You are on page 1of 8

ምስጋና

በመጀመሪያ በምህረቱ እና በቸርነቱ ጠብቆ ለዚህ ላደረሰኝ ለድንግል ማርያም ልጅ ለልዑል እግዚአብሔር
ምስጋና ይድረሰው በመቀጠልም ጥናታዊ ፅሁፉ እዚህ ደረጃ እስኪደርስ የጎደለውን አሟልቶ የተጣመመውን
አቃንቶ ዘወትር የሆነውን ምክሩን እየለገሰ ጥናቱ አሁን ካለበት ደረጃ እንዲደርስ ለረዳኝ አማካሪዬ ለኢሳያስ
ይልማ ከልብ የመነጨ ምስጋና አቀርባለሁ። በመቀጠልም እኔን ከፍ ለማድረግ እነሱ ዝቅ ብለው እዚህ ላደረሱኝ
ቤተሰቦቼ ምስጋናየ ከልብ ነው። በመጨረሻም በችግሬ ጊዜ ከፊቴ ሳይጠፉ መፍትሔ በመፈለግ አብረውኝ
የነበሩ ጓደኞቼን ከልብ አመሰግናለሁ።
አጠቃሎ
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ አገልግሎት ላይ የዋሉ የማስታወቂያ ፅሁፎች የቋንቋ
አጠቃቀምን ተንትኖ ማሳየት ነው። ጥናቱ አመቺ የናሙ ናአመራረጥ ዘዴን በመከተል ተካሂዷል። የመረጃ
መሰብሰቢያ ዘዴዎችም ሰነድ ፍተሻ እና ያልታቀደ ምልከታ ናቸው። በተገኘው መረጃ መሠረትም የቋንቋ
አጠቃቀም፣ የቃላት ምስል ከሳችነት እና ታዋሽነት ሁኔታ እንዲሁም ሰዋሰዋዊ የቃላት አጠቃቀም
ተተንትነዋል። በዚህ ጥናት ማወቅ የተቻለው በቃላት አጠቃቀም የዘዬ (ቀበልኛ) ቃላትን ማዘውተር፣ ድረታ
እና ተደጋጋሚ ቃላትን የመጠቀም ችግር፤ ከሰዋሰው አንፃር ደግሞ የቁጥር እና የመደብ አለመስማማት
እንዲሁም ስርአተ ነጥብን በአግባቡ ያለ መጠቀም ችግር ያለበት መሆኑን ነው። እነዚህ ችግሮች ደግሞ
በማስታወቂያ አማካይነት መልዕክት ለአንባቢ በሚቀርብበት ወቅት መልዕክቱን ለማንበብ እና ለመረዳት
አዳጋች እንዳደረጉት ተደርሶባቸዋል።
ምዕራፍ አንድ
1 መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
የሠው ልጅ ሀሳቡን በፅሁፍ መግለፅ የጀመረው የዛሬ አምስት አመት ገደማ እንደነበር ይነገራል። ፅሁፍ
ከመጀመሩ ወይም ከመገኘቱ በፊትም ሠዎች ለብዙ ዘመናት ሀሳባቸውን፣ ስሜታቸውን፣ ወዘተ. ሲገልፁ
የኖሩት በንግግር ነበር። ፅሁፍ የሚታዩ እና የሚዳሰሱ ልማዳዊ ወይም ስምምነታዊ ምልክቶች አማካኝነት
የሚቀርብ የንግግር ቋንቋን ቀርፆ የማቆያ ስልት ነው(አብነት፣277) ።
የመጀመሪያው ፅህፈት ተጀመረ ተብሎ የሚነገረው በሱሜሪያውያን ህዝቦች አማካኝነት ሜሶፓታሜያ ውስጥ
