27
ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝባችን የነፍስ ወከፍ ገቢ በአማካይ በ 38 በመቶ ጨምሯል።
በ2010 በጀት ዓመት ከነበረበት 882 የአሜሪካን ዶላር በ2014 በጀት ዓመት ወደ 1,218
የአሜሪካን ዶላር ደርሷል። በሀገር ውስጥ ብር ሲገለጽ በ157 በመቶ በመጨመር በ2010
በጀት ዓመት ከነበረበት 23,038 ብር፣ በ2014 በጀት ዓመት ወደ 59,169 ብር ደርሷል። ይህ
ውጤት የወል ውጤት የወል ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በፍትሐዊነት መታየት መጀመሩን
ያየንበት ነው። የኢኮኖሚ ፖሊሲያችን ሁለንተናዊ የወል እውነታችንን የሚያረጋግጥ መሆኑን
በውጤት የተገለጠበት ተጨባጭ ማሳያ ነው።
የውጭ ንግድ ባለፉት 5 የለውጥ ዓመታት ትልቅ እመርታ ከታየባቸው ዘርፎች ውስጥ
በዋነኝነት ይጠቀሳል። የሸቀጦች የወጪ ንግድ በ2010 በጀት ዓመት ከነበረበት 2.84 ቢልዮን
ዶላር በ2014 ወደ 4.1 ቢልዮን ዶላር ደርሷል። ይህም ከ2010 በጀት ዓመት በፊት በነበሩት
5 ተከታታይ ዓመታት ቅናሽ ሲያሳይ ከነበረበት በመነሣት መሆኑ አፈጻጸሙን የላቀ
ያደርገዋል። በተለይም የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ በተደረገባቸው ባለፉት 3
ዓመታት የሸቀጦች ወጪ ንግድ አፈጻጸም በአማካይ 136 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
በዚህ በጀት ዓመት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ የግድቡን ግራና ቀኝ 634 ሜትር ከባሕር
ጠለል በላይ ለማድረስ ታቅዷል። የግድቡን መካከለኛ አካል ከባሕር ጠለል በላይ ወደ 620
ሜትር ለማድረስ ታቅዶ እየተሠራ ነው። ከቀሪ ዩኒቶች በቀጣይ ዓመት ቢያንስ በ5
ጄነሬተሮች ኃይል ለማመንጨትን የተርባይኖች እና የጀነሬተሮች ተከላ እየተከናወነ
ይገኛል። በአጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 66.2 በመቶ (ከለዉጡ በፊት) ከነበረበት ወደ
90.7 በመቶ ከፍ ብሎ ኃይል ለማመንጨት ተደርሷል። የግድቡም ሥራ በመጪዉ ዓመት
እንዲጠናቀቅ እየተሠራ ነው። 13ቱም ጀነሬተሮች በ2017 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀዉ በሙሉ
ዐቅማቸዉ ኃይል የሚያመነጩበት ደረጃ ላይ ይደርሳሉ። በዚህም ፕሮጀክቱን በድል
ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየሠራን እንገኛለን።
የሸቀጦች የወጪ ንግድ አፈጻጸም በ2015 በጀት ዓመት ስድስት ወራት 2.285 ቢልዮን
የአሜሪካ ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 1.76 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል።
ይሄም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 7 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል። ከግብርና
ምርቶች 1,607 ሚልዮን ዶላር ታቅዶ 1,359.78 (84.59 በመቶ) ሚልዮን ዶላር ተገኝቷል።
ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 36.34 ሚልዮን ዶላር ጭማሪ
አሳይቷል። በሌላ በኩል ከማኑፋክቸሪንግ ምርቶች 308.89 ሚልዮን ዶላር ታቅዶ 227,61
ሚልዮን ዶላር ተገኝቷል። ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 10.65
(4.89 በመቶ) ሚልዮን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል። በተመሳሳይ ከማዕድን ምርቶች 324.67
ሚልዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 116.54 ሚልዮን ዶላር ተገኝቷል። ከባለፈው ዓመት
ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘው 28152 ሚልዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር 164,97 ቅናሽ አሳይቷል።
በማኅበራዊ ልማት ዘርፍ በተለይም በትምህርት ዘርፍ የተሠሩ ሥራዎች ነገን አመላካች
ናቸው። ባለፈው ዓመት የተመዘገበው አስደንጋጭ የ12ኛ ክፍል የማጠናቀቂያ ውጤት
የዘርፉን ስብራት አሳይቶናል። በቀጣይ ውጤታማ ትውልድ የሚያፈራ እንዲሆን አዲሱን
የትምህርት ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ የትምህርት ዘርፉ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ወሳኝ
የሆነውን ምክንያታዊ ትውልድ የሚያፈራ ተቋም እንዲሆን ተደርጎ እየተሠራበት ይገኛል።
ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንጻር በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለ1.83 ሚልዮን ዜጎች ቋሚ
29
የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ለ1,49 ሚልዮን ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።
ይሄም የዕቅዱ 81 በመቶ ነው።
ዕድገት ሲመዘገብ ጉድለት ሁሌም ከጎን ይኖራል። በመሆኑም የዋጋ ንረትን እና የኑሮ
ውድነትን ለማርገብ ብዙ ሥራዎች ቢሠሩም ለማስቀጠል በዋጋ ፈተናነቱ ገና አልቀነሰም።
