Professional Documents
Culture Documents
Þÿp 3íë - Cu 'Sè E (-Ë H 0Ë5Í: Dspace Institution Dspace Repository
Þÿp 3íë - Cu 'Sè E (-Ë H 0Ë5Í: Dspace Institution Dspace Repository
2020-11-13
þÿHCñ 5M•
http://hdl.handle.net/123456789/11610
Downloaded from DSpace Repository, DSpace Institution's institutional repository
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
ሂዩማኒቲስ ፋኩልቲ
የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል
በፈቃዱ መስፍን
ሐምሌ 2012
ባሕር ዳር
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
ሂዩማኒቲስ ፋኩልቲ
በፈቃዱ መስፍን
የጥናቱ አማካሪ
አብርሃም አዱኛ
ሐምሌ 2012
ባሕር ዳር
© 2019 ፈቃዱ መስፍን
ማረጋገጫ
“ተመኵሳይያን ቃላት በታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው” በሚል ርእስ በባሕር ዳር
ዩኒቨርሲቲ፣ ሂውማኒቲስ ፋኩልቲ፣ የግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ለአርትስ
ማስተርስ ዲግሪ በግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ ለማግኘት እንደ ማሟያ ያቀረብኩት ይህ
ጥናት ከዚህ በፊት በማንኛውም አካል ያልተሠራ የራሴ ወጥ ሥራ መኾኑንና
የተጠቀምኩባቸው ድርሳናትም በትክክል ዋቢዬ የኾኑና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲም የጥናቱ
ሕጋዊ የባለቤትነት መብት ያለው መኾኑን በፊርማዬ አረጋግጣለሁ፡፡
የሂውማኒቲስ ፋኩልቲ
የሂውማኒቲስ ፋኩልቲ
እንደ ፈተና ቦርድ አባላት ይህን “ተመኵሳይያን ቃላት በታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ
ሰዋስው” በሚል ርእስ በፈቃዱ መስፍን የቀረበውን የመመረቂያ ጽሑፍ ፈትነናል፡፡ ይህ
የመመረቂያ ጽሑፍ “የአርትስ ማስተርስ ዲግሪ በግእዝ ቋንቋና ሥነ ጽሑፍ” ለማግኘት
የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን በማሟላቱ ተቀባይነት ማግኘቱን እናረጋግጣለን፡፡
ሊቀ መንበር ስም ፊርማ ቀን
.
ምስጋና
i
.
አኅጽሮተጽሑፍ
ይህ ጥናት “ተመኵሳይያን ቃላት በታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው” በሚል ርእስ
ተመሥርቶ የተከናወነ ሲኾን ዐላማዉም ከሌሎች ተዛማጂ የሴም ቋንቋዎች እና ምሁራን
መጣጥፎች አንጻር ታየ በገለጸበት አግባብ የቃላት ሞኵሼነት ያለ ስለመኾን አለመኾኑ
መመርመር ነው፡፡ ለዚህ ጥናት የታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው መነሻ የተደረገው
ከሌሎች ምሁራን ጽሑፎች በተለየ መልኩ ተመኵሳይያን ቃላት በተለይ በተለምዶ ሞኵሼ
ተብለው የሚጠሩ ፊደላትን መሠረት በማድረግ በሰፊው መብራራታቸው ነው፡፡ ይህም
በሌሎች ምሁራን ዘንድ እንዳለ መቀጠሉ ተለምዷዊ ሞኵሼ ፊደላት እውን ተመሳሳዮች
ናቸውን በእነዚህ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉ ፊደላት የተዋቀሩ ቃላትስ
ሞኵሼነትን ያሟላሉን የሚል ጥያቄ በመነሣቱ ነው ፡፡ የጥናቱ መረጃም የተሰበሰበው
በዋናነት ሰነድ በመፈተሽ ሲኾን ምርመሩ ከዐይነታዊ የምርምር ዘውግ የሚመደብ
እንደመኾኑ መጠን ገላጪ ንጽጽራዊ ዘዴን በመጠቀም ነው ማስረጃዎቹ የተተነተኑት፡፡
በጥናቱም ታየ ተለምዷዊ መኵሼ እየተባሉ የሚጠሩ ፊደላትን በዘፈቀደ እንደሚጠቀም
እና ቃላት የተዋቀሩባቸው ፊደላት ቅርጻቸዉ ግምት ውስጥ ሳይገባ በድምፃቸዉ መመሳሰል
ብቻ ተመኵሳይያን እንደሚባሉ እንዲሁም አዕማድ ግሶች ከተዋቀሩበት ፊደላት መለያየት
በተጨማሪ የተለየ ትርጕም ሳይኖራቸውና የአድራጊነትን፣ የተደራጊነትንና የአስደራጊነትን
ቅርጽ ሳያሟሉ ተመኵሳይያን የሚባሉ መኾናቸው ተረጋግጧል፡፡ ከአንድ የግስ ሥር
በርባታ የተገኙ እና በርባታቸዉ ምክንያት የተለያየ ፆታ፣ መደብና ቁጥር የሚገልጹ ኾነው
በንባብ በመመሳሰላቸው ቃላት ሞኵሼዎች የተባሉ ስለመኾናቸውም ጥናቱ አሳይቷል፡፡
በመጨረሻም ይህ ጥናት በቅርጽ እንጅ በድምፅ የማንለያቸውን ፊደላት ድምፃቸዉን
መልሶ ለማገኘት እንደመነሻ ኾኖ እንደሚያገለግል እና በምሁራኑ ዘንድም ስሕተትን
ከማረም ጀምሮ ለተጨማሪ ጥናት መነቃቃትን በመፍጠር በኩል አስተዋፅኦ እንደሚኖረው
ተመላክቷል፡፡
ii
.
የይዘት ማውጫ
ርእስ ገጽ
ምስጋና .............................................................................................................................. i
1. መግቢያ ....................................................................................................................... 1
iii
.
3.2.2 የፊደላት አጠቃቀም ችግር ሳይኖራቸው በትርጕም አንድ የኾኑ ቃላት ........... 55
4. 1 ማጠቃለያ ........................................................................................................... 68
iv
.
ዓ. ም ዓመተ ምሕረት
የሐዋ. የሐዋርያት ሥራ
ያዕቆ. ያዕቆብ
ግን. ግንዘት
v
.
ምዕራፍ አንድ
1. መግቢያ
1.1 የጥና ቱዳራ
የግእዝ ቋንቋ ከደቡባዊ የሴም ቋንቋዎች ምድብ ውስጥ የሚካተት ሲኾን በሀገር ቤት የሴም
ቋንቋ ምደባ መሠረት ደግሞ የኢትዮጵያ ሰሜናዊ ቋንቋ በመባል ነው የሚታወቀው
(ሊፒንስኪ፣ 1997፣ 49፣ 81፣) ፡፡ ስለቋንቋዉ የትመጤነትና እድገት በምሁራን ዘንድ
የተለያየ አመለካከት ቢኖርም በዓለም ከሚነገሩ ቀደምት ጥቂት ቋንቋዎች መካከል አንዱ
ግእዝ ስለመኾኑ ግን አከራካሪ አይደለም፡፡
1
.
አማርኛ የመንግሥት የሥራ ቋንቋ መኾኑን ተከትሎ የግእዝ ቋንቋ በ12ኛዉ ወይም
በ13ኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ ከመነጋገሪያ ቋንቋነቱ የተገታ ስለመኾኑ በምሁራኑ
ዘንድ የሚታመን ሲኾን (ዲልማን፣ 1907፣ 2፤ ሌስሎው፣ 1991፣ መግቢያ) በጽሑፍ ረገድ
ግን በተለይ በቀጣዮቹ ሦስት ምዕት ዓመታት እንደገና ያበበበት ጊዜም ነበር (ዝኒ ከማሁ)
፡፡ ቋንቋዉ ካለው ጥንታዊነት እና በቋንቋዉ ከተሰነዱት ቁም ነገሮች ጠቀሜታ አንጻር
በውጭና በሀገር ቤት የብዙ ምሁራንን ትኩረት እንደሳበ በተለይ ደግሞ በውጭ ምሁራንና
ተቋማት በቋንቋዉ ላይ የተሠሩ ሥራዎች በዐይነትም ኾነ በብዛት ከሀገር ውስጡ ጋር
ሲነጻጸር የላቀ ስለመኾኑ አምሳሉ (2006፣ 10) በአንደኛዉ ሀገር አቀፍ የግእዝ ጉባኤ ላይ
“የግዕዝ ጥናት ምጥን ምልከታ” በሚል ርእስ ባቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ አረጋግጧል፡፡
በሀገር ውስጥ ምሁራንም በረካታ ሥራዎች የተሠሩ ሲኾን በግንባር ቀደም ከሚጠቀሱ
ሥራዎች መካከል አንዱ እና የመጀመሪያዉ በ1889 ዓ. ም የታተመው የታየ ገብረ
ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው ነው (ሌስሎው፣ 1991፣ መግቢያ) ፡፡ ይህም መጽሐፍ
በሃይማኖት መሪዎችና በሊቃውንት ዘንድ ተቀባይነት ያለው እና እንደ አብነት የሚጠቀስ
ስለመኾኑ ዘመንፈስ ቅዱስ አብርሃ በ1958 ዓ. ም ባሳተመው የታየ ገብረ ማርያም
መጽሐፈ ሰዋስው (ይህ ዕትም ከዚህ በኋላ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ መሰ2 በሚል ተወክሏል)
መግቢያዉ ላይ ገልጧል፡፡ ብዙዎቹ የውጭና የሀገር ውስጥ ምሁራን ሥራዎች ባብዛኛዉ
የሚያተኩሩት ስለፊደላት አመጣጥና አጠቃቀም፤ ስለቃላት አመሠራረትና ዐይነቶቹ እና
ስለዐረፍተ ነገር አወቃቀር ነው፡፡ የታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው ግን ከሌሎች
ቀደምት የግእዝ መጻሕፍተ ሰዋስው በተለየ መልኩ የዚህ ጥናት ርእሰ ጉዳይ የኾኑትን
ተመኵሳይያን ቃላትን በየፈርጃቸዉ በመመደብ ሞኵሼነትን በተጨማሪ በስፋት
አብራርቷል፡፡
ተመኵሳይያን ማለት ምን ማለት ነው? የሚለው ቀጣዩ ጥያቄ ሲኾን ነገር ግን ለዚህ ጥያቄ
ምላሽ ከመሰጠቱ በፊት መጀመሪያ ስለ መጽሐፉ ባለቤት ታየ ገብረ ማርያም የተወሰነ
ግንዛቤ መያዝ አስፈላጊ ነው፡፡
2
.
እንደ ዓለም (1971-72፣ 14) ገለጻ ታየ ገብረ ማርያም የተወለደው በበጌምድር1 ከምከም
ቃሮዳ2 ይፋግ3 በተባለ መንደር በ1853 ዓ. ም በዐፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት ሲኾን
ከዚህ ዓለም ሕይወቱ ያለፈው ደግሞ በነሐሴ ወር 1916 ዓ.ም ነው፡፡ ታየ እናቱ በልጅነቱ
በመሞቷ እና አባቱም በአካባቢዉ ባለመኖሩ ምክንያት አጎቱን ፍለጋ ወደ ትግራይ ሲኼድ
አጎቱም ወደ ህንድ ቦምባይ ኺዶ ስላገኘው ወደ ህንድ ለመሄድ ምጽዋ በደረሰ ጊዜ
እምኩሉ4 ከሚባል የሚሽን ትምህርት ቤት ገብቶ የትርጕም እና የማስተማር ሥራ
ማከናወን ጀመረ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር መጽሐፈ ሰዋስው የተባለውን ሥራዉን ያዘጋጀው፡፡
1
በጌምድር- በምሥራቅ ተከዜ፣ በምዕራብ ጣና ሐይቅ፣ በሰሜን በለሳ ወንዝ፣ በደቡብ በሽሎና ዐባይ ወንዝ የሚያዋስኑት ኮረብታማ ሀገር ነው (ቤሪ
,2003 )፡፡ በአሁኑ ሰአት አብዛኛውን የደቡብ እና የሰሜን ጎንደር ዞኖችን ያካልላል፡:
2
ከምከም- ቃሮዳ- በአሁኑ ሰአት በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦ ከምከም ወረዳ ውስጥ የተወሰኑ ቀበሌዎች በጋራ የሚጠሩበት ስም ነው፡፡
3
ይፋግ-በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦ ከምከም ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ ቀበሌዎች አንዱ ነው
4
ምንኩሉ/እምኩሉ- ምጽዋ አካባቢ የሚገኝ የሰዊድሽ ወንጌላውያን መልእክተኞች ማእከል የነበርና የአካባቢ ልጆችን የሚያስተምሩበት የነበር ቦታ
ነው (ስሚድት,2005)::
3
.