ሲሆን የፅሑፉ መጠሪያ ኩኒፎርም ወይም የሽብልቅ ፅሁፍ በመባል ይታወቃል። ሌሎች ደግሞ ጥንታዊ ፅሁፍ
በግብፃውያን የተፃፈው ሔሮግራፊክስ የተሠኘው ነው ይላሉ። አንዳንዶች ደግሞ የአሜሪካኖች ኮሎምቢያ
የዖልሜክ እና የማያን ህዝቦች እንደጀመሩት እና አየዳበረ እንደመጣ ይታመናል በማለት አብነት (2007፣277)
ገልፆታል።
ከዚሁ ጋር አያይዞ የስርዓተ ፅሕፈት አጀማመር እና እድገትን ያጠኑ ጠበብት እንደገለፁት ለዛሬዎቹ ልዩ ልዩ
የፅሁፍ የመሠረቶች ስዕላዊ ፅህፈት፣ ቀለማዊ ፅህፈት፣ ፊደላዊ ፅህፈት የተባሉት ደረጃ በጀረጃ እያደረጉ አሁን
ካለበት እንደደረሰ ያብራራሉ (አብነት 2007፣232) ።
ፅሁፍ ስርዓትን ተከትሎ መልዕክት ለአንባቢ የሚያደርሰው ቋንቋ የሚፈቅደውን የድምፆች፣ የቃላት፣
የሀረጋት፣ የዓአረፍተ ነገሮች፣ የአንቀፅ እና የድርሰት አገባብ ስርዓትን ማወቅ ሲቻል ነው። ይህ ካልሆነ ትርጉም
አልባ መሆን እና የትርጉም መለወጥን በማስከተል ትርጉም እንዲፋለስ ያደርጋል።
በፅሁፍ አማካኝነት ሀሳብን ለማስተላለፍ ደግሞ የፅሁፍ ስርዓቶችን ማወቅ እና መጠቀም ያስፈልጋል። ይሄንን
አስመልክቶ ሳሙኤል (1999) ባዩሬኒ (1988፣1)ን በመጥቀስ የሚከተለውን ሀሳብ አስፍሯል።
ሰንፅፍ እና ስንናገር ከምናወጣቸው ድምፆች ጋር የሚመሳሰሉ ምልክቶች ማለትም
ፊደሎች (የፊደሎችን ቅንጅት) እንጠቀማለን። በአንድ በኩል ፅህፈት የንግግር ድምፆችን
የሚወክሉ ምልክቶችን የመቅዳት እና በወረቀት ላይ የማስፈር ተግባር ነው ሊባል ይችላል፤
ነገር ግን የንግግር ድምፆችን የሚወክሉ ምልክቶችን፣ ቃላትን፣ ዓረፍተ ነገሮችን
ለመመስረት በቋንቋው ስርዓት መሰረት ተቀናብረው መዋቀር (መሰደር) አለባቸው።
ከዚህም እንደምንረዳው ፅህፈት የራሱ ስርዓት ያለው ድምፆች ቃላትን፣ ቃላት ሀረጋትን፣ ሀረጋት ዓረፍተ
ነገሮችን መገንባት እና አረፍተ ነገሮችም ርስ በዕርሳቸው ተገናኝተው የቋንቋዉን ስርዓት መጠበቅ
እንዳለባቸው ነው። ዐረፍተ ነገሮች የተዛመዱ፣ የተከታተሉ እና የተቆራኙ ከሆነ የሀሳብ አንድነት እና ጥምረት
ያለው ፅሁፍ መፃፍ ይቻላል።
በአጠቃላይ ፅሁፍ በአካል መግለፅ ማለትም በንግግር መልዕክትን ማስተላለፍ በማንችልበት ሁኔታ መልዕክትን
ለማስተላለፍ፣ ሀሳብን ቀርፆ ለትውልድ ለማቆየት፣ ዘመን ተሻጋሪነትን ለማጎልበት፣ ወዘተ ያገለግላል።