ሁለንተናዊ ዕድገቱን ማረጋጋት ላይ በትኩረት መሥራት ይጠበቅብናል።
የተናጠል ቡድናዊ እውነት ይዞ የተነሣ ኃይል የቡድኑን እውነት ልክነት ለማሳየት ካመነበት
እውነት በተቃራኒ በቆሙ ኃይሎች ላይ ሁሉንም የማስተግበሪያ ዐቅሞች ተጠቅሞ በኃይል
ይጭናል። በጊዜ ሂደት ያላመነበት እውነት በላዩ ላይ የተጫነበት ቡድን ደግሞ የራሱን
የተናጠል እውነት ገዥ እውነት ለማድረግ ትግል ያደርጋል። ይህ ዓለም ላይ የምናየው
ተጨባጭ እውነት ነው። በምድራችን ላይ የተደረጉ እልፍ ጦርነቶች የተናጠል እውነትን
30
ልክነት በአሸናፊነት ለማጽናት የተደረጉ ናቸው። የተናጠል ቡድናዊ እውነት የቡድኑን
ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ እውነቶችን ለማሳካት በሚደረግ ትግል፣ በተናጠል
ቡድናዊ ፍላጎት ልኬት የበላይነት የሚቃኝ ነው። ይሄውም ከህገር እስከ ዓለም ሥርዓታዊ
የበላይነት ድረስ ሊይዝ ይችላል።
31
አዲስ ሥርአት ለመገንባት ያለመ ነው። በዚህም በጅምር ላይ ያለውን የሀገረ መንግሥት
ግንባታ ሂደት ዳር በማድረስ፣ ለመጪው ትውልድ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የወል እውነት
ገዥ የሆነባት ሀገር ማስረከብ ነው።
32
3.2.1 የወል እውነቶችን የማጽናት ፖለቲካዊ እመርታችን
ከቀደምት ነገሥታት እስከ ቅርብ ጊዜዎቹ የሀገራችን የፖለቲካ ሥርዓቶች ድረስ የነጠላ
ቡድናዊ እውነቶች የበላይነት ዓይነተኛ መገለጫቸው ነው። የሺ ዘመናት የሀገረ መንግሥት
ታሪክ ቢኖረንም የፖለቲካ ሥርዓቶቻችን በነጠላ ቡድናዊ እውነቶች ዕሳቤ ላይ ብቻ
በመመራታቸው፤ ከነጠላ ቡድን ወደ ሌላ ነጠላ ቡድን የፖለቲካ የበላይነት በሚደረግ ሽግግር፤
የወል እውነቶች የሚገባቸውን ቦታ በፖለቲካ ሥርዓቶቹ አላገኙም። በዚህም ምክንያት ቀድሞ
መጠናቀቅ የነበረበት የሀገረ መንግሥት ግንባታችን ሳይጠናቀቅ ዛሬ ላይ ደርሷል። ይህ
ክሥተት ከዓለም ቀዳሚ ሥልጣኔዎች ውስጥ ተጠቃሽ ለሆነችው ሀገራችን የማይመጥን፤
ከሥልጣኔ ፈር ቀዳጅነት እና ከነጻነት ቀንዲልነት ታሪካችን ጋር የማይጣጣም ነው። ታላቋን
ሀገር በአግባቡ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ዑደቷን ያላጠናቀቀች ሀገር እንድትሆን
አድርጓታል።
ሐሳብ ሽጠው ፖለቲካዊ ሥልጣን ማግኘት ያልቻሉ የነጠላ ቡድናዊ ፍላጎት አቀንቃኞች፣
ከዴሞክራሲያዊ መንገድ ባፈነገጠ መልኩ፤ ጅምሩን የፖለቲካ ጉዟችንን ወደ ኋላ የሚመልስ
ተግባር ላይ ሲረባረቡ ይስተዋላሉ። ይህም የጥላቻ እና የፍረጃ ፖለቲካን ተጠቅመው ሥልጣን
ለመቆናጠጥ የሚያደርጉት ሩጫ ነው። የጥላቻ ፖለቲካ ከግለሰብ እስከ ማኅበረሰብ ይረጫል።
በዚህ የጥላቻ ፖለቲካ ዘመቻ አይነኬ የሚባሉ ማኅበረሰባዊ የሞራል ዕሴቶች ጭምር
በአደባባይ እንዲዋረዱ ይደረጋሉ። ጥላቻው ከፖለቲካኛው አልፎ የሕዝብ አጀንዳ ሆኖ
እልቂት እንዲፈጠር በብርቱ ይሠራል። ጥፋቱን ያቀጣጠሉት ዳር ሆነው እሳቱን እየሞቁ
የድኻውን ልጅ ማግደው ሥልጣን ለማግኘት ይቋምጣሉ።
በሕጋዊ መንገድ ሥልጣን ማግኘት ያልቻሉ የነጠላ ቡድን ፍላጎት አስፈጻሚዎች እንችላለን
ያሉት በጦርነት አሸንፈው ሥልጣን ለማግኘት ሞክረው አልቻሉም። የጥላቻ ፖለቲካ
አራምደው ሥልጣን ለመያዝ እየሞከሩ ያሉ ኃይሎች ደግሞ እጅግ አደገኛ እና አክሳሪውን
መንገድ መርጠው እየሠሩ ይገኛሉ። ድል ቀንቷቸው ባይችሉ እንኳን ወደ ሕዝብ እየወረደ
ያለው ሥልጣን ለማግኘት የጥላቻ መርዝ ወደተግባር ተቀይሮ ጥፋት ሊያደርስ የሚችልበት
ዕድል ዝግ አይደለም። በመሆኑም ፓርቲያችን ይህን አደገኛ አካሄድ በብስለት በማስተዳደር
መርዙን የማርከስ (ኖርማላይዝ የማድረግ) ቁልፍ ተግባር ይጠብቀዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት የዘመናት የሕዝቦች ፍላጎት የነበረውን ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ
ዴሞክራሲያዊ መብት በሚገባ ለማስተናገድ ፓርቲያችን ብዙ ሥራ ሠርቷል፤ እየሠራም _
33
ይገኛል። ሕጎችን ከማሻሻል፤ የጸጥታ ተቋማትን ሪፎርም ለማድረግ፣ የሰብአዊ መብት
ኮሚሽንንና የምርጫ ቦርድን ነጻና ገለልተኛ ለማድረግ፣ የፍትሕ ሥርዓታችን የዜጎችን
አመኔታ እንዲያገኝ ለማድረግ ተሞክሯል። በሌላ በኩል የትብብር ዴሞክራሲ ልምድ
እንዲዳብር ፓርቲያችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተፎካካሪ ፓርቲዎች በምርጫ ድምፅ አግኝተው
ባይመረጡ እንኳን ከሚኒስትር እስከ ቀበሌ አመራር ሥልጣን ተሰጥቷቸው ሕዝባቸውን
እንዲያገለግሉ ሆነዋል። ዴሞክራሲን በትብብር እና በፉክክር ሚዛን ጠብቆ እንዲሄድ መነሻ
የሚሆን ሥራ እየሠራን ነው።
ሰላማችንን ዘላቂ ለማድረግ፤ ቂምን በመሻር፤ ከሂሳብ ማወራረድ የጥላቻ መንገድ ለመውጣት
የሚያስችል ፍትሕን ማረጋገጥ ይገባናል። በመሆኑም የሽግግር ፍትሕ ማሕቀፍ ተግባራዊ
እንዲሆን በሕግ እና በመመሪያ ተደግፎ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ስምምነት ተደርሶ፣
የዝግጅት ምእራፍ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ምእራፍ ይገባል። በዚህ ሂደት በሙሉ መተማመን
ወደ ትግበራ የገባውን ሀገራዊ ሰላም ዘላቂ የማድረግ ውጥናችን ይበልጥ የሚጸናበት፤ ፍትሕን
የማረጋገጥ እና የተጎጂዎችን የፍትሕ ፍላጎት የማርካት ዓላማን እንዳይስት በማድረግ፣
ሰላማችንን አስቀጣይ የሽግግር ፍትሕ ተፈጻሚ እንዲሆን እናደርጋለን።
35
