You are on page 1of 17

ቀን 9/01/2014

ለኦዲት እና ኢንስፔክሽን ዳ/ት

የ 2013 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የግዥ አፈፃፀም የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት

ኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

አዲስ አበባ

ክፍል አንድ
መግቢያ፡-

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በአዋጅ ቁጥር 1151/2011 እንደገና የተቋቋመ ሲሆን ዓላማው በመገናኛ ብዙኃን በፕሬስና
በሌሎች አግባብ ባላቸው ሕጐች መሠረት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ለሚፈፀመው አበይትና ወቅታዊ ጉዳዮች
እንዲሁም ትምህርታዊና አዝናኝ ዝግጅቶችን ለሕዝብ ማቅረብ ሲሆን የድርጅቱ በጀት በመንግሥት ከሚመደብለት
የድጋፍ በጀት እና በዚህ አዋጅ መሠረት ከሚሰበሰብ የአገልግሎት ክፍያ እንዲሁም ከሌሎች ምንጮች ናቸው፡፡

የኦዲቱ አላማ

በድርጅቱ የሚከናወኑ ግዥዎች እኮኖሚያዊ በሆነ መንገድ የሚከናወኑ መሆኑና የግዥ ሥርአቱም በመመሪያና
በደንብ እንደዚሁም በመንግስት አዋጅ የተደገፈ መሆኑን፣ የግዥ አፈፃፀም ለመከታተል የሚያስችል ብቃት
ያለዉ የግዥ ሥርአት የተዘረጋና ስራ ላይ የዋለ መሆኑን በመገምገም የድርጅቱ ግዥ ሂደት ላይ የሚታዩ ድክመቶችን
እና መንስኤዎቻቸዉን በመለየት የማሻሻያ ሀሳብ ለማቅረብ ነው፡፡

የኦዲቱ የትኩረት አቅጣጫዎች

ከላይ የተገለጸውን የኦዲት ዓላማ ለማሳካት አ ን ድ የኦዲት የትኩረት አቅጣጫ ተለይቷል፡፡ እሱም፡-
1. የድርጅቱ የግዥ ሥርዓት ወጪ ቆጣቢ ብቃት ያለው እና ውጤታማ መሆኑን ማረጋገጥ፣
የኦዲት መመዘኛ መስፈርቶች
ለዝርዝር ኦዲቱ ለተመረጡት አንድ የኦዲት የትኩረት አቅጣጫዎች 28 መመዘኛ መስፈርቶች የተዘጋጁ ሲሆን፣
መመዘኛ መስፈርቶቹ ከዚህ ሪፖርት ጋር (በአባሪ 1) ተያይዘዋል፡፡
የኦዲቱ ወሰን

ዝርዝር ኦዲቱ የሚሸፍነዉ ከ 2013 ሐምሌ- መጋቢት 2013 ዓ.ም ያለውን የዘኝ ወራት የግዥ አፈፃፀም
ሥርዓት ነዉ፡፡

የኦዲቱ ዘዴ
ዝርዝር ኦዲቱ የተከናወነው፣ በድርጅቱ በተከናወኑ የግዥዎች አፈፃፀምን በናሙና በመምረጥ
ከሚመለከታቸው ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ጥያቄዎችን በማቅረብ እናቃለ መጠይቅ በማድረግ
ተከናውኗል፡፡

ክፍል ሁለት
የኦዲት ግኝቶች
1-የኦዲቱ ግኝቶች የድርጅቱ የግዥ መመሪያ ወቅታዊ አለመደረጉን በተመለከተ፡-

ድርጅቱ እንደገና በተቋቋመዉ አዋጅ ቁጥር 1151/2011 መሰረት ለሚያከናዉነዉ የቋሚና አላቂ ዕቃዎች እንዲሁም
ያአግልገሎት ግዥ የሚያገለግል ወቅታዊ የሆነ የግዥ መመሪያ ሊኖረዉና በሚወጣዉ መመሪያ መሰረት ሊፈፀም ይገባል፡፡
 ነገር ግን የድርጅቱ የ 2013 በጀት አመት እስከ መጋቢት ወር የግዥ አፈፃፀም ሲታይ በአዋጁ መሰረት የወጣ
መመሪያ አለመኖሩን በተሰጠዉ ቃለ መጠይቅ የተረጋገጠ ሲሆን እንደዚሁም አብዛኛው የግዥ ክንዉን ሲታይ
የመንግስት የግዥ አዋጅ ቁጥር 649/2001 መሰረትም ያልተፈፀመ መሆኑን በቀረቡት ሰነዶች ሳምፕል
መሠረት ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
 ይሁን እንጂ የበላይ አመራሩ መመሪያዉ ተዘጋጅቷል ነገር ግን ለቦርድ ቀርቦ አልፀደቀም፡፡ ይሄ ግኝት በ 2012
የዋና ኦዲት ግኝት ላይም ቀርቧል፡፡ስለዚህ ማኔጅመንቱ አስተያየት ሰጥቶበት መመሪያዉን ቶሎ ቦርዱ
እንዲያፀድቀዉ ማድረግ ይገባል የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

2. የቁጥቁጥ ግዥን በተመለከተ:-

የፌደራል መንግሥት የግዥ መመሪያ አንቀጽ 25 (7) (ሀ) ላይ የመንግስት መ/ቤት ዕቅድ ውስጥ ያልተካተቱ ዋጋቸው
ከብር 5,000.00(አምስት ሺ) ያልበለጠ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን ወይም በጉዞ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችን ከመፍታት ጋር
የተያያዙ የቀጥታ ግዥዎችን ከማናቸውም ሻጭ ድርጅት መፈፀም ይችላል፡፡ ሆኖም በዚህ ዓይነት የሚፈፀሙ ጥቃቅን ግዥዎች
ድምር በአንድ የበጀት ዓመት ውሰጥ ከብር 75,000.00 (ሰባ አምስት ሺህ ብር) መብለጥ አይኖርበትም ይላል፡፡
 ነገር ግን ከታች በሰንጠረዡ እንተዘረዘረው በ 2013 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የቁጥቁጥ ግዥ አፈፃፀም ሲታይ በድምሩ
ብር 111,419.78 ሲሆን አመት ሳይ ሞላዉ(በ 9 ወር ውስጥ) ለአመቱ ከተፈቀደው በላይ በድምር ብር 36,419.78
በብልጫ ተፈፅሞ መገኘቱን በቀረቡት ሰነዶች ሳምፕል መሠርት የተረጋገጠ መሆኑ እንዲሁም በ 2013 በጀት ዓ.ም
በግልፅ ጨረታ ይገዛሉ ተብሎ የታቀዱት ሁሉ በቁጥቁጥ ግዥ ተፈፀሞ መገኘቱ፡፡

