You are on page 1of 18

የአብክመ ከተማና መስረተ ልማት ቢሮ

አሸባሪው ህወሃት የከፈተብንን ጦርነት አስመልክቶ ለህዝቡ


ማስጨበጥ ያለብን

ዋና ዋና መልዕክቶች
ነሐሴ 2014 ዓ.ም

ባህር ዳር -ኢትዮጵያ
አሸባሪው ህወሃት የከፈተብንን ጦርነት አስመልክቶ
ለህዝቡ ማስጨበጥ ያለብን
ዋና ዋና መልዕክቶች

1. አገራዊ ለውጡና ህወሃት

➢ ባለፉት አራት አመታት በአገራችን የተቀጣጠለው የለውጥ እንቅስቃሴ አገርን ከብተና

ያዳነ ነበር

➢ በርካታ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎች ተወስደዋል፣

➢ በርካታ ተጨባጭ ለውጦችም መጥተዋል

➢ አገራችንን ከቁልቁለት ጉዞ የታደገ አገራዊ ለውጥ ነበር

➢ በዚህ የለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ህወሃት ዋነኛ ተሳታፊና የትግራይ ህዝብም የለውጡ ተጠቃሚ
እንዲሆን ያልተደረገ ጥረት የለም፣ 
የቀጠለ…..

➢ በዚህም የትግራይ ህዝብም ሆነ ህውሀት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በለውጡ አመራር


በርካታና ተደጋጋሚ ሙከራዎች ተደርገዋል፣

➢ የአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ እናቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተለያዩ


የህብረተሰብ ክፍሎች መቀሌ ድረስ በመሄድ ቡድኑ ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣ
ለምነዋል፡፡

 
የቀጠለ……
ይሁን እንጂ አሸባሪው ህወሃት ከለውጡ መነሻ ጀምሮ የማደናቀፍና አገር የማፍረስ
ተልዕኮ ይዞ ሲንቀሳቀስ ነበር፣
➢ ከጅምሩ ለውጡ እንዳይሳካና እንዲደናቀፍ የተለያዩ መሰናክሎችን ሲፈጥር
ቆይቷል፡፡
➢ ለውጡን በተመለከተ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመንዛት ህዝቡ በለውጡ ላይ
ጥርጣሬ እንዲያድርበት የቻለውን ሁሉ ቢሞክርም አልተሳካለትም፣
➢ የሽግግር መንግሥት መቋቋም አለበት በሚል በግራ በቀኝ ቢወተውትም ሰሚ
ሳያገኝ ቀርቷል፣
➢ ቡድኑ መቀሌ መሽጎ የትግራይን ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለመነጠል
ሙሉ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፣
➢ ከፌደራል መንግሥቱ ተነጥሎ የራሱን ህገወጥና ኢ-ህገ መንግስታዊ ምርጫ
ለማድረግም ሞክሯል፣
➢ በአገሪቱ ጽንፈኛና አክራሪ ሀይሎችን በማደራጀት፣ በማሰልጠን፣ በሎጀስቲክስ
በመደገፍና በማሰማራት በመላው አገሪቱ ህይወት እንዲጠፋ፣ ንብረት
የቀጠለ……
 ዜጎች እንዲፈናቀሉና የህዝብ ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ ሲያደርግ
ቆይቷል፣
 በተለያዩ አካባቢዎች የተቀናጀ የኢኮኖሚ አሻጥር በመፈጸም የአገሪቱን ኢኮኖሚ
ለማሽመድመድ በርካታ ጥረቶችን አድርጓል፣
 ከላይ ከተገለጹት ከፍ ባለ ሁኔታ በአገሪቱ ላይ ወታደራዊ ጥቃት ለመፈጸም እቅድ
አዘጋጅቶ የሰው ሀይል አሰልጥኖ፣ ከቀላል እስከ ከባድ የጦር መሳሪያ ታጥቆ የጥላቻ
ፕሮፓጋንዳ በህዝቡ ውስጥ አሰራጭቶ በኢትዮጵያ ላይ ወታደራዊ ጥቃት ለመፈጸም
ሙሉ ዝግጅት ሲያደርግ ነበር፣
 በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ሁሌም ለሰላም እጁን እንደዘረጋ፣ ቡድኑ
ወደ ሰላም መንገድ እንዲመጣ አሉ የተባሉ አማራጮችን ሁሉ ያለመታከት ሲያቀርብ
ነበር፡፡
 መንግሥት ከጅምሩ ለአንድ ደቂቃም የሰላም እጁን ከመዘርጋት ቦዝኖ አያውቅም
 በለውጡ ወቅት የተዘረጉ የሰላም እጆች ሁሉ ግን በአሸባሪው ቡድን ተነክሰዋል፡፡
2. የአሸባሪው ህወሃት የመጀመሪያ ዙር ጥቃት
 አሻባሪው ህወሃት ኢትዮጵያን ማፈራረስና አ ማ ራ ን ቅ ስ ሙ ን መ ስ በ ር አቅዶ
አስቦበት የሚያከናውነው እኩይ ተግባር ነው፣
 ከለውጦ እለት ጀምሮ እኔ ያልመራኋት ኢትዮጵያ መፍረስ አለባት በሚል እኩይ ሀሳብ ነው
የጥፋት ተልዕኮውን ሲፈጽም የነበረው፣
 ጥቅምት 24 ቀን 2 0 1 3 ዓ.ም በጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው
ታሪክ የማይረሳው ጥቃት የቡድኑን የጭካኔ ልክ ያሳየ ነው፡፡
 ህብረ-ብሄራዊ የአገር መከላከያ ሰራዊታችን የኢትዮጵያዊነት አርማ በመሆኑ እሱን ቀድሞ
ለማፈራረስ አቀደ፡፡
 አገራዊ ክብራችንን ያስጠበቀ ሰራዊትን በለሊት በጭካኔ ጨፈጨፈ
 በታሪክ ዉስጥ አንገታችንን ቀና አድርገን በአለም ፊት እንድንታይ ያደረገ የሉዓላዊነታችን
መገለጫን የኔ ብሄር ከሚለው ውጭ ያለውን ለይቶ አረደ፣
 የትግራይን ህዝብ በሰላሙም በልማቱም ሲደግፍ ከ20 ዓመት በላይ አብሮት የኖረን ሰራዊት
በተኛበት በበርካታ ምሽጎች በአንድ ጊዜ ተኩስ ከፍቶ ወታደሩን ከነሲቪል ሚስቶቹና ልጆቹ
ጨፈጨፈ 
 