አልበኝነት ተግባር ላይ ተሠማርተዋል። ፓርቲያችን የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የጸጥታ
እና የሕግ አስከባሪ ተቋማትን ለማሻሻል ረጅም ርቀት ሄዷል።
ዴሞክራሲ የሀገር ህልውና አደጋ ውስጥ እየወደቀ ሊገነባ አይችልም። ዴሞክራሲ ሀገር ካፈረሰ
መቆሚያውን አጥቷል ማለት ነው። የሕግ የበላይነት እየተረጋገጠ ሲሄድ ሚዛን በመጠበቅ
በሂደት ዴሞክራሲ ይገነባል። በጥላቻ ፖለቲካ በተገኘው አጀንዳ የነጠላ ቡድናዊ የበላይነትን
ለመያዝ የሚደረግን ተግባር፣ በሕግ እና በሥርዓት መግራት ይገባል። በእንጭጩ ያልገራነው
የጥላቻ ፖለቲካ መሥመር ካልያዘ፣ ሶሪያ እና ሊቢያን የሚያስንቅ ጥፋት ያመጣል።
36
አስከባሪ ተቋማትን እንፈጥራለን። ይህን ግብ እውን ማድረግ ለብልጽግና ጉዟችን የግድ
ነው።
ለሕዝብ ጸጥታ እና ደኅንነት ተገቢ ትኩረት በመስጠት የሕግ የበላይነት እንዲከበር ዐቅም
ከመሆን ይልቅ ሰብአዊ መብቶችን ሽፋን በማድረግ ፍትሕን የማዛባት ሁኔታ ይታያል።
ፍትሕን መንግሥትን ለማጥቂያ የመጠቀም አዝማሚያም አለ። መንግሥት የሚከስሳቸውን
በመልቀቅ ግላዊ ጀግና የመሆንና ራስን ታላቅ አድርጎ የማሳየት አካሄድ እየተስተዋለ ነው።
በተጨማሪም በጽንፈኝነት አመለካከቶች መወሰድ እና የግል እምነትን በፍትሕ ወንበር ላይ
መጫን ይታያል። እነዚህ አደገኛ አዝማሚያዎች ዋና ዋና ችግሮች መሆናቸው ተለይተዋል።
በመሆኑም በፍርድ ቤቶች ላይ የተጀመረው ሪፎርም እክል እንደገጠመው ታይቷል።
የገጠመውን ችግር ሥር ሳይሰድ የማስተካከያ ርምጃዎች ተወስደዋል። በሁሉም ደረጃ የሚገኙ
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አመራሮችን የመለወጥ ሥራዎች እየተሠራ ነው። በቀጣይነት
ሪፎርሙ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጣ በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ የሚሆን ይሆናል።
በፓርቲ ደረጃ ከማዕከል እስከ ታችኛው ርከን አመራርም ይሁን አባላችን የሌብነት ተግባር
ላይ የግድ ተጨባጭ መረጃ ባይገኝበት እንኳን ከመጠቃቃት በጸዳ መልኩ አዝማሚያውን
እያየን ፖለቲካዊ እርምት መውሰድ ይጠበቅብናል። በፓርቲ ደረጃ የተደራጀ የሙስና ትግል
አድርገን ሌላውን ካላታገልን በቀር ትግላችን ግብ አይመታም። ፓርቲያችን ራሱን ንጽሕ
በማድረግ ከሙስና የነጻች ሀገር የመገንባት ትግል መምራት አለበት። የፓርቲ እጅ ሳይነጻ
የሀገር እጅ አይነጻም።
በመሆኑም በፓርቲ መሪነት የፀረ ሙስና መሪነት የፀረ ሙስና ትግላችን መፋፋም
ይኖርበታል። ነጠላ ቡድናዊ እውነታቸው የተሸነፈባቸው ኃይሎች ሥርዓት አልበኝነት
አንግሠው የጥላቻ ፖለቲካ ቸርችረው፤ በቻሉት ዐቅም እጃችን ጠምዝዘው ሥልጣን ለመያዝ
እየደሚሠሩ አይተናል። በመሆኑም የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ የግድ ነው። የነጻነት
አስተዳደር እና አጠቃቀም በሕግ አግባብ ሚዛን እንዲጠብቅ አድርገን ሌብነትን በተቀናጀ
37
የፓርቲ እና የሕዝብ ዐቅም እየገታን መሄድ የሕግ የበላይነት ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው
ቀይ መሥመራችን መሆኑን በተጨባጭ ርምጃዎች ማረጋገጥ አለብን።
በዘመናዊ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ቁልፍ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ መንግሥት በብቸኝነት
ኃይልን የመጠቀም መብቱን ማስከበሩ ነው። መንግሥት በብቸኝነት ኃይል የመጠቀም
ሥልጣኑን ሥራ ላይ የሚያውለው በመሠረታዊነት ለሁለት ዓላማዎች ነው። የመጀመሪያው
ዓላማ በሀገር ውስጥ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር ነው። ይህ ብዙውን ጊዜ በፖሊስ ኃይል
የሚሠራ የወንጀል መከላከል እና የምርመራ ሥራ ነው። ሁለተኛው መንግሥት ኃይልን
የሚጠቀምበት ዓላማ ሀገርን ከወረራና ከውጭ ጠላት ለመከላከል እና አስፈላጊ በሆነ ወቅት
ወታደራዊ ኃይልን በመጠቀም ሀገራዊ ጥቅምን ለማስከበር ነው።
ግለሰብ ዜጎች ውሱን በሆነ እና በሕግ በተፈቀደ ልዩ ሁኔታ ራስን ለመከላከል ኃይል
ለመጠቀም መብት አላቸው። ቢሆንም፣ በመርሕ ደረጃ ኃይልን በብቸኛነት የመጠቀም መብት
የመንግሥት ሥልጣን ነው:: በፌደራል ሥርዓት ውስጥ፣ በሀገር ውስጥ ሕግ እና ሥርዓት
የማስጠበቅ ኃላፊነትን የፌደራል መንግሥት እና የክልል አስተዳደሮች የሚካፈሉበት አሠራር
የተለመደ ነው። ሆኖም ለዚሁ ዓላማ በክልልም ሆነ በፌደራል ደረጃ የሚደራጀው የፖሊስ
ኃይል በፖሊሳዊ የሞያ መሥፈርት የተደራጀ የሲቪል ተቋም ነው። ሥልጠናው፣
የሚታጠቀው መሣሪያ፣ አጠቃላይ አደረጃጀቱ እና ቅኝቱ ለውጊያ ወይም ለጦርነት ሳይሆን
የውስጥ ጸጥታን እና ሕግን ለማስከበር የተዘጋጀ ነው።
ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከሀገራዊ ለውጡ ጀምሮ በነበሩ የሕዝብ
ውይይቶች እና በምርጫ ክርክሮች ላይ የልዩ ኃይል አደረጃጀትና አላስፈላጊነት ዋነኛ አጀንዳ
አድርገው ሲያነሡት ነበር። በእነዚህ ውይይቶች ጊዜ የልዩ ኃይል አደረጃጀት ለሀገረ
መንግሥት ቀጣይነት ቀጣይ ፈተና ሆኖ እንደሚመጣ ተነሥቶ ነበር። የኃይል አጠቃቀም
በሕገ መንግሥቱ መሠረት ለፖሊስ እና ለሀገር መከላከያ ሠራዊት መሆን እንዳለበት ሲያነሡ
ነበር። ፓርቲያችን በጉዳዩ ላይ ክልሎችን ያሳተፈ ጥናት እንዲካሄድ በማድረግ ከጥቂት
38