ሌላዉ ደግሞ ሰብሐ--አመሰገነ (ብ) ይጠብቃል እና ሰብሐ--ሰባ/ወፈረ (ብ) ይላላል (ገጽ 36)
የሚለውን ብንወስድ የግእዙ ኹለቱም ግሶች ከ ‘ብ’ መጥበቅና መላላት ውጭ በአጻጻፍ
ቅርጻቸዉ ተመሳሳዪ ናቸው፡፡ ነግር ግን ሰባ ወይም ወፈረ የሚለው የግእዝ ግስ የሚጻፈው
በ“እሳቱ ሰ” ወይስ በ“ንጉሡ ሠ” የሚለውን ከሌሎች ምሁራን ጽሑፎች አንጻር ስናየው
ኪዳነ ወልድ (1948፣ 660) እና ዲልማን (1907፣248) ሰባ ለሚለው የአማርኛ ቃል
የሚጠቀሙት የግእዝ ግስ ሠቢሕ -ሠቢሖት ከሚለው አርእስት የሚገኘውን ሠብሐን ነው፡፡
5
ሣልስ ውስጠዘ- አገባብ ሳይኖረው በውስጡ ‘የ’ የሚል ትርጕም የሚያሰጥ እና መጨረሻዉ ፊደል ሣልስ የኾነ ቅጽል (አቤሴሎም 2009) ነው ፡፡
ምሳሌ፡ጸሓፊ--የሚጽፍ፡፡
4
.
የታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው ከቀደምት የሀገር ውስጥ ሥራዎች አንዱ ሲኾን
ሞኵሼነትንም ተመኵሳይያን በሚል ንኡስ ርእስ ሥር በሰፊው በማብራራት ቀዳሚዉ
ነው፡፡ አጥኚዉ ይህን መጽሐፍ መሠረት በማድረግ ጥናቱን ተመኵሳይያን ላይ ያደረገበት
ዋናዉ አነሣሺ ምክንያት ሞኵሼነት የተገጸበት መንገድ በተለይ አሁን ላይ ድምፃቸዉ
የማይለየው ፊደላት ( ሀ፣ ሐ እና ኀ፤ አ እና ዐ፤ ሰ እና ሠ፤ ጸ እና ፀ) ተመሳሳዪ እንደኾኑ
በመቁጠር በመጽሐፉ ውስጥ በዘፈቀደ መጻፋቸውና በእነዚህ ፊደላት የተዋቀሩ ቃላት
ተመኵሳይያን መባላቸው፤ እንዲሁም ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉም ኾነ በሌሎች
ፊደላት የተዋቀሩ አዕማድ ግሶችም አንዱ የሌላው አስደራጊ ወይም ተደራጊ ግስ ኾኖ እያለ
እና የተለየ ትርጕም በመካከላቸው ሳይኖር በምስጢር የተለያዩ አድራጊ፣ አስደራጊ እና
ተደራጊ የመሰሉ ተመኵሳይያን/ ሞኵሼዎች ቃላት መባላቸው እና ከአንድ የግስ ሥር
በርባታ የተገኙ እና በርባታቸው ምክንያት የተለያየ ጾታ፣ መደብና ቁጥር የሚገልጹ ቃላት
በትርጕም ተለያይተው በንባብ የተመሳሳሉ ተመኵሳይያን ቃላት መባላቸው እና ይህን
መነሻ በማድረግም ሌሎች ጸሓፊዎችና መምህራንም መጻፋቸውና ማስተማራቸው ሲታይ
በእርግጥስ በመጽሐፉ በተገለጸው አግባብ ሞኵሼነት አለ? የለም? የሚለው ጥያቄ መነሣቱ
ነው ፡፡
5
.
ከመልክእ ደራሲዎች እስከ ቅኔ ዘራፊዎች ድረስ ፊደላቱ በቤት መምቻነት በዘፈቀደ ጥቅም
ላይ የሚውሉ ስለመኾኑ ተከታዮቹ ምሳሌዎች ማሳያዎች ናቸው ፡፡
ይህ ዐይነት አጠቃቀም በአንድ ፊደል የአናባቢ ርባታ ውስጥም በግእዝና በራብዕ ፊደላት
መካከል ይስተዋላል፡፡ ለምሳሌ ያክል፦ ጉበኤ ቃና ቅኔ-
በእርግጥ አሁን ባለው ተጨባጪ ኹኔታ በጕረሮ እና በጥርስ የሚነገሩ ፊደሎችን በቅርጽ
እንጅ በድምፅ መለየት ከማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ እንደ ዲልማን (1907፣ 2፣
47) አገላለጽ ይህ ኹኔታ የተፈጠረው አማርኛ የመንግሥት የሥራ ቋንቋ መኾኑን ተከትሎ
በአማርኛ ቋንቋ ተጽዕኖ እና የቋንቋዉ ተናጋሪ የሴሜቲክ ቋንቋ ተናጋሪ ካልኾኑ ህዝቦች
6
.
ምንም እንኳ ተግባራዊ ውጤት ባይመጣም የእነዚህ ፊደላት ድምፅ ከመጥፋቱ የተነሣ
ለአንድ ድምፅ ተደጋጋሚ ፊደላትን መጠቀም አያስፈልግም በሚል አስተሳሰብ ፊደላቱን
የመቀነስ እንቅስቃሴ ከዐፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ በተለያዩ ግለሰቦችና ተቋማት
ዘንድ ሲከወን የቆየ ተግባር ነው (ሙሉሰው፣ 2001፣ 96-97) ፡፡ ይህንም ሐሳብ በመደገፍ
ፊደላቱን ቀንሶ ድርሰቱን እንደጻፈ ሀዲስ (1996፣ 8) ይገልጻል፡፡
7
.
ከዚህ ዋና ዐላማ በመነሣት ጥናቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዝርዝር ዐላማዎች አሉት፡፡
እነሱም
8
.
1.6. የጥናቱ ዘዴ
9
.
ለዚህ ጥናት መነሻ የኾነው በ1889 ዓ.ም የታተመው የታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ
ሰዋስው ሲኾን የጥናቱን ጥያቄዎች መፍትሔ የሚሰጡ መረጃዎች ደግሞ የሚገኙት ከላይ
እንደተገለጸው ሰነድ በመፈተሽ ነው፡፡ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸውና አስተማማኚ
መረጃዎች ለማግኘት ደግሞ አጥኚዉ የተለያዩ ሰነዶችን የተጠቀመ ሲኾን ለጉዳዩ
አግባብነት ያላቸው መረጃዎች የተገኙት ከተመረጠው ርእሰ ጉዳይ ጋር ተዛማጂ ጉዳዮችን
ከየሰነዶቹ በመፈተሽ ነው፡፡
10
.
ነው፡፡ በመኾኑም ጽሑፉ በእነዚህ የቃል ክፍሎች በተለይ በተለምዶ ሞኵሼ እየተባሉ
በሚጠሩ ፊደላት በተዋቀሩ ቃላት ላይ ሞኵሼነት አለ? የለም? የሚለውን ከተሰበሰቡ
መረጃዎች አንጻር መመርመር በመኾኑ ጥናቱ በእነዚህ የቃላት ክፍሎች ላይ ብቻ የተገደበ
ነው፡፡ እንዲሁም ጥናቱ በመጽሐፈ ሰዋስው “ተመኵሳይያን” በሚለው ርእስ ብቻ የተገደበ
በመኾኑ ሌላዉን የዚሁን መጽሐፍ ክፍል አይዳሰስም ፡፡ በተጨማሪም ከመጻሕፍቱ
ተደራሽነት አንጻር ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ ፊደላትን በሥርዐተ ጽሕፈት
አጠቃቀማቸዉ የተለያዩ ስለመኾናቸው በአስረጂነት እና በማነጻጸሪያነት ሥራ ላይ የዋሉት
ተዛማጂ ሌሎች የሴም ቋንቋዎች የዐረብኛ፣ የዕብራይስጥ፣ ትግረ እና የትግረኛ ቋንቋዎች
በመኾናቸው ንጽጽሩ በእነዚህ ቋንቋዎች ብቻ የታጠረ ነው፡፡
11
.
ምዕራፍ ኹለት
ይህ ምዕራፍ በዋናነት ኹለት ንኡሳን ርእሶችን የያዘ ሲኾን፣ የመጀመሪያዉ ከዋናዉ ርእሰ
ጉዳይ ተመኵሳይያን ማለት ምን ማለት ነው ከሚለው ጀምሮ በመጽሐፈ ሰዋስው
ተመኵሳይያን የተባሉ የቃላት ክፍሎች (ግስ፣ አዕማድ፣ ዘር፣ ነባርና አገባብ) እንዲሁም
ተመኵሳይያንን በየፈርጁ ለመመደብ ሥራ ላይ የዋሉ መሠረታዊ ሐሳቦችን ማለትም
የቃላት ሥርዐተ ንባብ (ጥብቀት፣ ወዳቂና ተነሺ፣ ተጣዪና ሰያፍ) እና የአንድ ቃል
የተለያየ ትርጕም መስጠት በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ በዝርዝር የሚብራሩበት ክፍል ነው፡፡
ኹለተኛዉ ክፍል ደግሞ በርእሰ ጉዳዩ ዙሪያ የተጻፉ መጻሕፍትና የተሠሩ ጥናታዊ
ጽሑፎች የሚዳሰሱበት ነው፡፡
2.1.ፅንሰ ሐሳባዊ ዳራ
12
.
13
.
ከዚህም የምንረዳው መልከ ጼዴቅ በመኾን ያይደለ (አኮ በአማን) እንደ ኢየሱስ ካህን
መባሉ በተቀብዖ ስም6 ተመሳሳዪነት ያለው በመኾኑ፤ ኢያሱ ደግሞ በባሕርይ ያልኾነ
እንደ ኢየሱስ ተፈጥሮአዊ ኺደትን መቀየር መቻሉ የድርጊት ተመሳሳዪነት ያለ በመኾኑ
ከኢየሱስ ጋር ስምን በመያዝ ሞኵሼዎች የተባሉ መኾኑን ነው፡፡
ብህለ--አለ/ ለ አይጠብቅም/
6
በሹመት የሚገኝን ስም የሚያመለከት ስያሜ ሲኾን ምሳሌ ዲያቆን፣ ጳጳስ ደጅ አዝማቺ ወዘተርፈ (ታየ፣ 1889፣ 4)፡፡
14
.
አይደለም፡፡ ይህም ደስታ ለሞኵሼ ከሰጠው ትርጕም አንጻር ምሳሌነቱ ተገቢነት ያለው
አይደለም፡፡
ለይኩን (1998፣ 325) ደግሞ አንድ ግስ ከአንድ በላይ ትርጕም ኖሮት በተለያየ ንባብ
የተለያየ ትርጕም ሲሰጥ ሞኵሼነት እንደሚፈጠር ምሳሌዎችን በመጥቀስ ያብራራል፡፡
የተጠቀሱት ማሳያዎችም በመጽሐፈ ሰዋስው ላይ የተገለጹት በመጠበቅና በመላላት
የተለያየ ትርጕም የሚሰጡ እና ባንድ ቃል ተነበው የተለያየ ፍች የሚሰጡ ግሶች ናቸው፡፡
15
.