2.የ 2013 በጀት ዓመት እስከ መጋቢት ወር የቁጥቁጥ ግዥ አፈፃፀም


ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን በዓመቱ የግዥ ዕቅድ ላይ መኖሩ

1 ፍሬን ሸራ የተሰራበት ግዥ 8736 13/06/2013 690.00 


2 ሞተሪኖ የማሰሪያ ግዥ 8803 25/06/2013 700.01 
3 የመፅሐፍት ግዥ 8902 1/7/2013 2,849.70 
4 ቡና ሻይ ስኳር ውሃ 7320 13/03/2012 5,000.00 
5 የክላሰር ግዥ 8750 17/07/2013 900.00 
6 የፎቶ ኮፒ ማሽን ማሳሪያ ግዥ 8798 24/06/2013 1,499.99 
7 የቲተር ግዥ 8256 28/04/2013 1,800.00 
8 የሳር፤እጣን፤የፀጉር ጌጥ ግዥ 7333 6/1/2013 4,563.06 
9 የአርማታና የጣዉላ ግዥ 8459 20/05/2013 2,475.73 
10 የቲተር ግዥ 7646 17/02/2013 2,699.99 
11 የሰርተፍኬት ህትመት ግዥ 8807 1/7/2013 3,125.13 
12 የቲተር ግዥ 7882 23/03/2013 3,599.96 
13 የአየር ትኬት ግዥ 8085 9/4/2013 4,311.00 
14 የአርማታና የጣዉላ ግዥ 8458 20/05/2013 4,449.00 
15 የቲተር ግዥ 7936 29/03/2013 4,800.00 
16 የበር ቁልፍ የማይቀረፅ 7320 3/12/2012 3,891.71 
17 ቡና፤ ውሃ፤ሻይቅጠል 7604 11/2/2013 4,890.37 
18 የቡና መጥመቅያ፤የሻይ ማፍያ፤ ብርጭቆ፤የቡና ሲኒ፤ሻይ ማንኪያ 7706 27/02/2013 4,842.45 
19 ማስቲሽ እና ሶከት ማከፋፈያ 7685 24/02/2013 4,918.51 
20 የሞዴል 22 ግዥ 8131 14/04/2013 4,201.79 
21 የኤል ብረት ግዥ 8119 14/04/2013 4,600.00 
22 የሎረሰንት ግዥ 8011 2/4/2013 4,890.91 
23 የዉሻ ቆዳ እና የዳሽ ቦርድ ግዥ 8311 3/5/2013 4,889.97 
24 የቲተር ግዥ 8012 1/4/2013 900.00 
25 የፎቶግራፍ ፍሬም ግዥ 8974 07/07/2013 3,400.00
26 የአየር ትኬት ግዥ 9064 0307/2013 3,000.00
27 የቲተር ግዥ 8972 07/07/2013 1,799.98
28 የቲተር ግዥ 9118 15/07/2013 2,000.00
29 ባለ እንድ እና ባለ ሁለት ተወርዋሪ ቁልፍ 9127 21/07/2013 3,898.44
30 ለቁልፍ ማስቀረፅ 9088 21/07/2013 2,648.94
31 የፋይል ካቢኔት ቁልፍ 9087 21/07/2013 4,684.94
32 የፋይል ካቢኔት ቁልፍ 9086 21/07/2013 4,498.20
33 ቡና ስኳር ሻይ ቅጠል ግዥ 8975 07/07/2013 4,000.00
ድምር 111,419.78

 ይሁን እንጂ የበላይ አመራሩ የሰጠዉ መልስ የመስሪያቤቱ አሰራር የተለየ በመሆኑ አብሮ የሚህድ የድርጅቱ
የግዥ መመሪያ ባለመፅደቁ ከድርጅቱ የሥራ ሁኔታ ጋር የሚመጡ ችግሮችን መፍትሄ ማግኝት አልተቻለም፡፡
እንደዚሁም የ 2014 እቅድ አልፀደቀም አመራሩ እጅ ላይ ነዉ ያለዉ እንደ አመራር ተቀብለን የበላይ አመራሩ
መመሪያዉን እና እቅዱን ቶሎ ቢያፀድቅ ጥሩ ነዉ በማለት ሃሳባቸዉን ተናገረዋል፡፡

3-ከአንድ አቅራቢ የተፈፀመ ግዥን በተመለከተ፡-


በ ፌ ደ ራ ል መ ን ግ ስ ት የ ግዥ አዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀጽ 51 መሰረት ከአንድ አቅራቢ የሚፈፀም ግዥ
መፈፀም የሚቻለው ዕቃው፤የግንባታ ዘርፍ ሥራው፤የምክር ወይም ተፈላጊው ሌላ አገልግሎት የሚገኘው ከአንድ
ዕጩ ተወዳዳሪ ብቻ በመሆኑ ምክንያት ማወዳደር የማይቻል መሆኑ ሲረጋገጥ ነው ይላል፡፡
 ነግር ግን ከታች በሰንጠረዡ እንደተገለፀዉ በድምር ብር 167,175.99 የተፈፀመ ግዥ በቀጥታ
ከአንድ አቅራቢ ተከናውኖ መገኘቱ፡፡

ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን በዓመቱ የግዥ ዕቅድ ላይ
መኖሩ
1 የጠጠርና የብሎኬት ግዥ 8139 14/4/2013 7,240.00  
2 የሆቴል አገልገሎት ግዥ 9132 30/07/2013 7,574.22  
3 የአሸዋ ግዥ 9070 1 4/07/2013 8,510.00  
የለቀማ ግዥ(ከህንፃመሳሪያ
4 የሚገኝ) 8926 2/7/2013 10,000.00  
5 የአንድ መኪና ድንጋይና አሸዋ ግዥ 8076 9/4/2013 12,095.01  
6 የመኪና መፍቻ ዕቃዎች ግዥ 7891 24/03/2013 16,617.50  
7 የአዳራሽ ኪራይ ግዥ 8908 1/7/2013 17,250.00  
8 የናፍጣና የዘይት ፊልትሮ ግዥ 7863 21/03/2013 17,435.01  
9 የእምነ በረድ ግዥ 9156 18/07/2013 65,000.00  
10 የመኪና እስፔር ፓርት 8784 22/06/2013 879.12  
11 የኬብል ግዥ 8751 17/06/2013 850.00  
12 የሰርትፍከት ህትመት ግዥ 8808 22/06/2013 3,125.13  
13 የፎቶግራፍ ህትመት ግዥ 10503 22/7/2013 600.00  
ድምር 167,175.99

 የበላይ አመራሩ አንዳንድ ግዥዎችን በተመለከተ በፕሮፎርማ ማግኘት አይቻልም ምክንያቱም አብዛኛዎቹ
አቅረቢዎች ፕሮፎርማ ለመስጠት ፍቃደኛ ስላልሆኑ ችግሩን ለመፍታት ተነጋግረን በቃለጉበኤ በመወሰን ግዥው
በቀጥታ ግዥ እንዲፈፀም ተደርጓል የሚል ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡

4. ድርጅቱ የጥቅል (bulk) ግዥ ስለማያከናውን የዋጋ የቅናሽ ተጠቃሚ ስላለመሆኑ፡-


የ ፌ ደ ራ ል መ ን ግ ስ ት የ ግዥ አፈፃፀም መመሪያ አንቀፅ 24. እና 24፤8 ላይ የመንግስት መ/ቤቶች አስቀድሞ ማቀድ
እስከተቻለ ድረስ ግዥን በግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ መፈፀም አለባቸው ፡፡ ሆኖም ሊታቀዱ ያልቻሉና ወዲያውኑ ጥቅም ላይ
የሚውሉ ወይም በጅምላ ሊገዙ ያልቻሉ እና ዋጋቸው ከ 200,000.00 በታች የሆነ ግዥዎችን በዋጋ ማቅረቢያ ግዥ መፈፀም
እንደሚችሉ ይገልፃል፡፡ በተጨማሪም በዋጋ ማቅረቢያ በተደጋጋሚ ለሚፈፅማቸው ግዥዎች በኤጀንሲው ድረ-ገፅ የሚወጣውን
ወቅታዊየ ዋጋ ዝርዝር በግዥ ሥራ ክፍሉ የሚካሄድ የገበያ ዋጋ ጥናትን በመጠቀም ዝቅተኛ ተብለው የሚመረጠው ዋጋ ትክክለኛ
የገበያ ዋጋ መሆኑን ማረጋገጥ ይኖርበታል ይላልለ፡፡
ነገር ግን የ 2013 ዓ.ም እስከ መጋቢት ወር በቀረበልን ሰነድ ሳምፕል መሠረት የግዥ አፈፃፀም ሲታይ በዕቀዱ መሰረት በጨረታ የተገዛዉ
ከስድስት ያልበለጡ የተወሰኑ ዕቃዎች ብቻ ሲሆን የቀሩት ግዥዎች ግን በድምር ብር 2,895,721.03 የሚሆን በፕረፎርማ እና በቀጥታ ግዥ
በማከፋፈል የተገዙ እና ዋጋቸዉ በገበያ ዋጋ ጥናት ያልተረጋገጠ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን በዓመቱ የግዥ ዕቅድ ላይ መኖሩ