ዓመታት በፊት ምክረ ሐሳብ አቅርቦ ነበር። ነገር ግን በወቅቱ ከነበርንበት ሀገራዊ ሁኔታ
የተነሣ ምክረ ሐሳቡን ተግባራዊ ለማድረግ አልተቻለም። ስለዚህ ጉዳዩ በይደር እንዲቆይ
የተደረገ፣ የዘገየ ግን የግድ አስፈላጊ የሆነ የቤት ሥራ ነው።
ሌላው ኢመደበኛ አደረጃጀት የሚባል ነገር በማንኛውም ክልል አያስፈልግም። ይህም ኃይል
ወደ መደበኛ ሕይወቱ እንዲመለስ የማድረግ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። የኃይል
አጠቃቀምን የማስተካከል ጉዳይ፣ የሀገረ መንግሥት ቀጣይነትና የሕዝቦችን ሁንተናዊ የወል
እውነት የማጽናት ጉዳይ ነው። የጸጥታ ኃይላችንን ይበልጥ በማጠናከር፤ የሀገር ውስጥ
ሰላማችንን ከማረጋገጥ በተጨማሪ ባልተረጋጋው ባልተረጋጋው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናችን
ላይ ብሔራዊ ጥቅማችንን በዲፕሎማሲም፤ በወታደራዊ መስክም ይበልጥ የምናስከብርበት፣
ከውስጣዊ ፍላጎቶቻችን የውጭ ጉዳያችንን የምናስፈጽምበት ዐቅም የምንፈጥርበት መንገድም
ነው።
39
ዕይታዎች፣ በአንድ ሰነድ የተጠናቀረ፣ የአንድን ሀገረ መንግሥት አወቃቀር፣ ቅርጽ እና
በሀገረ መንግሥቱ ሥልጣን የሚያዝበትንና እንዲሁም ሥራ ላይ የሚውልበትን መንገድ፣
የሚከፋፈልበትን፣ እንዲሁም ሥራ ከዚያም አልፎ መሠረታዊ የዜጎችን መብቶች የያዘ የሕግ
ማሕቀፍን ለዓለም አስተዋውቀዋል። ይህ ተሞክሮ በሰሜን አሜሪካ እና በአውሮፓ እየተስፋፋ
በላቲን አሜሪካ፣ በእስያ እና በአፍሪካም በተለያየ መልኩ ተተግብሯል።
40
የምናያቸው በሕገ መንግሥቱ ላይ የሚነሡ የቅቡልነት ፈተናዎች የመቅረት ዕድል
ይኖራቸው ነበር።
41
ስምምነት እንዲኖራቸው ማድረግ የሚቻል ባይሆንም፣ ምልዓተ ሕዝቡ በአብዛኛው የሕገ
መንግሥቱ ይዘቶች ላይ ይዘቶች ላይ እንዲግባባ ማድረግ ያስፈልጋል። ሕገ መንግሥቱን
የእኔም ነው ብሎ እንዲቀበለው ማድረግ ለሀገራዊ አንድነት እና ሰላም ትልቅ ግብአት ነው።
በሕገ መንግሥታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያለን ተቃርኖ፣ ከታሪክ ምልከታችን ጋር ተሣሥሮ ወደፊት
መራመድን አስቸጋሪ አድርጎታል።
43
3.3 የታደሰው የዓለም አቀፍ ግኑኘነትና ዲፕሎማሲ
ኢትዮጵያ እንደሚታወቀው የውጭ ግንኙነቷ በገለልተኝነት (non- ሉዓላዊነት በማከብር፣
በሀገራት የውስጥ aligned) መርሕ ላይ የቆመ ነው። ይህም በዋናነት የሌሎች ሀገራትን ጉዳይ
ላይ ጣልቃባለመግባት፣ በሁለትዮሽ ከሀገራት ጋርም ሆነ በባለ ብዙ ወገኖች የግንኙነት
መድረኮች ላይ (multilateral platforms) ዓለም አቀፋዊ የሰላምና የኢኮኖሚያዊ ዕድገት
ትብብሮችን በማጠናከር ላይ የተመሠረተ መንገድን ታራምዳለች። በዚህም ሰላሟን
ለማጽናትና ከድህነት በመላቀቅ ለመልማት ከሚተባበሯት ሀገራት ጋር በሙሉ በትብብር
ትሠራለች::
የውጭ ግንኙነት ሪፎርሙ ገና በሁለት እግሩ ሳይቆም በተከፈተብን የመረጃ ጦርነት የተነሣ
ብልጫው ተወሰደብን። የመረጃ ጦርነቱ ሀገሪቷን አጠልሽቶ ማሳየት ጀመረ። የግጭቱ ጠባይ
የውጭ ኃይሎችን ጭምር የጋበዘ በመሆኑና ይህም ከፍ ያለ የውጭ ጫናን በማስከተሉ ከፍ
ያለ ሰብአዊ ሰብአዊ ጉዳትና የሀብት ውድመት አስከትሎብናል። በውጤቱም በዓለም አቀፉ
ማኅበረሰብ ዘንድ፣ በተለይም በምዕራባውያኑና ከፍተኛ ተጽዕኖ ባላቸው እንደ የዓለም ገንዘብ
ተቋም (IMF)፣ የዓለም ባንክ (World Bank)፣ የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ ድጋፍ
ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) አማካይነት ከፍ ያለ ሆነ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጫናና
ክልከላዎችን ጭምር አስተናግደናል።
ኢትዮጵያ ከቀኝ ግዛት ነጻ ሆና የቆየችው በቅኝ ገዥነት የመጡባትን ሀገራት በጦርነት ገጥማ
አስደናቂ ድል በማስመዝገብ ነጻነቷን ጠብቃ ስለቆየች ነው። ቅኝ ገዥዎች አፍሪካን በዕጣ
ተከፋፍለው ሕዝቦቿን በባርነት አሰቃይተዋል። የተፈጥሮ ሀብቷን በመዝረፍ ለዘመናት
የጨለማ አህጉር እንድትባል አድርገዋል። ኢትዮጵያ የነጻነትን ዋጋ ታውቃለች። በክንዷ
ነጻነቷን አስጠብቃ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን ወደ ነጻነት እንዲመጡ ከማንዴላ እስከ
ሮበርት ሙጋቤ ድረስ ዐቅሟ የቻለውን ሁሉ ድጋፍ አደርጋለች።
46
3.3.5 የጋራ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ ቀጣናዊ ትሥሥር
የፓርቲያችን የውጭ ጉዳይ ሌላኛው መርሕ ለጎረቤት ሀገራት ትኩረት የሚሰጥ መሆኑ ነው።
ይህንንም ተከትሎ በውጭ ግንኙነታችን ውስጥ የመጀመሪያው ትኩረት ከጎረቤት ሀገራት ጋር
በመተባበርና በመነጋገር ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መመሥረትና ማጠናከር ነው። የኛ እና
የጎረቤት ሀገሮቻችን ዕጣ ፈንታ የተሣሠረ ስለሆነ የጋራ ጥቅማችንን መሠረት ያደረገ
መተጋገዝና ትብብር ያስፈልጋል ብለን አናምናለን። በመሆኑም ከጎረቤት ሀገራት ጋር
በሚኖረን ግንኙነት ብሔራዊ ጥቅም በአብዛኛው በፍጹማዊ የጋራ ጥቅም ላይ ተመሥርቶ
ሊበየን ይገባዋል። ስለሆነም በቀጣናው ካሉ ሀገሮች ጋር የጋራ ጥቅሞቻችንን መሠረት
ያደረገ፣ አካባቢያዊ የልማት፣ የኢኮኖሚ እና የሰላም ዲፕሎማሲ ትሥሥር እንዲፈጠር
በማድረግ፣ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ጥምረት እንዲገነባ ከሀገራዊ ለውጡ ጀምሮ እየሠራን
