You are on page 1of 246

አማርኛ

እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ


የመምህር መምሪያ
5ኛ ክፍል

አዘጋጆች
ሐዋዝ ወልደየስ በየነ
ቦሰና ጀጃው መኮንን
ነጅም ፈጅር መሐመድ
ቻላቸው አንዳርጌ ተገኘ

አማካሪ
ጌታቸው እንዳላማው አስፋው (ረ/ፕ)

የቡድን መሪ
ቻላቸው ገላው ሰጠኝ

የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስቴር እና አብክመ ትምህርት ቢሮ


ይህ መጽሐፍ የተዘጋጀው ከአሜሪካ ህዝብ በአሜሪካ ዓለማቀፍ የልማት ድርጅት (United States
Agency for International Development (USAID) በኩል በተገኘው የገንዘብና የቴክኒክ
ድጋፍ፣ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በክልሉ ትምህርት ቢሮና በREAD TA ፕሮጀክት ትብብር ሲሆን
የህትመቱ ወጪ በሁለተኛው የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ፕሮግራም (General Education
Quality Improvement Program (GEQIP II) ተሸፍኗል።
የመጽሐፉ ህጋዊ የቅጂ ባለቤት ©2007 ዓ.ም. በኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴርና የአማራ ክልል
ትምህርት ቢሮ ናቸው።

ISBN: 978-99944-2-041-4
የይዘት ማውጫ

የማስተማር መርሖችና የመምህር መምሪያ  iv

ምዕራፍ 1
ጓደኝነት  1

ምዕራፍ 2
አካባቢያችን  25

ምዕራፍ 3
ልማዶች  47

ምዕራፍ 4
የትራፊክ ደህንነት  69

ምዕራፍ 5
ጽዳትና ንፅህና  88

ምዕራፍ 6
ምግብ  107

ምዕራፍ 7
የዱር እንሰሳት በኢትዮጵያ  125

ምዕራፍ 8
ባህላዊ ጨዋታዎች  143

ምዕራፍ 9
ሥነቃል  161

ምዕራፍ 10
ኤች.አይ.ቪ./ኤድስ፤ መድሎና መገለል፣  180

ሙዳየቃላት  198

መርሃትምህር
አንደኛ ወሰነትምህርት  201

ሁለተኛ ወሰነትምህርት  209

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ማውጫ iii


የማስተማር መርሖችና የመምህር መምሪያ
መግቢያ
ይኽ የመምህር መምሪያና ከዚህ ጋርም አብሮ የሚሄደው የተማሪ መጽሐፍ ከ5ኛ እስከ8ኛ ክፍል ድረስ
አማርኛን በአፍ መፍቻ ቋንቋነት የሚማሩ ተማሪዎች በቋንቋዉ በብቃት ማዳመጥ፣ መናገር፣ ማንበብና
መጻፍ እንዲችሉ ለማድረግ ተሻሽሎ የተዘጋጀው የአፍ መፍቻ ቋንቋ ሥርዓተትምህርት አካል ናቸው።
የመጽሐፍ ዝግጅቱም፣ የተማሪዎች የማንበብና የመጻፍ ችሎታ ስለሚዳብርበትና ከ5ኛ-8ኛ ላሉ የክፍል
ደረጃዎች ተስማሚ በሆኑ ጠቃሚ የማስተማሪያ ዘዴዎች መለዮ ባሕርያት በተደረጉ ጥናቶች ላይ
የተመሠረተ ነው።

የመምህር መምሪያዉ በሥርዓተትምህርቱ ላይ በመመሥረት በአዳዲሶቹ የመማሪያ-ማስተማሪያ


መሣሪያዎች ውስጥ በጥቅም ላይ ስለዋሉት የማስተማር አቀራረቦችና ስለተሻሻለው መርሃትምህርት
(ሥርዓተትምህርት) መነሻ ሀሳቦች መሠረታዊ መረጃ ይሰጣል። በአንድ ምዕራፍ ሥርም ለተሰናዱት
የሦስት ሣምንታት ትምህርቶች ግልጽ መመሪያ ያቀርባል። በተጨማሪም ተማሪዎች የሚማሩትን
ትምህርት ለመከታተልና አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ ተገቢውን ድጋፍና ማጠናከሪያ ለመስጠት
ተከታታይ ምዘናን መተግበር የሚቻልበትን መርሕ ይዟል። በትምህርቱ ሂደት ውስጥ የሥርዓተፆታንና
አካቶ ትምህርትን እንዴት ማረጋገጥ እንደሚገባ ድጋፍ ይሰጣል።

በመጨረሻ ላይም ለ5ኛ-8ኛ ክፍሎች የተዘጋጀው አማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት
ተያይዟል። ይኽ መርሃትምህርትም በየደረጃው በእያንዳንዱ ወሰነትምህርት ተማሪዎች ሊያዳብሯቸው
ስለሚገቡ የቋንቋ ብቃቶች ያሳያል። ከመርሃትምህርቱ ቀጥሎም ለመምህራን አዲስ/እንግዳ ለሆኑ
በአፍመፍቻ ቋንቋ ከማንበብና ከመጻፍ ትምህርት ጋር በጥቅም ላይ የዋሉ ቃላትንና ሐረጋትን የያዘ
ሙዳየቃላት (ሐረጋት) ተያይዞ ቀርቧል።

የማንበብ/የመጻፍ አላባውያን
ተማሪዎች ቀልጣፋ አንባቢና ጸሐፊ ይሆኑ ዘንድ ሊያዳብሯቸው የሚገቡ የማንበብና የመጻፍ አምስት
አላባውያን መኖራቸውን በመስኩ የተደረጉ ምርምሮች ያመለክታሉ። ተማሪዎቹ ራሳቸውን የቻሉ
አንባቢዎችና ጸሐፊዎች እንዲሆኑ ለመርዳት መምህራን ሥርዓት ባለውና ግልጽ በሆነ መንገድ
እነዚህን አላባውያን ማስተማር ይጠበቅባቸዋል። ግልጽ በሆነ መንገድ ሲባል፣ መምህራን አርኣያ
(ሞዴል) ሆነው እያሳዩ፣ ለተማሪዎች ክሂሎቹንና ክሂሎቹ ስለሚዳብሩበት መንገድ ማስተማር ማለት
ነው። ትምህርቱ ሥርዓት ባለው ሁኔታ ይሰጣል ሲባልም፣ በትምህርቱ ሂደት በየምዕራፉ ያለ አንድም
ተፈላጊ አላባ ሳይዘለል፣ በየደረጃው ክሂሎችን ከቀላል ወደከባድ ማስተማር ማለት ነው። እነዚህም
አምስት አላባውያን የሚከተሉት ናቸው፤
• የንግግር ድምጾች ግንዛቤ

• ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ

• አቀላጥፎ ማንበብ

• የቃላት ዕውቀት

• አንብቦ መረዳት

ወደፊት በሂደት እንደሚታየው ሌሎች አላባውያንም በጣም ጠቃሚ ቢሆኑም፣ እነዚህ አምስት አላባውያን

iv አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


ግን የተማሪዎችን የማንበብና የመጻፍ ክሂሎች ለማጐልበት ልናስተምራቸው የሚገቡ ክሂሎች ናቸው።
እነዚህን በአግባቡ ማስተማር፣ ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው እንዲያነቡና እንዲጽፉ የሚያስችሏቸውን
መሠረታዊ ክሂሎች ማስገንዘብ ማለት ነው።

የንግግር ድምጾች ግንዛቤ፡- የንግግር ድምጾችን የመስማት፣ የመለየትና የመገንዘብ ችሎታ ነው። ይኼም
በ1ኛ እና በ2ኛ ክፍል መርሃትምህርቶችና የትምህርት ዝግጅቶች ውስጥ ተገቢ ትኵረት የተሰጠው አላባ
ነው። አላባዉ በጣም ጠቃሚ ነው፤ ምክንያቱም፣ ድምጾችን ከፊደሎች ጋር አገናኝቶ ለመረዳት በጣም
አስፈላጊ ስለሆነ ነው። ለማንበብና ፊደላትንም በሥርዓት ሰድሮ ቃላትን ለመጻፍ ያግዛል። ይሁንእንጂ፣
በዚህ ረገድ ተማሪዎች የሚቸግራቸውና የሚቀራቸው ነገር መኖሩን መምህራን ካልተገነዘቡ በስተቀር፣
ከ5ኛ-8ኛ ክፍል ባሉት ደረጃዎች በቀጥታ የሚቀርብ አላባ አይደለም። መምህራን አስፈላጊ መሆኑን
ሲገነዘቡ ግን፣ ድጋፉ ለሚያስፈልጋቸው የተወሰኑ ተማሪዎች ጊዜ መድበው ስለንግግር ድምጾች ግንዛቤ
ክለሳ ማድረግ ይችላሉ። በዚህ ረገድም የበለጠ ውጤታማ ለመሆን የ1ኛና የ2ኛ ክፍል መምህራንን
ማማከር ጠቃሚ ነው።

ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ፡- ፊደሎችን ከሚወክሏቸው ድምጾች ጋር የማገናኘት ችሎታ ነው።


ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም፣

• ቃላትን ለይቶ ለመጥራት ያስችላል። ይኽም ተማሪዎቹ ራሳቸውን የቻሉ አንባቢዎች


እንዲሆኑ ያግዛቸዋል።

• ፍደላን (በቃላት መዋቅር የፊደላትን አሰዳደር ሥርዓት) ያግዛል፤ በዚህም ተማሪዎች


የሚያዳምጧቸውን ድምጾች ከትክክለኛዎቹ ፊደሎች ጋር ማዛመድ ይችላሉ።

ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ ከ1ኛ- 4ኛ ክፍል የበለጠ ትኵረት የተሰጠው አላባ ሲሆን፣ ተማሪዎችም
ፊደላትንና የሚወክሏቸውን ድምጾች በተናጠል፣ እንዲሁም ቃላትን በመነጣጠልና በማጣመር
ተምረዋል። ከ5ኛ-8ኛ ክፍል ግን ትእምርተድምጻዊ ግንዛቤ የሚተገበረው ተማሪዎች በቃላት ጥናትና
በአቀላጥፎ ማንበብ ትምህርታቸው ረገድ የሚሰጧቸውን ተግባራት ሲያከናውኑ ብቻ ነው።

አቀላጥፎ ማንበብ፡- አቀላጥፎ ማንበብ ተማሪዎች ለራሳቸውና ለሚያዳምጧቸው ሰዎች ስሜት እንዲሰጥ
አድርገው አንድን ጽሑፍ በትክክልና በተገቢው ፍጥነት ማንበብ መቻላቸውን የሚመለከት ነው። ከዚህ
በተጨማሪም ጽሑፍን በተገቢው አገላለጽ (የጽሑፉን መልዕክት የሚያመለክቱትን የድምጽ ቃናንና
ጫናን ለይቶ) ማንበብን ያካትታል። አቀላጥፎ ማንበብ አስፈላጊ የሚሆንበት ምክንያት፣ ተማሪዎች
ያለችግርና ያለግድፈት በፍጥነት ማንበብ ከቻሉ፣ በአንብቦ መረዳት ላይ ማተኮር ስለሚችሉ ነው።

አቀላጥፎ መናገርና አቀላጥፎ መጻፍ በተገቢ ሁኔታ ራስን መግለጽን ይመለከታል። ይኽም ቋንቋውን
በትክክል መጠቀምንና ሀሳብን ለሌላ አካል በንግግርም ሆነ በጽሑፍ በግልጽ ማስተላለፍን ይጨምራል።

አቀላጥፎ ማንበብ ሊዳብር የሚችለው በርካታ ድምጽ በማሰማት የማንበብ ልምምዶችን ከተገቢ
ግብረመልሶች ጋር በመስጠት ነው። በመሆኑም የንግግርና የጽሑፍ አቀላጥፎ የሚዳብረው ተማሪዎች
በተቻለ መጠን ራሳቸውን እንዲገልጹ በርካታ ዕድሎችን ሲመቻቹላቸውና ወቅታዊ ግብረመልሶችም
ሲያገኙ ክሂሉን በቀላሉ ማዳበር ይችላሉ።

የቃላት ዕውቀት፡- ቃላትን የመለየት/የመረዳትና ፍቻቸውን የመገንዘብ ችሎታ ነው። የተገደበ የቃላት
ዕውቀት ያላቸው ተማሪዎች የሚያነቡትንም ሆነ የሚያዳምጡትን ጽሑፍ መልዕክት ለመረዳትና
በደረጃቸው ስለጽሑፉ ያላቸውን አስተያየት በንግግርም ሆነ በጽሑፍ ለመስጠት ይቸገራሉ። ስለሆነም
የቃላት ዕውቀት በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም ተማሪዎች፣

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ v


• ለአቀላጥፎ ማንበብ አሰተዋጽዖ ያላቸውን ቃላት ወይም ሐረጋት ከጽሑፍ ውስጥ ለይተው
ይረዳሉ።

• ስለምን እያነበቡ ወይም እያዳመጡ እንደሆነ ይረዳሉ።

• ሀሳባቸውን ለሌላ ሰው በንግግርም ሆነ በጽሑፍ ይገልጻሉ።

የቃላት ዕውቀት የሚዳብረው አዳዲስ ቃላትን ከነፍቻቸው በማስተማር፣ ተማሪዎች እነዚህን ቃላት
በንግግርም ሆነ በጽሑፍ እንዲጠቀሙባቸው በማበረታታትና ከሚያነቡት ወይም ከሚያዳምጡት ጽሑፍ
ውስጥ የቃላትን ፍቺ የሚያገኙበትን ብልሃት (ስትራተጂ) በማስተማር ነው።

(አዳምጦ/አንብቦ) መረዳት፡- አንድን ጽሑፍ ወይም ንግግር የመረዳትና የመተርጐም ችሎታ ነው።
የማዳመጥና የማንበብ የመጨረሻ ግብም ነው። ይኽ ክሂል ቀጥተኛ መረዳትን ወይም በጽሑፍ ውስጥ
ያለን መረጃ ማስታወስን፣ ፈልፍሎ/አንጠርጥሮ መረዳትን ወይም በቀጥታ ያልተገለጸን መረጃ መረዳትንና
የመረዳት ስልቶችን ወይም ጽሑፉን ለመረዳት ወይም ለመተርጐም አንባቢዎች የሚጠቀሙባቸውን
ብልሃቶች ያጠቃልላል። ክሂሉ በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም፣

• ተማሪዎች በሁሉም ትምህርቶች በማንበብ እንዲማሩ ብቁ ያደርጋል።

• ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው የሚያነቡና የሚያዳምጡ እንዲሆኑ ያስችላል፤ ከዚህም


በላይ በሕይወት ዘመናቸው ለመማርና ከተለያዩ ምንጮች መረጃ ለማግኘት ክሂሉን
ይጠቀሙበታል።

አዳምጦ/አንብቦ መረዳት የሚዳብረው በቅድመማዳመጥ/ማንበብ፣ በማዳመጥ/በማንበብ ሂደትና


በድኅረማዳመጥ/ማንበብ ተግባራት ነው። ተማሪዎች ስለጽሑፉ (በቅድመማዳመጥ/ማንበብና በማዳመጥ/
በማንበብ ሂደት ወቅት) እንዴት መገመት እንደሚችሉ፣ መረዳታቸውን (በራሳቸው) እንዴት መቆጣጠር
እንደሚችሉና ያዳመጡትን ወይም ያነበቡትን እንዴት መገምገም እንደሚችሉ መማር አለባቸው።

የትምህርቱ ምዕራፎች
በእያንዳንዱ ምዕራፍ በሁሉም ክሂሎች (ማዳመጥ፣ መናገር፣ ማንበብና መጻፍ) የቀረቡት የትምህርት
ይዘቶች የማንበብንና የመጻፍን ችሎታዎች በሚያዳብሩበት መልክ ተደራጅተዋል። ይኽም ማለት፣
• የምንባብ ይዘቶችና ርዕሰጉዳዮች ማዳመጥን፣ መናገርን፣ ማንበብንና መጻፍን ለማስተማር
ለምናዘጋጃቸው የትምህርት ይዘቶች በመሣሪያነት ወይም በዐውድነት ያገለግላሉ።

• በሁሉም ምዕራፎች የትምህርት ይዘቶች፣ አራቱ የቋንቋ ክሂሎች ተዋህደው ቀርበዋል።

የተማሪ መጽሐፍና የመምህር መምሪያ በእያንዳንዱ ምዕራፍ የሦስት ሳምንት የትምህርት ይዘቶች
እንዲይዙ ተደርገው ተደራጅተዋል። እያንዳንዱም ሳምንት 40፣ 40 ደቂቃ ርዝማኔ ያላቸው ሦስት
ክፍለጊዜያት ስላሉት፣ የትምህርት ይዘቶችም በዚሁ መሠረት ተዋቅረው ቀርበዋል። ምንም እንኳ
በትምህርትቤቶች የትምህርት ዓመት መርሃግብር (ካሌንደር) ላይ መመሥረት የግድ ቢሆንም፣
በመጻሕፍቱ የተካተቱትን የየምዕራፉን ትምህርት ይዘቶች ለማጠናቀቅ ከሦስት ሳምንትም በላይ
ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል። በዚህ ጊዜ መምህራን ይዘቶቹን ለማጠናቀቅ አማራጭ ዘዴ መፈለግ
ይጠበቅባቸዋል። እያንዳንዱ ሳምንት ቀጥሎ በዝርዝር የምንጠቅሳቸው ሰባት የትምህርት አላባውያን
አሉት።

የቃላት ጥናት፡- በምንባቦች ውስጥ ያሉትን ውስብስብ ቃላት (ረጃጅም፣ የተውሶና ተዘውታሪ ያልሆኑ

vi አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


ቃላትን) ይዘቶቸን በመማር ላይ ያተኩራል። በቃላቱ ውስጥ ያሉ ፊደላትን ወይም ቅጥያዎችንና
ዋና ቃላትን በመነጠልና በማጣመር፣ እንዲሁም የዋና ቃላቱንና የቅጥያዎቹን ፍቺዎች በመማር ላይ
የተመሠረተ ነው።

አንብቦ መረዳት፡- በእያንዳንዱ ምዕራፍ ሥር በተለያዩ ርዕሰጉዳዮች ላይ ተመሥርተው የቀረቡትን


ሦስት ምንባቦች በማንበብና በመረዳት ላይ ያተኩራል። አቀራረባቸውም ተማሪዎችን በተለያዩ
የመናገርና የመጻፍ ተግባራት በሚያሳትፍ መልኩ ነው። ተግባራቱም የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፤

• የምንባቦች ርዕሰጉዳዮችን ወይም የምንባብ ይዘቶችን ከተማሪዎች የቀደመ ዕውቀት ጋር


የሚያይዙ ተግባራት፣

• ከንባብ በፊት ስለምንባቦቹ ይዘት ምንነት የመገመት የቅድመንባብ ተግባራት፣

• በምንባብ ውስጥ ያሉ ቊልፍ ቃላትን መማር ወይም በነሱ ላይ የመወያየት ተግባር፣

• ምንባቦችን የማንበብ ተግባር፣

• በማንበብ ሂደት ምን ያህል እንደተረዱ ራስን የመለካት ብልሃቶችን (self-checking strate-


gies) የመጠቀም ተግባር፣

• በምንባቡ ላይ የተመሠረቱ ልዩ ልዩ የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን የመመለስ ተግባር፣

• በምንባቡ ይዘት ላይ በክፍል ወይም በአነስተኛ ቡድን የመወያየት ተግባር፣

• ስለምንባቡ፣ ስለርዕሰጉዳዩ ወይም ስለምንባብ ይዘት የመጻፍና የመናገር ተግባር፣

• የተለያዩ ክንዋኔዎችን ለማዘጋጀትና ለመከወን ምንባቡን (ግጥም ወይም አፈታሪክ ወይም


ተውኔት) እንደናሙና የመጠቀም ተግባር፣

የቃላት ዕውቀት፡- በሚነበቡና በሚደመጡ ምንባቦች ውስጥ የሚገኙ አዳዲስ ቃላትን በመማርና
በመጠቀም ላይ ያተኩራል። በዚህ ሥር የሚዘጋጁ ተግባራት የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፤

• የቃላቱን ንበት፣ ፍቺ፣ ክፍሎችና የተለያዩ አጠቃቀሞች መማር፣

• ተመሣሣይ አወቃቀርና ፍቺ ያላቸውን ሌሎች ቃላትን መማር፣

• በሚነበቡና በሚደመጡ ምንባቦች ውስጥ ያሉ አዳዲስ ቃላትን መለየትና መረዳት፣

• ቃላቱን በመናገርና በመጻፍ ተግባራት ውስጥ መጠቀም፣

መጻፍ፡- በምዕራፉ የምንባብ ይዘቶች፣ ርዕሰጉዳዮችና የጽሑፍ ዓይነቶች ላይ በመመሥረት በርካታ


ጽሑፎችን በመጻፍ ላይ ያተኩራል። መጻፍ፣ ድርሰት መጻፍንና የአጻጻፍ ሥርዓቶችን ያጠቃልላል።

ድርሰት የመጻፍ ተግባራት የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፤


• ቅድመመጻፍ፡- አንድን ጽሑፍ ወይም ጽሑፎች ካነበቡ በኋላ በምንባቡ ጭብጥ ወይም
ርዕሰጉዳይ ላይ መወያየት፣ የቢጋር ሠንጠረዥ ማዘጋጀት፣ በዚህም ላይ ተመሥርቶ
ቊልፍ ሀሳቦችን ማደራጀት፣

• ማርቀቅ፡- ሀሳብን አሰባስቦ መግቢያ፣ አካል፣ መደምደሚያ ያለው ጽሑፍ መጻፍ፣


• መከለስ፡- የጽሑፉን ሀሳብ አደረጃጀትና ሙሉነት፣ እንዲሁም ግልጽነት፣ ሳቢነትና
ግጥምጥምነት ለማሳካት የመሻጋገሪያ ቃላትና ሐረጋት በአግባቡ በጥቅም ላይ መዋላቸውን

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ vii


መልሶ በማንበብ ማረጋገጥ፣

• ማረም፡- የአጻጻፍ ሥርዓቶች (ፍደላ፣ ሥርዓተነጥብ፣ ሰዋስዋዊ ትክክለኛነት፣ የቃላት


አጠቃቀም፣ የአንቀጽ አከፋፈል) በአግባቡ መከበራቸውን ለማረጋገጥ የአርትኦት ሥራ
መሥራት፤

• ማሳተም፡- በአንድ ዓይነት መንገድ፣ በጽሑፍም ሆነ በቃል፣ ጽሑፉ ለሕዝብ የሚቀርብበትን


መንገድ ማመቻቸት፣

እነዚህ ሁሉ ተግባራት በግል ወይም በቡድን ወይም በጥንድ ሊፈጸሙ ይችላሉ።

የአጻጻፍ ሥርዓቶች ለደረጃው ተገቢ የሆኑትን የትክክለኛ ጽሑፍ መዋቅራዊ አካላትን መማር
ያጠቃልላሉ።
• ፍደላ

• ንበት

• ምኅፃረቃላት

• ሥርዓተነጥብ ወዘተ.

አቀላጥፎ ማንበብ፡- አንድን ምንባብ ለክፍል ደረጃው በተወሰነው የንባብ ፍጥነት፣ በትክክልና ለጽሑፉ
ተሳማሚ በሆነ አገላለጽ (አነባበብ) ድምጽ እያሰሙ በማንበብ ችሎታ ላይ ያተኩራል።

ቃላዊ ክሂሎች፣ ማዳመጥና መናገር፡- በምዕራፉ የምንባብ ይዘትና ርዕሰጉዳይ ላይ ተመሥርቶ የቀረበን
ምንባብ አዳምጦ በመረዳት፣ በምንባቡ መሠረት በቃልና በጽሑፍ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ሀሳብን
አደራጅቶ በንግግር በማቅረብ ላይ ያተኩራል። በዚህ ሥር ከሚካተቱት ተግባራት መካከል የሚከተሉት
ይጠቀሳሉ፤
• የማዳመጥ ምንባቦችን ርዕሰጉዳዮች ወይም የምንባብ ይዘቶችን ከተማሪዎች የቀደመ ዕውቀት ጋር
የሚያያይዙ ተግባራት፣

• ከማዳመጥ በፊት ስለምንባቦቹ ይዘት ምንነት የመገመት የቅድመማዳመጥ ተግባራት፣

• በማዳመጥ ምንባብ ውስጥ ያሉ ቊልፍ ቃላትን መማር ወይም በነሱ ላይ የመወያየት ተግባር፣

• ምንባቦችን የማዳመጥ ተግባር፣

• በማዳመጥ ምንባቦች ላይ የተመሠረቱ ልዩ ልዩ የአዳምጦ መረዳትና አመራማሪ ጥያቄዎችን


የመመለስ ተግባር፣

• በማዳመጥ ምንባቡ ይዘት ላይ በክፍል ወይም በአነስተኛ በቡድን የመወያየት ተግባር፣

• ስለማዳመጥ ምንባቦች ይዘት/ስለርዕሰጉዳዮች ለሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች የመዘጋጀትና


በንቃት የመሳተፍ ተግባር፣

• በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተዘጋጅቶ ንግግር የማቅረብ ተግባር፣

ሰዋስው፡- በመርሃትምህርቱ ላይ ተመሥርቶ ለየደረጃው በተዘጋጀው የትምህርት ወሰንና ተለጣጥቆ


(Scope and Sequence) መሠረት (ለምሳሌ፣ ነጠላና ብዙ ቊጥር፣ የአሁንና የኃላፊ ጊዜያት ግሶች፣

viii አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


ቅጽሎችና ተውሳከግሶች፣ ውስብስብ ዓረፍተነገሮች ወዘተ.) የተለያዩ ሰዋስዋዊ መዋቅሮችን በመማርና
በትክክል በመጠቀም ላይ ያተኩራል።

በአጠቃላይ ከላይ የዘረዘርናቸው የትምህርት አላባውያን ማዕከል ያደረጉት በምዕራፍ የምንባብ ይዘቶችና
በርዕሰጉዳዮች ላይ ተመሥርተው በተዘጋጁት የማንብብና የማዳመጥ ምንባቦች ላይ ነው። ተግባራቱም
ተማሪዎቹ ከ5ኛ ክፍል ጀምረው 8ኛ ክፍል እስከሚደርሱ ድረስ የውስብስብነት ደረጃቸውን ጠብቀው፣
አምስቱን የማንበብና የመጻፍ አላባውያንና አራቱን የቋንቋ ክሂሎች (ማዳመጥ፣ መናገር፣ ማንበብና
መጻፍ) መማርንና ማስተማርን የሚያጠናክሩ ናቸው። የእያንዳዱ ምዕራፍ የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት
ይዘቶች ተማሪዎች የሚማሯቸውን ክሂሎች በማስተዋወቅ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ሁለተኛዎቹ ሳምንታት
ክሂሎችን በማለማመድ ላይ፣ ሦስተኞቹ ሳምንታት ደግሞ ክሂሎችን በተለያዩ ተግባራት በመጠቀምና
ተማሪዎች የተማሯቸውን በመመዘን ላይ እንዲያተኩሩ ሆነው የተዘጋጁ ናቸው። በተለይ በሦስተኛዎቹ
ሳምንታት ተማሪዎቹ በተማሩት መሠረት በቃላቸው ወይም በጽሑፍ የሚመልሷቸው የቤትሥራዎችን
በመስጠት ምን ያህል የምዕራፉን ትምህርት እንደተገነዘቡ መምህራን ይገመግማሉ።

የማስተማር መርሖች
ልሥራ፣ እንሥራ፣ ሥሩ
በዚህ ሥርዓተትምህርት ውስጥ ዋነኛው የማስተማሪያ ዘዴ በተለምዶ “ልሥራ፣ እንሥራ፣ ሥሩ” ወይም
በትክክለኛ አጠራሩ “ሚናን ለተማሪዎች ቀስበቀስ የማስተላለፍ ናሙና (ሞዴል)” (gradual release
model) ተብሎ ይታወቃል። ተማሪዎች በመጀመሪያ ጥያቄዎች ወይም ተግባራት በመምህር ሲሠሩ
ያያሉ፤ ቀጥሎም የክፍሉ ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር አብረው በጋራ ይሠራሉ፤ በመጨረሻም
ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው በግላቸው እንዲሠሩ የሚደረግበት የማስተማር ዘዴ ነው። ምንም እንኳ
ሁሉም ደረጃዎች በሁሉም ቦታ ተሟልተው የማይገኙበት ሁኔታ ቢኖርም፣ ሞዲሉ ለአብዛኛዎቹ
የትምህርት ክንውኖች ወይም ተግባራት በዚህ መምሪያ ውስጥ በግልጽ ተብራርቶ ቀርቧል። ዘዴው
ተማሪዎች አዳዲስ ክንውኖችን ወይም ተግባራትን ለመሥራትና በራስ የመተማመን አቅማቸውን
ለመገንባት ይረዳቸዋል።

በመተባበር መማር (Cooperative Learning)

በመተባበር መማር ተማሪዎች በቢጤ ወይም በቡድን ተደራጅተው ከክፍል ጓደኞቻቸው ጋር


በመደበኛነት ወይም ለአጭር ጊዜ ተወስነው የሚሰጧቸውን ተግባራት የመሥራት ዕድልን ይፈጥራል።
ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር አዳዲስ መረጃዎችን የመለዋወጥ ዕድል ስለሚፈጥር የክፍል ውስጥ መማርን
ያጠናክራል። በመተባበር መማር ብዙ ተማሪዎች ባሉበት ክፍል ውስጥ በንቃት እንዲሳተፉ ዕድል
ይፈጥራል።

ግብረመልስ መስጠት

አንዱ የማስተማር ዋነኛ አካል ተማሪዎች በተናገሯቸው፣ ባነበቧቸው፣ ባቀረቧቸው ወይም በጻፏቸው
ነገሮች ላይ ግብረመልስ መስጠት ነው። አንዳንድ ጊዜ ግብረመልስ ሳይሰጡ በሚሠሩ መለማመጃዎች
ላይ ብቻ ማተኮር ጠቃሚ ሊመስል ይችላል። ነገርግን ተማሪዎች የተሰጣቸውን ተግባር እንዴት
መሥራት እንዳለባቸውና የሠሩትም ትክክል መሆኑን ወይም አለመሆኑን ለመረዳት ስለሚጠቅማቸው
ግብረመልስ መስጠት አስፈላጊ ነው። ግብረመልስ መስጠት ውጤታማ ይሆን ዘንድ መምህራን
የሚከተሉትን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
• ተማሪዎች የሰጡት ምላሽ ትክክል ወይም ስህተት መሆኑን መንገር፤

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ ix


• ተማሪዎቹ የሰጡት መልስ ለምን ትክክል ወይም ስህተት ሊሆን እንደቻለ ማብራራት፤

• በትክክል የተሠራውን ለተማሪዎች መንገር፤

• የሚጠበቅባቸውን ተግባር በትክክል እንዴት መሥራት እንዳለባቸው ወይም ምን ዓይነት


ብልሃት መጠቀም እንደላባቸው መንገር፤

ተማሪዎች የሚነገራቸውን ትክክለኛ መልስ ወይም አቀራረብ ከመስማት ይልቅ በራሳቸው ትክክለኛ
መልስ ላይ እንዲደርሱ ወቅታዊ ግብረመልስ በመስጠት ይታገዛሉ። ለምሳሌ አንድ ተማሪ አንድ
አንቀጽ ሲያነብ/ስታነብ አንድ ቃል ሲጠራ/ሰትጠራ ቢሳሳት/ብትሳሳት በሚከተለው አኳኋን ሊነገረው/
ራት ይገባል፤ አንቀጹን ጥሩ አንበሃል/ሻል፤ ግን የሁለተኛው ዓረፍተነገር ሁለተኛ ቃል “ቤቶች” ሳይሆን
“ቤታችን” ነው፤ ስለ“-ኣችን” መማራችንን ታሳታውሳለህ/ሻለሽ? ወይም አንድ ተማሪ ከምንባቡ ውስጥ
ያሉትን ዋናዋና ነጥቦች እንዲዘረዝር/እንድትዘረዝር ለቀረበለት/ላት ጥያቄ የሰጠውን/ቺውን ምላሽ
በማጤን፣ ከምንባቡ ዋናዋና ነጥቦች ውስጥ ሁለቱን በትክክል መልሰሃል/ሻል፤ ጥሩ ነው፤ ሦስተኛው
ነጥብ ምን እንደሆነ ልትነግረኝ/ሪኝ ትችላለህ/ቺያለሽ? ወዘተ.

የማስተማሪያ መርጃ

በብዙ አካበቢዎች የሚገኙ የመማሪያ ክፍሎች ለትምህርት አገልግሎት የሚውሉ ቁሳቁሶች የተሟላላቸው
ናቸው ማለት አዳጋች ነው። ስለዚህ በቀላሉ ባካባቢው ሊዘጋጁ የሚችሉ የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችን
ለማዘጋጀት ወይም ለመፍጠር ጥረት ማድረግ ተገቢ ነው። ስለሆነም ለዚህ ሥርዓተትምህርት ጠቃሚ
ከሆኑት ቀላል የማስተማሪያ መርጃ መሣሪያዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል።

ፍላሽ ካርዶች፡- እነዚህ ለምሳሌ ተማሪዎች የሚማሯቸውን ቃላት የሚያሳዩ ክርታሶች/ ካርዶች ናቸው።
እነዚህ ካርዶች ቃላቱን ሰሌዳ ላይ ከመጻፍና ያን እያጠፉ በመጻፍ ጊዜ ከማጥፋት በፍጥነት ካንዱ
ፊደል ወይም ቃል ወደሌላው በቀላሉ እየለዋወጡ ለመጠቀም አመቺ ናቸው። ከርቀት ለማንበብም
ቀላል ስለሆኑ፣ ለሁሉም የክፍል ተማሪዎች፣ ለአነስተኛ ቡድኖች ወይም ለግለሰቦችም በቀላሉ ለመጠቀም
ያመቻሉ። በቀላሉም ቀደም ብሎ ለማዘጋጀትና እንዳስፈላጊነቱ ደጋግሞ ለመጠቀም አመቺ ናቸው።

ባዶ የመውጫ ካርዶች፡- እነዚህ እንደፍላሽ ካርዶች ተቆራርጠው የተዘጋጁ ስለሆኑ፣ ተማሪዎች


እየጻፉባቸው ለመምህራቸው የሚያሳዩባቸው ናቸው። ለምሳሌ የማንበብ ሂደት ተግባራት እነዚህን
ክርታሶች በመጠቀም ቢመለሱ መልካም ነው።

ባለኪስ ሠንጠረዥ (Pocket-Chart )፡- የፖስተር መጠን ያለውና ከሸራ ወይም ከጨርቅ የተዘጋጀ
ባለኪስ ሠንጠረዥ ሲሆን፣ ተማሪዎች እንዲያዩዋቸው ፍላሽ ካርዶችን ሊይዝ የሚችል ነው። ይኼ
ሠንጠረዥ በአንድ ጊዜ በርካታ ፍላሽ ካርዶችን ለማቅረብና ለማሳየት እንዲሁም በማዘዋወር ለመጠቀም
ያመቻል። ዓረፍተነገሮችንም በአዳዲስ ቃላት ለመመሥረትና ስለቃላቱም ፍቺ ለመነጋገር ያስችላል።

ትልልቅ መጻሕፍት፡- እነዚህ፣ መምህራን ድምጽ በማሰማት ሲያነቡ፣ ሁሉም የክፍል ተማሪዎች
ሊያዩዋቸው የሚችሉ በጣም ትላልቅ መጻሕፍት ናቸው። ተማሪዎች ከነዚህ መጻሕፍት ቃላትን፣
ሥዕሎችን፣ ምሥሎችን፣ ሠንጠረዦችን ወዘተ. ሲያነቡ ስለርዕሰጉዳዩ ያላቸውን ግንዛቤ ያዳብራሉ፤
ስለርዕሰጉዳዩም በአዲስና በተለየ መንገድ ለማሰብ ዕድል ይፈጥርላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ በመጽሐፉ
የቀረቡት መረጃዎች የቀረቡባቸውን መንገዶች ለመተንተን ያስችላቸዋል።

ሥዕላዊ መግለጫ (ፖስተር)፣ ለጭብጥና ለርዕሰጉዳይ የሚዘጋጁ ሥዕላዊ መግለጫዎች (ለምሳሌ፣


በሥራቸው አርኣያ ስለሆኑ ሴቶችና በማኅበረሰቡ ውስጥ ስላላቸው ሚና፣ ሰላካባቢ ጥበቃ ዕቅድ፣

x አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


በተውኔት ውስጥ ቀርቦ ስለነበረ ወይም ወደፊት ስለሚቀርብ ክፍል ወዘተ. የሚዘጋጁ) የተማሪዎችን
ፍላጎትና ተሳትፎ ይጨምራሉ። መምህራን እነዚህን ሥዕላዊ መግለጫዎች ርስበርስ ሊለዋወጡ ይችላሉ፤
ተማሪዎችም አዳዲስ ሥዕላዊ መግለጫዎችን በመፍጠር ረገድ ሊሳተፉ ይችላሉ።

ተከታታይ ምዘናና ድጋፍ/ማበልፀግ


• ተከታታይ ምዘና ማለት ተማሪዎች እንዴት እየሠሩ እንደሆነና ትምህርቱን መረዳታቸውንና
ክሂሎችን በሚፈለገው መጠን ማወቃቸውን ለመረዳት በተከታታይ መረጃ የሚሰበሰብበት ሂደት
ነው። ይኼ ምዘና ስለማስተማር ሂደት ወይም ሊከለሱ ስለሚገባቸው ወይም በድጋሚ ማስተማር
ስለሚያስፈልጋቸው ትምህርቶች ውሳኔ ለመስጠት ስለሚያስችል ለመምህራን በጣም ጠቃሚ
ነው። በተጨማሪም መምህራን ተማሪዎች በመንፈቀዓመቱ ውስጥ ከሚጠበቁባቸው ብቃቶች
አንጻር የሚያሳዩትን ዕድገት በሚመለከት ያላቸውን ምልከታና የተከታታተይ ምዘና ወጤቶችን
ለመመዝገብ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።

መምህራን ተማሪዎች እንዴት እየሠሩ እንደሆነ በተከታታይ ምዘና ለመረዳት፣ በመማር ሂደት
ውስጥ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ለመርዳትና ጥሩ ለሚሠሩትም ዕውቀታቸውን ለማበልፀግ
የሚከተሉት ሁለት ዓይነት አጠቃላይ የምዘና ስልቶች (ቴክኒኮች) ጠቃሚዎች ናቸው።

ኢመደበኛ ተከታታይ ምዘና


ይኼ ምዘና የመማር-ማስተማሩን ሂደት የተማሪዎችን መማር እግር በእግር እየተከታተሉ፣ ጕድለት
ካለ ለመሙላትና ድጋፍ ለማድረግ ታልሞ የሚተገበር ምዘና ነው። በዚህ ረገድ ከሚጠቀሱት ዘዴዎች
ቀጥሎ የቀረቡትን መጠቀም ይቻላል።
o ምልከታ፡- መምህራን እንሥራ፣ በተለይ ደግሞ ሥሩ በሚለው የትምህርቱ ሂደት
ወቅት በክፍል ውስጥ መዘዋወርና ተማሪዎቻቸውን መከታተል አለባቸው። በዚህ ጊዜ
መምህራን ተማሪዎቹ በግላቸው፣ ከቢጤያቸው ወይም ከአነስተኛ ቡድን ጋር እንዴት
እየሠሩ እንደሆነና የትኞቹ የተለየና ተጨማሪ ድጋፍ፣ የትኞቹ ደግሞ የተሻለ ለመሥራት
ከአቅማቸው ጋር የሚሄድና የሚገዳደራቸው ተግባር እንደሚፈልጉ ለመለየት ይችላሉ።

o የመውጫ ካርዶች፡- የዕለቱ ትምህርት ከመጠናቀቁ በፊት መምህራን ተማሪዎችን


ጥያቄ ሊጠይቁ ወይም አጭር ተግባር ሊሰጡ ይችላሉ። ለምሳሌ ለቃላት ተመሳሳይ
እንዲሰጡ፣ ከተማሯቸው ቃላት የተወሰኑትን በዓረፍተነገር እንዲጠቀሙ ወይም ለአጭር
አንቀጽ ማጠቃለያ እንዲሰጡ ወዘተ. የመሳሰሉትን መጠየቅ ይቻላል። ተማሪዎቹም
ምላሾቻቸውን በቁራጭ ወረቀት ወይም ካርድ ላይ በመጻፍ ለመምህራቸው ሰጥተው
ይወጣሉ። ከዚያም መምህራኑ ያን በመመልከት ምን ያህሉ ተግባሩን በትክክል መሥራት
እንደቻሉ መገምገም ይችላሉ።

o ተነሺ ቃላት፡- ተማሪዎች በትናንሽ ሰሌዳዎች ወይም ወረቀቶች ላይ መልሶችን ጽፈው፣


መምህራቸው ጥያቄዎችን በግላቸው (ለምሳሌ፣ ጥያቄ መጠየቅ፣ መልስ መመለስ፣
በቃላት ዓረፍተነገር መሥራት) እንዴት እንደመለሱ እንዲያዩላቸው በፊትለፊታቸው
በጠረጴዛቸው (በዴስካቸው) ላይ ያስቀምጣሉ።

መደበኛ ተከታታይ ምዘና


የዚህ ምዘና ዋና ዓላማ ተማሪዎች ትምህርቱን መረዳታቸውንና ክሂሎችን በሚፈለገው መጠን
ማወቃቸውን በየደረጃውና በየምዕራፉ መጨረሻ መለካት ነው። የሚከተሉትን ዘዴዎች ለአብነት

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xi


መጠቀም ይቻላል።
o የክፍል ልምምዶችና የቤትሥራዎች፡- መምህራን፣ ትምህርቱን መረዳታቸውንና ክሂሎች
በተገቢው ሁኔታ መዳበራቸውን ለመረዳት ተማሪዎች በጽሑፍ የመለሷቸውን የክፍልና
የቤትሥራዎች ሰብስበው ይገመግማሉ።

o ሙከራዎችና ፈተናዎች፡- ተማሪዎች አንድን የትምህርት ይዘት ወይም ክሂል


መረዳታቸውን ለማወቅ ሙከራዎችና ፈተናዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ከ5ኛ-8ኛ ባሉት ክፍል
ደረጃዎች የሚሰጡት ሥራዎችና ፈተናዎች በአብዛኛው በጽሑፍ የሚመለሱ ናቸው።
ይሁንና ፈተናዎች በቃል የሚመለሱም ሊሆኑ (ለምሳሌ፣ የአቀላጥፎ ማንበብ ችሎታቸውን
ለመለካት ከአንድ ጽሑፍ የተወሰነውን ድምጽ በማሰማት እንዲያነቡ ወይም የአንብቦ/
የአዳምጦ መረዳት ችሎታቸውን ለማወቅ ጥያቄዎችን በቃላቸው እንዲመልሱ ወይም
ስለአንድ ጉዳይ በቃላቸው እንዲያቀርቡ ማድረግ) ይችላሉ።

ድጋፍ ምን ማለት ነው? ድጋፍ ማለት መምህራን ተማሪዎችን ለማበረታታት የሚፈጸሙት ተግባር
ወይም የሚሰጡት የማበረታቻ ቃል ነው።

አንዱ የተከታታይ ምዘና አስፈላጊነት ተጨማሪ ድጋፍ የሚፈልጉ ተማሪዎችን ለመለየት ነው።
ይኽም በእንሥራና በተለይ በልሥራ ልምምድ ወቅት መምህራን ትምህርቱን ለመገምገምና ችግር
ላለባቸው ተማሪዎች በወቅቱ ድጋፍ ለማድረግ ዕድል ይሰጣቸዋል። አንዳንድ ጊዜም ከክፍል ውጪ
ድጋፍ የሚሹ የተወሰኑ ተማሪዎች ሊያጋጥሙ ይችላሉ።
o ለክፍሉ፣ ለአነስተኛ ቡድን ወይም ተማሪዎች (በግል) ድጋፍ የማድረጊያው አንዱ
መንገድ ወደልሥራ ወይም ወደእንሥራ ተመልሶ ለተማሩት ይዘት ወይም ክሂል
ተጨማሪ ምሳሌዎች እየሰጡ ማለማመድ ነው።

ማበልፀግ ምን ማለት ነው? አንዳንድ ተማሪዎች ፅንሰሃሳብን ቶሎ ሊረዱ ስለሚችሉ ትኩረታቸውን


ለመያዝ የሚገዳደራቸው ነገር ይሻሉ። ማበልፀግ የሚያመለክተው ለእንደነዚህ ያሉ ተማሪዎች ተጨማሪ
መረጃ በማቅረብ ያላቸውን ዕውቀት የሚያሰፋና የሚያዳብር ተግባር መስጠትን ነው። በዚህም ተማሪዎች
በአዲስ መልክ የቀረቡላቸውን መረጃዎች እንዲጠቀሙባቸው በማድረግ ዕውቀታቸውን እንዲያሰፉ
መገዳደር ይቻላል።

በተከታታይ ምዘና ሂደት የቀረበው ተግባር ወይም ክሂል የሚቀላቸውንና ከበድ ያለ ተግባር ወይም
ክሂል የሚያስፈልጋቸውን ተማሪዎች ለይቶ ማወቅ ይቻላል። የነዚህን ተማሪዎች ዕውቀት ማበልፀግ
ካልተቻለ በትምህርቱ ሊሰላቹና ፍላጎት ሊያጡ ወይም የተለየ ባሕሪ ሊያሳዩና ችግር ሊፈጥሩ ይችላሉ።

ለእነዚህ ተማሪዎች የማበልፀጊያ ተግባር የሚሰጠው በሁለት ዓይነት መንገድ ነው፤ አንደኛው ተጨማሪ
የማንበብ ተግባር (ከመጽሐፋቸው ሌላ ተጨማሪ ንባብ እንዲያነቡ) እና ሁለተኛው ተጨማሪ የመጻፍ
ተግባር (በመጽሐፋቸው ውስጥ የሌለ ሌላ የመጻፍ ሥራ) መስጠት ናቸው። ምናልባት በተጨማሪ
የሚነበቡ ጽሑፎች ወይም መጻሕፍት ከሌሉ፣ መምህራን በተማሪዎች መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ ያሉትን
የሚመሥሉ የመጻፍ ተግባራት ሊፈጥሩ ይችላሉ። ከዚያም ላቅ ያለ ችሎታ ያላቸው ተማሪዎች አንዳቸው
የአንዳቸውን ሥራ እንዲያነቡና ግብረመልስ እንዲሰጣጡ፣ አርትኦት እንዲያደርጉ፣ በሥራዎቻቸው
ላይ እንዲወያዩ ወዘተ. ማድረግ ይቻላል። ይኽም ተጨማሪ ንባብ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል። አንዳንድ
ጊዜ መምህራን ተማሪዎችን በማቧደን ችግር ያለባቸው ተማሪዎች ከጎበዞቹ የሚማሩበትንም መንገድ
ሊያመቻቹ ይችላሉ።

xii አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


ለእያንዳንዱ የትምህርት አላባ ምዘና፣ ድጋፍና ማበልፀጊያ ለመስጠት የሚከተሉት ዝርዝሮች ተጨማሪ
አስተያየቶች ይሰጣሉ።

የቃላት ጥናት
ማጣመርና መነጠል
ምዘና
• ሥሩ በሚለው ሂደት ተማሪዎች ከማጣመራቸው በፊት ወይም ከነጣጠሉ በኋላ እያንዳንዱን
ፊደል፣ ቀለም ወይም የቃላቱን አካላት መጥራት መቻላቸውን ማረጋገጥ፣
• ተማሪዎችን እየመረጡ ቃላቱን እያጣመሩና እየነጠሉ እንዲያነቡ ማድረግ፣

ድጋፍ
• ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች በቅድሚያ ቀደም ሲል በሠሯቸው ቀለል ያሉ ቃላት ላይ
ማለማመድ፣ ቀጥሎም አዳዲሶቹን እንዲሞክሩ ማድረግ፣ አሁንም ችግር ያለባቸው ተማሪዎች
ካሉ እንደገና ያስቸገሯቸውን ፊደሎች በጋራ ሆኖ መከለስ።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች የቀረቡትን ቃላት ፊደላት፣ ቀለሞች፣ አካላት በቀላሉ ማጣመርና መነጣጠልና ከቻሉ
በሚያውቋቸው ፊደላት ወይም ቀለሞች የተመሠረቱ በርካታ ቃላት በተጨማሪ መስጠት።

ያልተዘወተሩ/እንግዳ ቃላትን ለመረዳት ስለቅጥያዎች ያለን ዕውቀት መጠቀም


ምዘና
• ሥሩ በሚለው ሂደት ተማሪዎች የቃላቱን መዋቅር አካላትና ሙሉውን ቃል በደብተራቸው ላይ
በትክክል እየጻፉ መሆናቸውን (ለምሳሌ፣ ደብተር-ኦች-ኣቸው) ማረጋገጥ ያስፈልጋል።

• ከዚያም ራሳቸው ተመሳሳይ የቃላት መዋቅር ያላቸውን ቃላት (ለምሳሌ፣ ዋና ቃሉ ልብስ፣


የመድረሻ ቅጥያዎች -ኦች እና -ኣቸው = ልብሶቻቸው ወዘተ.) ሊጨምሩ ይችላሉ።

• ተማሪዎች በግል ወይም በቢጤ ወይም በቡድን ሆነው የሰፋፊ ቃላትን ዋና ቃልና ቅጥያዎችን
እንዲነጣጥሉ መምህራን መጠየቅ ይችላሉ።

• ተማሪዎች እንዲህ ዓይነቱን መለማመጃ ሲሠሩ መምህራን እየተዘዋወሩ ይመለከታሉ።

ድጋፍ
• በተግባር ልምምዱ ወቅት ቀላል ቃላትን እንኳ ሲሠሩ ችግር ያለባቸው ተማሪዎች የተማሯቸውን
በድጋሚ እንዲሠሩና ከዚያ ወደአዳዲሶቹ እንዲሄዱ በማድረግ መደገፍ ይገባል።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች የተሰጧቸውን ቃላት መለየትና በቃላቱ ውስጥ ያሉትን አካላት ፍቺ መረዳት ከቻሉ
ሌሎች ተጨማሪ ቃላትን በመስጠትና እንዲሠሩ በማድረግ የቃላት ዕውቀታቸውን የበለጠ
ማበልፀግ ይቻላል፤ ወይም፣

• ተማሪዎቹ ቃላቱን ተጠቅመው በቃላቸው ወይም በጽሑፍ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ማድረግም


ይቻላል።

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xiii


አንብቦ መረዳት
ምዘና
• ምንባብ ከማንበባቸው በፊት የምንባብን ርዕስ፣ ሥዕል፣ ሠንጠረዥ ተመልክተው እንዲገምቱ
ተማሪዎችን ተራ በተራ መጠየቅ፣

• ተማሪዎችን በምንባብ ላይ የተመሠረቱና አመራማሪ ጥያቄዎችን ተራ በተራ መጠየቅ፣

• ለጽሑፉ ተገቢ የሆኑ የቢጋር ሠንጠረዦችን እንዲሠሩ/እንዲያዳብሩ መጠየቅ፣

• ተማሪዎች በምንባብ ውስጥ ያነበቧቸውን ቊልፍ ቃላት በደብተራቸው ወይም በመውጫ ካርድ
ላይ እንዲዘረዝሩ፣ ከምንባቡ 3 (ቊጥሩ ሊለይ ይችላል) ዋና ሀሳቦችን እንዲለዩ፣ ምንባቡን
በአጭሩ እንዲያሳጥሩ ወይም የጽሑፉን አዘጋጅ ቢያገኙት/ኟት ሊጠይቁት/ቋት የሚችሏቸውን
3 (ቊጥሩ ሊለይ ይችላል) ጥያቄዎች እንዲጽፉ መጠየቅ፣

• ተማሪዎች አንብቦ መረዳታቸውን ለማሳየት ሲጽፉ የሠሩትን ሥራ (የቢጋር ሠንጠረዥ፣ የአንብቦ


መረዳት ጥያቄዎች መልስ፣ ያሳጠሩትን አንቀጽ ወይም ምንባብ ወዘተ.) መሰብሰብና መገምገም፣

መደገፍ
• ተማሪዎች ምንባብ ከማንበባቸው በፊት የመገመት ችግር ካለባቸው ቊልፍ ቃላትን ከርዕሱ
ወይም ከሥዕሉ የተወሰነ ክፍል ለይቶ በመጠቆም መደገፍ፣

• ተማሪዎች በሚያነቡበት ሂደት እንዲገምቱ ለመርዳት በተነበበው ክፍል ምን እንደተፈጸመ


መጠየቅና ወደፊት ስለሚሆነው ነገር መገመት እንዲችሉ በምሳሌ ማሳየት፣

• ምናልባት ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚቸገሩ ካሉ፣

o የቃላትን ጥያቄዎች፣ በተለይ ሙያዊ ስያሜዎችን (ለምሳሌ፣ ገፀባሕርይ፣ መቼት፣ መዋቅር


ወዘተ.) በመከለስ ተማሪዎቹ የተጠየቁት ምን እንደሆነ እንዲረዱ በማድረግ መደገፍ፣

o ጥያቄዎቹን ለመመለስ እንዲረዳቸው የምንባቡን ክፍል ወይም ፍንጮችን እንዲፈልጉ


በማድረግ መደገፍ፣ ተማሪዎቹ ግን የምንባቡን ክፍል ለይተው ማግኘት ካልቻሉ፣ ተገቢ
የሆነውን የምንባብ ክፍል መጠቆም፣

• ተማሪዎች ተገቢ የሆነ ራስን የመከታተያ/የመለኪያ ብልሃት የማይጠቀሙ ከሆነ ድምጽን


በማሰማት እያነበቡ በምሳሌ ማሳየት፣

• ተማሪዎች በቃልም ሆነ በጽሑፍ ምንባብን የማሳጠር ተግባር መሥራት ካልቻሉ፣ አሁንም


በምሳሌ ሠርቶ በማሳየት መደገፍ።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች በምንባብ ላይ በቀጥታ የተመሠረቱ ወይም አመራማሪ የሆኑ ጥያቄዎችን ቀላል
ሆነው ካገኟቸው፣ መልሶቻቸውን እንዲጽፉ ወይም የበለጠ ውስብስብ ወይም ከበድ ያሉና ጥያቄ
የሚያጭሩ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ዕውቀታቸውን ማበልፀግ፣

• ተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን በቀላሉና በቶሎ የጨረሱ እንደሆነ፣ ሌሎች ተማሪዎች
ሊመልሷቸው የሚችሉ በምንባብ ላይ ተመሥርተው የራሳቸውን ጥያቄዎች ከነመልሳቸው
እንዲያወጡ ማድረግ፣ እነዚህም ጥያቄዎች ከምንባቡ ላይ በቀጥታ የሚመለሱ ወይም አመራማሪ
ሊሆኑ ይችላሉ።

xiv አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


• ከምንባቡ ደስ ያሰኛቸውን ወይም የወደዱትን ክፍል አውጥተው እንዲጽፉ ወይም ለክፍሉ
(ለቡድንም ሊሆን ይችላል) እንዲገልጹ፣ ስለምንባቡ ያላቸውን የግል አስተያየት (ጥንካሬ፣
ድክመት፣ ዝርዝር መረጃ ወዘተ.) እንዲሰጡ፣ ወይም ላነበቡት ምንባብ ምላሽ ሊሆን የሚችል
የራሳቸውን ጽሑፍ እንዲጽፉ ተማሪዎችን በመጠየቅ ዕውቀታቸውን ማበልፀግ።

ቃላት
ምዘና
• ተማሪዎች የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት በቃላዊ ተራክቦ ውስጥ መጠቀማቸውንና በትክክል
መጥራታቸውን እየተዘዋወሩ በማየት መገምገም፣

• ተማሪዎች የመሠረቷቸውን ወይም ያሳጠሯቸውን አንቀጾች ሲያቀርቡ በመከታተል በምንባቡ


ውስጥ ያሉትን ቃላት መረዳታቸውን መገምገም፣

• በዕለቱ ወይም በዚያው ሳምንት ተማሪዎች ከተማሯቸው ውስጥ 5 (ቊጥሩ ሊለይ ይችላል)
ቊልፍ ቃላትን ከአጫጭር ብያኔ ጋር እንዲጽፉ መጠየቅ፣ ወይም ቃላቱንና በእያንዳንዱ ቃልም
የመሠረቱትን ዓረፍተነገር እንዲጽፉ መጠየቅ፣

• በዚያ ሳምንት ወይም በምዕራፉ የተማሯቸውን ቃላት ሰፋ ያለ ጽሑፍ ወይም ድርሰት ሲጽፉ
ወይም በንግግር ሲያቀርቡ መጠቀማቸውን በመመልከት መመዘን።

ድጋፍ
• ተማሪዉ/ዋ ቃሉን መረዳት ካልቻለ/ች፣ ለምሳሌ ቃሉ በምንባቡ ውስጥ ላለው ፍቺ የማይስማማ
ፍቺ ከሰጠ/ች፣ ለቃሉ የተሳሳተ ብያኔ ካቀረበ/ች ወይም ቃሉን በንግግርም ሆነ በጽሑፍ በትክክል
ካልተጠቀመ/ች፣ መምህራን ከራሳቸው ተጨማሪ ምሳሌዎችን በመስጠት፣ ቃሉን በተለያዬ
መንገድ በማብራራትና በአዲስ ዓረፍተነገር ውስጥ ተጠቅሞ በማሳየት መደገፍ።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች የቃላት መለማመጃውን በቀላሉ ከሠሩት፣ ተቀራራቢ በሆኑ ሌሎች ውስብስብ ቃላት
ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ ወይም የሚችሉትን ያህል ቃላት ተጠቅመው አንድ ጽሑፍ እንዲጽፉ
በማድረግ ያላቸውን ዕውቀት ማበልፀግ፣

• 4 ወይም 5 አባላት ባሉት ቡድን አደራጅቶ ተማሪዎች በዙር (ለምሳሌ፣ አንድ ተማሪ አንድ
ዓረፍተነገር ከጻፈ/ች በኋላ ሌላኛው/ዋ ቀጣይና ተስማሚ ዓረፍተነገር ቀጥሎ/ላ እንዲጽፍ/
እንድትጽፍና በዚሁ ዓይነት ሌሎቹም እንዲቀጥሉ በማድረግ) ሀሳብ በማዋጣት በጋራ እንዲጽፉ
ማድረግ አንዱ የማበልፀጊያ መንገድ ነው። በመጀመሪያ ወረቀት የያዘው/ችው ተማሪ አንድ
ቃል፣ ሐረግ ወይም ዓረፍተነገር ጽፎ/ፋ በቀኝ በኩል ላለ/ች ሌላ ተማሪ ይሰጣል/ትሰጣለች፤
ሌላኛው/ዋም ተቀብሎ/ላ በተመሳሳይ የራሱን/ሷን ጽፎ/ፋ በማስተላለፍ መምህር አቁሙ እስከሚሉ
(በግምት አንድ ደቂቃ እስከሚሆን) ድረስ ተግባሩ ይቀጥላል። ብዙ ቡድኖች ይኼን ተግባር
የሚሠሩ ከሆነ የትኛው ቡድን ብዙ እንደጻፈ ማየትም ይችላሉ።

የተማሪዎች የራስ ምዘና


• ተማሪዎች የተማሯቸውን ቃላት በደብተራቸው ላይ እየመዘገቡ ሊይዙ ይችላሉ፤ በየሳምንቱ
ወይም በየምዕራፉ የሚያገኟቸውንም አዳዲስ ቃላት እየጨመሩ መሄድ ይችላሉ። ይኼም
አዳዲስ የመሰሏቸውን ቃላት ከጻፉ በኋላ ፍቻቸው ምን ምን ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ፤

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xv


ከተማሯቸውም በኋላ ምን ማለት እንደሆኑ የተረዷቸውን ቃላት በቃላት ሠንጠረዥ ሊዘረዝሯቸው
ይችላሉ።

አዲሱ ቃል (ለእኔ) በእኔ ግምት ፍቺዉ አዎ! ትክክኛ ፍቺዉ ይኼ ነው።

መጻፍ
ድርሰት መጻፍ
ምዘና
• ተማሪዎች በሚጽፉበት ርዕሰጉዳይ ላይ ማተኮራቸውን ለማረጋገጥና ለጽሑፋቸው የሚሆን
ሀሳብ ለማፍለቅ አጠቃላይ ውይይት በሚያደርጉበት ጊዜ መምህራን እየተዘዋወሩ በመመልክት
መመዘን ይችላሉ።

• ጽሑፋቸውን ከመጀመራቸው በፊት ሀሳብ ለማፍለቅና ለማደራጀት የቢጋር ሠንጠረዦችን


በአግባቡ እየተጠቀሙ መሆናቸውን መከታተል ይገባል።

• ተማሪዎች ጽፈው ያቀረቡት ሥራ ሙሉ መሆኑን፣ አደረጃጀቱን (መጀመሪያ፣ መካከል፣


መጨረሻ፣ የዋናና ዝርዝር አቀራብ)፣ ግጥምጥምነቱንና ተገቢነቱን በመገምገም ችሎታቸውን
ማወቅ ይቻላል።

• በተማሪዎች ሥራ ላይ የጽሑፍ አላባውያንን ለመገምገም የጽሑፍ መከታተያ ዝርዝሩን (ከታች


የቀረበውን ተመልከቱ) ከተማሪዎች ጋር በመተባበር መጠቀም ወይም ተማሪዎች ይኽን በጥንድ
በጥንድ ሆነው እንዲሠሩት በማድረግ መመዘን ይቻላል።

• በተማሪዎች ሥራ ላይ የተሰጠውን ግምገማ ለክፍሉ ተማሪዎች እያዟዟሩ ማሳየት፣ አንድ ደረጃ


እንደጨረሱ ከተማሪዎች ጋር በግል መወያየት፣ ለአንዱ የቤትሥራ የግማሹን ክፍል፣ በሌላ
የቤትሥራ ደግሞ የሌላውን ግማሽ ክፍል ሥራ አስተያየት ማቅረብ ይቻላል።

xvi አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


የጽሑፍ መከታተያ ቅጽ
ድርሰት:-
በተሰጠው የቤትሥራ መሠረት መጻፍ፣

ዋናውን ሀሳብ በግልጽ ማቅረብ፣

ዋናውን ሀሳብ ለመደገፍ በቂ ዝርዝር መጠቀም፣

የራስን ሀሳብ ተጠየቃዊ በሆነ መንገድ አንዱ ሀሳብ ሌላውን እየተከተለ እንዲዋቀር ማድረግ፣

ስልት/አንባቢ:-
ለአንባቢህ/ሽ (ግለሰብም ሆነ ቡድን) ጻፍ/ፊ።

ሀሳብህ/ሽን በተሻለ የሚገልጹልህን/ሽን ቃላት ተጠቀም/ሚ።

አንባቢዎችህ/ሽ ሊረዷቸው የሚችሏቸው ዓረፍተነገሮች ተጠቀም/ሚ።

ዓረፍተነገር ምሥረታ:-
ሙሉ ዓረፍተነገሮችን ተጠቀም/ሚ።

አጠቃቀም:-
ተገቢ የሆነ የባለቤት-ተሳቢ-ግስ ስምምነት፣ የግስ ጊዜ፣ የቃላት ፍቺ በዓረፍተነገር ውስጥ
መጠቀም፣

የአጻጻፍ ሥርዓት:-
ተገቢ ሥርዓተነጥቦችን በመጠቀም መጻፍ፣

በቋንቋው የአንቀጽ አጻጻፍ ሥርዓት መሠረት መጻፍ፣

ፍደላ (የፈደል አሰዳደር):-


ተገቢ የሆነ የፊደል ሥርዓት ተክትሎ መጻፍ

ድጋፍ
• በመጻፍ ሂደት ለመጻፍ የሚቸገሩ (ቅድመመጻፍ፣ ማርቀቅ፣ መጻፍ፣ ወይም መከለስ፣ ተገቢ
መግቢያና በቂ ዝርዝር አለማቅረብ) ተማሪዎች ሲያጋጥሙ፣ መምህራን ለሁሉም ክፍል እነዚህን
አላባውያን በምሳሌ ማሳየትና ወደተማሪው/ዋ ወይም ወደቡድኑ በመሄድ ሠርቶ ማሳየትና
መወያየት ይጠበቅባቸዋል።

• በቂ ምሳሌ፣ ደጋፊና ውጤታማ ግብረመልስ በተማሪዎች ጽሑፍ ላይ መስጠት፣ የታተሙ


ቅንጫቢዎችን (በቃል የቀረቡ የጽሑፍ ክፍሎችን ጨምሮ) ማቅረብና አንዳቸው ላንዳቸው

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xvii


ግብረመልስ እንዲሰጣጡ ማድረግ፣

• በመከታተያ ዝርዝሩ መሠረት ሥራቸውን መከታተል፣

ማበልፀግ
• መምህራን ከተማሪዎቹ ጋር የገመገሟቸውን የተማሪዎች ሥራዎች፣ ተማሪዎች ርስበርስ
እንዲገማገሙ መጠየቅ፣ ሥራዎቻቸውን እንዲያሻሽሉም (በሙሉነት፣ በአደረጃጀት፣ በመግቢያና
በመጨረሻ፣ እንዲሁም በሀሳብ አስተዳደግና በዝርዝር አቀራረብ) ግብረመልስና ሀሳብ መስጠት፣

• ተማሪዎች ከላይ ለተዘረዘሩት ባህርያት የራሳቸውን ሥራ እንዴት መገምገም እንደሚችሉና


ለሌሎች ተማሪዎች ተገቢ ግብረመልስና ድጋፍ መስጠት እንዳለባቸው ለተማሪዎች ማሳየት፣

• ተማሪዎች በሚጽፉት ሥራ ከተሰላቹ፣ ተመሳሳይ ጭብጥ ስላላቸው ከአንድ በላይ ጽሑፎች


(ለምሳሌ በአንድ ምዕራፍ ስላሉት 3-4 ምንባቦች) እንዲጽፉ፣ ሀሳብና ቊልፍ ጭብጦችን ለይተው
እንዲያደራጁ ማድረግ ይጠቅማል።

ያጻጻፍ ሥርዓት፡- (ፍደላ፣ ሥርዓተነጥብ፣ ሰዋስዋዊ ትክክለኝነት፣ የአንቀጽ መክፈያ ምልክት፣ ትክክለኛ
ቃልና አጠቃቀም)

ምዘና
• ተማሪዎች በትክክል የሚጽፏቸውን ቃላት የያዘ ዝርዝር በመስጠት ወይም በቃል በማስጻፍ
የፍደላ ፈተና መምህራን ይስጡ። ታላሚዎቹ ቃላት በ1ኛ፣ በ2ኛና በ3ኛ ሳምንቶች ይሰጣሉ፤
በ3ኛው ሳምንት ምዘናው ይካሄዳል።

• ተማሪዎች ለፍደላ፣ ለሥርዓተነጥብ፣ ለሰዋስዋዊ ትክክለኛነት፣ ለአንቀጽ አቀማመጥ፣ ለትክክለኛ


ቃል ምርጫና ለአጠቃቀም የራሳቸውን ወይም የጓደኞቻቸውን ሥራ ሲያርሙ መምህራን
እየተዘዋወሩ ይመለከታሉ።

• ተማሪዎች በመውጫ ካርድ ላይም ሆነ በደብተራቸው አጫጭር የቤትሥራዎች ሲሠሩ፣


ለተግባሩ አስፈላጊ ከሆነ ተገቢ ሥርዓተነጥብና ፍደላ እንዲጠቀሙ መምህራን ያሳስቧቸው፤
ሥራዎቻቸውንም ይገምግሙ።

• ተማሪዎችን ድርሰት ወይም ሰፊ ጽሑፍ ሲጽፉ፣ ተገቢ ያጻጻፍ ሥርዓት መከተላቸውን መምህራን
ይገምግሙ።

• የጽሑፍ መከታተያ ዝርዝሩን በመያዝ ተማሪዎች የተወሰነ ያጻጻፍ ሥርዓትን መሠረት አድርገው
እንዲያርሙ መምህራን ይደግፏቸው።

• ተማሪዎች መምህራቸው የሚነገሯቸውን የተወሰነ ያጻጻፍ ሥርዓት ርስበርሳቸው እንዲተራረሙ


ካደረጉ በኋላ ትክክል ለመሆናቸው ያርሙላቸው።

ድጋፍ
• የተወሰኑ ተማሪዎች የፍደላ ችግር ካለባቸው መምህራን መሠረታዊውን የፊደል አጠቃቀም
ሥርዓት ይከልሱላቸው፤ የተወሰኑ መለማመጃዎችም ይስጧቸው።

• ተማሪዎች በተወሰኑ ያጻጻፍ ሥርዓቶች ላይ ችግር ካለባቸው፣ መምህራን በእነሱ ላይ በማተኮር


ያሳዩዋቸው።

xviii አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


• ተማሪዎች በተወሰኑ ያጻጻፍ ሥርዓቶች ላይ ችግር ካለባቸው፣ በእነዚህ ያጻጻፍ ሥርዓቶች
መሠረት ተማሪዎች ሲጽፉ፣ ክለሳና አርትኦት ሲያደርጉ ትኵረት ሰጥተው መጠቀማቸውን
መምህራን ይከታተሏቸው። ባንድ ክፍለጊዜም ከሁለት በማይበልጡ ያጻጻፍ ሥርዓቶች ላይ
ብቻ እንዲያተኩሩ ይጠይቋቸው።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች ታላሚዎቹን ቃላት በቀላሉ ከፈደሉ፣ መምህራን ተመሳሳይ ግን ከበድ ያሉ ተጨማሪ
ቃላትን እንዲፈድሉ ይስጧቸው።

• ተማሪዎች መምህራን የሚነግሯቸውን የተወሰኑ ያጻጻፍ ሥርዓቶች በተመለከተ የራሳቸውንና


የሌሎችን ሥራ ርስበርስ እንዲገመግሙ ያድርጉ። በዚህ መሠረት የራሳቸውን ያስተካክሉ፣
ለሌሎችም እንዲያስተካክሉ ያድርጉ።

• መምህራን ከተማሪዎች ጋር በሚነበቡ ጽሑፎች ውስጥ ያሉትን ያጻጻፍ ሥርዓቶች ይገምግሙ፤

አቀላጥፎ ማንበብ (ፍጥነት፣ ትክክለኛነት፣ አገላለጽ)


አቀላጥፎ ማንበብ ቃላትን በትክክል የማንበብ ፍጥነትንና ጽሑፍን በተገቢ አገላለጽ ማንበብን
ያካትታል። አንዳንድ ተመራማሪዎች አቀላጥፎ ማንበብን ጽሑፍን በፍጥነት፣ በቀላሉ፣ ያለችግር፣
ሳይንገዳገዱ (ፊደላትን ሳይገድፉ) ማንበብ መቻል እንደሆነ ይገልጻሉ (ሜየር እና ፌልተን 1999)።
ተማሪዎች አቀላጥፈው አነበቡ የሚባለው በፍጥነት ሳይቸገሩ፣ ፊደላትን ሳይገድፉ ማንበብ ሲችሉ ነው።
ኢመደበኛ ምዘና
• ተማሪዎች የተለያዩ ጽሑፎችን (ለሳምንቱ የተመደበውን ምንባብ ወይም ከምዕራፉ ምንባቦች
አንዱን ወይም መምህራን መርጠው የሚያመጧቸውን ወይም ተማሪዎች ራሳቸው ወይም
ጓደኞቻቸው ወደክፍል ያመጧቸውን ተራኪና መረጃ ሰጪ ጽሑፎችን፣ ንግግሮችን፣ ግጥሞችን፣
ተውኔቶችን ጨምሮ) በግል፣ ለጓደኛ ወይም ለክፍሉ ድምጽ እያሰሙ ሲያነቡ፣ መምህራን
ተማሪዎች አቀላጥፈው በተገቢ ፍጥነት፣ ትክክለኛነትና አገላለጽ ማንበባቸውን በማዳመጥ
ይከታተላሉ።

• መምህራን ተማሪዎች በሚያነቡበት ጊዜ ማስታወሻ በመያዝ የተማሪዎችን የማንበብ ሂደት


ዕድገት መከታተልና የትኞቹ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ለይተው ይረዳሉ።

መደበኛ ምዘና
የተማሪዎችን ድምጽ እያሰሙ አቀላጥፎ የማንበብ ዕድገት ሥርዓት ባለው መንገድ ለመረዳት እያንዳንዱን/
ዷን ተማሪ በግል መመዘን ይገባል። ይኼንንም ለማድረግ በእያንዳንዱ ሳምንት የሚመዘኑ የተወሰኑ
ተማሪዎችን መምረጥ ይጠቅማል። መምህራን ቀደም ብለው ያላነበቡትን አጠር ያለ ምንባብ ሰጥተው
ድምጽ በማሰማት እንዲያነቡ ያድርጉ። ይኽ በተወሰኑ አነስተኛ ቡድኖች ወይም ተማሪዎች ከ3-4
የሚሆኑ ዓረፍተነገሮች በተራ እንዲያነቡ ወይም ሌሎቹ ተማሪዎች የተሰጣቸውን ሌላ ሥራ ሲሠሩ
የተወሰኑ ተማሪዎች በግል ለመምህራቸው ድምጽ በማሰማት እንዲያነቡ በማድረግ ሊካሄድ ይችላል።
ምንባቡም ገና ክፍሉ ያላነበበው ግን በዚያው ሳምንት የሚነበብ ሊሆን ይችላል። ተማሪዎች ድምጽ
እያሰሙ አቀላጥፈው ማንበብ መቻላቸውን ለማረጋገጥ በሚከተሉት ዘዴዎች ሊጠቀሙ ይችላሉ፤
ሀ. ፍጥነትና ትክክለኛነት፣ በተናጠል ተማሪዎች 1 ደቂቃ ለማንበብ ይወሰንላቸው፤ ከዚያ በአንድ
ደቂቃ ውስጥ በትክክል ያነበቧቸውን ቃላት ያስሉ።

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xix


ለ. አገላለጽ፣ ተማሪዎች በሚያነቡበት ጊዜ ተገቢ በሆነ አገላለጽ (በተገቢ የድምጽ ቅላፄና አፅንኦት)
ማንበባቸውን መምህራን ያረጋግጡ።

ከ5ኛ-8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች አቀላጥፈው የሚያነቡበት መርሕ ቀጥሎ በሠንጠረዥ ቀርቧል።


ምናልባት አንዳንድ ተማሪዎች 5ኛ ወይም 6ኛ ክፍል ሆነው ከተወሰነው በተሻለ ሊያነቡ ይችላሉ።

ክፍል መግለጫ

5 • በክፍል ደረጃው ምንባብ ውስጥ ያሉትን ቃላት ቢያንስ 90% በትክክል ማንበብ፣
• በቃላቱ ውስጥ የሚገኙትን ፊደሎች በትክክል መጥራት መቻል፣
• ቃላትንና ሐረጋትን መልሶ ያለችግር ለማንበብ መቻል፣
• በምንባቡ ውስጥ ያሉትን ሥርዓተነጥቦች በመከተል በተገቢ አገላለጽና የድምፅ ቅላፄ
ማንበብ፣
6 • በክፍል ደረጃው ምንባብ ውስጥ ያሉትን ቃላት ቢያንስ 90% በትክክል ማንበብ፣
• ቃላትንና ሐረጋትን መልሶ ያለችግር ለማንበብ መቻል፣
• በምንባቡ ውስጥ ያሉትን ሥርዓተነጥቦች በመከተል በተገቢ አገላለጽና የድምፅ ቅላፄ
ማንበብ፣
• ከምንባቡ ዓይነትና ፍቺ ጋር የሚስማማ አገላለጽ ተጠቅሞ ማንበብ (የተውኔት ንባቦችን
ጨምሮ)
7 • በክፍል ደረጃው ምንባብ ውስጥ ያሉትን ቃላት ቢያንስ 90% በትክክል ማንበብ፣
• ቃላትንና ሐረጋትን መልሶ ያለችግር ለማንበብ መቻል፣
• በምንባቡ ውስጥ ያሉትን ሥርዓተነጥቦች በመከተል በተገቢ አገላለጽና የድምፅ ቅላፄ
ማንበብ፣
• ከምንባቡ ዓይነትና ፍቺ ጋር የሚስማማ አገላለጽ ተጠቅሞ ማለትም ግጥምን፣ ምልልስን፣
ገፀባህርያትንና ሁኔታን የሚያሳዩ የድምጽ ለውጦችን ተረድቶ ማንበብ፣
8 • በክፍል ደረጃው ምንባብ ውስጥ ያሉትን ቃላት ቢያንስ 90% በትክክል ማንበብ፣
• ቃላትንና ሐረጋትን መልሶ ያለችግር ለማንበብ መቻል፣
• በምንባቡ ውስጥ ያሉትን ሥርዓተነጥቦች በመከተል በተገቢ አገላለጽና የድምፅ ቅላፄ
ማንበብ፣
• ለጽሑፉ ዓይነትና ፍቺ የሚስማማ ሐረጋዊ አገላለጽን መጠቀምማለትም ግጥምን፣
ምልልስን፣ ገፀባህርያትንና ሁኔታን የሚያሳዩ የድምጽ ለውጦች በመረዳት፣ ተደራሲን
ለማግባባት የሚዘጋጁ ንግግሮችን፣ ቃለመጠይቆችን፣ ተውኔታዊ ጽሑፎችን ማንበብ፣
ድጋፍ
• መምህራን ከማንበብ ጋር የተያያዘ ፊደሎችን የመጥራትና ሐረጋትን የማንበብ ችግር ያለባቸውን
ተማሪዎች ለይቶ በመረዳት በቅርብ እየተከታተሉ ፊደላቱንና ቃላቱን እየለዩ በማንበብ
ይርዷቸው፤ አንብበውም ያሳዩዋቸው፤ ከነሱም ቀጥለው ተማሪዎቹ እንዲያነቡ ያድርጉ። ከዚያም
ቃላቱንና ሐረጋቱን መልሰው ያንብቡ። ለተማሪዎቹ ከበድ ያሉ ቃላት ወይም ሐረጋት ካሉ
ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል። ከተቻለም ተመሳሳይ መዋቅር ያላቸውን ቃላትና ሐረጋት አዘጋጅቶ
በማንበብ እንዲለማመዱበት ማድረግ ይጠቅማል።

xx አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


• በተገቢ አገላለጽ ለማንበብ የሚቸገሩ ተማሪዎች ካሉ ዓረፍተነገሮቹን በመምረጥ እያነበቡ
ማሳየትና ተማሪዎቹ ተከትለው እንዲያነቡ ማድረግ ስፈልጋል።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች በሚጠበቅባቸው መሠረት አቀላጥፈው ካነበቡ፣ የበለጠ ከፍ ያለ ጽሑፍ (ካለ)
እንዲያነቡ መምህራን ያበረታቷቸው። መምህራን እነዚህ ተማሪዎች የማንበብ ችግር ያለባቸውን
ሌሎች ተማሪዎች ከማገዝ አኳያ አብረው እንዲያነቡና እንዲረዱ ያድርጉ። ይኼን በሚያደርጉበት
ጊዜ ድጋፍ ያስፈልጋቸው ይሆናልና መምህራን ይርዷቸው።

• የተወሰኑ ተማሪዎች የተለያዩ የጽሑፍ ዓይነቶችን (ለምሳሌ፣ ግጥሞች፣ በታሪክ ውስጥ ያሉ


ምልልሶች፣ የተውኔት ቅንጫቢ…) በተገቢ አገላለጽ ካነበቡ፣ መምህራን ይኼን ከጓደኞቻቸው
ጋር ወይም በቡድን በክፍል ተማሪዎች ፊት ወይም በትምህርትቤት ማኅበረሰብ ስብሰባ
ላይ እንዲያነቡ ዕድሉን ያመቻቹላቸው። ለወላጆቻቸውም ድምጽ በማሰማት እንዲያነቡ
ያበረታቷቸው። መምህራን የተሻለ ያነበቡት ተማሪዎች የማንበብ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች
ከማገዝ አኳያ አብረው እንዲያነቡና እንዲረዳዱ ያድርጉ። ይኼን በሚያደርጉበት ጊዜ ድጋፍ
ያስፈልጋቸው ይሆናልና መምህራን ይርዷቸው።

ቃላዊ ክሂሎች
ማዳመጥ
ምዘና
• ተማሪዎችን ባዳመጡት ምንባብ መሠረት ከምንባብ የወጡና አመራማሪ ጥያቄዎችን ተራበተራ
መጠየቅ፣

• ተማሪዎች ምንባቡን መረዳቸውን ለማሳየት ለጽሑፉ የሚስማማ የቢጋር ሠንጠረዥ እንዲያዘጋጁ


ማድረግ፣

• ተማሪዎች በደብተራቸው ወይም በመውጫ ካርድ ቊልፍ ቃላትን እንዲዘረዝሩ ማድረግ፣

• ተማሪዎች ከምንባብ ያዳመጧቸውን ቊልፍ ቃላት በደብተራቸው ወይም በመውጫ ካርድ ላይ


እንዲዘረዝሩ፣ ከማዳመጥ ምንባቡ 3 (ቊጥሩ ሊለይ ይችላል) ዋና ሀሳቦችን እንዲለዩ፣ የማዳመጥ
ምንባቡን በአጭሩ እንዲያሳጥሩ ወይም የጽሑፉን አዘጋጅ ቢያገኙት/ኟት ሊጠይቁት/ቋት
የሚችሉትን 3 (ቊጥሩ ሊለይ ይችላል) ጥያቄዎች እንዲጽፉ መጠየቅ፣

• ተማሪዎች በደብተራቸው ወይም በመውጫ ክርታስ (ካርድ) ላይ ያልተረዷቸውን ቃላት ወይም


ነጥቦች እንዲጽፉ ማድረግ፣

• ተማሪዎች አዳምጦ መረዳቸውን ለማሳየት ከጻፉ በኋላ የሠሩትን (የቢጋር ሠንጠረዥ፣ የአንብቦ
መረዳት ጥያቄዎች መልስ፣ ያሳጠሩትን አንቀጽ ወይም ምንባብ ወዘተ.) መሰብሰብና መገምገም።

መደገፍ
• ተማሪዎች ምንባብ ከማዳመጣቸው በፊት የመገመት ችግር ካለባቸው ቊልፍ ቃላትን ከርዕሱ
ወይም ከሥዕሉ የተወሰነ ክፍል ለይቶ በመጠቆም መደገፍ፣

• ተማሪዎችን በማዳመጥ ሂደት እንዲገምቱ ለመርዳት ባዳመጡት ክፍል ምን እንደተፈጸመ


መጠየቅና ወደፊት ስለሚሆነው ነገር መገመት እንዲችሉ በምሳሌ ማሳየት፣

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xxi


• ምናልባት ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚቸገሩ ካሉ፣

o የቃላት ጥያቄዎችን፣ በተለይ ሙያዊ ስያሜዎችን (ለምሳሌ፣ ገፀባሕርይ፣ መቼት፣ መዋቅር


ወዘተ.) በመከለስና ተማሪዎቹ የተጠየቁት ምን እንደሆነ እንዲረዱ በማድረግ መደገፍ፣

o ጥያቄዎቹን ለመመለስ እንዲረዳቸው የምንባቡን ክፍል ወይም ፍንጮችን እንዲፈልጉ


በማድረግ መደገፍ ይጠቅማል። ተማሪዎቹ ግን የምንባቡን ክፍል ለይተው ማግኘት
ካልቻሉ፣ ተገቢ የሆነውን የምንባብ ክፍል መጠቆም፣

• ተማሪዎች በቃልም ሆነ በጽሑፍ ምንባብን የማሳጠር ተግባር መሥራት ካልቻሉ፣ አሁንም


መምህራን አርኣያ ሆነው በምሳሌ በማሳየት መደገፍ።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች በማዳመጥ ምንባብ ላይ በቀጥታ የተመሠረቱ ወይም አመራማሪ ጥያቄዎችን ቀላል
ሆነው ካገኟቸው፣ መልሶቻቸውን እንዲጽፉ ወይም የበለጠ ወሰብሰብ ወይም ከበድ ያሉና
ተጨማሪ ጥያቄ የሚያጭሩ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ዕውቀታቸውን ማበልፀግ ይቻላል።

• ተማሪዎች የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎችን በፍጥነትና በቀላሉ መመለስ ከቻሉ፣

o ሌሎች ተማሪዎች የሚመልሷቸው ስለምንባቡ የራሳቸውን ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸው


እንዲያዘጋጁ መጠየቅ፣ ይኼ ከምንባቡ በቀጥታ የሚመለሱ ወይም አመራማሪ ጥያቄዎችን
ሊያካትት ይችላል።

o ከማዳመጥ ምንባቡ ደስ ያሰኛቸውን ክፍል ወይም በማዳመጥ ምንባቡ ላይ ያላቸውን የግል


አስተያየት (ጥንካሬውን፣ ድክመቱን፣ የያዘውን መረጃና ዝርዝሮች) ወይም ላዳመጡት
ምንባብ ምላሽ የሚሆን ጽሑፍ ጽፈው ለክፍሉ (ለአነስተኛ ቡድንም ሊሆን ይችላል)
እንዲናገሩ ማድረግ፣

መናገር
ምዘና
• ምንባቡን ካዳመጡ በኋላ በተለያዩ የመናገር ተግባራት ላይ ሲሳተፉ ማዳመጥ፣

• ተማሪዎች በቃል አቅርቦት ዝግጅት፣ በክርክር ወይም በውይይት በሚሳተፉበት ጊዜ ማዳመጥ፣


መምህራን እያዳመጡ ሳሉም፣ ተማሪዎቹ የሚሳተፉባቸውን ተግባራት መረዳታቸውን፣ የተሰጣቸውን
መመሪያ መከተላቸውንና መፈጸማቸውን፣ የሚሠሩባቸውን የጽሑፍ ዓይነቶች መረዳታቸውን
መከታተል ይጠበቅባቸዋል።

ድጋፍ
• የተወሰኑ ተማሪዎች ሀሳባቸውን በቃላቸው በተገቢ ሁኔታ አደራጅተው የማቅረብ ችግር ካለባቸው፣
በመጀመሪያ ጥያቄዎችን እንዲጠይቁና እንዲመልሱ፣ ከዚያም ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ
በቡድን ውስጥ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እንዲሠሩ ማድረግ፤ በሚመቻቸው ቦታ ከሚደግፏቸው
ጓደኞቻቸው ጋር ሆነው እንዲያቀርቡና እንዲከውኑ ዕድል መሥጠት።

ማበልፀግ
• የተወሰኑ ተማሪዎች በቀላሉ ሀሳባቸውን አዘጋጅተው የሚያቀርቡ ከሆነ፣ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው
ተማሪዎች ጋር ሆነው እንዲሠሩ ማድረግ፣ ይኼን ሲያደርጉ ድጋፍ ያስፈልጋቸው ይሆናልና

xxii አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


መምህራን ይርዷቸው።

ሰዋስው
ምዘና
• በምዕራፉ ሥር በተማሯቸው የሰዋስው ትምህርቶች ላይ መልመጃዎች ሲሠሩ እየተዘዋወሩ
ማየትና ማዳመጥ፣

• እነዚህን ሰዋስዋዊ ዕውቀቶች ተማሪዎች በንግግራቸውና በጽሑፋቸው ውስጥ እየተጠቀሙባቸው


መሆናቸውን ማረጋገጥ፣

• ተማሪዎች በጻፏቸው ድርሰቶች ውስጥ እነዚህ ሰዋስዋዊ ሕግጋት መጠቀማቸውን ማረጋገጥ፣

• በመምህራቸው ተሰጥቷቸው ለተወሰኑ ሰዋስዋዊ ትምህርቶች የሠሯቸውን ሥራዎች ርስበርስ


እንዲተራረሙ ማድረግና ስለትክክለኛነቱም ግብረመልስ መስጠት፣

ድጋፍ
• የተወሰኑ ተማሪዎች የተማሯቸውን ወይም እየተማሯቸው ያሉትን ሰዋስዋዊ ሕግጋት
ለመጠቀም ችግር ካለባቸው መምህራን ይከልሱላቸው፤ ሕግጋቱንም የሚለማመዱባቸው ቃላትና
ዓረፍተነገሮች ይስጧቸው።

• አስፋለጊ ሆኖ ከተገኘም በሚያነቧቸውና በሚያዳምጧቸው ምንባቦች ውስጥ ሕግጋቱ ሲያጋጥሙ


ለይተው በማመልከትና እንዲጽፏቸው በማድረግ ትኵረት ይስጡ።

• ተገቢ ከሆነ እነዚህን የሰዋስው ሕግጋት ተማሪዎች ጽሑፍ ሲጽፉ፣ ሲከልሱና ሲያርሙ (አርትኦት
ሲያደርጉ) እንዲጠቀሙባቸውና በአንድ ጊዜ በሁለት ሰዋስዋዊ ሕግጋት ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ
ማድረግ ጠቃሚ ነው።

ማበልፀግ
• ተማሪዎች ሰዋስዋዊ ሕግጋቱን በቀላሉ የሚማሯቸውና የሚጠቀሙባቸው ከሆነ፣ ተጨማሪ ከበድ
ያሉ ዓረፍተነገሮችን እንዲሠሩ መስጠትና በአንቀጽ ውስጥ እንዲጠቀሙባቸው ማድረግ፣

• የተሰጧቸውን ሰዋስዋዊ ሕግጋት በሚመለከት የሠሯቸውን የራሳቸውን ወይም የሌሎችን


ሥራዎች ርስበርስ እንዲተራረሙና ግብረመልስ እንዲሰጣጡ ማድረግ፣

ሥርዓተፆታና አካቶ ትምህርት

ሥርዓተፆታን ከግምት ውስጥ ያስገባ ማስተማርና መማር


መምህራን ወንድና ሴት ተማሪዎች እኩል የሚሳተፉበትና የሚጠቀሙበት የመማር ከባቢ መፍጠር
አለባቸው። ስለሥርዓተፆታ በቂ ግንዛቤ የሌላቸው መምህራን በክፍል ውስጥ አዘውትረው የሚጠሩት፣
ከባድ ጥያቄዎችን የሚጠይቁት፣ ለቡድን መሪነት የሚመድቡት ወንድ ተማሪዎችን ብቻ ነው። እንዲህ
ዓይነቱ ወዳንድ ፆታ ያደላ አቀራረብ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ፣ ውጤት፣ የወደፊት ችሎታና
ተስፋ በእጅጉ ይጎዳል።

ስለሆነም የሁለቱንም፣ የሴቶችንና የወንዶችን ተማሪዎች የትምህርት ውጤት ለማሳደግና የሥርዓተፆታ


እኩልነት የሰፈነበት ሥነትምህርት በክፍል ወስጥ ለመጠቀም ይችሉ ዘንድ መምህራን ራሳቸው መማር

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xxiii


አለባቸው። ከግምት ውስጥ ሊገቡ ከሚገባቸውና ማስተማርንና መማርን የሥርዓተፆታ እኩልነት
የሚንፀባረቅባቸው ለማድረግ ከሚጠቅሙ ጉዳዮች መካከል የሚከተሉት ይገኙባቸዋል፤

• የማስተማሪያና የመማሪያ መሣሪያዎች፡- መምህራን የትምህርት መሣሪያዎችን ከሥርዓተፆታ


እኩልነት አንፃር የወንድና የሴት ገፀባሕርያትን ውክልናና ሥዕሎችን መገምገም አለባቸው።
በአዳዲሶቹ የመማሪያ መጻሕፍት በምንባቦች ውስጥ በሚኖሩ የወንድና የሴት ገፀባህርያት
ውክልናና በሥዕሎች ረገድ የሥርዓተፆታ ሚዛናዊነት እንዲኖራቸው ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በጽሑፎችና በሥዕሎች ውስጥ ልጃገረዶች/ሴቶች ወንዶች ልጆች/ወንዶች
ጐልማሶች በተመጣጠነ ሁኔታ እንዲወከሉ ተደርጓል። በቋንቋ አጠቃቀም ረገድም እንዲሁ
የሥርዓተፆታ ወገናዊነት ሳይኖር፣ ሁለቱንም ፆታዎች በእኩልነት በሚያማክል አገላለጽ
ለመጠቀም ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። ለዚህም ሲባል ገፀባህርያቱ በቤት ውስጥም ሆነ በአደባባይ
በሚኖራቸው የተግባር ተሳትፎ ሚዛናዊነት እንዲኖራቸው ከመደረጉም በላይ ሥርዓተፆታ
ነክ የሆኑ ጭብጦችና ርዕሰጉዳዮች፣ ለምሳሌ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ ሴቶችን ማጐልበት፣
ሥርዓተፆታና ትምህርት ወዘተ. የሚሉ ተካተውበታል። ይሁንእንጂ፣ ምናልባት በስህተት
የተዘለለና የነበረው የሥርዓተፆታ አድሎ የሚንጸባረቅበት ጽሑፍ ካጋጠመ፣ መምህራን
አስተካክለው ያለውን ክፍተት እንዲሞሉ ይጠበቃል።

• የቋንቋ አጠቃቀም፡- መምህራን በክፍል ውስጥ በቋንቋ አጠቃቀማቸውም ሆነ በሌላ የቀደመውን


የተዛባ የሥርዓተፆታ አገላለጽ እንዳይጠቀሙ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ምሳሌዎችና
መመሪያዎች ሲሰጡም በተቻለ መጠን ሁለቱንም ፆታ የሚያማክሉ ተውላጣተስሞችን መጠቀም
ይኖርባቸዋል። ቋንቋዊ ያልሆነውንም የሰውነት ቋንቋ በሚጠቀሙበት ጊዜም የዚያኑ ያህል
ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። ሁሉንም ተማሪዎች በማበረታት ሴት ተማሪዎች በራስ የመተማመን
መንፈስ እንዲያድርባቸው ማድረግም እንዲሁ ትኵረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው።

• የክፍል ውስጥ አደረጃጀት፡- የክፍል ውስጥ የመቀመጫ አቀማመጥ ሥርዓተፆታን ከግምት


ውስጥ ያስገባ መሆን አለበት፤ ለምሳሌ፣ የሴት ተማሪዎች ወደኋላ ባሉት መቀመጫዎች መቀመጥ
ለክፍል ውስጥ ተሳትፏቸው ችግር ይፈጥራል። ስለሆነም መምህራን በቡድን የተከፋፈለ
አቀማማጥ እንዲኖር ወይም የተለየ መንገድ ፈልገው ሁሉም ተማሪዎች እንዲሳተፉ ለማድረግ
የተሻለ ሥርዓተፆታን ያማከለ አቀማመጥ መፍጠር ይኖርባቸዋል።

• የክፍል ውስጥ መስተጋብር፡- በክፍል መስተጋብር ጊዜ መምህራን ለሁሉም ሴትና ወንድ


ተማሪዎች እኩል ዕድል መስጠታቸውን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ በክፍል ውስጥ ስም
በሚጠሩበት ጊዜ በተመሳሳይ መጠን ሁለቱንም ፆታዎች እኩል በመጥራት ማሳተፍ ይገባል።
በማበረታቻም ሆነ በግብረመልስ አሰጣጥ ሁለቱም ፆታዎች ተገቢ ትኵረት ማግኘታቸውንም
በማረጋገጥ ረገድም አስፈላጊ ነው። የተለያዩ ባሕርያትን እንዲላበሱ ወይም ወክለው እንዲከውኑ
ሲደረግም ከተዘወተረው የተዛባ አመለካከት በፀዳ መልክ ትኵረት ሰጥቶ በእኩልነት ማከፋፈል
ይገባል።

በመተግበር ላይ ካለው ርዕሰጉዳይ ጋር በተገናኘ በክፍል ውስጥ ሥርዓተፆታ ነክ ጉዳይ


ሲነሳም፣ መምህራን ለአንዱ ሳይወግኑ ተገቢ ትኵረት ሰጥተው በሚዛናዊነት ማስተናገድ
ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች የሚለው ርዕሰጉዳይ በሚነሳበትና በዚህ ላይ
ውይይት በሚደረግብት ጊዜ መምህራን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በሴቶች ላይ ስላደረሱትና
ስለሚያደርሱት ጉዳት ትኵረት ሰጥተው ማብራራትና የተማሪዎቹም ተግባር እንዲህ ዓይነቱን
ጎጂ ድርጊት ማስወገድ መሆን እንዳለበት ማስረዳት ይኖርባቸዋል።

xxiv አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


• ለአካለመጠን መድረስ፡- ልጆች ወንዶችም ሆኑ ሴቶች እያደጉ ሲመጡ በትምህርታቸው ላይ
ተጽዕኖ ሊኖራቸው የሚችሉ አካላዊና ሥነልቦናዊ ለውጦች ማሳየታቸው አይቀሬ ነው። ሴቶች
በወር አበባቸው ወቅት በሚሰማቸው የህመም ስሜት የተነሳ ከክፍል እስከመቅረት ሊደርሱ
ይችላሉ። ይኽ በሚሆንበት ጊዜ መምህራን የተቋረጠባቸውን ትምህርት ጊዜ ሰጥተውና የማካካሻ
መርሐግብር አውጥተው ማስተማር ይኖርባቸዋል። ወንዶች ልጆችም እንዲሁ በሚጎረምሱበት
ወቅት ለትምህርታቸው ትኵረት ላይሰጡና በራሳቸው ላይ ስላለው ለውጥ ብቻ ሊያስቡ ይችላሉ።
በመሆኑም መምህራን ይኼን ለውጥ ተገንዝበው ተገቢውን ድጋፍና ምክር ለሁለቱም ፆታዎች
መስጠት ይጠበቅባቸዋል።

• ወሲባዊ ትንኮሳ፡- ወንዶችንም ሆነ ሴት ተማሪዎችን በአካል፣ በሥነልቦናና በስሜት እንደሚጎዳ


ተገንዝበው፣ መምህራን በምንም ሁኔታ ወሲብ ነክ የሆነ አስተያየት ከመስጠት፣ አካላዊ እንቅስቃሴ
ከማድረግ፣ አልፎ ተርፎም ትንኮሳ ከማድረግ መቆጠብ አለባቸው። እንዲህ ዓይነቱም ተግባር
በራሳቸው በተማሪዎችም ቢሆን እንዳይፈጸም መከላከል አለባቸው።

አካቶ ትምህርት
አንዳንድ ተማሪዎች ለትምህርት ተደራሽ ለመሆንና በእኩልነት የትምህርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ለማድረግ የተለየ ተጨማሪ ድጋፍ የሚሹ ይሆናሉ። ይኽ የሚሆነው ልጆች ባለባቸው አካል ጉዳተኝነት
ምክንያት (ውሱን የመማር፣ የመስማት፣ የማየት፣ ዕድገት/ውስንነት፣ የቋንቋ ወይም የመንተባተብ፣
የኦቲዝም፣ የአእምሮ ጉዳት፣ የመስማትና የማየት ወይም የተለያዩ የአካል ጉዳተኛነት ችግሮች) ሊሆን
ይችላል። በተጨማሪም ከክፍል ደረጃቸው በላይ የአእምሮ ብስለት ወይም የመፍጠር ችሎታም ባላቸው
ተማሪዎች ዘንድም ሊከሰት የሚችል ችግር ነው።

ስለዚህ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ በዚህ የመምህር መምሪያ ውስጥ የተለያዩ የማስተማሪያ ስልቶች
ተካትተዋል። በመሆኑም መምሪያው የተለያዩ የማስተማሪያ ዘዴና የተለያዩ የተግባራት አቀራረቦች፣
የሚታዩ፣ የሚደመጡ፣ የሚዳሰሱ፣ የሚሞከሩ ተግባራትን በማካተት ተማሪ ተኮር የሆነ አጠቃላይ መርሕ
የተከተለና ተከታታይ ምዘናን ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ይኽ ክፍል የልዩ ፍላጎት
ተማሪዎችን ለማገዝና ለመደገፍ በክፍል ውስጥ ሊተገበሩ የሚችሉ አጠቃላይ ስልቶችን ያቀርባል።
ትኵረት የተሰጠውም የማስታወስ፣ የተግባቦት፣ የቃላት ዕውቀትና የቋንቋ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች
የበለጠ በማገዝ ላይ ነው። አንዳንዶቹን ችግሮች ለመቅረፍ የሚከተሉትን መተግበር ይጠቅማል፣

• መመሪያን ወይም ትዕዛዝን በራሳቸው ቋንቋ መልሰው እንዲሉት ተማሪዎችን መጠየቅ፣ ይኽ


የመረዳትና የመመለስ ችግር ላለባቸውና መመሪያው ላመለጣቸው ተማሪዎች በጣም ጠቃሚ
ነው። መመሪያውን ደግሞ የመናገሩን ተግባር ለቢጤያቸው ወይም ለመምህር ሊያቀርቡ ይችላሉ።
መምህራንም በአንድ ጊዜ የሚሰጡትን የቃል መመሪያዎች ቊጥር መወሰን ይኖርባቸዋል።

• የፅንሰሀሳብና የስልተትግበራ ግምገማዎች መስጠት፣ እያንዳንዱን ቀን በቀደመው ክፍለጊዜ


የተማሯቸውን ክሂሎችና ሀሳቦች በመከለስ መጀመር ይቻላል። የቀደሙ ትምህርቶች ዕለታዊ
ግምገማ ተማሪዎች አዲሱን ትምህርት ከቀደመ እወቀታቸው ጋር ለማገናኘት ይጠቅማቸዋል።

• የተለያዩ የመገናኛ መንገዶችን (የብዝኀ-ስሜት ፍንጮች) መጠቀም፣ በተቻለ መጠን መረጃዎች


በተለያዬ መንገድ ለምሳሌ፣ በሚደመጡ፣ በሚታዩ፣ በሚዳሰሱ፣ በእንቅስቃሴ በሚታገዙ ዘዴዎች
ለማቅረብ መሞከር ጥሩ ነው። ለምሳሌ መዝሙሮችን ከአካል እንቅስቃሴ ጋር አንድ ላይ
መጠቀም ይቻላል።

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xxv


• የዕለት ዝውትሮችን አለመለዋወጥ፡ (“ለ” አይጠብቅም)፣ የመማር ችግር ያለባቸው በርካታ
ተማሪዎች እነዚህን የየዕለት ዝውትሮችን ለማወቅና ምን እንደሚጠበቅባቸው ለመረዳት
ይጠቀሙባቸዋል። ስለዚህ እነዚህን ዝውትሮችና የሚጠበቁባቸውን ትምህርታዊ ግቦች በሰሌዳ፣
በግድግዳ ወይም በጠረጴዛቸው ላይ መጻፍ ወይም መለጠፍ ይጠቅማል።

• ለተግባራትና ለተማሪዎች ሥራዎች የበለጠውን ጊዜ መመደብ፡ አንዳንድ ተማሪዎች አዳዲስ


መረጃዎችን ለማጤን፣ ከራስ ጋር አዋህዶ ለማቆየትና አዲሱን ዕውቀትና ክሂል ለመጠቀም ረዘም
ያለ ጊዜ ሊወስድባቸው ይችላል። በመሆኑም ተግባሩንና የተሰጣቸውን ሥራ እንዲጨርሱ ዘለግ
ያለ ጊዜ መስጠት አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። የሚሰጣቸውንም የሥራ መጠን መቀነስ አስፈላጊ
ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ፣ ጥቂት ዓረፍተነገሮችን ወይም ቃላትን ሰጥቶ እንዲያነቡ ማድረግ
አንዱ መንገድ ነው።

• ምንባቡን መከታተል የማይችሉ ከሆነ የሚሰጡ መመሪያዎችን በሰሌዳ መጻፍ፡- በተለይ


በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ መስማት የማይችሉ ተማሪዎች ሲኖሩ የሚተላለፉ መመሪያዎችን፣
ቊልፍ ዕሳቤዎችንና ቃላትን ሰሌዳ ላይ መጻፍ አስፈላጊ ነው። ከዚህ ጋር የተያያዘ በክፍል ውስጥ
ተገቢ የሆነ መቼት መፍጠር ለምሳሌ የድምጽ ማስተጋባትና የመቆራረጥ ችግር እንዳይኖር
በማድረግ በመምህርና በተማሪዎች መካከል ለሚኖረው ተግባቦት አመቺ ሁኔታ መፍጠር
ይገባል። አስፈላጊ ሲሆንም የማዳመጡን ምንባብ አባዝቶ መስጠት፣ ሥዕሎችንና የሚታዩ
ተጨባጭ ነገሮችን በድጋፍ መልክ መጠቀም ጠቃሚ ነው።

• መመሪያዎችን በቃል ማንበብ፣ ጽሑፎችን ማጕላት፡- የማየት ችግር ላለባቸው ተማሪዎች


መምህራን ለሌሎች ተማሪዎች በሰሌዳ ላይ እየጻፉ እያሉ ለእነዚህ ተማሪዎች መመሪያዎችን
ጮክ ብለው ያንቡላቸው፤ ወደሰሌዳው ጠጋ ብለው እንዲቀመጡም ይፍቀዱላቸው፤ ከተቻለም
መመሪያዎችን በጕልህ ጽፈው በሚታይ ቦታ ሊያደርጉላቸው ይችላሉ።

• በመደጋገፍ የመማርና የቢጤ መማማር ዘዴን መጠቀም፡- ተመሳሳይ ወይም የተለያየ ችሎታ
ያላቸውን ተማሪዎች በቡድን አዋቅሮ ርስበርስ እንዲማማሩ ማድረግ ጠቃሚ ነው። በተማሪዎችም
መካከል መተዋወቅንና መከባበርንም ይፈጥራል፤ በራስ የመተማመንን ስሜትና ማኅበራዊ
ክሂል ያዳብራል። መምህራን ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ለትምህርቱ ሂደት አስተዋጽዖ
እንዳላቸውና የነቃ ሚና እንደሚጫወቱ ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።

• አንድ ተግባር ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ግልጽ፣ ወቅታዊና አዎንታዊ ግብረመልስ መስጠት፡-የልዩ
ፍላጎት ተማሪዎች ከሌሎቹ ተማሪዎች እኩል በተመሳሳይ ፍጥነት ላይማሩ ይችላሉ። በዚህም
ራሳቸውን ከሌሎቹ ያነሱ አድርገው እንዲቆጥሩ ሊያደርጋቸው ይችላል። ይኼም ለትምህርት
ያላቸውን ተነሳሽነትና የመማር አቅም ሊጎዳው ይችላል። በመሆኑም ያሳዩት መሻሻል ጥቂት
እንኳ ቢሆን አዎንታዊ የሆነ አበረታች ግብረመልስ መስጠት መዘንጋት የለበትም።

ከላይ የተዘረዘሩትን ስልቶች በሚገባ ለመተግበር መምህራን የተማሪዎቻቸውን ፍላጎትና ችሎታ


መረዳት ይኖርባቸዋል። በትምህርትቤት ውስጥ የልዩ ፍለጎት ትምህርት ሥልጠና ያላቸው መምህራን
ካሉ ከነሱ ጋር በመሆን በጋራ በመሥራት የተማሪዎቹን ፍላጎቶች መለየትና በትምህርቱም ሂደት
ለማካተት መሞከር ያስፈልጋል።

xxvi አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


የመምህር መምሪያ አጠቃቀም

ይኽ የመምህር መምሪያ ለተማሪ የተዘጋጀውን መጽሐፍ ደረጃ በደረጃ ይከተላል። ለሳምንቶችና ለቀናት
የተሰጡ ቊጥሮች ከተማሪ መጽሐፍ ጋር አንድ ናቸው። እያንዳንዱ ምዕራፍ የሚጀምረው በምዕራፉ
ዓላማዎች ነው። በመምህር መምሪያ ላይ ያሉ የራስጌ ጽሁፎች ትምህርቱን ለመከታተልና በተማሪዎች
መጽሐፍ ውስጥ ትክክለኛውን ይዘት ለማግኘት እንዲቻል ከተማሪ መጽሐፍ ጋር የተጣጣሙ ናቸው።

ለእያንዳንዱ የትምህርት ይዘት የመምህር መምሪያዉ የሚከናወኑ ተግባራትን በልሥራ - እንሥራና -


በሥሩ አቀራረብ መንገድ አዘጋጅቶ አቅርቧል። የትምህርቱንም ሂደት ቀላል ለማድረግና ተግባራቱንም
ለማመቻቸት ለመምህራን በጣም ግልጽና ተጨባጭ መመሪያዎችን ይሰጣል። ከጥቂት ሳምንታት
ማስተማር በኋላ መምህራን ከተለያዩ ተግባራት ጋር ስለሚተዋወቁ የሚሰጧቸው መመሪያዎች ያጥራሉ፤
ነገርግን ሁልጊዜ መምህራን እያንዳንዱን ተግባር እንዴት መተግበር እንዳለባቸው ወደኋላ ተመልሰው
የቀደሙትን ሳምንታት መመሪያዎች መመልከት ይጠበቅባቸዋል።

አጻጻፍን በሚመለከት በጥቅም ላይ የዋሉ ማሻሻያዎች

በአማርኛ ቋንቋ አጻጻፍ ረገድ አንድ ወጥ የሆነ ስምምነት ያለ የለም። በዚህም መምህራን ትኵረት
ሰጥተው በራሳቸው ለመጠቀምም ሆነ ለማስተማር ሲቸገሩ ይታያሉ። በመሆኑም ያለውን መሠረታዊ
ችግር በመቅረፍ ተማሪዎችን በተመሳሳይና ወጥ በሆነ መንገድ ለማስተማር በአዳዲሶቹ የመምህር
መምሪያና የተማሪ መጻሕፍት (ከ5ኛ-8ኛ) ውስጥ ትኵረት ከተሰጣቸው ትምህርታዊ ጉዳዮች አንዱ
እንዲሆን ተደርጓል። በዚህ ረገድ ከተደረጉት ማሻሻያዎች የሚከተሉት ይጠቀሳሉ።
1.ሀ. እንደትምህርትቤት፣ ዳቦቤት፣ መሥሪያቤት ወዘተ. ያሉት ጥምር ቃላት በመሆናቸው በወጥነት
አንድ ላይ ተጠጋግተው እንዲጻፉ ተደርገዋል፤ በዚህም መምህራን ትኵረት ሰጥተው ራሳቸውም
በጥንቃቄ እየተጠቀሙ ለተማሪዎቻቸው እንዲያለማምዷቸው ያስፈልጋል።

ለ. እንደቅድመንባብ፣ ድኅረንባብ፣ ኅብረተሰብ፣ ቅድመማዳመጥ ወዘተ. ያሉ ባለአጣማሪ (-ኧ-) ቃላትም


በተዘበራረቀ መንገድ መጻፋቸውና በትምህርት አሰጣጣችንም ሆነ በአጻጻፍ ሥርዓታችን ላይ
ችግር መሆናቸው የቆየ ጉዳይ ነው፤ ስለዚህ በአሁኖቹ መጻሕፍት ውስጥ አንድ ላይ ተጠጋግተው
እንዲጻፉና በዚሁ መንፈስም መምህራን ራሳቸው በጥንቃቄ እየተጠቀሙ ለተማሪዎቻቸው
እንዲያስተምሩ ይጠበቃል።

ሐ. ሌላው እዚህ ላይ የሚጠቀስ ማሻሻያ በመስተዋድዳዊ ሐረግ ውስጥ መስተዋድዳኑንና አብረዋቸው


የተዋቀሩትን ስማዊ ሐረጎች በተዘበራረቀ መንገድ ከመጻፍ በወጥነት ለመጠቀም የተደረገው
ሙከራ ነው። እንደሚታወቀው መስተዋድዳናችን ስ-፣ ስለ- እንደ-፣ እንድ-፣ ወደ-፣ እስከ- ወዘተ.
በሙሉ ማለት በሚቻልበት ሁኔታ (ዘንድ የሚለው መኖሩን ሳንዘነጋ) ራሳቸውን ችለው ለብቻቸው
መቆም የሚችሉ አለመሆናቸውን በሰዋስው እያስተማርን፣ አብዛኞቻችን ስንጽፍ ግን ልክ ራሳቸውን
እንደቻሉት ቃላት በሁለት ነጥብ እየለየን ነው። ይሁንና በነዚህ አዳዲስ መጻሕፍት ውስጥ
በወጥነት፣ ለምሳሌ፣ እንዲበላ፣ እንደመጣ፣ እንደአባቱ፣ ወደትምህርትቤት፣ ስለመጣ፣ ስለአበበ፣ ስበላ፣
ሲበላ፣ ከቤቱ በላይ፣ ወዘተ. የሚሉት አንድ ላይ እንዲጻፉና ትምህርቱም በዚሁ ዓይነት እንዲሰጥ
ተዘጋጅቷል።

መ. ሌላው ትኵረት የሚሻ ጉዳይ የብዙ ቊጥር ቃላትን የምንጽፍበት ሥርዓት ነው። እንደሚታወቀው

አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ xxvii


ቃላትን ወደብዙ ቊጥር የምንለውጥባቸው መንገዶች እንደቃላቱ ክፍል የተለያዩ ቢሆኑም፣ በተለይ
በስሞች ላይ የሚታየው ወጥነት የጎደለው ይመስላል። ለምሳሌ፣ ቃል ብሎ ቃሎች ወይም ቃላት
ማለት ሥርዓት የተከተለ ሲሆን፣ ቃላቶች ማለት ግን ብዙ ቊጥርን የሚያመለክተውን ቃል እንደገና
የብዙ ቊጥር ምዕላድ ጨምሮ (ቃል+ -ኣት= ቃላት + -ኦች= ቃላቶች) ማብዛትን የሚያሳይ
የተዘወተረ ግድፈት ነው። በመሆኑም በወጥነት በአንዱ መንገድ ማለትም በአማርኛው የብዙ
ቊጥር ምዕላድ -ኦችን (ከነዘሮቹ) መጠቀምና ቃሎች፣ መምህሮች፣ ሕፃኖች፣ ዕፆች ወዘተ. እያሉ፣
አለበለዚያም ከግእዝ ቋንቋ ወስደን በምንጠቀምበት የብዙ ቊጥር ሥርዓት፣ ቃላት፣ መምህራን፣
ሕፃናት፣ ዕፅዋት ወዘተ. በማለት መጻፍና ይኼንኑም ለተማሪዎች በወጥነት ማስተማር በጣም
አስፈላጊ ሆኗል። ከዚህ በተለየ ግን መምህራኖች፣ ቃላቶች፣ ዕፅዋቶች እያሉ መጠቀም (በቋንቋዉ
ውስጥ መነሻ ምክንያት ያለው ቢመስልም) ሥርዓታዊም ተገቢም አይመስልም፤ እንደትልቅ ሕፀፅ
የሚወስዱ ሰዎች ቢያጋጥሙም አይደንቅም። ስለሆነም መምህራን ከላይ በተመለከተው መሠረት
በተግባር እንዲጠቀሙና እንዲያስተምሩ አደራ ተጥሎባቸዋል።

2. በሁለተኛ ደረጃ ትኵረት የሚሠጠው ጉዳይ በአማርኛ የፊደል ገበታ ላይ ሞክሼ ፊደላት የመኖራቸው
ጉዳይ ነው። እዚህ ላይ የቆየውን አተካሮ ትተን (ወደፊት መሠረታዊ እልባት እስኪያገኝ) በተቻለ
መጠን በወጥነት ፊደላቱን መጠቀም ግን ለሌላ ጊዜ የሚተው ባለመሆኑ በአሁኖቹ መጻሕፍት (ከ5ኛ-
8ኛ) ውስጥ ትኵረት ለመስጠት ጥረት ተደርጓል። እንደመነሻ የተወሰደውም በአብዛኛው በጥቅም
ላይ እየዋሉ ያሉበት መንገድ ነው። በዚህም፣ ለምሳሌ ከመጻፍ ጋር የተገናኙትን ከነዝርዝራቸው
ጽሕፈት፣ ጸሐፊ፣ መጻፍ፣ አጻጻፍ ወዘተ.፣ ከሥን ጋር የሚዋቀሩትን ሥነጽሑፍ፣ ሥነሕዝብ፣
ሥነሥርዓት ወዘተ.፣ ከሕግ ጋር የሚዋቀሩትን ሕገመንግሥት፣ ሕገተፈጥሮ፣ ሕገወጥ፣ ወዘተ፣
ዝርዝሩ ብዙ በመሆኑ ጉዳዩን በጥሞና በማጤንና መጻሕፍቱን በጥንቃቄ እያነበቡ፣ በመጻሕፍቱ
ውስጥ በተጻፉበት መንገድ መረዳትና በዚሁ ዓይነትም ለተማሪዎች ማስተማር ስለሚገባ መምህራን
ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው።

3. በመጨረሻም መጠቀስ ያለበት ሌላው ከአጻጻፍ ጋር የሚያያዝ ጉዳይ የቋንቋ ክሂሎችን ለመሠየም
የምንጠቀምበትና የምንጽፍበት መንገድ ነው። ስለሆነም አራቱ የቋንቋ ክሂሎች በወጥነት ማዳመጥ
(ማድመጥ አይደለም)፣ መናገር (ንግግር አይደለም)፣ ማንበብ (ንባብ አይደለም) እና መጻፍ
(ጽሕፈት ወይም ጽሑፍ አይደለም) በመሆናቸው በዚሁ ዓይነት መንገድ እንዲጻፉና በተግባር
ላይ እንዲውሉ ይጠበቃል።

xxviii አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ መግቢያ


ምዕራፍ 1 ጓደኝነት
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይጽፋሉ፤
• በገላጭ የአጻጻፍ ስልት ተገቢ ሥርዓተነጥቦችን በመጠቀም አንድ አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• “ጓደኝነት” የሚለውን ምንባብ ይዘት መሠረት በማድረግ በቀረቡት ጥያቄዎች ላይ ይናገራሉ።
• የተጸውዖና የወል ስሞችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር ይጽፋሉ።

1ኛ ሳምንት ሠላምታ
ልሥራ
መ. አንድን ምንባብ በምታነቡበት ጊዜ ውስብስብ
1ኛ ቀን ቃላት/ሐረጋት ሊያጋጥሟችሁ ይችላሉ።
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች እነዚህን ቃላት/ሐረጋት በትክክል ማንበብ
ካልቻላችሁ የምንባቡን ሀሳብ ለመረዳት
• የቃላት ጥናት እንቅፋት ሊሆኑባችሁ ይችላሉ። ስለዚህ
• ማንበብ “ሐዋና ጓደኞቿ” በሚል ርዕስ የቀረበውን
ምንባብ ስታነቡ፣ ይህ ችግር እንዳያጋጥማችሁ
ውስብስብ ቃላት/ሐረጋት ተለይተው
የቃላት ጥናት ቀርበዋል። ለጥቂት ደቂቃዎች ያህል እነዚህን
ቃላት/ሐረጋት በመጀመሪያ በመነጣጠል፣
መነጠልና ማጣመር (10 ደቂቃ) ከዚያም በማጣመር አነባለሁ።
መ. በመጀመሪያ “ስሜታቸውን” የሚለውን ቃል
ማስታወሻ፡-
ነጣጥዬ ሳነበው [“ስሜት-ኣቸው-ን” ይሆናል።]
መነጠል፡- ውስብስብ ቃላትና ሐረጋትን (ቃሉን እየነጣጠሉ ያንብቡላቸው።)
በመነጣጠል የምናነብበት ዘዴ ነው።
መ. አሁን ደግም ይህንኑ ቃል አጣምሬ ሳነበው
ማጣመር፡- ተነጣጥለው የቀረቡ ልዩ ልዩ [“ስሜታቸውን” ይሆናል።] (ቃሉን ሳይነጣጥሉ
የቃላትና የሐረጋት ክፍሎችን በማጣመር አንድ ላይ ያንብቡላቸው።)
የምናነብበት ዘዴ ነው።
መ. “በብሔራዊ” የሚለው ሐረግ ተነጥሎ
የመነጠልም ሆነ የማጣመር ዓላማ ለማንበብ ሲነበብ [“በ-ብሔር-ኣዊ” ይሆናል።] (ሐረጉን
አስቸጋሪ የሆኑ ውስብስብ ቃላትና ሐረጋትን እየነጣጠሉ ያንብቡላቸው።)
በትክክል ማንበብ ማስቻል ነው።
መ. አሁን ደግሞ ይህንኑ ሐረግ አጣምሬ ሳነበው
በአጠቃላይ አንድን ቃል እየነጠሉና እያጣመሩ [“በብሔራዊ” ይሆናል።] (ሙሉ ሐረጉን
ማንበብ አቀላጥፎ የማንበብ ክሂል ዕድገትን ሳይነጣጥሉ ያንብቡላቸው።)
ያፋጥናል።

፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 1


እንሥራ 2. ከርዕሱና ከሥዕሉ በመነሳት ስለምንባቡ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እናንብብ። ይዘት እንዲገምቱ በማድረግ፣
መ. በመጀመሪያ “እያንዳንዳችን” የሚለውን ሐረግ 3. በምንባቡ ውስጥ የሚገኙ አዳዲስ ተተኳሪ
ነጣጥለን እናንብበው። ቃላትን በማስተዋወቅ
[መተ. “እየ-አንዳንድ-ኣችን”]
መ. አሁን ደግም ይህንኑ ሐረግ አጣምረን እናንብበው።
ልሥራ
[መተ. “እያንዳንዳችን”] መ. ተማሪዎች የቅድመንባብ ጥያቄዎችን
መ. “የተዘጋጀችው” የሚለውን ሐረግ ነጣጥለን ከማንበባችሁ በፊት መመለሳችሁ ከፍተኛ
እናንብበው። ጥቅም አለው። የቅድመንባብ ጥያቄዎች
የማንበብ ጉጉታችሁን ይቀሰቅሳሉ፤
[መተ. “የ-ተዘጋጀ-ችው”] ትኩረታችሁ ሙሉ በሙሉ ምንባቡ ላይ
መ. አሁን ደግሞ አጣምረን እናንብበው። እንዲሆን ያደርጋሉ። ስለዚህ ዛሬ የተወሰኑ
የቅድመንባብ ጥያቄዎችን እንመልሳለን።
[መተ. “የተዘጋጀችው”] ከቅድመንባብ ተግባራት መካከል ዛሬ
ሥሩ ተግባራዊ የምናደርገው ስለሚነበብ ምንባብ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን፣ መገመት ነው። በመጀመሪያ እኔ እገምታለሁ።
በቃላት ጥናት ሥር የቀረቡትን ቃላትና
መ. ሥዕሉን በመመልከት ልጆቹ ያሉበት ቦታ
ሐረጋትን በአነስተኛ ቡድን በመሆን
የት ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ።
በየተራ በመጀመሪያ እየነጣጠላችሁ ከዚያም
እያጣመራችሁ አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ [መ. የትምህርትቤት መማሪያ ክፍል ውስጥ
ሌሎቻችሁ ደግሞ ቃሉ በትክክል መነበቡን ይመስለኛል፤ ምክንያቱም ከልጆቹ ጀርባ
ተከታተሉ። ሰሌዳ ይታየኛል።]
(መ. ተማሪዎቹ በአነስተኛ ቡድን ሆነው በየተራ እንሥራ
እንዲያነቡ ያድርጉ። ተማሪዎች ሲያነቡ መ. በሥዕሉ ላይ የሚታዩት ልጆች ምን እያደረጉ
እየተዘዋወሩ በትክክል እያነበቡ መሆናቸውን ያሉ ይመስላችኋል?
ይከታተሉ። በትክክል ያልተነበቡትን ቃላትና
[መተ. የተለያዩ መልሶች ሊሠጡ ይችላሉ።]
ሐረጋት እርስዎ ያንብቡላቸው።)
ሥሩ
ማንበብ (30 ደቂቃ) መ. አሁን በተመሳሳይ ሁኔታ በ1ኛው ሳምንት፣
በ1ኛው ቀን የሚገኘውን የቅድመንባብ ጥያቄ
ሐዋና ጓደኞቿ መልሱ።
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) [ተ. ግምታቸውን ይናገራሉ።]
መገመት የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
ማስታወሻ ልሥራ
ወደንባብ ሂደት ከመግባት በፊት የተማሪዎችን መ. በቅድመንባብ የገመትኩት ትክክል መሆኑን
የማንበብ ጉጉት መቀስቀስና ትኩረታቸውንም ወይም አለመሆኑን በንባብ ሂደት ማረጋገጥ
መሰብሰብ ያስፈልጋል። ይህንንም በሚከተሉት ይገባኛል። ለምሳሌ “ልጆቹ በመማሪያ ክፍል
የቅድመንባብ ተግባራት ማሳካት ይቻላል ውስጥ መሆናቸውን ገምቼ ነበር። የግምቴን
ትክክለኛነት አንብቤ አረጋግጣለሁ።” (3ኛውን
1. የምንባቡን ርዕስና ንዑስ ርዕሶች፣ ሥዕሎችን፣
አንቀጽ ድምፅዎን እያሰሙ ያንብቡላቸው።)
ጥያቄዎችን፣ ተረቶችን ወዘተ. በመጠቀም
የቀደመ ዕውቀትና ገጠመኝ በመቀስቀስ፣ መ. ልጆቹ ስለሚገኙበት ቦታ የሠጠሁት ግምት
ትክክል ነበር?