ለምሳሌ ደብዳቤዎች፣ መልዕክቶች፣ የተለያዩ የደስታም ሆነ ሀዘን መግለጫዎች፣ ትምህርታዊ ሰነዶች፣
መፅሄቶች፣ ጋዜጦች፣ ማስታወቂያዎች እና የመሳሰሉት ሁሉ የሚቀርቡበት የሚቀርቡት በፅሁፍ ነው።
በመሆኑም የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት የሆነው በፅሁፍ ሀሳብ ከሚገለፅባቸው መንገዶች መካከል አንዱ የሆነው
የማስታወቂያ የቋንቋ አጠቃቀም ነው። የቀደሙ አባቶች ወይም ነገስታት ማስታወቂያ የሚውሉ የክተት
ጥሪዎችን፣ የአዋጅ ነጋሪ ቃሎችን፣ የቤተክርስቲያን ደውሎችን፣ የከበሮና ፅናፅል ድምፆችን፣ ወዘተ. ሲሆን
በአሁኑ ጌዜ ደግሞ መስሪያ ቤቶች፣ ድርጅቶች (ግለሰቦች) ለጨረታ፣ ለቅጥር፣ ለደንብ እና ለትዕዛዛት ገለፃ፣
ለመሸጥ፣ ለመግዛት፣ ለመለወጥ፣ የጠፋን ለመፈለግ፣ አዳዲስ ምርቶችን ለማስተዋወቅ፣ ወዘተ.
የሚጠቀሙበት ፅሁፍ ነው። በመሆኑም ነገሮችን ለማስተላለፍ ግልፅ እና ለሰው እይታ በሚመች ቦታ ላይ
በመለጠፍ፣ በጋዜጣ፣ በመፅሔት እና በመሳሰሉት ላይ በመፃፍ እንዲሁም በዜና ማሰራጫዎች በሬድዮ፣
ቴሌቪዥን፣ በኢንተርኔት፣ ወዘተ. የሚያደርጉበት የሀሳብ መግለጫ ነው (ባህሩ 2004፣122) ።
የማስታወቂያ መሰረተ ሀሳቦች ሲነሱ ብዙዎች የተለያዩ ትርጉም የሚሰጡ ተያያዥ ቃላት እና ሀሳባቸውን
ይሰነዝራሉ። ብዙውን (advertising) ሲነሳ የማሻሻጥ የእወቁልን እና የህዝብ ግንኙነት የሚሉትን ቃላት
በተለዋዋጭነት እንጠቀምባቸዋለን። ዳንኤል (200፣57) “እወቁልን የሚለው ሀሳብ ዕወቁ ብቻ ሳይሆን
የማግባባት እና የዕእመኑኝ ፍላጎትም አለበት። ዕወቁልኝ እነዚህ ባህሪያት ከማስታወቂያ ጋር እጅጉን ያቆራኙት
እንጂ የልዩነት ነጥቦችም አሉት፤ ዕወቁልኝ የመረጃ ምንጭ ሆኖ በማገልገል እጅጉን የቀረበ ነው።” በማለት
ይገልፁታል።
ማስታወቂያ የአንድን ምርት፣ አገልግሎት (ሀሳብ) ለማስተዋወቅ ሲሆን ምርቶችን ለማማሻሻጥ ወይም
አገልግሎትን ለሰዎች ለማሳወቅ እና ረጅም የሚቆይ አመኔታን ለማምጣት የሚጠቅም ነው። ስለሆነም
ማስታወቂያ በግል፣ በፓለቲካ ፓርቲዎችና እጩዎች፣ በማህበራዊ ተቋማት፣በጎ ፈቃደኛ ቡድኖች እና
በመንግስት መስሪያ ቤቶች ጥቅም ላይ ይውላል (ወርልድ ቡክስ ሳይክሎፒድያ 1994፣72) ።