1 የመኪና አላርምና የፀሃይ መከላከያ 7603 11/2/2013 125,92.50 

2 የመኪና ጎማ 205 የመኪናባትሪ 8632 5/6/2013 78,400.00 

3 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9232 24/07/2013 26,739.32 

4 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 8985 8/7/2013 22,012.40 

5 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 8765 18/07/2013 2,875.00 

6 የመኪና ፍሬን ሸራ ግዥ 7755 4/3/2013 5,899.07 

7 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 7842 17/03/2013 10,592.92 

8 የፎልደር ግዥ 8022 05/4//2013 61,548.00 

9 ዉሃ ግዥ 7350 7/12/2012 36,567.79 

10 ሰራምክ ፤ዘኩሎ 8226 14/4/2013 92,172.5 

11 ስማርት የሞባይል ቀፎ 7785 8/3/2013 15,500.00 

12 የመኪና እስፔር ፓርት 8784 22/06/2013 879.12 

13 ጅፕሰም ንፋስ ስልክ ቀለም 8113 13/04/2013 24,024.36 

14 ሲምንቶ ቀለም ብሩሽ ብርጭቆ ወረቀት ግዥ 8114 13/04/2013 22,734.78 

15 የፕሪንተር ቀለም ግዥ 8205 22/04/2013 16,249.96 

16 የፕሪንተር ቀለም ግዥ 8204 22/04/2013 40,999.8 

17 የተለያዩ ፒቪሲ ግዥ 8200 21/04/2013 9,545.74 

18 የመኪና ኪራይ 7190 01/12/2012 25,9389.4 

19 የመኪና ኪራይ 7256 19/12/2012 238,470.9 

20 ስማርት የሞባይል ቀፎ ግዥ 7304 29/12/2013 12,075 

21 የዕጅ ጓንት ጃንጥላ የሴትና የወንድ 7178 06/12/2012 18,795.6 

22 የችግኝ ግዥ 7151 04/12/2012 72,777.00 

23 የላፕ ቶፕ ግዥ ኮር አይ 7 7899 25/03/2013 154,000.00 

24 የጀነሬተር ጥገና ግዥ 7889 24/03/2013 39,157.5 

25 የፖስታ ህትመት 7733 01/03/2013 14,329.00 

26 የመጋረጃ ግዥ 8128 14/04/2013 11,299.9 

27 የሆቴል አገልግሎት ግዥ 8075 10/4/2013 30,249.94 

28 የሆቴል አገልግሎት ግዥ 8074 10/4/2013 11,950.85 

29 የመደርደሪ ማሰሪያ 8263 28/04/2013 115,000.00 

30 የፒቪሲ ግዥ 8222 23/04/2013 4,002.00 

31 የተወዛዋዥ ግዥ 7838 16/03/2013 25,000.00 

32 የዲኮደር ግዥ 7813 12/03/2013 7,399.97 

33 የፌሮ ብረት እና እስታፍ ግዥ 7880 23/03/2013 8,919.4 

34 የሲምንቶ እና የፍሮ ማሰሪያ ግዥ 7881 23/03/2013 8,059.94 

35 የፓድ ህትመት ግዥ 7895 24/03/2013 39,876.25 

36 የመኪና መፍቻ ግዥ 7892 24/03/2013 4,858.75 

37 የወለል ምጣፍ ግዥ 7819 14/03/2013 18,249.99 

38 የሆቴል አገልግሎት ግዥ 7730 30/02/2013 8,249.98 

39 32 ጂቢ ፍላሽ ስድርያ 7724 30/02/2013 140,998.05 


40 የአሮጌ ህንፃ እድሳት አገልግሎት ግዥ 8247 26/04/2013 119,999.99 

41 የመክና ዲኮር ግዥ 8230 26/04/2013 15,226.00 

42 የመክና ዲኮር ግዥ 8239 26/4/2013 19,722.5 

43 የቀለም ግዥ 8058 07/04/2013 2,732.4 

44 የሲሚንቶ ግዥ 8053 7/4/2013 14,799.40 

45 የእስቲከር ህትመት ግዥ 7751 30/3/2013 1,840.00 

46 የሳኒተሪ ዕቃዎች ግዥ 8202 22/04/2013 3,673.65 

47 የፒሲ እና የአታኪኒ ግዥ 8203 21/04/2013 4,263.83 

48 የክላሰር ግዥ 8750 17/07/2013 900.00 


49 ቆርቆሮ፤ሚስማር፤ቀለም፤ብሩሽ 8868 30/062/013 6,500.47 
ግዥ
50 ሴራም እና ዘኮሎ ግዥ 8868 29/06/2013 188,577.00 
51 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8764 18/06/2013 14,702.75 
52 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8763 18/06/2013 13,213.5 

53 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8758 18/06/2013 17,595.00 

54 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8713 12/06/2013 1,840.00 

55 የኤለክትሮንክስ ዕቃ ግዥ 8679 10/06/2013 62,000.00 

56 የኤለክትሮንክስ ዕቃ ግዥ 8678 10/06/2013 125,752.25 

57 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8612 4/06/2013 2,114.85 

58 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8611 4/06/2013 3,206.2 

59 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8610 4/06/2013 3,163.6 

60 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8609 4/06/2013 5,635.00 

61 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8427 17/05/2013 14,950.00 

62 የዋተር ፕሩፍ ጅብሰን ቦርድ ግዥ 9114 15/07/2013 103,155.00 

63 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8973 07/07/2013 27,000.00 

64 ወተር ፕሩፍ ኤምዲፍ ግዥ 8954 03/07/2013 24,906.7 

65 የፓወር ባንክ ባትሪ ግዥ 8915 01/07/2013 5,060.00 

66 የሆተል አገልግሎት ግዥ 8907 1/7/2013 198,174.9 

67 የሮቤርቶ አታኪኒ ግዥ 8448 19/05/2013 22,266.30 

68 የኔትወርክ ዝርጋታ ዕቃዎች ግዥ 8345 5/5/2013 6,100.15 

69 የሳነተሪ ዕቃዎች ግዥ 8446 19/5/2013 11,711.6 

70 የጅብሰም የግድግዳ ቀለም ሲሚንቶ 8866 30/06/2013 23,920.00 


ግዥ
71 የሆቴል አገልግሎት ግዥ 8572 1/06/2013 60,000 

72 የፖታ ህትመት ግዥ 8373 12/05/2013 27,214.75 

73 የጠረጰዛ ስም እና የሥራ ድርሻ 8331 4/5/2013 31,050 


ግዥ
74 የዝገት መከላከያ ግዥ 8447 19/5/2013 2,111.4 
75 የማርሪያ ማጥፍያ፤የኤለክትርክ ክዳን 8308 03/05/2013 791.66 
ግዥ
ድምር 2,895,721.03 