2 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፪


[መ. አዎ! ትክክል ነበር፣ ምክንያቱም ሦስተኛው እንሥራ
አንቀጽ “ጀማል አንድ የመማሪያ ክፍል ፈልጎ መ. አሁን ደግሞ አንድ ጥያቄ አብረን እንሥራ።
ቦታ ካመቻቸ በኋላ ገቡና ውይይታቸውን በቀጠሯቸው ዘግይቶ/ታ የደረሰው/ችው ማን
ቀጠሉ” ይላል።] ነው/ናት?
እንሥራ [መተ. ሳምራዊት]
መ. በቅድመንባብ ላይ “ልጆቹ ምን እያደረጉ
መ. ትክክል!
እንደሆነ አብረን ገምተን ነበር።ግምታችንን
ለማረጋገጥ አንቀጽ ሦስትን አብረን ሥሩ
እናንብብ። መ. የቡድኑን ሀሳብ አጠናቅራ/ሮ እንድትመጣ/
እንዲመጣ የተመደበችው/የተመደበው ማን
[መተ. አንቀጽ ሦስትን ያነባሉ።]
ናት/ነው?
መ. ግምታችን ትክክል ነበር?
[ተ. አያልነህ]
[መተ. አዎ፣ ምክንያቱም አንቀጹ መጨረሻ ላይ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በዚሁ መሠረት በ1ኛው
“… ውይይታቸውን ቀጠሉ” ይላል።]
ሳምንት በ1ኛው ቀን በአንብቦ መረዳት ሥር
መ. በጣም ጥሩ! ያሉትን ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ።
ሥሩ (መ.የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎቹን እርስዎ
መ. ርዕሱንና ሥዕሉን በመመልከት ምንባቡ እየጠየቁ ተማሪዎች በቃል እንዲመልሱ
ስለምን እንደሚገልፅ ገምታችሁ ነበር። ያድርጉ። ተማሪዎቹ ከመለሱ በኋላ
በምታነቡበት ጊዜ ግምታችሁ ትክክል እንደአስፈላጊነቱ ማስተካከያ ይስጡ።
መሆኑን ወይም አለመሆኑን እያረጋገጣችሁ በመጨረሻም በተግባር “2” የቀረበውን ጥያቄ
አንብቡ። የቤትሥራ ይስጧቸው።)
(መ.ተ ማ ሪ ዎ ች በሚያነቡበት ጊዜ
ድምፅ አለማሰማታቸውን፣ ከንፈር 2ኛ ቀን
አለማንቀሳቀሳቸውን፣ የሚያነቡትን ምንባብ
በጣታቸው አለመጠቆማቸውን ያረጋግጡ። የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ጭንቅላታቸውን ሳያንቀሳቅሱ፣ ዓይኖቻቸውን
ብቻ በማንቀሳቀስ የሚያነቡ መሆናቸውን • ቃላት
ይከታተሉ።) • መጻፍ
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
ልሥራ የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መ. አሁን ምንባቡን አንብባችሁ ጨርሳችኋል።
ሥሩ
በቅ ድመ ንባብ ለ ቀ ረቡ ት ጥ ያቄዎች
የሠጣችሁት ምላሽ ትክክል ነበር? (መ.ባለፈው ክፍለጊዜ የሠጧቸውን የቤትሥራ
(የተማሪዎቹን ምላሽ ይቀበሉ፤ መልሳቸውን መሥራታቸውን ያረጋግጡ። ተማሪዎች
ከምንባቡ ጋር አገናዝበው እንዲናገሩ የሠሩትን እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
ያድርጉ።) መ. በተለያዩ በዓላት ጊዜ ሰዎች ሲገናኙ ምን
[ተ. አዎ ትክክል ነበር/ ትክክል አልነበረም።] ምን እንደሚባባሉ በተግባር አሳዩ።

መ. አሁን ምንባቡን አንብበናል። በተነበበው [ተ. “እንኳን አደረሳችሁ፣ እንኳን አብሮ አደረሰን”
ታሪክ ውስጥ የቡድን መሪው/ዋ ማን ነው/ እየተባባሉ በመሳሳም በተግባር ያሳያሉ።]
ናት? ጥያቄውን እኔ እመልሳለሁ። መ. በጣም ጥሩ! (ተማሪዎች እንደየአካባቢውና
[መ. የቡድን መሪዋ ሐዋ ናት።] እንደየእምነቱ የተለያዩ የመልካም ምኞት
መግለጫዎችን ሊያቀርቡ ይችላሉ።)

፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 3


ቃላት (10 ደቂቃ) መጻፍ (25 ደቂቃ)
የቃላትና የሐረጋት ተመሳሳይ ፍቺ ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ልሥራ በገላጭ ስልት የቢጋር ሠንጠረዥ
መ. ዛሬ ባለፈው ጊዜ ካነበባችሁት ምንባብ ማዘጋጀት
ውስጥ ለወጡ ቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይ
ልሥራ
ፍቺ እንሠጣለን። በመጀመሪያ እኔ ሠርቼ
መ. ዛሬ ገላጭ ጽሑፍ እንዴት እንደሚጻፍ
ላሳያችሁ።
እንማራለን። ከዚያ በፊት ግን ስለገላጭ
መ. “ጓደኛ” ለሚለው ቃል ተመሳሳዩ ምንድን ጽሑፍ ምንነት እገልፅላችኋለሁ።
ነው? ጥያቄውን እኔ እመልሳለሁ።
መ. ገላጭ ጽሑፍ የአንድን ነገር ቅርፅ፣
[መ.ባልንጀራ] (ቃሉን ደግመው ይጥሩላቸው) መልክ፣ መጠን፣ ባህርይ፣ ወዘተ. በዓይናችን
መ. “ምኞት” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቹ እንዲታይ፤ በጆሯችን እንዲሰማ አድርጎ
ምንድን ነው? ጥያቄውን እኔ እመልሳለሁ። የሚያቀርብ የጽሑፍ ዓይነት ነው።

[መ.ፍላጎት] (ቃሉን ደግመው ይጥሩት) መ. “ሐዋ በጓደኞቿና በመምህሮቿ ዘንድ ተወዳጅ


ናት” የሚለውን ዓረፍተነገር ስትሰሙ ስለሐዋ
እንሥራ ሙሉ መረጃ የሚሰጥ ይመሥላችኋል?
መ. አሁን ደግሞ ሌሎቹን ቃላት አብረን
[መ.ዝርዝር መረጃ ስላልያዘ ስለሐዋ ሙሉ
እንሥራ።
ምሥል አይፈጥርልንም።]
መ. “ሥርዓት” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቹ
መ. አሁን ደግሞ “ሐዋና ጓደኞቿ” በሚል ርዕስ
ምንድን ነው?
ከቀረበው ምንባብ ውስጥ የመጀመሪያውን
[መተ. ደንብ] አንቀጽ ላንብላችሁ። (መምህር
የመጀመሪያውን አንቀጽ ያንቡላቸው።)
መ. ትክክል! “ተወዳጅ” የሚለው ቃል ተመሳሳይ
ፍቺ ምንድን ነው? መ. አሁን አንቀጹን አንብቤላችኋለሁ። አንቀጹ
ስለሐዋ አካላዊም ሆነ ባህርያዊ ማንነት
[መተ. ተፈቃሪ]
የተሟላ መረጃ ስለሚሰጥ በአዕምሯችን
መ. በጣም ጥሩ! እንድናያት አድርጎናል።
ሥሩ እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ ተመሳሳይ ፍቺ የመስጠቱ ሥራ መ. አሁን ገላጭ ጽሑፍ ለማዘጋጀት የሚረዳ
የናንተ ነው። የቢጋር ሠንጠረዥ አብረን እናዘጋጅ።
መ. “መተሳሰብ” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቹ (የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ ሰሌዳው
ምንድን ነው? ላይ ይሣሉላቸው፤ ሥዕላዊ የቢጋር ሠንጠረዡ
በውስጡ የያዘውን መረጃ አይጻፉ።)
[ተ. መረዳዳት፣ መተጋገዝ]
መ. በዚህ መሠረት በ1ኛው ሳምንት በ2ኛው
ቀን የቀረበውን ተግባር ቃላቱን ከተመሳሳይ
ፍቻቸው ጋር በማዛመድ በደብተራችሁ
ጽፋችሁ ታሳዩኛላችሁ።
(መ. ተማሪዎች ተግባሩን እንዲሠሩ 7 ደቂቃ
ይስጧቸው፤ በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ
በትክክል መሥራታቸውን ያረጋግጡ፤
የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤
በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎችዎ
ጋር በመወያየት ግብረ መልስ ይስጡ።)

4 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፬


ትዘረዝራላችሁ።
አካላዊ መግለጫ
[መተ. የመረጡትን/ጧትን ገፀባህርይ መልክና
ቁመት ረጅም
ቁመና፣ ባህርይና የትምህርት ተሳትፎ በቢጋር
መልክ ጠይም ሠንጠረዥ ይዘረዝራሉ።]
ውፍረት/ቅጥነት ቀጭን
(መ.ተማሪዎች የቢጋር ሠንጠረዥ ሲያዘጋጁ
ሌላ ንፁህ በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ እንዴት መሥራት
እንዳለባቸው በመጠቆም ይደግፏቸው።)
ባህርይያዊ መግለጫ የአጻጻፍ ሥርዓት (5 ደቂቃ)
ተግባቢ ልሥራ
ሐዋ ተወዳጅ መ. ዛሬ ስለሥርዓተነጥቦች እንማራለን።
ሥርዓተነጥቦች፣ በምንጽፍበት ጊዜ የተሟላ
መልዕክትን ለማስተላለፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ
አላቸው።
በትምህርትቤቱ ያላት
ተሳትፎ መ. በዛሬው ዕለት ከሥርዓተነጥቦች መካከል
በትምህርት ጎበዝ በሁለቱ ላይ ብቻ እናተኩራለን። እነሱም፦
ነጠላ ሰረዝና አራት ነጥብ ናቸው። ነጠላ ሰረዝ
በክበባት
(፣) በዓረፍተነገር ውስጥ የሚዘረዘሩ ነገሮችን/
በስፖርት ሀሳቦችን የሚወክሉ ቃላትና ሐረጋትን
ለመለየት ይጠቅማል። ለምሳሌ “ሐዋ ቀጭን፣
መ. የሐዋን ቁመት ንግሩኝ ረጅም፣ ጠይም፣ ልጅ ናት” የሚለውን
ዓረፍተነገር ልውሰድ። በዚህ ዓረፍተነገር
[መተ. ረጅም] ውስጥ ስለሐዋ አካላዊ ገጽታ የተዘረዘሩትን
መ. የሐዋን መልክ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ? ነገሮች ለመለየት ነጠላ ሠረዝ አገልግሎት ላይ
ውሏል።ሌላው የምናተኩርበት ሥርዓተነጥብ
[መተ. ጠይም] አራት ነጥብ (።) ነው። አራት ነጥብ አንድ
መ. ሐዋ ቀጭን ናት ወይስ ወፍራም? የተሟላ ሀሳብ በሚያስተላልፍ ዓረፍተነገር
መጨረሻ ላይ እንደመዝጊያ (መደምደሚያ)
[መተ. ቀጭን]
ሆኖ የሚያገለግል ሥርዓተነጥብ ነው። “ጀማል
(መ. በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎችንም ጥያቄዎች አንድ የመማሪያ ክፍል ፈልጎ ቦታ ካመቻቸ
እየጠየቁ በቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ በኋላ ገቡና ቦታቸውን ያዙ” የሚለውን
ተፈላጊውን መረጃ ያሟሉ።) ዓረፍተነገር ለምሳሌ ያህል ልውሰድ።
ሥሩ መ. “ጀማል አንድ የመማሪያ ክፍል ፈልጎ …”
መ. አሁን በሠራነው መሠረት የቢጋር ሠንጠረዥ የሚለውን የዓረፍተነገሩ ክፍል ድርጊቱ
አዘጋጁ። ከዚያም ካነበባችሁት ምንባብ ውስጥ መጠናቀቁን ያሳያል? መልሱን እኔ
አንዱ/ዷን ገፀባህርይ ምረጡ። በመቀጠል እሰጣለሁ።
የገፀባህርይው/ዋን አካላዊና ባህርያዊ [መ. አያሳይም፤ ምክንያቱም ሀሳቡ የተንጠለጠለ
ገጽታዎች፣ በትምህርትቤቱ ያላትን/ውን ነው።]
ተሳትፎ ባዘጋጃችሁት የቢጋር ሠጠንረዥ
ውስጥ ዘርዝሩ። መ. “ጀማል አንድ የመማሪያ ክፍል ፈልጎ ቦታ
ካመቻቸ በኋላ…” የሚለው የተሟላ ሀሳብ
መ. በምንባቡ ውስጥ ከሐዋ በስተቀር የሌሎቹ ያስተላልፋል? መልሱን እኔ እመልሳለሁ።
ገፀባህርያት ማንነት አልተገለፀም። ስለዚህ
ራሳችሁ ለገፀባህርያቱ አካላዊ፣ ባህርያዊና [መ. አያስተላልፍም፤ ምክንያቱም የዓረፍተነገሩ
የትምህርትቤት ተሳትፎ በመፍጠር ሀሳብ አልተቋጨም።]
ባዘጋጃችሁት የቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ መ. “ጀማል አንድ የመማሪያ ክፍል ፈልጎ

፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 5


ቦታ ካመቻቸ በኋላ ገቡና ቦታቸውን ያዙ” “ተገኝተዋል” በሚለው ግስ ተደምድማል]
የሚለው የተሟላ ሀሳብ ይዟል? መልሱን እኔ
ሥሩ
እመልሳለሁ።
መ. ቀደም ሲል ነጠላ ሠረዝና አራት ነጥብን
[መ. አዎ! ይህ ዓረፍተነገር “ቦታቸውን ያዙ” በዓረፍተነገር ውስጥ እንዴት መጠቀም
በሚለው ሐረግ አማካይነት መቋጫ እንዳለብን ተምረናል። አሁን ደግሞ በ1ኛው
አግኝቷል።] ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን የሚገኘውን የአጻጻፍ
መ. ስለዚህ “ያዙ” ከሚለው የዓረፍተነገሩ መጨረሻ ሥርዓት ተለማመዱ። ሥርዓተነጥቦቹ
ቃል ቀጥሎ በአራት ነጥብ (።) መደምደም ያልተሟሉ አንቀጽ ቀርቦላችኋል። እናንተ
ያስፈልጋል። (“ጀማል አንድ የመማሪያ ክፍል ተገቢዎቹን ሥርዓተነጥቦች በባዶ ቦታው
ፈልጎ ቦታ ካመቻቸ በኋላ ገቡና ቦታቸውን ታስገበላችሁ።
ያዙ” ብለው ዓረፍተነገሩን አሟልተው (መ.ተማሪዎች ይህን ተግባር የሚሠሩበት 5
ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው። ከ “ያዙ” ቀጥሎ ደቂቃ ይስጧቸው። በመጀመሪያ በግል
አራት ነጥብ ማድረግ አይዘንጉ።) ሥርዓተነጥቦቹን በባዶ ቦታዎች እንዲያስገቡ
እንሥራ ያድርጉ። ከዚያም ጥንድ ጥንድ ሆነው
የሠሩትን እንዲያስተያዩና እንዲተራረሙ
መ. አሁን ከምንባቡ አንድ ዓረፍተነገር
ያድርጉ። በመጨረሻም ትክክለኛውን
እንውሰድና ተገቢዎቹን ሥርዓተነጥቦች
መልስ ይንገሯቸው።ተግባር ሁለትን ደግሞ
በቦታቸው እናስገባ።
የቤትሥራ ይስጧቸው።)
“ሐዋ_ አያልነሽና ጀማል የተሰጣቸውን
የቤትሥራ ለመሥራት በያዙት ቀጠሮ
መሠረት በቦታው ተገኝተዋል_” (ሰሌዳው
3ኛ ቀን
ላይ ይጻፉላቸው።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. በመጀመሪያው ክፍት ቦታ መግባት ያለበት
ሥርዓተነጥብ ምንድን ነው? • አቀላጥፎ ማንበብ

[መተ. ነጠላሠረዝ (፣) (÷)] (አንድ ተማሪ • ማዳመጥ


ወጥታ/ቶ ሰሌዳው ላይ ሥርዓተነጥቡን • ሰዋስው
በዓረፍተነገሩ ውስጥ አስገብታ/ቶ በመጻፍ
እንድታሳይ/ እንዲያሳይ ያድርጉ።)
መ. ነጠላሠረዝ የተጠቀምነው ለምንድን ነው? የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
[መተ. ምክንያቱም በዓረፍተነገሩ መነሻ ላይ ሦስት (መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ተማሪዎች የጻፏቸውን
ነገሮች ተዘርዝረዋል። ከመጀመሪያው ዝርዝር ዓረፍተነገሮች ተዘዋውረው ይመልከቱ፤
ቀጥሎ ነጠላሠረዝ እንጠቀማለን።አያልነሽነና የተወሰኑ ተማሪዎች የጻፏቸውን ዓረፍተነገሮች
ሐዋ የሚለው ግን በ“እና” ስለተያያዙ ነጠላ ሰሌዳው ላይ እንዲጽፉ ያድርጉ።)
ሠረዝ አያስፈልግም።] [ተ. የጻፏቸውን ዓረፍተነገሮች ሰሌዳ ላይ
መ. በሁለተኛው ባዶ ቦታ መግባት ያለበት ይጽፋሉ።]
ሥርዓተነጥብስ ምንድን ነው? (መ.የሥርዓተነጥብ ስህተት ካለ በማስተካከል
[መተ. አራት ነጥብ (።)] (አንድ ተማሪ ወጥቶ/ታ ግብረመልስ ይስጡ።)
ሰሌዳው ላይ ከተጻፈው ዓረፍተነገር ውስጥ
ሥርዓተነጥቡን እንዲያስገባ/እንድታስገባ
ያድርጉ።)
መ. አራት ነጥብ በዓረፍተነገሩ መጨረሻ
የተጠቀምነው ለምን ይመስላችኋል?
[መተ. ምክንያቱም የዓረፍተነገሩ ሀሳብ

6 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፮


አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) (መ.ተማሪዎች ምንባቡን የሚያነቡበት 2 ደቂቃ
ይስጧቸው።ተማሪዎች ማንበብ ሲጀምሩ
ሐዋና ጓደኞቿ ሰዓት ይያዙ፤ አንድ ተማሪ ሲያነብ/ስታነብ
ሌላው/ዋ ስህተቶችን ይመዝግብ/ትመዝግብ፣
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
2 ደቂቃ ሲሞላ ያስቁሙ፤ይህንኑ ተመሳሳይ
ማስታወሻ ተግባር ያላነበቡ ተማሪዎች በ2 ደቂቃ ውስጥ
እንዲያነቡ ያድርጉ። በመጨረሻም ተማሪዎቹ
አቀላጥፎ ማንበብ ቃላትን፣ ሐረጋትንና ያነበቧቸውን ቃላት ብዛትና የተሳሳቷቸውን
ዓረፍተነገሮችን በትክክል ማንበብ፣ በሐረጋት የቃላት ብዛት እንዲቆጥሩ ያድርጉ። ከዚያም
መካከል አጭር ዕረፍት፣ በዓረፍተነገር መጨረሻ ተማሪዎቹ የመዘገቧቸውን ወረቀቶች
ሙሉ ዕረፍት በማድረግ፣ እንደታሪኩ ሁኔታ ይሰብስቡና ጥቂት ስህተት የሠሩትንና ብዙ
በሐዘንና በደስታ፣ በአድናቆትና በማንኳሰስ ስህተቶች የሠሩትን አንባቢዎች ይለዩ።
ወዘተ. በተገቢው ፍጥነት ሳይሳሳቱ ማንበብን ይህን የመጨረሻውን ተግባር ከክፍል ውጪ
ይመለከታል። ሊያደርጉት ይችላሉ።)

ሥሩ ማዳመጥ (15 ደቂቃ)


መ. ዛሬ ባለፈው ክፍለጊዜ ካነበብነው ምንባብ ሠላምታ መቼና እንዴት?
የመጀመሪያዎቹን ሁለት አንቀጾች በማንበብ
እንለማመዳለን። ባለፈው ጊዜ “ሐዋና
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
ጓደኞቿ” የሚል ምንባብ አንብበን ነበር፤ ልሥራ
ታሪኩን አስታውሳችሁ ንገሩኝ። መ. ተለያይተን በተገናኘን ቍጥር ሠላምታ
[ተ. የሚያስታውሱትን ይናገራሉ።] እንለዋወጣን። ለምሳሌ እኔ ወደእናንተ
ክፍል ስገባ “እንደምን አደራችሁ?” ወይም
መ. በጣም ጥሩ! “እንደምን ዋላችሁ?” እላለሁ። “እንደምን
ማንበብ (8 ደቂቃ) አደራችሁ?” የምለው ጧት ስንገናኝ ነው።
“እንደምን ዋላችሁ?” የምለው ከሰዓት በኋላ
ልሥራ ስንገናኝ ነው።
መ. አሁን “ሐዋና ጓደኞቿ” በሚል ርዕስ ከቀረበው
መ. ረፋድ ላይ ስንገናኝ ምን እላለሁ?
ምንባብ ውስጥ የመጀመሪያውን አንቀጽ እኔ
አነብላችኋለሁ። እኔ ሳነብ እናንተ አንቀጹን [መ. ረፋድ ላይ ስንገናኝ “እንደምን አረፈዳችሁ?”
በዝምታ ንባብ እያነበባችሁ ተከታተሉኝ። እላለሁ።]
(መምህር የመጀመሪያውን አንቀጽ ድምፅ
መ. ያገኘሁት/ኋት አንድ ተማሪ ብትሆን/ቢሆንስ?
በማሰማት ያንብቡላቸው።)
[መ. “እንደምን አረፈድሽ/ህ?” እላለሁ።]
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ ይህንኑ አንቀጽ አብረን መ. ሳንገናኝ ከርመን ትምህርትቤት ሲከፈት
እናንብብ። (መምህር አንቀጹን ተማሪዎች መስከረም ላይ ተገናኘን። ተነፋፍቀን ነበር
ከርስዎ ጋር ድምፅ እያሰሙ እንዲያነቡ የተገናኘነው። ስለዚህ በዚህ ጊዜ ስንገናኝ ምን
ያደርጉ።) እላለሁ?

ሥሩ [መ.ተለያይተን ስለከረምን፣ እንደምን ሰነበታችሁ?


ደህና ናችሁ ወይ? ቤተሰቦቻችሁ ደህና ናቸው
መ. ተማሪዎች አሁን ጥንድ ጥንድ በመሆን
ወይ? ክረምቱን እንዴት አሳለፋችሁ?...”
ተራበተራ እኔ ያነበብኩትን አንቀጽ
እላለሁ።]
ደግማችሁ ታነባላችሁ። አንድ ተማሪ
ስታነብ/ሲያነብ ሌላው/ዋ ጓደኛ ምን ያህል እንሥራ
ቃላት እንደተሳሳተ/ች፣ ሥርዓተነጥቦቹን መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። ባለፈው
በአግባቡ ጠብቆ/ቃ ማንበቡን/ቧን ተከታተል/ ክፍለጊዜ ባነበባችሁት ምንባብ፣ ሰዎች ጧት፣
ተከታተይ።

፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 7


ቀንና ማታ የሚለዋወጧቸው የሠላምታ ማዳመጥ (5 ደቂቃ)
ዓይነቶች ምን ምን እንደሆኑ ተገንዝባችኋል።
ዛሬ ደግሞ “የሠላምታ አቀራረብ ከጊዜ ማስታወሻ
አንፃር” የሚለውን ምንባብ ከማዳመጣችሁ የሚከተሉት የአዳምጦ መረዳት መርሆች
በፊት ጥቂት የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎችን ናቸው።
አብረን እንሥራ።
1 ሙሉ ትኩረትን በሚደመጠው ነገር ላይ
መ. ለረጅም ጊዜ ተለያይተው የቆዩ ሰዎች ማድረግ፣
ሠላምታ የሚለዋወጡት እንዴት ነው?
2 ዋናዋና ነጥቦችን በማስታወሻ መመዝገብ፣
[መተ. እንደምን ሰነበትክ? እንደምን ከረምክ?
እንደምን ሰነበቱ? እንደምን ከረምሽ? 3 ዋናውን ሀሳብ ከዝርዝር ሀሳቦች መለየት፣
እንደምን ሰነበታችሁ?] 4 የሚደመጠውን ነገር አጠቃላይ መልዕክት
መ. በሠላምታ ልውውጥ ሂደት ደህንነቱን/ቷን ለመረዳት መጣር፣
የተጠየቀው/ችው የሚሠጠው /የምትሰጠው 5. የሚደመጠውን ምንባብ አቀራረብ
ምላሽ ምንድን ነው? የሚያመለክቱ አያያዥ ቃላትን በትኩረት
[መተ. እግዚአብሔር ይመስገን፣ አልሃምዱሊላህ፣ መከታተል። ለምሳሌ በትረካ ጽሑፍ
ደህና ነኝ] በመጀመሪያ፣ ከዚያም፣ ቀጥሎ የመሳሰሉት
አያያዥ ቃላት የታሪኩን አካሄድ
ሥሩ ይጠቁማሉ።
መ. አሁን የእናንተ ተራ ነው። ሁለት ሁለት
እየሆናችሁ፣ ለረጅም ጊዜ ተለያይተው
እንደቆዩ ጓደኞሞች በመሆን፣ ሠላምታ ሥሩ
ተለዋወጡ። መ. ሦስት ኮኮቦች ባሉበት ላይ ንባብዎን አቁመው
የማዳመጥ ሂደት ጥያቄ ይጠይቁ።
(መ. የተወሰኑ ተማሪዎች ጥንድ ጥንድ እየሆኑ
ለረጅም ጊዜ ተለያይተው እንደከረሙ መ. ***ስንት የሠላምታ ዓይነቶች አሉ?***
ጓደኞሞች መስለው፣ ከተማሪዎች ፊት [ተ. አራት]
ለፊት ወጥተው፣ የሠላምታ ልውውጥ ሂደቱን
እንዲያቀርቡ ያድርጉ። ይህ ተግባር ግን መ. ምን ምን?
ረጅም ጊዜ መውሰድ የለበትም፤ ጥቂት [ተ. የመሰንበቻ፣ የመልካም ምኞት፣ የበዓላት፣
ተማሪዎች ብቻ ለ2 ደቂቃ ያህል እንዲያቀርቡ የአክብሮት]
ያድርጉ።)
መ. በጣም ጥሩ! በሚገባ አዳምጣችኋል። አሁን
መ. ተማሪዎች አሁን “ሠላምታ መቼና እንዴት?” ደግሞ የሚቀጥለውን ክፍል በደንብ አዳምጡ።
የሚለውን ምንባብ አነብላችኋላሁ። እናንተ (ንባቡን ይቀጥሉ)
ደግሞ ሙሉ ትኩረታችሁን ሰብስባችሁ
አዳምጡ። ሠላምታ መቼና እንዴት ?
ፎዚያና ሸዋነሽ በጋራ ለማጥናት በነሸዋነሽ ቤት
ተገናኝተዋል። የሚያጠኑት የትምህርት ዓይነትም
የአማርኛ ቋንቋ ነው። የመወያያ ርዕሳቸው ደግሞ
“ሠላምታ” የሚል ነው። ለውይይት እንዲረዳቸው
ሸዋነሽ ሦስት ጥያቄዎችን ይዛ ቀርባለች።
ጥያቄዎቹም “አንደኛ የሠላምታ ዓይነቶች ምን
ምን ናቸው? ሁለተኛ ሠላምታ ከጊዜ አንጻር
ምን ምን ተብሎ ይከፈላል? ሦስተኛ የሠላምታ

8 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፰


መተላለፊያ መንገዶች ምን ምን ናቸው?” መንገዶችም ጽሑፍ፣ ንግግርና አካላዊ ንክኪ
የሚሉት ናቸው። ናቸው። በጽሑፍ ሠላምታ ለማስተላለፍ በጣም
ለመጀመሪያው ጥያቄ መልስ የሰጠችው ፎዚያ የተለመደው ደብዳቤ ነው። ሆኖም የዘመኑ
ናት። እንዲህ በማለትም ገለጸች። “ብዙ ቴክኖሎጅ በወለዳቸው ሞባይሎች ወይም
የሠላምታ ዓይነቶችን መጥቀስ ይቻላል። ለአሁኑ ኮምፒዩተሮች አጫጭር የጽሑፍ መልዕክቶችን
አራቱን ብቻ ልንገርሽ፣ ቀሪዎቹን በሌላ ጊዜ በመጻፍ ሠላምታ መለዋወጥ ይቻላል። ሠላምታ
እነግርሻለሁ።” አለች። በመቀጠልም “አንደኛው በቃል የሚተላለፈው በአብዛኛው ሰዎች ፊት
የሠላምታ ዓይነት፣ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ለፊት ሲገናኙ ወይም በቅርብ ርቀት ሲተያዩ
ለረጅም ጊዜ ተለያይተው ሲገናኙ ናፍቆታቸውን ነው። ሆኖም በጣም በርቀት የሚኖሩ ሰዎች
የሚገልጹበት የናፍቆት ሠላምታ ነው። ሁለተኛው እንደስልክ ባሉ ዘመናዊ መሣሪያዎች በቃል
የሠላምታ ዓይነት የመልካም ምኞት መግለጫ ሠላምታ ሊለዋወጡ ይችላሉ። በአካል ንክኪ
የሚባለው ነው። ይህም በብሔራዊና በሃይማኖታዊ ሲባል ደግሞ ሰዎች በአካል ተገናኝተው ጉንጭ፣
በዓላት ጊዜ የሚቀርብ ሠላምታ ነው። ማለትም ወይም ግንባርን፣ ወይም አንገትን፣ ወዘተ.
በዘመን መለወጫ፣ በአድዋ፣ በገና፣ በመውሊድ፣ በመሳሳም የሚከወን ነው” በማለት አስረዳች።
ወዘተ. በዓላት ጊዜ የሚቀርብ ነው። ሦስተኛው ጊዜው መሽቶ ስለነበርም ቀሪውን በሌላ ጊዜ
የሠላምታ ዓይነት የአክብሮት ሠላምታ ነው። ለመወያየት ተስማምተው ተለያዩ።
ለአረጋውያን፣ ለባለስልጣናት፣ ለሃይማኖት አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ)
አባቶችና ለወላጆች የሚቀርብ ሠላምታ ነው።
እንሥራ
አራተኛው ዓይነት ደግሞ የደህንነት ሠላምታ
መ. ያነበብኩላችሁን ምንባብ አዳምጣችኋል።
ነው። ይህም የሰዎችን የጤንነት ሁኔታ ለማወቅ
አሁን፣ በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን
የሚቀርብ ሠላምታ ነው።” አለች።
የሚገኙትን የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎች
***ስንት የሠላምታ ዓይነቶች አሉ?*** በቃላችሁ ትመልሳላችሁ። ከዚያ በፊት ግን
“የሁለተኛውን ጥያቄ መልስ ደግሞ እኔ ልንገርሽ” ሁለቱን ጥያቄዎች አብረን እንሥራ።
አለች፣ ሸዋነሽ። መ. የሠላምታ አጠቃቀሞች ከጊዜ አንፃር ምን
ፎዚያም “ቀጥይ፣ ግን እንደኔ አብራርተሽ ማቅረብ ምን ተብለው ተዘርዝረዋል?
አለብሽ” አለች፣ ፈገግ ብላ። [መተ. የጧት፣ የረፋድ፣ የቀን፣ የማታ፣ የመሰንበቻ]
ሸዋነሽም፣ “እንዳቺ አድርጌ እንኳን አላቀርበውም፤ መ. በጣም ጥሩ ነው!
ሆኖም ልሞክር” አለች። በመቀጠልም “ሠላምታን
ከጊዜ አንጻር በአምስት ከፍሎ ማቅረብ ይቻላል። ሥሩ
እነሱም አንደኛው፣ ተለያይተው ያደሩ ሰዎች መ. ከቀኑ 7 ሰዓት የተገናኙ ሰዎች የሚያደርጉት
የሚያቀርቡት የጧት ሠላምታ የሚባለው ነው። የሠላምታ ልውውጥ ምን ይባላል?
ሁለተኛው ከጧት 4 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት
[ተ. የቀትር ሠላምታ]
አካባቢ የሚገናኙ ሰዎች የሚያቀርቡት የረፋድ
ሠላምታ ነው። ሦስተኛው ከ6 ሰዓት በኋላ መ. ይህን ምላሽ እንዴት ልትሰጡ ቻላችሁ?
እስከ 12 ሰዓት አካባቢ የሚቀርበው የቀትር [ተ. ሦስተኛው የቀትር ሠላምታ መሆኑ በምንባቡ
ሠላምታ ነው። አራተኛው ጀንበር ከጠለቀች ውስጥ ተገልጿል። ቀትር ማለት ደግሞ
ወይም ከ12ሰዓት በኋላ የሚቀርበው የምሽት እኩለቀን ማለት ነው፤ 7 ሰዓት እኩለቀን
ሠላምታ ነው። አምስተኛው ለረጅም ጊዜያት ስለሆነ፣ በዚህ ሰዓት የቀትር ሠላምታ
ተለያይተው የተገናኙ ሰዎች የሚጠቀሙበት ይቀርባል ማለት ነው።]
የመሰንበቻ ወይም የክራሞት ሠላምታ ነው”
በማለት ማብራሪያዋን አጠናቀቀች። (መ.በዚህ ዓይነት የቀሩትን ጥያቄዎች እየጠየቁ
ተማሪዎቹ እንዲመልሱ ያድርጉ። ተማሪዎች
“ሦስተኛውን ጥያቄ ደግሞ አንቺ አስረጅኝ”
ምላሽ ከሠጡ በኋላ ግብረመልስ ይስጧቸው።)
በማለት ሸዋነሽ፣ ፎዚያን ጋበዘቻት።
ፎዚያም፣ “ካልሽ እሺ!” ካለች በኋላ “ሠላምታ
በሦስት መንገዶች ይተላለፋል። መተላለፊያ

፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 9


ሰዋስው (10 ደቂቃ) የተለያየ መልስ ሊሰጡ ይችላሉ)

የተጸውዖ ስም መ. በጣም ጥሩ! “አባይ” በሚለው ቃል ዓረፍተነገር


እንመሥርት።
ልሥራ
[መተ. ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ታላቁን
መ. ተማሪዎች፣ ዛሬ የምንማረው ስለስም ነው።
የህዳሴ ግድብ እየገነባች ነው።]
ስም የአንድ ነገር፣ ሰው፣ እንስሳ ወይም ቦታ
መጠሪያ ነው። ብዙ ዓይነት ስሞች አሉ። እኔ መ. በጣም ጥሩ!
የማውቃቸውን ስሞች ልንገራችሁ። ለምሳሌ
ሥሩ
ከሰው ስም፣ ሐዋ፣ ጀማል፣ አበበ፣ ከበደ፣
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን፣
ጣይቱ፣ ሰናይት ወዘተ. የቦታ/የከተማ ስሞች
በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኘውን
ደግሞ ጎጃም፣ ጎንደር፣ ወሎ፣ ሸዋ፣ አዲስ አበባ
ተግባር በምሳሌው መሠረት ሥሩ።
ወዘተ. አባይ፣ አዋሽ፣ ገናሌ የመሳሰሉትን
የወንዝ ስሞችንም አውቃለሁ። ጣና፣ ዝዋይ፣ (መ.ተማሪዎች የሚያውቋቸውን የሰው፣ የወንዝ፣
ሻላ የመሳሰሉ የሐይቅ ስሞችም አሉ። የሐይቅ፣ የቦታ ወይም የከተማ ስሞች
በደብተራቸው ሠንጠረዥ አዘጋጅተው
እንሥራ እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ለእያንዳንዱ የስም
መ. የአንድ ሰው የግል መጠሪያ የሆነ ስም አብረን ዓይነት ከስምንት ያላነሱ ስሞችን ይዘርዝሩ)
እንጥራ።
(መ. ተግባሩን ለማሠራት 5 ደቂቃ ይስጧቸው።
[መተ. ተማሪዎች የተለያዩ ስሞችን ይጠራሉ] ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ በክፍሉ ውስጥ
(መ. ተማሪዎች የራሳቸውን ስም እንዲናገሩ እየተዘዋወሩ በአግባቡ መሥራታቸውን
ማድረግ ይችላሉ።) ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤
በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር
መ. አሁን ደግሞ የምታውቋቸውን ቦታዎች/
ይወያዩ። ተግባር ሁለትን ደግሞ የቤትሥራ
ከተማዎች ስም ንገሩኝ።
እንዲሠሩ ይንገሯቸው።)
[መተ. የተለያዩ የቦታና ከተሞች ስም ይጠራሉ።]
(መ.ተማሪዎች የመጡበት/የሚኖሩበትን አካባቢ
ስም መጠየቅም ይችላሉ።)
መ. አሁን፣ የምታውቋቸውን የወንዝ፣ የተራራ፣
የሐይቅ ስሞች ንገሩኝ።
[መተ. ተማሪዎች የሚያውቋቸውን የወንዝ፣
የተራራ፣ የሐይቅ ስም ይዘረዝራሉ።]
መ. ከላይ እንደዘረዘርናቸው ያሉ የሰው፣ የቦታ፣
የወንዝ፣ የባህር፣ የሐይቅ፣ የተራራ እንዲሁም
የውቅያኖስ የግል መጠሪያ የሆኑ ቃላት
የተጸውዖ ስም ይባላሉ።
መ. ስለዚህ የተጸውዖ ስም ለአንድ ተለይቶ
ለሚታወቅ ነገር የግል መጠሪያ ወይም
መታወቂያ የሚሆን ቃል ነው።
መ. አሁን አንድ የሰው ስምና አንድ የወንዝ ስም
እንውሰድና ዓረፍተነገሮች እንመሥርት።
በመጀመሪያ “ሐዋ” በሚለው ስም ዓረፍተነገር
እንመሥርት።
[መተ. ሐዋ ትጉህ ተማሪ ናት።] (ተማሪዎች

10 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፲


ይመስለኛል። ሥዕሉንና ርዕሱን በአንድነት
2ኛ ሳምንት ታማኝነት ስመለከት ከዛፍ ላይ ያለው ልጅ የተኛውን
ልጅ የከዳው ይመስለኛል። ስለሆነም ምንባቡ
ስለማይተማመኑ ጓደኛሞች የሚገልጽ ነው
4ኛ ቀን ለማለት እችላለሁ።
የዕለቱ ትምህርት ይዘት እንሥራ
• ማንበብ መ አሁን ደግሞ በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን፣
በቅድመንባብ ሥር የ“ለ”ን ጥያቄ በቃላችሁ
መልሱ።
የቤትሥራ (10 ደቂቃ)
ሥሩ መ. “ለጓደኛ አለመታመን” ከሚለው ርዕስና
ከሥዕሉ በመሳነት ምንባቡ ስለምን የሚያወሳ
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ የሠጧቸውን የቤትሥራ
ይመስላችኋል?
እንዲያቀርቡ ያድርጉ። በመጀመሪያ
ተማሪዎች የቤትሥራውን የሠሩ መሆናቸውን [ተ. ስለታማኝነት፣ በጓደኛው ላይ ክህደት
ያረጋግጡ። ስለፈፀመ ሰው ታሪክ ወዘተ. የሚያወሳ ሊሆን
ይችላል።]
መ. ከዘረዘራችኋቸው የተጸውዖ ስሞች አንዱን
ንገሩኝ። መ. ግምታችሁ ትክክል መሆን አለመሆኑን
በንባባችሁ ታረጋግጣላችሁ።
[ተ. አንድ የተጸውዖ ስም ይናገራሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በነገራችሁኝ የተጸውዖ ስም
ሥሩ
የሠራችሁትን ዓረፍተነገር ንገሩኝ። መ. አሁን ደግሞ በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን
በቅድመንባብ ሥር የ“ለ” ጥያቄ በቃላችሁ
[ተ. የሠሩትን ዓረፍተነገር ለክፍሉ ተማሪዎች መልሱ።
ያነባሉ።]
መ. “ለጓደኛ አለመታመን” ከሚለው ርዕስና
መ. በጣም ጥሩ! ከሥዕሉ በመነሳት ምንባቡ ስለምን የሚያወሳ
(መ. በዚህ ዓይነት በመልሶቹ ላይ እየተነጋገሩ ይመስላችኋል?
ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ [ተ. ስለታማኝነት፣ በጓደኛው ላይ ክህደት
ይተራረሙ፤ በመጨረሻም ተማሪዎች ስለፈፀመ ሰው ታሪክ ወዘተ. የሚያወሳ ሊሆን
ያልተስማሙባቸውን በመውሰድ ማጠቃለያ ይችላል።]
ይስጡ።)
መ. ርዕሱንና ሥዕሉን በአንድነት ስትመለከቱ
ምንባቡ ስለምን የሚገልጽ ይመስላችኋል?
ማንበብ (30 ደቂቃ)
[ተ. የተለያዩ ግምቶች ይሰጣሉ።]
ለጓደኛ አለመታመን
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
ልሥራ
መገመት
መ. ተማሪዎች ዛሬ “መልሶ ማንበብ” የሚባለው
ልሥራ ራስን የመገምገሚያ ስልት ተግባራዊ
መ. ዛሬ “ለጓደኛ አለመታመን” በሚል ታደርጋላችሁ። መልሶ ማንበብ ማለት አንድን
ርዕስ የቀረበ ምንባብ አነባለሁ። ርዕሱን ምንባብ በምታነቡት ጊዜ ያነበባችሁት ክፍል
ስመለከተው ስለማይተማመኑ ጓደኛሞች ያልገባችሁ መስሎ ሲታያችሁ እንደገና
የተጻፈ ይመስለኛል። ግምቴን የበለጠ ተመልሳችሁ በማንበብ መረዳታችሁን
ለማጠናከር ሥዕሉን ልመልከት። ሥዕሉን የምታረጋግጡበት ስልት ነው። ይህ ስልት
ስመለከተው አንበሳ ሊበላው ሲል ፈርቶ የተኛ እንዴት እንደሚተገበር አንብቤ ላሳያችሁ።
ልጅ ይታየኛል፤ ሌላው ልጅ ደግሞ ከዛፍ ላይ (መ. ሁለተኛውን አንቀጽ ድምፅዎን እያሰሙ
ተቀምጧል። ስለሆነም ጓደኛውን ጥሎት የሸሸ

፲፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 11


ያንብቡላቸው።) [መተ. በሁለተኛው አንቀጽ ውስጥ “ሁለቱ
ጓደኛሞች ራቅ ወዳለ ቀበሌ ሲሔዱ በድንገት
መ. እንደሞተ ሰው ሆኖ በመሬት ላይ ተኛ።
አንበሳ አጋጠማቸው” ይላል።]
እንዴ! አንበሳው ቢበላውስ? ለምን ሮጦ
አላመለጠም? ወይም እንደጓደኛው ዛፍ ላይ ሥሩ
አልወጣም? የሆነ ሳልረዳው ያለፍኩት ነገር መ. ተማሪዎች አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው
አለ ማለት ነው። ስለዚህ አንቀጹን ደግሜ ቀን የቀረቡትን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች
ማንበብ አለብኝ። መልሱ።
(መ.አንቀጹን ደግመው ያንብቡ።) መ. ሁለቱ ጓደኛሞች ያልተጠበቀ ክስተት
መ. አሃ…! አሁን ገባኝ። አንደኛው እግሩ ሲያጋጥማቸው ምን አደረጉ?
በመኪና አደጋ ተጎድቶ ስለነበረ ነው ሮጦ [ተ. ደረጀ ከዛፍ ላይ ሲወጣ፣ በላይ ደግሞ የሞተ
ያላመለጠው። መስሎ መሬት ላይ ተኛ።]
ሥሩ መ. ይህን መልስ እንዴት ልታገኙ ቻላችሁ?
መ. እኔ እንዳደረኩት ያልገባችሁ ነገር [ተ. አንቀጽ ሁለት ላይ ደረጀ ባልንጀራውን ትቶ
ሲያጋጥማችሁ ደግማችሁ እያነበባችሁ ድምፅ ዛፍ ላይ መውጣቱ፣ በላይ ደግሞ የሞተ ሰው
ሳታሰሙ በትኩረት አንብቡ። መስሎ መሬት ላይ መተኛቱ ተጠቅሷል።]
(መ. ሁለቱን አንቀጾች አንብበው እንደጨረሱ (መ. ጥያቄዎቹን እያነበቡላቸው ወይም
መጽሐፋቸውን እንዲያጥፉ ያድርጉ ተማሪዎችን እያስነበቡ በቃላቸው ምላሽ
የሚከተለውን ጥያቄ ይጠይቋቸው።) እንዲሰጡ ያድርጉ። የተማሪዎችን ምላሽ
መ. በሁለቱ አንቀጾች ውስጥ የተከናወኑትን ከአዳመጡ በኋላ ግብረመልስ ይስጡ።)
ድርጊቶች በቅደምተከተል ከጎናችሁ ላለ/ች
ልሥራ
ተማሪ ተናገሩ።
መ. “ለጓደኛ አለመታመን” በሚል ርዕስ የቀረበ
[ተ. በአንቀጾቹ የተከናወኑ ድርጊቶችን ትረካ አንብባችኋል። በትረካው ውስጥ
በቅደምተከተል ይናገራሉ።] ገፀባህርያት፣ መቼትና ድርጊቶች የሚባሉ
መ. ይህን ማድረግ ካልቻላችሁ አንቀጾቹን መሠረታዊ ነገሮች ይገኛሉ። ገፀባህርይያት
ደግማችሁ አንብቡ። በታሪኩ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ወይም
እንስሳት ናቸው። መቼት ታሪኩ የተፈፀመበት
[ተ. ድርጊቶቹን በቅደምተከተል መናገር ያልቻሉ ጊዜና ቦታ ነው። ድርጊት ደግሞ ገፀባህርያቱ
ደግመው ያነባሉ።] የሚፈጽሙት ተግባር ነው። አሁን
ባነበባችሁት ትረካ ውስጥ ያሉትን ገፀባህርያት
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ )
መቼትና ድርጊት በትረካ የቢጋር ሠንጠረዠ
እንሥራ ውስጥ ትዘረዝራላችሁ። በመጀመሪያ ግን
መ. ምንባቡን አንብባችሁ ጨረሳችሁ? በጣም እኔ እሠራለሁ። (በመማሪያ መጽሐፍ 2ኛ
ጥሩ! አሁን በመጽሐፋችሁ የቀረቡ የአንብቦ ሳምንት፣ 4ኛ ቀን፣ በአንብቦ መረዳት ሥር
መረዳት ጥያቄዎችን ትመልሳላችሁ። የሚገኘውን ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ ይሣሉ።)
በመጀመሪያ ግን የተወሰኑ ጥያቄዎችን
መ. በታሪኩ ውስጥ ካሉት ገፀባህርያት መካከል
አብረን እንሥራ።
አንዱ ማን ነው?
መ. ግምታችሁ ትክክል ነበር?
[መ. ደረጀ ] (ገፀባህርያት በሚለው “ደረጀ” ብለው
[ተ. አዎ/አይደለም።] ይጻፉ።)
መ. ሁለቱ ጓደኛሞች ራቅ ወዳለ ቀበሌ ሲሔዱ እንሥራ
ምን አጋጠማቸው? መ. ታሪኩ የተፈጸመው መቼ ነው?
[መተ. አንበሳ] [መተ. ክረምት እንዳለፈ] (“መቼ?” በሚለው
መ. ይህን መልስ ያገኘነው እንዴት ነው? ትይዩ ይጻፉ።)

12 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፲፪


መ. ጥሩ! ገፀባህርያቱ በመጀመሪያ ያከናወኑት መ. “አገሬው” የሚለው ቃል ከምንባቡ በየትኛው
ምንድን ነው? አንቀጽ ይገኛል?
[መተ. ራቅ ወዳለ ቀበሌ ሄዱ።] (ድርጊት ከሚለው [መተ. በመጀመሪያው አንቀጽ በሦስተኛው
ሥር ይጻፉ።) ዓረፍተነገር ውስጥ]
ሥሩ መ. ጥሩ! ዓረፍተነገሩን እናንብበው።
መ. እስካሁን በሠራነው መሠረት ባነበባችሁት [መተ. አገሬው ሁሉ ጉድ እስኪል ድረስ ርስበርስ
ታሪክ ውስጥ ያሉትን ገፀባህርያት፣ መቼትና በመተሳሰብ መንፈስ ኖረዋል።]
ድርጊቶች በደብተራችሁ ባዘጋጃችሁት
ሠንጠረዥ ውስጥ ዘርዝሩ። (ይህን ተግባር መ. ስለዚህ “አገሬው” የሚለው ቃል በዚህ
የቤትሥራ ይስጧቸው።) ዓረፍተነገር ውስጥ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
[መተ. “ህዝቡ፣ የአካባቢው ሰው” የሚል ፍቺ
5ኛ ቀን አለው።]
መ. በጣም ጥሩ! “ትንፋሹን ዋጠ” የሚለው
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ዓረፍተነገር የሚገኝበትን ፈልገን እናግኝ።
• ቃላት [መተ. ሦስተኛው አንቀጽ፣ ሁለተኛው ዓረፍተነገር]
• መጻፍ መ. ጥሩ ነው! አሁን ደግሞ ቃሉ የሚገኝበትን
ዓረፍተነገር እናንብብ።
[መተ. እሱ ግን ፈጽሞ እንደሞተ ሰው ትንፋሹን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ውጦ ዝምአለ።]
ሥሩ መ. ስለዚህ “ትንፋሹን ዋጠ” ፍቺው ምንድን ነው?
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ በአንብቦ መረዳት ላይ
[መተ. ትንፋሹን አጠፋ።]
የሠጧቸውን የቤትሥራ መሥራታቸውን
ያረጋግጡ።) መ. በጣም ጥሩ!
መ. “ለጓደኛ አለመታመን” በሚል ርዕስ በቀረበው መ. አሁን ደግሞ ለተወሰኑ ቃላት ተቃራኒ ፍቺ
ምንባብ ውስጥ ታሪኩ የተፈፀመው የት ነው? በመስጠት እንለማመድ።
[ተ. ጥቅጥቅ ያለ ደን ውስጥ] መ. “መተሳሰብ” የሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺ
ምንድን ነው?
መ. በጣም ጥሩ! በቢጋር ሠንጠረዡ ውስጥ “የት”
ከሚለው ፊት ለፊት መጻፋችሁን አረጋግጡ። [መተ. መጠላላት]
(መ. በዚህ ዓይነት ከተማሪዎች ጋር በተግባሩ መ. ጥሩ! “ሩቅ” የሚለው ቃል ተቃራኒስ?
ላይ ሲነጋገሩ ተማሪዎች ደብተራቸውን [መተ. ቅርብ]
ተቀያይረው እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
ሥሩ
ቃላት (10 ደቂቃ) መ. ተማሪዎች አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው
የቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይና ተቃራኒ ቀን የሚገኘውን የቃላት ተግባር በቡድን
ፍቺ ሆናችሁ ከምንባቡ ለወጡ ቃላት ተመሳሳይ
ፍቺ በመስጠት ሥሩ። የቃላቱን ተመሳሳይ
እንሥራ ፍቺ ለመረዳት፣ በመጀመሪያ ቃላቱ
መ. ዛሬ ባለፈው ክፍለጊዜ ካነበባችሁት “ለጓደኛ ከሚገኙበት ዓረፍተነገር ሀሳብ በመነሳት
አለመታመን” ውስጥ ቃላትንና ሐረጋት የቃሉን ተመሳሳይ ፍቺ ለመረዳት ሞክሩ።
እያወጣን ተመሳሳይ ፍቻቸውን እንሰጣለን። ከዚያም የተረዳችሁትን የቃሉን ፍቺ
በመጀመሪያ ጥቂት ጥያቄዎችን አብረን በደብተራችሁ ጻፉ።
እንሥራ።
(ተማሪዎች በቡድን ሠርተው ሲጨርሱ

፲፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 13


በሚከተለው መልክ ምላሽ እንዲሰጡ ያድርጉ።) በትምህርትቤቱ
ባህርይ
መ. “ቀዬ” የሚለው ቃል በምንባቡ በየትኛው ያለው ተሳትፎ
አንቀጽ ይገኛል?
የአንደኛ ደረጃ
ሳቂታ
[ተ. በሁለተኛው አንቀጽ፣ በሁለተኛው ተማሪ
ዓረፍተነገር] የትምህርትቤቱ ታደሰ
መ. ጥሩ! ቃሉ የሚገኝበትን ዓረፍተነገር የእግርኳስ ዝነኛ ቀልድ አዋቂ
አንብቡልኝ። ቡድን አባል ነው

[ተ. ሁለቱ ጓደኛሞች ከመኖሪያ ቀያቸው አጥቂ


ተግባቢ
ራቅ ወዳለ ቀበሌ ሲሄዱ በድንገት አንበሳ ተጫዋች
አጋጣማቸው።]
መ. ስለዚህ “ቀዬ” የሚለው ቃል በዚህ ዓረፍተነገር አካላዊ ገጽታ
ውስጥ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
ቀይ
[ተ. አካባቢ፣ መንደር]
መካከለኛ ቁመት ያለው
(መ. ሌሎችንም ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት ጠንካራ
ያሠሯቸው። ተግባር ሁለትን ደግሞ
የቤትሥራ እንዲሠሩ ይንገሯቸው።)
መ. አሁን የተዘጋጀውን የቢጋር ሠንጠረዥ
በመጠቀም ለምጽፈው አንቀጽ መንደርደሪያ
መጻፍ (25 ደቂቃ)
የሚሆን ዓረፍተነገር ልመሥርት።
በገላጭ ስልት አንቀጽ መጻፍ
“ታደሰ በሚማርበት የአንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) በጣም ዝነኛ ተማሪ ነው።”
ልሥራ መ. “ዝነኛ” የሚለውን ለመንደርደሪያ ዓረፍተነገር
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ “ሐዋና ጓደኞቿ” መነሻ ያደረኩት ሌሎች በሣጥኖች ውስጥ
ከሚለው ምንባብ ውስጥ “ሐዋ” የተባለችውን የተዘረዘሩት ነገሮች ሁሉ ለዝነኛነቱ
ገፀባህርይ በመውሰድ የቢጋር ሠንጠረዥን አስተዋፅኦ ያበረከቱ ባህርያት ስለሆኑ ነው።
በመጠቀም በገላጭ ስልት አንቀጽ እንዴት እንሥራ
መጻፍ እንደሚቻል ተምረናል። ዛሬ ደግሞ
መ. በመቀጠል የታደሰን ዝነኛነት የሚያሳዩ
የቢጋር ሠንጠረዥን በመጠቀም እንዴት
ዝርዝር ሀሳቦችን አብረን እንለይ።
መንደርደሪያ ዓረፍተነገር መመሥረት
እንደሚቻልና መንደርደሪያ ዓረፍተነሩን በመጀመሪያ በቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ
በመጠቀም እንዴት ማስፋፋትና አንቀጽ የተጠቀሱትን የታደሰን ባህርያት
መገንባት እንደሚቻል አሳያችኋለሁ። ልትዘረዝሩልኝ ትችላላችሁ?
(መ. የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ በሰሌዳው [መተ. ሳቂታ፣ ቀልድ አዋቂና ተግባቢ]
ላይ ይሣሉላቸው።) መ. በጣምጥሩ! ከዚህ በመነሳት “ሳቂታ፣ ቀልድ
አዋቂና ተግባቢ በመሆኑ በርካታ ጓደኞችን
አፍርቷል” የሚል ዓረፍተነገር መመሥረት
እንችላለን።
መ. አሁን ደግሞ የታደሰን አካላዊ ገጽታ ንገሩኝ።
[መተ. ቀይ፣ መካከለኛ ቁመት ያለው፣ ጠንካራ]
መ. ጥሩ! ይህን መሰረት አድርገን፣ “ታደሰ ቀይ፣
መካከለኛ ቁመትና ጠንካራ ተክለሰውነት
ያለው፣ እግርኳስ መጫወት የሚወድ ተማሪ

14 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፲፬


ነው።” አሁን ቀደምሲል የቀረበውን የቢጋር መ. የመጀመሪያው ክፍት ቦታ ላይ የሚገባው
ሠንጠረዥ መሠረት በማድረግ የተጻፈውን ሥርዓተነጥብ ምንድ ነው?
አንቀጽ እናንብብ። የሚከተለውን አንቀጽ
[መተ. ነጠላ ሠረዝ (፣)]
ሰሌዳ ላይ ጽፈው አብረው ያንብቡ።
መ. ጥሩ! ሁለተኛው ባዶ ቦታ ላይስ?
[መተ. “ታደሰ በሚማርበት የአንደኛ ደረጃ
ትምህርትቤት በጣም ዝነኛ ተማሪ ነው። [መተ. ነጠላ ሠረዝ (፣)]
ሳቂታ፣ ቀልድ አዋቂና ተግባቢ በመሆኑ መ. በጣም ጥሩ! በመጨረሻው ክፍት ቦታ ላይስ
በርካታ ጓደኞችን አፍርቷል። ታደሰ ቀይ፣ ምን ዓይነት ሥርዓተነጥብ ይገባል?
መካከለኛ ቁመትና ጠንካራ ተክለሰውነት
የተቸረ፣ እግርኳስ መጫወት የሚወድ ልጅ [መተ. አራት ነጥብ (።)]
ነው። በትምህርትቤቱ የእግርኳስ ቡድን መ. በጣም ጥሩ!
ውስጥ አጥቂ ሲሆን ለቡድኑ በርካታ ግቦችን
በማስቆጠሩ የትምህርትቤቱ ኮከብ ተጫዋች ሥሩ
ሆኗል።”] መ. ተማሪዎች አሁን በሠራነው መሠረት በ2ኛው
ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ በአጻጻፍ ሥርዓት
ሥሩ ሥር የሚገኘውን ተግባር፣ ተገቢ የሆኑትን
መ. ተማሪዎች፣ አሁን ባለፈው ሳምንት ሥርዓተነጥቦች በማስገባት አሟሉ።
ያዘጋጃችሁትን የቢጋር ሠንጠረዥ በመጠቀም
አንቀጽ ትጽፋላችሁ። በመጀመሪያ (መ. ይህን ተግባር ተማሪዎች በደብተራቸው
ያዘጋጃችሁትን የቢጋር ሠንጠረዥ መነሻ እንዲሠሩ ያድርጉና ያርሙላቸው።
በማድረግ መንደርደሪያ ዓረፍተነገር ከዚያም ያልተሟላውን አንቀጽ በሰሌዳው
አዘጋጁ፤ ከዚያም መንደርደሪያ ዓረፍተነገሩን ላይ በመጻፍ ተማሪዎች ሥርዓተነጥቦቹን
የሚያጠናክሩ ሌሎች ዓረፍተነገሮችን በተገቢ ቦታቸው ላይ እንዲጽፉ ያድርጉ።
በመጨመር አንድ አንቀጽ ጻፉ። በመቀጠል የተሳሳቱትን ነገር እየተወያዩ
እንዲያስተካክሉት ያመቻቹ። ዓይነስውራን
(መ. መንደርደሪያ ዓረፍተነገር በመመሥረቱ ተማሪዎች ካሉ አንቀጹን እያነበቡላቸው
ላይ ሊያግዟቸው ወይም ተማሪዎቹን እየመሩ ክፍት ቦታ ያለበትንም እየጠቆሟቸው
መንደርደሪያ ዓረፍተነገሩን አዘጋጅተው በቃላቸው እንዲመልሱ ማድረግ ይችላሉ።)
መስጠት ይችላሉ። ከዚያም በመንደርደሪያ
ዓረፍተነገሩ ተመሥርተው ተማሪዎች በቡድን
አንቀጹን እንዲጽፉ ማድረግ ይችላሉ።) 6ኛ ቀን

የአጻጻፍ ሥርዓት (5 ደቂቃ) የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች


እንሥራ • አቀላጥፎ ማንበብ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለአራት ነጥብና ነጠላሠረዝ • መናገር
ምንነትና አገልግሎት ተምራችኋል። ዛሬ
• ሰዋስው
ደግሞ እነዚህን ሥርዓተነጥቦች እንዴት
መጠቀም እንዳለብን እንለማመዳለን።
ሥርዓተነጥቦች ያልተሟሉለት ዓረፍተነገር የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
አቀርብላችኋለሁ፤ በክፍት ቦታዎቹ ተገቢ
ናቸው የምትሏቸውን ሥርዓተነጥቦች አስገቡ።
ሥሩ
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ በቃላት ላይ የሠጧቸውን
መ. “አልማዝ ለሰርጉ መደገሻ የሚሆኑ ጋኖች የቤትሥራ መሥራታቸውን ያረጋግጡ።)
___ ምጣዶች ___ ድስቶችና ሌሎች
ቁሰቁሶችን ከጎረቤቶቿ ተዋሰች ___” መ. “ከመቅፅበት” ለሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺውን
በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ተገቢዎቹን ንገሩኝ።
ሥርዓተነጥቦች እናስገባ። [ተ. ዘግይቶ]

፲፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 15


መ. በጣም ጥሩ! ቃሉ በየትኛው አንቀጽ ውስጥ ተማሪዎች ከርስዎ ጋር በጋራ ድምፅ እያሰሙ
ይገኛል? እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. በሁለተኛው] ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ! መ. ተማሪዎች ሦስት ሦስት ሆናችሁ አብረን
ያነበብነውን ምንባብ ተራበተራ ድምፅ
(መ.በዚህ ዓይነት በተግባሩ ላይ እየተነጋገሩ እያሰማችሁ ታነባላችሁ። አንዳችሁ
ደብተራቸውን ተለዋውጠው እንዲያርሙ በምታነቡት ጊዜ አንዳችሁ ደግሞ ጓደኛችሁ
ያድርጉ፤ በመጨረሻም ስህተት በሠሩባቸው በማመሳከሪያ ሠንጠረዡ መሠረት ምን
ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ በመስጠት እንደተሳሳተ/ች ትመዘግባላችሁ።
ግብረመልስ ይስጡ።)
(መ.ተማሪዎች ለሚያነቡበት 2 ደቂቃ
መልሶቹ በቅደምተከተል ድርግም፣ ማመን፣ ይስጧቸው። ማንበብ ሲጀምሩ ሰዓት
ደስታና፣ ቀና አለ ናቸው። ይያዙላቸው። 2 ደቂቃ ሲሞላ ያስቁሙ።
የተማሪዎችን የስህተት መመዝገቢያ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) በመጨረሻ ያሰባስቡ። ከዚያም ጥሩ የማንበብ
ችሎታ ያላቸውንና የሌላቸውን ተማሪዎች
ለጓደኛ አለመታመን በመለየት ጥሩ ያነበቡትን ያበረታቱ፤ ጥሩ
ቅድመንባብ ያላነበቡትን ሌላ የመለማመጃ ስልት/ጊዜ
መ. ባለፈው ሳምንት “ሐዋና ጓደኞቿ” በሚል ያዘጋጁላቸው።)
ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ጥንድ ጥንድ
ሆናችሁ ድምፅ በማሰማት የማንበብ የማመሳከሪያ ሠንጠረዥ
ልምምድ አድርጋችኋል። ዛሬ ደግሞ “ለጓደኛ
የፊደል ግድፈት ተቆራርጠው በትክክል
አለመታመን” የሚለውን ምንባብ በመጠቀም
የተፈጸመባቸው የተነበቡ ያልተነበቡ
የማንበብ ልምምዳችሁን ትቀጥላላችሁ። ከዚያ
ቃላት ብዛት ቃላት ብዛት ሥርዓተ
በፊት ግን የሚከተለውን ጥያቄ መልሱ።
ነጥቦች ብዛት
ደረጀ በጓደኛው ላይ ክህደት የፈጸመው
ለምንድን ነው?
[መተ. በጉዞ ላይ እያሉ ድንገት አንበሳ መናገር (15 ደቂቃ)
ስለመጣባቸውና ደረጀ የራሱን ህይወት ብቻ እንሥራ
ለማትረፍ በማሰቡ።]
መ. ተማሪዎች ዛሬ ባለፈው ጊዜ ባነበባችሁት
ማንበብ (8 ደቂቃ) “ለጓደኛ አለመታመን” በሚል ርዕስ ከቀረበው
ምንባብ በወጡ የመወያያ ጥያቄዎች ላይ
ልሥራ
ትወያያላችሁ። ከዚያ በፊት ግን በአንድ
መ. በመጀመሪያ “ለጓደኛ አለመታመን” ከሚለው
ጥያቄ ላይ አብረን እንወያይ።
ምንባብ አንደኛውን አንቀጽ አነብላችኋላሁ።
እኔ ሳነብ እናንተ የአነባበብ ፍጥነቴን፤ መ. ደረጀ ጓደኛውን ጥሎ ዛፍ ላይ መውጣቱ ተገቢ
የአነባበብ ትክክለኛነቴን፣ ሥርዓተነጥቦች ይመስላችኋል? በመጀመሪያ ተገቢ ነው የምትሉ፣
ካሉበት ቦታ የማደርገውን ቆምታና የድምፅ ተገቢ ነው ያላችሁበትን ምክንያት ንገሩኝ።
ሁኔታ ወዘተ. እያስተዋላችሁ፣ ድምፅ ሳታሰሙ [መተ. ምክንያቱም ደረጀ ዛፍ ላይ ባይወጣ
እያነበባችሁ ተከታተሉኝ። አንበሳው ይበላው ነበር።] (ተማሪዎች
(መ.“ለጓደኛ አለመታመን” ከሚለው ምንባብ የተለያየ መልስ ሊሠጡ ይችላሉ።)
አንደኛውን አንቀጽ ድምፅ እያሰሙ መ. አሁን ደግሞ ተገቢ አይደለም የምትሉ፣ ተገቢ
ያንብቡላቸው።) አይደለም ያላችሁበትን ምክንያት ንገሩኝ።
እንሥራ [መተ. ምክንያቱም በችግር ጊዜ ጓደኛን ችግር
መ. በመቀጠል አሁን ያነበብኩትን ምንባብ ላይ ጥሎ መሸሽ ተገቢ ስላልሆነ ነው።]
አብረን እናንበው። (መምህር አሁን ደግሞ

16 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፲፮


(መ. ተማሪዎች ሀሳባቸውን በተለየ መንገድ የሆኑ ነገሮች በጋራ የሚጠሩበትን ስም
ሊገልፁ ይችላሉ።) የሚይዝ ንዑስ ክፍል ነው።
ሥሩ እንሥራ
መ. ተማሪዎች አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው መ. አሁን የምታውቋቸውን የቤት እንስሳት ስም
ቀን “በመናገር” ንዑስ ክፍል ሥር በቀረቡት ንገሩኝ።
የመወያያ ጥያቄዎች ላይ በቡድን ተወያዩ።
[መተ. በግ፣ ፍየል፣ ላም…]
ከዚያም በቡድን ተጠሪያችሁ አማካይነት
ሀሳባችሁን ለክፍል ጓደኞቻችሁ አቅርቡ። መ. አሁን ደግሞ የምታውቋቸውን የዱር እንስሳት
ስም ንገሩኝ።
(መ.ተማሪዎች ሲወያዩ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ
ተማሪዎችን በመጠየቅና ፍንጭ በመስጠት [መተ. ቀበሮ፣ ዝሆን፣ የሜዳ አህያ…]
ውይይታቸውን እንዲቀጥሉ ያበረታቱ። መ. በጣም ጥሩ! አሁን እንደዘረዘራችኋቸው ያሉ
በመጨረሻም ከየቡድኑ አንዳንድ ተጠሪዎችን ነገሮች በጋራ የሚጠሩበት የስም ዓይነት ምን
አስነስተው የቡድናቸውን ሀሳብ እንዲያቀርቡ ይባላል?
ያድርጉ።)
[መተ. የወል ስም]
ሰዋስው (10 ደቂቃ) መ. በጣም ጥሩ!
የወል ስም ሥሩ
ልሥራ መ. ተማሪዎች በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን፣
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለተጸውዖ ስሞች በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኘውን
ተምረናል። የምታስታውሱትን ንገሩኝ። ተግባር በምሳሌው መሠረት ሥሩ።

[ተ. የሚያስታውሱትን ይናገራሉ።] (መ.ተማሪዎች የሚያውቋቸውን የቤት እንስሳትና


የዱር እንስሳት ሠንጠረዥ በደብተራቸው
መ. እኔም የማስታውሰውን ልንገራችሁ። አዘጋጅተው እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ተግባሩን
[መ.የተጸውዖ ስም የሚባለው የሰው፣ የቦታ፣ ለመሥራት 5 ደቂቃ ይስጧቸው። ተግባሩን
የወንዝ፣ የባህር፣ የሐይቅ፣ የተራራ እንዲሁም ሲሠሩ በትክክል መሥራታቸውን እየተዘዋወሩ
የውቅያኖስ መጠሪያ ወይም መታወቂያ ያረጋግጡ፤ ለመሥራት የተቸገሩ ተማሪዎችን
የሚሆን ቃል ነው። ለምሳሌ ከሰው ስም ይደግፉ። በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ
ስንታየሁን፣ ከቦታ መቅደላን፣ ከወንዝ አባይን፣ ከተማሪዎችዎ ጋር ይወያዩ፤ እንዲሁም
ከባህር ቀይባህርን፣ ከሐይቅ ሎጎን መጥቀስ ተግባር “2”ን፣ ከዘረዘሯቸው ስሞች 5 በቤት
ይቻላል።] እንስሳት፣ 5 ደግሞ በዱር እንስሳት ስም
ዓረፍተነገሮች ቤታቸው ሠርተው እንዲመጡ
መ. ዛሬ የምንማረው ደግሞ የወል ስሞችን ነው። ይስጧቸው።)
በመጀመሪያ እኔ የማውቃቸውን የቤት
እንስሳትን የሚያመለክቱ የወል ስሞች
ልንገራችሁ። “ውሻ፣ በሬ፣ ላም ወዘተ.” የሚሉ
ስሞችን አውቃለሁ።
መ. አሁን ደግሞ የማውቃቸው የዱር እንስሳትን
የሚያመለክቱ የወል ስሞች ልንገራችሁ።
“አንበሳ፣ ነብር፣ ጅብ…”
መ. በሬ፣ ውሻ፣ ነብር፣ ጅብ የወል ስሞች ናቸው።
ምክንያቱም “በሬ”ን እንደምሳሌ ወስደን
ብንመለከት፣ “በሬ” የሚለው ስም በሬ የሆኑ
እንስሳት ሁሉ ከሌሎች እንስሳት ተለይተው
በጋራ የሚታወቁበት የወል ስማቸው ነው።
ስለዚህ የወል ስም የሚባለው አንድ ዓይነት

፲፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 17


እንሥራ
3ኛ ሳምንት የአቻ ግፊት መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ።
መ. ዩኒቨርሲቲ (የሚለውን ነጥለን እናንብበው)
7ኛ ቀን [መተ. ዩ-ኒ-ቨ-ር-ሲ-ቲ]
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መ. አሁን ደግሞ አጣምረን እናንብበው፤
• የቃላት ጥናት
[መተ. “ዩኒቨርሲቲ”] (ቃሉን ተማሪዎች ከርስዎ
• ማንበብ ጋር እንዲያነቡ ያድርጉ።)
መ. አሁን ደግሞ “ተጠቃሚዎቹም” የሚለውን
ቃል ነጣጥለን አብረን እናንብብ።
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
[መተ. ተ- ጠቃሚ-ዎች-ኡ-ም]
ሥሩ
(መ. ተማሪዎች በወል ስሞች የመሠረቷቸውን መ. ቃሉን አንድ ላይ (አጣምረን) እናንብብው።
ዓረፍተነገሮች እንዲያቀርቡ ያድርጉ።) [መተ. ተጠቃሚዎቹም]
መ. በዱር እንስሳትና በቤት እንስሳትም መ. በጣም ጥሩ!
የሠራችኋቸውን ዓረፍተነገሮች ለጓደኞቻችሁ
አንብቡ። ሥሩ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን
[ተ. የሠሯቸውን ዓረፍተነገሮች ለክፍል የሚገኙትን ቃላትና ሐረጋት በመነጠልና
ጓደኞቻቸው ያነባሉ።] በማጣመር አንበቡ። (ተማሪዎች እየነጠሉና
መ. በጣም ጥሩ! እያጣመሩ እንዲያነቡ ያበረታቱ፡)

የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ) ማንበብ (30 ደቂቃ)


መነጠልና ማጣመር ሱስኝነትና መዘዙ
ልሥራ ቅደመንባብ (5 ደቂቃ)
መ. ዛሬ “ሱሰኝነትና መዘዙ” በሚል ርዕስ
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት
የቀረበ ምንባብ ልታነቡ ነው። በመጀመሪያ
ግን ምንባቡን ለማንበብ እንቅፋት ልሥራ
እንዳይሆኑባችሁ ውስብስብ ቃላትና ሐረጋት መ. ዛሬ “ሱሰኝነትና መዘዙ” በሚል ርዕስ የቀረበ
ማንበብ ትለማመዳላችሁ። በመጀመሪያ ምንባብ ታነባላችሁ። ወደንባቡ ከመግባታችሁ
“ተጠቃሚዎቹም” የሚለውን ቃል ነጥዬ በፊት ግን የቅድመንባብ ጥያቄዎችን
አነባለሁ። ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ የተወሰኑ
ጥያቄዎችን እኔ እሠራለሁ። ወጣቶችን
መ. [“ተ-ጠቃሚ-ዎች-ኡ-ም”] (ቃሉን ነጣጥለው
በተለያዩ ሱሶች ውስጥ እንዲጠመዱ
በማንበብ ያሳዩ።)
የሚያደርጓቸው ምክንያቶች ምን ምን
መ. በመቀጠል አጣምሬ ሳነበው ናቸው?
[መ. “ተጠቃሚዎቹም” ይሆናል።] [መ. ወጣቶች በተለያዩ ሱሶች እንዲጠመዱ
መ. አሁን ደግሞ “ታታሪነት” የሚለውን ቃል ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች አንዱ
ነጥዬ ሳነበው የአስተዳደግ ሁኔታ ነው። ለምሳሌ ከቤተሰቡ
አባል አንዱ/አንዷ አጫሽ ከሆነ/ች ልጁም/
[መ. ታታሪ-ነት ይሆናል።] (ቃሉን ነጣጥለው ልጂቱም አጫሽ የመሆን እድሉ/ሏ ከፍተኛ
ያንብቡላቸው።) ነው።]
መ. አጣምሬ ሳነበው ደግሞ [“ታታሪነት”
ይሆናል።]

18 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፲፰


እንሥራ [ተ. ቍጥር “1” ተማሪዎች ጥያቄ ይጠይቃሉ።]
መ. አሁን ደግሞ ሌላ ወደሱስ የሚገፋፋ ምክንያት መ. ቍጥር “2” ደግሞ የተጠየቃችሁትን ጥያቄ
ንገሩኝ። መጽሐፉን ሳትመለከቱ መልሱ።
[መተ. የአቻ/የጓደኛ ግፊት] [ተ. ቊጥር “2” ተማሪዎች ጥያቄውን ይመልሳሉ።]
መ. ጥሩ! ግምታችን ትክክል መሆኑን ወይም መ. ጥያቄ መጠየቅም ሆነ መመለስ ካልቻላችሁ
አለመሆኑን በምታነቡበት ጊዜ አረጋግጡ። አንቀጹን ደግማችሁ አንብቡ።
ሥሩ (መ. 2ኛውን አንቀጽ ደግሞ ጠያቂ የነበሩትን
መ. ሥዕሉን አስተውላችሁ የተረዳችሁት መላሽ፣ መላሽ የነበሩትን ጠያቂ በማድረግ
ምንድን ነው? (ተማሪዎች እንዲገምቱ ያስነብቧቸው። በዚህ ዓይነት ሚናቸውን
ያድርጉ።አንብበው እንደጨረሱ ግምታቸውን እየተቀያየሩ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
እንዲያረጋግጡ ያድርጉ።)
15ሐ. አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
[ተ. ግምታቸውን ጽፈው ይይዛሉ።]
እንሥራ
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) መ. አንብባችሁ ጨረሳችኋል? ጥሩ! ሥዕሉን
ልሥራ በተመለከተ የየራሳችሁን ግምት ሰጥታችሁ
መ. አንድን ምንባብ ስናነብ ግልፅ ያልሆነ ነገር ነበር። ግምታችሁ ትክክል ነበር?
ሊያጋጥም ይችላል። በዚህ ጊዜ ደግሞ [ተ. አዎ! አይደለም ይላሉ።]
በማንበብ ልንረዳው እንችላለን። አንድ
መ. ትክክል የገመታችሁ በጣም ጥሩ ነው።
ምሳሌ ሠርቼ ላሳያችሁ። (3ኛውን አንቀጽ
በትክክል ያልገመታችሁ ደግሞ ትክክለኛውን
ያንብቡላቸው።)
ከምንባቡ አውቃችኋል።
መ. “…በአቻ ግፊት ወደሱስ እንደገባ
መ. አሁን ከምንበቡ የወጡ ጥያቄዎችን
አጫውቶኛል” የሚለው አገላለጽ አልገባኝም።
ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ አብረን
ምን ማለት ነው? ስለዚህ አንቀጹን ደግሜ
እንሥራ።
ማንበብ ይኖርብኛል ማለት ነው። (3ኛውን
አንቀጽ ደግመው ያንብቡላቸው።) መ. ዮሐንስ ስንት ዓመቱ ነው?
መ. አሁን ገባኝ! የመጀመሪያው ዓረፍተነገር [መተ. 25 ዓመቱ ነው፣ ምክንያቱም ዕድሜው 25
“…በጓደኞቹ ግፊት ሱሰኛ እንደሆነ መሆኑ በምንባቡ ውስጥ ተጠቅሷል።]
ይናገራል” ይላል። ሁለተኛው ዓረፍተነገርም
መ. ሱሰኞች ከገቡበት ሱስ ለመውጣት እየፈለጉ
“በዩኒቨርስቲ በመማር ላይ እያለ ያፈራቸው
ለማቆም የሚቸገሩት ለምን ይመስላችኋል?
ጓደኞቹ ገፋፍተው ሲጋራ ማጨስና ጫት
መቃም እንዳስጀመሩት ይገልፃል።” ይላል። [መተ. ለረጅም ጊዜ ልማድ ሆኖ አብሮ የኖረን
ስለዚህ የአቻ ግፊት ማለት የጓደኛ ግፊት ባህርይ በአንድ ጊዜ መተው አስቸጋሪ
ማለት ነው። መሆኑን ከቀደመ ዕውቀታችን ተነስተን
መናገር እንችላለን።]
ሥሩ
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ። “1” እና “2” ሥሩ
በማለት በቍጥር ይሠይሟቸው።) መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን
የሚገኙትን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች
መ. ሁላችሁም የመጀመሪያውን አንቀጽ ድምፅ
በቃላችሁ መልሱ።
ሳታሰሙ አንብቡ። (አንብበው እንደጨረሱ
መጽሐፋቸውን እንዲያጥፉ ያድርጉ።) መ. ዮሐንስ የጀመረውን ሥራ ሳይጨርስ
የሚጠፋው ለምንድን ነው?
መ. አሁን ቍጥር አንዶች ያነበባችሁትን
አንቀጽ በተመለከተ መጽሐፉን ሳትመለከቱ [መ. ሲጋራ ለማጨስ]
ጓደኛችሁን ጥያቄ ጠይቁ። መ. መልሱን እንዴት አወቃችሁት?

፲፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 19


[መ. የሁለተኛው አንቀጽ የመጨረሻ ዓረፍተነገር እንሰጣለን። በመጀመሪያ እኔ አሳያችኋለሁ።
“ከአፉ የሚወጣ ጠረን…” የሚለው ሐሳብ
መ. “ሱስ” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ ምንድን
ሲጋራ ሊያጨስ እንደሚወጣ አመላካች ነው።]
ነው?
(መ. በዚሁ መሠረት ጥያቄዎቹን እያነበቡላቸው፣
[መ. ልማድ]
ተማሪዎች እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ለሚሠጡት
ምላሽም ምክንያት/ማስረጃ እንዲያቀርቡ መ. መልሱን ያገኘሁት አንቀጽ አንድ ውስጥ
ያበረታቱ። በመጨረሻም ግብረመልስ ስለ“ሱስ” የሚገልጸውን ሐሳብ በመመልከት
ይስጡ።) ነው።

ልሥራ መ. “ተጎጂ” የሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺ ምንድን


መ. አሁን ደግሞ ተግባር ሁለትን ትሠራላችሁ። ነው?
በመጀመሪያ እኔ አንድ ምሳሌ ልሥራ። [መ. ተጠቃሚ፣ ምክንያቱም መጎዳቱ
በዚህ ታሪክ ውስጥ ያስደነገጠኝ ነገር አለመጠቀምን ይገልፃል።]
ሲጋራና ጫት ለሳንባ ነቀርሳ፣ ለካንሰር፣
ለደምግፊት እና ለመሳሰሉት በሽታዎች እንሥራ
የሚያጋልጡ መሆናቸው ነው። ምክንያቱም መ.አሁን አብረን እንሥራ።
እነዚህ በሽታዎች ለሞት ሊዳርጉ የሚችሉ መ.“ባህርይ” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ ምን
በሽታዎች ናቸው። በአሁኑ ጊዜ ደግሞ ሊሆን ይችላል?
በርካታ ወጣቶች ሲጋራ እንደሚያጨሱ ጫት
እንደሚቅሙ አውቃለሁ። ስለዚህ እነዚህ [መተ. ፀባይ]
ወጣቶች ከነዚህ አደገኛ ሱሶች ካልተላቀቁ መ.“ተወደደ” የሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺ ምንድን
ገና በወጣትነታቸው መቀጠፋቸው ወይም ነው?
የአልጋቁራኛ መሆናቸው አይቀርም። ይህ
ከሆነ ደግሞ ሀገራችን የልማት ቀኝ እጅ [መተ. ተጠላ]
የሆነውን ትኩስ ሀይል አጣች ማለት ነው። መ.ከላይ የቀረቡትን ቃላት ተመሳሳይም ሆነ
ሥሩ ተቃራኒ ፍቺ ስንሰጥ ለፍቺው መሠረት
ያደረግነው “ሱሰኝነትና መዘዙ” የሚለውን
መ.በምሳሌው መሠረት ካነበባችሁት ታሪክ ውስጥ
ምንባብ ነው።
ከወደዳችሁት፣ ካናደዳችሁ፣ ካሳዘናችሁ
ወይም ካስደነገጣችሁ፣ ነገር መካከል አንዱን ሥሩ
መርጣችሁ በምክንያት አስደግፋችሁ አንድ መ. አሁን የእናንተ ተራ ነው። እኔ ጥያቄውን
አንቀጽ ጻፉ። ሳነብ እናንተ መልስ ትሰጣላችሁ።
መ. “ሲጋራ” የሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ
8ኛ ቀን ምንድን ነው?
[ተ. ትምባሆ]
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. “የበለጠ” የሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺ ምንድን
• ቃላት ነው?
• መጻፍ
[ተ. ያነሰ]

ቃላት (10 ደቂቃ) መ. በጣም ጥሩ!


መ. “ወጣት” የሚለው ቃል ተቃራኒ ፍቺ ምንድን
የቃላት ተመሳሳይና ተቃራኒ ፍቺ
ነው?
ልሥራ
[ተ. ሽማግሌ፣ ባልቴት]
መ. ዛሬ ባለፈው ክፍለጊዜ ካነበባችሁት
“ሱሰኝነትና መዘዙ” ከሚለው ምንባብ ውስጥ መ. ጥሩ ነው!
ለወጡ ቃላት ተመሳሳይና ተቃራኒ ፍቺ መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን

20 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፳


የቀረቡትን የቃላት ተግባራት ሥሩ። ያሉትን ስህተቶች ትጠቁሙኛላችሁ።
(መ. የመጀመሪያውን ተግባር የክፍልሥራ ታደሰ በሚማርበት የአንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት
ይስጧቸው። ተማሪዎች ከሠሩ በኋላ በጣም ዝነኛ ተማሪ ነው። ሳቂታ፣ ቀልድ
እየጠየቋቸው በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ። አዋቂ እና ተግባቢ በመሆኑ በርካታ ጓደኞች
ከዚያም ተማሪዎች ከተሳሳቱ ያስተካክሉ። አፍርቷል። ታደሰ ቀይ፣ መካከለኛ ቀመትና
በመጨረሻም ተግባር ሁለትን እቤታቸው ጠንካራ ተክለሰውነት የተቸረ፣ እግርኳስ
ሠርተው እንዲመጡ የቤትሥራ ይስጧቸው።) መጫወት የሚወድ ልጅ ነው። በትምህርትቤቱ
የእግርኳስ ቡድን ውስጥ አጥቂ ሲሆን ለቡድኑ
መጻፍ (30 ደቂቃ) በርካታ ግቦችን በማስቆጠሩ የትምህርትቤቱ
ኮከብ ተጫዋች ሆኗል።
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
መ. አንቀጹ ያለበትን ችግር ንገሩኝ።
በገላጭ ስልት የቀረበ አንቀጽን
[መተ. የፊደል ስህተት አለበት።]
አስተካክሎ መጻፍ
መ. የፊደል ስህተት ያለበት/ያለባቸው ቃል/ቃላት
ልሥራ
የትኛው/የትኞቹ ናቸው?
መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት የቢጋር ሠንጠረዥ
እንዴት እንደሚዘጋጅ፣ የቢጋር ሠንጠረዥን [መተ. ቀለደ እና ቀመት]
በመጠቀም በገላጭ ስልት እንዴት አንቀጽ መ. እንዴት ይስተካክሉ?
እንደሚጻፍ አሳይቻችኋለሁ። ከዚያም አንድ
ገፀባህርይ መርጨ፣ ስለገፀባህርይው/ዋ ገላጭ [መተ. ቀልድ እና ቁመት]
አንቀጽ ጽፌ ነበር። ዛሬ ደግሞ የጻፍኩትን መ. በጣም ጥሩ
አንቀጽ አስተካክዬ የመጨረሻውን ጽሑፍ
አቀርባለሁ። (መ. የተሳሳተውን አንቀጽ በሚከተለው መልኩ
አስተካክለው ይጻፉላቸው።)
መ. ጽሑፌን በማስተካክልበት ጊዜ የሚከተሉትን
ነጥቦች ከግምት ውስጥ ማስገባት ታደሰ በሚማርበት የአንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት
ያስፈልገኛል። በጣም ዝነኛ ተማሪ ነው። ሳቂታ፣ ቀልድ
አዋቂና እና ተግባቢ በመሆኑ በርካታ ጓደኞችን
1. ጽሑፌ የገላጭ አጻጻፍ ስልትን ተከትሏል?
አፍርቷል። ታደሰ ቀይ፣ መካከለኛ ቁመትና
2. የቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ የተዘረዘሩትን ጠንካራ ተክለሰውነት የተቸረ፣ እግርኳስ
ነጥቦች አካቷል? መጫወት የሚወድ ልጅ ነው። በትምህርትቤቱ
የእግርኳስ ቡድን ውስጥ አጥቂ ሲሆን ለቡድኑ
3. ፊደላትን በትክክል ጽፌያለሁ?
በርካታ ግቦችን በማስቆጠሩ የትምህርትቤቱ
4. አንቀጼ የሀሳብ አንድነት አለው? ኮከብ ተጫዋች ሆኗል።
መ. ጽሑፌን እያነበብኩ ስገመግም ከላይ ሥሩ
ለተጠቀሱት ጥያቄዎች ምላሼ “አይደለም” መ. አብረን በሠራነው ምሳሌ መሠረት
ከሆነ ተገቢውን ማስተካከያ ማድረግ ደብተራችሁን ተቀያየሩና በተዘረዘሩት ነጥቦች
ይኖርብኛል። መሠረት በጽሑፋችሁ ያሉትን ችግሮች ለዩ።

ምሳሌ፡- ጽሑፌ የገላጭ ጽሑፍ አጻጻፍ ስልትን መ. ጽሑፋችሁ የገላጭ ጽሑፍ አጻጻፍ ስልትን
ተከትሏል? ለሚለው ጥያቄ በሠንጠረዡ ውስጥ ተከትሏል?
“አዎ” በሚለው ሥር ምልክት ካደረግሁ ትክክል [ተ. አዎ/አይደለም]
ስለሆንኩ ምንም አልለውጥም፤ ነገር ግን ምልክት
ያደረግሁት “አይደለም” በሚለው ሥር ከሆነ መ. ምላሻችሁ “አዎ” ከሆነ “አዎ” በሚለው
ማስተካከል ይጠበቅብኛል ማለት ነው። ረድፍም ምልክት አድርጉ፤ ምላሻችሁ
“አይደለም” ከሆነ ደግሞ “አይደለም” በሚለው
እንሥራ
ረድፍ ምልክት አድርጉና በዚሁ ዓይነት
መ. አሁን አንድ አንቀጽ ሰሌዳው ላይ በሌሎቹ መመዘኛዎች መሠረት ምልክት
እጽፍላችኋለሁ። ከዚያም በአንቀጹ ውስጥ

፳፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 21


አድርጉ። ከዚያም እያንዳንዳችሁ ጓደኞቻችሁ ይጻፉላቸው።)
የጠቆሟችሁን ችግሮች አስተካክላችሁ ጻፉ።
(መ. ተማሪዎች ሲፅፉ እየተዘዋወሩ መነሻ ሀሳብ
(መ. ደብተራቸውን ተቀያይረው ለመተራረም 5 በመስጠት ይደግፏቸው።)
ደቂቃ፣ ጽሑፋቸውን ለማስተካከል 5 ደቂቃ
ይስጧቸው። በመጨረሻም ጽሑፋቸውን
በወረቀት ላይ አስፍረው ለርስዎ እንዲሰጡ
9ኛ ቀን
ያድርጉ። ጽሑፎቹን ከገመገሙ በኋላ በቀጣዩ
ክፍለጊዜ የሚቀርቡትን የተሻሉ ሥራዎች የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ይምረጡ። በጥሩ ሁኔታ ያልጻፉ ተማሪዎች • አቀላጥፎ ማንበብ
ችሎታቸውን የሚያሻሽሉበትን ስልትም • መናገር
ይቀይሱ።)
• ሰዋስው
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
እንሥራ የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት የተማርናቸው ሥሩ
ሥርዓተነጥቦች ምን ምን እንደሆኑ (መ. የሠጧቸውን የቃላት ተግባር ለማረም
ልታስታውሱኝ ትችላላችሁ? ተማሪዎች ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ
[መተ. ነጠላ ሠረዝ እና አራት ነጥብ] (በቃል ያድርጉ፤ በመልሶቹ ላይ እየተነጋገሩ ርስበርስ
ይመልሱ) እንዲተራረሙ ያድርጉ።)

መ. በጣም ጥሩ! መ. “ተጎጂ” ለሚለው ቃል ከ“ለ” ረድፍ ተቃራኒው


የትኛው ነው?
መ. እነዚህን ሥርዓተነጥቦች ሰሌዳው ላይ ጽፋችሁ
አሳዩኝ። [ተ. ተጠቃሚ]

[ተ. ፣ (÷)።] (የተወሰኑ ተማሪዎች ሰሌዳው ላይ መ. ቃሉን የያዘው ፊደል የትኛው ነው?
ጽፈው እንዲያሳዩ ያድርጉ።) [ተ. ሠ]
መ. ነጠላ ሠረዝ ለምን ያገለግላል? መ. በጣም ጥሩ!(በዚህ ዓይነት በሌሎቹም
[መተ. በአንድ ዓረፍተነገር ውስጥ የሚዘረዘሩ ጥያቄዎች ላይ ይወያዩ።)
ነገሮችን ወይም ሀሳቦችን ለመለየት
ያገለግላል።] አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
መ. በጣም ጥሩ! የአራት ነጥብ አገልግሎት ሱሰኝነትና መዘዙ
ምንድን ነው?
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
[መተ. የተሟላ ሀሳብ በሚያስተላልፍ ዓረፍተነገር
ሥሩ
መጨረሻ ላይ እንደመዝጊያ ሆኖ ይገባል።]
መ. በዚህ ክፍለጊዜ ድምፅ እያሰማችሁ
ሥሩ በፍጥነት፣ በትክክልና በተገቢው የድምፅ ቃና
መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት በቀረቡላችሁ ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን “ሱሰኝነትና
አንቀጾች ውስጥ ነጠላ ሠረዝንና አራት መዘዙ” የሚለውን ምንባብ ለማስታወስ ያህል
ነጥብን በማስገባት፣ እንዲሁም እነዚህን የተወሰኑ ጥያቄዎችን መልሱ።
ሥርዓተነጥቦች ተጠቅማችሁ ዓረፍተነገሮችን
መ. የጫት ተክል ጥቅም ምንድን ነው?
መመሥረት ተለማምዳችኋል።
[ተ. ለጫት አምራቾች ወይም ለነጋዴዎች ገንዘብ
መ. ዛሬ ደግሞ ነጠላ ሠረዝንና አራት ነጥብን
ያስገኛል።
በመጠቀም አንድ አንቀጽ ትጽፋላችሁ።
የጽሑፋችሁ ርዕስ “የትምህርት ቤት መ. ጥሩ!
ጓደኛዬ” የሚል ነው። (ርዕሱን ሰሌዳው ላይ
መ. ጫት መቃም ምን ጉዳት አለው?

22 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፳፪


[ተ. ጊዜን ያባክናል፣ ገንዘብን ያባክናል፣ ጤናን ሲያልቅ መስመሮቹን በመቍጠር የስህተት
ይጎዳል፣ መገለልን ያስከትላል] መጠኑን እንዲገልጹ ይንገሯቸው።)
መ. ጥሩ ነው! (መ.ተማሪዎች በሠንጠረዡ ውስጥ ቋሚ
መሥመሮችን በመጠቀም እንዴት ስህተቶቹን
መ. የሲጋራ ምርት ምን ጥቅም አለው?
እንደሚመዘግቡ ያሳዩ። የስህተቶቹንም
[መ.ለአምራቾች ገንዘብ ያስገኛል።] ብዛት ቈጥረው እንዲመዘግቡ በምሳሌ
መ. ሲጋራ ማጨስ ምን ጉዳት አለው? ያስረዷቸው።)

[ተ. ለጤና ጠንቅ ነው፣ ገንዘብ ያባክናል፣ መጥፎ ምሳሌ


ጠረን ያመጣል፤ መገለልን ያስከትላል...] ሲነበቡ የፊደል ተቆራርጠው በሐረጎችና
መ. በጣም ጥሩ! ከጥቅምና ጉዳቱ የትኛው ስህተት የተነበቡ ነጠላሠረዝ
ይበልጣል? የተፈፀመባቸው ቃላት ብዛት ላይ ግማሽ
ቃላት ብዛት ዕረፍት፣
[ተ. ጉዳቱ ይበልጣል።]
አራት ነጥብ
መ. በጣም ጥሩ ነው! ላይ ሙሉ
ዕረፍት
መ. ጉዳቱ የበለጠበት ምክንያት ምንድን ነው?
ማድረግ
[ተ. ጎልቶ የሚታየው ጉዳቱ በመሆኑ፣ ከጉዳቱ /// // ////
አንፃር ሲታይ ጥቅሙ እዚህ ግባ የሚባል
አይደለም።] 3 2 4

ማንበብ (8 ደቂቃ) (መ.ቋሚ መስመር ስህተት በተሠራ ቊጥር


በየርዕሱ ሥር የሚደረግ ምልክት ነው። ድምሩ
ልሥራ የመስመሮቹ ብዛት ነው።ተማሪዎች ተግባሩን
(መ. በአንደኛ ሳምንት በማስታወሻ የቀረበውን በትክክል እየሠሩ መሆናቸውንና ሠንጠረዡን
በመግለጽ ያስታውሷቸው።) በትክክል እየተጠቀሙበት መሆናቸውን
መ. “ሱሰኝነትና መዘዙ” የሚለውን ምንባብ አረጋግጠው ድጋፍ ያድርጉ። በመጨረሻም
1ኛና 2ኛ አንቀጽ እኔ ሳነበው እናንተ ተማሪዎች የስህተት ብዛት የመዘገቡባቸውን
ምንባቡን ድምጻችሁን ሳታሰሙ ሠንጠረዦች የያዙ ወረቀቶችን በመሰብሰብ
እያነበባችሁ ተከታተሉ። (ሁሉም ተማሪዎች ይገምግሙ። ከዚያም ጥሩ ያነበቡትን ጥሩ
መጽሐፋቸውን መግለጣቸውን አረጋግጠው፤ ካላነበቡት አንባቢ ይለዩ። የተማሪዎችን
ማንበብዎን ይቀጥሉ።) የንባብ ችሎታ የሚያዳብሩበትን ስልትም
ይንደፉ።)
እንሥራ
መ. አሁን እኔ ያነበብኳቸውን አንቀጾች መናገር (15 ደቂቃ)
አብረን እናንብብ። (ተማሪዎች ከርስዎ ጋር
ድምፃቸውን እያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ።) ሥሩ
መ. ዛሬ “ሱሰኝነትና መዘዙ” ከሚለው ምንባብ
ሥሩ ይዘት በመነሳት በተዘጋጁ የመወያያ
(መ. ተማሪዎችን ከ3-5 አባላት ባሉት ቡድን ጥያቄዎች ላይ ትወያያላችሁ። በመጀመሪያ
ያደራጁ፣ የቡድን መሪ ያስመርጡ፤ አራት አራት ወይም አምስት አምስት በመሆን
በመቀጠል1ኛና 2ኛውን አንቀጽ ተራበተራ ቡድን መሥርቱ። ቀጥሎ ለቡድናችሁ
ድምፃቸውን እያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ። ሰብሳቢ፣ ጸሐፊና የቡድን ሀሳብ አቅራቢ
የማንበብ ተራ የደረሳቸው ተማሪዎች ምረጡ። ከዚያም በሰብሳቢው መሪነት
ሲያነቡ ሌሎች ቀጥሎ የቀረበውን ሠንጠረዥ (አስተባባሪነት) በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው
እየተጠቀሙ ማስታወሻ እንዲይዙ ያድርጉ። ቀን በመናገር ክሂሎች ንዑስ ክፍል ሥር
ስህተት በተሠራ ቊጥር አንድ ቋሚ መስመር በቀረቡት የመወያያ ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ።
(/) በማስቀመጥ ምልክት ካደረጉ በኋላ ንባቡ በምትወያዩበት ጊዜ ጸሐፊው/ዋ የቡድን

፳፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 23


አባላትን ሀሳብ በማስታወሻ ይያዝ/ትያዝ። ለይታችሁ በሠንጠረዡ ውስጥ መድቡ።
(ጸሐፊዋ/ው ሀሳብ መስጠት እንደሚችል/
መ. ከተዘረዘሩት ስሞች የተጸውዖ ስም የሆነ
እንደምትችል ያስታውሷቸው። በመጨረሻም
ንገሩኝ።
የቡድኑን ሀሳብ ካጠቃለላችሁ በኋላ፣
እንዲያቀርብ/እንድታቀርብ የተመረጠው/ችው [ተ. ተከዜ]
ተማሪ በአጠቃላይ ለክፍሉ ተማሪ ያቅርብ/
መ. በጣም ጥሩ!
ታቅርብ። አንድ ቡድን በአንዱ ጥያቄ ላይ
ብቻ እንዲያተኩር ያድርጉ።) (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ስሞች እንዲመደቡ
ያድርጉ። ተግባሩን ሲሠሩ በትክክል
ሰዋስው (10 ደቂቃ) መሥራታቸውን በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ
ይገምግሙ፤ የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤
የተጸውዖና የወል ስም ከዚያም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎችም ጋር
እንሥራ ይወያዩ። በመቀጠልም ሁለተኛውን ተግባር
መ. ባለፉት ሁለት ሳምንታት ስለተጸውዖና የወል በቡድን እንዲሠሩ ያድርጉ።)
ስሞች ተመልክተናል። ዛሬ ደግሞ ምን ያህል መ. “ሱሰኝነትና መዘዙ” ከሚለው ምንባብ ውስጥ
እንደተረዳችኋቸው እንገመግማለን። ስለዚህ የተጸውዖና የወል ስሞችን አውጡ።
የተማራችሁትን አስታውሳችሁ ስለተጸውዖ [ተ. ዮሐንስ]
ስም ምንነት ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ከዚሁ ምንባብ
[መተ. የግል መጠሪያ ነው።] የወል ስም አውጡ።
መ. በጣም ጥሩ! የተጸውዖ ስም የሚባለው የሰው፣ [ተ. ሰው]
የቦታ፣ የወንዝ፣ የባህር፣ የሐይቅ፣ የተራራ
እንዲሁም የውቅያኖስ የግል መጠሪያ ወይም መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት የተጸውዖና የወል
መታወቂያ የሚሆን ቃል ነው። ስሞችን ለይተው እያወጡ በደብተራቸው
እንዲጽፉ ያድርጉ። በመጨረሻም
መ. ለተፀውዖ ስም ምሳሌ ሊሠጠኝ/ልትሰጠኝ/ ያወጧቸውን ስሞች ለእርስዎ እንዲነግሩዎ
የሚችል/የምትችል ማነው/ማን ናት? ያድርጉ። የቀሩ ስሞች ካሉ በመጨመር
[መተ. አለሙ፣ ሉባባ፣ መሐመድ፣ አዋሽ፣ ወሎ፣ ግብረመልስ ይስጡ።)
አዊ፣…]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ የወል ስምን ምንነት
ንገሩኝ።
[መተ. የጋራ መጠሪያ ቃል]
[መ.ትክክል! የወል ስም የሚባለው አንድ ዓይነት
የሆኑ ነገሮች በጋራ የሚጠሩበት ቃል ነው።]
መ. ለወል ስሞች ምሳሌ ልትሰጡ ትችላላችሁ?
[መተ. በሬ፣ ዶሮ፣ አይጥ፣ ሰው፣ ነብር፣ አህያ…]
መ. በጣም ጥሩ!
ሥሩ
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን በሰዋስው ንዑስ
ክፍል ሥር የሚገኘውን የመጀመሪያውን
ተግባር የክፍልሥራ ሥሩ።
መ. ከሠንጠረዡ በላይ የተጸውዖና የወል
ስሞች ተቀላቅለው ቀርበዋል። እያንዳንዱ
ቃል የተጸውዖ ወይም የወል ስም መሆኑን

24 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 1 ፳፬


ምዕራፍ 2 አካባቢያችን
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• በምዕራፉ ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• ተተኳሪና አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• ተተኳሪና አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይጽፋሉ፤
• የቢጋር ሠንጠረዥ ተጠቅመው በምክንያትና ውጤት ስልት አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• የቀረቡትን ምንባቦች በተገቢው ፍጥነት፣ በትክክልና በተገቢው አገላለፅ ያነባሉ፤
• በምክንያትና ውጤት የቀረበ ጽሑፍ አዳምጠው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• “የውኃ ብክለት” በሚል የምንባብ ይዘት ዙሪያ በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ ተመርኩዘው ይናገራሉ።
• የመጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮችን ተጠቅመው ዓረፍተነገር ይጽፋሉ።

1ኛ ሳምንት ብክለት በፍጥነትና በተገቢው ለዛ የማንበብ ክሂልን


ማዳበር ነው።
በአጠቃላይ አንድን ቃል እየነጠሉና እያጣመሩ
1ኛ ቀን ማንበብ አቀላጥፎ የማንበብ ክሂል እድገትን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ያፋጥናል።

• የቃላት ጥናት
• ማንበብ ልሥራ
መ. ምንባቡን ከማንበባችሁ በፊት ከምንባቡ
የወጡ ረዘም ያሉ ቃላትን እያጣመርኩና
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) እየነጠልኩ በማንበብ አሳያችኋላሁ።
መነጠልና ማጣመር መ. “በ-ነዋሪ-ዎች” የሚለውን ቃል አጣምራችሁ
ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
ማስታወሻ
መ. በጣም ጥሩ [“በነዋሪዎች” ብዬ በአንድነት
መነጠልና ማጣመር ቃላትን በማጥናት ሂደት አነበዋለሁ።]
የምንጠቀምባቸው ዘዴዎች ናቸው። ማጣመር፦
መ. “ሥርዓት-ኣቸው” የሚለውን ቃል አጣምራችሁ
በአንድ ቃል ውስጥ የተዋቀሩ ፊደላትን፣ ዋና
ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
ቃልና ቅጥያዎችን አጣምረን የምናነብበት
ዘዴ ነው። መ. በ ጣ ም ጥሩ ነው፤ በትክክል
መነጠል፡- በአንድ ቃል ውስጥ የተዋቀሩ ዋና አንብባችሁታል። [“ሥርዓታቸው” ብዬ
ቃልንና ቅጥያዎችን (ፊደላትን) እየነጠልን በአንድነት አነበዋለሁ።]
የምናነብበት ዘዴ ነው። በቃል ጥናት መ. “ንጥረነገሮች” የሚለውን ቃል ነጥላችሁ
ላይ የመነጠልና የማጣመር ዓላማ አንድ ልታነቡልኝ ትችላላችሁ? በጣም ጥሩ።
ቃል የሚመሰርቱ ፊደሎችና ቅጥያዎችን [“ንጥረ-ነገር-ኦች” ብዬ ነጥዬ አነበዋለሁ።]
በቅደምተከተል አስተካክሎ በትክክል፣
መ. “በነፍሳት” የሚለውን ቃል ነጥላችሁ አንብቡ!

፳፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 25


በጣም ጥሩ [“በ-ነፍስ-ኣት” ብዬ ነጥዬ ቃል ስትሰሙ ወደአዕምሯችሁ የሚመጡትን
አነበዋለሁ።] ሀሳቦች ዘርዝሩ” ይላል።
እንሥራ [መ. እኔ “ብክለት” የሚለውን ቃል ስሰማ ቆሻሻ፣
ንፅህና የጎደለውና መጥፎ ሽታ ያለበት
መ. ቃላትን ለማንበብ ይረዳን ዘንድ የቃላትን አካባቢ፣ ወዘተ. ትዝ ይለኛል። ይህንንም
ልዩ ልዩ ክፍሎች እያጣመርን እናነባለን። ለማለት የቻልኩት ከዚህ በፊት ከማውቀው
በመነሳት ነው።]
መ. በመጀመሪያ እያንዳንዱን የቃል ክፍል በጣቴ
ስጠቁማችሁ ዋና ቃሉንና ቅጥያዎችን ነጥለን [መ.“ዝቃጭ” የሚል ቃል በምንባቡ ውስጥ
ቀጥሎ አጣምረን እናነባለን። አይቻለሁ። ዝቃጭ ማለት ከፈሳሽ ነገር
ሥር የሚቀር ቆሻሻ ነው። ይህንንም ለማለት
መ. አካል-ኣት
የቻልኩት ቀደም ብሎ ከማውቀው በመነሳት
[መተ. አካል-ኣት] ነው።]
መ. አሁን ደግሞ አጣምረን እናንብበው። እንሥራ
[መተ. አካላት ] መ. አሁን ደግሞ በጋራ እንሥራ፤ “ሰደድእሳት”
የሚለው ቃል ፍቺ ምንድን ነው?
መ. “እድገታቸውን” የሚለውን ቃል ነጥለን
እናንብበው። [መተ. በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት የሚፈጠር
የደን ቃጠሎ ነው።]
[መተ. እድገት-ኣቸው-ን]
መ. ትክክል!
መ. አጣምረን ስናነበው ምን ይሆናል?
መ. “የአንጀት ተስቦ” የሚለውስ?
[መተ. እድገታቸውን]
[መተ. በምግብና በውኃ መበከል የሚከሰት
ሥሩ ተላላፊ በሽታ]
መ. ተማሪዎች አሁን ደግሞ ተራው የናንተ ነው።
ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን መ. አሁን ደግሞ እናንተ ሥሩ፤ በአካባቢያችሁ
በ“ቃላት ጥናት” ንዑስ ክፍል ሥር ተነጥለው አካባቢን የሚበክሉ ነገሮች አሉ? ካሉ ምን
የቀረቡትን ቃላት በመጀመሪያ ባሉበት ምን ናቸው?
ሁኔታ በአነስተኛ ቡድን በመሆን ተራበተራ
ነጥላችሁ አንብቡ፤ ቀጥሎም የተነጠሉትን [ተ. የቤት ጥራጊ፣ የሰውና የእንስሳት ሽንትና
አንድ ላይ አጣምራችሁ አንብቡ። ዓይነምድር፣ ቆሻሻ ሲቃጠል የሚፈጠር ጪስ
ወዘተ. ]
(መ.የተነጠሉትን ሲያነቡ በጣትዎ ያመላክቷቸው።
የተመረጡትን አዳዲስ ቃላት በዚህ መልኩ መ. የአካባቢ መበከል ምን ምን ጉዳቶችን
ያለማምዷቸው።) የሚያስከትል ይመስለችኋል?
[ተ. ሰዎችና እንስሳትን ለልዩ ልዩ በሽታዎች
ማንበብ (30 ደቂቃ) ይዳርጋል።]
የአየርና የውኃ ብክለት መ. ተማሪዎች ሥዕሉን ተመልከቱና ጽሑፉ
ስለምን ሊሆን እንደሚችል ገምቱ።
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) ግምታችሁንም ለጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
አዳዲስ ቃላትን ማስተዋወቅና መገመት [ተ. ግምታቸውን ለጓደኞቻቸው ይናገራሉ።]
ልሥራ የማንበብ ሂደት(10 ደቂቃ)
መ. ምንባቡን ከማንበባችን በፊት በመጽሐፋችሁ
በቀረቡት የቅድመንባብ ጥያቄዎች ሥሩ
እንወያያለን። መ. የምታነቡት ምንባብ በምክንያትና ውጤት
የተደራጀ ነው። የምክንያትና ውጤት ስልት
መ. የመጀመሪያው ጥያቄ “ብክለት የሚለውን

26 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፳፮


የሚባለው አንድ ድርጊት የተከሰተበትን አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
መንስኤና በዚህም ሳቢያ የተገኘውን ውጤት
የሚገልፅ የአጻጻፍ ዓይነት ነው። ምንባቡን
እንሥራ
በምታነቡበት ጊዜ የምክንያትና ውጤት መ. ማንበብ ከመጀመራችሁ በፊት ሥዕሉን
ግንኙነት መኖሩን የሚጠቁሙ ቃላት ተመልክታችሁ ገምታችሁ ነበር፤ ግምታችሁ
ሊያጋጥሟችሁ ይችላሉ። ለምሳሌ ስለዚህ፣ ትክክል ነበር?
ስለሆነም፣ ምክንያቱም፣ መንስኤ፣ በመሆኑም፣ [መተ. አዎ/አይደለም]
በዚህም የተነሳ የመሳሰሉት ናቸው።
መ. አሁን ደግሞ በምንባቡ መሠረት የቀረቡ
መ. ተማሪዎች ምንባቡን በምታነቡበት ጊዜ ጥያቄዎችን እንመልስ።
ያልገባችሁ ነገር ሲያጋጥማችሁ ወደኋላ
መ. የሞቱ እንስሳት ለብክለት መንስኤ የሚሆኑት
ተመልሳችሁ ደግማችሁ በማንበብ፣ ግልጽ
እንዴት ነው?
ያልሆነላችሁን ጉዳይ የበለጠ ልትረዱት
ትችላላችሁ። [መተ. ከአካላቸው ብስባሽ በሚወጣ ጋዝ
አማካይነት]
መ. አሁን በመማሪያ መጽሐፋችሁ “የአየርና
የውኃ ብክለት” በሚል ርዕስ ከቀረበው ሥሩ
ምንባብ 1ኛውን፣ 2ኛውንና 3ኛውን አንቀጾች መ. በሠራነው ምሳሌ መሠረት በመጽሐፋችሁ
ድምፅ ሳታሰሙ አንብቡ። በ1ኛው ሳምንት በ1ኛው ቀን የሚገኙትን
[ተ. ድምፅ ሳያሰሙ በግል ያነባሉ።] የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች መልሱ።
መጀመሪያ ተግባር “1”ን ሥሩ።
(መ. አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ሦስቱን አንቀጾች
አንብበው መጨረሳቸውን ሲያረጋግጡ መ. በምንባቡ ውስጥ የተጠቀሱት የብክለት
ያስቁሙ።) ዓይነቶች ምንና ምን ናቸው?

መ. አሁን ማንበብ አቁሙና በምጠይቃችሁ [ተ. የአየርና የውኃ ብክለት]


ጥያቄዎች ላይ በጥንድ ተነጋገሩ። መ. በጣም ጥሩ! የውኃ ብክለት እንዴት
መ. 2ኛው አንቀጽ ያተኮረው በምን ላይ ነው? ይፈጠራል?

[ተ. "በአየር ብክለት መንስኤዎች ላይ" በማለት [ተ. ከፋብሪካዎች የሚወገዱ ፈሳሽ
አንዳቸው ላንዳቸው መልሱን ይናገራሉ።] መርዛማ ንጥረነገሮች፣ ዝቃጮች፣ ሰዎች
የሚያስወግዷቸው ልዩ ልዩ ቆሻሻዎች
መ. በጣም ጥሩ! 3ኛው አንቀጽስ ያተኮረው በምን ከወንዝ፣ ከሐይቅ ወዘተ ጋር ሲቀላቅሉ የውኃ
ላይ ነው? ብክለት ይፈጠራል።]
[ተ. "የአየር ብክለት የሚያስከትላቸው ጉዳቶች"
(በዚህ ዓይነት የቀሩትን ጥያቄዎች እየጠየቁ
በማለት አንዳቸው ላንዳቸው ይናገራሉ።]
ተማሪዎች በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ፤
(ጥያቄዎቹን መመለስ ካልቻሉ ደግመው
ከተማሪዎች መልስ በኋላ ግልፅ ባልሆኑ ጥያቄዎች
እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ተጨማሪ ማብራሪያ በማቅረብ ግብረመልስ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ 4ኛውና 5ኛው ይስጡ። ተግባር “2”ን ደግሞ የቤትሥራ
አንቀጾች ስለምን እንደሚገልፁ ገምቱ። ይስጧቸው።)
[ተ. 4ኛውና 5ኛው አንቀጾች ስለምን እንደሚገልፁ
አንዳቸው ላንዳቸው ግምታቸውን ይናገራሉ።]
መ. አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ።
[ተ. በግል በለሆሳስ ማንበባቸውን ይቀጥላሉ።]
(መ. አንብበው እንደጨረሱ ግምታቸውን በጥንድ
እንዲያረጋግጡ ያድርጉ።)

፳፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 27


“ዝናብ በመዝነቡ ምክንያት መሬቱ ጨቀዬ”
2ኛ ቀን ይላል።
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረበትን ቃል
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ፍቺ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?

• ቃላት [መተ. ራሰ፣ ረጠበ፣ጭቃ ሆነ ወዘተ.]


• መጻፍ ሥሩ
መ. በምሳሌው መሠረት ከሀ-ሠ የቀረቡትን
ጥያቄዎች ሥሩ። (ጥያቄዎቹን ለመመለስ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
5 ደቂቃ ይስጧቸው። መምህር፣ ተማሪዎች
ሥሩ ተግባሩን ሲሠሩ እየተዘዋወሩ ይመልክቱ፤
(መ. ተማሪዎች የተሠጣቸውን የቤትሥራ የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤ ከዚያም
መሥራታቸውን ይመልከቱና ጥንድ ጥንድ በመልሶቹ ላይ ይወያዩ።)
ሆነው የጻፉትን አንቀጽ አንዳቸው ለአንዳቸው መ. ቃሉ የሚገኝበትን ዓረፍተነገር የያዘውን
እንዲያነቡ ያድርጉ።) ፊደል ስጠራ፣ እናንተ የተሠመረበትን ቃል
መ. የጻፋችሁትን አንቀጽ ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ፍቺ ትናገራላችሁ።
አንዳችሁ ለአንዳችሁ አንብቡ።
መ. "ሀ"
[ተ. የጻፉትን አንቀጽ አንዳቸው ለአንዳቸው [ተ. የውኃ መመረዝ]
ያነባሉ።]
መ. "ለ"
(መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ በመከታተል
የተሻለውን ጽሑፍ በመምረጥ ለክፍሉ [ተ. ያጋልጣል]
ተማሪዎች እንዲያነቡ ያድርጉ።) መ. በጣም ጥሩ! "ሐ"

ቃላት (10 ደቂቃ) [ተ. ለመተንፈስ የምንጠቀምባቸው የሰውነት


ክፍሎች]
ለቃላትና ለሐረጋት ፍቺ መስጠት
መ. "መ"
ልሥራ
[ተ. ለጥፋት]
መ. በምንባቡ ውስጥ ካሉ ዓረፍተነገሮች መካከል
አንዱን እንመልከት። “የአየር ብክለት በጪስ፣ መ. "ሠ"
በብናኝና በጋዝ መልክ ያሉት ነገሮች ከአየር [ተ. ያዛባል]
ጋር በሚገናኙበት ጊዜ ይከሰታል።” (ይህን
ዓረፍተነገር ለተማሪዎች ድምፅዎን እያሰሙ
ያንብቡላቸው።)
መጻፍ (25 ደቂቃ)
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ የምናተኩርበት ድርሰት መጻፍ (17 ደቂቃ)
ሐረግ “የአየር ብክለት” የሚለው ነው። የአየር የምክንያትና ውጤት ስልት የቢጋር
ብክለት ማለት የከባቢ አየር መመረዝ ነው። ሠንጠረዥ ማዘጋጀት
ምክንያቱም በዓረፍተነገሩ ውስጥ “የአየር
ብክለት” የአካባቢያችን አየር በጪስ፣ በብናኝ፣
ልሥራ
በጋዝ ወዘተ. መቆሸሽ ወይም መመረዝ መሆኑ መ. ዛሬ በምክንያትና ውጤት ስልት የተደራጀ
ተገልጿል። ጽሑፍ እንዴት ማዘጋጀት እንደምትችሉ
እንመለከታለን። ምክንያት ለአንድ ድርጊት
እንሥራ መከሰት መነሻ ሲሆን፣ ውጤት ደግሞ
መ. ቀደም ሲል በሠራነው መሠረት በ1ኛው መነሻው የሚያስከትለው ነገር ነው። ባለፈው
ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን የሚገኘውን ምሳሌ “2” ክፍለጊዜ “የውኃና የአየር ብክለት” በሚል
ተመልከቱ። ርዕስ ያነበብነው ምንባብ በምክንያትና
ውጤት የተደራጀ ጽሑፍ ነው።

28 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፳፰


መ. ምንባቡን መሠረት በማድረግ የምክንያትና መ. በዚህ አንቀጽ ውስጥ ውጤቱ ምንድን ነው?
ውጤት ስልት የቢጋር ሠንጠረዥ እንዴት
[መተ. የአየር ብክለት]
እንደሚዘጋጅ አሳያችኋላሁ። በዚህም ጊዜ፣
ምክንያቱም፣ ከዚያም፣ ከዚህ የተነሳ፣ ስለዚህና መ. የአየር ብክለት ከሚከሰትባቸው ምክንያቶች
የመሳሰሉ አያያዥ ቃላት ምክንያቶችንና የመጀመሪያውን ንገሩኝ፡
ውጤቶችን ከምንባቡ ለመለየት [መተ. ፋብሪካዎችና መኪናዎች ከሚፈጥሩት
ይጠቅሙኛል።(መምህር የሚከተለውን ብናኝ፣ አቧራና ጭስ]
ዓረፍተነገር ያንብቡላቸው) “ወደውኃ
በሚገቡ መርዛማ ንጥረነገሮች፣ ዝቃጭና መ. ሁለተኛ የአየር ብክለት መንስኤ ምንድን
ቆሻሻ ምክንያት የውኃ ብክለት ይከሠታል።” ነው?
“ምክንያት” የሚል ቃል በመኖሩ በዚህ [መተ. ከሰደድ እሳትና ከመኖሪያ ቤቶች በሚወጣ
ዓረፍተነገር ውስጥ የምክንያትና ውጤት ጪስ]
ግንኙነት መኖሩን ያሳየናል።
መ. ይህንኑ ምክንያትና ውጤት በቢጋር
መ. ምን ይከሰታል ብዬ ራሴን ብጠይቅ፤ ምላሼ ሠንጠረዥ እንመልከተው።
“የውኃ ብክለት ይከሰታል” የሚል ይሆናል።
“የውኃ ብክለት ለምን ይከሰታል?” ብዬ ምክንያት ውጤት
ስጠይቅ ደግሞ “ወደውኃ በሚገቡ መርዛማ
ንጥረነገሮች፣ ዝቃጮችና ቆሻሻዎች”
የሚል መልስ አገኛለሁ። ስለዚህ መርዛማ የፋብሪካዎችና መኪናዎች
ንጥረነገሮች፣ ዝቃጮችና ቆሻሻዎች ወደውኃ ብናኝ፣ አቧራና ጪስ
ሲገቡ የውኃ ብክለት ያስከትላሉ ማለት ነው። ከሰደድ እሳትና መኖሪያ ቤቶች የአየር
ይህንንም የቢጋር ሠንጠረዥ በመጠቀም የሚወጣ ጪስ ብክለት
አሳያችኋላሁ። (ቀጥሎ የቀረበውን የቢጋር ከመሬት የሚነሳ አቧራ
ሠንጠረዥ ሠሌዳው ላይ ይጻፋላቸው።)
መ. ተማሪዎች ይህ የቢጋር ሠንጠረዥ ምን
ምክንያት ውጤት
ያመለክታል?
[መተ. የቢጋር ሠንጠረዡ የሚያሳየው የአየር
የመርዛማ ብክለት መንስኤዎች ከፋብሪካዎችና
ንጥረነገሮች ከመኪናዎች የሚወጣ ብናኝ፣ አቧራና ጪስ፣
የውኃ ብክለት ከሰደድእሳትና ከመኖሪያ ቤቶች የሚወጣ
ዝቃጭና ቆሻሻ
ጪስና ከመሬት የሚነሳ አቧራ መሆናቸውን
ወደውኃ መግባት
ነው።]
መ. ይህ የቢጋር ሠንጠረዥ የሚያመለክተው ሥሩ
ለውኃ ብክለት መንስኤው የመርዛማ መ. የምክንያትና ውጤት የቢጋር ሠንጠረዥ
ንጥረነገሮች፣ ዝቃጮችና ቆሻሻዎች ውኃ አብረን አዘጋጅተናል። አሁን ደግሞ
ውስጥ መግባት መሆኑን ነው። “ለግብርና ምርት መቀነስ ምክንያቶች”
እንሥራ በሚል ርዕስ የምክንያትና ውጤት አንቀጽ
ለመጻፍ የሚያስችል የቢጋር ሠንጠረዥ
መ. አንዳንድ ጊዜ በርካታ ምክንያቶች ለአንድ
ታዘጋጃላችሁ።
ውጤት መከሰት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ።
በዚህ ጊዜ የቢጋር ሠንጠረዡ የተለየ ሊሆን (መ. ተግባሩን ቀላል ለማድረግ የሚከተለውን
ይችላል። የቢጋር ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ
ይሣሉላቸው። ለመነሻ ያህልም የግብርናን
(መ.“የአየርና የውኃ ብክለት” በሚል ርዕስ
ምርት ከሚቀንሱ ምክንያቶች አንዱን
ከቀረበው ምንባብ ሁለተኛውን አንቀጽ
ይጻፉላቸው።)
ያስነብቡ።)
“ለግብርና ምርት መቀነስ ምክንያቶች”

፳፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 29


ምክንያት ውጤት
3ኛ ቀን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
በቂ የሆነ የዝናብ • አቀላጥፎ ማንበብ
የግብርና ምርት
የውኃ/ የመስኖ ውኃ
መቀነስ • ማዳመጥ
አለመኖር
• ሰዋስው
(ተማሪዎች በቡድን እየተወያዩ ሌሎች የግብርና
ምርትን የሚቀንሱ የተወሰኑ ምክንያቶችን
በክፍል ውስጥ እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። በርካታ አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
ምክንያቶችን በራሳቸው ለመዘርዘር ሊቸገሩ
የአየርና የውኃ ብክለት
ስለሚችሉ፣ እርስዎ መረጃዎችን በመስጠት
በቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ እንዲዘረዝሩ ያድርጉ።) ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
4ለ. የአጻጻፍ ሥርዓት (8 ደቂቃ) ሥሩ
በተወሰነ አካባቢ ብቻ አገልግሎት ያላቸውን መ. ተማሪዎች "የአየርና የውኃ ብክለት" በሚል
ቃላት በብዙ አካባቢዎች አገልግሎት ባላቸው ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ከማንበባችሁ በፊት
ቃላት ለውጦ መጻፍ አንድ ጥያቄ መልሱ።

ልሥራ መ. የአየርና የውኃ ብክለት በሰዎች ላይ


መ. አንዳንድ ቃላት በተወሰነ አካባቢ ብቻ የሚያደርሱትን ጉዳቶች ዘርዝሩ።
አገልግሎት ሲሰጡ ሌሎች ቃላት ደግሞ [ተ. የአየርና የውኃ ብክለት በሰዎች ላይ
በብዙ አካባቢዎች ያገለግላሉ። በብዙ ሰዎች የሚያደርሱትን ጉዳቶች አስታውሰው
ይታወቃሉ ማለት ነው።፡ ይናገራሉ።]
መ. “ቲበላ” የሚለው ቃል ሰፊ አገልግሎት ማንበብ (8 ደቂቃ)
የሌለው ነው፤ ሰፊ አገልግሎት እንዲኖረው
ልለውጠው፤ ልሥራ
መ. በመጀመሪያ እኔ “የአየርና የውኃ ብክለት”
[መ. ሲበላ] የሚለውን ምንባብ የመጀመሪያ አንቀጽ
እንሥራ አነብላችኋለሁ፤ እናንተ ደግሞ እንዴት
መ. አብረን እንሥራ። “አይሰልጥም” የሚለውን እንደማነብ በትኩረት ተከታተሉ።
ቃል ሰፊ አገልግሎት ባለው ቃል እንለውጥ። (መ.“የአየርና የውኃ ብክለት” የሚለውን ምንባብ
[መተ. አይፈጥንም] የመጀመሪያ አንቀጽ በተገቢ ፍጥነት
ለተማሪዎችዎ ያንብቡላቸው።)
መ. “ክፈተኝ” የሚለውን ቃል ሰፊ አገልግሎት
ባለው ቃል እንለውጥ። እንሥራ
መ. አሁን ይህንኑ አንቀጽ ሁላችንም በህብረት
[መተ. ክፈትልኝ]
ድምፅ እያሰማን እናንብብ።
ሥሩ (መ.ተማሪዎች እርስዎን እየተከተሉ ድምፃቸውን
መ. አሁን በመማሪያ መጽሐፋችሁ፣ በ1ኛው እያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ሳምንት በ2ኛው ቀን የሚገኘውን ተግባር
በምሳሌው መሠረት በግል ሥሩ። ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ
(መ. ተማሪዎች በግል እንዲሠሩ ካደረጉ በኋላ
አንደኛችሁ ስታነቡ ሌላችሁ ደግሞ ፊደላቱ
ደብተራቸውን ተለዋውጠው እንዲተራረሙ
በትክክል መነበባቸውን ተከታተሉ። ከተሳሳቱ
አድርገው ግብረመልስ ይስጡ።)
ስህተታተቸውን እንዲያርሙ ይንገሯቸው።

30 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፴


(ተማሪዎች በጥንድ ሲያነቡ በክፍሉ ውስጥ በገጠር ገበሬዎች በማሳዎቻቸው ላይ ፀረተባይና
እየተዘዋወሩ የንባብ ፍጥነታቸውን፣ ፊደላቱን ፀረአረም መርዛማ ንጥረነገሮችን ይጠቀማሉ።
ሳይሳሳቱ ማንበባቸውን፣ በተገቢው ቦታ ላይ እነዚህም መርዛማ ንጥረነገሮች በባለሙያ
ዕረፍት ማድረጋቸውን ወዘተ. ይከታተሉ።) እየታገዙ ካልተጠቀሙባቸው ወደመሬት እየሰረጉ
ወይም በዝናብ እየታጠቡ የምንጭና የጉድጓድ
ውኃን ይበክላሉ። በከተማ ከፋብሪካዎች
ማዳመጥ(20 ደቂቃ) የሚለቀቀው ጪስ ከአካባቢ አየር ጋር ከተቀላቀለ
የውኃ ብክለት በኋላ በዝናብ መልክ ወደመሬት ይመለሳል።
ከባህር፣ ከወንዝና ከሐይቅ ጋር በመቀላቀልም
ቅድመማዳመጥ ( 5 ደቂቃ) ለውኃ መበከል ምክንያት ይሆናል።
እንሥራ ፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻም ለውኃ ብክለት መንስኤ
መ. ዛሬ “የውኃ ብክለት” የሚል አንድ ምንባብ ነው። በዓለም በየዓመቱ 400 ቢሊዮን ቶን
አነብላችኋለሁ። የኢንዱስትሪ ቆሻሻ ያላግባብ ወደወንዝና
ውቅያኖስ እንዲገባ ይደረጋል። ሰዎች በየቀኑ
መ. ምንባቡን ከማንበቤ በፊት ከዚህ ርዕስ ምን የሚጠቀሙባቸውን ልዩ ልዩ የመገልገያ
እንገነዘባለን? እንገምት። መሣሪያዎችና የመመገቢያ እቃዎች ለማጽዳት
ሳሙናን ይጠቀማሉ። በአትክልት ቦታዎች ላይ
[መተ. በውኃ ብክለት ምክንያት የሚከሰቱ ፀረተባይ መርዛማ ንጥረነገሮችን ይረጫሉ።
ችግሮችን የሚመለከት ይመስላል።] የእነዚህ ሁሉ መዳረሻ ወንዞችና ውቅያኖሶች
መ. ተማሪዎች በአካባቢያችሁ ውኃን የሚበክሉ ስለሆኑ ሁሉም ለውኃ ብክለት መንስኤዎች
ነገሮች ምን ምን ናቸው? ናቸው።
***የውኃ ብክለት መንስኤዎች ምን ምን
[መተ. ከመፀዳጃቤቶች የሚለቀቅ ቆሻሻ፣
ናቸው?***)
የከብቶችና የሰዎች ሽንትና ዓይነምድር፣
ከከተሞች ወደወንዞችና ሀይቆች የሚቀላቀል
ጎርፍ ወዘተ…] የውኃ ብክለት በሰዎች፣ በእንስሳትና በዕፅዋት ላይ
መ. በጣም ጥሩ! የውኃ መበከል ምን ምን በርካታ ችግሮችን ያስከትላል። የተበከለውን ውኃ
ችግሮችን የሚያስከትል ይመስላችኋል? የሚጠጡ ሰዎች ለተለያዩ ውኃወለድ በሽታዎች
ይጋለጣሉ። እንስሳትና በውኃ ውስጥ የሚኖሩ
[መተ. ሰዎችን፣ እንስሳትንና ዕፅዋትን ለልዩ ልዩ ሌሎች ፍጥረታት በውኃ ብክለት ምክንያት
በሽታዎች ያጋልጣሉ።] በከፍተኛ መጠን ይሞታሉ፤ ዕፅዋት እድገታቸው
እንዳይፋጠንና እንዲቀጭጩ የሚያደርገው
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ምንባቡን አነብላችኋለሁ
የተበከለ ውኃ ነው።
በትኩረት አዳምጡ
እነዚህን የውኃ ብክለት ችግሮች ለመቀነስም
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ) የተለያዩ ዘዴዎችን መጠቀም ይቻላል።
(መ. የማዳመጥ ምንባቡን እያነበቡ እያለ የኮከብ ተጠቃሚ ሰዎችን ማስተማር አንዱ መንገድ
ነው፤ ሁለተኛው ዘዴ ደግሞ በካይ ጋዞችን
ምልክት ባለበት ቦታ ላይ ሲደርሱ፣ ንባብዎን
የሚለቁ ዜጎችንና አገሮችን ተጠያቂ የሚያደርግ
ገታ አድርገው የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን
ብሔራዊና ዓለምአቀፋዊ ህግ ማውጣት ነው።
(*የውኃ ብክለት መንስኤዎች ምን ምን ሶስተኛው ዘዴ አካባቢን የሚበክሉ ሀገራት
ናቸው።*) ይጠይቋቸውና መልሶቻቸውን በብክለት ተጎጅ ለሆኑ ሀገራት ካሣ እንዲከፍሉ
ይቀበሉ፤ ከዚያም ማንበብዎን ይቀጥሉ።) ማድረግ ነው። እነዚህ ሦስት ዘዴዎች ተግባራዊ
ከተደረጉ የውኃ ብክለት ችግሮችን መቀነስ
የውኃ ብክለት ይቻላል።
አብዛኛው የውኃ ብክለት ችግር ከራሱ ከውኃ በአጠቃላይ አብዛኛው የውኃ ብክለት የሚፈጠረው
ብቻ አይፈጠርም። ዋነኛው የውኃ ብክለት በሰው ልጆች አማካይነት ነው። የሰው ልጆች
መንስኤ የሰው ልጆች የዕለት ኑሯቸውን ለማሳካት በካይ ነገሮችን በውኃ ውስጥ ስለሚጨምሩ ውኃ
በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ነው። ይህም የገጠርና ይበከላል። ስለሆነም ሰዎች ከእነዚህ አሉታዊ
የከተማ ተብሎ በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል። ተግባራት መታቀብ ይኖርባቸዋል። ይህ ከሆነ
ደግሞ ውኃ ንጹህ ስለሚሆን ሰዎች፣ እንስሳትና

፴፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 31


ዕፅዋት በውኃወለድ ምክንያት ከሚፈጠሩ የሚያመለክቱ ቍጥሮች ደረጃ አመልካች
በሽታዎች ነፃ ይሆናሉ። ቍጥሮች ይባላሉ። ምሳሌ አንደኛ፣ ሁለተኛ፣
/ክሪስ ውድፎርድ፣ ግንቦት 24/2014 አሻሽለው ካቀረቡት ሦስተኛ ወዘተ. አሁን «ደረጃ አመልካች
ጽሑፍ የተተረጎመ።) ቍጥሮች» የሚለውን ሐረግ በተለያየ ሁኔታ
አዳምጦ መረዳት (10 ደቂቃ) (አገላለፅ) እለዋለሁ።
ሥሩ መ. አሁን በተከፋ ድምፅ እለዋለሁ።
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን የቀረቡት [መ.ደረጃ አመልካች ቍጥሮች።]
ጥያቄዎች፣ ካዳመጣችሁት ምንባብ የወጡ
ናቸው። ባዳመጣችሁት መሠረት ጥያቄዎቹን መ. አሁን በደስተኛ ድምፅ እለዋለሁ።
“እውነት” ወይም “ሐሰት” እያላችሁ መልሱ። [መ.ደረጃ አመልካች ቍጥሮች]
“እውነት” ወይም “ሐሰት” ያላችሁበትንም
ምክንያት ግለጹ። መ. አሁን በሹክሹክታ እለዋለሁ።

መ. ዓረፍተነገሩ የሚገኝበትን ፊደል ስጠራ [መ.ደረጃ አመልካች ቍጥሮች።]


"እውነት" ወይም "ሐሰት" ካላችሁ በኋላ መ. አሁን ደግሞ ድምፄን ከፍ አድርጌ እለዋለሁ።
ምክንያታችሁን ትገልጻላችሁ።
[መ.ደረጃ አመልካች ቍጥሮች።]
መ. "ሀ"
እንሥራ
[ተ. ሐሰት፣ ምክንያቱም በምንባቡ መጀመሪያ መ. አሁን አብረን እንሥራ። ቍጥሩ መጣኝ
አብዛኛው የውኃ ብክለት ችግር ከራሱ ከውኃ ወይም ደረጃ አመልካች መሆኑን ለይተን
እንደማይፈጠር ተገልጿል።] እንናገራለን። ቍጥሩ መጣኝ ከሆነ
መ. በጣም ጥሩ! "ለ" አውራጣታችንን፣ ቍጥሩ ደረጃ አመልካች
ከሆነ ደግሞ አመልካች ጣታችንን እናወጣለን።
[ተ. እውነት፣ ምክንያቱም ፍሳሽ ቆሻሻ ወደውኃ
አካላት ሲቀላቀል ውኃውን የሚጠቀሙትን መ. አንድ
ሰዎችና እንስሳት ለልዩ ልዩ በሽታዎች [መተ. አውራ ጣት ያወጣሉ።]
ይዳርጋል።]
መ. አንደኛ
(መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት
እንዲሠሩ ያድርጉ። በመጨረሻም በትክክል [መተ. አመልካች ጣት ያወጣሉ።]
ያልተመለሱ ጥያቄዎችን በመመለስ መ. አራት
ግብረመልስ ይስጡ።)
[መተ. አውራ ጣት ያወጣሉ።]
ሰዋስው (10 ደቂቃ) መ. አምስተኛ

መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮች [መተ. አመልካች ጣት ያወጣሉ።]


ልሥራ መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ለመጣኝ ቍጥር
መ. የዛሬው ትምህርታችን መጣኝና ደረጃ ምሳሌ እንስጥ።
አመልካች ቍጥሮችን የሚመለከት ነው። [መተ. 1፣ 2፣ 3…]
ሁለት ዓይነት ቍጥሮች አሉ። 1፣ 2፣ 3
የምንላቸው ቍጥሮች ከሌላ ቃል አጠገብ መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ለደረጃ አመልካች
(ቀድመው ሲገቡ) የአንድን ነገር ብዛት ቍጥር ምሳሌ እንስጥ።
ያመለክታሉ። እነዚህ የአንድን ነገር መጠን [መተ. 1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ…]
(ብዛት) የሚያመለክቱ ቍጥሮች መጣኝ
መ. አሁን የመጀመሪያውን ምሳሌ እናንብብ።
ቍጥሮች ይባላሉ።
መ. በሌላ በኩል በነዚሁ ቍጥሮች ላይ “-ኧኛ” (የአንድ/የአንዲት ተማሪ ስም ይጥሩና
የሚል ቅጥያ ሊጨመርባቸው ይችላል፤ የመጀመሪያውን ዓረፍተነገር ያስነብቡ።)
እንደነዚህ ያሉ አንድ ነገር ያለበትን ደረጃ መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ያለው ቍጥር

32 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፴፪


የትኛው ነው?
[መተ. አንደኛ]
መ. በጣም ጥሩ! ቍጥሩ መጣኝ ነው ወይስ ደረጃ
አመልካች?
[መተ. ደረጃ አመልካች ቍጥር]
መ. በጣም ጥሩ! ደረጃ አመልካች ቍጥር ነው፤
ምክንያቱም ስለአልማዝ ደረጃ ይነግረናል።
መ. አሁን ሁለተኛውን ምሳሌ እናንብብ።
(የአንድ/የአንዲት ተማሪ ስም ይጥሩና ሁለተኛውን
ምሳሌ ያስነብቡ)
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ያለው ቍጥር
የትኛው ነው?
[መተ. አንድ]
መ. በጣም ጥሩ! ቍጥሩ መጣኝ ነው ወይስ ደረጃ
አመልካች?
[መተ. መጣኝ ቍጥር]
መ. በጣም ጥሩ! ቍጥሩ መጣኝ ነው፤ ምክንያቱም
የአሊን ወንድሞች ብዛት ይነግረናል።
ሥሩ
መ. አሁን የሚከተሉትን ዓረፍተነገሮች በግል
ሥሩ። በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣
በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር ከቀረቡት
ዓረፍተነገሮች ውስጥ የሚገኙትን ቍጥሮች
ከለያችሁ በኋላ፣ በፊት ለፊታቸው መጣኝ
ወይም ደረጃ አመልካች ቍጥር በማለት ጻፉ።
(መ.ለተማሪዎቹ ተግባሩን እንዲሠሩ 5 ደቂቃ
ይስጧቸው። ከሀ-ሠ ብቻ ያሉትን ጥያቄዎች
በክፍል ውስጥ እንዲሠሩ ያድርጉ። ተማሪዎቹ
ተግባሮቹን ሲሠሩ በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ
በአግባቡ መሥራታቸውን ያረጋግጡ፤
የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ። ከረ-ቀ
ያሉትን ጥያቄዎች የቤትሥራ ይስጧቸው።
ምሳሌዎቹን በሠሩበት መንገድ በመልሶቹ
ላይ ከተማሪዎቹ ጋር ይወያዩበት።ሠንጠረዥ
በማዘጋጀት ትክክለኛውን መልስ በሰሌዳው
ላይ ይጻፉላቸው።)

፴፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 33


አሟልተው ይናገራሉ።]
2ኛ ሳምንት ቆሻሻ
መ. በምንባቡ ሥር የቀረበውን ሥዕል በማስተዋል
ምንባቡ ስለምን እንደተጻፈ ግምታችሁን
4ኛ ቀን ተናገሩ።

የዕለቱ ትምህርት ይዘት [ተ. ሥዕሉን በማስተዋል የተለያዩ ግምቶችን


ይናገራሉ።]
• ማንበብ
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ማስታወሻ
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ የሰጧቸውን የቤትሥራ
ማንበብን መቀጠል፡- በማንበብ ሂደት ያልገባን
ተማሪዎች ደብተራቸውን ተለዋውጠው
ነገር ሲያጋጥመን ቀጣይ ሁለት ወይም ሦስት
እንዲያርሙ ካደረጉ በኋላ ግብረመልስ
ዓረፍተነገሮችን በማንበብ ስለጉዳዩ የተገለፀ
ይስጡ)
ነገር ካለ አንብበን የምንረዳበት የንባብ ሂደት
[መልስ፡- ጥያቄ ረ እና ሰ ደረጃ አመልካች ሲሆኑ፤ ራስን የመከታተያ ስልት ነው። በዚህ መንገድ
ቀ እና ሸ ደግሞ መጣኝ ቍጥሮች ናቸው።] ግራ መጋባታችን ካልተቀረፈ ግን ሌላ ዘዴ
መሞከር ያስፈልጋል።
ማንበብ (35 ደቂቃ)
የቆሻሻ አፈጣጠርና
ልሥራ
የሚያስከትላቸው ችግሮች መ. ተማሪዎች በምታነቡበት ጊዜ ያልገባችሁ
ቅድመንባብ (10 ደቂቃ) ነገር ሲያጋጥማችሁ በቀጣዮቹ ዓረፍተነገሮች
ውስጥ በሚገባ የተብራራ ሊሆን ስለሚችል
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
ወደፊት ሁለት ወይም ሦስት ዓረፍተነገሮች
እንሥራ በማንበብ ስለጉዳዩ መረዳት ትችላላችሁ።
መ. “የቆሻሻ አፈጣጠርና የሚያስከትላቸው “ማንበብን መቀጠል” እንዴት እንደሚተገበር
ችግሮች” በሚል ርዕስ የቀረበ ምንባብ አንብቤ ላሳያችሁ።
እናነባለን። ከዚያ በፊት ግን የቆሻሻ መፈጠሪያ
(መ. ከሦስተኛው አንቀጽ የመጀመሪያውንና
ምክንያቶችንና ቆሻሻ የሚያስከትለውን ጉዳት
ሁለተኛውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።)
በቢጋር ሠንጠረዥ እንዘረዝራለን።
መ. የተከማቸ ቆሻሻ አካባቢን እንዴት
(በመማሪያ መጽሐፍ የቀረበውን የምክንያትና እንደሚበክል አልገባኝም። ምናልባት
ውጤት የቢጋር ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ በቀጣዮቹ ዓረፍተነገሮች የተከማቸ ቆሻሻ
ይሣሉላቸው።) ብስባሽ እንዴት አካባቢን እንደሚበክል
[መተ. የቢጋር ሠንጠረዡን ይሥላሉ።] ተገልጾ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ወደፊት
ማንበቤን ልቀጥል።
(መ. በሠንጠረዡ በተገለጸው ሁኔታ ቆሻሻ
በየቦታው በመፀዳዳት እንደሚፈጠር፣ በዚሁ (መ. አንቀጹን አንብበው ይጨርሱ።)
መንገድ የተፈጠረ ቆሻሻም እንደተቅማጥ ላሉ
መ. አሃ! አሁን ገባኝ፤ ከብስባሽ ቆሻሻ የሚወጣው
በሽታዎች እንደሚዳርግ ይንገሯቸው።)
ጋዝ አየርን ይበክላል። የተበከለውም አየር
ሥሩ የሰዎችንና የእንስሳትን የአተነፋፈስ ሥርዓት
መ. ከላይ በሠራነው መሠረት የቆሻሻ መፈጠሪያ በማቃወስ ለበሽታ ይዳርጋቸዋል።
ምክንያቶቹንና የሚያስከትሉትንም ጉዳት ሥሩ
በሠንጠረዡ ውስጥ አሳዩ። (ለ5 ደቂቃ ያህል
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ። "1" እና "2"
ተማሪዎችን እያሳተፉ ይሥሩ።)
በማለት በቍጥር ይሰይሟቸው።)
[ተ. የቢጋር ሠንጠረዡን በምክንያትና በውጤት

34 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፴፬


መ. አሁን አንድ ቍጥሮች የመጀመሪያውን ወይም “ሐሰት” ያላችሁበትን ምክንያትም
አንቀጽ ድምፅ እያሰማችሁ አንብቡ፤ 2 ግለጹ።
ቍጥሮች ደግሞ ድምፅ ሳታሰሙ እያነበባችሁ
መ. ዓረፍተነገሩ የሚገኝበትን ፊደል ስጠራ
ተከታተሉ።
"እውነት" ወይም "ሐሰት" ካላችሁ በኋላ
[ተ. 1 ቍጥሮች ድምፅ እያሰሙ ያነባሉ፤ 2 ምክንያታችሁን ተናገሩ።
ቍጥሮች በለሆሳስ እያነበቡ ይከታተሉ።]
መ. "ሀ"
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ አንድ ቍጥሮች
[ተ. እውነት፣ ምክንያቱም ፋብሪካዎች በሥራ
የአንቀጹን ዋና ሀሳብ ተናገሩ፤ 2 ቍጥሮች
ሂደት የሚፈጥሯቸውን ተረፈምርቶች
ደግሞ ዝርዝር ሀሳቦችን ተናገሩ።
ሲያስወግዱ ቆሻሻ እንደሚፈጠር በምንባቡ
[ተ. 1 ቍጥሮች የአንቀጹን ዋና ሀሳብ ይናገራሉ፤ ተገልጿል።]
2 ቍጥሮች ዝርዝር ሀሳቦችን ይናገራሉ።]
መ. "ለ"
(መ. ቀሪዎቹንም አንቀጾች በዚህ ዓይነት
[ተ. ሐሰት፣ ምክንያቱም ኤች.አይ.ቪ./
የተማሪዎችን ሚና እየቀያየሩ እንዲያነቡ
ኤድስ በቆሻሻ ምክንያት የሚመጣ በሽታ
ያድርጉ።)
አይደለም።]
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) መ. "ሐ"
እንሥራ [ተ. እውነት፣ ምክንያቱም በአግባቡ ያልተወገደ
መ. ባነበባችሁት መሠረት የአንብቦ መረዳት ቆሻሻ ለዝንቦች፣ ለአይጦችና ለልዩ ልዩ
ጥያቄዎችን እንመልሳለን። የማነብላችሁ ነፍሳት መራቢያ እንደሚሆን በአንቀጽ 2
ዓረፍተነገር ከምንበቡ ሀሳብ ጋር የሚስማማ ተገልጿል።]
ከሆነ “እውነት” ከምንባቡ ሀሳብ ጋር
የማይስማማ ከሆነ ደግሞ “ሐሰት” እያልን መ. ተማሪዎችን ከ3-5 አባላት ባለው ቡድን
እንመልሳለን። ለመልሳችን ምክንያት አደራጅተው የቡድን መሪ ያስመርጡ።
እንሰጣለን። በመቀጠል በተግባር “2” ሥር ያሉትን
ጥያቄዎች እየተወያዩ እንዲሠሩ ያድርጉ።
መ. ቆሻሻ ከሚፈጠርባቸው መንገዶች አንዱ በመጨረሻም ከየቡድኑ ተማሪዎችን
በየቦታው መፀዳዳት ነው። በመምረጥ መልሳቸውን ለክፍሉ ያንፀባርቁ።
[መተ. እውነት፣ ምክንያቱም የመጀመሪያው (መ.ተግባር ሦስትን እቤታቸው ሠርተው
አንቀጽ ውስጥ “ሽንታችንንና ዐይነምድራችንን እንዲመጡ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
በመፀዳጃቤቶች ከመፀዳዳት ይልቅ በየቦታው
እንፀዳዳለን። ይህን በማድረጋችንም ቆሻሻ
እንፈጥራለን” ይላል።] 5ኛ ቀን
መ. በቆሻሻ ምክንያት ከሚመጡ በሽታዎች መካከል
አንዱ ደምግፊት ነው። የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
[መተ. ሐሰት፣ ምክንያቱም በሁለተኛው • ቃላት
አንቀጽ ከተገለፁት በቆሻሻ ምክንያት • መጻፍ
ከሚመጡት በሽታዎች መካከል ደምግፊት
አልተካተተም።]
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ሥሩ ሥሩ
መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን፣
(መ. ሁሉም ተማሪዎች መጻፋቸውን ተዘዋውረው
የሚገኘውን የመጀመሪያውን የአንብቦ
ያረጋግጡ።)
መረዳት ተግባር ሥሩ። ዓረፍተነገሮቹ የያዙት
ሀሳብ ትክክል ከሆነ “እውነት” ትክክል ካልሆነ መ. ተማሪዎች ደብተራችሁን ተቀያይራችሁ
ደግሞ “ሐሰት” በማለት መልሱ።”እውነት” በጻፋችሁት አንቀጽ አስተያየት ተሰጣጡ።

፴፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 35


(አንድ ወይም ሁለት ተማሪዎች እንዲያቀርቡ የከበዳቸውን ይደግፉ፤ በመጨረሻም ከላይ
ካደረጉ በኋላ፣ የማስተካከያ አስተያየት የቀረቡትን መልሶች መሠረት አድርገው
ይስጡና ወደእለቱ ትምህርት ይሸጋግሩ።) ግብረመልስ ይስጡ።)

ቃላት (10 ደቂቃ) መጻፍ (25 ደቂቃ)


ለቃላትና ለሐረጋት ፍቺ መስጠት ድርሰት መጻፍ (15 ደቂቃ)
ልሥራ በምክንያትና ውጤት ስልት የድርሰት
መ. ተማሪዎች ዛሬ “የቆሻሻ አፈጣጠርና ረቂቅ መጻፍ
የሚያስከትላቸው ችግሮች” ከሚለው ምንባብ ልሥራ
የወጡ ቃላትንና ሐረጋት በምንባቡ መሠረት መ. ባለፈው ሳምንት ስለምክንያትና ውጤት
ያላቸውን ፍቺ እንመለከታለን። የቢጋር አዘገጃጀት ተምረን ነበር። ዛሬ ደግሞ
[መ.“በዚሁ ሳቢያ” የሚለው ሐረግ በዚህ ምክንያት፣ የምክንያትና ውጤት የቢጋር ሠንጠረዥን
በዚሁ የተነሳ የሚል ፍቺ አለው።] በመጠቀም እንዴት መጻፍ እንደሚቻል
እንመለከታለን። በመጀመሪያ የሁለቱን ቃላት
መ. ሌላ ቃል ልጨምር ተከታተሉኝ።
ልዩነት ለማየት እንሞክር።”ምክንያት” አንድ
[መ.“ነቃ” ሲል አወቀ፣ ተማረ ማለት ነው።] ድርጊት ለምን እንደተከሰተ/እንደተፈፀመ
የሚነግረን ነው። ለምሳሌ “ድስቱ እሳቱ ላይ
እንሥራ ብዙ በመቆየቱ ወጡ አረረ” ብንል፣ የድስቱ
መ. በመቀጠል ሌሎች ቃላትን ከምንባቡ ወስደን እሳቱ ላይ ብዙ መቆየት ለወጡ ማረር
ፍቻቸውን አብረን እንመለከታለን። ምክንያት ሲሆን የወጡ ማረር ደግሞ ውጤት
መ. “ሰረገ” የሚለው ቃል ምን ፍቺ አለው? ነው።

[መተ. ወደ ውስጥ ገባ] እንሥራ


መ. አሁን "በትምህርት ከፍተኛ ውጤት
መ. በጣም ጥሩ!
የማስመዝገብ ምስጢር" በሚል ርዕስ አንቀጽ
መ. “ቀጨጨ” የሚለው ቃል ፍቹ ምንድን ነው? ለመጻፍ የሚያስችል የቢጋር ሠንጠረዥ
[መተ. ኮሰሰ፣ ቀጠነ] እናዘጋጃለን። (የሚከተለውን የቢጋር
ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ ያዘጋጁላቸው።)
መ. ጥሩ ነው።
ሥሩ ምክንያት ውጤት
መ. አሁን ደግሞ ከላይ በሠራነው መሠረት በትምህርት
በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን የቀረቡትን ከፍተኛ ውጤት
ቃላትና ሐረጋት ከተመሳሳይ ፍቻቸው ጋር ማስመዝገብ።
አዛምዱ።
መ. ጎበዝ ተማሪዎች በትምህርታቸው ከፍተኛ
መ. ቃሉ የሚገኝበትን ተራቍጥር ስጠራ ውጤት ለማስመዝገብ ከሚያስችሏቸው
ተመሳሳይ ፍቹን ትነግሩኛላችሁ። ምክንያቶች አንዱ ምን ሊሆን ይችላል?
መ. "1" [መተ. የመምህርን ገለፃ በትኩረት መከታተል]
[ተ. ሠ. ደረቅ ቆሻሻ] (መ. ምክንያት በሚለው ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)
መ. "2" መ. ሌላስ?
[መ. ሐ. ሳቢ] [መተ. በክፍል ተግባራት በንቃት መሳተፍ]
(ቀሪዎቹን በዚሁ ዓይነት ያሠሩ።) መ. በጣም ጥሩ! ሌላ?
(ተማሪዎች ተግባሩን እንዲሠሩ 5 ደቂቃ [መተ. የቤትሥራዎችን በአግባቡ መሥራት]
ይስጧቸው፤ ሲሠሩ እየተዘዋወሩ ይከታተሉ፤

36 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፴፮


መ. ሌላስ? ያነበብኩትንም ጽፌ አሳይችኋለሁ። (“አኳኋን”
የሚለውን ቃል መጀመሪያ ያንብቡላቸው፤
[መተ. በእቅድ ማጥናት]
ከዚያም ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው)
(መ. ሁሉንም ምክንያቶች "ምክንያት" በሚለው
መ. እንደ “ጠራሁ” እና “ነገርኩ”ያሉ ቃላት ላይ
ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)
“ኣቸው” የሚል ቅጥያ ሲጨመርም እነዚህን
መ. አሁን ባዘጋጀነው የቢጋር ሠንጠረዥ ፊደሎች (ኋ፣ኳ ወዘተ.) እንጠቀማለን እነዚህ
መሠረት የተጻፈውን አንቀጽ አነብላችኋለሁ። ቃላት ላይ “-ኣቸው”ን ጨምሬ ላሳያችሁ
(መ. የሚከተለውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።) ጠራሁ -ኣቸው = ጠራኋቸው
በትምህርት ከፍተኛ ውጤት ነገርኩ - ኣቸው = ነገርኳቸው
የማስመዝገብ ምስጢር እንሥራ
ጎበዝ ተማሪዎች በትምህርታቸው ከፍተኛ መ. አሁን ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ አብረን
ውጤት ለማስመዝገብ ያስቻሏቸው ምክንያቶች እንሥራ። “እንዳስተማራችሁ” የሚለው ቃል
ምንድን ናቸው? ጎበዝ ተማሪዎች መምህራቸው ላይ “-ኣቸው” ስንጨምር እንዴት ይጻፋል?
ገለፃ ሲያደርጉላቸው በትኩረት ይከታተላሉ።
[መተ. እ ን ዳ ስ ተ ማ ራ ች ሁ - ኣ ቸ ው =
ከዚያም በክፍል ውስጥ በሚሰጡ ልዩ ልዩ
እንዳስተማራችኋቸው]
ተግባራት ላይ በንቃት ይሣተፋሉ። ከዚያም
ሌላ የሚሰጧቸውን የቤትሥራዎች በአግባቡ መ. በጣም ጥሩ! “አጠብኩ” የሚለው ቃል ላይ
ስለሚሠሩ በክፍል የተማሩትን በጥልቀት “-ኣቸው” ሲጨመር እንዴት ይጻፋል?
መረዳት ይችላሉ። እቅድ አዘጋጅተው ዘወትር [መተ. አጠብኩ-ኣቸው = አጠብኳቸው]
ስለሚያጠኑም ሁልጊዜ ለፈተና ዝግጁ ናቸው።
በነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ጎበዝ ተማሪዎች መ. በጣም ጥሩ!
በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ያመጣሉ። ሥሩ
ሥሩ መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን የሚገኘውን
መ. አሁን የምክንያትና ውጤት የቢጋር ተግባር በራሳችሁ ሥሩ። በጽሑፋችሁ
ሠንጠረዥን በመጠቀም አንቀጽ እንዴት በተዘረዘሩት ቃላት ላይ “_ኣቸው” ሲጨመር
እንደሚጻፍ ተመልክተናል። አሁን ደግሞ እንዴት እንደሚጻፍ አሳዩ።
ባለፈው ሳምንት የግብርና ምርት የሚቀንሱ
(መ.ከሀ-ሐ ያሉትን ቃላት የክፍልሥራ እንዲሠሩ
ምክንያቶችን በተመለከተ ያዘጋጃችሁትን
ያድርጉ። ተግባሩን ለመሥራት 5 ደቂቃ
የቢጋር ሠንጠረዥ በመጠቀም በምክንያትና
ይስጧቸው። ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ
ውጤት የተደራጀ አንቀጽ ትጽፋላችሁ።
እየተዘዋወሩ በትክክል መሥራታቸውን
አንቀጹን ስትጽፉ፣ በዚህም ምክንያት፣ በዚህ
ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤
የተነሳ፣ ምክንያቱም ወዘተ. የመሳሰሉትን
በመጨረሻም ከመ-ረ ያሉትን የቤትሥራ
አያያዥ ቃላት ልትጠቀሙ ትችላላችሁ።
ይስጧቸው።)
(መ.ተማሪዎች አንቀጽ እንዲጽፉ 12 ደቂቃ
ይስጧቸው። ተማሪዎቹ ሲጽፉ በየቡድኑ
እየተዘዋወሩ ይከታተሉ፤ የከበዳቸውን
ተማሪዎች ይደግፉ።)
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ )
ልሥራ
መ. ዛሬ የተወሰኑ ፊደሎችን አጻጻፍ
እንለማመዳለን። በተለይም እንደ “ኋ” ፣ “ኳ”፣
“ሯ”፣ “ሏ”፣ “ቿ” ፊደሎች ላይ እናተኩራለን።
መ. አሁን አንድ ቃል አነብላችኋለሁ፤

፴፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 37


አስታውሰው ይናገራሉ።]
6ኛ ቀን 11ለ. ማንበብ (8 ደቂቃ)
ልሥራ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. ተማሪዎች ዛሬ አቀላጥፎ የማንበብ
• አቀላጥፎ ማንበብ ልምምድ እናደርጋለን። ባለፈው ሳምንት
• መናገር እንደተነጋገርነው ይህ ተግባር የማንበብ
ፍጥነታችሁን፣ በትክክል የማንበብና ምንባቡን
• ሰዋስው
በተገቢው የድምፅ ቃና (ለዛ) የማንበብ
ችሎታችሁን ያዳብራል።
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) መ. ተማሪዎች በመጀመሪያ እኔ አነባለሁ።
ሥሩ ከዚያም እናንተ ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ
ታነባላችሁ። አሁን በ2ኛው ሳምንት፣
ባለፈው ክፍለጊዜ የሰጧቸውን የቤትሥራ
በ4ኛው ቀን የሚገኘውን “የቆሻሻ አፈጣጠርና
መሥራታቸውን ያረጋግጡ።
የሚያስከትላቸው ችግሮች” በሚል ርዕስ
መ. ቃሉን ስጠራ፣ ቃሉ ላይ "-ኣቸው" ሲጨመር ከቀረበው ምንባብ ሁለተኛውን አንቀጽ
እንዴት እንደሚጻፍ ሰሌዳው ላይ ጽፋችሁ አነብላችኋለሁ። (“ቆሻሻ የሚፈጠርበት
ታሳዩኛላችሁ። መንገድና የሚያስከትላቸው ችግሮች”
መ. "የሚያስከትሉ" የሚለውን ምንባብ ሁለተኛውን አንቀጽ
ያንብቡላቸው።)
[ተ. "የሚያስከትሏቸው" ብለው በሰሌዳው ላይ
ይጽፉሉ።] [መ. ድምጽ በማሰማት ያነባሉ።]
መ. "ያከማቹ" እንሥራ
[ተ. "ያከማቿቸው" ብለው በሰሌዳው ላይ መ. አሁን ያነበብኩላችሁን አንቀጽ ሁላችንም
ይሠራሉ።] በአንድ ላይ ድምፅ እያሰማን እናንብብ።
(ተማሪዎች ከርስዎ ጋር ድምፃቸውን ከፍ
መ. "ሰበሰብኩ" አድርገው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. "ሰበሰብኳቸው" ብለው በሰሌዳው ላይ [መተ. መምህርና ተማሪዎች ድምፅ እያሰሙ
ይጽፋሉ።] ያነባሉ።]
(መ. በትክክል ያልተጻፉትን አስተካክለው ሥሩ
በመጻፍ ግብረመልስ ይስጡ።) መ. አሁን ደግሞ ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ተራበተራ
አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ አንዳችሁ ደግሞ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) እያዳመጣችሁ ማስታወሻ ያዙ።
የቆሻሻ አፈጣጠርና መ. ጓደኞቻችሁ በሚያነቡበት ጊዜ በምን ያህል
የሚያስከትላቸው ችግሮች ቃላት ላይ ስህተት እንደተፈጸመ፣ በተሠጠው
ጊዜ ምን ያህል ቃላት እንዳነበቡ ማስታወሻ
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) ያዙ።
ሥሩ (መ. ተማሪዎችን በቡድን ሲያደራጁ “ጥሩ
መ. "የቆሻሻ አፈጣጠርና የሚያስከትላቸው የሚያነቡትን” ደከም ካሉት አንባቢዎች ጋር
ችግሮች በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ቢያቀናጇቸው የተሻለ ነው። ተማሪዎች
ከማንበባችሁ በፊት አንድ ጥያቄ መልሱ። ማንበብ ሲጀምሩ ሰዓት ይያዙላቸው፤ 2
መ. ቆሻሻ የሚፈጠርባቸውን ምክንያቶች ደቂቃም ይስጧቸው፤ በ2 ደቂቃ የተነበበውን
ተናገሩ። ቃላት ብዛት እንዲቆጥሩ ያድርጉ፤
የተሳሳቷቸውንም ቃላት ብዛት ቈጥረው
[ተ. ቆሻሻ የሚፈጠርባቸውን ምክንያቶች እንዲመዘግቡ ያድርጉ። በመጨረሻም

38 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፴፰


ተማሪዎች የመዘገቡትን ማስታወሻ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ይሰብስቡና ፈጣኖቹንና ፈጣን ያልሆኑትን
አንባቢዎች ይለዩ፤ ባለፉት ክፍለጊዜያት መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮች
ከታየው የማንበብ ፍጥነትና የቃላት ስህተት እንሥራ
አንፃር የታየውን መሻሻል ይገምግሙ፤ መ. ባለፈው ሳምንት ቍጥሮቹን የሚገልጹ ሁለት
የተማሪዎችን የማንበብ ፍጥነትና ትክክለኛነት ሐረጋትን ተመልክተናል። እነዚህን ሐረጋት
ለማሻሻል የሚረዳ ስልት ይንደፉ።) ልናስታውስ እንችላለን?

መናገር (15 ደቂቃ) [መተ. መጣኝ ቍጥሮች እና ደረጃ አመልካች


ቍጥሮች ናቸው]
ልሥራ
መ. በመጀመሪያ የመጣኝ ቍጥር ምንነት መናገር
መ. ዛሬ “የውኃና የአየር ብክለትን” በተመለከተ
እንችላለን?
የቡድን ውይይት እናደርጋለን። የውይይቱ
ትኵረት የውኃና የአየር ብክለት ምክንያቶችና [መተ. መጣኝ ቍጥር የአንድን ነገር ምን
ጉዳቶች ናቸው። በመጀመሪያ አንድ ምሳሌ ያህልነት የሚያሳይ ቍጥር ነው።]
እኔ እሠራለሁ።
መ. አሁን ደግሞ የደረጃ አመልካች ቍጥር
[መ. ውኃን ከሚበክሉ ነገሮች አንዱ መርዛማ ምንነት እንናገር።
ንጥረነገሮች በዝናብ እየታጠቡ ወደወንዞችና [መተ. ደረጃ አመልካች ቍጥር አንድ ነገር
ሐይቆች መቀላቀላቸው ነው። በዚህም ያለበትን ደረጃ የሚያመለክት ቍጥር ነው።]
ምክንያት ውኃ ውስጥ የሚኖሩ እንስሳትና
ነፍሳት ይሞታሉ።] መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ ለመጣኝ ቍጥር ምሳሌ
እንስጥ።
እንሥራ
መ. አንድ ምሳሌ ደግሞ አብረን እንሥራ። ሌላ [መተ. 1፣ 2፡ …]
ለውኃ ወይም ለአየር ብክለት ምክንያት ምን መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ለደረጃ አመልካች
ሊሆን ይችላል? ቍጥሮች ምሳሌ እንስጥ።
[መተ. ከመፀዳጃቤቶች የሚለቀቅ ቆሻሻ [መተ. 1ኛ፣ 2ኛ….]
ወደወንዞች መቀላቀል]
መ. አሁን ለምሳሌ የቀረበውን ዓረፍተነገር
(ተማሪዎች ሌላም መልስ ሊሠጡ ይችላሉ።) እናነባለን።
መ. በጣም ጥሩ! በዚህ ምክንያት የሚደርስ ጉዳት
(የአንድ ተማሪ ስም ይጥሩና ለምሳሌ የቀረበውን
ልንናገር እንችላለን?
ዓረፍተነገር ያስነብቡ።) “የቆሻሻ አይያዝና
[መተ. ውኃውን የተጠቀሙ እንስሳትና ሰዎች አወጋገድ 4 ደረጃዎች አሉት።”
ለበሽታና ሞት ይዳረጋሉ።] መ. 4 የሚለው ቍጥር መጣኝ ነው ወይስ ደረጃ
ሥሩ አመልካች?
መ. በዚህ ዓይነት ካነበባችሁትና ካዳመጣችሁት፣ [መተ. መጣኝ ቍጥር]
እንዲሁም ከዚህ በፊት ከምታውቁት
መ. በጣም ጥሩ! ቍጥሩ መጣኝ ነው፤ ምክንያቱም
በመነሳት በቡድን ሆናችሁ በውኃና በአየር
የቆሻሻ አወጋገድ ደረጃዎች መጠን ወይም
ብክለት ምክንያቶችና ጉዳቶች (ውጤቶች)
ብዛት 4 መሆናቸውን ይገልፃል።
ላይ ተወያዩ።
መ. 4 የሚለውን ቍጥር በፊደል ጻፉ?
(መ. በመጨረሻ ከየቡድኑ አባላት አንድ
አንድ ተማሪ በማስወጣት እንዲያቀርቡ (አንድ ተማሪ ወጥታ/ቶ ሰሌዳው ላይ እንድትጽፍ
ያድርጉ፤ ለውይይቱ 10 ደቂቃ ይስጧቸው፤ እንዲጽፍ ያነሳሱ)
በመጨረሻም ማጠቃለያ ይስጡ።) [መተ. አራት]
መ. በጣም ጥሩ

፴፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 39


ሥሩ
መ. አሁን 2ኛ ሳምንት፣ 6ኛ ቀን በስዋስው
ንዑስ ክፍል ሥር ከምሳሌው ቀጥሎ ያሉትን
ተግባሮች ሥሩ። በመጀመሪያ በዓረፍተነገሮች
ውስጥ ያሉትን ቍጥሮች ለይታችሁ ጻፉ፤
በመቀጠል ቍጥሮቹ መጣኝ ወይም ደረጃ
አመልካች መሆናቸውን ከፊት ለፊቱ ጻፉ፤
በመጨረሻም ቍጥሮቹን በፊደል ጻፉ።
(መ.ተማሪዎች ተግባሩን እንዲሠሩ 5 ደቂቃ
ይስጧቸው። ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ
በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ በትክክል
መሥራታቸውን ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን
ተማሪዎች ይደግፉ።)
(መ.ምሳሌውን በሠሩበት መንገድ በመልሶቹ
ላይ ከተማሪዎቹ ጋር ይወያዩ። ሠንጠረዥ
በማዘጋጀት ትክክለኛ መልሶቹን በሰሌዳው
ላይ ይጻፉላቸው። ተግባር “2”ን የቤትሥራ
ይስጧቸው።)

40 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፵


[መተ. በለምነቱ]
3ኛ ሳምንት የአካባቢ ጥበቃ
መ. ማብሰያ-ነት (ነጣጥለው ያንብቡላቸው)
[መተ. ማብሰያ-ነት] (ተማሪዎች ከርስዎ ጋር
7ኛ ቀን አብረው ነጣጥለው ያንብቡ።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መ. አሁን ደግሞ ቃሉን አጣምረን እናንብበው።
• የቃላት ጥናት [መተ. ማብሰያነት]
• ማንበብ ሥሩ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን
የቀረቡትን ቃላትና ቅጥያዎቻቸውን በቡድን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ሆናችሁ፣ የቡድን መሪያችሁን እየተከተላችሁ
ሥሩ በመጀመሪያ በመነጠል፣ ከዚያም በማጣመር
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ በሰዋስው ንዑስ ክፍል አንብቡ።
የተሠጠውን የቤትሥራ ደብተራቸውን (መ. ተማሪዎች ቃላቱን በቡድን ካነበቡ በኋላ
ተለዋውጠው እንዲያርሙ ያድርጉ።) የተወሰኑ ተማሪዎችን እያስነሱ እንዲያነቡ
መ. በአንቀጹ ውስጥ የሚገኘውን ቍጥር ስጠራ ያድርጉ። ተማሪዎች ሲያነቡ ከተሳሳቱ
የቁጥሩን ዓይነት ትናገራላችሁ። እንዴት በትክክል ማንበብ እንዳለባቸው
ያሳዩ።)
መ. ስድስተኛ
[ተ. ደረጃ አመልካች ቍጥር] ማንበብ (28 ደቂቃ)
መ. ስድስት በኢትዮጵያ የደን መመናመን
[ተ. መጣኝ ቍጥር] መንስኤዎችና የሚያስከትሏቸው
መ. ሦስት ችግሮች
[ተ. መጣኝ ቍጥር] ቅድመንባብ (8 ደቂቃ)
(መ. የቀሩትን በዚህ ዓይነት ያሠሩ። በትክክል የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
ያልተመለሱትን በማረም ግብረመልስ ልሥራ
ይስጡ።)
መ. ዛሬ “በኢትዮጵያ የደን መመናመን
መንስኤዎቹና ውጤቶቹ” በሚል ርዕስ
የቃላት ጥናት (7 ደቂቃ) የቀረበውን ምንባብ እናነባለን። ከዚያ በፊት
መነጠልና ማጣመር ግን ደኖች የሚመናመኑበትን ምክንያትና
የሚያስከትለውን ጉዳት እንመልከት።
እንሥራ (የሚከተለውን የምክንያትና ውጤት የቢጋር
መ. “በኢትዮጵያ የደን መመናመን መንስኤዎቹና ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
ውጤቶቹ” በሚል ርዕስ በቀረበው ምንባብ
ውስጥ ረጃጅምና ውስብስብ ናቸው ተብለው ለደኖች የደኖች
የተገመቱ ቃላት ተነጣጥለው ቀርበዋል። መመናመን መመናመን
እነዚህን ቃላት እያጣመርን የማንበብ
ምክንያቶች የሚያስከትለው
ልምምድ እናደርጋለን።
ጉዳት
ዛፎችን ለማገዶ
መ. በ-ለም-ነት-ኡ (ነጣጥለው ያንብቡላቸው) የአፈር መሸርሸር
መቁረጥ
[መተ. በ - ለም - ነት - ኡ] (ተማሪዎች ከርስዎ
ጋር አብረው ነጣጥለው እንዲያነቡ ይድርጉ።)
መ. አሁን ደግሞ ቃሉን አጣምረን እናንብበው።

፵፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 41


መ. ይህ የቢጋር ሠንጠረዥ የሚያሳየን ደኖች አንብቦ መረዳት (10 ደቂቃ )
ከሚመናመኑበት ምክንያት አንዱ ዛፎችን
ለማገዶ ሲባል መቆረጥ ነው። ዛፎች
የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች
በመቆረጣቸው ምክንያት አፈሩ ይጋለጥና ሥሩ
በውኃና በንፋስ እንደሚጠረግም ያመለክታል። መ. ምንባቡን አንብባችኋል። አሁን በመጽሐፋችሁ
እንሥራ በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን የሚገኘውን
የአንብቦ መረዳት ተግባር ሥሩ ።
መ. ለደኖች መመናመን ሌላ ምክንያት መግለጽ
እንችላለን? መ. ጥያቄ “1”ን ልታነቡልኝ ትችላላችሁ? (አንድ/
ዲት ተማሪ ይምረጡ።)
[መተ. ዛፎችን ለግንባታ ሲባል መቁረጥ]
[ተ. ከብዙ ዓመታት በፊት ከሀገሪቱ መሬት ምን
መ. ለደኖች መመናመን ሌላው ምክንያትስ
ያህሉ በደን ተሸፍኖ ነበር?]
ምንድን ነው?
መ. ሀሳቡ የተገለፀበትን አንቀጽ ፈልጋችሁ
[መተ. እርሻ ለማስፋፋት ሲባል ደኖችን
አግኙ?
መመንጠር]
[ተ. አንቀጽ አንድ]
ሥሩ
መ. ከላይ በሠራነው መንገድ በተዘጋጀላችሁ መ. በአንቀጽ አንድ ውስጥ ምን ያህሉ መሬት
ሠንጠረዥ ውስጥ ደኖች የሚመናመኑበትን በደን ተሽፍኖ ነበር ይላል?
ምክንያትና የሚያሰከትለውን ጉዳት ዘርዝሩ። [ተ. 40 በመቶ]
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ ) መ. ስለዚህ ከቀረቡት ምርጫዎች ውስጥ መልሱን
ሥሩ የያዘው የትኛው አማራጭ ነው?
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ በጥንድ ያደራጁ።) [ተ. መ]
መ. አሁን በመጽሐፋችሁ የቀረበውን ምንባብ መ. በጣም ጥሩ፣ ሌሎቹን ጥያቄዎች በዚሁ
በግል ድምፅ ሳታሰሙ አንብቡ። ምንባቡን መሠረት ሥሩ።
በምታነቡበት ጊዜ ያልገባችሁ ነገር ካለ
ወደፊት ማንበባችሁን ስትቀጥሉ ግልጽ (የመጀመሪያው ተግባር በግል በቃል የሚሠራ
ሊሆንላችሁ ስለሚችል ማንበባችሁን ሲሆን፣ ሁለተኛው ተግባር ደግሞ ክፍል ውስጥ
አታቋርጡ። በቡድን የሚሠራ ነው። ተግባር ሦስት ደግሞ
የቤትሥራ ይስጧቸው።)
(መ. እስከ 4ኛው አንቀጽ ድረስ ብቻ አንብበው
እንዲያቆሙ ይንገሯቸው። አብዛኛዎቹ
ተማሪዎች አራቱን አንቀጾች አንብበው 8ኛ ቀን
መጨረሳቸውን ሲያረጋግጡ ያስቁሙ። )
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. አሁን በምጠይቃችሁ ጥያቄዎች ላይ በጥንድ
ትነጋገራላችሁ። በሦስተኛው አንቀጽ • ቃላት
የተገለፀው የደን መመናመን ምክንያት • መጻፍ
ምንድን ነው?
[ተ. በመልሱ ላይ በጥንድ ይነጋገራሉ። ]
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መ. ቀጣዮቹ አንቀጾች በምን ላይ እንደሚያተኩሩ
ገምቱ። ሥሩ
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ የሠጡትን የቤትሥራ
[ተ. ይገምታሉ።] ተዘዋውረው ይመልክቱ። የአንድ ወይም
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ። የሁለት ተማሪዎችን ሥራ ለምሳሌ ያህል
ስታነቡም የግምታችሁን ትክክለኛነት ያስቀርቡ፤ ከዚያም በቀረበው አንቀጽ
አረጋግጡ። የማስተካከያ አስተያየት ይስጡ።)

42 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፵፪


ቃላት (10 ደቂቃ) ቀን የቀረቡላችሁን ቃላት በመጀመሪያ
በምንባቡ ውስጥ የያዙትን ፍቺ ጻፉ። ከዚያም
ቃላትን በዓረፍተነገር ውስጥ መጠቀም ይህንኑ ፍቻቸውን የሚያሳዩ ዓረፍተነገሮችን
ልሥራ መሥርቱ።
መ. ባለፈው ሳምንት ከምንባቡ የወጡ ቃላትን መ. ቃሉን ስጠራ ቃሉ በምንባቡ ውስጥ ያለውን
ፍቺ ለማየት ሞክረናል። ዛሬ ደግሞ ከምንባቡ ፍቺ ትነግሩኛላችሁ። ከዚያም ፍቹን
ቃላትን እያወጣን በምንባቡ ውስጥ የያዙትን የሚያሳይ ዓረፍተነገር ትሠራላችሁ።
ፍቺ መሠረት በማድረግ ዓረፍተነገር
መ. መስፋፋት
እንመሠርታለን።
መ. “ተመናመነ” የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ
[ተ. መጨመር]
“ቀነሰ” የሚል ፍቺ አለው። በዚሁ ፍቺው መ. ዓረፍተነገር ሥሩበት።
ዓረፍተነገር መሥርቼ ላሳያችሁ።
[ተ. የኢንዱስትሪ መስፋፋት ለሀገር ዕድገት
[መ. ዛፎች ለቤት መሥሪያነት በመቆረጣቸው ጠቃሚ ነው።]
የአካባቢያችን ደን ተመናመነ።]
መ. ፍልሰት
መ. “መሠረት” የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ
[ተ. ስደት]
“ዋና፣ ቁልፍ አስፈላጊ ነገር/ጉዳይ” የሚል
ፍቺ አለው። በዚህ ፍቹ ዓረፍተነገር መሥርቼ መ. ዓረፍተነገር ሥሩበት።
ላሳያችሁ።
[ተ. ርሃብ ለህዝብ ፍልሰት መንስኤ ነው።]
[መ. የደኖች መኖር ለሰውና ለእንስሳት ህልውና (ተማሪዎች የተለያዩ ዓረፍተነገሮች
መሠረት ነው።] ሊመሠርቱ ይችላሉ።)
እንሥራ (መ. በዚህ ዓይነት ለሌሎቹም ቃላት ፍቺ
መ. አሁን ደግሞ ሁለት ቃላትን ከምንባቡ እንዲሠጡና ዓረፍተነገር እንዲሠሩ ያድርጉ።)
አውጥተን ዓረፍተነገር በጋራ እንሠራለን። (መ. ለቃላቱ ፍቺ መስጠትን የክፍልሥራ
በመጀመሪያ “ቁሳቁስ” የሚለው ቃል በምንባቡ ሊያደርጉት ይችላሉ። በቃላቱ ዓረፍተነገር
የያዘው ፍቺ ምንድነው? መመሥረትን ደግሞ የቤትሥራ ሊሆን
[መተ. ቁሳቁስ ልዩ ልዩ የመገልገያ እቃዎች ይችላል።)
ማለት ነው]
መ. አሁን “ቁሳቁስ” በሚለው ቃል ዓረፍተነገር
መጻፍ (25 ደቂቃ)
እንመሥርት ድርሰት መጻፍ (17 ደቂቃ)
[መተ. ወንበር፣ ጠረጴዛና አልጋ የቤት ውስጥ የጻፉትን ረቂቅ አስተከክሎ መጻፍ
መገልገያ ቁሳቁሶች ናቸው።]
ሥሩ
መ. ጥሩ! “ከርሰምድር” የሚለው ቃል በምንባቡ መ. ባለፈው ሳምንት “የግብርና ምርት የሚቀንሱ
ውስጥ የያዘው ፍቺ ምንድን ነው? ምክንያቶችን” በተመለከተ በምክንያትና
[መተ. “ከርሰምድር” ማለት የመሬት ውስጥ ውጤት የተዋቀረ አንቀጽ ጽፋችኋል። የዛሬው
ማለት ነው።] ተግባራችን የጻፋችሁትን አንቀጽ መከለስ
ይሆናል። አሁን ደብተራችሁን አውጡና
መ. አሁን “ከርሰምድር” በሚለው ቃል ዓረፍተነገር የጻፋችሁትን ተመልከቱ። ስህተት የሆኑ
እንመሥርት ነገሮችን ለይታችሁ አስተካክሉ። ጽሑፉን
[መተ. በከርሰምድር ውስጥ በርካታ ማዕድኖች በምታስተካክሉበት ጊዜ የሚከተሉትን
ይገኛሉ።] ጥያቄዎች ራሳችሁን ጠይቁ።

ሥሩ 1. የተሟሉ ዓረፍተነገሮች ተጠቅሜያለሁ?


መ. ከዚህ በመቀጠል በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው 2. ሥርዓተነጥቦችን በአግባቡ ተጠቅሜያለሁ?

፵፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 43


3. ጽሑፌ የምክንያትና ውጤት አወቃቀርን ይጠይቋቸው።
የተከተለ ነው?
[መተ. የተወሰኑ ተማሪዎች ሰሌዳ ላይ ይጽፋሉ።]
4. በጽሑፌ ውስጥ ያካተትኳቸው ሀሳቦች
መ. በጣም ጥሩ! (ስህተት ካለ ያስተካክሉ)
ከርዕሱ ጋር የተያያዙ ናቸው?
ሥሩ
(መምህር እነዚህን የግል መገምገሚያ ነጥቦች
መ. አሁን የማነብላችሁን ቃላት በደብተራችሁ
ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
ትጽፋላችሁ። (የሚከተሉትን ቃላት አንድ
መ. በመጀመሪያ ከላይ የተዘረዘሩትን ነጥቦች ባንድ እያነበቡላቸው ተማሪዎች እንዲጽፉ
ራሳችሁን እየጠየቃችሁ ጽሑፋችሁን ያድርጉ።)
ራሳችሁ አስተካክሉ። (ለዚህ ተግባር 5 ደቂቃ
ይስጧቸው) ሀ. ድርጅቶች

መ. አሁን ደብተራችሁን ተቀያየሩና ርስበርስ ለ. እንደሰማኋቸው


ተራረሙ፤ የማስተካከያ ሀሳብ ስጡ። (ለዚህ ሐ. እያነበብኳቸው
ተግባር 5 ደቂቃ ይስጧቸው።)
መ. መረጃዎች
መ. በተሠጣችሁ አስተያየት አስተካክላችሁ ጻፉ።
(5 ደቂቃ) ሠ. እያነሳኋቸው

(መ. ከየቡድኑ የተሻለውን ሥራ ለክፍሉ ረ. አርሶአደሮች


ተማሪዎች እንዲያቀርቡ ያድርጉ። ቀሪውን ስ. ስላስታወስኳቸው
2 ደቂቃ ለዚህ ተግባር ማዋል ይችላሉ።)
(መ.ጽፈው እንደጨረሱ ደብተራቸውን
(መ. መምህር በእያንዳንዱ ተግባር ጊዜ በየቡድኑ እንዲቀያየሩ ያድርጉ፤ ከዚያም በመልሶቹ
እየተዘዋወሩ ተማሪዎች ተግባሩን በአግባቡ ላይ እየተወያዩ እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
እየሠሩ መሆናቸውን ይከታተሉ፣ ድጋፍ
የሚሹ ተማሪዎችን ይደግፏቸው። ጎን ለጎንም
የሚቀርቡ የተሻሉ ሥራዎችን ይፈትሹ።) 9ኛ ቀን
የአጻጻፍ ሥርዓት (8 ደቂቃ) የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
እንሥራ • አቀላጥፎ ማንበብ
መ. ባለፉት ሳምንታት ቃላት ላይ የብዙ ቍጥር
• መናገር
አመልካች ቅጥያዎች “-ኦች” እና “-ዎች”
ሲጨመሩ እንዴት እንደሚጻፍ፣ እንደ • ሰዋስው
“ጠራሁ” እና “ነገርኩ”ያሉ ቃላት ላይ ደግሞ
“-ኣቸው” ሲጨመር ያለውን የአጻጻፍ ሁኔታ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ተመልከተናል።
ሥሩ
መ. ዛሬ ደግሞ ቃላቱን እኔ ሳነብላችሁ እናንተ
በደብተራችሁ ትጽፋላችሁ። ከዚያ በፊት ግን
(መ.ባለፈው ክፍለጊዜ በቃላት ላይ የሰጧቸው
የተወሰኑ ምሳሌዎች አብረን እንሥራ።
የቤትሥራ ተማሪዎች የመሠረቷቸውን
ዓረፍተነገሮች እንዲናገሩ ካደረጉ በኋላ
መ. አካባቢዎች (ድምፅዎን ከፍ አድርገው ግብረመልስ ይስጡ።)
ያንብቡላቸው) ይህን የጠራሁትን ቃል ማነው/
ናት ሰሌዳው ላይ የሚጽፍልኝ/የምትጽፍልኝ?
[መተ. አራት ተማሪዎች ይጽፋሉ] (ከዚያም
ስህተት ካለ ያስተካክሉ)
መ. “ስለተውኳቸው” የሚለውን ቃል (ድምፅዎን
ከፍ አድርገው ያንብቡላቸው) “ይሄን ቃልስ
ጽፋችሁ ልታሳዩኝ ትችላላችሁ?” በማለት

44 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፵፬


አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) መናገር (15 ደቂቃ)
በኢትዮጵያ የደን መመናመን እንሥራ
መንስኤዎችና የሚያስከትሏቸው መ. ተማሪዎች አሁን በሚሠጣችሁ ርዕሰጉዳይ
ላይ በቡድን ትወያያላችሁ። ከዚያ በፊት ግን
ችግሮች አንድ ሁለት ጥያቄዎችን አብረን እንሥራ።
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) መ. በሀገራችን የደን ሽፋንን ከሚቀንሱ
ሥሩ ምክንያቶች አንዱን እንናገር?
መ. "በኢትዮጵያ የደን መመናመን መንስኤዎችና [መተ. ዛፎችን ለማገዶ መቁረጥ] (ሌሎች
የሚያስከትሏቸው ችግሮች" በሚል ርዕስ ምላሾችንም ሊሰጡ ይችላሉ።)
የቀረበውን ምንባብ ከማንበባችሁ በፊት አንድ
ጥያቄ መልሱ። መ. የዛፎቹ ለማገዶ መቆረጥ የሚያስከትለው
ጉዳትስ ምንድን ነው?
መ. የደን መመናመን የሚያደርሳቸውን ጉዳቶች
አስታውሳችሁ ተናገሩ። [መተ. የመሬት በንፋስና በውኃ መሸርሸርና
የአፈር ለምነት መቀነስ] (ሌሎች ውጤቶችም
[ተ. የደን መመናመን የሚያደርሳቸውን ጉዳቶች ሊቀርቡ ይችላሉ።)
አስታውሰው ይናገራሉ።]
ሥሩ
ማንበብ (8 ደቂቃ) መ. ከላይ በሠራነው መልኩ በሀገራችን የደን ሽፋን
እንሥራ የቀነሰበትን ምክንያትና የደኖች መመናመን
መ. ተማሪዎች ባለፉት ክፍለጊዜያት አቀላጥፎ የሚያስከትለውን ጉዳት በተመለከተ በቡድን
ማንበብን ተለማምዳችኋል። ዛሬ ደግሞ ተወያዩ። ከተወያያችሁ በኋላ የቡድኑን ሀሳብ
“በኢትዮጵያ የደን መመናመን መንስኤዎቹና ለክፍሉ ታቀርባላችሁ።
ውጤቶቹ” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ
(እያንዳንዱ ቡድን ሲወያይ እየተዘዋወሩ
አንቀጽ 2 አብረን እናንብብ።
የተማሪዎቹን ንግግር በማዳመጥ፣ በንግግራቸው
(መምህር አንቀጹን ተማሪዎች ከርስዎ ጋር ምክንያትና ውጤትን የሚገልጹ/የሚያሳዩ
ድምፅ እያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ) አገላለጾችን መጠቀማቸውን፣ ሀሳባቸውን
ሥሩ በቅደም ተከተል አደራጅተው ማቅረባቸውን፣
የድምፃቸውን ተሰሚነት ወዘተ. ይገምግሙ።
መ. አሁን ደግሞ ሦስት ሦስት በመሆን ተራበተራ
ጥሩ የሚናገሩትን ያበረታቱ፣ ድጋፍ ለሚሹት
አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ ሌሎቻችሁ
ተገቢ ድጋፍ ያድርጉ።)
ደግሞ እያዳመጣችሁ ማስታወሻ ያዙ።
መ. አንዳችሁ ስታነቡ ሌሎቻችሁ በማስታወሻችሁ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ላይ ጓደኞቻችሁ ሲያነቡ የተሳሳቱትን ቃላት
መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮች
ብዛት መዝግቡ።
እንሥራ
(መ.እያንዳንዷ/ዱ ተማሪ ለ2 ደቂቃ ያህል
መ. ባለፈው ሳምንት ስለመጣኝና ደረጃ አመልካች
እንድታነብ/እንዲያነብ ያድርጉ። ተማሪዎች
ቍጥሮች ተምረናል። ዛሬ ስለነዚህ ቍጥሮች
ማንበብ ሲጀምሩ ሰዓት ይያዙ። 2 ደቂቃ
የምታስታውሱትን ትነግሩኛላችሁ።
ሲሞላ ያስቁሙ። ከዚያም ተማሪዎች በ2 ደቂቃ
ያነበቧቸውን ቃላት ብዛትና የተሳሷቷቸውን መ. መጣኝ ቍጥር ማለት ምን ማለት ነው?
ቃላት እንዲቆጥሩ ያድርጉ። ከዚያም ፈጣን
[መተ. የአንድን ነገር መጠን የሚያመለክቱ
ያልሆኑ አንባቢዎችን ይለዩ፤ ካለፉት
ቍጥሮች ናቸው።]
ክፍለጊዜያት ያሳዩትን መሻሻል ይገምግሙ
ተማሪዎችዎ በትክክል የሚያነቡበትን ዘዴ መ. ደረጃ አመልካች ቍጥርስ ምን ማለት ነው?
ይቀይሱ።) [መተ. አንድ ነገር ያለበትን ደረጃ የሚያመለክት
ቊጥር ነው።]

፵፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 45


ሥሩ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን
የቀረቡትን ተግባር “1”ና “2” መመሪያዎችን
በደንብ አንብባችሁ በቃላችሁ መልሱ፤
ተግባር “3”ን ደግሞ በቡድን እተወያያችሁ
በጽሑፍ መልሱ።
(መ.ተማሪዎች ተግባሩን የሚሠሩበት 8 ደቂቃ
ይስጧቸው። ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ
በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ በትክክል
መሥራታቸውን ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን
ተማሪዎች ይደግፉ፣ በመጨረሻ በመልሶቹ
ላይ ከተማሪዎችዎ ጋር ይወያዩ።)

46 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 2 ፵፮


ምዕራፍ 3 ልማዶች
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• “ልማዶች” በሚል ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይጽፋሉ፤
• በዋናና መዝርዝር ሀሳብ የአጻጻፍ ስልት አንድ አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• የቃላትን ቅደምተከተል እንደገና በማዋቀር ዓረፍተነገሮችን አስተካክለው ይጽፋሉ፤
• የቀረቡላቸውን ምንባቦች አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• “ልማድ” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• “ልማዶች” በሚል ይዘት ሥር በቀረቡ ምንባቦች መሠረት በሚጠየቁ ጥያቄዎች መነሻነት ይናገራሉ፤
• ኢሳቢ ግሶችን ለይተው በዓረፍተነገር ይገለገላሉ።

ሳይነጣጥሉ ያንብቡላቸው።)
1ኛ ሳምንት
እንሥራ
አካባቢያዊ ልማዶች መ. አሁን ደግሞ ሌሎች ቃላትን እየነጣጠልንና
እያጣመርን በጋራ እናንብብ።

1ኛ ቀን መ. “ጨመርኩበት” የሚለውን ቃል ነጥለን


እናንብበው። (ቃሉን በሰሌዳው ላይ ነጣጥለው
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ይጻፉላቸው።)
• የቃላት ጥናት
[መተ. ጨመርኩ-በት]
• ማንበብ
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምረን
እናንብበው። (አጣምረው ይጻፉላቸው።)

የቃላት ጥናት [መተ. ጨመርኩበት]


መነጠልና ማጣመርና (10 ደቂቃ) መ. ጥሩ ነው! ሌላ ምሳሌ እንጨምር።
“እየታጀብኩ” የሚለውን ቃል ነጣጥለን
ልሥራ እናንብብ (ቃሉን ነጥለው እየ-ት-አጀብኩ)
መ. “ቡና ጠጡ” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ በማለት በሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
ውስጥ ንባብ አደናቃፊ ናቸው የተባሉ
ውስብስብ ቃላት ቀርበዋል። ከነዚህ ቃላት [መተ. እየ-ት-አጀብኩ]
ጥቂቶቹን በመነጣጠልና በማጣመር መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ አጣምረን
አነባለሁ። እናብበው። (ቃሉን አጣምረው ይጻፉላቸው።)
መ. “ጎረቤቶቻችን” የሚለውን ቃል ነጣጥዬ ሳነበው [መተ. እየታጀብኩ]
“ጎረቤት-ኦች-ኣችን” ይሆናል። (ዋና ቃሉንና
ቅጥያዎቹን እየነጣጠሉ ያንብቡላቸው።) ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን
መ. አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምሬ ሳነበው የቀረቡትን ቃላት በመጀመሪያ እየነጣጠላችሁ፣
“ጎረቤቶቻችን” ይሆናል። (ሙሉውን ቃል ከዚያም እያጣመራችሁ አንብቡ።

፵፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 47


(በመጽሐፉ የተዘረዘሩትን ቃላት፣ እያንዳንዱን ሥሩ
ቃል በአንድ ካርድ ላይ ነጥለው፣ በሌላው መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን
ላይ ደግሞ ሙሉው ቃል ሳይነጣጠል ጽፈው የቀረቡትን የቅድመንባብ ጥያቄዎች በቃላችሁ
ያዘጋጁ። ከዚያም አንዱን ተነጣጥሎ የተጻፈ መልሱ።
ቃል የያዘውን ካርድ አውጥተው ለተማሪዎች
ሲያሳዩ ተማሪዎች ቃሉን ነጣጥለው በጋራ መ. በቡና ሥርዓት ምርቃት የሚከናወነው መቼ
ያነባሉ። ከዚያም ቃሉ ሳይነጣጠል የተጻፈበትን ነው?
ካርድ ያሳዩአቸው፤ተማሪዎች ሙሉውን ቃል [ተ. የመጀመሪያው ቡና ከመቀዳቱ በፊትና
ሳይነጣጥሉ በጋራ ያንብቡ። በመጨረሻም የመጨረሻው ቡና ተጠጥቶ ሲያበቃ]
ተማሪዎችን በተናጠል ካርዶቹን እያሳዩ
መ. ጥሩ! በታሪኩ ውስጥ ምርቃት የተከናወነው
በመጀመሪያ ነጣጥለው፣ ከዚያም አጣምረው
መቼ ነው? ምላሹን ምንባቡን አንብባችሁ
እንዲያነቡ ያድርጉ። ተግባሩን እንዴት
ስትጨርሱ ትነግሩኛላችሁ።
እንደሚያሠሩ አንድ ምሳሌ ቀጥሎ ቀርቧል።)
መ. በ“ሀ” የቀረበውን ቃል ተነጣጥሎ የተጻፈበትን የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
ካርድ ያሳዩ። (መ. ተማሪዎች በሚያነቡበት ጊዜ ድምፅ
[ተ. ከ-ተንተከተከ] ማሰማት፣ ከንፈር ማንቀሳቀስ፣ የሚያነቡትን
ጽሑፍ በጣታቸው መጠቆም ተገቢ
መ. ቃሉ ሳይነጣጠል (ተጣምሮ) የተጻፈበትን
አለመሆኑን ይንገሯቸው። ሲያነቡ ይህን
ካርድ ያሳዩ።
አለማድረጋቸውን ይከታተሉ። ምክንያቱም
[ተ. ከተንተከተከ] (ይህንኑ ተግባር ተማሪዎችን እነዚህ ልምዶች የማንበብ ፍጥነትንና
እየጠየቁ በግል ሊያሠሩ ይችላሉ።) የመረዳት ችሎታን ስለሚቀንሱ ነው።)
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
ማንበብ (30 ደቂቃ)
እንሥራ
ቡና ጠጡ መ. ምንባቡን አንብባችሁ ጨረሳችሁ? በጣም
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) ጥሩ! አሁን ምንባቡን መሠረት ያደረጉ
ጥያቄዎችን ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ ግን
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት የተወሰኑ ጥያቄዎችን አብረን እንመልሳለን።
እንሥራ መ. ተራኪዋ በሕፃንነቷ ምን ታደርግ ነበር?
መ. ዛሬ “ቡና ጠጡ” በሚል ርዕስ የቀረበ ምንባብ
ታነባላችሁ። ከዚያ በፊት ግን የቅድመንባብ [መተ. ጎረቤቶቿ ቡና እንዲጠጡ ትጠራ ነበር።]
ጥያቄዎችን እንሠራለን። መ. ይህን መልስ ያገኘነው እንዴት ነው?
መ. በቤተሰባችሁ ውስጥ ቡና የሚያፈላው ማን [መተ. በመጀመሪያው አንቀጽ ተራኪው
ነው/ናት? በሕፃንነቷ እናቷ ቡና አፍልተው
ጎረቤቶቻቸውን እንድትጠራ ይልኳት
[መተ. እናት፣ ወንድም፣ እህት…] (ተማሪዎች
እንደነበረ ተገልጿል።]
የተለያየ መልስ ሊሰጡ ይችላሉ።)
መ. በዚህ ታሪክ ውስጥ ቡና በማን እንደተፈላ መ. ጥሩ! “… ሥነሥርዓቱ ውበቱ ነው” ማለት ምን
ከሥዕሉና ከምንባቡ ተነስታችሁ ንገሩኝ። ማለት ነው? የዚህን ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት
“…ሥነሥርዓቱ ውበቱ ነው…” የሚለውን
[መተ. እናትየዋ ናት።] ሐረግ እንፈልግ። ይህ ሐረግ በስንተኛው
መ. መልሳችን ትክክል መሆን ወይም አለመሆኑን አንቀጽ ይገኛል?
ለማረጋገጥ ሁለተኛውን አንቀጽ እናንብብ። [መተ. በሦስተኛው አንቀጽ]
(4ኛውን አንቀጽ ከተማሪዎች ጋር አብረው
ያንብቡና ያረጋግጡ።) መ. ስለዚህ፣ “ሥነሥርዓቱ ውበቱ ነው” ማለት ምን
ማለት ነው?

48 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፵፰


[መተ. የቡና ውበቱ ረጋ ብሎ መፈላቱ፣ ቡናው
ተፈልቶ እስኪጠጣ ያለው ሥርዓት ውበት 2ኛ ቀን
አለው ማለት ነው። ይህም ሲባል የቡና
አቆላል፣ እጣኑ፣ ፈንድሻው፣ መመራረቁ
ወዘተ. ልዩ ውበት አለው ማለት ነው።] የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. ይህን መልስ እንዴት ልናገኝ ቻልን? • ቃላት
• መጻፍ
[መተ. የዚህ ጥያቄ ምላሽ በቀጥታ በምንባቡ
ውስጥ አልተገለፀም። ነገርግን ስለቡና አፈላል
ሥርዓት ከዚህ በፊት ከምናውቀው በመነሳት
ጥያቄውን መመለስ እንችላለን።]
ቃላት (10 ደቂቃ)
ሥሩ
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን የሚገኙትን ለቃላትና ለሐረጋት ተመሳሳይና ተቃራኒ
የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች በቡድን ፍቺ መስጠት
እየተወያያችሁ ሥሩ። አንድ/ዲት ተማሪ እንሥራ
ጥያቄውን ያንብብላችሁ/ታነብብላችሁ፤ መ. ዛሬ “ቡና ጠጡ” ከሚለው ምንባብ ውስጥ
ከዚያም መልሱ የሚገኝበትን አንቀጽና ለወጡ ቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይና ተቃራኒ
ዓረፍተነገር በጋራ ፈልጉ። ቀጥሎ ፍቺ እንሠጣለን። በመጀመሪያ ለቃላቱና
የጥያቄው መልስ ምን ሊሆን እንደሚችል ለሐረጋቱ ተመሳሳይ ፍቻቸውን ከምንባቡ
ከአንቀጹ፣ ከዓረፍተነገሩ በመነሳት ተወያዩ። እንፈልጋለን።
የተስማማችሁበትን መልስ በማስታወሻችሁ
ጻፉ። መ. “የሚያረካ” ለሚለው ሐረግ ተመሳሳይ ፍቹን
ከምንባቡ ፈልገን እናውጣ። ለዚህ ሐረግ
(መ. ተማሪዎች ለ8 ደቂቃ ያህል ከተወያዩ በኋላ ተመሳሳይ ፍቺ የምናገኘው በአንቀጽ 2 ነው።
በሚከተለው መልኩ የተማሪዎችን መልስ ስለዚህ ቃሉ የትኛው ይመስላችኋል?
ይቀበሉ።)
[መተ. የሚቆርጥ]
መ. በታሪኩ ውስጥ ቡና ያፈላው ማን ነው/ናት?
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ “አጫጭር ታሪኮች”
[ተ. ተራኪዋ] ለሚለው ሐረግ ተመሳሳይ ፍቺ የምናገኘው
መ. ይህን መልስ እንዴት አገኛችሁት? በ6ኛው አንቀጽ ውስጥ ነው። ስለዚህ ቃሉ
የትኛው ይመስላችኋል?
[ተ. ምክንያቱም በሦስተኛው አንቀጽ ውስጥ
ተራኪዋ “ዛሬ ቡና የማፍላት ተራው የኔ [መተ. ወግ]
ነው።” ስትል ተናግራለች።] (ሌሎቹንም መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ከተግባር “2” አንድ
ጥያቄዎች በዚሁ መሠረት ያሠሯቸው።) ምሳሌ እንሥራ። “ታዳሚ” ለሚለው ቃል
ተቃራኒ ፍቺ እንፈልግ። በመጀመሪያ ግን
“ታዳሚ” የሚለው ቃል ተመሳሳዩ ምንድን
ነው?
[መተ. ተጋባዥ]
መ. ስለዚህ በዚህ መሠረት ተቃራኒ ፍቹ ምን
ይመስላችኋል?
[መተ. ጋባዥ]
ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን
የቀረቡትን ቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይ

፵፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 49


ፍቻቸውን ከምንባቡ ውስጥ ፈልጉ። አፈላልና አጠጣጥ ሥነሥርዓት መሆኑን
መረዳት ይቻላል።
መ. “የመጀመሪያ ቡና” ለሚለው ሐረግ ተመሳሳይ
ፍቺ በ6ኛው አንቀጽ ውስጥ ታገኛላችሁ። መ. አሁን የዋና ሀሳብና መዘርዝር ሀሳቦች
አንቀጹን አገኛችሁት? የቢጋር ሠንጠረዥ እንዴት እንደሚዘጋጅ
አሳያችኋለሁ። በመጀመሪያ ከምንባቡ
[ተ. አዎ]
ውስጥ አንድ አንቀጽ አነብላችኋለሁ። (“ቡና
መ. በጣም ጥሩ! ለሐረጉ ተመሳሳይ ፍቺ የሚሆነው ጡጡ” ከሚለው ምንባብ 5ኛውን አንቀጽ
ቃል የትኛው ነው? ያነብቡላቸው። ተማሪዎችም ድምጻቸውን
[ተ. አቦል] ሳያሰሙ እያነበቡ ይከታተሉ።)

(መ. በዚህ ዓይነት በቡድን ሆነው እየተወያዩ መ. ባነበብኩት አንቀጽ ውስጥ ዋናውን ሀሳብ
ለቃላቱና ለሐረጋቱ ተመሳሳያቸውን ከምንባቡ ምንድን ነው?
እንዲያወጡ ያድርጉ። ከዚያም ከየቡድኑ [መ. የአንቀጹ ዋና ሀሳብ የቡና አፈላል የተለያዩ
ተማሪዎች መልስ እንዲሰጡ ያድርጉ። ሂደቶችን ያልፋል የሚል ነው።]
በመቀጠል ከቀረበው ጽብረቃ በመነሳት
መ. ይህን ዋና ሀሳብ የሚያብራሩ ዝርዝር ሀሳቦች
ግበረመልስ ይስጡ። በመጨረሻም ተግባር
በአንቀጹ ውስጥ ይገኛሉ። ዋና ሀሳቡንና፣
“2”ን የቤትሥራ ይስጧቸው)
መዘርዝር ሀሳቦቹን በቢጋር ሠንጠረዥ
መጻፍ (30 ደቂቃ) ላሳያችሁ። (በመማሪያ መጽሐፉ ላይ
የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ይሳሉላቸው። የቢጋር ሠንጠረዡን በሰሌዳው
የዋናና መዘርዝር ሀሳቦችን በቢጋር ላይ ሲሥሉ ራስጌ ላይ ያለውን ዋናው ሀሳብ
ሠንጠረዥ ማስፈር ብቻ ይጻፉላቸው። ከታች ያሉትን ሳጥኖች
ግን ባዶ አድርገው ይሣሉላቸው። ከዚያም
ልሥራ
በሂደት ዝርዝር ሀሳቦቹን ይሞላሉ።)
መ. ዛሬ የምናተኩረው “ዋና ሀሳብና መዘርዝር
ሀሳቦች” በመባል በሚታወቀው የአጻጻፍ ስልት መ. ዋናውን ሀሳብ ከሚደግፉ ዝርዝር ሀሳቦች
ላይ ነው። ዋና ሀሳብ የሚባለው ጽሑፉ ውስጥ የመጀመሪያው የትኛው ነው? (ተማሪዎች
ሊገለጽ የተፈለገው ዐቢይ ጉዳይ ነው። 5ኛውን አንቀጽ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ዋናውን ሀሳብ የሚያብራሩት ዝርዝር ሀሳቦች [መ. “የተያያዘ ከሰል አቀረብኩ” የሚለው
ደግሞ መዘርዝር ሀሳቦች ይባላሉ። ከምናነበው መጀመሪያ ላይ የምናገኘው መዘርዝር ሀሳብ
ምንባብ ውስጥ ዋናውን ሀሳብ ለመለየት ነው።]
የሚረዱ የሚከተሉት ስልቶች ናቸው።
እንሥራ
• ርዕሱን መመልከት፣
መ. አሁን በአንቀጹ ውስጥ የተዘረዘሩትን ሀሳቦች
• ምሥሉን (ሥዕሉን) መመልከት፣ እየለየን በቢጋር ሠንጠረዡ ውስጥ አብረን
እናሰፍራለን። በአንቀጹ ውስጥ የተጠቀሰው
• ዝርዝር ሀሳቦችን ማንበብ ናቸው።
ቀጣዩ መዘርዝር ሀሳብ የትኛው ነው?
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ያነበብነውን ምንባብ
[መተ. “ብረት ምጣዱን ጥጄ ቡናውን ቆላሁ።”]
እንደምሳሌ እንውሰድ።
መ. የምንባቡ ርዕስ ምን ይላል?
ሥሩ
መ. አብረን በሠራነው መሠረት በ1ኛው ሳምንት፣
[መ. “ቡና ጠጡ”] በ2ኛው ቀን “በመጻፍ” ንዑስ ክፍል ሥር
መ. ሥዕሉ ላይ ምን ይታያል? የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ “ቡና ጠጡ”
ከሚለው ምንባብ 5ኛ አንቀጽ ውስጥ
[መ. ብዙ ሰዎች ከፊት ለፊቷ ተቀምጠው ቡና መዘርዝር ሀሳቦችን እየመረጣችሁ ሙሉ።
የምትቀዳ ሴት ትታያለች።]
መ. አብረን ከጠቀስናቸው ሌላ መዘርዝር ሀሳብ
መ. ከዚህ በመነሳት የምንባቡ ዋና ሀሳብ የቡና ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?

50 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፶


[ተ. ታጥቦ የቀረበውን ጀበና ጣድኩት።] [መ.ምክንያቱም “ሽማግሌው” የሚለው ስም
የዓረፍተነገሩ ባለቤት ስለሆነ በዓረፍተነገሩ
መ. ትክክል!
መጀመሪያ መምጣት አለበት። “ወጡ”
(መ.ተማሪዎች በአነስተኛ ቡድን ሆነው አንቀጹን የሚለው ግስ ደግሞ የዓረፍተነገሩ ማሰሪያ
እያነበቡ የቢጋር ሠንጠረዡን እንዲሞሉ ስለሆነ፣ በዓረፍተነገሩ መጨረሻ ላይ መምጣት
ማድረግ ይችላሉ። ከዚያም ከየቡድኑ አለበት።”ተራራውን” የሚለው ድርጊቱ
የተወሰኑ ተማሪዎች እየተነሱ በሰሌዳው ያረፈበት ቃል ስለሆነ ከማሰሪያው ግስ ቀድሞ
ላይ ባዘጋጁት የቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ መምጣት አለበት ስለዚህ የተስተካከለው
እንዲያሰፍሩ ያድርጉ።) ዓረፍተነገር “ሽማግሌው በምርኩዝ እየተደገፉ
መ. የዋና ሀሳብና መዘርዝር ሀሳቦች የአጻጻፍ ተራራውን ወጡ።”]
ስልት በመጠቀም “የምግብ ዓይነቶች” በሚል እንሥራ
ርዕስ አንድ አንቀጽ ለመጻፍ መነሻ የሚሆን መ. “ተኛ በስፖንጅ ፍራሽ ላይ አለባቸው።”
የቢጋር ሠንጠረዥ በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ያለቦታቸው
ቀን እቤታችሁ አዘጋጅታችሁ ትመጣላችሁ። የገቡት ቃላት የትኞቹ ናቸው?
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) [መተ. “ተኛ”ና “አለባቸው”]
የቃላትን ቅደምተከተል እንደገና መ. በጣም ጥሩ! ያለቦታቸው ገብተዋል ያልንበት
በማዋቀር ዓረፍተነገር አስተካክሎ መጻፍ ምክንያት ምንድን ነው?
ልሥራ [መተ. “አለባቸው” ስምና የዓረፍተነገሩ ባለቤት
መ. ስለማንኛውም ጉዳይ አንድ ጽሑፍ ስለሆነ ቦታው በዓረፍተነገሩመጀመሪያ ነው።
በምንጽፍበት ጊዜ ትኵረት ልንሰጣቸው “ተኛ” ደግሞ ግስ ስለሆነ ቦታው በዓረፍተነገሩ
ከሚገቡ ነገሮች መካከል አንዱ በዓረፍተነገር መጨረሻ ነው።]
ውስጥ የቃላትን ቅደምተከተል መጠበቅ ነው።
መ. ጥሩ ነው! ስለዚህ ተስተካክሎ ሲጻፍ እንዴት
ቃላት በዓረፍተነገር ውስጥ የራሳቸው ቦታ
ይሆናል?
አላቸው። ስለዚህ ይህን ቦታቸውን ጠብቆ
መጻፍ ተገቢ ነው። [መተ. አለባቸው በስፖንጅ ፍራሽ ላይ ተኛ።]
መ. በዓረፍተነገር ውስጥ የቃላትን ቅደምተከተል ሥሩ
ጠብቄ የመጻፍ ችሎታዬን ለማዳበር መ. እስከአሁን በሠራነው መሠረት በ1ኛው
የቀረበው ተግባር እንዴት እንደሚሠራ ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን በ“አጻጻፍ ሥርዓት”
አሳያችኋለሁ። የቃላት ቅደምተከተላቸው ንዑስ ክፍል ሥር የቃላት ቅደምተከተላቸው
የተዛቡ ዓረፍተነገሮች ቀርበዋል፤ ከነዚህ ተዛብቶ የቀረቡትን ዓረፍተነገሮች
ዓረፍተነገሮች መካከል የተወሰኑትን እኔ አስተካክሉ።
አስተካክላለሁ።
(መ.ተግባሩ ውስብስብ እንዳይሆንባቸው
መ. ወጡ ተራራውን በምርኩዝ እየተደገፉ ተማሪዎች ምክንያት እንዲሰጡ አያድርጉ።
ሽማግሌው።(ይህን ዓረፍተነገር በሰሌዳው ላይ ተግባሩን ተማሪዎች በግል እንዲሠሩ
ይጻፉላቸው።) ያድርጉ። ከዚያም ደብተራቸውን ተቀያይረው
እንዲያርሙ ያድርጉ። ተግባሩን በሚከተለው
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ያለቦታቸው
መልክ ሊያሠሩ ይችላሉ።)
የገቡት ቃላት የትኞቹ ናቸው? (ተማሪዎች
እንዲመልሱ ያድርጉ።) መ. “አለቀሰች በጣም ስለራባት አምርራ ሕፃኗ ”
የሚለውን ዓረፍተነገር አስተካክላችሁ ጻፉ።
[መ.ትክክል! “ወጡ”፣ “ሽማግሌ”ና “ተራራውን”
የሚሉት ቃላት በትክክለኛ ቦታቸው [ተ. ሕፃኗ በጣም ስለራባት አምርራ አለቀሰች።]
አልገቡም።] (መ.በመማሪያ መጽሐፍ ከ“ሀ-ረ” የቀረቡትን
መ. ያለቦታቸው አልገቡም ያልሁበት ምክንያት በዚሁ መሠረት ያሠሩ።)
ምንድን ነው?

፶፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 51


ምንባብ የመጀመሪያዎቹን ሦስት አንቀጾች
3ኛ ቀን አነብላችኋለሁ። (ከላይ የተዘረዘሩትን
አራቱን ብልሀቶች ተግባራዊ በማድረግ
ያንብቡላቸው። በተለይ በሐረግ ደረጃ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ማንበብን በሚገባ ያሳዩኣቸው። ለምሳሌ ያህል
• አቀላጥፎ ማንበብ የምንባቡ የመጀመሪያ አንቀጽ የመጀመሪያ
• መናገር ዓረፍተነገር ቀጥሎ በተከፋፈለው መልኩ
ቢነበብ የተሻለ ነው።)
• ሰዋስው
ሕፃን እያለሁ /እናቴ ቡና አፍልታ ጎረቤቶቻችንን
/ቡና ጠጡ በይ/ ትለኝ ነበር። (እዝባር የተለዩትን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ባንድ ትንፋሽ በማንበብ ያሳዩ።)
(መ.ተማሪዎች ደብተራቸውን ተለዋውጠው እንሥራ
ይተራረሙ። በመቀጠልም ከእያንዳንዳቸው መ. አሁን ደግሞ እኔ ያነበብኳቸውን አንቀጾች
መልስ እየተቀበሉ ማስተካከያ ይስጡ። 1. አብረን እናንብብ። (ተማሪዎች ከርስዎ
ሠ፣ 2. ረ፣ 3. መ. 4፣ ሀ፣ 5. ለ 6. ሐ) ጋር አብረው ድምፅ እያሰሙ እንዲያነቡ
ያድርጉ።)
አቀላጥፎ ማንበብ (10)
ሥሩ
ቡና ጠጡ መ. ተማሪዎች አሁን እኔ በምመድባችሁ መሠረት
ሁለት ሁለት ሆናችሁ ትቀመጣላችሁ።
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
(ባለፉት ክፍለጊዜያት ባደረጉት ክትትል
መሠረት አቀላጥፈው የሚያነቡትን
ማስታወሻ አቀላጥፈው ከማያነቡ ተማሪዎች ጋር ያቀናጁ።
ምንባቡን በምታነቡበት ጊዜ፡- ከዚያም የተማሪዎችን ስም በመጥራት
• በተቻለ መጠን ፊደላትን አትግደፉ፤
አብረው እንዲቀመጡ ያድርጉ። በጥንድ
ሲያስቀምጧቸው አቀላጥፈው የሚያነቡትን
• ቃላትን አትደጋግሙ፤ “1”፣ አቀላጥፈው የማያነቡትን ደግሞ “2”
• ፊደላትን ሳትነጥሉ ሙሉውን ቃል ቍጥር መሆናቸውን ይንገሯቸው።አቀላጥፈው
አንብቡ፤ የሚያነቡ ወይም አቀላጥፈው የማያነቡ
የሚለውን ቃል ተማሪዎች ፊት
• ቃል በቃል ሳይሆን ሐረግ በሐረግ
አንብቡ፤
አይጠቀሙ።”1”ና “2” ብቻ እያሉ በቍጥር
ይንገሯቸው። ከዚያም በመጀመሪያ “1”
ቍጥሮች አንድ ጊዜ እንዲያነቡ ያድርጉ፤
(መ.ተማሪዎች እነዚህን ነጥቦች ተከትለው እነሱ ሲያነቡ “2” ቍጥሮች አነባበባቸውን
እንዲያነቡ ይንገሯቸው።) ይከታተሉ። በመቀጠልም “2” ቍጥሮች
እንዲያነቡ ይንገሯቸው። “1” ቍጥሮች ደግሞ
መ. ዛሬ “ቡና ጠጡ” በሚል ርዕስ በቀረበው ቀጥሎ በቀረበው ሠንጠረዥ ውስጥ ስህተት
ምንባብ ድምፅ እያሰሙ የማንበብ ልምምድ በተሠራ ቍጥር ምልክት (/) እያደረጉ
እናደርጋለን። ወደልምምዱ ከመግባታችሁ ይከታተሉ። በመጨረሻም የተመዘገቡትን
በፊት በምታነቡበት ጊዜ ትኵረት ስህተቶች በመደመር፣ በመጀመሪያውና
ልትሰጧቸው የሚገቡ ጉዳዮች በማስታወሻው በሁለተኛው ንባብ ጊዜ የታዩትን የስህተቶች
ቀርበውላችኋል። (በማስታወሻው ውስጥ ብዛት ልዩነት ይገምግሙ።)
ያሉትን ሀሳቦች ግልጽ ያድርጉላቸው።)

ማንበብ (8 ደቂቃ)
ልሥራ
መ. አሁን “ቡና ጠጡ” በሚል ርዕስ ከቀረበው

52 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፶፪


የመገምገሚያ በመጀመሪያ በሁለተኛ ይመስላችኋል? (ተማሪዎች በተለያየ መንገድ
መስፈርት ንባብ ንባብ ሊገምቱ ይችላሉ።)

1 በስህተት [ተ. ስለልዩ ልዩ ጠቃሚና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች


የተነበቡ የሚገልጽ ሊሆን ይችላል።]
ቃላት ብዛት መ. በጣም ጥሩ!
2 በንባብ ጊዜ
የተደገሙ
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)
ቃላት ብዛት መ. አሁን “ልማድ” በሚል ርዕስ የቀረበውን
3 ተነጥለው ምንባብ አነብላችኋለሁ። እናንተ ደግሞ
የተነበቡ በሙሉ ትኵረት አዳምጡ።
ቃላት ብዛት (መ.የመጀመሪያዎቹን ሁለት አንቀጾች ካነበቡ
4 በሐረግ በኋላ የሚከተለውን ጥያቄ ይጠይቋቸው።
መነበብ
ሲገባቸው፣ ***ልማድ በስንት ይከፈላል? ምን ምን
ቃል በቃል ተብሎ?***
የተነበቡ መልሱን ከተማሪዎች ከተቀበሉ በኋላ
ቃላት ብዛት ትክክል መሆንና አለመሆናቸውን አዳምጠው
እንዲያረጋግጡ አስታውሰው ንባብዎን
ማዳመጥ (15 ደቂቃ) ይቀጥሉ።)
ልማድ ልማድ
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ) ልማድ ከአንድ ትውልድ ወደሚቀጥለው ትውልድ
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ ሲወርዱ ሲዋረዱ የሚመጡ ማኅበረሰባዊ ሕጎች
ስብስብ ነው። በዚህ አባባል መሠረት ልማድ
እንሥራ የአንድን ማኅበረሰብ ዕውቀት አመለካከትና
መ. ዛሬ “ልማድ” በሚል ርዕስ የቀረበ ምንባብ አሠራር ያካትታል። ለምሳሌ አመጋገብን፣
ከማዳመጣችሁ በፊት ጥቂት የቅድመማዳመጥ አኗኗርን፣ ሥነቃልንና ሥነምግባርን መጥቀስ
ጥያቄዎችን አብረን እንመልሳለን። ይቻላል። በዚህም የተነሳ ልማድ ትውልድን
ከትውልድ የሚያገናኝ ድልድይ ነው ማለት
መ. “ልማድ” ማለት ምን ማለት ነው? ይቻላል።
[መተ. አንድ ማኅበረሰብ ለረጅም ዘመናት ልማድ ጠቃሚና ጎጂ ተብሎ በሁለት ሊከፈል
ሲተገብራቸው የኖሩ ልዩ ልዩ ጠቃሚ ወይም ይችላል። የአንድን ማኅበረሰብ አኗኗር፣ አሠራርና
ጎጂ ድርጊቶች፣ አመለካከቶች፣ የሥነምግባር ሥነምግባር የተሻለ እንዲሆን የሚያደርገው
ደንቦች ወዘተ. ናቸው። ይህንን መልስ ጠቃሚ ልማድ ይባላል። ጎጂ ልማድ የሚባለው
ያገኘነው ከቀደመ ዕውቀታችን በመነሳት ደግሞ የአንድን ማኅበረሰብ አኗኗር፣ አሠራርና
ነው።] (ተማሪዎች የተለያየ መልስ ሊሰጡ ሥነ-ምግባር እንዳይሻሻል አንቆ የሚይዝ ነው።
ይችላሉ።) *** ልማድ በስንት ይከፈላል? ምን ምን
ተብሎ?***
መ. አንድ ነገር ልማድ መሆኑን እንዴት ማወቅ
ይቻላል? ጠቃሚ ልማድ በተገቢው መንገድ ከተጠቀምንበት
የማኅበረሰብን አኗኗርና አስተሳሰብ ያስተካክላል።
[መተ. ማኅበረሰብ ድርጊቱን በተደጋጋሚ
እንዲሁም የሥነምግባር ደንቦችን በማስረጽ
ሲፈጽመው መታየቱና ትክክል ነው ብሎ
ማህበራዊ መረጋጋትንና ሰላምን ያሰፍናል።
ማሰቡ ነው።] ጊዜንና ጉልበትን ቆጥቦ የመማሪያና የመዝናኛ
መ. እጅግ በጣም ጥሩ! ጊዜ ያስገኛል። ይህም ራስን ከማኅበረሰቡ ጋር
አስማምቶ ጥሩ ኑሮ ለመኖር ያግዛል።
ሥሩ
የልማድ አስፈላጊነት ከኢትዮጵያ ተጨባጭ
መ. ከርዕሱ በመነሳት ምንባቡ ስለምን የሚገልፅ

፶፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 53


ሁኔታ አንፃር ሲታይ ደግሞ ጠቀሜታው የጎላ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ነው። ኢትዮጵያ የበርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና
ህዝቦች ሀገር ናት። እነዚህ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ኢሳቢ ግሶች
ህዝቦች ደግሞ የየራሳቸው ልማዶች አሏቸው።
ህዝቦች ልማዶቻቸውን ርስበርስ በመለዋወጥ ማስታወሻ
ሀገራዊ ዕውቀታቸውን ያዳብራሉ። የሀገራዊ
ዕውቀት መዳበር አብሮነትን ይፈጥራል። ኢሳቢ ግስ የሚባለው ድርጊቱ በራሱ በባለቤቱ
አብሮነቱም መቀራረብን፣ መተሳሰብንና ላይ ያለቀ መሆኑን የሚያሳይ ወይም ድርጊቱ
መደጋገፍን በመፍጠር አብሮ የመኖር ስሜትን ወደሌላ አካል (ተሳቢ) የማይሻገር የግስ ዓይነት
ያዳብራል። በተጨማሪም የጋራ ሥነምግባራዊ ነው። ለምሳሌ፡- መጣ፣ ሄደ፣ ቆመ፣ ተቀመጠ…
እሴቶችን በመገንባት ብሔራዊ አንድነትን የመሳሰሉት ቃላት ኢሳቢ ግሶች ናቸው።
ለማጠናከር ያስችላል።
በአጠቃላይ ልማድ ከዘመናዊ አስተሳሰብና
አሠራር ጋር እየተስማማ እስከሄደ ድረስ ልሥራ
ጠቀሜታው የጎላ ነው። ማኅበረሰቡም ወደተሻለ
መ. ባለፈው ሳምንት ስለመጣኝና ስለደረጃ
የእድገት አቅጣጫ እንዲያመራ አጋዥ ነው።
አመልካች ቍጥሮች ተምረን ነበር። ዛሬ
(ደ/ብ/መ/ት/ሙ/ማ/ኮ፣ 2002፣ ከገጽ 198-199፣ ደግሞ ኢሳቢ ግሶችን እንመለከታለን።
መጠነኛ ለውጥ ተደርጎበት የተወሰደ።) ተማሪዎች ቀጥሎ የቀረቡትን ሁለት
አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ) ዓረፍተነገሮች እንመልከት።
እንሥራ ሀ. ሁሴን በግ አረደ።
መ. ያነበብኩላችሁን ምንባብ አዳምጣችኋል። ለ. ውሻው ሞተ።
አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን
የሚገኙትን የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎች መ. በሁለቱ ዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉት ግሶች
ትመልሳላችሁ። ከዚያ በፊት ግን ጥቂት “አረደ”ና “ሞተ” ናቸው።
ጥያቄዎችን አብረን እንመልሳለን። መ. በመጀመሪያው ዓረፍተነገር ውስጥ የማረድ
መ. ልማድ ምንድን ነው ? ተግባር የፈፀመው “ሁሴን” ሲሆን የመታረድ
ድርጊት የተፈፀመው ደግሞ በ“በግ” ላይ ነው።.
[መተ. ልማድ ከአንድ ትውልድ ወደሚቀጥለው በሁለተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ የመሞት
ትውልድ ሲወርዱ ሲዋረዱ የሚመጡ አደጋ የደረሰበት የዓረፍተነገሩ ባለቤት የሆነው
ማኅበረሰባዊ ሕጎች ስብስብ ነው።] “ውሻ” ነው። ስለዚህ ኢሳቢ ግስ የሚባሉት
መ. የዚህን ጥያቄ ምላሽ እንዴት አገኘን? በሁለተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ እንደሚታየው
እንደ“ሞተ” ያሉት ግሶች ናቸው።
[መተ. በመጀመሪያው አንቀጽ ውስጥ የልማድ
ምንነት በቀጥታ ተጠቅሷል።] እንሥራ
መ. ኢሳቢ ግስ የሚባለው ድርጊቱ በራሱ በባለቤቱ
ሥሩ
ላይ የሚያልቅ መሆኑን የሚያሳይ የግስ
መ. ልማድ ምን ምን ነገሮችን ያካትታል?
ዓይነት ነው። አሁን ለኢሳቢ የግስ ዓይነት
[ተ. የአንድን ማኅበረሰብ ዕውቀት፣ አመለካከትና ምሳሌ እንስጥ።
አሠራር]
[መተ. ሄደ፣ መጣ፣ ቆመ…]
መ. ትክክል ነው! ይህን መልስ እንዴት አገኛችሁ?
መ. ከነዚህ ከጠቀስናቸው ግሶች “ሄደ” የሚለውን
[ተ. በሁለተኛው አንቀጽ፣ በሁለተኛው ዓረፍተነገር ወስደን በተለያየ ቅርፅ እናርባው።
ውስጥ ተገልጿል።]
መ. እኔ---------------------
መ. በዚህ መሠረት በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው
[መተ. እኔ ሄድኩ…]
ቀን በማዳመጥ ሥር የሚገኙትን የአዳምጦ
መረዳት ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ። መ. እኛ---------------
[መተ. እኛ ሄድን።]

54 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፶፬


ሥሩ
መ. አሁን ዓረፍተነገሮቹን ማሟላት የናንተ ተራ
ነው።
መ. አንቺ-------------
[መተ. አንቺ ሄድሽ።]
መ. አንተ--------------------------።
[ተ.አንተ ሄድክ።]
መ. እናንተ---------።
[ተ.እናንተ ሄዳችሁ።]
መ. እሱ--------------።
[ተ. እሱ ሄደ።]
መ. እሷ---------።
[ተ. እሷ ሄደች።]
መ. እነሱ---------።
[ተ.እነሱ ሄዱ።]
(መ.በ1ኛው ሳምንት፣ በሦስተኛው ቀን፣ ሰዋስው
በሚለው ንዑስ ርዕስ ሥር የቀረበውን ተግባር
“2”ን የቤት ሥራ ይስጧቸው።)

፶፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 55


መ. አሁን ትክክል መሆኔን ወይም መሳሳቴን
2ኛ ሳምንት ለማረጋገጥ ከመጀመሪያው አንቀጽ
ጠቃሚ ልማዳዊ ድርጊቶች 2ኛውና 3ኛውን ዓረፍተነገር ላንብብ።
(ያንብቡላቸው።) በዚህ አንቀጽ ውስጥ
“አመሠራረቱም በሁለት መንገድ ሊሆን
4ኛ ቀን ይችላል። አንደኛው በሠፈር ሲሆን ሁለተኛው
በሥራ ቦታ ነው” የሚል ሀሳብ ስለሚገኝ
የዕለቱ ትምህርት ይዘት ትክክል ነኝ።
• ማንበብ
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አንድ ጥያቄ አብረን እንሥራ።
ሁለተኛውን ጥያቄ እናንብብ። (ተማሪዎች
የቤትሥራ (10 ደቂቃ)
ጥያቄውን እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ሥሩ
[መተ. “ዕድር በሐዘንም ሆነ በደስታ ጊዜ
(መ. ተማሪዎች ደብተራቸውን ተለዋውጠው
ለመደጋገፍ ይጠቅማል።”]
እንዲያርሙ ያድርጉ።)
መ. ዓረፍተነገሩ “እውነት” ነው ወይስ “ሐሰት”
መ. እኔ -----------------------
[መተ. እውነት/ሐሰት]
[ተ. እኔ ተኛሁ።]
መ. አሁን የሰጠነው መልስ ትክክል ወይም ስህተት
መ. በጣም ጥሩ! እኛ-----------------------------።
መሆኑን ከ4ኛው አንቀጽ የመጀመሪያውን
[ተ. እኛ ተኛን።] ዓረፍተነገር በማንበብ እናረጋግጥ።
መ. በጣም (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም
ጥሩ! [መተ. “የዕድር ዓላማ በችግርና በደስታ ጊዜ
እንዲሠሩ ያድርጉ።) ተባብሮና ተረዳድቶ ችግርን ለመፍታት ነው”
ይላል። ስለዚህ “እውነት” ብለን የመለስን
ማንበብ (30 ደቂቃ) ትክክል ነን።]

ዕድር ሥሩ
መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) በቅድመንባብ ሥር ከቀረቡት የቀሩትን
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ (“ሐ”ና “መ”) ዓረፍተነገሮች ትክክል ከሆኑ
“እውነት” ስህተት ከሆኑ “ሐሰት” በማለት
ልሥራ በደብተራችሁ ጻፉ። ምንባቡን አንብባችሁ
መ. በመጽሐፋችሁ የቀረበላችሁን የቅድመንባብ ስትጨርሱ የሰጣችሁት ምላሽ ትክክል ወይም
ተግባር ከዚህ በፊት የምታውቁትን መነሻ ስህተት መሆኑን አረጋግጡ።
በማድረግ ትሠራላችሁ። ምንባቡን አንብባችሁ
ከጨረሳችሁ በኋላ ለቅድመንባብ ለጥያቄዎቹ የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
የሠጣችሁት ምላሽ ትክክል መሆኑን ወይም
አለመሆኑን ታረጋግጣላችሁ። በመጀመሪያ ማስታወሻ
ግን አንድ ጥያቄ እኔ እመልሳለሁ። የአዲስ ቃላትን ፍቺ ፈልጎ ማግኘት፣ በንባብ
መ. ዕድር የሚመሠረተው በአንድ ሠፈር በሚኖሩ ሂደት ወቅት ራስን የመከታተያ ስልት ነው።
ሰዎች ብቻ ነው። (ዓረፍተነገሩን በሰሌዳው ከምንባቡ ውስጥ የሚገኙ ዐውዳዊ ፍንጮችን
ላይ ይጻፉላቸው።) ይህ ዓረፍተነገር የያዘው በመጠቀም፣ ዋና ቃልንና ቅጥያዎችን በመለየት፣
ሀሳብ ትክክል ነው ወይስ ስህተት? መዝገበቃላትን በመጠቀም በንባብ ጊዜ የአዲስ
ቃላትን ፍቺ የምንረዳበት ስልት ነው።
[መ. ስህተት ነው። ስለዚህ “ሐሰት” ብዬ
መልሻለሁ። ምክንያቱም ዕድርን በሠፈር ብቻ
ሳይሆን በተመሳሳይ የሥራ መስክ ያሉ ሰዎች
ሊመሠርቱም እንደሚችሉ አውቃለሁ።]

56 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፶፮


ሥሩ [ተ. በ4ኛው አንቀጽ የዕድር ዓላማ ተዘርዝሯል።]
(መ. ምንባቡን በሚያነቡበት ጊዜ ፍቻቸውን (በዚህ መልኩ በተማሪዎች መጽሐፍ በ2ኛው
የማያውቋቸው አዳዲስ ቃላት ሲያጋጥሟቸው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን የቀረቡትን የአንብቦ
በምንባቡ ውስጥ የሚገኙ ዐውዳዊ ፍንጮችን መረዳት ጥያቄዎች እንዲመልሱ ያድርጉ።)
በመጠቀም፣ ዋና ቃሉን ከቅጥያው በመለየት
ወይም መዝገበቃላት በመጠቀም የቃላቱን ልሥራ
ፍቺ እንዲረዱና በማስታወሻቸው እንዲጽፉ መ. አሁን ደግሞ ሁለተኛውን ተግባር
ይንገሯቸው።) ትሠራላችሁ። በ“ሀ” ረድፍ የአንቀጾቹ ቍጥር፣
በ“ለ” ረድፍ ደግሞ የአንቀጾቹ ቁልፍ ሀሳቦች
መ. ተማሪዎች ዕድር በሚል ርዕስ የቀረበውን
ቀርበዋል፤ ስለዚህ የአንቀጾቹን ቁልፍ ሀሳቦች
ምንባብ የዋናና መዘርዝር ሀሳቦችን ግንኙነት
ከአንቀጾቹ ቍጥር ጋር ታዛምዳላችሁ።
በማስተዋል አንብቡ።
በመጀመሪያ ግን አንድ ጥያቄ እኔ
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) እመልሳለሁ።

እንሥራ መ. የመጀመሪያው አንቀጽ ስለምን ይገልጻል?


(መ. ተማሪዎች ምንባቡን አንብበው ከጨረሱ ጥያቄውን ለመመለስ አንቀጹን አነባለሁ።
በኋላ ምን ያህል አዳዲስ ቃላት ከምንባቡ (አንደኛውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።)
እንዳወጡ ይጠይቋቸው። ባወጧቸው አዳዲስ የመጀመሪያው አንቀጽ ስለዕድር ምንነትና
ቃላት ላይም ከተማሪዎችዎ ጋር ይወያዩ።) ስለአመሠራረቱ ይገልጻል። ስለዚህ በ“ለ”
ረድፍ ከተዘረዘሩት ትክክለኛውን መልስ
መ. “ዕድር” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ የያዘው የትኛው ነው።?
አንብባችኋል፤ በቅድመንባብ ላይ ለቀረቡት
ጥያቄዎች የሠጣችሁት ምላሽ ትክክል ነበር? [መ. “ሠ”]
(የተማሪዎችን ምላሽ ይቀበሉ።) አሁን እንሥራ
በምንባቡ መሠረት የቀረቡ ጥያቄዎችን መ. አሁን ደግሞ አንድ ጥያቄ አብረን እንመልስ።
አብረን እንመልስ። ሁለተኛው አንቀጽ ስለምን ይገልጻል? (አንድ/
መ. ዕድር የሚመሠረትባቸው ሁለት መንገዶች ዲት ተማሪ ሁለተኛውን አንቀጽ እንዲያነብ/
ምንና ምን ናቸው? ይህን ጥያቄ ለመመለስ እንድታነብ ያድርጉ።)
የመጀመሪያውን አንቀጽ እናንብብ። [መተ. ስለዕድር መተዳደሪያ ደንቦች]
መ. ስለዚህ የጥያቄው መልስ ምንድን ነው? መ. ትክክል! ስለዚህ በ“ለ” ረድፍ ከተዘዘሩት
[መተ. የሠፈርና የመሥሪያቤት እድር] ትክክለኛውን መልስ የያዘው የትኛው ነው?

መ. በጣም ጥሩ! በ4ኛው አንቀጽ “በገንዘብ [መተ. “ረ”]


የሚደረገው እርዳታ ግን እንደሟች ቤተሰባዊ ሥሩ
ግንኙነት የተለያየ ነው” ይላል። የዓረፍተነገሩ
መ. አብረን በሠራነው መሠረት በ2ኛው ሳምንት፣
መልዕክት ምን ይመስላችኋል?
በ4ኛው ቀን የሚገኘውን የተግባር “2”፣ ከ3-6
[መተ. ከሟች ጋር የቅርብ ዝምድና ያላቸው ያሉትን ጥያቄዎች በደብተራችሁ ሥሩ።
ሰዎች ብዙም ቅርበት ከሌላቸው ሰዎች ይልቅ
ከፍ ያለ የገንዘብ ድጋፍ ያገኛሉ።]
ሥሩ
መ. ሰዎች ዕድር መመሥረት ለምን
አስፈለጋቸው?
[ተ. በችግርና በደስታ ጊዜ ተባብሮና ተረዳድቶ
ችግርን ለመፍታት።] (ተማሪዎች ግን ዝርዝር
ምላሽ ሊሠጡ ይችላሉ።)
መ. ይህን መልስ እንዴት አገኛችሁት?

፶፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 57


ሊሰጣቸው ይችላል።”]
5ኛ ቀን መ. መልካም! ስለዚህ የቃሉ ተመሳሳይ ፍቺ
ምንድን ነው?
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች [መተ. ያልተጠበቀ/ያልታሰበ የሚል ፍቺ
• ቃላት ይሆናል።]
• መጻፍ ሥሩ
መ. እስካሁን በሠራነው መሠረት በ2ኛው
ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን ለቀረቡት ቃላት
ቃላት (10 ደቂቃ) ተመሳሳይ ትሠጣላችሁ።
መ. “ማስተዛዘን” የሚለው ቃል በስንተኛው
ለቃላትና ለሐረጋት ተመሳሳይ ፍቺ
አንቀጽና ዓረፍተነገር ይገኛል?
መስጠት
[ተ. በ4ኛው አንቀጽ በመጨረሻው ዓረፍተነገር]
ልሥራ
መ. ዛሬ “ዕድር” ከሚለው ምንባብ ውስጥ መ. ጥሩ! ዓረፍተነገሩን ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
ለወጡ ቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይ ፍቺ [ተ. “የዕድሩ አባላትም ከሀዘንተኞች ቤት
ትሠጣላችሁ። በመጀመሪያ ግን እኔ በመገኘት ያስተዛዝናሉ።]
“ሀዘንተኛ” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ
ልሥጥ። የቃሉን ተመሳሳይ ፍቺ ለማግኘት መ. በጣም ጥሩ! አሁን ለቃሉ ተመሳሳይ ፍቺ
በመጀመሪያ ቃሉ ያለበትን አንቀጽና ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
ዓረፍተነገር ልፈልግ። ቃሉ በ4ኛው አንቀጽ [ተ. ያፅናናሉ]
በመጨረሻው ዓረፍተነገር ውስጥ ይገኛል።
ዓረፍተነገሩን ላንብብላችሁ። መ. ትክክል!

[መ. የዕድሩ አባላት በሀዘንተኞች ቤት በመገኘት (መ. በዚህ ዓይነት በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው
ያስተዛዝናሉ።] ቀን ለቀረቡት ቃላትና ሐረጋት፣ ተማሪዎች
ተመሳሳይ ፍቺ እንዲሰጡ ያድርጉ።
መ. ስለዚህ “ሀዘንተኞች” የሚለው ቃል ፍቺ በመጨረሻም በነዚሁ ቃላት ፍቻቸውን
ምንድን ነው።? የሚያሳዩ ዓረፍተነገሮች እንዲመሠርቱ
[መ. ዘመድ/ወዳጅ የሞተባቸው ሰዎች] የቤትሥራ ይስጧቸው።)
እንሥራ መጻፍ (30 ደቂቃ)
መ. እኔ በሠራሁት መልክ ሌላ የአንድ ቃል ፍቺ
አብረን እንፈልግ። “ድንገተኛ” የሚለው ቃል ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ተመሳሳይ ምንድን ነው? በዋናና መዘርዝር ሀሳብ ስልት አንቀጽ
መ. በመጀመሪያ ማድረግ ያለብን ምንድን ነው? መጻፍ
[መተ. ቃሉ የሚገኝበትን አንቀጽና ዓረፍተነገር እንሥራ
ማፈላለግ] መ.ተማሪዎች ባለፈው ክፍለጊዜ “የምግብ ዓይነት”
መ. ስለዚህ ቃሉ በስንተኛው አንቀጽና ዓረፍተነገር በሚል ርዕስ በዋና ሀሳብና መዘርዝር ሀሳቦች
ይገኛል? የአጻጻፍ ስልት አንቀጽ ለመጻፍ የሚያስችል
የቢጋር ሠንጠረዥ እንድታዘጋጁ የቤትሥራ
[መተ. በአራተኛው አንቀጽ በሁለተኛው ተሰጥቷችኋል። ሁላችሁም አዘጋጅታችኋል?
ዓረፍተነገር] (በክፍሉ ውስጥ ተዘዋውረው መሥራታቸውን
መ. ጥሩ! ዓረፍተነገሩን አብረን እናንብበው። ያረጋግጡ።)

[መተ. “የዕድር አባላት ድንገተኛ ችግር መ. በጣም ጥሩ! አሁን የሠራችሁትን


ሲደርስባቸው ተመጣጣኝ ብር በብድር እየነገራችሁኝ ለሁላችሁም ለመጻፍ

58 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፶፰


የሚያስችል የቢጋር ሠንጠረዥ በጋራ መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ የሚሰፍሩበት ቦታ የት
እናዘጋጅ። ላይ ነው?
መ. ዋናው ርዕሰጉዳያችን ምንድን ነው? [መተ. የምግብ ዓይነቶች በሚለው ሥር ባሉት
ሦስት ሳጥኖች ውስጥ]
[መተ. የምግብ ዓይነቶች]
መ.ትክክል! (ኃይልና ሙቀት ስጪ፣ በሽታ
መ. ትክክል! ምግቦች ለሰውልጅ ከሚሠጡት
ተከላካይና ገንቢ የሚሉትን በዋናው ሳጥን
ጥቅም አንፃር በስንት ይመደባሉ?
ሥር በተዘጋጁት ሦስት ሣጥኖች ውስጥ
[መተ. በሦስት] ይጻፉላቸው።)
መ. በጣም ጥሩ! ምን ምን ተብለው? መ. ኃይልና ሙቀት ሰጪ የሚባሉትን የምግብ
[መተ. ኃይልና ሙቀት ሰጪ፣ በሽታ ተከላካይና ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?
ገንቢ] [መተ. ዳቦ፣ እንጀራ፣ ፓስታ፣ ማር፣ ስንዴ፣ ገብስ
መ. ጥሩ ነው! አሁን ይህን መነሻ በማድረግ ወዘተ]
የቢጋር ሠንጠረዥ እናዘጋጅ። (የሚከተለውን (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎችንም ተማሪዎች ራሳቸው
የቢጋር ሠንጠረዥ በውስጡ ያሉትን አሟልተው እንዲያሰፍሩ ያደርጉ።)
መረጃዎች ሳይጽፉ ይሣሉላቸው።)
መ. አሁን አንቀጹን ለመጻፍ የሚያስችል
መንደርደሪያ ዓረፍተነገር እንመሥርት።
የምግብ መንደርደሪያ ዓረፍተነገሩ የአንቀጹን
ዓይነቶች አጠቃላይ ሀሳብ መያዝ አለበት። ይህንን
ከግምት ውስጥ በማስገባት መንደርደሪያ
ዓረፍተነገር መሥርታችሁ ልትነግሩኝ
ኃይልና በሽታ
ገንቢ ትችላላችሁ? (ተማሪዎች ዓረፍተነገር
ሙቀት ሰጪ ተከላካይ
እየመሠረቱ እንዲነግሩዎት ያድርጉ። ከዚያም
ዳቦ የተማሪዎቹን ምላሽ በማቃናት/ በማስተካከል
የአንቀጻቸውን መንደርደሪያ ዓረፍተነገር
እንጀራ ይንገሯቸው።)

ፓስታ መ. “ምግቦች ለሰው ልጅ ከሚሰጡት ጥቅም አንፃር


በሦስት ይመደባሉ” የሚለው ዓረፍተነገር
ማር የአንቀጻችሁ መንደርደሪያ ዓረፍተነገር
ይሆናል።
ስንዴ
ሥሩ
ገብስ መ. “ምግቦች ለሰው ልጅ ከሚሰጡት ጥቅም
አንፃር በሦስት ይመደባሉ” የሚለውን
መንደርደሪያ ዓረፍተነገር ያዘጋጃችሁትን
መ. የምንጽፈው አንቀጽ ዋና ሀሳብ ምንድን የቢጋር ሠንጠረዥ መነሻ በማድረግ “በዋናና
ነው? መዘርዝር ሀሳቦች የአጻጻፍ ስልት አንድ
[መተ. የምግብ ዓይነቶች] አንቀጽ ጻፉ።” (ተማሪዎች ሲጽፉ እየተዘዋወሩ
ይደግፏቸው።)
መ. ስለዚህ በቢጋር ሠንጠረዡ በየትኛው ክፍል
ይሠፍራል? የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
[መተ. ከራስጌ] የቃላትን ቅደምተከተል እንደገና
በማወቀር ዓረፍተነገር አስተካክሎ መጻፍ
መ. ትክክል! መዘርዝር ሀሳቦቹስ የትኞቹ ናቸው?
ልሥራ
[መተ. ኃይልና ሙቀት ሰጪ፣ በሽታ ተከላካይና
መ. ባለፈው ሳምንት የቃላትን ቅደምተከተል
ገንቢ]

፶፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 59


እንደገና በማዋቀር ዓረፍተነገሮችን
የማስተካከል ተግባር ሠርተናል። ዛሬም 6ኛ ቀን
ይህንኑ ተግባር መለማመድ እንቀጥላለን።
በመጀመሪያ አንድ የቃላት ቅደምተከተሉ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
የተዛባ ዓረፍተነገር አስተካክላለሁ።
• አቀላጥፎ ማንበብ
መ. “አለምነሽ ሄደች ወደትምህርት ቤት።”
የሚለው ዓረፍተነገር ተስተካክሎ ሲጻፍ ምን • መናገር
ይሆናል? • ሰዋስው
[መ. “አለምነሽ ወደትምህርትቤት ሄደች”
ይሆናል።] የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
እንሥራ ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ ሌላ ቅደምተከተሉን ያልጠበቀ
ተማሪዎች የመሠረቷቸውን ዓረፍተነገሮች
ዓረፍተነገር አብረን እናስተካክል።
እንዲናገሩ ያድርጉ፤ የመሠረቷቸው
መ. “አብደላ ሠራ ትልቅ ቤት።” የሚለው ዓረፍተነገሮች የቃላቱን ፍቺ በትክክል የሚያሳዩ
ዓረፍተነገር ተስተካክሎ ሲጻፍ እንዴት መሆናቸውን በማረጋገጥ ግብረመልስ ይስጡ።
ይሆናል?
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
[መተ. አብደላ ትልቅ ቤት ሠራ።]
ዕድር
ሥሩ
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
መ. አሁን ደግሞ ሌላ የቃላት ቅደምተከተሉን
ያልጠበቀ ዓረፍተነገር እነግራችኋለሁ፤ (መ. ቀጥሎ ያለውን ማስታወሻ ያብራሩላቸው።)
እናንተ ታስተካክላላችሁ።
ማስታወሻ
መ.“ፋጡማ አለፈች ፈተናውን” የሚለው
የማንበብ ልምምድ በሚደረግበት ጊዜ ትኵረት
ዓረፍተነገር ተስተካክሎ የሚጻፈው እንዴት
ሊሠጣቸው የሚገቡ ነጥቦች አሉ። እነዚህም፡-
ነው?
ፊደላትን በትክክል መጥራት፣ ቃልን ሳይነጥሉ
[ተ. ፋጡማ ፈተናውን አለፈች።] ማንበብ፣ ቃልን አለመደጋገምና ቃል በቃል
መ. በጣም ጥሩ!(በዚህ ዓይነት በ2ኛው ሳይሆን በሐረግ ማንበብ የመሳሰሉት ናቸው።
ሳምንት በ5ኛው ቀን የሚገኙትን የቃላት ከነዚህ በተጨማሪ በንባብ ጊዜ ሥርዓተነጥቦችን
ቅደምተከተላቸው የተዛቡ ዓረፍተነገሮችን በአግባቡ መጠቀም ሌላው ትኵረት ሊሰጠው
አስተካክለው እንዲጽፉ ያድርጉ። የሚገባ ጉዳይ ነው። ለምሳሌ ነጠላ ሠረዝ
በመጨረሻም የጻፉትን ተመልከተው ላይ ከፊል (አጭር) ዕረፍት፣ አራት ነጥብ ላይ
ቃላቱን በትክክለኛ ቦታቸው መግባታቸውን ደግሞ ሙሉ ዕረፍት ማድረግ ያስፈልጋል።
በማረጋገጥ ግበረመልስ ይስጧቸው።)
ማንበብ (8 ደቂቃ )
ልሥራ
መ. ዛሬ ባለፈው ሳምንት ካነበብነው፣ “ዕድር”
በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ በሦስተኛውና
በአራተኛው አንቀጾች ድምፅ እያሰሙ
የማንበብ ልምምድ እናደርጋለን።
በመጀመሪያ እኔ አነባለሁ።
(መ.“ዕድር” በሚለው ርዕስ ከቀረበው ምንባብ
ሦስተኛውና አራተኛውን አንቀጾች
በማስታወሻው ላይ የሠፈሩትን ስልቶች
ተግባራዊ በማድረግ ድምፅዎን በማሰማት

60 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፷


ያንብቡላቸው።) እችላላሁ። ለምሳሌ፣ ዕድር በሰዎች መካከል
መቀራረብንና መተሳሰብ ያዳብራል።የሚል
እንሥራ
ሀሳብ አቅርባለሁ።]
መ. አሁን ደግሞ እኔ ያነበብኳቸውን ሁለት አንቀጾች
አብረን እናንብብ። (አሁንም በማስታወሻው እንሥራ
ላይ የተዘረዘሩትን ስልቶች ተግባራዊ እያደረጉ መ. አሁን ደግሞ ይህንኑ የመከራከሪያ ሀሳብ
ተማሪዎች ድምፃቸውን እያሰሙ ከርስዎ ጋር ይዘን አብረን እንሥራ።
እንዲያነቡ ያድርጉ።)
መ. “ዕድር ጉዳቱ ያመዝናል” የምትሉ እጃችሁን
ሥሩ አውጡ።
መ. አሁን ደግሞ አብረን ያነበብናቸውን መ. እኔ ከጠቀስኩት ሌላ የዕድርን ጉዳት
ሁለት አንቀጾች ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ልትነግሩኝ ትችላለችሁ? (ተማሪዎች
ተራበተራ ድምፅ እያሰማችሁ አንብቡ። እንዲናገሩ ያድርጉ።)
(ባለፈው ክፍለጊዜ እንዳደረጉት አቀላጥፈው
የሚያነቡትን አቀላጥፈው ከማያነቡት [መተ. አንዳንድ ጊዜ ወርሃዊ መዋጮውን
ጋር ያቀናጁ፤ በመጀመሪያ አቀላጥፈው የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሰዎች ገለልተኛ
የሚያነቡትን አንድ ጊዜ እንዲያነቡ፣ ከዚያም ያደርጋል። ለምሳሌ በተደጋጋሚ ወርሃዊ
አቀላጥፈው የማያነቡት ሁለት ጊዜ እንዲያነቡ መዋጮ ያልከፈሉ ሰዎች ከዕድር አባልነት
ያድርጉ። አንዳቸው ሲያነቡ ሌሎቹ ይሠረዛሉ።]
ደግሞ በመጽሐፋቸው በቀረበው የስህተት መ. ጥሩ ነው! አሁን ደግሞ ዕድር ጥቅሙ
መመዝገቢያ ሠንጠረዥ ውስጥ ማስታወሻ ያመዝናል የምትሉ እጃችሁን አውጡ።
ይያዙ። በመጨረሻም ተማሪዎች ስህተት
የመዘገቡበትን ወረቀት ይሰብስቡ። በተለይም መ. እኔ ከጠቀስኩት ሌላ የዕድርን ጥቅም
አቀላጥፈው የማያነቡትን በመጀመሪያውና ልትነግሩኝ ትችላላችሁ? (እጃቸውን ካወጡት
በሁለተኛው ንባብ የተመዘገበላቸውን ስህተት መካከል የተወሰኑት ምክንያታቸውን
ያነፃፅሩ።) እንዲናገሩ ያድርጉ።)
[መተ. ዕድር ሰዎች የሚያጋጥሟቸውን ልዩ
መናገር (15 ደቂቃ) ልዩ ችግሮች ተረዳድተው ለመቅረፍ
ያስችላቸዋል።]
ልሥራ
መ. ዛሬ “ዕድር” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንበብ ሥሩ
መነሻ በማድረግ ክርክር ታደርጋላችሁ። መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን
በመጀመሪያ ግን አንድ የመወያያ ሀሳብ “በመናገር” ሥር ከቀረቡት የመከራከሪያ
መነሻ በማድረግ እንዴት ክርክር ማድረግ ርዕሰጉዳዮች አንዱን መርጣችሁ ተከራከሩ።
እንደሚቻል አሳያችኋለሁ። (ተቃራኒ አቋም ይዘው የሚከራከሩ ሦስት
ሦስት በድምሩ ስድስት ተማሪዎችን
መ. ዕድር ከጠቀሜታውና ከጉዳቱ የትኛው
በየቡድኑ ውስጥ ይመድቡ። ከዚያም
ያመዝናል?
ተማሪዎቹ የያዙትን አቋም በማስረጃ
[መ.ዕድር ጉዳቱ ያመዝናል፤ ወይም ዕድር እያስደገፉ እንዲከራከሩ ያድርጉ። ተማሪዎች
ጥቅሙ ያመዝናል ብዬ መከራከር እችላለሁ። በሚከራከሩበት ጊዜ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ
ነገር ግን ይህን ሳደርግ ምክንያት/ማስረጃ በመከታተል ጥያቄ በመጠየቅ፣ ፍንጭ
ማቅረብ ይጠበቅብኛል። ለምሳሌ ያህል ዕድር በመስጠት ክርክሩ እንዲቀጥል ያበረታቱ።
ጉዳቱ ያመዝናል ብዬ ልከራከር ነው። ስለዚህ በመጨረሻም ከየቡድኑ የተወከሉ ሁለት
የዕድርን ጉዳቶች እዘረዝራለሁ። በመጀመሪያ ሁለት ተማሪዎች የቡድናቸውን ሀሳብ
ደረጃ በዕድር ምክንያት የሚባክነው ጊዜ ቀላል ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
አይደለም። በሞት፣ በመርዶ፣ በስብሰባ ወዘተ.
በርካታ የሥራ ሰዓት ይባክናል። በሌላ በኩል
ዕድር ጠቀሜታው ያመዝናል ብዬ ለመከራከር
ብወስን በርካታ ምክንያቶችን መዘርዘር

፷፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 61


ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ኢሳቢ ግሶች
እንሥራ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለኢሳቢ ግሶች
ተምረናል። ኢሳቢ ግስ ምን ማለት እንደሆነ
አስታውሳችሁ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
[መተ. ኢሳቢ ግስ የሚባለው ድርጊቱ በራሱም
በባለቤቱም ያለቀ የግስ ዓይነት ነው።]
መ. አሁን ለኢሳቢ ግሶች የተወሰኑ ምሳሌዎች
ልትሠጡኝ ትችላላችሁ?
[መተ. ሮጠ፣ ተነሳ፣ ሄደ፣ ሳቀ፣ በራ…] (መምህርና
ተማሪዎች የተለያዩ ምሳሌዎች ያቀርባሉ።)
መ. በጣም ጥሩ! ካቀረብናቸው ምሳሌዎች መካከል
“ተነሳ”ን ወስደን በተለያየ ቅርፅ እናርባው።
መ. እኔ----------------------።
[መተ. እኔ ተነሳሁ]
መ. አንቺ----------------------
[መተ. አንቺ ተነሳሽ።]
መ. እነሱ ––––––––።
[መተ. እነሱ ተነሱ።]
ሥሩ
መ. ተማሪዎች በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን
የሚገኝውን ተግባር “1”ን በምሳሌው መሠረት
በግል ሥሩ።
(መ.ተግባሩን የሚሠሩበት 5 ደቂቃ ይስጧቸው፤
ተግባሩን በሚሠሩበት ጊዜ በክፍሉ ውስጥ
እየተዘዋወሩ በትክክል መሥራታቸውን
ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ።
በመጨረሻም ተግባር “2”ን የቤትሥራ
እንዲሠሩ ይንገሯቸው።)

62 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፷፪


መ. “በመተሳሰራቸው” የሚለውን ሐረግ ነጥለን
3ኛ ሳምንት እናንብበው።
ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች [መተ. በ- መተሳሰር-ኣቸው]
መ. ጥሩ ነው! አሁን ይህንኑ ሐረግ አጣምረን
7ኛ ቀን እናንብበው።

የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች [መተ. በመተሳሰራቸው]


• የቃላት ጥናት መ. ጥሩ! “ኢኮኖሚያዊ” የሚለውን ቃል ነጥለን
እናንብበው።
• ማንበብ
[መተ. ኢኮኖሚ-ኣዊ]
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምረን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) እናንበው።
ሥሩ [መተ. ኢኮኖሚያዊ]
(ተማሪዎች የሠሩትን የቤትሥራ ይመልከቱ፤ (መ. በጣም ጥሩ!)
መልሶቹን በመንገር ደብተራቸውን ተቀያይረው
እንዲተራረሙ ያድርጉ። መልሶቹ ሀ. መጣሁ፣ ለ. ሥሩ
ሳቅን፣ ሐ. ወፈርሽ፣ መ. ቀላህ፣ ሠ. ወደቃችሁ፣ መ. አሁን ደግሞ በ3ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን
ረ. ነቃ፣ ሰ. ተናገረች፣ ሸ. ተከፋ ናቸው።) በቃላት ጥናት ሥር የቀረቡትን ሐረጋት/
ቃላት በመነጠልና በማጣመር አንብቡ።
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ) መ. “ያላገናዘበ” የሚለውን ሐረግ ነጣጥላችሁ
መነጠልና ማጣመር አንብቡ።

ልሥራ [ተ. ይ-ኣል-አገናዘበ]


መ. ዛሬ “ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት” በሚል ርዕስ (መ. ትክክል! አሁን ደግሞ አጣምራችሁ
ከቀረበው ምንባብ የወጡ ውስብስብ ቃላትንና አንብቡት።)
ሐረጋትን እየነጠላችሁና እያጣመራችሁ
ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን እኔ አነባለሁ፤ [ተ. ያላገናዘበ]
ተከታተሉኝ። (በዚህ ዓይነት ቀሪዎቹን ሐረጋት ያስነብቡ።)
[መ. “በመተሳሰራቸው” የሚለውን ሐረግ ነጣጥዬ
ሳነበው” በ-መተሳሰር-ኣቸው ይሆናል።] ማንበብ (30 ደቂቃ)
(ሐረጉን ነጣጥለው ያንብቡላቸው።)
ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች
[መ. አሁን ይህንኑ ሐረግ አጣምሬ ሳነበው
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
“በመተሳሰራቸው” ይሆናል።] (ሙሉውን
ሐረግ ሳይነጣጥሉ ያንብቡላቸው።) የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
[መ. “ኢኮኖሚያዊ” የሚለውን ቃል ነጣጥዬ እንሥራ
ሳነበው “ኢኮኖሚ-ኣዊ” ይሆናል።] መ. ዛሬ “ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች” በሚል ርዕስ
የቀረበ ምንባብ እናነባለን። ከዚያ በፊት
[መ. አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምሬ ሳነበው
ግን በጥቂት የቅድመንባብ ጥያቄዎች ላይ
“ኢኮኖሚያዊ” ይሆናል።] (ሙሉውን ቃል
እንወያያለን።
ሳይነጥሉ ያንብቡላቸው።)
መ. ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ምን ማለት
እንሥራ
ይመስላችኋል?
መ. አሁን እኔ ብቻዬን ያነበብኳቸውን ቃላት
አብረን እናነባለን። [መተ. በሰዎች ላይ አካላዊ፣ ሥነልቦናዊ፣
ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት የሚያደርሱ

፷፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 63


ልማዶች ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት ይባላሉ።] አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ )
መ. ጥሩ! በአካባቢያችሁ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ልሥራ
አሉ? መ. አሁን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎቹን
[መተ. አዎ] ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ ግን ጥቂት
ጥያቄዎችን እኔ እመልሳለሁ። አንዳንድ
መ. ምን ምን ናቸው? የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች ቀጥተኛ
[መተ. እንጥል ማስቆረጥ፣ ጉሮሮ ማስቧጠጥ፣ መልስ ሊኖራቸው ይችላል። የእንደነዚህ
አቅምን ያላገናዘበ ድግስ...] ዓይነት ጥያቄዎችን መልሶች ከምንባቡ
ውስጥ በቀጥታ ልናገኝ እንችላለን። ይህን
ሥሩ በሚከተለው ምሳሌ እንመልከት።
መ. በአካባቢያችሁ ያሉ ሌሎች ጎጂ ልማዳዊ
ድርጊቶች ልትነግሩኝ ትችላላችሁ? መ. አንድ ነገር ወይም ድርጊት ልማድ የሚሆነው
እንዴት ነው?
[ተ. የሴት ልጅ ግርዛት፣ ያለዕድሜ ጋብቻ፤
አቅምን ያላገናዘበ ድግስ…] [መ. አንድ ነገር በተመሳሳይ ሁኔታ ለብዙ
ጊዜያት ተደጋግሞ ሲከወን ልማድ እንደሚሆን
መ. በጣም ጥሩ! ጠቃሚ ልማዶችስ አሉ? በመጀመሪያው አንቀጽ ተገልጿል።]
[ተ. አዎ] መ. አንዳንድ ጥያቄዎች ደግሞ አመራማሪ
መ. ምን ምን ናቸው? ሊሆኑ ይችላሉ። የእንደነዚህ ዓይነት
ጥያቄዎች ምላሽ በምንባቡ ውስጥ በቀጥታ
[ተ. በዕድርና በዕቁብ መደጋገፍ፣ ባህላዊ የግጭት ላይገኝ ይችላል። ነገርግን በምንባቡ ውስጥ
መፍቻ መንገዶች…] የተነገረውን መነሻ በማድረግ ስላልተነገረው
መ. በጣም ጥሩ! አሁን “ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት” መግለፅ ይቻላል። ይህንንም በአንድ ጥያቄ
በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ በተሰጣችሁ ምሳሌ እንመልከት።
7 ደቂቃ አንብቡ። መ. ድግስ ጎጂ የማይሆነው መቼ ነው?
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) [መ. አንቀጽ 5 ላይ አቅም ያላገናዘበ ድግስ ጎጂ
(መ. ተማሪዎች ምንባቡን በሚያነቡበት ጊዜ ልማድ መሆኑ ተጠቅሷል። ስለዚህ ድግስ
አዳዲስ ቃላት ሲያጋጥሟቸው በምንባቡ አቅምን ከግምት ውስጥ ያስገባ ከሆነ ጎጂ
ውስጥ የሚገኙ ዐውዳዊ ፍንጮችን አይደለም ማለት ነው።]
ተጠቅመው፣ ዋና ቃልን ከቅጥያው ለይተው እንሥራ
ወይም መዝገበ ቃላትን ተጠቅመው፣ የቃላቱን
መ. አሁን ደግሞ ሁለት ጥያቄዎች አብረን
ፍቺ እየተረዱ እንዲያነቡ ያሳስቧቸው።
እንሥራ።
ያጋጠሟቸውን አዳዲስ ቃላትና የሰጧቸውን
ፍቾች በማስታወሻቸው እንዲመዘግቡም መ. በአንዳንድ አካባቢዎች የሴት ልጅ ግርዛት
ይንገሯቸው። ምንባቡን አንብበው ሲጨርሱም በሰባተኛ ቀን የሚፈፀመው ለምንድን ነው?
በማስታወሻቸው ላይ የመዘገቧቸውን አዳዲስ [መተ. ምክንያቱም ሰውነት ሲጠነክር የሚፈፀም
ቃላት እንዲነግሩዎት ያድርጉ። ለነገሩዎት ግርዛት ለስቃይ ይዳርጋል ተብሎ
አዳዲስ ቃላትም የሰጡትን ፍቺ እንዲናገሩ ስለሚታመን።]
ያድርጉ።)
መ. ያለዕድሜ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ፍላጎት
(መ. ለምሳሌ “ግርዛት” የሚለውን ቃል ፍቺ ሊፈፀም የሚችል ይመስላችኋል?
ሊጠይቋቸው ይችላሉ። የዚህን ቃል ፍቺ
በምንባቡ ውስጥ የተገለፀውን ሀሳብ መነሻ [መተ. ያለዕድሜ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ፍላጎት
በማድረግ ሊረዱ ይችላሉ። “ኢኮኖሚያዊ” ሊፈፀም አይችልም።]
የሚለውን ቃል ፍቺ ደግሞ መዝገበ ቃላት መ. ለምን?
በማየት መረዳት ይችላሉ።)
[መተ. ምክንያቱም የተጋቢዎቹ አካልና አዕምሮ

64 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፷፬


ሳይበስል የሚፈፀም በመሆኑ፣ ተጋቢዎቹ በዚህ ሥሩ።
እድሜያቸው የመወሰንና ሀላፊነት የመሸከም
መ. “ዕድገት” ለሚለው ቃል በ“ለ” ረድፍ
አቅም ስለማይኖራቸው ነው።]
ከቀረቡት ቃላት መካከል ተመሳሳዩ የትኛው
ሥሩ ነው?
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን “በአንብቦ [ተ. ብልፅግና]
መረዳት” ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኙትን
ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ። መ. ትክክል!

