Professional Documents
Culture Documents
Amharic Proverb
Amharic Proverb
ሲተረጉሙ ይደረግሙ።
%
ዓባይ ማደሪያ የለው፥ ግንድ ይዞ ይዞራል።
አልሸሽም ዞር አሉ።
%
ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል።
ሥጋ እበላ ብዬ የቆረጥኩትን፣
%
እብድ ቢጨምት እስከ እኩለ ቀን ብቻ ነው።
በሬ ካራጁ ይውላል።
ማን ቢስምሽ ማሞጥሞጥሽ።
ሳይከካ ተቦካ።
ሴቷንም መፍታት፣
ቤቱንም ለእሳት።
ሰው በሰው፣ ቅቤ በጨው።
%
ስትሠራ ውላ አበላሸችው ባተላ።
ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ።
%
ደባልና ሹመት አለሰበብ አይሄድም።
ቅቤ አንጣሪዋ እያለች፣
ድኃ ሞኝ ነው ሞቱን ይመኛል።
%
የተነቃነቀ ጥርስ ሳይወልቅ አያርፍም።
ውሻ ካልቀበጠ ጅብ አይበላውም።
%
ከጉንዳን ቤተሰብ ትልቁ ትንሽ ነው።
%
የሞተ ሰው ሠርጉ ሦስት ቀን ነው።
ዕቃ እንደባለቤቱ ነው።
ጠላ ነው መልሱ ከነበረበቱ።
ማድጋውን ሁሉ ታስቆጥራላችሁ፣
ሰውን ሰው ናቀው፣
የራሱን ሳያውቀው።
%
ዳኛ ሲገኝ ተናገር፣
ውኃ ሲጎድል ተሻገር።
ሐሰተኛ በቃሉ፣
ስደተኛ በቅሉ።
መዋቀስ፣
መራከስ።
አባይ ከደፈረሰ፣
አባይም አያሻግር፣
ባለጌም አያናግር።
%
ወንድሙን ሲገድሉት ወንድሙን ካልከፋው፣
ፍሬ ፍሬ ላይ ቆሞ ጎተራ ይሞላል።
ገረዴ ሄዳ በድንገት፣
አሽክሬ ሆና ወጥ ቤት፣
የምበላው ሳይጠይቀኝ፣
ሥራ ሰርቶ አስጨነቀኝ።
እንኳንስ ለኔ ለሰው፣
ማን ባመጣልኝ እምነት፣
እሱ ነበር መድኃኒት።
ሰው በሰው ላይ እየገባ።
ዳማ ሲሄድ ዳማ፣
ሌላ ባለጋማ፣
ሌላ ባለጭራ፣
ይመጣል በተራ።
%
መገለባበጡን ጥሩ ተክህኖታል።
%
አባት የላት አያት አማራት።
ከቆረበች ባሰች።
%
ክረምትና ጊዜ የማያወጡት ምስጢር የለም።
ሰውን ሰው ናቀው፣
የራሱን ሳያውቀው።
ሲያረጁ
አምባር ይዋጁ።
መጭውን ሁሉ ገልጦላቸው፣
ሁሉ እንዳለሙት ነው።
ሞት ገበሬ ነው በእውነት፣
እሰው ቤት ኗሪ ስዋትት፣
ያስደንቀኛል በተግባሩ፣
ያፍሰዋለና አትመን።
ይታረቀዋል አሁን፣
እረግሞት አይቀርም።
እዚያ ላይ ሆኖ ቢጠራኝ፣
አቤት!አቤት!ጌታዬ።
አክፍሎት አለ በግድ፣
የሰው ሁሉ መጎጃው
የእየሩሣሌም ነጋዴ፣
ጣለበት አሉ ወንበዴ፣
ለገንዘቡማ ማን አዘነ፣
አወይ ነፍሱን ያዳነ።
ያደኩባትን መሬት፣
ማነው ደጋ ናት ያለት፣
ልናገር እኔ የማውቃት፣
አገሬ ጋራ ናት።
ተው እየሠራህ እለፍ።
አህያ እንደምትታለብ፣
ከላሞች ፊት ትቅለበለብ።
ከተመቱ ማንጠርጠር፣
ጅብ ከሄደ ማጠር።
ቅን በቅን ከማገልገል
ፊት ለፊት ማውደልደው።
ቢበሉበት አያደቅ፣
ቢስቁበት አያደምቅ።
የውኃ ውኃ፣
ምን አለኝ ቀሐ!?