 ሆኖም ግን የበላይ አመራሩ ህግን ብቻ ጠብቆ መሄድ ስራዉ እንዲጓተት ስለሚያደርግ አመራሩ ስራ ተጓተተ
ማለት የለበትም፡፡ ቢሆንም ግን አመራሩ ብልሹ አሰራር እንዳይፈጠር የቁጥጥር ስረዓቱን ማጠናከር አለብን፡፡
ቀጣይ በሚፀድቀዉ መመሪያ ዉስጥ የፕሮፎርማ ግዥ ለምን አላማ እንደሚዉል በመመሪያዉ ዉስጥ ማካተት
አለበት በማለት ተናግረዋል፡፡

5. በተደጋጋሚ ከተወሰኑ ድርጅት ብቻ በፕሮፎርማ የተፈፀመ ግዥን በተመለከተ፡-

የ ፌ ደ ራ ል መ ን ግ ስ ት የ ግዥ አፈፃፀም መመሪያ አንቀፅ 24.3 ፊደል (ሀ) መሰረት በዋጋ ማቅረቢያ የሚፈፀም ግዥ መፈፀም
የሚቻለዉ የመንግስት መ/ቤቱ በአቅራቢዎች ዝርዝር ዉስጥ የተመዘገቡት ሁሉም ተሳታፊዎች በዙር የመወዳደር እድል ማግኘታቸዉን እና
ለመ/ቤቱ ጠቃሚ የሆነ የተለየ ሁኔታ መኖሩ ካልተረጋገጠ በስተቀር አንድ ወይም የተወሰኑ አቅራቢዎችን ብቻ በተደጋጋሚ መጋበዝ
አይኖርባቸዉም ይላል፡፡
 ነግር ግን ከታች በሰንጠረዡ የተዘረዘሩት የመኪና መለዋወጫ ዕቃ ግዥዎች እና ተንቀሳቃሽ የፅህፈትና የጋዜጣ
መደርደሪያ የሁለቱም ለየብቻ በጠቅላላ ድምር ከ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ብር በላይ ስለሆነ በጨረታ መግዛት
ሲቻል ከፋፍሎ በፕሮፎርማ ከመገዛቱም በላይ ለሌሎች አቅራቢዎች እድል ሳይሰጥ ከአራት አቅራቢዎች ብቻ ተለይቶ
ከኤልሳቤጥ ፈለቀች የመኪና እቃ መለዋወጫ፤ ኳሊቲ የመኪና እቃ መለዋወጫ፤ ፤ሞኤንኮ፤የሺዋስ አሰፋ እና ሳስኮ
ኢንዱስተሪያል ንግድና ትራንስፖርት በተደጋጋሚ አወዳድሮ ግዥ ተፈፅሞ የተገኘ መሆኑ፡፡

ሰነጠረዥ(1)
ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን በዓመቱ የግዥ ዕቅድ ላይ መኖሩ

1 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9231 23/07/2013 30,475.00 


2 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9226 23/07/2013 18,400.00 
3 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9227 23/07/2013 97,950.00 
4 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9232 24/07/2013 26,739.32 
5 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 9033 11/07/2013 13,685.00 
6 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 8985 08/07/2013 22,012.40 
7 የመኪና መለዋወጫ ግዥ 8987 08/07/2013 10,580.00 
8 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8427 17/05/2013 14,950 
9 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8713 12/06/2013 1,840 
10 የመክና መለዋወጫ ዕቃ 8758 18/06/2013 17,595 

ድምር 254,226.72
ሰነጠረዥ(2)
አራት ተመሳሳይ አቅራቢዎች ሶስት ጊዜ ተወዳድረዉ ሶስት ጊዜም ከይስሃቅ ዘላለም ንግድ ድርጅት ብቻ
በድምሩ 588,052.50(አምስት መቶ ሰማንያ ስምንት ሺህ ሃምሳ ሁለት ከ 50/100) ብር የተገዛ መሆኑ፡፡
ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን በዓመቱ የግዥ ዕቅድ ላይ መኖሩ


1 ተንቀሳቃሽ የፅህፈትና የጋዜጣ መደርደሪያ 8115 13/06/2013 196,017.50

2 ተንቀሳቃሽ የፅህፈትና የጋዜጣ መደርደሪያ 8013 05/04/2013 196,017.50

3 ተንቀሳቃሽ የፅህፈትና የጋዜጣ መደርደሪያ 7926 28/03/2013 196,017.50
ድምር 588,052.50

 ይሁን እንጂ የበላይ አመራሩ በተደጋጋሚ ከተወሰኑት አቅራቢዎች የተፈፀሙ ግዥዎች


ለአበዛኛዎቹ አቅራቢዎች ፕሮፎርማ እንዲሰጡን ብንጠይቅም ለመስጠት ፍቃደኛ
ባለመሆናቸዉ ምክኒያት በተደጋጋሚ ከተወሰኑ አቅራቢዎች ግዥ የተፈፀመ መሆኑን ገልፀዉ
አሰራሩ ግን መፈተሸ አለበት ብለዋል፡፡ በተጨማሪም እንደዚህ አይነት ችግሮች ሲከሰቱ
ምክንያቶቹ በቃለ ጉባኤ ተገልፆ ከሰነዱ ጋር መያያዝ እንዳለበት ገልፀዋል፡፡

6. የጨረታ እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሰነዶች የታሸጉባቸዉ ፖስታዎች ሲከፈቱ የታሸጉባቸዉ ፖስታዎች ላይ ቢያንስ ሶስት የግዥ ኮሚቴዎች
ሳይፈርሙ የተገዙ ዕቃዎች፡፡
የጨረታ እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሰነዶች አቀባበልና አከፋፈት ግልጽና ተጠያቂነትን ለመወጣት እንዲያስችሉ የጨረታ እና የዋጋ
ማወዳደሪያ ግዥ ሠነዶች ታሽገው የሚመጡባቸው ፖስታዎች ከሶስት ባላነሱ የግዥ ኮሚቴዎች ተፈርሞባቸው ከተከፈቱ
በኋላ በመረጃነት ከግዥ ሠነዶቹ ጋር ተያይዘው ሊቀመጡ ይገባል፡፡ በተጨማሪም የ ፌ ደ ራ ል መ ን ግ ስ ት የ ግዥ አፈፃፀም
መመሪያ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 13 መሰረት የግዥ ማወዳደሪያ ሰነዶችን በቡድን በመሆን መገምገም እንዳለበት ይገልፃል፡፡
 ነግር ግን በእያንዳንዱ የግዥ ክፍያ ሰነዶች ላይ ሙሉ የጨረታ ሰነዶች ተያይዘዉ የማይገኙ እና ለዋጋ
ማወዳደሪያ ግዥ ለቀረቡት የማወዳደሪያ ፖስታዎች ላይ ያልተፈረሙ እንዲሁም በአንድ ሰዉ ብቻ
ተፈርሞ ግዥ የተፈፅመ መሆኑ ከታች በሰንጠረዥ የተገለፀ ሲሆን ይህ ደግሞ በቡድን ያላወዳደሩት
መሆኑን የሚያሳይ ሆኖ መገኘቱ፡፡

ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቀን የብር መጠን ምርመራ


ቁጥር
6,100.15
1 የኔትወርክ ዝርጋታ ዕቃዎች ግዥ 8345 05/05/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
3,379.85
3 የኮምፒዉተር መለዋወጫ ዕቃ ግዥ 8347 13/05/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
9,119.86
4 የአሸንዳ ብረት ግዥ 8355 07/05/2013 ፊርማ የሌለዉ
115,000.00
5 የመደርደሪያ ማሰሪያ ግዥ 8263 28/04/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
14,799.40
7 የሲሚንቶ ግዥ 8053 07/04/2013 ፊርማ የሌለዉ
30,249.94
8 የሆቴል አገልግሎት ግዥ 8075 10/04/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
3,673.65
9 የሳኒተሪ ዕቃዎች ግዥ 8202 22/04/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
22,266.30
10 የሮቤርቶ አታኪኒ ግዥ 8448 19/05/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
140,998.05
11 ሎጎ ያለዉ 32 ጂበ ፋላሽ ግዥ 7724 30/02/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
14,229.00
12 የፖስታ ህትመት ግዥ 7733 01/03/2013 ፊርማ የሌለዉ
3379.85
13 የከብል ግዥ 8347 05/05/2013 በአንድ ሰዉ ብቻ በፖስታ ላይ የተፈረመ
363,196
  ድምር .05  

 በመሆኑም የበላይ አመራሩ በስራ ክፍሉ የሰዉ ሃይል እጥረት ምክንያት የተፈጠረ ነዉ በማለት
ቀጣይ የሚስተካከል ነዉ ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በዚህ አመት የማወዳደሪያ ሰነዶች ከክፍያ ሰነድ
ጋር አብሮ እንዲቀርብ የተስተካከለ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

7. የጉልበት አገልግሎት ግዥን በተመለከተ፡፡


በመስሪያ ቤቱ ውስጥ የጉልበት ስራ የሚሰሩ ሁለት የጉልበት ሰራተኞች በኮንተራት መቀጠራቸዉ ይታወቃል፡፡ ሆኖም
ግን ከዚህ በፊት በቀረቡት የኦዲት ግኝቶች ለተቀጠሩት ጉልበት ሰራተኞች የሥራ ድርሻ ተለይቶ እንዲታወቅ እና
ከእነሱ ዉጪ የሚሰራ የጉልበት ስራ በበላይ ሃላፊ እንዲፈቀድ የሚል አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበረ ይታወቃል፡፡
 ነገር ግን ከታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረዉ የጉልበት ዋጋ ክፍያ በበላይ ኃላፊ ሳይፈቀድ የተፈፀመ
ሆኖ ተግኝቷል፡፡
ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን ምርመራ

1 የጎማና የባትሪ ማዉረጃ ዋጋ 8670 10/6/2013 400.00  ያለተፈቀደ


2 የወረቀትና የዉሃ ማዉረጃ ዋጋ 8619 5/6/2013 2,000.00  ያለተፈቀደ
3 የሞተር ዘይት ማዉረጃ 8618 5/6/2013 400.00  ያለተፈቀደ
4 የጉልበት አገልግሎት ግዥ 8416 15/05/2013 1,200.00  ያለተፈቀደ
5 የጉልበት አገልግሎት ግዥ 8414 15/05/2013 1,500.00  ያለተፈቀደ
6 የሲሚንቶ እና ሴራሚክስ ማዉረጃ 8983 7/7/2013 2,700.00  ያለተፈቀደ
7 የአሮጌዉ ህንፃ ወለል መፋቅ 9183 7/7/2013 3,000.00  ያለተፈቀደ
8 የአሮጌዉ ህንፃ ወለል መፋቅ 9185 21/07/2013 2,500.00 በኮፒ
9 የአሬጌዉ ህንፃ ፍቅፋቂ ማንሳት 9306 8/7/2013 2,000.00 በኮፒ
ድምር 15,700.00  

 ይሁን እንጂ የበላይ አመራሩ ከተቀጠሩት የጉልበት ሰራተኞች አቅም በላይ ሲሆን የበላይ አመራሩ
መፍቀድ እንዳለበት አቅጣጫ የተቀመጠ ቢሆንም አንዳነዴ እቃዎቹ ከስራ ሰዓት ዉጪ
ሰለሚመጡ ይሄ ችግር ሊፈጠር የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ገልፀዉ ቀጣይ ከበላይ አመራሩ እና
ከስራ ክፍሉ ኃላፊ ማን መፍቀድ እንዳለበት ማስቀመጥ አለብን የሚል ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡

8. የሙያ ፍቃድ ሳይኖረዉ ያለዉድድር የተፈፀመ የአገልግሎት ግዥን በተመለከተ፡-

ማንኛዉም ግዥ ሲፈፀም ኢኮኖሚን ብቃትን እና ዉጤታማነትን ያገናዘበ ሆኖ መንግስት ያወጣዉን ህግ እና መመሪያ


መሰረት መፈፀም ይገባ ነበር፡፡
ነገር ግን ከታች በሰንጠረዡ የተገለፀዉ መመሪያዉን ያልተከተለ የሙያ ፍቃድ ሳይኖረዉ ያለዉድድር የተፈፀመ
የአገልግሎት ግዥ ሆኖ መገኘቱ፡፡
ተ.ቁ የግዥዉ ምክንያት የደረሰኝ ቁጥር ቀን የብር መጠን ምርመራ

1 ሙዚቃ ለማቅረብ አገልግሎት ግዥ 8072 9/4/2013 12,000.00 የሙያ ፈቃድ የሌለዉ


2 የመድረክ መሪ ክፍያ 7778 8/3/2013 30,000.00 የሙያ ፈቃድ የሌለዉ
ድምር 42,000.00  

 ሆኖም ግን የበላይ አመራር ተቋሙ ሚዲያ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ችሎታ ያላቸዉን ለማኔጅመነት ፕሮፖዛል
በማቅረብ ተወስኖ የተፈፀመ ግዥ መሆኑን ገልፀዉ ለቀጣይ ተቋሙ መመሪያ ተዘጋጅቶ በቦርድ ስላፀደቀ ቀጣይ
በመመሪያዉ መሰረት የሚከናወን ይሆናል የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

9. የ 2013 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ እና የግዥ አፈፃፀም ሪፖርትን በተመለከተ፡፡

የግዥአዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀፅ 22 ንዑስ አነቀፅ 2 መሰረት የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ በዓመቱ የሚፈፀመዉን የግዥ
ዕቅድ አፅድቆ እሰከ ሐምሌ 30 ለመ/ቤቱ የስራ ክፍሎች እና ለኤጀንሲዉ መላክ ይኖርበታል ይላል፡፡ እንደዚሁም
የፌደራል መንግስት የግዥ አፈፃፀም መመሪያ ክፍል ሶስት አንቀፅ 7 ተራቁጥር 1 ማናኛዉም የመንግስት መ/ቤት በሰሩ
የተደራጁ አካላት የታቀዱ የሰራ ፕሮግራሞቻቸዉን ተግባራዊ ለማድረግ የሚስፈልጋቸዉን ግዥ በወቅቱ ለመፈፀም
የሚያስችል በመርሃግብር የተደገፈ የግዥ ዕቅድ ማዘጋጀት አለባቸዉ ይላል፡፡እንደዚሁም ዕቅዱ የመንግስት ግዥ መረሆችን
(ቁጠባ ፤ብቃት እና ዉጤታማነትን)መከተል ይገባል፡፡ በተጨማሪም የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት በመርሃ ግብሩ መሰረት
በየጊዜዉ መቅረብ ይገባ ነበር፡፡
 ነገር ግን የ 2013 በጀት ዓ.ም የግዥ ዕቅድ ፀድቆ ለስራ ክፍሎች የደረሰዉ የካቲት 04/2013 ዓ.ም መሆኑ፤ እቅዱ
በመርሃ ግብር ያለተደገፈ እና የመንግስትን የግዥ መርሆችን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲሁም የቁጥቁጥ ግዥን
ለመከላከል የሚስችል ሆኖ አልተገኘም፡፡ እንደዚሁም የስራ ክፍሉ በየጊዜዉ የግዥ አፈፃፀም ሪፖረት የሌለዉ ሆኖ
ተግኝቷል፡፡
 ይሁን እንጂ የበላይ አመራሩ የ 2013 ዕቅድን በተመለከተ በጊዜው አልታቀደም አሁንም ይሄ ችግር እየተደገመ ስለሆነ የ 2014
የግዥ ዕቅድ ማኔጅመንቱ ቶሎ አይቶ ማፅደቅ አለበት በማለት አስተያየት የሰጡ ሲሆን የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት ግን
በየጊዜዉ ለሚመለከተዉ የስራ ኃላፊዎች መቅረብ አለበት ብለዋል፡፡