(መ. ጥያቄዎቹን አንድ ባንድ እየጠየቁ (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎችንም ጥያቄዎች
ተማሪዎች ለጥያቄዎቹ ምላሽ እንዲሰጡ ያሠሯቸው። ተማሪዎች ምላሽ ከሰጡ በኋላ
ያድርጉ። ለተግባር ሁለት ደግሞ “የሴት ለቃላቱ ተገቢ ፍቺ መስጠት መቻላቸውን
ልጅ ግርዛት የሚያስከትለውን ጉዳት ይገምግሙ።)
በተመለከተ” ከምንባቡ በመነሳት አንድ
ምሳሌ ከሠጡ በኋላ ሌሎቹም በተመሳሳይ መጻፍ (30 ደቂቃ)
ሁኔታ በደብተራቸው በአዘጋጇቸው ክቦች
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ውስጥ እንዲሞሉ ያድርጉ። ተግባሩን
በትክክል እየሠሩ መሆናቸውን እየተዘዋወሩ በዋናና መዘርዝር ሀሳቦች ስልት የተጻፈ
ይከታተሉ፤ ከዚያም በቡድን የሠሩትን አንቀጽ መከለስ
እያስተያዩ እንዲወያዩ ያድርጉ።)
እንሥራ
መ. ዛሬ ባለፈው የጻፋችሁትን አንቀጽ
8ኛ ቀን ታስተካክላላችሁ። በመጀመሪያ ግን
ጽሑፋችሁን እንዴት እንደምታስተካክሉ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ለማሳየት አንድ ተግባር እንሥራ።
በመጽሐፋችሁ የቀረበውን አንቀጽ
• ቃላት
በደብተራችሁ ጻፉ። (አንድ/ዲት ተማሪ
• መጻፍ እንዲያነብ/እንድታነብ ያድርጉ)
መ. በጽሑፉ ውስጥ ዋና ሀሳብ አለ?
[መተ. አዎ]
ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. ዋና ሀሳቡን የያዘው ዓረፍተነገር የትኛው
ለቃላት ተመሳሳይ ፍቺ መስጠት ነው?
እንሥራ [መተ. የመጀመሪያው ዓረፍተነገር]
መ. ዛሬ “ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት” በሚል ርዕስ
መ. ጥሩ! በጽሑፉ ውስጥ ዋናውን ሀሳብ
ከቀረበው ምንባብ ለወጡ ቃላት ተመሳሳይ
የሚያብራሩ ዝርዝር ሀሳቦች አሉ?
ፍቺ እንሰጣለን።
[መተ. አዎ]
መ. “ኋላቀርነት” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ
እንስጥ። መ. ጥሩ! መዘርዝር ሀሳብ የያዙት ዓረፍተነገሮች
የትኞቹ ናቸው?
[መተ. አለመሰልጠን]
[መተ. ከመጀመሪያው ዓረፍተነገር በስተቀር
መ. ጥሩ ነው! አሁን ደግሞ “ያላገናዘበ” ለሚለው
ሌሎቹ ዓረፍተነገሮች መዘርዝር ሀሳብ የያዙ
ቃል ተመሳሳይ ፍቺ እንስጥ።
ናቸው።]
[መተ. ከግምት ያላስገባ]
መ. በጣም ጥሩ! በጽሑፉ ውስጥ ሥርዓተነጥቦቹ
ሥሩ በአግባቡ ጥቅም ላይ ውለዋል?
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን “በቃላት”
[መተ. አልዋሉም።]
ንዑስ ክፍል ሥር የቀረበውን የቃላት ተግባር

፷፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 65


መ. በአግባቡ ጥቅም ላይ ያልዋለው ሥርዓተነጥብ ጽሑፎች በመነሳት ተማሪዎች አሻሽለው
የትኛው ነው? እንዲጽፉ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
[መተ. ነጠላ ሠረዝ] የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
መ. ትክክል! ነጠላ ሠረዝ የሚገባው በየትኞቹ እንሥራ
ዓረፍተነገሮች ላይ ነው? መ. ባ ለ ፉ ት ክፍለጊዜያት የቃላት
[መተ. በ1ኛው፣ በ3ኛውና በ5ኛው ዓረፍተነገሮች ቅደምተከተላቸው የተዛቡ ዓረፍተነገሮችን
ውስጥ] ማስተካከል ተለማምዳችኋል። ዛሬም የቃላት
ቅደምተከተላቸው የተዛቡ ዓረፍተነገሮችን
መ. ስለዚህ ነጠላ ሠረዞቹን በተገቢ ቦታቸው አስተካክላችሁ ታሳያላችሁ። በመጀመሪያ ግን
ላይ እናስገባ። (ተማሪዎችን በማሳተፍ ነጠላ ጥቂት ዓረፍተነገሮችን አብረን እናስተካከል።
ሠረዞቹን በተገቢ ቦታቸው ያስገቡ)
መ. “በድንገት ውሻ ደነገጠች ሰሚራ ስለመጣባት።”
ሥሩ የሚለውን ዓረፍተነገር አብረን እናስተካክል።
መ. አሁን ደግሞ አብረን በሠራነው መሠረት
[መ. ሰሚራ ውሻ በድንገት ስለመጣባት
የቀሩትን ስህተቶች አስተካክሉ።
ደነገጠች።]
መ. በጹሑፉ ውስጥ የሰዋስው ስህተት አለ?
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ “ልጃቸው ፈተናውን
[ተ. አዎ] አቶ ንጉሴ ስላለፈ በጥሩ ውጤት ኮሩ።”
መ. ስህተት ያለባቸው ዓረፍተነገሮች የትኞቹ የሚለውን ዓረፍተነገር አብረን እናስተካክል።
ናቸው? [መተ. አቶ ንጉሴ ልጃቸው በጥሩ ውጤት
[ተ. ሁለተኛውና አምስተኛው] ፈተናውን ስላለፈ ኮሩ።]

መ. ሁለተኛውን ዓረፍተነገር ውስጥ ያለውን ሥሩ


ስህተት እናስተካከል። መ. አሁን ባለፉት ሁለት ሳምንታትና ዛሬም
የተለማመዳችሁትን ተግባር ምን ያህል
[ተ. “ነው” የሚለው “ናቸው” ይሆናል።] እንደተረዳችሁት ለመገምገም፣ በ3ኛው
መ. በጣም ጥሩ! በአምስተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ ስምንት፣ በ8ኛው ቀን የቀረቡትን
ያለውን ስህተት እናስተካክል። ዓረፍተነገሮች አስተካክላችሁ ጻፉ።

[ተ. በዚህ የእንስሳት ምድብ ውስጥ እንደውሻ፣ (መ. ይህን ተግባር ተማሪዎች በግል እንዲሠሩ
አንበሳና ነብር ያሉት ይካተታሉ።] ይንገሯቸው። ከዚያም ደብተራቸውን
እንዲቀያየሩ ያድርጉና በመልሶቹ ላይ
ሥሩ እየተነጋገራችሁ ርስበርሳቸው እንዲተራረሙ
መ. አሁን ባለፈው ሳምንት “የምግብ ዓይነቶች” ያድርጉ። የተማሪዎችን ደብተርም
በሚል ርዕሰ የጻፋችሁትን አንቀጽ ይመልከቱ።ተማሪዎች ያሳዩትን መሻሻል
በመጽሐፋችሁ በቀረበው ሠንጠረዥ ውስጥ ይገምግሙ።)
በተዘረዘሩት የመገምገሚያ መስፈርቶች
መሠረት ገምግሙ። ከዚያም በጽሑፋችሁ
ውስጥ የሚታዩትን ስህተቶች አስተካክሉ።
በመጨረሻም የተስተካከለውን ጽሑፍ ለኔ
ትሰጡኛላችሁ።
(መ. ተማሪዎች ጽሑፋቸውን ሲያርሙ
እየተዘዋወሩ እንዴት ማስተካከል እንዳለባቸው
ያማክሯቸው። ተማሪዎች ጽሑፋቸውን
አስተካክለው ሲጨርሱ፣ ይሰብስቡና ያርሙ።
ከዚያም የተሻሉ ሥራዎችን ለክፍሉ
ተማሪዎች እንዲያነቡ ያደርጉ። ከተነበቡት

66 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፷፮


ተማሪዎችንም ወረቀት ላይ እንዲያዘጋጁት
9ኛ ቀን ያድርጉ።)

የመገምገሚያ በመጀመሪያ በሁለተኛ


የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መስፈርቶች ንባብ ንባብ
• አቀላጥፎ ማንበብ 1 በስህተት
• መናገር የተነበቡ ቃላት
ብዛት
• ሰዋስው
2 በንባብ ጊዜ
የተደገሙ ቃላት
ብዛት
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
3 ተነጥለው
ሥሩ የተነበቡ ቃላት
መ. አሻሽላችሁ የጻፋችሁትን አንቀጽ ለክፍል ብዛት
ጓደኞቻችሁ አንብቡ። 4 በሐረግ መነበብ
[ተ. ያሻሻሉትን አንቀጽ ለጓደኞቻቸው ያነባሉ] ሲገባቸው፣ ቃል
በቃል የተነበቡ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ቃላት ብዛት

ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች
መ. በመጀመሪያ “1” ቍጥሮች በምሠጣችሁ 2
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) ደቂቃ ድምፃችሁን እያሰማችሁ ታነባላችሁ።
ሥሩ “1” ቍጥሮች ሲያነቡ “2” ቍጥሮች ወረቀት
መ. ባለፈው በአንበቦ መረዳት ሂደት ምንባብ ላይ ባዘጋጃችሁት ሠንጠረዥ ውስጥ “1”
ስታነቡ ማድረግ የሚጠበቅባችሁ ነገሮች ቍጥሮች ስህተት በፈፀሙ ቍጥር የ“/”
ተምራችኋል። እነዚህን ነገሮች አስታውሳችሁ ምልክት አድርጉ። አንድ ቍጥሮች ማንበብ
ንገሩኝ። (ከተማሪዎች መልሱን ይቀበሉ።) ጀምሩ!
[ተ. “1” ቍጥሮች ድምፅ እያሰሙ ያነባሉ። “2”
ማንበብ (8 ደቂቃ)
ቍጥሮች እያዳመጡ ማስታወሻ ይይዛሉ።]
ሥሩ
(መ.2 ደቂቃ ሲሞላ ያስቁሙ።)
(መ.በመጀመሪያ አቀላጥፈው የሚያነቡትን
አቀላጥፈው ከማያነቡት ጋር በጥንድ በጥንድ መ. በጣም ጥሩ! ያቆማችሁበት ቦታ በጣታችሁ
ያቀናጇቸው። አቀላጥፈው የሚያነቡትን “1” ምልክት ያዙ። ከዚያም “2” ቍጥሮች፣ “1”
ቍጥር፣ አቀላጥፈው የማያነቡትን “2” ቍጥር ቍጥሮች ያነበቡትን ቃላት ብዛት ቁጠሩ።
በማለት ይሰይሟቸው። ይህን ግን በቀደሙት በመቀጠልም በእያንዳንዱ የስህተት ዓይነት
ክፍለጊዜዎች ባደረጉት ክትትል መሠረት ላይ የፈፀሙትን የስህተት ብዛት ቁጠሩና
አስቀድመው ወስነው ቢመጡ የተሻለ የመጀመሪያ ንባብ በሚለው የሠንረዡ ክፍል
ነው። የተማሪዎችን ስሜት ላለመንካት ጻፉ።
“አቀላጥፈው የሚያነቡ” ወይም “አቀላጥፈው [ተ. ቍጥር “2” ተማሪዎች፣ ቊጥር “1” ቍጥሮች
የማያነቡ” የሚለውን አገላለጽ ክፍል ውስጥ የፈፀሙትን ስህተት ቈጥረው ይመዝግባሉ።]
አይጠቀሙ። ዝምብለው “1” ቍጥር የሆኑትን
ስማቸውን በመዘርዘር፣ ቀጥሎም “2” ቍጥር (መ. በተመሳሳይ አሠራር “1” ቍጥሮች ለ2
የሆኑትን ስማቸውን በመዘርዘር ቍጥራቸውን ደቂቃ ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ። “2”
እንዲያውቁ ያድርጉ። ማስነበብ ከመጀመርዎ ቍጥሮች ደግሞ “በሁለተኛ ንባብ” በሚለው
በፊት የሚከተለውን የንባብ መገምገሚያ ውስጥ ስህተቶች እንዲመዘግቡ ያድርጉ።
ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ ይሣሉላቸውና በመቀጠልም “2” ቍጥሮች አንባቢ፣ “1”
ቍጥሮችን ገምጋሚ በማድረግ ከላይ

፷፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 67


በቀረበው ሂደት መሠረት ደረጃ በደረጃ ትችላላችሁ?
እንዲሠሩ ያድርጉ። በመጨረሻም ተማሪዎች
[ተ. አንድ/ዲት ተማሪ የኢሳቢ ግስን ምንነት
የገመገሙበትን ወረቀት በመሰብሰብ
ይናገራል/ትናገራለች።]
የተማሪዎችን መሻሻል ይገምግሙ።
አቀላጥፈው የማያነቡ ተማሪዎች የንባብ መ. በጣም ጥሩ ኢሳቢ ግስ፣ ድርጊቱ ባለቤቱ ላይ
ችሎታቸውን የሚያዳብሩበትን ስልት ያለቀ የግስ ዓይነት ነው።
ይንደፉ። የንባብ የቤትሥራዎች በመስጠት መ. ባለፉት ሁለት ሳምንታት ኢሳቢ ግሶችን
ለተማሪዎች የማንበብ ዕድል መፍጠር እየመረጥን ቅርፃቸውን በመለዋወጥ
ይችላሉ።) ዓረፍተነገር ስናሟላ ነበር። አንድ ኢሳቢ ግስ
ንገሩኝ።
መናገር (15 ደቂቃ)
[መተ. መጣ]
ሥሩ
መ. “መጣ” የሚለውን ግስ የተለያየ ቅርፅ ንገሩኝ”።
መ. ዛሬ በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን በመናገር
ሥር ከቀረቡት የመወያያ ጥያቄዎች አንዱን [ተ. መጣች፣ መጣሁ…]
መርጣችሁ በቡድን ትወያያላችሁ።
መ. በጣም ጥሩ!
(መ. በመጀመሪያ ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን በሰዋስው
ባሉት ቡድን ያደራጇቸው፤ ተማሪዎች ሥር የቀረበውን ተግባር በደብተራችሁ
በቡድናቸው ውስጥ አንድ ሰብሳቢ፣ አንድ ጸሐፊ፣ ሥሩ። (8 ደቂቃ ይስጧቸው። ደብተራቸውን
አንድ አቅራቢ እንዲመርጡ ያድርጉ። ከዚያም በማረም ይገምግሙ። እንዳስፈላጊነቱ
ከቀረቡት ሁለት ጥያቄዎች መካከል ሊያወያያቸው ውጤቱን ሊመዘግቡ ይችላሉ።)
የሚችለውን አንዱን ይምረጡላቸው፣ ወይም
ተማሪዎች እንዲመርጡ ያድርጉ። ተማሪዎች
በሚወያዩበት ጊዜ የሰብሳቢ ሥራ ቡድኑን
ማስተባበርና አባላቱ እንዲናገሩ ዕድል መስጠት
መሆኑን፣ የጸሐፊ ደግሞ አባላቱ ሲናገሩ
ማስታወሻ መያዝ፣ የአቅራቢ ደግሞ የቡድኑን
ሀሳብ በመጨረሻ ለክፍሉ ተማሪዎች ማቅረብ
መሆኑን ይንገሯቸው። ተማሪዎች ሲወያዩ
እየተዘዋወሩ ጥያቄ በመጠየቅ፣ ፍንጭ በመስጠት
ውይይታቸውን ያበረታቱ። ለውይይት የተሰጠው
6 ደቂቃ ሲያበቃ ያስቁሙ። ከዚያም ከየቡድኑ
አንድ አንድ ተማሪ እያስነሱ የቡድኑን ሀሳብ
እንዲያቀርቡ ያድርጉ። በውይይቱ ሂደትም ሆነ
ተማሪዎች በሚያቀርቡበት ጊዜ የተማሪዎቹን
ሀሳብን በቅደምተከተል የመግለፅ ችሎታ፣ ማስረጃ
የማቅረብ አቅም፣ የድምፅ መሰማት ይገምግሙ።
ጥሩ የተናገሩትን ተማሪዎች ያበረታቱ። ደከም
ላሉትም የማጠናከሪያ ተግባራት አዘጋጅተው
ያሠሩ።)

ሰዋስው (10 ደቂቃ)


ኢሳቢ ግሶች
እንሥራ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ከተማርነው በመነሳት
ስለኢሳቢ ግስ ምንነት ልትነግሩኝ

68 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3 ፷፰


ምዕራፍ 4 የትራፊክ ደህንነት
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• “የትራፊክ ደህንነት” በሚል ይዘት ስር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይጽፋሉ፤
• በድርጊት ቅደምተከተል የተዋቀረ አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• ቃላትንና ዓረፍተነገሮችን አዳምጠው በትክክል ይጽፋሉ፤
• አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• የሚነበብላቸውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• የቅደምተከተል ስልትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• ሳቢ ግሶችን በተለያዩ ቅርጾች ያረባሉ።

እናንብበው።
1ኛ ሳምንት
[መተ. ባለማድረጋቸው]
የመንገድ ደህንነት
ሥሩ
መ. “ዜብራ” የሚለውን ቃል ነጣጥላችሁ
1ኛ ቀን አንብቡልኝ።

የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች [ተ. ዜ-ብ-ራ]


• የቃላት ጥናት መ.ትክክል! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል
አጣምራችሁ አንብቡልኝ።
• ማንበብ
[ተ. ዜብራ]
መ. በዚህ ዓይነት በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን
በቃላት ጥናት ሥር የቀረቡትን ቃላት በቡድን
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ)
ሆናችሁ እየነጠላችሁና እያጣመራችሁ
መነጠልና ማጣመር አንብቡ።
እንሥራ
መ. ዛሬ “የመንገድ ላይ ጥንቃቄ” በሚል ርዕስ ማንበብ (35 ደቂቃ)
የቀረበ ምንባብ ታነባላችሁ። ከዚያ በፊት የመንገድ ላይ ጥንቃቄ
ግን ከምንባቡ የወጡ ቃላትን እየነጠላችሁና
እያጣመራችሁ በማንበብ ትለማመዳላችሁ። ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
በመጀመሪያ አብረን እናነባለን። የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
መ.“ባለማድረጋቸው” የሚለውን ቃል በመጀመሪያ መ. ዛሬ “የመንገድ ላይ ጥንቃቄ” በሚል ርዕስ
ነጣጥለን እናንብበው። የቀረበ ምንባብ ታነባላችሁ። በመጀመሪያ
[መተ. ባለ-ማድረግ-ኣቸው] ግን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን የቀረቡትን
የቅድመንባብ ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ።
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምረን

፷፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 69


መ. በአካባቢያችሁ የመንገድ ላይ አደጋ ደርሶ ያስቁሟቸው።)
ያውቃል? የምታስታውሱትን ገጠመኝ
መ. ሦስተኛውን አንቀጽ ስታነቡ እግረኞች
ተናገሩ።
የመኪና መንገድ ሲያቋርጡ ማድረግ
[ተ. በአካባቢያቸው ስለደረሱ የመንገድ አደጋዎች ስላለባቸው ጥንቃቄ በአዕምሯችሁ ውስጥ
አስታውሰው ይናገራሉ።] የተፈጠረውን ሥዕል ለጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
(ከዚያም ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት የቀረቡትን
የቅድመንባብ ጥያቄዎች እየጠየቁና፣ ፍንጭ አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)
እየሰጡ ተማሪዎች በቃላቸው እንዲመልሱ
እንሥራ
ያድርጉ።)
መ. አሁን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን በጋራ
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) እንመልሳለን።
ልሥራ መ. የእግረኞች መንገድ በሌለባቸውና፣
መ. አዕምሯዊ ምሥል መፍጠር ከአንብቦ ተሽከርካሪዎች በሚበዙባቸው አካባቢዎች
መረዳት ብልሀቶች አንዱ ነው። በምታነቡበት ሰዎች መጓዝ ያለባቸው እንዴት ነው?
ጊዜ በጹሑፉ ውስጥ የተገለፁ ነገሮችን፣
[መተ. የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዘው መጓዝ
ድርጊቶችን ወዘተ. በአዕምሯችሁ ውስጥ
አለባቸው።]
ለመሣል እየሞከራችሁ ማንበብ፣ የምታነቡትን
ነገር ለመረዳት ያግዛችኋል። ይህን እንዴት መ. በጣም ጥሩ! የዚህን ጥያቄ ምላሽ እንዴት
ማድረግ እንደምትችሉ አንብቤ ላሳያችሁ። አገኘን?
(3ኛውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።) መተ. በ2ኛው አንቀጽ ውስጥ “የእግረኞች መንገድ
[መ.“ለእግረኛ ማቋረጫ ተብሎ ነጭ ቀለም ከሌለ ሁለተኛው አማራጭ የመንገዱን ግራ
የተቀባ ቦታ (ዜብራ)…” የሚለውን አገላለፅ ጠረዝ ይዞ መጓዝ ነው” ይላል።]
ሳነብ በመኪና መንገዶች ላይ (አስፋልት) መ. በጣም ጥሩ ነው።
ላይ በቀጥታ መስመር የተቀቡ ነጫጭ
መስመሮች ታዩኝ። ምናልባት የማቋረጫውን ሥሩ
ምልክት ከዚህ በፊት የማላውቀው ቢሆንና መ. አሁን ደግሞ እናንተ ትሠራላችሁ። የመንገድ
ዜብራ (የሜዳ አህያ) የማውቅ ከሆነ፣ የሜዳ ላይ አደጋ በሰዎች ላይ ምን ጉዳት እያደረሰ
አህያን ሥዕል ወደአዕምሮዬ በማምጣት ነው?
ሀሳቡን ልረዳው እችላለሁ። ማለትም የሜዳ
[ተ. ሰዎች ሕይወታቸውን ያጣሉ፤አካል ጉዳተኛ
አህያ በጥቁር አካሏ ላይ ነጫጭ መስመሮች
ይሆናሉ።]
እንዳሏት አውቃለሁ። የመኪና መንገድ
ደግሞ ጥቁር መሆኑን አውቃለሁ። ስለዚህ መ. በጣም ጥሩ! ይህን መልስ እንዴት
“የዜብራ” ምልክት ለማቋረጫ ተብሎ አገኛችሁት?
በመንገዱ የሆነ ቦታ ላይ ነጭ ቀለም የተቀባ [ተ. ምክንያቱም በመጀመሪያው አንቀጽ ውስጥ
መስመር መሆኑን እረዳለሁ።] በመንገድ ላይ አደጋዎች በየዓመቱ ብዙ
ሥሩ ሰዎች ሕይወታቸውን ያጣሉ፤ አያሌ ሰዎች
መ. እናንተም በምታነቡበት ጊዜ በምንባቡ ውስጥ የአካል ጉዳተኛ ይሆናሉ ተብሎ ተገልጿል።]
የተገለፁ ነገሮችንና ድርጊቶችን በአዕምሯችሁ (መ. በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎቹንም ጥያቄዎች
ውስጥ ለመሣል እየሞከራችሁ አንብቡ። እየጠየቁ ተማሪዎች ምላሽ እንዲሰጡ
መ. ሁለተኛውን አንቀጽ ስታነቡ እግረኞች ያድርጉ። ተግባር “2”ን በቡድን ያሠሩ፤
በመኪና መንገድ ሲጓዙ ማድረግ ስላለባቸው በመጨረሻም የቢጋር ሠንጠረዡን በሰሌዳ
ጥንቃቄ በአዕምሯችሁ ውስጥ የተፈጠረውን ላይ ጽፈው ከተማሪዎች ጋር አብረው
ሥዕል ለጓደኞቻችሁ ተናገሩ። (ከዚያም በመሥራት ግበረመልስ ይስጡ።)
ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።
ሦስተኛውን አንቀጽም አንብበው እንደጨረሱ

70 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፸


መጻፍ (30 ደቂቃ)
2ኛ ቀን ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች በቅደምተከተላዊ መረጃ ሰጪ ገላጭ ስልት
የቢጋር ሠንጠረዥ ማዘጋጀት
• ቃላት
• መጻፍ
እንሥራ
መ. የድርጊቶችን ቅደምተከተል በደረጃ ለመግለፅ
የምንጠቀምባቸው ቃላት አሉ። እነሱም፦
ቃላት (10 ደቂቃ)
መጀመሪያ፣ ቀጥሎ፣ ከዚያ፣ በመካከል፣
ለቃላትና ለሐረጋት ዐውዳዊ ፍቺ በመጨረሻ... አንደኛ፣ ሁለተኛ የመሳሰሉት
መስጠት ናቸው። የድርጊቶችን ቅደምተከተል
በምናነብበት ጊዜ እነዚህ ቃላት ከመጀመሪያ
እንሥራ
እስከመጨረሻ ምን ምን ድርጊቶች
መ. ዛሬ “የመንገድ ላይ ጥንቃቄ” ከሚለው እንደተፈፀሙ ያመለክታሉ። ስለሆነም እኛም
ምንባብ ለወጡ ቃላት ዐውዳዊ ፍቺ አብረን ስንጽፍ እንገለገልባቸዋለን።
እንሰጣለን።
መ. አሁን ባለፈው ጊዜ ካነበባችሁት ምንባብ
መ. “እግረኞች፣ ለእግረኞች ተብሎ የተዘጋጀ 3ኛውን አንቀጽ መነሻ በማድረግ
መንገድ ካለ በዚያ መጠቀም ይኖርባቸዋል።” ቅደምተከተል ያለውን ድርጊት አብረን
“በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ “መጠቀም” እንመልከት። መንገድ ስናቋርጥ በመጀመሪያ
የሚለው ቃል ዐውዳዊ ፍቺ ምንድን ነው? ምን እናደርጋለን?
[መተ. መሄድ፣ ምክንያቱም “የተዘጋጀ መንገድ” [መተ. በመጀመሪያ ከመንገድ ጠርዝ ላይ
የሚለው ሐረግ “መጠቀም” የሚለው ቃል ፍቺ እንቆማለን።]
“መሄድ” መሆኑን ፍንጭ ይሰጣል።]
መ. ጥሩ! ቀጥሎ ምን እናደርጋለን?
መ. በጣም ጥሩ!
[መተ. ቀጥሎ ነጭ ቀለም የተቀባ ማቋረጫ ቦታ
ሥሩ (ዜብራ) መኖሩን እናያለን።]
መ. አሁን አብረን በሠራነው መሠረት በ1ኛው
ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን የቀረቡትን ቃላት መ. ከዚያስ?
ዐውዳዊ ፍቺ ስጡ። [መተ. ከዚያ ግራና ቀኝ በመመልከት በአቅራቢያ
መ. “የእግረኞች መንገድ ከሌለ የመንገዱን መኪና አለመኖሩን ወይም መኪኖች
ግራ ጠርዝ ይዞ መጓዝ ይገባል” በሚለው ለእግረኞች ቅድሚያ ሰጥተው መቆማቸውን
ዓረፍተነገር ውስጥ “ጠርዝ” የሚለው ቃል እናረጋግጣለን።]
ዐውዳዊ ፍቺ ምንድን ነው? መ. በመጨረሻ ምን እናደርጋለን?
[ተ. “ዳር”፣ “ግራ” ና “መጓዝ” የሚሉት ቃላት [መተ. በመጨረሻ ተገቢ በሆነ ፍጥነት መንገዱን
“ጠርዝ” የሚለው ቃል ፍቺ “ዳር” መሆኑን እናቋርጣለን።]
ይጠቁማሉ።]
መ. አሁን ይህን ያየነውን ቅደምተከተላዊ ሂደት
መ. በጣም ጥሩ! (በመጀመሪያ በቃላቱ ፍቺ ላይ በቢጋር ሠንጠረዥ እንመልከተው።
ለ5 ደቂቃያህል እንዲወያዩ ያድርጉዋቸው።
ከዚያም ከላይ በቀረበው መሠረት እየጠየቁ (መ.በመጀመሪያ የቢጋር ሠንጠረዡን ብቻ
ምላሽ እንዲሰጡ ያድርጉ፤ በመጨረሻም ይሣሉላቸው። ከዚያም በቅደምተከተል
ግብረመልስ ይስጡ። ተግባር ሁለትን ደግሞ የሚከናወኑትን ተግባራት እየጠየቁ
የቤትሥራ ይስጧቸው።) ሠንጠረዡን ይሙሉ።)
መ. መንገድ ለማቋረጥ በዘረዘርናቸው ድርጊቶች

፸፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 71


ውስጥ ቅደምተከተሉን የሚያመለክቱት ቃላት የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ምንምን ናቸው?
ዓረፍተነገሮች በድርጊት ቅደም ተከተል
[መተ. በመጀመሪያ፣ ቀጥሎ፣ ከዚያ፤ በመጨረሻ] ማስተካከል
መ. በጣም ጥሩ! ልሥራ
መ. አንቀጽ በሚጻፍበት ጊዜ ዓረፍተነገሮች
የቢጋር ሠንጠረዥ በሀሳብ ቅደምተከተላቸው መሠረት መደራጀት
በመጀመሪያ፡- ከመንገዱ ጠርዝ ላይ አለባቸው። የዓረፍተነገሮች ቅደምተከተል
መቆም ከተዛባ፤ ሀሳብ/መልዕክት በአግባቡ
አይተላልፍም። ስለዚህ ዛሬ የዓረፍተነገሮችን
ቀጥሎ፡- ነጭ ቀለም የተቀባ ማቋረጫ ቅደምተከተል ማስተካከል ትለማመዳላችሁ።
ቦታ መኖሩን ማየት (የሚከተሉትን ዓረፍተነገሮች በሰሌዳው ላይ
ይጻፉላቸው።)
ከዚያ፡- ግራናቀኝ መመልከት ሀ. ወደዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜው እንደደረሰም
በአውቶብስ ወደባህር ዳር ተጓዘ።

በመጨረሻ፡- መንገዱን ማቋረጥ ለ. በለጠ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናውን አለፈ።


ሐ. ስለዚህ ለጉዞ የሚያስፈልገውን ዝግጅት ሁሉ
አስቀድሞ አጠናቀቀ።
ሥሩ
መ. አሁን ከመኝታችሁ ተነስታችሁ ትምህርትቤት መ. ብዙም ሳይቆይ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
እስከምትደርሱ ድረስ የፈፀማችኋቸውን መመደቡን አወቀ።
ድርጊቶች አስቡና ለጥያቄዎቹ መልስ ስጡ። መ. ከተዘረዘሩት ዓረፍተነገሮች መካከል በያዘው
(በመጀመሪያ በቡድን ሆነው አንዳቸው ሀሳብ መሠረት በመጀመሪያ ላይ መምጣት
ለሌላቸው ያደረጉትን እንዲናገሩ ማድረግ ያለበት የትኛው ነው?
ይችላሉ።)
[መ. በ“ለ” ትይዩ ያለው ዓረፍተነገር ነው፤
መ. ዛሬ ጧት መጀመሪያ ምን አደረጋችሁ? ምክንያቱም ፈተናውን ማለፉ ከሌሎች
[ተ. ከመኝታዬ ተነሳሁ።] ድርጊቶች ሁሉ ስለሚቀድም ነው።]
መ. በጣም ጥሩ! ከመኝታችሁ ከተነሳችሁ በኋላ መ. በጣም ጥሩ!
ምን አደረጋችሁ?
እንሥራ
[ተ. መፀዳጃ ቤት ሄድሁ።] መ. አሁን ደግሞ በጋራ እንሥራ፤ በሁለተኛ ደረጃ
መ. እጅግ በጣም ጥሩ! ከመፀዳጃ ቤት መልስ የሚመጣው ዓረፍተነገርስ የትኛው ነው?
ምን አደረጋችሁ? [መተ. ብዙም ሳይቆይ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
[ተ. እጄንና ፊቴን በውኃና በሳሙና ታጠብኩ።] መመደቡን አወቀ።]

(በተመሳሳይ ሁኔታ በቡድን ሆነው እየተጠያየቁ መ. በጣም ጥሩ! ሦስተኛውስ?


ከቤት ተነስተው ትምህርትቤት እስከሚደርሱ [መተ. ስለዚህ ለጉዞ የሚያስፈልገውን ዝግጅት
ያደረጉትን በማስታወሻቸው ላይ እንዲያሰፍሩ ሁሉ አስቀድሞ አጠናቀቀ።]
ያድርጉ።)
መ. ጥሩ ነው! በመጨረሻ ላይ መምጣት ያለበት
መ. አሁን የዘረዘራችኋቸውን ድርጊቶች ዓረፍተነገርስ?
በቅደምተከተል በቢጋር ሠንጠረዥ አስፍሩ።
[መተ. ወደዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜው
(በመማሪያ መጽሐፍ ላይ የቀረበውን የቢጋር
እንደደረሰም በአውቶብስ ወደባህር ዳር
ሠንጠረዥ ይጀምሩላቸው።)
ተጓዘ።]
መ. በጣም ጥሩ!

72 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፸፪


ሥሩ አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን የሀሳብ
ቅደምተከተላቸው ተዛብቶ የቀረቡትን የመንገድ ላይ ጥንቃቄ
ዓረፍተነገሮች አስተካክላችሁ ጻፉ። ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
መ. በመጀመሪያ መምጣት ያለበት ዓረፍተነገር ሥሩ
የትኛው ነው? መ. ተማሪዎች፣ ወደአቀላጥፎ ማንበብ ልምምድ
[ተ. አቡሽ ከውሻው ጋር ይሄድ ነበር።] ከማለፋችን በፊት የምንባቡን ሀሳብ
ለማስታወስ ያህል አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ።
መ. በጣም (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም
ጥሩ!
እንዲሠሩ ያድርጉ።) መ.ተሽከርካሪዎች በሚበዙባቸው አካባቢዎች
ለመጓዝ እግረኞች ምን ምን ጥንቃቄዎችን
(መ. በመጀመሪያ ተማሪዎች በቡድን ሆነው ማድረግ አለባቸው?
ዓረፍተነገሮቹን በሀሳብ ቅደምተከተል
እንዲያደራጁ ያድርጉ። ከዚያም ከየቡድኑ [ተ. በእግረኞች መንገድ መጠቀም ወይም
አንድ አንድ ተማሪዎች እያስነሱ በቡድናቸው የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዞ መጓዝ]
የተሠራውን እንዲያቀርቡ ያድርጉ።) መ. በጣም ጥሩ!

ማንበብ (8 ደቂቃ)
3ኛ ቀን
እንሥራ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መ. ዛሬ በጋራ ንባብ የአቀላጥፎ ማንበብ ልምምድ
እናደርጋለን። የጋራ ንባብ የሚባለው
• አቀላጥፎ ማንበብ በቡድን/በህብረት ሆኖ እኩል ድምፅ እያወጡ
• መናገር የማንበብ ሂደት ነው።
• ሰዋስው መ. አሁን ባለፈው ክፍለጊዜ ያነበባችሁትን፣
“የመንገድ ላይ ጥንቃቄ” በሚል ርዕስ
የቀረበውን ምንባብ፣ 3ኛውን አንቀጽ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ሁላችሁም ከእኔ ጋር እኩል ድምፅ እያሰማችሁ
ሥሩ እናነበዋለን።
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በቃላት [መተ. አንቀጹን በጋራ ድምፅ እያሰሙ 1 ጊዜ
ሥር በተግባር “2” የተሰጠውን የቤትሥራ ያነባሉ።]
እንመለከታለን።
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ከመጀመሪያው በተሻለ
መ. “ነጭ” በሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ ያለውን ድምፃችንን እኩል ለማምጣት ደግመን
ፍቺ የሚያሳይ ዓረፍተነገር መሥርቱ። እናንብብ።
[ተ. የቤቱ ግድግዳ ነጭ ቀለም ተቀባ።] [መተ. ደግመው ያነባሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት የተማሪዎቹን መ. ጥሩ ነው! አሁን ደግሞ ከ2ኛው በተሻለ
መልስ ይቀበሉ። ተማሪዎች ደብተራቸውን ድምፃችን የአንድ ሰው ድምፅ እስኪመስል
ተቀያይረው እንዲተራረሙ ያድርጉ።ከዚያም እኩል እናንብብ።
ከሚያነሱት ጥያቄ ተነስተው ግብረመልስ
[መተ. ለ3ኛ ጊዜ ያነባሉ]
ይስጡ።)
መ. በጣም ጥሩ!
ሥሩ
(መ. በየቡድኑ አንድ ጥሩ አንባቢ እያካተቱ ከ4-6
የሚሆኑ ተማሪዎች ያሉበት ቡድን ያደራጁ።)
መ. አሁን ከእኔ ጋር ያነበብነውን አንቀጽ በቡድን

፸፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 73


ሆናችሁ በአንድነት ድምፅ እያሰማችሁ በማዳመጥ ምንባቡ ውስጥ የኮከብ ምልክት
ታነባላችሁ። አሁን ማንበብ ጀምሩ። ያለበት ቦታ ላይ ሲደርሱ፣ የቀረበውን ጥያቄ
ይጠይቋቸው፤ ምላሻቸውንም ይቀበሉና
[ተ. በቡድን ድምፅ እያሰሙ ያነባሉ።]
ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
(መ.ተማሪዎች ሲያነቡ እኩል ድምፅ
ማውጣታቸውን፣ በተገቢው ቦታ ላይ አርአያነት ያለው ተግባር
ዕረፍት ማድረጋቸውን፣ ቃላትን በትክክል ጠንቃቃ ተማሪዎች በቅድሚያ የመኪና
ማንበባቸውን ይከታተሉ። አንቀጹን አንብበው አደጋ እንዳይደርስባቸው ጥረት ያደርጋሉ።
ሲጨርሱ በድጋሜ ለ2ኛ ጊዜ እንዲያነቡ ቀጥሎ ወላጆቻቸው፣ ዘመዶቻቸው፣ ወይም
ይንገሯቸው። በዚህ ዓይነት ለ3ኛና ለ4ኛ የአካባቢያቸው ነዋሪዎች ከአደጋ እንዲጠበቁ
ጊዜ እንዲያነቡ ያድርጉ።በእያንዳንዱ ይጥራሉ። በተጨማሪም በየትምህርትቤታቸው
ዙር ድምፃቸውን በተቻለ መጠን እኩል የሚማሯቸውን የትራፊክ ደንቦች ለሌሎች ሰዎች
እንዲያመጡ ጥረት እንዲያደርጉ በማስረዳት ግንዛቤ የማስፋት ሥራ ይሠራሉ።
ይንገሯቸው።)
በኢትዮጵያ ካሉት ትምህርትቤቶች መካከል
ለመጀመሪያ ጊዜ ስለመንገድ አጠቃቀም ሥርዓት
ማዳመጥ (15 ደቂቃ)
ያስተዋወቁት የአምቦ ትምህርትቤት ተማሪዎች
አርአያነት ያለው ተግባር ናቸው። በቅድሚያ ተማሪዎቹ ወደትምህርትቤት
ሲሄዱም ሆነ ሲመለሱ የመንገዳቸውን ግራ ጠርዝ
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ) መያዝ እንዳለባቸው ተማመኑ። በመቀጠል ሌሎች
ሥሩ ሰዎችም የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዘው እንዲሄዱ
መ. ዛሬ “አርአያነት ያለው ተግባር” በሚል ርዕስ በተደጋጋሚ ትምህርት ሰጡ። በመጨረሻም
የቀረበ ምንባብ አነብላችኋለሁ። ከዚያ በፊት ሁሉም የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች የመንገዳቸውን
ግን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን የቀረቡትን ግራ ጠርዝ ይዘው መጓዝ አዘወተሩ። አሁን
የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎች በቃላችሁ በአምቦ ከተማ የመንገዳቸውን ግራ ጠርዝ
ትመልሳላችሁ። ይዘው የማይጓዙ ሰዎች እንግዶች መሆናቸው
ይታወቃል። በመሆኑም ትክክለኛውን አቅጣጫ
መ. በትምህርትቤታችሁ የትራፊክ ደህንነት ክበብ
ይዘው እንዲጓዙ ትምህርት ይሰጣቸዋል። ከዚህም
አለ? ካለ ምን ምን ተግባራትን እያከናወነ
የተነሳ ብዙዎቹ የአምቦ እንግዶች ለምን በኛ
ነው?
አካባቢ አልተለመደም?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።
[ተ. በትምህርትቤታቸው ያለ የትራፊክ ደህንነት *** የአምቦ ትምህርትቤት ተማሪዎች
ክበብ ያከናወናቸውን ተግባራት ይናገራሉ።] የመንገድ ሥርዓትን ለማለማመድ
መ. በጣም ጥሩ! የመንገድ ሥርዓቱን የማስተማር በቅደምተከተል ያከናወኗቸው ተግባራት
ኃላፊነት የማን ይመስላችኋል? ምን ምን ናቸው? ***

[ተ. የመንገድ ሥርዓትን የማስተማር ኃላፊነት በአምቦ ትምህርትቤት የተጀመረው መልካም


የማን እንደሆነ የሚያስቡትን ይናገራሉ።] ተግባር በአቅራቢያው ባሉ ትምህርትቤቶችና
ወደሌሎችም አካባቢዎች ተስፋፍቷል። ይህም
መ. በጣም ጥሩ!
በመሆኑ በአካባቢው በመኪና ምክንያት የሚፈጠር
መ. አሁን ምንባቡን አነብላችኋላሁ፤ በትኩረት አደጋ በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል። በአሁኑ ጊዜ ይህ
አዳምጡ። በምታዳምጡበት ጊዜ ዋና ዋና መልካም ተግባር ራቅ ወዳሉ ሌሎች ክልሎችም
ሀሳቦችና እንግዳ የሆኑ ቃላት ካጋጠሟችሁ እየተስፋፋ ይገኛል።
በደብተራችሁ ያዙ። ተማሪዎች፣ እናንተም ይህንን መልካም ተሞክሮ
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ) ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅባችኋል። ትምህርትቤት
ስትሄዱና ስትመለሱ የመንገዳችሁን ግራ ጠርዝ
ሥሩ ይዛችሁ ሂዱ። ሌሎች ሰዎችም የመንገዳቸውን
(መ.ምንባቡን ያንብቡላቸው፤ ተማሪዎች ግራ ጠርዝ ይዘው እንዲሄዱ አግዙ። ይህንን
በአግባቡ እያዳመጡ መሆኑን ለማረጋገጥ ካደረጋችሁ የእናንተንና የሌሎችን ሰዎች

74 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፸፬


ደህንነት ትጠብቃላችሁ። ሰውዬው ወደቀ።
(ከብሔራዊ የመንገድ ደህንነት አስተባባሪ ጽ/ቤት። ሀብቴ ጃኬት ገዛ።
1996። ከ1ኛ-4ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የመንገድ
ደህንነት ግንዛቤ ለማዳበር የተዘጋጀ መማሪያ [መ. በመጀመሪያው ዓረፍተነገር ውስጥ
(ማጣቀሻ አጋዥ መጽሐፍ) ካሪኩለም ጋይድ ገጽ “የመውደቅ አደጋ” የደረሰበት “ሰውዬው”
45 ተሻሽሎ የተወሰደ።) ሲሆን ድርጊቱ ወደሌላ አካል ስላልተሸጋገረ፣
“ወደቀ” የሚለው ቃል ኢሳቢ ግስ ነው።
አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ)
መ. ሁለተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ ግን “የመግዛት”
እንሥራ ድርጊት የፈፀመው “ሀብቴ” እና የመገዛት
መ. ያነበብኩላችሁን ምንባብ በትክክል ድርጊት የተፈፀመበት “ጃኬት” ሁለት አካላት
እንዳዳመጣችሁ ተስፋ አደርጋለሁ። አሁን ስላሉ “ገዛ” የሚለው ቃል “ሳቢ ግስ” ነው።
በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን የቀረቡትን
የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎች በቃላችሁ
እንሥራ
ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ ግን የተወሰኑ መ. ሳቢ ግስ በዓረፍተነገር ደረጃ ሲዋቀር
ጥያቄዎችን አብረን እንሥራ። ድርጊት ፈፃሚንና ድርጊት የሚያርፍበትን
ሁለት ስሞች የሚወስድ የግስ ዓይነት ነው።
መ. ጠንቃቃ ተማሪዎች አደጋን ለመከላከል ምን ይህንን ሁኔታ በሚቀጥለው ዓረፍተነገር ውስጥ
ያደርጋሉ? እንመልከተው።
[መተ. በቅድሚያ የመኪና አደጋ ልጁ ዳቦ በላ።
እንዳይደርሳባቸው ጥረት ያደርጋሉ።]
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ያሉት ስሞች
መ. በጣም ጥሩ። የትኞቹ ናቸው?
ሥሩ [መተ. ልጁና ዳቦ]
መ. አሁን ተራው የናንተ ነው! ቀሪዎቹን
መ. ትክክል! ከሁለቱ ስሞች የመብላትን ድርጊት
ጥያቄዎቹን በቃላችሁ መልሱ።
የፈፀመው ማን ነው?
መ. የአምቦ ተማሪዎች በሁለተኛ ደረጃ ያከናወኑት
[መተ. ልጁ]
ተግባር ምንድን ነው?
መ. በጣም ጥሩ የተበላው ነገርስ ምንድን ነው?
[ተ. ሌሎች ሰዎችም የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዘው
እንዲሄዱ በተደጋጋሚ ትምህርት ሰጡ።] [መተ. ዳቦ]
መ. በጣም ጥሩ። መ. በጣም ጥሩ!
(መ. ሌሎችን ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት እየጠየቁ፣ መ. ስለዚህ እንደ“በላ” ያሉ ግሶች አብሯቸው
ተማሪዎች በቃላቸው መልስ እንዲሰጡ የሚዋቀር ስም የሚፈልጉ በመሆናቸው ሳቢ
ያድርጉ። ከዚያም ከበድ ባሉ ጥያቄዎች ላይ ግስ ይባላሉ።
በማወያየት ግብረመልስ ይስጧቸው።)
መ. አሁን እንደ “በላ” ያሉ ሌሎች ግሶችን
አብረን እንጥራ።
ሰዋስው (10 ደቂቃ)
[መተ. ገዛ፣ ሸጠ፣ ሰበረ፣ ቀደደ ወዘተ.]
ሳቢ ግሶች
መ. ሳቢ ግሶች በተለያየ ቅርጽ ይረባሉ። ለምሳሌ
ልሥራ አሁን “ሰበረ” የሚለውን ሳቢ ግስ በተለያየ
መ. ባለፈው ሳምንት ስለ “ኢሳቢ ግሶች” ቅርፅ እናርባው።
ተምራችኋል፣ ዛሬ ደግሞ ስለ “ሳቢ ግሶች”
እንማራለን።
[መተ. እሱ ሰበረ፣ እኔ ሰበርኩ፣ አንቺ ሰበርሽ፣
እሷ ሰበረች፣ እናንተ ሰበራችሁ…]
መ. የኢሳቢና ሳቢ ግሶችን ልዩነት ቀጥሎ
መ. አንድ ምሳሌ እንጨምር። “ገዛ”ን በተለያየ
በቀረቡት ምሳሌዎች አሳያችኋለሁ።
ቅርጽ እናርባው።

፸፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 75


[መተ. እሱ ገዛ፣ እኔ ገዛሁ፣ አንቺ ገዛሽ፣ እሷ
ገዛች፣…]
ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት በ3ኛው ቀን “ሰዋስው”
በሚለው ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኘውን
ተግባር “1” ሥሩ።
መ. “ወሰደ” የሚለውን ግስ በተለያየ ቅርፅ
አርቡት።
[ተ. እኔ ወሰድኩ፣ እኛ ወሰድን፣ አንተ ወሰድክ፣
አንቺ ወሰድሽ…]
መ. በጣም ጥሩ!
(መ.ተግባሩን ለመሥራት 5 ደቂቃ ይስጧቸው።
ተማሪዎቹ ተግባሮቹን ሲሠሩ በክፍሉ ውስጥ
እየተዘዋወሩ በአግባቡ መሥራታቸውን
ያረጋግጡ፣ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው
ድጋፍ ያድርጉ። በመጨረሻም በመልሶቹ
ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ፣ ተግባር “2”ን
የቤትሥራ ይስጧቸው።)

76 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፸፮


(መ. በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎቹንም ጥያቄዎች
2ኛ ሳምንት የመኪና አደጋ እየጠየቁ ተማሪዎች ምላሽ እንዲሰጡ
ያድርጉ።)

4ኛ ቀን የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


የዕለቱ ትምህርት ይዘት ሥሩ
መ. ዛሬ በምታነቡበት ጊዜ “አዕምሯዊ ምሥል
• ማንበብ
መፍጠር” የሚባለውን የማንባብ ሂደት ራስን
የመከታተያ ስልት ተግባራዊ ታደርጋላችሁ።
አዕምሯዊ ምሥል መፍጠር ማለት በምንባቡ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ውስጥ ያሉ ድርጊቶችን በቅደምተከተል
በሀሳብ መሣል ነው። ስለሆነም በአዕምሯችሁ
ሥሩ ውስጥ ምሥል ለመፍጠር ሞክሩ።
(መ. በሳቢ ግስ ሥር በተግባር “2” የተሰጠውን
የቤትሥራ ተማሪዎችን እየጠየቁ እንዲመልሱ (መ. ሁለተኛውን አንቀጽ አንብበው እንደጨረሱ
ያድርጉ፤ በመጨረሻም ትክክለኛውን መልስ ያስቁሙና፣ ሁለተኛውን አንቀጽ ሲያነቡ
ይንገሯቸው።) በአዕምሯችሁ ውስጥ የተፈጠረውን ምሥል
በመጀመሪያ ለጓደኞቻቸው በመቀጠልም
መ. እሷ ውኃ---------------። ለእርስዎ እንዲናገሩ ያድርጉ። ከዚያም
[ተ. እሷ ውኃ ጠጣች።] ማንበባቸውን ይቀጥሉ።)
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
እንዲመልሱ ያድርጉ። መልሶቹ፡- ቆረጠምክ፤ ልሥራ
ለበስሽ፤ተመለከቱ፤ አዳመጥኩ፤ ዘፈንን
መ. አንብባችሁ ጨረሳችሁ? ጥሩ! ከማንበባችሁ
ናቸው።)
በፊት ርዕሱንና ሥዕሉን ተመልክታችሁ
ታሪኩን ገምታችሁ ነበር። ትክክል ሆኖ
ማንበብ (35) አገኛችሁት? (ተማሪዎች መልሶችን እንዲሰጡ
“...አስቀድሞ መጠንቀቅ” ያበረታቷቸው።)

ቅድመንባብ (10 ደቂቃ) መ. በአነበባችሁት ትረካ ውስጥ ዋናው/ዋ


ገፀባህርይ ማን ነው/ናት?
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት
[መ. ትርንጎ ]
ሥሩ
መ. ጥሩ፣ አሁን ስለትርንጎ እያሰብን መረጃዎችን
መ. ዛሬ “...አስቀድሞ መጠንቀቅ” በሚል ርዕስ
ከምንባቡ እያወጣን የቢጋር ሠንጠረዥ
የቀረበውን ምንባብ በለሆሳስ ታነባላችሁ።
እናዘጋጃለን። በመጀመሪያ እኔ እሠራለሁ።
ከዚያ በፊት ግን ጥቂት የቅድመንባብ
ጥያቄዎችን መልሱ። መ. በምንባቡ ውስጥ የሚገኙትን መረጃዎች፣
የትርንጎ የትምህርትና የአስተዳደግ ሁኔታ፣
መ. “...አስቀድሞ መጠንቀቅ” የሚለው ሐረግ
የማኅበረሰብ አገልግሎት ለመስጠት የገፋፏት
ያልተሟላ ምሳሌያዊ አነጋገር ነው።
ሁኔታዎች፣ ያከናወነቻቸው ተግባራትና
ልታሟሉት ትችላላችሁ?
ያገኘችው/የደረሰችበት ውጤት በማለት
[ተ. “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ] በአራት ዘርፎች መመደብ ይቻላል። አሁን
መ. በጣም ጥሩ! መረጃዎችን የምናደራጅባቸውን አራት
ዘርፎች መነሻ በማድረግ የቢጋር ሠንጠረዥ
መ. “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ” እሠራለሁ። (የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ
ሲባል ምን ማለት ይመስላችኋል? በውስጡ ያሉትን መረጃዎች ሳይሞሉ ርዕሶቹን
[ተ. አንድ ችግር ከመድረሱ በፊት መጠንቀቅ ብቻ በማካተት ሰሌዳው ላይ ይሣሉ።)
ይጠቅማል ማለት ነው።]

፸፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 77


የትምህርትና የማኅበረሰብ ያከናወነቻቸው
የአስተዳደግ ሁኔታ አገልግሎት ተግባራት ውጤት
ለመስጠት የገፋፏት
ሁኔታዎች
1ኛ ደረጃ ትምህርቷን
ከወላጆቿ ጋር ሆና

ተምራለች።
2ኛ ደረጃ ትምህርቷን
ራቅ ያለ ከተማ
ተምራለች።

መ. በምንባቡ ውስጥ ስለ ትርንጎ የትምህርትና


የአስተዳደግ ሁኔታ የተጠቀሱ ሀሳቦች ምን 5ኛ ቀን
ምን ናቸው?
[መ.1ኛ ደረጃ ትምህርቷን ከወላጆቿ ጋር ሆና የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ተምራለች።] (ይህን የትምህርትና የአስተዳደግ
• ቃላት
ሁኔታ በሚለው ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)
• መጻፍ
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። ስለትርንጎ
የትምህርትና የአስተዳደግ ሁኔታ፣ በምንባቡ
ውስጥ ከተጠቁሱት መካከል አንዱን አብረን ቃላት (10 ደቂቃ)
መናገር እንችላለን?
ለቃላትና ለሐረጋት ተመሳሳይ ፍቺ
[መተ. የ2ኛ ደረጃ ትምህርቷን ራቅ ያለ መስጠት
ከተማ ተምራለች።] (ይህንም የትምህርትና
ሥሩ
የአስተዳደግ ሁኔታ በሚለው ክፍል ውስጥ
መ. ዛሬ ከምንባቡ ለወጡ ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ
ይጻፉ።)
ትሰጣለችሁ።
ሥሩ
መ. “ጠንቃቃ” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ
መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
በአንብቦ መረዳት ሥር የሚገኘውን የቢጋር
ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም [ተ. አስተዋይ]
“…አስቀድሞ መጠንቀቅ” በሚል ርዕስ መ. ትክክል!
በቀረበው ምንባብ ውስጥ ስለትርንጎ የተገለጹ
ልዩ ልዩ ክንውኖችን በአራቱ ሳጥኖች ውስጥ (መ. በመጀመሪያ በቡድን እንዲወያዩ ካደረጉ
ሙሉ። (ተግባር “1”ን ለማሠራት ተማሪዎችን በኋላ ከላይ በቀረበው መንገድ እየጠየቁ
ከ4-6 አባላት ባሉት ቡድን ያደራጁ። ከዚያም ለቃላቱ ተመሳሳይ ፍቺ እንዲሰጡ
ሳጥኖችን መጀመሪያ በግል እንዲሞሉ ያድርጉ። ከዚያም ትክክለኛ ተመሳሳያቸው
ያድርጉ። ቀጥሎም የሠሩትን እያስተያዩና ላልተሰጣቸው ቃላት ተመሳሳይ ፍቻቸውን
እየተወያዩ በጋራ እንዲሠሩ ያድርጉ። ተግባር ይንገሯቸው። በመጨረሻም ተግባር “2”ን
“2”ን ደግሞ እየጠየቁ በቃላቸው እንዲመልሱ የቤትሥራ እንዲሠሩ ይንገሯቸው።
ያድርጉ።)

78 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፸፰


መጻፍ (30 ደቂቃ) ሠንጠረዡን ያሟሉት።)

ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) መ. አንቀጽ ለመጻፍ የሚረዳንን ቢጋር


አዘጋጅተናል። አሁን ዓረፍተነገሮችን
በድርጊት ቅደምተከተል ስልት አንቀጽ እያዋቀርን አንቀጹን እንጻፍ። “እሳት ማያያዝ”
መጻፍ የሚለውን ሐረግ መነሻ በማድረግ የአንቀጹን
እንሥራ የመጀመሪያ ዓረፍተነገር እንመሥርት።
መ. ባ ለ ፈ ው ክፍለጊዜ ከቤታችሁ [መተ. ሻይ ለማፍላት በመጀመሪያ እሳት ማያያዝ
ጀምሮ ትምህርትቤት እስክትደርሱ ያስፈልጋል።]
ያከናወናችኋቸውን ተግባራት በድርጊት
መ. ጥሩ! ሁለተኛው ዓረፍተነገርስ ምን ይሆናል?
ቅደምተከተል ማሳያ የቢጋር ሠንጠረዥ
ውስጥ ዘርዝራችኋል። ዛሬ ደግሞ የቢጋር [መተ. ሁለተኛ የታጠበ የሻይ ጀበና ውስጥ
ሠንጠረዡን መሠረት በማድረግ አንቀጽ የሚፈለገውን የውኃ መጠን ጨምሮ እሳት
ትጽፋላችሁ። በመጀመሪያ ግን የቢጋር ላይ መጣድ ነው።]
ሠንጠረዡን መሠረት አድርጋችሁ እንዴት መ. በዚህ መልኩ በቢጋሩ የተዘረዘሩትን ሀሳቦች
አንቀጽ እንደምትጽፉ ለማሳየት አንድ ምሳሌ በቅደምተከተል በማደራጀት አንቀጹን
አብረን እንሥራ። አሟልተው እንዲጽፉ ያድርጉ።

አንደኛ እሳት ማያያዝ ሥሩ


መ. አብረን ስንሠራ የቢጋር ሠንጠረዥን
ሁለተኛ የሻይ ጀበናው ውስጥ ውኃ በመጠቀም እንዴት ቅደምተከተላዊ
ጨምሮ መጣድ ጽሑፍ እንደሚዘጋጅ አይታችኋል። በዚሁ
ሦስተኛ ሻይ ቅጠሉን በፈላው ውኃ መሠረት ባለፈው ሳምንት ያዘጋጃችሁትን
ውስጥ መጨመር የቢጋር ሠንጠረዥ በመጠቀም ሃሣቦችን
አስፋፍታችሁ አንድ አንቀጽ ጻፉ።(ተማሪዎች
አራተኛ ሻዩ ሲፈላ የሻይ ጀበናውን
ማውጣት
አንቀጹን ሲጽፉ እየተዘዋወሩ ይደግፏቸው፤
ያበረቷቷቸው።)
አምስተኛ ስኳሩን በሻይ ብርጭቆ ውስጥ
መጨመር የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ስድስተኛ ሻዩን መቅዳት፣ የዓረፍተነገሮች ቅደምተከተል
በመጨረሻም አማስሎ መጠጣት፣
ማስተካከል
ሥሩ
(መ. በመጀመሪያ የቢጋር ሠንጠረዡን መረጃውን መ. ባለፈው ክፍለጊዜ የሀሳብ ቅደምተከተላቸው
ሳይሞሉ ሰሌዳው ላይ ይሣሉላቸው። የተዛቡ ዓረፍተነገሮችን እንዴት
ከዚያም በሻይ አፈላል ሂደት ከመጀመሪያ እንደምታስተካክሉ ተምራችኋል።
እስከመጨረሻ የሚከናወኑትን ተግባራት ዛሬም ይህንኑ ተግባር መለማመዳችሁን
ተማሪዎችን እየጠየቁ/እያሳተፉ ሠንጠረዡን ትቅጥላላችሁ። በመጀመሪያ ዓረፍተነገሮቹን
ያሟሉ።) በትኩረት አንብቡ። ከዚያም እነዚህን
መ. በሻይ አፈላል ሂደት የመጀመሪያው ተግባር ዓረፍተነገሮች በትክክለኛው ቅደምተከተላቸው
ምንድን ነው? አስተካክላችሁ ጻፉ።

[መተ. እሳት ማያያዝ] [ተ. በግል የዓረፍተነገሮቹን ቅደምተከተል


እያስተካከሉ ይጽፋሉ።]
መ. ጥሩ! ሁለተኛው ተግባርስ ምን ይመስላችኋል?
መ. አሁን ደብተራችሁን ተቀያየሩና ትክክለኛው
[መተ. በሻይ ጀበናው ውስጥ ውኃ ጨምሮ ቅደምተከተል ምን መሆን እንዳለበት
መጣድ] ተወያዩ። (ተማሪዎችን እየጠየቁ ትክክለኛውን
(መ.በዚህ መልኩ ተማሪዎችን እያሳተፉ ቅደምተከተል እንዲናገሩ ካደረጉ በኋላ
ግብረመልስ ይስጡ።)
፸፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 79
መ. በጣም ጥሩ!
6ኛ ቀን ማንበብ (8 ደቂቃ)
እንሥራ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ በጋራ የማንበብ ልምምድ
• አቀላጥፎ ማንበብ አድርጋችሁ ነበር። ዛሬም “…አስቀድሞ
• መናገር መጠንቀቅ” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ
3ኛውን አንቀጽ በመጠቀም የጋራ ንባብ
• ሰዋስው ልምምዳችሁን ትቀጥላላችሁ። በመጀመሪያ
ግን ይህን አንቀጽ አብረን እናንብብ።

የቤትሥራ (5 ደቂቃ) [መተ. ድምፃቸውን እያሰሙ በጋራ ያነባሉ።]

ሥሩ መ.አሁን ከቅድሙ በተሻለ ድምፃችንን እኩል


ለማውጣት እየሞከርን እናንብብ።
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ቃላት ላይ የሰጧቸውን
የቤትሥራ ይመልከቱ፤ ተማሪዎች [መተ. ድምፃቸውን እያሰሙ ለ2ኛ ጊዜ ያነባሉ።]
ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ ያድርጉ፤
በመልሶቹ ላይ እየተነጋገሩ ርስበርስ
ሥሩ
እንዲተራረሙ ያድርጉ። (መ.ከ4-6 ተማሪዎችን ያካተቱ ቡድኖች
ይመሥርቱ። በእያንዳንዱ ቡድን ውስጥ አንድ
መ. በ“ሀ” ሥር ለቀረበው ጥያቄ ተስማሚው ቃል አንድ ጥሩ የሚያነቡ ተማሪዎች መኖራቸውን
የትኛው ነው? ያረጋግጡ። ከዚያም የተመረጠውን አንቀጽ
[ተ. መፍትሔ] ሦስት ወይም አራት ጊዜ በቡድን ድምፃቸውን
እያሰሙ እንዲያነቡ ያድርጉ። ከአንደኛው
መ. በጣም ጥሩ! በ“ለ” ሥር ለቀረበው የትኛውን ወደሁለተኛው፣ ከሁለተኛው ወደሦስተኛው
ቃል መረጣችሁ? ከሦስተኛው ወደአራተኛው ንባብ በተሸጋገሩ
[ተ. አስገነዘበች።] ቍጥር ድምፃቸውን የበለጠ እኩል ለማምጣት
ጥረት እንዲያደርጉ ይንገሯቸው። በየቡድኑ
መ. በጣም (በዚሁ መልክ የሌሎቹን
ጥሩ! እየተዘዋወሩ በትክክል ማንበባቸውን፣
ጥያቄዎች መልስ በመስጠት እንዲተራረሙ ድምፃቸው እኩል መሆኑን፣ ቃል በቃል
ያበረታቱ።) ሳይሆን ሐረግ በሐረግ ማንበባቸውን
ይከታተሉ።)
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
“…አስቀድሞ መጠንቀቅ” መናገር (15 ደቂቃ)
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) የድርጊት ቅደምተከተልን ጠብቆ
መናገር
ሥሩ
“…አስቀድሞ መጠንቀቅ” በሚል ርዕስ በቀረበው እንሥራ
ምንባብ አቀላጥፎ ማንበብን ትለማመዳላችሁ። መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት በድርጊት ቅደምተከተል
ከዚያ በፊት ግን ባለፈው ያነበባችሁትን ስልት የቀረቡ ምንባቦችን አንብበናል፤
ለማስታወስ ያህል የሚከተለውን ጥያቄ አዳምጠናል።
ትመልሳላችሁ። መ. በድርጊት ቅደምተከተል ስልት የቀረቡት
መ. “… አስቀድሞ መጠንቀቅ” በሚል ርዕስ ምንባቦች ይዘት ምን ነበር?
ያነበባችሁትን ምንባብ ዋና ሀሳብ በአጭሩ [መተ. የመጀመሪያው ምንባብ ስለመንገድ
ግለጹ። ደህንነትና አጠቃቀም የሚገልፅ ሲሆን
[ተ. የመኪና አደጋን አስቀድሞ መከላከል ሁለተኛው ምንባብ ደግሞ ስለመንገድ
ይገባል።] ደህንነትና አጠቃቀም ለተማሪዎችና

80 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፹


ለኅብረተሰቡ ስላስተማረች አንዲት ተማሪ መ. ከዚያስ ምን አደረጋችሁ?
የሚተርክ ነበር።]
[መተ. ጓደኛዬን አግኝቼ ወደቤታችን ጉዞ
መ. ጥሩ! ያዳመጥነው ምንባብስ ስለምን የሚገልፅ ጀመርን።] (በተመሳሳይ ሁኔታ እየጠየቁ
ነበር? ተማሪዎቹ እቤታቸው እስከሚደርሱ ያለውን
ይሙሉ።)
[መተ. የአምቦ ተማሪዎች ስለመንገድ አጠቃቀም
ለማኅበረሰቡ ለማስተማር ስላደረጉት መ. ንግግር ስናደርግ ቀጥሎ ባለው መንገድ
አርአያነት ያለው ተግባር የሚገልጽ ነበር።] መጠቀም እንችላለን።
መ. በጣም ጥሩ፣ ያነበብናቸውም ሆነ ያዳመጥናቸው በመጀመሪያ ደብተሮቼንና መጽሐፎቼን ሰብስቤ
ምንባቦች የድርጊት ቅደምተከተልን የተከተሉ በርሳዬ ውስጥ ከተትኩ። ቀጥሎ ጓደኛዬን ፈልጌ
ነበሩ። ዛሬም ይህንኑ የሀሳብ አወቃቀር ዘዴ አገኘሁ። ከዚያ ጉዟችንን ቀጥለን፤ የመኪና
ተጠቅመን ሀሳባችንን በንግግር እንገልፃለን። መንገድ ላይ ደረስን። በመቀጠል የመንገዱን
ለምሳሌ ትናትና ከትምህርትቤት ግራ ጠርዝ ይዘን ተጓዝን። ከሰፈራችንም
ተነስተን ቤታችን እስክንደርስ የተለያዩ ስንደርስ “ዜብራ” መንገድ ፈልገን አቋረጥን።
ድርጊቶችን ፈፅመናል። እነዚህን ድርጊቶች በመጨረሻም ተሰነባብተን ተለያየን።
በቅደምተከተል ለማደራጀት የሚከተለውን
የቢጋር ሠንጠረዥ መጠቀም እንችላለን። ማሳሰቢያ
(የቢጋር ሠንጠረዡን በውስጡ የያዛቸውን
(በገጠር አካባቢ ባሉ ትምህርትቤቶች ተማሪዎች
ዓረፍተነገሮች ሳይጻፉ፣ በሰሌዳው ላይ
ከላይ የቀረቡትን ምላሾች ላይሰጡ ይችላሉ።
ይጻፉላቸው።)
ስለዚህ ለእነዚህ ተማሪዎች በሚከተለው መልኩ
ምሳሌ ሊሰጧቸው ይችላሉ።)
ደብተሮቼንና መጽሐፎቼን ሰበሰብኩና
1
በቦርሳዬ ውስጥ ከተትኩ። ደብተሮቼንና መጽሐፎቼን ሰበሰብኩና
1
በቦርሳዬ ውስጥ ከተትኩ።
ጓደኛዬን አግኝቼ ወደቤታችን ጉዞ
2
ጀመርን። ጓደኛዬን አግኝቼ ወደቤታችን ጉዞ
2
ጀመርን።
3 ከትምህርትቤት እንደወጣን የመኪና
መንገድ ላይ ደረስን። ከትምህርትቤት ወረድ እንዳልን ወንዝ
3
አገኘን።
4 የመንገዱን ግራ ጠርዝ ይዘን ተጓዝን።
4 ወንዙን ለመሻገር ጠበብ ያለ ሥፍራ
ፈለግን።
5 ከሠፈራችን ስንደርስ “ዜብራ” መንገድ
ፈልገን አቋረጥን።
5 በጠባቡ ስፍራ ዘለን ተሻገርን።

6 ተሰነባብተን ወደየቤታችን ገባን።


6 ዳገቱ ላይ፣ ጫካው አጠገብ ደረስን።

(በመቀጠልም እንደሚከተለው ተማሪዎችን


እየጠየቁና እያሳተፉ ሠንጠረዡን ይሙሉ።) 7 ተጠባብቀን በጥንቃቄ ጫካውን
አለፍን።
መ. ትናትና ከትምህርትቤት ወደቤታችሁ ልትሄዱ
ስትሉ በመጀመሪያ ምን አደርጋችሁ? 8 ሠፈራችን ስንደርስ ተሰነባብተን
[መተ. ደብተሮቼንና መጽሐፎቼን ሰበሰብኩና ተለያየን።
ቦርሳዬ ውስጥ ከተትኩ።]

፹፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 81


ሥሩ ቀን፣ በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኘውን
መ. በመጀመሪያ አብረን በሠራነው መሠረት ተግባር ሥሩ።
የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ መ. እኔ አሮጌ መጽሐፍ-----------------።
በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያ በትናትናው
ዕለት ከትምህርትቤት ተነስታችሁ ከቤታችሁ [ተ. እኔ አሮጌ መጽሐፍ ገዛሁ።]
እስክትደርሱ ድረስ የፈፀማችኋቸውን መ. በጣም ጥሩ (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም
ድርጊቶች እያሰባችሁ ባዘጋጃችሁት እንዲሠሩ ያድርጉ።)
ሠንጠረዥ ውስጥ አጠር አጠር እያደረጋችሁ
ዘርዝሩ። (ተግባሩን የሚሠሩበት 5 ደቂቃ
ይስጧቸው።ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ በክፍሉ
መ. ተማሪዎች አሁን 5 አባላት ባሉት ቡድን ውስጥ እየተዘዋወሩ በአግባቡ መሥራታቸውን
ተደራጁ፤ የቡድን መሪም ምረጡ። ከዚያም ያረጋግጡ። የከበዳቸውን ተማሪዎች ይደግፉ፤
ያዘጋጃችሁትን እንደማስታወሻ በመጠቀም በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር
እያብራራችሁ ለቡድን አባላቱ ተናገሩ። እየተወያዩ ግብረመልስ ይስጡ።)
መ. ስትናገሩ በመጀመሪያ፣ ቀጥሎ፣ ከዚያ…
እያላችሁ መናገርን አትርሱ።

(መ. ተማሪዎች ሲናገሩ ሀሳባቸውን በቅደም


ተከተል ማቅረባቸውን፣ ተገቢ የመሸጋገሪያ
ቃላት መከታተላቸውን ይከታተሉ።)

ሰዋስው (5 ደቂቃ)
ሳቢ ግሶች
እንሥራ
መ. ባለፈው ሳምንት ስለሳቢ ግሶች ተምረናል።
ሳቢ ግስ ምን ማለት እንደሆነ አስታውሳችሁ
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
[መተ. በግሱ የተገለፀውን ድርጊት በሌላ አካል
ላይ የሚያሳርፍ/የሚያሻግር ግስ ነው።]
መ. አሁን ለሳቢ ግሶች ምሳሌዎችን ልትሰጡኝ
ትችላላችሁ?
[መተ. በላ፣ ጠጣ፣ ሰጠ፣ ሸጠ…]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ካቀረብናቸው ምሳሌዎች
መካከል “ሸጠን” በተለያየ ቅርፅ በዓረፍተነገር
ውስጥ እንጠቀምበታለን።
መ. እሷ ሁለት ኪሎ ሙዝ---------------።
[መተ. እሷ ሁለት ኪሎ ሙዝ ሸጠች።]
መ. እሱ አምስት መጽሐፎች -------------።
[መተ. እሱ አምስት መጽሐፎች ሸጠ።]
መ. በጣም ጥሩ!
ሥሩ
መ.ተማሪዎች አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው

82 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፹፪


(መ.በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎቹንም ቃላት በቡድን
3ኛ ሳምንት ሆነው እንዲያነቡ ያድርጉ።)
የመጀመሪያ ርዳታና
ማንበብ (35 ደቂቃ)
በድንገተኛ አደጋ ጊዜ
የሚወሰዱ እርምጃዎች በድንገተኛ አደጋ ጊዜ የሚወሰድ
እርምጃ
7ኛ ቀን ቅድመንባብ (5ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘት የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት
• የቃላት ጥናት ሥሩ
መ. አሁን ምንባቡን ከማንበባችሁ በፊት
• ማንበብ በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን የቀረቡትን
የቅድመንባብ ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ።
መ. ድንገተኛ አደጋ ምንድን ነው?
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ)
[ተ. ድንገተኛ አደጋ በተለያዩ ምክንያቶች
መነጠልና ማጣመር በሰውነታችን ክፍል ላይ የሚደርስ ያልተጠበቀ
ሥሩ ጉዳት ነው።]
መ. ዛሬ “በድንገተኛ አደጋ ጊዜ የሚወሰድ መ. በጣም ጥሩ! የምታውቋቸውን ድንገተኛ
እርምጃ” በሚል ርዕስ የቀረበ ምንባብ አደጋዎች ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን ከምንባቡ
የወጡ ቃላትን በመነጣጠልና በማጣመር [ተ. የመኪና አደጋ፣ ከፎቅ ወይም ከገደል ላይ
ማንበብ ትለማመዳላችሁ። የመውደቅ፣ ውኃ ውስጥ የመስመጥ አደጋ፣
ወዘተ.]
መ. በመጀመሪያ በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው
ቀን በቃላት ጥናት ሥር የቀረቡትን የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
ቃላት በመጀመሪያ እየነጣጠላችሁ ከዚያም ልሥራ
እያጣመራችሁ አንብቡ። (መ. ተማሪዎች ማንበብ ከመጀመራቸው በፊት
መ. “ኑሯቸውን” የሚለውን ቃል ነጣጥላችሁ የሚከተለውን ይንገሯቸው።)
አንብቡ። መ. ተማሪዎች በምታነቡበት ጊዜ፣ በምንባቡ ውስጥ
[ተ. ኑሮ-ኣቸው-ን] ያሉ ድርጊቶችን እያሰባችሁ በአዕምሯችሁ
ውስጥ ምሥል ለመፍጠር ሞክሩ። እንዲህ
(መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል አጣምራችሁ ማድረጋችሁ ምንባቡን በተሻለ ሁኔታ
አንብቡልኝ።) ለመረዳት ያስችላል። በምታነቡበት ጊዜ
[ተ. ኑሯቸውን] እንዴት በአዕምሯችሁ ውስጥ ምሥል
እንደምትፈጥሩ አንብቤ ላሳያችሁ። (ከ2ኛው
መ. በጣም ጥሩ!
አንቀጽ የመጀመሪያዎቹን 2 ዓረፍተነገሮች
መ. “ነርቮች” የሚለውን ቃል ፊደሎችን ድምፅዎን እያሰሙ ያንብቡ።)
በመነጣጠል አንብቡ።
መ. “አከርካሪ ከጭንቅላት የታችኛው ክፍል እስከ
[ተ. ነ-ር-ቮ-ች] መቀመጫ የላይኛው ክፍል ያሉትን አጥንቶች
ያካትታል” የሚለውን ዓረፍተነገር ሳነብ
መ. ፊደሎቹን አጣምራችሁ አንብቡ።
በሥነሕይወት ትምህርት ላይ የሚታወቀው
[ተ. “ነርቮች” ] የሰው አጽም ክፍል በአዕምሮዬ መጣ። በዚህም
ከማጅራት ጀምሮ እስከ መቀመጫ(ዳሌ) ድረስ
መ. በጣም ጥሩ
እየተቀጣጠለ የሚወርድ አጥንት በአዕምሮዬ

፹፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 83


ውስጥ በመሣል ለማየት ችያለሁ። እናንተም
እኔ እንዳሳየኋችሁ በአዕምሯችሁ ምሥል 8ኛ ቀን
ለመፍጠር እየሞከራችሁ አንብቡ።
(መ.ሁለተኛውን አንቀጽ አንብበው እንደጨረሱ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
የአከርካሪ አጥንት ስብራት የደረሰበትን • ቃላት
ሰው ለማንሳት ስለሚደረገው ጥንቃቄ
• መጻፍ
በአዕምሯቸው ውስጥ የተፈጠረውን ምሥል
ለጓደኞቻቸው እንዲናገሩ ያድርጉ። ከዚያም
ማንበባቸውን ይቀጥሉ። ሦስተኛውን አንቀጽ
አንብበው እንደጨረሱ የሚከተለውን ጥያቄ ቃላት (10 ደቂቃ)
ይጠይቋቸው።)
ለቃላትና ለሐረጋት ዐውዳዊ ፍቺ
መ. “የዳሌ አጥንት ዋንጫ መሰል አጥንት ነው” መስጠት
የሚለው አገላለፅ ስለዳሌ አጥንት ቅርፅ
በአዕምሯችሁ ውስጥ የፈጠረውን ምሥል ልሥራ
ግለጹ። ምሥሉንም በደብተራችሁ ሥላችሁ መ. ዛሬ “በድንገተኛ አደጋ ጊዜ የሚወሰድ
ለጓደኞቻችሁ አሳዩ። እርምጃ” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ
ለወጡ ቃላት ዐውዳዊ ፍቺ ትሠጣላችሁ።
[ተ. ይናገራሉ፤ ምሥሉንም በደብተራቸው ዐውዳዊ ፍቺ አንድ ቃል በገባበት ዓረፍተነገር
ይሥላሉ።] ወይም ጽሑፍ ውስጥ የሚኖረው ፍቺ ነው።
(መ. ከዚያም ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።) ለምሳሌ አንድ ቃል ወስጄ ላሳያችሁ።
በምንባቡ ውስጥ “ተከትሎ” የሚል ቃል
አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ) አለ። የዚህን ቃል ዐውዳዊ ፍቺ ለማግኘት
ሥሩ በመጀመሪያ ቃሉ የሚገኝበትን ዓረፍተነገር
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በአንብቦ ልፈልግ። ሦስተኛው አንቀጽ ውስጥ “የዳሌ
መረዳት ሥር የቀረቡትን ጥያቄዎች አጥንት ስብራትን ተከትሎ ከፍተኛ መጠን
በምንባቡ መሠረት በቃላችሁ መልሱ። ያለው ደም መፍሰስ ሊከሰት ይችላል” ይላል።
ስለዚህ ስብራትን ተከትሎ ሲል፣ በስብራት
መ. በጥያቄ “ሀ” ሥር ከቀረቡት አማራጮች
ምክንያት ማለቱ ነው። በመሆኑም “ተከትሎ”
መካከል በአንቀጽ 1 ውስጥ በተጠቀሱት
የሚለው ቃል ዐውዳዊ ፍቺ “ምክንያት” ማለት
አደጋዎች ከሚደርሱት ጉዳቶች የማይመደበው
ነው።
የትኛው ነው?
እንሥራ
[ተ. የደም መርጋት ]
መ. አሁን ደግሞ አንድ ምሳሌ አብረን እንሥራ።
መ. ይህን መልስ እንዴት አገኛችሁ? “ሊደርስባቸው” የሚለው ቃል ዐውዳዊ ፍቺ
[ተ. አንቀጽ አንድ ላይ በተጠቀሱት አደጋዎች ምንድን ነው? በመጀመሪያ ቃሉ የሚገኝበት
የሚፈጠሩት ጉዳቶች የደም መፍሰስ፣ አንቀጽ የትኛው ነው?
የአጥንት ስብራትና ውልቃት መሆናቸው [መተ. አንደኛው አንቀጽ]
ተገልጿል።]
መ. ዓረፍተነገሩን አብረን እናንብብ።
መ. በጣም ጥሩ!
[መተ. በመኪና ሲጓዙ ጉዳት ሊደርስባቸው
(መ. የተግባር “1” የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች ይችላል።]
በተመሳሳይ ሁኔታ እየጠየቁ ተማሪዎች
መ. ስለዚህ ሊደርስባቸው የሚለው ቃል ዐውዳዊ
እንዲመልሱ እያደረጉ የአንብቦ መረዳት
ፍቺ ምንድን ነው?
ክሂላቸውን ይገምግሙ። ተግባር “2”ን ደግሞ
በጹሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ።) [መተ. ሊያጋጥማቸው]
መ. ይህን ያልንበት ምክንያት ምንድን ነው?

84 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፹፬


[መተ. ምክንያቱም “ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል” መጻፍ (30 ደቂቃ)
ሲል ጉዳት ሊያጋጥማቸው ይችላል ማለት
ነው።] ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ሥሩ በቅደም ተከተል ስልት አንቀጽ መጻፍ
መ. አሁን በሠራነው መሠረት በ3ኛው ሳምንት፣ ሥሩ
በ8ኛው ቀን የቀረቡትን ቃላት ዐውዳዊ ፍቺ መ. ባለፈው ሳምንት ከቤታችሁ ተነስታችሁ
ግለጹ። (የተማሪዎችን ደብተር ያርሙ፤ ትምህርትቤት እስከምትደርሱ ድረስ
ትክክለኛ መልሶችን በመንገር ተማሪዎች ያከናወናችሁትን በቅደምተከተል በአንድ
ስህተታቸውን እንዲያስተካክሉ ያድርጉ።) አንቀጽ ጽፋችኋል።ዛሬ ደግሞ የጻፋችሁትን
መልሶቹ ፡- ሀ. ደግፎ፣ ለ. መያዝ፣ መከላከል፣ ከጓደኞቻችሁ ጋር በመቀያየር ርስበርሳችሁ
ሐ. ብድግ ማድረግ፣ መ. ማድረስ፣ ሠ . አስተያየት ትሰጣጣላችሁ፤ በተሰጣችሁ
ሲሻገሩ ረ. የደረሰባቸው፣ ናቸው አስተያየት መሠረት ጽሑፋችሁን እንደገና
አስተካክላችሁ ትጽፋላችሁ።
ልሥራ
መ. ጹ ሑ ፉ ን ለመገምገም በሠንጠረዡ
መ. አሁን ደግሞ ተግባር “2”ን እንዴት
የተመለከቱትን መስፈርቶች ተጠቀሙ።
እንደምትሠሩ አሳያችኋለሁ። “ተከትሎ”
የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ ያለው ፍቺ
አይደለም/
“ምክንያት” መሆኑን አይተናል። ይህ ቃል የመገምገሚያ መስፈርቶች አዎ
የለም
ከምንባቡ ውጪ ሌላ ፍቺ አለው። ይህም
“ከኋላ መምጣት” የሚል ነው። አሁን 1 ድርጊቶች በተገቢው
“ተከትሎ” የሚለውን ቃል ተጠቅሜ ከምንባቡ ቅደምተከተል
ውጪ ያለውን ፍቺ የሚያሳይ ዓረፍተነገር ቀርበዋል?
ልመሥርት። የጓደኛዬ ውሻ እኔን ተከትሎ 2. ዓረፍተነገሮቹ የተሟሉ
ከቤቴ ድረስ መጣ። ናቸው?
እንሥራ 3. የፊደል ስህተት አለ?
መ. አሁን አንድ ምሳሌ አብረን እንሥራ። 4. ዓረፍተነገሮቹ የሰዋስው
“ሊደርስባቸው” የሚለው ቃል ከምንባቡ ውጪ ችግር አለባቸው
ያለው ፍቺ ምንድን ነው? መ. ደብተራችሁን ተቀያየሩ። በመሥፈርቶቹ
[መተ. እኩል ሊሆን] መሠረት የ“√” ምልክት አድርጉ።

መ. ጥሩ! አሁን “ሊደርስባቸው” ለሚለው ቃል [ተ. የጓደኛቸውን ጽሑፍ እያነበቡ፣ በሠንጠረዡ


ከምንባቡ ውጪ ያለውን ፍቺ የሚያሳይ ውስጥ በተዘረዘሩት መስፈርቶች ፊት ለፊት
ዓረፍተነገር እንመሥርት። “አዎ” ወይም “አይደለም” የሚለው ላይ የ“√”
ምልክት ያደርጋሉ።]
[መተ. ማሙሽ ዕድሜው ገና 15 ዓመት ቢሆንም
በቁመት አባቱን ሊደርስባቸው ነው።] መ. አሁን በጽሑፉ ውስጥ የሚታዩትን ችግሮች
ለጓደኞቻችሁ ጠቁሟቸው።
መ. በጣም ጥሩ!
[ተ. በጽሑፍ ውስጥ ችግር ያለበትን ዓረፍተነገር፣
ሥሩ ቃል ወይም ፊደል ለጓደኞቻቸው
መ. አብረን በሠራነው መሠረት በ3ኛው ሳምንት፣ ይጠቁማሉ።]
በ8ኛው ቀን በቀረቡት ቃላት ከምንባቡ ውጪ
ያላቸውን ፍቺ የሚያሳዩ ዓረፍተነገሮችን መ. ደብተሩን ለባለቤቱ/ቷ መልሱ።
ሥሩ። (ይህን ተግባር የቤትሥራ ይስጧቸው።) [ተ. ደብተሩን ለባለቤቱ/ቷ ይመልሳሉ።]
መ. አሁን ደግሞ በተሰጣችሁ አሰተያየት መሠረት
ጽሑፋችሁን አስተካክሉ።
[ተ. በተሰጣቸው አስተያየት መሠረት ጽሑፋቸውን

፹፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 85


ያስተካክላሉ።] [ተ. የጻፉትን ዓረፍተነገር ያነባሉ።]
(መ. በመጨረሻ የተማሪዎችን ደብተር ሰብስበው መ. በጣም ጥሩ! ሌሎቻችሁም አንብቡ! (በዚህ
ግምገማ ያድርጉና የተሻሉ ናቸው ያሏቸውን ሁኔታ ቀጥሎ በቀረበው ፍቺ መሠረት
የሁለት ወይም የሦስት ተማሪዎች ጽሑፍ ግብረመልስ ይስጡ።)
በሌላ ክፍለጊዜ መግቢያ ላይ እንዲያቀርቡ
ሀ. ተሸክሞ ሰውዬው ልጁን በደረቱ ይዞ ለ.
ማድረግ ይችላሉ።)
ማገድ (ከብት መጠበቅ)፣ ሐ. የሰውን ስም
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) በሌለበት መጥራት፣ መ. መቀማት/ መንጠቅ፣
ሠ. ሲያቆሙ፣ ሲተዉ ረ. ያለጥንቃቄ
ዓረፍተነገሮችን በድርጊት ቅደምተከተል
ማስተካከል (ቃላቱ ሌላም ፍቺ ሊኖራቸው ይችላል።)
ሥሩ
አቀለጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
መ. ተ ማ ሪ ዎ ች ባለፉት ክፍለጊዜያት
ዓረፍተነገሮችን በሀሳብ ቅደምተከተላቸው በድንገተኛ አደጋ ጊዜ የሚወሰድ
መሠረት እያስተካከሉ መጻፍ እርምጃ
ተለማምዳችኋል። ዛሬም በ3ኛው
ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን ቅደምተከተላቸውን ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
ያልጠበቁ ዓረፍተነገሮች ቀርብውላችኋል። ሥሩ
ዓረፍተነገሮቹን በጥሞና አንብቡ፤ ከዚያም መ. ዛሬ የጋራ ንባብ ልምምድ እናደርጋለን።
ቅደምተከተላቸውን በማስተካከል እንደገና በመጀመሪያ ግን የምታነቡትን ምንባብ ሀሳብ
ጻፉ። (ተማሪዎች ተግባሩን በግል ሠርተው ለማስታወስ ያህል አንድ ጥያቄ በቃላችሁ
እንደጨረሱ ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ ትመልሳላችሁ።
ያድርጉ። ከዚያም በዓረፍተነገሮቹ ቅደም
ተከተል ላይ እየተወያዩ ርስበርሳቸው መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ባነበባችሁት ምንባብ
እንዲተራረሙ ያድርጉ።) ውስጥ የተጠቀሱት፣ ሦስቱ በድንገተኛ አደጋ
ምክንያት የሚፈጠሩ ጉዳቶች ምን ምን
ናቸው?
9ኛ ቀን
[ተ. የአከርካሪ አጥንት ስብራት፣ የዳሌ አጥንት
ስብራትና የአጥንት ውልቃት ናቸው።]
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• አቀላጥፎ ማንበብ መ. በጣም ጥሩ!
• መናገር ማንበብ (8 ደቂቃ)
• ሰዋስው ሥሩ
መ. ባለፈው ሳምንት የጋራ ንባብ ልምምድ
አድርጋችሁ ነበር። ዛሬም መለማመዳችሁን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ትቀጥላላችሁ።
ሥሩ (መ.በየመካከላቸው አንድ ጥሩ አንባቢ በማካተት
(መ. የሰጧቸውን የቤትሥራ ይመልከቱ፤ ከ4-6 ተማሪዎችን የያዙ ቡድኖችን
ተማሪዎች ሠርተው የመጡትን ዓረፍተነገር ይመሥርቱ።)
እንዲያነቡ በማድረግ ግብረመልስ ይስጡ።) መ. አሁን “በድንገተኛ አደጋ ጊዜ የሚወሰድ
መ. “ሲያቋርጡ” ከምንባቡ ውጪ ምን ፍቺ እርምጃ” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ
አለው? አውጡ። ሁለተኛውን አንቀጽ በቡድን
ሆናችሁ ድምፃችሁን እያሰማችሁ በአንድ ላይ
[ተ. ሲያቆሙ፣ ሲተዉ…]
አንብቡ። በምታነቡበት ጊዜ ተጠንቅቃችሁ
መ. የጻፋችሁትን ዓረፍተነገር አንብቡ። ቃላትን በትክክል እየጠራችሁ፣ በሐረጋት
መካከል አጭር ዕረፍት፣ አራት ነጥብ ላይ

86 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 ፹፮


ደግሞ ሙሉ ዕረፍት እያደረጋችሁ አንብቡ። ይናገራሉ።]
በተቻለ መጠን ድምፃችሁን አንዳችሁም
መ. በጣም ጥሩ፣ ሳቢ ግስ ማለት በዓረፍተነገር
ሳትቀድሙ ወይም ሳትዘገዩ እኩል ለማንበብ
ደረጃ ሲዋቀር ድርጊት ፈጻሚና ድርጊት
ሞክሩ።
የሚያርፍበት ሁለት ስሞች የሚያስፈለጉት
[ተ. በቡድን ድምፅ እያሰሙ በጋራ ያነባሉ።] የግስ ዓይነት ነው።
(መ.በየቡድኑ እየተዘዋወሩ በመመልከት መ. አሁን ለሳቢግሶች ምሳሌ እንስጥ
የተማሪዎችን አነባበብ ይከታተሉ፤ ካለፉት
[መተ. ቀደደ፣ አጠበ፣ ለበሰ፣ ሸጠ...]
ክፍለጊዜያት ያሳዩትን መሻሻል ይገምግሙ።
ተማሪዎች ጊዜው የፈቀደውን ያህል ከ3-4 መ. አሁን የሚከተለውን ተግባር አብረን እንሥራ
ጊዜ ደጋግመው ሊያነቡ ይችላሉ።) ልጂቱ ጋዜጣ (ቀደደ)።
(መ.ከላይ የቀረበውን ዓረፍተነገር በሰሌዳ ላይ
መናገር (15 ደቂቃ) ይፃፉ)
መ. በቅንፍ ውስጥ ያለውን ግስ ለዓረፍተነገሩ
ቅደምተከተልን ጠብቆ መናገር
በሚስማማ ቅርፅ እናስተካክለው።
ሥሩ
[መተ. ልጂቱ ጋዜጣ ቀደደች።]
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ “በድንገተኛ አደጋ ጊዜ
የሚወስድ እርምጃ” በሚል ርዕስ የቀረበ መ. በጣም ጥሩ፤ “ቀደደ”፤ የሚለው “ቀደደች”
ምንባብ አንብባችኋል። አሁን ምንባቡን ይሆናል ማለት ነው።
መሠረት ያደረገ ጥያቄ ላይ በጥንድ መ. “እነከድር ልብሳቸውን (አጠበ)።” ይህስ
ትነጋገራላችሁ። እንዴት ይሆናል?
መ. የአከርካሪ አደጋ፣ የዳሌ ስብራትና [መተ. እነከድር ልብሳቸውን አጠቡ።]
የአጥንት ውልቃት የደረሰባቸውን ሰዎች
ለማንሳት መደረግ ያለባቸውን ጥንቃቄዎች መ. በጣም ጥሩ፤ “አጠበ” የሚለው “አጠቡ”
በቅደምተከተል እየተቀባበላችሁ ተናገሩ። ይሆናል ማለት ነው።
ስትናገሩ በመጀመሪያ፣ ከዚያ፣ ቀጥሎ...ወይም ሥሩ
አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ሦስተኛ... የመሳሰሉትን መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን፣
ቃላት መጠቀማችሁን አትርሱ። በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር የሚገኘውን
[ተ. ጥንድ ጥንድ ሆነው በምንባቡ ውስጥ ተግባር ከላይ በሠራነው ምሳሌ መሠረት
በቅደምተከተል የተከናወኑትን ሁኔታዎች በራሳችሁ ሥሩ።
ተራበተራ ይናገራሉ።] (ጊዜ ካለ ሁለት (መ.ተግባራቱን ለመሥራት 6 ደቂቃ ይስጧቸው።
ጥንዶች ወጥተው ለክፍሉ ተማሪዎች ተማሪዎች ተግባራቱን ሲሠሩ በክፍሉ ውስጥ
ሊያቀርቡ ይችላሉ።) እየተዘዋወሩ በአግባቡ መሥራታቸውን
(መ.ተማሪዎች ሲናገሩ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ ይገምግሙ። የከበዳቸውን ተማሪዎች ይለዩና
የተማሪዎቹን ንግግር ይገምግሙ። ይደግፉ። በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ
ድርጊቶቹን በትክክለኛው ቅደምተከተል ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ።)
መግለፃቸውን በትኩረት ይገምግሙ።)
ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ሳቢ ግስ
እንሥራ
መ. ባለፈው ሳምንት ስለሳቢ ግስ ተምረናል፤
አስታውሳችሁ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
[ተ. አንዳንድ ተማሪዎች የሳቢ ግስን ምንነት

፹፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 4 87


ምዕራፍ 5 ጽዳትና ንጽህና
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይናገራሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን ተጠቅመው ይጽፋሉ፤
• በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• ዓረፍተነገሮችን በሀሳብ ቅደምተከተል በማደራጀት ይጽፋሉ።
• የሚነበብላቸውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይገልጻሉ።
• የምንባቦችን ይዘት የሚመለከቱ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገው ይናገራሉ።
• ቅጽሎችን ከስሞች ለይተው ያመለክታሉ።

ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በቃላት ጥናት


1ኛ ሳምንት ጽዳት ሥር የቀረቡትን ቃላት በቡድን ሆናችሁ
በመነጠልና በማጣመር አንብቡ።
(መ.ተማሪዎች ሲያነቡ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ
1ኛ ቀን
በትክክል ማንበባቸውን ይከታተሉ።
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች በመጨረሻም በትክክል ያነበቡ ተማሪዎች
• የቃላት ጥናት ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ ያድርጉ።)
• ማንበብ
ማንበብ (30 ደቂቃ)
...ማቃጠል ወይስ መቅበር ...?
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
መነጠልና ማጣመር የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት
ሥሩ ሥሩ
መ. ተማሪዎች የዛሬ ትምህርታችን ማንበብ ነው። መ. አሁን “…ማቃጠል ወይስ መቅበር…?” በሚል
ከማንበባችሁ በፊት ግን ከምንባቡ የወጡ ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ከማንበባችሁ በፊት
ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን ታነባላችሁ፡ ጥቂት የቅድመንባብ ጥያቄዎችን በቃላችሁ
ትመልሳላችሁ።
መ. “መጠበቂያ” የሚለውን ቃል ነጣጥላችሁ
አንብቡ። መ. በአካባቢያችሁ ቆሻሻ እንዴት እንደሚወገድ
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
[ተ. መጠበቅ- ኢያ]
[ተ. ቆሻሻ መጣያ ቦታ በመጣል፣ በማቃጠል፣
መ.ይህንኑ ቃል አጣምራችሁ አንብቡ።
በመቅበር...]
[ተ. መጠበቂያ] መ. ሁለቱን ሥዕሎች አስተውሉና ስለምን
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በዚሁ ዓይነት በ1ኛው እንደሚገልጹ ተናገሩ።

88 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፹፰


[ተ. በአንደኛው ሥዕል ላይ ደግሞ ሁለት ትክክል ነበር?
ወንዶችና ሁለት ሴቶች ቆሻሻ ሲቀብሩ
[ተ. አዎ/ አይደለም]
ይታያሉ። በሁለተኛው ሥዕል ላይ ሁለት
ወንዶችና ሁለት ሴቶች ቆሻሻ ሲያቃጥሉ መ. ተማሪዎች በጥንድ ሆናችሁ የሞላችሁትን
ይታያሉ።] ሠንጠረዥ አስተያዩ። ርስበርስ በመወያየት
መረጃዎቻችሁን ማጠናከር ትችላላችሁ።
መ. በጣም ጥሩ!
መ. በጣም ጥሩ አሁን፣ በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው
መ. የምንባቡን ርዕስና ሥዕሉን በማገናዘብ
ቀን በአንብቦ መረዳት ሥር የቀረቡትን
ምንባቡ ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ።
ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ።
[ተ. ቆሻሻን ለማስወገድ ከማቃጠልና ከመቅበር
መ. የአካባቢንና የግል ንጽህናን በመጠበቅ ምን
የተሻለው ዘዴ የትኛው እንደሆነ የሚገልጽ
ይገኛል?
ሊሆን ይችላል።] (ተማሪዎች ግምታቸውን
በተለያየ መንገድ ሊገልፁ ይችላሉ።) [ተ. ደስተኛነትና ጤንነት…]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን “...ማቃጠል ወይስ መቅበር መ. ትክክል! ቆሻሻን መቅበር ብዙ ጊዜንና
…?” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ በ10 ጉልበትን የሚጠይቀው በምን ምክንያት ነው?
ደቂቃ ውስጥ አንብቡ። [ተ. ቆሻሻው የሚቀበርበትን ጉድጓድ ለመቆፈር፣
2ለ. የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) ቆሻሻውን ወደጉድጓድ ለመውሰድና
በመጨረሻም አፈር ለማልበስ ጉልበትና ጊዜ
ሥሩ ይጠይቃል።]
(መ. ቀጥሎ የቀረበውን ሠንጠረዥ ሰሌዳው
ላይ ይሣሉላቸውና ተማሪዎች ማንበብ መ. መልሳችሁ ትክክል መሆኑን በምን ማረጋገጥ
ከመጀመራቸው በፊት ሠንጠረዡን ትችላላችሁ?
በደብተራቸው እንዲያዘጋጁ ያድርጉ።) [ተ. በምንባቡ ውስጥ በቀጥታ ባይገለጽም ቆሻሻን
መቅበር ሲባል፣ ለመቅበር የግድ ጉድጓድ
ጥቅም ጉዳት እንደሚያስፈልግ ከልምድ ይታወቃል።]
ቆሻሻን 1. 1. መ. በጣም ጥሩ! (በተመሳሳይ ሁኔታ እየጠየቁ
ማቃጠል 2. 2. ተማሪዎች ምላሽ እንዲሰጡ ያድርጉ። ከዚያም
3. 3. የጋራ ውይይት በማድረግ ግብረመልስ
ይስጡ።)
1. 1.
ቆሻሻን መቅበር 2. 2. ልሥራ
መ. ያነበባችሁት ምንባብ የተዋቀረው በአመዛኙ
3. 3.
በማነፃፀርና በማወዳደር ነው። በውስጡ
መ. በምታነቡበት ጊዜ ከምንባቡ ውስጥ ግን የአከራካሪ ጽሑፍ ባህርይንም ይዟል።
የምታገኟቸውን ቆሻሻን የማቃጠልና የመቅበር ምክንያቱም ጸሐፊው/ዋ ቆሻሻን ከማቃጠል
ጥቅሞችና ጉዳቶች በሠንጠረዡ ውስጥ ጻፉ። ይልቅ መቅበር እንደሚሻል ለማሳመን ሲጥር/
(መ. ተማሪዎች በሚያነቡበት ጊዜ ድምፅ ሳያሰሙ ስትጥር ይታያል/ትታያለች። አከራካሪ ጽሑፍ
የማንበብን መርህ መከተላቸውን፣ የማንበብ የሚባለውም ጽሐፊው/ዋ ሁለት ሀሳቦችን
ሂደት ተግባሩን እየሠሩ ማንበባቸውን በማንሳት፣ አንዱን በመደገፍ ሌላውን
ይከታተሉ።) በመንቀፍ አንባቢዎች የሱን/የሷን አቋም
እንዲደግፉ የሚያግባባ የጽሑፍ ዓይነት ነው።
2ሐ. አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
መ. አንድ ምሳሌ እንመልከት። በምንባቡ አንቀጽ
ሥሩ 3፣ ጽሐፊው/ዋ “ቆሻሻን ከማቃጠል መቅበር
መ. አንብባችሁ ጨረሳችሁ? ጥሩ ነው! ማንበብ ጠቃሚ ነው” የሚለውን ሀሳብ ለማጠናከር
ከመጀመራችሁ በፊት ምንባቡ ስለምን የተለያዩ ሀሳቦች አንስቷል/ታለች።
እንደሚገልጽ ገምታችሁ ነበር። ግምታችሁ
መ. በዚህ አንቀጽ ውስጥ ጸሐፊው/ዋ ሊገልፀው/

፹፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 89


ልትገልጸው የፈለገው/ችው ዋና ሀሳብ ምንድን ረድፍ ከተዘረዘሩት የትኛው ነው?
ነው?
[ተ. አስተላላፊ]
[መ. ቆሻሻን ከማቃጠል መቅበር ይሻላል የሚል
መ. ጥሩ ነው! (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም እንዲሠሩ
ነው።]
ያድርጉ። ከዚያም የተማሪዎችን ምላሽ
መ. ይህን ሀሳብ ለማጠናከር ያቀረበው/ችው ተቀብለው በከበዳቸው ጥያቄ ላይ ማብራሪያ
ማስረጃ ምንድን ነው? በመስጠት ግብረመልስ ይስጡ።)
[መ. ቆሻሻ ከተቀበረ አየር አይበክልም፤ ሌላ መ. ከተግባር ሁለት “በጋራ” ለሚለው ቃል
ቆሻሻ አይፈጥርም፤ ለማዳበሪያነት ያገለግላል ተቃራኒው ከ “ለ” ረድፍ የትኛው ነው?
የሚል ነው።]
[ተ. በግል]
መ. ሀሳቡና የቀረበው ማስረጃ ትክክል ነው?
መ. በጣም ጥሩ! በተመሳሳይ ሁኔታ የተግባር
[መ. አዎ፣ ምክንያቱም የተጠቀሱትን ሀሳቦች “2”ን ጥያቄዎች እቤታችሁ ሠርታችሁ
በልምድ፣ ባለሙያዎችን በማነጋገር ወይም እንድትመጡ።
መጻሕፍትን በማንበብ ማረጋገጥ ይቻላል።]
ሥሩ መጻፍ (30 ደቂቃ)
መ. ተማሪዎች በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ቀን በአንብቦ መረዳት ተግባር “2” ሥር
የቀረበውን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ።
በማነፃፀርና በማወዳደር ስልት የቢጋር
ከዚያም የጸሐፊውን/ዋን የመከራከሪያ ሀሳብና ሠንጠረዥ ማዘጋጀት
ማስረጃዎች አስፍሩ። ቀጥሎ የመከራከሪያ ልሥራ
ሀሳቡ ትክክል ወይም ስህተት መሆኑን መ. አሁን በማነፃፀርና በማወዳደር ስልት አንቀጽ
ጠቁሙ። ትጽፋላችሁ። ማወዳደር በሁለት ነገሮች
[ተ. የመከራከሪያ ሀሳቦቸን እየመዘገቡና መካከል ያለውን ተመሳሳይነት ማሳየት ነው።
ትክክለኛነቱን እየመዘኑ ይከታተላሉ።] ማነፃፀር ደግሞ በነገሮች መካከል ያለውን
ልዩነት ተንትኖ በማቅረብ ላይ ያተኩራል።
(መ. በመመሪያው መሠረት እየተገበሩ የማወዳደሪያና የማነፃፀ ሪያ የቢ ጋር
መሆናቸውን እየተዘዋወሩ ይከታተሉ።) ሠንጠረዥን መጠቀም በነገሮች መካከል
ያለውን ተመሳሳይነትና ልዩነት ለማሳየት
2ኛ ቀን ይረዳል።
መ. ይህን ሀሳብ ካነበባችሁት ምንባብ በመነሳት
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች እንመልከት። በምንባቡ ውስጥ ያሉት ሁለት
• ቃላት ሀሳቦች ምን ምን ናቸው?
• መጻፍ [መ. ቆሻሻን ማቃጠልና ቆሻሻን መቅበር]
መ. ጥሩ! ሁለቱን ሀሳቦች በሁለት ክቦች
እንወክላቸው።
ቃላት (10 ደቂቃ) (የሚከተሉትን ክቦች ሰሌዳው ላይ ይሣሉላቸው።)
ለቃላት ተመሳሳይና ተቃራኒ ፍቺ
መስጠት
ሥሩ
መ. ዛሬ ቃላትን በምንባቡ መሠረት በማመሳሰልና
በማቃረን ታዛምዳላችሁ።
መ. “አምጪ” ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ በ“ለ”

90 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፺


ሀ ለ [መተ. ክብ “ሀ” ውስጥ ብዙ ጊዜና ጉልበት
አይጠይቅም፤ ክብ “ለ” ውስጥ ደግሞ ብዙ
ጊዜና ጉልበት ይፈልጋል።]
መ፡ በጣም ጥሩ! ሌላ ልዩነትስ አለ ወይ?
ቆሻሻን ቆሻሻን
ማቃጠል ቆሻሻን መቅበር [መተ. ቆሻሻን በማቃጠል ሌላ ቆሻሻ ይፈጠራል፤
ማስወገድ
• አየር • አየር ቆሻሻን በመቅበር ግን ሌላ ቆሻሻ
ይበክላል። • አይበክልም። አይፈጠርም።]
• • • መ. ትክክል! ስለዚህ በክቦቹ ውስጥ ምን ብለን
እንጻፍ?
[መተ. በክብ “ሀ” ውስጥ ሌላ ቆሻሻ ይፈጠራል፤
ክብ “ለ” ውስጥ ደግሞ ሌላ ቆሻሻ አይፈጠርም]
መ. በመጀመሪያ “ቆሻሻን ማቃጠል” ና “ቆሻሻ መ. በጣም ጥሩ!
መቅበርን” የሚያመሳስላቸው ነገር ምንድን ሥሩ
ነው?
መ. አሁን በደብተራችሁ በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው
[መ. በሁለቱም መንገዶች ቆሻሻን ማስወገድ ቀን፣ በድርሰት መጻፍ ሥር የቀረበውን
ይቻላል።] የቢጋር ሠንጠረዥ አስፍሩ። ከዚያም
የእንስሳትንና የዕፅዋትን ተመሳሳይነት ሁለቱ
መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ ተመሳሳይነቱን ከክቦቹ
ክቦች በሚጋሩት መካከለኛው ክፍል ውስጥ
በየትኛው ክፍል ልጻፈው?
ዘርዝሩ። የእንስሳትና ዕፅዋትን ልዩነት ደግሞ
[መ. ሁለቱ ክቦች በሚጋሩት በመካከለኛው ቦታ] ሁለቱ ክቦች ከማይጋሩት ክፍል ውስጥ
(ከሁለቱ ክቦች መካከል ይጻፉት።) ዘርዝሩ።
መ. ጥሩ! ለምን? እንሰሳት ዕፅዋት

[መ. ምክንያቱም በሁለቱም መንገዶች ቆሻሻን


ማስወገድ መቻሉ የጋራ ባህርያቸው ስለሆነ።]
መ. ማቃጠልንና መቅበርን ከሚያለያዩዋቸው
ባህርያት የመጀመሪያው ምንድን ነው? •ከቦታ ቦታ ይንቀሳቀሳሉ

•ህይወት አላቸው

•ከቦታ ቦታ አይንቀሳቀሱም

• • •

[መ. ቆሻሻን ማቃጠል አየርን ሲበክል፣ መቅበር


• • •
• • •
• •
ግን አየርን አይበክልም።]

መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ “አየርን ይበክላል”


የሚለውን በክብ “ሀ” ውስጥ እጽፋለሁ፤ በክብ
“ለ” ውስጥ ደግሞ “አየር አይበክልም” ብዬ
እጽፋለሁ።
እንሥራ የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
መ. አሁን ደግሞ ተጨማሪ ልዩነቶችን አብረን የቃል ጽሕፈት
እንለይ።
እንሥራ
መ. እኔ ከጠቀስኳቸው ሌላ ልዩነት አለ? መ. በመጀመሪያ የማነብላችሁን ቃል በሰሌዳው
ላይ እንጽፋለን።
[መተ. ቆሻሻን ማቃጠል ብዙ ጊዜና ጉልበት
አይጠይቅም፣ ቆሻሻን መቅበር ግን ብዙ መ. ተማሪዎች “የሚያጸዷቸው” የሚለውን ቃል
ጊዜና ጉልበት ይፈልጋል።] በሰሌዳው ላይ እንጻፍ።
መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ በክቦቹ ውስጥ ምን ብየ (መ. ተማሪዎች በሰሌዳው ላይ እንዲጽፉ
ልጻፍ? ያድርጉ። በትክክል ከጻፉ ያድንቋቸው

፺፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 91


ከተሳሳቱ አስተካክለው በመጻፍ ያሳዩዋቸው።) በተግባር “2” በ“ሀ” ረድፍ ለቀረቡት ከ“ለ”
ረድፍ ካሉት ተቃራኒያቸውን በመምረጥ
[መተ. “የሚያጸዷቸው” የሚለውን ቃል በሰሌዳ
እንድታዛምዱ የተሠጣችሁን የቤትሥራ
ላይ ይጽፋሉ።]
እንመልከት። በ“ጋራ” ለሚለው ቃል በ“ለ”
ሥሩ ረድፍ ከተዘረዘሩት ተቃራኒው የትኛው ነው?
መ. አሁን እኔ ቃላቱን አነብላችኋለሁ። [ተ. በግል]
እናንተ ደግሞ ቃላቱን በደብተራችሁ በግል
ትጽፋላችሁ። መ. መልሱን የያዘው ፊደል የትኛው ነው?

መ. “ትኋን” የሚለውን ቃል ጻፉ። (አንድ [ተ. ሠ]


ጊዜ ያንብቡላቸው በትክክል ካልጻፉት መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ መልኩ እየጠየቁ
ይድገሙላቸው።) መልሳቸውን ይቀበሉ። ደብተራቸውን
[ተ. ቃሉን በደብተራቸው ይጽፋሉ።] ተቀያይረው እንዲተራረሙ ያድርጉ።
መልሱ፡- 1. ረ፣ 2. ሐ፣ 3. ለ፣ 4. መ፣ 5.
(መ. በተመሳሳይ ሁኔታ የሚከተሉትን ቃላትና ሠ፣ 6. ሀ መሆኑን ይንገሯቸው።)
ሐረጋት ሁለት ሁለት ጊዜ እያነበቡላቸው
በደብተራቸው እንዲጽፉ ያድርጉ።)
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
ሀ. ብልኋ ረ. መፋሰሻ
...ማቃጠል ወይስ መቅበር ...?
ለ. ልዩነት ሰ. ጉድጓድ
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
ሐ. ተላላፊ ሸ. የሚተላለፉ
ሥሩ
መ. አረንቋ ቀ. ንጽህናቸውን
መ. ዛሬ ድምፅ እያሰማችሁ በማንበብ
ሠ. ትኋን በ. ተግባሮቻቸውን ትለማመዳላችሁ። በመጀመሪያ ግን ባለፈው
ክፍለጊዜ ያነበባችሁትን በማስታወስ
(መ. ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ ያድርጉ፤
የሚከተለውን ጥያቄ መልሱ።
የጓደኞቻቸውን ስህተት ለይተው ግብረመልስ
እንዲሰጡ ያድርጉ፤ በመጨረሻም መ. እንደምንባቡ ሀሳብ ከማቃጠልና ከመቅበር
ትክክለኛውን አጻጻፍ ሰሌዳው ላይ በመጻፍ የትኛው ይሻላል?
ርስበርስ እንዲተራረሙ ያድርጉ። ሲገመግሙ [ተ. መቅበር]
እንደ ኋ፣ ዩ፣ ቋ፣ ጓ፣ ፊ፣ ፋ፣ ፉ፣ ጽ፣ ያሉትን
ፊደሎች በትክክል መጻፋቸውን ያረጋግጡ።) መ. ለምን?
[ተ. ምክንያቱም ቆሻሻን መቅበር አየር
3ኛ ቀን አይበክልም፣ ሌላ ቆሻሻም አይፈጥርም።]
መ. በጣም ጥሩ!
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• አቀላጥፎ ማንበብ
ማንበብ (8 ደቂቃ)

• ማዳመጥ
ልሥራ
መ. ዛሬ “…ማቃጠል ወይስ መቅበር …?” በሚል
• ሰዋስው ርዕስ ከቀረበው ምንባብ የመጀመሪያዎቹን
ሦስት አንቀጾች ድምፅ በማሰማት ተራበተራ
ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን እኔ አነባለሁ፤
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ተከታተሉኝ።
ሥሩ [መ. ያነባሉ።]
(መ. ተማሪዎች የተሰጣቸውን የቤትሥራ እንሥራ
መሥራታቸውን ያረጋግጡ።)
መ. አሁን ደግሞ እነዚህኑ አንቀጾች አብረን
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በቃላት ሥር፣

92 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፺፪


እናንብብ። (ተማሪዎች ከርስዎ ጋር ያድርጉ።)
ድምፃቸውን በማሰማት እንዲያነቡ ያድርጉ።)
[ተ. የግል ንፅህና ልብስ ማጠብ፣ እጅ፣ እግር፣
[መተ. ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር አብረው ፀጉር፣ አጠቃላይ ሰውነትን መታጠብ፣ ፀጉርን
ያነባሉ።] መላጫት ወይም መስተካከል ሲሆን የአካባቢ
ንጽህና ደግሞ ሰፈርን፣ መንገድን፣ የውኃ
መ. በጣም ጥሩ ነው።
መውረጃን ማፅዳት ነው።]
ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ
መ. ተማሪዎች፣ አሁን ጥንድ ጥንድ በመሆን
ተራበተራ ሦስቱን አንቀጾች ድምፅ በማሰማት (ከተማሪዎች ምላሽ ከተቀበሉ በኋላ ማንበብዎን
አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ አንዳችሁ ይቀጥሉ።)
የጓደኛችሁን አነባበብ እየተከታተላችሁ
መዝግቡ። በወረቀት በትክክል ያልተነበቡ
የግልንና የአካባቢን ንጽህና
ቃላትን፣ በንባቡ ጊዜ በትክክል ያልተነበቡ መጠበቅ
ሥርዓተነጥቦችን ብዛት መዝግቡ። የግልና የአካባቢ ንጽህና ቆሻሻን
(መ.ተማሪዎች ሲያነቡ በትክክል ማንበባቸውን የምናስወግድባቸው ስልቶች ናቸው። ሁለቱም
ይከታተሉ። አንብበው ሲጨርሱ ተማሪዎች በሽታን ለመከላከል ያስችላሉ። የግልና የአካባቢ
የመዘገቡትን/የያዙትን ማስታወሻ መረጃ ንጽህና ከተጠበቀ በሽታ በቀላሉ አይዛመትም።
ይመልከቱ። ጊዜ ካለ ጥሩ ያነበቡ ተማሪዎች ንጽህናቸውን የጠበቁ ሰዎች ጤነኛና ደስተኛ
ወጥተው ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ ሆነው የዕለት ተግባሮቻቸውን ያከናውናሉ።
ያድርጉ።) የግል ንጽህናን መጠበቅ የአካባቢን ንጽህና
ከመጠበቅ ይለያል። የግል ንጽህና የሚባለው
ማዳመጥ (15 ደቂቃ) ሰዎች በተናጠል የሚያከናውኑት ሥራ ነው።
የአካባቢ ንጽህና ደግሞ ሰዎች በጋራ የሚሠሩትን
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
የጽዳት ሥራ ይመለክታል። የሁለቱን ልዩነት
ሥሩ የበለጠ ለመረዳትም በተናጠል እንመልከታቸው።
መ. “የግልንና የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ” *** የግል ንጽህና ምን ምን ነገሮችን
የሚለውን ምንባብ ከማዳመጣችሁ በፊት ያካትታል? የአካባቢ ንጽህናስ?***
ጥቂት የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎችን
በቃላችሁ መልሱ። የግል ንጽህና ሰዎች ንጽህናቸውን ለመጠበቅ
የሚያከናውኗቸውን ልዩ ልዩ ተግባራትን
መ. ንጽህና ማለት ምን ይመስላችኋል? ይመለከታል። ሰዎች የቆሸሹ ልብሶቻቸውን
[ተ. ንጽህና ሰዎች በበሽታ እንዳይጠቁ በየጊዜው ያጥባሉ፤ እጆቻቸውን፣ እግሮቻቸውን፣
አካባቢያቸውን፣ ሰውነታቸውንና ፀጉራቸውንና የሰውነት ክፍሎቻቸውን ያፀዳሉ።
የሚገለገሉባቸውን ልዩ ልዩ ቁሶች ፀጉራቸው ሲያድግ ይስተካከላሉ፤ ወይም ይላጫሉ።
የሚያጸዱበት ሂደት ነው።] (ተማሪዎች የእግርና የእጅ ጥፍሮቻቸውን ይቆርጣሉ።
በተለያየ አገላለጽ መልስ ሊሠጡ ይችላሉ።) በሌላ በኩል ደግሞ በመኖሪያቤት ውስጥ በጋራ
የሚገለገሉባቸውን ቁሳቁሶች ያፀዳሉ። የምግብ
(መ.በተመሳሳይ ሁኔታ የ”ለ”ና “ሐ”ን ጥያቄዎች
ማብሰያ፣ ማቅረቢያና መመገቢያ ዕቃዎችን
በመጠየቅ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ያጥባሉ። መኖሪያቤታቸውንና ግቢያቸውን
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ) በመጥረግ ደረቅ ቆሻሻውን ጉድጓድ ቆፍረው
ይቀብራሉ። ፍሳሽ ቆሻሻዎችንም የፍሳሽ ቆሻሻ
ሥሩ ማስረጊያ በማዘጋጀት ያስወግዳሉ። የመጸዳጃ
(መ. “የግልንና የአካባቢን ንጽህና መጠበቅ” ቤታቸውን ንጽህና ይጠብቃሉ።
በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ለተማሪዎች
ያንብቡላቸው። የኮከብ ምልክት ካለበት ቦታ የአካባቢ ንጽህና ደግሞ በመኖሪያና
ላይ ሲደርሱ የማዳመጥ ሂደት ጥያቄውን በመሥሪያቤት አካባቢዎች የሚከናወን የጋራ
ይጠይቋቸው። ተማሪዎችን መልስ እንዲሠጡ ጽዳት ነው። ሰዎች በብዛት በሚንቀሳቀሱባቸው

፺፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 93


አካባቢዎች የሚፈጠሩ ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻዎችን መጻሕፍትን መጠንና ቀለም ወዘተ.
ለማስወገድ የአካባቢ ንጽህና ተግባራዊ ይደረጋል። በመጥቀስ እንደመግቢያ መጠቀም ይችላሉ።
ከየመኖሪያቤቱ እየወጡ በግዴለሽነት በየቦታው ምሳሌ፣ ቀይ ሸሚዝ፣ ሰሌዳ፣ ትልቅ መጽሐፍ፣
የሚጣሉና የሚደፉ ቆሻሻዎች ይወገዱበታል ። አረንጓዴ ቀሚስ…)
ደረቅ ቆሻሻዎች ተሰብስበው በተቆፈረ ጉድጓድ
መ. “ጥቁር ሰሌዳ” በሚለው ሐረግ ውስጥ ቅጽሉ
ውስጥ ይቀበራሉ። ፍሳሽ ቆሻሻዎች መፋሰሻ
የትኛው ነው?
እየተዘጋጀላቸው ይወገዳሉ።
[መ. ጥቁር]
በአጠቃላይ ሰዎች የግልና የአካባቢ ንጽህናቸውን
በመጠበቅ ራሳቸውን ከልዩ ልዩ ተላላፊ በሽታዎች መ. በጣም ጥሩ! “ጥቁር” የሚለው ቃል የገለፀው
ይከላከላሉ። በቀላሉ በሽታ እንዳይዛመት ምንን ነው?
ማድረግ ይችላሉ። ይህም በተሰማሩበት ቦታ
[መ. ሰሌዳውን]
ሁሉ ውጤታማ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።
አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ) መ. “ጥቁር” የሚለው ቃል የገለፀው የሰሌዳውን
ምንድን ነው?
ሥሩ
[መ. የሰሌዳውን ቀለም]
መ. ምንባቡን በጥሞና አዳምጣችኋል? በጣም
ጥሩ! አሁን የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎችን መ. በጣም ጥሩ! “ትልቅ መጽሐፍ” በሚለው
ትመልሳላችሁ። ሐረግ ውስጥ ቅጽሉ የትኛው ነው?
መ. ንጽህናን የመጠበቂያ መንገዶች የተባሉት [መ. ትልቅ]
ምንና ምን ናቸው?
መ. ጥሩ! “ትልቅ” የሚለው ቃል የገለፀው ምንን
[ተ. የግልና የአካባቢ ንጽህና] ነው?
መ. በጣም ጥሩ! (ሌሎችንም ጥያቄዎች [መ. መጽሐፉን]
በተመሳሳይ ሁኔታ የተለያዩ ተማሪዎች
መ. በጣም ጥሩ! “ትልቅ” የሚለው ቃል የገለፀው
እንዲመልሱ ያድርጉ። ከተግባር “2” ደግሞ
የመጽሐፉን ምንድን ነው?
አንድ ምሳሌ በመሥራት ሌሎቹን የቤትሥራ
ይስጧቸው።) [መ. የመጽሐፉን መጠን ]
መ. “በግቢያችን ውስጥ የፈሳሽ ቆሻሻ____ እንሥራ
ጉድጓድ አዘጋጀን።” መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። “ብልጥ ልጅ”
የሚለውን ዓረፍተነገር የሚያሟላው ቃል የትኛው በሚለው ሐረግ ውስጥ ቅጽሉ የትኛው ነው?
ነው? [መተ. ብልጥ]
[ተ. ማስረጊያ] መ. በጣም ጥሩ “ብልጥ” የሚለው ቃል የገለፀው
መ. በጣም ጥሩ! በዚሁ ዓይነት ሌሎችንም ምንን ነው?
የተጓደሉ ዓረፍተነገሮች ከተዘረዘሩት ቃላት [መተ. ልጁን]
መካከል የሚስማማቸውን ቃል እየመረጣችሁ
መ. በጣም ጥሩ “ብልጥ” የሚለው ቃል የሚገልፀው
አሟሉ።
የልጁን ምንድን ነው?