ሰው እንደነገሩት፣
በቅሎ እንዳሰሩት።
ወርቁን በሚዛን፣
እህሉን በላዳን።
በጦር አንደበት፣
በፈረስ አንገት።
ነፍጥ ቢያጓር፣
የወደዱትን ሲያጡ፣
የጠሉትን ቀላውጡ።
አንተ ግፋኝና፣
እኔ ስጋ ላይ እወድቃለሁ።
ወድደህ ከተደፋይ፣
ቢረግጡህ አይክፋህ።
ከብርንዶ ይጥም።
ምላጮች ቢያብጡ፣
በምን ይበጡ!?
%
ብለው ግዛኝ ግዛኝ፣
ሊሸጠኝ አስማማኝ።
ቀን በበቅሎ፣
ማታ በቆሎ።
ብረት ካልፈላ፣
አይሳሳ።
ከመቃለል፣
መጠቃለል።
ገንፎ እፍ እፍ ቢሉህ፣
ሊውጡህ!
ሀሰተኛ በቃሉ፤
ስደተኛ በቅሉ።
ሀሰተኛን ሲረቱ፤
በወንድሙ በእህቱ።
ኃጢያት በንስሀ
በደል በካሳ።
ሄዳ ጉበት ይነሷታል፤
ሆድ ባዶ ይጠላል።
ሆዱን ያለ፤
ሆዱን ተወጋ።
ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል።
ለሞኝ ሰኔ በጋው፤
መስከረም ክረምቱ።
ለፈሪ ሜዳ አይነሱም።
ለሰው ሞት አነሰው።
ለእብለት ስር የለው፤
%
ለብልህ አይነግሩም፤
ለአንበሳ አይመትሩም።
ለምሽት መብራት፤
ለመከራ ጊዜ ብልሃት።
%
ለውጠኝ ባይ የሚሻለውን አውቆ።
ለሆዴ ጠግቤ፤
ለልብሴ አንግቤ።
ለውሽማ ሞት ፊት አይነጭለትም።
%
ለሴት ጠላ ለፈረስ ቆላ አይረባውም።
ለደህና ሰው ዋጋ አነሰው።
ሊያስቡት አይገድም።
ላህያ ማር አይጥማትም።
ላይመራው አማሰነው።
%
ላይበላው አበላሸው።
ላንድ ብርቱ፤
ሁለት መድኃኒቱ።
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል።
ልጅ ያለናት፤
ቤት ያለጉልላት።
%
ልጅ በጡት፤
እህል በጥቅምት።
ልጅና ጥሬ አይተጣጣም።
ልጅ ያለ፤
ልጅ አከለ።
ልጅና ጦጣ ውሀ ይጠጣ።
ልጅ አይወልድ፤
እውነት አይፈርድ።
%
መልካም ወጥ እጅ ያስመጥጥ።
መጓጓት ያከሣል።
መሰስ ሲል ምን ደስ ይል።
መቼ መጣሽ ሙሽራ፤
መቼ ቆረጠምሽ ሽንብራ።
መንገድ ሳለ በዱር፤
በቅሎ ሳለ በእግር።
መሬት በድንበር፤
ውበት በከንፈር።
ሚዳቋ ዘላ ዘላ ተምድር።
ማን ሊስምሽ፤
ታሞጠሙጫለች።
ማን ይንገር የነበረ፤
ማን ያርዳ የቀበረ።
ማን ያውቅ አገር፤
ማን ያጠብቅ ማገር።
ማቅ ያሞቃል፤
ሻሽ ይደምቃል።
ማተብና አንገት፤
ክታብና ደረት።
%
ማሩን አምርሮ፤
ወተቱን አጥቁሮ።
ማረገ ቢስ፤
ራቱ ገሚስ።
ማሽላ ለማሽላ፤
ተያይዞ ቆላ።
ሜዳ መራመድ ሣታውቅ፤
ምን ቢያርሱ፤
እንደጐመን አይጐርሱ።
ምን በእግሩ እየመጣ፤
በእጁ እንዳይመጣ።
%
ምን ያምጣ ድኃ፤
ምን ያግሣ ውሀ።
ምን ያስጠምዱ በዘጠና፤
ቤቱ አይተነ ቀጠና።