10.የግዥ ሰነዶች አያያዝን እና አተገባበርን በተመለከተ፡-


ማናኛዉም የግዥ ሰነዶች ለሶስተኛ ወገን ግልፅ ሆኖ የሚታይ ወይም የሚነበብ እና የተሟላ መሆን ያለበት ሲሆን
አተገባበሩም ሃላፊነት ባለባቸዉ ሰራተኞች መረጋገጥ ይገባል፡፡
 ነገር ግን አብዛኞቹ የፕርፎርማ ግዥ ሰነዶች ላይ ተወዳዳሪዎች ያቀረቡት የመወዳደሪያ ሰነዶች (ንግድ ፈቃድ፤
የተጨማሪ እሴት ታክስ፤የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር፤የአቅራቢነት ማስረጃ ) የማይነበብ የማይታይ እና ለኦዲት ሥረ
ግልፅ ያልሆነ እንዲሁም የተወሰኑ ግዥዎች በቃለ ጉባኤ ቦታ የተዘጋጀ ቅፅ የቃለ ጉባኤ አርዕስት የሌለዉ እና
በብዙ ደረሰኞች ላይ በጀት ለመኖሩ ያረጋገጠዉ ፤የተቀባይ ፊርማ እና ያዘጋጀው ፊርማ የሌለው ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ምሳሌ ፡-ከብዙዎች የተወሰኑትን ለማሳያ ከታች በሰንጠረዥ ተገልፀዋል፡፡
ተ. የደረሰኝ የወጪው ምርመራ
ቁ ቁጥር ቀን
1 7655 06/01/2013
ያዘጋጀዉ እና የተቀባይ ፊርማ አለመኖሩ እንዲሁም በጀት ሰለመኖሩ ያልተረጋገጠ፡፡
2 9114 15/07/2013
የንግድ ማስረጃዎች የማይነበቡ እና ግልፅ ያልሆኑ
3 8247 26/04/2013
ያዘጋጀዉ ፊርማ አለመኖሩ እንዲሁም በጀት ሰለመኖሩ ያልተረጋገጠ፡፡
4 9231 23/07/2013
የንግድ ማስረጃዎች የማይነበቡ እና ግልፅ ያልሆኑ
5 9226 23/07/2013
የንግድ ማስረጃዎች የማይነበቡ እና ግልፅ ያልሆኑ
6 9227 23/07/2013
የንግድ ማስረጃዎች የማይነበቡ እና ግልፅ ያልሆኑ

 የበላይ አመራሩ ኮፒ ሰነዶቹ ታሽገዉ ነዉ የሚሰጣቸዉ ይሄን የፈጠረዉ የኢትዮጵያ የንግድ ስርዓቱ መሆኑን ገልፀዉ ለወደፊቱ
የሚሰተካከል ይሆናል በማለት ገልፀዋል፡፡

11. የአሮጌ ህንፃ እድሳት ውል በተመለከተ

የግዥ አዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀጽ 51 ላይ ባስቀመጠው መስፈርት መሠረት ተጨማሪ ግዥ ለመፈፀም እና ተጨማሪ
ውል ለመግባት ቀደም ሲል በጨረታ ለተገዛው ግዥዎች ብቻ የተፈቀደ ሲሆን በዋጋ ማወዳደሪያ ለሚፈፀም ግዥዎች
ተጨማሪ ግዥ እና ዉል ማራዘም የሚፈቅድ ሆኖ አልተገኝም፡፡

በተጨማሪም የ ፌ ደ ራ ል መ ን ግ ስ ት የ ግዥ አፈፃፀም መመሪያ አንቀፅ 24. እና 24፤8 ላይ የመንግስት መ/ቤቶች አስቀድሞ


ማቀድ እስከተቻለ ድረስ ግዥን በግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ መፈፀም አለባቸው፡ሆኖም ሊታቀዱ ያልቻሉና ወዲያውኑ ጥቅም ላይ
የሚውሉ ወይም በጅምላ ሊገዙ ያልቻሉ እና ዋጋቸው ከ 200000.00 በታች የሆነ ግዥዎችን በዋጋ ማቅረቢያ ግዥ መፈፀም
እንደሚችሉ ይገልፃል፡፡፡

 ነገር ግን ለአሮጌ ህንፃ እድሳት የአገልግሎት ግዥ በመመሪያው መሠረት በፕርፎርማ መግዛት አግባብ ባይሆንም
ተፈፅሞ የተገኘ እንዲሁም በዋጋ ማቅረቢያ ግዥ ላይ ተጨማሪ ግዥ ተፈፅሞ ተጨማሪ ውል መግባት
ያልተፈቀደ ቢሆንም ተፈፅሞ የተገኝ ሆኖ

ምሳሌ፡- ገዛኽኝ በሱፍቃድና ጓደኛቻቸው ህንፃ ኮ/ስ/ተ/ህ/ሽ/ማ ፕሮፎርማ ተወዳደድሮ አሸናፊ ሆኖ ውል የፈረመው በቀን
1/4/2013 ዓ.ም ሲሆን ውሉ የሚቆይበት ጊዜ ከታህሳስ 1-2013 ዓ.ም እስከ ጥር 1/05/2013 ዓ.ም ሲሆን ተጨማሪ ውል በቀን
20/4/2013 የተፈረመ ሲሆን ውሉ የሚቆይበት ጊዜ ከታህሳስ 20-2013 ዓ.ም እስከ ጥር 5/05/2013 ዓ.ም የሆነ እና
ለመጀመሪያ ውል ብር 181,499.79 የተከፈለ ሲሆን ለሁለተኛ ውል ለመጀመሪያ ብር 23,920.00 የተከፈለ ሆኖ መገኘቱ፡፡

 ሆኖም ግን የበላይ አመራሩ ለመስሪያ ቤቱ ጥቅም ሲባል በዚህ መንገድ ቢሰራ አዋጪ መሆኑ ታይቶ
የተሰራ ስራ ነዉ በማለት ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡
ክፍል ሶስት
የመደምደምያ ሃሳብ
በተመረጠው አንድ የኦዲት የትኩረት አቅጣጫዎች አንፃር የድርጅቱ የግዥ ሥርዓት ወጪ ቆጣቢ ብቃት ያለው እና ውጤታማ
መሆኑን ለማረጋገጥ፣ ፣ ኦዲት ተደርጎ በዝርዝር የኦዲት ግኝቶች ላይ የተመለከቱት ጉልህ የሆኑ የአሠራር እና የአፈፃፀም ችግሮች
ታይተዋል፡፡ ዋና ዋናዎቹም፣