እንገኛለን።
47
ክፍል አራት
ሁሉም ነገር የተገናኘ ነው። በግንኙነቶች ውስጥ መጣጣምና መላተም ፍጥነትን ይወስነዋል።
የመኪናችን መዋቅራዊ ንድፍ(ዲዛይን) ከንፋስ ጋር ያለው ግንኙነት የፍጥነት መጠንን
ይወስነዋል። በመደበኛ መኪናዎችና በስፖርት መኪናዎች መካከል አንዱ ልዩነት ለነፋስ
ያላቸው የተጋላጭነት መጠን ነው። መዋቅራችን በውዥንብር መረጃና በአሉባልታ ነፋስ
እየተፈተነ ይገኛል። ይሄም ፍጥነታችንን እየገደበው ነው።
በዩኒቨርስ ውስጥ ሁሉም ነገር የተገናኘ ነው። ሁሉም ከአንዱ ጋር አንዱም ከሁሉም ጋር
ተጣጥሞ ይኖራል። አንዱ ቦታ የሚፈጠር እንከን መላ ሥርዓቱን ይመለከተዋል። የጣት
መቁሰል የሳንባን ተግባር ባይገታም በሰውነት ሥርዓት ውስጥ በአንድ አካልነቱ ጉዳቱ
ለሁሉም ይደርሳል። በዚህ የሰውነት ሥርዓት ውስጥ ለጉዳት የሚሰጠው ምላሽ ፍጠነትና
ፈጠራ የተሞላበት ነው። ጉዳቱን ለመላ አካል የማድረስ ፍጥነትና የተቀናጀ ምላሽ አሰጣጥ
ተፈጥሮዊ ፈጠራን ያሳያል።
49
በፓርቲና በመንግሥት ሥርዓት ውስጥ ፍጥነትና ፈጠራን ለማረጋገጥ የሥርዓቱ አካላት
ጤናማነት መረጋጥ ቀዳሚው አጀንዳ ነው። በሥርዓት ውስጥ የኃይሎች ግንኙነትና የነገሮች
ግንኙነት እንዳለ ሁሉ መገፋፋትም አለ። በሥርዓት ውስጥ በሚደረግ ትግል ፍጥነት በሦስት
ይከፈላል፤
በዚህ ረገድ የፓርቲና የመንግሥትን ፍጥነት የሚስቡ ውጫዊና ውስጣዊ አካላት አሉ።
የፍጥነት ትግላችን ውጫዊና ውስጣዊ ኃይሎችን ጠርምሶ የሚያልፍ አስወንጫፊ ኃይል
መብዛት አለበት። ፍጥነታችንን የምናስጠብቀውና ተገዳዳሪ ኃይሎችን ድል የምንነሣው
የፈጠራ ዐቅማችንን አሟጠን በመጠቀም ነው። በፖርቲና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ
ፈጠራና ፍጥነት የሚያሣልጥ ሥርዓት ዘርግተናል። ፍጥነትና ፈጠራ በሥርዓት ውስጥ
ይገኛሉ። አንድ ሥርዓት በፍጥነትና በፈጠራ ውስጥ መሆኑ የሚወሰነው የዕምቅ ዐቅሙን
በገለጠበት ልክ ነው። ተያያዥነት ባለው ሥርዓት ውስጥ ፈጠራና ፍጥነት አይነጣጠሉም።
የፓርቲያችን መሠረታዊ ፈተና ሠርጎ ገብነት እና ሠርጎ ገቦች ናቸው᎓᎓ ሠርጎ ገብነት
የአንድን ፓርቲ ወይም መንግሥት መዋቅር ወይም አባላትን በመጥለፍ የራስን ግብ
ለማስፈጸም ወይም ፓርቲውንና መንግሥትን ለማዳከም የሚደረግ ጥረት ነው። ሠርጎ ገቦች
የሌላን ቡድን ወይም ዓላማ ይዘው ከእነርሱ ተቃራኒ ወይም ተገዳዳሪ ነው ብለው በሚያስቡት
ፓርቲ ወይም መንግሥት ውስጥ በመግባት ያንን ፓርቲ ወይም መንግሥት የሚሰልሉና እና
ለማዳከም የሚሠሩ ናቸው።
50
አስፈላጊ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ተለጣፊነት እና ተጠላፊነት ከፍጥነታችን ይገቱናል።
ተለጣፊዎች ማለት ፖለቲካዊ ዓላማና ግብ ሳይኖራቸው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማጋበስ ሲሉ
ፓርቲውን ተለጥፈው የሚኖሩ ናቸው። ተለጣፊዎችን ተሸክሞ መጓዝ የጉዟችን ፍጥነት
ይገታዋል። ስለዚህም ማራገፍ አለብን።
ብልጽግናን ማረጋገጥ በጋራ መሰባሰብና በጋራ መቆምን ይጠይቃል። ይሄንን የጋራ መሰባሰብ
ለመፍጠር የጋራ ስምምነትን መፍጠር ይሻል። ፈጣን ለውጥና ዕድገት አረጋግጠዋል
በሚባሉት ሀገራት ውስጥ ልማት ሊረጋገጥ የቻለው ለጋራ ከፍታ በጋራ መቆም በቻሉ ሕዝቦች
ነው። በተቃራኒ ተናጠላዊ ፍላጎትን ለማሳካት እና አንጻራዊ ጥቅምን ለማግኘት የሚደረግ
ሽኩቻ የጋራ ከፍታን ሳይሆን የጋራ ድቀትን የሚፈጥር ነው። የተናጠል እውነት ይዞ የሚደረግ
ሩጫ ግጭትን እንጂ ስኬትን አይፈጥርም።
ለብልጽግና ደንቃራ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ የመሪዎች ያልተገባ ክብር እና ሀብት
ፍለጋ ውስጥ መግባት ነው። ይህ የመሪዎች ያልተገባ ውዳሴን እና ጥቅም ፍለጋ በዋነኝነት
በሞቅታ የዓላማ መሳትን ይፈጥራል። በተጨማሪም ሂደቶችን በማወሳሰብ ቅልጥፍና እና
ውጤታማነትን ያጠፋል። መሪዎች ያልተገባ ክብርና ጭብጨባ ለማግኘት ሲሉ የፓርቲና
የመንግሥትን ዓላማ ይስታሉ። ባልተገባና በሕዝባዊ አጀንዳዎች ይወሰዳሉ። ለዓላማና
ለመርሕ ከመሥራት ይልቅ ለመወደድና ለመደነቅ ይሠራሉ። እንደዚህ ዓይነት አመራሮች
ጉዟቸው ወደ ዓላማና ወደ ግባቸው ሳይሆን ገንዘብና ጭብጨባ ወዳለበት ሜዳ ነው።
52
4.4 ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን አለመላመድ፡ ጠባቂነት እና መርሕ አልባነት
ለመፍጠን እና ለመፍጠር ፈተና ከፈጠሩብን ጉዳዮች አንዱ አዲስ ሐሳብ እና አዲስ ባህል
ለመላመድ ያለን ዝግጁነት አዝጋሚ መሆኑ ነው። ብልጽግና አዲስ ሐሳብ እና አዲስ ባህልን
እያስተዋወቀ ያለ ፓርቲ ነው᎓᎓ አዲስ ሐሳብ እና አዲስ ባህልን ማሥረጽ ፈታኝ እና ጊዜ
የሚወስድ እንደሆነ የሚታወቅ ቢሆንም በሀገራችን አዲስ ሐሳብን እና አዲስ ባህልን ለመቀበል
ያለው ዝግጁነት ደካማ በመሆኑ ፈተናውን ያከብደዋል። ይህ ፈተና ደግሞ የሚጀመረው
የአዲሱ ሐሳብ አስፈጻሚ ከሆኑት ከፓርቲያችን አባላት በመሆኑ ችግሩን ከባድ ያደርገዋል።
ፓርቲያችን እንደ ፓርቲ ከቀደመው የተለየ የአሠራር ሥርዓትና አዲስ የፖለቲካ ልምምድ
ይዞ የሚንቀሳቀስ ነው። ነገር ግን አዲሱን ባህል ተዋውቆ በፍጥነት ለዚያ ባህል ተገዥ
የመሆን ችግር አለ። ከዚህ መካከል ቀዳሚ ሆኖ የሚታየው ዴሞክራሲያዊ መርሐዊነት እና
የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲን የመላመድ እና ለዚያ ተገዥ የመሆን ፓርቲዎች ከቀደሙትን