ሰዋስው (10 ደቂቃ) [መተ. የልጁን ባህርይ ]


መ. በጣም ጥሩ “ክብ ጠረጴዛ” በሚለው ቃል
ቅጽል ውስጥ ቅጽሉ የትኛው ነው?
ልሥራ [መተ. ክብ]
መ. ዛሬ ስለቅጽል እንማራለን።
መ. “ክብ” የሚለው ቅጽል የገለፀው ምንን ነው?
(መ. የሰሌዳውን ቀለም፣ ልጆቹ የለበሱትን
[መተ. ጠረጴዛውን]
ልብስ ቀለም፣ የተለያዩ የትምህርት ዓይነት

94 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፺፬


መ. መልካም “ክብ” የሚለው ቅጽል የገለፀው
የጠረጴዛውን ምንድን ነው?
[መተ. የጠረጴዛውን ቅርፅ]
መ. “ሱዳናዊ ገበሬ” በሚለው ሐረግ ውስጥ ቅጽሉ
የትኛው ነው?
[መተ. ሱዳናዊ]
መ. መልካም! ሱዳናዊ የሚለው ቅጽል የገለፀው
ምንን ነው?
[መተ. ገበሬውን]
መ. “ሱዳናዊ” የሚለው ቅጽል የገለፀው የገበሬውን
ምንድን ነው?
[መተ. ወገን፣ ዜግነት]
መ. በጣም ጥሩ።
መ. እስካሁን ባየናቸው ሐረጎች ውስጥ ያሉት
ሰሌዳ፣ መጽሐፍ፣ ልጅ፣ ጠረጴዛ፣ ገበሬ
የሚሉት ቃላት ስሞች ናቸው። ከስሞቹ በፊት
የመጡት ጥቁር፣ ትልቅ፣ ብልጥ፣ ክብ፣ ሱዳናዊ
የሚሉት ቃላት ደግሞ ቅጽሎች ናቸው።
ሥሩ
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ በሰዋስው
ይዘት ሥር የሚገኘውን ተግባር በምሳሌው
መሠረት ሥሩ።
መ. “አረንጓዴ ቀሚስ ገዛሁ።” በሚለው
ዓረፍተነገር ውስጥ ቅጽሉ የትኛው ነው?
[ተ. አረንጓዴ]
መ. በጣም ጥሩ! የገለፀው ምንን ነው?
[ተ. ቀሚሱን]
መ. በጣም ጥሩ! ቅጽሉ የገለፀው የቀሚሱን
ምንድን ነው?
[ተ. የቀሚሱን ቀለም ]
መ. ጎበዞች! ስለዚህ “አረንጓዴ” የሚለውን ቃል
“ቅጽል” በሚለው የሠንጠረዥ ክፍል ጻፉና
“ቀለም/መልክ” ከሚለው ሥር የ“√” ምልክት
አድርጉ። (ተግባሩን እንዲሠሩ 5 ደቂቃ
ይስጧቸው። ተማሪዎቹ ተግባሩን ሲሠሩ
በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ በአግባቡ
መሥራታቸውን ያረጋግጡ፤ የከበዳቸውን
ተማሪዎች ይደግፉ። በመጨረሻም በመልሶቹ
ላይ ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ።)

፺፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 95


መ. በጣም ጥሩ!
2ኛ ሳምንት የግል ንፅህና
(መ. ተማሪዎች በቡድን እንዲወያዩ ካደረጉ
በኋላ፣ ሌሎቹንም የቅድመንባብ ጥያቄዎች
4ኛ ቀን እንዲመልሱ ያድርጉ።)

የዕለቱ ትምህርት ይዘት የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)


• ማንበብ ሥሩ
መ. “ምስጋና ለጓደኛዬ” በሚል ርዕስ የቀረበውን
ምንባብ ድምፅ ሳታሰሙ አንብቡ።
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ለመረዳታችሁ እርግጠኛ ካልሆናችሁ
ሥሩ ደግማችሁ አንብቡ።
(መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን የሰጧቸውን (መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጇቸው። ከዚያም
የአዳምጦ መረዳት ተግባር “2” የቤትሥራ እያንዳንዳቸውን “1” ወይም “2” ቍጥር
ተማሪዎች ደብተራቸውን ተለዋውጠው በማለት ይሠይሟቸው።)
ርስበርስ እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
መ. አሁን በግል ድምፅ ሳታሰሙ የመጀመሪያውን
መ. “በግቢያችን ውስጥ የፈሳሽ ቆሻሻ----- ጉድጓድ አንቀጽ አንብቡ። (1ኛውን አንቀጽ አንብበው
አዘጋጀን” በሚለው ዓረፍተነገር ለባዶው ቦታ ሲጨርሱ ያስቁሙና መጽሐፋቸውን
የሚስማማው ቃል የትኛው ነው? እንዲያጥፉ ያድርጉ።)
[ተ. ማስረጊያ] መ. ቍጥር አንዶች ካነበባችሁት አንቀጽ
የምታስታውሱትን ለቍጥር ሁለቶች ንገሩ።
መ. በጣም ጥሩ! “ማስረጊያ” ብለው ለጻፉ
ተማሪዎች የራይት ምልክት አድርጉ። [ተ. ቍጥር “1” ተማሪዎች ያስታወሱትን
(በዚህ መሠረት እስከ “ረ” ያሉትን ጥያቄዎች ይናገራሉ።]
እየመለሱ ያርሙ።) መ. አሁን ደግሞ ቍጥር ሁለቶች፣ ቍጥር አንዶች
የዘነጓቸውን ዝርዝር ሀሳቦች ጨምሩ/ተናገሩ።
(መልሶቹ ፡- ሀ. ማስረጊያ፣ ለ. ማስወገድ፣ ሐ.
መዛመት፣ መ. መላጨት፣ ሠ. መቁረጥ፣ ረ. [ተ. ቊ.2 ተማሪዎች ተጨማሪ ሀሳቦችን
መፋሰሻ መሆናቸውን ይንገሯቸው።) ይናገራሉ።]
መ. አሁን ሁላችሁም በግል ድምፅ ሳታሰሙ
ማንበብ (35 ደቂቃ) 2ኛውን አንቀጽ አንብቡ። (2ኛውን አንቀጽ
ምስጋና ለጓደኛዬ አንብበው ሲጨርሱ ያስቁሙና መጽሐፋቸውን
እንዲያጥፉ ያድርጉ።)
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
መ. ቍጥር ሁለቶች ካነበባችሁት አንቀጽ
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስና መገመት የምታስታውሷቸውን ዝርዝር ሀሳቦች ለቍጥር
ሥሩ አንዶች ተናገሩ።
መ. “ምስጋና ለጓደኛዬ” በሚል ርዕስ የቀረበውን [ተ. ቊጥር “2” ተማሪዎች ያስታወሱትን
ምንባብ ታነባላችሁ። ከማንበባችሁ በፊት ይናገራሉ።]
ግን የተወሰኑ የቅድመንባብ ጥያቄዎችን ለ3
መ. አሁን ደግሞ ቍጥር አንዶች፣ ቍጥር ሁለቶች
ደቂቃ ያህል በቡድን ከተወያያችሁ በኋላ
የዘነጓቸውን ዝርዝር ሀሳቦች ጨምሩ/ተናገሩ።
በቃል ትመልሳላችሁ።
[ተ. ቊጥር አንዶች ተጨማሪ ሀሳቦችን
መ. ሰዎች ምስጋና የሚያቀርቡት ምን
ይናገራሉ።]
ሲደረግላቸው ወይም ምን ሲያገኙ ነው?
[ተ. ሰዎች ከሌሎች ሰዎች እርዳታ፣ ድጋፍ፣
ምክር ወዘተ. ሲያገኙ ምስጋና ያቀርባሉ።] መ. ስላነበባችሁት አንቀጽ መናገር ካልቻላችሁ፣

96 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፺፮


አንቀጹን ደግማችሁ አንብቡ። (“ልዩነታቸው” በሚለው ረድፍ፣ ከነጠላ ሠረዙ
በፊት ያለውን “ሴቷ ልጅ” ከሚለው ፊትለፊት
(መ. በዚህ ዓይነት ምንባቡን ያስነብቡ።)
ይጻፉ፤ ከነጠላ ሠረዝ በኋላ ያለውን ደግሞ
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) “ወንዱ ልጅ” ከሚለው ፊትለፊት ይጻፉ
ሥሩ ወይም ተማሪዎችን አስነስተው ያጽፉ።)
መ. ተማሪዎች አንብባችሁ ጨረሳችሁ? በጣም ሥሩ
ጥሩ? ማንበብ ከመጀመራችሁ በፊት ሥዕሉን መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን በአንብቦ
ተመልክታችሁ የተረዳችሁትን ተናግራችሁ መረዳት ተግባር “2” ሥር የሚገኘውን
ነበር። የተናገራችሁት ከምንባቡ ሀሳብ ጋር ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም
የሚስማማ ነበር? (ተማሪዎች እንዲናገሩ እስከአሁን በሠራነው መሠረት የሴቷንና
ይፍቀዱላቸው።) የወንዱን ልጅ ተመሳስሎና ልዩነቶች
በሠንጠረዡ ውስጥ ዘርዝሩ።
[ተ. ይስማማል/ አይስማም በማለት ይመልሳሉ።]
መ. በጣም ጥሩ!
(መ.ተግባሩን በግል ከሠሩ በኋላ፣ 3 ወይም
4 ተማሪዎች በአንድ ቡድን ሆነው
(መ. በመጀመሪያ በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው የዘረዘሯቸውን ተመሳስሎዎችና ልዩነቶች
ቀን የቀረቡትን የአንብቦ መረዳት ተግባር ለቡድን አባላቱ እንዲያካፍሉ ያድርጉ።
“1” ጥያቄዎች በግል እንዲሠሩ ያድርጉ። ተመሳስሎዎችንና ልዩነቶችን በትክክለኛው
ከዚያም በግል የሠሩትን በቡድን እያስተያዩ ምድባቸው መለየታቸውን አስተያየት
እንዲወያዩበት ያድርጉ። በመጨረሻም እንዲሰጣጡ፣ አንዳቸው ያልጠቀሱትን
ጥያቄዎቹን እያነበቡ ወይም ተማሪዎች ከሌሎቹ በመቀበል ሠንጠረዣቸው የተሟላ
እንዲያነቡ እያደረጉ ከየቡድኑ ተማሪዎች እንዲሆን ያድርጉ።)
ምላሽ እንዲሰጡ ያድርጉ። ዝርዝር አካሄዱን
በምዕራፍ አምስት፣ በ1ኛው ሳምንት
በአንብቦ መረዳት “ሥሩ” ላይ የተገለፀውን 5ኛ ቀን
ይመልከቱ።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ልሥራ • ቃላት
መ. አሁን ደግሞ ተግባር “2”ን ትሠራላችሁ።
በመጀመሪያ ግን እኔ እሠራለሁ። ባነበባችሁት • መጻፍ
ምንባብ ውስጥ ሁለት ገፀባህርያት አሉ።
አንዷ ሴት ስትሆን፣ ሁለተኛው ወንድ ቃላት (10 ደቂቃ)
ነው። የሁለቱን ገፀባርያት ተመሳስሎና
ልዩነት በሠንጠረዥ ውስጥ እዘረዝራለሁ። ለቃላት ተመሳሳይ ፍቺ መስጠት
(በመማሪያ መጽሐፍ በ2ኛው ሳምንት፣ ልሥራ
በ4ኛው ቀን በአንብቦ መረዳት ተግባር “2” መ. ዛሬ ከምንባቡ በተወሰዱ ዓረፍተነገሮች
ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ ውስጥ የተሠመረባቸውን ቃላት በምንባቡና
ያዘጋጁ።) ከምንባቡ ውጪ ያላቸውን ፍቺ ትገልጻላችሁ።
መ. ሴቷ ልጅና ወንዱ ልጅ በምን ይመሳሰላሉ? ከዚያም ቃላቱ ከምንባቡ ውጪ ያላቸውን
ፍቺ እንዲያሳዩ አድርጋችሁ ዓረፍተነገሮች
[መ. ሁለቱም በአንድ ሰፈር ይኖራሉ።] ትመሠርታላችሁ። በመጀመሪያ እኔ አንድ
(“ተመሳስሏቸው” በሚለው ረድፍ ይጻፉ።) ምሳሌ ሠርቼ ላሳያችሁ።
እንሥራ መ. ለግል ንጽህናዋ ትኵረት ትሠጣለች።(በሰሌዳው
መ. ሁለቱ ገፀባህርያት ከሚለያዩባቸው ባህርያት ላይ ይጻፉላቸው።)
መካከል አንዱን በጋራ እንናገር።
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ “ትሠጣለች”
[መተ. ሴቷ ልጅ በትምህርቷ ጎበዝ ስትሆን፣ ወንዱ የሚለው ቃል ዐውዳዊ ፍቺ ምንድን ነው?
ልጅ ግን ለትምህርቱ ትኵረት አይሰጥም።]
[መ. ታደርጋለች፣ ምክንያቱም ትኵረት

፺፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 97


ትሠጣለች ሲባል ትኵረት ታደርጋለች የተሠመረባቸውን ቃላት ዐውዳዊ ፍቺና
እንደማለት ነው።] ከምንባቡ ውጭ ያላቸውን ፍቺ በሠንጠረዥ
ውስጥ ግለጹ።
መ. ከምንባቡ ውጪ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
(መ. ለተሠመረባቸው ቃላት ዐውዳዊ ፍቺና
[መ. ትለግሳለች]
ከምንባቡ ውጪ ያላቸውን ፍቺ መግለጹን
መ. ስለዚህ “ትሠጣለች” የሚለው ቃል የክፍልሥራ እንዲሠሩ ያድርጉ። ይህን
“ትለግሳለች” የሚል ፍቺ እንዲያስተላልፍ ተግባር ተማሪዎች በቡድን እየተወያዩ
አድርጌ ዓረፍተነገር ልመሥርትበት። እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም ከየቡድኑ ሦስት
[መ. ሴትዮዋ በየዓመቱ አሥር አሥር ሺህ ብር ሦስት ተማሪዎች በማሳተፍ አንዳቸው ቃሉን
ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ትሠጣለች።] በመጥራት፣ አንዳቸው ደግሞ በምንባቡ ውስጥ
(ይህን ዓረፍተነገር በሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው) ያለውን ፍቺ በመግለጽና ሌሎቻቸው ደግሞ
ከምንባቡ ውጪ ያለውን ፍቺ በመናገር
እንሥራ እንዲሳተፉ ያድርጉ። ከዚያም ቃላቱ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። “ፀጉሯን ከምንባቡ ውጪ ያላቸውን ፍቺ እንዲያሳዩ
አበጥራ ትጎነጉናለች” በሚለው ዓረፍተነገር አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ
ውስጥ “ትጎነጉናለች” የሚለው ቃል ዐውዳዊ የቤትሥራ ይስጡ።)
ፍቺ ምንድን ነው?
[መተ. ፀጉሯን ትሠራለች።] መጻፍ (30 ደቂቃ)
መ. ጥሩ! ከምንባቡ ውጪ ሌላ ፍቺ ልትነግሩኝ ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ትችላላችሁ? በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት አንቀጽ
[መተ. ታሴራለች] መጻፍ
(በቃላቱ በምንባቡ ውስጥና ከምንባቡ ውጪ እንሥራ
ያላቸውን ፍቺ በሠንጠረዥ ያሳዩ።) መ. ባለፈው ሳምንት “የእንስሳትንና የዕፅዋትን
ተመሳስሎና ልዩነት” በቢጋር ሠንጠረዥ
ቃሉ በምንባቡ ከምንባቡ ውስጥ ገልጻችኋል። አሁን ያዘጋጃችሁትን
ውስጥ ያለው ውጪ የቢጋር ሠንጠረዥ አብረን እንመልከት።
ፍቺ ያለው ፍቺ (የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ በውስጡ
ትጎነጉናለች ፀጉሯን ታሴራለች ያሉትን መረጃዎች ሳያሰፍሩ በሰሌዳው ላይ
ትሠራለች ይሣሉላቸው።)

እንስሳት ዕፅዋት

• ይራባሉ።
• ከቦታ ቦታ • ከቦታ ከቦታ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን “ትጎነጉናለች” የሚለው • ያድጋሉ። አይንቀሳቀሱም።
ይንቀሳቀሳሉ።
ቃል “ታሴራለች” የሚል ፍቺ እንዲሠጥ • ይመገባሉ። • ምግባቸውን
አድርገን ዓረፍተነገር እንሥራ። • ምግባቸውን • ህይወት ያዘጋጃሉ።
አላቸው።
[መተ. ልጅቷ ከጓደኛዋ ጋር ሆና በእኔ ላይ ነገር አያዘጋጁም።
• ይሞታሉ።
ትጎነጉናለች።]
መ. በጣም ጥሩ!
ሥሩ (መ. እንስሳትና ዕፅዋት የሚመሳሰሉበትንና
መ. እስከ አሁን በሠራነው መሠረት በ2ኛው የሚለያዩበትን እየጠየቁ ተማሪዎች
ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን “በቃላት” ሥር እንዲመልሱ እያደረጉ በሣሉት የቢጋር
ሠንጠረዥ ውስጥ ይዘርዝሩ።)

98 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፺፰


መ. አሁን አንቀጻችሁን ለመጻፍ መነሻ የሚሆን ያድርጉ።)
መንደርደሪያ ዓረፍተነገር አብረን እንሥራ።
ሀ. ቤት በሚገባ ካልጸዳ ትኋን ይፈጥራል።
የምትጽፉት አንቀጽ የሚያተኩረው በምን
ላይ ነው? ለ. ቆሻሻ ለተላለፊ በሽታዎች መንስዔ ሊሆን
ይችላል?
[መተ. በእንስሳትና በዕፅዋት ተመሳሳይነትና
ልዩነት ላይ ነው።] ሐ. የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችን በጉድጓድ ውስጥ
መቅበር ይገባል።
መ. ስለዚህ መንደርደሪያ ዓረፍተነገሩ ምን መሆን
አለበት? መ. የመንደሩ ጠባብ መንገድ ፈሳሽ ቆሻሻ
ስለሚደፋበት አረንቋ ሆኗል።
[መተ. እንስሳትና ዕፅዋትን ብዙ
የሚያመሳስሏቸውና የሚያለያዩዋቸው ነገሮች ሠ. ንጽህናቸውን የማይጠብቁ ሰዎች የተሟላ
አሉ።] ጤንነት ሊኖራቸው አይችልም።
መ. በጣም ጥሩ! እንስሳትንና ዕፅዋትን በዋነኛነት [ተ. የሚነበቡላቸውን ዓረፍተነገሮች አዳምጠው
የሚያመሳስላቸው ምንድን ነው? በትክክል ይጽፋሉ።]
[መተ. ሁለቱም ህይወት ያላቸው ነገሮች (መ. ዓረፍተነገሮቹን ሰሌዳ ላይ በመጻፍ
መሆናቸው።] ርስበእርስ እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
መ. ስለዚህ፣ ይህንኑ በተሟላ ዓረፍተነገር
እንግለጸው። 6ኛ ቀን
[መተ. ሁለቱም ህይወት ያላቸው ነገሮች
መሆናቸው በዋነኛነት የሚጠቀስ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ተመሳስሏቸው ነው።] (ተማሪዎች ይህንኑ • አቀላጥፎ ማንበብ
ሀሳብ በራሳቸው አባባል ሊገልፁት ይችላሉ።) • መናገር
ሥሩ • ሰዋስው
መ. አ ሁ ን በቢጋር ሠንጠረዡ ውስጥ
የዘረዘራችኋቸውን ተመሳስሎና ልዩነቶች
መሠረት በማድረግ በማወዳደርና በማነፃፀር የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ስልት አንድ አንቀጽ ጻፉ። በመጀመሪያ ሥሩ
የእንስሳትንና የዕፅዋትን ተመሳስሎ፣ ከዚያም (መ. በ2ኛው ሳምንት በ5ኛው ቀን በቃላት ተግባር
ልዩነታቸውን በመግለፅ፣ ሀሳባችሁን በተሟሉ ሥር የተሰጠውን የቤትሥራ ተማሪዎች
ዓረፍተነገሮች እያዋቀራችሁ አንቀጹን መሥራታቸውን ያረጋግጡ።)
ማደራጀት ትችላላችሁ።
መ. “ይወሩታል” የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ
[ተ. በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት አንድ አንቀጽ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
ይጽፋሉ።]
[ተ. ይሰፍሩበታል ማለት ነው።]
(መ. ተማሪዎች አንቀጹን ሲጽፉ እየተከታተሉ
ይደግፏቸው፤ ያበረታቷቸው።) መ. በጣም ጥሩ ነው። ይህ ቃል ከምንባቡ ውጪ
ምን ፍቺ አለው?
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
[ተ. በኃይል ይቆጣጠሩታል።]
የቃል ጽሕፈት
መ. በጣም ጥሩ! “በኃይል ይይዙታል” የሚል
ሥሩ ፍቺ እንዲሰጥ አድርጋችሁ የጻፋችሁትን
መ. ባለፈው ሳምንት ቃላት እያነበብኩላችሁ ዓረፍተነገር አንብቡልን።
ጽፋችሁ ነበር። ዛሬ ደግሞ የማነብላችሁን
[ተ. የጻፉትን ዓረፍተነገር ድምፅ በማሰማት
ዓረፍተነገሮች ትጽፋላችሁ። (የሚከተሉትን
ያነባሉ።]
ዓረፍተነገሮች እያነበቡላቸው እንዲጽፉ

፺፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 99


(መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ቃላት በማሠራት ዕረፍት መደረጉን እየተከታተላችሁ ማስታወሻ
ግብረመልስ ይስጡ።) ያዙ። ከዚያም በማስታወሻችሁ መሠረት
መስተካከል ያለባቸውን ነገሮች ለጓደኛችሁ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ንገሩ። በሁለተኛው ንባብ ጊዜ ደግሞ
የተነገራችሁን አስተያየት አስተካክላችሁ
ምሥጋና ለጓደኛዬ አንብቡ።
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
መናገር (15 ደቂቃ)
ሥሩ
መ. ዛሬ ድምፅ በማሰማት እያነበባችሁ ሥሩ
ትለማመዳላችሁ። ከዚያ በፊት ግን ባለፈው መ. አሁን “የግልና የአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ”
ያነበባችሁትን አስታውሳችሁ የሚከተለውን በተመለከተ በቡድን ትወያያላችሁ።
ጥያቄ በቃል መልሱ። በውይይታችሁ የግልና የአካባቢ ንጽህናን
ምንነት፣ ጠቀሜታ፣ አንድነትና ልዩነት
መ. “ምስጋና ለጓደኛዬ” በሚለው ምንባብ ውስጥ
እያነሳችሁ ተናገሩ። በምትናገሩበት ጊዜ
ሴቷና ወንዱ ልጅ ከሚለያዩባቸው ባህርያት
በመጽሐፋችሁ የቀረቡትን ቃላት መጠቀም
አንዱን ልትነግሩኝ ትችላችሁ?
ይኖርባችኋል። ሀሳባችሁን ተጠየቃዊ በሆነ
[ተ. ሴቷ በትምህርቷ ጎበዝ ስትሆን ወንዱ ግን መንገድ ታቀርባላችሁ። ይህም ማለት
በትምህርቱ ጎበዝ አይደለም።] ሀሳባችሁን በምክንያት እያስደገፋችሁ፣
ቅደምተከተል ጠብቃችሁ የሀሳብ ፍሰት ያለው
መ. ጥሩ! ሌላ ልዩነት ካለ ንገሩኝ።
ንግግር ታደርጋላችሁ ማለት ነው። ከዚህ
[ተ. ሴቷ ንጽህናዋን ስትጠብቅ ወንዱ ግን በተጨማሪም በንግግራችሁ ውስጥ አያያዥ
አይጠብቅም።] (በዚህ ዓይነት ተማሪዎች ቃላትን ትጠቀማላችሁ። አያያዥ ቃላት
እንዲናገሩ ያድርጉ።) የሚባሉት ዓረፍተነገሮችን ከዓረፍተነገር
ለማያያዝ የሚረዱ ስለዚህ፣ ሌላው፣ ከዚህ
ማንበብ (8 ደቂቃ)
በተጨማሪም እና የመሳሰሉት ቃላትና
ልሥራ ሐረጋት ናቸው። ንግግራችሁን ከማቅረባችሁ
መ. ዛ ሬ ድምፅ በማሰማት ማንበብ በፊት በመጽሐፋችሁ የቀረበውን የቢጋር
ትለማመዳላችሁ። በመጀመሪያ ግን “ምሥጋና ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁና
ለጓደኛዬ” ከሚለው ምንባብ የመጀመሪያዎቹን እየተወያያችሁ ሀሳባችሁን አደራጁ።
ሁለት አንቀጾች እኔ አነብላችኋለሁ። (ሁለቱን
(መ. በመጀመሪያ ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት
አንቀጾች ድምፅዎን እያሰሙ ያንብቡላቸው።)
ባሉት ቡድን ያደራጁ። ከዚያም በቡድን
እንሥራ እየተወያዩ ሀሳባቸውን በቢጋር ሠንጠረዥ
መ. አሁን ደግሞ እኔ ያነበብኳቸውን ሁለት እንዲያደራጁ ያድርጉ። በመጨረሻም
አንቀጾች አብረን እናንብብ። (ተማሪዎች ከየቡድኑ አንድ አንድ ተማሪዎች ለአጠቃላይ
ከርስዎ ጋር ድምጻቸውን በማሰማት የክፍሉ ተማሪዎች የቡድናቸውን ሀሳብ
እንዲያነቡ ያድርጉ።) እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
[መ. ድምፃቸውን በማሰማት በጋራ ያነባሉ።]
ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ሥሩ
እንሥራ
መ. አሁን “ምስጋና ለጓደኛዬ” በሚል ርዕስ
መ. ባለፈው ስለቅጽል ተምረናል። ዛሬ ደግሞ
ከቀረበው ምንባብ የመጀመሪያዎቹን ሦስት
ቅጽሎችን በጾታና በቍጥር መግለፅ
አንቀጾች ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ተራበተራ
እንለማመዳለን። አንድን ወንድ ልጅ “ቀዩ
ድምፅ በማሰማት አንብቡ። በመጀመሪያ
ልጅ” እንላለን፤ ሴቷን ደግሞ ምን እንላለን?
ንባብ ጊዜ አንዳችሁ ስታነቡ አንዳችሁ
ፊደላት ሳይገደፉ፣ ቃላት ሳይቆራረጡ [መተ. “ቀዪቱ/ቀዩዋ ልጅ” እንላለን]
በትክክል መነበባቸውንና አራት ነጥብ ላይ
መ. ጥሩ! ወንዱን ልጅ “ጎበዝ ልጅ” ካልን፣

100 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፻


ሴቷንስ ምን እንላለን?
[መተ. “ጎበዚቱ/ጎበዝዋ ልጅ” እንላለን]
መ. ስለዚህ ቅጽሎች ወንድና ሴት ጾታን ለይተው
ያመለክታሉ ማለት ነው።
መ. አሁን ደግሞ ቍጥርን እንመልከት። አንድን
ረጅም ልጅ ስንመለከት “ልጁ ረጅም ነው”
እንላለን። የሚመጡት ልጆች ከአንድ በላይ
ከሆኑ ምን እንላለን?
[መተ. ልጆቹ ረጃጅም ናቸው።]
መ. ስለዚህ ቅጽሎች ነጠላና ብዙ ቍጥር አላቸው
ማለት ነው።
ሥሩ
መ. ተማሪዎች በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን
በሰዋስው ንዑስ ክፍል ሥር የሚኙትን
ተግባራት ተመልከቱ፤ ተግባር “1” የቀረበው
በሠንጠረዥ ነው። የመጀመሪያው አምድ ላይ
ቅጽሎች ተዘርዝረዋል፤ ሁለተኛው አምድ
እነዚህን ቅጽሎች ወደብዙ ቍጥር ለውጣችሁ
የምታሳዩበት ነው፤ ሶስተኛው አምድ ደግሞ
የቀረቡትን ቅጽሎች በአንስታይ ጾታ
የምትገልፁበት ነው።
(መ. በመማሪያ መጽሐፍ የቀረቡትን ምሳሌዎች
ሠርተው ያሳዩአቸው። የመጀመሪያውን
ተግባር ክፍል ውስጥ፣ ሁለተኛውን ተግባር
ደግሞ የቤትሥራ ሊሠጧቸው ይችላሉ።)

፻፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 101


ማንበብ (30 ደቂቃ)
3ኛ ሳምንት የአካባቢ ጽዳት
ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ
7ኛ ቀን ቅደመንባብ (5 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘት የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
• የቃላት ጥናት ሥሩ
(መ. “ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ” በሚል
• ማንበብ
ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ከማስነበብዎ በፊት
በቅደመንባብ ሥር የቀረቡትን የቅድመንባብ
ጥያቄዎች እየጠየቁ ተማሪዎች በቃላቸው
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መልስ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
ሥሩ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን የተሰጠውን
የማንባብ ሂደት (10 ደቂቃ)
የቤትሥራ እንሠራለን። ልሥራ
መ. “ነጭ” የሚለውን በምሳሌው መሠረት ወደብዙ መ. ዛሬ ተግባራዊ የምታደርጉት መረዳትን
ቍጥር ቀይሩ። የመከታተያ ስልት “ወደፊት ማንበብ” ነው።
አንድ ምሳሌ እኔ ሠርቼ ላሳያችሁ። (ርዕሱን
[ተ. ነጫጭ] ያንብቡላቸው።)
(መ.ተማሪዎች ደብተራቸውን ተለዋውጠው መ. ርዕሱ “ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ”
ያርሙ።መልሶቹም፡- ነጫጭ፣ ጥቋቁር፣ ይላል። “ቆሼ” ምንድን ነው? ይህን ቃል
አጫጭር፣ ቀጫጭን፣ ደጋግ ናቸው።) ሰምቼው አላውቅም። እስኪ ምንባቡ ውስጥ
ስለቆሼ ምንነት የተገለፀ ነገር ካለ ልፈልግ።
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) (የመጀመሪያውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።)
መነጠልና ማጣመር መ. የመጀመሪያው አንቀጽ ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ
ማስወገጃ ቦታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ቆሻሻ
ሥሩ
መድፊያ ቦታ መሆናቸው ያመሳስላቸዋል
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በቃላት
ይላል። ስለዚህ ቆሼ አዲስ አበባ ውስጥ
ጥናት ሥር የቀረቡትን ቃላት በመነጠልና
የሚገኝ የቆሻሻ መድፊያ ቦታ ነው ማለት
በማጣመር አንብቡ።
ነው።
መ. በፊደል ተራ “ሀ” የተመለከተውን ነጣጥላችሁ
ሥሩ
አንብቡ!
መ. አሁን ባሳየኋችሁ መንገድ “ቆሼና አዲሱ
[ተ. ኘላስቲክ-ኦች] የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ” የሚለውን ምንባብ
መ. “ኘላስቲክ-ኦች” የሚለውን ቃል አጣምራችሁ 1ኛና 2ኛ አንቀጽ አንብቡ።
አንብቡ! (መ. ተማሪዎች በሚያነቡበት ጊዜ ያልገባቸው
[ተ. ኘላስቲኮች] ነገር ሲያጋጥማቸው ማንበባቸውን ወደፊት
እንዲቀጥሉ ይንገሯቸው። ምክንያቱም
መ. በጣም ጥሩ! ሌሎቹንም ቃላት በዚህ ዓይነት ያልገባቸው ሀሳብ በቀጣዮቹ ዓረፍተነገሮች
እያነበባችሁ ተለማመዱ። ወይም አንቀጾች ውስጥ ተገልጾ ሊሆን
(መ.ተማሪዎችን በአነስተኛ ቡድን ያደራጇቸው። ይችላል። ሁለቱን አንቀጾች አንብበው
ከዚያም ከመካከላቸው አንድ/አንዲት ተማሪ ሲጨርሱ ያስቁሙ።)
ቃሉን ነጥሎ/ላ ሲያነብ/ስታነብ ሌሎቹ (መ. ሦስተኛውን አንቀጽ የመጀመሪያ ዓረፍተነገር
ተማሪዎች አጣምረው በቡድን እንዲያነቡ ብቻ አንብባችሁ አቁሙ።)
ያድርጉ። በዚህ መልኩ ተራበተራ
እየተለዋወጡ እንዲያነቡ ያድርጓቸው።) [ተ. የ3ኛውን አንቀጽ የመጀመሪያ ዓረፍተነገር

102 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፻፪


ያነባሉ።] በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ አብረን
እንሥራ።
መ. “አሁን ግን የቆሼ ህልውና ሊያበቃ የግድ
ሆኗል” ሲል ምን ማለት ነው? የቆሼ መ. በምንባቡ ውስጥ መድፊያ የሚል ቃል አለ።
ህልውናስ የሚያበቃው ለምንድን ነው? የዚህን ይህ ቃል በምንባቡ ውስጥ የያዘው ፍቺ
ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት ሦስተኛውን አንቀጽ ምንድን ነው?
አንብቡ።
[መተ. መጣያ]
[ተ. ሦስተኛውን አንቀጽ ያነባሉ።] (አንቀጹን
መ. ትክክል! “ቆሻሻ መድፊያ” ሲል “የቆሻሻ
አንብበው ሲጨርሱ ያስቁሙ።)
መጣያ” ማለቱ ነው። “መድፊያ” የሚለው
መ. አሁን ምላሻችሁን ለጓደኞቻችሁ ቃል ከምንባቡ ውጪ ያለውን ፍቺ ልትነግሩኝ
ተናገሩ።(ከዚያም ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ትችላላችሁ?
ያድርጉ።)
[መተ. የድፎ ዳቦ መጋገሪያ ገበር ምጣድ]
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ “መድፊያ” በሚለው
ሥሩ ቃል ከምንባቡ ውጪ ያለውን ፍቺ እንዲያሳይ
መ. ምንባቡን አንብባችሁ ጨረሳችሁ? በጣም አድርገን ዓረፍተነገር እንመሥርት።
ጥሩ! አሁን፣ በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን [መተ. ለዳቦ መድፊያ የሚሆን ገበር ምጣድ
በአንብቦ መረዳት ሥር የቀረቡትን ጥያቄዎች ገዛሁ።]
በቃላችሁ መልሱ።
ሥሩ
መ. ቆሼና አዲሱን የቆሻሻ መጣያ ስፍራ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛ ቀን “በቃላት”
የሚያመሳስላቸው ምንድን ነው?
ንዑስ ክፍል ሥር በሠንጠረዥ ውስጥ
[ተ. ሁለቱም የቆሻሻ መድፊያ ቦታ መሆናቸው] ለቀረቡት ቃላት በምንባቡና ከምንባቡ ውጪ
ያላቸውን ፍቺ ግለጹ።
መ. በጣም ጥሩ!
(መ. በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎቹንም ጥያቄዎች (በመጀመሪያ ተማሪዎችን በአነስተኛ ቡድን
እየጠየቁ ተማሪዎች እንዲመልሱ ያድርጉ። ያደራጇቸው፤ ከዚያም ተማሪዎች በቡድን
ከዚያም ግብረመልስ ይስጧቸው።) እየተወያዩ ቃላቱ በምንባቡና ከምንባቡ ውጪ
ያላቸውን ፍቺ በሠንጠረዡ ውስጥ እንዲጽፉ
ያድርጉ። ቀጥሎ ተማሪዎቹ የሠጡትን ፍቺ
8ኛ ቀን ከየቡድኑ የተወሰኑ ተማሪዎች እንዲናገሩ ያድርጉ።
ከዚያም በትክክል ፍቻቸው ያልተገለጹ ቃላት ካሉ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ትክክለኛውን ፍቺ ይንገሯቸው። በመጨረሻም
• ቃላት ጥያቄ “ለ”ን በዚሁ በሠንጠረዥ ውስጥ በቀረቡት
ቃላት ከምንባቡ ውጭ ያላቸውን ፍቺ እንዲያሳዩ
• መጻፍ
አድርገው ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ የቤትሥራ
ይስጧቸውና ሥራቸውን ይገምግሙ።)

ቃላት (10 ደቂቃ) መጻፍ (30 ደቂቃ)


ለቃላት ተመሳሳይ ፍቺ መስጠት ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
እንሥራ በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት አንቀጽ
መ. ቃላት እንደዐውዳቸው የተለያዩ ፍቺዎች መጻፍ
እንደሚሠጡ ባለፈው ክፍለጊዜ ሠርታችኋል።
ሥሩ
ዛሬ “ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ”
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ የእንስሳትንና የዕፅዋትን
በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ ለወጡ ቃላት
ተመሳሳይነትና ልዩነት በተመለከተ
በምንባቡ ውስጥ ያላቸውን ፍቺና ከምንባቡ
በማወዳዳርና በማነፃፀር ስልት አንድ አንቀጽ
ውጪ ያላቸውን ፍቺ ትገልጻላችሁ።

፻፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 103


ጽፋችኋል። ዛሬ ደግሞ የጻፋችሁትን አንቀጽ ውስጥ ያቋተውን ቆሻሻ ውኃ በማፋሰስ
አስተካክላችሁ በመጻፍ ታቀርባላችሁ። አካባቢውን አደረቁ። ከዚያም ደረቅ ቆሻሻዎችን
በመጀመሪያ በመጽሐፋችሁ የቀረበውን በመለቃቀም በጉድጓድ ውስጥ ቀበሩ። ለፈሳሽ
የጽሑፍ መገምገሚያ መስፈርት የያዘ ቆሻሻ መፋሰሻ የሚሆን ቦይ በአካፋና በዶማ
ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አስፍሩ። ከዚያም ቆፈሩ። ከብዙ ጥረት በኋላ መንደራቸው ጽዱ
የጻፋችሁትን አንቀጽ በመስፈርቶቹ መሠረት ሆኖ ሲያዩት ተደሰቱ።
ገምግሙ። ቀጥሎ ያገኛችኋቸውን ስህተቶች [ተ. መምህር ሲያነቡላቸው ተማሪዎች ይጽፋሉ።]
አስተካክላችሁ አንቀጹን እንደገና ጻፉ።
መ. ጽፋችሁ ጨርሳችኋል፤ አሁን ደብተራችሁን
[ተ. ጽሑፋቸውን አስተካክለው ይጽፋሉ።] ተቀያየሩ። ጓደኞቻችሁ የጻፉትን
መ. አሁን ደብተራችሁን ከጎናችሁ ካለው/ችው ታርማላችሁ። ስታረሙ ፊደላትን በትክክል
ተማሪ ጋር ተቀያየሩ። ከዚያም በመጽሐፋችሁ መጻፋቸውን ብቻ ሳይሆን ሥርዓተነጥቦችን
የቀረበውን የመገምገሚያ ሠንጠረዥ በአግባቡ መጠቀማቸውን አስተውሉ።
በወረቀት ላይ አዘጋጁና የጓደኛችሁን ጽሑፍ (መ.አንቀጹን ትናንሽ ወረቀቶች ላይ አስቀድመው
በመስፈርቶቹ መሠረት እየገመገማችሁ ጽፈው ለየቡድኑ አንድ አንድ ሊሠጧቸው
ስህተቶቹን በሠንጠረዡ ውስጥ መዝግባችሁ ወይም ትልቅ ወረቀት ላይ በጉልህ ጽፈው
ለጓደኛችሁ ስጡ። አንብበውላቸው እንደጨረሱ ለሁሉም
[ተ. የጓደኛቸውን ጽሑፍ ይገመግማሉ፤ የስህተት ተማሪዎች የሚታይ ቦታ ላይ ሊሠቅሉላቸው
መጠን ይመዘግባሉ።] አልያም ሰሌዳው ላይ ሊጽፉላቸው ይችላሉ።)

መ. አነስተኛ ስህተት የተመዘገበባችሁ እጃችሁን [ተ. ተማሪዎች በቀረበላቸው ጽሑፍ መሠረት


አውጡ። (እጃቸውን ያወጡትን ተማሪዎች የጓደኞቻቸውን ጽሑፍ ያርማሉ። ከዚያም
ደብተር ይመልከቱና ከሁሉም አነስተኛ ደብተራቸውን መልሰው ይቀያየሩና
ስህተት የተመዘገበባቸውን/ ምንም ስህተት ስህተታቸውን ያስተካክላሉ።]
ያልተገኘባቸው ተማሪዎች ለክፍሉ ተማሪዎች (መ. ከሰጡት መመሪያ አንፃር የተማሪዎችን
ጽሑፋቸውን እንዲያነቡ ያድርጉ። ) ሥራ ይገምግሙ።)
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
የቃል ጽሕፈት 9ኛ ቀን
ሥሩ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. ባ ለ ፈ ው ክፍለጊዜ ዓረፍተነገሮችን • አቀላጥፎ ማንበብ
እያነበብኩላችሁ ጽፋችሁ ነበር። ዛሬ
ደግሞ አንድ አንቀጽ እያነበብኩላችሁ። • መናገር
ትጽፋላችሁ። • ሰዋስው
(መ.በዚህ እያዳመጡ መጻፍ ተግባር በዋነኛነት
ትኵረት የተደረገባቸው እንደ ዩ፣ ጓ፣ ፋ፣
ፉ፣ ፊ፣ ቋ፣ ኋ፣ ሯ፣ ጽ፣ ያሉ ፊደሎችን የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
አጻጻፍ ተማሪዎች እንዲለማመዱ ስለሆነ ሥሩ
ሲያነቡላቸው ጥንቃቄ ያድርጉ። የሚከተለውን
(መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን በቃላት
አንቀጽ ያንብቡላቸው።)
ሥር በተግባር “2” የተሠጠውን የቤትሥራ፣
ከጥቂት ወራት በፊት የእነተሻለ ሰፈር በጣም ተማሪዎች የመሠረቷቸውን ዓረፍተነገሮች
የቆሸሸና ለኑሮም የማይመች ነበር። በመሆኑም ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ ያድርጉ፤
ቆሻሻ ለጤና ጠንቅ መሆኑን የጤና ባለሙያዎች ግብረመልስም ይስጡ።)
አስተማሯቸው። ስለንጽህና ከተገነዘቡ በኋላ ግን መ. “ማዕዘን” የሚለው ቃል ከምንባቡ ውጪ
መንደራቸውን ጽዱ ለማድረግ ጥረት ጀመሩ። ያለው ፍቺ ምንድነው?
በመጀመሪያ በየቦታው በትንንሽ ጉድጓዶች

104 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፻፬


[ተ. ጠርዝ፣ ጥግ] ከቀረበው ምንባብ ከመጀመሪያው አንቀጽ
ጀምራችሁ ለ1 ደቂቃ ያህል ድምፅ
መ. ይህን ፍቺ እንዲያሳይ አድርጋችሁ
እያሰማችሁ አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ
የመሠረታችሁትን ዓረፍተነገር አንብቡ።
ሌሎቻችሁ ደግሞ የአንባቢዎቹን ስህተት
[ተ. የቤቱ ግዳግዳ አንደኛው ማዕዘን ተሰንጥቋል።] በደብተራችሁ ባዘጋጃችሁት የንባብ
(ተማሪዎች ሌሎች ዓረፍተነገሮች ሊመሠርቱ መከታተያ ሠንጠረዥ ውስጥ መዝግቡ።
ይችላሉ።) አቁሙ ስላችሁ የቆማችሁበትን ስፍራ
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም በጣታችሁ ያዙ።
የመሠረቷቸውን ዓረፍተነገሮች እንዲያነቡ [ተ. ተማሪዎች እየተፈራረቁ ያነባሉ፤ ሌሎቹ
ያድርጉ።) ያዳምጣሉ።]
(ለቀረቡት ቃላት ከምንባቡ ውጪ ያላቸው መ. አሁን ማንበባችሁን አቁሙ፤ ያቆማችሁበትን
አማራጭ ፍቺ በቅደምተከተል፣ ጠርዝ፣ የሚቆም፣ ቦታ ምልክት አድርጉ፤ በ1 ደቂቃ ውስጥ
ፋንታ፣ ማዳን፣ ምርኩዝ) ያነበባችኋቸውን ቃላት ብዛት ቊጠሩና በንባብ
መከታተያ በሠንጠረዡ ለሚመዘግቡት
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ጓደኞቻችሁ ንገሩ። አድማጮች ደግሞ
የመዘገባችሁትን ስህተት ለአንባቢዎቹ
ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ
ንገሯቸው።
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) [ተ. አንባቢዎች የተነገሯቸውን ስህተቶች
ሥሩ አስተካክለው ከመጀመሪያው በተሻለ ያነባሉ።]
መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት ድምፅ በማሰማት (መ.በዚህ ዓይነት ተማሪዎች ሚና እየተቀያየሩ
የማንበብ ልምምድ አድርጋችኋል። ተራበተራ እንዲያነቡ ያድርጓቸው።
ዛሬ የማንበብ ችሎታችሁ ምን ያህል እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ጊዜ ካነበቡ
እንደተሻሻለ ለመገምገም የጥንድ ንባብ በኋላ በመጀመሪያውና በሁለተኛው ንባብ
ተግባር ትሠራላችሁ። በመጀመሪያ ጥንድ ያሳዩትን መሻሻል እንዲገመግሙ ያድርጉ፤
ጥንድ ሆናችሁ ትቀመጣላችሁ። ከዚያም እርስዎም ይገምግሙ።)
አንዳችሁ አንባቢ አንዳችሁ ደግሞ አድማጭ
ትሆናላችሁ። እያንዳንዳችሁ ሁለት ሁለት ጊዜ
ድምፅ በማሰማት ታነባላችሁ። አንባቢዎቹ
መናገር (15 ደቂቃ)
ስታነቡ አድማጮቹ ደግሞ መጽሐፋችሁ ሥሩ
ላይ የቀረበውን የንባብ መከታተያ ሠንጠረዥ መ. አሁን የንግግር መለማመጃ ጊዜ ነው። ስለዚህ
በደብተራችሁ በማዘጋጀት የአንባቢዎቹን “ቆሼና አዲሱ የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ” በሚል
ስህተቶችና ያነበቧቸውን ቃላት ብዛት ርዕስ የቀረበውን ምንባብ መነሻ በማድረግ
ትመዘግባላችሁ። አድማጮች በመጀመሪያው በቡድን ከተወያያችሁ በኋላ ከየቡድኑ
ንባብ ጊዜ የመዘገባችሁትን ስህተት አንድ አንድ ተማሪዎች የቡድናችሁን ሀሳብ
ለአንባቢዎቹ ትነግራላችሁ። አንባቢዎች ለክፍሉ ታቀርባላችሁ። በምትናገሩበት ጊዜ
ደግሞ በተነገራችሁ አስተያየት መሠረት በመጽሐፋችሁ የተዘረዘሩትን ከምንባቡ የወጡ
ለሁለተኛ ጊዜ አሻሽላችሁ ታነባላችሁ። ቃላት መጠቀም፣ ሀሳባችሁን ምክንያታዊ
መ. አሁን ማንበብ ከመጀመራችሁ በፊት፣ በሆነ መንገድ መግለፅ ይጠበቅባችኋል።
በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን በአቀላጥፎ ስለዚህ፣ በሌላ በኩል፣ ከዚህ አንፃር፣ በአንፃሩ፣
ማንበብ ሥር የሚገኘውን የንባብ መከታተያ ሌላው የመሳሰሉትን አያያዥ ቃላትን
ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። መጠቀማችሁንም አትዘንጉ። ከመናገራችሁ
በፊት በመጽሐፋችሁ የቀረበውን የማወዳደርና
ማንበብ (8 ደቂቃ) የማነፃፀር የቢጋር ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
ሥሩ አዘጋጅታችሁ ሀሳባችሁን አደራጁ።
መ. አሁን ሰዓት ይዤያለሁ፤ “ቆሼና አዲሱ (መ. በመጀመሪያ ከ4-6 አባላት ባሏቸው ቡድኖች
የቆሻሻ ማስወገጃ ቦታ… ?” በሚል ርዕስ ተማሪዎችን ያደራጁ። ከዚያም በመነሻ

፻፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 105


ጥያቄዎቹ እንዲወያዩ ያድርጉ። ቀጥሎ [መተ. ፈጣን]
ከየቡድኑ አንድ አንድ ተማሪዎች ተነስተው
ሥሩ
ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያቀርቡ ያድርጉ።
ተማሪዎች ሲወያዩም ሆነ፣ ለክፍሉ ተማሪዎች መ. ተማሪዎች በ3ኛው ሳምንት፣ በሰዋስው ንዑስ
ሲያቀርቡ አዳዲሶቹን ቃላት በንግግራቸው ርዕስ ሥር የቀረቡትን ሁለት ተግባሮች
ውስጥ መጠቀማቸውን፣ ሀሳባቸውን በተጠየቃዊ በቀረቡት ምሳሌዎች መሠረት ሥሩ።
መንገድ ማቅረባቸውንና አያያዥ ቃላትን መ. ለመጀመሪያው ተግባር ከተዘረዘሩት
በአግባቡ መጠቀማቸውን ይገምግሙ።) ቅጽሎች መካከል ለዓረፍተነገሩ ተስማሚ
(መ.ተማ ሪ ዎ ች ን ለውይይት ለመጋበዝ የሆነውን ቅጽል መርጣችሁ በባዶ ቦታው
የሚከተሉትን ጥያቄዎች ይጠይቋቸው።) አስገቡ። (የመጀመሪያውን ጥያቄ እንደምሳሌ
ሊሠሩላቸው ይችላሉ።)
ሀ. የሚበሰብሱ ቆሻሻዎች ምን ምን ናቸው?
መ. ለሁለተኛው ተግባር ደግሞ ከሠንጠረዡ
ለ. ጥሩ! የማይበሰብሱ ቆሻሻዎች ምን ምን በላይ የተዘረዘሩትን ቅጽሎች በምሳሌው
ናቸው? መሠረት በሠንጠረዡ ውስጥ በተገቢ ቦታቸው
ሐ. የሚበሰብሱ ቆሻሻዎችን ለምን ለምን ተግባር መድቧቸው።
መልሶ መጠቀም ይቻላል? (መ.የ መ ጀ መ ሪ ያ ው ን ተግባር በቃል
መ. በጣም ጥሩ! የማይበሰብሱ ቆሻሻዎችን ለምን ሁለተኛውን ደግሞ በጽሑፍ ሊያሠራቸው
ለምን አገልግሎት መልሶ መጠቀም ይቻላል? ይችላሉ። ተማሪዎቹ ተግባሮቹን በአግባቡ
መሥራታቸውን ይገምግሙ፤ የከበዳቸውን
ሠ. በሁለቱ የቆሻሻ ዓይነቶች መካከል ያለው ተማሪዎች ይደግፉ፤ በመጨረሻም በመልሶቹ
ተመሳሳይነትና ልዩነት ምንድን ነው? ላይ ከተማሪዎችዎ ጋር ይወያዩ።)
[ተ. ከሀ-ሠ ለተጠየቋቸው ጥያቄዎች የተለያዩ
መልሶች ይመልሳሉ።]

ሰዋስው (10 ደቂቃ)


ቅጽል
እንሥራ
መ. በመጽሐፋችሁ ከቀረቡት ቃላት ቅጽል
የሆኑትን እየመረጣችሁ ዓረፍተነገሮቹን
ታሟላላችሁ። በመጀመሪያ ግን ሁለት
ምሳሌዎች አብረን እንሥራ።

“ቀጠፈ” ፣ “ቀይ”ና “ፈጣን” ከሚሉት ቃላት ቅጽል


የሆኑትን መርጠን በሚከተሉት ዓረፍተነገሮች
ውስጥ እናስገባ። (የሚከተሉትን ዓረፍተነገሮች
ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
1. -------------- አበባ እወዳለሁ።
2. ---------------መኪና ተገዛልኝ።
መ. በመጀመሪያው ዓረፍተነገር ውስጥ የሚገባው
ቅጽል የትኛው ነው?
[መተ. ቀይ]
መ. ጥሩ ነው! በሁለተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ
የሚገባው ቃል የትኛው ነው?

106 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 5 ፻፮


ምዕራፍ 6 ምግብ
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• “ምግብ” በሚል የምንባብ ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላት በንግግርና በጽሑፍ ይጠቀማሉ፤
• ዋናና መዘርዝር ሀሳቦችን በማደራጀት አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• በጽሑፋቸው ውስጥ ይዘትን (አንድ ነጥብን) ይጠቀማሉ፤
• በዋናና በመዘርዝር ሀሳቦች የተዋቀሩ ምንባቦችን አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• “በሽታ ተከላካይ ምግቦች” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• “ምግብ” በሚል የምንባብ ይዘት መነሻነት ይናገራሉ፤
• ከዓረፍተነገር ውስጥ ግሶችን፣ የተጸውዖና የወል ስሞችን ይለያሉ።

[ተ. ተዋጽኦዎችን]
1ኛ ሳምንት
(መ. በመጀመሪያ በጥንድ በጥንድ ሆነው
የምግብ ዓይነቶች እንዲያነቡ ያድርጉ። ከዚያም በተናጠል
እንዲያነቡ ያድርጉ። በመጨረሻም በትክክል
ያልተነበቡ ቃላት ካሉ ያንብቡላቸው።)
1ኛ ቀን
የዕለቱ ትምህርት ይዘት ማንበብ (33 ደቂቃ)
• የቃላት ጥናት ምግቦቻችን
• ማንበብ ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
እንሥራ
የቃላት ጥናት (7 ደቂቃ) መ. አሁን ምንባቡን ከማንበባችን በፊት
መነጠልና ማጣመር የቅድመንባብ ተግባሩን እንሠራለን።
ከእንስሳት ከሚገኙ ምግቦች መካከል አንዱን
ሥሩ
እንጥቀስ፤
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በቃላት ጥናት
ሥር “ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ ከቀረበው [መተ. እርጎ] (ከመማሪያ መጽሐፍ የሚገኘውን
ምንባብ የወጡ ውስብስብ ቃላትና ሐረጋት ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ ከሣሉ በኋላ “እርጎ”
ቀርበዋል። ቃላትና ሐረጋቱን በመነጠልና የሚለውን ቃል “ከእንስሳት የሚገኙ ምግቦች”
በማጣመር አንብቡ። በሚለው አምድ ይጻፉ።)
መ. “ተዋጽኦዎችን” የሚለውን ቃል በመነጠል መ. ጥሩ! ከዕፅዋት ከሚገኙ ምግቦች ደግሞ አንድ
አንብቡ። ንገሩኝ።

[ተ. ተዋጽኦ-ዎች-ን] [መተ. ሙዝ] (ከዕፅዋት የሚገኙ ምግቦች በሚለው


አምድ ይጻፉ።)
መ. ጥሩ! ይህንኑ ቃል በማጣመር አንብቡ።

፻፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 107


መ. በጣም ጥሩ! መ. አሁን በምንባቡ ላይ የተመሠረቱ የምርጫ
ጥያቄዎችን እንመልሳለን።
ሥሩ
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በቅድመንባብ መ. ገብስ፣ ዳጉሳ፣ በቆሎና ማሽላ ምን ዓይነት
ሥር የሚገኘውን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ ምግብ ይዘጋጅባቸዋል?
አዘጋጁ። ከዚያም በምሳሌው መሠረት [መተ. እንጀራ]
ከእንስሳትና ከዕፅዋት የሚገኙ ምግቦችን
በሠንጠረዡ ውስጥ ዘርዝሩ። ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ እናንተ ብቻችሁን
መ. ከእንስሳት የሚገኙ ምግቦችን ንገሩኝ።
ትመልሳላችሁ፣ በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው
[ተ. ሥጋ፣ እንቁላል፣ ወተት…] ቀን በአንብቦ መረዳት ሥር የቀረቡ
የተግባር “1” ጥያቄዎችን በጽሑፍ መልሱ።
መ. ጥሩ ነው! ከዕፅዋት የሚገኙ ምግቦችንስ
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ? መ. “አሹቅ” ከየትኛው የእህል ዓይነት ይዘጋጃል?
[ተ. ብርቱካን፣ ፓፓያ፣ ሠላጣ፣ ድንች…] [ተ. ከባቄላ]
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) መ. “ከባቄላ” የሚለው ሐረግ የሚገኝበት ፊደል
የትኛው ነው?
ሥሩ
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ። ከዚያም “1” [ተ. ለ]
እና “2” በማለት በቍጥር ይሰይሟቸው።) (መ. ይህን ተግባር የሚሠሩበት 8 ደቂቃ
መ. “1” ቍጥሮች የመጀመሪያውን አንቀጽ ይስጧቸው። ተግባሩን ከሠሩ በኋላ
ድምፃችሁን እያሰማችሁ አንብቡ። “2” ደብተራቸውን ተቀያይረው፣ በመልሶቹ ላይ
ቍጥሮች በለሆሳስ እያነበባችሁ ተከታተሉ። ከርስዎ ጋር እየተነጋገሩ እንዲተራረሙ
ያድርጉ።)
[ተ. የመጀመሪያውን አንቀጽ ያነባሉ።]
እንሥራ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን መጽሐፋችሁን እጠፉ።
መ. አሁን ደግሞ በተግባር “2” ሥር የቀረቡትን
“1” ቍጥሮች የአንቀጹን ዋና ሀሳብ ተናገሩ።
ጥያቄዎች ከመሥራታችሁ በፊት አንድ
[ተ. “1” ቍጥሮች የመጀመሪያውን አንቀጽ ዋና ጥያቄ አብረን እንመልስ።
ሀሳብ ይናገራሉ።]
መ. ከአትክልት ምግቦች መካከል ተቀቅለው
መ. በጣም ጥሩ! “2” ቍጥሮች ደግሞ ዝርዝር የሚበሉት የትኞቹ ናቸው?
ሀሳቦቹን ተናገሩ።
[መተ. ጎመን፣ ቆስጣ፣ ድንች፣ ቀይሥር፣ ካሮት፣
[ተ. “2” ቍጥሮች የመጀመሪያውን አንቀጽ ቲማቲም…]
ዝርዝር ሀሳቦች ይናገራሉ።]
መ. በጥሬው የሚበሉትስ?
(መ. ሌሎቹንም አንቀጾች በተመሳሳይ ሁኔታ
[መተ. ሠላጣ፣ ቃሪያ፣ ቲማቲም፣ ካሮት…]
ተማሪዎች ሚናቸውን እየተቀያየሩ እንዲያነቡ
ያድርጉ። ተማሪዎች ሲያነቡ በሰጧቸው መ. በጣም ጥሩ! ይህን ማለት የቻልነው ከምን
መመሪያ መሠረት እያነበቡ መሆኑን ተነስተን ነው?
እየተዘዋወሩ ይከታተሉ።) [መተ. በምንባቡ ውስጥ አንዳንድ አትክልቶች
አንብቦ መረዳት (18 ደቂቃ) ተቀቅለው ሌሎቹ ጥሬውን እንደሚበሉ
ተገልጿል። እነዚህን ምግቦች መዘርዘር
እንሥራ የቻልነው ከቀደመ እውቀታችን በመነሳት
መ. አሁን በሠንጠረዡ ውስጥ ከዘረዘራችኋቸው ነው።]
መካከል በምንባቡ ውስጥ ያገኛችኋቸው
የትኞቹ ናቸው? እናንተ ከዘረዘራችኋቸው ሥሩ
ውጪ ከምንባቡ ውስጥ ያገኛችኋቸው አሉ? መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን
(ከተማሪዎች መልስ ይቀበሉ።) በአንብቦ መረዳት ሥር የቀረቡትን የተግባር

108 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፰


“2” ጥያቄዎች በቡድን ከተወያያችሁ በኋላ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ይደግፉ።
የደረሳችሁበትን ማጠቃለያ በቃላችሁ በመጨረሻም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር
አቅርቡ። (ተማሪዎች በቡድን ሲወያዩ እየተነጋገሩ ግብረመልስ ይስጡ።)
እየተዘዋወሩ ይከታተሉ። ፍንጭ ሰጪ
ልሥራ
ጥያቄዎችን በመጠየቅ፣ እንዲወያዩ ያድርጉ።
በመጨረሻም የየቡድኑ ተወካዮች ተማሪዎች መ. በተግባር “2” ሥር በተሠመረባቸው ቃላትና
የቡድናቸውን ሀሳብ እንዲያቀርቡ ያድርጉ።) ሐረጋት የዓረፍተነገሩን ሀሳብ የማይለውጥ
ሌላ ዓረፍተነገር ትመሠርታላችሁ።
በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ እኔ
2ኛ ቀን እሠራለሁ።
መ. “የእንስሳትን ተዋጽኦ መመገብ አካልን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ይገነባል።” በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ
• ቃላት “ተዋጽኦ” የሚለው ቃል ተሠምሮበታል፤ ፍቹ
• መጻፍ ምንድን ነው?
[መ. ውጤት]
መ. ጥሩ! አሁን “ተዋጽኦ” የሚለውን
ቃላት (10 ደቂቃ) ቃል ተጠቅሜ፣ የዓረፍተነገሩን ሀሳብ
እንሥራ ሳልቀይር፣ በእኔ አገላለጽ ሌላ ዓረፍተነገር
እመሠርታለሁ።
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በቃላት
ተግባር 1 ሥር ከምንባቡ የወጡ ጥቅል [መ. የእንስሳትን ተዋጽኦ መብላት ሰውነትን
የምግብ መጠሪያዎች በሠንጠረዥ ውስጥ ያዳብራል።]
ቀርበዋል። ከሠንጠረዡ በላይ ደግሞ በነዚህ
ጥቅል ቃላት ሥር የሚካተቱ ዝርዝር ቃላት
እንሥራ
ቀርበዋል። ከሠንጠረዡ በላይ የቀረቡትን መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። “የከተማ
ዝርዝር ቃላት በሠንጠረዡ ውስጥ ከቀረቡት ሰዎች የተለያዩ የአዝዕርት ዓይነቶችን ከገበያ
ጥቅል መጠሪያቸው ሥር እንመድባለን። ይሸምታሉ።” በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ
“አዝዕርት” የሚለው ቃል ተሠምሮበታል፤
መ. ከሠንጠረዡ በላይ ከቀረቡት ቃላት መካከል ፍቹ ምንድን ነው?
በአትክልት ውስጥ የሚመደበው የትኛው
ነው? [መተ. እህልማለት ነው።]

[መተ. ሰላጣ] መ. ጥሩ! “አዝዕርት” የሚለውን ቃል ተጠቅመን፣


የዓረፍተነገሩን ሀሳብ ሳንቀይር፣ በራሳችን
መ. ስለዚህ “ሰላጣ” የሚለውን ቃል “አትክልት” አገላለጽ ዓረፍተነገር እንመሥርት።
ከሚለው ሥር እንጽፋለን።
[መተ. የከተማ ኗሪዎች ልዩ ልዩ አዝዕርትን
ሥሩ ከገበያ ይገዛሉ።]
መ. አሁን ደግሞ እናንተ ትሠራላችሁ
ሥሩ
መ. ከሠንጠረዡ በላይ ከቀረቡት ቃላት መካከል መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን
በ”ፍራፍሬ” ውስጥ የሚመደበው የትኛው በቃላት ሥር በቀረቡት ዓረፍተነገሮች ውስጥ
ነው? የተሠመረባቸውን ቃላት ሳትቀይሩ፣ በራሳችሁ
[ተ. እንጆሪ] አገላለጽ ጻፉ።

መ. ትክክል! “እንጆሪ” የሚለውን ቃል “ፍራፍሬ” መ. “ቅመም ለምግብ ማጣፈጫነት ይውላል”


ከሚለው ሥር ጻፉ። በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ “ቅመም”
የሚለውን ቃል ሳትቀይሩ በራሳችሁ አገላለጽ
(መ. ተግባሩን ለመሥራት 5 ደቂቃ ይስጧቸው። ጻፉ።
ተማሪዎች ሲሠሩ እየተዘዋወሩ ይከታተሉ።
[ተ. ቅመም ለምግብ ጣዕም ለመስጠት

፻፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 109


ያገለግላል።] (ተማሪዎች ዓረፍተነገሩን
በተለያየ መንገድ ሊጽፉት ይችላሉ።) ሥጋ
(መ. ይህን ተግባር የቤትሥራ ይስጧቸው)
እንስሳት እንቁላል
መጻፍ (30 ደቂቃ)
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) ወተትና
የወተት
በዋናና መዘርዝር ሀሳቦች ስልት የቢጋር
ምግብ ተዋጽኦ
ሠንጠረዥ ማዘጋጀት
ልሥራ አትክልት
መ. አሁን “ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ የቀረበውን
ምንባብ ዋናና መዘርዝር ሀሳቦች በቢጋር
ዕፅዋት ፍራፍሬ
ሠንጠረዥ አደራጃለሁ። የምንባቡ ዋና ሀሳብ
ስለምንድን ነው?
[መ. ስለምግብ] አዝርዕት
መ. ስለዚህ “ምግብ” የሚለውን ቃል በማዘጋጀው
የቢጋር ሠንጠረዥ ራስጌ (ከላይ በኩል) (መ. የቢጋር ሠንጠረዡ ለምሳሌ ከላይ በቀረበው
እጽፋለሁ። (ቃሉን በሳጥን ውስጥ ይጻፉ።) ሁኔታ ቢቀርብም፣ በእያንዳንዱ ሥር ሌሎች
ንዑሳን ዘርፎች መጨመር ይቻላል። ለምሳሌ
መ. ምግቦች በዋነኛነት ከምን ከምን ይገኛሉ?
በአትክልት ሥር ብርቱካን፣ ማንጎ፣ ፓፓያ
[መ. ከእንስሳትና ከዕፅዋት] (ሁለቱንም ሐረጋት የመሳሰሉትን መዘርዘር ይቻላል።)
በተለያዩ ሳጥኖች ውስጥ አድርገው በምግብ ሥሩ
ሥር ይጻፉ።)
መ. አሁን ደግሞ የበሽታ ዓይነቶችን በተለያዩ
እንሥራ ምድቦች ከፋፍላችሁ በቢጋር ሠንጠረዥ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ፤ ከእንስሳት ታደራጃላችሁ።በሽታዎችን በሁለት ዋና
የሚገኙ ምግቦች ምን ምን ናቸው? ዋና ዘርፎች መክፈል ይቻላል። ምን ምን
ተብለው ሊከፈሉ ይችላሉ? (ተማሪዎች
[መተ. ሥጋ፣ እንቁላል፣ ወተትና የወተት
በቡድን ተወያይተው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ተዋጽኦዎች] (በሦስት የተለያዩ ሣጥኖች
ውስጥ እንስሳት ከሚለው ሥር ይጻፉ።) [ተ. ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች]
(በምሳሌው መሠረት “በሽታዎች” ከሚለው
መ. ከዕፅዋት የሚገኙ ምግቦች ምን ምን ናቸው?
ሥር በሁለት የተለያዩ ሳጥኖች ውስጥ
መተ. አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ አዝርዕት] (በሦስት እንዲጽፉ ይንገሯቸው።)
የተለያዩ ሳጥኖች ውስጥ ዕፅዋት ከሚለው ሥር
መ. ተላላፊ በሽታዎች ከሚተላለፉበት መንገድ
ይጻፉ። የሚያዘጋጁት የቢጋር ሠንጠረዥ
አንፃር ምን ምን ተብለው ሊከፈሉ
የሚከተለውን ሊመስል ይችላል።)
ይችላሉ?(በቡድን ተወያይተው እንዲመለሱ
ያድርጉ)
[መ. በተበከለ ምግብና መጠጥ የሚተላለፉ፣
በግብረስጋ ግንኙነት የሚተላለፉ፣ በትንፋሽ
የሚተላለፋ ወዘተ.]
መ. ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምን ምን ናቸው?
(በቡድን ተወያይተው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
[ተ. የጨጓራ ህመም፣ የኩላሊት ህመም ወዘተ.]
(መ. ከላይ በቀረበው መልክ፣ እየተወያዩ እንዲሠሩ

110 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፲


ካደረጉ በኋላ የቢጋር ሠንጠረዣቸውን የተሟላ በመጠቀም አሳጥራችሁ ጻፉ።
ለማድረግ የቤትሥራ ይስጧቸው)
መ. “ማቴዎስ” የሚለውን ቃል አሳጥራችሁ ጻፉ።
መ. የበሽታ ዓይነቶችንና ባህርያቸውን
[ተ. ማቴ.]
በተመለከተ መጻሕፍት በማንበብ ወይም
የጤና ባለሙያዎችን ወይም የሳይንስ መ. በጣም ጥሩ! በተራ ቍጥር 2 ላይ የቀረቡትን
መምህራንን በመጠየቅ በሽታዎችን በተለያዩ ቃላት ደግሞ የመጀመሪያና የመጨረሻዎቹን
ምድቦች ከፋፍላችሁ በቢጋር ሠንጠረዥ ፊደላት በመጠቀም አሳጥራችሁ ጻፉ።
አደራጁ። መ. “ወታደር” የሚለውን ቃል አሳጥራችሁ ጻፉ።
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) [ተ. ወር.]
ይዘት/አንድ ነጥብ (.) (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ያሠሯቸው።
ልሥራ ተግባሩን ሠርተው ሲጨርሱ ደብተር
መ. ዛሬ ስለአንድ ነጥብ አገልግሎትና አጠቃቀም ተቀያይረው እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
እንማራለን። አንድ ነጥብ በርካታ
አገልግሎቶች አሉት። አንድ ነጥብ አንድን 3ኛ ቀን
ቃል በተወሰኑ ፊደላት አሳጥሮ ለመጻፍ
ያገለግላል። አንድን ቃል አሳጥሮ ለመጻፍ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
የተለያዩ መንገዶች አሉ። • አቀላጥፎ ማንበብ
መ. “መስተዳደር” የሚለውን ቃል እንዴት አሳጥሬ • ማዳመጥ
ልጻፈው? የተለመደው የቃሉን የመጀመሪያ
ፊደላት በመጠቀም አሳጥሮ መጻፍ ነው። • ሰዋስው

[መ. መስ.]
መ. “ወይዘሮ” የሚለውን ቃል እንዴት አሳጥሬ የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ልጻፈው? የተለመደው የቃሉን የመጀመሪያና
ሥሩ
የመጨረሻ ፊደላት በመጠቀም አሳጥሮ
መጻፍ ነው።
(መ. በ2ኛው ቀን በቃላት ሥር የተሰጠውን
የቤትሥራ ተማሪዎች የቤትሥራውን
[መ. ወሮ.] መሥራታቸውን ያረጋግጡ። ተራበተራ
እንሥራ በማስነበብ ግብረመልስ ይስጡ።)
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። “ምዕራፍ” መ. የተሠመረበት ቃል (ቅመም) ፍቺ ምንድን
የሚለውን ቃል፣ የቃሉን የመጀመሪያ ሁለት ነው?
ፊደላት ተጠቅመን እናሳጥር።
[ተ. ማጣፈጫ]
[መተ. ምዕ.] (በሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
መ. “ቅመም” የሚለውን ቃል ሳትቀይሩ
መ. ጥሩ! ዶክተር የሚለውን ቃል የመጀመሪያና የሠራችሁትን ዓረፍተነገር አንብቡ።
የመጨረሻ ፊደላት በመጠቀም አሳጥረን
[ተ. ቅመም ለምግብ ጣዕም ለመስጠት
እንጻፍ።
ያገለግላል።]
[መተ. ዶር.] (ሰሌዳው ላይ ይጻፉና ተማሪዎች
(መ.በዚህ ዓይነት ተማሪዎች የመሠረቷቸውን
እንዲጽፉት ያድርጉ።)
ዓረፍተነገሮች ያስነብቡ።)
ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን በአጻጻፍ
ሥርዓት ሥር የሚገኙትን ተግባራት
ሥሩ። በተራ ቍጥር 1 ሥር የቀረቡትን
ቃላት የመጀመሪያዎቹን ሁለት ፊደላት

፻፲፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 111


አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ በቅድመማዳመጥ ሥር
የቀረበውን ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ ይሣሉ።)
ምግቦቻችን [መ. እኔ ከማውቃቸው በሽታ ተከላካይ ምግቦች
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) መካከል አንዱ “ካሮት” ነው።] (“ካሮት”
ሥሩ የሚለውን ቃል “የማውቃቸው በሽታ ተከላካይ
ምግቦች” በሚለው አምድ ይጻፉ።)
መ. ዛሬ ድምፅ እያሰማችሁ በማንበብ
ልምምድ ታደርጋላችሁ። ከዚያ በፊት ግን [መ. በምሽት የማየት ችግር።] (ይህን ደግሞ
የምታነቡትን የምንባብ ይዘት በማስታወስ “የሚከላከሉት የበሽታ ዓይነት” በሚለው
አንድ ጥያቄ ትመልሳላችሁ። አምድ ይጻፉ።)
መ. “ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ በቀረበው ምንባብ ሥሩ
መሠረት ምግቦች ከምን ከምን እንደሚገኙ መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን የቀረበውን
ተናገሩ። ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም
[ተ. ከእንስሳት፣ ከዕፅዋት] በአንደኛው አምድ የምታውቋቸውን በሽታ
ተከላካይ ምግቦች ዘርዝሩ። በሁለተኛው
(መ. ከእንስሳትና ከዕፅዋት የሚገኙ ምግቦችን አምድ ምግቦቹ የሚከላከሉትን የበሽታ
እንዲዘረዝሩ ያድርጉ።) ዓይነቶች ዘርዝሩ።
ማንበብ (8 ደቂቃ) የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)
እንሥራ (መ. ተማሪዎች ዋናና መዘርዘር ሀሣብን
መ. በመጀመሪያ ወሰነትምህርት በምዕራፍ 4 ለመለየት እየሞከራችሁ አዳምጡ። ምንባቡን
በጋራ ንባብ ልምምድ አድርጋችሁ ነበር። ያንብቡላቸው፤ ተማሪዎች በአግባቡ
ዛሬም በተመሣሣይ የጋራ ንባብ ልምምድ እያዳመጡ መሆኑን ለማረጋጋጥ በማዳመጥ
እናደርጋለን። ምንባቡ ውስጥ የኮከብ ምልክት ካለበት
(መ. በምዕራፍ 4፣ በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቦታ ላይ ሲደርሱ፣ የቀረቡትን ጥያቄዎች
ቀን በ“እንሥራ” ሥር የቀረበውን አሠራር ይጠይቋቸው፤ ምላሻቸውን ይቀበሉና
በመከተል “ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ ከቀረበው ማንበብዎን ይቀጥሉ።)
ምንባብ 3ኛውን አንቀጽ ከተማሪዎች ጋር በሽታ ተከላካይ ምግቦች
ድምፅ እያሰሙ በጋራ ያንብቡ።)
በየዕለቱ ከምንመገባቸው ምግቦች ለጤናችን
ሥሩ ጠቃሚ የሆኑ ንጥረነገሮች እናገኛለን። እነዚህ
መ. “ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ ንጥረነገሮች ሰውነት፣ በሽታ ተከላካይ የሆኑ
3ኛውንና 4ኛውን አንቀጽ በቡድን ሆናችሁ ሆርሞኖችን በማመንጨት ለበሽታዎች
ድምፅ እያሰማችሁ በጋራ አንብቡ። እንዳንጋለጥ ያደርጋሉ። በሽታ የመከላከል ሚና
ያላቸውን ምግቦች በሽታ ተከላካይ እንላቸዋለን።
(መ. አሠራሩን በምዕራፍ 4፣ በ1ኛው ሳምንት፣ ከበሽታ ተከላካይ ምግቦች መካከል ሙዝን፣ ነጭ
በ3ኛው ቀን፣ አቀላጥፎ ማንበብ በ”ሥሩ” ሥር ሽንኩርትን፣ ሻይንና ሎሚን ለአብነት መጥቀስ
የቀረበውን ይመልከቱ።) ይቻላል።
ማዳመጥ ሙዝ ለጤንነት አስፈላጊ የሆነ ምግብ ነው።
ሲበሉት ፈጥኖ ጉልበት (ኃይል) ይሰጣል።
በሽታ ተከላካይ ምግቦች በማግኒዚየም ማዕድንና በቫይታሚን ቢ-6
የበለፀገ ነው። ባልበሰለ ሙዝ ውስጥ ያለው አሰር
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ) በደም ውስጥ የሚገኝን የቅባት መጠን ይቀንሳል።
ልሥራ ሆድ ሲጎረብጥ ሙዝ መመገብ መፍትሔ ሊሆን
መ. “በሽታ ተከላካይ ምግቦች” በሚል ርዕስ ይችላል። ምግብ አልፈጭ ብሎ ቃር ሲሰማ
የቀረበውን ምንባብ ከማንበባችሁ በፊት ሙዝ በመብላት እፎይታ ማግኘት ይቻላል።
ሙዝ በጭንቅላት ውስጥ የደም መፍሰስ በሽታ
አንድ ተግባር ትሠራላችሁ። (በ1ኛው
(ስትሮክ) ይቀንሳል። የደም ግፊትን በሚቀንሰው

112 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፲፪


ፖታሺየም በተባለ ማዕድንም የበለፀገ ነው። መ. እናንተ ከዘረዘራችኋቸው ውጭ ሌሎች በሽታ
ነጭ ሽንኩርትም ለጤና ጠቃሚ የሆነ የአትክልት ተከላካይ ምግቦች በምንባቡ ውስጥ አገኛችሁ?
ዓይነት ነው። አንዳንድ ሰዎች የተቀመመ ምግብ (ተማሪዎች እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ብለው ይጠሩታል። ነጭ ሽንኩርት የጉንፋንና መ. አሁን በመጽሐፋችሁ የቀረቡትን ጥያቄዎች
የኢንፍሉዌንዛ የመቆያ ጊዜን በግማሽ ይቀንሳል። ባዳመጣችሁት መሠረት እንመልሳለን።
የተፈጨ ነጭ ሽንኩርት በጠረኑ ብቻ እስከ20
ባዳመጣችሁት ምንባብ ውስጥ ከተጠቀሱት
ሳንቲሜትር ርቀት ድረስ የሚገኝን ባክቴርያ
በሽታ ተከላካይ ምግቦች መካከል አንዱን
ይገድላል። ሰውነታችን በሽታን ለመከላከል
የሚያስችል አቅም እንዲኖረው ያደርጋል። ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
ለምግብ መፈጨት፣ ለነርቭ፣ ለመተንፈሻና [መተ. ሙዝ] (“ሙዝ” የሚለውን ቃል “በሽታ
ለቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ይረዳል። እንዲሁም ተከላካይ ምግቦች” በሚለው አምድ ይጻፉ።)
ለልብ፣ ለሳንባ፣ ለፀጉርና ለዓይን ጤንነት
መጠበቅ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። የሆድ መ. ጥሩ! ሙዝ ከሚከላከላቸው በሽታዎች መካከል
ካንሰርንም ይቀንሳል። ይህ ሁሉ ጥቅም ያለው አንዱን ንገሩኝ።
ነጭ ሽንኩርት ጥሬውን ቢበላ ይመረጣል።
[መተ. በደም ውስጥ የሚገኝ የቅባት መጠን።]
***1. ሙዝ በምን በምን የበለፀገ ነው? (ይህን “የሚከላከሏቸው የበሽታ ዓይነቶች”
2. ነጭ ሽንኩርት በምን ያህል ርቀት ላይ በሚለው አምድ ይጻፉ።)
ያለን ባክቴሪያ ይገድላል?*** ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን
በአዳምጦ መረዳት ሥር የቀረበውን
ሌላው ለጤንነት አስፈላጊ የሆነ ምግብ ሻይ
ነው። ሻይ ጥምን ከማርካቱ በላይ በሽታ ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም
ተከላካይ ነው። የካንሰርና የልብ በሽታን ባዳመጣችሁት መሠረት በሽታ ተከላካይ
ይከላከላል። ይህ የሚሆነው ግን ወተት ወይም ምግቦችን በአንድ በኩል፣ የሚከላከሏቸውን
ስኳር ካልተጨመረበት ነው። ስለዚህ ሻይውን የበሽታ ዓይነቶች በሌላ በኩል ዘርዝሩ።
ብቻ መጠጣቱ ይመረጣል። [ተ. በሽታ ተከላካይ ምግቦችንና የሚከላከሏቸውን
ሎሚም እንደሌሎች የምግብ ዓይነቶች የበሽታ ዓይነቶች በቢጋር ሠንጠረዥ ውስጥ
ሁሉ በሽታን ይከላከላል። ለምግብ ስልቀጣ፣ ይዘረዝራሉ።]
ለሥርዓተትንፈሳ፣ ለልብ ጤንነትና ለደም
ዝውውር አስፈላጊ የሆነ ንጥረነገር አለው። ሎሚ፣ መ. አሁን ደግሞ በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን
የቆዳና የሰውነት ህብረህዋሳት ጤናማ ሆነው በአዳምጦ መረዳት ሥር የቀረቡትን የተግባር
እንዲቆዩ ያደርጋል። በመሆኑም በመምጠጥ “2” ጥያቄዎች በቡድን እየተወያያችሁ
ወይም በዕቃ ላይ በመጭመቅ መጠጣት ይቻላል። መልሱ።
በአጠቃላይ ሙዝ፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ሻይ፣ መ.የበሰለ ሙዝ በደም ውስጥ የሚገኝ ቅባት
ሎሚና የመሳሰሉት የምግብ ዓይነቶች የተለያዩ መጠን ለመቀነስ ይችላል?
በሽታዎችን ይከላከላሉ። ምክንያቱም በውስጣቸው
በሽታ ተከላካይ የሆኑ ንጥረነገሮችን በመያዛቸው [ተ. አይችልም]
ነው። ስለዚህ በየቀኑ እንደነዚህ ዓይነት ምግቦችን መ. ለምን?
በመመገብ ጤንነታችንን መጠበቅ እንችላለን።
[ተ. ምክንያቱም በአንቀጽ 2 “ባልበሰለ ሙዝ
(አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ እ.አ.አ ሰኔ 28/2014
መጠነኛ ለውጥ ተደርጎበት የተወሰደ) ውስጥ ያለው አሰር በደም ውስጥ የሚገኝን
የቅባት መጠን ይቀንሳል” ይላል። ስለዚህ
አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ) ሙዝ ሲበስል ሙዝ ውስጥ የሚኖረው የአሰር
እንሥራ መጠን አነስተኛ ስለሚሆን በደም ውስጥ
መ. ከማዳመጣችሁ በፊት በሠንጠረዣችሁ የሚገኘውን ቅባት የመቀነስ ችሎታውን
ከዘረዘራችኋቸው መካከል በምንባቡ ውስጥ ያጣል ማለት ነው።]
የተካተቱን አገኛችሁ? (ተማሪዎች ምላሽ (መ.በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ጥያቄዎች
እንዲሰጡ ያድርጉ።) እንዲመልሱ ያድርጉ።)

፻፲፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 113


ሰዋስው (10 ደቂቃ) እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። “ሀገርን
የተጸውዖ ስሞችን፣ የወል ስሞችንና ከጠላት መጠበቅ የዜግነት ግዴታ ነው።”
ግሶችን መለየት በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረበት
ልሥራ ቃል ምንድን ነው?
መ. በምዕራፍ አንድ ስለወልና ስለተጸውዖ [መተ. የወል ስም፣ ምክንያቱም “ሀገር” የሚለው
ስሞች ተምረን ነበር። የወል ስምን ምንነት ቃል የተለያዩ ሀገሮች ጥቅል መጠሪያ ነው።]
አስታውሳችሁ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
(ተማሪዎች የወል ስምን ምንነት እንዲናገሩ መ. “አስቴር መጽሐፍ ገዛች።” በሚለው
ያድርጉ።) ዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረበት ቃል ከምን
ይመደባል?
መ. ጥሩ፣ [የወል ስም አንድ ዓይነት የሆኑ ነገሮች
በጋራ የሚጠሩበት ስያሜ ነው።] [መተ. ከግስ፣ ምክንያቱም “ገዛች” የሚለው ቃል
በዓረፍተነገሩ መጨረሻ ከመገኘቱም በላይ
መ. ለወል ስሞች ምሳሌ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ? የተፈፀመውን ድርጊት የሚገልጽ ቃል ነው።]
(ተማሪዎች ምሳሌ እንዲናገሩ ያድርጉ።)
ሥሩ
[መ. በሬ፣ ላም፣ ሰው፣ እናት፣ አባት፣ አገር…] መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ በሰዋስው
መ. የተጸውዖ ስምስ ምን እንደሆነ አስታውሳችሁ ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?(ተማሪዎች አዘጋጁ። ከዚያም የተሠመረበት ቃል ግስ
እንዲመልሱ ያድርጉ።) ከሆነ፣ “ግስ” በሚለው አምድ ይህን”√” ምልክት
አድርጉ። የተሠመረበት ቃል የተጸውዖ ስም
[መ.የተጸውዖ ስም የሚባለው የሰው፣ የቦታ፣
ከሆነ “የተጸውዖ ስም” በሚለው አምድ፣ የወል
የወንዝ፣ የባህር፣ የሐይቅ፣ የተራራ፣ የቀን፣
ስም ከሆነ ደግሞ “የወል ስም” በሚለው አምድ
የወር ወዘተ. የግል መጠሪያ የሆነ ቃል ነው።]
የ“√” ምልክት አድርጉ።
መ. ለ ተ ፀ ው ዖ ስም ምሳሌ ልትሰጡኝ
መ.“ፈረሱ ሳር ይግጣል።” በሚለው ዓረፍተነገር
ትችላላችሁ?(ተማሪዎች መልስ እንዲሰጡ
ውስጥ የተሠመረበት ቃል ምንድን ነው?
ያድርጉ።)
[ተ. የወል ስም፣ ምክንያቱም፣ “ፈረሱ” የሚለው
[መ. ሽመልስ፣ መይረማ፣ ራስዳሸን፣ ማክሰኞ፣
ቃል የፈረሶች ሁሉ የጋራ መጠሪያ ስለሆነ
መስከረም…]
ነው።]
መ. “ግስ” በዓረፍተነገር መጨረሻ ላይ የሚመጣና
(መ.ይህን ተግባር ተማሪዎች በግል እንዲሠሩ
ድርጊትን የሚያመለክት ቃል መሆኑን
ያድርጉ። ሠርተው እንደጨረሱ ደብተራቸውን
ከዚህ በፊት ተምረናል። ለምሳሌ፡- “ሕፃኑ
እንዲቀያየሩ ያድርጉ፤ ከዚያም በመልሶቹ
ብርጭቆ ሰበረ።” ብንል “ሰበረ” የሚለው
ላይ ከተማሪዎች ጋር እየተነጋገሩ ርስበርስ
ቃል በዓረፍተነገሩ መጨረሻ በመምጣቱና
እንዲተራረሙ ያድርጉ። በመጨረሻም
ድርጊቱን የሚያመለክት በመሆኑ ግስ ነው።
“ምግቦቻችን” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ
መ. አሁን በዓርፍተነገሮች ውስጥ የወል ስሞችን፣ የተጸውዖና የወል ስሞችን እንዲሁም
የተጸውዖ ስሞችንና ግሶችን እየለየሁ ግሶችን ለይተው እንዲያወጡ የቤትሥራ
አሳያችኋላሁ። ይስጧቸው።)
“መስከረም የአዲስ ዓመት መጀመሪያ ነው።”
በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረበት ቃል
ምንድን ነው?
[መ. የተጸውዖ ስም፣ ምክንያቱም መስከረም
የአንድ የተለየ ወር የግል መጠሪያ የሆነ ስም
ነው።]

114 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፲፬


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
2ኛ ሳምንት
የምግብ አዘገጃጀት ማስታወሻ
ጥያቄ መጠየቅ፡- በማንበብ ሂደት ራስን
ከመከታተያ ስልቶች አንዱ ነው።
4ኛ ቀን በምታነቡበት ጊዜ ጥያቄዎች የምትጠይቁ
የዕለቱ ትምህርት ይዘት ከሆነ፣ ጽሑፉን በጥልቀት እንድታነቡና
እንድትረዱት ያስችላችኋል። ጥያቄ መጠየቅ፣
• ማንበብ ለጥያቄዎቻችሁ ምላሽ እንድትፈልጉ ከማድረጉ
ባሻገር ያነበባችሁትን ማስታወስ እንድትችሉ
ያግዛል። በንባብ ሂደት ከሚነሱ ጥያቄዎች
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) መካከል የሚከተሉት ይገኛሉ።
ሥሩ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ “ምግቦቻችን” ከሚለው

ተስማምቻለሁ? ግር ያለኝ
ምንባብ የተጸውዖና የወል ስሞች እንዲሁም

• ከጸሐፊው/ዋ ሀሳብ ጋር
ግሶችን እንድትለዩ የቤትሥራ ሰጥቻችሁ

ማንበቡ እንደተገባደደ
• ጥያቄዎች አሉኝ?
ነበር። እስኪ መጀመሪያ የተጸውዖ ስሞችን
ንገሩኝ።

• ምን ተሰማኝ?

ነገርስ አለ?
[ተ. በምንባቡ ውስጥ የተጸውዖ ስሞች የሉም።]
መ. በጣም ጥሩ! የወል ስሞችን ንገሩኝ!
[ተ. ጤፍ፣ ስንዴ፣ ገብስ…]
መ. በጣም ጎበዞች! ግሶችን ንገሩኝ!

• ትርጉም ያልሰጠኝ ለምንድን ነው?

መቀነስ ወይስ መጨመር አለብኝ?


[ተ. ያካትታሉ፣ መጥቷል፣ ያመነጫል… ]
(መ. በዚሁ መሠረት መልሳቸውን ይቀበሉ።)
• የማነበው ምንባብ ትርጉም

ማንበብ (35 ደቂቃ)


ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?
• የንባብ ፍጥነቴን

ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
• ያልገባኝ ነገር
ምንድን ነው?
በማንበብ ጊዜ

የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ


ሰጥቶኛል?

ሥሩ
መ. ዛሬ “ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?” በሚል ርዕስ
የቀረበ ምንባብ ታነባለችሁ። ከዚያ በፊት ግን
የቅድመንባብ ጥያቄ ትመልሳላችሁ።
የማውቀው ምንድን ነው?
• ከዚህ ጽሑፍ ምን ጥቅም
• ይህን ጽሑፍ የማነበው

መ. ዳቦ ለመጋገር ምን ምን ነገሮች የሚያስፈልጉ


ይመስላችኋል?
• ስለዚህ ርዕሰጉዳይ
ለምንድን ነው?
ከማንበብ በፊት

[ተ. ዱቄት፣ ውኃ፣ ጨው፣ እርሾ]


አገኛለሁ?

፻፲፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 115


ልሥራ አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)
መ. ዛሬ ተግባራዊ የምታደርጉት የንባብ ሂደት እንሥራ
ራስን የመከታተያ ስልት ጥያቄ መጠየቅ መ. በጣም ጥሩ! አሁን በመጽሐፋችሁ የቀረቡትን
ነው። ስለዚህም አንድን ምንባብ ማንበብ የአንብቦ መረዳት ተግባራት እንሠራለን።
ከመጀመራችን በፊት “ስለርዕስጉዳዩ ከዚህ በሠንጠረዡ ውስጥ ዳቦ ለማዘጋጀት
በፊት የማውቀው ምንድን ነው?” በማነብበት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችና ጠቀሜታዎች
ጊዜ “ያልገባኝ ነገር ምንድን ነው?” አንብበን ተዘርዝረው ቀርበዋል። ጠቀሜታዎቹን
ስንጨርስ ደግሞ “ምን ጥያቄዎች አሉኝ?”፣ ከግብዓቶቹ ጋር በማዛመድ ይህን“√” ምልክት
“ስለምንባቡ ምን ተሰማኝ?” የመሳሰሉ እናደርጋለን።
ጥያቄዎችን ራሳችንን በመጠየቅ ምንባቡን
የምናነብበት ስልት ነው። መ. “የዳቦውን ጣዕም ያሻሽላል” የተባለው
ምንድን ነው?
መ. የመጠየቅ ስልትን እንዴት ተግባራዊ
እንደምታደርጉ አንድ ምሳሌ ሠርቼ [መተ. ጨው] (“ጨው” በሚለው ሥር
ላሳያችሁ። የምንባቡ ርዕስ “ዳቦ ከምን ከምን ይህን”√”ምልክት ያድርጉ።)
ይዘጋጃል?” ይላል። ስለዚህ “ዳቦ ከምን ሥሩ
እንደሚዘጋጅ ከዚህ ቀደም ምን አውቃለሁ?” መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን በአንብቦ
[መ. ለዳቦ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ዱቄት፣ ውኃ፣ መረዳት ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
ጨው ወዘተ. መሆናቸውን አውቃለሁ።] በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም በሠንጠረዡ
ቁልቁል የተዘረዘሩትን መረጃዎች በማንበብ
መ. ከዚህ ምንባብ ማወቅ የምፈልገው ምንድን
አግድም ከተዘረዘሩት ግብዓቶች ሥር የ“√”
ነው?
ምልክት አድርጉ።
[መ. እያንዳንዱ ግብዓት በምን ያህል መጠን
መ. የተቃጠለ አየርና አልኮል በማስወጣት ሊጡ
መጨመር አለበት?]
እንዲነፋ የሚያደርገው ምንድን ነው?
መ. በማነብበት ጊዜ ለጠየቅሁት ጥያቄ ምላሽ
[ተ. እርሾ]
ለማግኘት መጣር ይኖርብኛል።
መ. ስለዚህ “እርሾ” በሚለው አምድ ይህን“√”
ሥሩ ምልክት አድርጉ።
መ. “ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?” የሚለውን
ምንባብ በምታነቡበት ጊዜ፣ በአዕምሯችሁ (መ.ተማሪዎች ከሠሩ በኋላ ደብተራቸውን
ውስጥ የሚመላለሱትን ጥያቄዎች እንዲቀያየሩ አድርገው ርስበርስ
በደብተራችሁ ጻፉ። አንብባችሁ ስትጨርሱ እንዲተራረሙ ያድርጉ። ከዚያም የተግባር
ጥያቄዎቻችሁን ተመልከቱ። ካነበባችሁት 2 ጥያቄዎችን እየጠየቁ ተማሪዎች በቃል
በመነሳት ጥያቄዎቻችሁን ለመመለስ እንዲመልሱ ያድርጉ። በመጨረሻም
ሞክሩ። (ጥያቄዎቻቸውንና መልሶቻቸውን አጫጭር ማብራሪያዎችን በማከል
የሚከተለውን ሠንጠረዥ በደብተራቸው ግብረመልስ ይስጡ።)
በማዘጋጀት መጻፍ እንደሚችሉ ይንገሯቸው።
መልስ ያላገኙላቸው ጥያቄዎች ቢኖሩ
ርስበርስ ተወያይተው እንዲመልሱ 3 ደቂቃ
ይስጧቸው።)

ጥያቄዎች መልሶች
ይህን ምንባብ የማነበው
ለምንድን ነው?
ያልገባኝ ነገር ምንድን
ነው?
ጥያቄዎች አሉኝ?

116 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፲፮


መጻፍ (30 ደቂቃ)
5ኛ ቀን ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ዋናና መዘርዝር ሀሳቦችን በመጠቀም
• ቃላት አንቀጽ መጻፍ
• መጻፍ ሥሩ
መ. ባለፈው ሳምንት የበሽታ ዓይነቶችን በዋናና
መዘርዝር ሀሳቦች ስልት የቢጋር ሠንጠረዥ
ቃላት (10 ደቂቃ) አዘጋጅታችኋል። ዛሬ ባዘጋጃችሁት የቢጋር
ሠንጠረዥ መሠረት አንድ አንቀጽ
የቃላት ተመሳሳይና ዐውዳዊ ፍቺ ትጽፋላችሁ።
ሥሩ (መ. ተማሪዎች ሲጽፉ እየተዘዋወሩ በአግባቡ
መ. ዛሬ ከምንባቡ የወጡ ቃላትን ከተመሳሳይ እየሠሩ መሆኑን ይከታተሉ። መንደርደሪያ
ፍቻቸው ጋር ታዛምዳላችሁ። ሀሳብ በመስጠት፣ ጠቋሚ ጥያቄዎች
መ. “ግብዓት” ለሚለው ቃል በ“ለ” ረድፍ በመጠየቅ ተማሪዎች እንዲጽፉ ያበረታቱ።
ከተዘረዘሩት መካከል ተመሳሳይ ፍቹ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ድጋፍ
የትኛው ነው? ያድርጉ።)
[ተ. አስፈላጊ ነገር] የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
መ. ስለዚህ መልሱ የሚገኝበት ፊደል የትኛው የይዘት/የአንድ ነጥብ (.) አገልግሎት
ነው? ልሥራ
[ተ. ለ] መ. ባለፈው ሳምንት ከአንድ ነጥብ አገልግሎት
መካከል ሁለቱን ተመልክተናል። አንድን
መ. ጥሩ!
ቃል አሳጥሮ ለመጻፍ የሚቻልበት አንዱ
(መ. ቀሪዎቹን ቃላት ለማዛመድ 5 ደቂቃ መንገድ ምንድን ነው?
ይስጧቸው። በደብተራቸው ሠርተው
እንደጨረሱ ተማሪዎች ርስበርስ እየተጠያየቁ [መ. የቃሉን የመጀመሪያ ፊደላት በመጠቀም
መልስ እንዲሰጡ ያድርጉ። ይህን ተግባር አሳጥሮ መጻፍ]
እንደጨረሱ ወደሁለተኛው ተግባር መ. ሌላኛው አንድን ቃል አሳጥሮ መጻፍ
ይሸጋገሩ።) የሚቻልበት መንገድስ?
መ. አሁን ደግሞ ከምንባቡ ለወጡ ቃላትና [መ. የቃሉን የመጀመሪያና የመጨረሻ ፊደላት
ሐረጋት ዐውዳዊ ፍቻቸውን ትሠጣላችሁ። በመጠቀም አሳጥሮ መጻፍ]
መ. “ደባል ነገሮች” በሚል በአንቀጽ 2 መ. ዛሬ ደግሞ ተጨማሪ የአንድ ነጥብን
የተመለከተው ሐረግ በምንባቡ ውስጥ ያለው አጠቃቀም እንመለክታለን። ሌላው የአንድ
ፍቺ ምንድን ነው? ነጥብ አገልግሎት ጥምር ቃላትን አሳጥሮ
መጻፍ ነው። ጥምር ቃልን ስናሳጥር፣ ጥምር
[ተ. ቆሻሻ፣ አላስፈላጊ ነገሮች]
ቃሉን የገነቡትን ሁለት ቃላት የመጀመሪያ
(መ. ቀሪዎቹን በግል በደብተራቸው እንዲሠሩ ፊደላት በመውሰድ፣ ከፊደላቱ ቀጥሎ
የቤትሥራ ይስጧቸው። አንድ ነጥብን ተጠቅሞ አሳጥሮ መጻፍ
ነው። ለምሳሌ “ዓመተምህረት” የሚለውን
ጥምርቃል “ዓ.ም.” ብሎ አሳጥሮ መጻፍ
ይቻላል።
መ. ከአንድ ቃል በላይ ያለውን ስም ለማሳጠር፣
በስሙ ውስጥ የሚገኙትን ቃላት የመጀመሪያ

፻፲፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 117


ፊደላት በመውሰድ ከእያንዳንዱ ፊደል ተግባር “2” ሥር ከምንባቡ ለወጡ ቃላት
ቀጥሎ አንድ ነጥብን በመጠቀም አሳጥሮ ዐውዳዊ ፍቺ እንድትሰጡ የቤትሥራ
መጻፍ ይቻላል። ለምሳሌ “የአማራ ብሔራዊ ሰጥቻችሁ ነበር። የሰጣችሁትን ፍቺ ንገሩኝ።
ክልላዊ መንግሥት” የሚለውን ስያሜ “ደባል ነገሮች” የሚለው ሐረግ ዐውዳዊ ፍቺ
“አ.ብ.ክ.መ.” ብሎ ማሳጠር ይቻላል። ምንድን ነው።?
እንሥራ [ተ. ቆሻሻ/አላስፈላጊ ነገሮች ማለት ነው።]
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሠራለን። “ትምህርት (መ. ሌሎችንም በዚሁ ዓይነት ያሠሯቸውን።
ሚኒስቴር” የሚለውን ቃል አሳጥረን እንጻፍ። ከዚያም ትክክለኛውን መልስ በመስጠት
[መተ. ት.ሚ.] ግብረመልስ ይስጡ።)
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ “አማራ ብድርና ቁጠባ
ተቋም” የሚለውን ስም አሳጥረን እንጻፍ።
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
[መተ. አ.ብ.ቁ.ተ.] ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?
ሥሩ ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
መ. አሁን ደግሞ በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን ሥሩ
በአጻጻፍ ሥርዓት ሥር የቀረቡትን ጥምር መ. ዛሬ ድምፅ እያሰማችሁ የማንበብ ልምምድ
ቃላትና ከአንድ ቃል በላይ ያላቸውን ስሞች ታደርጋላችሁ፤ ከዚያ በፊት ግን ስለምታነቡት
አሳጥራችሁ ጻፉ። ምንባብ ይዘት በማስታወስ አንድ ጥያቄ
መ. “ትምህርትቤት” የሚለውን ጥምር ስም ትመልሳላችሁ።
አሳጥራችሁ ጻፉ። መ. “ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?” በሚል ርዕስ
[ተ. ት.ቤት] ከቀረበው ምንባብ የምታስታውሱትን ተናገሩ።

መ. “አፍሪካ ሕብረት” የሚለውን ስም አሳጥራችሁ [ተ. አስታውሰው ይናገራሉ።]


ጻፉ። ማንበብ (8 ደቂቃ)
[ተ. አ.ሕ.] እንሥራ
(ቀሪዎቹን ስሞች ተማሪዎች በግል በደብተራቸው መ. ባለፈው ሳምንት የጋራ ንባብ ልምምድ
እንዲሠሩ ያድርጉ፤ ከዚያም አንድ አንድ አድርጋችኋል። ዛሬም ይህንኑ ልምምድ
ተማሪዎች እየተነሱ በሰሌዳው ላይ ጽፈው ትቀጥላላችሁ። በመጀመሪያ ግን አብረን
እንዲያሳዩ ያድርጉ። በመጨረሻም እናንብብ። (በምዕራፍ 4፣ በ1ኛው ሳምንት፣
ግብረመልስ ይስጡ።) በ3ኛው ቀን “በእንሥራ” ሥር የቀረበውን
አሠራር በመከተል “ዳቦ እንዴት ይዘጋጃል?”
በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ 1ኛውንና
6ኛ ቀን 2ኛውን አንቀጾች ከተማሪዎች ጋር ድምፅ
እያሰሙ በጋራ ያንብቡ።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• አቀላጥፎ ማንበብ
ሥሩ
መ. “ዳቦ ከምን ከምን ይዘጋጃል?” በሚል ርዕስ
• መናገር ከቀረበው ምንባብ ከ1-3 ያሉትን አንቀጾች
• ሰዋስው በቡድን ሆናችሁ ድምፅ እያሰማችሁ በጋራ
አንብቡ። (አሠራሩን በምዕራፍ 4፣ በ1ኛው
ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን በአቀላጥፎ ማንበብ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) “በሥሩ” ሥር የቀረበውን ይመልከቱ።)
ሥሩ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ በቃላት

118 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፲፰


መናገር (15 ደቂቃ) ክፍል ይጻፉ።)

በዋናና መዘርዝር ሀሳብ ስልት ውይይት መ. ጥሩ! ግስ የሆነ ቃል እንለይ።


ማድረግ [መ. አገዘ] (“ግስ” በሚለው ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)
ሥሩ ሥሩ
መ. አሁን ስለዶሮ ወጥ አሠራር በቡድን መ. አሁን ደግሞ ቀሪዎቹን ቃላት የተጸውዖ ስም፣
ትወያያላችሁ። በምትወያዩበት ጊዜ የወል ስምና ግስ መሆናቸውን እየለያችሁ
ንግግራችሁ የዋናና መዘርዝር ሀሳቦች ስልትን በተመደበላቸው ሳጥን ውስጥ መድቡ።
የተከተለ መሆኑን ልብ በሉ።
መ. ከተዘረዘሩት መካከል የተጸውዖ ስም ንገሩኝ፤
(ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት ባሉት ቡድን
[ተ. ሐረገወይን]
ያደራጇቸው፤ ከዚያም በመማሪያ መጽሐፉ
የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ በደብተራቸው መ. ስለዚህ “ሐረገወይን” የሚለውን ቃል፣
እንዲያዘጋጁ ያድርጉ። በመቀጠል የዶሮ የተጸውዖ ስም በሚለው ሳጥን ውስጥ ጻፉ።
ወጥ ለመሥራት የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፣
(መ. ቀሪዎቹን ቃላት በመጀመሪያ ተማሪዎች
የግብዓቶቹን መጠንና የወጡን አሠራር ሂደት
በግል በደብተራቸው እንዲሠሩ ያድርጉ።
የሚሉትን ሀሳቦች መነሻ በማድረግ እየተወያዩ
ከዚያም ጥንድ ጥንድ ሆነው በሠሩት ላይ
እንዲሞሉ ያድርጉ።)
እንዲወያዩ ያድርጉ። በመጨረሻም ርስበርስ
[ተ. የቢጋር ሠንጠረዡን በደብተራቸው እንዲተራረሙ በማድረግ ግበረመልስ
አዘጋጅተው እየተወያዩ ይሞላሉ] ይስጡ።)
(መ. በመጨረሻም የቡድን ተወካዮች ለክፍሉ
ተማሪዎች የቡድናቸውን ሀሳብ እንዲያቀርቡ
ያድርጉ።)
ሰዋስው (10 ደቂቃ)
የወል ስሞችን፣ የተጸውዖ ስሞችንና
ግሶችን መለየት
ልሥራ
መ. ዛሬ ተቀላቅለው የቀረቡ የተጸውዖና የወል
ስሞችን እንዲሁም ግሶችን ትለያላችሁ።
በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ እኔ
አሳያለሁ። (የቢጋር ሠንጠረዡን በሰሌዳው
ላይ ይሣሉ።)
መ. በመጽሐፋችሁ ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል
“ደመላሽ” የሚል ቃል ይገኛል። ይህ ቃል
ከየትኛው የስም ዓይነት ይመደባል?
[መ. የተጸውዖ ስም] (“የተጸውዖ ስም” ተብሎ
በተከፈለው ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)

እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሠራለን። የወል
ስም የሆነ ቃል ከተዘረዘሩት መካከል ለይተን
እናውጣ።
[መተ. ተራራ] (“የወል ስም” በሚለው የሳጥን

፻፲፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 119


ማንበብ (30 ደቂቃ)
3ኛ ሳምንት
የተመጣጠነ ምግብ የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
7ኛ ቀን የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ሥሩ
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በቅድመንባብ
• የቃላት ጥናት ሥር በአበባ ምሥል የቀረበውን የቢጋር
• ማንበብ ሠንጠረዥ በደብተራችሁ ሣሉ። ከዚያም
“የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም” በሚል
ከቀረበው ምንባብ ያሉትን ሥዕሎች በሚገባ
አስተውሉ። ቀጥሎ በሥዕሉ ውስጥ ያሉትን
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) ምግቦች ገንቢ፣ ሙቀትና ኃይል ሰጪና
በሽታ ተከላካይ መሆናቸውን በመለየት
መነጠልና ማጣመር በቢጋር ሠንጠረዡ ውስጥ አስፍሩ።
ሥሩ 15ለ. የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን “በቃላት
ጥናት” ሥር “የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም” ሥሩ
በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ የወጡ (መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ።)
ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን፣ በማንበብ
በማጣመር አንብቡ።
ሂደት ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
መ. “ካሎሪ የሚለውን ቃል በመነጣጠል አንብቡ። በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከርዕሱና
ከሥዕሎቹ በመነሳት ወደአዕምሯችሁ
[ተ. ካ-ሎ-ሪ]
የመጡ ጥያቄዎችን በሠንጠረዡ ውስጥ
መ. አሁን ደግሞ በማጣመር አንብቡ! አስፍሩ። ከዚያም ለጥያቄዎቻችሁ ምላሽ
ለማግኘት እየጣራችሁ አንብቡ። ስታነቡ
[ተ. ካሎሪ]
ያልገባችሁን (ጥያቄያችሁን) በሠንጠረዡ
መ. በጣም ጥሩ! ውስጥ መዝግቡ። ይህንን እያደረጋችሁ
(መ. ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት ባላቸው ቡድኖች በግል በለሆሳስ አንብቡ።
ያደራጁ። ከዚያም በቡድን መሪ አማካይነት [ተ. በለሆሳስ በግል ያነባሉ።]
ቀሪዎቹን በ“ሀ”ና በ“ለ” ሥር ያሉትን ቃላትና
ሐረጋት እየነጠሉና እያጣመሩ እንዲያነቡ (መ. እስከአምስተኛው አንቀጽ አንብበው
ያድርጉ። ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ እንደጨረሱ ያስቁሟቸው።)
በትክክል ማንበባቸውን ይከታተሉ። ከዚያም መ. አሁን በማንበብ ሂደት ያልገባችሁን ነገር
ከየቡድኑ አንድ አንድ ተማሪዎች ድምፃቸውን ጓደኛችሁን ጠይቁ። የተጠየቃችሁ ተማሪዎች
በማሰማት ቃላቱን ለክፍሉ ተማሪዎች የገባችሁን ነገር ለጓደኛችሁ አስረዱ። እንዴት
እንዲያነቡ ያድርጉ። በትክክል ያልተነበቡ እንደተረዳችሁትም ንገሯቸው። (መላሾችም
ቃላትን በትክክል በማንበብ ግብረመልስ በተራቸው ያልገባቸውን ጠይቀው እንዲረዱ
ይስጡ።) ያድርጉ።)
[ተ. ባልገቧቸው ነጥቦች ላይ ይወያያሉ።] (ለ2
ደቂቃ ያህል እንዲወያዩ ያድርጉ።)
መ. አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ።
[ተ. በግል በለሆሳስ ያነባሉ።]

120 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፳


(መ. አንብበው እንደጨረሱ ባልገቧቸው ነጥቦች (መ.ተማሪዎች ቀሪዎቹን ጥያቄዎች
ላይ እየተጠያየቁ እንዲወያዩ ያድርጉ።) የሚመልሱበት 8 ደቂቃ ሰጥተው በመጀመሪያ
በግላቸው እንዲሠሩ ያድርጉ። በመጨረሻም
15ሐ. አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ) ጥያቄዎቹን እየጠየቁ ከየቡድኑ አንድ አንድ
ሥሩ ተማሪዎች ምላሽ እንዲሰጡ አድርገው
መ. በምታነቡበት ጊዜ ባልገቧችሁ ነጥቦች ላይ ያጠቃሉ።)
ተወያዩ። ልሥራ
[ተ. ይወያያሉ።] መ. በተግባር “3” ሥር ቋሚ ግራፍ ቀርቧል።
ግራፉ “የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም” በሚል
መ. በጣም ጥሩ! በውይይታችሁ ልትመልሷቸው
ርዕስ ከቀረበው ምንባብ ውስጥ በሚገኘው
ያልቻላችኋቸውን ጥያቄዎች ንገሩኝ።
ሠንጠረዥ ላይ የተመሠረተ ነው። ግራፉ
[ተ. የከበዷቸውን ጥያቄዎች ይናገራሉ።] በሠንጠረዡ ውስጥ የሚገኙት ልዩ ልዩ
(የተጠየቁትን ጥያቄዎች የክፍሉ ተማሪዎች የምግብ እህል ዓይነቶች የያዙትን የ“ኘሮቲን”
እንዲመልሱ ያድርጉና ያልተመለሱትን መጠን ያሳያል። (በ2 ደቂቃ ውስጥ አሠራሩን
እርስዎ በመመለስ ያጠቃሉ።) ካሳዩ በኋላ ለ9ኛው ቀን የቤትሥራ ይስጡ።)
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በአንብቦ መ. ለምሳሌ በግራፉ ላይ የሚታየው የመጀመሪያው
መረዳት ሥር የቀረበውን ተግባር “1” ሥሩ። ቋሚ የሚያመለክተው ቍጥር ስንት ነው?
በ“ሀ” ረድፍ የተዘረዘሩትን አንቀጾች በ“ለ”
[መ. 11.1]
ረድፍ ከተዘረዘሩት የአንቀጾቹ ዋና ሀሳብ
ጋር አዛምዱ። መ. በሠንጠረዡ ውስጥ ከተዘረዘሩት የምግብ
እህል ዓይነቶች የኘሮቲን መጠኑ 11.1
መ. የአንቀጽ 1 ዋና ሀሳብ ምንድን ነው?
የሆነው የትኛው ነው?
[ተ. የተመጣጠነ ምግብ ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ
[መ. ነጭ ጤፍ]
ንጥረምግቦች የያዘ ነው።]
መ. ስለዚህ የመጀመሪያውን ቋሚ በሚወክለው
መ. በጣም ጥሩ! ይህን ዓረፍተነገር የያዘው ፊደል
‘ሀ’ ፊት ለፊት “ነጭ ጤፍ” ብዬ እጽፋለሁ።
የትኛው ነው።
[ተ. ለ]
ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ እናንተ ትሠራላችሁ፤ ግራፉንና
(መ. ተማሪዎች ቀሪዎቹን የሚሠሩበት 5 ደቂቃ በሠንጠረዡ ውስጥ የቀረበውን መረጃ
ሰጥተው ርስበርስ እንዲተራረሙ አድርገው በማገናዘብ፣ በግራፉ የሚገኙት ቋሚዎች
ካጠቃለሉ በኋላ ወደሚቀጥለው ተግባር የሚወክሉትን የምግብ እህል ዓይነት
ይሸጋገሩ።) በምሳሌው መሠረት ጻፉ።
ሥሩ መ. በግራፉ ላይ ሁለተኛው ቋሚ የሚያመለከተው
መ. ተማሪዎች አሁን ደግሞ ሠንጠረዡን ስንት ቊጥር ላይ ነው?
መሠረት በማድረግ የተግባር “2”ን ጥያቄዎች
[ተ. 4.1]
በጽሑፍ መልሱ። በሠንጠረዡ ከተዘረዘሩት
ከፍተኛ የካርቦሃይድሬት መጠን ያለው መ. በሠንጠረዡ ውስጥ ከተዘረዘሩት የምግብ
ምግብ የትኛው ነው? እህል ዓይነቶች የኘሮቲን መጠኑ 4.1 የሆነው
የትኛው ነው?
[ተ. ገብስ]
[ተ. ነጭ ሽንኩርት]
መ. ለምን?
መ. ስለዚህ ሁለተኛውን ቋሚ በሚወክለው “ለ”
[ተ. ምክንያቱም የገብስ የካርቦሃይድሬት መጠን
ፊት ለፊት “ነጭ ሽንኩርት” ብላችሁ ጻፉ።
75.4 ግራም መሆኑ በሠንጠረዡ ተጥቅሷል።]
መ. በጣም ጥሩ

፻፳፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 121


መገምገምያ ሠንጠረዥ በወረቀት አዘጋጁ።
8ኛ ቀን [ተ. የጽሑፉን መገምገምያ ሠንጠረዥ በወረቀት
ያዘጋጃሉ።]
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መ. አንዳችሁ ስታነቡ አንዳችሁ በሠንጠረዡ
• ቃላት ውስጥ የ“ ” ምልክት እያደረጋችሁ
• መጻፍ ተከታተሉ።
[ተ. አንዳቸው ሲያነቡ አንዳቸው በሠንጠረዡ
ውስጥ የ“ ” ምልክት እያደረጉ ይከታተላሉ።]
ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. አሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ሲያነቡ
ቃላትንና ሐረጋትን በዓረፍተነገር ውስጥ ለነበሩት ማስተካከል ያለባቸውን ንገሯቸው።
መጠቀም [ተ. በተሰጣቸው አስተያየት መሠረት
ሥሩ አስተካክለው ይጽፋሉ።]
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን በቃላት (መ. በዚህ ዓይነት ሚናቸውን በመቀያየር
ሥር “የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም” በሚል እንዲሠሩ ያድርጉ። በመጨረሻም የተወሰኑ
ርዕስ ከቀረበው ምንባብ የወጡ ቃላት ድርሰቶችን መርጠው ለክፍሉ ተማሪዎች
ተዘርዝረዋል። ከቃላቱም ሥር ያልተሟሉ እንዲነበቡ ያድርጉ።)
ዓረፍተነገሮች ቀርበዋል። ቃላቱን በተገቢ
ቦታቸው በማስገባት ዓረፍተነገሮቹን የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
አሟልታችሁ ጻፉ።
የአንድ ነጥብ (.) አጠቃቀም
መ. በሳጥኑ ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል እንሥራ
“------ ተግባርን ለማከናወን ጤነኛ መሆን
መ. ባለፉት ሁለት ሳምንታት ስለአንድ ነጥብ
ያስፈልጋል።” የሚለውን ዓረፍተነገር
አጠቃቀም ተምራችኋል። ዛሬም በአንድ
የሚያሟላው የትኛው ነው?
ነጥብ አጠቃቀም ላይ ያተኮሩ ተግባራት
[ተ. የዕለትተዕለት] ትሠራላችሁ። በመጀመሪያም አጥረው
የተጻፉ ቃላትን ወይም መጠሪያዎችን
መ. በጣም ጥሩ! ሐረጉን በዓረፍተነገሩ ውስጥ
ዘርዝረን እንጽፋለን። “አ.አ.ዩ.” የሚለውን
አስገብታችሁ ጻፉ።
አህፅሮተቃል ዘርዝረን እንጻፈው።
(መ. ተማሪዎች ተግባሩን በግል እንዲሠሩ
ያድርጉ። ቀጥሎ ደብተራቸውን ተቀያይረው [መተ. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ]
ርስበርሳቸው እንዲተራረሙ ያድርጉ።) መ. አሁን ደግሞ “የዓለም ቀይ መስቀል ማህበር”
የሚለውን መጠሪያ አሳጥረን እንጻፍ።
መጻፍ (30 ደቂቃ) [መተ. ዓ.ቀ.መ.ማ.]
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) ሥሩ
በዋናና መዘርዝር ሀሳብ አጻጻፍ ስልት መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን በአጻጻፍ
የተጻፈ አንቀጽ መከለስ ሥርዓት ሥር የአንድ ነጥብን አጠቃቀም
በሚመለከት የቀረበውን ተግባር ሥሩ።
ሥሩ በተግባሩ ሥር ሁለት ጥያቄዎች አሉ።
መ. ባለፈው ሳምንት ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በመጀመሪያ አጥረው የተጻፉትን ዘርዝራችሁ
የበሽታ ዓይነቶችን በተመለከተ በዋናና ጻፉ። በመቀጠል ደግሞ ተዘርዝረው
መዘርዝር ሀሳቦች የአጻጻፍ ስልት አንድ የተጻፉትን መጠሪያዎች አሳጥራችሁ ጻፉ።
አንቀጽ ጽፋችኋል። ዛሬ ደግሞ የጻፋችሁትን
መ. “ተ.መ.ድ.” የሚለውን አህፅሮተቃል
አንቀጽ እንደገና አስተካክላችሁ ትጽፋላችሁ።
ዘርዝራችሁ ጻፉ።
መ. በመጽሐፋችሁ ላይ ያለውን የጽሑፍ

122 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፳፪


[ተ. የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት] አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
(መ. የቀሩትንም በተራ ቊጥር 1 የቀረቡትን
በዚህ ዓይነት ያሠሩ።)
የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ በተራቊጥር 2
የቀረቡትን ሥሩ። “የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ” ሥሩ
የሚለውን ስያሜ አሳጥራችሁ ጻፉ። መ. ዛሬ አቀላጥፎ የማንብብ ልምምድ
ታደርጋላችሁ። ከዚያ በፊት ግን ባለፈው
[ተ. ኢ.ን.ባ.]
ሳምንት ያነበባችሁትን ምንባብ በማስታወስ
መ. በጣም ጥሩ! ያህል የሚከተለውን ጥያቄ መልሱ።
(መ. ቀሪዎቹን ተማሪዎች በግል እንዲሠሩ መ. የተመጣጠነ ምግብ አለመመገብ ምን
ያድርጉ። ከዚያም በቡድን ደብተራቸውን ጉዳት ያለው ይመስላችኋል? (ተማሪዎች
በመቀያየር እየተወያዩ ርስበርስ እንዲተራረሙ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ያድርጉ።)
[ተ. አስታውሰው ይናገራሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ወደማንበቡ እንሸጋገር።
9ኛ ቀን
ማንበብ (8 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ሥሩ
• አቀላጥፎ ማንበብ መ. ዛሬም “የተመጣጠነ ምግብ ጥቅም” በሚል
• መናገር ርዕስ ከቀረበው ምንባብ የመጀመሪያዎቹን
አምስት አንቀጾች በቡድን ሆናችሁ በጋራ
• ሰዋስው
ታነባላችሁ።
(መ. ተማሪዎችን ከ4-6 አባለት ባሏቸው ቡድኖች
ያደራጁ። ከዚያም የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) አንቀጾች በጋራ እንዲያነቡ ይንገሯቸው።
ሥሩ ተማሪዎች ሲያነቡ ቃላትን በትክክል
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ በግራፉ ውስጥ ያሉት መጥራታቸውን፣ ሥርዓተነጥቦችን ጠብቀው
ቋሚዎች የሚወክሉትን የምግብ ዓይነት ማንበባቸውን፣ እኩል ድምፅ ማውጣታቸውን
እንድትጽፉ የቤትሥራ ሠጥቻችሁ ነበር። ይገምግሙ።)
የሠራችሁትን ትነግሩኛላችሁ። በግራፉ [ተ. በጋራ በመሆን በአንድ ላይ ያነባሉ።]
ሦስተኛው ቋሚ የሚያመለክተው ቍጥር
ስንት ነው? መናገር (15 ደቂቃ)
[ተ. 0.7] ሀሳብን በቢጋር ሠንጠረዥ አደራጅቶ
መ. በጣም ጥሩ! የኘሮቲን መጠኑ 0.7 ግራም መናገር
የሆነው የምግብ ዓይነት ምንድን ነው? ሥሩ
[ተ. ብርቱካን] መ. አሁን በአካባቢያችሁ የሚመረቱ ምርቶችን
መሠረት በማድረግ ንግግር ታደርጋላችሁ።
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ተማሪዎች በመጀመሪያ በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው
እንዲመልሱ ያድርጉ። ስህተቶቹን ቀን በመናገር ሥር የቀረበውን የቢጋር
በማስተካከል ያጠቃሉ።) ሠንጠረዠ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ቀጥሎ
በአካባቢያችሁ የሚመረቱ የምግብ እህሎችን፣
ፍራፍሬና አትክልቶችን እንዲሁም
የእንስሳት ተዋጽኦዎችን ገንቢ፣ ኃይልና
ሙቀት ሰጪ ወይም በሽታ ተከላካይ

፻፳፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 123


መሆናቸውን እየለያችሁ በቢጋር ሠንጠረዡ
ውስጥ መድቡ። ከዚያም ቁርስ፣ ምሳና እራት
ምን ምን ብትመገቡ የየዕለት አመጋገባችሁ
የተመጣጠነ እንደሚሆን ለጓደኞቻችሁ
ተናገሩ።
(መ. በመጀመሪያ ተማሪዎችን በአነስተኛ ቡድን
አደራጅተው ተግባሩን ያሠሩ።)
[ተ. ተማሪዎች በቢጋር ሠንጠረዥ ያዘጋጁትን
መሠረት አድርገው ለየቡድናቸው ይናገራሉ።]
(መ. ተማሪዎች ሲናገሩ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ
የሀሳብ አደረጃጀታቸውን፣ በተሰጣቸው ርዕስ
ላይ ማተኮራቸውንና የድምፃቸውን ተሰሚነት
ይገምግሙ።)

ሰዋስው (10 ደቂቃ)


የወል ስምን፣ የተጸውዖ ስምንና ግሶችን
መለየት
ሥሩ
መ. ተማሪዎች! በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን
የተጸውዖ ስሞች፣ የወል ስሞችና ግሶች
በሳጥን ውስጥ ተዘርዝረዋል። እነዚህን ቃላት
በተገቢ ቦታቸው በማስገባት ዓረፍተነገሮችን
አሟልታችሁ ጻፉ።
መ. በሳጥኑ ውስጥ ከተዘረዘሩት የተጸውዖ ስሞች፣
የወል ስሞችና ግሶች መካከል “በ----------
---ወር ዝናብ-----------------።” የሚለውን
ዓረፍተነገር የሚያሟሉት ቃላት ምንና ምን
ናቸው?
[ተ. ነሐሴና ይበዛል።]
መ. ጥሩ! ቃላቱን በክፍት ቦታው አስገብታችሁ
ዓረፍተነገሩን ጻፉ።
[ተ. በነሐሴ ወር ዝናብ ይበዛል።]
(መ. ቀሪዎቹን በመጀመሪያ በግል እንዲሠሩ
ያድርጉ። ከዚያም ጥንድ ጥንድ በመሆን
ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ
እንዲተራረሙ ያድርጉ።)

124 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 6 ፻፳፬


ምዕራፍ 7 የዱር እንስሳት በኢትዮጵያ
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• “የዱር እንስሳት በኢትዮጵያ” በሚል የምንባብ ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው
የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት በንግግርና በጽሑፍ ይጠቀማሉ፤
• በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት ድርሰት ይጽፋሉ፤
• በጽሑፋቸው ውስጥ ይዘትን (አንድ ነጥብን) ይጠቀማሉ፤
• በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት የተዋቀሩ ምንባቦችን አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• “የዝንጀሮዎች አኗኗር” በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• “የዱር እንስሳት በኢትዮጵያ” በሚል የምንባብ ይዘት መነሻነት ይናገራሉ፣
• የዓረፍተነገርን ሰዋስዋዊ ባለቤት ይለያሉ።

መ. “የሚታወቁባቸው” የሚለውን ሐረግ


1ኛ ሳምንት የዱር እንስሳት በመነጣጠል አንብቡ!
[ተ. የሚ-ታወቁ-ብ-ኣቸው]
1ኛ ቀን መ. አሁን ደግሞ ይህኑ ሐረግ በማጣመር
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች አንብቡ።

• የቃላት ጥናት [ተ. የሚታወቁባቸው]


• ማንበብ (መ. ተማሪዎችን በጥንድ በጥንድ አደራጅተው
ቀሪዎቹን ቃላትና ሐረጋት በመነጠልና
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) በማጣመር እንዲያነቡ ያድርጉ።)

መነጠልና ማጣመር ማንበብ (30 ደቂቃ)


ሥሩ
የአጋዘን አስተኔ
መ. “የአጋዘን አስተኔ” በሚል ርዕስ ከቀረበው
ምንባብ የወጡትን ቃላትና ሐረጋት ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
በመነጠልና በማጣመር አንብቡ። የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
መ. “ውድንቢ” የሚለውን ቃል በመነጣጠል ልሥራ
ፊደል በፊደል አንብቡ!
መ. ዛሬ “የአጋዘን አስተኔ” በሚል ርዕስ የቀረበ
[ተ. ው-ድ-ን-ቢ] ምንባብ ታነባላችሁ። በቅድሚያ ግን ጥቂት
የቅድመንባብ ጥያቄ ትመልሳላችሁ። እንዴት
መ. ጎበዞች! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል በማጣመር
እንደምትሠሩ አንድ ምሳሌ እሰጣለሁ።
አንብቡ!
[ተ. ውድንቢ] (መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በቅድመንባብ
ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ
መ. በጣም ጥሩ!

፻፳፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 125


ይሣሉላቸው።) የደጋአጋዘን በሚለው ንዑስ ርዕስ ያሉትን
መ. ስለአጋዘን ዝርያዎች ከዚህ በፊት ምን አንቀጾች ካነበቡ በኋላ ያስቁሙ።)
አውቃለሁ? መ. በቅድመንባብ ላይ “ማወቅ የምፈልገው”
[መ. የአጋዘን ዝርያዎች የዱር እንስሳ መሆናቸውን በሚለው ሥር ከመዘገባችኋቸው ጥያቄዎች
አውቃለሁ።] (“የማውቀው” በሚለው አምድ እስካሁን ባነበባችኋቸው አንቀጾች
ይጻፉ።) የተመለሱ አሉ?

መ. ስለአጋዘን ማወቅ የምፈልገው ምንድን ነው? [ተ. በጥንድ ሆነው በቅድመንባብ ላይ ባነሷቸው
ጥያቄዎችና ከአንቀጾቹ ባገኟቸው መልሶች
[መ. አጋዘን አስተኔዎች ምን ይመገባሉ?] ላይ ይወያያሉ።]
(“ማወቅ የምፈልገው” በሚለው የሠንጠረዡ (መ. ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።
አምድ ይጻፉ።) ከዚያም “ድኩላ” በሚለው ንዑስ ርዕስ ሥር
ሥሩ የቀረቡትን አንቀጾች አንብበው እንደጨረሱ
መ. ባሳየኋችሁ ምሳሌ መሠረት ስለአጋዘን ያስቁሟቸው።)
ዝርያዎች የምታውቁትን “የማውቀው” መ. አሁንስ በቅድመንባብ ካነሳችኋቸው ጥያቄዎች
በሚለው የሠንጠረዥ አምድ ዘርዝሩ። በዚህኛው ንዑስ ርዕስ ሥር በቀረቡት
ስለአጋዘን ዝርያዎች ማወቅ የምትፈልጉትን አንቀጾች ውስጥ የተመለሱ አሉ?
ደግሞ “ማወቅ የምፈልገው” በሚለው
የሠንጠረዡ አምድ ዘርዝሩ። አንብባችሁ [ተ. በጥንድ ሆነው በቅድመንባብ ላይ ባነሷቸው
እንደጨረሳችሁ ደግሞ ሦስተኛውን አምድ ጥያቄዎችና ከ2ኛው ንዑስ ርዕስ (ድኩላ)
ትሞላላችሁ። ባገኟቸው መልሶች ላይ ይወያያሉ።]

(መ. “ማወቅ የምፈልገው” በሚለው የሠንጠረዡ (መ. ከዚያም ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)
አምድ፣ አጋዘኖች ምን ይመገባሉ፣ የት አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
አካባቢ ይኖራሉ፣ በምን ይመሳሰላሉ/
ይለያያሉ? የሚሉ ጥያቄዎች ማስፈር ልሥራ
እንደሚችሉ ይጠቁሟቸው።) መ. አሁን ምንባቡን አንብባችሁ ጨርሳችኋል።
በመጀመሪያ በቅድመንባብ ላይ ባዘጋጀሁት
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) ሠንጠረዥ ውስጥ “ከምንባቡ የተማርኩት”
ልሥራ በሚለው የሠንጠረዡ አምድ ስለአጋዘን
መ. በቅድመንባብ ላይ ባዘጋጀሁት ሠንጠረዥ አስተኔዎች የተማራችኋቸውን ነገሮች
ውስጥ ስለአጋዘን አስተኔዎች ማወቅ ዘርዝሩ። አሁን የአንብቦ መረዳት ተግባር
የምፈልገውን ጽፌ ነበር። በማነብበት ጊዜ ትሠራላችሁ። በቅድሚያ ግን ተግባሩን
ለጥያቄዬ ከምንባቡ መልስ ለማግኘት እንዴት እንደምትሠሩ ላሳያችሁ። (በ1ኛው
እሞክራለሁ። (የመጀመሪያውን አንቀጽ ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በአንብቦ መረዳት ሥር
ድምፅዎን እያሰሙ ያንብቡላቸው።) የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ
ይሣሉ።)
መ. ካነበብኩት አንቀጽ ሁሉም የአጋዘን
አስተኔዎች ቅጠላቅጠል እንደሚበሉ መ. በመጀመሪያ የእያንዳንዱን የአጋዘን አስተኔ
ተረድቻለሁ። ስለዚህ “ቅጠላቅጠል ዝርያ የቀንድ ሁኔታ እንመልከት። ከሴቶቹና
ይመገባሉ” የሚል ከምንባቡ የተማርኩት ከወንዶቹ የደጋ አጋዘን ቀንድ ያላቸው
በሚለው የሠንጠረዥ አምድ እጽፋለሁ። የትኞቹ ናቸው?