 ድርጅቱ እንደገና በተቋቋመዉ አዋጅ ቁጥር 1151/2011 መሰረት ለሚያከናዉነዉ የቋሚና አላቂ ዕቃዎች እንዲሁም የአግልገሎት
ግዥ የሚያገለግል መመሪያ ወቅታዊ አለመደረጉ፡፡
 የቁጥቁጥ ግዥን በተመለከተ ከተፈቀደለት ገደብ በላይ ተፈፅሞ ስለ መገኘቱ፡፡
 ከአንድ አቅራቢ የተፈፀመ ግዥ ከመመሪያው ውጪ ተፈፅሞ ስለመገኘቱ፡
 ድርጅቱ የጥቅል (bulk) ግዥ ( በጨረታ)ስ ለማያከናውን የዋጋ የቅናሽ ተጠቃሚ ስላለመሆኑ
 በተደጋጋሚ ከተወሰኑ ድርጅት ብቻ በፕሮፎርማ የተፈፀመ ግዥን ስለመፈፀም፡-
 የጨረታ እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሰነዶች የታሸጉባቸዉ ፖስታዎች ላይ በቡድን ያለመፈረም ወይም ምንም ፍርማ ስላለመኖር፡፡
 በመስሪያ ቤቱ ውስጥ የጉልበት ሰራተኞች እያሉ በእነሱ መሰራት እየተቻለ በበላይ ኃላፊ ሳይፈቀድ በውጪ
የጉልበት ሰራተኞች የጉልበት ግዥ ስለመፈፀሙ፡፡
 የሙያ ፍቃድ ሳይኖረዉ ያለዉድድር የተፈፀመ የአገልግሎት ግዥን ስለመፈፀሙ
 የ 2013 በጀት ዓመት የግዥ ዕቅድ እና የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት በመንግስት የግዥ መሪሆች ስላለመዘጋጀቱ፡፡
 የአሮጌ ህንፃ እድሳት የአገልግሎት ግዥ በፕርፈፐርማ ስለ መገዛቱ እና የፕርፎርማ ተጨማሪ ግዥ
ተፈፅሞ ስለመገኝቱ፡፡
ክፍል አራት
የማሻሻያ ሃሳብ
 ድርጅቱ እንደገና በተቋቋመዉ አዋጅ ቁጥር 1151/2011 መሰረት ለሚያከናዉነዉ የቋሚና አላቂ ዕቃዎች እንዲሁም
ያአግልገሎት ግዥ የሚያገለግል ወቅታዊ የሆነ የግዥ መመሪያ በአዋጅ ቁጥር 649/2001
መሠረት ያደረገ መመሪያ ሊኖረዉና ይገባል፡፡
 በቁጥቁጥ ግዥ የሚከናወኑ ግዥዎች መመሪያውን መሠረት ባደረገ የአፈፃፀም ዜዴን በመጠቀም ለአመቱ የተፈቀደውን የግዥ
የገንዘብ ጣሪያ ሳይበልጥ ውጤታማ እና ወጪ ቆጣቢ የሆነ የግዥ አፈፃፀም ሊያከናወን ይገባል፡፡-
 ከአንድ አቅራቢ የሚፈፀም ግዥ አቅራቢው ብቸኛ አቅራቢ መሆኑ በመስረጃ ሲረጋገጥ መንግስት ባወጣው መመሪያ
መሠረት ግዥው ሊፈፀም ይገባል፡፡
 ድርጅቱ የዋጋ ቅናሽ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ቁጠባን የአፈፃፀም ብቃትን እና ዉጤታማነትን ለማረጋገጥ ግዥዎችን
አ ስቀድሞ ማቀድ እስከተቻለ ድረስ ግዥን በግልፅ ጨረታ የግዥ ዘዴ መፈፀም አለባቸው፡፡ሆኖም ሊታቀዱ ያልቻሉና
ወዲያውኑ ጥቅም ላይ የሚውሉ ወይም በጅምላ ሊገዙ ያልቻሉ የገበያ ዋጋ መሆኑን በጥናት በማረጋገጥ ግዥዎችን
በዋጋ ማቅረቢያ ግዥ መፈፀም የሚችል በመሆኑን አውቆ ግዥን ሊያከናውን ይገባዋል፡፡
 በዋጋ ማቅረቢያ የሚፈፀም ግዥን ለመፈፀም በመመሪያው የፈቀደ መሆኑን በማረጋገጥ ከአንድ ወይም የተወሰኑ
አቅራቢዎችን ብቻ በተደጋጋሚ በመጋበዝ ግዥ ከመፈፀም የመንግስት መ/ቤቱ በአቅራቢዎች ዝርዝር ዉስጥ የተመዘገቡት
ሁሉም ተሳታፊዎች በዙር የመወዳደር እድል ማግኘታቸዉን እና ለመ/ቤቱ ጠቃሚ የሆነ የተለየ ሁኔታ መኖሩ በማረጋገጥ ግዥው
ሊተገበር ይገባል፡፡
 በተደጋጋሚ ከተወሰኑ ድርጅቶች ብቻ በፕሮፎርማ ግዥ መፈፀም በመመሪያዉ መሰረት አግባብ ባለ መሆኑ ግዥ
ሲፈፀም በአቅራቢዎች ዝርዝር ዉስጥ የተመዘገቡት ሁሉም ተሳታፊዎች በዙር የመወዳደር እድል ማግኘታቸዉን እና ለመ/ቤቱ
ጠቃሚ የሆነ የተለየ ሁኔታ መኖሩ በማረጋገጥ መተገበር አለበት፡፡
 የጨረታ እና የዋጋ ማወዳደሪያ ሰነዶች አቀባበልና አከፋፈት ግልጽና ተጠያቂነትን ለመወጣት እንዲያስችሉ የጨረታ
እና የዋጋ ማወዳደሪያ ግዥ ሠነዶች ታሽገው የሚመጡባቸው ፖስታዎች ከሶስት ባላነሱ የግዥ ኮሚቴዎች
ተፈርሞባቸው ከተከፈቱ በኋላ በመረጃነት ከግዥ ሠነዶቹ ጋር ተያይዘው ሊቀመጡ ይገባል፡፡
 የጉልበት አገልግሎት ግዥን በተመለከተ በመስሪያ ቤቱ ውስጥ ተቀጥረው የጉልበት ስራ የሚሰሩ
የጉልበት ሰራተኞች መሰራት ይገባል፡፡ሆኖም ከእነሱ አቅም በላይ ሆኖ ተጨማሪ የጉልበት ሥራ ማሰራት
ከተፈለገ የገንዘብ ብክነት ለመከላከል በበላይ ሃላፊ እየተፈቀደ ማሰራት ይገባዋል፡፡
 የሙያ ፍቃድ ሳይኖረዉ ያለዉድድር የተፈፀመ የአገልግሎት ግዥን በተመለከተ ማንኛዉም ግዥ ሲፈፀም
ኢኮኖሚን ብቃትን እና ዉጤታማነትን ያገናዘበ ሆኖ መንግስት ያወጣዉን ህግ እና መመሪያ መሰረት መፈፀም
ይገባል፡፡
 መ/ቤት በሰሩ የተደራጁ የሥራ ክፍሎችን የታቀዱ የሰራ ፕሮግራሞቻቸዉን ተግባራዊ ለማድረግ
የሚስፈልጋቸዉን ግዥ በወቅቱ ለመፈፀም የሚያስችል በመርሃግብር የተደገፈ የግዥ ዕቅድ ማዘጋጀት
አለባቸዉ ፡፡እንደዚሁም ዕቅዱ የመንግስት ግዥ መረሆችን (ቁጠባ ፤ብቃት እና ዉጤታማነትን)መከተል ይገባል፡፡
በተጨማሪም የግዥ አፈፃፀም ሪፖርት በመርሃ ግብሩ መሰረት በየጊዜዉ መቅረብ ይገባል፡፡
 በዋጋ ማቅረቢያ ግዥ የሚፈፀም የአገልግሎት ግዥ በመመሪያው መሠረት በፕርፎርማ መግዛት የሚገባቸው ብቻ
መገዛት ያለበት ሲሆን በዚህ የግዥ ሂደት ተጨማሪ ግዥ መፈፀምና ዉል ማራዘም አይገባም፡፡