የቀጠለ…..
➢ በዚያች ለሊት በሰሜን ዕዝ ካምፖች የተፈጠረዉ አሳዛኝ ጭካኔ ተጽፎ የዚህ ት ዉልድ ታሪክ ሆኖ
ተቀምጧል፡፡ አሁን ያለዉም ቀጣዩም ትዉልድ ይማርበታል፡፡
➢ መከላከያችን ጀግና በመሆኑ መስዋዕትነት ከፍሎ ጥቃቱን መቋቋምና እንደ አገር
አለኝታ ተቋም ተጠናክሮ መቀጠል ችሏል፣
➢ የተከፈተበትን ጥቃት ተከትሎ መንግሥት በወሰደው የህግ ማስከበር እርምጃ አሸባሪ ቡድኑ
አከርካሪው ተመቶ ተንቤን ዋሻ ሊገባ ችሏል፡፡
➢ መንግሥት የወቅቱን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት ከምንም በላይ የትግራይ ህዝብ የሰላም አማራጭ
ተጠቃሚ እንዲሆን በማሰብ ሁለተኛ ዙር የሰላም እጁን ለቡድኑ ዘረጋ፣
➢ ለዚህ እንዲመችም የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ በመወሰን ከትግራይ ክልል ወጣ፣ ዓላማው
ለቡድኑና ለትግራይ ህዝብ የጥሞና ጊዜ በመስጠት ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱና የትግራይ
ህዝብም እፎይ እንዲል ነበር፣
➢ በዚህ ጊዜ የተዘረጋው የሰላም እጅም ለሁለተኛ ጊዜ ተነከሰ፣ አሻባሪው የሰላም አማራጭ የሚባል
ነገር መስማት አይፈልግም፣ ጦርነትና ደም መፋሰስ ብቻ ነው ስሪቱ፣
3. የአሸባሪው ህወሃት ሁለተኛ ዙር ጥቃት

