You are on page 1of 10

ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕራፍ፡4፤

1፤እንግዲህ፡በጌታ፡እስር፡የኾንኹ፡እኔ፡በተጠራችኹበት፡መጠራታችኹ፡እንደሚገ፟ባ፟፡ትመላለሱ፡ዘንድ፡እለምናችዃለኹ፤

( ኤፌ 3÷1 ) ( ፊልሞኖ 1÷1 )

#
ቅዱስ_ጳውሎስ_በጌታ_እስር_የሆንኩ_እኔ_እያለ_ደጋግሞ_የሚጽፍበትን_ምክኒያት_ስሁለት_ነገር_ነው_ይላሉ_የቤተክርስቲያን_አ
ባቶች

# ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን÷#ቅዱስ_ጳውሎስ የክርስቶስ እስር ብሎ እራሱን መግለጹ ስለሁለት ነገር ነው ይላሉ።

1 ኛ,የክርስቶስ እስረኛ መሆኑን ሲመለከቱ ልባቸው እንዲራራ በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ ለኤ ፌሶን ሰዎች መልእክቱን እየጻፈላቸው
መሆኑን አውቀው ልባቸው እንዲመለስ።

2 ኛ, በክርስትና ስደት መከራ እንግልት ፈተና እስር ስላለ በዚህም መከራና ስደት ፈተና እስር ቢደርስባቸው የኤፌሶን ሰዎች
መምህራችን ከታሰረ መከራ ከደረሰበት ብለው የኤፌሶን ሰዎች እነሱም በእስር በስደት በመከራ እንዲጸኑና በክርስቶስ ክርስቲያን
የተባልን እኛም የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን እንግልት እና ጽናት እያሰብን በመከራ እንድንጸና ነው።

# የቤተ_ክርስቲያን_አባቶች÷መጠራት_የሚለው÷በክርስቶስ ኢየሱስ ማመን መጠመቅን የሚገልጽ ሲሆን በእምነታቸው እንዲጸኑና


ለክርስትና ተገቢ የሆነውን ሥራ እንዲሰሩ ይማጸናቸዋል ይላሉ። ( ማር 16÷16 )

# አንድም÷ለክርስትናው እንደሚገባ ክርስቶስን መስላችሁ እንድትመላለሱ እለምናችኋለሁ ሲላቸው ነው። ( ገላ 5÷24 ) ( ገላ 2


÷20 ) ( ሮሜ 12÷2 ) ( ራእይ 21 )

2፤በትሕትና፡ዅሉና፡በየዋህነት፡በትዕግሥትም፤ርስ፡በርሳችኹ፡በፍቅ ር፡ታገሡ፤

# ቅዱስ_ጳውሎስ_አባታዊ_ምክርን_እየመከራቸው ነው📚።

👇👇👇👇👇

#ትሕትና_ማለት÷እራስን ዝቅ ማድረግ ማዋረድ ማለት ነው። #ሊቁ_አውገስጢኖስ÷ትሕትና_ለክርስቲያን_ልብሱ_ነው_ይላሉ።

#የዋህነት_ማለት ÷ገር ወይም ቅን መሆን ማለት ነው።


#ትዕግስት_ማለት÷በፈተናዎች ሁሉ መጽናት መታገስ ማለት ነው።( ቆላስያስ 3÷12 )

3፤በሰላም፡ማሰሪያ፡የመንፈስን፡አንድነት፡ለመጠበቅ፡ትጉ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_በሰላም_ማሰሪያ÷የታሰሩ እጆች ወዲያና ወዲህ እንደማይሉ የኤፌሶን ሰዎች ከሰላም ውጭ በመጥፎ


ተግባራት ወዲህና ወደዚያ እንዳይሉ ከሰላም ህይዎት እንዳያፈነግጡ ሲመክራቸው ነው ሰላማዊያን ሁኑ ሁከትን ጥልን ጦርነትን
እራቁ በሰላም ማሰሪያ ታሰሩ ሲላቸው ነው ቅዱስ ጳውሎስ።

#አንድም÷የለበስነው ክርስቶስ ኢየሱስ ሰላማዊ ነውና ሰላማዊያን ሁኑ ሲል ነው በሰላም በፍቅር ኑሩ ሲል ነው።

# መንፈስ_የሚለው÷በአካል ብርቅም በመንፈስ ከእናንተ ነኝ አለ ቅዱስ ጳውሎስ #ሊቃው ንተ_ቤተ_ክርስቲያን÷የኤፌሶን ሰዎች


ልብ ለልብ እ ንዲገናኙ ስለቤተ ክርስቲያን በአንድ በመንፈስ አንድ ሀሳብ እንዲጸኑ ያዛቸዋል አንድነታቸው ምንድነው ቢሉ
ክርስቶስን ማምለክ በ ክርስትና መጽናት።( ቆላስይስ 2÷5 )