ማስታወቂያን በሁለት መድበን ስንመለከት የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ወይም የብሮድካስት በማለት


ልንለየው እንችላለን። ከዚህ አመዳደብ በመነሳት የዚህ ጥናት ትኩረት የሆነው የፅህፈት ማስታወቂያ
መነሻውም ከህትመት ወገን ከሆኑት ማስታወቂያዎች ነው። ሳራ (1992፣269) “የህትመት ማስታወቂያ ሰፋ
ያለ ቅርፅ ያለው እና ሠፊውን ሽፋን የሚይዝ ነው። ስለሆነም አስተዋዋቂዎች ለመሳብ በሚፈልጉት ታላሚ
አይነት ምስሎች፣ የድምፅ ቃና፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ዘመቻዎችን
ያከናውናሉ።” በማለት ገልፃዋለች። የህትመት ማስታወቂያ በጋዜጣ፣ በመፅሄት፣ እንዲሁም በበራሪ ወረቀቶች
የሚወጡ ማስታወቂያዎችን ይመለከታል። ከነዚህም መካከል በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ለተለያየ
አገልግሎት የሚወጡ ማስታወቂያዎችን የቋንቋ አጠቃቀም ይመረምራል።
1.2 የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት
የዚህ ጥናት አነሳሽ ምክንያት በዋናነት ሁለት ሲሆን የመጀመሪያው አጥኚዋ በሁለት አመት ቆይታዋ የሚወጡ
ማስታወቂያዎች ላይ የተሰሩ ስህተቶችን በማየቷ ነው። ይህም ማለት በኦዳ'ያኣ ግቢ በየቦታው ተለጥፈው
የምንመለከታቸውና የምናነባቸው ፅሁፎች በአብዛኛው የቃላት አጠቃቀም እና ምርጫ፣ የቋንቋ ሰዋሰው
አጠቃም ችግር፣ ወዘተ. እንከኖች ይታዩበታል። በመሆኑም ይህንን ችግር በጥናት ለመመርመር መታሰቡ ነው።
ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በቤተ መዛግብት፣ በቤተ መፅሀፍት እና አጥኚዋ በእስካሁኑ ቆይታዋ የተለያዩ
መመረቂያ ፅሁፍ ስታነብ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ኣያ ግቢ ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም ላይ የተሰራ
ጥናትና ምርምር ስላላጋጠማት ነው ። ስለዚህ እነዚህ ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ጥናቱን ለማጥናት በር
ከፍተዋል።

1.3 የጥናቱ አላማ


የዚህ ጥናት ዋና አላማ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ የሚዘጋጁ የማስታወቂያ ፅሑፎች የቋንቋ አጠቃቀም ላይ
ትንተና ማካሄድ ነው። በተጨማሪም ጥናቱ የሚከተሉትን ዝርዝር አላማዎች ይዟል።
 የማስታወቂያዎቹ የቃላት ምርጫ ምን እንደሚመስል መዳሰስ፤
 የማስታወቂያዎቹ ሰዋሰዋዊ የቋንቋ አጠቃቀም ሁኔታ ምን እንደሚመስል መፈተሽ፤
 የማስታወቂያ የቋንቋ አጠቃቀም ከታዋሽነት አይረሴነት አኳያ ምን እንደሚመስል መገምገም
ናቸው።

1.4 የጥናቱ ጠቀሜታ


ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት ተብሎ ይታሰባል።
1. ስለ ማስታወቂያ አፃፃፍ እና ምንነት እንዲሁም ምን ምን ነገሮችን ማሟላት እንዳለበት ግንዛቤ
ያስጨብጣል።
2. የሚወጡት ማስታወቂያዎች ምን ምን ችግሮች እንዳሉባቸው ይጠቁማል።
3. ለሚያወጧቸው ማስታወቂያዎች የማስተካከል እና የማረም ብቃት እንዲኖራቸው ያግዛል።
4. ተሰንዶ ቢቀመጥ ለሌሎች ተመራማሪዎች ወይም አጥኚዎች እንደ መነሻ በመሆን ያገለግላል።

1.5 የጥናቱ ክልል እና ገደብ


ይህ ጥናት በዋናነት የሚያተኩረው በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ በህንፃዎች በር እና ግድግዳ
፣በመመገቢያ አዳራሽ በር፣ በቤተ መፅሀፍት በር እና በማስታወቂያ መለጠፊያ ሰሌዳ ላይ በሚወጡ የአማርኛ
ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም ላይ ብቻ ያተኮረ ነው። ከዚህም ውጭ ግን ተማሪዎች መታወቂያ
ጠፋብን፣ መመገቢያ ካርድ ጠፋብን፣ ሀገር የሚለውጥ፣ ትምህርት ክፍል የሚለውጥ እና የመሳሰሉትን በማለት
የሚፅፉትን አያካትትም። ምክንያቱም ሁሉንም በግቢው ውስጥ የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችን ለመቃኘት እና
ለመመርመር የአቅም፣ የጊዜ እንዲሁም የገንዘብ እጥረት ስለሚገድብ ነው። በመሆኑም በኦዳ'ያኣ ግቢ ውስጥ
ከተለያዩ ቢሮዎች በሚወጡ በአማርኛ ቋንቋ በተፃፉ ማስታወቂያዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጥናቱ ተካሂዷል።