ምድር በአለቃ፤
ሰማይ በጨረቃ።
ምጥ ለእናቷ አስተማረች።
ምርት ከአላባ፤
ግዳይ ለሰለባ።
ምስለኔ ሁን እንደኔ።
%
ምስክር ከተጠራ፤
መስዋዕት ከተሠራ።
ራሱን ይነቅል።
ምድር ሲደላደል፤
መሣ ሲታደል።
ምከረው ምከረው፤
ሞኝ ሞኝ አያውቁብኝ ባይ።
ሞት ላይቀር ፍራት፤
%
ሞት ሲደርስ ቄስ፤
ጦር ሲደርስ ፈረሰ።
ሞኝ የተከለው፤
ልባዊ አይነቅለው።
ሞኝና ውሀ፤
እንደወሰዱት ይሄዳል።
ሞኝ ካመረረ፤
በግ ከበረረ፤
መመለሻ የለውም።
ረጅሙን ባላማ፤
አጭሩን በጫማ።
ሩቅ አሳቢ፤
ቅርብ አዳሪ።
ራስ ሳይጠና ጉተና።
%
ራስ ተላጭቶ ወለባ፤
ሮቃ የዝሆን አለቃ፤
ለምሣር አትበቃ።
ሠርቆ ከማሰብ፤
እጅን መሰብሰብ።
ሰው ያመነ ውሀ የዘገነ።
ሰምቶ ዝም፤
አይቶ ዝም።
ሲምር ያስተምር።
ሲሸኝ ጢስ ወጋኝ።
ሲያጌጡ ይመላለጡ።
%
ሲያጣ እጅ ላፍ ይጠናል።
ሲበሉ የላኩት።
ሲዋጥ በመረቅ።
ሲቆፍሩ አንፈራጦ።
ሲያልቅ አያምር።
ሲበላ ለሚከሣ፤
ሲመክሩት ለሚረሣ፤
ለዛ እህል ንሣ፤
ሲሱ ሲበላ ይታነቃል፤
%
ሲወርዱ ይዋረዱ።
ሲፈሩ አይከሱ፤
በቁጣ አያይሱ።
ሲሞቱ ገመድ፤
ሳይከካ ተቦካ።
ሳይርቅ በቅርቡ፤
ሳይደርቅ በእርጥቡ።
ሳይረቱ አይበረቱ።
ሳይተርፋት አበደረች፤
ሳትበቅል ሞተች።
%
ሳትቸገር ተበደረች፤
ሳትከፍል ሞተች።
ሳይቀደስ ያርዳል፤
ሳይታየው ይፈርዳል።
ሳይጠሩት አቤት፤
ሳይልኩት ወዴት።
ሳይሰበር ጥግን።
ሳይጣሉት የተጣላ፤
ሳይገድሉ ጐፈሬ፤
ሳያስረግጡ ወሬ።
ሴት ያመጣው ጠብ አይበርድም።
ሴትና ቄስ ቀስ።
ስለጤሰ አይነድም፤
ስለዳመነ አይዘንብም።
ስንቅህን ባህያ፤
አመልህን በጉያ።
ዋስ ያለው አይታሠር።
ስንዴ በጭምቅ፤
ባለጌ በጥብቅ።
ስም ይወጣ ከቤት፤
ይቀበል ጐረቤት።
ስለከሰሱ አይፈወሱ።
ሥጋ ቀረ፤
ዕዳ ቀረ።
ሥጋ ለጥጋብ፤
አጥንት ለትካዜ።
ሥራ ያጣ ጢስ ይሞቃል።
ሸማ በየፈርጁ ይለብሳል።
%
ሺኚ እቤት አያገባም።
ሸማ ማዋስ ለባላገር፤
ሹም ቢሞት አምሳ፤
ሹመት በተርታ፣
ሥጋ በገበታ።
ሾላ በድፍኑ።
ቀባሪ በፈጣሪ።
%
ቀርቀሬ ወርጄ ማር ስልስ ማር ልክፈል።
ቀስ በመቀስ።
ቀን በበቀሎ ማታ በቆሎ።
ቀን እስኪያልፍ፤
ቀን እንደ ተራዳ፤
ቀን ተጣለው ሁሉ ይጥለው።
ቁራ ስሙን ይጠራ።
ቂል ያገኘው ፈሊጥ፤
ውሻ ያየው ሊጥ።
%
ቂል አይሙት እንዲያጫውት።
በጥባጭ ካለ ጥሩ አይጠጣም።
በዝሆን አፍ ቅርፊት።
%
በእጅ የያዙት ወርቅ ስለመዳብ አንድ ነው።
በቡሐ ላይ ቆረቆር።
በቃል ያለ ይረሣል፤
በመጽሐፍ ያለ ይወረሣል።