4፤በመጠራታችኹ፡ባንድ፡ተስፋ፡እንደ፡ተጠራችኹ፡አንድ፡አካልና፡አንድ፡መንፈስ፡አለ፤

# በአንድ_ተስፋ_ሲል÷ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል ለማመን የተጠራ ሁሉ አንድ መንግስተ ሰማይን ለመውረስ ተስፋ ይዞ
እንደተከተለው የሚያስረዳ ነው ይላሉ ሊቃውንቱ ። ክርስቲያን ሁሉ ተስፋ የሚያደርገው አንድ ነገር አለ እሱም ከኢየሱስ ክርስቶስ
ጋር በአድሲቷ ሰማይ በአድሷ ኢየሩሳሌም መኖር ( 1 ኛ ጴጥ 1÷3 ) ( ቆላስያስ 1÷3-5 )

#አንድም÷_ቅዱስ_ጳውሎስ_አንድ_አካል_ሲል ÷ክርስቲያኖች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ አካል ነን ሲል ነው።( ሮሜ 12÷5 )

#አንድ_መንፈስ_ማለቱ÷አንድ ልብ አንድ ሀሳብ ማለት ሲሆን በአንድ ልብ በአንድ ሀሳብ በፍቅር ሁኑ ሲላቸው ነው። ( ኤፌሶን
4÷1-3 )

5፤አንድ፡ጌታ፡አንድ፡ሃይማኖት፡አንዲት፡ጥምቀት፤

#ሊቃውንተ_ቤተክርስቲያን_

#አንድ_ጌታ_ሲል÷ ኢየሱስ ክርስቶስን ነው።( ዮሐ 3÷16 )

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_አንድ_ሐይማኖት_ሲል÷የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ ኢየሱስ ክርስቶስ ( እግዚአብሔር ) መሆኑን


ተረድቶ በትክክለኛው የአምልኮ ስርአት መጽናት ነው።

# አንድም÷ መታመንና መመለክ የሚገባው አንድ ጌታ ስለሆነ አንድ ጌታ መሆኑን ሲያስረዳ አንድ ሐይማኖት ሊ ል ችሏል
ሐዋርያው አንድ ሐይማኖት ሲል የክርስትናን ሐይማኖት መሆኑን አንዲት ጥምቀት በማ ለት አረጋግጧል አንዱን ጌታ በማምለክ
ልዩነቶች አሉ የእግዚአብሔር ልጅ ሰው መሆኑ የተገለጠ ሲሆን እግዚአብሔር አይወርድም አይወለድም የሚሉም አሉ ይላሉ
ሊቃውንቱ።

#የቤተ_ክርስቲያን_አባቶች_አንዲት_ጥምቀት_ሲል÷የሥላሴ ልጅነት ጸጋን ለማገኘት አንድም ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ


ለመሆን ጥምቀት ያስፈልጋል የጥምቀት ዋነኛው አላማ የሰው ልጆችን የእግዚአብሔር ልጆች ማድረግ ነው። ( ማቴ 28÷19-20 )(
ሮሜ 6÷1 )
ከክርስቶስ ጋር አንድ ለመሆን ተጠምቀናል እና ኃጢአትን መስራት አይገባንም።

6፤ከዅሉ፡በላይ፡የሚኾን፡በዅሉም፡የሚሠራ፡በዅሉም፡የሚኖር፡አንድ፡አምላክ፡የዅሉም፡አባት፡አለ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን÷ቅዱስ_ጳውሎስ_አንድ_አምላክ_የሁሉም_አባት_ማለቱ÷እግዚአብሔር አብን ነው የሚያጠቅሰው (


መዝ 109/110÷1 ) ( ሮሜ 9÷5 ) ( 1 ኛ ቆሮ 8÷6 )

7፤ነገር፡ግን፥እንደክርስቶስ፡ስጦታ፡መጠን፡ለያንዳንዳችን፡ጸጋ፡ተሰጠን።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ÷የጸጋዎች ሁሉ ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ለክቶ መጥኖ መዝኖ ለእያንዳንዳችን


ጸጋን ይሰጣል።ለአንዳንዱ የዝማሬ ጸጋ ለአንዳንዱ የማስተማር ለአንዳንዱ የመተርጎም በዚህ መልኩ ብዙ የተለያዩ ጸጋን
እንደሚሰጠን የሚያሳይ ክፍል ነው።

8፤ስለዚህ፦ወደ፡ላይ፡በወጣ፡ጊዜ፡ምርኮን፡ማረከ፡ለሰዎችም፡ስጦታን፡ሰጠ፡ይላል።

ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ቃል ያጣቀሰው ከመዝሙረ ዳዊት ነው።( መዝ 67÷18 )