የሀገራችን ፓርቲያችን ችግር ነው።
53
ክፍል አምስት
54
ብልጽግናዊ መንግሥት ብልጽግናን ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ የሚንቀሳቀስ አመራር
ይፈልጋል። ያለንን ትኩረት፣ ዐቅም እና ጊዜ ብልጽግናን እውን ለማድረግ ማዋልና መጠቀም
ያስፈልጋል። ይህ ሲሆን ፍጥነትን መጨመር ይቻላል። ምክንያቱም ለተጓዳኝ አጀንዳዎች
የሚውል ትኩረት፣ በፍትጊያ የሚጠፋ ዐቅም እና ትኩረት በሙሉ ብልጽግናን ወደ ማረጋገጥ
ሲውል፣ ፍጥነትን መጨመር እና ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት ይቻላል።
“የአሉ” ድኅረ እውነት ፖለቲካ፡- የፖለቲካችን መሠረታዊ ችግር ነገርን በቅጡ እና ከሥሩ
አለመረዳት ነው። አሉባልታ ለማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ዕድገታችን ትልቅ እንቅፋት ነው።
ብዙ ሀገር ሊለውጡ የሚችሉ ዕሳቤዎችና ሰዎች የደረቁት በአሉባልታ ነው። አንድ ወሬ ከየት
መጣ? እንዴት ተነሣ? እና ምክንያቱ ምንድነው? ሳይባል በጋራ ይፈረጃል፣ በማኅበር
ይጠላል፤ በማኅበር ይደነቃል፣ በጋራ ይወደዳል። “በአሉ” ብቻ ፍርድ ይሰጣል፣ ሰው ይቀጣል፣
ብዙ ነገሮች ይደረጋሉ። “በአሉ” ብቻ ብዙ ጥፋት ደርሷል።
ፖለቲካችን አንዱ የሚያስፈልገው ትልቅ ለውጥ ነገርን ከሥሩ መመልከት ነው። ወቅቱ
ደግሞ ከምንም በላይ በጥልቀት መመልከት እና ከሥሩ መመርመር የሚፈልግበት ነው።
ገበታ ለሀገር ብለን ከአዲስ አበባ ውጪ በአማራ ክልል በጎርጎራ ላይ አስገራሚ የቱሪስት
መዳረሻ በመጠናቀቅ ላይ ነው። የጎርጎራ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ታሪክ ጠገብ የቱሪዝም መዳረሻ
ያለው የአማራ ክልል ከዘርፉ ይበልጥ ተጠቃሚ ይሆናል። ሌላኛው በደቡብ ክልል እየተሠራ
ያለው የኮይሻ ፕሮጀክት እና በኦሮሚያ ክልል እየተሠራ ያለው የወንጪ ፕሮጀክትም
ከተፈጥሮ ጋር የተስማሙ ሆነው እየተገነቡ ይገኛሉ። ቦታዎቹ ሲጠናቀቁ ሀገራችንን በቱሪስት
ተመራጭነቷን የሚያልቁ፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል ከሚገኙ የኢኮ ቱሪዝም መዳረሻዎች
ጋር መወዳደር የሚችሉ፣ የሰው እና የተፈጥሮን መስተጋብር የጠበቁ ውብ የቱሪስት
መዳረሻዎች እንደሚሆኑ ይታመናል። መጀመር ብቻ ሳይሆን ጨርሰን ማሳየት እንደምንችል
56
አረጋግጠናል። ሲጀመር የሚነሡ አቧራዎች እየተነኑ የሥራ ዐሻራ ብቻ መመዘኛ እንደሚሆን
ባለፉት አምስት ዓመታት አይተናል። ይህ የሚያሳየን ፓርቲያችን ትውልድ አስቀጣይ
ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ በመደመር ትውልድ ተጀምሮ የሚፈጸም እንጂ ተጀምሮ የሚቆም
ተግባር አለመኖሩን ለማስመስከር መቻሉን ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ ስኬትን ማስቀጠል በአረንጓዴ ዐሻራ ዓመታዊ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር፣
በስንዴ ምርታማነት እና በአጠቃላይ በግብርና ምርታማነት ላይ የታየውን ስኬት ማስቀጠል
_ አለብን። በምርት ዘመኑ በመኸር ወቅት በስንዴ ዘር ከተሸፈነው 2.82 ሚልዮን 02013/14
ምርት ሄ/ር ከ112 ሚልዮን ኩንታል በላይ ስንዴ የተመረተ ሲሆን ይህ ዘመን በማዕከላዊ
ስታትስቲክስ አገልግሎት ከተገመተው 52.13 ሚልዮን ኩንታል ምርት በ52.6 በመቶ ብልጫ
ያለው ምርት እንደተመረተ የሚያመለክት ነው። በዘንድሮ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 1.32
ሚልዮን ሄክታር ለመሸፈን ታቅዶ 1.33 ሚልዮን ሄክታር በዘር ተሸፍኗል። ከዚህም 52
ሚልዮን ኩንታል እንደሚሰበሰብ ይጠበቃል። በመሆኑም አሁንም የታቀደውን ግብ ለማድረስ
መሥራት አለብን። በስንዴ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የግብርና ምርቶች እየታየ ያለውን ውጤት
ክረምቱን በአግባቡ በመጠቀም በፍጥነት ማጠናከር ያስፈልጋል።
57
ባለፉት አራት ዓመታት ከፍተኛ ውጤት ያገኘንበት ዓመታዊ የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ
መትከል መርሐ ግብር ወርዶ የነበረውን ሀገራዊ የደን ሽፋናችንን ወደ 17 በመቶ እንዲያድግ
ያደረግንበት ነው። በጥቅሉ በአራት ዓመት ውስጥ ከ25 ቢልዮን በላይ ተክለናል። ለዘንድሮ
በጀት ዓመት ቅድመ ዝግጅት የተጀመረ ሲሆን 6.3 ቢልዮን ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ አሁን
ላይ 5.4 ቢልዮን ተዘጋጅቷል። ስለዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ የታቀደውን ችግኝ ያህል
ማድረስ ይጠበቅብናል።
የሌማት ትሩፋት ጅምሮችን ማስፋት- የወተት ምርት (የላም፣ የግመል፣ የፍየል) ባለፉት
ወራት 4.1 ቢልዮን ሊትር አፈጻም ነበረው። ዓመታዊ ዕቅዱ 75 ቢልዮን ሊትር ነው፤ ባለፉት
ወራት የሥጋ ምርት ከዳልጋ ከብት፣ ከበግ፣ ከፍየል እና ከግመል 237ሺ ቶን ተገኝቷል።
ዓመታዊ ዕቅዱ 505 ሺህ ቶን የሥጋ ምርት ነው፤ የዶሮ ዕንቁላል ምርትን በበጀት ዓመቱ
ወደ 3.47 ቢልዮን ለማድረስ ታቅዶ ባለፉ ወራት1.8 ቢልዮን ለማምረት ተችሏል።
በተጨማሪም ባለፉት ወራት የዶሮ ሥጋ ምርት 48 ሺቶን የተገኘ ሲሆን ዓመታዊ ዕቅዱ
95990 ቶን ነው የዓሣ ምርት ባለፉት ወራት 45.41 ሺ ቶን ሲመረት ዓመታዊ ዕቅዱ