በየወንዙ ሃሌ።
በማያድሩበት ቤት አያምሻሹበት።
በበትሩ አይመታ፤
በዘመዱ አይረታ።
%
በትር ለገና ነገር ለዋና።
ቢስቁበት አያደምቅ፤
ቢበሉት አያደምቅ።
በሁለት ዳኛ አይሟገቱ።
ሎሌ እንደ ነገሩ።
በሬ ተሽካሽኰ ከቀንበር፤
በጦም ቆሎ ፤
በዳገት በቅሎ፤
ቆሎም ይከካል፤
በቅሎውም ይነካል።
%
በውል ከሄደች በቅሎዬ፤
ያለ ውል የተበላች ቆሎዬ።
በለፈለፉ ባፍ ይጠፉ።
የት ውዬ ዬት ልደር ጌታዬ።
%
በሰው ቁስል እንጨት ቀርቅርበት።
በጋለሞታ ቤት ሁሉ ይጣላበታል።
በእውር ይጠቃቀሷል፤
በደንቆሮ ይሾካሾኳል።
%
በሰው ምድር ልጅዋን ትድር።
በሰኔ ካልዘሩ፤
በጥቅምት ካልለቀሙ፤
በዝሆን ጆሮ ትንኝ።
ሁል ጊዜ ፋሲካ ይመስላታል።
አሟጦ አይጋግርም።
ቢሰጡኝ እነዳ፤
ቢነሱኝ እረዳ።
ቢጠረጥሩ፤
ጠጠር ይጥሉ።
ቢያብዱም ቢሞቱም፤
ባልፈሱበት ቂጥ አያፍሩበት።
ባንዱ ታዘብ፤
ባንዱ ተለዘብ።
%
ባእድ ስር የለውም።
ባልነቃ ሰንጥቆ፤
ባልነበረ በርቆ።
ባልንጀራህ ሲታማ፤
የኔ ብለህ ስማ።
ባወጡት ዳኛ ቢረቱ፤
ባልፈጠጥሽ በኖብሽ፤
ባልነበርሽ በርቆብሽ።
ባሪያ ቅቤ ወዶ፤
ማን ሊሸከም ነዶ።
ባመጣኸው ዳኛ፤
ትሆን አሣርኛ።
ባፄ ይሙቱ የተከተረ፤
በስለት የተመተረ።
ባለጌ የተመከረለት፤
ቁንጫ የተጠረገለት።
በፈሳ ይታፈሳል፤
በነጠር ይመለሳል።
ባላደራ ጮኸ በተራራ።
%
ባስተጋባ ከባሕር ሆዴ ገባ።
ቤት ያለ አጥር ሰው ያለልብስ።
ቤት ከነጉልላቱ፤
ምድጃ ከነማዘንቱ።
ብልጥ ለብልጥ፤
ዓይን ብልጥጥ።
ብርሌ ከነቃ፤
አይሆንም እቃ።
ብነጨው ፊቴን፤
ብመታው ደረቴን።
ብርቅና ድንቅ፤
አለ ሳምንት አይደምቅ።
%
ተባለ ቀትር፣አትቀታተር።
ተናገር በከንፈሬ፤
ተቀመጥ በወንበሬ።
ተው ፈረሴን ለጉም ፤
ተግደርዳሪ ጦም አዳሪ።
ታከረሩት ይበጠሳል።
ነገር በዋስ፤
እህል በነፋስ።
ነገር በእርቅ፤
መንገድ በደረቅ።
ነገር አዳምጦ፤
እህል አላምጦ።
ነገር ሲጀመር፤
እህል ሲከመር።
ነገር ካወቂ፤
ብረት ከጠራቂ።
ነገር ካንሺው፤
ሥጋ ከጠባሺው።
ነገር ከግቡ፤
ጋሻ ከንግቡ።
ነገር ተሥሩ፤
ውሃ ከጥሩ።
ነገር ለበለጥ፤
ውድማ ለመለጥ።
%
ነብር ሳይገድል ቆዳውን ይስማማል።
ኑሮ በዜዴ፤ አቶ ዘወልዴ።
ንጉሥ አይከሰስ፣
ሰማይ አይታረስ።
ንጉስ አንጋሹን፤
ቤተ ክርስቲያን ቀዳሹን።
አባት ያበጀው፤
ልጅ ይበጀው።
አዬ ጉድን አታበላሽ፤
ለባሰ ቀን ይሆናል።
አር ጠንቁላ መጣች።
%
አያ ጅቦ ሳታመኻኝ ብላኝ።
አንድ ሲሻር፤
አንድ ይሾማል።
ሁሉ ቢናገር ማን ይሰማል?