# ወደ_ላይ_ በወጣ_ጊዜ_ሲል÷ጌታችን ሞትና መቃብርን ድል አድርጎ መነሳቱን ነው በአረገ ጊዜ ማለቱ ነው እርገቱን ይናገራል።

# ምርኮ ን_ማረከ_ማለቱ÷በሲኦል በዲያቢሎስ ባርነት ተይዘው የሚኖሩ ነፍሳትን ማርኮ ወደ ገነት መውሰዱን ያመለክታል። ( 1 ኛ
ጴጥ 3÷19 )

#ለሰዎችም_ሥጦታን_ሰጠ÷ይህን ክፍል ሊቃውንተ ቤተብክርስቲያን በሁለት ከፍለውታል።

1 ኛ,ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ለሐዋርያት ሰጠ ( የሐዋ 2 )

2 ኛ,በሲኦል ለነበሩ ነፍሳት እረፍትን ሰላምን ሰጣቸው።


9፤ወደምድር፡ታችኛ፡ክፍል፡ደግሞ፡ወረደ፡ማለት፡ካልኾነ፥ይህ፡ወጣ፡ማለትስ፡ምን፡ማለት፡ነው፧

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን÷ወደ_ምድር_ታችኛው_ክፍል_ማለቱ÷ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ መቃብር ወረደ


ማለት ነው።

ጌታችን ወደመቃብር ወረደ ካላልን ተነሳ ወደ ላይ አረገ ድል አደረገ ማለት አንችልም ።ይህ ክፍል ስለትንሳኤው ይናገራል።

10፤ይህ፡የወረደው፡ዅሉን፡ይሞላ፡ዘንድ፡ከሰማያት፡ዅሉ፡በላይ፡የወጣው፡ደግሞ፡ያ ው፡ነው።

#የወረደው_ሲል÷ ወደ መቃብር የወረደው

#ሁሉን_ይሞላ_ዘንድ_ከሰማያት_ሁሉ_በላይ_የወጣው_ሲል ÷ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው ያረገው በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው

#ደግሞም_ያው_ነው_ማለቱ÷ ያ የሞተው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው የተቀበረው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ከሙታንመካከል ተለይቶ


ደግሞ በኩር ሆኖ ያጥቢያ ኮከብ ሆኖ የተነሳው ያረገው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ሲል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ለምን እንዲህ አለ ቢባል
አንዳንዶች የተሳሳተ ትምህርት እንዳይናገሩ ይህም የተወለደው የሞተው የተነሳው ያረገው ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ያውቁ ዘንድ
ነው።

11፤ርሱም፡አንዳንዶቹ፡ሐዋርያት፥ሌላዎቹም፡ነቢያት፥ሌላዎቹም፡ወንጌል
ን፡ሰባኪዎች፥ሌላዎቹም፡እረኛዎችና፡አስተማሪዎች፡እንዲኾኑ፡ሰጠ፤

# እንዲሆኑ_ሰጠ_ማለት_እግዚአብሔር_አምላክ_ የተለያየ_ጸጋን_ሰጣቸው_ሲል_ነው

# እርሱ_ያለው_ኢየሱስ_ክርስቶስን_ነው_ኢየሱ_ክርስቶስን_ነው።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን÷#ሐዋርያት_የሚላቸው 12 ቱን ሐዋርያት ሲሆን

#ነብያት_የሚላቸው÷ሰባ ዐርድዕትን ናቸው።

# ወንጌል_ሰባኪያን_የሚላቸው÷ ጳጳሳትን ነው

#እረኞች_የሚላቸው÷ቀሳውስትን ነው /የንስሀ አባቶችን ነው።

#አስተማሪዎች_የሚላቸው÷ተርጓሚዎችን ነው።
12-13፤ዅላችን፡የእግዚአብሔርን፡ልጅ፡በማመንና፡በማወቅ፡ወደሚገኝ፡አንድነት፥ሙሉ፡ሰውም፡ወደ፡መኾን፥የክርስቶስም፡ሙላቱ፡
ወደሚኾን፡ወደ ፡ሙላቱ፡ልክ፡እስክንደርስ፡ድረስ፥ቅዱሳን፡አገልግሎትን፡ለመሥራትና፡ለክርስቶስ፡አካል፡ሕንጻ፡ፍጹማን፡ይኾኑ፡ዘንድ።

# ሁላችን_የእግዚአብሔርን_ልጅ_በማመንና_በማወቅ_ወደሚገኝ_አንድነት_ሲል_ሊቃውንተ_ቤተክር ስቲያን÷ከክርስትና በፊት


በሰው ልጆች መካከል ህዝብና አህዛብ የሚል ሰፊ መለያየት እብደነበረ ይታወቃል በክርስትናው ግን የሰው ዘር አንድ መሆን
እንዲገባቸው ሐዋርያው ይነግረናል ይህም ማለት በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር አምላክ የአይሁድ አምላክ ነበረ በኃዲስ ኪዳን
ግን በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ሁላችንም ልጆቹ ነን እሱ አምላካችን እ ኛ ህዝቦቹ ነን ሲል ነው።( የሐዋ,ሥራ 1÷7 )