 አሸባሪው ለሁለተኛ ጊዜ የተዘረጋለትን የሰላም እጅ ነክሶ ሁለተኛ ዙር ጥቃት በኢትዮጵያ


ላይ ከፈተ፣
 ለኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ደግሞ ለትግራይ ክልል በዚህ የጥፋት ቡድን ምክንያት
ለዘመናት ለሚሰቃዩ ወገኖቻችን ወርቃማ የሰላም አጋጣሚ ነበር፣ እሱንም አመከነው፡፡
 ይባስ ብሎ የመንግሥትን የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ ወስኖ ከትግራይ ክልል መውጣት
እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ በአማራና በአፋር ክልሎች ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት ከፈተ፣
 የደሃ የትግራይ እናቶችን ልጆች እንደ ማገዶ ተጠቅሞ ሁለተኛ ዙር መጠነ ሰፊ ጥቃት
ሰነዘረ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናትና ታዳጊዎችን ማግዶ አገር የማፍረስ ጥማቱን
ለማሳካት ሞከረ፣
የቀጠለ…
 በአገሪቱ በተለይም በአማራና በአፋር ክልሎች ንጹሃን ለፍቶ አዳሪዎችን ፈጀ፣ የሺዎችን
ህይወት አጠፋ፣ አካል አጎደለ፣ አፈናቀለ፣ አስገድዶ ደፈረ፣ በጅምላ ጨፈጨፈ፣
ማህበረሰብን አወደመ፣
 የህዝብና የግል ንብረቶችን በጭካኔ አወደመ፣ ነቅሎ ጭኖ ወሰደ፣ ቤተ እምነቶችን ሳይቀር
በከባድ መሳሪያ አጋየ፣ የመንግሥት ንብረቶችን አወደመ፣ የህዝብ መሰረተ ልማቶችን
እንዳይጠገኑ አድርጎ አፈራረሰ፣
 ይህ ቡድን ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን አጥብቆ የሚጠላ፣ ሰላም ጸሩ የሆነ ኢትዮጵያን
ለማፈራረስ የራሱንና የውጭ ታሪካዊ ጠላቶቻችንን ተልዕኮ ይዞ በጭካኔ የዘመተብን አሸባሪ
ቡድን ነው፡፡
 ህብረ ብሄራዊ ኢትዮጵያዊ አንድነታችን ለዘለዓለም ይለምልምና አሸባሪው እንደተመኘው
ኢትዮጵያን ማፍረስ አልቻለም፣
የቀጠለ…

 ኢትዮጵያውያን በርካታ የውስጥና የውጭ ጫናዎችን ተቋቁመው የአሸባሪውን ቡድን አከርካሪ


መስበር ችለዋል፣
 ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን ጨምሮ በፌደራልና በክልል ያሉ የጸጥታ ሃይሎቻችን
ተቀናጅተው በመሥራትና አሸባሪውን በመቅጣት ማንኛውም ምድራዊ ሀይል ኢትዮጵያችንን
ማፍረስ እንደማይችል ለአሸባሪው ብቻ ሳይሆን ለአለምም ትምህርት ሰጥተዋል፡፡
 በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ የብሄር፣ የኃይማኖት፣ የጎሳ፣ የፖለቲካ አመለካከትም ሆነ ማንኛውም ልዩነት
እንደማይገድበን ለአለም አሳይተዋል፣
 የአሸባሪው ሁለተኛ ዙር ጥቃትም በህልውና ዘመቻው በኢትዮጵያውነት አሸናፊነትና በቡድኑ
አሳፋሪ ሽንፈት ምክንያት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
 አሸባሪው ዳግም ተመቶ ከተመለሰም በኋላ የመንግሥት ዋና ትኩረት አሉ የተባሉ የሰላም
አማራጮችን በመጠቀም የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም ደግሞ የትግራይ ህዝብ የሰላም እፎይታ
እንዲያገኝ ነበር፣
የቀጠለ…

