You are on page 1of 15

የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ፡10፤

👉1፤በቂሳርያም፡ኢጣሊቄ፡ለሚሉት፡ጭፍራ፡የመቶ፡አለቃ፡የኾነ፡ቆርኔሌዎስ፡የሚሉት፡አንድ፡ሰው፡ነበረ።

#ቂሳርያ የታሪክ ተመራማሪዎች ቆፍረው እንዳዘጋጁትና አሁንም ድረስ ሂዶ መጎብኘት እንደሚቻል ማሳወቅን እንዎዳለን በዚች ቦታ
ለቆርኔሌዎስ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለታል ስለሱ ታላቅነትም በዚች ቦታ ተነግሯል።

#ቂሳርያ ወደብ ነች በይሁዳ የምትገኝ የሮማዊያን ግዛት የሮማውያን ዋና ቦታቸው ነች ።

በብዙ ስያሜ ትጠራለች ከቴላቪቭ ወደ 30 ማይል ያህል እርቀት አለው በኪ,ሜ 45 -46 ኪ,ሜ አካባቢ የሚሆን ነው።

#ሮማዊያን ይገዟት የነበረች ታላቅ ከተማ ነች ሮማውያን እንደ ዋና ከተማ አድርገው የሚጠቀሙባት ከተማ ነች።

#ቆርኔሌዎስ_ማነው? ሮማዊ አህዛብ ነው ከስሩ ብዙ ሰዎች አሉ የሚገዙለት ሹም ነው በሮማውያን ዘንድ ትልቅ ሥልጣን ያለው መቶ
አለቃ ነው { ማቴ 8÷5-11 }

#ቆርኔሌዎስ፦ታላቅ ሥልጣን እና ክብር ቢኖረውም በምድር ላይ የተንጣለለ ኑሮ ቢኖርም እንኳን እግዚአብሔርን ግን በሓብትና
በሥልጣን ምክንያት አረሳም ከቤተሰቦቹ ጋር እግዚአብሔርን አብዝቶ እፈራና ይፈልግ ነበር ይህም የሚያሳየው ታላቅነቱን ነው።
እንደምሳሌ አስቴርን ብንወስድ አሥቴር ንግስት ነች ነገር ግን በሐማ ምክንያት የመጣውን ያንን የሞት ደብዳቤ መርዶኪዎስ ሲነግራት
ያማረ ነገር ስለበላች ያማረ ነገር ስለጠጣች ያማረ አልጋ ላይ ስለተኛች ስልጧና ትልቅ ስለሆነ ህዝቦቿን ችላ አላለችም እንዲሁም
ቆርኔሌዎስ የተመቻቸ ህይዎት ቢኖረውም አህዛብ ቢሆንም አብዝቶ ግን እግዚአብሔርን ከልቡ ይፈልግ ነበር ያለ ማስመሰል እውነት
በሆነ ፍለጋ ከልቡ እግዚአብሔርን ከቤተሰቦቹጋ ይፈልግ ነበር። { ማቴ 27÷1-ፍጻሜው }

👉2፤ርሱም፡ከቤተ፡ሰዎቹ፡ዅሉ፡ጋራ፡እግዚአብሔርን፡የሚያመልክና፡የሚፈራ፡ለሕዝብም፡እጅግ፡ምጽዋት፡የሚያደርግ፡ወደ፡
እግዚአብሔርም፡ዅልጊዜ፡የሚጸልይ፡ነበረ።

#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈዎርቅ_ስለ_ቆርኔሌዎስ_ስናገር፦በጣም ይገርማል እንደ ቆርኔሌዎስ አይነት ሰው ማግኘት እጅግ ከባድ ነው