# የክርስቶስም_ሙላቱ_ወደ_ሚሆን_ወደ_ሙላቱ_ልክ_እስክንደርስ_ማለቱ÷ሙሉ ሰው ወይም ወደ ሙላቱ የሚለው የአካል


ሙሉነት አይደለም በመንፈሳዊ ህይዎት ሙሉ መሆንን ነው ማለትም በእምነት በስነ ምግባር መሞላት ወይም መብቃት ማለት
ነው።

#ለክርስቶስ_አካል_ህንጻ_ሲል÷ምዕመናን የክርስቶስ አካል ለመሆን እንደ ህንጻ ያድጋሉ ማለት ነው።ማለትም በእግዚአብሔር ቃል
እየተሰሩ

#ፍጹማን_ይሆኑ_ዘንድ_ሲል÷በክርስቶስ ኢየሱስ ፍጹማን መሆን ቅዱሳንን መምሰል በፍቅር መሞላት ለተፈጠርንበት ዓላማ መኖር
ማለት ነው።( ኤፌ 2÷10 )

1 4፤እንደ፡ስሕተት፡ሽንገላ፡ባለ፡ተንኰል፡በሰዎችም፡ማታለል፡ምክንያት፡በትምህርት፡ነፋስ፡ዅሉ፡እየተፍገመገምን፡ወዲያና፡ወዲህም፡
እየተንሳፈፍን፡ሕፃናት፡መኾን፡ወደ፣ፊት፣አይገ፟ባ፟ንም፥

#እንደ_ስህተት_ሽንገላ_ባለ_ተንኮል_ሲል_ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህንን_ክፍል_ሲተረጉሙ ÷ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን


ሰዎች በስህተት ቃል በስህተት ትምህርት ከሚያስተምሩ ሰዎች ትምህርት መሰናከል እንደማይገባ ይጠበቁ ዘንድ ሲያሳስባቸው ነው
( 2 ኛ ጴጥ 2 ÷ 1 )

#በሰዎችም_ማታለል_ምክንያት_በትምህርት_ነፋስ_ዅሉ_እየተፍገመገምን_ወዲያና_ወዲህም_እየተንሳፈፍን_ሕፃናት_መኾን_ወደ
_ፊት_አይገ፟ባ፟ንም_ሲል_ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲተረጉሙ÷የስህተቱን_ትምህርት_በነፋስ_ይመስለዋል። የነ
ፍስ ኃይል የቆሙ ነገሮችን ገፍትሮ እንደሚጥል ክብደታቸው ቀላል የሆኑ ነገሮችንም እንደሚያንሳፍፍ ሁሉ በስህተተኞች ትምህርት
የምንንሳፈፍ ሕፃናት እንዳንሆን ይመክረናል።#አንድም ስር ሰዳችሁ ተሰሩ ሲል ነው።

15፤ነገር፡ግን፥እውነትን፡በፍቅር፡እየያዝን፡በነገር፡ዅሉ፡ወደርሱ፡ራስ፡ወደሚኾን፡ወደ፡ክርስቶስ፡እንደግ፤

#ቅዱስ_ጳውሎስ÷በፍቅርና በእውነት ማደግ አስፈላጊ መሆኑን ያሳስበናል።

# ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህንን_ክፍ ል_ሲተረጉሙ÷በእውነትና በፍቅር ማደግ አስፈላጊ መሆኑን ከመንገሩም በላይ


የእውነትና የፍቅር እራስ ወይም ቁንጮ ወደሚሆነው ወደ ክርስቶስ መድረስ/ማደግ እንዳለብን ያስረዳናል።
#አንድም÷እርሱን እንምሰል ሲል ነው ( 1 ኛ ቆሮ 11÷1 )

16፤ከርሱም፡የተነሣ፡አካል፡ዅሉ፡እያንዳንዱ፡ክፍል፡በልክ፡እንደሚሠራ፥በተሰጠለት፡በዥማት፡ዅሉ፡እየተጋጠመና፡እየተያያዘ፥ራሱን፡
በፍቅር፡ለማነጽ፡አካሉን፡ያሳድጋል።

#የኃዲስ_ኪዳን_ትርጓሜ_መምህራን_ይህንን_ክፍል_ሲፈቱ÷የሰውነት አካላት በጅማት እየተያያዙ እየተጋጠሙ እንደሚያድጉ


በመንፈሳዊ ህይዎታችንም በፍቅር ተያይዘን ማደግ እንዳለብን ይመክረናል። ( የሐዋርያት ሥራ 2÷43-ፍጻሜው ) ( ገላ 6÷1 )