%
አንደኛ ልብ አንድድ፤
ሁለተኛ ልብ አብርድ፤
አንዳይና በጎ ሄደች፤
አባት ካለ አጊጥ፤
ጀንበር ካለ ሩጥ።
አቦን አይጠምቅ፤
አብ ሲነካ፤
ወልድ ይነካ።
አለዋንጫ አይስማት፤
አለቀንጠፋ አይስባት።
አለ አሽከር በቅሎ፤
አለ በለኝ ቀለቤን፤
ሞተ በለኝ ከፈኔን።
አለቃ ያውቃል፤
ድኃ ይጠይቃል።
አለ አንኰበር ሾላ ሜዳ አይገኝም።
%
አልቅትና ድኃ ውሀ ለውሀ።
ምን ይከፍላል ማን ተናግሮ?።
አንበሳ የሰበረው፤
አህያ ለሰርዶ፤
ሰው ለመርዶ።
አህያና ጓያ በምስያ።
አገር ጥሎ፤
ቁርበት ጠቅሎ።
ማርያም ውሀ፤
ዘመዴ ነሀ።
አገባሻለሁ ያለ ላያገባሽ፤
ተባልሽ ሆድ አትባባሽ።
አፍ ያለው ጤፍ ይቆላል።
አፈኛ በአፉ፤
ኃይለኛ በመዳፉ።
አፉ ከኛ ልቡ ከወሬኛ።
አፍና እጅ፤
እጅና ፍንጅ።
%
አጥብቆ ጠያቂ የናቱን ሞት ይረዳል።
አርጂ ጥኑ ነው።
አዛኝ ቅቤ አንጓች።
አመስጋኝ አማሳኝ።
%
አስቀድሞ ማመስገን ለማማት ይቸግራል።
አታበድር እንዳትቸገር።
አካል የወለደው፤
ዘመድ የወደደው።
አለመመከት መመታት።
አዎን ባይ እንደከፋይ፤
አሌ ባይ ሞት ተቀባይ።
%
አተር መዝራት አቦ ብልሃት።
ወይ እኛ እንሆን አሣርኛ።
አውቆ መተው፤
ነገሬን ከተተው።
እንስራውን ጥላ ውሀ ወረደች።
እንዳያማህ ጥራው፤
እንዳይበላ ግፋው።
እንኳን ዘንቦብሽ፤
እንዲያውም ጤዛ ነሽ።
እንኳን ለቤቱ፤
ያተርፋል ለጐረበቱ።
እንደመረብ ሸፍኖ፤
እንጀራ ከባእድ፤
መከራ ከዘመድ።
እንደ ልጅ በቀለበት፤
እንዳትበላ ለጐሟት፤
እንዳትሄድ ቀየዷት።
እንደ ሰው ትመጪ፤
%
እንግዳ ፊት ወርቅ ኋላ ብር ኋላ ብረት።
እንደ ውሀ ይፍሰስ፤
እንደ ጋጃ ይፈስ።
እንዲያው ብትመለሺ፤
እኔ እበላው ሳጣ፤
ልጄ ጥርስ አወጣ።
እኔ የምሞት ዛሬ ማታ፤
እህል ከበዩ፤
ሰው ከገዳዩ።
እርሟን ብታፈላ፤
አንድ ቁና አተላ።
እጅና አፍ አይተጣጡም።
እጅና ጭራ፤
አፍና እንጀራ።
እጅ ሲነድ ልብ ይንደድ።
እጅ እየታጠቡት ያድፋል፤
ልጅ እየነገሩት ያጠፋል።
%
እጄ ተበትር፤
አፌ ከነገር።
እጄን በጄ ቆረጥሁት።
እሺ ባይ አክባሪ፤
እምቢ ባይ አቅላይ።
እሾህ አጣሪውን፤
ነገር ፈጣሪውን።
እናቱ የሞተችበትና፤
እኛ በአገራችን፤
ዳቦ ፍሪዳችን።
እኖር ባይ ተጋዳይ።
%
እራት ቢንቁ አንድ እጅ ይለቃልቁ፤
እጭን ያለ ኰርቻውን፤
እለምን ያለ ስልቻውን።
እካስ ያለ ታግሶ፤
እጸድቅ ያለ መንኩሶ።
%
እጸድቅ ብዬ ባዝላት ተንጠልጣል ቀረች።
እውሻ ሆድ ቅቤ አያድርም።
ከሺ ዋቢ እራሱ ቆራቢ።
ከሺ ደብተራ፤
የቄስ ደንካራ።