106190 ሺህ ቶን ነው። በመሆኑም በቀሪ ጊዜያት ዕቅዱን ከግብ ለማድረስ በፍጥነትና
በትጋት መሠራት አለበት።
ይህን ሀገር የሚገዘግዝ አደገኛ አካሄድ መከላከል የኛ የገንቢዎቹ ወሳኙ ዓላማችን ነው። ለዚህ
የሚከፈለው መሥዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል ዝግጁዎች መሆን አለብን። አፍራሾ የሚሸነፉት
ገንቢዎች ከአፍራሾች ከጠነከሩ፤ ከአፍራሾች በላይ ከወሰኑ ከአፍራሾች በላይ መሥዋዕትነት
ከከፈሉ ብቻ ነው። በምንገነባት ኢትዮጵያ የሁላችንም በላይ የወል እውነት ገዥ ሐሳብ
እንዲሆን፣ ለምንፈልጋት ሀገር ለመክፈል የተዘጋጀነው የገንቢነት ዋጋ ይወስነዋል።
ማፍረስ እንደ መገንባት ከባድ ባለመሆኑ አፍራሾች ለመናጆነት የሚሰበስቡት የሚነዳ ኃይል
በቀላሉ ማሰባሰብ ይችላሉ። መገንባት አድካሚ ነው፤ ደምም ላብም ስለሚፈልግ ጊዜ
ይወስዳል፤ ያደክማል፤ በቀላሉ ኃይል ለማሰባሰብም ይፈትናል። ትውልድ ግንባታ፤ ሀገር
ማስቀጠል፤ ብልጽግናን ማረጋገጥ ወሳኝ ሥራዎቹ የሆነ ፓርቲ ውስጥ ነን። የመናጆ ፖለቲካ
ሳይፈታን፤ ለሕዝብ በመቆርቆር ሽፋን በተለወሰው ሀገር በታኝ የጥላቻ ፖለቲካ ሳንሸነፍ፤
አሰላለፋችን ሳይደበላለቅብን፤ በአመለካከት ሳንሰለብ፤ የወል እውነታችን አሸናፊነትን ወደ
ምናረጋግጥበት ረጅሙ የብልጽግና ጉዞ እስከ መዳረሻው ለመድረስ በትክክለኛው ባቡር ላይ
ተሳፍረናል ወይ? የሚለው የአመራሩና አባሉ ወሳኝ ጥያቄ ነው።
59
በመሆኑም ቀጣይ የፖለቲካ ሥራችን የወል እውነቶቻችን መሠረት የሆኑትን የፍትሕ፤
የነጻነት እና የእኩልነት ፍላጎቶች ምላሽ እንዲያገኙ የሚከተሉት ቁልፍ ፖለቲካዊ
ሥራዎቻችንን በትኩረት የምንሠራባቸው ይሆናሉ።
60
መንግሥት እንደ ቀዳሚዎቹ በሥርዓት መቀያየር የመሻር ዕጣ አልገጠመውም።
የመታደስ እና ሁሉንም አካታች የመሆን ዕድል ደርሶታል። ሕገ መንግሥታችን
የሁላችንን የወል እውነት እንዲካተትበት ተደርጎ ለረዥም ጊዜ የሚቆይ ገዥ ሰነድ
እንዲሆን ለማድረግ መሥራት ይገባናል። በመሆኑ ዘላቂ ስላም፤ ኢኮኖሚያዊ እና
ፖለቲካዊ ድሎች የሚጸኑት ቅቡልነት ባለው ሕገ መንግሥት በመሆኑ፣ ሕገ
መንግሥታዊ ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በልዩ ትኩረት ፓርቲያችን ይሠራል።
ሀገራዊ ምክክሩ ሰላማችንን ማዝለቂያ፤ ልዩነቶቻችንን ማጥበቢያ፤ የወል እውነቶቻችን
የበለጠ ገዥ ሐሳብ ማድረጊያ፤ ጅምሩ የሀገረ መንግሥት ግንባታን ማጠናቀቂያ
እንዲሆን እንሠራለን። ዛሬም ድረስ ፖለቲካዊ ችግሮቻችንን መፍቻ መሣሪያ መሣሪያ
ሆኖ ፈተና የሆኑብን በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ በልዩ ትኩረት ተግባሩን የምንደግፍ
ይሆናል።
የነጻነት አስተዳደር እና አጠቃቀም ሚዛን መጠበቅ:- ሀገራዊ ለውጡ ከአፈና ወደ
ነጻነት ያደረገው ሽግግር ነጻነትን በአግባቡ የመጠቀም ፈተና እየገጠመው ነው። ነጻነት
እና ተጠያቂነት ትውውቅ የሌላቸው ትውውቅ የሌላቸው በሚመስል መልኩ የሀገር
አንድነት መሠረቶችን ወደ ሚነቀንቅ መሣሪያነት እየተሻገረ ነው።
በመሆኑም ነጻነት ያለ ኃላፊነት ሥርአት አልበኝነት በመሆኑ፣ የአጠቃቀም መዛነፎችን
የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ መሥመር ማስያዝ ያስፈልጋል። የመብት እና
የተጠያቂነትን ሚዛን ሚዛን ስንጠብቅ ስንጠብቅ ዴሞክራሲን ልቅነት አድርገው
ለሚመለከቱ ኃይሎች፣ ዴሞክራሲ ከተጠያቂነት ጋር እኩል ካልተጓዘ ችግር እንዳለው
ማሳየት ይገባል። በመሆኑም በነጻነት ስም የሀገረ መንግሥታችን አደጋ የሚሆኑ
ኃይሎችን በሕግ አግባብ መግራት አለብን። ሀገር ማስቀጠል የፓርቲም፣ የአመራር፣
የዜግነትም ግዴታችን በመሆኑ ሚዛን ያልሳተ ሕግ የማስከበር ዘርፈ ብዙ ሥራ
የምንሠራ ይሆናል።
የተማከለ የኃይል አጠቃቀም ትግበራን ዳር ማድረስ:- ፓርቲያችን ለመገንባት
የሚያስበው እና እየሠራበት ያለው የሁላችንም የወል እውነቶች ገዥ ሐሳቡ የሆነ
ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ነው። በዚህም የሀገረ መንግሥት ግንባታችን እንዲፋጠን
የኃይል አጠቃቀም ሥርዓት ሀገር በሚያስቀጥል መልኩ መደራጀት አለበት። በዚህም
ምክንያት ሕገ መንግሥታዊ ባልሆነ መልኩ ክልሎች ልዩ ኃይል በሚል ያደራጇቸው
ወታደራዊ ኃይሎች ነጠላ ቡድናዊ እውነታችን ገዥ ሥርዓት ለማድረግ ሲሞክሩ
በተግባር ከትግራይ ክልል አይተናል። ሌሎችም ክልሎች ይህን ሕገ መንግሥታዊ
61
ያልሆነ አደረጃጀት የነጠላ ቡድናዊ እውነታቸው ማስከበሪያ ለማድረግ ሲሠሩ እያየን
ነው። አሁን ላይ ሀገራችን በተግባር ተፈትነው የተደራጁ የፌዴራል የጸጥታ ተቋማት
እየገነባች ናት።
ክልሎች በሕገ መንግሥቱ በተሰጣቸው ሥልጣን መሠረት የክልል ፖሊስ እና ሚሊሻ
ብቻ እንዲያደራጁ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል። የወል እውነቶቻችን ገዥ የሆኑበትን
ሥርዓት ለመገንባት የኃይል አጠቃቀም ሥርዓት መያዝ የግድ የሚልበት ወቅት ላይ
እንገኛለን። በመሆኑም በተወሰነው ውሳኔ መሠረት የክልል ልዩ ኃይሎችን በማፍረስ
ወጥ የሆነ የኃይል አጠቃቀም ተግባራዊ ማድረግ በምንም ምድራዊ ኃይልም ሆነ
ምክንያት ወደኋላ የምንመልሰው ተግባር አይደለም። ባስቀመጥነው አቅጣጫ
መሠረት በአጭር ጊዜ ተፈጻሚ እንዲሆን መረባረብ ይኖርብናል።
የተደራጁ ወንጀሎችን መከላከል:- የፀረ ሙስና ትግል እንደ ሀገር ከጀመርን ወዲህ
አንዳንድ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ነገር ግን ከችግሩ ስፋት አንጻር በቂ