17፤እንግዲህ፡አሕዛብ፡ደግሞ፡በአእምሯቸው፡ከንቱነት፡እንደሚመላለሱ፡ከእ ን ግዲህ፡ወዲህ፡እንዳትመላለሱ፡እላለኹ፡በጌታም፡ኾኜ፡
እመሰክራለኹ።

# ቅዱስ_ ጳውሎስ_አህዛብ_የሚላቸው÷ያላመኑትን ዛሬም ጣኦትን የሚያመልኩትን በኤፌሶን የሚኖሩ አህዛብን ነው ።

#በአእምሯቸው_ከንቱነት_ሲል_የኃዲስ_ኪዳን_መምህራን_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ÷እግዚአብሔር የፈጠረው አእምሮ ከንቱ ሆኖ


ሳይሆን ነገር ግን መልካም ሆኖ እንዲያስብ የተፈጠው አእምሮ ለመልካም ነገር የተፈጠረው አእምሮ መልካም መስራት መልካምን
ማሰብ ሲችል እነሱ ግን ለከቱ ነገር አውለውታል እና ነው።

#ከእንግዲህ_ወዲህ_እንዳትመላለሱ_እላለሁ_በጌታም_ሆኜ_እመሰክራለሁ_ሲል_ቅዱስ_ጳውሎስ÷እየገሰጻቸው ነው ምን እያለ
ቢሉ÷እናንተ በቀድሞ ህይዎታችሁ ከንቱ የሆነ ነገር ትከተሉ ነበር ጣኦትን ታመልኩ ነበር አሁን ግን ክርስቲያን ከሆናችሁ በኋላ
ትታችሁት የመጣችሁትን የአህዛብን ልማድ ወይም መንገድ ዞራችሁ እንዳትመለከቱ ሲላቸው ነው። ( ገላ 5÷24 ) ( ሮሜ 12÷2 )

18፤እነርሱ፥ባለማወቃቸው፡ጠንቅ፥በልባቸውም፡ደንዳናነት፣ጠንቅ፣ልቡናቸው፣ጨለመ፥ከእግዚአብሔርም፡ሕይወት፡ራቁ፤

#ቅዱስ_ጳውሎስ_እነርሱ_እሚላቸው÷በኤፌሶን ያሉትን አህዛብን ነው በክርስቶስ ያላመኑትን


በጥምቀት አማካኝነት ወደ ቤተ ክርስቲያን ያልተጨመሩትን ነው።ስለዚህ ክርስቶስን ባለመቀበላቸው ህይዎት የላቸውም ሲለን
ነው።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲተረጉሙ÷በኤፌሶን ያሉ አህዛቦች በሁለት መንገድ ተሳስተዋል ይላሉ

1 ኛ,የሚሰሩት ሥራ እንደሚያጠፋቸው ባለማወቃቸው የሚጠቅማቸውን መለየት ባለ መቻላቸው ሲሆን

2 ኛ,ልባቸውን ቆልፈው የሚነገራቸውን ባለመቀበል ወደ ጥፋት ይገሰግሳሉ

{ ዮሐ 14÷ 6 } { ዮሐ 1÷4 } { ዮሐ 10÷10 } { ፊልጵስዩስ 1÷21 } { ዮሐ 6÷48 }


19፤ደንዝዘውም፡በመመኘት፡ርኵሰትን፡ዅሉ፡ለማድረግ፡ራሳቸውን፡ወደ፡ሴሰኝነት፡አሳልፈው፡ሰጡ።

# መጋቤ _ኃዲስ_መምህር_ስቡህ_አዳምጤ_ይህንን_ክፍል_ሲፈቱ÷አህዛብ የሚሰሩትን ኃጢያት ሴሰኝነት ብሎ ገለጸው ይላሉ።

#ሴሰኝነት_ማለት_ዝሙት_ማለት_ሲሆን÷ ባለማስተዋል እንደሚሰሩት ለመግለጽ ደንዝዘዋል አለ።

# አንድም÷ደንዝዘው_ሲል ÷የኤፌሶን ሰዎች ባለማወቅ በዝሙት ደንዝዘው በኃጢያት ይመላለሳሉ ሲል ነው።

ሴሰኝነት ማለት ዝሙት ነው ሲንል መዘሞት ስንል የስጋን ዝሙት ብቻ ሳይሆን ሰው የተፈጠረበትን አላማ ክርስቶስን ማምለክ
ሆኖ ሳለ የኤፌሶን ሰዎች ግን የተፈጠሩለትን አምልኮ እግዚአብሔር ትተው የፈጠራቸውን አምላክ ትተው ለጣኦትም ሲሰግዱ
እግዚአብሔርን ሲክዱ ዘሞቱ ማለት ነው ግን ይህን ሲያደርጉ ባለማወቅ ነው ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ደንዝዘው አለ።