ሥሩ [መ. ወንዶቹ] (ቀንድና የደጋ አጋዘን በሚለው


(መ. ተማሪዎችን በጥንድ በጥንድ ያደራጁ። ትክክል ባለው ሣጥን ውስጥ ይጻፉት።)
ከዚያም በግል ድምፅ ሳያሰሙ እንዲያነቡ መ. የቀንዳቸው ቅርፅ ምን ዓይነት ነው?
ያድርጉ። የመጀመሪያዎቹን 4 አንቀጾች
[መ. ጥምዝ ነው።] (ይህንንም በተመሳሳይ ሣጥን
ማለትም የመንደርደሪያ አንቀጾቹንና
ውስጥ ይጻፉት።)

126 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፳፮


እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ የ“ውድንቢን” የቀንድ ሁኔታ 2ኛ ቀን
አብረን እንመልከት። ከወንዱና ከሴቷ አጋዘን
ቀንድ ያለው/ያላት የትኛው/የትኛዋ ናት? የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
[መተ. ሁለቱም ጾታዎች] (“ውድንቢ”ና “ቀንድ” • ቃላት
በሚለው ትክክል ባለው ሣጥን ውስጥ • መጻፍ
ይጻፉት።)
መ. የቀንዳቸው ቅርፅ ምን ዓይነት ነው?
[መተ. ጥምዝ] (በተመሳሳይ ሣጥን ውስጥ ቃላት (10 ደቂቃ)
ይጻፉት።)
ለቃላት ተመሳሳይ ፍቺ መስጠት
መ. የውድንቢ ቀንድ ከሌሎቹ በምን ይለያል?
ሥሩ
[መተ. አጭር ነው።] (በተመሳሳይ ሣጥን ውስጥ መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን የቀረቡትን
ይጻፉ።) ተግባሮች ትሠራላችሁ።
ሥሩ መ. በመጀመሪያ ተግባር “1”ን ሥሩ። “እጥፍ”
መ. አሁን ደግሞ በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ለሚለው ቃል በ“ለ” ረድፍ ከቀረቡት
ቀን በአንብቦ መረዳት፣ በተግባር 1 ሥር ተመሳሳይ ፍቹ የትኛው ነው?
የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
አዘጋጁ። ቀጥሎ የአጋዘን አስተኔዎችን ልዩ [ተ. ድርብ]
ልዩ ባህርያት በክቦቹ ውስጥ ዘርዝሩ። መ. በጣም ጥሩ! መልሱን የያዘው ፊደል የቱ
መ. ከድኩላዎች ቀንድ ያላቸው ወንዶቹ ናቸው ነው?
ወይስ ሴቶቹ? [ተ. ሐ]
[ተ. ወንዶች] (ስለዚህ “ድኩላ”ና “ቀንድ” በሚለው መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም
ትክክል ባለው ሣጥን ውስጥ እንዲጽፉ በደብተራቸው እንዲጽፉ ያድርጉ። ከዚያም
ይንገሯቸው።) በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር ይነጋግሩ።)
መ. የቀንዳቸው ቅርፅ ምን ዓይነት ነው? መ. አሁን ደግሞ ተግባር “2”ን ሥሩ። በምንባቡ
[ተ. ባለአንድ ጥምዝ ነው።] (በተመሳሳይ ሣጥን ውስጥ ከሚገኙ ቀለምን ከሚገልፁ ቃላት
ውስጥ እንዲጽፉ ይንገሯቸው።) አንድ ንገሩኝ።

መ. በጣም ጥሩ! [ተ. ነጭ]

(መ. ተግባሩን በግል ከሠሩ በኋላ የሠሩትን መ. በጣም ጥሩ! በአካባቢያችሁ ከምታውቋቸው
በቡድን በማስተያየት ሀሳብ እንዲለዋወጡ ነገሮች መካከል ነጭ ቀለም ያላቸውን
ያድርጉ። በመጨረሻም ትክክለኛውን መልስ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
በመንገር ግብረመልስ ይስጡ።) [ተ. በረዶ፣ ጥጥ፣ ጨው፣ ስኳር፣ ኖራ፣ ፉርኖ
መ. አሁን ደግሞ በተግባር “2” የቀረቡ ጥያቄዎችን ዱቄት፣ ሽበት…]
በምንባቡ መሠረት በጽሑፍ መልሱ። (ይህን (መ. በዚህ ዓይነት በጥንድ እየተወያዩ ከምንባቡ
ተግባር በ3ኛው ቀን ሠርተው እንዲመጡ ሌሎች ቀለሞችን የሚገልጹ ቃላት
የቤትሥራ ይስጧቸው።) እንዲያወጡና ምሳሌዎችን እንዲዘረዘሩ
ያድርጉ።)

፻፳፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 127


መጻፍ (30 ደቂቃ) የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) ልሥራ
መ. በምዕራፍ 5 የተወሰኑትን የአንድ ነጥብ
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት የቢጋር አገልግሎቶች ተምራችኋል። በዚህ ምዕራፍ
ሠንጠረዥ ማዘጋጀት ደግሞ የቀሩትን የአንድ ነጥብ አገልግሎቶች
እንሥራ ትማራላችሁ። አንድ ነጥብ በመጻፍ ሂደት
መ. በምዕራፍ አምስት ስለማወዳደርና ማነፃፀር ምን አገልግሎት አለው?
የአጻጻፍ ስልት ተምራችኋል። ስለማወዳደርና [መ. ብርና ሳንቲምን ለመለየት ያገለግላል።
ማነፃፀር የተማርነውን እናስታውስ። ለምሳሌ “ሁለት ብር ከሃምሳ ሳንቲም”
[መተ. ማወዳደርና ማነፃፀር፣ የተለያዩ፣ ነገርግን የሚለውን “ብር 2.50” ብሎ ለመጻፍ
ተቀራራቢ የሆኑ ነገሮችን ተመሳስሎና ይቻላል።]
ልዩነት የሚያሳይ የጽሑፍ ዓይነት ነው።] መ. ሌላው የአንድ ነጥብ አገልግሎት ምንድን
መ. አሁን ድኩላንና ውድንቢን በተመለከተ ነው?
ተመሳስሏቸውንና ልዩነታቸውን አብረን [መ. ሙሉና ሽርፍራፊ ቍጥሮችን ለመለየት
በቢጋር ሠንጠረዥ እናደራጅ። (በተማሪ ያገለግላል። ለምሳሌ 3.14፣ 1.5 ወዘተ]
መጽሐፍ ያለውን የቢጋር ሠንጠረዥ
በውስጡ ያሉትን መረጃዎች ሳይጽፉ መ. እንዴት ይነበባል?
በሰሌዳው ላይ ይጻፉት።) [መ. ሦስት ነጥብ አንድ አራት፣ አንድ ነጥብ
መ. ድኩላና ውድንቢ የሚመሳሰሉባቸው ነገሮች አምስት]
ምን ምን ናቸው? መ. ሌላው የአንድ ነጥብ አገልግሎት ምንድን
[መተ. ሁለቱም ቅጠላቅጠልና ሳር ይበላሉ፤ ነው?
ሁለቱም አጥቢ ናቸው፤ ወንዶቹ ጥምዝ [መ. ተራ ቍጥርን ከጽሑፉ ለመለየት ያገለግላል።
ቀንድ አላቸው።] ለምሳሌ የሚከተሉት የቤት እንስሳት ናቸው።
መ. በጣም ጥሩ! ድኩላና ውድንቢ የሚለያዩባቸው 1. ድመት 2. ውሻ 3. በግ 4. ላም
ነገሮች ምን ምን ናቸው? እንሥራ
[መተ. ድኩላዎች የሰውነታቸው መጠን አነስተኛ መ. ሠላሳ አንድ ብር ከሰባ አምስት ሳንቲም
ሲሆን፣ ውድንቢዎች ግዙፍ ናቸው።] የሚለውን አንድ ነጥብን በመጠቀም እንጻፍ።

መ. በጣም ጥሩ! ሌላው ልዩነቱ ምንድን ነው? [መተ. ብር 31.75]


[መተ. ድኩላዎች ወንዶቹ ቀንድ ሲኖራቸው፣ መ. በጣም ጥሩ! “አንድ ተኩል” የሚለውን አንድ
ሴቶቹ ግን የላቸውም። ውድንቢዎች ግን ነጥብን በመጠቀም እንጻፍ።
ሁለቱም ቀንድ አላቸው።] [መተ. 1.5]
(መ. በዚህ ዓይነት ተማሪዎችን እያሳተፉ መ. ትክክል! አሁን ደግሞ የዱር እንስሳትን
ሌሎቹንም ልዩነቶች በቢጋር ሠንጠረዡ በተራ ቍጥር ወደጎን እንዘርዝር
ውስጥ እንዲሞሉ ያበረታቷቸው።)
[መተ. 1. አንበሳ 2. ነብር 3. ዝሆን
ሥሩ 4. ጅብ]
መ. አሁን በሠራነው ምሳሌ መሠረት በ1ኛው
ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን በድርሰት መጻፍ ሥር ሥሩ
የቀረበውን የቢጋር ሠንጠረዥ በደብተራችሁ መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን
አዘጋጁ። ከዚያም “የበግና የፍየልን በአጻጻፍ ሥርዓት ሥር የቀረበውን ተግባር
ተመሳስሎና ልዩነት” በቢጋር ሠንጠረዡ በደብተራችሁ ሥሩ።
ውስጥ ዘርዝሩ። (መ. ተግባሩን በመጀመሪያ በግል እንዲሠሩ
ያድርጉ። ከዚያም በመልሶቻቸው ላይ

128 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፳፰


በቡድን እንዲወያዩ ያድርጉ።) አቀላጥፎ ማንበብ፣ በ”ሥሩ” ሥር የቀረበውን
ይመልከቱ።)
3ኛ ቀን ማዳመጥ (15 ደቂቃ)

የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች የዝንጀሮዎች አኗኗር


• አቀላጥፎ ማንበብ ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
• ማዳመጥ እንሥራ
• ሰዋስው መ. ዛሬ “የዝንጀሮዎች አኗኗር” በሚል
ርዕስ የቀረበ ምንባብ አነብላችኋለሁ፤
እናንተ ታዳምጣላችሁ። ከዚያ በፊት
የቤትሥራ (7 ደቂቃ) ግን የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎችን
ሥሩ እንሥራ።( በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በአንብቦ
በቅድመማዳመጥ ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
መረዳት ሥር የሠራችሁትን የቤትሥራ
በሰሌዳው ላይ ይሣሉ፣ ተማሪዎችም
እንመልከት። ከአጋዘን አስተኔዎች በቡድን
በደብተራቸው እንዲሥሉ ያድርጉ።)
የማይታዩት የትኞቹ ናቸው? መ. ስለዝንጀሮዎች ከዚህ ቀደም ምን
እናውቃለን? (ተማሪዎች የሚያውቁትን
[ተ. ድኩላዎች]
እንዲናገሩ ያድርጉ።)
(መ. በዚህ ዓይነት መልሳቸውን ይቀበሉ።)
[መተ. ዝንጀሮዎች የዱር እንስሳት ናቸው፤
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) አጥቢዎች ናቸው…]

የአጋዘን አስተኔ (መ. የእርስዎንና የተማሪዎችን ምላሽ


“ስለዝንጀሮዎች የማውቀው” በሚለው ክፍል
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) ይጻፉ።)
ሥሩ መ. ስለዝንጀሮዎች ምን ምን ነገሮችን ማወቅ
መ. ዛሬ በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ አቀላጥፎ እንፈልጋለን?
የማንበብ ልምምድ ታደርጋላችሁ። ከዚያ
በፊት ግን ባለፈው ሳምንት ያነበባችሁትን
[መተ. ስለአመጋገባቸው፣ ስለአኗኗራቸው…]
ምንባብ ይዘት በማስታወስ የቅድመንባብ (መ. “ስለዝንጀሮዎች ማወቅ የምፈልገው”
ጥያቄውን መልሱ። “የአጋዘን አስተኔ” በሚል በሚለው ክፍል ይጻፉ።)
ርዕስ በቀረበው ምንባብ ውስጥ የተጠቀሱት
መ. በጣም ጥሩ ነው! “ስለዝንጀሮዎች የተማርኩት”
የዱር እንስሳት ምን ምን ናቸው?
የሚለውን ክፍል የምታሟሉት ምንባቡን
[ተ. የደጋ አጋዘን፣ አምባራይሌ፣ አጋዘን፣ ድኩላና ካዳመጣችሁ በኋላ ነው።
ውድንቢ ናቸው።]
ሥሩ
አቀላጥፎ ማንበብ (8 ደቂቃ) መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፤
ሥሩ በቅድመማዳመጥ ሥር የቀረበውን
ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም
መ. በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ “የአጋዘን
ስለዝንጀሮዎች የምታውቋቸውንና ማወቅ
አስተኔ” በሚል ርዕስ ከቀረበው ምንባብ
የምትፈልጓቸውን ሁሉ በመጀመሪያዎቹ
የመጀመሪያዎቹን ሦስት አንቀጾች
ሁለት የሠንጠረዥ አምዶች ውስጥ ዘርዝሩ።
ተራበተራ ድምፅ በማሰማት አንብቡ። (ይህን
ተግባር አቀላጥፈው የሚያነቡ ተማሪዎችን (መ. ዋናዋና ሀሳቦችን ማስታወሻ እየያዙ
አቀላጥፈው ከማያነቡት በማጣመር ያሠሩ። እንዲያዳምጡ ይንገሯቸው።)
ዝርዝር አሠራሩን በመምህር መምሪያ
ምዕራፍ 3፣ በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ 6ለ. የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)

፻፳፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 129


(መ. በቅደመማዳመጥ ላይ “ስለዝንጀሮዎች መንጋው አባትና እናት ዝንጀሮዎችን፣ ወጣት
ማወቅ የምፈልገው” ብለው የያዟቸውን ወንዶችና ሴቶች ዝንጀሮዎችን፣ እንዲሁም
ነጥቦች በምንባቡ ውስጥ መጠቀስ ወይም ትንንሽ ግልገሎችን ያቀፈ ነው። ሳር፣ ፍራፍሬና
አለመጠቀሳቸውን እያስተዋሉ እንዲያዳምጡ ሥራሥር ይመገባሉ። ቅጠላቅጠሎችን ግን
ይንገሯቸው። ከዚያም ምንባቡን አይመገቡም። ጥራጥሬ እህሎችን ስለሚወዱ
ያንብቡላቸው። የመጀመሪያው የኮከብ የገበሬዎችን ሰብል በማሳ ላይ እያለና ከተከመረ
በኋላም ክፉኛ ይጎዳሉ። በተጨማሪም አንበጣ፤
ምልክት ካለበት ቦታ ላይ ሲደርሱ በኮከቡ
ጉንዳንና የመሳሰሉትን ነፍሳት ይመገባሉ።
ውስጥ ያለውን ጥያቄ ይጠይቋቸው።
አልፎአልፎም ወፎችን፣ ጥንቸሎችንና ግልገል
(መ. ከተማሪዎች መልስ ከተቀበሉ በኋላ የሜዳ ፍየሎችን ይበላሉ። የሚመገቡት
ማንበብዎን ይቀጥሉ መልስ መንገር በቀን ሁለት ጊዜ ነው። ጧትና ማታ ለሁለት
አያስፈልግም። ከዚያም ሁለተኛው የኮከብ ወይም ለሦስት ሰዓታት ያህል የቻሉትን ያህል
ምልክት ካለበት ቦታ ላይ ሲደርሱ በኮከቡ ያጋብሳሉ።
ውስጥ ያለውን ጥያቄ ይጠይቋቸው።) ለ. የጭላዳ ዝንጀሮዎች አኗኗር
(ከተማሪዎች መልስ ከተቀበሉ በኋላ ማንበብዎን *** የጭላዳ ዝንጀሮዎች ለመኖሪያነት
ይቀጥሉ።) የሚመርጡት ምን ዓይነት ሥፍራ
ይመስላችኋል?***
የዝንጀሮዎች አኗኗር
ጭላዳ ዝንጀሮዎች ገደላገደሎችንና ቋጥኞችን
በኢትዮጵያ ሦስት ዓይነት ዝንጀሮዎች አሉ። ለመኖሪያነት ይመርጣሉ። ምግብ ፍለጋ
እነሱም፡- ነጭ ዝንጀሮ፣ ጥቁር ዝንጀሮና ጭላዳ ሲሰማሩ ከሚኖሩበት ቋጥኝና ገደል ብዙ ርቀው
ዝንጀሮ በመባል ይታወቃሉ። ዝንጀሮዎቹ አይሄዱም።
ተመሳስሎም ልዩነትም አላቸው።
በአንድ መንጋ ውስጥ እስከ400 የሚሆኑ የጭላዳ
የሦስቱም ዓይነት ዝንጀሮዎች ተፈጥሮ ተመሳሳይ ዝንጀሮዎች ይገኛሉ። የመንጋው አለቃ አንድ
ነው። ሁሉም ዝንጀሮዎች ከወደትከሻቸው አበጥ፣ ወንድ ሲሆን በውስጡ ሴቶችና ግልገሎች
ከወደዳሌያቸው ደግሞ አነስ ያሉ ናቸው። የውሻ ይገኙበታል። አንዳንድ ጊዜም ወንዶች
ክራንቻቸው ረጅምና ሹል ነው። በአንገታቸውና ብቻ የሚገኙበት መንጋም አለ። ጭላዳዎች
በትከሻቸው ላይ ያለው ፀጉር ይበዛል። ከማደሪያቸው ወጥተው ቀኑን ሙሉ ሜዳ ላይ
መቀመጫቸው ፀጉር አልባ ወይም መላጣ ነው። ተሰማርተው ይውላሉ። የመኝታ አካባቢያቸውን
ሦስቱም ዓይነት ዝንጀሮዎች በየቀኑ ይለዋውጣሉ። ምግባቸው እንደጥቁርና
እንደተመሳስሎዎቻቸው ሁሉ ልዩነትም ነጭ ዝንጀሮዎች ሳር፣ ሥራሥር፣ ፍራፍሬና
አላቸው። ከሚለያዩባቸው ነገሮች አንዱ መኖሪያ እህል ነው። እንደጥንዚዛ ካሉት አነስተኛ ነፍሳት
አካባቢያቸው ነው። ጥቁር ዝንጀሮዎች በቆላና በቀር እንስሳትን ብዙም አይመገቡም።
በደጋ፣ ነጭ ዝንጀሮዎች በቆላ፣ ጭላዳ ዝንጀሮዎች ጭላዳ ዝንጀሮን ከሌሎች ዝንጀሮዎች የሚለየው
ደግሞ በደጋ አካባቢዎች ይኖራሉ። ሁለተኛው ሌላው ጉዳይ ድምፁ ነው። የሌሎች ዝንጀሮዎች
ልዩነት ደግሞ አኗኗራቸው ነው። የዝንጀሮዎችን ድምፅ ጎርናና ሲሆን የጭላዳ ዝንጀሮ ድምፅ ግን
አኗኗር እንደሚከተለው በሁለት ከፍሎ ማየት ቀጭንና ከፍ ያለ ነው።
ይቻላል።
(ፍሰሐ ሃይለመስቀል። 1966። የኢትዮጵያ
ሀ. የጥቁርና የነጭ ዝንጀሮዎች አኗኗር ታላላቅ አራዊት፣ ከገጽ 99-105 ለደረጃው
***ጥቁርና ነጭ ዝንጀሮዎች ለመኖሪያነት እንዲስማማ ለውጥ ተደርጎበት የተወሰደ።)
የሚመርጡት ምን ዓይነት ሥፍራ 6ሐ. አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ)
ይመስላችኋል?***
ሥሩ
ጥቁርና ነጭ ዝንጀሮዎች ጥቅጥቅ ያለ ደን መ. “የዝንጀሮዎች አኗኗር” በሚል ርዕስ
አይወዱም። በአብዛኛው ገላጣ ሥፍራዎችንና ያነበብኩላችሁን ምንባብ አዳምጣችኋል።
አልፎ አልፎ ዛፍ ያለባቸውን ቆላማ ቦታዎች አሁን በቅድመማዳመጥ ባዘጋጃችሁት
ለመኖሪያነት ይመርጣሉ። የሚኖሩትም ሠንጠረዥ ውስጥ “ስለዝንጀሮዎች
በማኅበር ነው። በአብዛኛው ከ40 እስከ80 የሚሆኑ
የተማርኩት” በሚለው በሦስተኛው አምድ
ዝንጀሮዎች በአንድ መንጋ ውሰጥ ይገኛሉ።
ከምንባቡ ስለዝንጀሮዎች ያወቃችኋቸውን

130 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፴


ነገሮች ዘርዝሩ። (ተማሪዎች በግል በደብተራችሁ ጻፉ።
የዘረዘሯቸውን ለ2 ደቂቃ ያህል በጥንድ
(መ. ተማሪዎቹ ተግባሩን ሲሠሩ እየተዘዋወሩ
እንዲወያዩበት ያድርጉ። ከዚያም ከ“ለ”
ይከታተሉ። ተግባሩን ለመሥራት የተቸገሩ
እስከ“ረ” የቀረቡትን ጥያቄዎች በጽሑፍ
ተማሪዎችን ይደግፉ። ተግባሩን ሠርተው
እንዲመልሱ ያድርጉ። ቀጥሎም በመልሱ ላይ
ሲጨርሱ በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር
በጥንድ እንዲወያዩ ያድርጉ። በመጨረሻም
ይወያዩ። በመጨረሻም “የአጋዘን አስተኔ”
ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ።)
ከሚለው ምንባብ የዓረፍተነገር ባለቤት
ሰዋስው (8 ደቂቃ) የሆኑ ስሞችን በደብተራቸው እንዲዘረዝሩ
የቤትሥራ ይስጧቸው።)
ስም እንደባለቤት
ልሥራ
መ. ዛሬ የምንማረው ከዓረፍተነገር ውስጥ
ባለቤትን መለየት ነው። በዓረፍተነገር
ውስጥ ድርጊት ፈፃሚው ባለቤት ይባላል።
አንድ ምሳሌ ሠርቼ ላሳያችሁ። “ራህመት
ወደትምህርትቤት ሄደች።” (ይህን ዓረፍተነገር
በሰሌዳው ላይ ይጻፉና ያንብቡላቸው።)
መ. አሁን የዓረፍተነገሩን ባለቤት ልለይ።
ወደትምህርትቤት የሄደችው ማን ናት?
[መ. ራህመት]
[መ. ስለዚህ የዓረፍተነገሩ ባለቤት “ራህመት” ናት
ማለት ነው። ]
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ ሌላ ምሳሌ አብረን እንሥራ።
“መኰንን ሙዝ ገዛ።” (ዓረፍተነገሩን
በሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
መ. ዓረፍተነገሩን ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
(አንድ/ዲት ተማሪ ያስነብቡ።)
መ. በጣም ጥሩ! ባለቤቱን ለማግኘት ምን ብለን
እንጠይቅ?
[መተ. ሙዝ የገዛው ማን ነው?]
መ. መልሱ ምንድን ነው?
[መተ. መኰንን]
መ. ስለዚህ! የዓረፍተነገሩ ባለቤት ማን ነው?
[መተ. መኰንን]
መ. በጣም ጥሩ! [ስለዚህ በዓረፍተነገር ውስጥ
ደርጊቱን የፈፀመው ባለቤት ይባላል።]
ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ የእናንተ ተራ ነው። በቀሪዎቹ
ዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉትን ባለቤቶች
በጥንድ እየተወያያችሁ በመለየት

፻፴፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 131


ከንባብ በፊት ከርዕስና ከሥዕል በመነሳት፣
2ኛ ሳምንት በንባብ ጊዜ ደግሞ ንዑስ ርዕሶችን፣
በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ሥዕሎችን፣ አንቀጾችን ወዘተ. መሠረት
በማድረግ ራስን እየጠየቁ፣ እየተመራመሩ
የዱርእንስሳት ማንበብ፣ አንብቦ ለመረዳት ያግዛል። ይህ
ስልት እንዴት ተግባራዊ እንደሚሆን ግልጽ
እንዲሆንላችሁ እኔ ሳነብ ተከታተሉኝ።
4ኛ ቀን (ከማንበብዎ በፊት የሚከተለውን ሠንጠረዥ
የዕለቱ ትምህርት ይዘት በሰሌዳው ላይ ያዘጋጁ።)
• ማንበብ
ጥያቄዎች መልሶች

የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ሥሩ መ. ዋልያና ቀይ ቀበሮ (ርዕሱን ድምፅዋን
መ. የ“አጋዘን አስተኔ” ከሚለው ምንባብ በማሰማት ያንብቡ።) ስለዋልያና ቀይ ቀበሮ
ያገኛችኋቸውን ባለቤት የሆኑ ስሞች ንገሩኝ! ምን አውቃለሁ? (ድምፅዎን በማሰማት
[ተ. የአጋዘን አስተኔ፣ የደጋ አጋዘኖች፣ ድኩላ፣ ራስዎን ይጠይቁ። “ጥያቄዎች” በሚለው
ሴቶቹ፣ ቀለም፣ ቀንዶች…] (በዚህ ዓይነት የሠንጠረዥ ክፍል ጥያቄዎን ይጻፉ።)
ምላሽ ይቀበሉ፤ትክክለኛ መልሶችን [መ. ዋልያና ቀይ ቀበሮ ብርቅዬ የዱር እንስሳት
በመንገር ግብረመልስ ይስጡ።) መሆናቸውን አውቃለሁ።] (መልስ በሚለው
የሠንጠረዡ ክፍል ይጻፉ። ከዚያም አንቀጹን
ማንበብ (35 ደቂቃ) ማንበብ ይጀምሩ። ከአንደኛው አንቀጽ፣
ዋልያና ቀይ ቀበሮ አንደኛውን ዓረፍተነገር ብቻ አንብበው
ያቁሙ።)
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
መ. የማነበው ነገር ገብቶኛል? ዋልያንና
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ ቀይ ቀበሮን ከጭላዳ ዝንጀሮና ከምኒሊክ
ሥሩ ዱኩላ እንዲሁም ከደጋ አጋዘን ጋር ምን
መ. “ዋልያና ቀይ ቀበሮ” በሚል ርዕስ የቀረበውን አገናኛቸው? (ይህን ጥያቄ በሠንጠረዡ
ምንባብ ከማንበባችሁ በፊት የቅድመንባብ ውስጥ ይጻፉ። ከዚያም ዓረፍተነገሩን
ጥያቄዎችን ትመልሳላችሁ። ደግመው ያንብቡ።)
(መ. በመጀመሪያ ተማሪዎች በቡድን [መ. አሃ!...! አሁን ገባኝ። ዋልያንና ቀይ ቀበሮን
ሆነው የሚያውቋቸውን የዱር እንስሳት ከጭላዳ ዝንጀሮና ከሌሎቹ ከተጠቀሱት
እንዲዘረዝሩ ያድርጉ። ከዚያም ከየቡድኑ የዱር እንስሳት ጋር ያመሳሰላቸው ሁሉም
የተመረጡ ተማሪዎች ቡድናቸውን ወክለው በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ
እንዲናገሩ ያድርጉ። በመቀጠልም ሥዕሉን የዱር እንስሳት መሆናቸው ነው።]
ተመልክተው ምንባቡ ስለምን እንደሚገልፅ ሥሩ
እንዲገምቱ ያድርጉ።) (መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ። ከዚያም
የማንበብ ሂደት (15 ደቂቃ) እርስዎ ሰሌዳው ላይ ያዘጋጁትን “የጥያቄና
መልስ ሠንጠረዥ” በደብተራቸው
ሥሩ እንዲያዘጋጁ ያድርጉ።)
መ. አንብቦ መረዳትን ከማረጋገጫ ስልቶች
መካከል አንዱ መጠየቅ ነው። አንድ ጽሑፍ መ. “ዋልያና ቀይ ቀበሮ” ከሚለው ርዕስና
በሚነበብበት ጊዜና ከመነበቡ በፊት ራስን ከሥዕሉ በመነሳት ወደአዕምሯችሁ የመጡ
እየጠየቁ ማንበብ መረዳትን ያፋጥናል። ጥያቄዎችን ባዘጋጃችሁት ሠንጠረዥ

132 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፴፪


ውስጥ ጻፉ። ያሰፈሩባቸውን ወረቀቶች ከየቡድኑ
ያሰባስቡ።)
[ተ. በግል ወደአዕምሯቸው የመጡ ጥያቄዎችን
በሠንጠረዡ ውስጥ ይጽፋሉ።] አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
መ. ከማንበባችሁ በፊት ልትመልሷቸው ሥሩ
የምትችሏቸውን ጥያቄዎች መልሱ። መ. ከማንበባችሁ በፊት ሥዕሉን በመመልከት
[ተ. ጥያቄዎቻቸውን ይመልሳሉ።] ምንባቡ ስለምን እንዲሚገልጽ ገምታችሁ
ነበር። ግምታችሁ ትክክል ነበር? (ተማሪዎች
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ማንበብ ጀምሩ። እንዲናገሩ ያድርጉ።)
[ተ. በግል በለሆሳስ ያነባሉ። በግል ሲያነቡ [ተ. አዎ/ አይደለም።]
ወደአዕምሯቸው የመጡ ጥያቄዎችን
ይመዘግባሉ።] መ. በጣም ጥሩ! አሁን በማንበብ ሂደት
ያዘጋጃችኋቸውን ጥያቄዎች ትመልሳላችሁ።
(መ. የመጀመሪያዎቹን ሁለት አንቀጾች (ከየቡድኑ ያሰባሰቧቸውን ጥያቄዎች
እንዳነበቡ ያስቁሟቸው።) ያንብቡላቸው።)
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በግል ያነሳችኋቸው [ተ. በተለያዩ ቡድኖች የተነሱ ጥያቄዎችን
ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ። ይመልሳሉ።]
[ተ. ባነሷቸው ጥያቄዎች ላይ በጋራ ይወያያሉ።] መ. በጣም ጥሩ! አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው
መ. በጣም ጥሩ! ካነሳችኋቸው ጥያቄዎች መካከል ቀን በአንብቦ መረዳት ሥር ከ“ሀ” እስከ“ሠ”
ያስቸገሯችሁን ጥያቄዎች መርጣችሁ በንፁህ የቀረቡትን ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ።
ወረቀት ላይ ጻፉ። (እነዚህን ጥያቄዎች እየጠየቁ ተማሪዎች
በቃላቸው መልስ እንዲሠጡ ያድርጉ።)
[ተ. ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል ያስቸገሯቸውን
ጥያቄዎች መርጠው ይጽፋሉ።] መ. ከዋልያና ቀይ ቀበሮ በተጨማሪ በምንባቡ
ውስጥ የተጠቀሱት በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ
መ. አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ።
የዱር እንስሳት ምን ምን ናቸው?
[ተ. በግል በለሆሳስ ያነባሉ። ወደአዕምሯቸው
[ተ. ጭላዳ ዝንጀሮ፣ የምኒሊክ ድኩላ፣ ኒያላ/የደጋ
የመጡ ጥያቄዎችን በደብተራቸው
አጋዘን]
ይመዘግባሉ።]
መ. በጣም ጥሩ አሁን ደግሞ ከ“ረ” እስከ“ተ”
(መ. ሦስተኛውን አንቀጽ እንዳነበቡ
የቀረቡትን ጥያቄዎች በቡድን እየተወያያችሁ
ያስቁሟቸው።)
በቃላችሁ መልሱ። (የጥያቄዎቹን መልስ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በግል ያነሳችኋቸው የቡድን ተወካዮች እንዲያቀርቡ ያድርጉ።
ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ። የተማሪዎቹን መልስ ካዳመጡ በኋላ
የራስዎን አስተያየት በመጨመር ያጠቃሉ።
[ተ. ባነሷቸው ጥያቄዎች ላይ በጋራ ይወያያሉ።]
በመጨረሻም በኢትዮጵያ ስለሚገኙ የዱር
መ. በጣም ጥሩ! ካነሳችኋቸው ጥያቄዎች መካከል እንስሳት ጽሑፎችን አንብበው በማጠቃለል
አስቸጋሪ የሆኑባችሁን ጥያቄዎች መርጣችሁ ለክፍል ጓደኞቻቸው እንዲናገሩ በ6ኛው ቀን
የመጀመሪያውን ጥያቄ በጻፋችሁበት ወረቀት ሠርተው እንዲመጡ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
ላይ ጻፉ።
[ተ. ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል አንዱን
መርጠው ይጽፋሉ።]
መ. አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ።
[ተ. ማንበባቸውን ይቀጥላሉ።]
(መ. ተማሪዎች አንብበው ሲጨርሱ ጥያቄያቸውን

፻፴፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 133


በመጀመሪያው አንቀጽ ተመሳስሏቸውን
እገልጻለሁ። ይህን ለማድረግ መንደርደሪያ
5ኛ ቀን ዓረፍተነገሩ ምን ሊሆን ይችላል?
[መ. ድኩላና ውድንቢ የአጋዘን አስተኔ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
በመሆናቸው በብዙ ነገሮች ይመሳሰላሉ።]
• ቃላት
መ. በዚህ መንደርደሪያ ዓረፍተነገር ሥር
• መጻፍ
የሁለቱን እንስሳት ተመሳሳይ ባህርያት
በተሟሉ ዓረፍተነገሮች እያደራጀሁ
ጽፌያለሁ።
ቃላት (10 ደቂቃ) መ. ሁለተኛውን አንቀጽ ለመጻፍ መንደርደሪያ
በአንቀጽ ውስጥ የተጓደሉ ቃላትን ዓረፍተነገሩ ምን መሆን አለበት?
ማሟላት [መ. ድኩላና ውድንቢ እንደተመሳስሏቸው ሁሉ
ልዩነትም አላቸው።]
ሥሩ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን ከምንባቡ መ. በዚህ መንደርደሪያ ዓረፍተነገር ሥር
የውጡ ቃላትና የተጓደሉ ቃላት ያሉት ደግሞ ልዩነታቸውን በተሟሉ ዓረፍተነገሮች
አንቀጽ ቀርቧል። ቃላቱን እየመረጣችሁ እያደራጀሁ ጽፌያለሁ። በዚህ መልኩ
በተገቢ ቦታቸው በማስገባት አንቀጹን የጻፍኩትን አንቀጽ ላንብብላችሁ። (ቀጥሎ
አሟልታችሁ በደብተራችሁ ጻፉ። የቀረቡትን ሁለት አንቀጾች ያንብቡላቸው።)
መ. በሳጥን ውስጥ ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል ድኩላና ውድንቢ የአጋዘን አስተኔ ዝርያዎች
የአንቀጹን የመጀመሪያ ዓረፍተነገር በመሆናቸው በብዙ ነገሮች ይመሳሰላሉ።
የሚያሟላው ቃል የትኛው ነው? ከሚመሳሰሉባቸው ነገሮች አንዱ ሁለቱም
አጥቢ እንስሳት መሆናቸው ነው። ከዚህም
[ተ. ብርቅዬ] ሌላ ቡናማ ቀለም ያለው ፀጉር ሲኖራቸው
መ. ትክክል! ቃሉን በቦታው በማስገባት አንቀጹን በሆዳቸውና በደረታቸው የሚወርዱ ነጫጭ
አሟልታችሁ ጻፉ። መስመሮችም አሏቸው። ወንድ ድኩላዎችንም
ሆኑ ውድንቢዎች ጥምዝ ቀንድ አላቸው።
[ተ. ቃሉን በክፍት ቦታው በማስገባት አንቀጹን በተጨማሪም ሁለቱ የአጋዘን አስተኔ ዝርያዎች
አሟልተው ይጽፉሉ።] ቅጠላቅጠል ይመገባሉ።
(መ. ቀሪዎቹን ቃላት በመጀመሪያ በግል ድኩላና ውድንቢ እንደተመሳስሏቸው ሁሉ
እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም በጥንድ ልዩነትም አላቸው። ከልዩነታቸው አንዱ
እየተወያዩ ስህተታቸውን እንዲያስተካክሉ የአካላቸው ሁኔታ ነው። ከአጋዘን አስተኔዎች
ያድርጉ።) ሁሉ ግዙፎቹ ውድንቢዎች በመሆናቸው
በአካላቸው መጠን ከድኩላዎች ይልቃሉ። ሴት
መጻፍ (30 ደቂቃ) ውድንቢዎች ቀንድ ሲኖራቸው ድኩላዎች ግን
የላቸውም። ሌላው ልዩነታቸው በአኗኗራቸው
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) ላይ የተመሠረተ ነው። ድኩላዎች አብዛኛውን
ጊዜ ውኃና ደኖች በሚበዙበት አካባቢ ይኖራሉ።
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት አንቀጽ
ውድንቢዎች ግን በየትኛውም የአየር ንብረት
መጻፍ መኖር ከመቻላቸውም በላይ ላልተወሰነ ጊዜ
ልሥራ ያለውኃ መቆየት ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪ
ውድንቢዎች በቡድን ሲኖሩ ድኩላዎች ግን
መ. አሁን ባለፈው ሳምንት ያዘጋጀሁትን
ብቸኝነትን ይመርጣሉ።
የቢጋር ሠንጠረዥ መሠረት በማድረግ
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት ድርሰት ሥሩ
እንዴት እንደጻፍኩ ላሳያችሁ። ድርሰቴ መ. አሁን ባለፈው ክፍለጊዜ “የበግና የፍየልን
የሚያተኩረው በድኩላና በውድንቢ ተመሳስሎና ልዩነቶች” በቢጋር ሠንጠረዥ
ተመሳስሎና ልዩነት ላይ ነው። ስለዚህ ዘርዝራችኋል። ዛሬ ደግሞ ያዘጋጃችሁትን

134 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፴፬


የቢጋር ሠንጠረዥ መነሻ በማድረግ
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት ሁለት አንቀጽ 6ኛ ቀን
ትጽፋላችሁ። በግና ፍየል የሚመሳሰሉባቸውን
ነገሮች በአንድ አንቀጽ፣ የሚለያዩባቸውን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ደግሞ በሌላ አንቀጽ አድርጋችሁ ባለሁለት
• አቀላጥፎ ማንበብ
አንቀጽ ድርሰት ጻፉ።
• መናገር
(መ. ተማሪዎች ድርሰቱን በሚጽፉበት ጊዜ
በክፍል ውስጥ እየተዘዋወሩ ይከታተሉ፤ • ሰዋስው
ይደግፉ። መጻፍ ለተቸገሩ ተማሪዎች
መንደርደሪያ ዓረፍተነገሮች በመስጠት፣
በቢጋር ሠንጠረዣቸው የዘረዘሯቸውን የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ሀሳቦች እንዴት ማደራጀት እንደሚችሉ
ፍንጭ በመስጠት ያበረታቷቸው።) ሥሩ
መ. በኢትዮጵያ ውስጥ ስለሚገኙ የዱር እንስሳት
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) ያነበባችሁትን በማጠቃለል ጥንድ ጥንድ
የይዘት (የአንድ ነጥብ) አገልግሎት ሆናችሁ ተራበተራ ተናገሩ።

ሥሩ [ተ. ጥንድ ጥንድ ሆነው ተራበተራ ይናገራሉ።]


መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን (መ. ተማሪዎች ሲናገሩ በመመልከት ጥሩ
በአጻጻፍ ሥርዓት ሥር የቀረበውን ተግባር የተናገሩትን በማበረታት ግብረመልስ
ሥሩ። በመጀመሪያው ጥያቄ ብርና ሳንቲሞች ይስጡ።)
በፊደል ተጽፈው ቀርበዋል፤ አንድ ነጥብን
በመጠቀም በቍጥር ጻፏቸው። በሁለተኛ አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
ጥያቄ ደግሞ፣ በፊደል የተጻፉትን ሙሉና
ሽርፍራፊ ቍጥሮች አንድ ነጥብን በመጠቀም ዋልያና ቀይ ቀበሮ
በቍጥር ጻፉ። በመጨረሻም የአጋዘን አስተኔ ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
ዝርያዎችን በተራ ቍጥር ወደታች ዘርዝሩ።
ሥሩ
መ. አሥራሦስት ብር ከሰማኒያ ሳንቲም የሚለውን መ. ዛሬ ጥንድ በመሆን ድምፅ እያሰሙ የማንበብ
በቍጥር ጻፉ። ልምምድ ታደርጋላችሁ። ከዚያ በፊት ግን
[ተ. ብር 13.80] የምታነቡትን ምንባብ ይዘት በማስታወስ
አንድ ጥያቄ መልሱ። ዋልያና ቀይ ቀበሮ
መ. ጥሩ! አሁን ደግሞ “ሦስት ነጥብ አምስት” የሚመሳሰሉባቸና የሚለያዩባቸው ነገሮች
የሚለውን በቍጥር ጻፉ። ምን ምን ናቸው? (ተማሪዎች በቡድን ሆነው
[ተ. 3.5] በጥያቄው ላይ እንዲነጋገሩ ያድርጉ።)
መ. ትክክል! የአጋዘን አስተኔ ዝርያዎችን በተራ ማንበብ (8 ደቂቃ)
ቍጥር ወደታች ዘርዝሩ።
ሥሩ
[ተ. 1. የደጋ አጋዘን] (መ. አቀላጥፈው የሚያነቡትን አቀላጥፈው
2. አምባራይሌ ከማያነቡት ተማሪዎች ጋር በማቀናጀት
በጥንድ በጥንድ እንዲቀመጡ ያድርጉ።)
3. ውድንቢ ወዘተ]
መ. አሁን “ዋልያና ቀይ ቀበሮ” የሚለውን
(መ. በትክክል ያልተጻፉትን በማስተካከል ምንባብ በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ ድምፅ
ግብረመልስ ይስጡ።) እያሰማችሁ ተራበተራ አንብቡ። (በመምህር
መምሪያ ምዕራፍ 3፣ በ1ኛው ሳምንት፣
በ3ኛው ቀን፣ አቀላጥፎ ማንበብ በ“ሥሩ”
ሥር የቀረበውን ዝርዝር አሠራር በመከተል

፻፴፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 135


ተማሪዎች ማንበብ እንዲለማመዱ ያድርጉ።) የዓረፍተነገር ባለቤት ሊሆኑ ይችላሉ።
በሌሎች ዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉት
መናገር (15 ደቂቃ) ባለቤቶች የተጸውዖ ወይም የወል ስም
መሆናቸውን እንለይ። “መስታወት ፈረስ
በማወዳደርና በማነፃፀር መናገር ጋለበች።”
ሥሩ
መ. ባለቤቱን ለማግኘት ምን ብለን እንጠይቅ?
(መ. አሁን ተማሪዎችን በቡድን አደራጅተው
በድመቶችና በውሾች ተመሳስሎና ልዩነት [መተ. ፈረስ የጋለበችው ማን ናት?]
ላይ እንዲነጋገሩ ያድርጉ። ከዚያም ከሁለቱ መ. መልሱ ምንድን ነው?
እንስሳት ይበልጥ ለሰው ልጅ ጠቃሚ የሆኑት
የትኞቹ እንደሆኑ በምክንያት አስደግፈው [መተ. መስታወት]
እንዲናገሩ ያድርጉ። ተማሪዎች ሲነጋገሩ መ. ስለዚህ የዓረፍተነገሩ ባለቤት የትኛው ነው?
በክፍሉ ውስጥ እየተዘዋወሩ ይመልከቱ።
ሀሳብ ካጠራቸው ፍንጭ በመስጠት፣ [መተ. መስታወት]
ጥያቄዎችን በመጠየቅ እንዲናገሩ ያበረታቱ። መ. “መስታወት” የሚለው ቃል ምን ዓይነት ስም
ለምሳሌ እንደሚከተለው ያሉ ጥያቄዎችን ነው?
መጠየቅ ይችላሉ።)
[መተ. የተጸውዖ ስም]
መ. ድመትና ውሻን የሚያመሳስሏቸው ባህርያት
መ. “ልጆቹ ምግብ ያዘጋጃሉ።” በሚለው
ምን ምን ናቸው?
ዓረፍተነገር ባለቤቱን ለማግኘት ምን ብለን
[ተ. ለማዳ የቤት እንስሳ ናቸው፤ ሥጋ በል… እንጠይቅ?
ናቸው።]
[መተ. ምግብ የሚያዘጋጁት እንማን ናቸው?]
መ. ከድመት የበለጠ ውሻ ይጠቅማል የምትሉ፣ መ. መልሱስ ምን ይሆናል?
ምክንያታችሁ ምንድን ነው?
[መተ. ልጆቹ]
[ተ. ውሻ፣ ቤት በሌባና በጠላት እንዳይደፈር
ይጠብቃል።] መ. ስለዚህ የዓረፍተነገሩ ባለቤት የትኛው ነው?

(መ. በዚህ ዓይነት ተማሪዎች እንዲናገሩ [መተ. ልጆቹ]


ይገፋፉ።) መ. “ልጆቹ” የሚለው ስም ምን ዓይነት ስም
ነው?
ሰዋስው (10 ደቂቃ) [መተ. የወል ስም]
የወልና የተጸውዖ ስሞች እንደባለቤት ሥሩ
እንሥራ መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን በሰዋስው
መ. ባለፈው ሳምንት ስለዓረፍተነገር ባለቤት ሥር በቀረቡት ዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉትን
ተምራችኋል። የዓረፍተነገርን ባለቤት ባለቤቶች ለዩ። ከዚያም ባለቤቶቹ የተጸውዖ
ለማግኘት የምንጠይቀውን ጥያቄ ለማወቅ ወይም የወል ስሞች መሆናቸውን ለይታችሁ
አንድ ምሳሌ እንመልከት። “አንሻ ውኃ በደብተራችሁ ጻፉ።
ጠጣች” በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱን
መ. “ዓሣ በባህር ውስጥ ይኖራል” በሚለው
ለማግኘት ምን ብለን እንጠይቅ?
ዓረፍተነገር ውስጥ ያለውን ባለቤት
[መተ. ውኃ የጠጣችው ማን ናት?] ለማግኘት ምን ብላችሁ ትጠይቃላችሁ?
መ. መልሱስ ምንድን ነው? [ተ. በባህር ውስጥ የሚኖረው ምንድን ነው?]
[መተ. አንሻ] መ. ጥሩ! መልሳችሁ ምንድን ነው?
መ. ስለዚህ “አንሻ” የዓረፍተነገሩ ባለቤት ናት [ተ. ዓሣ]
ማለት ነው። የተጸውዖ ወይም የወል ስሞች

136 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፴፮


መ. ስለዚህ የዓረፍተነገሩ ባለቤት የትኛው ነው?
[ተ. ዓሣ]
መ. ጥሩ ነው! “ዓሣ” የሚለው ቃል ምን ዓይነት
ስም ነው?
[ተ. የወል ስም]
(መ. በዚህ ዓይነት የሌሎቹንም ዓረፍተነገሮች
ባለቤቶች በግል እንዲለዩ ያድርጉ። ከዚያም
ሠርተው እንደጨረሱ በጥንድ እንዲወያዩ
ያድርጉ። በመጨረሻም ትክክለኛውን
መልስ በመናገር እንዲተራረሙ ያድርጉ።
“ዋልያና ቀይ ቀበሮ” በሚለው ምንባብ
ውስጥ የሚገኙትን የተጸውዖና የወል ስሞች
በደብተራቸው እንዲዘረዝሩ የቤትሥራ
ይስጧቸው።)

፻፴፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 137


በማጣመር እንዲያነቡ ያድርጉ።)
3ኛ ሳምንት
ማንበብ (30 ደቂቃ)
የዱር እንስሳት ጥበቃና
እንክብካቤ በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ይዞታ
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)

7ኛ ቀን ከካርታ መረጃ ማግኘት


የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ሥሩ
መ. “በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ይዞታ” በሚል
• የቃላት ጥናት ርዕስ ከቀረበው ምንባብ የሚገኘውን ካርታ
• ማንበብ አስተውሉ። በካርታው ላይ የተጠቀሱት
ብሔራዊ ፓርኮች ማን ማን ናቸው?
[ተ. የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የአዋሽ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ብሔራዊ ፓርክ፣ የባሌ ተራራዎች ብሔራዊ
ሥሩ ፓርክ…]
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን በሰዋስው መ. ብሔራዊ ፓርኮቹ በየትኞቹ ክልሎች
ሥር የሠጠኋችሁን የቤትሥራ መልስ ይገኛሉ? (ተማሪዎች ካርታውን በማንበብ
ታረጋግጣላችሁ። እንዲመልሱ ያድርጉ።)
መ. “ዋልያና ቀይ ቀበሮ” በሚል ርዕስ ከቀረበው (መ. ተማሪዎች ማንበብ ከመጀመራቸው
ምንባብ ያገኛችሁትን የተጸውዖ ስም ንገሩኝ። በፊት ስለኢንሹ የቀረበውን መግለጫ
[ተ. ኢትዮጵያ] ያብራሩላቸው፤ ከተቻለም ሥዕሉን
ያሳዩዋቸው።
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ የወል ስም ንገሩኝ።
ኢንሹዎች ከፍታቸው ከ35-40ሴ.ሜ.፣
[ተ. ዋልያ ፣ ቀይ ቀበሮ፣ ተራራ…] ርዝመታቸው ከ62-75ሴ.ሜ.፣ ክብደታቸው
(መ. በዚህ ዓይነት እየጠየቁ የተማሪዎችን መልሶች ከ3.7-5.5ኪ.ግ. ይሆናሉ። ወንዶቹ ወደኋላ
ያረጋግጡ፣ ተማሪዎች ያልዘረዘሯቸውን ዘመም ያለ እስከ 6ሴ.ሜ. ርዝመት ያላቸው
ስሞች በመጨመር ያጠቃሉ።) ቀንዶች አላቸው። የኢንሹዎች መልክ
የቆሸሸ ግራጫ ይመስላል። ሆድና ደረታቸው
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ) ነጣ ያለ ነው። ለመኖሪያነት የሚመርጡት
ቁጥቋጦ ያለው ሞቃትና ደረቅ ስፍራ ነው።
መነጠልና ማጣመር (ሰሎሞን፣ 2000፣ 55።))
ሥሩ
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በቃላት
ጥናት ሥር የቀረቡትን ቃላት በመነጠልና ሥሩ
በማጣመር አንብቡ። መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን፣ በማንበብ
ሂደት የቀረበውን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
መ. “ፓርኮች” የሚለውን ቃል በመነጣጠል
አዘጋጁ። ከዚያም “በኢትዮጵያ የዱር
አንብቡ!
እንስሳት ይዞታ” በሚል ርዕስ የቀረበውን
[ተ. ፓርክ-ኦች ] ምንባብ አንብቡ። ስታነቡ በሠንጠረዡ
ውስጥ የቀረቡትንና ሌሎችንም ጥያቄዎች
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ቃል
በአዕምሯችሁ እያሰላሰላችሁ ባዘጋጃችሁት
በማጣመር አንብቡ።
ሠንጠረዥ ውስጥ አስፍሩ። አንብባችሁ
[ተ. ፓርኮች ] እንደጨረሳችሁም ለጥያቄዎቻችሁ መልስ
(መ. በዚህ ዓይነት ተማሪዎች ቀሪዎቹን ስጡ።
ቃላትና ሐረጋት በቡድን ሆነው በመነጠልና

138 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፴፰


(መ.ተማሪዎችን በጥንድ በጥንድ ያደራጁ። ሥሩ
ተማሪዎች “1” ወይም “2” በማለት ራሳቸውን መ. አሁን ደግሞ የተግባር “2” ጥያቄዎችን
በቍጥር እንዲሰይሙ ያድርጉ።) መልሱ። በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ቍጥር
መ. “1” ቍጥሮች ከመጀመሪያው አንቀጽ እየተመናመነ የመጣው በምን ምክንያት
የመጀመሪያውን ዓረፍተነገር ድምፅ ይመስላችኋል?
እያሰማችሁ አንብቡ። [ተ. በአደን፣ ደኖች ለእርሻ ሲባል
[ተ. “1” ቍጥሮች የ1ኛውን አንቀጽ፣ በመመንጠራቸውና በመቃጠላቸው]
የመጀመሪያውን ዓረፍተነገር ድምፅ እያሰሙ (መ. በቀሪዎቹ ጥያቄዎች ላይ በቡድን
ያነባሉ።] ተወያይተው በቃላቸው መልስ እንዲሰጡ
መ. በጣም ጥሩ “1” ቍጥሮች 1ኛው አንቀጽ ያድርጉ። በትክክል ያልተመለሱ ጥያቄዎች
ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ። ካሉ ትክክለኛውን መልስ ይንገሯቸው።)

[ተ. “1” ቍጥሮች ይገምታሉ።] ሥሩ


መ. አሁን ደግሞ የተግባር “3”ን ጥያቄዎች
መ. በጣም ጥሩ! አሁን “1” ቍጥሮች 1ኛውን
መልሱ። ሦስቱ ብሔራዊ ፓርኮች
አንቀጽ በሙሉ አንብቡ።
ከሚመሳሰሉባቸው ነገሮች አንዱን ንገሩኝ!
[ተ. “1” ቍጥሮች ያነባሉ።]
[ተ. ሁሉም ፓርኮች ለዱር እንስሳት መጠለያ
መ. አሁን “1” ቍጥሮች የአንቀጹን ሀሳብ በመሆን ያገለግላሉ።] (መካከል ላይ በሚገኘው
አጠቃላችሁ ተናገሩ። ሳጥን ውስጥ እንዲጽፉ ይንገሯቸው።)
[ተ. “1” ቍጥሮች አጠቃለው ይናገራሉ።] መ. ፓርኮች ከሚለያዩባቸው ነገሮች አንዱን
ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?
መ. በጣም ጥሩ! “2” ቍጥሮች ደግሞ ዝርዝር
ሀሳቦችን ተናገሩ። [ተ. በስፋታቸው የሰሜን ብሔራዊ ፓርክ
14,400፣ የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ 72,000፣
[ተ. 2 ቍጥሮች የአንቀጹን ዝርዝር ሀሳቦች
የባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ 300,000
ይናገራሉ።]
ሄክታር ስፋት አላቸው።] (የእያንዳንዱን
(መ. የቍጥር “1”ና የቍጥር “2” ተማሪዎችን ፓርክ ስፋት “ልዩነት” በሚሉት ሳጥኖች
ሚና በማቀያየር 2ኛውን አንቀጽ ያስነብቡ። ውስጥ እንዲጽፉ ይንገሯቸው። ይህን ተግባር
በዚህ ዓይነት የተማሪዎችን ሚና እየቀያየሩ በ9ኛው ቀን ሠርተው እንዲመጡ የቤትሥራ
ሌሎቹንም አንቀጾች እንዲያነቡ ያድርጉ።) ይስጧቸው።)
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
ሥሩ 8ኛ ቀን
መ. ምንባቡን አንብባችኋል፤ አሁን የአንብቦ
መረዳት ጥያቄዎችን ትመልሳላችሁ። የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
በመጀመሪያ በተግባር “1” የቀረቡትን • ቃላት
የምርጫ ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ። የዛሬ • መጻፍ
70 ዓመት በኦጋዴን አካባቢ ይገኝ የነበረው
የዱር እንስሳ ምን ነበር?
[ተ. ቆርኪ]
ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. በጣም ጥሩ! “ቆርኪ” የሚለውን ቃል የያዘው
ፊደል የትኛው ነው? ለቃላትና ሐረጋት ተመሳሳይ ፍቺ
በመስጠት ዓረፍተነገር መሥራት
[ተ. መ]
ሥሩ
(መ. ቀሪዎቹን ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን የቀረቡትን
ያሠሯቸው።)

፻፴፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 139


ቃላት ተመሳሳይ ፍቻቸውን በመስጠት በመዘርዘር መልሱ።
ዓረፍተነገር መሥርቱባቸው። “አዛውንት”
መ. አሥራሁለት ብር ከሃያ ሳንቲም የሚለውን
ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቺ ስጡ!
በቊጥር ጻፉ!
[ተ. ሽማግሌ]
[ተ. ብር 12.20]
መ. በጣም ጥሩ! “አዛውንት” በሚለው ቃል
መ. ጥሩ! አሥራሦስት ነጥብ አምስት ብላችሁ
ዓረፍተነገር መሥርቱ!
በቍጥር ጻፉ።
[ተ. አንድ አዛውንት የዱር እንስሳትን
[ተ. 13.5]
እንዳንገድል መከሩን።]
መ. ጎበዞች! አሁን ደግሞ የምታውቋቸውን
(መ. ቀሪዎቹን በግል ከሠሩ በኋላ በተመሳሳይ
ብርቅዬ የዱር እንስሳት በተራቍጥር ወደጎን
ሁኔታ እየጠየቁ መልስ እንዲሠጡ ያድርጉ።
ዘርዝሩ።
ስህተታቸውን በማስተካከል ያርሟቸው።)
[ተ. 1. ዋልያ 2. ቀይ ቀበሮ 3. የደጋ
መጻፍ (30 ደቂቃ) አጋዘን…]

ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) (መ. ተማሪዎች የሠሩትን ይመልከቱ፤


ይገምግሙ። የሠሩትን በሰሌዳው ላይ ጽፈው
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት ድርሰት እንዲያሳዩ ያድርጉ። በትክክል ያልተጻፉትን
መጻፍ በማስተካከል ግብረመልስ ይስጡ።)
ሥሩ
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን፣ በድርሰት 9ኛ ቀን
መጻፍ ሥር የቀረበውን የጽሑፍ
የመገምገሚያ ሠንጠረዥ በደብተራችሁ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
አዘጋጁ። ከዚያም ምንባቡን አስተካክላችሁ • አቀላጥፎ ማንበብ
እንደገና ጻፉ።
• መናገር
(መ. ተማሪዎች የራሳቸውን ጽሑፍ ካስተካከሉ
በኋላ ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ • ሰዋስው
እንዲገማገሙ ያድርጉ። ከዚያም
ጓደኞቻቸው በሰጧቸው አስተያየት መሠረት
እንደገና አስተካክለው እንዲጽፉ ያድርጉ። የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
በመጨረሻም በየቡድናቸው እያንዳንዳቸው ሥሩ
ለቡድኑ አባላት እንዲያነቡ ያድርጉ።)
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን፣
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) በአንብቦ መረዳት የሠጠኋችሁን የቤትሥራ
መልሳችሁን አረጋግጡ። ሦስቱ ብሔራዊ
ይዘትን (አንድ ነጥብን) በጽሑፍ ውስጥ ፓርኮች ከሚመሳሰሉባቸው ነገሮች አንዱን
መጠቀም ንገሩኝ!
ሥሩ [ተ. የገቢ ምንጭ በመሆን ያገለግላሉ።] (መካከል
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን፣ በአጻጻፍ ላይ በሚገኘው ሳጥን ውስጥ እንዲጽፉ
ሥርዓት ሥር የቀረበውን ተግባር ሥሩ። ይንገሯቸው። በተመሳሳይ ሁኔታ ሌሎቹንም
በጥያቄ ቊጥር 1 ሥር በፊደል የተጻፉትን ያሠሩ።)
ብርና ሳንቲሞች አንድ ነጥብን በመጠቀም
በቍጥር ጻፉ። በጥያቄ ቊጥር 2 ሥር በፊደል 18. አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
የተጻፉትን ሙሉና ሽርፍራፊ ቍጥሮች አንድ
ነጥብን ተጠቅማችሁ በቍጥር ጻፉ። በጥያቄ
በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ይዞታ
ቊጥር 3 ሥር ደግሞ የምታውቋቸውን
ብርቅዬ የዱር እንስሳት በተራቍጥር ወደጎን

140 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፵


18ሀ. ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) የትኛው የበለጠ ጥቅም ይሠጣል?
ሀሳባችሁን በምክንያት በማስደገፍ
ሥሩ ተከራከሩ። በመማሪያ መጽሐፋችሁ
መ. ዛሬ በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ ድምፅ ያለውን ሠንጠረዥ በመጠቀም መሬቶቹ
እያሰማችሁ ታነባላችሁ። ከዚያ በፊት ግን ለፓርክ ወይም ለእርሻ አገልግሎት ቢውሉ
ባለፈው ክፍለጊዜ ያነበባችሁትን ምንባብ የሚኖረውን ጥቅምና ጉዳት እያወዳደራችሁ
ይዘት በማስታወስ አንድ ጥያቄ መልሱ። ተከራከሩ። (ተማሪዎች ሲከራከሩ በየቡድኑ
“በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ይዞታ” በሚል እየተዘዋወሩ የማወዳደርና የማነፃፀር ስልትን
ርዕስ በቀረበው ምንባብ ውስጥ የተጠቀሱት መጠቀማቸውን፣ ሀሳባቸውን በምክንያት
ፓርኮች ማን ማን ናቸው? ማስደገፋቸውን፣ ሀሳባቸውን በቅደምተከተል
[ተ. የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የባሌ ማደራጀታቸውንና የንግግራቸውን ግልፅነት
ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የአዋሽ ብሔራዊ ይገምግሙ።)
ፓርክ]
መ. በጣም ጥሩ! እነዚህ ፓርኮች የተቋቋሙበት ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ዓላማ ምንድን ነው?
የወልና የተጸውዖ ስሞች እንደባለቤት
[ተ. በውስጣቸው የሚገኙ የዱር እንስሳት ሥሩ
እንዳይጠፉ ለመጠበቅ]
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው፣ ቀን በሰዋስው ሥር
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ለማንበብ ተዘጋጁ! በቀረቡት ዓረፍተነገሮች ውስጥ የሚገኙትን
ባለቤቶች እያወጣችሁ በደብተራችሁ
ማንበብ (8 ደቂቃ) ጻፉ። ከዚያም ከፊትለፊታቸው የተጸውዖ
ሥሩ ወይም የወል ስም እያላችሁ ጻፉ። ለምሳሌ
(መ. አቀላጥፈው የሚያነቡትን ተማሪዎች “መጻሕፍት የዕውቀት ምንጭ ናቸው”
አቀላጥፈው ከማያነቡት ጋር በማቀናጀት በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱ የትኛው
በጥንድ በጥንድ እንዲቀመጡ ያድርጉ።) ነው?

መ. አሁን “በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ይዞታ” [ተ. መጻሕፍት] (ቃሉን በደብተራቸው እንዲጽፉ
የሚለውን ምንባብ የመጀመሪያዎቹን አራት ይንገሯቸው።)
አንቀጾች ድምፅ እያሰማችሁ ተራበተራ መ. በጣም ጥሩ! ቃሉ የተጸውዖ ስም ነው ወይስ
አንብቡ። (በመምህር መምሪያ ምዕራፍ 3፣ የወል?
በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን አቀላጥፎ
ማንበብ በ“ሥሩ” ሥር የቀረበውን ዝርዝር [ተ. የወል] (መጻሕፍት ከሚለው ቃል ፊት ለፊት
አሠራር በመከተል ተማሪዎች እንዲያነቡ “የወል ስም” ብለው እንዲጽፉ ይንገሯቸው።)
በማድረግ የማንበብ ችሎታቸውን መ. ለምን የወል ስም አላችሁ?
ይገምግሙ።)
[ተ. ምክንያቱም “መጽሐፍ” የሚለው ቃል
መናገር (15 ደቂቃ) መጻሕፍት በሙሉ የሚጠሩበት የጋራ ስያሜ
ነው።]
በማወዳደርና በማነፃፀር ስልት ሀሳብን
አደራጅቶ መከራከር (መ. ሠርተው እንደጨረሱ ደብተራቸውን
እንዲቀያየሩ ያድርጉ። በመልሶቹ ላይ
ሥሩ እየተወያዩ እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
(መ. ተማሪዎችን ስድስት አባላት ባሏቸው
ቡድኖች ያደራጁና ሦስት ሦስት ሆነው መ. አሁን ደግሞ አምስት የወል፣ አምስት
የተለያየ ሀሳብ ደግፈው እንዲከራከሩ የተጸውዖ ስሞች መርጣችሁ እንደባለቤት
ያድርጉ) በመጠቀም ዓረፍተነገር ሥሩባቸው። ለምሳሌ
በመጽሐፋችሁ “ውሻ”ና “አፍሪካ” የሚሉ
መ. የፓርኮች መሬት ለዱር እንስሳት ሁለት ቃላት ቀርበዋል። ከሁለቱ የወል ስም
መኖሪያነት ከሚውልና ለእርሻ ከሚውል የሆነው የትኛው ነው? (ለአንድ/ዲት ተማሪ

፻፵፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 141


ዕድል ይስጡ።)
[ተ. ውሻ]
(መ. “ውሻ”ን ለምን የወል ስም ነው አላችሁ?)
[ተ. ምክንያቱም የብዙ ውሾች የጋራ መጠሪያ
ነው።]
መ. በጣም ጥሩ! በዚህ ቃል ዓረፍተነገር ሥሩበት።
[ተ. ውሻ ግቢን ይጠብቃል።] (ተማሪዎች ሌሎች
ዓረፍተነገሮች ሊመሠርቱ ይችላሉ።)
መ. “አፍሪካ” የሚለው ቃል ምን ዓይነት ስም
ነው?
[ተ. የተጸውዖ]
መ. ለምን የተጸውዖ ስም ነው አላችሁ?
[ተ. ምክንያቱም አፍሪካ ለምትባለው አህጉር
የግል መጠሪያ ነው።]
መ. በጣም ጥሩ! በዚሁ ቃል ዓረፍተነገር
መሥርቱ።
[ተ. የአፍሪካ አህጉር በርካታ ሀገራትን ይዛለች።]
(ተማሪዎች ሌሎች ዓረፍተነገሮች ሊመሠርቱ
ይችላሉ። በዚህ ሁኔታ የተማሪዎችን መልሶች
ይቀበሉ።)

142 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 7 ፻፵፪


ምዕራፍ 8 ባህላዊ ጨዋታዎች
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• "ባህላዊ ጨዋታዎች" በሚል የምንባብ ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት በንግግርና በጽሑፍ ይጠቀማሉ፤
• የአንድን ባህላዊ ጨዋታ ሂደት በቅደምተከተል ይጽፋሉ፤
• የሠላምታ ደብዳቤ ይጽፋሉ፤
• በቅደምተከተል ስልት የቀረቡ ምንባቦችን አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• "አሸንድዬ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• "ባህላዊ ጨዋታዎች" በሚል የምንባብ ይዘት መነሻነት ይናገራሉ፤
• ቅጽሎችን፣ መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮችን በዓረፍተነገሮች ውስጥ ይጠቀማሉ።

ተጣምሮ የተጻፈውን በማጣመር አንብቡ።


1ኛ ሳምንት
[ተ. ሩሯን]
የዐውዳመት ባህላዊ ጨዋታዎች
(መ. ቀሪዎቹን በዚህ ዓይነት ቃላት ያስነብቡ፤
በትክክል ያልተነበቡ ቃላትን፣ በትክክል
1ኛ ቀን በማንበብ ያሳዩዋቸው።)

የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ማንበብ (30 ደቂቃ)


• የቃላት ጥናት
የገና ጨዋታ ትውስታ
• ማንበብ
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
የቃላት ጥናት (10 ደቂቃ) ሥሩ
መ. ዛሬ "የገና ጨዋታ ትውስታ" በሚል ርዕስ
መነጠልና ማጣመር የቀረበ ምንባብ ታነባላችሁ። በቅድሚያ ግን
ሥሩ የቅድመንባብ ተግባራትን ሥሩ። ምን ምን
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን በቃላት ባህላዊ ጨዋታዎች (ስፖርቶች) ታውቃላችሁ?
ጥናት ሥር የቀረቡትን ቃላት በመነጣጠልና [ተ. ገበጣ፣ ቅልሞሽ ፣ የገና ጨዋታ፣ ትግል…]
በማጣመር አንብቡ።
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ከምንባቡ ርዕስ
መ. አሁን ደግሞ በሁለተኛው ሠንጠረዥ ሥር የሚገኘውን ሥዕል ተመልከቱና ምንባቡ
ውስጥ በ"ሀ" ትይዩ ተነጣጥሎ የተጻፈውን ስለምን እንደሚገልፅ ገምቱ። (ተማሪዎች
በመነጣጠል አንብቡ። ግምታቸውን እንዲናገሩ ያድርጉ።)
[ተ. ሩር-ዋ-ን]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ በ"ሀ" ትይዩ

፻፵፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 143


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) መ. ፍቺው ምንድን ነው?
ልሥራ [መተ. አዛዥ፣ ኃላፊ…]
መ. ተማሪዎች፣ በምታነቡበት ወቅት መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ "አለቃ" የሚለው ቃል
የማታውቋቸው አዳዲስ ቃላት ሊያጋጥሟችሁ ተቃራኒ ፍቺ ምንድን ነው?
ይችላሉ። የአዳዲስ ቃላትን ፍቺ ለማወቅ
አንዱ መንገድ ቃላቱ በዓረፍተነገሮች ውስጥ [መተ. ታዛዥ፣ የበታች ሠራተኛ]
የገቡበትን ሁኔታ ወይም ዐውድ ማጤን ነው። መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ ምንዝር ማለት የበታች፣
አንድ ምሳሌ ሠርቼ ላሳያችሁ። (13ኛውን ታዛዥ ወዘተ. ማለት ይሆናል።
ምልልስ ለተማሪዎች ያንብቡላቸው። ከዚያም
"…ተቆራቁሰው ይለጓታል" የሚለው ላይ ሥሩ
ሲደርሱ ማንበብዎን ያቁሙ።) መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን
"በማንበብ ሂደት" ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
መ. ባነበብኩት አንቀጽ ውስጥ "ተቆራቁሰው" አዘጋጁ። "የገና ጨዋታ ትውስታ" በሚል
የሚል አዲስ ቃል አጋጥሞኛል። የዚህን የቀረበውን ምንባብ ድምፅ ሳታሰሙ አንብቡ።
ቃል ፍቺ ከዚህ በፊት አላውቀውም። የሚያጋጥሟችሁን አዳዲስ ቃላት በሠንጠረዡ
ነገርግን በዓረፍተነገሩ ውስጥ ያሉ ፍንጮችን ውስጥ መዝግቡ። ከቃላቱ ጎን የሚገኙ
በመጠቀም የቃሉን ፍቺ መረዳት እችላለሁ። ፍንጮችን በመጠቀም የቃላቱን ዐውዳዊ ፍቺ
ዓረፍተነገሩ "ከሁለቱ ቡድኖች ቀልጣፋ ተረዱ፤ የተረዳችሁትንም በሠንጠረዡ ውስጥ
የሆኑት ተመርጠው ጥንጓን ተቆራቁሰው ጻፉ።
ይለጓታል" ይላል። ቀልጣፋ የሆኑ ሁለት
ተጫዋቾችን ከተቃራኒ ቡድኖች መምረጥ (መ. እስከ ምልልስ ሰባት(7) ድረስ ካነበቡ በኋላ
ለምን አስፈለገ? ጥንጓን ለመለጋት በፍጥነት ያስቁሙ።)
መሻማት ያስፈልጋል ማለት ነው። ስለዚህ መ. እስካሁን ስታነቡ ያጋጠሟችሁን አዳዲስ
"ተቆራቁሰው" የሚለው ቃል "ተሻምተው" ቃላት ንገሩኝ። (ተማሪዎች የሚነግሩዎትን
የሚል ዐውዳዊ ፍቺ አለው። ቃላት በሰሌዳው ላይ ይጻፉ።)
እንሥራ [ተ. ተማሪዎች ያጋጠሟቸውን አዳዲስ ቃላት
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። (21ኛውን ይናገራሉ።]
ምልልስ ያንብቡ "በመቀጠልም፣ በገና
መ. በጣም ጥሩ! የቃላቱ ፍቺ ምንድን ነው?
ጨዋታ ጊዜ ትልቅ ትንሽ፣ አለቃ ምንዝር
የሚባል ነገር የለም" የሚለውን ዓረፍተነገር [ተ. ፍቻቸውን ይናገራሉ።]
ከተማሪዎች ጋር አብረው ያንብቡ።)
መ. ፍቻቸውን እንዴት አወቃችሁ?
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ የሚገኘው አዲስ
[ተ. ፍቻቸውን ለማወቅ የተጠቀሙበትን
ቃል የትኛው ነው?
ስልት ይናገራሉ።] (መልሳቸውን ባዘጋጁት
[መተ. ምንዝር] ሠንጠረዥ ውስጥ ይጻፉ።)
መ. በጣም ጥሩ! የቃሉን ፍቺ ለመረዳት መ. በጣም ጥሩ ነው! አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ!
በዓረፍተነገሩ ውስጥ ፍንጭ ሰጪ ቃላት/
ሐረጋት ካሉ አብረን እናስተውል። ከጎኑ
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
"ትልቅ ትንሽ" የሚሉ ቃላት አሉ። የእነዚህ ሥሩ
ቃላት ግንኙነት ምንድን ነው? መ. አሁን አንብባችሁ ጨርሳችኋል። ስታነቡ
[መተ. ተቃራኒ ናቸው።] ያገኛችኋቸው አዳዲስ ቃላት ምን ምን
ናቸው? ፍቻቸውስ ምንድን ነው? ፍቻቸውን
መ. በጣም ጥሩ! ስለዚህ "አለቃ" እና "ምንዝር" እንዴት እንዳወቃችሁት በቡድን ተወያዩ።
የሚሉት ቃላትም ተቃራኒ ናቸው ማለት ነው። (ለ2 ደቂቃ ያህል እንዲወያዩ ያድርጉ።)
"አለቃ" የሚለውን ቃል ፍቺ ታውቃላችሁ?
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ የአንብቦ መረዳት
[መተ. አዎ!] ጥያቄዎችን መልሱ። በታሪኩ ውስጥ ያሉት

144 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፵፬


ገፀባህርያት እነማን ናቸው? ጠባሳ ይፈጠራል።] (ተማሪዎች በልዩ ልዩ
መንገድ ሊመልሱ ይችላሉ።)
[ተ. አቶ ጫኔ፣ ወይዘሮ ፈትለወርቅና ተመስገን
ናቸው።] ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ከሀ-መ የቀረቡትን መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን በቃላት
ጥያቄዎች ተማሪዎች በቃላቸው እንዲመልሱ ሥር ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሠመረባቸውን
ያድርጉ።) ቃላት በመጠቀም ጥያቄዎቹን በጽሑፍ
መልሱ።
መ. ከሠ-ቀ የቀረቡትን ጥያቄዎች በአነስተኛ
ቡድን ተደራጅታችሁ ሥሩና መልሳችሁን መ. ከጨዋታ በፊት የሚያቧድኑት እነማን
አንፀባርቁ። (መልሳቸውን የሚያንፀባርቁበት ናቸው?
ጊዜ ያመቻቹላቸው።) [ተ. ከጨዋታ በፊት የሚያቧድኑት የቡድን
አባቶች ናቸው።
2ኛ ቀን (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ጥያቄዎች ተማሪዎች
በጽሑፍ እንዲመልሱ ያድርጉ። ተግባሩን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች እንደጨረሱ ደብተር ተቀያይረው በጻፏቸው
• ቃላት ዓረፍተነገሮች ላይ እየተወያዩ እንዲተራረሙ
ያድርጉ። በመጨረሻም ተግባር "2"ን ለ3ኛ
• መጻፍ
ቀን የቤትሥራ ይስጧቸው።)

መጻፍ (30 ደቂቃ)


ቃላት (10 ደቂቃ) ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
አዳዲስ ቃላትንና ሐረጋትን ተጠቅሞ እየተቀባበሉ መጻፍ
ጥያቄ መመለስ
ሥሩ
ልሥራ (መ. ተማሪዎችን አራት፣ አራት አባላት ባሏቸው
መ. አሁን የተማራችኋቸውን አዳዲስ ቃላት ቡድኖች ያደራጁ። ከዚያም "የገና ጨዋታ
በመጠቀም የሚቀርቡላችሁን ጥያቄዎች ትውስታ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ
እንዴት እንደምትመልሱ አሳያችኋለሁ። ለ5 ደቂቃ ያህል እንዲያነቡ ያድርጉ። ቀጥሎ
ለምሳሌ በጥያቄው ውስጥ የተሠመረበትን እያንዳንዱ ቡድን አንድ አንድ ወረቀት
ቃል በመጠቀም የሚጠየቀውን ጥያቄ እንዲያዘጋጅ ያድርጉ። ከዚያም ከየቡድኑ
እመልሳለሁ። መካከል አንድ አንድ ተማሪዎች የገና ጨዋታ
መ. መገላገል የሚያስፈልገው ምን ሲያጋጥም ሂደትን በተመለከተ አንድ ዓረፍተነገር
ነው? (ጥያቄውን በሰሌዳው ላይ ይጻፉ። እንዲመሠርቱ ያድርጉ። በመቀጠል ወረቀቱን
"መገላገል" የሚለውን ቃል "ገ"ን አላልተው ከጎናቸው ላሉ ተማሪዎች ያስተላልፉ።
ያንብቡ።) ሁለተኛዎቹ ተማሪዎች የመጀመሪያዎቹ
የጻፉትን ዓረፍተነገር አንበው ከመጀመሪያው
[መ. መገላገል የሚያስፈልገው ሰዎች ሲጣሉ ሀሳብ ጋር የሚስማማ ሌላ ዓረፍተነገር
ጠባቸው እንዳይባባስ ነው።] (በሰሌዳው ላይ እንዲመሠርቱ ያድርጉ። በዚህ ዓይነት
ይጻፉ።) ተማሪዎች በቡድናቸው ውስጥ ወረቀቱን
እንሥራ እየተቀባበሉ ተከታታይ ዓረፍተነገሮችን
መጻፋቸውን ይቀጥሉ። ተማሪዎች ሲጽፉ
መ. አሁን በቀረበው ጥያቄያዊ ዓረፍተነገር
በየቡድኑ እየተዘዋወሩ ይመልከቱ፤ በመጠየቅ፣
የተሠመረበትን ቃል በመጠቀም ጥያቄውን
ፍንጭ በመስጠት ይደግፏቸው። ለምሳሌ
እንመልሳለን።
"በገና ጨዋታ ሂደት የመጀመሪያው ተግባር
መ. ጠባሳ በምን ምክንያት ይፈጠራል? ምንድን ነው?፣ ከዚያስ…" በማለት ተማሪዎች
[መተ. በአደጋ ምክንያት የሚከሰት ቁስለት ሲድን እንዲጽፉ ማበረታታት ይቻላል። ከዚያም

፻፵፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 145


በቡድን እየተወያዩ የጻፉትን አደራጅተው [መተ. የላኪ ፊርማና ስም]
በአንድ አንቀጽ እንዲጽፉ ያድርጉና ወረቀቱን
ሥሩ
ይሰብስቡ። በመጨረሻም የተሻለ ፍሰት
ያለውን፣ ተገቢውን ቅደምተከተል የያዘውን መ. አሁን የቀረበውን የሠላምታ ደብዳቤ ቅርፅ
ጽሑፍ በመምረጥ የቡድኑ ተወካይ እንዲያነብ/ የሚመለከቱ ጥያቄዎችን ትመልሳላችሁ።
እንድታነብ ያድርጉ። በአካባቢያቸው በላኪ አድራሻ የተገለጹት ነገሮች ምን ምን
ከሚያውቋቸው ባህላዊ ጨዋታዎች መካከል ናቸው?
ድርሰት ለመጻፍ የሚያመቻቸውን ርዕስ [ተ. የላኪዋ ስም፣ የምትገኝበት ቦታ፣ የመልዕክት
መርጠው በቅደምተከተል ስልት የቢጋር ሣጥን ቍጥር፣ የምትኖርበት ከተማና ቀን]
ሠንጠረዥ አዘጋጅተው እንዲመጡ ለቀጣዩ
መ. በጣም ጥሩ! በተቀባይ አድራሻ የተገለጹት
ሳምንት የቤትሥራ ይስጧቸው።)
ነገሮችስ?
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) [ተ. የተቀባይ ስም፣ የሚገኝበት ልዩ ቦታ፣
የሠላምታ ደብዳቤ አጻጻፍ የመልዕክት ሣጥን ቍጥር፣ የከተማው ስም]
እንሥራ መ. ጎበዝ! ከተቀባይ አድራሻ ቀጥሎ የተገለጸው
መ. የሠላምታ ደብዳቤ የሚባለው ሰዎች ሩቅ ላሉ ምንድን ነው?
ወዳጆቻቸው ወይም ዘመዶቻቸው የሚጽፉት [ተ. ሠላምታ]
መልዕክት ነው። የሠላምታ ደብዳቤ የራሱ
የሆነ ቅርፅ አለው። ቅርፁን ከ1ኛው ሳምንት (መ. በዚህ ዓይነት እየጠየቁ ከተማሪዎች መልስ
ከ2ኛው ቀን በአጻጻፍ ሥርዓት ሥር ከቀረበው ይቀበሉ።በመጨረሻም ትክክለኛ መልስ
ደብዳቤ መመልከት ይቻላል። በመንገር ግብረመልስ ይስጡ።)
መ. ተማሪዎች! በመጽሐፋችሁ የቀረበውን
ደብዳቤ በመጠቀም በሠላምታ ደብዳቤ ቅርፅ 3ኛ ቀን
ላይ እንወያይ። በደብዳቤው ቅርፅ፣ የቀኝ
ጠርዝ ራስጌ ላይ የተጻፈው ምንድን ነው? የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
[መተ. የላኪ አድራሻ] • አቀላጥፎ ማንበብ

መ. በጣም ጥሩ! ወረድ ብሎ በስተግራ ጠርዝ • ማዳመጥ


የተጻፈውስ ምንድን ነው? • ሰዋስው
[መተ. የተቀባይ አድራሻ]
መ. ጎበዝ! ከተቀባይ አድራሻ ቀጥሎ የተጻፈው
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ምንድን ነው?
ሥሩ
[መተ. ሠላምታ]
(መ. ተማሪዎች የቤትሥራውን መሥራታቸውን
መ. በጣም ጥሩ! ከሠላምታው ቀጥሎስ ምን በማረጋገጥ እየጠየቁ መልሳቸውን ይቀበሉ።)
ተጽፏል?
መ. በመጀመሪያው ዓረፍተነገር ባለው ክፍት ቦታ
[መተ. መግቢያ] የሚገባው ቃል የቱ ነው?
መ. በጣም ጎበዝ! ከመግቢያው ቀጥሎ የተጻፈው [ተ. ስለመታኝ]
ምንድን ነው?
መ. በጣም ጥሩ! ቃሉን በዓረፍተነገሩ ውስጥ
[መተ. ሐተታ] አስገብታችሁ አንብቡ።
መ. ከሐተታው ቀጥሎ የተጻፈው ምንድን ነው? [ተ. ግንባሬ ያበጠው የገና ሩር ስለመታኝ ነው።]
[መተ. መደምደሚያ] መ. በጣም ጥሩ! (የቀሩትንም መልሶች በዚህ
መ. በጣም ጥሩ! በመጨረሻስ ምን ተጽፏል?
ዓይነት ይቀበሉ። በትክክል ያልተመለሱ ካሉ
ትክክለኛውን መልስ በመንገር ግብረመልስ

146 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፵፮


ይስጡ።) [መተ. በቅብብሎሽ ያነባሉ።]
ሥሩ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) መ. አሁን ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ምልልሱን
የገና ጨዋታ ትውስታ እየተቀባበላችሁ አንብቡ። የተቀበላችሁት
ሚና (ድርሻ) የልጅ ከሆነ እንደልጅ፣
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) የአባት ከሆነ እንደትልቅ ሰው ድምጻችሁን
ሥሩ እያስመሰላችሁ አንብቡ። ገፀባህርያቱ ሲደነቁ
መ. አሁን ድምፅ እያሰሙ የማንበብ ልምምድ እየተደነቃችሁ፣ ሲጠይቁ እየጠየቃችሁ፣
ታደርጋላችሁ። በቅድሚያ ግን ለማንበብ ሲቆጩ እየተቆጫችሁ ለማንበብ ሞክሩ።
የሚረዳችሁን አንድ ተግባር ትሠራላችሁ። የመጀመሪያውን ገፅ በዚህ ሁኔታ አንብባችሁ
ስትጨርሱ ሚና (ድርሻ) በመቀያየር
አቶ ጫኔ፡- "የገና ጨዋታ! ወይኔ!...አምልጦሃል ደግማችሁ አንብቡ።
በለኛ!" አሉ በቁጭት። (ይህን ዓረፍተነገር
ሰሌዳው ላይ ይጻፉ።) [ተ. በቅብብሎሽ ያነባሉ።]
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ የሚታየው የአቶ (መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ እርስዎ
ጫኔ ስሜት ምን ይመስላችኋል? በሠጧቸው መመሪያ መሠረት እያነበቡ
መሆኑን ይከታተሉ። በተለይም በተገቢው
[ተ. የቁጭት ስሜት] የድምፅ ቃና ማንበባቸውን በትኩረት
መ. በጣም ጥሩ! ይህን ዓረፍተነገር በቁጭት ይከታተሉ።)
ስሜት አንብባችሁ ልታሳዩኝ ትችላላችሁ?
(ተማሪዎች በተራ ድምፅ በማሰማት ማዳመጥ (15 ደቂቃ)
እንዲያነቡ ያድርጉ።)
አሸንድዬ
[ተ. በቁጭት ስሜት ያነባሉ።]
ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
ማንበብ (8 ደቂቃ)
ከሥዕል የምንባብ ሀሳብ መገመት
ልሥራ
ሥሩ
መ. ዛሬ ድምፅ እያሰሙ የማንበብ ልምምድ
ታደርጋላችሁ። በመጀመሪያ እኔ አነባለሁ። መ. "አሸንድዬ" ከሚለው የማዳመጥ ምንባብ
("የገና ጨዋታ ትዝታ" የሚለውን ምንባብ ርዕስ ሥር የቀረበውን ሥዕል ተመልከቱ፤
እስከ 11ኛው ምልልስ ድረስ ያንብቡላቸው። ምን ዓይነት ባህላዊ ጨዋታ እየተጫወቱ
ድምፅዎን እንደሽማግሌ፣ እንደልጅ እየቀያየሩ፣ ይመስላችኋል?
የገፀባህርይያቱን የመደነቅ፣ የቁጭት…ስሜት [ተ. ግምታቸውን ይናገራሉ።]
በሚገልጽ ሁኔታ የድምፅዎን ቃና እየለዋወጡ
መ. በጣም ጥሩ! ግምታችሁ ትክክል መሆን
ያንብቡ።)
አለመሆኑን አዳምጣችሁ ታረጋግጣላችሁ።
[መ. አንብበው ያሳያሉ።]
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)
እንሥራ
ሥሩ
(መ. ከርስዎ ጋር የሚያነብ/የምታነብ አንድ
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን በማዳመጥ
ተማሪ ይምረጡ። ተማሪዎቹም ጥንድ ጥንድ
ሂደት ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
ሆነው ለማንበብ እንዲዘጋጁ ያድርጉ።)
በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም "አሸንድዬ"
መ. አሁን ጥንድ ጥንድ ሆነን አንዳችን እንደአባት፣ በሚል ርዕስ የማነብላችሁን ምንባብ
ሌሎቻችን እንደልጅ ሆነን እየተቀባበልን እያዳመጣችሁ በሠንጠረዡ ውስጥ የቀረቡትን
ምልልሱን እናንብብ። (እርስዎና የተመረጠው/ ቃላት ፍቺ ጻፉ።
ችው ተማሪ የምታነቡበትን ሁኔታ ተማሪዎች
[ተ. ሠንጠረዥ አዘጋጅተው የቃላቱን ፍቺ እየጻፉ
እየተከተሉ እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ያዳምጣሉ።]

፻፵፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 147


አሸንድዬ አሉ እንጂ ተዘንብሏል ጠጂ።
እያሉ በጨዋ ወግ አወድሰውና አስፈቅደው
የአሸንድዬ ባህላዊ ጨዋታ የሚከወነው በክረምት
ወደውስጥ ይገባሉ። ከዚያም በጥዑም ዜማ
መገባደጃ ላይ ነው። ጊዜው ብሩህ ሰማይ ሊታይ፣
ይጫወታሉ። የጨዋታቸው ስንኞች ፍቅርን፣
አበባው በምድር ላይ ሊፈነድቅ፣ ፀሐይ ሙቀቷን
ጀግንነትን፣ የሥራ ክቡርነትን፣ ሙያን፣ ውበትን
ልትሰጥ፣ አዝመራ ሊያፈራ የሚቃረብበት ወቅት
ወዘተ. የሚያወድሱ ናቸው። ባለቤቱ ሞቅ ያለ
ነው። በዚህ ጊዜ በልጃገረዶች ዘንድ ደስታና
ስጦታ እንዲያበረክቱላቸው ለመገፋፋትም፣
ፈንጠዝያ ይሆናል።
*** ምን የሚሉ ይመሥላችኋል?***
ልጃገረዶች በበዓሉ ዋዜማ ከወንዝ ዳር
አሸንድዬ የተባለውን ረጅም ቄጠማ ቆርጠው ጌታው ስም ይሻል፣ ስም ይሻል
ያመጣሉ። በበዓሉ ዕለት አምረው፣ ተውበው፣
አንድ ብር እንኳን ጠፍቶ ያመሻል፣
በነጫጭ ባህላዊ ልብሳቸው ላይ አሸንድያቸውን
በወገባቸው ታጥቀው ብቅ ይላሉ። በየአጥቢያቸው በሬ ከጋጡ ሞቶ ያመሻል፣
ይሰበሰቡና በመጀመሪያ ታላላቅ ከሚባሉና ይሉታል።
ከሹሞች ቤት በመሄድ የደስታ መግለጫቸውን
ያሰማሉ። ከዚያም በሥልጣንና በዕድሜ ተዋረድ ከዚያም ተሸልመው፣ አመስግነውና ተመሰግነው
ወዳሉት ሰዎች ቤት ያመራሉ። ሁሉንም ከቤት ይወጣሉ። ወደሌላ ቤትም ሄደው
ነዋሪዎች በስድስት ቀናት ውስጥ ያዳርሳሉ። ይጨፍራሉ። በገጠር አካባቢ እህል፣ ዳቦ፣ ጠላ፣
እስከእንቁጣጣሽ ድረስም የሚቆዩ አሉ። ሀብታም እንጀራ፣ በግ፣ ፍየል፣ እርጎ፣ በከተማ ደግሞ ብር
ነው፤ ድሃ ነው ብለው የሚለዩት ሰው አይኖርም። ይሰጣሉ። ቀኑን ሙሉ በየቤቱ እየዞሩ ሲጨፍሩ
ይውሉና አመሻሽ ላይ ወደሜዳ ወጥተው
አሸንድዬዎች ከአንዱ ቤት ወደሌላው ቤት ሲሄዱ በየቡድናቸው ሲዘፍኑ ያመሻሉ። በዚህ ዓይነት
በዜማ አውራጃቸው እየተመሩና እየተቀባበሉ ሰንብተው በዓሉ ነሐሴ 21 ቀን ያበቃል።
እንደሚከተለው ያዜማሉ። በመስቀል ከ"ሆያ ሆዬ" ጨፋሪዎች ጋር ደግሰው
***ከዜማዎቹ መካከል የምታውቁትን የሸለሟቸውን ሰዎች አብልተው፣ አጠጥተው፣
ንገሩኝ?*** ተጫውተው ይሰነባበታሉ።

አጀባ ሆኗል ጅብጀባ፤ በአጠቃላይ ዓመታዊው የአሸንድዬ በዓል


በትግራይና በአማራ ክልል፣ በዋግና በላስታ
በየት ልንገባ፤ በደመቀ ሁኔታ ይከበራል። የጊዜና የቦታ
አጀባ ሆኗል ፈረሱ፣ መራራቅ እንዲሁም የቋንቋ ልዩነት ቢኖርም
አከባበሩ በሁሉም ቦታ አንድ ዓይነት ነው።
ወዴት ነው እሱ?
አሸንድዬ ባህላዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ
አሽንድዬ አሸንድ አበባ፣ ጠቀሜታ ያለው አኩሪ ባህል ስለሆነ ሊጠበቅና
እሽርግፍ እንደወለባ። ሊስፋፋ ይገባዋል።
(ከሃራተዋህዶ ወርድኘሬስ፡ ድረገጽ፣ ነሐሴ 19/2001
አደይ አበባ አደይ አበባ፣ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎ የተወሰደ።)
ነሽ ውባ ውባ። አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ)
አደዪቱ መስከረሚቱ፣
ሥሩ
መውደድ እንደሌሊቱ። መ. አሁን በሠንጠረዥ ውስጥ ለቀረቡት
እንዲህ እያሉ ዜማውን ተከትለው እየተወዛወዙ፣ ቃላት እያዳመጣችሁ የሰጣችሁትን ፍቺ
ወደላይም እየዘለሉ፣ ይጨፍራሉ። ከመኖሪያቤት እንመልከት። "አሸንድዬ" የሚለው ቃል
አካባቢም ሲደርሱ ከግቢው ውጪ ሆነው፣ በምንባቡ ውስጥ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
አስገባኝ በረኛ፣ [ተ. የበዓል ስያሜ፣ ረጅም ቄጤማ]
አስገባኝ ከልካይ፣
(መ. በዚህ ዓይነት የሌሎቹንም ቃላት ፍቺ
እመቤቴን ልይ። እንዲናገሩ ያድርጉ።)
ጌታው አሉ ወይ፣ አሉ ወይ፣ መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን በአዳምጦ
አሉ እንጂ ግቡ ይላሉ እንጂ፣ መረዳት ሥር የቀረቡትን ጥያቄዎች መልሱ።
በአሸንድዬ በዓል ልጃገረዶች ምን ዓይነት

148 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፵፰


ልብስ ይለብሳሉ? መ. በጣም ጥሩ! ቍጥሮች ከቅጽሎች ጋር
ተቀናጅተው ስምን ይገልጻሉ። መጣኝ
[ተ. ነጭ ባህላዊ ልብስ]
ቍጥሮች ከቅጽሎች ጋር ተቀናጅተው እንዴት
መ. በጣም ጥሩ! (ከ"ሀ"-"መ" የቀረቡትን ጥያቄዎች ስምን እንደሚገልጹ በምሳሌ ልታሳዩኝ
በግል በቃል እንዲመልሱ ያድርጉ። ትችላላችሁ?
ከ"ሠ" እስከ"ሰ" የቀረቡትን ደግሞ በቡድን
[መተ. አንድ ቀይ ፍየል]
እየተወያዩ እንዲመልሱ ያድርጉ።)
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ደረጃ አመልካች
(መ. በአካባቢያቸው የሚያውቁትን የልጆች
ቍጥሮች ከቅጽሎች ጋር ተቀናጅተው
ጨዋታ ለሚቀጥለው ሳምንት በቡድን
እንዴት ስምን እንደሚገልጹ በምሳሌ ልታሳዩ
ተለማምደው እንዲመጡ ይንገሯቸው።)
ትችላላችሁ።?

ሰዋስው (10 ደቂቃ) [መተ. ሁለተኛዋ ረጅም ልጅ]

ቅጽል፣ መጣኝና ደረጃ አመልካች መ. በጣም ጥሩ! "ስድስት ነጫጭ በጎች አሉኝ"
ቍጥሮች በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ያለው ቍጥር
ምንድን ነው?
እንሥራ
[መተ. ስድስት]
መ. በምዕራፍ 5 ስለቅጽሎች ተምራችኋል።
የቅጽልን ምንነት አስታውሳችሁ ልትነግሩኝ መ. ቍጥሩ መጣኝ ነው ወይስ ደረጃ አመልካች?
ትችላላችሁ?
[መተ. መጣኝ]
[መተ. ቅጽሎች የነገሮችን ቀለም፣ መጠን፣
መ. በጣም ጥሩ! በዓረፍተነገሩ ውስጥ ያለው
ባህርይ፣ ወዘተ. የሚገልጹ ቃላት ናቸው።]
ቅጽል የትኛው ነው?
መ. በጣም ጥሩ! ለቅጽሎች ምሳሌ ልትነግሩኝ
[መተ. ነጫጭ]
ትችላላችሁ?
ሥሩ
[መተ. ቀይ፣ ረጅም፣ ጎበዝ…]
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን በሰዋስው ሥር
መ. ቅጽሎች የሚገልጹት ምንን ነው? የቀረቡት ዓረፍተነገሮች ውስጥ የሚገኙትን
[መተ. ስምን] መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮች እንዲሁም
ቅጽሎች ለይታችሁ ጻፉ። "የከተማው
መ. በጣም ጥሩ! ቅጽሎች እንዴት ስምን ሰባተኛ ትልቅ ፎቅ ቀለም ተቀባ" በሚለው
እንደሚገልጹ በምሳሌ ልታሳዩኝ ትችላላችሁ? ዓረፍተነገር ውስጥ ቍጥሩ የትኛው ነው?
[መተ. ቀይ አበባ] [ተ. ሰባተኛው]
መ. ጎበዝ! "ቀይ" የሚለው ቅጽል የአበባውን ቀለም መ. ምን ዓይነት ቍጥር ነው?
ይገልጻል። በምዕራፍ 2 ላይ ስለቍጥሮች
ተምራችኋል። ስንት ዓይነት ቍጥሮች አሉ? [ተ. ደረጃ አመልካች ቍጥር]

[መተ. ሁለት ዓይነት] መ. በጣም ጥሩ! ቅጽሉስ የትኛው ነው?

መ. ምንና ምን ናቸው? [ተ. ትልቅ]

[መተ. መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮች] መ. በጣም (በዚህ ዓይነት በግል


ጥሩ!
በደብተራቸው እንዲሠሩ ያድርጉ።
መ. በጣም ጥሩ! ለመጣኝ ቍጥሮች ምሳሌ ስጡ። በመጨረሻም ደብተራቸውን ተቀያይረው
[መተ. አንድ፣ ሁለት፣ ሦስት…] በመልሱ ላይ እየተነጋገሩ እንዲተራረሙ
ያድርጉ።)
መ. ጎበዝ! ለደረጃ አመልካች ቍጥሮች ምሳሌ
ንገሩኝ።
[መተ. አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ሦስተኛ...]

፻፵፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 149


"ይህም የሚከናወነው በዜማ ጭምር ነው"
2ኛ ሳምንት ይላል። "ይህም" የሚለው ቃል ምንን
የሰርክ/የዘወትር ጨዋታዎች ይገልፃል?
[ተ. የእቴ ሜቴ ጨዋታን]

4ኛ ቀን መ. በጣም ጥሩ! (የተማሪዎችን ምላሽ ከተቀበሉ


በኋላ ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘት
አንብቦ መረዳት (25 ደቂቃ)
• ማንበብ
ሥሩ
መ. ከማንበባችሁ በፊት ስለሥዕሉ ገምታችሁ
ነበር። ግምታችሁ ትክክል ነበር? (ተማሪዎች
ማንበብ (40 ደቂቃ) እንዲናገሩ ያድርጉ።)
እቴ ሜቴ [ተ. አዎ/አይደለም።]
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) መ. በጣም ጥሩ! አሁን የተግባር አንድን የአንብቦ
መረዳት ጥያቄዎች በምክንያት አስደግፋችሁ
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
"እውነት" ወይም "ሐሰት" በማለት በቃላችሁ
ሥሩ መልሱ።
መ. ዛሬ "እቴ ሜቴ" በሚል ርዕስ የቀረበ ምንባብ
መ. የልጆች ጨዋታዎች ደንብና ሥርዓት
ታነባላችሁ። ከማንበባችሁ በፊት ግን
የላቸውም።
ጥቂት የቅድመንባብ ጥያቄዎችን መልሱ።
በአካባቢያችሁ ምን ምን ዓይነት የልጆች [ተ. ሐሰት]
ጨዋታዎች እንደምትጫወቱ ንገሩኝ። መ. ለምን "ሐሰት" አላችሁ?
[ተ. ሰኞ ማክሰኞ፣ መሀረቤን ያያችሁ፣ እቴ [ተ. ምክንያቱም የልጆች ጨዋታዎች የራሳቸው
ሜቴ…] ደንብና ሥርዓት አላቸው፤ ይህም
መ. በጣም ጥሩ! አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በመጀመሪያው አንቀጽ ውስጥ ተገልጿል።]
በ4ኛው ቀን "እቴ ሜቴ" ከሚለው ርዕስ (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ጥያቄዎች በቃል
ሥር የቀረበውን ሥዕል ተመልከቱና ያሠሯቸው። በተግባር 1 ጥያቄ 2 ሥር
ልጆቹ ምን ዓይነት ጨዋታ እንደሚጫወቱ የቀረቡትን አመራማሪ ጥያቄዎች ደግሞ
ገምቱ። (ተማሪዎች ግምታቸውን እንዲናገሩ በቡድን በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ያድርጉ።)
ልሥራ
[ተ. ሥዕሉን ተመልክተው ምንባቡ ስለምን ሊሆን
መ. በአንዳንድ ጽሑፎች ውስጥ ለየት ያሉ
እንደሚችል ይገምታሉ።]
በአዕምሮ ውስጥ ሥዕል የመፍጠር ኃይል
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) ያላቸው አገላለጾችን እናገኛለን። እነዚህ
አገላለጾች አንድን ነገር ከሌላ ነገር ጋር
ሥሩ
በማነፃፀር ወይም በማመሳሰል፣ ሰው ያልሆኑ
መ. "እቴ ሜቴ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ
ነገሮች፣ ሰው የሚፈጽማቸውን ድርጊቶች
ድምፅ ሳታሰሙ አንብቡ። በምታነቡበት ጊዜ
እንደሚፈጽሙ አድርገው ያቀርባሉ ።
የጨዋታውን ሂደት፣ በግጥሙ ውስጥ ያሉ ልዩ
በምንባቡ ውስጥም እንደነዚህ ዓይነት
አገላለጾች የሚፈጥሩትን ሥዕል በአዕምሯችሁ
አገላለጾች እናገኛለን። ለምሳሌ "የጎበዝ ልቡ
እየሳላችሁ አንብቡ።
ተራራ ነው" የሚል አገላለጽ አለ። በዚህ
(መ. እስከ 4ኛው አንቀጽ ድረስ ካነበቡ በኋላ አገላለጽ ውስጥ "የጎበዝ ልብ" እንደ"ተራራ"
ማንበባቸውን እንዲያቆሙ ያድርጉ።) ተቆጥሯል። በዚህም የጎበዝ ወይም የጀግና
ሀሳብ/ዓላማ ትልቅ መሆኑን ምሥል ፈጣሪ
መ. በ4ኛው አንቀጽ ውስጥ 8ኛው ዓረፍተነገር
በሆነ መልኩ ተገልጿል።

150 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፶


ሥሩ እንዲጽፉ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
መ. እናንተም እኔ እንዳደረኩት አገላለጾችን
(ሐረጎችን) ከምንባቡ ውስጥ አውጡና ሐረጋቱ መጻፍ (30 ደቂቃ)
የሚገልጹትን ሀሳብ አብራሩ።
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
(መ. ይህን ተግባር በቡድን እየተወያዩ
በድርጊት ቅደምተከተል ስልት ድርሰት
እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም እያንዳንዱ
ቡድን ያወጣቸውን ሐረጋት (አገላለጾች) መጻፍ
መልዕክታቸውን እንዲናገር ያድርጉ። ልሥራ
ሐረጋቱ አህያ ሞቶ ጅብ ሲያለቅስ፣ ቁንጫ መ. ያዘጋጀሁትን የቢጋር ሠንጠረዥ መሠረት
ቆሞ ሲቀድስ፣ እባብ አንገቱን ሲነቀስ በማድረግ "ስለገበጣ መጫወቻ አሠራር"
የሚሉት ናቸው። እነዚህ አገላለጾች ዘይቤ እንዴት ድርሰት እንደጻፍኩ ላሳያችሁ
መሆናቸውንና የዘይቤዎቹን ዓይነቶች (የሚከተለውን የቢጋር ሠንጠረዥ በሰሌዳው
ከመግለጽ ይቆጠቡ።) ላይ ይሣሉላቸው።)
ሥሩ
የገበጣ መጫወቻ አሠራር
መ. ተማሪዎች አሁን ተግባር "3"ን ትሠራላችሁ።
በጥንድ በጥንድ ተቧደኑ። ከዚያም በምንባቡ 48 የመጫወቻ ጠጠሮች ይዘጋጃሉ።
በተገለጸው ሁኔታ "እቴ ሜቴ" የተሰኘውን
የልጆች ጨዋታ ተጫወቱ። (ተማሪዎች
ሲጫወቱ እየተዘዋወሩ በትክክል በምንባቡ 84 ሳ.ሜ. በ27 ሳ.ሜ. ስፋት ያለው የገበጣ
የተገለጸውን መተግበራቸውን ያረጋግጡ።) መጫወቻ ይዘጋጃል።

5ኛ ቀን
በገበጣ መጫወቻው ላይ 12 ጉድጓዶች
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ይዘጋጃሉ።
• ቃላት መ. የምጽፈው አንቀጽ የሚያተኩረው ስለገበጣ
• መጻፍ መጫወቻ አሠራር ስለሆነ "የገበጣ መጫወቻ
ለማዘጋጀት በቅድሚያ የሚያስፈልጉ
ቁሳቁሶቹን ማሟላት ያስፈልጋል" በሚል
መንደርደሪያ ዓረፍተነገር አንቀጹን
ቃላት (10 ደቂቃ) ጀምሬያለሁ። ከዚያም በቢጋር ሠንጠረዡ
ቃላትን ከፍቻቸው ጋር ማዛመድ በቅደምተከተል የቀረቡትን የገበጣ መጫዎቻ
አዘገጃጀት ሂደቶች በተሟሉ ዓረፍተነገሮች
ሥሩ እያዋቀርኩ ጽፌያለሁ። አሁን የጻፍኩትን
መ. አሁን በሳጥን ውስጥ የቀረቡትን ቃላት አንቀጽ ላንብላችሁ። (የሚከተለውን አንቀጽ
ከፍቻቸው ጋር አዛምዱ። ከጉበት ውስጥ ያንቡላቸው።)
የሚመነጭ፣ በሆድዕቃ ውስጥ ምግብን ለማላም
የሚረዳ፣ ቅጠላማ ቀለም ያለው መራራ ፈሳሽ የገበጣ መጫወቻ ለማዘጋጀት በቅድሚያ
ምን ይባላል? አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማሟላት ያስፈልጋል።
በመጀመሪያ የመጫወቻ ጠጠሮች በአካባቢ
[ተ. ሀሞት]
ከሚገኙ ነገሮች በክብ (በድቡልቡል) ቅርፅ
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ይዘጋጃሉ። የሚሠሩትም ጠጠሮች ብዛት 48
በደብተራቸው እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም ነው። በመቀጠልም 84 ሳ.ሜ. በ27 ሳ.ሜ. ስፋት
ትክክለኛውን መልስ በመንገር ደብተራቸውን ያለው ገበጣ ይዘጋጃል። የመጫወቻ ጉድጓዶች
ተቀያይረው እንዲተራረሙ ያድርጉ። አቀማመጥ በሁለት ረድፍ ሆኖ በየረድፉ ስድስት
በመጨረሻም በተግባር ሁለት ለቀረቡት ስድስት ጉድጓዶች ይኖራሉ። በቁመቱ ግራና
ቃላት ተመሳሳይ ፍቻቸውን በደብተራቸው ቀኝ በኩል አንድ አንድ የጠጠር ማከማቻ

፻፶፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 151


ጉድጓድ ይዘጋጃል።
ሥሩ 6ኛ ቀን
መ. ባለፈው ሳምንት ድርሰት ለመጻፍ
በአካባቢያችሁ ከሚታወቁት ባህላዊ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ጨዋታዎች አንዱን መርጣችኋል። ከዚያም • አቀላጥፎ ማንበብ
የቢጋር ሠንጠረዥ አዘጋጅታችኋል። ዛሬ
ደግሞ በመረጣችሁት አንድ ባህላዊ ጨዋታ • መናገር
በቅደምተከተል ስልት ባለሁለት አንቀጽ • ሰዋስው
ድርሰት ትጽፋላችሁ።
(መ. ተማሪዎች ድርሰቱን ሲጽፉ እየተዘዋወሩ
ይመልከቱ፣ ፍንጭ በመስጠት ለምሳሌ የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
የመንደርደሪያ ዓረፍተነገር በመንገር፣ ሥሩ
ቅደምተከተልን የሚያመለክቱ (መ. ተማሪዎች በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው
እንደመጀመሪያ፣ ከዚያም፣ ቀጥሎ፣ በተጨማሪ፣ ቀን በቃላት ሥር የተሰጠውን የቤትሥራ
በመጨረሻም…ያሉ ቃላትን በመጠቆም መሥራታቸውን ያረጋግጡና መልሳቸውን
ተማሪዎች እንዲጽፉ ያበረታቱ።) ይቀበሉ።)
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) መ. "አጋጣሚ" ለሚለው ቃል ተመሳሳይ ፍቹ
የሠላምታ ደብዳቤ ምንድን ነው?

ሥሩ [ተ. ምቹ ሁኔታ/ዕድል]
መ. ባለፈው ሳምንት ስለሠላምታ ደብዳቤ መ. በጣም ጥሩ! "የታጀበ" የሚለው ቃል
አጻጻፍ ተምራችኋል። ዛሬ እኔ እየመራኋችሁ ተመሳሳይ ፍቺ ምንድን ነው?
ደብዳቤ ትጽፋላችሁ። ራሳችሁን ከቤተሰብ
ተለይታችሁ በሌላ ከተማ ከዘመድ ጋር [ተ. የታገዘ] (በዚህ ዓይነት ሌሎቹን መልሶች
ሆናችሁ እንደምትማሩ አድርጋችሁ ቁጠሩ። ይቀበሉ።)
ጊዜውም ነሐሴ አጋማሽ መሆኑን አስቡ።
ደብዳቤውን የምትጽፉትም ለአባታችሁ አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
ወይም ለእናታችሁ ነው። ስለዚህ በደብዳቤው
መግቢያ ላይ የቤተሰቦቻችሁን ጤንነትና
"እቴ ሜቴ"
ደህንነት ጠይቁ፤ የራሳችሁን ደህንነት ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
ግለጹ። በሐተታው ክፍል ደግሞ በቅርብ ጊዜ
ሥሩ
ትምህርት እንደሚጀመር ግለጹ። በመሆኑም
መ. "የእቴ ሜቴ" ጨዋታ ሂደት ምን
ለደንብልብስ፣ ለእስክቢርቶና ደብተር፣
እንደሚመስል በአጭሩ ግለጹ። (ተማሪዎች
ለአጋዥ መጻሕፍት መግዣ የሚሆን ገንዘብ
ለ2 ደቂቃ ያህል እንዲናገሩ ያድርጉ።)
እንዲላክላችሁ ጠይቁ። በመደምደሚያው
ደግሞ በሰላም እንደምትገናኙ ያላችሁን ማንበብ (8 ደቂቃ)
ተስፋ በመግለጽ ተሰናበቱ፤ ሠላምታችሁን
ሥሩ
ለሌሎች ዘመዶቻችሁ እንዲያቀርቡላችሁ
ግለጹ። መ. "እቴ ሜቴ" በሚለው ምንባብ ውስጥ ያለውን
ግጥም በቡድን ሆናችሁ በጋራ ድምፅ
(መ. ተማሪዎች ሲጽፉ እየተዘዋወሩ በመግቢያ፣ እያሰማችሁ አንብቡ። በምታነቡበት ጊዜ
በሐተታና በመደምደሚያ ላይ የሚካተቱትን ሳትቀዳደሙ ድምፃችሁን እኩል አውጡ፤
ከላይ የዘረዘሯቸውን ሀሳቦች በማስታወስ የግጥሙን ዜማ ጠብቃችሁ አንብቡ።
እንዲጽፉ ያበረታቷቸው።)
(መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ በሠጡት
መመሪያ መሠረት ማንበባቸውን ይከታተሉ።)

152 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፶፪


መናገር (15 ደቂቃ) በሳጥን ውስጥ ከተዘረዘሩት ቍጥሮችና
ቅጽሎች ጋር በማዋቀር ዓረፍተነገሮቹን
የሚና ጨዋታ አሟሉ።
ሥሩ መ. "የትምህርት ቤቱ--------------------ተማሪ
መ. ባለፈው ሳምንት በአካባቢያችሁ አስቻለው ነው።" የሚለውን የተጓደለ
ከምትጫወቷቸው የልጆች ጨዋታዎች ዓረፍተነገር የሚያሟላው ቅጽል የቱ ነው?
መካከል አንዱን ተለማምዳችሁ እንድትመጡ
[ተ. ጎበዝ]
የቤትሥራ ሠጥቻችሁ ነበር። ስለዚህ
የተዘጋጃችሁበትን ጨዋታ በቡድን ሆናችሁ መ. በጣም ጥሩ! ከቍጥሮቹ ደግሞ አንድ
አቅርቡ። እንምረጥ።
(መ. ተማሪዎች ጨዋታውን ሲያቀርቡ የቡድኑ [ተ. ሁለተኛው] (አራተኛው ወይም አንደኛው
አባላት ተመጣጣኝ ሚና መያዛቸውን ማለትም እንደሚቻል ይንገሯቸው።)
የተሠጣቸውን ሚና በሚገባ መወጣታቸውን
መ. በጣም ጥሩ! ዓረፍተነገሩን አሟልታችሁ ጻፉ።
ይከታተሉ። ሲጫወቱ በመከታተል
ያበረታቱ።) [ተ. የትምህርትቤቱ ሁለተኛው ጎበዝ ተማሪ
አስቻለው ነው።]
ሰዋስው (10 ደቂቃ) (መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም እንዲሠሩ ያድርጉ።
ቅጽሎች፣ መጣኝና ደረጃ አመልካች ከዚያም ደብተራቸውን ተቀያይረው በሠሩት
ላይ እንዲወያዩ ያድርጉ። ቀጥሎም የተወሰኑ
ቍጥሮች
ዓረፍተነገሮች ሠርተው በማሳየት ግብረመልስ
እንሥራ ይስጡ። በመጨረሻም ተማሪዎች ቅጽሎችን፣
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ መጣኝና ደረጃ መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮችን
አመልካች ቍጥሮችን እንዲሁም ቅጽሎችን ተጠቅመው በራሳቸው ዓረፍተነገሮችን
ከዓረፍተነገር ውስጥ ለይተናል። ዛሬ ደግም እንዲመሠርቱ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮችን
ከቅጽሎች ጋር በማዋቀር በዓረፍተነገሮች
ውስጥ እንጠቀማለን። አንድ ምሳሌ አብረን
እንሥራ።
መ. "---------------ጠረጴዛዎች ብዙ ቢያገለግሉም
አልተሰበሩም" የሚለውን የተጓደለ ዓረፍተነገር
ለማሟላት የሚስማማው ቅጽል የትኛው ነው?
[መተ. ጠንካራ]
መ. በጣም ጥሩ! ከቍጥሮቹ ደግሞ አንድ
እንምረጥ
[መተ. ሁለቱ]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ዓረፍተነገሩን አሟልተን
እንጻፍ።
[መተ. ሁለቱ ጠንካራ ጠረጴዛዎች ብዙ
ቢያገለግሉም አልተሰበሩም።]

ሥሩ
መ. አሁን በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን በሰዋስው
ሥር የቀረቡትን የተጓደሉ ዓረፍተነገሮች

፻፶፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 153


ማንበብ (32 ደቂቃ)
3ኛ ሳምንት
ባህላዊ ጨዋታዎች የፈረስ ሽርጥ (ሽምጥ) የውድድር
ጨዋታ
ቅድመንባብ (7 ደቂቃ)
7ኛ ቀን
የአዳዲስ ቃላትን ፍቺ ማስተዋወቅ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ልሥራ
• የቃላት ጥናት መ. አሁን ምንባቡን ከማንበባችሁ በፊት
• ማንበብ ከምንባቡ ውስጥ በሚገኙ ቃላት ፍቺ ላይ
እንወያያለን። በመጀመሪያ ግን ቃላቱ
የሚገኙበትን አንቀጽ ላንብብላችሁ። ("የፈረስ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) ሽርጥ የውድድር ጨዋታ" ከሚለው ምንባብ
ሥሩ 3ኛውን አንቀጽ ያንብቡላቸው።) በዚህ
አንቀጽ ውስጥ "ኮርቻ፣ ግላስና ልባብ" የተባሉ
(መ. ተማሪዎች በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን
አዳዲስ ቃላት ይገኛሉ።
የተሠጣቸውን የቤትሥራ መሥራታቸውን
ያረጋግጡ። ከዚያም የመሠረቷቸውን እንሥራ
ዓረፍተነገሮች ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ መ. አሁን ቃላቱን አብረን እናንብብ።
ያድርጉ።) በመጀመሪያ "ኮርቻ" የሚለውን ቃል ሦስት
መ. መጣኝና ደረጃ አመልካች ቍጥሮችን ጊዜ እናንብብ።
እንዲሁም ቅጽሎችን በመጠቀም [መተ. ኮርቻ፣ ኮርቻ፣ ኮርቻ]
የመሠረታችኋቸውን ዓረፍተነገሮች አንብቡ።
መ. አሁን ደግሞ "ግላስ" የሚለውን ቃል 3 ጊዜ
[ተ. የመሠረቷቸውን ዓረፍተነገሮች ለክፍሉ አብረን እናንብብ።
ተማሪዎች ያነባሉ።]
[መተ. ግላስ፣ ግላስ፣ ግላስ]
መ. በጣም ጥሩ! (ስህተት ያለባቸው ዓረፍተነገሮች
መ. በጣም ጥሩ! አሁን "ልባብ" የሚለውን ቃል
ካሉ በማስተካከል አስተያየት ይስጡ።)
3 ጊዜ አብረን እናንብብ።

የቃላት ጥናት (3 ደቂቃ) [መተ. ልባብ፣ ልባብ፣ ልባብ]

መነጠልና ማጣመር ልሥራ


መ. አሁን ደግሞ የቃላቱን የመዝገበቃላት ፍቺ
ሥሩ
እነግራችኋለሁ። "ኮርቻ" በበቅሎ፣ በፈረስ…
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን በቃላት ጥናት ጀርባ ላይ ተደርጎ የሚታሠርና ሰው
ሥር በሠንጠረዥ ውስጥ የቀረቡትን ቃላትና የሚቀመጥበት ከእንጨትና ከቆዳ የሚሠራ
ሐረጋት በመነጣጠልና በማጣመር አንብቡ። ዕቃ ነው። "ግላስ" ከሃር ወይም ከግምጃ፣
መ. "ሽርጥ" የሚለውን ቃል ነጣጥላችሁ አንብቡ። የተሠራ የኮርቻ ልብስ ነው። "ልባብ" ደግሞ
ከጠፍር የተሠራ፣ በፈረስና በበቅሎ ራስ ላይ
[ተ. ሽ-ር-ጥ]
የሚጠለቅ የፊት ላይ ጌጥ ነው።
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ አጣምራችሁ
መ. ቀደም ሲል የነገርኳችሁ የቃላቱን
አንብቡ።
የመዝገበቃላት ፍቺ ነው። አሁን ደግሞ
[ተ. ሽርጥ] የቃላቱን ፍቺ ቀለል አድርጌ በእኔ አገላለፅ
ልንገራችሁ። "ኮርቻ" በበቅሎ ወይም ፈረስ
(መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹን ቃላት ያስነብቡ።
ጀርባ ላይ የሚጫን ከእንጨትና ከቆዳ
ሽርጥና ግላስ የሚሉት ቃላት የመሐል
የሚሠራ መቀመጫ ነው። "ግላስ" ከሃር
ፊደላቸው ላልቶ እንደሚነበብ ልብ ይበሉ።)
ወይም ደማቅ ቀለም ካለው ለስላሳ ጨርቅ

154 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፶፬


የተሠራ የኮርቻ ልብስ ነው። "ልባብ" ደግሞ መ. አሁን የመጀመሪያውን አንቀጽ ላንብብ
ለስልሶ በቀጭኑ ከተተለተለ ቆዳ የተሠራ፣ (የመጀመሪያውን አንቀጽ ድምፅዎን እያሰሙ
አልፎ አልፎ ደማቅ ቀለም ባላቸው ክሮች ያንብቡ።)
ያጌጠ፣ በፈረስና በበቅሎ ራስ ላይ የሚጠለቅ
[መ. ግምቴ ትክክል ነበር። ይህ የውድድር ዓይነት
ጌጥ ነው።
ሰዎች ፈረሶችን እየጋለቡ የሚወዳደሩበት
ሥሩ ስፖርት ነው።]
መ. እኔ የቃላቱን ፍቺ በእኔ አባባል ሥሩ
ነግሬያችኋለሁ። አሁን ደግሞ እናንተ
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ በጥንድ ያደራጁ።
የቃላቱን ፍቺ በራሳችሁ አባባል ግለጹ።
ከዚያም ተማሪዎች ራሳቸውን "1" እና "2"
[ተ. በቡድን ሆነው የቃላቱን ፍቺ ተራበተራ ብለው እንዲሰይሙ ያድርጉ።)
ይናገራሉ።]
መ. አሁን ቍጥር አንዶች የመጀመሪያውን ንዑስ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ "የፈረስ ሽርጥ ርዕስ አንብቡ፤(ቍጥር ሁለቶችም በለሆሳስ
የውድድር ጨዋታ" ከሚለው ምንባብ በፊት እያነበቡ እንዲከታተሉ ይንገሯቸው።)
የሚገኘውን ሥዕል አስተውሉና ኮርቻው፣
ከዚያም ከንዑስ ርዕሱ በመነሳት በሥሩ ያሉት
ግላሱና ልባቡ የትኛው እንደሆነ ለይታችሁ
አንቀጾች ስለምን እንደሚገልጹ ገምቱ፤
አመልክቱ።
• ቀጥሎ በንዑስ ርዕሱ ሥር ያሉትን ሁለት
[ተ. ከሥዕሉ ኮርቻውን፣ ግላሱንና ልባቡን አንቀጾች አንብቡ፤
ለይተው ያመለክታሉ።]
• ከዚያም የአንቀጾቹን ዋና ሀሳብ
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) ጨምቃችሁ/አጠቃላችሁ ተናገሩ፣

ንዑሳን ርዕሶችን በመጠቀም መገመት • አሁን ቍጥር ሁለቶች፣ ቍጥር አንዶች


ያላነሷቸውን ዝርዝር ሀሳቦች ጨምሩ/
ልሥራ ተናገሩ።
መ. ምንባቡን ስታነቡ በአዕምሯችሁ ውስጥ መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ቍጥር ሁለቶች፣
እየጠየቃችሁ፣ ለጥያቄዎቻችሁ መልስ ሁለተኛውን ንዑስ ርዕስ አንብቡ፤ ከዚያም
ለማግኘት እየጣራችሁ፣ እየተመራመራችሁ፣ ከንዑስ ርዕሱ በመነሳት በሥሩ ያሉት
እየገመታችሁ መሆን አለበት። ለምሳሌ አንቀጾች ስለምን እንደሚገልጹ ገምቱ፤
ያህል የምንባቡን የተወሰነ ክፍል በማንበብ
ላሳያችሁ። በመጀመሪያ ርዕሱን አነባለሁ • ቀጥሎ በንዑስ ርዕሱ ሥር ያሉትን
አንቀጾች አንብቡ፤
(ርዕሱን ድምፅዎን እያሰሙ ያንብቡላቸው።)
• ከዚያም የአንቀጾቹን ዋና ሀሳብ
መ. ርዕሱ "የፈረስ ሽርጥ (ሽምጥ) የውድድር ጨምቃችሁ/ አጠቃላችሁ ተናገሩ፤
ጨዋታ" ይላል። በዚህ ርዕስ ውስጥ
የማላውቃቸው "ሽርጥ" እና "ሽምጥ" የሚሉ • አሁን ቍጥር አንዶች፣ ቍጥር ሁለቶች
ያላነሷቸውን ዝርዝር ሀሳቦች ጨምሩ/
ቃላት አሉ። ሌሎቹን ቃላት አውቃቸዋለሁ።
ተናገሩ።
በርካታ የውድድር ጨዋታዎችን አውቃለሁ፤
ሩጫ፣ ዝላይ፣ እግርኳስ፣ ወዘተ. ይህኛውን አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
የሚለየው ምንድን ነው? ሥሩ
[መ. "የፈረስ ሽርጥ/ሽምጥ" ከሚለው በመነሳት መ. አሁን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን
ፈረሶች የሚሳተፉበት የውድድር ዓይነት ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ፣ የተግባር 1
መሆኑን መገመት እችላለሁ። ሰዎች የምርጫ ጥያቄዎችን በቃላችሁ መልሱ።
በብስክሌት፣ በመኪና፣ ወዘተ. እንደሚወዳደሩ "በመሙ የውስጥ መስመሮች በየ100 ሜትር
አውቃለሁ። ስለዚህ ይህ ውድድርም ሰዎች ርቀት የሚተከሉት የባንዲራ መስቀያ
በፈረሶቻቸው እየጋለቡ የሚወዳደሩበት እንጨቶች ቁመት ምን ያህል ነው?"
የውድድር ዓይነት መሆኑን መገመት የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በመጀመሪያ ምን
እችላለሁ።] ታደርጋላችሁ?