 ችግሩን በሰላማዊ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የቀረበውን አማራጭና የአለም


አቀፍ ማህበረሰብ ጥሪ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በመቀበል ለዚህ ዝግጅት ማድረግ ጀመረ፣
 ለሰላማዊ መፍትሄ ያለውን ቁርጠኝነትና ዝግጁነትም ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ
በተደጋጋሚ ሲያሳውቅ ቆይቷል፣
 ከፍላጎትም በላይ በመሄድ በርካታ ተግባራዊ እርምጃዎችን ወስዷል፣ የሰላም አማራጭ
ኮሚቴ ሰይሞ ይፋ አድርጓል፣ የውይይት እቅድ አውጥቶ እንቅስቃሴ ጀምሯል፣
 በይፋም መንግሥት ከቡድኑ ጋር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የትም፣ መቼም፣ በማንኛውም
ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል፣
 በዚህም ለሰላማዊ መፍትሄ ያለውን የማይናወጥ አቋም ገልጧል፣
የቀጠለ…
 ይሁን እንጂ አሸባሪው አሁንም የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር የሰላም አማራጩ
እንዳይሳካ ሲያደርግ ቆይቷል፣ ሰላም ፈላጊ ባለመሆኑ በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ
ጉዳዮችን ሁሉ እንደ ቅድመ ሁኔታ እየደረደረ ለሶስተኛ ጊዜ የተዘረጋውን የሰላም
አማራጭ ረግጧል፡፡
 እኛ ድርድርን እንደ ማደናገሪያ ነው የምንጠቀመው ብሎ በሰነድ እንደጻፈው ሁሉ
በተግባርም የሰላም አማራጭ እንዲመክን አድርጓል፣
 የሰላም እጅ ሲዘረጋለት ለሶስተኛ ጊዜ ነክሶ የጦርነት ነጋሪት ከመጎሰም አልፎ ጦርነት
አውጇል፡፡
4. የአሸባሪው ህወሃት ሶስተኛ ዙር ጥቃት

 የአለም አቀፉን ማህበረሰብና የኢትዮጵያውያንን የሰላም አማራጭ ልመና ረግጦ አሸባሪው


ቡድን ሶስተኛ ዙር ጦርነት በክልላችን በሰሜን ወሎ ዞን ግዳንና ቆቦ አካባቢ እና በአፋር
አዋሳኝ አካባቢወች ጦርነት ከፍቷል፣
 በተለያዩ አካባቢዎች እንደለመደው የሰው ማዕበል እያሰለፈ ጥቃት እየፈጸመ ይገኛል፣
 ከባድ መሳሪያዎችን በንጹሃን መንደር ላይ እየተኮሰ ሰላማዊ ዜጎችን በጅምላ እየፈጀ
ይገኛል፣
 አሁንም መተማመኛችን ክንዳችን ነው፣ እንዋጋለን በማለት ለሰላም አማራጭ በር እየዘጋ
ይገኛል፣
 ከታሪካዊ የውጭ ጠላቶቻችን የሚደረግለትን ድጋፍ በመጠቀም ኢትዮጵያን የማፈራረስ
ተልዕኮውን ለማሳካት እየተፍጨረጨረ ይገኛል፣
የቀጠለ…

 ስለሆነም አሸባሪው ህወሃት በተደጋጋሚ የተፈጠረውን የሰላም አማራጭ


ለሶስተኛ ጊዜ ረግጦ ሶስተኛ ዙር ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ ከፍቷል፣
 ለጥቃቱ እንዲረዳው ለዘመናት የተካነበትን የስርቆትና የዘረፋ ተግባር
አጠናክሮ
 በመቀጠል የተባበሩት መንግሥታት ለሰብዓዊ ድጋፍ ያዘጋጁትን ነዳጅ
ጭምር በመዝረፍ የወረደ አሸባሪ ቡድን መሆኑን ለአለም አስመስክሯል
5. የመንግሥት አቋምና አቅጣጫ