20፤እናንተ፡ግን፡ክርስቶስን፡እንደዚህ፡አልተማራችኹም፤

#ቅዱስ_ጳውሎስ_እናንተ_ግን_ያላቸው_የኤፌሶንን_ክርስቲያኖች_ነው።

#እንዴት_ለምን_ቢሉ÷ ክርስቲያን ከሆናችሁ በኋላ አህዛቦች የሚያደርጉትን ተግባር አታደርጉም ሲላቸው ነው።

#የኃዲስ_ኪዳን_ትርጓሜ_መምህራን_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ_አንድም÷በክርስቶስ ያመናችሁት ክርስቶስን ለመምሰል እንጅ አህዛብን


ልትመስሉ አይደለም እንደ አህዛብ ለጣኦት ልትሰግዱ ሳይሆን ስለክርስቶስ ለክርስቶስ በክርስቶስ እንድትኖሩ ነው ሲላቸው ነው።
{ 1 ኛ ዮሐ 1÷6 }

21፤በርግጥ፡ሰምታችኹታልና፥እውነትም፡በኢየሱስ፡እንዳለ፡በርሱ፡ተምራችዃል፤

# ቅዱስ_ጳውሎስ_እውነት_ብሎ_እሚጠራው_ወንጌልን_ነው_በእርግጥ_ሰምታችኋልና_ማለቱም_የኤፌሶን_ሰዎች_የወን

ጌልን_እውነት_ሰምተው_ከአህዛብ_ማንነታቸው_ከጣኦት_አምላኪነታቸው_ወጥተው_ወደ_አምልኮተ_እግዚአብሔር_በመምጣታ
ቸው_ነው።

# አንድም_እውነት_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ነው።

# አንድም÷ከብሉይ ኪዳን የተሻለውን የኃዲስ ኪዳንን ትምህርት ሰማያዊ በረከት የሚያላብሰንን ወንጌል ሰምተው ቃለ እግዚአብሔ
ርን ተቀብለው አምነዋልና ነው ።
ስለዚህም ዲያና አምላክ እንዳልሆነች ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ሰምታችኋል
#አንድም÷ወንጌልን ሰምታችኋል እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ቃል አውቃችኋል ሲል ነው። { ዮሐ 14÷6 } { 1 ኛ ዮሐ 2÷23 }

22፤ፊተኛ፡ኑሯችኹን፡እያሰባች ኹ፡እንደሚያታልል፡ምኞት፡የሚጠፋውን፡አሮጌውን፡ሰው፡አስወግዱ፥

#ፊተኛ_ኑሯችሁን_እያሰባችሁ_ማለቱ÷ያለፈውን ያን ትታችሁት የመጣችሁት የኃጥያት ህይዎታችሁ ሲል ነው አንድም አርጤምስን


ስታመልኩበት የነበረው የአህዛብነት ህይዎታችሁ ሲል ነው።

#እንደሚያታልል_ምኞት_ሲል÷ደስታን የሚሰጥ የሚመስል ነው ነገር ግን ።ዘለዓለማዊ እረፍት የሚሰጥ ግን ክርስቶስ ነው።

#የሚጠፋውን_አሮጌውን_ሰው_አስወግዱ_ሲል÷የአለፋችሁበት በኃጥያት አሮጌ የሆነ ሰውነታችሁን ማንነት አስወግዱ አንድም


ኃጥያትን አስወግዱ ማለቱ ነው።

#አንድም አሮጌ ያለው ኃጢያትን ነው።

23፤በአእምሯችኹም፡መንፈስ፡ታደሱ፥

# ቅዱስ_ጳውሎስ_በአእም ሯችሁም_መን
ፈስ_ታደሱ_ሲል÷እናንተ_የኤፌሶን_ሰዎች__አሁን_አዲስ_ፍጥረት_ናችሁ_በፊተኛው_ኑሮአችሁ_ቀድሞ_ታስቡት_የነበረውን_የኃ
ጢያት_ልምምድ_ቁረጡት_ሲላቸው_ነው።ምድራዊን ሳይሆን ሰማያዊ በረከት ሰማያዊ ጸጋን የሚያላብሰውን ህይዎት አስቡ
ሲላቸው ነው።{ ራእይ 21÷26-ፍጻሜው }