ነገር ግን ባብዛኛዉ የሚታየው የፊደላቱን ድምፅ መልሶ ለማግኘት ጥረት በማድረግ ፈንታ
ለፊደላቱ እና በእነዚህ ፊደላት ተዋፅኦ ለተዋቀሩትም ቃላት/ግሶች ጭምር ሞኵሼ የሚል
ስያሜ በመስጠት ፊደላቱን ማመሳሰልና በዘፈቀደ መጠቀም ነው፡፡ ከዚህም አልፎ ፊደላቱ
አላስፈለጊ ናቸው በሚል ይቀነሱ የሚል ዝንባሌ በምሁራኑ መቀንቀን ከጀመረም ውሎ
አድሯል፡፡ ይህ ደግሞ ከታሪክና ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት አንጻር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ
የሚያመዝንና ፊደላቱ ከተቀረጹበት ዐላማና ከሥነ ልሳን መርሕ ጋርም የሚቃረን ነው
የሚኾነው፡፡ ምክንያቱም አሁን ላይ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው ፊደላት ለጊዜው ድምፃቸዉ
የተመሳሰለ ቢመስልም ነገር ግን የፊደላቱ መካነ ፍጥረትና ባሕርየ ፍጥረት የተለያየ
መኾኑ ፊደላቱ የተለያየ ድምፅ፣ ትርጒምና ዐላማ ያላቸው መኾኑን ስለሚያሳይ ነው፡፡
16
.
የግእዝ ቃላት ክፍሎችን አመዳደብ በተመለከተ በምሁራን ዘንድ ወጥ የኾነ ምደባ የለም፡፡
እያንዳንዱን የቃላት ክፍሎች እና የምደባ ዐይነቶች ከዚህ ላይ መዘርዘር የዚህ ጽሑፍ
ዐላማ ባለመኾኑ በዚህ ክፍል በተወሰነ መልኩ የሚብራሩት በመጽሐፈ ሰዋስው ሞኵሼነትን
ለማሳየት የተጠቀሱት ግስ ከነአዕማዱ፣ ዘር፣ ነባርና አገባብ የተባሉት ውሱን የቃላት
ክፍሎች ብቻ ናቸው፡፡
ሀ. ግስ
የግስ መነሻዉ ዘመድ ዘር7? ወይስ አርእስት8? በሚለው ላይ ያለው የተለያየ የሊቃውንት
እይታ እንዳለ ኾኖ (አቤሴሎም፣ 2009፣ 93) ግስ የሚለው ቃል የተገኘው- ገሲስ ገሲሶት
ከሚል አርእስት ወይም ገሰሰ-ገሰሰ/ዳሰሰ ከሚል ቀዳማይ አንቀጽ እንደኾነና ገሰሳ፣ ዳሰሳ፣
ግስገሳ ተብሎ እንደሚተረጐም፤ የቃላት መውጫና መግቢያ በመኾኑ አንቀጽ፤
ተቀነባብረው የሚነገሩ የተለያዩ ቃላትን ስለሚያስር ማሰሪያ እና ቃላትን በመሳቡ ሳቢ
በሚል የሙያ ስም እንደሚጠራ አፈወርቅ (1988፣ 266-270) ያብራራል፡፡ ግስ ማለት
ከቀዳማይ ወደ ካልኣይ ከካልኣይ ወደ ሣልሳይ የሚገሰግስ ማለት ነው የሚል ትርጕም
የሰጠው ደግሞ ዐቢይ (2010፣ 167) ነው፡፡
ኪዳነ ወልድ (1948፣ 54) ደግሞ የቋንቋ ጓዝ የዘርና የነባር ማከማቻ ግሰት ነው ብለው
በመወራረስ እና በመመላለስ መርባቱና መዘርዘሩ ደግሞ ተወራራሺ ተመላላሺ የሚል
ትርጕም መስጠት እንደሚሻል ይገልጻል፡፡
ባጠቀላይ በግእዝ ቋንቋ ግስ የሚባለው 3ተኛ መደብ በወንድ ነጠላ ቁጥር በኀላፊ ጊዜ
የሚነገረው ቃል በመኾኑና ይህ አንዱ አንቀጽ /ግስ/ በዐሥሩ መራሕያን9 እስከ ሰማኒያ
ተጠቃሺ መደብ10 ድረስ መርባቱና መዘርዘሩ ሲታይ ግስ በትርጕም ደረጃ የማይረጋ/
የሚገሰግስ ኾኖ የቋንቋዉ የብዙ ዐይነት ቃላት መፈልፈያ እና መራቢያ ማለት ነው ብሎ
የምሁራኑን ገለጻ ማጠቃለል ይቻላል፡፡
7
ዘመድ ዘር--ግሱን መስሎ የሚወጣ ስም፣ ምሳሌ--ቀተለ ብሎ ቀትል ይላል፡፡
8
አርእስት--ሥረ ነገር፣ ምንጭ ማለት ሲሆን ምሳሌ ቀተለ ብሎ ቀቲል ቀቲሎት ይላል፡፡
9
የአንድ ዐረፍተ ነገር ባለቤት ኾነው የሚያገለገሉ ዐሥሩ ተውላጠ ስሞች/ የስም ምትኮች (ታየ፣ 1889፣ 21)
10
ሰማኒያ ተጠቃሺ መደብ የተባለው እያንዳንዱ ግስ በዐሥሩ መራሕያን ባለቤትነት ከራሱ ውጭ ያሉትን ዘጠኙን
መራሕያንን በተጠቃሺነት ወይም በተሳቢነት በመጠቀም እንደ አእመረ የሚረባበት መንገድ ነው ( አፈወርቅ፣
1988፣ 271) ፡፡
17
.
በግእዝ ቋንቋ መዝገበ ቃላት አዘጋጆች ዘንድ ለቃላት ትርጕም ለመስጠት መጀመሪያ
የሚጠቀሰው ነጠላ ግስ መኾኑ እና በየቅኔ ጉባኤ ቤቱም ከስሙ ጀምሮ ግስ ማውረድ
የሚባለውና ግሱ ሲወርድም መነሻዉን ነጠላ ግስ በማድረግ ርባታዉን ማስከተሉ ግስ
የቃላት መራቢያ እና መፈልፈያ ነው የሚለውን ሐሳብ የሚያጠናክር ነው፡፡
ለ. አዕማድ
መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ደግሞ እነዚህ የግስ ነገዶች ለግስ ርባታ መነሻ፣ መቋቋሚያ
በመኾናቸው አዕማድ ወይም ምሰሶዎች የሚል ስያሜ እንደተሰጣቸው ይገልጻል (1948፣
79) ፡፡
18
.
የአዕማድ ግሶችን ቁጥር በተመለከተ ታየ ገብረ ማርያምን ጨምሮ በብዙ የሀገር ውስጥ
ሊቃውንት የተለመደው አምስት እንደኾኑ ሲኾን ነገር ግን በላይ (2009፣ 101)
በተለመዱት አምስት አዕማድ ውስጥ ተዳራጊዉ--ተደራራጊ፣ አዳራጊዉ--አደራራጊ ኾኖ
መቀመጡ ተገቢ እንዳልኾነ በመግለጽ እንደ አማርኛ ቋንቋ ደራራጊ፣ ተደራራጊ እና
አደራራጊ የተባሉትን ሦስት ዐምዶችን በመጨመር የግእዝ አዕማድ ወደ ስምንት ከፍ ሊሉ
እንደሚችሉ በጥናቱ እንዳረጋገጠ ያብራራል ፡፡ በእነዚህ ሦስት ተጨማሪ አዕማድ ውስጥ
በአድራጊና በደራራጊ፤በአዳራጊና በአደራራጊ፤ በተዳራጊና በተደራራጊ ግሶች ውስጥ
የድርጊቱ ፈጻሚ (ባለቤት) ተመሳሳዪ ቢኾንም ነገር ግን በድርጊቱ መደጋገም እና
አለመደጋገም ላይ ልዩነት ስለሚያሳይ ግኝቱ ተገቢነት ያለው ነው፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በአምስቱ አዕማድ ውስጥ አቅተለ የአድራጊ አስደራጊን የሚመለከትና
የተደራጊዉ አስደራጊ የሌለ በመኾኑ ለተደራጊዉ አስደራጊ አስተቅተለን በመጨመር
አዕማድን በስድስት የሚከፍለው አቤሴሎም (2009፣104) ነው፡፡ በኹለቱም ምሁራን ዘንድ
የተጨመሩት አዕማድ ከሚሰጡት የተለየ ትርጕም አንጻር ሐሳቡ ተቀባይነት ያለው
በመኾኑ የግእዝ አዕማድ እስከ ዘጠኝ ሊደርሱ እንደሚችሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡
ሐ. ዘር
እንደ ኪዳነ ወልድ (1948፣ 50) አገላለጽ ዘር ማለት ነጠላ ግስን ከነርባው የሚያስገኝ
በሦስት ፊደል የተዋቀረ ቃል ሲኾን መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ የተባለውን መዝገበ ቃላቱን
ሲያዘጋጅም ዘሩን/ አርእስቱን በማስቀደም ግሱን ከነርባተዉ ማስከተሉ ከዚህ ትርጕም
በመነሣት እንደኾነ አብራርቷል፡፡ በታየ (1889፣ 4) መጽሐፈ ሰዋስው ደግሞ አንቀጽ
11
አጓጕል ግስ--የተለየ ገባሪም ኾነ ተሳቢ የሌላው አድራጊዉም ተደራጊዉም እሱ ራሱ የኾነ ግስ ( ኪዳነ ወልድ፣
1948፣ 65) ፡፡
19
.
በታየ መጽሐፈ ሰዋስው ተመኵሳይያንን ለማሳየት የተገለጹት እንደ ዘመድ ዘር፣ ባዕድ
ዘር12፤ ቅጽል13 እና የመሳሰሉት የቃል ክፍሎች በዘር መካተታቸው አስገኘዉ አርእስት
ከኾነው ነጠላ ግስ በርባታ መገኘታቸውን የሚያመላክት ነው፡፡ ምክንያቱም ታየ
በአራተኛዉ የተመኵሳይያን ምድብ ውስጥ የንባብ አንድነት የነገር ልዩነት በማለት
የመደበው አንዱ ዘር ሲኾን በምሳሌ የተጠቀሱት ደግሞ ቅጽል፣ ዘመድ ዘር እና ባዕድ ዘር
በመኾናቸው ነው ፡፡
መ. ነባር
ነባር በታየ (1889፣ 4) እርባ [ርባ] የሌለው በቁም ቀሪ በማለት ትርጕም ሲሰጠው በኪዳነ
ወልድ (1948፣ 5) ደግሞ ዘርነት የሌላው፣ ከዘር የማይገኝ፣ የማይለወጥ ስም ኾኖ
በውስጡም ነባር የመሰለ አንቀጽና አገባብ የሚወጣበት እንደኾነ ነው የተገጸው፡፡ ከነባር
የሚገኘው አንቀጽ ነባር የሚመስል መባሉ ከዘር የሚገኘው አንቀጽ በኀላፊ፣ በትንቢት፣
በዘንድና በትእዛዝ እና በዝርዝር ርባታ ሲረባ ነባር አንቀጹ ግን በኀላፊ ብቻ በዐሥሩ
መደብ/ መራሕያን በመዘርዘሩ (ደስታ፣ 1962፣ 8) የርባታዉን ውሱንነት ለመግለጽ እንጅ
ሙሉ ለሙሉ ርባታ የለውም ለማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ከተጸውዖ ስሞች ውጭ
የማይረባ ነባር ስም እንደሌለ እና ብዙ ነባር ስሞችም ለምሳሌ ሰብእ ብሎ ተሰብአ፣
ደብተራ ብሎ ተደብተረ በማለት አንቀጽ ሊወጣለት እንደሚችል ኪዳነ ወልድ (1948፣ 52)
ያብራራል፡፡
ሠ. አገባብ
አገባብ በተለያዩ ሊቃውንት በተለያየ መንገድ የተገለጸ ሲኾን ኪዳነ ወልድ (1948 86) “---
የብትን ቃል ኹሉ መሰብሰቢያና ማስማሚያ፤ የቋንቋ ቅመም፤ የንባብ ማጣፈጫ፤የምስጢር
ባዕድ ዘር--ከግሱ በሌለ ባዕድ ፊደል ዘሩ ሲነሣ፡፡ ለምሳሌ ነበረ ካለው ግስ መንበር የሚል ዘር ሲወጣ፡፡
12
13
ቅጽል-- የአንድን ነገር ምንነት ማለትም የነገሩን መጠን፣ ቀለም፣ ግብር፣ ዐይነት፣ ወዘተርፈ በተጨማሪነት
የሚገልጽ ቃልን የሚያመለክት ነው፡፡
20
.