 መንግሥት የሰላም አማራጭ በር ምን ጊዜም የማይዘጋ መሆኑን ያሳውቃል፣


 የአገራችን የፖለቲካ ችግር መፍትሄ የሚያገኘው በሰላማዊ አማራጭ ብቻ ነው፡፡
 ሰላም ፈላጊነታችንን አለም እየተገነዘበ በመምጣት ላይ ይገኛል፣
 ዛሬም፣ ነገም፣ መቼም ችግሩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ ነን፣
 ይህ ቡድንም ወዶም ሆነ ተገዶ ወደ ሰላማዊ መፍትሄ እንዲመጣ፣ ቁጭ ብሎ እንዲወያይ
የሚያደርጉ አማራጮችንና እርምጃዎችን እንወስዳለን፣
 አለም አቀፉ ማህበረሰብም በዚህ አሸባሪ ቡድን ላይ ጫና እንዲያሳድርበት የሚያደርግ
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ እንሰራለን፣
 ቡድኑ የሰላም አማራጮችን እየረገጠ በጦርነት ጎዳና የሚያደርገው ጉዞ እንዲቆም
የሚያደርጉ እርምጃዎችን እንወስዳለን፣
የቀጠለ…
 የተዘረጋው የሰላም እጃችን አይታጠፍም፣ አለምም ይህን ይወቅልን፣
 ነገር ግን አሁን ጥቃት ተከፍቶብናል፣ አሸባሪው በበርካታ ግንባሮች ጦርነት ከፍቶብናል፤ ይህን
እናስቆማለን፡፡
 የጸጥታ ሀይሎቻችን የዚህን አሸባሪ ቡድን ጥቃት በጀግንነትና በብቃት እየመከቱ ይገኛሉ፤ የትላት
አማራን እና መላው የኢትዮጰያ ህዝብ ለማንበርከክና ሀገር ለመበተን ያለመውን ፍላጎቱንም
ያመክናሉ፡፡
 የተከፈተብንን ጦርነት በብቃት በመመከት የአሸባሪውን ፍላጎት እናመክናለን፣
 ለዚህ ደግሞ ጀግናው መከላከያ ሀይላችንና ሌሎች የጸጥታ አካላት በሙሉ ዝግጅትና ሞራል
በተጠንቀቅ ቆመው ይገኛሉ፣
 የተቃጣብንን ጥቃትም በከፍተኛ ጀግንነት በመመከት ላይ ይገኛሉ፣ የአሸባሪውን
 ፍላጎት ፍጹም እንዳይሳካ አድርገው በመከላከል ላይ ናቸው፡፡
 የአሸባሪው የማያባራ የጦርነት ፍላጎትና የሰላም እጆች ንክሻ ማብቂያ ሊበጅለት እንደሚገባ
መንግሥት ያምናል፣
የቀጠለ…
 ይህንን መላው ኢትዮጵያውያን እንዲረዱትና ይህ እኩይ ቡድን ኢትዮጵያን የማተራመስ ፍላጎቱ
እስከ ወዲያኛው እንዲመክን ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና መጫወት አለባቸው፣
 ይህ ቡድን አሁን በጀመረው መልኩ ኢትዮጵያ ላይ ጥቃት እየፈጸመ የአገርን ሰላም እያደፈረሰ
እንዲቀጥል አይፈቅድም፣
 ለሰላም የተዘረጋው እጃችን ሳይታጠፍ አስፈላጊ የተባለ እርምጃ በአስፈላጊው ሰዓት ይወሰዳል፣
 ለዚህ ሁሉም የጸጥታ ሀይሎቻችን ዝግጁ ናቸው፣ በተመሳሳይ በሁሉም አካባቢ ያለው ህዝባችን
ዝግጁነቱን ዳግም እንዲያረጋግጥ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
 ኢትዮጵያውያንም እንደተለመደው በብሄር፣ በሀይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከትም ሆነ
በማንኛውም የልዩነት ሀሳብ ሳንከፋፈል በአንድነት መቆም ይገባናል፣
 ማንኛውም ዜጋ በአስፈላጊ ቦታና ጊዜ አገሩን ከጥቃት ለመከላከልና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር
በሚደረገው እንቅስቃሴ ውስጥ በሚችለው ነገር በንቃት መሳተፍ ይጠበቅበታል፣
የቀጠለ…

 በህብረ ብሄራዊ አንድነታችን ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ከውጭ ሆነው የሚያሰማሩትንም


ሆነ ተልዕኮ ወስደው የሚያተራምሱን ሀይሎች አከርካሪያቸው ተሰብሮ አፍረው
እንደሚመለሱ ለሰከንድም አንጠራጠርም፡፡
 
ሰላማዊ መንገድ እንዳይዘጋ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ህወሃትን ወደ
ሰላም መንገድ ሊያመጣው ይገባል
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች !!
ነሀሴ 2014
በህርዳር-ኢትዮጵያ

You might also like