24፤ለእውነትም፡በሚኾኑ፡ጽድቅና፡ቅድስና፡እንደእግዚአብሔር፡ምሳሌ፡የተፈጠረውን፡ዐዲሱን፡ሰው፡ልበሱ።

# እንደ_እግ
ዚአብሔር_ምሳሌ_ሲል÷ኢየሱስ_ክርስቶስ_ወልደ_እግዚአብሔር_ከእግዚአብሔር_አብ_ጋር_አንድ_መሆኑን_ለመግለጽ_ነው
#ይላሉ_ሊቃውንተ_ቤተ ክርስቲያን።

# የተፈጠረውን_ማለቱ÷ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ከድንግል ማርያም ስጋ ተዋህ ዶ በስጋ መገለጡን የሚያመለክት
ነው።#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን የተፈጠረውን የሚለው ቃል ጥያቄ እንዳይፈጥር በምሳሌ እንዲህ አስቀምጠውልናል ለምሳሌ
አንድ ሳይንቲስ ት አንድን ቁስ ከሌላው ቁስ ጋር በማገናኘት አንድ ጠቃሚ የሆነ ነገርን ሊፈጥር እንደሚችል ያም እርሱ የሰራው ነገር
የሳይንቲስት እገሌ ፈጠራ እየተባለ ይነገራል ነገር ግን ሳይንቲስቱ ማዕድኖቹን አልፈጠረም የማዕድኑ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው
ሳይንቲስቱም ማዕድን ስራ ላይ እንዲውል ስላደረገ ብቻ የእሱ ፈጠራ እየተባለ ይነገርለታል ሳይፈጥር ፈጣሪ እንደተባለ እናስተውል
ይላሉ ።

#ቅዱስ_ጳውሎስ_አዲስ_ሰው_ያለው_ለስም_አጠራሩ_ክብርና_ምስጋና_ይግባውና_ኢየሱስ_ክርስቶስን_ነው።
25፤ስለዚህ፥ውሸትን፡አስወግዳችኹ፥ርስ፡በርሳችን፡ብልቶች፡ኾነናልና፥እያንዳንዳችኹ፡ከባልንጀራዎቻችኹ፡ጋራ፡እውነትን፡ተነጋገሩ።

# ስለዚህ_ውሸት_አስወግዳችሁ_ማለቱ÷በኢየሱስ_ክርስቶስ_አካል_ላሉ_እኅቶቻችሁና_ወንድሞ
ቻችሁ_ጋር_በውሸት_ቃል_አትነጋገሩ_በእውነት_ተነጋገሩ_ውሸት_የአህዛቦች_ፀባይ_ነውና_ሲል ነው።

#እርስ_በእርሳችን_ብልቶች_ኾነናልና_ይህንን_ክፍል_ሲተረጉሙ_ሊቃውንተ_ቤተክርስቲይን÷የተለያዩ የአካል ክፍሎች ማለት


ሲሆን አንድ ሰው ብዙ የአካል ክፍሎች ይኖሩታል እነዛም አካላት ያሉት ሰው አንድ ሰው እንደሆነ ሁሉ ክርስቲያኖች ሁሉም የአንድ
የክርስቶስ አካል ክፍሎች ናቸውና።

26፤ተቈጡ፡ኀጢአትንም፡አታድርጉ፤

#ተቈጡ__ይህ_ቃል_የሚያሳየው÷ሰው በባህሪው ቁጡ እንደሆነ እንደሚቆጣ ነው።

#ኃጢአትንም_አታድርጉ_ሲል÷ሰው ቁጣውን ማብረድ እንዳለበት የሚያሳይ ነው።

27፤በቍጣችኹ፡ላይ፡ፀሓይ፡አይግባ፥ለዲያብሎስም፡ፈንታ፡አትስጡት።

#ቅዱስ_ጳውሎስ_በቁጣችሁ_ላይ_ጽሓይ_አይግባ_ማለቱን_የኃዲስ_ኪዳን_ትርጓሜ_መምህራን_ሲፈቱት_ጽሓይ_ሳይገባ_ቁጣች
ሁን_አብርዱት #አንድም ጽሓይ ሳይገባ ይቅር ማለት መታረቅ እንደሚያስፈልግ ይመክራል { ማቴ 5÷22-24 } { ሆሴ 6÷6 }

# አንድም_ቁጣ_መባሉን_ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_እንዲህ_ይፈቱታል÷ የሚገባ ቁጣ አለና ነው ይላሉ ይህ የሚገባ ቁጣ የተባለ


ምንድ ነው ቢሉ ÷#አንድም ልጆች አንማርም ሲሉ የተማሩትንም ሲያጠፉ

# አንድም መናፍቃን በጉባኤ እንዳይሰለጥኑ #አንድም ምእመናን ከሀይማኖት እንዳይወጡ ከምግባር እንዳይናወጡ ለማድረግ
መቆጣት እንደሚገባ ተገልጧል።

28፤የሰረቀ፡ከእንግዲህ፡ወዲህ፡አይስረቅ፥ነገር፡ግን፥በዚያ፡ፈንታ፡ለጐደለው፡የሚያካፍለው፡እንዲኖርለት፡በገዛ፡እጆቹ፡መልካምን፡
እየሠራ፡ይድከም።