የቃላት ሥርዐተ ንባብ ማለት ከቃሉ መረዳት እንደሚቻለው ቃላት አንዴትና በምን
ዐይነት መንገድ/ ስልት ሊነበቡ እንደሚችሉ የሚያሳይ ሕገ ንባብ ነው በማለት መተርጐም
ይቻላል፡፡ በብዙ የሀገር ውስጥ ምሁራን ዘንድ የግእዝ ሥርዐተ ንባብ ሲባል የሚታወሰው
ተነሺ፣ ተጣዪ፣ ሰያፍና ወዳቂ የተባሉት አራቱ የንባብ ዐይነቶች ናቸው፡፡ በቅኔ ቤትም
ዜማ ልክ የሚሰፈረውና የሚለከው በነዚሁ የንባብ ዐይነቶች መነሻነት ነው፡፡ ነገር ግን
ከእነዚህ የንባብ ዐይነቶች ተጣዪ ወይም ወዳቂንና ተነሺን በመያዝ ማጥበቅና ማላላት፤
መዋጥና መቁጠር፤ ማናበብና አለማናበብ የሚሉትን በመጨመር የግእዝ የንባብ ዐይነቶች
14
ዐቢይ አገባብ በማሰሪያ አንቀጽ ላይ እየወደቀ ማሰሪያነትን የሚያስቀር ፤ ደቂቅ አገባብ በዐቢይ አናቅጽ እየገባ
ማሰሪያነትን የማያስቀር ቢኾንም በሰዋስው ላይ እየወደቀ ማድረጊያ መነሻ፣ መገስገሻ፣ መድረሻ፣ አቀባዪ፣ ተሳቢ
ወዘተ..በመኾን የሚያገለግል ፤ ንኡስ አገባብ ደገሞ በነባር፣ በዘማቺ፣ በዐቢይ፣ በንኡስ፣ በአናቅጽ ኹሉ እየገባ
ማሰሪያነትን የማያስለቅቅ ጥያቄ እና አንክሮ፣ ደስታ እና ሐዘን፣ ልመና እና ምኞት፣ አሉታ እና አፍራሺ፣ እሽታ
እና እንቢታ ሌላም ይኸን የመሳሰሉትን የሚያሳይ ፊደል ወይም ቃል ነው፡፡
21
.
ለይኩን (1998፣ 353) ደግሞ ተነሺ፣ ወዳቂ፣ ጠባቂ፣ የሚላላ እና ተናባቢ በማለት በዐምስት
ይከፍላቸዋል፡፡ ባጠቃላይ በኹሉም ምሁራን ዘንድ የተጠቀሱት የንባብ ዐይነቶች በቋንቋዉ
ሥርዐተ ንባብ ውስጥ መኖራቸው እሙን እሰከኾነ ድረስ ኹሉም የግእዝ ቋንቋ ሥርዐተ
ንባብ ክፍሎች ናቸው በማለት መደምደም ይቻላል፡፡
እነዚህን የአነባብ ዐይነቶች በተለይ ጠብቆና ላልቶ እንዲሁም ውጦና ቆጥሮ የሚነበበውን
ፊደል ሊያስለይ የሚችል ምልክት በቋንቋዉ ሥርዐተ ጽሕፈት ውስጥ አለመኖር ቋንቋዉን
በቀላሉ ለመልመድ አስቸጋሪ ከመኾኑም በላይ ሥርዐተ ንባቡን ጠብቆ ማንበብ አለመቻል
ደግሞ የሚያስከትለው የትርጕምና የምስጢር መፋለስ ከፍተኛ ነው፡፡ ከዚህ ላይ ኹሉንም
መዘርዘር ባይቻልም በተወሰነ ደረጃ ግን ታየ በመጽሐፉ የጠቀሳቸው ጥብቀት፣ ተነሺና
ወዳቂ፤ ሰያፍና ተጣዪ እንደሚከተለው ይብራራሉ፡፡
ጥብቀት (gemination)
ጥብቀት ማለት የተነባቢን ድምፅን የቆይታ መጠን የሚያመለክት ሲኾን ይህም በኹሉም
የሴም ቋንቋዎች እንደሚንጸባረቅ እና የፊደላትን ድምፅ ከማለያየት በተጨማሪ ሥነ
ምዕላዳዊ ለውጥ በማምጣት በኩል የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ እንደኾነ ምሁራን ይገልጻሉ
(ኡሌንዶርፍ፣ 1951፣ 215፤ ጎልደንበርግ፣ 2013፣ 72)፡፡
22
.
(1988፣ 219) ደግሞ ከሚጠብቀው ፊደል በላይ ኹለት ነጥብ በማስቀመጥ ጠብቆ
የሚነበበውን ፊደል ለመለየት ጥረት ሲያደርግ ይታያል፡፡ ቢኾንም ግን ለኹሉም ጠብቀው
ለሚነበቡ ፊደላት ምልክቱ ካለመቀመጡም በላይ ምልክቶቹ የሚቀመጡበት ቦታ ወጥነት
ያለው አይደለም፡፡ ከዚህም የምንረዳው ቋንቋዉ አሁንም ከዚህ ዐይነት ችግር ያልወጣ
መኾኑን ው፡፡
ተነሺና ወዳቂ
ተነሺ ማለት የመጨረሻ ፊደሉ ከሳድስ ፊደል ውጭ ከግእዝ እስከ ሳብዕ ባሉት ፊደሎች
የሚጨርስ ኾኖ በከፍተኛ ድምፅ የሚነገር ወይም የሚነበብ ቃል ነው (ደሴ፣ 2007፣ 275)፡፡
ይህም አብዛኛዎቹ ግሶች የሚነበቡበት ሥርዐት ነው፡፡ ለምሳሌ በዐሥሩ መራሕያን
ከሚዘረዝሩት ግሶች ውስጥ ቀተልኩ፣ ቀተልነ፣ ቀተልከ፣ ቀተልክሙ፣ቀተልኪ፣ ቀተለ፣ ቀተሉ፣
ቀተላ (ብዙ ሴቶች) በከፍተኛ ድምፅ በተነሺነት ሲነበቡ ቀተልክን ከፍ ባለ ድምፅ
ባለመነበቡ፤ ቀተለት ደግሞ በሳድስ ፊደል በመጨረሱ ተነሺ አይባሉም፡፡ እንዲሁም
ዝንቱሰ፣ ዝንቱመ በማለት ‘ሰ’ እና ‘መ’ ትራስ የኾኑበት ወዳቂ ቃልም በተነሺነት ይነበባል
(አፈወርቅ፣ 1988፣ 63)፡፡
23
.
ጣይና ሰያፍ
ኹለቱም የሥርዐተ ንባብ ዐይነቶች የሚጨርሱት በሳድስ ፊደል ሲኾን ተጣዪ የመጨረሻ
ፊደሉን ያዝ ሳያደርግ ኀይል በሌላው ድምፅ የሚነበብ ሲኾን ሰያፍ ደግሞ ተነሺ
በተነበበት አግባብ በከፍተኛ ድምፅ የሚነበብ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ግስንና ከግስ ርባታ የሚገኙ
ዘሮችን/ ስም/ በተመለከተ ሰያፍ ወይስ ተጣዪ ነው የሚለውን ለመለየት ባያዳግትም ነገር
ግን ከነባር ስሞች ጋር በተያያዘ በአነባበብ ሥርዐቱ ላይ በሊቃውንቱ ዘንድ ስምምነት
የለም፡፡
ይህም በአንድ ቋንቋ ውስጥ አሻሚ ሐሳብ/ ቃል ወይም ዐረፍተ ነገር / በሚኖርበት ወይም
አንዱ ሐሳብ ከሌላው ሐሳብ በሚጋጭበት ጊዜ ጉዳዩን ግልጽ ለማድረግና ተቃርነኖዉን
ለማስታረቅ ነው፡፡ በዋናነት ለዚህ በማሳያነት የሚጠቀሰው በኢኦተቤ የመጻሕፍት ትርጓሜ
ትምህርት ቤት የሚሰጠው የአንድምታ ትርጓሜ ስልት ነው፡፡ አንድ ተርጓሚ ለአንድ ገጸ
ንባብ በአንድም ትርጓሜ ማብራሪያ የሚሰጠው አማራጪ ትርጕሞች በሚኖሩበት ጊዜ
እንደኾነና ይህም ከገጸ ንባቡ ጀርባ ያለውን ምስጢር ይበልጥ ግልጽ እንደሚያደርገው
መርሻ (2003፣ 36) አብራርቷል፡፡ ከትርጕም ባሕርያቱ ውስጥ ደግሞ ይበልጥ ገዢ እና
ተስማሚ የኾነ ተዛማጂ ትርጕም [association of meanings] መስጠትና ከኹኔታዎች
በመነሣት ትርጕም ማስፋት [extention by inference] የሚሉት ይገኙበታል (ዝኒ
24
.
አሁን ላይ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ የግእዝ ፊደሎች በጊዜ ኺደት ድምፃቸዉ
ቢመሳሰልም እንደ ቅርጻቸዉ ድምፃቸዉም የተለያየ እንደነበር በምሁራኑ ዘንድ ሲያወዛግብ
አይታይም፡፡ ለዚህ ሐሳብ ቅቡልነት ደግሞ በብዙ ምሁራን ተደጋግሞ እንደተጠቀሰው
ፊደላቱ የሚፈጠሩበት ቦታና ኹኔታ የተለያየ መኾኑ (አቤሴሎም፣ 2009፣ 30-31፣
ጎልደንበርግ፣ 2013፣ 67) እና በሌሎች የሴም ቋንቋዎች ድምፃቸዉ ተለይቶ የሚታወቅ
መኾኑ ነው፡፡ ለምሳሌ ኡሌንዶርፍ (1995፣ 41) ሀ፣ ሐ፣ ኀ፣ አ እና ዐ በዐረብኛ ቋንቋ
እንደሚገኙ እንዲሁም ከ ‘ኀ’ ውጭ ያሉት አራቱ የጒረሮ ድምፆች በትግረኛ እና በትግረ
ቋንቋዎች እንደሚገኙ ገልጧል፡፡
በሥነ ልሳን ጥናት መሠረትም ለአንድ ድምፅ የሚሰጠው ውክልና አንድ በመኾኑ (ሀበተ
ማርያም፣ 1986፣ 324) ለአንድ ድምፅ ኹለትና ከዚያ በላይ ውክልና ሊኖር የሚችልበት
አግባብ የለም፡፡ በሥነ ልሳን ተመራማሪዎች ዘንድም ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው ለሚመስሉ
ፊደላት ለእያንዳንዳቸው ልዩ ልዩ የመተርጐሚያ ምልክት መስጠት የተለመደ ነው
(ኡሌንዶርፍ፣ 1995፤ 33-34፤ ሌስሎው፣ 1991፣ መግቢያ) ፡፡
25
.