ከሺ ሎሌ፤
አንድ ወሬ።
ከመሞት፤መሰንበት።
ከመታገል፤መታደል።
ከመልካም ጠላ ክፉ ጠጅ፤
ከመንግሥት ልብ ያዛል።
ከመነኮሰች ባሰች፤
ከተተኰሰች አነከሰች።
ከመንር᎐ሴ ቤት ስስት፤
ከሸማኔ ቤት ቁቲት።
የልብ ቅንነት።
ከመምሩ፤ ደቀ መዝሙሩ።
%
ከመጠምጠም፤ መማር ይቅደም።
ከማይናገር ከብቱን፤
ከማይራገጥ ወተቱን።
ከተማረ የተመራመረ።
ከወፈሩ፤ሰው አይፈሩ።
ከራስ፤በላይ ንፋስ።
%
ከድኃ ከመበደር ከባለ ፀጋ መለመን።
ከነገሩ ጦም እደሩ።
ከጨርቅ ነጩ፤
ከባሀ ልጩ።
ከድስት አፍላል፤
ከቅመም ድንብላል።
%
ከእህል ክፉ አጃ፤
ከሳር ክፉ ሙጃ፤
ከነገር ክፉ አንጃ።
ከሩቅ ዘመድ፤
የቅርብ ጐረቤት።
ከሰጪው፤ አስጪው።
ከቁንጫ መላላጫ።
ከንጉስ ላይ ሰው አይፈርድ፤
ከሰው ክፉ ደባል፤
ከጭነት ክፉ አላል።
ከውርርድ ላይ ውርርድ፤
ከነብር ላይ ስማርድ።
%
ከጐተት እስከ ሽበት፤
ሰው አይወደም በደል።
ከተመቱ ማንጠርጠር፤
ከገበያ ሄዶ ማንቀላፋት፤
በአፋፍ ላይ ሆኖ ማንጠራራት።
ከዲዳ ላም ንዳ።
%
ከፍትፍቱ፤ ፊቱ።
ይሆናል ፌንጣ።
አብረህ ተወቀጥ።
ካፍ ከወጣ አፋፍ።
ካነጋገር ይፈረዳል፤
ካያያዝ ይቀደዳል።
%
ካይጥ ቤት ብቅል፤
ከውሻ ቤት ጠፍር።
ፈስ ተምራ መጣች።
ካልጠገቡ አይዘሉ፤
ካልዘለሉ አይሰበሩ።
ካረጁ አይበጁ።
ካልተገለባበጠ ያራል።
ካረገዘች፤ክታብ ያዘች።
ካጭር ምከር፤
ከረጅም ውረር።
ካፍ የወጣ ቃል፤
ካረጁ መንገድ፤
ከመነኮሱ መውለድ።
ካገር ደጋ፤
ከመኝታ አልጋ።
ካጉል ጥንቆላ፤
የሰው ልጅ መላ።
ካዋቂ ጠራቂ፤
ካጣቢ አድራቂ፤
ከሂያጅ ጠያቂ።
ክዶ ከመሟገት፤
አምኖ መረታት።
ክፉ ሰው በከንፈሩ ያለቅሳል።
ክፉ ነገር ከከርስ፤
ክፉ ሥጋ በጥርስ።
ኰሶ ሲጠጣ ስቅጥጥ፤
ወደሽ ከተደፋሽ፤
ቢረግጡሽ አይክፋሽ።
%
ወልደው ሳይጨርሱ በሰው ልጅ አይስቁ።
ወንድ ባለ በዕለት፤
ሴት ባለች በዓመት።
ወይፈን ለገራፊ፤
ዓሣ ለጠላፊ።
ወልዶ አይሳምለት፤
ተናግሮ አይሳቅለት።
ወዶ የዋጡት ቅልጥም፤
ከብርንዶ ይጥም።
ወጥ ማን ያውቃል፤ ቀላዋጭ።
ወይ ጋሻ፤
ቀድሞ ቀረሻ።
ወፍ ዛፍ አይቶ፤
ወታደር ቤት አይቶ።
%
ወንዝ ለወንዝ እሯጭ ፤ የሰው በግ አራጅ።
ወተት ለእንቦሣ፤
ሥጋ ለአንበሣ።
ወጥ ያጣ ዱባ።
ወልዶ አይስም፤
ወይ ባልዘፈንሽ፤
ከዘፈንሽም ባላሳፈርሽ።
ወንድ ለግርግርታ፤
ጋሻ ለመከታ።
ዳኛ ሳለ ዘራፊ።
ዋቢ ያለው ያመልጣል፤
ዋቢ የሌለው ይሰምጣል።
ዋሽ ቢሉት እዋሻለሁ፤
ውሎ ውሎ ከቤት፤
ኑሮ ኑሮ ከመሬት።
%
ውሀን የሚያናግረው፤ ደንጊያ ነው።