#የሰረቀ_ከእንግዲህ_ወዲህ_አይስረቅ÷#ይህ_ክፍል_የሚያሳየው÷#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
ታላቁ_ተአምር_ይህ_ነው።መጥፎ ነገርን ሲያይ የኖረ ዓይን መልካም ነገርን ሲመልከት ሲሰርቅ ሲዘርፍ የኖረ እጅ ምጽዋትን
በመስጠት ሲጠመድ ክፉ ነገር ሲሰማ የኖረ ጆሮ የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል ወንጌልን በመስማት ሲለምልም ክፋትን ስድብን
ሲናገር የኖረ አንደበት በማመስገን በመዘመር ሲቀደስ ይላል። { የሐዋ,ሥራ 2÷45-ፍጻሜ }

# የኃዲስ_ኪዳን_ትርጓሜ_መምህራን÷ሐዋርያው በስርቆት እሚተዳደሩ ሰዎችን ስርቆታቸውን በስርቆት ፋንታ እየሰሩ እየደከሙ


እንዲበሉ ያሳስባል።
29፤ለሚሰሙት፡ጸጋን፡ይሰጥ፡ዘንድ፥እንደሚያስፈልግ፡ለማነጽ፡የሚጠቅም፡ማናቸውም፡በጎ፡ቃል፡እንጂ፡ክፉ፡ቃል፡ከአፋችኹ፡ከቶ፡
አይውጣ።

# ቅዱስ_ጳውሎስ_ለሚሰሙት_ጸጋን_ይሰጥ_ዘንድ_ሲል÷ምህረትን የሚያስገኘውን ከእግዚአብሔር ዘንድ ጸጋን የሚያላብሰውን


የሚያንጸውን ወደ ክርስቶስ የሚያቀርበውን ቃል ስበኩ እናንተም በምትሰብኩት ቅዱስ ቃል ሰዎች ወደ ክርስቶስ ይቀርባሉ ሲል
ነው።{ 1 ኛ ጴጥ 2÷12 } { ቆላስይስ 4÷5-6 } { ቲቶ 3÷10-15 }

30፤ለቤዛም፡ቀን፡የታተማችኹበትን፡ቅዱሱን፡የእግዚአብሔርን፡መንፈስ፡አታሳዝኑ።

#ቅዱስ_ጳውሎስ_የቤዛ_ቀን_ማለት የድኅነት ቀን ማለት ነው።

# የታተማችሁበት_ማለት÷የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆን መታወቂያችሁ ነው ሲል ነው።የልጅነት ጸጋን ያገኛችሁበ ት።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ_የእግዚአብሔን_መንፈስ_አታሳዝኑ_ማለቱ÷በኃጥያታችሁ ምክንያት መንፈስ


ቅዱስ እንዲርቃችሁ አታድርጉ ማለት እንጅ ለእግዚአብሔር #አንድም ለመንፈስ ቅዱስ ኃዘን አይስማማውም።

31፤መራርነትና፡ንዴት፡ቍጣም፡ጩኸትም፡መሳደብም፡ዅሉ፡ከክፋት፡ዅሉ፡ጋራ፡ከእናንተ፡ዘንድ፡ይወገድ።

#ይህ_ክፍል_የሚያሳየው÷ቅዱስ ጳውሎስ ክፉ ነገሮችን ሁሉ ክርስቲያኖች ሁላችሁ ከናንተ አርቁ እናንተ የክርስቶስ አካል ናችሁና
እርኩስ ነገርን ከሰውነታችሁ አርቁ ሲል ነው

{ 1 ኛ ጴጥ 3÷10 }

32፤ርስ፡በርሳችኹም፡ቸሮችና፡ርኅሩኆች፡ኹኑ፥እግዚአብሔርም፡ደግሞ፡በክርስቶስ፡ይቅር፡እንዳላችኹ፡ይቅር፡ተባባሉ።

#እግዚአብሔር_የሚለውና_ክርስቶስ_የሚለው_የተለየ_ነገር_አይደለም እግዚአብሔር ይቅር የሚል ኃይል ክርስቶስ ይቅርታ


የተደረገበት መሳሪያ አይደለም እግዚአብሔር ስጋ ተዋሐደ ክርስቶስ ስለተባለ በተዋሐደው ስጋም ሞቶ ዓለሙን ይቅር ስላለው
በክርስቶስ ይላል እንጅ።

{ ገላ 5÷19-22 }

ስብሐት ለአብ🍀 ስብሐት ለወልድ🍀 ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ 🍀ወለዓለም ዓለም አሜን

You might also like