ነገር ግን ግእዝ ከሚለው የቋንቋዉ ስያሜ ጀምሮ በጕረሮ እና በጥርስ የሚነገሩ ፊደላት
ወጥ በኾነ መንገድ ሲጻፉ አይታይም፡፡ ችገሩ በ13ኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን ከተጻፉ የብራና
መጻሕፍት ጀምሮ እየባሰ እንደመጣና በተለይ ትግረኛና ትግረ ከሚናገሩ ይልቅ አማርኛ
ተናጋሪ በኾኑ ጸሓፊዎች በተጻፉ መጻሕፍት ላይ በስፋት እንደሚንጸባረቅ ኡሌንዶርፍ
(1995፣ 35-36) ይገልጻል፡፡ የተወሰኑ በጕረሮ የሚፈጠሩ ፊደላት ድምፃቸዉ በትግረኛ እና
በትግረ ቋንቋዎች እስካሁን ድረስ ተጠብቆ መቆየቱ የዚህ ማሳያ ሊኾን ይችላል፡፡ በግእዝ
ቋንቋ ውስጥ ለድምፆቹ መጥፋት የአማርኛ ቋንቋ ተፅእኖ ነው የሚለው የብዙኃኑ ምሁራን
ሐሳብም ከዚሁ ጋር አብሮ የሚሄድ ነው፡፡ይህ የፊደላት አጠቃቀም ችግር የታየ ገብረ
ማርያም መጽሐፈ ሰዋስውን ጨምሮ በዘመናዊ የኅትመት ውጤቶች ላይም በስፋት
ይንጸባረቃል፡፡
26
.
ኡሌንዶርፍም (1955፣ 38፣ 29) በኢትዮጵያ የሴም ቋንቋዎች ላይ ባደረገው የሥነ ድምፅ
ንጽጽራዊ ጥናት [The Semitic Languages of Ethiopia Comparative Phonology] የ‘አ’
እና ‘ዐ’፣ እንዲሁም የ‘ሀ’ እና ‘ሐ’ ልዩነት በትግረኛ እና በትግረ ቋንቋዎች በግልጽ
እንደሚንጸባረቅ ያረጋገጠ ሲኾን ኮምፓራቲቭ ኢቲሞሎጅ (comparative etymology)
ዘዴን በመጠቀም ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ ፊደሎችን አስተካክሎ መጻፍ
እንደሚቻል ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡ ይህም የሌስሎውን ሐሳብ የሚደግፍ ነው፡፡
27
.
ሌላው ደግሞ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ ፊደላት ላይ ከተደረጉ ጥናቶች ውስጥ
የሚጠቀሰው የዙፋን ገብረ ሕይወት “Why the Gee Pharyngeal Sounds Pronounced
as Glottal Sounds” (2018) በሚል ርእስ የቀረበው ጥናት ነው፡፡ በዚህ ጥናትም “ሐመሩ
ሐ” እና “ዐይኑ ዐ” ከ“ሃሌታዉ ሀ” እና ከ“አልፋዉ አ” እንደቅደም ተከተላቸዉ የተለየ ባሕሪ
እና አጠቃቀም ያላቸው ስለመኾኑና ድምፃቸዉም የተመሳሰለው በአማርኛ ቋንቋ ተፅእኖ
ስለመኾኑ ለማሳየት ተሞክሯል፡፡ ጥናቱም ትንተናዉን መሠረት ያደረገው የግእዝ ቋንቋ
ከሌሎች የሴም ቋንቋዎች ጋር ያለውን ግንኙነት፣ ዒላማ የተደረጉትን የኹለቱን ፊደላት
ቅርጻዊ ባሕሪ እና ታሪካዊ የጥናት ውክልናን (Linguistic, Pictographic and Historic
Functions) ነው፡፡ ከእነዚህም የመተንተኛ መንገዶች ውስጥ አንደኛዉ ንጽጽራዊ
የመተንተኛ ዘዴ አጥኚዋ የተጠቀመች ስለመኾኑ መረዳት ይቻላል፡፡
ባጠቃላይ ከዚህ በላይ ከቀረበው የዘርፉ ምሁራን ገለጻ መረዳት የሚቻለው ተመሳሳዪ
ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ ፊደላት እንደ ሌሎች የሴም ቋንቋዎች ኹሉ በግእዝ ቋንቋም
ድምፃቸዉ የተለያየ ስለመኾኑ በኹሉም ምሁራን ዘንድ ስምምነት ያለ ስለመኾኑና አሁን
ላይ ድምፃቸዉን መለየት ባይቻልም ነገር ግን በጽሕፈት ደረጃ ታሪካዊ ንጽጽራዊ ዘዴን
በመጠቀም በዘፈቀደ የመጻፍ ችግርን ማስወገድ እንደሚቻል ነው፡፡
28
.
29
.
ከዚህ ቀጥሎ በርእሰ ጉዳዩ ላይ የሌሎች ምሁራን ሥራዎች የሚዳሰሱ ሲኾን በመጀመሪያም
አፈወርቅ ዘውዴ ሀገረ--መጻሕፍት/ ሰዋስው ግእዝ ወዐማርኛ/ (1988) በሚል ርእስ
ባሳተመው መጽሐፍ ስለተመኵሳይያን ቃላት ከገጽ 31-32 ያሰፈረውን ነው
የምንመለከተው፡፡ አፈወርቅ ለሞኵሼነት ትርጕም ባይሰጠውም የቃላት ሞኵሼነትን
በሦስት መንገዶች በጥብቀት፣ በልህላሄ እና በፊደል ዐይነቶቹ መለየት እንደሚቻል
ይገልጻል፡፡ ከተጠቀሱት ምሳሌዎች ውስጥ ጥብቀት የሌለው ኾኖ በፊደል ዐይነት የሚለይ
ሠረቀ--ወጣ/ተወለደ እና ሰረቀ--ሰረቀ፤ በመጥበቅና በመላላት እንዲሁም በፊደል ዐይነት
ደግሞ የሚለይ ቀሠመ--ቀሠመ እና ቀሰመ/ ሰ ይጠብቃል/--አጣፈጠ የሚሉትን መጥቀስ
ይቻላል፡፡ ኹለቱም ጥንድ ግሶች በተዋቀሩበት የፊደል ዐይነት ልዩነት አላቸው፡፡ ነገር ግን
ተመሳሳዪ ድምፀ ንባብ ያላቸው በመኾኑ ነው ኹለቱም ግሶች ተመኵሳይያን የተባሉት፡፡
ኹለተኛ ዐቢይ ለቤዛ “ዐምደ ግእዝ” (2010) በተሰኘው መጽሐፉ ስለተመኵሳይያን ቃላት
ከገጽ 261-263 በመጠኑ ዳሷል፡፡ ዐቢይ “ለማንኛዉም ነገር ተመሳሳዪ እንዳለው ኹሉ
ለስሞችና ለግሶች ኹሉ ተመሳሳዪ ወይም ሞኵሼዎች አላቸው” በማለት ይጀምርና
ተመሳሳዪነታቸዉም በፊደል ተመሳስለው በትርጕም የሚለያዩ እና በፊደል ተለያይተው
በትርጕም የሚመሳሰሉ ቃላት በማለት ይከፍላቸዋል፡፡
30
.
ግሶች ደግሞ በ “ንጉሡ ሠ” ነው፡፡ ከዚህም በግሶቹ መካከል በተለይ በመጀመሪያዉ ጥንድ
ግስ የትርጕም ልዩነት አለ የለም የሚለው ጥያቄ እንዳለ ኾኖ ዐቢይ በፊደል መመሳሰል
ምክንያት የተፈጠሩ ሞኵሼዎች በማለት የጠቀሳቸው ጥንድ ግሶች አሁን ላይ ተመሳሳዪ
የሚመስሉት በድመፀ ንባብ እንጅ በቅርጸ ፊደል አለመኾኑን ነው የምንገነዘበው፡፡ ይህም
በመጽሐፈ ሰዋስው ኹለተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሰው የሞኵሼ ዐይነት ነው፡፡
15
መልካቸዉን፣ ድምፃቸውንና አካኼዳቸዉን ለውጠው ካዕብንና ሳብዕን ትተው በሕጹጹነት የሚጻፉ አራቱ ፊደሎች ሲኾኑ እነሱም ኰ፣ ኈ፣ ቈ እና
ጐ ናቸው (ኪዳነ ወልድ፣ 1926፣ 10)፡፡
31
.
አራተኛ በአቤሴሎም ነቅዐ ጥበብ “መሠረታዊ ሰዋስወ ግእዝ (በቀላል አቀራረብ)” (2009)
በሚል በተዘጋጀው መጽሐፉ ላይ ነው ተመኵሳይያን ቃላት የተብራሩት ፡፡ ነገር ግን
በአመዳደብም ኾነ በዐይነት በቀጥታ ከመጽሐፈ ሰዋስው የተወሰደ እንጅ ተመኵሳይያን
ቃላት በተለይ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉ ፊደላት የተዋቀሩ ቃላት ሞኵሼነትን
የሚያሟሉ ስለመኾን አለመኾናቸው የሚገልጽ አይደለም ፡፡
32
.
የሚባል ሥራ ያልተሠራ መኾኑን ነው፡፡ የዚህ ጥናት ትኩረትም በተለይ ተመሳሳዪ ድምፅ
ያላቸው በሚመስሉ ፊደላት የተዋቀሩ ቃላትን እንዲሁም ቃላት ካላቸው የትርጕም
አንድነትና ልዩነት አንጻር ተመኵሳይያን ቃላት በመጽሐፈ ሰዋስው የተገለጹበትን አግባብ
መመርመር ላይ በመኾኑ ይህም በሌሎች ምሁራን ያልተዳሰሰ ከመኾኑ ጋር ተያይዞ በዚህ
ላይ ያለውን ክፍተት ይሞላል በሚል ሐሳብ ነው፡፡
33
.
ምዕራፍ ሦስት
34
.
36
.
37
.
አምሐረ --አሳዘነ
እንደ መጽሐፈ ሰዋስው አገላለጽ ሦስቱም ግሶች የተለያየ ትርጕም ሰላላቸው፣ አምሐረ
የመሐረ አስደራጊ፣ አስተምሐረ የአምሐረ አስደራጊ ወይም የመሐረ አደራራጊ
ስለሚመስሉ በግሶቹ መካከል ሞኵሼነት አለ ማለት ነው፡፡ የግሶቹን የትርጕም መለያየት፣
በተመሳሳዪ ፊደል መጻፋቸው እና አንዱ የሌላዉ አስደራጊ መምሰላቸዉን እንዲሁ
ስንመለከት አባባሉ ትክክል ሊመስል ይችላል፡፡ ነገር ግን ጉዳዩን በጥልቀት ስንመለከተዉ
ከፊደል አጠቃቀም ጀምሮ በግሶቹ መካከል የትርጕም ልዩነት መኖር አለመኖርና አንዱ
የሌላዉ አስደራጊ መምሰል አለመምሰል ላይ ጥያቄ ይነሣል፡፡
38
.
በመኾኑም በታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስው መሐረ የሚለው ግስ በተገቢዉ ፊደል
ሳይከተብ፤ በኋለኞቹ ኹለት ዕትሞች ደግሞ አስተማረ ለሚለው የግእዝ ግስ የተጠቀሙት
ተገቢዉን ፊደል ቢኾንም ነገር ግን ከአምሐረ እና አስተምሐረ ከሚሉት ግሶች ጋር በቅርጸ
ፊደል የተለያዩ ኾነው እያለ ግሶቹ ተመኵሳይያን መባላቸው ተገቢ አለመኾኑን
39
.
ኪዳነ ወልድ (1948፣ 591) በመዝገበ ቃላቱ መልአ--መላ የሚለው ግስ በዐረብኛ መለአ፣
መሊአ፤ በዕብራይስጥ ማሌእ ተብሎ እንደሚተረጐም የገለጸ ሲኾን በእንግሊዝኛ--ዐረብኛ--
አማርኛ መዝገበ ቃላት መሙላት/ fill up የሚለው ግስ መለአ የሚል ትርጕም ነው ያለው
(ሙኒር፣ 2007፣ 62) ፡፡ እንዲሁም መሮጥ/ run የሚለው የእንግሊዝኛ ግስ በዐረብኛ
መለዐ፤ በትግረኛ ደግሞ ማምለጥ/ escape ብሎ አመልዔ የሚል አቻ ትርጕም ያለው
ሲኾን (ሌስሎው፣ 1991፣ 342) ይህም አመልአ--ወደ ፊት ሄደ፣ መራ ከሚለው ግስ ጋር
ተቀራራቢ ትርጕም ያለው ነው፡፡ ከዚህም ንጽጽራዊ ትንተና የምንረዳው መልአ--መላ
በመጽሐፈ ሰዋስው በ“አልፋዉ አ” መጻፉ ትክክል ሲኾን አመልአ-ወደ ፊት ሄደ፣ መራ
የሚለው ግስ ግን በ“ዐይኑ ዐ” ምትክ በ“አልፋዉ አ” መጻፉ ስሕተት መኾኑን ነው ፡፡
40
.