1.6 የጥናቱ ዘዴ
የጥናቱ ዘዴ ሲባል ጥናቱ በምን መልክ እንደሚጓዝ የሚያሳይ እና የጥናቱን ጠቅላላ ሁኔታ የሚመለከት ነው።
በመሆኑም ጥናቱ በገላጭ የምርምር ስልት ላይ የተመሰረተ ሲሆን በዚህ ክፍል ውስጥም የናሙና አመራረጥ
ዘዴ፣ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ እና የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተብራርተዋል።

1.6.1 የናሙና አመራረጥ ዘዴ


ለዚህ ጥናት የተመረጠው አመቺ የናሙና አመራረጥ ዘዴ ነው። ምክንያቱም አጥኚዋ የምትማረው በኦዳ'ያኣ
ግቢ መሆኑ ለጥናቱ የሚመቸው በዚሁ ግቢ ውስጥ የሚገኙ ማስታወቂያዎች ማግኘት ስለሆነ ከጥቅምት 14
እስከ የካቲት 15/2012 ዓ.ም ድረስ የተለጠፉትን በመሰብሰብ መረጃውን ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት ተደርጓል።
በኦዳ'ያኣ ግቢ በአመቺ ናሙና ከተመረጠ በኋላ በዚህ መሰረት ለጥናቱ መሰረት ከተመረጠ ለጥናቱ መረጃ
ይገኝባቸዋል ተብለው ከታሰቡት ቦታዎች፣ መመገቢያ አዳራሽ፣ በማስታወቂያ ሰሌዳዎች እና በተማሪዎች
የመኖሪያ ህንፃዎች አካባቢ የተገኙ 40 ማስታወቂያ ፅሁፎች ተሰብስበዋል። ነገር ግን ሁሉንም ለመስራት የጊዜ
እና የአቅም ችግሮች ስላሉ እንደገና በተራ የእጣ ናሙና ስልት 16 ማስታወቂያዎች ተመርጠው በዚህ ጥናት
ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል።
1.6.2 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
በዚህ ጥናት አገልግሎት ላይ የዋሉት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ምልከታ እና ሰነድ ፍተሻ ናቸው።
1.6.2.1 ምልከታ
አንድን መረጃ ትክክለኛ እና እውነተኛ እንዲሆን መረጃ ከሚገኝበት ቦታ ድረስ ዘልቆ በመግባት መረጃን
ለመሰብሰብ ከሚረዱ መሳሪያዎች ትልቁ ምልከታ ነው። ስለሆነም በዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ መረጃ ለማግኘት
ሲባል ባልታቀደ ምልከታ ለአምስት ወራት ያህል በተደጋጋሚ በየማስታወቂያ መለጠፊያዎች ድረስ በመሄድ እና
የተለጠፉትን ማስታወቂያዎች በመመልከት እና ፎቶግራፍ በማንሳት መረጃን ለመሰብሰብ ተሞክሯል።
1.6.2.2 ሰነድ ፍተሻ
ሌላው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሰነድ ፍተሻ ነው። በመሆኑም አጥኚዋ ከርዕሱ ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን
የተለያዩ ሠነድና ሠነድ ነክ ፅሁፎች በማንበብ ለጥናታዊ ፅሁፍ ተሰብስቧል።
1.6.3 የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
በዚህ ጥናት የተሰበሰበው መረጃ የሚተነተነው በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ነው። ያለው (2004፣410)
አይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ በሚገባ ከተጠናከረና ተጨባጩን አለም በትክክለኛ መንገድ እንዲያሳይ