፻፶፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 155


[ተ. ስለመወዳደሪያ ሜዳው የሚገልጸውን አንቀጽ
እናነባለን።] (አንቀጹን እንዲያነቡ ጊዜ 8ኛ ቀን
ይስጧቸው።)
መ. ስለዚህ የእንጨቶቹ ቁመት ስንት ነው? የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• ቃላት
[ተ. 2 ሜትር]
• መጻፍ
መ. በጣም ጥሩ! መልሱን የያዘው ፊደል የትኛው
ነው?
[ተ. መ] ቃላት (10 ደቂቃ)
( መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ጥያቄዎች የቃላት ፍቺ፣ ምደባና ቃላትን በአንቀጽ
እንዲመልሱ ያድርጉ። በትክክል ያልተመለሱ ውስጥ መጠቀም
ጥያቄዎች ካሉ እንደገና አንብበው ጥያቄዎቹን
ልሥራ
በትክክል እንዲመልሱ ያድርጉ።)
መ. አሁን ከምንባቡ የወጡ ቃላትን በየወገናቸው
መ. አሁን ደግሞ የተግባር 2ን ጥያቄዎች በጽሑፍ እንመድባለን። በመጀመሪያ አንድ ምሳሌ እኔ
መልሱ። የሜዳው ስፋት 600 ሜትር በ60 እሠራለሁ። (በመማሪያ መጽሐፍ የቀረበውን
ሜትር ከሆነ የእያንዳንዱ መም ስፋት ስንት ሠንጠረዥ ሰሌዳ ላይ ይሣሉ።) በተግባር “2”
ይሆናል? ሥር ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል ከፈረስ
[ተ. 10 ሜትር] ሽርጥ የውድድር ሂደትና ሥርዓት ጋር
ከተያያዙት ቃላት መካከል አንዱን ልጥቀስ።
መ. በጣም ጥሩ! መልሱን እንዴት አገኛችሁት?
[መ. ጥሎ ማለፍ] (ይህን ቃል "የውድድር ሂደትና
[ተ. የሜዳው ስፋት ቢያንስ 400 ሜትር በ48 ሥርዓት" በሚለው የሠንጠረዡ ክፍል
ሜትር፣ ቢበዛ 600 ሜትር በ60 ሜትር ነው። ይጻፉ።)
የእያንዳንዱ መም ስፋት ቢያንስ 8 ሜትር፣
ቢበዛ 10 ሜትር ነው። የመሞች ብዛት ደግሞ እንሥራ
ሁልጊዜም 6 ነው። ስለዚህ የሜዳው ስፋት መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። ከሠንጠረዡ
ሲጨምር የመሞቹም ስፋት ይጨምራል። በላይ ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል ከፈረስ
በመሆኑም የሜዳው ስፋት 600 ሜትር በ60 ዕቃዎች የሚመደበው የትኛው ነው?
ሜትር ከሆነ በእያንዳንዱ የመም መስመር [መተ. ግላስ] (ይህን ቃል "የፈረስ ዕቃ" በሚለው
መካከል ያለው ርቀት ስፋት 10 ሜትር ነው የሠንጠረዡ ክፍል ይጻፉ።)
ማለት ነው።]
ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት የጥያቄዎቹን መልስ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን
በደብተራቸው እንዲጽፉ ያድርጉ። ከዚያም
በቃላት ተግባር “1” ሥር ከሠንጠረዡ በላይ
በቡድን እንዲወያዩ ያደርጉ፤ መልሳቸውን
የተዘረዘሩትን ቃላት በየወገናቸው መድቡ።
ይቀበሉ፤ በመጨረሻ የእርስዎንም አስተያየት
ከተዘረዘሩት ቃላት መካከል ከመወዳደሪያ
በመጨመር ያጠቃሉ።)
ሜዳው ጋር ከተያያዙት አንዱን ንገሩኝ።
[ተ. አባጣጎርባጣ]
መ. በጣም ጥሩ! ይህን ቃል "የመወዳደሪያ ሜዳ"
በሚለው የሠንጠረዡ ክፍል ጻፉ።
(መ. በዚህ ዓይነት ተግባሩን በደብተራቸው
እንዲሠሩ ያድርጉና ሠርተው ሲጨርሱ
ደብተራቸውን እንዲቀያይሩ ያድርጉ
በመልሶቹ ላይ እየተነጋገሩ እንዲተራረሙ
ያድርጉ።)

156 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፶፮


ሥሩ ረድፍ ሆኖ በየረድፉ ስድስት ስድስት ጉድጓዶች
(መ. ተግባር "2"ን ደግሞ በሳጥን ውስጥ ይኖራሉ። በቁመቱ ግራና ቀኝ በኩል አንድ
ከተዘረዘሩት ቃላት በመምረጥ በክፍት አንድ የጠጠር ማከማቻ ጉድጓድ ይዘጋጃል።
ቦታዎቹ በማስገባት አንቀጹን አሟልታችሁ መ. አሁን መሻሻል ያለባቸውን ቃላትና
ጻፉ። በመጀመሪያው ክፍት ቦታ የሚገባው ዓረፍተነገሮች ላስምርባቸው። (ከላይ
ቃል የትኛው ነው?) የተሰመረባቸውን እርስዎ በጻፉት ወረቀት
ላይም በእርሳስ አስምረው ያሳዩዋቸው።)
[ተ. ኮርቻውን]
መ. አሁን ያሰመርኩባቸውን ቃላትና
መ. በጣም ጥሩ! በሁለተኛው ክፍት ቦታ የሚገባው
ዓረፍተነገሮች አስተካክላለሁ። በመጀመሪያው
ቃል የቱ ነው?
ዓረፍተነገር ውስጥ "ያስፈልጋል" የሚለው
[ተ. ግላስ] ቃል የተደገመ ስለሆነ ቃሉን ሰርዤ "ይገባል"
በሚል ቃል እተካዋለሁ። በ2ኛው፣ በ4ኛውና
መ. ጎበዝ! አሁን ዓረፍተነገሩን አሟልታችሁ
በ6ኛው ዓረፍተነገሮች መጨረሻ "ይዘጋጃል"
በደብተራችሁ ጻፉ።
የሚል ቃል ተደጋግሟል። ስለዚህ ሁለተኛውን
[ተ. ጋላቢው ፈረሱ ጀርባ ላይ ኮርቻውን ጭኖ "ይበጃል" በሚል ቃል፣ አራተኛውን ደግሞ
ያማረውን ግላስ ለበስ አደረገው።] "ይቆፈራል/ይቦረቦራል" በሚሉ ቃላት
ሠርዤ እተካለሁ። (ያስፈልጋልና፣ ይዘጋጃል
(መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ክፍት ቦታዎች
የሚሉትን ቃላት ሠርዘው ራስጌያቸው ላይ
እንዲያሟሉ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
ይገባል፣ ይበጃል፣ ይቆፈራል/ይቦረቦራልየሚሉ
ቃላት ጽፈው ያሳዩዋቸው።)
መጻፍ (30 ደቂቃ)
መ. ሌላው ሁለተኛው ዓረፍተነገር ተጨማሪ
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) ዝርዝር ያስፈልገዋል። ማለትም ጠጠሮቹ
በድርጊት ቅደምተከተል ስልት የተጻፈን ከምን እንደሚሠሩ አልተገለፀም። ስለዚህ
ድርሰት አስተካክሎ መጻፍ "ቅርፅ ይዘጋጃሉ።" ከሚለው ሥር"
የሚዘጋጁትም ጠጠሮች…" የሚለውን ወደታች
ልሥራ ትቼ ወረቀቱን እቆርጣለሁ። በመቀጠል ሌላ
(መ. ባለፈው ሳምንት ስለገበጣ መጫወቻ ንፁህ ወረቀት ከሥር እለጥፋለሁ። ከዚያም
አዘገጃጀት የጻፉትን አንቀጽ በትልቅ ወረቀት "ጠጠሮቹ ከብይ፣ ከወንዝ ጠጠሮች፣ ከዛፍ
ጽፈው ይምጡ። በተጨማሪ የተለያየ ቀለም ፍሬዎች፣ ከትናንሽ ብረቶች ወዘተ. ሊሠሩ
ያላቸው ያልተጻፈባቸው ወረቀቶች፣ መቀስ፣ ይችላሉ" የሚል ዓረፍተነገር ከለጠፍኩት
ስቴኘለር ወይም ኘላስተር ይዘው መግባትዎን (ከቀጠልኩት) ወረቀት ላይ እጽፋለሁ።
አይዘንጉ።) ከዚያም ከአዲሱ ዓረፍተነገር ሥር የታችኛውን
መ. ዛሬ ባለፈው ሳምንት የጻፋችሁትን ድርሰት ቅዳጅ እቀጥላለሁ።
ታስተካክላላችሁ። ጽሑፋችሁን ስታስተካክሉ/ መ. 4ኛው ዓረፍተነገርም ተጨማሪ ዝርዝር
ስታሻሽሉ የምትጠቀሙበትን አንድ ዘዴ ያስፈልገዋል። የመጫወቻ ገበጣ ከምን
አሳያችኋለሁ። በቅድሚያ የመጀመሪያ ረቂቅ እንደሚዘጋጅ አልተገለጸም። ስለዚህ ከ4ኛው
ጽሑፍ ላንብብላችሁ። (የሚከተለውን አንቀጽ ዓረፍተነገር ሥር ወረቀቱን እቆርጣለሁ።
ያንብቡላቸው።) ከዚያም ያልተጻፈበት ወረቀት ከሥር
የገበጣ መጫወቻ ለማዘጋጀት በቅድሚያ እቀጥላለሁ። በመቀጠል "የመጫወቻ ገበጣው
አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ማሟላት ያስፈልጋል። መሬት ላይ በመቆፈር ወይም ጣውላና
በመጀመሪያ የመጫወቻ ጠጠሮች በአካባቢ ድንጋይን በመቦርቦር ሊዘጋጅ ይችላል። ከዚህ
ከሚገኙ ነገሮች በክብ (በድቡልቡል) ቅርፅ በተጨማሪም አሸዋና ሲሚንቶ ወይም ጭቃ
ይዘጋጃሉ። የሚሠሩትም ጠጠሮች ብዛት በማቡካት የመጫወቻ ገበጣ መሥራትም
48 ነው። በመቀጠልም 84 ሳንቲሜትር በ27 የተለመደ ነው።" የሚል ዓረፍተነገር
ሳንቲሜትር ስፋት ያለው ገበጣ ይዘጋጃል። የተለጠፈው ያልተጻፈበት ወረቀት ላይ
የመጫወቻ ጉድጓዶች አቀማመጥ በሁለት እጽፋለሁ። ከዚያም የታችኛውን ቅዳጅ

፻፶፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 157


ከአዲሱ ዓረፍተነገር ሥር እቀጥላለሁ። ሥሩ
(የተቀጣጠለው ጽሑፍ የሚከተለውን መ. አሁን እኔ ባሳየኋችሁ መሠረት ባለፈው
ይመስላል።) ክፍለጊዜ ስለባህላዊ ጨዋታዎች የጻፋችሁትን
(መ. የሚከተለውን የተሻሻለ ጽሑፍ ያንቡላቸው።) ድርሰት ጥንድ ጥንድ ሆናችሁ ተቀያየሩና
አንብቡ። ስታነቡ ግልፅ ያልሆኑ፣ በተሻለ
ሁኔታ መገለጽ ባለባቸውና ተጨማሪ
ማብራሪያ በሚያስፈልጋቸው ዓረፍተነገሮች
ሥር በእርሳስ ምልክት አድርጉ። ከዚያም
ጽሑፉ በምን ሁኔታ መሻሻል እንዳለበት
ተነጋገሩ። ቀጥሎ መሻሻል አለበት ያላችሁት
ዓረፍተነገር ካለበት ቦታ ላይ ወረቀቱን
በቀጥታ መስመር ቅደዱ። በመቀጠል ከሥር
ሌላ ንፁህ ወረቀት ለጥፉ/ቀጥሉ። ከዚያም
ንፁህ ወረቀት ላይ መጨመር የምትፈልጉትን
ሀሳብ ጻፉ። ምናልባት ሙሉ በሙሉ
መቀየር ያለበት/ያለባቸው ዓረፍተነገር/ሮች
ካሉ፣ እነዚህን ዓረፍተነገሮች ቀንብባችሁ
በመቁረጥ መጣልና በቀጠላችሁት ወረቀት
ላይ አሻሽላችሁ ልትጽፉ ትችላላችሁ።
ከዚያም ሌላውን የጽሑፋችሁን አካል
አዲስ ከቀጠላችሁት ወረቀት ቀጥሎ ለጥፉ
(ቀጥሉ)። በመጨረሻም የተሻሻለውን ጽሑፍ
ለጓደኛችሁ አንብቡ።
(መ. ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ እየተዘዋወሩ
ይከታተሉ። ተግባሩን ለመፈፀም ከተቸገሩ
እንዴት መሥራት እንዳለባቸው በማሳየት
ይደግፏቸው። በመጨረሻም የተሻለው ጽሑፍ
ተመርጦ ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲነበብ
ያድርጉ።)
የተሻሻለ ጽሑፍ የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
የገበጣ መጫወቻ ለማዘጋጀት በቅድሚያ አስፈላጊ የሠላምታ ደብዳቤ
ቁሳቁሶችን ማሟላት ይገባል። በመጀመሪያ
የመጫወቻ ጠጠሮች በአካባቢ ከሚገኙ ነገሮች ሥሩ
በክብ (በድቡልቡል) ቅርጽ ይዘጋጃሉ። ጠጠሮቹ መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለሠላምታ ደብዳቤ
ከብይ፣ ከወንዝ ጠጠሮች፣ ከዛፍ ፍሬዎች፣ ከትናንሽ አጻጻፍ ተምራችኋል። ዛሬ ለዘመዳችሁ
ብረቶች ወዘተ. ሊሠሩ ይችላሉ። የሚሠሩትም ወይም ለጓደኛችሁ የሠላምታ ደብዳቤ
ጠጠሮች ብዛት 48 ነው። በመቀጠልም 84 ጽፋችሁ ለክፍል ጓደኞቻችሁ ታነባላችሁ።
ሳንቲ ሜትር በ27 ሳንቲ ሜትር ስፋት ያለው
ገበጣ ይበጃል። የመጫወቻ ገበጣው መሬት ላይ (መ. በመጀመሪያ ደብዳቤውን በግል እንዲጽፉ
በመቆፈር፣ ጣውላ ወይም ድንጋይ በመቦርቦር ያድርጉ። ከዚያም ጥንድ ጥንድ ሆነው
ሊዘጋጅ ይችላል። ከዚህ በተጨማሪም አሸዋና ተራበተራ የጻፉትን ለጓደኞቻቸው እንዲያነቡ
ሲሚንቶ ወይም ጭቃ በማቡካት የመጫወቻ ያድርጉ። በመጨረሻም ከተማሩት የሠላምታ
ገበጣ መሥራትም የተለመደ ነው። የመጫወቻ ደብዳቤ አጻጻፍ ሥርዓት አንጻር አስተያየት
ጉድጓዶች አቀማመጥ በሁለት ረድፍ ሆኖ እንዲሰጥበት ያድርጉ።)
በየረድፉ ስድስት ጉድጓዶች ይኖራሉ። በቁመት
ግራናቀኝ በኩል አንድ አንድ የጠጠር ማከማቻ
ጉድጓድ ይቆፈራል/ይቦረቦራል።

158 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፶፰


ይመልከቱ።)
9ኛ ቀን
መናገር (15 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች በተነበበ ጽሑፍ ላይ የግምገማ አስተያየት
• አቀላጥፎ ማንበብ መስጠት
• መናገር ሥሩ
• ሰዋስው (መ. ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት ባሏቸው ቡድኖች
ያደራጁ።)
መ. ዛሬ በተነበበላችሁ ጽሑፍ ላይ የግምገማ
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) አስተያየት የመስጠት ተግባር ትሠራላችሁ።
ሥሩ ከቡድን አባላት መካከል አንዳችሁ ባለፈው
ክፍለጊዜ ስለባህላዊ ጨዋታዎች አሻሽላችሁ
(መ. ባለፈው ክፍለጊዜ በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው
የጻፋችሁትን ድርሰት ለቡድናችሁ አንብቡ።
ቀን በቃላት ሥር የሠጧቸውን የቤትሥራ
ሌሎቻችሁ ካዳመጣችሁ በኋላ በጽሑፉ
መሥራታቸውን ያረጋግጡ። ከዚያም
ላይ የግምገማ አስተያየት ስጡ። በዚህ
በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር ይነጋገሩ።)
ዓይነት ተራበተራ እያነበባችሁ አስተያየት
መ. በመጀመሪያው ክፍት ቦታ የሚገባው ቃል ተሰጣጡ። ጓደኞቻችሁ የሚያነቡላችሁን
የቱ ነው? ጽሑፍ አዳምጣችሁ አስተያየት ስትሰጡ
[ተ. ኮርቻውን] ንግግራችሁን በሚከተሉት መንደርደሪያዎች
መጀመር ትችላላችሁ።
(መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ክፍት ቦታዎች
እንዲያሟሉ ያድርጉ። በትክክል ያልተመለሱ 1. ከዚህ ጽሑፍ የወደድኩት…
ካሉ ትክክለኛውን መልስ በመንገር 2. ጽሑፉን ስታነብልኝ/ስታነቢልኝ/ ያሰብኩት/
ግብረመልስ ይስጡ።) በአዕምሮየ የሣልኩት/የፈጠርኩት ሥዕል…
3. በጽሑፉ ውስጥ መካተት የሚገባቸው ዝርዝር
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ሀሳቦች…
የፈረስ ሽርጥ (ሽምጥ) የውድድር 4. ከጽሑፉ ውስጥ መሻሻል አለባቸው ብ ዬ
ጨዋታ የማስባቸው አገላለጾች…
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) 5. መግቢያውን/መደምደሚያውን ለማሻሻል…
ሥሩ (መ. ተማሪዎች ተግባሩን ሲሠሩ በየቡድኑ
መ. "የፈረስ ሽርጥ (ሽምጥ) የውድድር ጨዋታ" እየተዘዋወሩ በአግባቡ መሥራታቸውን
ከሚለው ምንባብ አምስቱን አንቀጾች ጥንድ ይከታተሉ። ከላይ የተዘረዘሩትን
ጥንድ ሆናችሁ ተራበተራ ድምፅ እያሰማችሁ የመንደርደሪያ ሀሳቦች በማስታወስ እንዲናገሩ
አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ ሌሎቻችሁ ያበረታቱ። ተማሪዎች አስተያየት ሲሰጡ፣
ጓደኞቻችሁ ማሻሻል ያለባቸውን ነገሮች የንግግራቸውን የሀሳብ ፍሰት፣ ምክንያታዊነት፣
መዝግቡ። ለአመዘጋገብ እንዲያመቻችሁ ግልፅነት… ይገምግሙ።)
በሰሌዳ ላይ የቀረበውን ሠንጠረዥ
በደብተራችሁ ሥሩ። (የመገምገሚያ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ሠንጠረዡን ይሣሉላቸው።)
ቅጽል፣ መጣኝና ደረጃ አመልካች
(መ. ዝርዝር አሠራሩን ከምዕራፍ 1፣ ከ3ኛው ቍጥሮች
ሳምንት፣ ከ9ኛው ቀን አቀላጥፎ ማንበብ፣
የመምህር መምሪያውን ይመልከቱ። ሥሩ
የመገምገሚያ ሠንጠረዡን ደግሞ ከምዕራፍ (መ. የሚከተለውን ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ
1፣ ከ3ኛው ሳምንት ከመማሪያ መጽሐፍ ያዘጋጁ።)

፻፶፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 159


ደረጃ አመልካች
መጣኝ ቍጥር ቅጽል
ቍጥር

መ. በሰሌዳው ላይ ያዘጋጁትን ሠንጠረዥ


በደብተራችሁ አዘጋጁ። ከዚያም "የፈረስ
ሽርጥ (ሽምጥ) የውድድር ጨዋታ" ከሚለው
ምንባብ ቅጽሎችን፣ መጣኝና ደረጃ አመልካች
ቍጥሮችን ለይታችሁ በሠንጠረዡ ውስጥ
ጻፉ።
(መ. ተግባሩን ተማሪዎች መጀመሪያ በግል
እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም እያንዳንዳቸው
በለዩዋቸው ቅጽሎች፣ መጣኝና ደረጃ
አመልካች ቍጥሮች ላይ በጥንድ እየተወያዩ
ሠንጠረዣቸውን እንዲያሟሉ ያድርጉ።
ከዚያም ሁለት ጥንዶችን በአንድ (ባለ4
አባላት)፣ ከዚያም እንደገና በማቀናጀት
(ባለ8 አባላት) በማድረግ ያደራጇቸው።
በመቀጠል ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ
ያድርጉ። ደብተራቸውን ሲቀያየሩ አብረው
የሠሩት ርስበርስ አይቀያየሩም። ከዚያም
ባዘጋጁት ሠንጠረዥ ውስጥ መልሱን ሰሌዳው
ላይ ይጻፉላቸውና በቡድን እንዲተራረሙ
ያድርጉ።)

ደረጃ
መጣኝ
አመልካች ቅጽል
ቍጥር
ቍጥር
4 ፣ 100 1ኛ ታዋቂ
400 ፣ 1 2ኛ ፈጣን
48 ፣ 2 3ኛ ምቹ
60 ፣ 13 4ኛ ብዙ
8 ፣ 3 5ኛ አነስተኛ
10 ፣ 4 6ኛ ያሸበረቁ
6 ፣ 600 አባጣጎርባጣ
18
(መ. ሌሎች አማራጮችም ሊቀርቡ ይችላሉ።)

160 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 8 ፻፷


ምዕራፍ 9 ሥነቃል
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• "ሥነቃል" በሚል የምንባብ ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት በንግግርና በጽሑፍ ይጠቀማሉ፤
• ባነበቡት ታሪክ ውስጥ ስለሚገኙ ገፀባህርያት በማወዳደርና በማነፃፀር ይጽፋሉ፤
• የላኪና የተቀባይ አድራሻን በፖስታ ላይ በትክክል ይጽፋሉ።
• በትረካ ስልት የተጻፉ ምንባቦችን አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• "እንቆቅልሽ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• "ሥነቃል" በሚል የምንባቡ ይዘት መነሻነት ይናገራሉ፤
• ከዓረፍተነገሮች ውስጥ ግሳዊ ሐረጎችን ይለያሉ።

ያድርጉ። በዚህ ዓይነት በትክክል ያልተነበቡ


1ኛ ሳምንት ሐረጋት ካሉ ደጋግመው እንዲያነቡ በማድረግ
እንቆቅልሽና ቃላዊ ግጥም ያለማምዷቸው።)

ማንበብ (35 ደቂቃ)


1ኛ ቀን
ቃላዊ ግጥም
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
• የቃላት ጥናት
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
• ማንበብ
ልሥራ
መ. በየአካባቢው ሰዎች ልዩልዩ ሥራዎችን
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ) ሲሠሩ፣ በበዓላትና፣ በሠርግ ጊዜ ወዘተ.
መነጠልና ማጣመር ከትውልድ ወደትውልድ እየተላለፉ በመጡ
ቃላዊ ግጥሞች አማካይነት ያዜማሉ፤
ሥሩ ያንጎራጉራሉ። ለምሳሌ ገበሬዎች ሲያርሱ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን፣ በቃላት ከሚያንጎራጉሯቸው ግጥሞች መካከል ሁለቱን
ጥናት ሥር፣ በሠንጠረዡ ውስጥ የቀረቡትን ልንገራችሁ። (የሚከተለውን ቃላዊ ግጥም
ሐረጋት በመነጣጠልና በማጣመር አንብቡ። ዜማውን ጠብቀው ያንብቡላቸው።)
"በዕልልታም" የሚለውን ሐረግ ነጣጥላችሁ
አንብቡ። [መ. አርሳለሁ እንጂ አልመረርም፣
[ተ. በ-ዕልል-ታ-ም] ችግር በወንጭፍ አይባረርም።
መ. በጣም ጥሩ! ይህንኑ ሐረግ አጣምራችሁ ማረስ ነው እንጂ ከዲቡ ድረስ፣
አንብቡ። የመጣው ዘመድ ስቆ እንዲመለስ።]
[ተ. በዕልልታም] ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ! (ሌሎቹንም ሐረጋት እንዲያነቡ መ. እስኪ እናንተም በአካባቢያችሁ ሰዎች

፻፷፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 161


በሥራ፣ በበዓላት፣ በሠርግ ወይም በሌላ ንዑስ ርዕስ ተራበተራ አንብቡ። ከዚያም
አጋጣሚ የሚያንጎራጉሯቸውን ቃላዊ ግጥሞች መጽሐፋችሁን እጠፉ። ተራበተራ አንቀጹ
ንገሩኝ። ስለምን እንደሚገልጽ፣ በንዑስ ርዕሱ
የተጠቀሱት የቃል ግጥም ዓይነቶች ምን
[ተ. በአካባቢያቸው የሚነገሩ ቃላዊ ግጥሞችን
ዓይነት ባህርይ እንዳላቸው ተራበተራ ገምቱ።
ይናገራሉ።]
[ተ. ቍጥር "1"ና "2" ተማሪዎች ተራበተራ
መ. አሁን ደግሞ በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው
ይገምታሉ።]
ቀን፣ በምንባቡ ውስጥ ያሉትን ርዕስ፣ ንዑስ
ርዕሶችና ሥዕሎች ተመልከቱና ምንባቡ መ. አሁን "1" ቍጥሮች በመጀመሪያው ንዑስ
ስለምን እንደሚገልጽ ገምቱ። ርዕስ ሥር የቀረበውን የምንባቡን አካል
ድምፅ እያሰማችሁ አንብቡ። "2" ቍጥሮች
[ተ. ከርዕሶቹና ከሥዕሉ ተነስተው ስለምንባቡ
ደግሞ በለሆሳስ እያነበባችሁ ተከታተሉ።
ይዘት ይገምታሉ።]
[ተ. ያነባሉ።]
የማንበብ ሂደት (15 ደቂቃ)
መ. በመጀመሪያ "1" ቍጥሮች ከገመታችሁት
መገመትና ግምትን እያረጋገጡ ማንበብ ትክክል የሆነው የትኛው እንደሆነ ተናገሩ።
ልሥራ በመቀጠልም ከገመታችሁት ውጭ በምንባቡ
መ. አሁን "ቃላዊ ግጥም" በሚል ርዕስ የቀረበውን ያገኛችሁትን አዲስ ነገር ተናገሩ። ከዚያም
ምንባብ ከማንበቤ በፊት ከርዕሱ በመነሳት "2" ቍጥሮች፣ "1" ቍጥሮች በተናገሩት
ስለምንባቡ ይዘት እገምታለሁ። ("ቃላዊ መንገድ ተናገሩ።
ግጥም" የሚለውን ርዕስ ድምፅ በማሰማት (መ. በዚህ ዓይነት የተማሪዎቹን ሚና እየቀያየሩ
ያንብቡላቸው።) ሌሎቹንም ንዑስ ርዕሶች "እየገመቱና"
[መ. ቃላዊ ግጥም … ቃላዊ ግጥም ምን ማለት ግምታቸውን ከአንቀጾቹ እያረጋገጡ
ነው? ግጥም ምን እንደሆነ አውቃለሁ። ቤት እንዲያነቡ ያድርጉ።)
የሚመታ፣ ዜማ ያለው፣ ቁጥብ የሆነ፣ ውበት
አንብቦ መረዳት (15 ደቂቃ)
ያለው ጥበባዊ የቋንቋ አጠቃቀም መሆኑን
አውቃለሁ። "ቃላዊ" ማለት በጽሑፍ ሳይሆን ሥሩ
በቃል የሚነገር ማለት ይሆን? ባደኩበትም መ. አሁን የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን
ሆነ በምኖርበት አካባቢ በሥራ፣ በበዓላት፣ ትመልሳላችሁ። በመጀመሪያ ተግባር አንድን
በሠርግ፣ በለቅሶ ወዘተ. ጊዜ የሚነገሩ ሥሩ። ጥያቄዎቹን "እውነት" ወይም "ሐሰት"
ግጥሞችን አውቃለሁ። ቃላዊ ግጥም በማለት ከመለሳችሁ በኋላ ምክንያታችሁን
የሚባሉት ምናልባት እነዚህ ሊሆኑ ይችላሉ። ተናገሩ።
ግምቴ ትክክል መሆኑን ወይም አለመሆኑን
መ. ቃላዊ ግጥም በየጊዜውና በየቦታው አንዳንድ
አንብቤ አረጋግጣለሁ።] (የመጀመሪያውን
የአቀራረብና የትርጉም ለውጥ ሊደረግበት
አንቀጽ ያንብቡላቸው።)
ይችላል። እውነት ወይስ ሐሰት?
[መ. ግምቴ ትክክል ነበር። ቃላዊ ግጥሞች
[ተ. ሐሰት]
ያልተጻፉ መሆናቸው፣ የሥራ፣ የበዓል፣ የለቅሶ
ወዘተ. ግጥምች መሆናቸው ተገልጿል።] መ. ለምን ሐሰት አላችሁ?

ሥሩ [ተ. ቃላዊ ግጥሞች በየጊዜውና በየቦታው


መ. እናንተም ልክ እኔ እንዳደረግሁት አንዳንድ የአቀራረብና የትርጉም ለውጥ
እየገመታችሁና ግምታችሁን እያረጋገጣችሁ እንደሚደረግባቸው ተገልጿል። የዚህም
አንብቡ። ምክንያቱ ያልተጻፈ በመሆኑ ነው።]

(መ. ተማሪዎችን "1"ና "2" ቍጥር ብለው (መ. በዚህ ዓይነት እየጠየቁ በቃል እንዲመልሱ
በመሰየም በጥንድ ያደራጁ።) ያድርጉ። ትክክለኛ መልሶቹን በመንገርም
ግብረመልስ ይስጡ።)
መ. ቍጥር "1"ና "2" ተማሪዎች የመጀመሪያውን

162 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፷፪


እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው 2ኛ ቀን
ቀን የቀረበውን ተግባር "2"ን እንሥራ።
(በመማሪያ መጽሐፍ የቀረበውን ሠንጠረዥ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
በሰሌዳው ላይ ይሣሉ።) አሁን የሥራ • ቃላት
ዘፈኖችን፣ የቀረርቶ ግጥሞችንና የሠርግ
ዘፈኖችን ተመሳስሎና ልዩነት በሠንጠረዥ • መጻፍ
ውስጥ እንዘርዝር። እነዚህን ቃላዊ ግጥሞች
የሚያመሳስል አንድ ነገር ንገሩኝ።
[መተ. ሁሉም ያልተጻፉ ናቸው።] ቃላት (10 ደቂቃ)
መ. በጣም ጥሩ! የሥራ ቃላዊ ግጥሞች ከሌሎቹ እንሥራ
የሚለዩበትን አንድ ነገር ንገሩኝ። መ. አሁን በምንባቡ ውስጥ የተሠመረባቸውን
ቃላትና ሐረጋት፣ የዓረፍተነገሩን ሀሳብ
[ተ. የሥራ ቃላዊ ግጥሞች የሚከወኑት በሥራ
በማይቀይሩ ተመሳሳይ ቃላትና ሐረጋት
ላይ ወይም ሥራው እንዳለቀ ነው።]
እንተካ። የሥራ ዘፈኖች በሚል ንዑስ ርዕስ
መ. በጣም ጥሩ! ሥር በቀረበው አንቀጽ፣ በ2ኛው ዓረፍተነገር
ሥሩ ውስጥ "ለማቀላጠፍ" የሚለው ሐረግ
ተሰምሮበታል። እስኪ ሐረጉ የሚገኝበትን
መ. አብረን በሠራነው ምሳሌ መሠረት
ዓረፍተነገር አንብቡልኝ። (ተማሪዎች
በመጽሐፋችሁ የቀረበውን ሠንጠረዥ
ዓረፍተነገሩን እንዲያነቡ ያድርጉ።)
በደብተራችሁ አዘጋጁና የቃላዊ ግጥሞቹን
ተመሳስሎና ልዩነት ዘርዝሩ። ለምሳሌ መ. በጣም ጥሩ! "ለማቀላጠፍ" የሚለውን ሐረግ
የቀረርቶ ግጥሞች ከሌሎች ቃላዊ ግጥሞች ሊተካ የሚችል ቃል ወይም ሐረግ ንገሩኝ።
የሚለዩበትን አንድ ነጥብ ንገሩኝ።
[መተ. ለማፋጠን]
[ተ. የቀረርቶ ግጥሞች በዋናነት በጦርነት ጊዜ መ. በጣም ጥሩ! እስኪ አሁን አዲሱ ሐረግ
ሠራዊቱ ወደጦር ግንባር ከመዝመቱ በፊት፣ የዓረፍተነገሩን ሀሳብ የማይቀይር መሆኑን
ከድል መልስ ወይም ጀግኖቹን ለማሞገስ ለማረጋገጥ "ለማቀላጠፍ" የሚለውን ሐረግ፣
ወይም በሌሎች አጋጣሚዎች ይከናወናሉ።] "ለማፋጠን" በሚለው ሐረግ ተክተን
(መ. በዚህ ዓይነት ተመሳስሏቸውንና ልዩነታቸውን እናንብብ።
ባዘጋጁት ሠንጠረዥ እንዲዘረዝሩ [መተ. "ለማቀላጠፍ" የሚለው ሐረግ "ለማፋጠን"
ያድርጉ። ከዚያም በግል የሠሩትን በቡድን በሚል ሐረግ ተክተው ሙሉውን ዓረፍተነገር
እንዲወያዩበት ያድርጉ። ተግባር ሦስትን ያነባሉ።
ደግሞ በቡድን በወረቀት ላይ ለ3ኛ ቀን
ሠርተው እንዲመጡ የቤትሥራ ይስጧቸው።) ( መ. ሐረጉ በሌላ ሐረግ ተተክቶ ሲነበብ
ከዓረፍተነገሩ ጋር ካልተስማማ በሌላ ተስማሚ
ቃል ወይም ሐረግ መተካት እንደሚገባ
ያሳስቧቸው።)
ሥሩ
መ. አሁን አብረን በሠራነው መሠረት "ቃላዊ
ግጥም" በሚል ርዕስ በቀረበው ምንባብ
ውስጥ የተሠመረባቸውን ቃላትና ሐረጋት
የዓረፍተነገሩን ሀሳብ በማይቀይሩ ተመሳሳይ
ቃላት ወይም ሐረጋት ተኩ። በሁለተኛው
አንቀጽ በአምስተኛው ዓረፍተነገር ውስጥ
የተሠመረበት ሐረግ የትኛው ነው?

፻፷፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 163


[ተ. እንዳይጫናቸው] በሰሌዳው ላይ ይጻፉ።)
መ. በጣም ጥሩ! ሐረጉ የሚገኝበትን ዓረፍተነገር ቦርሳ ቢዳብሱ አሁን ምን ይገኛል፣
አንብቡ።
አይገኝም ዋሱ አበዳሪው ቢገኝ።
[ተ. ዓረፍተነገሩን ያነባሉ።]
መ. የስንኞቹ የመጨረሻ ፊደሎች ስለማይመሳሰሉ
መ. በጣም ጥሩ! የዓረፍተነገሩን ሀሳብ ሳንቀይር ግጥሙ ቤት አልመታም። ቤት እንዲመታ
ሐረጉን ሊተካ የሚችል ተመሳሳይ ቃል ምን እናድርግ?
ወይምሐረግ ንገሩኝ።
[መተ. በየስንኞቹ ውስጥ ያሉትን ሐረጎች
[ተ. እንዳይሰማቸው] ቦታቸውን ማቀያየር]
መ. ጎበዞች! የቀድሞውን ሐረግ በአዲሱ ሐረግ መ. በጣም ጥሩ! ይህን በሰሌዳው ላይ ጽፈን
ተክታችሁ ሙሉውን ዓረፍተነገር አንብቡ። እናሳይ። (ተማሪዎች በሰሌዳው ላይ ጽፈው
እንዲያስተካክሉ የድርጉ።)
[ተ. የቀድሞውን ሐረግ በአዲሱ ሐረግ ተክተው
ሙሉውን ዓረፍተነገር ያነባሉ።] [መተ. አሁን ምን ይገኛል ቦርሳ ቢዳብሱ፣
(መ. በዚህ ዓይነት ሌሎቹንም ቃላት/ሐረጋት አበዳሪው ቢገኝ አይገኝም ዋሱ።]
በተመሳሳይ ቃላት/ሐረጋት እንዲተኩ
ሥሩ
ያድርጉ። አዲሱን ቃል/ሐረግ ተክተው
ሲያነቡ ትርጉም ካልሰጣቸው ወይም መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በመጻፍ
የዓረፍተነገሩን ሀሳብ ከቀየረው ሌላ ተመሳሳይ ሥር የቀረቡ የተዛቡ ቃላዊ ግጥሞች ቤት
ቃል/ሐረግ እንዲፈልጉ ያድርጉ።) እንዲመቱ አድርጋችሁ አስተካክላችሁ ጻፉ።
"ሥነዜጋ የሚባል የምናውቅበት፣
መጻፍ (30 ደቂቃ) መጥቶልን ትምህርት መብትና ግዴታን።"
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) የሚለውን ግጥም አስተካክላችሁ በደብተራችሁ
የተዛባን ግጥም አስተካክሎ መጻፍ ጻፉና አንብቡ።

ልሥራ [ተ. ሥነዜጋ ሚባል መጥቶልን ትምህርት፣


መ. አሁን ሐረጎቻቸው ተዛብተው የቀረቡ መብትና ግዴታን የምናውቅበት።]
ግጥሞችን እንዴት ቤት እንዲመቱ አድርጎ
ማስተካከል እንደሚቻል ላሳያችሁ። (መ. በዚህ ዓይነት ቀሪዎቹን ግጥሞች አስተካክለው
(የሚከተለውን የተዛባ ግጥም በሰሌዳው ላይ እንዲጽፉ ያድርጉ። ከዚያም ደብተራቸውን
ጽፈው ያንብቡላቸው።) እንዲቀያየሩ አድርገው ትክክለኛውን መልስ
በመንገር ርስበርስ ይተራረሙ።)
ኋላ ሲቸገሩ የሰው እጅ ከማየት፣
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ከልብነው መሥራት ወገብን አጥብቆ።
የፖስታ ላይ አድራሻ አጻጻፍ
መ. የስንኞቹ የመጨረሻ ፊደሎች ስለማይመሳሰሉ
ግጥሙ ቤት አልመታም። ስለዚህ በሁለተኛው ልሥራ
ስንኝ ውስጥ ያሉትን ሐረጎች ቦታቸውን መ. በምዕራፍ 8 ስለሠላምታ ደብዳቤ አጻጻፍ
በመቀያየር አስተካክላለሁ። (እንደሚከተለው ተምራችኋል። ዛሬ ደግሞ በፖስታ ላይ
አስተካክለው በሰሌዳው ላይ ይጻፉ።) አድራሻ እንዴት እንደሚጻፍ ትማራላችሁ።
ደብዳቤ ከተጻፈ በኋላ ከአንድ ቦታ ወደሌላ
[መ. ኋላ ሲቸገሩ የሰው እጅ ከማየት፣ ቦታ በፖስታ ቤት በኩል ለመላክ አድራሻን
ወገብን አጥብቆ ከልብነው መሥራት።] በተገቢው መንገድ በፖስታው ላይ መጻፍ
ያስፈልጋል። (በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን
እንሥራ በመማሪያ መጽሐፍ የቀረበውን የፖስታ ቅጽ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። (የሚከተለውን ሰሌዳው ላይ ያዘጋጁ።) በፖስታው ጀርባ
የሐረጋቱ ቅደምተከተል የተዛባ ግጥም በስተግራ ራስጌ ምን ይጻፋል?

164 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፷፬


[መ. የላኪ አድራሻ ] (በሰሌዳው ላይ ያዘጋጁትን እንደሚጻፍ ነው። አንዳንድ ጊዜ ግን
ቅጽ እየጠቆሙ ይንገሯቸው።) የፖስታውን ጀርባና ፊት ተጠቅሞ አድራሻ
የመጻፍ ልማድ አለ። ሁለቱንም ገጾች
መ. በፖስታው ጀርባ በስተቀኝ ግርጌ ምን
መጠቀም ሲያስፈልግ በጀርባው በኩል
ይጻፋል?
በቴምብሩ በስተግራ ዝቅ ብሎ የተቀባይ
[መ. የተቀባይ አድራሻ] አድራሻ ሲጻፍ የላኪ አድራሻ ደግሞ በፊት
መ. በፖስታው ጀርባ በስተቀኝ ራስጌ ያለው ቦታ ለፊቱ ይጻፋል። የአቀማመጥ ቅደምተከተሉ
የምን ቦታ ነው? ግን ተመሳሳይ ነው ስለሆነም ይህንኑ ሁኔታ
ለተማሪዎች ይግለጹላቸው።
[መ. የፖስታ ቴምብር] (የቀረጥና የፖስታ
ቴምብሮች አሉ። ፖስታ ላይ የሚለጠፈው
ግን የፖስታ ቴምብር መሆኑን ያሳስቧቸው።) 3ኛ ቀን
እንሥራ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ፤ በላኪ • አቀላጥፎ ማንበብ
አድራሻ፣ በመጀመሪያው ክፍት ቦታ ምን
ይጻፋል? • ማዳመጥ

[መተ. የላኪ ስም] • ሰዋስው

መ. በጣም ጥሩ! በላኪ አድራሻ በሁለተኛው


ክፍት ቦታ ምን ይጻፋል? የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
[መተ. የልዩ ቦታው ስም] ሥሩ
መ. በጣም ጥሩ! በላኪ አዳራሻ በሦስተኛው ክፍት (መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን፣ በተግባር 3
ቦታ ምን ይጻፋል? የተሠጣቸውን የቤትሥራ፣ ከየቡድኑ የተወከሉ
ተማሪዎች እንዲያቀርቡ ያድርጉ።)
[መተ. የመልዕክት/የፖስታ ሣጥን ቍጥር]
መ. ቃላዊ ግጥሞች ለከዋኙ ማኅበረሰብ ምን
መ. በጣም ጥሩ! በላኪ አድራሻ በአራተኛው
ጠቀሜታ አላቸው?
ክፍት ቦታ ምን ይጻፋል?
[ተ. ሥራን ያቀላጥፋሉ፣ ወኔን ይቀሰቅሳሉ
[መተ. ከተማ]
(ያደፋፍራሉ)፣ ያዝናናሉ፣ ድካምና መሰላቸትን
ሥሩ ያስወግዳሉ፣ በማኅበረሰቡ ውስጥ የመቀራረብ
(መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ) መንፈስ ይፈጥራሉ፣ ያስተምራሉ…]
መ. አሁን ደግሞ በተቀባይ አድራሻ በኩል (መ. በዚህ ዓይነት የየቡድኑ ተወካዮች
ምን ምን ነገሮች እንደሚጻፉ ለጓደኞቻችሁ እንዲያቀርቡ ያደርጉና የማስተካከያ
በምሳሌ አስደግፋችሁ ተናገሩ። በተቀባይ አስተያየት ሰጥተው ያጠቃሉ።)
አድራሻ በመጀመሪያው መስመር ምን
ይጻፋል? አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
[ተ. የተቀባይ ስም] ቃላዊ ግጥም
መ. ለምሳሌ የራሳችሁን ስም በተቀባይ አድራሻ ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
ላይ ጻፉ።
ሥሩ
(መ. በዚህ ዓይነት በቡድን እየተወያዩና ምሳሌ መ. ዛሬ በጥንድ ድምፅ እያሰማችሁ የማንበብ
እየሰጡ እንዲሠሩ ያድርጉ።) ልምምድ ታደርጋላችሁ። በመጀመሪያ ግን
ማሳሳበያ፡- "ቃላዊ ግጥም" በሚል ርዕስ የቀረበውን
ምንባብ ይዘት በማስታወስ የቅድመንባብ
እስካሁን ያየነው የአድራሻ አጻጻፍ በፓስታው
ጥያቄዎችን መልሱ። የቃላዊ ግጥም
ጀርባ ላይ የላኪና የተቀባይ አድራሻ

፻፷፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 165


ዓይነቶችን ዘርዝሩ። ግጥም" በሚለው ርዕስ በቀረበው ምንባብ
ውስጥ የሚገኙትን ግጥሞች ተራበተራ ድምፅ
[ተ. የሥራ ግጥም፣ የፉከራ ግጥም፣ የልመና
እያሰማችሁ አንብቡ። ስታነቡ የግጥም
ግጥም፣ የቀረርቶ ግጥም፣ የሠርግ ዘፍኖች…]
አነባበብ ሥርዓትን ጠብቃችሁ መሆን
መ. በጣም ጥሩ! ቃላዊ ግጥሞች በምን በምን አለበት። ትክክለኛውን አነባበብና ቅላፄ/ዜማ
ይመሳሰላሉ? እስከሚመጣላችሁ ደጋግማችሁ አንብቡ።
[ተ. ያልተጻፉ ናቸው፤ ዜማ አላቸው፤ ይከወናሉ።] (መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ በሰጧቸው
መመሪያ መሠረት እየሠሩ መሆናቸውን
ማንበብ (8 ደቂቃ)
ይከታተሉ። በትክክል የማያነቡትን አነባበቡን
ልሥራ በማሳየት ይደግፏቸው።)
መ. ዛሬ "ቃላዊ ግጥም" በሚል ርዕስ በቀረበው
ምንባብ ውስጥ የሚገኙ ቃላዊ ግጥሞችን ማዳመጥ (15 ደቂቃ)
በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ ድምፅ እያሰማችሁ
ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን እኔ እንዴት እንቆቅልሽ
ማንበብ እንዳለባችሁ ላሳያችሁ። ግጥም ቅድመማዳመጥ (5 ደቂቃ)
የራሱ የሆነ የአነባበብ ስልት አለው። ግጥም
ሲነበብ በስንኝ ውስጥ ባሉ ሐረጎች መካከል ሥሩ
አጭር ዕረፍት፣ በስንኝ መጨረሻ ደግሞ ሙሉ (መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ።)
ዕረፍት ይደረጋል። ከዚህ በተጨማሪ ግጥም፣ መ. ሥዕሉን ተመልክታችሁ የተረዳችሁትን
እንደግጥሙ ዓይነት ስሜት የየራሱ የሆነ ተናገሩ።
የአነባበብ ቅላፄ/ዜማ አለው። (የሚከተለውን
የሥራ ግጥም ዜማውን ጠብቀው ያንብቡላቸው [ተ. ከሥዕሉ የተረዱትን ይናገራሉ።]
አንድ ቋሚ "/" ካለበት ላይ አጭር ዕረፍት፣ መ. አሁን በጥንድ በጥንድ ሆናችሁ እንቆቅልሽ
ሁለት ቋሚ "//" ያለበት ላይ ሙሉ ዕረፍት ተጫወቱ።
ያድርጉ። እንደዚህ ዓይነት ግጥሞች ድምፅን
ሳብ/ረዘም እያደረጉ እንደሚነበቡ ልብ [ተ. በጥንድ ሆነው እንቆቅልሽ ይጫወታሉ።]
ይበሉ። አራት ነጥብ ላይም ሙሉ ዕረፍት (መ. ሁሉም ተማሪዎች እየተሳተፉ መሆኑን
ይደረጋል።) እየተዘዋወሩ ይከታተሉ።)
የአበሻ ማሽላ/ በጤፍ ከመበደር// የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ)
እርሻ ሲያርሱ ውሎ/ሲያርሱ ነበር ማደር። ሥሩ
መ. የፉከራ ግጥሞች ስንኞች አጠር አጠር ያሉ መ. አሁን "እንቆቅልሽ" በሚል ርዕስ የቀረበ
ናቸው። ሲነገሩም ፈጠን ፈጠን ባለና ወኔን ምንባብ አነብላችኋለሁ፤ ጠቃሚ/ዋና ሀሳቦችን
በሚቀሰቅስ ጠንካራ ድምፅ ነው። ሲከወኑም ማስታወሻ እየያዛችሁ፣ በእንቆቅልሽ ምልልሱ
ራስ እየተነቀነቀ ትከሻ እየተሰበቀ ነው። ክፍል ላይ መልሱን እየገመታችሁ አዳምጡ።
(የሚከተለውን ግጥም ትክክለኛውን ቅላፄ/ (መ. የማዳመጥ ምንባቡን ያንብቡላቸው።
ዜማና ስሜት ጠብቀው ከአካላዊ እንቅስቃሴ ሦስተኛውን አንቀጽ አንብበው ሲጨርሱ
ጋር በማንበብ ያሳዩአቸው።) በኮከብ ምልክት ውስጥ ያለውን ጥያቄ
የወይኖ ጌታ/ የስመ ጥሩ// ይጠይቋቸው።)
የጫሉ ጌታ/ የስመ ጥሩ// [ተ. ጨዋታውን የሚከታተሉ፣ ለመጫወት ተራ
የሚጠባበቁትና ዳኞች]
የጀንበር ጌታ/የስመ ጥሩ//
( መ. መልሱን ከተማሪዎች ከተቀበሉ በኋላ
መብረቅ ያረሰው/ይመስላል ፈሩ።
ማንበብዎን ይቀጥሉ። ሁለተኛው የኮከብ
ሥሩ ምልክት ካለበት ቦታ ሲደርሱ ጥያቄውን
መ. ተማሪዎች በጥንድ በጥንድ ተደራጁና "ቃላዊ ይጠይቋቸው።)

166 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፷፮


[ተ. ተማሪዎች ይገምታሉ።] ጦቢያው፡- ለራሱ ሳይቀምስ፣ የቆረሰውን ያጎርስ፣
(መ. ተማሪዎች እንዲገምቱ ካደረጉ በኋላ ሰማኸኝ፡- እጅ!
ማንበብዎን ይቀጥሉ።) ጦቢያው፡- በጣም ጥሩ! መልሰሃል። አሁን
ደግሞ አንተ ጠይቀኝ።
እንቆቅልሽ
ሰማኸኝ፡- እንቆቅልሽ፣
እንቆቅልሽ ጠያቂና ተጠያቂ ኖሮት በጥንድ
ጦቢያው፡- ምን አውቅልህ?
የሚጫወቱት ውድድር አከል የጥያቄና መልስ
ሥነቃል ነው። ልጆችና ወጣቶች ይሳተፉበታል። ሰማኸኝ፡- ለማታምነው ፈቷ ምራቅ ነው ቅባቷ።
አመራማሪ ባህርይ ስላለው የልጆችን አእምሮ *** የዚህ እንቆቅልሽ ጥያቄ መልስ ምን
ያበለጽጋል። አካባቢያቸውንም እንዲያውቁ ይመስላችኋል?***
ያግዛቸዋል። እንዲሁም የእንስሳትንና የተፈጥሮን
ልዩልዩ አፈጣጠርና ፀባይ እንዲገነዘቡ ያደርጋል። ጦቢያው፡- ድመት!
በእንቆቅልሽ የሚጠየቁት ጥያቄዎች፣ በአብዛኛው ሰማኸኝ፡- በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ አንቺ
ከማኅበረሰቡ የዕለትተዕለት ህይወት ጋር ጠንካራ ጠይቂኝ።
ቁርኝት አላቸው። የሰው የአካል ክፍሎች፣ ጦቢያው፡- እንቆቅልህ፣
የእንስሳት፣ የተክሎች፣ የምግብና የእህል ዓይነቶች
ወዘተ. ትኵረት ይደረግባቸዋል። ሰማኸኝ፡- ምን አውቅልሽ?
የእንቆቅልሽ ጨዋታ ተሳታፊዎች አሉት። እነሱም ጦቢያው፡- ዐይኗን ተኩላ ገበያ ትወጣ፣
ጨዋታውን የሚከታተሉና ተራ የሚጠባበቁት ሰማኸኝ ፡- ሴት!
ናቸው። በጨዋታው ሂደትና በሥነሥርዓቱ ላይ
ጦቢያው፡- አይደለም።
ስህተት ቢፈጠር የሚያስተካክሉና በመልሱ ላይ
ክርክር ቢነሳ የሚዳኙ አዋቂዎችም ይታደማሉ። ሰማኸኝ፡- መርፌ!
***የእንቆቅልሽ ጨዋታ ተሳታፊዎች ጦቢያው፡- አይደለም።
እነማን ናቸው?*** ሰማኸኝ፡- (እያሰበ ቆየ)
የእንቆቅልሽ ጨዋታ የራሱ የሆነ ሕግና ሥርዓት ጦቢያው፡- ዋለብህ አደረብህ፣
አለው። ጨዋታውን ጠያቂ "እንቆቅልህ/ሽ"፣
ሰርዶ በቀለብህ፣
ተጠያቂ "ምን አውቅልህ/ሽ" በማለት ይጀምሩታል።
በመቀጠልም ጠያቂ ጥያቄውን ያቀርባል/ እንደእንጀራ ነፈሰብህ፣
ታቀርባለች። ተጠያቂ መልስ ይሆናል ያለውን/ ሰማኸኝ፡- እሽ ይግባልሽ!
ያለችውን በማሰላሰል ይናገራል/ትናገራለች፤
መልሱ ትክክል ካልሆነ ተጠያቂው/ዋ ሌላ መልስ ጦቢያው፡- እንኳን ገባልኝ፣
እንዲሰጥ/እንድትሰጥ ጉትጎታ ይደረጋል። ተንቧለልኝ፣
መመለስ ካልቻለ/ች አገር እንዲሰጥ/እንድትሰጥ ፈረስ ከበቅሎ ታሰረልኝ፣
ተደርጎ የስድብ ናዳ ከወረደበት/ባት በኋላ
መልሱ ይነገራል። ተሸናፊም ከጨዋታው ውጭ ከሰሜን፣ ከደቡብ፣ ከምዕራብ፣
ይደረጋል/ትደረጋለች። ተረኛ ተጫዋች እንዲገባ/ ከምሥራቅ ተነጠፈልኝ፣
እንድትገባ ይደረግና ጨዋታው ይቀጥላል። በዚህ አገር ስጠኝ።
ዓይነት ሥርዓት እስከመጨረሸው ይሄዳል።
ሰማኸኝ፡- ጎንደርን ሰጥቼሻለሁ።
የእንቆቅልሽ ጨዋታ በአብዛኛው ማታማታና
በበዓል ቀናት ይከናወናል። የሰፈሩ ልጆችም ጦቢያው፡- ኖሬበታለሁ፤ ሌላ ስጠኝ!
ቀኑ እሁድ በመሆኑ ሰብሰብ ብለው ተቀምጠው ሰማኸኝ፡- ጎጃምን ሰጥቼሻለሁ።
እንቆቅልሽ ይጫወታሉ። ጦቢያው፡- እሱም አገሬ ነው።
ጦቢያውና ሰማኸኝ ተራቸው ደርሶ እንቆቅልሽ ሰማኸኝ፡- አዲስአበባን ሰጥቼሻለሁ።
እየተጫወቱ ነው።
ጦቢያው፡- አዲስ አበባ ሆኜ ምን አጥቼ፣
ጦቢያው፡- እንቆቅልህ፣
ሁሉ በጄ ሁሉ በደጄ፤
ሰማኸኝ፡- ምን አውቅልሽ?
ግርድ ግርዱን ለፈረሴ፣

፻፷፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 167


ምርት ምርቱን ለእኔ፤ እንሥራ
እንዳልሰድብህ ወንድሜ፣ መ. አሁን ደግሞ አንድ እንቆቅልሽ አብረን
እንሥራ። "ቀይ ዘንዶ ዋሻ ውስጥ ተጋድሞ"
እንዳልተውህ ጠላቴ፤
እወቁልኝ?
ከቤትህ በታች ያለው ልምጭ፣
[መተ. ምላስ]
እንዳንተው ነጭ፤
እንደሰፌድ ይዘርጋህ፣ ሥሩ
መ. አብረን በሠራነው መሠረት በ1ኛው ሳምንት፣
እንደደጋን ያጉብጥህ፤
በ3ኛው ቀን፣ በአዳምጦ መረዳት፣ በተግባር 2
ከዚህ እንደይፋት፣ ሥር የቀረቡትን እንቆቅልሾች በደብተራችሁ
ያብርህ እንቅፋት፤ ሙሉ።
በኔ ጉሮሮ ጠጅ ይንቆርቆር፣ መ. "አልቀረም ተቀጥቅጦ አስተኛው ፈልጦ
በአንተ ጉሮሮ አጥንት ይሰንቀር፤ ፈልጦ።" እወቁልኝ!
ና እንሂድ ጓሮ ለጓሮ፣ [ተ. ጌሾ]
አበላሀላሁ የገማች ዶሮ፤ ( መ. በዚህ ዓይነት ቀሪዎችን እንዲመልሱ
ጦቢያው፡- በቃህ ወይስ ልጨምርህ? የቤትሥራ ይስጧቸው፡)
ሰማኸኝ፡- ኧረ በቃኝ! መልሱን ንገሪኝ።
ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ጦቢያው፡- "ዐይኗን ተኳኩላ ገበያ ትወጣ" ማለት
ባቄላ ናት አለችው። ግሳዊ ሐረግን መለየት
ከዚህ በኋላ ተረኛው/ዋ ይገባና/ትገባና ልሥራ
ይጫወታል/ትጫወታለች። በዚህ ዓይነትም ዙሩ መ. ግሳዊ ሐረግ ባለቤቱ የፈፀመውን ወይም
እስከመጨረሻው ይቀጥላል።
የሆነውን ነገር የሚነግር የዓረፍተነገር አካል
አዳምጦ መረዳት (5 ደቂቃ) ነው። ዛሬ የምንማረው በዓረፍተነገር ውስጥ
ሥሩ ግሳዊ ሐረግን መለየት ነው።
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ ያለው ቤቱን አፀዳ። (ይህን ዓረፍተነገር በሰሌዳው
በአዳምጦ መረዳት በተግባር “1” ሥር ላይ ይጻፉ።)
የቀረቡትን ጥያቄዎች ባዳመጣችሁት ምንባብ
መ. ይህን ዓረፍተነገር ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
መሠረት በቃላችሁ መልሱ። በእንቆቅልሽ
(አንድ/ዲት ተማሪ ያስነብቡ።)
ጨዋታ ተሸናፊ የሚለየው እንዴት ነው?
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱ ማን ነው?
[ተ. ተጠያቂ የተጠየቀውን/የተጠየቀችውን
እንቆቅልሽ መመለስ ሳይችል/ ሳትችል [መ. ያለው]
ሲቀር/ ስትቀር ተሸናፊ ይሆናል/ ትሆናለች።] መ. ያለው ምን አደረገ?
(መ. በዚህ ዓይነት ከለ-ሰ የቀረቡትን በቃላቸው [መ. ቤቱን አፀዳ]
እንዲመልሱ ያድርጉ። ከዚያም በትክክል
ያልተመለሱ እንቆቅልሾችን በመመለስ [መ. "ቤቱን አፀዳ" የሚለው ባለቤቱ ያደረገውን
ግብረመልስ ይስጡ።) ስለሚነግረን ግሳዊ ሐረግ ነው ማለት ነው።]
ልሥራ እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ ተግባር "2"ን ትሠራላችሁ። መ. አሁን ሌላ ምሳሌ አብረን እንሥራ።
በመጀመሪያ ግን እኔ እሠራለሁ። "ሲቀመጥ መ. በለጡ ወደቤቷ ሮጠች። (ይህን ዓረፍተነገር
ረጅም ሲቆም አጭር" እወቁልኝ? ሰሌዳው ላይ ይጻፉ።)
[መ. ውሻ] መ. ይህን ዓረፍተነገር ልታነቡልኝ ትችላላችሁ?
(አንድ/ዲት ተማሪ ያስነብቡ።)

168 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፷፰


መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱ ማን ነው/
ናት?
[መተ. በለጡ]
መ. በጣም ጥሩ! በለጡ ምን አደረገች?
[መተ. ወደቤቷ ሮጠች]
መ. ስለዚህ በዓረፍተነገሩ ውስጥ ግሳዊ ሐረጉ
የትኛው ነው?
[መተ. ወደቤቷ ሮጠች]
ሥሩ
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣
በሰዋስው ሥር በቀረቡት ዓረፍተነገሮች
ውስጥ የሚገኙትን ግሳዊ ሐረጎች ለይታችሁ
በደብተራችሁ ጻፉ። "ማስተዋል የቤትሥራዋን
ሠራች።" በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱ
የትኛው ነው?
[ተ. ማስተዋል]
መ. በጣም ጥሩ! ማስተዋል ምን አደረገች?
[ተ. የቤትሥራዋን ሠራች]
መ. ስለዚህ ግሳዊ ሐረጉ የትኛው ነው?
[ተ. የቤትሥራዋን ሠራች] (ይህን በደብተራቸው
እንዲጽፉ ይንገሯቸው። በዚህ ዓይነት
የቀሩትንም እንዲሠሩ ያድርጉ።)

፻፷፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 169


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
2ኛ ሳምንት
ሥሩ
አፈታሪክና እንቆቅልሽ መ. "ጌራና አሰቦ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ
ራሳችሁን እየጠየቃችሁና ለጥያቄያችሁ
ምላሽ ለማግኘት እየሞከራችሁ አንብቡ።
4ኛ ቀን (የመጀመሪያዎቹን ሁለት አንቀጾች ካነበቡ
የዕለቱ ትምህርት ይዘት በኋላ ያቁሙ።)
• ማንበብ መ. ከሁለቱ ወንድማማቾች ታላቁ ማን
ይመስላችኋል?

የቤትሥራ (5 ደቂቃ) [ተ. አሰቦ]


ሥሩ መ. ታላቁ አሰቦ ነው ያላችሁበት ምክንያት
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን በማዳመጥ ምንድን ነው?
ሥር የተሰጣችሁን የቤትሥራ መልስ ንገሩኝ። [ተ. ጌራ የአንተ ጋሻጃግሬ/ አጃቢ ሆኜ ብኖር
"ላዩ ሰርዶ ውስጡ ብርንዶ" ምንድን ነው? ምን ገዶኝ ብሏል። ይህም ለታላቅ ወንድሙ
[ተ. ሽንኩርት] ያለውን አክብሮት ስለሚያሳይ አሰቦ ታላቅ
ነው ማለት ነው።]
መ. “ሰው ሳይቀምስ የምትቀምስ” ምንድን ናት?
መ. በጣም ጥሩ! ማንበባችሁን ቀጥሉ። (3ኛውን
[ተ. የወጥ ማማሰያ] አንቀጽ አንበብው እንደጨረሱ አስቁመው
መ. “ወገበ ጎባጣ ሀገሩን ሁሉ ቆምጣ ቆምጣ” ይጠይቁ።)
ምንድን ናት? መ. "ልጓም የማይገታቸው፣ አለንጋ የማያርፍባቸው
[ተ. ማጭድ] ሆኑ" የተባሉት ምኖቹ ናቸው?

መ. “ከመሬት ወደቀ አንስቼ ብይዘው አለቀ” [ተ. ፈረሶቹ]


ምንድን ነው? መ. በጣም ጥሩ! አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ።
[ተ. በረዶ] አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)
መ. “ህይወት የሌለው ሌት ተቀን የሚሄድ” ልሥራ
ምንድን ነው?
መ. አሁን በምንባቡ መሠረት የቀረቡትን
[ተ. ነፋስ] ጥያቄዎች ትመልሳላችሁ። በተግባር 1፣
በታሪኩ ውስጥ የተከናወኑትን ድርጊቶች
ማንበብ (35 ደቂቃ) በቅደምተከተል በሠንጠረዥ ውስጥ
ትዘረዝራላችሁ። (በመማሪያ መጽሐፉ ላይ
ጌራና አሰቦ የቀረበውን ሠንጠረዥ በሰሌዳው ላይ ይሣሉ።
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ) ሠንጠረዦቹ 4 ብቻ ላይሆኑ ይችላሉ።)
አንድ ምሳሌ እኔ እሠራለሁ። ጌራና አሰቦ
መገመት በመጀመሪያ ምን አደረጉ?
ሥሩ [መ. ጌራና አሰቦ ከጎንደር ተነስተው ወደመንዝ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን፣ በማንበብ ጓሳ ሄዱ። ] (በ"1" ቍጥር ፊት ለፊት ባለው
ሥር የቀረበውን የምንባብ ርዕስ አንብቡ፤ ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።)
ሥዕሉንም ተመልከቱ፤ ከዚያም ምንባቡ
ስለምን እንደሚገልፅ ገምቱ።
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። ወንድማማቾቹ
[ተ. ይገምታሉ።] በመቀጠል ምን አደረጉ?
[መተ. መሬቱን የመከፋፈል ጥያቄ አነሱ።] (ይህን

170 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፸


ዓረፍተነገር ደግሞ በ"2" ቍጥር ፊት ለፊት
ባለው ሳጥን ውስጥ ይጻፉ።) 5ኛ ቀን
ሥሩ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን በአንብቦ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መረዳት ሥር የቀረበውን የድርጊት • ቃላት
ቅደምተከተል ማሳያ ሠንጠረዥ በደብተራችሁ • መጻፍ
አዘጋጁ። ከዚያም "ጌራና አሰቦ" በሚለው
ምንባብ ውስጥ የተከናወኑትን ድርጊቶች
በቅደምተከተል ጻፉ።
መ. ወንድማማቾቹ በመቀጠል ያደረጉት ምንድን
ነው?
ቃላት (10 ደቂቃ)
[ተ. አሰቦ፣ ወንድማማቾቹ መሬቱን ቃላትን በድርጊት መግለፅ፤ ለቃላት
ስለሚከፋፈሉበት ዘዴ ሀሳብ አቀረበ።] ተመሳሳይ ፍቺ መስጠት
መ. በጣም ጥሩ! በደብተራችሁ ባዘጋጃችሁት ልሥራ
ሠንጠረዥ በተራቊጥር 3 ፊትለፊት መ. ዛሬ ከምንባቡ የወጡ ቃላትን በድርጊት
ዓረፍተነገሩን ጻፉ። ትገልፃላችሁ። በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ
ላሳያችሁ።
(መ. ቀሪዎቹን ጥያቄዎች በግል እንዲመልሱ
ያድርጉ። ከዚያም በታሪኩ ቅደምተከተል ላይ "ሰሜን" የሚለውን ቃል ስጠራ ፊቴን ወደሰሜን
ከተማሪዎች ጋር ይወያዩ። ስህተታቸውንም አቅጣጫ አዙሬ እቆማለሁ።
እንዲያስተካክሉ ያድርጉ።) መ. ሰሜን
ሥሩ [መ. ፊትዎን ወደሰሜን አቅጣጫ አዙረው
መ. አሁን ደግሞ የተግባር "2"ን ጥያቄዎች በመቆም ያሳያሉ፡]
በቃላችሁ መልሱ። በአንቀጽ 2
መ. በምንባቡ ውስጥ "እመር ብለው" የሚል ቃል
ወንድማማቾቹ አንተ ምረጥ፣ አንተ ምረጥ
አለ።
ሲባባሉ የቆዩበት ጉዳይ ምን ነበር?
[ተ. የሚካፈሉትን መሬት በመጀመሪያ አንተ "እመርን በድርጊት ላሳይ (ወደፊት ዘልለው
ምረጥ አንተ ምርጥ በማለት ነበር ሲገባበዙ ያሳዩኣቸው።)
የቆዩት።] [መ. እመር ብለው ያሳያሉ።]
(መ. በዚህ ዓይነት እየጠየቁ ተማሪዎች በቃላቸው ሥሩ
እንዲመልሱ ያድርጉ። በትክክል ያልተመለሱ (መ. ተማሪዎች ተነስተው እንዲቆሙ ያድርጉ።)
ጥያቄዎች ላይ የማስተካከያ አስተያየት
መ. "ሰሜን"
በመስጠት ግበረመልስ ይስጡ።)
[ተ. ፊታቸውን ወደሰሜን አዙረው ይቆማሉ።]
(መ. በዚህ ዓይነት ደቡብ፣ ምሥራቅና ምዕራብ
ሲጠሩ አቅጣጫቸውን በመለዋወጥ ፊታቸውን
እያዞሩ መቆማቸውን ይከታተሉ።)
መ. "እመር"
[ተ. አንድ እርምጃ ወደፊት ይዘላሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! "መተቃቀፍ"
[ተ. ጥንድ ጥንድ ሆነው ተቃቅፈው ያሳያሉ።]
መ. በጣም ጥሩ!

፻፸፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 171


ሥሩ እናትም ለልጇ ምድር ደግሞ ለሰው፣
መ. አሁን ደግሞ በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ ምንም ሳይሰስቱ ያላቸውን ሠጥተው፣
በቃላት ሥር የቀረበውን ተግባር “2”ን ሥሩ።
በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ የተሠመረባቸውን አይነግሩ ስሞታ አደረግሁ ብለው።]
ቃላት የሚተኩ ተመሳሳይ ቃላትን ከቀረቡት
አማራጮች መካከል ምረጡ። "እህቴ ማለፊያ
ሸሚዝ ሸለመችኝ" በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ሥሩ
የተሠመረበት ቃል ምንድን ነው? (መ. ተማሪዎችን ከ4-6 አባላት ባላቸው ቡድኖች
ያደራጁ።)
[ተ. ማለፊያ]
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን በድርሰት
መ. በጣም ጥሩ! "ማለፊያ" የሚለውን ቃል ሊተካ መጻፍ ሥር ከቀረቡት ርዕሶች አንድ ምረጡ።
የሚችለው ተመሳሳይ ቃል የትኛው ነው? ከዚያም አንድ ያልተጻፈበት ወረቀት አዘጋጁ፤
[ተ. ጥሩ] በመቀጠል ከቡድን አባላት አንዳችሁ
ከመረጣችሁት ርዕስ በመነሳት አንድ ስንኝ
(መ. በዚህ ዓይነት ከ2-5 የቀረቡትን ጥያቄዎች ጻፉ
ክፍል ውስጥ እንዲመልሱ ያድርጉ። ከዚያም
ትክክለኛውን መልስ በመንገር ርስበርስ [ተ. ከየቡድኑ አንድ አንድ ተማሪዎች በመረጡት
እንዲተራረሙ ያድርጉ። ከተራ ቍጥር 6-10 ርዕስ አንድ ስንኝ ይጽፋሉ።]
ያሉትን ቃላት ደግሞ የቤትሥራ ይስጧቸው) መ. አሁን ወረቀቱን ከጎናችሁ ላለው ተማሪ
አስተላልፉ። ወረቀቱን የተቀበላችሁ
መጻፍ (30 ደቂቃ) ተማሪዎች ከመጀመሪያው ስንኝ ጋር በሀሳብ
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ) የሚስማማ ስንኝ ጻፉ። የምትጽፉት ስንኝ
የመጨረሻ ፊደል ከመጀመሪያው ጋር
በተሰጠ ርዕስ ግጥም መጻፍ ተመሳሳይ ቢሆን የተሻለ ነው።
ልሥራ [ተ. ሁለተኛውን ስንኝ ይጽፋሉ።]
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ የተዛቡ ሐረጋትን
መ. በጣም ጥሩ! ወረቀቱን ከጎናችሁ ላሉት
ቅደምተከተል በማስተካከል ግጥሞቹ ቤት
ተማሪዎች አስተላልፉ፤ ወረቀቱን የተቀበላችሁ
እንዲመቱ አድርጋችሁ ነበር። ዛሬ ደግሞ
ተማሪዎች ከቀድሞዎቹ ስንኞች ጋር በሀሳብ
በሚሰጣችሁ ርዕስ ግጥም ትጽፋላችሁ። አንድ
የሚስማማ ስንኝ ጻፉ። የምትጽፉት ስንኝ
ምሳሌ ጽፌ ላሳያችሁ። "እናት" ከሚለው ርዕስ
የመጨረሻ ፊደል ከቀድሞዎቹ ስንኞች
ተነስቼ ግጥም እጽፋለሁ።" (የሚከተለውን
የመጨረሻ ፊደል ጋር ተመሳሳይ ወይም
አንድ ስንኝ ሰሌዳው ላይ ይጻፉ።)
የተለየ ሊሆን ይችላል።
እናትና ምድር ሁለቱ አንድ ናቸው፣
[ተ. ሦስተኛ ስንኝ ይጽፋሉ።]
መ. ይህን ጅምር ስንኝ ሊያሟላ የሚችል ስንኝ
መ. በጣም ጥሩ! ወረቀቱን ከጎናችሁ ላሉ
ምንድን ነው?
ተማሪዎች አስተላልፉ፣ ወረቀቱን የተቀበላችሁ
[መ. የልጃቸው ነገር ሁሌም ጉዳያቸው።] ተማሪዎች ከቀድሞዎቹ ስንኞች ጋር
(ከመጀመሪያው ስንኝ ሥር ይጻፉና በሀሳብ የሚስማማ ስንኝ ጻፉ። የምትጽፉት
ያንብቡላቸው።) ስንኝ የመጨረሻ ፊደል ከሦስተኛው ስንኝ
የመጨረሻ ፊደል ጋር ተመሳሳይ ቢሆን
እንሥራ የተሻለ ነው።
መ. ይህንን ስንኝ በሌላ ስንኝ ማሟላት ይቻላል።
[ተ. አራተኛ ስንኝ ይጽፋሉ]
"እናትና ምድር ሁለቱ አንድ ናቸው" የሚለውን
(መ. በዚህ ዓይነት ተማሪዎች ለ10 ደቂቃ
ስንኝ የሚያሟላ ሌላ ስንኝ ንገሩኝ።
ያህል በቡድን እየተቀባበሉ ከመረጡት
[መተ. እናትና ምድር ሁለቱ አንድ ናቸው፣ ርዕስ ተነስተው ግጥም እንዲጽፉ ያድርጉ።
ተማሪዎች ሲጽፉ እየተዘዋወሩ ተግባሩን

172 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፸፪


በአግባቡ እየሠሩ መሆናቸውን ይመልከቱ።
ተግባሩን ለመሥራት የተቸገሩ ቡድኖች ካሉ
ፍንጭ በመስጠት ይደግፉ።)
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ፖስታ ማዘጋጀትና አድራሻ መጻፍ
እንሥራ
መ. ዛሬ ፖስታ አዘጋጅተን አድራሻ እንጽፋለን።
አንድ ያልተጻፈበት ወረቀት እናዘጋጅ።
(እርስዎም ተማሪዎችም ወረቀት አዘጋጁ።)
[መተ. ለፖስታ መሥሪያ ወረቀት ያዘጋጃሉ።]
መ. አሁን የወረቀቱ አራቱም ማዕዘን እኩል
እንዲሆን አድርገን እንቁረጥ
ሥሩ
[መተ. ያዘጋጁትን ወረቀት አራቱም ማዕዘን መ. በጣም ጥሩ! ፖስታውን ለጓደኞቻችሁ
እኩል እንዲሆኑ አድርገው ይቆርጣሉ።] እንደምትልኩ አድርጋችሁ በፖስታው ጀርባ
መ. ወረቀቱ የሚታጠፍባቸውን መስመሮች የላኪና የተቀባይ አድራሻ ጻፉ።
እንደሚከተለው በእርሳስ ነጠብጣብ በማድረግ [ተ. በፖስታው ላይ የላኪና የተቀባይ አድራሻ
ምልክት እናድርግ። ይጽፉሉ።]
(መ. በፖስታው ላይ የላኪና የተቀባይ አድራሻ
ከጻፉ በኋላ ያዘጋጁትን ፖስታ እንዲቀያየሩ
ያድርጉ። ከዚያም እርስዎ ባዘጋጁት ፖስታ
ላይ የላኪና የተቀባይ አድራሻ ጽፈው
ያሳዩአቸውና ርስበርስ እንዲተራረሙ
ያድርጉ።)

6ኛ ቀን
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• አቀላጥፎ ማንበብ
• መናገር
[መተ. ወረቀቱ የሚታጠፍባቸውን መስመሮች • ሰዋስው
ምልክት ያደርጋሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ሦስቱን ጠርዞች እኩል የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
ወደመሀል ካጠፍን በኋላ በማጣበቂያ
እናያይዝ። የተሠራው ፖስታ የሚከተለውን ሥሩ
ይመስላል። መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ የሠራችሁትን
የቤትሥራ መልስ ንገሩኝ። "ሰካራሙ ሰውዬ
ጉድባ ውስጥ ገብቶ ተሰበረ" በሚለው
ዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረበትን ቃል
ሊተካ የሚችለው ከቀረቡት አማራጮች
ውስጥ የትኛው ነው?
[ተ. ጉድጓድ]

፻፸፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 173


( መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚህ ዓይነት አንብቡ። "1" ቍጥሮች ሲያነቡ፣ "2"
ያሠሩ።) ቍጥሮች ደግሞ ድምፃቸውን በተገቢው
ሁኔታ መቀያየራቸውን፣ ሥርዓተነጥብ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) መጠበቃቸውን ተከታተሉ። ከተሰጠው
መመሪያ ሲወጡ/ሲያፈነግጡ አስተያየት
ጌራና አሰቦ ስጧቸው።
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) [ተ. "1" ቍጥሮች ያነባሉ። "2" ቍጥሮች
ሥሩ ያዳምጣሉ፤ አስተያየት ይሠጣሉ።]
መ. ዛሬ በጥንድ የማንበብ ልምምድ መ. አሁን ደግሞ "2" ቍጥሮች አንብቡ። "1"
ታደርጋላችሁ። በመጀመሪያ ግን ቍጥሮች ደግሞ እየተከታተላችሁ አስተያየት
ስለምንባቡ ይዘት ለማስታወስ አንድ ጥያቄ ስጡ።
ልጠይቃችሁ። ከሁለቱ ወንድማማቾች
[ተ. "2" ቍጥሮች ያነባሉ። "1" ቍጥሮች
መሬቱን ስለሚከፋፈሉበት ዘዴ ሀሳብ
ያዳምጣሉ፤ አስተያየት ይሰጣሉ።]
ያፈለቀው ማን ነበር?
(መ. በዚህ ዓይነት ደግመው እንዲያነቡ ያድርጉ።
[ተ. አሰቦ]
ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ በተሰጠው
ማንበብ (8 ደቂቃ) መመሪያ መሠረት ማንበባቸውን ይከታተሉ።
ተግባሩን በትክክል ካልሠሩ አሠራሩን ግልፅ
ልሥራ
በማድረግ በትክክል እንዲሠሩ ያድርጉ።)
መ. ዛሬ የድምፅ ቅላፄን እንደአስፈላጊነቱ
እየቀያየሩ ሥርዓተነጥብን ጠብቆ የማንበብ
ልምምድ ታደርጋላችሁ፤ በመጀመሪያ ግን
መናገር (15 ደቂቃ)
"ጌራና አሰቦ" ከሚለው ምንባብ 2ኛውን እንቆቅልሽ መጫወት
አንቀጽ አነባለሁ። (በሚያነቡበት ጊዜ ሦስት
ዓይነት ድምፆችን መጠቀም እንዳለብዎት
ሥሩ
ልብ ይበሉ። አንዱ የተራኪው/ዋ ድምፅ፣ (መ. ተማሪዎችን 6 አባላት ባሏቸው ቡድኖች
ሁለተኛው የአሰቦ ድምፅ፣ ሦስተኛው ደግሞ ያደራጁ።)
የጌራ ድምፅ ነው። እርስዎም ሲያነቡ መ. ሁለት ሁለት እየሆናችሁ እንቆቅልሽ
የተራኪውን ድምፅ በራስዎ መደበኛ ድምፅ፣ ተጫወቱ። ሁለቱ ሲጫወቱ ሌሎቻችሁ
የአሰቦና የጌራን ድምፅ ደግሞ በሌሎች ሁለት በመዳኘት አሸናፊውን ለዩ። በዚህ ዓይነት
የተለያዩ ድምፆች ያንብቡ። በአንቀጹ ውስጥ ርስበርስ እየተወዳደራችሁ ከስድስታችሁ
ያሉትን ሥርዓተነጥቦች ጠብቀው በማንበብ አንድ አሸናፊ ምረጡ።
ያሳዩአቸው።)
[ተ. ርስበርስ እንቆቅልሽ በመጫወት
[መ. የድምፅ ቅላፄን እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየሩ ይወዳደራሉ።]
ሥርዓተነጥቦችን ጠብቀው ያነባሉ።]
(መ. ከየቡድኑ የተመረጡትን አሸናፊዎች
ሥሩ ርስበርስ እንዲወዳደሩ ያድርጉና የዕለቱን
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ፡- "1"ና "2" የእንቆቅልሽ ጨዋታ አሸናፊ ይለዩ።
በማለት ቍጥር ይስጡ።) አሸናፊውን ያበረታቱ። የክፍሉ ተማሪዎች
እንዲያጨበጭቡለት ያድርጉ።)
መ. "1" ቍጥሮች "ጌራና አሰቦ" ከሚለው
ምንባብ የመጀመሪያዎቹን ሦስት አንቀጾች
አንብቡ። በምታነቡበት ጊዜ የድምፃችሁን ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ቅላፄ እንደአስፈላጊነቱ እየቀያየራችሁ፣ ባለቤትና ግሳዊ ሐረግን መለየት
ሥርዓተነጥቦችን ጠብቃችሁ አንብቡ።
የተራኪውን ድምፅ በራሳችሁ መደበኛ ድምፅ፣ ልሥራ
የአሰቦንና የጌራን ድምፅ ደግሞ በሌሎች መ. ዛሬ በዓረፍተነገር ውስጥ የሚገኙ
ሁለት የተለያዩ ድምፆች እየቀያየራችሁ ባለቤትና ግሳዊ ሐረጎችን የመለየት ተግባር

174 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፸፬


ትሠራላችሁ። በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ (መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚህ ዓይነት
እኔ እሠራለሁ። በደብተራቸው ጽፈው እንዲመልሱ ያድርጉ።
ከዚያም ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ ያድርጉ።
ጌራና አሰቦ ጓሳውን ተመለከቱ። (ይህን
በመቀጠልም በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር
ዓረፍተነገር ሰሌዳው ላይ ይጻፉ።)
ይወያዩ። ተማሪዎች ርስበርስ እንዲተራረሙ
መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ የዓረፍተነገሩ ያድርጉ።)
ባለቤት የትኛው ነው?
[መ. ጌራና አሰቦ]
መ. ጌራና አሰቦ ምን አደረጉ።?
[መ. ጓሳውን ተመለከቱ።]
መ. ስለዚህ "ጌራና አሰቦ" የዓረፍተነገሩ ባለቤት
ሲሆኑ፣ "ጓሳውን ተመለከቱ" የሚለው ደግሞ
ግሳዊ ሐረግ ነው። ስለዚህ "አሰቦ"ና "ጓሳውን"
በሚሉት ቃላት መካከል እዝባር(/) በማድረግ
ባለቤቱንና ግሳዊ ሐረጉን እለያለሁ።
[መ. ጌራና አሰቦ/ ጓሳውን ተመለከቱ።] (በዚህ
መልኩ ሰሌዳው ላይ በጻፉት ዓረፍተነገር
ውስጥ ምልክት ያድርጉ።)
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። "አሰቦ ሀሳብ
አቀረበ" በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ባለቤቱ
የትኛው ነው?
[መተ. አሰቦ]
መ. አሰቦ ምን አደረገ?
[መተ. ሀሳብ አቀረበ]
መ. በጣም ጥሩ! ግሳዊ ሐረጉስ የትኛው ነው?
[መተ. ሀሳብ አቀረበ]
መ. በባለቤቱና በግሳዊ ሐረጉ መካከል እዝባር (/)
እናድርግ። (ተማሪዎች ሰሌዳው ላይ በጻፉት
ዓረፍተነገር ውስጥ ምልክት እንዲያደርጉ
ይፍቀዱላቸው።)
[መተ. አስቦ/ ሀሳብ አቀረበ።]
ሥሩ
መ. በ2ኛው ሳምንት፤ በ6ኛው ቀን፣ በሰዋስው
ሥር የቀረቡትን ዓረፍተነገሮች በደብተራችሁ
ጻፉ። ከዚያም በዓረፍተነገሮች ውስጥ ያሉትን
ባለቤቶችና ግሳዊ ሐረጎች እዝባር(/) በማድረግ
ለዩ። "ስመኝ ጥቁሩን ቦራ ፈረስ ሸጠችው።"
በሚለው ዓረፍተነገር ውስጥ ያሉትን ባለቤትና
ግሳዊ ሐረግ እዝባር(/) በማድረግ ለዩ።
[ተ. ስመኝ/ ጥቁሩን ቦራ ፈረስ ሸጠችው።]

፻፸፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 175


ሥሩ
3ኛ ሳምንት መ. አሁን ደግሞ እናንተ የምታውቋቸውን
የባህል ተስተላልፎና የቃላዊ ምሳሌያዊ ንግግሮች ንገሩኝ።
ልማዶች ጠቀሜታ [ተ. የሚያውቋቸውን ምሳሌያዊ ንግግሮች
ይናገራሉ።]
የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
7ኛ ቀን
ሥሩ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መ. "የምሳሌያዊ ንግግሮች ፋይዳ" በሚል ርዕስ
• የቃላት ጥናት የቀረበውን ምንባብ ራሳችሁን እየጠየቃችሁና
• ማንበብ ለጥያቄዎቻችሁ መልስ እያሰባችሁ አንብቡ።
[ተ. እየጠየቁና ከምንባቡ መልስ እየፈለጉ
ያነባሉ።]
የቃላት ጥናት (3 ደቂቃ)
አንብቦ መረዳት (22 ደቂቃ)
መነጠልና ማጣመር
ሥሩ
ሥሩ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን፣ በቃላት በአንብቦ መረዳት ሥር የቀረቡትን የተግባር
ጥናት ሥር የቀረቡትን ከምንባብ የወጡ 1 ጥያቄዎች መልሱ።
ውስብስብ ቃላትን በመነጣጠልና በማጣመር
አንብቡ። "ቅሬታቸውን" የሚለውን ቃል መ. ምሳሌያዊ ንግግሮች ለምን ይጠቅማሉ?
ነጣጥላችሁ አንብቡ። [ተ. ምሳሌያዊ ንግግሮች በጥቅሉ ሀሳብን
[ተ. ቅሬታ-ኣቸው--ን] ለመቋጨት፣ ለማጠናከርና ለማጉላት
ይጠቅማሉ።] (ሌሎቹንም በዚህ ዓይነት
መ. በጣም ጥሩ! ይህንኑ ቃል በማጣመር እንዲሠሩ ያድርጉ።)
አንብቡ።
መ. አሁን ደግሞ በተግባር “2” ሥር የቀረቡትን
[ተ. ቅሬታቸውን] የተጓደሉ ምሳሌያዊ ንግግሮች በተለመደው
(መ. የቀሩትንም ቃላት በዚሁ ዓይነት ያስነብቡ።) መንገድ የሚያሟሉ አባባሎች ከቀረቡት
አማራጮች ምረጡ። "ፈሪና ንፉግ
ማንበብ (37 ደቂቃ) -------------" የሚለውን ምሳሌያዊ ንግግር
የምሳሌያዊ ንግግሮች ፋይዳ የሚያሟላው የትኛው ነው?

ቅደመንባብ (5 ደቂቃ) [ተ. እያደር ይቆጫሉ።]


መ. ይህ ምሳሌያዊ ንግግር ከምንባቡ ውስጥ
የቀደመ ዕውቀትን መቀስቀስ
ከተጠቀሱት ምድቦች በየትኛው ይካተታል?
ልሥራ
[ተ. በ3ኛውና በ4ኛው ተራ ቍጥር በቀረቡት
መ. ሰዎች ሀሳባቸውን ለማጉላትና ለማጠናከር
ምድቦች ውስጥ ሊካተት ይችላል።]
በንግግራቸውና በጽሑፋቸው ውስጥ ምሳሌያዊ
ንግግሮችን ይጠቀማሉ። ከማውቃቸው (መ. የቀሩትንም በዚሁ ዓይነት ያሠሩ። ከዚያም
ምሳሌያዊ ንግግሮች መካከል ጥቂት ደብተራቸውን አቀያይረው መልሶቹን
ልንገራችሁ። በመንገር እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
[መ. ካንድ ብርቱ፣ ሁለት መድሃኒቱ። መ. ያበረ ወገኑን -----------------------
•ታሞ ከመማቀቅ፣ አስቀድሞ መጠንቀቅ። [ተ. አስከበረ]
•መጠየቅ፣ ያደርጋል ሊቅ።] መ. በምንባቡ ከተጠቀሱት ምድቦች በየትኛው

176 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፸፮


ይካተታል? ምንባብ ለወጡ ቃላት ዐውዳዊ ፍቻቸውን
በደብተራችሁ ጻፉ።
[ተ. በተራ ቁጥር 6 ይመደባል]
መ. "መቋጫ" የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ
መ. ለተራበ ቂጣ፣ -----
ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
[ተ. ለተጠማ ዋንጫ]
[ተ. መደምደሚያ]
መ. በምንባቡ ከተጠቀሱት ምድቦች በትኛው
(መ. በዚህ ዓይነት የቃላትን ዐውዳዊ ፍቺ
ይካተታል?
በደብተራቸው እንዲጽፉ፣ ከዚያም
[ተ. በተራ ቁጥር 2 ይመደባል] ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ
መ. የቆጡን አወርድ ብላ ---------------- እንዲተራረሙ ያድርጉ። በመጨረሻም
ትክክለኛውን መልስ በመንገር ግብረመልስ
[ተ. የብብቷን ጣለች] ይስጡ።)
መ. በምንባቡ ከተጠቀሱት ምድቦች በየትኛው መ. አሁን ደግሞ ተግባር "2"ን ሥሩ። በ"ሀ"
ይካተታል ? ረድፍ ለተዘረዘሩት ቃላት ተቃራኒ ፍቻቸውን
[ተ. በተራ ቁጥር 3 ይመደባል] ከ"ለ" ረድፍ በመምረጥ አዛምዱ። "አስነዋሪ"
ለሚለው ቃል በ"ለ" ረድፍ ከተዘረዘሩት
መ. ጋን በጠጠር ---------------። ተቃራኒው የትኛው ነው?
[ተ. ይደገፋል] [ተ. አኩሪ]
መ. በምንባቡ ከተጠቀሱት ምድቦች በየትኛው (መ. በዚህ ዓይነት የቀሩትንም እንዲሠሩ
ይካተታል? ያድርጉ። ከዚያም መልሶቹን እርስዎ
[ተ. በተራ ቁጥር 6 ይመደባል] በመንገር ራሳቸው የራሳቸውን ደብተር
እንዲያርሙ ያድርጉ።)
መ. ሰነፍ ተቀምጦ ተቀምጦ -----።
[ተ. ከብት ሲገባ ይሠራል።] መጻፍ (30 ደቂቃ)
መ. በምንባቡ ከተጠቀሱት ምድቦች በየትኛው ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
ይካተታል?
ግጥም አስተካክሎ መጻፍ
[ተ. በተራ ቁጥር 1 ይመደባል።]
ልሥራ
(መ. አንድ ምሳሌያዊ ንግግር እንደሁኔታው መ. ባለፈው ክፍለጊዜ በቡድን ሆናችሁ ግጥም
ከአንድ በላይ ምድብ ውስጥ ሊካተትም ጽፋችሁ ነበር። ዛሬ ደግሞ የጻፋችሁትን
ይችላል።) ግጥም አስተካክላችሁ ትጽፋላችሁ። በቅድሚያ
ግን ግጥማችሁን እንዴት እንደምታስተካክሉ
8ኛ ቀን እኔ ሠርቼ ላሳያችሁ። (የሚከተለውን ግጥም
ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች የፍቅር አዝመራ ዛሬ ከተዘራ፣
• ቃላት
ሰው ለሰው አስቦ ፈጣሪን ከፈራ፣
• መጻፍ
ለዕውቀት ከተጋ በርትቶ ካጠና፣
ለኔ ማለት ትተን በጋራ ብንሠራ፣
ቃላት(10 ደቂቃ)
ባልተኛ ካቧራ ሰው ባልተሰቃየ።
ለቃላት ዐውዳዊና ተቃራኒ ፍቺ መስጠት
መ. በዚህ ግጥም ውስጥ ሁለት ችግሮች አሉ።
ሥሩ አንደኛው ችግር የሀሳብ አንድነት አለመኖር
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን፣ በቃላት ነው። የግጥሙ አጠቃላይ ጭብጥ ፍቅርና
ሥር "የምሳሌያዊ ንግግሮች" ፋይዳ ከሚለው

፻፸፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 177


መተሳሰብ ነው። ሦስተኛው ስንኝ ግን ከሌሎቹ [ተ. የሠላምታ ደብዳቤ ይጽፋሉ።]
ስንኞች በተለይ ስለዕውቀትና ስለማጥናት
መ. አሁን ባለፈው ክፍለጊዜ በተማራችሁት
ያወሳል። ስለዚህ ይህን ስንኝ እሠርዘዋለሁ።
መሠረት ፖስታ አዘጋጁና የላኪና የተቀባይ
[መ. ሦስተኛውን ስንኝ ይሠርዛሉ።] አድራሻ ጻፉ።
መ. ሌላው ችግር የአምስተኛው ስንኝ የመጨረሻ [ተ. ፖስታ አዘጋጅተው አድራሻ ይጽፋሉ።]
ፊደል የተለየ ስለሆነ ቤት አይመታም። ስለዚህ
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ የጻፋችሁትን
የሐረጋቱን ቦታ በማቀያየር ቤት እንዲመታ
ደብዳቤ በፖስታው ውስጥ አስገብታችሁ
አደርጋለሁ። (ግጥሙን እንደሚከተለው
አሽጉት።
አስተካክለው ያሳዩ።)
[ተ. የጻፉትን ደብዳቤ በፖስታ ውስጥ አስገብተው
[መ. የፍቅር አዝመራ ዛሬ ከተዘራ፣
ያሽጋሉ።]
ሰው ለሰው አስቦ ፈጣሪን ከፈራ፣
(መ. በመጨረሻ ፖስታዎቹን ሰብስበው
ለኔ ማለት ትተን በጋራ ብንሠራ፣ ለባለአድራሻዎቹ ከሰጡ በኋላ በተማሩት
መሠረት የተጻፈ መሆኑን እንዲገመግሙ
ሰው ባልተሰቃየ ባልተኛ ካቧራ።]
ያበረታቷቸው፤ እርስዎም በትክክል መሥራት
ሥሩ አለመሥራታቸውን ይገምግሙ።)
(መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ።)
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ በቡድን የጻፋችሁትን 9ኛ ቀን
ግጥም ገምግሙ። ግጥማችሁን ስትገመግሙ፣
ግጥሙ ቤት ይመታል? ግጥሙ የሀሳብ የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
አንድነት አለው? በሚሉት ጥያቄዎች ላይ • አቀላጥፎ ማንበብ
ትኵረት አድርጉ።
• መናገር
[ተ. ግጥማቸውን ይገመግማሉ።]
• ሰዋስው
መ. አሁን ግጥማችሁ ቤት እንዲመታና የሀሳብ
አንድነት እንዲኖረው አድርጋችሁ ጻፉ።
[ተ. ግጥማቸውን አስተካክለው ይጽፋሉ።] አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
መ. ከየቡድኑ አንድ አንድ ተማሪዎች በጋራ የምሳሌያዊ ንግግሮች ፋይዳ
የጻፋችሁትን ግጥም ለክፍሉ ተማሪዎች
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ)
አንብቡ።
ሥሩ
[ተ. የጻፉትን ግጥም ለክፍሉ ተማሪዎች ያነባሉ።]
መ. ዛሬ በጋራ የማንበብ ልምምድ ታደርጋላችሁ።
(መ. በመጨረሻም በግጥሞቹ ላይ አስተያየት በመጀመሪያ ግን ባለፈው ክፍለጊዜ
እንዲሠጡ ያድርጉ። የእርስዎንም አስተያየት ያነበባችሁትን ምንባብ ይዘት በተመለከተ
በማከል ያጠቃሉ።) አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ። የምሳሌያዊ
ንግግሮችን ጠቀሜታ ዘርዝሩ።
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
[ተ. ያነበቡትን በማስታወስ የምሳሌያዊ
የሠላምታ ደብዳቤ ጽፎ በፖስታ መላክ
ንግግሮችን ጠቀሜታ ይዘረዝራሉ።]
ሥሩ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለፖስታ አዘገጃጀትና
ማንበብ (8 ደቂቃ)
አድራሻ አጻጻፍ ተምራችኋል። ዛሬ ደግሞ ሥሩ
የሠላምታ ደብዳቤ ጽፋችሁ በፖስታ (መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ።)
አሽጋችሁ ትልካላችሁ። በመጀመሪያ ለአንድ
መ. "የምሳሌያዊ ንግግሮች ፋይዳ" በሚል
የክፍል ጓደኛችሁ የሠላምታ ደብዳቤ ጻፉ።
ርዕስ የቀረበውን ምንባብ በቡድን ሆናችሁ

178 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 ፻፸፰


ድምፅ በማሰማት በጋራ አንብቡ። ስታነቡ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ሥርዓተነጥቦችን ጠብቁ፤ ድምፃችሁንም
እኩል ለማውጣት ሞክሩ። ዓረፍተነገር በመሥራት ግሳዊ ሐረግ
መለየት
[ተ. ድምፅ እያሰሙ በጋራ ያነባሉ።]
ልሥራ
(መ. በምዕራፍ 4፣ በመምህር መምሪያ፣ በአቀላጥፎ
መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት ግሳዊ ሐረግን
ማንበብ፣ “ሥሩ” በሚለው ሥር ያለውን
መለየት ተምራችኋል። ዛሬ ደግሞ ግሶችን
አሠራር በመመልከት በዚያው መሠረት
በመጠቀም ዓረፍተነገር ሠርታችሁ ግሳዊ
ያሠሩ። ተማሪዎች ሲያነቡ ሥርዓተነጥቦችን
ሐረግን ትለያላችሁ። በመጀመሪያ ግን
ጠብቀው ድምፃቸውን እኩል እያወጡ፣
"ቀዳ" የሚለውን ግስ በመጠቀም ዓረፍተነገር
ቃላቱን ሳያሳስቱ ማንበባቸውን ይከታተሉ።)
እመሠርታለሁ።

መናገር (20 ደቂቃ) [መ. የወይዘሮ ሐረግ ልጅ ከወንዝ ውኃ ቀዳ።]

ምሳሌያዊ ንግግሮች የሚነገሩበትን [መ. በዚህ ዓረፍተነገር ውስጥ "ከወንዝ ውኃ ቀዳ"


ዐውድ መናገር የሚለው ግሳዊ ሐረግ ነው።]

ልሥራ እንሥራ
መ. አሁን ልዩ ልዩ ምሳሌያዊ ንግግሮች መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። "ተሰደዱ"
የሚነገሩበትን ዐውድ/አጋጣሚ ትናገራላችሁ። የሚለውን ቃል ተጠቅመን ዓረፍተነገር
በመጀመሪያ ግን አንድ ምሳሌ እሰጣለሁ። እንሥራ።

ሰዎች ቀድሞ ካጋጠማቸው የባሰ ወይም


[መተ. በርካታ የዱር እንስሳት ደኑ ስለተመነጠረ
የበለጠ ችግር ሲያጋጥማቸው ወይም በሌሎች ተሰደዱ።]
ላይ ሲመለከቱ "የባሰ አለ አገርህን አትልቀቅ" መ. በጣም ጥሩ! ግሳዊ ሐረጉን ከባለቤቱ በመለየት
የሚለውን ምሳሌያዊ አነጋገር ይጠቀማሉ። እዝባር(/) ተጠቅመን እንለይ?
ለምሳሌ አንድ ሠራተኛ መጀመሪያ ይሠራበት
የነበረው ድርጅት ሥራው እጅግ ብዙ በመሆኑ [መተ. በርካታ የዱር እንስሳት/ደኑ ስለተመነጠረ
ሰለቸው። ከዚህ የተነሳ ሥራውን ለቆ በሌላ ተሰደዱ።]
ድርጅት ተቀጠረ። አዲስ በተቀጠረበት ድርጅት
ውስጥ የገጠመው ሁኔታ ግን የባሰ መጥፎ ነበር።
ሥሩ
ሥራው ከመብዛቱ በተጨማሪ የአሠሪዎቹ ባህርይ መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን፣
አስቸጋሪ ሆነበት። ይህ ሁኔታ ያጋጠመው በስዋሰው ሥር የቀረቡትን ግሶች በመጠቀም
ሠራተኛ "የባሰ አለ አገርህን አትልቀቅ" ሊል ዓረፍተነገር መሥርቱ።
ይችላል።
መ. "ጠገነ" የሚለውን ቃል በመጠቀም
ሥሩ ዓረፍተነገር ሥሩ።
(መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ።)
[ተ. "ጠገነ" በሚለው ቃል በደብተራቸው
መ. በ3ኛው ሳምንት፣ በ9ኛው ቀን፣ በመናገር ዓረፍተነገር ይጽፋሉ። ከዚያም ግሳዊ ሐረጉን
ሥር የቀረቡት ምሳሌያዊ ንግግሮች ሊነገሩ በእዝባር ለይተው ያመለክታሉ።]
የሚችሉበትን ዐውድ/አጋጣሚ በምሳሌ
(መ. በዚህ ዓይነት የቀሩትንም በራሳቸው
በማስደገፍ ለቡድን ጓደኞቻችሁ ተናገሩ።
እንዲሠሩ ያድርጉ። ተማሪዎች የሠሯቸውን
[ተ. በመጽሐፋቸው የተዘረዘሩት ምሳሌያዊ ዓረፍተነገሮች ይመልከቱ፣ በየግሶቹ ግሳዊ
ንግግሮች ስለሚነገሩበት ዐውድ/አጋጣሚ ሐረግ መመሥረታቸውን ያረጋግጡ። ስህተት
ለጓደኞቻቸው ይናገራሉ።] ባለባቸው ዓረፍተነገሮች ላይ ተማሪዎችን
(መ. ተማሪዎች ሲናገሩ በየቡድኑ እየተዘዋወሩ እያሳተፉ በማስተካከል ግብረመልስ ይስጡ።)
ይከታተሉ። የሚያቀርቡት ዐውድ ለምሳሌያዊ
ንግግሩ የሚስማማ መሆኑን ይገምግሙ።)

፻፸፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 9 179


ምዕራፍ 10 ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፤ መድሎና መገለል
የምዕራፉ ዓላማዎች
ከዚህ ምዕራፍ ትምህርት በኋላ ተማሪዎች፡-
• ውስብስብ ቃላትንና ሐረጋትን በመነጠልና በማጣመር ያነባሉ፤
• "ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፤ መድሎና መገለል" በሚል የምንባብ ይዘት ሥር የቀረቡትን ምንባቦች
አንብበው የተረዱትን ይገልጻሉ፤
• አዳዲስ ቃላትን በንግግርና በጽሑፍ ይጠቀማሉ፤
• በምክንያትና ውጤት ስልት ድርሰት ይጽፋሉ፤
• የማመልከቻ ደብዳቤ ይጽፋሉ፤
• በምክንያትና ውጤት የተዋቀሩ ምንባቦችን አቀላጥፈው ያነባሉ፤
• "የበቀል ጥንስስ" በሚል ርዕስ የቀረበውን ምንባብ አዳምጠው የተረዱትን ይናገራሉ፤
• "ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፤ መድሎና መገለል" በሚል የምንባብ ይዘት መነሻነት ይናገራሉ፤
• አወንታና አሉታ ሐተታዊ ዓረፍተነገሮችን ይመሠርታሉ።

መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ ይህንኑ ሐረግ


1ኛ ሳምንት ኤች.አይ.ቪ/ በማጣመር አንብቡ።
ኤድስ፤ የመድሎና የመገለል [ተ. የተከታተሉት]
ተጽእኖዎች (መ. የቀሩትንም በዚሁ ዓይነት እንዲያነቡ
ያድርጉ።)
1ኛ ቀን
ማንበብ (35 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
ወይኔ ሰውዬው!
• የቃላት ጥናት
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
• ማንበብ
መገመት
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ) ሥሩ
መ. ምንባቡን ከማንበባችሁ በፊት የቅድመንባብ
መነጠልና ማጣመር ጥያቄዎችን መልሱ።
ሥሩ "ወይኔ ሰውዬው!" የሚለው አገላለጽ ምንን
መ. ዛሬ "ወይኔ ሰውዬው!" በሚል ርዕስ የቀረበ ያመለክታል?
ምንባብ ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን
በ1ኛው ሳምንት በቃላት ጥናት ሥር [ተ. የቁጭት፣ የፀፀት፣ ወዘተ. ስሜትን
የቀረቡትን ውስብስብ ቃላትና ሐረጋት ያመለክታል።]
በመነጣጠልና በማጣመር አንብቡ። (መ. የቀረውንም ጥያቄ በዚህ ዓይነት እንዲመልሱ
መ. "የተከታተሉት" የሚለውን ሐረግ በመነጣጠል ያድርጉ።)
አንብቡ።
[ተ. የ-ተከታተሉ-ት]

180 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፹


የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ) ማንበባችሁን ቀጥሉ።

መገመትና ግምትን ማረጋገጥ [ተ. ግምታቸውን እያረጋገጡ ያነባሉ።]


ሥሩ (መ. አንብበው እንደጨረሱ በጥንድ በጥንድ ሆነው
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ።) በግምታቸው ትክክለኛነት ላይ እንዲነጋገሩ
ያድርጉ።)
መ. በቅደመንባብ ጥያቄዎች ላይ የገመታችሁት
ትክክል መሆኑን ወይም አለመሆኑን አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)
እያረጋገጣችሁ በግል ድምፅ ሳታሰሙ ሥሩ
አንብቡ።
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ1ኛው ቀን፣ በአንብቦ
(መ. የመጀመሪያውን አንቀጽ ብቻ አንብበው መረዳት፣ በተግባር “1” ሥር የቀረበውን
መጽሐፋቸውን እንዲያጥፉ ያድርጉና ቀጥሎ ተግባር ሥሩ። በመጀመሪያ በመጽሐፋችሁ
የቀረበውን ጥያቄ ይጠይቁ።) የቀረበውን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
አዘጋጁ። ከዚያም ባነበባችሁት ምንባብ
መ. በሰውዬው ወይም በቤተሰቡ ላይ ምን
ውስጥ በመጀመሪያ፣ በመካከልና በመጨረሻ
የሚደርስ ይመስላችኋል?
የተከናወኑትን ድርጊቶች በቅደምተከተል
[ተ. በጥንድ በጥንድ ሆነው ግምታቸውን ዘርዝሩ።
አንዳቸው ለሌላቸው ይናገራሉ።]
መ. በምንባቡ መሠረት በመጀመሪያ የተከናወነው
(መ. ለ1 ደቂቃ ያህል ከተነጋገሩ በኋላ ድርጊት ምን ነበር?
ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)
[ተ. ሰውዬው በየቀኑ እየሰከረ አምሽቶ ከመግባት
መ. አሁን ማንበባችሁን ቀጥሉ፤ ስታነቡ አልፎ ውጪ ማደር ጀመረ።] (ተማሪዎች
ግምታችሁ ትክክል መሆኑን ወይም በራሳቸው መንገድ መግለጽ ይችላሉ።)
አለመሆኑን አረጋግጡ።
መ. በጣም ጥሩ! አሁን የተናገራችሁትን
[ተ. በግምታቸው ትክክል መሆኑን/አለመሆኑን ባዘጋጃችሁት ሠንጠረዥ "መጀመሪያ"
እያረጋገጡ ያነባሉ።] በሚለው ክፍል ውስጥ ጻፉ። (የቀሩትንም በዚህ
(መ. እስከሦስተኛው አንቀጽ ብቻ አንብበው ዓይነት በግል እንዲሠሩ ያድርጉ። ከዚያም
እንዲያቆሙ ያድርጉ።) የሠሩትን በቡድን እየተወያዩ እንዲያስተካክሉ
ያድርጉ። እርስዎም ተማሪዎች የሠሩትን
መ. የማንኛችሁ ግምት ትክክል ነበር? በማየት ተገቢውን ማስተካከያ ይስጡ።)
ግምታችሁን ካነበባችሁት ጋር በማገናዘብ
መ. አሁን ደግሞ የተግባር "2"ን ጥያቄዎች
ተነጋገሩ።
በቃላችሁ መልሱ። ሰውዬው በዘመድና
[ተ. ግምታቸው ትክክል መሆን/አለመሆን ላይ በሽማግሌ ከተመከረ በኋላ ያመጣው የባህርይ
ይነጋገራሉ።] ለውጥ ምንድን ነው?
(መ. ለ1 ደቂቃ ያህል ከተነጋገሩ በኋላ [ተ. ምንም ዓይነት የባህርይ ለውጥ አላመጣም፤
የመጨረሻውን አንቀጽ የመጀመሪያ ሁለት እንዲያውም ብሶበታል።]
ዓረፍተነገሮች ብቻ አንብበው መጽሐፋቸውን
እንዲያጥፉ ያድርጉ።) (መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚህ ዓይነት
በቃላቸው እንዲመልሱ ያድርጉ። በትክክል
መ. ሰውዬውና ቤተሰቡ የገጠማቸው ችግር ምን ላልተመለሱ ጥያቄዎች ትክክለኛውን መልስ
ይመስላችኋል? በመንገር ግብረመልስ ይስጡ።)
[ተ. በጥንድ በጥንድ ሆነው ግምታቸውን
አንዳቸው ለሌላቸው ይናገራሉ።]
(መ. ለ1 ደቂቃ ያህል ከተነጋገሩ በኋላ
ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ።)
መ. አሁንም ግምታችሁን እያረጋገጣችሁ

፻፹፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 181


[ተ. ምክር አልተቀበለም]
2ኛ ቀን መ. በጣም ጥሩ! (የቀሩትንም በዚህ ዓይነት
እንዲሠሩ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• ቃላት መጻፍ (30 ደቂቃ)
• መጻፍ ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
በምንባብ ውስጥ የሚገኝን ምክንያትና
ውጤት መተንተን
ቃላት (10 ደቂቃ)
ልሥራ
የተለየ ፍቺ ያለውን ቃል መለየትና መ. አንድ ምክንያት አንዳች ውጤትን
ለፈሊጣዊ ንግግሮች ፍቺ መስጠት። ያስከትላል። በመጀመሪያው ምክንያት
ሥሩ የተከሰተው ውጤት ለሌላ ውጤት መከሰት
ምክንያት ሊሆን ይችላል። ይህን በአንድ
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በተግባር “1”
ምሳሌ እንመልከት።
ሥር የቀረበውን የቃላት ተግባር ሥሩ። ቀጥሎ
ለቀረቡት ቃላት ከተዘረዘሩት አማራጮች ወቅቱ ክረምት ቢሆንም በዕለቱ ሰማዩ ብሩህ
መካከል በፍቺ የተለየውን በደብተራችሁ በመሆኑ ጥላ ሳትይዝ ከቤቷ ወጣች። ነገርግን
ጻፉ። ድንገት ዝናብ መጣል ጀመረ። በዚህ የተነሳ
ልብሷ ራሰ። እንደዚህ ሆና ለፈተናው መቅረብ
መ. በ"1"ኛ ተራቍጥር "ሲያሰኘው" ለሚለው
ስላልፈለገች ወደቤቷ ተመልሳ ልብሷን ቀይራ፣
ቃል ከቀረቡት አማራጮች መካከል በፍቺ ጃንጥላ ይዛ ወጣች። በዚህም ምክንያት
የተለየው የትኛው ነው? ወደፈተናው የገባችው 30 ደቂቃ ዘግይታ ነበር።
[ተ. ሲያምረው] መ. አሁን ባነበብኩላችሁ አንቀጽ ውስጥ ያሉትን
ምክንያቶችና ውጤቶች በቢጋር ሠንጠረዥ
መ. በጣም ጥሩ! (በዚህ ዓይነት ሌሎችንም
እተነትናለሁ።(የሚከተለውን የቢጋር
ጥያቄዎች እንዲመልሱ ያድርጉ፤ ከዚያም
ሠንጠረዥ ሰሌዳው ላይ ያዘጋጁ።)
በመልሶቹ ላይ ከተማሪዎች ጋር እየተወያዩ
ግበረመልስ ይስጡ።)
ምክንያት

ምክንያት

ምክንያት
ሰማዩ ጥላ በጣለው
ውጤት

ውጤት

ሳትይዝ ዝናብ
ልሥራ ብሩህ
ነበር ወጣች ልብሷ ራሰ

መ. በተግባር "2" ሥር ከምንባቡ የወጡ ፈሊጣዊ


ንግግሮች ቀርበዋል። ፈሊጣዊ አነጋገር ከፈተናው
ምክንያት

ልብስ ለመቀየርና
ቃላት ከዘወትራዊ ፍቻቸው የተለየ ፍቺ
ውጤት

ውጤት

ጃንጥላ ለመያዝ ጊዜ 30
ወደቤቷ ተመለሰች ደቂቃ
እንዲኖራቸው አድርገን የምንጠቀምበት ዘገየች
የአነጋገር ስልት ነው። ለምሳሌ በምንባቡ
ውስጥ "ቀን ሲሠራ ውሎ ማታ ጠላና አረቄ
መ. ጥላ ሳትይዝ መውጣቷ ሰማዩ ብሩህ በመሆኑ
ጠጥቶ ሞቅ ብሎት ወደቤቱ ይገባል።" የሚል
ምክንያት የተከሰተ ውጤት ነው። በሌላ በኩል
ዓረፍተነገር አለ። "ሞቅ ብሎት" የሚለው
ጥላ ሳትይዝ መውጣቷ ለልብሷ በዝናብ መራስ
ሐረግ ፈላጣዊ ንግግር ነው። ፍቹም ሰክሮ
ምክንያት ሆኗል። (በዚህ ዓይነት በቢጋር
ማለት ነው።
ሠንጠረዡ የተዘረዘረውን የምክንያትና
ሥሩ ውጤት ትስሥር ይተንትኑላቸው።)
መ. አሁን በተግባር "2" ሥር ለቀረቡት የፈሊጣዊ ሥሩ
ንግግሮች ፍቺ ትሰጣላችሁ።
መ. አሁን ልክ እኔ እንዳደረግሁት እናንተም
መ. "ጆሮ አልሰጠም" የሚለው ፈሊጣዊ ንግግር "ወይኔ ሰውዬው!" በሚል ርዕስ በቀረበው
ፍቺ ምንድን ነው? (ተማሪዎች በፍቹ ላይ ምንባብ ውስጥ ያለውን የምክንያትና ውጤት
እንዲወያዩ ያድርጉና መልሱን ይቀበሉ።) ትስሥር የቢጋር ሠንጠረዥ አዘጋጅታችሁ

182 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፹፪


በቡድን ተንትኑ። [መተ. የአመልካች ስም፤ አመልካቹ የሚገኝበት
ልዩ ቦታ፣ ስልክ ቍጥርና ከተማ]
[ተ. በምንባቡ ውስጥ ያሉ ምክንያቶችንና
ውጤቶችን በቡድን ይተነትናሉ።] ሥሩ
(መ. ተማሪዎች ሲሠሩ እየተዘዋወሩ ተግባሩን መ. አሁን እስካሁን በሠራነው መሠረት
በትክክል መሥራታቸውን ይከታተሉ። በመጽሐፋችሁ የሚገኘውን የማመልከቻ
ተግባሩን በትክክል ለመሥራት የተቸገሩትን ደብዳቤ መነሻ በማድረግ በጽሑፍ
በመጠየቅና ፍንጭ በመስጠት ይደግፉ። ትመልሳላችሁ። (በልሥራና እንሥራ
በመጨረሻም እያንዳንዱ ቡድን የሠራውን የተሠራውን በደብተራቸው እንዲጽፉ
የምክንያትና ውጤት ትንታኔ እንዲያቀርብ በማድረግ ይጀምሩና ቀጥሎ ያለውን ጥያቄ
ያድርጉ። የመድሎንና መገለልን ምንነት፣ ይጠይቋቸው።)
መንስኤውንና ውጤቱን በተመለከተ መ. አመልካቹ ከሚገኝበት/ከተማ ዝቅ ብሎ ምን
ወላጆቻቸውን፣ መምህሮቻቸውን፣ የጤና ይጻፋል?
ባለሙያዎችን ጠይቀው ወይም መጽሐፍ
አንብበው ማስታወሻ ይዘው እንዲመጡ [ተ. ጉዳዩ ]
ይንገሯቸው።) መ. በጣም ጥሩ! "ጉዳዩ" በማመልከቻው ሊገለጽ
የተፈለገው መልዕክት ባጭሩ የሚጠቆምበት
የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
ነው።
የማመልከቻ ደብዳቤ አጻጻፍ
መ. ከጉዳዩ ቀጥሎስ ምን ይጻፋል?
ልሥራ
[ተ. በማመልከቻ ደብዳቤው ሊገለጽ የተፈለገው
መ. በምዕራፍ 8 ስለሠላምታ ደብዳቤ
ዝርዝር ሀሳብ (ሐተታ) በዝርዝር ይቀርባል።]
አጻጻፍ ተምራችሁ ነበር። በዚህ ምዕራፍ
ደግሞ ስለማመልከቻ ደብዳቤ አጻጻፍ መ. በጣም ጥሩ! ከሐተታው ሥር በስተቀኝ በኩል
ትማራላችሁ። የማመልከቻ ደብዳቤ የራሱ ምን ይሠፍራል?
የሆነ የአጻጻፍ ሥርዓት አለው። ይህንንም [ተ. መውጫና የአመልካች ፊርማ]
የአጻጻፍ ሥርዓት በመጽሐፋችሁ የቀረበውን
የማመልከቻ ደብዳቤ ናሙና መነሻ በማድረግ መ. በጣም ጥሩ! ከፊርማው ሥር ምን ይሠፍራል?
እንወያያለን። [ተ. የአመልካች ሙሉ ስም]
መ. በማመልከቻ ደብዳቤ ራስጌ፣ በስተቀኝ (መ. ተማሪዎች የጥያቄዎቹን መልስ ጽፈው
በኩል ምን ይጻፋል? እንደጨረሱ ደብተራቸውን እንዲቀያየሩ
[መ. ማመልከቻው የሚቀርብለት መሥሪያ ቤት/ ያድርጉ። ከዚያም መልሶቹን ይንገሯቸው፤
ድርጅት አድራሻ] ርስበርስ እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
መ. በአድራሻው ምንምን ነገሮች ይጻፉሉ?
3ኛ ቀን
[መ. የመሥሪያ ቤቱ ስም፣ የሚገኝበት ቦታ]
መ. ከአድራሻው ሥር ምን ይጻፋል? የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
[መ. ቀን] • አቀላጥፎ ማንበብ

እንሥራ • ማዳመጥ
መ. በማመልከቻ ደብዳቤ ከቀኑ ዝቅ ብሎ • ሰዋስው
በስተግራ በኩል ምን ይጻፋል?
[መተ. የአመልካች ስምና አድራሻ] የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መ. በአመልካች ስምና አድራሻ ውስጥ ሥሩ
የሚካተቱት ነገሮች ምን ምን ናቸው?
መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ2ኛው ቀን፣ በቃላት

፻፹፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 183


ተግባር “2” ሥር የሠራችሁትን የቤትሥራ [መ. ስህተቶቹን በመቀነስ ከመጀመሪያው በተሻለ
መልስ ንገሩኝ። "ጆሮ አልሠጠም" የሚለው ያነባሉ።]
ፈሊጣዊ አነጋገር ፍቺ ምንድን ነው?
መ. አሁን ደግሞ በምንባቡ መልዕክት ላይ
[ተ. አላዳመጠም] በማተኮር ለሦስተኛ ጊዜ አነባለሁ። በማነብበት
ጊዜ የምንባቡን መልዕክት ለመረዳት ራሴን
መ. በጣም ጥሩ! (የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚህ
እየጠየቅሁ፣ በአንቀጹ ውስጥ ያሉ አዳዲስ
ዓይነት እንዲመልሱ ያድርጉ። ከዚያም
ቃላት ፍቺ ከአውዱ ለመረዳት እየሞከርኩ
ትክክለኛውን መልስ በመንገር ግብረመልስ
ረጋ ብዬ አነባለሁ።
ይስጡ።)
[መ. በአንቀጹ በቀረበው መልዕክት ላይ በማተኮር
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) ያነባሉ።]

ወይኔ ሰውዬው መ. ከአንቀጹ እንደተረዳሁት ሰውዬው


ከሕመሙ ማገገሙን፣ የመኖር ተስፋው
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) መለምለሙን፣ እንዲሁም ማድረግ ያለበትን
ልሥራ ጥንቃቄ ይገልጻል። ስለዚህ አንቀጹን ተስፋ
መ. አንድን ጽሑፍ በጥሩ ሁኔታ በንባብ በሚንፀባረቅበትና የምክር ቅላፄ ባለበት
ለማቅረብ ከፈለግን በተደጋጋሚ መለማመድ ድምፀት ለአራተኛ ጊዜ አነባለሁ።
ይኖርብናል። የሬዲዮ አንባቢዎች ያለምንም [መ. አንቀጹን ተስፋ በሚንፀባረቅበትና የምክር
መደነቃቀፍ ማንበብ ይጠበቅባቸዋል፤ ቅላፄ ባለው ድምፀት ያነባሉ።]
ይህ ከሆነ አድማጮች የሚነበበውን ነገር
ይረዱታል። ዛሬ ልክ እንደሬዲዮ አንባቢ ሥሩ
ጽሑፍን በሬዲዮ እንደምታቀርቡ በማሰብ (መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ)
ትለማመዳላችሁ። መ. "ወይኔ ሰውዬው!" ከሚለው ምንባብ
መ. አንድን ጽሑፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ስታነቡ የመጨረሻውን አንቀጽ ድምፅ እያሰማችሁ
በተደጋጋሚ ልትሳሳቱ ትችላላችሁ። ለሁለተኛ ተራበተራ አንብቡ።
ጊዜ ስታነቡ ግን የምትሠሩት ስህተት በጣም [ተ. ድምፅ እያሰሙ ተራበተራ ያነባሉ።]
ይቀንሳል፤ ነገርግን የጽሑፉን መልዕክት
ሙሉ በሙሉ ላትረዱት ትችላላችሁ። መ. አሁንም ይህንኑ አንቀጽ ደግማችሁ አንብቡ።
ስለዚህ መልዕክቱ ላይ በማተኮር ለሦስተኛ [ተ. አንቀጹን ከመጀመሪያው በተሻለ ያነባሉ።]
ጊዜ ማንበብ ይኖርባችኋል። ለአራተኛ ጊዜ
ስታነቡ የድምፃችሁን ቅላፄ በማስተካከል መ. አሁን በአንቀጹ መልዕክት ላይ በማተኮር
የጽሑፉን ስሜት በትክክል ለማንፀባረቅ ተራበተራ አንብቡ። ስታነቡ ስለመረዳታችሁ
በሚያስችል ገለጻ ለማንበብ መሞከር ራሳችሁን እየጠየቃችሁ፣ የቃላቱን ፍቺ
ይጠበቅባችኋል። አንድን ጽሑፍ በዚህ እየተረዳችሁ፣ ረጋ ብላችሁ መሆን አለበት።
መልክ በተደጋጋሚ በመለማመድ ካነበባችሁ፣ [ተ. በአንቀጹ መልዕክት ላይ በማተኮር ያነባሉ።]
ያለምንም መደናቀፍ ልክ ከውስጣችሁ
መ. አሁን አንቀጹ በምን ዓይነት ስሜት መነበብ
እንደሚፈስ ንግግር ይሆናል።
እንዳለበት ወስኑ።
ማንበብ (8 ደቂቃ) [ተ. አንቀጹ በምን ዓይነት ስሜት መነበብ
ልሥራ እንዳለበት ተወያይተው ይወስናሉ።]
መ. አሁን "ወይኔ ሰውዬው!" በሚል ርዕስ ከቀረበው (አንቀጹ በሀዘን ስሜት የሚነበብ መሆኑን
ምንባብ 3ኛውን አንቀጽ አነብላችኋለሁ። ይጠቁሟቸው።)
[መ. ስህተቶችን እየፈፀሙ/እየተደነቃቀፉ መ. አሁን የተስማማችሁበትን (የሀዘን) ስሜት
ያነባሉ።] በሚያንፀባርቅ የድምፅ ቅላፄ ለአራተኛ ጊዜ
አንብቡ።
መ. አሁንም ይህንኑ አንቀጽ ደግሜ አነባለሁ።
[ተ. የሀዘን ስሜት በሚያንፀባርቅ የድምፅ ቅላፄ

184 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፹፬


ያነባሉ።] ልጅቷ በመተማ ዮሐንስ ከተማ ከእናትና
አባቷ ጋር ትኖራለች። የ28 ዓመት ወጣት
(መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ በሰጧቸው ስትሆን፣ አጠር ያለች ጠይም የደምገንቦ ናት።
መመሪያ መሠረት ማንበባቸውን ይከታተሉ።) እናትና አባቷ በጥብቅ ቁጥጥር ስለአሳደጓት
ዓይናፋር ናት። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን
ማዳመጥ (15 ደቂቃ) እስከምታጠናቅቅ ድረስ የወንድና የሴት ጓደኛ
አልነበራትም።
የበቀል ጥንስስ
ትምህርቷን እንደጨረሰች በመተማ ዮሐንስ
ቅድመማዳመጥ (3 ደቂቃ) ከተማ በሚገኝ አንድ የግል ድርጅት ውስጥ
ሥሩ ተቀጥራ መሥራት ጀመረች። በተቀጠረችበት
ድርጅት ውስጥ አብራት የምትሠራ አንዲት
መ. የማነብላችሁን ምንባብ ከማዳመጣችሁ በፊት
ጓደኛም አገኘች። በጓደኛዋ አማካይነት ከአንድ
የቅድመማዳመጥ ጥያቄዎችን መልሱ። ወጣት ጋር ተዋወቀች። ከወጣቱ ጋር ያላት
መ. በቀል ምንድን ነው? ግንኙነት ከቀን ወደቀን እየጠነከረ መጣ። እናም
በድብቅ የፍቅር ጨዋታ ጀመሩ። ከሁለት ዓመት
[ተ. በቀል፣ በደል የደረሰበት ሰው፣ በበዳዩ በኋላ ግን ጓደኛዋ በጠና ታሞ ሞተ። እሷም
ላይ የሚወስደው የጥቃት እርምጃ ነው። አልፎ አልፎ ያማት ጀመር።
ጥቃቱም አካላዊ፣ ሥነልቡናዊ፣ ኢኮኖሚያዊ
አንድ ቀን በከፋ ሁኔታ ስለታመመች በጎንደር
ሊሆን ይችላል።] (ተማሪዎች እንደራሳቸው ከተማ ውስጥ በአንድ የግል ክሊኒክ ምርመራ
የመረዳት አቅም ሊገልፁት ይችላሉ።) አደረገች። በጤንነቷ ሁኔታ ጥርጣሬ ያደረባቸው
መ. በጣም ጥሩ! (የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚህ ሐኪም የኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ ምርመራ
ዓይነት እንዲመልሱ ያድርጉ።) እንድታደርግ መከሯት። ልጅቷም ከጓደኛዋ
ሞት በኋላ ጥርጣሬ አድሮባት ስለነበር፣
የማዳመጥ ሂደት (5 ደቂቃ) የሐኪሙን ምክር ተቀብላ የደም ናሙና ሰጠች።
የምርመራ ውጤቱም ኤች.አይ.ቪ. በደሟ ውስጥ
ሥሩ እንዳለባት የሚያሣይ መሆኑን ሐኪሙ ነገሯት።
መ. የማነብላችሁን ምንባብ የምክንያትና ቀሪ ሕይወቷንም እንዴት አድርጋ መምራት
ውጤት ትስሥር እያስተዋላችሁ አዳምጡ። እንዳለባት አስረዷት። ከሐኪሟ በተሰጣት ምክር
ስታዳምጡ ዋና ዋና ነጥቦችን ማስታወሻ መሠረት የፀረኤች.አይ.ቪ. ሕክምና ተጠቃሚ
ያዙ። ሆነች። ይህንንም ለማንም ሳታሣውቅ በምስጢር
ይዛ ቁጭ አለች። ሕክምናዋንም በየሦስት ወሩ
(መ."የበቀል ጥንስስ" የሚለውን ምንባብ
ወደጎንደር እየተመላለሰች ቀጠለች።
ያንብቡላቸው። የመጀመሪያዎቹን ሦስት
***ልጅቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ህመም ሲሰማት
አንቀጾች ካነበቡ በኋላ፣ ማንበብዎን አቋርጠው
የተመረመረችው የት ነው?***
በኮከብ ምልክት ውስጥ ያለውን ጥያቄ
ይጠይቋቸው።)
[ተ. ጎንደር] የሥራ ኃላፊዋ በየሦስት ወሩ ፈቃድ
የምትጠይቅበትን ምክንያት ለማወቅ ፈልጋ
መ. በጣም ጥሩ!
ጠየቀቻት። እሷም ዘመዶቿ ባህር ዳር እንዳሉና
(መ. ከተማሪዎች መልስ ከተቀበሉ በኋላ እነሱን ለመጠየቅ እንደምትሄድ ነገረቻት።
ማንበብዎን ይቀጥሉ። ስድስተኛውን አንቀጽ ኃላፊዋም ድርጊቱ ትክክል አለመሆኑን አስረድታ
አንብበው እንደጨረሱ በኮከብ ምልክት ውስጥ ለወደፊቱ ግን ፈቃድ መጠየቅ እንደሌለባት
ያለውን ጥያቄ ይጠይቋቸው።) ነገረቻት። ልጂቱም ግራ ገባት። ወደፊት ምን
ማድረግ እንዳለባት በቀላሉ መወሰን ስላልቻለች
[ተ. ግምታቸውን ይናገራሉ።] ጨነቃት፤ የምታደርገውን ብታጣ “እሺ!” ብላ
ቢሮውን ለቃ ወጣች።
(መ. ከተማሪዎች መልስ ከተቀበሉ በኋላ
ማንበብዎን ይቀጥሉ።) “እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል” እንደሚባለው
ልጅቷ ኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ እንዳለባት ታወቀ።
የበቀል ጥንስስ የፀረኤች.አይ.ቪ. ሕክምና እንደምትከታተልም
ገሀድ ወጣ። የመሥሪያቤቷ ባልደረቦችም

፻፹፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 185


እየራቋት መጡ። የቁርጥ ቀን ትሆነኛለች ያለቻት ካዳመጡ በኋላ የእርስዎንም አስተያየት
ጓደኛዋም ቀስበቀስ እየራቀቻት ሄደች። ልጅቷም በመጨመር ያጠቃሉ።)
በተፈጠረው ሁኔታ ተረበሸች፤ ሆደባሻም ሆነች።
ሥሩ
ቤተሰቦቿም ሁኔታዋ አላማራቸውም። በየሦስት
መ. አሁን ተግባር “2” ትሠራላችሁ፤ በመጀመሪያ
ወሩ ወደጎንደር የምትመላለስበት ምከንያት
በመጽሐፋችሁ የቀረበውን የቢጋር
እያሳሰባቸው መጣ። እየተደበቀች የምትውጠው
መድኀኒትም ጥርጣሬያቸውን አናረው። ምን ሠንጠረዥ በደብተራችሁ አዘጋጁ።
እንደሆነም ጠየቋት። እሷም የግዷን ነገረቻቸው። [ተ. የቢጋር ሠንጠረዡን በደብተራቸው
ቤተሰቡ በሙሉ በድንጋጤ ክው አለ። ቀስበቀስ ያዘጋጃሉ።]
የምትጠቀምባቸውን ቁሳቁሶች ለይተው ለብቻ
ማስቀመጥ ጀመሩ። እሷም ቤተሰቦቿ እያገለሏት መ. በመቀጠል ባዳመጣችሁት ምንባብ ታሪኩ
መሆኑን ስትረዳ ተበሳጨች፤ መፈጠሯን ጠላች። የተከናወነበትን ጊዜና ቦታ "መቼት" በሚለው
***ባለታሪኳ ከዚህ በኋላ ምን የምታደርግ ሣጥን ውስጥ ጻፉ።
ይመስላችኋል?*** [ተ. መቼቱን በቢጋር ሠንጠረዥ ይጽፋሉ።]
መ. ከዚያም ባለታሪኮቹን "ገፀባህርያት" በሚለው
አሁን ሁኔታዎች ሁሉ ለልጅቷ ጥሩ አልሆኑላትም። ሳጥን ውስጥ ዘርዝሩ።
የሥራ ኃላፊዋ ፈቃድ ከለከለቻት። ጓደኛዋና [ተ. ገፀባህርያቱን በቢጋር ሠንጠረዥ
ቤተሰቦቿም አገለሏት። ዙሪያው ገደል ሆነባት፤
ይዘረዝራሉ።]
ብስጭትና የጥፋተኛነት ስሜት ተሰማት። ራሷን
አገለለች፤ መነጫነጭም አበዛች። የመድኀኒት መ. አሁን በታሪኩ ውስጥ የተከናወኑት ድርጊቶች
መውሰጃ ስዓት ማሳለፍ ጀመረች። ምግቧንም ሁሉ እንዲከሰቱ ምክንያት የሆነውን መነሻ
በአግባቡ መመገብ ተወች። ነጋ ጠባ ቤቷን ዘግታ ችግር "ችግሩ" በሚለው ሳጥን ውስጥ ጻፉ።
ታለቅሳለች። በጓደኛዋ፣ በቤተሰቦቿና በሰዎች
ላይ ጥላቻ አደረባት። ቀስበቀስም በውስጧ [ተ. የችግሩን መነሻ በቢጋር ሠንጠረዥ
የቋጠረችው የበቀል ጥንስስ እያደገ መጣ። ይጽፋሉ።]
(ማግለል፣ መድሎና አለመቀበልን ለመከላከል የተዘጋጀ፣ መ. ከመነሻው ችግር በኋላ በተከታታይ
የስልጠናና የአፈጻጸም መመሪያ፣ ግንቦት 2004 ከሚለው
የተከናወኑትን ድርጊቶች በቅደምተከተል
ጽሑፍ ተወስዶ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎበት የቀረበ።)
"ድርጊት 1፣ ድርጊት 2 ወዘተ." በሚሉ
አዳምጦ መረዳት (7 ደቂቃ) ሣጥኖች ውስጥ ጻፉ።
ሥሩ [ተ. ድርጊቶችን በቅደምተከተል በቢጋር
መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ ሠንጠረዥ ውስጥ ይዘረዝራሉ።]
በአዳምጦ መረዳት ሥር የቀረቡትን
የተግባር "1"ን ጥያቄዎች በቃላችሁ መልሱ። መ. በመጨረሻም በታሪኩ መጨረሻ የመጣውን
ውጤት፣ በመጨረሻው ሳጥን ውስጥ ጻፉ።
መ. የልጅቷ የወንድ ጓደኛ ታሞ የሞተው በምን
ምክንያት ነው? [ተ. በታሪኩ መጨረሻ የመጣውን ውጤት በቢጋር
ጨንጠረዥ ይጽፋሉ።]
[ተ. በኤች.አይ.ቪ/ኤድስ]
(መ. በመጨረሻም በግል የሠሩትን በቡድን
መ. ይህን እንዴት አወቃችሁ? እንዲወያዩበት ያድርጉ።)
[ተ. ጓደኛዋ ታሞ ከሞተ በኋላ እሷንም አመማት፤
ወዲያው ስትመረመርም በደሟ ውስጥ ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ኤች.አይ.ቪ. መኖሩ ተረጋገጠ። ኤች.አይ.ቪ.
ሐተታዊ ዓረፍተነገር
ደግሞ ተላላፊ በሽታ በመሆኑ ጓደኛዋ
የሞተው በኤች.አይ.ቪ. መሆኑን መገመት ልሥራ
ይቻላል።] መ. ስለአንድ ነገር መፈፀም ወይም መሆን
የሚያትት/የሚገልጽ ዓረፍተነገር ሐተታዊ
(መ.የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት
ዓረፍተነገር ይባላል። ሐተታዊ ዓረፍተነገር
እንዲመልሱ ያድርጉ። የተማሪዎችን መልስ

186 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፹፮


ደግሞ አወንታዊ ወይም አሉታዊ ሊሆን ያትታል።]
ይችላል። የሚከተሉትን ዓረፍተነገሮች
መ. በጣም ጥሩ! አሉታዊ ዓረፍተነገር የሆነውስ
እንመልከት። (ዓረፍተነገሮቹን ሰሌዳው ላይ
የትኛው ነው?
ይጻፉላቸው።)
[መተ. የመጀመሪያው ዓረፍተነገር]
ሀ. ሰይድ እንጨት ፈለጠ።
መ. ለምን አሉታዊ ዓረፍተነገር ነው አልን?
ለ. መቅደስ መምህር ሆነች።
[መተ. "ሴትየዋ ክፉ ሰው ይወዳሉ" ብንል
ሐ. ልጁ ምሳውን አልበላም።
ኖሮ ዓረፍተነገሩ አወንታዊ ዓረፍተነገር
መ. ሴትዮዋ ክፉ አይደለችም። ይሆን ነበር። ነገር ግን ይህን በማፍረስ
ሴትዮዋ የማይወዱትን ስለሚገልጽ አሉታዊ
መ. በሰሌዳው ላይ ከጻፍኳቸው ዓረፍተነገሮች
ዓረፍተነገር ነው።]
መካከል አወንታዊ ዓረፍተነገር የሆኑት
የትኞቹ ናቸው? ሥሩ
[መ. የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ ዓረፍተነገሮች] መ. አሁን በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣
በሰዋስው ሥር በተግባር “1” የቀረቡትን
መ. እ ነ ዚ ህ ን ዓረፍተነገሮች አወንታዊ ዓረፍተነገሮች አወንታዊ ወይም አሉታዊ
ዓረፍተነገሮች ናቸው ያልኩት በምን መሆናቸውን በምሳሌው መሠረት እየለያችሁ
ምክንያት ነው? በደብተራችሁ ጻፉ።
[መ. የመጀመሪያው ዓረፍተነገር ሰይድ ያደረገውን መ. በፊደል ተራ "ሀ" የቀረበው ዓረፍተነገር
ያትታል። ሁለተኛው ዓረፍተነገር ደግሞ አሉታዊ ነው ወይስ አወንታዊ?
መቅደስ የሆነችውን ያትታል።]
[ተ. አሉታዊ ዓረፍተነገር ]
መ. ሰሌዳው ላይ ከጻፍኳቸው ዓረፍተነገሮች
መካከል አሉታዊ የሆኑት የትኞቹ ናቸው? መ. ለምን አሉታዊ ዓረፍተነገር ነው አላችሁ?