እንዲሁም አጽንሐ-- አደባ /ሸመቀ/ ለሚለው ግስ ደግሞ የተጠቀሰው ማስረጃ “እስመ ሊተሰ
አጽንሑኒ ይቅስፉኒ” የአማርኛ ትርጕሙ እኔንስ ይገርፉኝ ዘንድ አቆዩኝ የሚለው ነው
(መዝ. 38 (37)÷ 17) ፡፡ ከዚህ ላይ ጸንሐ የሚለው ግስ የአማርኛ አቻ ትርጕሙ ተዘጋጀ፤
አጽንሐ ደግሞ አቆየ የሚል ትርጕም እንደተሰጠው ልብ ይሏል፡፡ ምንም እንኳ አደባ
ወይም ሸመቀ የሚለው የአማርኛ ግስ አንድን ነገር ለመያዝ በመደበቅ ተዘጋጅቶ
መጠባበቅን የሚያመላክት ኾኖ እያለ ቀድሞ የተያዘን ነገር ቀጣይ ሌላ እርምጃ ለመውሰድ
ማቆየትን የሚመለከተውን ጥቅስ ለዚህ ግስ በማስረጃነት መጥቀሱ ተገቢ ባይኾንም አደባ/
ሸመቀ የሚለው ግስ የአቆያየቱ ኹኔታ በድብቅ መኾኑን ከማሳየት ባለፈ ቆየ ከሚለው ግስ
ጋር የተለየ ትርጕም ያለው አይደለም፡፡ ምክንያቱም አንድ ግስ በተለያየ ዐረፍተ ነገር
41
.
ሲገባ መሠረታዊ ትርጕሙን ሳይለቅ እንደ ጉዳዩ ኹኔታ ዐውዳዊ ትርጕም የሚሰጠው
በመኾኑ ነው፡፡
እንዲሁም ጸንሐ--ቆየ፣ አደባ፣ ሸመቀ-- የሚል ትርጕም ያለው ስለመኾኑ በተለያዩ ምሁራን
ተገልጧል (ኪዳነ ወልድ፣ 1948፣ 759፤ ሌስሎው፣1991፣ 560) ፡፡ ለምሳሌ “ወሶበ ጠየቁ (ቁ
ይጠብቃል) ዘይገብሩ አይሁድ ዲበ ዝ ብእሲ በጸኒሕ ፈነውክዎ ኀቤከ/ አይሁድ በዚህ ሰው
ላይ በመሸመቅ የሚያደርጉትን በተረዳኹ ጊዜ ወደ አንተ ላኩት” (የሐዋ. 23፣ 30)
የሚለውን ስንመለከት ጸኒሕ መሸመቅ የሚል ትርጕም የተሠጠው መኾኑን እንገነዘባል፡፡
ይህም የሚያሳየው አጽንሐ የሚለው ግስ የጸንሐ አስደራጊ ግስ እንጅ ራሱን የቻለ የተለየ
ትርጕም ያለው አድራጊ ግስ ያለመኾኑን ነው ፡፡ በመጽሐፈ ሰዋስው ኹለቱ ግሶች
አድራጊና አስደራጊ የሚመስሉ ተመኵሳይያን መባላቸው ተገቢ አለመኾኑን ሐተታዉ
ያመለክታል፡፡
ኪዳነ ወልድ (1948፣ 444) ሐለየ ዘፈነ/ ዘመረ ከሚለው ትርጕሙ በተጨማሪ ሌሎች
ትርጕሞችም እንዳሉት የገለጸ ሲኾን ከነዚህም ውስጥ አንዱ ጉቦ ወይም መማለጃ መስጠት
የሚለው ተጠቅሷል፡፡ ኪዳነ ወልድ በማስረጃነት የጠቀሰው “ወሐለይኪዮሙ ይምጽኡ
42
.
ኀቤኪ”/ በዙሪያሽ ይከቡሽ ዘንድ መማለጃን ትሰጫቸዋለሽ (ሕዝ.፣ 17÷33) የሚለው አንዱ
ነው፡፡ ይህም ዋጋ ወይም ጉቦ በመስጠት ዝሙት በምትፈጽም ሴሰኛ ሴት ስለተመሰለች
ኢየሩሳሌም እምነት ማጉደል የተነገረ ቃል ነው፡፡ በዚህ ላይ ሐለየ ጉቦ ወይም መማለጃ
ሰጠ የሚል ትርጕም ነው የተሰጠው፡፡ይህም አሕለየ የሐለየ አስደራጊ ግስ እንጅ ራሱን
የቻለ የተለየ ትርጕም ያለው ግስ አለመኾኑን ነው ማስረጃዉ የሚያሳየው፡፡
44
.
ፊደላቱ ካላቸው የቅርጽ ልዩነት አንጻር ተመሳሳዪ ናቸው ለማለት የማይቻል በመኾኑ
በምሳሌዉ የተጠቀሱት ጥንድ ግሶች ተመኵሳይያን መባላቸው ተገቢነት ያለው አይደለም፡፡
ከገጸ ንባቡ መረዳት እንደሚቻለው የኹለቱ ግሶች ትርጕም የተለያየ በመኾኑ የሐለፈ--
አለፈ ተደራጊ ግስ ተነጋገረ ከሚል ትርጕም ካለው ግስ ተሐለፈ ጋር የሚሞካሽ ስለመኾን
አለመኾኑ የሚመረመረው ግሶቹ የተዋቀሩበትን የፊደል ዐይነት እና ቅርጸ ፊደሉን
መሠረት በማድረግ ነው፡፡
45
.
ጥንድ ግሶቹ የተዋቀሩት ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉ ኹለት ፊደላት በመኾኑ
በመጀመሪያ የሚፈተሸው በፊደል አጠቃቀም ረገድ ተመሳሳዪ መኾን አለመኾናቸዉና
ተገቢነታቸዉ ነው፡፡ ከገጸ ንባቡ እንደሚታየው የመጀመሪያዉ ግስ “እሳቱ ሰ” ን ሲጠቀም
ኹለተኛዉ ግስ ደግሞ በ“ንጉሡ ሠ” ነው የተጻፈው፡፡ በመኾኑም እንዲሁ ገጸ ንባቡን
በመመልከት በፊደል አጠቃቀም ረገድ በግሶቹ መካከል ተመሳሳዪነት ስለሌለ እና ሰአለ--
ለመነ የሚለው ግስ ወደ ተደራጊነት ሲቀየር በ“እሳቱ ሰ” ስለሚጻፍ የሰአለ--ለመነ
ተደራጊዉና ተሥእለ--ጠየቀ ሞኵሼዎች አይደሉም ማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን ከዚህ
ድምዳሜ ላይ ከመድረሳችን በፊት በመሰ3 እና በመሰ4 ዕትሞች ተሥእለ--ጠየቀ የሚለው
ግስ የተጻፈው ተስእለ በሚል በ“እሳቱ ሰ” በመኾኑና ይህም ከኅትመት ኅትመት የፊደል
አጠቃቀም ልዩነት መኖሩን ስለሚያሳይ የየዕትመቶችን የፊደል አጠቃቀም ተገቢነታቸዉን
እንመለከታለን፡፡
46
.
ሌስሎው (1991፣ 480) እና ኪዳነ ወልድ (1948፣ 842) ሰአለ ለሚለው የግእዝ ግስ ለመነ፣
ጠየቀ፣ ፈለገ ወዘተርፈ የሚል ትርጕም በመስጠት ተስእለ የሚለው ግስም የ ሰአለ ተደራጊ
ግስ እንደኾነ መግለጻቸው ሰአለ የሚለው ግስ እንደአገባቡ ትርጕም በሚሰጥ መልኩ
የሚፈታ እንጅ ጠየቀ የሚለው የአማርኛ ግስ የተለየ ትርጕም ያለው ሌላ የግእዝ ግስ
አለመኖሩን ያሳያል፡፡ ለዚህም ነው ኪዳነ ወልድ ጠየቀ ለሚለው የአማርኛ ግስ ሰአለ
በማለት ፈንታ ተስእለ እያለ መገኘቱ በልማድ የመጣ ስሕተት እንጅ ትክክል አለመኾኑን
የገለጸዉ (ዝኒ ከማሁ) ፡፡
47
.
ኹለቱም ጥንድ ግሶች ስለተዋቀሩበት የፊደል ዐይነት በኹሉም የመጽሐፈ ሰዋስው ዕትሞች
ልዩነት የለም፡፡ ኪዳነ ወልድም (1948፣ 642) ነሥአ የሚለው ግስ በዕብራይስጥ ቋንቋ
ናሣእ ተብሎ እንደሚተረጐም በመግለጽ ግሶቹን በ“ንጉሡ ሠ” እና በ“አልፋዉ አ” ነው
በተመሳሳዪ የከተባቸው፡፡ ዲልማንም (1907፣ 64) የተሻሉ በሚባሉ የብራና መጻሕፍት
ኹሉ በ“እሳቱ ሰ” ተጽፈው ከማይገኙ የግእዝ ግሶች ውስጥ አንዱ ነሥአ እንደኾነ ነው
የገለጸው፡፡ይህም የሚያሳያው ግሶቹ ስለተዋቀሩበት ፊደል አከራካሪ ጉዳይ የሌለ መኾኑን
ነው፡፡ ይህ ከኾነ ደግሞ የጥንድ ግሶቹ ሞኵሼነት መኖር አለመኖሩ የሚመረመረው
ከተዋቀሩበት የፊደል ዐይነት ሳይኾን ካላቸው የትርጕም አንድነትና ልዩነት እና አንዱ
የሌላዉ ተደራጊ ወይም አድራጊ መምሰል አለመምሰል አንጻር ነው፡፡
48
.
“ተዘከረኒ እግዚኦ አመ ትመጽእ በመንግሥትከ” (ሉቃ. 23÷ 42) የሚለው ጥቅስ ደግሞ
የተዘከረ--አሰበ የሚለው ግስ ማስረጃ ሲኾን ወደ አማርኛ ሲመለስ አቤቱ በመንግሥትህ
በመጣህ ጊዜ ዐስበኝ ማለት ነው፡፡ ይህም በዕለተ ዐርብ ጌታ በመስቀል ላይ እያለ ፈያታይ
ዘየማን የተናገረው ቃል ነው፡፡ ምንም እንኳን ጌታ “አማን እብለከ እመን ፈድፋደ ከመ
ዮም ትሄሉ ምስሌየ ውስተ ገነት” (ሉቃ. 23÷43) ትርጕሙም እውነት እልኻለኹ ዛሬ
በገነት አብረኸኝ እንደምትኾን ፈጽመኽ እመን በማለት ወዲያውኑ መልስ የሰጠው
49
.
ቀድሞ እንደተገለጸው በግእዝ ቋንቋ ውስጥ ጠብቆ የሚነበበው ፊደል ተደግሞ የማይጻፍ
ወይም ጠብቆ ለመነበቡ የሚያሳይ ምልክት ባለመኖሩ ከተሰጡት ግሶች ውስጥ የትኛዉ
ግስና ፊደል ጠብቆ እንደሚነበብ በቀላሉ ለመለየት አይቻልም፡፡ ታየ ይህን ችግር
በመገንዘብ ይመስላል ከተሰጡት ጥንድ ግሶች ውስጥ የመጀመሪያዉ ግስ የቀደሰን
ኹለተኛዉ ደግሞ የቀተለን አካኼድ እንደሚከተል የገለጸው፡፡ የየግሶቹ ማስረጃዎችም
የሚያሳዩት ይህንኑ ነው፡፡
በዚህ ክፍልም ለማሳያነት ተመርጠው ከቀረቡት ጥንድ ቃላት ውስጥ ጠብቆ የሚነበበው
የመጀመሪያዉ ቃል ኾኖ ፊደሉም ከመድረሻ ፊደሉ ቀድሞ የሚገኘው ፊደል ነው፡፡
የተጠቀሱት ጥንድ ቃላትም ተመኵሳይያን መኾን አለመኾናቸው የሚመረመረው ቃላቱ
ከተዋቀሩበት ፊደል ተመሳሳዪ መኾን አለመኾን እና ካላቸው የትርጕም ልዩነት አንጻር
ሲኾን በእያንዳንዱ ክፍል ለማሳያነት ምሳሌዎችን በመጥቀስ ነው፡፡
50
.