ተደርጎ ከተሰራበት ግልፅና ለአንባቢ ትርጉም ያለው ሀሳብ ለመስጠት ያስችላል ይላሉ። በዚህ ጥናት
የማስታወቂያ ፅሁፎችን በመጠቀም የተሠበሰቡት መረጃዎች በየመልካቸው ከተደራጁ በኋላ በአይነታዊ መረጃ
መተንተኛ ዘዴ ከስርዓተ ነጥብ እና ከቃላት ምርጫ እፃር ለመተንተን ተሞክሯል።
2.8 የተዛማጅ ፅሁፍ ቅኝት
አጥኚዋ ከዚህ ጥናት ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተዛማጅነት ያላቸውን በማስታወቂያ ዙሪያ የሚዳስሱ
ስራዎች በጥቂቱ የተመለከተች ሲሆን ከዚህ ጥናት ጋር ያላቸውን ልዩነት አጥኚዋ በትኩረት አሳይታለች።
ይሁን እንጂ ከዚህ ጥናት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የጥናት ፅሁፍ ማግኘት አልተቻለም። በዚህም መሠረት
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ጥናታዊ ፅሁፎች የሚከተሉት ናቸው።
በመጀመሪያ የተዳሰሰው የበአካሉ በላይ (2004) “በ 2003 ዓ.ም በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የወጡ
ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም ትንተና” የሚል ነው። የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት በተጠቀሰው ጋዜጣ ላይ
የወጡ ማስታወቂያዎችን ቋንቋ መመርመር ሲሆን በዚህ መሰረት ይህ ጥናት ከበአካሉ በአላማቸው ተመሳሳይ
ቢሆንም ልዩነት አላቸው። ልዩነትም የበአካሉ በላይ ፅሁፍ በህትመት ሚድያ ላይ ያተኮረ ሲሆን ይህ ጥናት
ሰሌዳ (መለጠፊያ) ቦታ ላይ በሚለጠፉ ፅሁፎች ላይ ነው። በተጨማሪም የጊዜ ልዩነትም አላቸው። የበአካሉ
ጥናት በ 2003 ዓ.ም በተሰራጩ ማስታወቂያዎች ሲሆን ይህ ጥናት ደግሞ በ 2012 ዓ.ም በወጡ
ማስታወቂያዎች ላይ ነው።
ሁለተኛው ከዚህ ጥናት ጋር ተዛማጅነት ያለው ፅሁፍ የከፍያለው (2004) “የኢትዩጵያ ቴሌቪዥን
የማስታወቂያ ይዘት ትንተና” የሚል ሲሆን ጥናቱ በማስታወቂያ ዙሪያ የተሠራ መሆኑ አንድ ሲያደርጋቸው
ልዩነታቸው ደግሞ የከፍያለው ጥናት የኤሌክትሮኒክስ ሚድያ ላይ የሚተላለፍ ማስታወቂያ ሲሆን ይህ ጥናት
ደግሞ ህትመት ሚድያ ላይ ያተኮረ መሆኑ ነው። በተጨማሪም የዚህ ጥናት ቋንቋ አጠቃቀም ትንተና ሲሆን
የከፍያለው ጥናት ደግሞ የይዘት ትንተና መሆኑ ያለያያቸዋል።
የመጨረሻው ከዚህ ጥናት ጋር ተዛማጅነት ያለው የኢሳያስ ኢልባሶ (2010) “ከየካቲት 2009 ዓ.ም ወዲህ
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የወጡ ማስታወቂያዎች የቋንቋ አጠቃቀም ትንተና” ሲሆን ከዚህ ጥናት ጋር አንድ
የሚያደርጋቸው የመጀመሪያው ቋንቋ አጠቃቀም ላይ ማተኮራቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሠዋሰው እና
የቃላት ምርጫን የሚተነትኑ መሆናቸው ነው። የኢሳያስ ጥናት ከዚህ ጥናት የሚለየው የኢሳያስ ጥናት
ማስታወቂያዎቹን ምስል እና የመልዕክት ቁጥብነት የሚያሳይ ሲሆን ይህ ጥናት በናሙናዎቹ ስዕል ያለው
ማስታወቂያ ባለመኖሩ ይህ አለማሳየቱ ነዉ።

You might also like