ክፍል አምስት
በአባሪ 1

የኦዲት መስፈርት (Evaluative Criteria)

ኦዲት ተደራጊው መ/ቤት፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

የኦዲት የትኩረት አቅጣጫ የኦዲት መመዘኛ መስፈርት

(Audit (Evaluative Criteria)


1. በድርጅቱ 1.0 ድርጅቱ ለሚያከናውነው የቋሚና አላቂ ዕቃዎች ግዥ

የሚያገለግል ወቅታዊ የግዥ መመሪያ ሊኖር ይገባል፡፡


የኦዲት የትኩረት አቅጣጫ የኦዲት መመዘኛ መስፈርት

(Audit (Evaluative Criteria)


የተፈፀሙት ግዥዎች 2.0 የግዥ ክፍሉ ከተጠቃሚ ክፍሎች የተሰበሰበውን ፍላጎት መሰረት
በተጠየቀው መሰረት
የግዥ ስርዓትን ተከትሎ ያደረገ ግልጽና ሊለካ የሚችል የግዥ መርሀግብር (ዕቅድ)
በወቅቱ ለተጠቃሚው
ክፍል የደረሰ መሆኑን በቅድሚያ ሊዘጋጅና ሊተገበር ይገባል፡፡
ማረጋገጥ:

1.1 ማንኛዉም ግዥ 2.1 የግዥ ዕቅድ ሲዘጋጅም አይነትን፤ፍላጎትን ፤እና ፍጆታን


3.0 ግዥዎች በቅድሚያ በተዘጋጀላቸው ዕቅድ መሰረት ሊሆኑ ይገባል፡፡
ሲከናወን የግዢ ዕቅድ
ተዘጋጅቶ በዕቅዱ
3.1 በዕቅድ ያልተያዙ ግዥዎች ከመከናወናቸው በፊት ጥያቄውን ያቀረበው የሥራ ክፍል
መሰረት እየተከናወነ
ቀደም ብሎ ያላሳወቀበትን ምክንያት በፅሁፍ ለድርጅቱ የበላይ አካል በማቅረብ ውሳኔ
መሆኑን ማጣራት፡፡
እንዲያገኝ መደረግ ይኖርበታል፡፡

4.ግዥ ከመፈቀዱ በፊት ለግዢ የተጠየቁ ዕቃዎች በግምጃ ቤት

በሚፈለገው መጠንና ዓይነት አለመኖሩ (out of stock) በቅድሚያ ሊረጋገጥ ይገባል፡፡

1.2 የድርጅቱ የግዥ 5. የግዥ ውሎች ሲዘጋጁ ተገቢው ጥንቃቄ ሊደረግና ለአገልግሎትም
ሂደት የመንግሰትን የግዢ
ደንብ እና መመሪያ ተከትሎ ሆነ ለዕቃ ግዢ ተፈላጊው መስፈርትና ሊጠናቀቅ የሚችልበት ወራት በግልጽ
የተፈጸመ መሆኑን ሊቀመጥ ይገባል፡፡
6. የአቅራቢዎች ዝርዝር እና የአቅርቦት ታሪክ በአግባቡ እየተመዘገበ
ማጣራት፡፡

ሊያዝ ይገባል፡፡
7. በግዥ ሂደቶች ላይ መጓተት እንዳይደርስ የግዥ ጥያቄዎች

ግልጽና የማያሻማ (በአይነት፣ በብዛት፣ በጊዜ፣ በቦታና በተለያዩ መስፈርቶች) ተዘርዝረው


መቀመጥ
8. ይኖርባቸዋል፡፡
የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ በወቅቱ በመገናኛ ብዙሀን (በጋዜጣና

በሬድዮ........) መውጣት አለበት፡፡

9. የጨረታ ግዥን የሚፈቅዱና የሚያጸድቁት በግዥ መመሪያ

መሰረት ሥልጣኑሰነድ
10. የጨረታ የተሰጣቸው
አቀባበልናሃላፊዎች
አከፋፈትሊሆኑ ይገባል፡፡
ግልጽና ተጠያቂነትን

11.የጨረታ ሰነድ አቀባበልና አያያዝ ሚስጥራዊነቱን በጠበቀ ሁኔታ


12. ማንኛውም ግዥ ሲፈፀም የግዥ የጨረታ ሠነዶች አከፋፈት

13. ጨረታ ገምጋሚ ኮሚቴ ሊቋቋምና ሥራውን በግዥ መመሪያው

14.የጨረታ ግምገማ ውጤት ትክክለኛነት በሚመለተው ክፍል መጽደቅ እና ለአሸናፊ


አቅራቢዎችም ግልጽ በሆነ ሁኔታ መገለጽ አለበት፡፡

15.የጨረታ ግዥን የሚፈቅዱና የሚያጸድቁት በግዥ መመሪያ

16. የግዥ ማዘዣ ለአሸናፊዉ ድርጅት ሲላክ ኮፒዉ ለሚመለከታቸዉ

17. በድርጅቱ ግዥዎችን ሲፈፀም የቅናሽ ተጠቃሚ እንዲሆን

18. ማንኛዉም ግዥ ሲፈፀም ድርጅቶችን በቀጥታ ባለፈዉተሞክሮአቸዉ ከመምረጥ


ይልቅ እንደ መጨረሻ አማራጭ

19. በድርጅቱ የሚፈጸም የዕቃ ወይም የአግልግሎት ግዢ በዉሉ

1.3 በድርጅቱ የተፈፀሙ 20. ዕቃ አቅራቢዎች በግዥ ውሉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ

የዕቃዎችና አገልግሎት ግዥ በውሉ


መሰረት መከናወናቸዉን 21. ተገዝተው መጋዘን ገቢ የሚሆኑ ዕቃዎች በትዛዙ መሰረት
ማጣራት፡፡
22. ከግዥ ትእዛዝ ውጪ ለሚቀርቡ ዕቃዎች አቅራቢው ሊወስደው

23. የግዥ ክፍሎች በየጊዜው ስለሚዘጋጀው የግዥ ዕቅድና ክንውን

24. የሥራ ክፍሉ የየወቅቱን ግዥ ሪፖርት በማዘጋጅት የግዢ


በመጨረሻም በኦዲቱ ጊዜ ሰነድ በማቅረብ እና የተጠየቁትን ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የተባበሩን የስራ ሃላፊዎች እና
ባለሙያዎችን እናመሰግናለን፡፡

ከሰላምታ ጋር

የክዋኔ ኦዲት ባለሙያዎች


1 ኛ- ወ/ሮ ተርፋቱ ዲባባ
2 ኛ- አቶ ዘነበ ሙሉ

You might also like