51
.
በመጽሐፈ ሰዋስው ለግሱ በማስረጃነት “አቀውም ገጽየ ላዕለ ይእቲ ነፍስ”/ በዚያ ሰው ላይ
ፊቴን አከብድበታለሁ (ዘሌ. 17፣ 10) በማለት የተጠቀሰውም ደም መብላት የተከለከለ
ስለመኾኑና ደም በሚበላ ሰው ላይም የእግዚአብሔር ቁጣዉ የከበደ እና የምሕረት ፊቱንም
የሚመልስ ስለመኾኑ የተነገረ በመኾኑ አቀመ ብሎ ፊቱን መለሰ/ ገታ ወይም አከበደ/
አበረታ ተብሎ ቢተረጐም ልዩነት የለውም፡፡ ይህም ቆመ--ቆመ ተብሎ በቁሙ16
16
በቁሙ መተርጐም ማለት የግእዙ እና የአማርኛዉ ቃላት በመልክአ ፊደልም ኾነ በትርጕም ተመሳሳዪ በመኾናቸው የግእዙን ትርጕም አማርኛዉ
እንዳለ መጠቀሙን ለማሳየት ነው፡፡
52
.
ነገር ግን ኪዳነ ወልድ (1948፣ 785) ቆመ በውስጡ የያዘው አንድ ዐመል17 ኾኖ እያለ
አቆመ እያለ መርባት ሲገባው እንደ ባለኹለት ዐመሉ ቦአ (የቦአ አስደራጊዉ አብአ ተብሎ
ስለሚረባ) አቀመ በሚል መገኘቱ ትክክል እንዳልኾነ ይገልጻል፡፡ አፈወርቅም (1988፣
294፣ 296) በተመሳሳዪ ቆመን ወደ አድራጊ ወይም አስደራጊ ግስ የሚቀይረው አቆመ
በሚል ሲኾን አቀመ ብሎ በመጽሐፍ እንደሚገኝም ጨምሮ ገልጧል፡፡
“አልፋዉ አ”፣ “እሳቱ ሰ” እና “ንጉሡ ሠ” ፊደሎች ናቸው በነዚህ ጥንድ ግሶች ውስጥ
የአጠቃቀም ተገቢነታቸው የሚመረመረው፡፡ አሠረ የሚለው ግስ በምሳሌዉ ላይ በ“አልፋዉ
አ” የተጻፈ ቢኾንም ነገር ግን በማስረጃነት በተጠቀሰው ዐረፍተ ነገር ላይ ካልአይ አንቀጹ
“አሥራተ ይዔሥር” በማለት የተጻፈው በ“ዐይኑ ዐ” ነው፡፡
17
ዐመል ማለት የግስ ዐመልን የሚመለከት ኾኖ እነዚህም አ፣ ዐ፣ ሀ፣ ሐ፣ ኀ፣ ወ፣ የ እና ደጊመ ቃል ሲኾኑ እነዚህ ፊደላት ያሉበት ግስ ቤቱን ሳይለቅ
የፊደላትን ቅረጽ እና መደበኛዉን የአረባብ መንገድ በመለወጥ የሚረባበት መንገድ ነው (ኪዳነ ወልድ፣ 1948፣ 54)፡፡
18
ልማድ ማለት የአዕማድ ግሶች መነሻ ፊደላትን የሚመለከት ነው፡፡ ኪዳነ ወልድ አ፣ ተ፣ አስ፣ አስተ፣ አን በማለት በአምስት የመደባቸው ሲኾን
(1948፣ 59 ) ታየ ደግሞ ተ፣ አ እና አስተ በማለት በሦስት ነው የመደባቸው (1889፣ 22)፡፡
53
.
54
.
55
.
በዚህ ክፍል ቃላት በአንድ ንባብ በብዙ ነገር የሚፈቱ መኾኑ የሚመረመው በእያንዳንዱ
ምሳሌ የተጠቀሱት ቃላት በአጻጻፍ፣ በንባብ ተመሳሳዪ መኾን አለመኾናቸው እንዲሁም
የሚሰጡት ትርጕም የተለያየ መኾን አለመኾኑን በመመርመር ነው፡፡
ሠረቀ--ተወለደ
ሠረቀ--ወጣ
56
.
በመኾኑም በግእዝ ሥርዐተ ጽሕፈት ውስጥ የ“እሳቱ ሰ”ን እና የ“ንጉሡ ሠ”ን ትክክለኛ
አጠቃቀም ለመለየት ከሀገር ቤት የሴም ቋንቋዎች ይልቅ የዐረብኛ ቋንቋ መኾኑን ነው
ገለጻው የሚያስረዳው፡፡ ከዐረብኛ ቋንቋ አንጻርም ሠረቀ--ወጣ የሚለው ግስ የአጻጻፍ
ችግር የሌለበት መኾኑን ነው ከገለፀው የምንገነዘበው፡፡ በመኾኑም በአማርኛ ሰረቀ
የሚለው ግስ በግእዝ የሚጻፈው በ“እሳቱ ሰ” ሰረቀ በሚል በመኾኑ ሠረቀ--ወጣ ከሚለው
ግስ ጋር በተዋቀረበት የፊደል ዐይነት ልዩነት አለ ማለት ነው፡፡
57
.
እንደመኾኑ መጠን “ወወለደት ወልደ ዘበኩራ/ የበኩር ልጇንም ወለደች” (ሉቃስ፣ 2÷7)
ከሚለው ዐረፍተ ነገር ጋርም አብሮ የሚሄድ ነው፡፡
መልሐ--መዘዘ
መልሐ--ነቀለ
መልሐ--አወጣ
መልሐ--ምግባር ሠራ
58
.
መዘዘ፣ ነቀለ፣ አወጣ በማለት የተጠቀሱት የአማርኛ ግሶች የአንድን ጉዳይ ከተጣበቀበት
ነገር መለየትን የሚያመለክት በመኾኑ ግሶቹ በአንዱ የግእዝ ግስ ሥር የሚጠቃለሉ
እንጅ የተለየ ትርጕም አላቸው ለማለት አያስደፍርም፡፡ አንጸባረቀ በሚል
የተተረጐመው ግስም ወጣ (አወጣ) ተብሎ እንደሚተረጐም በራሱ በመጽሐፈ ሰዋስው
የተገለጸ በመኾኑ መልሐ --ወጣ በሚለው ግስ ውስጥ የሚካተት ነው የሚኾነው፡፡
ከላይ ከተሰጠው ሐተታ በመነሣትም በግሶቹ መካከል የትርጕም ልዩነት ሲኖር የፊደል
ዐይነት ልዩነት በመኖሩ ፤ በተዋቀሩበት የፊደል ዐይነት ሲመሳሰሉ ደግሞ የትርጕም
ልዩነት ባለመኖሩ ምክንያት በምሳሌዉ የተጠቀሱት ግሶች ተመኵሳይያን ቃላት
አይደሉም በማለት ማጠቃለል ይቻላል፡፡
59
.
ነገር ግን ኪዳነ ወልድ (1948፣ 757) ጸልአ እና ጸልዐ አንድ ዘር እንደኾኑ እና ‘ዐ’ በ‘አ’
መለወጡ የቁስሉን ዐይን ወይም አፍ ለማመልከት ነው በማለት ጸልአ ብሎም ቈሰለ
ተብሎ እንደሚተረጐም ነው የገለጸው፡፡ ኾኖም ግን ጸልዐ--ቈሰለ ከሚለው ግስ ለወጣው
ጸልዕ--ቁስል/ እባጭ ለሚለው ዘር የተጠቀመው ሰልዐት የሚለው አቻ የዐረብኛ ቃል
የተጻፈው በ“ዐይኑ ዐ” መኾኑ በራሱ ሲታይ የኪዳነ ወልድ አመክንዮ ትክክል
አለመኾኑን ነው የሚያሳየው፡፡ በመኾኑም ጸልዐ--አቄመ ተብሎ ሲተረጐም የቁስሉ
አለመዳንን የሚገልጽ እንጅ ሰው በሰው ላይ ያለውን ጥላቻ እንደማይመለከት ኹሉ
ጸልአ--ጠላ ሲልም ባንድ ነገር ላይ ያለን ጥላቻ የሚያመለክት በመኾኑ ጸልአ--ቈሰለ
ብሎ መተርጐም ተገቢነት የለው አይደለም፡፡
60
.
በዚህ ምሳሌ ግሶቹ የተዋቀሩት ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉ ፊደላት ባለመኾኑ
በፊደል አጠቃቀም ረገድ የሚነሣ ጥያቄ የለም፡፡ ነገር ግን እነዚህ ግሶች ተመኵሳይያን
ናቸው በማለት በመጽሐፈ ሰዋስው የተጠቀሱት በአንድ ቃል ተነበው በብዙ ነገር
የሚፈቱ ግሶች በሚል በመኾኑ በመካከላቸው ያለውን የትርጕም አንድነትና ልዩነት
እንመረምራለን፡፡ ለዚህ መነሻ የሚኾነው ደግሞ በመጽሐፈ ሰዋስው የግሶቹን ትርጕም
መለያየት ለማሳየት የተጠቀሱት አስረጂዎች ናቸው፡፡
61
.
ሐፀነ--መገበ
በመጽሐፈ ሰዋስው እነዚህ ግሶች በአንድ ቃል ተነበው በብዙ ነገር የሚፈቱ በማለት
የተመደቡ በመኾኑ በመጀመሪያ የምናየው የንባብ አንድነታቸውን ነው፡፡ ከምሳሌዉ ገጸ
62
.
በዐረብኛ ቋንቋ ማሳደግ/ bring up ሐፀነ ፤ ጡት/ breast ሒፅን፤ በዕበራይስጥ ደግሞ
ደረት/ bosom ሔጻን፤ ልጅ/ boy, child/ በትግረኛ ሕጽኒ፣ በትግረ ሕጽን ወይም
ሕፃን--ሕጻን ተብሎ እንደሚተረጐም በሌስሎው (1991፣ 226) የግእዝ መዝገበ ቃላት
ላይ ተመላክቷል፡፡
63
.
64
.
65
.
በሌላ በኩል ኪዳነ ወልድ (1948፤ 228፣ 229) ዐወቀ ለሚለው የአማርኛ ግስ
ትክክለኛዉ የግእዝ ግስ አመረ (መ ሳይጠብቅ) እንደኾነና አእመረ--አወቀ ብሎ
አስደራጊዉ በአድራጊነት መተርጎሙ ስሕተት እንደኾነ ነው የሚገልጸው፡፡ ለዚህ
ምክንያቱ ደግሞ የሴም ቋንቋዎች የጋራ ባሕሪ የግስ ሥር/ ቅንጣጢት ሦስት መኾኑ
እና በትግረ ቋንቋም ዐወቀ ለማለት አመረ ተብሎ የሚገኝ መኾኑ ነው፡፡ ሌስሎውም
(1991፤ 25) የኪዳነ ወልድ ሐሳብን በሚያጠናክር መልኩ ማዎቅ፣ መገንዘብ/ know,
understand/ የሚለው ግስ በትግረ ኣማረ ተብሎ እንደሚጻፍ በመዝገበ ቃላቱ ያመለከተ
ቢኾንም ነገር ግን ዐወቀ ለማለት የተጠቀመው የግእዝ ግስ አእመረ የሚለውን ግስ
ነው፡፡
ባንድ በኩል የኪዳነ ወልድ ሐሳብ ተገቢነት ያለው ቢመስልም በሌላ በኩል እንደ
አጥረየ፣ ተንበለ፣ ኖለወ/ ነውለወ የመሳሰሉ ባለአራት እግር ግሶች መኖራቸው ሲታይ
አእመረም ከዚሁ የሚመደብ እንጅ የአስደራጊ ግስ መነሻ በኾነው ‘አ’ ስለተነሣ ብቻ
አስደራጊ ግስ ነው መባሉ ተገቢ አይደለም የሚል መከራከሪያም ሊያስነሣ ይችላል፡፡
66
.