አይደሉም። ሌብነት ግለሰቦችን እና ቡድኖች ብቻ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ አድርጎ
የሚያቆም ጉዳይ አይደለም። በጊዜ ሂደት በሌብነት የተሰባሰበ ኃይል ወደ ሥርዓት
ነጠቃ በመግባት ለሀገረ መንግሥት ጠንቅ የመሆን ዕድል ሊፈጥር ይችላል።
በተጨማሪም ሙሰኞች የተንሰራፉበት ሀገር እና ሥርዓት የነጠላ ቡድናዊ እውነቶች
የበላይ እንዲሆነ ኢኮኖሚያዊ ዐቅም ይፈጥራሉ። ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ዐቅሙን
ያጠናከረ ቡድናዊ ኃይል ፍላጎቱን የሥርዓቱ ገዥ ሐሳብ ለማድረግ መታገሉ
አይቀርም። ስለዚህም የፀረ ሙስና ትግላችንን ኢኮኖሚያዊ ብቻ አድርገን ሳንመለከት
የሀገረ መንግሥታችን ፈተና እንዳይሆን ልንሠራበት ይገባል።
VI. ማጠቃለያ
62
የለውጥ መሠረታዊ ባህርይ በመረዳት ግጭትን ለማስቀረት የተደረገው ይቅር ባይነት
ደካማነት መስሎ የታያቸው ኃይሎች አሉ። እነዚህ ኃይሎች ዓይነት ብዙ ቀውሶች በመጥመቅ
የነጠላ ቡድናዊ የበላይነታቸውን ለመመለስ ጥረት አድርገዋል።
ባለፋት ወራት በነበረው የፀረ ሙስና ትግላችን የሚታዩ ክፍተቶችን የሚሞላ የድርጊት
መርሐ ግብር በድጋሚ ማዘጋጀት አለብን። በሁሉም ክልሎች ወጥነት ያለውና ገዘፍ ያሉ
ሌብነቶችን የሚይዝ መሆን አለበት። በስፋት በቅንጅታዊ አሠራር በታገዘ መልኩ ውጤቶችን
ለማስመዝገብ መሥራት ይኖርብናል። በግራም በቀኝም ያሉ ሌቦች ሲነኩ የብሔር
ከረጢታቸው ውስጥ ለመወሸቅ ጥረት ማድረጋቸው አይቀርም፤ ነገር ግን ሥራችን በመረጃና
በማስረጃ የተረጋገጠ እንዲሆን በማድረግ ሌቦችን መደበቂያ ዋሻ ማሳጠት ያስፈልጋል።
ሂደቱን በሚገባ ግልጽ በማድረግና ሌቦቹን በማጋለጥ ሌብነትን ከልባችን ተጸይፈን ሌቦችን
የምንታገል ስብስቦች እንደሆንን በማስመስከር ሕዝባዊ ቅቡልነታችንን ማሳደግ ይገባል። ይህ
ሲደረግ ግን ጉዳዩ ከግለሰብ እስከ ቡድን የመጠቃቂያ፤ ንጹሐንን የመበቀያ መሣሪያ አድርጎ
የመጠቀም ዕድሎች እንዳይኖሩ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ዲስፕሊን ሊመራ ይገባዋል።
የወል እውነታችን ሥርዓታዊ መሪነት እንዳይኖረው፣ ዘላቂ ቀውስ ውስጥ እንድንገባና ነጠላ
ቡድናዊ የበላይነታቸውን ዳግም ለማንገሥ ጦርነት የገጠሙን ኃይሎች ድል ሆነዋል።
በደማችን ያገኘነውን ድል ዘላቂ ለማድረግ በላባችን ትርጉም ወዳለው የሰላም ስምምነት
ተሸጋግረናል። በየክልሎች ነፍጥ አንሥተው ከሚታገሉ ኃይሎች ጋር ችግሮችን በንግግር
እየፈታን ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ የተሐድሶ ኮሚሽን አቋቋመን እየሠራን ነው።
ከታጣቂ ኃይሎች ጋር የተጀመረው የሰላም ንግግር በውጤት እንዲጠናቀቅ በማድረግ ዘላቂ
ሀገራዊ ሰላም የምናሰፍን ይሆናል። የወል እውነቶቻችን መሠረት እንዲይዙ፤ የሕግ
የበላይነትን ማረጋገጥ፤ የተማከለ የኃይል አጠቃቀም ማስፈን፤ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን
63
ተግባራትን ማሳለጥ፤ ቅቡል የሆነ ሕገ መንግሥታዊነት መፍጠር፤ ቀጣይ ተግባሮቻችን
ናቸው።
64
ማስተዳደር፡- ኢኮኖሚያዊ ኢኮኖሚውን ማስተዳደር ዋና ችግራችን ነው። በመሆኑም
የተመረተን ምርት ደረጃውን ጠብቆ ተጠቃሚው ጋር እስኪደርስ ያለው በደላላ የሚመራ
የንግድ ሰንሰለት ለዋጋ ንረት ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረገ ነው። በመሆኑም የንግድ ቁጥጥር
ሥርዓታችንን ከፌዴራል እስከ ቀበሌ በመፈተሽ ጉድለቶችን መሙላትና ገበያውን ከደላላ
መዳፍ ማውጣት ይገባናል። ኢኮኖሚያዊ አሻጥር፣ ኮንትሮባንድ፣ ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር
እና ምርት ሥወራ ኢኮኖሚ የማስተዳዳር ተግዳሮቶች ናቸው። በዚህም ምክንያት የገበያ
አለመረጋጋት አሁን ካለበት እንዲያድግ እንዲያድግ በር ይከፍታል። በመሆኑም በጥናት
ላይ የተመሠረተ ሥር ነቀል አስተማሪ ርምጃዎች እንወስዳለን።
65
ፓርቲ ነው። ሁሌ ያስባል። ያሰበውን በፍጥነት ይተገብራል። የተገበረውን ዘላቂ ሀገራዊ
ብልጽግና አረጋጋጭ ዐቅም እንዲሆን ይሠራል። ሁሌም መፍጠን፤ሁሌም መፍጠር ከጊዜያዊ
ችግሮች በላይ ከፍ ብሎ መጓዝ ይገባናል። እንደ ተራራ የገዘፉ ችግሮችን ያለፈ ፓርቲ
በቋጥኞች አይደናቀፍም። በመሆኑም በፍጥነት እና በፈጠራ ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና
መጓዝ ቋሚ ርእያችን ነው። በጋራ ትግላችን ከርእያችን ለመድረስ የሚያግደን ምድራዊ
ኃይል አይኖርም።
ሀገር የትውልድ ቅብብሎሽ ውጤት ነች። ሁሉም ትውልድ በጊዜ፣ በቦታ እና በሁኔታ
ምሕዋርነት ከነጉድለቱ እና ሙላቱ ሲቀባበላት እኛ እጅ ላይ ደርሳለች። በመሆኑም
ሀገራችንን ጉድለቷን ሞልተን፣ ብልጽግናዋን እውን ለማድረግ እየተጋን እንገኛለን። ጉድለት
ስንሞላ የትናንትን ስብራት ለመጠገን እንጂ ዳግም ለመስበር አይደለም። ለዚህ ነው የሥርዓት
ስብራቷ መገለጫ የሆነውን ዘመናትን ያስቆጠረውን የነጠላ ቡድናዊ እውነት ሥርዓታዊ
የበላይነት በማስወገድ ፤ የሁላችን እውነት ገዥ ሥርዓታዊ ዕሳቤ እንዲሆን የምንሠራው።
ይህ አካሄዳችን የነጠላ ቡድናዊ የበላይነታቸውን ለማስጠበቅ በሚፈልጉ ኃይሎች ተፈትኗል።
ከባድ የሆኑ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን ተጋፍጠናል። ዓላማችን ሐቀኛ በመሆኑ
በድል አልፈናቸዋል።
66