[መ. የመጨረሻዎቹ ሁለቱ ዓረፍተነገሮች] [ተ. "መስታወት ልብስ ገዛች" ቢል ኖሮ


ዓረፍተነገሩ አወንታዊ ይሆን ነበር። ነገርግን
መ. እነዚህን ዓረፍተነገሮች አሉታዊ ዓረፍተነገሮች ይህን በማፍረስ መስተዋት ልብስ ስለመግዛቷ
ናቸው ያልኩት በምን ምክንያት ነው? ሳይሆን ስላለመግዛቷ ስለሚገልጽ ዓረፍተነገሩ
[መ. ለምሳሌ 3ኛው ዓረፍተነገር "ልጁ ምሳውን አሉታዊ ነው።]
በላ" የሚል ቢሆን አወንታዊ ዓረፍተነገር መ. በጣም ጥሩ! በደብተራችሁ “ሀ. አሉታዊ
ይሆን ነበር። ነገርግን ይህን በማፍረስ ዓረፍተነገር” ብላችሁ ጻፉ።
አሉታዊ በሆነ መንገድ ልጁ ያደረገውን
ሳይሆን ያላደረገውን የሚገልጽ በመሆኑ (መ. የቀሩትንም ዓረፍተነገሮች በዚህ ዓይነት
አሉታዊ ዓረፍተነገር ነው።] በራሳቸው ለይተው መልሶቻቸውን ርስበርስ
እንዲተራረሙ ያድርጉ። ተግባር "2"ን ደግሞ
እንሥራ የቤትሥራ ይስጧቸው።)
መ. አሁን ደግሞ አብረን እንሥራ። (የሚከተሉትን
ዓረፍተነገሮች ሰሌዳው ላይ ይጻፉላቸው።)
ሀ. ሴትዮዋ ክፉ ሰው አይወዱም
ለ. ወይንሸት አዲስ ኮምፒዩተር አላት።
መ. ከሁለቱ ዓረፍተነገሮች አወንታዊ ዓረፍተነገር
የሆነው የትኛው ነው?
[መተ. 2ኛው ዓረፍተነገር]
መ. ለምን አወንታዊ ዓረፍተነገር ነው አልን?
[መተ. ምክንያቱም ወይንሸት ያላትን ነገር

፻፹፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 187


(መ. የቀሩትን ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት
2ኛ ሳምንት እንዲመልሱ ያድርጉ።)
ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፤ መድሎና የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
መገለልን የመከላከያ መንገዶች ሥሩ
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ። "1"ና "2"
በማለት ቍጥር ይስጧቸው።)
4ኛ ቀን
መ. የመጀመሪያዎቹን ሁለት አንቀጾች
የዕለቱ ትምህርት ይዘት ድምፅ ሳታሰሙ በግል አንብቡ። ስታነቡ
• ማንበብ ያልገባችሁን ሀሳብ ራሳችሁን እየጠየቃችሁ
ጥያቄዎችን በማስታወሻ ያዙ።

የቤትሥራ (5 ደቂቃ) [ተ. ራሳቸውን የጠየቋቸውን ጥያቄዎች


በማስታወሻቸው እየያዙ ያነባሉ።]
ሥሩ
መ. አ ሁ ን ራሳችሁን በጠየቃችኋቸው
(መ. በ1ኛው ሳምንት፣ በ3ኛው ቀን፣ በሰዋስው
ጥያቄዎች ላይ በጥንድ ተወያዩ። እንዴት
ተግባር “2” የተሰጣቸውን የቤትሥራ መልሶች
እንደመለሳችኋቸውም ለጓደኛችሁ ንገሩ።
ያረጋግጡ።)
[ተ. በያዙት ማስታወሻ መሠረት ጥያቄዎችን
መ. "ወይኔ ሰውዬው!" በሚል ርዕስ ከቀረበው
እያነሱ አንዳቸው የገባቸውን ለአንዳቸው
ምንባብ ውስጥ ያገኛችኋቸውን አሉታዊ
ያስረዳሉ፤ ጥያቄዎቹን የመለሱባቸውን
ዓረፍተነገሮች ንገሩኝ።
ብልሃቶች ለጓደኞቻቸው ይናገራሉ።]
[ተ. እሱ ግን ጆሮ አልሰጠም፣… የቀን ሥራውን
(መ. ለ2 ደቂቃ ያህል ከተወያዩ በኋላ
እንደዱሮው መሥራት አልቻለም።]
ማንበባቸውን እንዲቀጥሉ ያድርጉ። የቀሩትን
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ አወንታዊ 4 አንቀጾች ያልገባቸውን ሀሳብ በተመለከተ
ዓረፍተነገሮችን ንገሩኝ። (በምንባቡ ውስጥ ራሳቸውን እየጠየቁና በማስታወሻቸው እየያዙ
ያሉት ብዙዎቹ አወንታዊ ዓረፍተነገሮች እንዲያነቡ ያድርጉ።)
ናቸው። የተወሰኑ ዓረፍተነገሮችን ብቻ
መ. አሁን በጥያቄዎቻችሁ ላይ ተወያዩ።
እንዲናገሩ ያድርጉ።)
አንዳችሁ የተረዳችሁት ለአንዳችሁ አስረዱ።
[ተ. በምንባቡ የሚገኙ ጥቂት አወንታዊ እንዴት እንደተረዳችሁትም ለጓደኞቻችሁ
ዓረፍተነገሮችን ይናገራሉ። ] ግለጹ።
[ተ. ከጠየቋቸው ጥያቄዎች በመነሳት አንዳቸው
ማንበብ (35 ደቂቃ) የገባቸውን ለአንዳቸው ያስረዳሉ። ለጥያቄዎቹ
ሁሉም የድርሻውን ይወጣ መልስ የሰጡበትን ብልሃት ለጓደኛቸው
ይናገራሉ።]
ቅድመንባብ (5 ደቂቃ)
መ. ልትመልሱት ያልቻላችሁትን ጥያቄ
መገመት (ያልገባችሁን ነገር) ተመልሳችሁ በማንበብ
ሥሩ ለመረዳት ሞክሩ።
መ. ዛሬ "ሁሉም የድርሻውን ይወጣ" በሚል ርዕስ አንብቦ መረዳት (20 ደቂቃ)
የቀረበ ምንባብ ታነባላችሁ። በቅድሚያ ግን
የቅድመንባብ ጥያቄዎችን መልሱ። ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎችን
መ. በሥዕሉ በምትታየው ልጅ ደረት ላይ ያለው
ትመልሳላችሁ። በተግባር “1” ሥር
የምን ምልክት ነው?
የቀረቡት ዓረፍተነገሮች የሚያስተላልፏቸው
[ተ. ኤች.አይ.ቪ./ኤድስን በጋራ የመከላከልና መልዕክቶች በምንባቡ መሠረት ትክክል ከሆኑ
የመቆጣጠር ምልክት ነው።] እስማማለሁ፣ ትክክል ካልሆኑ አልስማማም

188 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፹፰


በማለት ምክንያታችሁን ተናገሩ።
መ. ሙሳና ይታጠቁ በትምህርትቤቱ ውስጥ 5ኛ ቀን
የተመደቡ የጤና ባለሙያዎች ናቸው።
[ተ. አልስማማም] የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
• ቃላት
መ. ምክንያታችሁ ምንድን ነው?
• መጻፍ
[ተ. ምክንያቱም ሙሳና ይታጠቁ የስምንተኛ
ክፍል ተማሪዎችና የፀረኤች.አይ.ቪ./
ኤድስ ክበብ አባላት መሆናቸው በምንባቡ
ተገልጿል።]
ቃላት (10 ደቂቃ)
(መ. ቀሪዎቹንም ዓረፍተነገሮች በዚሁ ዓይነት
መስማማት አለመስማማታቸውን ያረጋግጡ፤ በቃላትና ሐረጋት ዓረፍተነገር
በትክክል ያልተመለሱ ጥያቄዎችን መመሥረት
ዓረፍተነገሮቹ የሚገኙበትን አንቀጽ ሥሩ
በመጠቆም እንደገና አንብበው ትክክለኛ
መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ በቃላት
መልስ እንዲሰጡ ያድርጉ።)
ተግባር ሥር የቀረቡት ቃላት በምንባቡ
ሥሩ ውስጥ ባላቸው ፍቺ ላይ በቡድን ተወያዩ።
መ. አሁን ደግሞ የተግባር “2”ን የምርጫ ከዚያም ፍቻቸውን የሚያሳዩ ዓረፍተነገሮችን
ጥያቄዎች መልሱ። በተራ ቊጥር 1 በደብተራችሁ ጻፉ።
የቀረበውን ጥያቄ አንብቡ። መ. "ማለባበስ" የሚለው ቃል በምንባቡ ውስጥ
[ተ. አንድ/ዲት ተማሪ ጥያቄውን ያነባል/ ያለው ፍቺ ምንድን ነው?
ታነባለች።] [ተ. መሸፋፈን፣ መደባበቅ፣ ግልጽ አለማድረግ…]
መ. አሁን ደግሞ ምርጫዎቹን ልታነቡ መ. በጣም ጥሩ! ይህን ፍቺ እንዲያሳይ
ትችላላችሁ? አድርጋችሁ "ማለባበስ" በሚለው ቃል
[ተ. አንድ/ዲት ተማሪ ምርጫዎቹን ያነባል/ ዓረፍተነገር መሥርቱ።
ታነባለች።] [ተ. ስለኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ ማለባበሱን ትተን
መ. ለተጠየቀው ጥያቄ ከቀረቡት አማራጮች በግልፅ ብንወያይ የበሽታውን ሥርጭት
ትክክለኛው መልስ የትኛው ነው? መቆጣጠር እንችላለን።]
[ተ. በማኅበረሰቡ ዘንድ ተአማኒነት ስላላቸው።] (መ. በዚህ ዓይነት በቀሩት ቃላትና ሐረጋት ፍቺ
ላይ ከተወያዩ በኋላ ዓረፍተነገር እንዲመሠርቱ
መ. በጣም ጥሩ! (የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚሁ
ያድርጉ። ተማሪዎች የመሠረቷቸውን
ዓይነት እንዲመልሱ ያድርጉ። በትክክል
ዓረፍተነገሮች ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ
ያልተመለሱ ጥያቄዎችን ምንባቡን እንደገና
አድርገው የተሰጠውን ፍቺ የማያሳዩ
በማንበብ እንዲመልሱ ያድርጉ። ተግባር
ዓረፍተነገሮችን፣ ፍቹን እንዲያሳዩ አድርገው
"3"ን ደግሞ በደብተራቸው እንዲሠሩ ለ6ኛው
በማስተካከል ግብረመልስ ይስጡ።)
ቀን የቤትሥራ ይስጧቸው።)
መጻፍ (30 ደቂቃ)
ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
በምክንያትና ውጤት ስልት የተዋቀረ
ድርሰት መጻፍ
ሥሩ
መ. ዛሬ "ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን በተመለከተ

፻፹፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 189


የመድሎና የመገለል መንስኤና ውጤቶች" የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ)
በሚል ርዕስ ባለሦስት አንቀጽ ድርሰት
ትጽፋላችሁ። ከዚያ በፊት ግን በምጠይቃችሁ
የማመልከቻ ደብዳቤ አጻጻፍ
ጥያቄዎች ላይ እየተወያያችሁ ሀሳባችሁን ሥሩ
ታደራጃላችሁ። መ. አሁን የሥነጽሑፍና ድራማ ክበብ አባል
መ. መድሎና መገለል ምን ማለት ነው? ለመሆን ለትምህርትቤታችሁ የማመልከቻ
ከሰበሰባችሁት መረጃና "ሁሉም የድርሻውን ደብዳቤ ትጽፋላችሁ። ስለሆነም በ2ኛው
ይወጣ" ከሚለው ምንባብ በመነሳት ሳምንት፣ በ5ኛው ቀን፣ በአጻጻፍ ሥርዓት
የመድሎንና መገለልን ምንነት ግለጹ። ሥር በቀረበው የማመልከቻ ደብዳቤ ቅፅ
ውስጥ መጻፍ የሚገባውን ነገር በደብተራችሁ
[ተ. በመድሎና በመገለል ምንነት ላይ እየተወያዩ ጻፉ።
ለድርሰታቸው መነሻ የሚሆን ማስታወሻ
ይይዛሉ።] መ. "ሀ" የሚወክለው ምን ምንን ነው?

መ. በጣም ጥሩ! የመድሎና የመገለል [ተ. ማመልከቻው የሚቀርብለት መሥሪያቤት


መንስኤዎች/ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? አድራሻና ቀን]
ወይም ሰዎች ኤች.አይ.ቪ. በደማቸው ውስጥ መ. በጣም ጥሩ! በመጀመሪያው መስመር ምን
ያለባቸውን ሰዎች የሚያገሉት ለምንድን ይጻፉል?
ነው? ከተወያያችሁ በኋላ መንስኤዎችን
በቢጋር ሠንጠረዡ ዘርዝሩ።
[ተ. ማመልከቻው የሚጻፍለት መሥሪያቤት ስም]
መ. በጣም ጥሩ! የትምህርትቤታችሁን ስም ጻፉ።
[ተ. በመድሎና መገለል መንስኤዎች ላይ
ተወያይተው በቢጋር ሠንጠረዡ ይዘረዝራሉ።] [ተ. የትምህርትቤታቸውን ስም ይጽፋሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! በመድሎና በመገለል የሚደርሱ መ. ቀጥሎ ባለው መስመር ላይ ምን ይጻፋል?
ጉዳቶች ምን ምን ናቸው? ከተወያያችሁ
[ተ. መሥሪያቤቱ የሚገኝበት ክልልና ዞን
በኋላ ጉዳቶቹን/ውጤቶቹን በቢጋር ሠንጠረዡ
ይጻፋል።]
ዘርዝሩ።
መ. ትክክል ነው! ትምህርትቤታችሁ የሚገኝበትን
[ተ. በመድሎና በመገለል በሚደርሱ ጉዳቶች/
ክልልና ዞን ስም ጻፉ።
ውጤቶች ላይ ተወያይተው በቢጋር
ሠንጠረዥ ይዘረዝራሉ።] [ተ. ክልላቸውንና ዞናቸውን ይጽፋሉ።]
መ. በጣም ጥሩ! አሁን የመድሎንና የመገለልን መ. 3ኛው መስመር ላይ ምን ይጻፋል?
ምንነት በአንደኛው አንቀጽ፣ የመድሎና
[ተ. መሥሪያቤቱ የሚገኝበት ከተማ ወይም ልዩ
የመገለል መንስኤዎችን በሁለተኛው
ቦታ ስም ይጻፋል።]
አንቀጽ፣ እንዲሁም መድሎና መገለል
የሚያስከትሏቸውን ጉዳቶች በሦስተኛው መ. የከተማችሁን ስም ጻፉ።
አንቀጽ በተሟሉ ዓረፍተነገሮች እያደራጃችሁ [ተ. የከተማቸውን ስም ይጽፋሉ።]
ጻፉ።
መ. በአራተኛው መስመር ላይ ምን ይጻፋል?
[ተ. በቢጋር ሠንጠረዥ የዘረዘሯቸውን ሀሳቦች
አንቀጽ በአንቀጽ አደራጅተው ይጽፋሉ።] [ተ. ማመልከቻው የተጻፈበት ቀን።]
(መ. ተማሪዎች ሲጽፉ እየተዘዋወሩ ይከታተሉ። መ. የዛሬውን ቀን ጻፉ። (ወሩን፣ ቀኑንና ዘመኑን
መጻፍ ለተቸገሩ ተማሪዎች ፍንጭ በመስጠት ይጠቁሟቸው።)
ይደግፏቸው።) [ተ. ቀን ይጽፋሉ።]
መ. "ለ" የሚወክለው ምን ምንን ነው?
[ተ. የአመልካቹ/ቿን አድራሻ ነው።]
መ. በጣም ጥሩ! በመጀመሪያው መስመር ምን

190 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፺


ይጻፋል? [ተ. የሚጠየቀው ጉዳይ በዝርዝር ይቀርብበታል።]
[ተ. የአመልካቹ/ቿ ስም ይጻፋል።] መ. የሥነጽሑፍና የድራማ ክበብ አባል ለመሆን
እንድትችሉ ዘርዝራችሁ ጻፉ።
መ. የራሳችሁን ሙሉ ስም ጻፉ።
[ተ. ጥያቄያቸውን ዘርዝረው ይጽፋሉ።]
[ተ. ሙሉ ስማቸውን ይጽፋሉ።]
መ. በ"ሠ" የሚጻፈው ምንድን ነው?
መ. በሁለተኛው መስመር ምን ይጻፋል?
[ተ. መውጫ ወይም መሰናበቻ ይጻፋል።]
[ተ. አመልካቹ/ቿ የሚኖርበት/የሚሠራበት
የምትኖርበት/የምትሠራበት ቦታ ስም መ. በጣም ጥሩ! የትምህርትቤታችሁን የዓመቱን
ይጻፋል።] መሪ ቃል ጻፉ። (ያስታውሷቸው።)
መ. ትክክል ነው! የትምህርትቤታችሁን ስም [ተ. የዓመቱን መሪ ቃል ይጽፋሉ።]
ጻፉ።
መ. በ"ረ" ምን ይጻፋል?
[ተ. የትምህርትቤታቸውን ስም ይጽፋሉ።]
[ተ. የአመልካቹ/ቿ ፊርማ።]
መ. ቀጥሎ በሚገኘው መስመር ምን ይጻፋል።
መ. ፈርሙ።
[ተ. አመልካቹ/ቿ የሚገኝበት/የምትገኝበት ክፍል፣
[ተ. ይፈርማሉ።]
ቀበሌ፣…ይጻፋል።]
መ. በ"ሰ" ምን ይጻፋል?
መ. በጣም ጥሩ! ክፍላችሁን ጻፉ።
[ተ. የአመልካቹ/ቿ ሙሉ ስም ይጻፋል።]
[ተ. 5ኛ ሀ፣ ለ… በማለት ይጽፋሉ።]
መ. ሙሉ ስማችሁን ጻፉ።
መ. በአራተኛው መስመር ላይ ምን ይጻፋል?
[ተ. ሙሉ ስማቸውን ይጽፋሉ።]
[ተ. የአመልካቹ/ቿ ስልክ ቍጥር፣ ፖስታ ሳጥን
ቍጥር …ይጻፋል።] (መ. አሁን ደብተራቸውን ተለዋውጠው
በትክክል መጻፍ አለመጻፋቸውን ርስበርስ
መ. ትክክል ነው! የራሳችሁን ወይም
እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
የቤተሰቦቻችሁን ወይም የምታውቁትን ስልክ
ቊጥር ጻፉ።
[ተ. ስልክ ቍጥር ይጽፋሉ።]
6ኛ ቀን
መ. በአምስተኛው መስመር ላይ ምን ይጻፋል። የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
[ተ. አመልካቹ/ቿ የሚኖርበት/የምትኖርበት • አቀላጥፎ ማንበብ
ከተማ ወይም ልዩ ቦታ ስም ይጻፋል።] • መናገር
መ. የከተማችሁን ስም ጻፉ። • ሰዋስው
[ተ. የከተማቸውን ወይም የቦታውን ስም
ይጽፋሉ።]
የቤትሥራ (5 ደቂቃ)
መ. በ"ሐ" የሚጻፈው ምንድን ነው? ሥሩ
[ተ. የሚጠየቀውን ጉዳይ ባጭሩ የሚቀርብበት (መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ4ኛው ቀን፣ በአንብቦ
ነው።] መረዳት፣ በተግባር “3” ሥር የሠሩትን
መ. ጉዳዩን በአጭሩ ጻፉ።
የቤትሥራ በትክክል መሥራታቸውን
ያረጋግጡ። መልሱንም ከተማሪዎች
[ተ. “የሥነጽሑፍና ድራማ ክበብ አባልነት ይቀበሉ።)
ጥያቄን ይመለከታል” ብለው ይጽፋሉ።]
መ. ኤች.አይ.ቪ. በደማቸው ያለባቸው ሰዎች
መ. በ"መ" የሚጻፈው ምንድን ነው? አወንታዊ የአኗኗር ዘዴን እንዲከተሉ
ማድረጉ ለምን ይጠቅማል?

፻፺፩ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 191


[ተ. ጤንነታቸው ተጠብቆ እንዲቆይ ያግዛቸዋል፤ መ. ቀደምሲል ያነበባችሁትን ተራበተራ
ጤናማ ሆነው መኖር ከቻሉ ኅበረተሰቡ ደግማችሁ አንብቡ።
ስለበሽታው ያለው የተጋነነ ፍርሃት ይቀንስና
[ተ. ወንዶች የይታጠቁን ንግግር፣ ሴቶች የሙሳን
ያቀርባቸዋል።]
ንግግር በጥንድ ሆነው በድጋሜ ተራበተራ
(መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት ያነባሉ።]
እንዲመልሱ ያድርጉ።)
መ. አሁንም ለሦስተኛ ጊዜ በመልዕክቱ ላይ
በማተኮር አንብቡ።
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ)
[ተ. ወንዶች በይታጠቁ ንግግር፣ ሴቶች በሙሳ
ሁሉም የድርሻውን ይወጣ ንግግር መልዕክት ላይ በማተኮር ለሦስተኛ
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) ጊዜ ያነባሉ።]

ሥሩ መ. በጣም ጥሩ! አሁን ወንዶች የይታጠቁን


ንግግር ድምፃችሁን የሴት ድምፅ በማስመሰል፣
መ. ዛሬ፣ የንግግር ልምምድ እንደምታደርጉ
ሴቶች ደግሞ የሙሳን ንግግር ድምፃችሁን
አድርጋችሁ በማሰብ የማንበብ ልምምድ
የወንድ ድምፅ በማስመሰል በጥንድ ሆናችሁ
ታደርጋላችሁ። በቅድሚያ ግን የምንባቡን
ተራበተራ አንብቡ።
ሀሳብ በማስታወስ አንድ ጥያቄ መልሱ።
[ተ. ወንዶቹ የሴት ድምፅ፣ ሴቶቹ የወንድ ድምፅ
መ. "ሁሉም የድርሻውን ይወጣ" በሚል ርዕስ
በማስመሰል ያነባሉ።]
በቀረበው ምንባብ ውስጥ የመድሎና የመገለል
መከላከያ መንገዶች ተብለው የተዘረዘሩት (መ. ተማሪዎች ሲያነቡ እየተዘዋወሩ ተግባሩን
ምን ምን ናቸው? በትክክል መሥራታቸው ይከታተሉ።)
[ተ. ማኅብረሰቡ ኤች.አይ.ቪ. ስለሚተላለፍባቸውና
ስለማይተላለፍባቸው መንገዶች መረጃ መናገር (15 ደቂቃ)
እንዲያገኝ ማድረግ፣ ኤች.አይ.ቪ. በደማቸው ሥሩ
ያለባቸው ሰዎች አወንታዊ የአኗኗር ዘዴን (መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ።)
እንዲከተሉ ማድረግ፣ ኤች.አይ.ቪ. ካለባቸው
ሰዎች ጋር ስንነጋገር የመገለል ስሜትን መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን፣ በመናገር
የሚያንፀባርቁ ቃላት አለመጠቀምና ሥር የቀረቡ ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ
ኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ በደማቸው ውስጥ ንግግራችሁን በምክንያትና ውጤት ስልት
ካለባቸው ሰዎች ጋር አብሮ መኖር ናቸው።] እያደራጃችሁ ተናገሩ። ስትናገሩ እንደመድሎ፣
መገለል፣ መከላከል፣ ማለባበስ፣ መቆጠብ፣
ማንበብ (8 ደቂቃ) ተሃዋስያን ያሉ የተማራችኋቸውን አዳዲስ
ሥሩ ቃላት ተጠቀሙ። ንግግራችሁን በምክንያትና
(መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ።) ውጤት ለማስተሳሰር እንደ ምክንያቱም፣ በዚህ
የተነሳ፣ በመሆኑ…የመሳሰሉትን አያያዥ
መ. ወንዶች የይታጠቁን ንግግር፣ ሴቶች ቃላትና ሐረጋትም ተጠቀሙ።
የሙሳን ንግግር በመድረክ ላይ ንግግር
እንደምታቀርቡ አድርጋችሁ በማሰብ [ተ. በጥያቄዎች ላይ ይወያያሉ።]
ለመጀመሪያ ጊዜ አንብቡ። (ተማሪዎች (መ. ተማሪዎች ሲወያዩ እየተዘዋወሩ ይከታተሉ።
የሚለማመዱት በትእምርተጥቅስ ውስጥ ሁሉም ተማሪዎች ንቁ ተሳታፊ መሆናቸውን፣
ያሉትን የገፀባህርያቱን ንግግር ብቻ ነው። በንግግራቸው ውስጥ ምክንያትና ውጤት
ለ3ኛ ጊዜ የሚያነቡት ወንዶችም ሴቶችም መኖሩንና የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት
በራሳቸው ድምፅ ነው። ድምፃቸውን እንዲሁም አያያዥ ቃላትና ሐረጋት
የሚያስመስሉት ለ4ኛ ጊዜ ሲያነቡ ነው።) መጠቀማቸውን ያረጋግጡ።)
[ተ. ወንዶች የይታጠቁን ንግግር፣ ሴቶች የሙሳን
ንግግር በጥንድ ሆነው ተራበተራ ያነባሉ።]

192 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፺፪


ሰዋስው (10 ደቂቃ) ያድርጉ። በተጨማሪም "ሁሉም የድርሻውን
ይወጣ" ከሚለው ምንባብ ውስጥ 5 አወንታ
አወንታዊና አሉታዊ ሐተታ ዓረፍተነገር ዓረፍተነገሮችን በማውጣት ወደአሉታዊ
እንሥራ ዓረፍተነገር እንዲቀይሩ የቤትሥራ
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለአወንታዊና አሉታዊ ይስጧቸው።)
ሐተታ ዓረፍተነገር ተምራችኋል። ዛሬ ደግሞ
አሉታዊ ዓረፍተነገሮችን ወደአወንታዊ፣
አወንታዊ ዓረፍተነገሮችን ደግሞ ወደአሉታዊ
ትቀይራላችሁ። በመጀመሪያ ግን አንድ
ምሳሌ አብረን እንሥራ።
መ. "ወደቤታችን ለመሄድ ታክሲ አያስፈልገንም"
የሚለውን አሉታዊ ዓረፍተነገር ወደአወንታዊ
እንለውጥ።
[መተ. ወደቤታችን ለመሄድ ታክሲ ያስፈልገናል።]
ሥሩ
መ. አሁን አብረን በሠራነው መሠረት
በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን፣ በሰዋስው
ሥር፣ በተግባር “1” የቀረቡትን አሉታዊ
ዓረፍተነገሮች ወደአወንታ እየለወጣችሁ
በደብተራችሁ ጻፉ።
መ. "ገበሬው በዚህ ዓመት ብዙ አላመረተም"
የሚለውን አሉታዊ ዓረፍተነገር ወደአወንታዊ
ለውጡ።
[ተ. ገበሬው በዚህ ዓመት ብዙ አምርቷል።]
(መ. የቀሩትንም በዚሁ ዓይነት እንዲሠሩ
ያድርጉ።)
እንሥራ
መ. አሁን ደግሞ ተግባር "2"ን እንሥራ።
"ዳዊት የገዛው መጽሐፍ በጣም ውድ ነው"
የሚለውን አወንታዊ ዓረፍተነገር ወደአሉታዊ
እንለውጥ።
[መተ. ዳዊት የገዛው መጽሐፍ በጣም ውድ
አይደለም።]
ሥሩ
መ. አብረን በሠራነው መሠረት በተግባር "2"
ሥር የቀረቡትን አወንታዊ ዓረፍተነገሮች
ወደአሉታ እየለወጣችሁ በደብተራችሁ ጻፉ።
መ. "ፋጡማ ከወሎ መጣች" የሚለውን አወንታዊ
ዓረፍተነገር ወደአሉታዊ ለውጡ።
[ተ. ፋጡማ ከወሎ አልመጣችም።]
(መ. የቀሩትም በዚሁ ዓይነት እንዲሠሩ

፻፺፫ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 193


[ተ. እንደሚፈጠርባት]
3ኛ ሳምንት
(መ. የቀሩትንም በዚሁ ዓይነት እንዲያነቡ
ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፤ ፍቅርና ያድርጉ።)
እንክብካቤ
ማንበብ (30 ደቂቃ)
ፍቅርና እንክብካቤ
7ኛ ቀን
ቅደመንባብ (3 ደቂቃ)
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች
መገመት
• የቃላት ጥናት
• ማንበብ
ሥሩ
መ. አሁን "ፍቅርና እንክብካቤ" በሚል ርዕስ
የቀረበ ምንባብ ታነባላችሁ። በመጀመሪያ ግን
የቤትሥራ (5 ደቂቃ) አንድ የቅድመንባብ ጥያቄ ትመልሳላችሁ።
ሥሩ መ. ከርዕሱና ከሥዕሉ በመነሳት ምንባቡ ስለምን
(መ. በ2ኛው ሳምንት፣ በ6ኛው ቀን፣ በሰዋስው እንደሚገልጽ ገምቱ።
ሥር የተሰጣቸውን የቤትሥራ በትክክል [ተ. ስለምንባቡ ይገምታሉ]
መሥራታቸውን አረጋግጠው የተወሰኑ
መልሶችን ከተማሪዎች ይቀበሉ።) የማንበብ ሂደት (10 ደቂቃ)
መ. በምንባቡ ውስጥ የሚገኝ አንድ አወንታዊ ሥሩ
ሐተታ ዓረፍተነገር የምታነብልኝ/ መ. በመጀመሪያ ጥያቄዎቻችሁንና መልሶቻችሁን
የሚያነብልኝ? የምታሠፍሩበት ሠንጠረዥ በደብተራችሁ
አዘጋጁ።
[ተ. እነሱ የሚናገሩት ተቀባይነት አለው።]
(የተለያዩ ዓረፍተነገሮችን ሊያነቡ ይችላሉ።) [ተ. በማንበብ ሂደት ጥያቄዎቻቸውንና
መልሶቻቸውን የሚያሠፍሩበትን ሠንጠረዥ
መ. በጣም ጥሩ! ይህንን ዓረፍተነገር ወደአሉታዊ
በደብተራቸው ያዘጋጃሉ።]
ዓረፍተነገር ለውጣችሁ አንብቡ።
መ. አሁን "ፍቅርና እንክብካቤ" በሚል
[ተ. እነሱ የሚናገሩት ተቀባይነት የለውም።]
ርዕስ የቀረበውን ምንባብ ያልገባችሁን
(መ. የቀሩትንም መልሶች በዚሁ ዓይነት እየጠየቃችሁና መልስ እየሰጣችሁ አንብቡ።
ይቀበሉ።)
[ተ. እየጠየቁ፣ መልሶቻቸውንና ጥያቄዎቻቸውን
በሠንጠረዣቸው እየመዘገቡ ያነባሉ።]
የቃላት ጥናት (5 ደቂቃ)
(መ. አንብበው እንደጨርሱ በማንበብ ሂደት
መነጠልና ማጣመር ከጠየቋቸው ጥያቄዎች ምላሽ ያላገኙላቸውን
ሥሩ ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያቀርቡ
መ. አሁን "ፍቅርና እንክብካቤ" በሚል ርዕስ ያድርጉ። እነዚህን ጥያቄዎችም ሌሎች
ከቀረበው ምንባብ የወጡ ቃላትንና ሐረጋትን ተማሪዎች እንዲመልሱ ያድርጉ። እንዴት
በመነጣጠልና በማጣመር ታነባላችሁ። እንደተረዱትም ለክፍል ጓደኞቻቸው
እንዲያብራሩ ያድርጉ።)
መ. "እንደሚፈጠርባት" የሚለውን ሐረግ
በመነጣጠል አንብቡ። አንብቦ መረዳት (17 ደቂቃ)
[ተ. እንደሚፈጠር-ብ-ኣት] ሥሩ
መ. አሁን በ3ኛው ሳምንት፣ በ7ኛው ቀን፣
መ. በጣም ጥሩ! ይህንኑ ሐረግ በማጣመር
በአንብቦ መረዳት፣ በተግባር “1” ሥር
አንብቡ።
የቀረበውን ተግባር ትሠራላችሁ። የቀረበው

194 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፺፬


ዓረፍተነገር፣ በምንባቡ መሠረት በያዘው በደብተራችሁ ጻፉ።
ሀሳብ የምትስማሙ ከሆነ፣ ሁለት ጊዜ
[ተ. እያለቀሰችና ድምፅዋ በሳግ እየተቆራረጠ
አጨብጭቡ፣ የማትስማሙ ከሆነ እጃችሁን
ችግሮቿን አጫውታቸዋለች።]
አውጡ። ከዚያም ምክንያታችሁን ተናገሩ።
(መ. የቀሩትንም በዚሁ ዓይነት እንዲሠሩ
መ. ልጅቷ አቶ ጉልማን ያነጋገረቻቸው
ያድርጉ። ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ
በደስታ እየተፍለቀለቀችና ድምፅዋ በሲቃ
እንዲተራረሙ ያድርጉ።)
እየተቆራረጠ ነበር።
[ተ. እጃቸውን ያወጣሉ። ምክንያቱም ልጅቷ አቶ መጻፍ (30 ደቂቃ)
ጉልማን ያነጋገረቻቸው በእንባ እየታጠበችና
በለቅሶ ሳግ ድምጿ እየተቆራረጠ ነበር።] ድርሰት መጻፍ (20 ደቂቃ)
(መ. የቀሩትንም ጥያቄዎች በዚሁ ዓይነት በምክንያትና ውጤት የተዋቀረ ድርሰት
እንዲመልሱ ያድርጉ።) መጻፍ
ሥሩ ሥሩ
መ. አሁን ደግሞ ተግባር "2"ን ሥሩ። አቶ መ. ባለፈው ክፍለጊዜ "የመድሎና መገለል
ጉልማን በጣም ሲያሳስባቸው የሰነበተው መንስኤና ውጤት" በሚል ርዕስ ድርሰት
ጉዳይ ምን ነበር? ጽፋችኋል። ዛሬ ደግሞ ባለፈው የጻፋችሁትን
ድርሰት አስተካክላችሁ ትጽፋላችሁ።
[ተ. ሰሞኑን አንዲት በኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ
የተያዘች ልጅ በማኅብረሰቡ ስለደረሰባት መ. በመጀመሪያ በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን፣
መድሎና መገለል፣ ስለነበረችበት ተስፋ በድርሰት መጻፍ ሥር የቀረበውን ሠንጠረዥ
የመቁረጥ ሁኔታ የነገረቻቸው ሲያሳስባቸው በደብተራችሁ አዘጋጁ።
ነበር።] [ተ. ሠንጠረዡን በደብተራቸው ያዘጋጃሉ።]
(መ. በዚህ ዓይነት የቀሩትንም እንዲሠሩ መ. ሠንጠረዡን በመጠቀም ድርሰታችሁን
ያድርጉ።) ገምግሙ።
[ተ. ድርሰታቸውን በሠንጠረዡ ውስጥ
8ኛ ቀን በተዘረዘሩት መሥፈርቶች መሠረት
ይገመግማሉ።]
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች መ. በሠንጠረዡ ውስጥ ለቀረቡት ጥያቄዎች
• ቃላት "አይደለም" የሚል መልስ የሰጣችሁባቸውን
• መጻፍ ነጥቦች መነሻ በማድረግ ድርሰታችሁን
አስተካክሉ።
[ተ. ድርሰታቸውን አስተካክለው ይጽፋሉ።]
ቃላት (10 ደቂቃ) መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደብተራችሁን ተቀያየሩና
በመሥፈርቶቹ መሠረት ተገማገሙ።
በዓረፍተነገር ውስጥ የተሠመረባቸውን
ቃላትና ሐረጋትን መተካት። [ተ. ደብተራቸውን ተቀያይረው ርስበርስ
ይተራረማሉ።]
ሥሩ
መ. "ፍቅርና እንክብካቤ" ከሚለው ምንባብ
(መ. ተማሪዎች ሲገማገሙ እየተዘዋወሩ በአግባቡ
የተሠመረባቸውን ቃላትና ሐረጋት
እየሠሩ መሆናቸውን ይከታተሉ። የተሻሉ
በተመሳሳይ ቃላትና ሐረጋት ተክታችሁ
ሥራዎችን የሠሩ ተማሪዎችን ይምረጡና
ዓረፍተነገሮቹን በደብተራችሁ ጻፉ።
ለክፍሉ ተማሪዎች እንዲያነቡ ያድርጉ።)

መ. በምንባቡ የመጀመሪያ አንቀጽ ውስጥ


የተሠመረበትን ሐረግ በተመሳሳይ ተክታችሁ

፻፺፭ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 195


የአጻጻፍ ሥርዓት (10 ደቂቃ) (መ. ተማሪዎች ሀሳባቸውን በራሳቸው መንገድ
ሊገልጹ ይችላሉ።)
የማመልከቻ ደብዳቤ መጻፍ
ሥሩ ማንበብ (8 ደቂቃ)
መ. ባለፈው ክፍለጊዜ ስለማመልከቻ ደብዳቤ ሥሩ
አጻጻፍ ተምራችኋል። አሁን በመጽሐፋችሁ (መ. ተማሪዎችን በጥንድ ያደራጁ።)
በ3ኛው ሳምንት፣ በ8ኛው ቀን፣ በአጻጻፍ
መ. "ፍቅርና እንክብካቤ" በሚል ርዕስ የቀረበውን
ሥርዓት ሥር ከቀረቡት ርዕሰጉዳዮች አንዱን
ምንባብ አውጡ። የመጀመሪያውን አንቀጽ
መርጣችሁ ለትምህርትቤታችሁ አስተዳደር
ድምፅ ሳታሰሙ ካነበባችሁ በኋላ፣ ምልልሱ
የማመልከቻ ደብዳቤ ጻፉ። (በአማራጭነት
ካለበት ክፍል ስትደርሱ፣ ምልልሱን በግላችሁ
በሌላ ርዕሰጉዳይና ለሌሎች መሥሪያቤቶችም ድምፅ እያሰማችሁ በማንበብ አንድ ጊዜ
የማመልከቻ ደብዳቤ መጻፍ እንደሚችሉ ተለማመዱ።
ይንገሯቸው።)
[ተ. በግላቸው ያነባሉ።]
[ተ. በተማሩት መሠረት የማመልከቻ ደብዳቤ
ይጽፋሉ።] መ. አሁን ከሁለት አንዳችሁ የምልልሱን
ክፍል እንደልጅቷና እንደአቶ ጉልማ
(መ. ተማሪዎች የጻፉትን የማመልከቻ ደብዳቤ ድምፃችሁን በመቀያየር፣ በድምፃችሁ ውስጥ
በመሰብሰብ ቅርጽና ይዘታቸውን በትክክል የገፀባህርያቱ ስሜት እንዲንፀባረቅ በማድረግ
መጻፋቸውን ገምግመው ግብረመልስ ይስጡ።) አንብቡ። አንዳችሁ ስታነቡ አንዳችሁ ደግሞ
በመማሪያ መጽሐፉ በተዘረዘሩት መገምገሚያ
9ኛ ቀን መሥፈርቶች መሠረት ገምግሙ።
(መነሻ ሰዓት ይዘው ማንበብ እንዲጀመሩ
የዕለቱ ትምህርት ይዘቶች ይንገሯቸው።)
• አቀላጥፎ ማንበብ [ተ. አንዳቸው ሲያነቡ፣ አንዳቸው ይገመግማሉ።]
• መናገር (3 ደቂቃ ሲሞላ ማንበባቸውን እንዲያቆሙ
ያድርጉ። በ3 ደቂቃ ያነበቧቸውን ቃላት
• ሰዋስው ብዛት እንዲቆጥሩ ያድርጉ።)
መ. አሁን ደግሞ ስትገመግሙ የነበራችሁ
ተማሪዎች፣ በተራችሁ አንብቡ። ስታነቡ
አቀላጥፎ ማንበብ (10 ደቂቃ) የነበራችሁ ተማሪዎች ደግሞ የጓደኛችሁን
አነባበብ ገምግሙ። (መነሻ ሰዓት ይዘው
ፍቅርና እንክብካቤ ማንበብ እንዲጀምሩ ይንገሯቸው።)
ቅድመንባብ (2 ደቂቃ) [ተ. አንዳቸው ሲያነቡ አንዳቸው ይገመግማሉ።]
ሥሩ (መ. 3 ደቂቃ ሲሞላ ማንበባቸውን እንዲያቆሙ
መ. ዛሬ “ፍቅርና እንክብካቤ” በሚል ርዕስ ያድርጉ። በ3 ደቂቃ ውስጥ ያነበቧቸውን
የቀረበውን ምልልስ ታነባላችሁ። ከዚያ በፊት ቃላት ብዛት እንዲቆጥሩ ያድርጉ።
ግን የምንባቡን ሀሳብ በማስታወስ አንድ ለእያንዳንዱ የመገምገሚያ ጥያቄ ምላሻቸውን
ጥያቄ መልሱ። በወረቀት እንዲያሰፍሩ፣ በተገመገሙበት
መ. "ፍቅርና እንክብካቤ" በሚል ርዕስ ወረቀት ላይም የተገምጋሚዎቹን ስም
ከቀረበው ምንባብ የተረዳችሁትን ቁም ነገር እንዲጽፉ ያድርጉ። ከዚያም ወረቀቶቹን
አስታውሳችሁ ተናገሩ። በመሰብሰብ የተማሪዎችዎን የማንበብ ችሎታ
መሻሻል ይገምግሙ።)
[ተ. በኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ የተያዙ ሰዎችን
ከማግለል ይልቅ ፍቅርና እንክብካቤ መስጠት
ተገቢ መሆኑን ይገልጻል።]

196 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 ፻፺፮


መናገር (20 ደቂቃ) ሰዋስው (10 ደቂቃ)
ሁለት ምንባቦችን እያነፃፀሩ መናገር አወንታዊና አሉታዊ ሐተታ
ሥሩ ዓረፍተነገሮች መመሥረት
(መ. ተማሪዎችን በቡድን ያደራጁ።) ሥሩ
መ. በቡድኑ ውስጥ ከምትገኙ ተማሪዎች መ. ባለፉት ክፍለጊዜያት ስለአወንታዊና አሉታዊ
የተወሰናችሁት "ወይኔ ሰውዬው!" የሚለውን ዓረፍተነገሮች ተምራችኋል። ዛሬ ደግሞ
ምንባብ ግለጡ። ሌሎቻችሁ ደግሞ "ፍቅርና በተማራችሁት መሠረት አምስት አወንታዊና
እንክብካቤ" የሚለውን ምንባብ ግለጡ። አሁን አምስት አሉታዊ ሐተታ ዓረፍተነገሮች
የሁለቱን ምንባቦች ይዘትና ቅርፅ አነፃፅሩ። ትመሠርታላችሁ።

[ተ. "ወይኔ ሰውዬው!" የሚለው ምንባብ የቀረበው [ተ. አወንታዊና አሉታዊ ሐተታ ዓረፍተነገሮች
በስድ ንባብ ትረካ ሲሆን፣ "ፍቅርና እንክብካቤ" ይመሠርታሉ።]
የሚለው ምንባብ ደግሞ በምልልስ ቀርቧል።] (መ. ተማሪዎች ዓረፍተነገሮችን በግላቸው
(ተማሪዎች ግን እነሱ በተረዱት መንገድ ሲመሠርቱ እየተዘዋወሩ ይመልከቱ። ድጋፍ
ሊያነፃፅሩ ስለሚችሉ ሁሉንም ካዳመጡ በኋላ የሚያስፈልጋቸውን አንድ ወይም ሁለት
ግብረ መልስ ይስጡ።) ዓረፍተነገሮች መሥርተው ፍንጭ በመስጠት
መ. አሁን ደግሞ የሁለቱን ምንባቦች ታሪክ ያበረታቷቸው። በመጨረሻም ተማሪዎች
አነፃፅሩ። የመሠረቷቸውን ዓረፍተነገሮች እንዲያቀርቡ
በማድረግ ይገምግሙ።)
[ተ. "ወይኔ ሰውዬው!" የሚለው ምንባብ በኤች.
አይ.ቪ/ኤድስ ምክንያት አንድ ቤተሰብ
አድሎና መገለል ሲደርስበት ያሳያል።
"ፍቅርና እንክብካቤ" ደግሞ መገለል
የደረሰባት ገፀባርይ ተነፍጓት የነበረውን
ፍቅርና እንክብካቤ በማኅበራዊ አገልግሎት
ባለሙያው አማካይነት ስታገኝ ያሳያል።]
(ተማሪዎች በራሳቸው አገላለጽ አብራርተው
ሊናገሩ ይችላሉ።)
መ. በጣም ጥሩ! አሁን ደግሞ በሁለቱ ምንባቦች
ውስጥ ያሉትን ገፀባህርያት አነፃፅሩ።
[ተ."ወይኔ ሰውዬው!" በሚለው ምንባብ ውስጥ
በኤች.አይ.ቪ./ ኤድስ የተያዘው ወንድ
ገፀባህርይ ሲሆን በ"ፍቅርና እንክብካቤ"
ውስጥ ግን ሴት ገፀባህርይ ናት።] (ተማሪዎች
ገፀባህርያቱን ከብዙ አቅጣጫ ማነፃፀር
ይችላሉ።)
(መ. ተማሪዎች ሁለቱን ምንባቦች እያነፃፀሩ
ሲወያዩ እየተዘዋወሩ የንግግራቸውን
ፍሰት፣ እንደ፣ ግን፣ ደግሞ፣ ቢሆንም፣ በሌላ
በኩል…ያሉ አወዳዳሪ የመሸጋገሪያ ቃላት
መጠቀማቸውን ወዘተ. ይገምግሙ።)

፻፺፯ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ምዕራፍ 10 197


ሙዳየቃላት/ሐረጋት

ቃላት ማብራሪያ
ትምህርታዊ ቃላት በመማሪያ መጽሐፍና በዚሁ ዐውድ ወስጥ አገልግሎት የሚሰጡ ቃላት
(በዕለትተዕለት ተግባቦት ያልተዘወተሩ)
ትክክለኛነት ጽሑፍን ያለስህተት ማንበብ

ማጣመር ፊደላትን፣ ቃላትንና/ወይም ቅጥያዎችን ማቀናጀት/ማዋቀር

ገፀባህርይ በአንድ ታሪክ ውስጥ ታሪኩን የሚመሩና የሚከውኑ የታሪኩ


ተሳታፊዎች (ሰዎች/እንስሳት)
አንብቦ መረዳት የጽሑፍን መልዕክት የመገንዘብ ሂደት

የተናባቢ ክትትሎሽ በቋንቋዉ ሥርዓት መሠረት በቃላት ውስጥ የተናባቢዎች ተከታትሎ


መግባት
መረዳት/መተርጐም በጽሁፍ ወይም በንግግር የቀረበን መልዕክት በትክክል መረዳት/
መተርጐም
ምሥርት ቃል በቋንቋዉ ሥርዓት መሠረት ከአንድ ቃል የተፈጠረ ሌላ አዲስ ቃል

ገላጭ ጽሁፍ መረጃ ሰጪ የሆነ የጽሑፍ ዓይነት

አገላለጽ በጽሑፍ ውስጥ የሚገኙትን ገፀባህርያት ንግግር ወይም


ሥርዓተነጥቦች መሠረት አድርጎ ስሜት በሚሰጥ መልክ ማንበብ
አቀላጥፎ ማንበበ ለክፍል ደረጃው በተወሰነ ፍጥነት፣ ትክለኛነትና አገላለጽ ማንበብ

ሥርዓተፆታ በወንዶች ወይም በሴቶች አንጻር እንዲኖራቸው የሚጠበቅ ባህሪ

ዘውግ የጽሑፍ ዓይነት (ተራኪ፣ ገላጭ፣ ተውኔት…)

የሂደት ጥያቄ በማንበብ/በማዳመጥ ሂደት በመካከል ንባብን/ማዳመጥን ተግ አድርጎ


የሚመለስ ጥያቄ
ሰዋስዋዊ ድምፀት የቃላትን፣የሀረግ እና የዓረፍተነገር ትርጉምና ሰዋስዋዊ አገባብ
የሚለውጥ ድምፀት
የትእምርተድምፅ ግንዛቤ ድምፅን ከምልክት ጋር አጣምሮ የመረዳት ዕውቀት

አመራማሪ ጥያቄ መልሱ ሙሉበሙሉ በቀጥታ ከጽሁፉ ውስጥ የማይገኝ፣ ምንባቡንና


የቀደመ ዕውቀትን መሠረት አድርጎ የሚመለስ ጥያቄ
ቅጥያ በዚህ መርሃ ትምህርት መሠረት አዳዲስ ቃላትንም ሆነ የቃላት
ቅርጾችን ለማግኘት በቃላት ላይ የሚገባ ቅንጣት ወይም ፍቺ አዘል
አሃድ
የምንባብ ደረጃ የመማሪያ መጽሐፉ ከተማሪው የማንበብ ደረጃ ጋር መመጣጠኑን
የሚያሳይ ደረጃ
የድምፅ ቃና በንባብም ሆነ በንግግር ወቅት የሚከሰት የድምፅ ከፍታና ዝቅታ

198 አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ሙዳየቃላት ፻፺፰


ቃላት ማብራሪያ
ሥርዓተጽሕፈት ቋንቋን የሚወክል የጽህፈት ዘዴ

የአጻጻፍ ሥርዓት በቃላት ውስጥ የፊደላትን አጠቃቀምን (ፍደላን)፣ ሥርዓተነጥብንና


የመሣሰሉትን የሚመለከት ሥርዓት
ድምጽ የቋንቋ መሠረት የሆነ፣ በአንደበት የሚፈጠር የንግግር ድምጽ

የንግግር ድምጾች ግንዛቤ በንግግር ቃላት ውስጥ በቃል ድምፅን የመለየትና የመረዳት ብቃት

የታሪክ መዋቅር በፈጠራ ሥራ (በልቦለድ፣ በተውኔት…) ውስጥ የታሪክ ቅደም


ተከተል፣ ሴራ
የንባብ ፍጥነት ተማሪዎች በደረጃቸው በተወሰነው መሠረት አንድ ጽሑፍ
የሚያነቡበት ፍጥነት (በደቂቃ ---ቃላት)
ማዘዝ/መምራት እንዴት ማድረግና መሥራት እንደሚቻል ማሳያና ተማሪዎችን
መፈተሽና መገምገም የሚቻልበት መስፈርት
ማገዝ/መርዳት ለተማሪው ተገቢ ድጋፍ ማድረግ (ቀስ በቀስ ግን ድጋፉን መቀነስ)

ወሰንና ተለጣጥቆ በየደረጃው አንድን ትምህርት ወይም ክሂል በምን ያህል መጠንና
በምን ዓይነት ቅደምተከተል እንደምናስተምር የሚያሰይ ዝርዝር
መጻፍ ሀሳብን በጽሑፍ የመግለጽ ብቃት/ ክሂል

መነጠል ቃላትን በፊደል፣ በቀለም፣ በዋና ቃልና/ወይም ቅጥያ ለያይቶ/


ነጥጥሎ የመረዳት ሂደት
ተተኳሪ ቃላት በምዕራፍ ትምህርት ትኵረት የሚሰጣቸው ቃላት

የድምጽና የትእምርት በትእምርቶችና በድምጾች መካከል ያለ ግንኙነት


ግንኙነት
የቃላት ዕውቀት የተማሪዎችን የቃላት ሀብትና የቃላቱን ፍቺ ዕውቀት

የቃላት አገባብ በቋንቋ ሥርዓት መሠረት በመዋቅር ውስጥ ቃላትን በዓረፍተነገር


ውስጥ ማቀናበር
ምንባብ ተኮር ጥያቄዎች መልሳቸው ከተነበበው/ከተደመጠው ምንባብ ውስጥ የሚገኝ ጥያቄዎች

ራስን መከታታያ ብልሃቶች በማንበብ ሂደት ምን ያህል እንደተረዳን የምንከታተልባቸው


ብልሃቶች
ቆም ብሎ ማሰብ በማንበብ ሂደት ተማሪዎች ማንበባቸውን ቆም አድርገው ምን ያህል
እንደተረዱና ወደፊት ምን ሊመጣ እንደሚችል ለመገመት የሚደረግ

፻፺፱ አማርኛ 5ኛ ክፍል የመምህር መምሪያ ሙዳየቃላት 199


200
አማርኛ 5ኛ ክፍል

5ኛ ክፍል
የመምህር መምሪያ

የአማርኛ እንደአፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት


መርሃትምህርት
፪፻
፪፻፩

የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8


አማርኛ 5ኛ ክፍል
የመምህር መምሪያ

5ኛ ክፍል- አንደኛ ወሰነትምህርት


መርሃትምህርት
201

11
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት
202
ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር
ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
ትእምርተድምፃዊ ተማሪዎች ------ ተማሪዎች ------ ተማሪዎች ------
ግንዛቤ ጓደኝነት
ማፍለቅ/ • የተማሯቸውን ቃላት • ቃላትን ለመለየት የተማ • ቃላትን መመስረት፤ ተማሪ ዎች
• በደረጃቸው ውስብስብ •በክፍል ውስጥ የተማሪን የመማር • ሰላምታ
መተርጎም / የፍደላ ህግጋትን ሯቸውን ውስብስብ በሆኑ የቀለም መዋቅሮች የቃላትን ክፍልፋዮች ተጠቅመው ለውጥ ለመምራትና • ታማኝነት
የቃላት ጥናት ይገልጻሉ፤ የቀለም መዋቅሮች ቃላትን ይፃፋሉ፤ አዳዲስ ቃላትን መስረትና መፈደል ለመከታተል ሥርዓታዊ • ተጽእኖ (ጥሩ/መጥፎ
ያጣምራሉ፤ ይለማመዳሉ ወይም የቃላትን ልምምድ ማድረግ፣ ጓደኞች)
• በደረጃቸው
ክፍልፋዮች በመጠቀም አዳዲስ
• ለቃላቱ ተገቢ/ጠቃሚ ውስብስብ የቃላት • ኢመደበኛ ክትትል፤ የትኞቹ
መዋቅሮችን ወደምዕላዶች ቃላትን ይፈጥራሉ፤
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ብልሃቶችን በመጠቀም ልጆች እንደተረዱና የትኞቹ አካባቢያችን


ውስብስብ መዋቅር በመነጣጠ ልና መልሶ • ቃላትን ማሰስ፤ ተማሪዎች የቀረበ ደግሞ ተጨማሪ ድጋፍ
በማገጣጠም ቃላትን • ብክለት (የአየር/የውሃ)
ያላቸውን ቃላት ያነባሉ፤ ይጽፋሉ፤ ውን ትምህርት በጥሞና እንደሚያስፈልጋቸው በክፍል
• ቆሻሻ
በመከታተል የታላሚ ቃላትን ውስጥ በመዘዋወር
• ኢተዘውታሪ ቃላትን • ኢተዘውታሪ ቃላትን • የአካባቢ ጥበቃ
ወይም ምዕላዶችን ምሳሌዎች ይከታተላሉ፡፡
ለማንበብ የሥነ ምዕላዳዊ ለመጻፍ የሥነ ምላዳዊ
በቀረበው ትምህርት ውስጥ (ጥቅምና ጉዳት)
ፍቺን (የምሥርታና/ወይም ፍቺን (የምሥርታና/ወይም
ከሚገኙ ቃላት ፈልገው ያወጣሉ፤ • ተግባር መር ክለሳ፤ ተማሪዎች
የርባታ) እውቀታቸውን የርባታ) እውቀታቸውን ለጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ፤
የመምህር መምሪያ

ይጠቀማሉ፤ ይጠቀማሉ፤ • መምረጥ (ማወዳደር)፤ ተማሪዎች ልማድ


ከቀደመው ትምህርት ያገኙትን
የቃላትን መዋቅር ወይም የፍደላ • የአካባቢ ልማዶች
ድምፀታዊነት ልምድ ይጋራሉ፡፡ መምህራን
ውቅሮችን ያወዳድራሉ ፡፡ ይህን መረጃ የቀጣዩን (የወቅቱን) (ለምሳሌ የቡና
ይህ የሚከተሉትን ሊያካትት ትምህርት አቅጣጫ ለመወሰን ሥነሥርዓት፣ የቤተሰብ
ይችላል፤ ይጠቀሙበታል፡፡ ግንኙነት፣
• ቃለትን በመዋቅራቸው ያለዕድሜ ጋብቻ)
ይዘረዝራሉ፤ ያደራጃሉ፣ • ጠቃሚና ጎጂ ልማዳዊ
መርሃትምህርት

ድርጊቶች

አቀላጥፎ ማንበብ ቃላዊ ማንበብ መጻፍ ናሙና የማስተማሪያ/ ናሙና የምዘና ስልቶች የትራፊክ ደኅንነት
ተማሪዎች… ተማሪዎች… ተማሪዎች… መማሪያ ስልቶች • የመንገድ ደህንነት
በትክክል ማንበብ •ለደረጃው የተመደበን • ለደረጃው የተመደቡትን ሞዴሎች፣ ከደረጃቸው ላቅ ያሉ መጻ • ኢመደበኛ ክትትል ፤መምህራኑ (ለምሳሌ በእግረኛ
ጽሑፍ በ95% በትክ ቃላት በ90% በትክ ሕፍትን በጎልማሶች የንባብ አቀላ ለተማሪዎቹ የጽሕፈት ተግባር ለተ መንገድ መሄድ፣ አን
ክል ያነብባሉ፤ ክል ይጽፋሉ፤ ጥፎ ደረጃ ሞዴልነት በመስተጋብራዊ ማሪዎቹ ይሰጣሉ፤ በክፍልም ውስጥ ደአካባቢው ሁኔታ
ንባብ ማንበብ፣ በመዘዋወር ኢመደበኛ በሆነ መልኩ በዜብራ ላይ ማቋረጥ፣
ቁጥጥር ያደርጋሉ፤ የትራፊክ መብራት
መጠበቅ..)
12
፪፻፪
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 6ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት
፪፻፫

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
• ለደረጃውና ለቋንቋው • ከመምሀራቸው ጋር ወይም ከሌሎች • ጠቋሚዎችን መመልከት፤ ማቀረብ (አቅርቦት፤) ተማሪዎች • የመኪና አዳጋ
ተገቢ የሆነውን የንባብ ጓደኞቻቸው ጋር ወይም በግል የመፃፍ አገላለጾችን ለማዳበር መምህራኑ ያላቸውን የአገላለጽ ችሎታና ምክንያቶቹና የመ
ፍጥነት ያጠናክራሉ፤ ክለሳ ይሰራሉ፤ ያዘጋጃሉ፤ የሥርዓተነጥቦችን ተግባር (ለደረጃቸው ትክክለኛነት ለመምህራኑ ወይም ከላከያ መንገዶቹ
በተመደበው መሠረት) እና እንዴት ለክፍሉ በተግባር ያሳያሉ፤. • የመጀመሪየ
• ለደረጃው የተመደበን • የተለያዩ የመፃፍ ግቦችን (ሁነቶችን
ጽሑፍ በተገቢ የሐረጋት በጥንቃቄ መግለጽ፣ ስሜትን በደንብ እነዚህ ምልክቶች በአገላለጾችና የህክምና ርዳታና
• ተማሪውን መከታተል ፤በክፍል
ክፍፍል ያነብባሉ፤ ማስተላለፍ፣ ታሪኮች በጽሑፍ መግለጽ፣ በአነባበብ ቅላፄዎች ላይ ተጽእኖ ውስጥ ሥርዓታዊ ልምምድ በድንገተኛ አደጋ
መመሪያዎችን መስጠት) ይለማመዳሉ፤ እንደሚያሳድሩ ማሳየት ማድረግ፤ ጊዜ የሚወሰዱ
• ለደረጃው የተመደቡትን ይጠበቅባቸዋል፤ እርምጃዎች
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ጽሑፎች በዝምታ/ • የቢጤ ግምገማ፤ አንድ የጽሕፈት የግል ንጽሕና


በጥሞና ማንበብ • በሰዓት የተገደቡ ተደጋጋሚ ንባቦች፤
ተግባር ካለቀ በኋላ ተማሪዎች • የአካባቢ ጽዳት
ይጀምራሉ፤ ተማሪዎች አጫጭር ምንባብ ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን
ደጋግመው ያነብባሉ፤ በእያንዳንዱ የግልና የአካባቢ
የማንበብ • አንድን ሃሳብ • ለደረጃው በተዘጋጀው • አንድን ሃሳብ/አስተያየት ለመደገፍ እንዲለዋወጡ በማድረግ
ንባባቸውም ንባቡን የጨረሱበትን ንጽሕና
ፍጥነት /አስተያየት ለመደገፍ ጽሑፍ ውስጥ ወይም ለመቃወም ተጠየቃዊና መምህሩ በሚሰጣቸው መመሪያ
ወይም ለመቃወም በሥርዓተነጥብ ሊረጋገጡ የሚችሉ እውነታዎችን ሰዓት በመያዝ፣ የማንበብ ፍጥነታቸውን መሠረት እንዲተራረሙ
ተጠየቃዊና ሊረጋገጡ ይጠቀማሉ፤ ይጠቀማሉ፤ እየመዘገቡ ይከታተላሉ፤ ከተደረገበኋላ፣ መምህሩ
የመምህር መምሪያ

የሚችሉ እውነታዎችን ወረቀታቸውን


• ሥርዓቱን በመጠበቅ፣ • ሀረግ በሀረግ ማንበብ፤ መምህራኑ /ደብተራቸውን ሰብስበው
ይጠቀማሉ፤ ሀረግ በሀረግ ማንበብን ያበረታታሉ፤
ሥርዓተነጥቦችን በአግባቡ ክንውናቸውን ይገመግማሉ፤
በመጠቀም ከአንድ አንቀጽ በላይ በዚህ አቀራረብ መምህራኑ የተዘወተሩ • የቡድን ሥራ፤ መምህሩ
ይጽፋሉ፤ ጽሑፎችን በተገቢ ሐረጎች በመከፋፈል በአነስተኛ ቡድን የሚሠራ
ማለትም በዓረፍተነገሮቹ ውስጥ የቤት ሥራ ይሰጣሉ፤ ሁሉም
• ከምንባቡ ይዘት ጋር የተዛመዱ ሁለት በሚገኙት ሐረጎች (ሐረጎችና ጥገኛ የቡድኑ አባላት
መርሃትምህርት

ወይም ሦስት አንቀጾችን ይጽፋሉ፤ ሐረጎች) ላይ በማተኮርና መሳተፋቸውንም ይቆ


• በሚሰጣቸው የአጻጻፍ ማዕቀፍ ሥርዓተነጥቦችን እንደንባብ ተግታ ጣጠራሉ፡፡ ለእያንዳንዱ
መሠረትና ዝርዝር መግለጫዎችን ምልክቶች በመውሰድ እንዴት የቡድን አባል የተወሰነ ሥራ
በመጠቀም ስለአንድ ታሪክ ወይም እንደሚነበብ ያሳያሉ፡፡ መስጠት ሁሉም አባላት
መሥራታቸውን ለማረጋገጥ
ሁነት ሁለት ወይም ሦስት አንቀጾችን • ቅድመ መፃፍ ተግባራት፤ ከመፃፍ ይጠቅማል፡፡ ቡድኑ ሥራው
ይጽፋሉ፤ በፊት ያሉ ተግባራት፣ ለምሳሌ ሥዕል፣ ሲጠናቀቅ ውጤት/ ነጥብ
• የተማሩትን ክንዋኔዎች የሚያመለከቱ የታሪክ ካርታ፣ ወዘተ. ሃሳብን ሊሰጠው ይችላል፡፡
ዘገባዎቸን መጻፍ ይጀምራሉ፤ በማበዳበርና በአግባቡ በማደራጀት (ማስታወሻ፡ -የቡደን ሥራ
ረገድ ያግዛሉ : በምንም መንገድ የግል ሥራን
ሊተካ አይችልም፡፡)

13
203
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 8ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት
204
ቃላዊ ክሂሎች /
ማንበብ መፃፍ ናሙና የመማር ማስተማር ስልቶች ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
መናገርና ማዳመጥ/
• ሂደታዊ ልምምድ የመፃፍ ሞዴል፤ ተራ በተራ መናገር፤
ሰዋስው • በንግግር ውስጥ የተጻፈውና • በጽሑፍ ውስጥ የተጸውዖና • በጽሕፈት ውስጥ የተጸውዖና የወል በሂደታዊ ልምምድ ኃላፊነትን ከመምህራኑ ተማሪዎች የማንበብ
የወል ስሞችን መግለጽና የወል ስሞችን መግለጽና መለየት ስሞችን መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ወደተማሪዎቹ በማሸሸጋገር መልክ የመጻፍ ፍጥነታቸውንና
መለየት ይጀምራሉ፡፡ ይጀ ምራሉ፡፡ (ለቋንቋው የሚ (የተዘወተሩ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ ብልሃቶችን በግልጽ ይማራሉ፤ ከመምህራኑ ትክክለኛነታቸውን
ተዘውታሪ የመደብ፣ የቁጥር፣ ሠራ ከሆነም የተዘወተሩ የመደብ፣ የሙያ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ሞዴልነት በመጀመር ተማሪዎቹ ለመወሰን አንዳቸው ላንዳቸው
የጾታ፣ የሙያ ወዘተ. ሰዋስዋዊ የቁጥር፣ የጾታ፣የሙያ ወዘተ. ሰዋስ ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) እንዲለማመዱ ማድረግ፣ ከዚያም በሂደት አንቀጽ ሊያነብቡ ይችላሉ፡
ስምምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) ዋዊ ስምምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) ተማሪዎቹ ብልሃቶቹን እንዲመርጡና ወይም ለመፃፍ የቤትሥራ
• ቀላል ግሶችን በጽሕፈት በአግባቡ እንዲተገብሩ እድል ይሰጣቸዋል፤ ሀሳቦችን ሊወያዩ ይችላሉ፡፡
አማርኛ 5ኛ ክፍል

• በንግግር ውስጥ ቀላል ግሶችን • በጽሑፍ ውስጥ ቀላል ግሶችን መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ተዘውታሪ መምህሩ በክፍሉ ውስጥ
መግለጽና መለየት ይጀምራሉ፡፡ መግለጽና መለየት ይጀምራሉ፡፡ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. • ተግባር መር መፃፍ፤ መምሀራኑ ለአንድ በመዘዋወር ሂደቱን
( የተዘወተሩ የመደብ፣ የቁጥር፣ (የተዘወተሩ የመደብ፣ የቁጥር፣ ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ተግባራዊ የተወሰነ የመፃፍ ልምምድ ተማሪዎቹ ይከታተላሉ፡፡
የጾታ፣ የሙያ ወዘተ. ሰዋስዋዊ የጾታ፣ የሙያ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስም ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) አሟልተው የሚጽፉባቸው ወይም እነሱን
ስምምነቶችን ይገነዘ ባሉ፡፡) ምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡)
• በመፃፍ ውስጥ ተዘውታሪ ቅጽሎች ተከትለው አንድ ጽሑፍ ለመጻፍ
• በንግግር ውስጥ ተዘውታሪ • በጽሑፍ ውስጥ ተዘውታሪ መጠቀም ጀምራሉ፡፡ (የተዘወተሩ የሚረዷቸው ቀድመው የተዘጋጁ
መነሻዎችን (ቴምፕሌቶችን)፣ ናሙና
የመምህር መምሪያ

ቅጽሎችን መግለጽና መለየት ቅጽሎች መግለጽና መለየት የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ የሙያ
ይጀምራሉ፡፡ (የተዘወተሩ ይጀምራሉ፡፡ የተዘወተሩ የመደብ፣ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ቅጾች፣ ወይም መምሪያዎች (ለምሳሌ
የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ የሙያ የቁጥር፣ የጾታ፣ የሙያ ወዘተ. ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) የዓፍተነገር መጀመሪያዎችን፣ የዘገባ
ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) ቅጾችን ወዘተ.) ያቀርባሉ፤
• በመፃፍ ውስጥ የተዘወተሩ ቁጥ
ይገነዘ ባሉ፡፡) • አሳታፊ የመፀፍ ማኅበረሰብ መፍጠር፤
ሮችን መጠቀም ይጀምራሉ፡፡
• በንግግር ውስጥ ተዘውታሪ • በጽሑፍ ውስጥ ተዘውታሪ (የተዘወተሩ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ - መምህሩ ሞዴል ጽሑፍ ጽፈው ለተማሪ
ቁጥሮችን መግለጽና መለየት ቁጥሮችን መግለጽና የሙያ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ዎቹ በማካ ፈል፤
መርሃትምህርት

ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ መለየት ይጀምራሉ፡፡ (የተዘወተሩ ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) - በመፃፍ የቤትሥራ ሂደት ለተማሪዎቹ
የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ የሙያ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ፣ የሙያ አማራጮችን በመስጠት፣
ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን
- ተማሪዎቹ እንደጸሐፊ እንዲተባበሩ በማ
ይገነዘባሉ፡፡). ይገነዘባሉ፡፡)
በረታታት፣
- ለተማሪዎቹ ምጋቤ-ምላሽ እንዲሰጡና
እንዲቀበሉ ዕድል በመስጠት፤

14
፪፻፬
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 6ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት
፪፻፭

ቃላዊ ክሂሎች / ናሙና የመማር ማስተማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
መናገርና ማዳመጥ/ ስልቶች
የቃላት • ዕውቀትን ለማግኘት፣ • በግል ንባብ ሂደት • በተለያዩ ዐውዶች ውስጥ • ተማሪዎች ቁልፍ ቃላትን መጠቀምንና • የመውጫ ካርድ፤ ተማሪዎች ክፍሉን
አውቀትን ለማሳደግና አገላለጽን አዳዲስ ቃላትን ለማወቅ ሲጽፉ የተማሯቸውን አዳዲስ በንግግር ተራክቦ ውስጥ መሳተፍን ለቅቀው ሲወጡ ለመምህራቸው ሰጥተው
ማስፋትና ለማጥራት የተማሯቸውን ጽሑፋዊ ፍንጮችን ቃላት ይጠቀማሉ፤ እንዲለማመዱ በርካታ ዕድሎችን ማመቻቸት፤ ወይም በር ላይ አስቀምጠዋቸው የሚሄዱ
መጠቀም አዳዲስ ቃላትን
በንግግራቸው ውስጥ ይጠቀማሉ፤ • ዕውቀትን ለማግኘት፣ • አዳዲስ ቃላትንና አገላለጾችን እንዲጠቀሙ ትንንሽ ወረቀቶች ናቸው፤ በእነዚህም
ይጠቀማሉ፤ • አዳዲስ ቃላትን ለማሳደግና አገላለጽን በርካታ ዕድሎችን ማመቻቸት፤ ወረቀቶች ላይ ተማሪዎች ስማቸውንና
• በመስተጋብራዊ ንባብ፣ ለማወቅና ፍቺያቸውን ለማጥራት የተማሯቸውን - ለመናገር ፍቃደኛ እንዲሆኑ ምቹ የክፍል ለተሰጧቸው ጥያቄዎችና የቃላት
ለመረዳት አጋዥ አዳዲስ ቃላትን ውስጥ ድባብ መፍጠር መልመጃዎች ምላሽ ይጽፉባቸዋል፡፡
አማርኛ 5ኛ ክፍል

በንግግር፣ በአቅጣጫ ማማሳከሪያዎችን


ጠቋሚዎች ወዘተ. በጽሑፋቸው ውሰጥ - ብዙ ጊዜ ከ“አዎ-አይደለም” ጥያቄዎች ይልቅ • ምር ክለሳ፤ተማሪዎች ለጥያቄዎች ምላሽ
(ለምሳሌ፡-
የቀረበን ጽሑፍ ፍቺ መዝገበቃላት፣ ሰዎችን፣ ይጠቀማሉ፤ ክፍት ጥያቄዎችን መጠየቅ፣ ይሰጣሉ፤ ባለፈው ስለተማሩት ትምህርት
ለመረዳት መዝገበቃላት መጣጥፎችን) - በአንድ ጭብጥ ላይ ለመወያየት፣ ለመጻፍ፣ ልምድ ይለዋወጣሉ፤ መምህሩ ይህን
ይጠቀማሉ፤ ይጠቀማሉ፤ ለክፍል ለማቅረብ ቡድኖችን (ከ4-5 የሚያደርጉት የዕለቱን ትምህርት አቅጣጫ
ትምህርታዊ • በቋንቋ በሰፊ ዐውድ
አባላት ያሉባቸው) መመስረት፤ ለመወሰን መረጃ ለማግኘት ነው፡፡
• ለደረጃው የተመደቡ • ጽንሰሃሳቦችን ለመወከል/
ቃላት አማካይነት የተማሯቸውን ትምህርታዊ ቃላትን ለመግለጽ በጽሑፋቸው
• ምልከታዎች፤. የእለት ማስታወሻዎች፤
የመምህር መምሪያ

አዳዲስ ቃላት በንግግራቸው ያነብባሉ፤ ውስጥ አዳዲስ ቃላትን • ቃላትን ማሰስ፤ ተማሪዎች በትምህርቱ ሂደት
ውስጥ ይጠቀማሉ፤ ይጠቀማሉ፤ በዓረፍነገር ውስጥ ወይም በሥዕል የተወከሉ ተማሪዎቹ በቡድን ወይም በግል ሲሰሩ
• ፍቺን ፈልፍሎ • ወጥ በሆነ ጽሑፍ ውስጥ የቃላት ምሳሌዎችንና በሌሎች ቃላት በትምህርቱ ሂደት የጻፏቸው፣ ወይም ደግሞ
በመረዳት ሂደት አዳዲስ የተማሯቸውን አዳዲስ ውስጥም የቃላቱን ክፍሎች (ምዕላዶችን) ትምህርቱ ከተጠናቀቀ በኋላ የሚጽፏቸው
ቃላትን ይማራሉ ቃላት ይጠቀማሉ፤ ለማግኘት አተኩረው እንዲከታተሉ አጫጭር ማስታወሻዎች፣
(ለምሳሌ፡-በቋንቋ ከሰፊ • የደረጃውን ትምህርታዊ ማድረግ፤ • አቅርቦት፤ ተማሪዎች የቃላት
ዐውድ፣ ከራዲዮ መር ቃላት ይጽፋሉ፤ • የግል ንባብ እድሎች/አጋጣሚዎች፤ የግል ዕድገታቸውን ለመምህራኑ ወይም ለክፍሉ
መርሃትምህርት

ሐግብር ወዘተ.) • የቃላትን አመሠራረት፣ ንባብ ለተማሪዎች በተያያዘ ጽሑፍ ውስጥ የሚያሳዩበት ዕድል አላቸው፡፡
• የደረጃውን ትምህርታዊ ፍደላና ፍቺ ለማረጋገጥ አዳዲስ ቃላትን እንዲያነቡና የንባብ ብልሃታቸ • የቢጤ ግምገማ፤ አንድ የጽሕፈት
ቃላት ይጠቀማሉ፤ መዝገበቃላትን ወይም የቃላት ውን እንዲያዳብሩ ዕድሎችን ይሰጣል፤ ተግባር ካለቀ በኋላ ተማረዎች ወረቀታቸውን
ዝርዝሮችን ይጠቀማሉ፤ /ደብተራቸውን እንዲለዋወጡ በማድረግ
• ቃላት መልበስ፤ በትናንሽ ካርዶች ወይም በመምህሩ በሚሰጣቸው መመሪያ መሠረት
ወረቀቶች ላይ የሚማሯቸው ቃላት ይጻፋሉ፤ እንዲተራረሙ ከተደረገ በኋላ፣ መምህሩ
እነዚህም በዕለቱ በልብሳቸው ላይ አያይዘው ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን ሰብስበው
ይውላሉ፤ በዚህም በንግግርም ሆነ በጽሑፍ ክንውናቸውን ይገመግማሉ፤
ወስጥ እንዚህን ቃላት ለመጠቀም ይበረታታሉ፡፡

15
205
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 8ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት
206
ቃላዊ ክሂሎች / ናሙና የመማር
ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
አንብቦ • በመስተጋብራዊ ንባብ • ያነበቡትን ለደረጃው የቀረበን • በክፍል ደረጃው ጽሑፍ • በተደጋጋሚ በሚመቻቹ እድሎች • የመውጫ ካርድ፤
የመረዳት የተነበበን ጸሑፍ አሳጥረው ጽሑፍ አሳጥረው ያቀርባሉ፤ ውስጥ የቀረቡ ሀሳቦችን ተጠቅሞ የተለያዩ ዘውጎችን ማንበብ ተማሪዎች ክፍሉን ለቅቀው
ብልሃቶችን ይናገራሉ፤ ለማደራጀት ሥዕላዊ የሀሳብ ዳራዊ ዕውቀትን ለማዳበርና በተዘወዋሪ ሲወጡ ለመምህራቸው ሰጥተው
• ያነበቡትን ለደረጃው የቀረበን
ማበልጸግ አደራጃጀቶችን ይጠቀማሉ፤ ጽሕፈትን ለማሻሻል ይጠቅማል፤ ወይም በርላይ አስቀምጠው
• በመስተጋብራዊ ንባብ ጽሑፍ ይገመግማሉ፤
• ኢመደበኛ ክትትል፤ ተማሪዎች የሚሄዷቸው ትንንሽ ወረቀቶች
የተነበበን ጸሑፍ ይገመግማሉ፤ • የቃላትን አመሠራረት፣
• ለክፍል ደረጃው የቀረበን ጽሑፍ በሚያነቡበት ወቅት ያልተረዷቸውን ናቸው፤ በእነዚህም ወረቀቶች
ፍደላና ፍቺ ለማረጋገጥ
• በመስተጋብራዊ ንባብ ከቀደመ ዕውቀታቸው፣ ልምድ እና ሌላ ቃላትና ዕሳቤዎች ከንባብ በኋላ ላይ ተማሪዎች ስማቸውንና
መዝገበቃላትን ወይም የቃላት
የተነበበን ጸሑፍ ከራሳቸው ጋር ጽሑፍ ጋር ያዛምዳሉ፤ እንዲወያዩባቸው ተከታለው ማስታወሻ ለተሰጧቸው ጥያቄዎችና
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ዝርዝሮችን ይጠቀማሉ፤
ያዛምዳሉ፤ እንዲይዙ መጠየቅ፤ የቃላት መልመጃ ዎች ምላሽ
• ለቀረበላቸው የጽሑፍ ዓይነትና
የንባብ ተግባር ተስማሚ የሆነ የአንብቦ • ማብራሪያ፤ ባነበቧቸው ጽሑፎች ይጽፉባቸዋል፡፡
መረዳት ብልሃት መርጠው ውስጥ ግልጽ ባልሆኑ (በሚያምታቱ) • ምር ክለሳ፤ ተማሪዋች ለጥያ
ይጠቀማሉ፤ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ እንዲጠይቁ ቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ፤ ባለፈው
ተማሪዎችን ማበረታታት፤ ስለተማሩት ትምህርት ልምድ
• ለክፍል ደረጃው የቀረበውን ጽሑፍ • የጥያቄና መልስ ተዛምዶዎች፤ የንባብ ይለዋወጣሉ፤ መምህሩ ይህን
መረዳታቸውን ለማረጋገጥ ራስን ጥያቄዎችን መለጠፍ፣ የሚከተሉትን የሚያደርጉት የዕለቱን ትምህርት
የመምህር መምሪያ

የመመዘን ብልሃታቸውን መጠቀም አራት ዓይነት ጥያቄዎችን ማካተት፤ አቅጣጫ ለመወሰን መረጃ
ይቀጥላሉ፤ - መልሱ እዚያው፤ (የጥያቄው መልስ ለማግኘት ነው፡፡
መረጃዎችን • ስለአንድ ርዕሰጉዳዩ • ለደረጃው የተመረጡ • ከክፍል ደረጃው ቻርቶች፣ እዚያው እተወሰነ ዓረፍነገር ውስጥ
• ተነሺ ካርዶች፤ ለተለያዩ
መለየት አስተያየት ሲሰጡ ሠንጠረዦችን፣ ካርታዎችን፣ ቻርቶችን ሠንጠረዦች፣ ግራፎች የሚገኝ) ጥያቄዎች ተማሪዎች የተለያዩ
(ከሁሉም የመሸጋገሪያ/ አያያዥ ስለርዕሰ ጉዳዩ ለማወቅ/ለመማር በመውሰድ የተጓደሉ - ማሰብና መመራመር፤ (መልሱ ቀለሞች ያሏቸውን ካርዶች
የጽሑፍ ቃላትን/ሐረጋት ይተረጉማሉ (ፈልገው መረጃ መረጃዎችን ያሟላሉ፤ በጽ ሑፉ ውስጥ የሚገኝ ግን ደግሞ በማንሳት ምላሽ የሚሠጡበት
ዓይነቶች) ይጠቀማሉ፤ ያወጣሉ)፡፡ • ጽሑፍ በሚጽፉበት ጊዜ
መርሃትምህርት

የሚ ፈለገው መረጃ ከአንድ ዓረፍተ (ለምሳሌ፡ - እውነት/ሀሰት፣


ርዕሶችና፣ ስያሜዎችንና ነገር በላይ በሆነ የጽሑፉ አካል ውስጥ እስማማለሁ/ አልስማማም)
• ጽሑፍን ለመረዳት ምልክቶችን፣
የግርጌ መግለጫዎችን የሚገኝ)
የግርጌ መግለጫዎችን፣ ስያሜዎችን
መጠቀም ይጀምራሉ፤
ያነብባሉ፤ - መልሱ ከራሴ፤ (መልሱ የሚገኘው
• ጽሑፍ በሚጽፉበት ጊዜ
ከአንባቢው (ከተማሪው) ከራሱ
• ለደረጃው የተመረጠን ጽሑፍ የተማሯቸውን ምዕላዶች፣
ዕውቀት የሚገኝ)
ለመረዳት ያግዝ ዘንድ የጽሑፍን መሸጋገሪያ፣ አያያዥ
- ፀሑፉና እኔ፤ (የጥያቄው መልስ
መዋቅር ይጠቀማሉ፤ ቃላትና ሐረጋት
ከአንባቢው ዳራዊ ዕውቀትና ከጽሑፉ
ይጠቀማሉ፡፡
በማውጣጣት የሚገኝ)

16
፪፻፮
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 6ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች /መናገርና ናሙና የመማር ማስተማር


፪፻፯

ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች


ማዳመጥ/ ስልቶች
• የጽሑፍ መዋቅር፤ ጽሑፉን • ኢመደበኛ ቁጥጥር፤ መምህራኑ
ተራኪ ጽሑፍን • በመስተጋብራዊ ንባብ ሂደት • ለደረጃው በተመረጡ አጭር • ጽሑፍን መሠረት ለመረዳት እንዴት ርዕሶችን፣ የግርጌ በክፍል ውስጥ በመዘዋወር የትኛቹ
መረዳት ታሪኩን ገጸባሕርያት፣ መቼት፣ ልቦለዶች ውስጥ የልቦለድን ያደረጉ ጥያቄዎች አንቀጽ መግለጫዎችን መጠቀም ተማሪዎች ተጨማሪ ድጋፍ
ሁነቶች ይለያሉ፤ መዋቅር አላባውያንን (መግቢያ፣ በመጻፍ ይመልሉ፤ እንደሚቻል በግልጽ መመሪያ እንደሚያስፈልጋቸውና
• በመስተጋብራዊ ንባብ መካከልና መጨረሻ) ይገነዘባሉ፤ • አመራማሪ ጥያቄዎችን መስጠት፤ እንደማያስፈልጋ ቸው ኢመደበኛ
በተነበበው ጽሑፍ ላይ • በደረጃው ጽሑፍ ውስጥ በተገለጸው አንቀጽ በመጻፍ በሆነ መልኩ ቁጥጥር ያደርጋሉ፤
• ሥዕላዊ የሀሳብ አደረጃጀቶች፤
በተገለጸው መሠረት ቀጥተኛ መሠረት ቀጥተኛ ጥያቄዎችን ይመሳሉ፤ ይመልሳሉ፤ እነዚህ ከንባብ በፊት፣ በንባብ ጊዜና • የቢጤ ግምገማ፤ አንድ የጽሕፈት
ጥያቄዎችን ይመልሳሉ፤ • በደረጃው ጽሑፍ በተገለጸው ከንባብ በኋላ መጠቀም፤ ሥዕላዊ ተግባር ካለቀ በኋላ ተማረዎች
አማርኛ 5ኛ ክፍል

• የፈጠራ ሥራ የሆኑትንና መረጃና ዳራዊ እውቀትን መሠረት የሀሳብ አደረጃጀቶች (ለምሳሌ፡- ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን
ያልሆኑትን (ኢልቦለዶችን) በማድረግ የሚመለሱ አመራማሪ • ለጅምር አንቀጽ ተገቢ
ማጠቃለያ ይጽፋሉ፤ የመረጃ ድሮች፣ ማወዳደርና ማነ እንዲለዋወጡ በማድረግ በመምህሩ
መለየት ይጀምራሉ፤ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ፤ ጻጸር፣ ቻርቶችን ማነጻጸር፣ በሚሰጣቸው መመሪያ መሠረት
• የፈጠራ ሥራ የሆኑትንና ያልሆኑትን መዋቅርን መንደፍ) መረጃዎችን እንዲተራረሙ ከተደረገ በኋላ፣
(ኢልቦለዶችን) መለየት ይጀምራሉ፤ ሊታይ በሚችል መልኩ ማደራጅት፤ መምህሩ ወረቀታቸውን /
ደብተራቸውን ሰብስበው
• የገጸባሕርይ መለያ፤ በአንድ ታሪክ ክንውናቸውን ይገመግማሉ፤
የመምህር መምሪያ

ውስጥ የሚገኙ ገጸባሕሪያትን


አስረጂ • የክፍል ደረጃውን ጽሑፍ • ለደረጃው የተመደበን ባለአንድ ገጽ • በተሰጣቸው ማዕቀፍ ለመረዳት ያግዛል፡፡ • የቡድን ሥራ፤ መምህሩ በአነስተኛ
ጽሑፎችን በቃል ይገመግማሉ፤ ጽሁፍ ያነባሉ፤ መሠረት ሁለት የተለያዩ - አምስቱ መጠይቆች (መጠይቅ ቡድን የሚሠራ የቤት ሥራ ይሰጣሉ፤
መረዳት • ተዘውታሪ ገላጭ ጽሑፎችን ጽሑፎችን ተውላጠስሞች)፤ ያለውን ሁነት ሁሉም የቡድኑ አባላት መሳተፋቸው
የጽሑፍ መዋቅር መለየት ይዘትበማወዳደር አንቀጽ (ማን፣ ምን፣ የት፣ መቼ፣ ለምን) ንም ይቆጣጠራሉ፡፡ ለእያንዳንዱ
ይጀምራሉ፤ መጻፍ ይጀምራሉ፤ ለመረዳት ያግዛሉ፤ የቡድን አባል የተወሰነ ሥራ መስጠት
መርሃትምህርት

• በሁለት የደረጃው ጽሑፎች • በተሰጣቸው ማዕቀፍ - ምን እንደተማሩ ማወቅ፤ ስለርዕሰ ሁሉም አባላት መሥራታቸውን
ላይ ይወያያሉ፤ መሠረት መረጃ አቀባይ ጉዳዩ ያወቁትን ለመጋራት ለማረጋገጥ ይጠቅማል፡፡ ቡድኑ
ያወዳድሯቸዋልም፤ ገላጭ ጽሑፎችን መጻፍ ያስችላል፤ ከዚያም ምን መማር ሥራው ሲጠናቀቅ ውጤት/ ነጥብ
• ምክንያትንና ውጤትን ይጀምራሉ፤ እንደፈለጉ ሊጋሩ ይችላሉ፤ ሊሰጠው ይችላል፡፡ (ማስታወሻ፡-
የሚመለከቱ ጥያቄዎችን • በተሰጣቸው ማዕቀፍ በመጨረሻም የተማሩትን የቡደን ሥራ በምንም መንገድ የግል
መመለስ ይጀምራሉ፤ መሠረት ሁለት የደረጃውን ይከልሳሉ፡፡ ሥራን ሊተካ አይችልም፡፡)
ጽሑፎች የሚያወዳድር
አጭር ጽሑፍ መጻፍ

17
207
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 8ኛ ክፍል‑ 1ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች /መናገርና ናሙና የመማር ማስተማር


208

ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች


ማዳመጥ/ ስልቶች
የሥነጽሐፍ • ልማዳዊ ታሪኮችን አዳምጠው • ልማዳዊ ታሪኮችን አንብበው • የዋና ሀሳብ ቻርት፤ የጽሑፉ ሀሳብ • በተራ መናገር፤ ተማሪዎች
ዘውጎችና የተሰማቸውን ይመልሳሉ፤ የተሰማቸውን ይመልሳሉ፤ ስለምን ነበር? ዝርዝሮቹ ምን ነበሩ? አጠገባቸው ካለ/ች (ካሉ)
አላባውያን • የመዋቅር ምስል፤ የታሪኩን ዋና ተማሪ/ዎች ጋር ምላሻቸውንና
• ታሪካዊ የፈጠራ ሥራዎችን አንብበው
ሀሳብ ለመመዝገብ፤ ሀሳባቸውን ይጋራሉ፤ መምህሩ
የተሰማቸውን ይመልሳሉ፤
• ማወዳደርና ማነጻጸር (የቬን ምስል) በክፍሉ ውስጥ በመዘዋወር ሂደቱን
• አፈታሪኮችን አንብበው የተሰማቸውን ይከታተላሉ፡፡
ሁለት ነገሮችን ለማወዳደርና
ይመልሳሉ፤ ለማነጻጻር (መጻሕፍትን፣ • ዞሮ መጥ ግለሰባዊ እርማት፤
• የሥነጽሑፍን አላባውያን ይገነዘባሉ፤ ገጸባሕርያትን፣ ወቅቶችን፣
አማርኛ 5ኛ ክፍል

በሰፋፊ ክፍሎች ውስጥ


ተዋስኦ (ምልልስ) ሥራዎችን) የሚዘዋወር አንድሰው (ተማሪ)
• የሥነጽሑፍን አላባውያን ይገነዘባሉ፤ • የምክንያትና የውጤት ቻርት በመዘዋወር የጽሕፈት ሥራዎች
ትረካ የሚገመገሙበት ሁኔታ
• እየተናገሩ ማሰብ፤ መምህሩ • ተማሪዎች ሥራቸውን በየደረጃው
እንዴት ትክክለኛ መልስ ማግኘት ሲጨርሱ ወደሌላው ከማለፋቸው
እንደሚችሉ ሞዴል ሆነው ያሳያሉ፤ በፊት ለማስገምገም ወደመምህሩ
የመምህር መምሪያ

ይሄዳሉ፤ ምናልባት በአንድጊዜ ብዙ


ተማሪዎች አንዱን ደረጃ ስራቸውን
የጨረሱ ከሆነ፣ የማስገምገም ተራቸው
እስከሚደርስ ድረስ የሚሠሩት ሌላ
ሥራ መስጠት
• ተማሪዎች የጽሕፈት ስራቸውን
ሲጨርሱ፣ አንዱን የክፍል አጋማሽ
መርሃትምህርት

በመውሰድ እርሱን በቅርበት


መገምገም፣ ምጋቤ ምላሽ መስጠት፣
በተከታዩ የጽሕፈት ስራ ወቅት ደግሞ
ለሌላኛው ግማሽ እድል ሰጥቶ
በተመሳሳይ ሁኔታ መገምገምና
ምጋቤ ምላሽ መስጠት፣

18
፪፻፰
፪፻፱

የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8


አማርኛ 5ኛ ክፍል
የመምህር መምሪያ

5ኛ ክፍል፣ ሁለተኛው ወሰነትምህርት


መርሃትምህርት
209

19
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


210
ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
ትእምርተድምፃዊ ተማሪዎች ------ ተማሪዎች ------ ተማሪዎች ------
ግንዛቤ ምግብ
• የምግብ ዓይነቶች
ማፍለቅ/መተርጎም / • የተማሯቸውን ቃላት • ቃላትን ለመለየት • በደረጃቸው ውስብስብ • ቃላትን መፍጠር፤ ተማሪዎች የቃ • በክፍል ውስጥ የተማሪን
የቃላት ጥናት - ሥጋ
የፍደላ ህግጋት የተማሯቸውን በሆኑ የቀለም መዋቅሮች ላትን ክፍልፋዮች ተጠቅመው ዕድገት ለመምራትና ለመቆጣጠር
- አትክልት
ይገልጻሉ፤ ውስብስብ የቀለም ቃላትን ይፈድላሉ፤ አዳዲስ ቃላትን ማፍለቅና መፈደል ሥር ዓታዊ ልምምድ ማድረግ፣ - ፍራፍሬ
መዋቅሮች ያጣምራሉ፤ • በደረጃቸው ውስብስብ ይለማመዳሉ ወይም የቃላትን • ኢርቱዕ ቁጥጥር፤ የትኞቹ - ጥራጥሬ
የቃላት መዋቅሮችን ክፍልፋዮች በመጠቀም አዳዲስ ልጆች እንደተረዱና የትኞቹ • የተመጣጠነ ምግብ
• ለቃላቱ ተገቢ/ጠቃሚ
ወደምዕላዶች በመነጣጠልና ቃላትን ይፈጥራሉ፤ ደግሞ ተጨማሪ ድጋፍ
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ብልሃቶችን በመጠቀም መመገብ


መልሶ በማገጣጠም ቃላትን እንደሚያስፈልጋቸው ለመረዳት
ውስብ ስብ መዋቅር • ቃላትን ማሰስ፤ተማሪዎች
ይጽፋሉ፤ መምህሩ በክፍል ውስጥ
ያላቸውን ቃላት ያነባሉ፤ የዱር እንሰሳት በኢትዮጵያ
• ኢተዘውታሪ ቃላትን የቀረበውን ትምህርት በጥሞና በመዘዋወር ይከታተላሉ፡፡
በመከታተል የታላሚ ቃላትን • ዋልያ
• የተማሯቸውን በደረጃቸው ለመጻፍ የሥነምላዳዊ ፍቺን
ወይም ምዕላዶችን ምሳሌዎች • ምር ክለሳ፤ ተማሪዎች • ቀይ ቀበሮ
ቀስበቀስ ውስብስብ የሆኑ (የምሥርታና/ወይም የርባታ)
እውቀታቸውን ይጠቀማሉ፤ ከሌሎች ቃላት ውስጥ ፈልገው ለጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ፤ • ጭላዳ ዝንጀሮ
ምዕላዶችን ማጣመር
ያወጣሉ፤ ከቀደመው ትምህርት • በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ
የመምህር መምሪያ

ቃላትን ለማንበብ ብርቅዬ የዱር እንስሳት


ይጠቀማሉ፤ • መምረጥ (ማወዳደር)፤ ተማሪዎች ያገኙትን ልምድ ይጋራሉ፡፡
የቃላትን መዋቅር ወይም የፍደላ መምህሩ ይህን መረጃ የቀጣዩን / ባህላዊ ጨዋታዎች
• ኢተዘውታሪ ቃላትን ውቅሮችን ያወዳድራሉ፡፡ ይህ የወቅቱን ትምህርት አቅጣጫ • ድብብቆሽ
ለማንበብ የሥነምላዳዊ የሚከተሉትን ሊያካትት ይችላል፤ ለመወሰን ይጠቀሙበታል፡፡ • የበዓላት ጨዋታዎች
ፍቺን (የምሥርታና • ሌሎች የአካባ ቢው
/ወይም የርባታ) • የተለመዱትን ካልተለመዱት ጋር
ማወዳደር፤ ትምህርቱ ባህላዊ ጨዋታዎች
እውቀታቸውን ይጠቀማሉ፤
መርሃትምህርት

የሚጀምረው ቀድሞ
ሥነቃል
የተማሯቸውን የቃላት መዋቅር • እንቆቅልሽ
በወቅቱ ከሚማሯቸው ቃላት • ቃላዊ ስነ ግጥም
መዋቅሮች ጋር በማነፃፀር ይሆናል) • አፈታሪኮች
• ሌሎች የአካባቢው
ሥነቃሎች
• የባህል ውርርስና የቃላዊ
ልማዶች ረብ

20
፪፻፲
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት

አቀላጥፎ ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


፪፻፲፩

ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች


ማንበብ /መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
- ቃላትን በመዋቅራቸው ወይም • ምልከታዋች፤. የእለት • መድልዎና መገለል
በውቅራቸው መምረጥ፣ ቃላትን ማስታወሻዎች፤ መምህሩ በኤች አይ ቪ ምክንያት
በመዋቅራቸው ወይም ተማሪዎች በግል የንባብ መገለል መድልዎ
በውቅራቸው መመደብ ተግባራትን ሲሠሩ ማስታወሻዎችን
• በተሰጣቸው መዋቅር ወይም ይዘው በመጨረሻ ስለ ጽሕፈት • ከኤች አይ ቪ ኤድስ
በትክክል • ለደረጃው የተመደበን • ለደረጃው የተመደቡትን ውቅር መሠረት ቃላትን መዘርዘር፣ ተግባሩ አስተያየት ያቀርባሉ፤ ጋር አብረው በሚኖሩ
ማንበብ ጽሑፍ በ95% ትክክለኛነት ቃላት በ90% ትክክለኛነት • አቅርቦት፤ ተማሪዎች የቃላት ሰዎች ላይ የመድልዎና
ያነብባሉ፤ ይጽፋሉ፤ • የአንባቢዎች ቲያትር፤ ዕድገታቸውን ለመምህራኑ ወይም የመገለል ተጸእኖዎች
አማርኛ 5ኛ ክፍል

• ለደረጃው የተመደበን • ከመምሀራቸው ጋር ወይም በትምህርት ደረጃ ወይም በራስ ለክፍሉ የሚያሳዩበት ዕድል
አላቸው፡፡ • መድልዎንና መገለልን
ገላጭ ጽሑፍ በ95% ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር ተናሳሽነት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው
• የቢጤ ግምገማ፤ አንድ የጽሕፈት የመከላከያ መንገዶች
ትክክለኛነት ያነብባሉ፤ ወይም በግል የጽሕፈት ክለሳ ተማሪዎች በቡድን ሆነው አንድን
ይሰራሉ፤ ተግባር ካለቀ በኋላ ተማሪዎች • ፍቅርና ክብካቤ ከኤች
ጽሑፍ ያጠናሉ፤ ቀጥለውም
ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን አይ ቪ ኤድስ ጋር
የማንበብ • በተለያዩ መንገዶች • ለደረጃውና ለቋንቋው • የተለያዩ የመፃፍ ግቦችን ለተመልካች ይከውናሉ፡፡ ዋናው
እንዲለዋወጡ በማድረግ አብረው ለሚኖሩ
ፍጥነት አንድን ነገር መግለጽ ተገቢ የሆነውን የንባብ (ሁነቶችን) በጥቃቄ መግለጽ፣ ትኩረት በድምጽ አጣጣልላይ ነው፡፡
(ሁነቶችን በጥንቃቄ በመምህሩ በሚሰጣቸው ሰዎች
ፍጥነት ያጠናክራሉ፤ ስሜትን በደንብ ማስተላለፍ፣ (ለምሳሌ፡- አገላለጾች) በዚህ ሂደት
የመምህር መምሪያ

መግለጽን፣ ስሜትን • ለደረጃው የተመደቡትን ታሪኮች/ ተረቶችን በጽሑፍ መደበኛ አገላለጾች በጥቅም ላይ መመሪያ መሠረት እንዲተራረሙ
በአግባቡ መግለጽን፣ ከተደረገ በኋላ፣ መምህሩ
ታሪኮችን ለሌላ ሰው ጽሑፎች በዝምታ/በጥሞና መግለጽ፣ መመሪያዎችን አይውሉም፤ መስመር በመስመርም
ማንበብ ይጀምራሉ፤ መስጠት) ይለማመዳሉ፤ አይሸመደዱም ፡፡ ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን
መንገርን፣ መምሪያ
መስጠትን) ይለማመዳሉ፤ • የራዲዮ ንባብ፤ በአነስተኛ ቁጥር ሰብስበው ክንውናቸውን
የተደራጁ ቡድኖች ወይም ግለሰብ ይገመግማሉ፤
አገላለጾች • ቃለመጠይቅ ይጠይቃሉ፣ • ለደረጃው በተዘጋጀ • ከሁለት በላይ የሆኑ አንቀጾችን
ይመልሳሉ፤ አንድን ሃሳብ/ ጽሑፍ ውስጥ የተሟላ ፍቺን ተገቢውን የጽሑፍ አቀማመጥ፣ ተማሪዎች የአንድን ጽሑፍ የተወሰነ
አስተያየት ለመደገፍ ለማመልከት ሥርዓተነጥቦችን ሥርዓተነጥብና ቦታ ጠብቀው ክፍል ይለማመዳሉ፤ ቀጥለውም
መርሃትምህርት

ወይም ለመቃወም ተጠየ ይጠቀማሉ፤ ይጽፋሉ፤ ለተመልካች ያቀርባሉ፤ ይህ ለንባብ


ቃዊና ሊረጋገጡ የሚችሉ • ስለአንድ ታሪክ ወይም ሁነት አቀላጥፎና ተገቢ ንባብ የሚያበረታታ
እውነታዎችን ይጠቀማሉ፤ • ባሕርያትንና ሁነቶችን ዝርዝር መግለጫዎችን፣ ግልጽ ይሆናል፡፡
መረዳታቸውን በሚያሳይ የሁነቶችን ቅደምተከተል፣ አርኪ
ሁኔታ ተዋስኦን (ምልልስን) መደምደሚያን የያዙ ከሁለት
በሐረጋትና በአገላለጽ በላይ አንቀጾችን ይጽፋሉ፤
በመከፋፈል ያነባሉ፤

21
211
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል-2ኛ ወሰነ ትምህርት
212
ቃላዊ ክሂሎች /መናገርና ናሙና የመማር ማስተማር
ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
ማዳመጥ/ ስልቶች
• አንድን ሃሳብ/አስተያየት ለመደገፍ • የግል አስተያየትን ለመግለጽ • መላልሶ ማንበብ፤ ተማሪዎች አጭር • የቡድን ሥራ፤ መምህሩ
ወይም ለመቃወም ተጠየቃዊና ከአንድ አንቀጽ በላይ ይጽፋሉ፤ ምንባብ የወሰደባቸውን ጊዜ እየመዘገቡ በአነስተኛ ቡድን የሚሠራ የቤት
ሊረጋገጡ የሚችሉ እውነታዎችን • አንድን ሃሳብ/አስተያየት ደጋግመው ያነብባሉ፤ የንባብ ፍጥነታቸው ሥራ ይሰጣሉ፤ ሁሉም የቡድኑ
ይለያሉ፤ ለመደገፍ ወይም ለመቃወም መሻሻሉንም ይመዘግባሉ፤ ያነበቡባቸው አባላት መሳተፋቸውንም
ተጠየቃዊና ሊረጋገጡ የሚችሉ ጊዜያትንም በግራፍ ይመለከታሉ፡፡ ይቆጣጠራሉ፡፡ ለእያንዳንዱ
እውነታዎችን ይጠቀማሉ፤ • ቅድመመፃፍ ተግባራት፤ ከመፃፍ የቡድን አባል የተወሰነ ሥራ
ሰዋስው • በንግግር ውስጥ የተጸውዖና • በጽሑፍ ውስጥ የተጸውዖና • በመፃፍ ውስጥ የተጸውዖና የወል በፊት ያሉ ተግባራት፣ ለምሳሌ ሥዕል፣ መስጠት ሁሉም አባላት
የወል ስሞችን መግለጽና መለየት የታሪክ ካርታ፣ ወዘተ. ሃሳብን በማዳበርና መሥራታቸውን ለማረጋገጥ
አማርኛ 5ኛ ክፍል

የወል ስሞችን መግለጽና መለየት ስሞችን መጠቀም


ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ ይጀ ምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ በአግባቡ በማደራጀት ረገድ ያግዛሉ፤ ይጠቅማል፡፡ ቡድኑ ሥራው
የቁጥር፣ የጾታ፣የሙያ ወዘተ. የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስም የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ • ተግባር መር መፃፍ፤ መምሀራኑ ሲጠናቀቅ ውጤት/ ነጥብ
ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) ስምምነቶችን ተግባራዊ ማድረግ ለአንድ የተወሰነ የመፃፍ ልምምድ ሊሰጠው ይችላል፡፡
በጽሑፍ ውስጥ ቀላል ግሶችን ተማሪዎቹ አሟልተው የሚጽፉባቸው (ማስታወሻ፡- የቡደን ሥራ
ይጠቀማሉ፡፡ ይጀምራሉ፡፡)
መግለጽና መለየት ይጀምራሉ፡፡ ወይም እነሱን ተከትለው አንድ ጽሑፍ በምንም መንገድ የግል ሥራን
• በንግግር ውስጥ ቀላል ግሶችን (ተዘውታሪ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ • ቀላል ግሶችን በፅሑ ውስጥ
መግለጽና መለየት ይጀምራሉ፡፡ በአግባቡ መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ለመጻፍ የሚረዷቸው ቀድመው ሊተካ አይችልም፡፡)
ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን
የተዘጋጁ መነሻዎችን (ቴምፕሌቶችን)፣
የመምህር መምሪያ

(ተዘውታሪ የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ ይገነዘባሉ፡፡) (ተዘውታሪ የመደብ፣ የቁጥር፣


ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን • በጽሑፍ ውስጥ ተዘውታሪ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ናሙና ቅጾች፣ ወይም መምሪያዎች • ዞሮ መጥ ግለሰባዊ እርማት፤
ይጠቀማሉ፡፡) ቅጽሎች መግለጽና መለየት ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) (ለምሳሌ የዓፍተነገር መጀመሪያ በትላልቅ ክፍሎች ውስጥ
• በንግግር ውስጥ ተዘውታሪ ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ • በፅሁፍ ውስጥ ተዘውታሪ ዎችን፣ የዘገባ ቅጾችን ወዘተ.) የሚዘዋወር አንድ ሰው (ተማሪ)
ቅጽሎችን መግለጽና መለየት የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ቅጽሎችን መጠቀም ያቀርባሉ፤ በመዘዋወር የጽሕፈት ሥራዎች
ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ ስምምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) ይጀምራሉ፡፡ (የመደብ፣ የቁጥር፣ የሚገመገሙበት ሁኔታ
• በጽሑፍ ውስጥ ተዘውታሪ • አሳታፊ የመፃፍ ማኅበረሰብ መፍጠር፤ ተማሪዎች ሥራቸውን
የሙያ፣ የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን - መምህሩ ሞዴል ጽሑፍ ጽፈው
ቁጥሮችን መግለጽና መለየት በየደረጃው ሲጨርሱ
መርሃትምህርት

ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) ለተማሪዎቹ በማካፈል፤


ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ ወደሌላው ከማ ለፋቸው በፊት
ይጠቀማሉ፡፡) የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ስም • በመፃፍ ተዘውታሪ ቁጥሮችን
• በንግግር ውስጥ ተዘውታሪ ምነቶችን ይገነዘባሉ፡፡) መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ( ተዘውታሪ - በመፃፍ የቤትሥራደት ለተማሪዎቹ ለማስገምገም ወደመምህሩ
ቁጥሮችን መግለጽና መለየት የመደብ፣ የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. አማራጮችን በመስጠት፣ ይሄዳሉ፤ ምናልባት በአንድ
ይጀምራሉ፡፡ (ተዘውታሪ የመደብ፣ • ስሞችን እንደባለቤት በጽሑፍ ሰዋስዋዊ ስምምነቶችን ተግባራዊ ጊዜ ብዙ ተማሪዎች አንዱን
የቁጥር፣ የጾታ ወዘተ. ሰዋስዋዊ ውስጥ መለየት ይጀምራሉ፤ ማድረግ ይጀምራሉ፡፡) ደረጃ ስራቸውን የጨረሱ
ስምምነቶችን ይጠቀማሉ፡፡). ከሆነ፣ የማስገምገም ተራቸው
• በዓረፍተነገር መዋቅር ውስጥ
የተዘወተረ ባለቤትና አንቀጽ፣ እስከሚደርስ ድረስ የሚሠሩት
እንዲሁም የተዘወተረ የሀተታዊ ሌላ ሥራ መስጠት፣
ዓረፍተነገር መዋቅርን በጽሑፍ
ውስጥ መጠቀም ይጀምራሉ፤

22
፪፻፲፪
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል-2ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች /መናገርና ናሙና የመማር ማስተማር


፪፻፲፫

ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች


ማዳመጥ/ ስልቶች
• ስሞችን እንደባለቤት መለየትና • በጽሑፍ ውስጥ • ስሞችን እንደባለቤት በጽሕፈት - ተማሪዎቹ እንደጸሐፊ እንዲተባበሩ • ተማሪዎች የጽሕፈት
መግለጽ ይጀምራሉ፤ በዓረፍተነገር መዋቅር ውስጥ ውስጥ መጠቀም ይጀምራሉ፤ በማበረታታት፣ ስራቸውን ሲጨርሱ፣
• በዓረፍተነገር መዋቅር ውስጥ የተዘወተረ ባለቤትና አንቀጽ፣ - ለተማሪዎቹ ምጋቤ-ምላሽ አንዱን የክፍል አጋማሽ
የተዘወተረ ባለቤትና አንቀጽ፣ እንዲሁም የተዘወተረ • በዓረፍተነገር መዋቅር ውስጥ እንዲሰጡና እንዲቀበሉ ዕድል በመውሰድ እርሱን በቅርበት
እንዲሁም የተዘወተረ የሀታታዊ የሀታታዊ ዓረፍተነገር የተዘወተረ ባለቤትና አንቀጽ፣ በመስጥት፤ መገምገም፣ ምጋቤ ምላሽ
ዓረፍተነገር መዋቅርን መግለጽና መዋቅርን መለየት ይጀምራሉ፤ እንዲሁም የተዘወተረ የሀተታዊ መስጠት፣ በተከታዩ
• ሥነግጥም፤ ተማሪዎች ለክፍላቸው
መለየት ይጀምራሉ፤ ዓረፍተነገር መዋቅርን በጽሑፍ የጽሕፈት ስራ ወቅት ደግሞ
የሚያቀርቡት ግጥም ይመርጣሉ፤
ውስጥ መጠቀም ይጀምራሉ፤ ለሌላኛው ግማሽ
የድምጽ አጣጣላቸውን የሚያሳድግ
አማርኛ 5ኛ ክፍል

በተመሳሳይ ሁኔታ
ይሆናል፡፡፡
መገምገምና ምጋቤምላሽ
• አስመስሎ መናገር፤ ተማሪዎች
መስጠት፣
ለአድማጭ የሚያቀርቡት አንድ
ታሪካዊ ንግግር ይመርጣሉ፤ በአግባቡ
በተዘጋጀ ጽሑፍ ላይ ተዘውትሮ
የሚከናወን ከሆነ የተማሪዎችን
የጽሕፈት ችሎታ ያበለጽጋል፡፡
የመምህር መምሪያ

የቃላት ተማሪዎች…
ዕውቀት ተማሪዎች… ተማሪዎች…
የቃላትን • ዕውቀትን ለማግኘት፣ • በደረጃው ጽሑፍ ውስጥ በተለያዩ ዐውዶች ውስጥ ሲጽፉ • ቁልፍ ቃላትን እንዲለማመዱና • የመውጫ ካርድ፤
ዐውቀት ለማሳደግና አገላለጽን ለማጥራት የቃላትን ፍቺ ከአውዱ የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት በቃላዊ ክሂሎች ላይ እንዲሳተፉ ተማሪዎች ክፍሉን ለቅቀው
ማስፋትና የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት ፈልገው ያገኛሉ፤ ይጠቀማሉ፤ ዕውቀትን ለማግኘት፣ ብዙ አማራጭ እድሎችን መስጠት፤ ሲወጡ ለመምህራቸው
መጠቀም በንግግራቸው ውሰጥ ይጠቀማሉ፤ • አዳዲስ ቃላትን ለማወቅና ለማሳደግና አገላ ለጽን ለማጥራት - አዳዲስ ቃላትንና አገላለጾችን ሰጥተው ወይም በርላይ
መርሃትምህርት

በመስተጋብራዊ ንባብ፣ ፍቺያቸውን ለመረዳት የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላትን እንዲጠቀሙ ብዙ እድሎች አስቀምጠው የሚሄዷቸው
• በንግግር፣ በአቅጣጫ አጋዥ ማመሳከሪያዎችን በጽሑፋቸው ውሰጥ ይጠቀ ማሉ፤ ማመቻቸት፤ ትንንሽ ወረቀቶች ናቸው፤
ጠቋሚዎች ወዘተ. የቀረበን ጽሑፍ (ለምሳሌ፡- መዝገበቃላትን፣ - ከ”አዎ-አይደለም” ጥያቄዎች ይልቅ በእነዚህም ወረቀቶች ላይ
ፍቺ ለመረዳት መዝገበቃላት ሰዎችን፣ መጣጥፎችን) ብዙ ጊዜ ክፍት ጥያቄዎችን ተማሪዎች ስማቸውንና
ይጠቀማሉ፤ ይጠቀማሉ፤ መስጠት፤ ለተሰጧቸው ጥያቄዎችና
ትምህርታዊ በቋንቋ በሰፊ ዐውድ አማካይነት በደረጃው የተዋወቋቸውን ጽንሰሃሳቦችን ለመወከል የቃላት መልመጃዎች ምላሽ
- የተለያዩ ችሎታዎች ያላቸው ጥንድ
ቃላት የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት አዳዲስ ቃላት ይገነዘባሉ (ለመግለጽ) በጽሑፋቸው ውስጥ ይጽፉባቸዋል፤
ልጆች በቡድን ሥራ ማሳተፍ፤
በንግግራቸው ውስጥ ይጠቀማሉ፤ (ያነብባሉ)፤ የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት
ይጠቀማሉ፤

23
213
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት
214

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
የቃላት ተማሪዎች… ተማሪዎች… ተማሪዎች…
ዕውቀት
• በአስረጂና በተራኪ ጽሑፍ • የተማሯቸውን አዳዲስ ቃላት - በአንድ ጭብጥ ላይ እንዲወያዩ፣ • ኢመደበኛ ቁጥጥር፤
መስተጋብራዊ ንባብ የተማሯቸውን በወጥ ጽሑፋቸው ውስጥ ይጠ እንዲጽፉና ለክፍል እንዲያቀርቡ መምህራኑ ለተማሪዎቹ የጽሕፈት
አዳዲስ ቃላት ይጠቀማሉ፤ ቀማሉ፤ ቡድኖች (ከ4-5 ተማሪዎች) ተግባር ለተማሪዎቹ ይሰጣሉ፤
• ፍቺን ፈልፍሎ በመረዳት ሂደት መመ ሥረት፤ በክፍልም ውስጥ በመዘዋወር
አዳዲስ ቃላትን ይማራሉ ኢመደበኛ በሆነ መልኩ ቁጥጥር
አማርኛ 5ኛ ክፍል

(ለምሳሌ፡- በቋንቋ ከበለጸገ


ያደርጋሉ፤
ዐውድ፣ ከራዲዮ መርሐግብር • አዳዲስ ቃላትን በቀጥታ ማስተማር፤
ወዘተ.) አዳዲስ ቃላትንና የተሟላ • አቅርቦት፤ ተማሪዎች ያላቸውን
• ቀለል ያሉ ፍቺዎችና ተተግባሪነት ፍቺያቸውን በብልሃት ማስተማር፤ የአገላለጽ ችሎታና ትክክለኛነት
ያላቸውን ቃላት በቀጥታ ተገቢ ምሳሌ በአውድ መስጠት፣ ለመምህራኑ ወይም ለክፍሉ
በሚሰጣቸው መመሪያ ይለምዳሉ፤ በተግባር ያሳያሉ፤
ተማሪዎች የራሳቸውን ቃላት
እንዲገልጹ ወይም ምሳሌ እንዲሰጡ • ማጠቃለያና ጽብረቃዎች፤
የመምህር መምሪያ

መጠየቅ፣ እንዲጠቀሙባቸውም ተማሪዎች ቆም ብለው


እድል መስጠት፤ ስላደመጡትና ስላነበቡት
የሚሰማቸውን ስሜት
• ቃላትን ማሰስ፤ ተማሪዎች ያንባርቃሉ፤ ከግል የትምህርት
በትምህርቱ ሂደት በዓረፍነገር ውስጥ ገጠመኛቸው ተነስተው
ወይም በሥዕል የተወከሉ የቃላት የራሳቸውን ፍቺ ይሰጣሉ፤
ምሳሌዎች ንና በሌሎች ቃላት ይህም ተተኳሪ ቃላትን
መርሃትምህርት

ውስጥም የቃላቱን ክፍሎች መጠቀምን ይጠይቃል፡፡


(ምእላዶችን) ለማግኘት አተኩረው • የቢጤ ግምገማ፤ አንድ
እንዲከታተሉ ማድረግ፤ የጽሕፈት ተግባር ካለቀ በኋላ
ተማሪዎች ወረቀታቸውን /
• የደረጃ ቀጣይነትን አመልካች፤
ደብተራቸውን እንዲለዋወጡ
ተመሳሳይ ነገርን የሚየመለክቱ
በማድረግ በመምህሩ
ግን ደግሞ የተለያየ ደረጃን አመልካች
በሚሰጣቸው መመሪያ መሠረት
ቃላት በመካከላቸው ያለውን ለውጥ
እንዲተራረሙ ከተደረገ መምህሩ
ለማሳየት በቅደምተከል በመስመር
ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን
ማደራጀት፤
ሰብስበው ክንውናቸውን
ይገመግማሉ፤

24
፪፻፲፬
፪፻፲፭ የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
አንብቦ ተማሪዎች… ተማሪዎች… ተማሪዎች…
መረዳት
አንብቦ • በመስተጋብራዊ ንባብ የተነበበን • ያነበቡትን ለደረጃው • ሥዕላዊ የሀሳብ • በተደጋጋሚ በሚመቻቹ እድሎች • ተነሺ ካርዶች፤ ለተለያዩ ጥያቄ
የመረዳት ጸሑፍ አሳጥረው ይናገራሉ፤ የቀረበን ጽሑፍ አደራጃጀቶችን መሠረት ዎች ተማሪዎች የተለያዩ ቀለሞች
ተጠቅሞ የተለያዩ ዘውጎችን ማንበብ
ብልሃቶችን • በመስተጋብራዊ ንባብ የተነበበን አሳጥረው ያቀርባሉ፤ በማድረግ በክፍል ደረጃው ዳራዊ ዕውቀትን ለማዳበርና ያሏቸውን ካርዶች በማንሳት
ማበልጸግ ጸሑፍ ይገመግማሉ፤ • ያነበቡትን ለደረጃው ጽሑፍ ውስጥ የቀረቡ ሀሳቦችን: በተዘወዋሪ ጽሕፈትን ለማሻሻል ምላሽ የሚሠጡበት (ለምሳሌ፡-
• በመስተጋብራዊ ንባብ የተነበበን የቀረበን ጽሑፍ ይገመግማሉ፤ አሳጥረው ይጽፋሉ፤ ይጠቅማል፤ እውነት/ሀሰት፣ እስማማለሁ
• ቁጥጥር፤ ተማሪዎች በሚያነቡበት / አልስማማም)
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ጸሑፍ ከራሳቸው ጋር ያዛምዳሉ፤ • የቃላትን አመሠራረት፣ ፍደላና


• ለክፍል ደረጃው የቀረበን ወቅት ያልተረዷቸውን ቃላትና • ኢመደበኛ ቁጥጥር፤
• በመስተጋብራዊ ንባብ የተነበ ጽሑፍ ከቀደመ ዕውቀታቸው፣ ፍቺ ለማረጋገጥ መዝገበቃላትን
በን ጸሑፍ ሀሳብ በራሳቸው ቋንቋ ዕሳቤዎች ከንባብ በኋላ መምህራኑ በክፍል ውስጥ
ልምዳቸው እና ሌላ ጽሑፍ ጋር ወይም የቃላት ዝርዝሮችን
(ቃላት) በዘገባ መልክ ያቀርባሉ፤ ይጠቀማሉ፤ እንዲወያዩባቸው ተከታለው በመዘዋወር የትኛቹ ተማሪዎች
ያዛምዳሉ፤ ማስታወሻ እንዲይዙ መጠየቅ፤ ተጨማሪ ድጋፍ
• ምናባዊነት፤ ተማሪዎች ምናባዊ እንደሚያስፈልጋቸውና
• ለቀረበላቸው የጽሑፍ
ምስል እንዲፈጥሩ ማድረግ፣ እንደማያስፈልጋቸው ኢመደበኛ
ዓይነትና የንባብ ተግባር
የመምህር መምሪያ

በዚያውም ያነበቡትን በሆነ መልኩ ቁጥጥር ያደርጋሉ፤


ተስማሚ የሆነ የአንብቦ
እንዲያስታውሱና እንዲረዱ ሞዴል ተማሪዎች የቃላት
መረዳ ዓይት ብልሃት
ሆኖ ማሳየትና እንዲለማመዱ • ዕድገታቸውን ለመምህራኑ
መርጠው ይጠቀማሉ፤
ሁኔታዎችን ማመቻቸት፤ ወይም ለክፍሉ የሚያሳዩበት
• ለክፍል ደረጃው የቀረበውን ዕድል አላቸው፡፡
• የጥያቄና መልስ ተዛምዶዎች፤
ጽሑፍ መረዳታቸውን • ማጠቃለያና ጽብረቃዎች፤
ድኅረንባብ ጥያቄዎች የሚከተሉትን
ለማረጋገጥ ራስን የመመዘን አራት ዓይነት ጥያቄዎችን ያካትታሉ፤ ተማሪዎች ቆምብለው
ብልሃታቸውን መጠቀም
መርሃትምህርት

ስላደመጡትና ስላነበቡት
- መልሱ እዚያው፤ (የጥያቄው
ይቀጥላሉ፤ የሚሰማቸውን ስሜት
መልስ እዚያው እተወሰነ ያንጸባርቃሉ፤ ከግል የትምህርት
ዓረፍነገር ውስጥ የሚገኝ) ገጠመኛቸው ተነስተው
- ማሰብና መፈለግ፤ (መልሱ የራሳቸውን ፍቺ ይሰጣሉ፤ ይህም
በጽሑፉ ውስጥ የሚገኝ ግን ተተኳሪ ቃላትን መጠቀምን
ደግሞ የሚፈለገው መረጃ ከአንድ ይጠይቃል፡፡
ዓረፍተነገር በላይ በሆነ የጽሑፉ
አካል ውስጥ የሚገኝ)

25
215
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት
216

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
የቃላት ቃላዊ ማንበብ መጻፍ ናሙና የማስተማ ሪያ/መማሪያ ናሙና የምዘና ስልቶች
ዕውቀት ተማሪዎች… ተማሪዎች… ተማሪዎች… ስልቶች
- መልሱ ከራሴ፤ (መልሱ • የቢጤ ግምገማ፤ አንድ የጽሕፈት
ከአንባቢው (ከተማሪው) ተግባር ካለቀ በኋላ ተማረዎች
ከራሱ ዕውቀት የሚገኝ) ወረቀታቸውን /ደብተራቸውን
- ጽሑፉና እኔ፤ (የጥያቄው እንዲለዋወጡ በማድረግ በመምህሩ
መልስ ከአንባቢው ዳራዊ በሚሰጣቸው መመሪያ መሠረት
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ዕውቀትና ከጽሑፉ እንዲተራረሙ ከተደረገ በኋላ፣


በማውጣጣት የሚገኝ) መምህሩ ወረቀታቸውን /ደብተራቸ
ውን ሰብስበው ክንውናቸውን
• መጠየቅ፤ ተማሪዎቹ ይገመግማሉ፤
ስለአነበቡት ጥያቄ እንዲያዘጋጁና
• በተራ መናገር፤ ተማሪዎች
የክፍል ጓደኞቻቸውንም
አጠገባቸው ካለ/ች (ካሉ) ተማሪዎች
እንዲጠይቁ ጊዜ መስጠት፤
ጋር ምላሻቸውንና ሀሳባቸውን
የመምህር መምሪያ

• የጽሑፍ መዋቅር፤ጽሑፉን ይጋራሉ፤ መምህሩ በክፍሉ ውስጥ


ለመረዳት እንዴት ርዕሶችን፣ በመዘዋወር ሂደቱን ይከታተላሉ፡፡
የግርጌ መግለጫዎችን መጠቀም • ዞሮ መጥ ግለሰባዊ እርማት፤
እንደሚቻል በግልጽ መመሪያ በትላልቅ ክፍሎች ውስጥ
መስጠት፤ የሚዘዋወር አንድ ሰው (ተማሪ)
መረጃዎችን ስለአንድ ርዕሰጉዳዩ አስተ • ለደረጃው የተመረጡ • ጽሑፍ በሚጽፉበት
መለየት በመዘዋወር የጽሕፈት ሥራዎች
ያየት ሲሰጡ የመሸጋገሪያ/ ሠንጠረዦችን፣ ካርታዎችን፣ ጊዜ የተማሯቸውን • ሥዕላዊ የሀሳብ አደረጃጀቶች
መርሃትምህርት

(ከሁሉም የሚገመገሙበት ሁኔታ


አያያዥ ቃላት/ሐረጋት ቻርቶችን ስለርዕሰ ጉዳዩ ለማወቅ/ ምዕላዶች፣ የመሸጋገሪያ፣ እነዚህ ከንባብ በፊት፣ በንባብ
የጽሑፍ ይጠቀማሉ፤ • ተማሪዎች ሥራቸውን በየደረጃው
ዓይነቶች) ለመማር ይተረጉማሉ (ፈልገው አያያዥ ቃላትና ሐረጋት ጊዜና ከንባብ በኋላ በጥቅም
መረጃ ያወጣሉ)፡፡ ጽሑፍን ይጠቀማሉ፤ ሊውሉ ይችላሉ፤ ሥዕላዊ የሀሳብ ሲጨርሱ ወደሌላው
ለመረዳት ምልክቶችን፣ የግርጌ አደረጃጀቶች (ለምሳሌ፡- የመረጃ ከማለፋቸው በፊት ለማስገምገም
መግለጫዎችን፣ ስያሜዎችን ድሮች፣ ማወዳደርና ማነጻጸር፣ ወደመምህሩ ይሄዳሉ፤ ምናልባት
ያነብባሉ፤ ቻርቶችን ማነጻጸር፣ መዋቅርን በአንድ ጊዜ ብዙ ተማሪዎች አንዱን
መንደፍ) መረጃዎችን ሊታይ ደረጃ ስራቸውን የጨረሱ ከሆነ፣
• ለደረጃው የተመረጠን ጽሑፍ የማስገምገም ተራቸው እስከሚደርስ
ለመረዳት ያግዝ ዘንድ የጽሑፍን በሚችል መልኩ ማደራጅት
ናቸው፡፡ ድረስ የሚሠሩት ሌላ ሥራ መስጠት
መዋቅር ይጠቀማሉ፤

26
፪፻፲፮
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት

ቃላዊ ክሂሎች /መናገርና ናሙና የመማር ማስተማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
፪፻፲፯

ማዳመጥ/ ስልቶች
• በደረጃው የተጻፉ ሁለት ጽሑፎችን - የመገመቻ መመሪያ፤ -ተማሪዎች የጽሕፈት
ሀሳብ ያወዳድራሉ፤ (የጽሑፎቹ ደረጃ ታሪኮችንና ገላጭ ጽሑፎችን ስራቸውን ሲጨርሱ፣
ተመሳሳይ ሆኖ ምንባቦቹ የተለያዩ ናቸው) (ኢልቦዶችን) ለማንበብ ይረዳል፤ አንዱን የክፍል አጋማሽ
በመውሰድ እርሱን
- ምን እንደተማሩ ማወቅ፤
• ያነበቡት ጽሑፍ ለመረዳት ስለታሪክ ሁነቶች ለመረዳት በቅርበት መገምገም፣
የተማሯቸውን ምዕላዶች፣ የመሸጋገሪያ፣ ይረዳሉ (ማን፣ ምን፣ መቼ፣ ምጋቤ ምላሽ መስጠት፣
አያያዥ ቃላትና ሐረጋት ይጠቀማሉ፤ የት፣ ለምን)፤ በተከታዩ የጽሕፈት ስራ
ወቅት ደግሞ ለሌላኛው
- የዋና ሀሳብ ቻርት፤ የጽሑፉ ግማሽ በተመሳሳይ ሁኔታ
አማርኛ 5ኛ ክፍል

ሀሳብ ስለምን ነበር? ዝርዝ መገምገምና ምጋቤምላሽ


ሮቹ ምን ነበሩ? መስጠት፣
- የመዋቅር ምስል፤ የታሪኩን
ዋና ሀሳብ ለመመዝገብ
መጠቀም፤
- ማወዳደርና ማነጻጸር
ተራኪ • በመስተጋብራዊ ንባብ ሂደት • ለደረጃው በተመረጡ አጭር ልቦለዶች • ለደረጃው የተመረጠ አጭር
የመምህር መምሪያ

(የቬን ምስል)፤
ጽሑፍን ታሪኩን ገጸባሕርያት፣ መቼት፣ ውስጥ የልቦለድን መዋቅር አላባውያንን ልቦለድ ገጸባሕርያትን
ሁለት ነገሮችን ለማወዳደርና
መረዳት ሁነቶች ይለያሉ፤ (መግቢያ፣ መካከልና መጨረሻ) ይገነዘባሉ፤ የሚያወዳድርና/ ወይም
ለማነጻጻር (መጻሕፍትን፣
• በመስተጋብራዊ ንባብ • በደረጃው በቀረበ አጭር ልቦለድ ውስጥ የገጸባሕርያቱን ድርጊቶች ገጸባሕርያትን፣ ወቅቶችን፣
በተነበበው ጽሑፍ ላይ የሚገኙ ገጸባሕርያት ድርጊቶችን የሚገመግም አንቀጽ ይጽፋሉ፤
ሥራዎችን መጠቀም)
በተገለጸው መሠረት ቀጥተኛ ይገመግማሉ፤ • ስለተነበበው ጽሑፍ ታሪክ
ጥያቄዎችን ይመልሳሉ፤ የተሰማቸውን ሀሳብ በአንድ ምጋቤ መጽሔት፤ .
• በደረጃው ጽሑፍ ውስጥ በተገለጸው ተማሪዎች ስለንባብ ሊነጋገሩ
• ዳራዊ ዕውቀትንና አንቀጽ ይጽፋሉ፤
መርሃትምህርት

መሠረት ቀጥተኛ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ፤ (ተግባቦት ሊፈጥሩ)


በመስተጋብራዊ ንባብ
በተነበበው ጽሑፍ የተገለጹ • በደረጃው ጽሑፍ በተገለጸው መረጃና • በተነበበው ጽሑፍ መሠረት ይችላሉ፤ መምህሩ
መረጃዎችን የሚመለከቱ ዳራዊ እውቀትን መሠረት በማድረግ የቀረቡ ጥያቄዎችን አንቀጽ በመጻፍ የተማሪዎችን መረዳት
አመራማሪ ጥያቄዎችን የሚመለሱ አመራማሪ ጥያቄዎችን ይመልሳሉ፤ መከታተልና ምጋቤ ምላሽ
ይመልሳሉ፤ ይመልሳሉ፤ • ጽሑፍን መሠረት ያደረጉ ጥያቄዎች ለመስጠት ይችላል፤ ይህም
• የፈጠራ ሥራ የሆኑትንና አንቀጽ በመጻፍ ይመልሉ፤ ጽሑፋዊ መስተጋብር
• የፈጠራ ሥራ የሆኑትንና ያልሆኑትን
• ለጅምር አንቀጽ ተገቢ ማጠቃለያ ተማሪዎች ቃላትን
ያልሆኑትን (ኢልቦለዶችን) (ኢልቦለዶችን) ይለያሉ፤፤
ይጽፋሉ፤ እንዲጠቀሙ እንደሞዴል
ይለያሉ፤
ሊያገለግላቸው ይችላል፤

27
217
የአማርኛ እንደኣፍ መፍቻ ቋንቋ መርሃትምህርት 5-8 5ኛ ክፍል- 2ኛ ወሰነ ትምህርት
218

ቃላዊ ክሂሎች ናሙና የመማር


ማንበብ መፃፍ ናሙና የምዘና ስልቶች ይዘቶች
/መናገርና ማዳመጥ/ ማስተማር ስልቶች
አስረጂ ፅሁፎችን • የክፍል ደረጃውን ጽሑፍ • ለደረጃው የተመደበን ባለአንድ ገጽ • በተሰጣቸው ማዕቀፍ መሠረት
መረዳት በቃል ይገመግማሉ፤ ጽሁፍ ያነባሉ፤ ሁለት የተለያዩ ጽሑፎችን ይዘት
በማወዳደር አንቀጽ ይጽፋሉ፤
• የተዘወተሩ አስረጂ ጽሑፎችን • ጽሑፍን መሠረት ላደረጉ
የጽሑፍ መዋቅር ይለያሉ፤ ጥያቄዎች አንቀጽ በመጻፍ ይመልሳሉ፤
አማርኛ 5ኛ ክፍል

• አመራማሪ ለሆኑ ጥያቄ ዎች አንቀጽ


• በሁለት የደረጃው ጽሑፎች
በመጻፍ ይመልሳሉ፤
ላይ ይወያያሉ፤
ያወዳድሯቸዋልም፤ • በተሰጣቸው ማዕቀፍ መሠረት
የተዘወተረ መረጃ አቀባይ ጽሑፍ
• ምክንያትንና ውጤትን ይጽፋሉ፤
የሚመለከቱ ጥያቄዎችን • በተሰጣቸው ማዕቀፍ መሠረት
ይመልሳሉ፤ ምከንያትንና ውጤትን የሚገለጹ
የመምህር መምሪያ

ጽሑፎችን ይጽፋሉ፤

የሥነጽሐፍ • ልማዳዊ ታሪኮችን አዳምጠው • ልማዳዊ ታሪኮችን አንብበው • በተሰጣቸው ማእቀፍ መሠረት
ዘውጎችና የተሰማቸውን ይመልሳሉ፤ የተሰማቸውን ይመልሳሉ፤ ተዋስኦንና ትረካን የሚጠቀሙ
አላባውያን • ታሪካዊ የፈጠራ ሥራዎችን አንብበው ጽሑፎችን ይጽፋሉ፤
የተሰማ ቸውን ይመልሳሉ፤
መርሃትምህርት

• አፈታሪኮችን አንብበው የተሰማቸውን


ይመልሳሉ፤
• የሥነጽሑፍን አላባውያን ይገነዘባሉ፤
ተዋስኦ (ምልልስ)
• የሥነጽሑፍን አላባውያን ይገነዘባሉ፤
(ትረካ)
፪፻፲፰

28

You might also like