67
.
ምዕራፍ አራት
4. 1 ማጠቃለያ
በርእሰ ጉዳዩ እና ከርእሰ ጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በፅንሰ ሐሳብ ደረጃ
ከተብራሩ በኋላ በምዕራፍ ሦስት በተሰበሰቡት መረጃዎች መነሻነት በርእሰ ጉዳዩ ላይ
ንጽጽራዊ ትንተና ተደርጎ ለተነሡት ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ ለማነጻጸሪያነት
አጥኚዉ የተጠቀማቸዉ ተዛማጂ የሴም ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ የዐረብኛ፣ የዕብራይስጥ፣
የትግረኛና የትግረ ቋንቋዎች ሲኾኑ ብዙዎቹ ማስረጃዎች የተወሰዱት ከኪዳነ ወልድ
መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት (1948) እና ከሌስሎው ንጽጽራዊ የግእዝ መዝገበ
ቃላት/ Comparative Dictionary of Geez (1991) ነው፡፡ የያሬድ መጽሐፈ ግስ ወሰዋስው
(2000) እና የግእዙ ሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስም (2009) እንዳስፈለጊነታቸው
ለማነጻጸሪያነት ተጠቅሰዋል፡፡
በመጽሐፈ ሰዋስው ተመኵሳይያን ቃላት በአራት መደብ ተለይተው የተብራሩ ሲኾን በዚህ
ጥናትም ተመኵሳይያን የተብራሩት በተመሳሳዪ በአራት ክፍሎች ተመድበው ነው፡፡
68
.
ቃላት ካላቸው ትርጕም አንጻር ደግሞ በጥናቱ የተረጋገጠው አድራጊና አስደራጊ ወይም
አድራጊና ተደራጊ መስለው ጥንድ ኾነው የተቀመጡት ግሶች ከአንድ የግስ ቅንጣጢት
69
.
70
.
የተለየ ትርጕም ያላቸው ቃላትም የቃሉ የግስ ቅንጣጢት አንድ እስከኾነ ድረስ ለቃሉ
የተለያየ ትርጕም መሰጠቱ ትርጕም ማስፋት ከሚባል ውጭ ሞኵሼነትን የሚያሟላ
አይደለም፡፡ ምክንያቱም አንድ ሰው የተለያየ ሙያ ባለቤት በመኾኑ ምክንያት በተካነበት
ሙያ ኹሉ መጠራቱ ሰውየውን የተለያየ ሰው እንደማያደርገው ኹሉ ቃላቱም በተመሳሳዪ
በትርጕም የበለጸጉ መኾኑን የሚያሳይ በመኾኑ ነው፡፡ ቃላቱ የተለየ ትርጕም
ባይኖራቸውም ተደጋግመው በተጻፉ ቁጥር የተዋቀሩበት ፊደልም እንደሚለያይ ነው
በጥናቱ የተረጋገጠው፡፡
71
.
4.2 መደመደሚያ
72
.
73
.
በተመሳሳዪ ግሶች በተገቢዉ ፊደል ሳይከተቡ፤ የተጻፉበት ፊደልም የተለያየ መኾኑ ከገጸ
ንባቡ በግልጽ እየታየ እና በመካከላቸዉ የትርጕም ልዩነት ሳይኖር ግሶች ተመኵሳይያን
የተባሉበት ሌላዉ ክፍል ደግሞ በአንድ ቃል ተነበው በብዙ ነገር የሚፈቱ ቀላትን
የሚመለከተው ክፍል ነው፡፡
ለምሳሌ፦ ኀፀነ--አሳደገ
ሐፀነ--መገበ
አእመራ--አወቃት
74
.
ይህ ጥናት የታየ ገብረ ማርያም መጽሐፈ ሰዋስውን መነሻ በማድረግ ተመኵሳይያን ቃላት
ላይ በማተኮር የተደረገ ሲኾን ታየ ቃላትን ለማዋቀር በተለምዶ ሞኵሼ እየተባሉ የሚጠሩ
ፊደላትን በዘፈቀደ የተጠቀመ መኾኑ የጥናቱ አንዱ እና ዋናዉ ውጤት ነው፡፡ የዚህ ቀላል
ማስረጃ ደግሞ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው በሚመስሉ ፊደላት የሚዋቀሩ ግሶች በተገቢዉ
ፊደል ካለመዋቀራቸውም በላይ ግሶቹ ሌላ ቦታ ላይ ሲጠቀሱ እንዲሁም ለየግሶቹ
በማስረጃነት ከሚጠቀሰው ዐረፍተ ነገር ውስጥ ግሶቹ ወደ ሌላ የቃል ክፍል ሲቀየሩ በሌላ
ተመሳሳዪ ድምፅ ባለው ፊደል ተጽፈው መገኘታቸው ነው፡፡ ይህም ተመሳሳዪ ድምፅ
ያላቸው የሚመስሉ ፊደላት አንድ ዐይነት ናቸው ከሚል ድምዳሜ ላይ ታየ የደረሰ
መኾኑን ያሳያል፡፡ በቅርጽ ተለያይተው በድምፅ ተመሳሳዪ በሚመስሉ ፊደላት የተዋቀሩ
ጥንድ ቃላትም ተመኵሳይያን መባላቸውም የዚሁ ውጤት ነው፡፡
በዘርፉ ምሁራንም ችግሩን ከማረም ይልቅ እንዳለ ማስቀጠላቸው ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸው
የሚመስሉ ፊደላትን አጠቃቀም በተመለከተ በዘፈቀደ መጠቀም የታየ ገብረ ማርያም ብቻ
ሳይኾን የሌሎች ምሁራንም አቋም መኾኑን ያሳያል፡፡ የዚህ ማሳያ ደግሞ ከመጀመሪያዉ
የመጽሐፈ ሰዋስው ዕትም በኋላ በተለያዩ ምሁራን የታታሙ የዚሁ የመጽሐፈ ሰዋስው
ቅጅዎች አንዳንዶቹ ከመጀመሪያዉ ዕትም ጋር ተመሳሳዪ በኾነ መልኩ ሌሎቹ ደግሞ
ከመጀመሪያዉ ዕትም በተለየ መልኩ ሌላ ዘፈቀዳዊ የኾነ የፊደል አጠቃቀም መከተላቸው
ነው፡፡ በመልክእ ደራሲዎች፣ በቅኔ ዘራፊዎች እና በግጥም ገጣሚዎችም ሳይቀር ተመሳሳዪ
ድምፅ ያላቸው የሚመስሉ ፊደላት በቤት መምቻነት በዘፈቀደ ጥቅም ላይ መዋላቸውም
ሌላዉ ማሳያ ነው ፡፡
75
.
ቋንቋ በተለይ የራሱ የኾነ ፊደል ያለው ቋንቋ ያንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የማንነት
መገለጫ እና መለያ እንደመኾኑ መጠን የግእዝ ቋንቋ ከነፊደላቱ ተጠብቆ መቆየት
ያለውን ታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በጥናትና በምርምር ተመሥርቶ ትውልዱ
ግንዛቤ እንዲኖረው ቢሠራ፡፡ ይህም በምላሹ በግእዝ ቋንቋ የተጻፉ ቀደምት
መዛግብትን አንብቦ ለመገንዘብና ከያዙት ቁም ነገርም ትውልዱ የጥቅሙ ተካፋይ
እንዲኾን ያስችላል፡፡
ፊደላት የሚቀረጹት ለአንድ ድምፅ አንድ ውክልና በሚል መርሕ መኾኑ እየታወቀ
በተለምዶ ሞኵሼ እየተባሉ የሚጠሩት ፊደላት ተመሳሳዪ አንደኾኑ ተቆጥሮ በሥርዐተ
ጽሕፈት ጊዜ ፊደላቱን በዘፈቀደ መጠቀምና ከዚህም አልፎ የፊደላት ድግግሞሽ ስለበዛ
ፊደላት ይቀነሱ የሚል መከራከሪያ መነሣቱ የፊደላቱን ድምፅ ለይቶ ካለማወቅ የተነሣ
በመኾኑ ድምፃቸዉን መልሶ ለማግኘት ፊደላቱን በጽሑፍ አንዳንዶቹንም ደግሞ
በድምፅ ለይቶ በማቆየት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ያላቸውን አካላትና የሌሎች ተዛማጂ
የሴም ቋንቋዎች ምሁራንን ጭምር በመጋበዝ ተገቢዉን ጥናትና ምርምር ቢደረግ፡፡
የግእዝ ቋንቋ የአንድ ሃይማኖትና ብሔር ቋንቋ ነው የሚል ዕሳቤ በትውልዱ እንዳይኖር
የሌሎች እምነት ተከታዮችም ኾኑ የሌሎች ብሔር ተወላጆች በግእዝ ቋንቋ ጥናትና
ምርምር ውስጥ እንዲሳተፉ ኹኔታዎችን ማመቻቸትና ዕድሎችን ማስፋት፡፡
ፊደላቱ ለአጠቃቀም ቀላልና ምቹ ይኾኑ ዘንድ ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂ የተደገፈ
ሥርዐተ ጽሕፈት እነዲኖር በማድረግ ተመሳሳዪ ድምፅ ያላቸውን ፊደላት ብሎም
አጠቃላይ የቋንቋዉን ተቀባይነት ማስፋት፡፡
የቋንቋዉን ሥርዐተ ሰዋስውና ርባታ በተመለከተ መጽሐፍ እንዲህ ሲል ይገኛል
በማለት በደፈናው ከመቀበል ይልቅ ትክክል የኾነውንና ያልኾነውን በምርምር ለይቶ
በማውጣት እና ስሕተት ኾኖ የተገኘውን በማረም ቋንቋዉን ማበልጸግ የሚሉት
በመፍትሔ ሐሳብነት የቀረቡ ናቸው፡፡
76
.
ማጣቀሻ መጻሕፍት
ድርጅት፡፡
CaliforniA.
ማተሚያ ቤት፡፡
ደራስያን ማኅበር ፡፡
77
.
Verlage
ስማቸው ንጋቱ፡፡ (2009) ፡፡ ቅኔና ባለቅኔዎች ፡፡ 3ኛዉ ሀገር አቀፍ የግእዝ ዐውደ
Allen.
በላይ መኮነን፡፡ (2009) ፡፡ የግእዝ ቋንቋ ትላንት፣ ዛሬና ነገ፡፡ 3ኛዉ ሀገር አቀፍ የግእዝ
በርግ= Bruce L, Berg. (2001). Qualitative Research Methods for Social Sciences.
78
.
ተስፋ ገብረ ሥላሴ፡፡ (1982) ፡፡ መጽሐፈ ሰዋስው (መጽሔተ አእምሮ) ፡፡ አዲሰ አበባ፣
አምሳሉ ተፈራ ፡፡ (2006) ፡፡ “ዓለም አቀፍ የግዕዝ ጥናት - ምጥን ምልከታ” ፡፡ ሐቃፌ
ቤት፡፡
University.
79
.
ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፡፡ (1948) ፡፡ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፡፡ አዲስ
Harrassowitz. Wiesbaden
አበባ፣ትንሣኤማሳተሚያ ድርጅት፡፡
80
.
ድርጅት፡፡
ደስታ ተክለ ወልድ፡፡ (1946) ፡፡ ግእዝ መሠረተ ትምህርት፡፡ አደስ አበባ፣ አርቲስቲክ
ማተሚያ ቤት፡፡
81