ውሻ የጌታውን ጌታ አያውቅም።
ውሻ ከሊጥ ጦጣ ከጥጥ።
ውሻ ምን ትበያለሽ አለ ጌኛ፤
ውሻ በቀደደው ጅብ ይገባል።
ውሻ በበላበት ይጮሃል።
ውል ያውላል፤
ታንኳ ያሻግራል።
ውረድ ከማማ፤
ውጣ ከጫማ።
%
እኔ አያሁህ በጉልበት።
ዓባይን በጭልፋ።
ዓሣ በወንዙ ይታረዳል፤
ዓሣ መብላት በብልሃት።
%
ዓሣ ለወጋሪ፤
ነገር ለጀማሪ
ዓለም አታላይ፤
እንደበቅሎ ኰብላይ።
ዕርቅ አይፈርስ፤
ዓይን አይፈስ።
ዘር ከልጓም ይስባል።
%
ዘሩ የጣቴ፤
ምድሩ የአባቴ።
ዝም ባለ አፍ ዝምብ አይገባበትም።
%
ዝናብ ሲያባራ ከዋሻ።
ዝናብ ከደመና፤
ነገር ከዋና።
ዝም አይነቅዝም።
ዝንጀሮና ጥዋ ካፋ ነው የሚይዝ።
የሁለት፤ ዕዳ አፋይ።
የልጅ ነገር፤
ሁለት ፍሬ፤
የለመደች ጦጣ ሁል ጊዜ ሽምጠጣ።
የልጅ ክፉ ድቃላ፤
የእህል ክፉ ባቄላ፤
የልብስ ከፉ ነጠላ፤
የቤት ከፉ ሰቀላ።
%
የልጅ ነገር ጥሬ በገል።
የሌባን ጠበቃ፤
አደባልቀህ ውቃ።
የሌባን ሞኝ፤
በጐተራ ሥር ይገኝ።
የመነ᎐ሴ ፈራጅ።
የመጠረቢያ ልጅ መዘለፊያ።
የመንታ እናት፤
ተንጋላ ትሙት።
%
የሚሮጥበት ሜዳ የሚመጣበት ቀዳዳ የለውም።
የሚያድግ ልጅ አይጥላህ።
የምትጠባ ጥጃ አትጮህም።
የማያደርሱበትን አያኩም።
%
የማሽላ ዘር ከነ አገዳው ቸር።
የሞተው ወንድምሽ፤
የገደለው ባልሽ፤
አዘንሽ ቅጥ አጣ፤
ከቤትሽም አልወጣ።
የሞተ አይከሰስ፤
የፈሰሰ አይታፈስ።
%
የባለቤት አዳይ ጦም ያሳድራል።
የዘነጋ ተወጋ።
የተሸሸገ ሆድ አይጠፋለትም።
የተማከሩት ዳኛ ያግዛል፤
የመተሩበት እጅ ይወዛል።
የተረገዘ በሆድ፤
የታዛለ በለምድ።
የተራበ ከባቄላ፤
የተበደለ ከሰቀላ።
የተሾመ ይሟገቱለታል፤
በተሻረ ይመሰከርበታል።
የተቀማጭ አፍ ምላጭ።
የሰከረ ሲተፋ፤
የገደለ ሲደነፋ።
የሰለጠነ ሰይጠነ።
የሰዳጅ ለወዳጅ።
%
የሺ ምት ሰርግ ነው፤
የጠገበ አበደ።
የጠሩት እንግዳ፤
እራቱ ፍሪዳ።
ከጨበጡ አይለቁም።
የፈሩት ይደርሳል፤
የጠሉት ይወርሳል።
የወደዱትን ቢያጡ፤
የጠሉትን ይቀላውጡ።
%
የጋራ ወንጋራ።
የቀበጡ ለት ሞት አይገኝም።
%
የዋስ ተሟጋች የቆማጣ ፈትፋች።
የነ ቶሎ ቶሎ ቤት ግድግዳው ሰንበሌጥ።
የወርካ ልጅ ሳንቃ፤
የአለቃ ልጅ አለቃ።
የደላው ውሻ ማር ይቀላውጣል።
የደላው ሙቅ ያኝካል።
%
የወደቀን አንሳ፤
የሞተን አትርሳ።
የካህን አፋር፤
የአህያ ዕውር።
የነገር ወጡ፣ማዳመጡ።
የጐበዝ ዱዳ፤
%
የጐበዝ ልብ ከደረቱ።
የረዘመውን በጦር፤
ያጠረውን በድግር።
%
የደገመ ተረገመ።
ያልጠረጠረ ተመነጠረ።
%
ያልገደለ ዘማች፤
ያልወለደ ሟች።
ያለው ይምዘዝ፤
የሌለው ይፍዘዝ።
ያልወለደ አይነሣ፤
የሽምብራ ማሳ።
ረጀቱን አይሰዱ።
ያልሠጡት ተቀባይ፤
%
ያንተን የሚመስል እኔም አለን ቁስል።
ያውቃል ብሎ ይሾሟል፤
ያምራል ብሎ ይሸልሟል።
ያውሬ ሥጋ ለወሬ።
%
ያንካሳ ልብ ኢየሩሳሌም።
ያባ ጐፍናኔ ቤቱ በሪድ።
ያመጣሁት ውሻ ነከሰኝ፤
%
ያገር እድር፤
ለንጉሥ ያስቸግር።
ያባት እዳ ለልጅ፤
ይሆናል ብዬ ጐሽ ጠመድሁ ፤
%
ይወደዋል ካሉ ይመክረዋል ፤
ዱላ ይዞ ሌባ መጠየቅ።
ዲያቆን ከዘፈነ፤
%
ዳኛ ከፈረደበት መርከብ የተሰበረበት።
ዳኛ ምን ያደላ፤
ከተረታ ሊበላ።
ዳኛ ቢያጋድል በዳኛ፤
ዳቦ ያለቅርፊት ጠላ ያለምርጊት።
ዳቦ ሲበሉ ልብ ልቡን።
ድኃ ጉልበቱን፤
ባለጸጋ ከብቱን።
ድኃ ተበድሎ፤
ድኃ ከንቡ ይደላል።
ድንኳን ያየ ባለጌ።
ዶሮ ብትታመም በግ አረደላት።
%
ዶሮ ካልጫረ ድኃ ካልዘራ።
ዶሮ ከቆጥ በሬ ከጋጥ።
ጀርባዬን አሣከከኝ፤
ጅብ ካኰተኰተ፤
ሰው ከተከተተ።
ጅብ እንደባቱ ይዘርጥጥ።
ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ።
%
ጅብ ከላይ ውሀ ሲጠጣ፤
ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው።
ዛፈ ጐበዝ ትቆጠራለች።
አላማኑኤል ማን ጠየቀኝ።
ጌታ ያዛል ውሀ ያነዛል።
ጎሽ ለልጅዋ ትወጋ።
ጐመን በጤና።
ጐኑ የኔ ቀኑ ሰኔ።
%
ጠላ ባለቤቱን አያውቅም።
ጠጅ የሌለበት አበጋዝነት።
ጠጅ በብርሌ፤
ነገር በምሳሌ።
ጠጅ የወራት ወዳጅ።
ጠባ ለኪዳን መሸ ለቁርባን።
%
ጢቢብ ይበላል በገል።
ጠብ ያለበት ቤት ዶሮ ትሞት።
ጣጣ ፈንጣጣ።
ጥምድ እንደበሬ፤
ጥል ያለሽ ዳቦ።
%
ጥቂት ሥጋ እንደ መርፌ ትወጋ።
ጥቂት ሽሮ ማታ ዶሮ።
ጦጣ ባለቤቱን ታስወጣ።
ጦጣ ተይዛ ትዘፍን።
ጦም ከማደር ዳቦ ቀርቅር።
ጧት ከበላተኛ ማታ ከጦመኛ፤
ጩኸት ለቁራ፤
መብል ለአሞራ።
ፈረሰኛ የወሰደው፤
እግረኛ አይመልሰው።
ፈሪ ለእናቱ ይገባል።
ፉት ቢሉ ጭልጥ።
%
ፊት የተናገረን ሰው ይጠላው፤
ፊት የደረሰን ወፍ ይበላው።
ፊት ያሞጠሙጧል ኋላ ይፏጯል።
%
ፀሎት በፍቅር ሃይማኖት በምግባር።
ንፅህና፣
ለሥጋ ለነፍስ ጤና
ሳይለፋ ያገኙት፣
ለቅፅበት።
ስትጠጣ አይተህ፣
ስትፈርም አንብበህ።
አንድ አይነድ፣
አንድ አይፈርድ።
ብዙ የሚያወራ፣
ጥቂት ይሠራ።
ቀዳሚ፣
ተጠቃሚ።
%
ሁሉም ያልፋል፣
እስኪያልፍ ያለፋል።
ውለታ፣
የልብ ትዝታ።
አንድ ይወድቀው።