ሥልጣኑንም እግዚአብሔርንም መፍራትን { መውደድ } አቅፎ የሚይዝ

#ግብጻዊው_አባት_ፋዘር_ቴዎድሮስ_ማላቲ፦እግዚአብሔር ለቅዱስ ጴጥሮስ ለአህዛቦች የእምነት በር ይከፍት ዘንድ ቆርኔሌዎስን


ተጠቀመበት ይላሉ { ዘፍ 19÷1}
እግዚአብሔር ቆርኔሌዎስን የመረጠበት ምክንያት👇👇

#ግብጻዊያን_አባቶች፦እርሱና ቤተሰቡ ጣኦትን አላመለኩም እግዚአብሔርን ይፈሩ ነበር

#የተቸገሩ_ሰዎችን_ይረዳል።

#የጸሎት_ሰው_ነው።

#የኢትዮጵያ_ቤተክርስቲያን_ሊቃውንት፦ከቤተሰቡ ጋር እግዚአብሔርን የሚፈራ ደግ ሰው ነበር። ፈራየ እግዚአብሔር የምግባር ነው 👉

እግዚአብሔርን መፍራቱ በተግባር የተገለጸ ነው። ለህዝቡ ብዙ ምጽዋትን ያደርግ ነበር 👉የተቸገሩትን አብዝቶ ይረዳ ነበር እለት እለት

ጸሎት ያደርግ ነበረ 👉ዘወትር በጸሎት ይተጋ ነበር።

👉3፤ከቀኑም፡ዘጠኝ፡ሰዓት፡ያኽል፦ቆርኔሌዎስ፡ሆይ፡የሚለው፡የእግዚአብሔር፡መልአክ፡ወደ፡ርሱ፡ሲገባ፡በራእይ፡በግልጥ፡አየው።

#ከቀኑ_ዘጠኝ_ሰዓት፦አይሁዳዊያን ጸሎት የሚያደርጉበት ምጽዋእት የሚያቀርቡበት ሰዓት ነው።

#ቆርኔሌዎስ_እሱ_አይሁዳዊ_አይደለም_እንዴት_በዚህ_ሰዓት_ሊጸልይ_ቻለ_ቢሉ፦የአይሁዳዊያንን አምላክ ያከብር ነበርና ይወድ


ነበርና ነው።ይህም የሚያሳየው ለእግዚአብሔር ያለውን ታላቅ ክብር ነው እነሱ በሚጸልዩበት ስዓት ጸለየ ከአይሁዳዊያን ተምሮ።

#ግብጻዊያን_አባቶች_መልአኩ_ቆርኔሌዎስ_ሆይ_ብሎ_ጠርቶታልና_ቆርኔሌዎስም ይህ የመጣው መልአክ የእግዚአብሔርን መልእክት


ይዞ ወደእርሱ እንደመጣ አውቋል።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦ቆርኔሌዎስ አለው ወደ እርሱ ተመለከተ ባየው ጊዜ ፈራ አለ፦አንድም ፍርሀት አደረበት አቤቱ ምን


ትላለህ አለው ፦ ተናገር ሲል ነው።

መልአኩን በግልጽ ነው ያየው ።


#ግብጻዊያን_አባቶች፦ጌታ ሆይ ማለቱ ከእግዚአብሔር የተላከ መሆኑን አውቋልና ነው ይላሉ።

👉4፤ርሱም፡ትኵር፡ብሎ፡ሲመለከተው፡ደንግጦ፦ጌታ፡ሆይ፥ምንድር፡ነው፧አለ።መልአኩም፡አለው፦ጸሎትኽና፡ምጽዋትኽ፡በእግዚአብሔር፡
ፊት፡ለመታሰቢያ፡እንዲኾን፡ዐረገ።

#ግብጻውያን_የቤተ_ክርስቲያን_አባቶች_ርሱም_ትኩር_ብሎ_ሲመለከተው_የሚለውን_ሀሳብ_ይህ_የተገለጠለት፦እግዚአብሔርንም
ሰውንም የሚወድ ልብ ስላለው ሰማያዊ ነገርን ሊያይ ችሏል ይላሉ።

#ጌታ_ሆይ_ምንድነው_ማለቱ፦ምን ልታዘዝ ሲል ነው።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህንን_ክፍል_ሲፈቱ፦አቤቱ ምን ትላለህ ማለቱ ነው ይላሉ።መልእክትህን ተናገር እኔ አደምጣለሁ


ማለት ነው።

#ጸሎትህና_ምጽዋትህ_በእግዚአብሔር_ፊት_ለመታሰቢያ_እንዲሆን_ዐረገ_የሚለውን_ቃል_ወስደው_ግብጻዊያን_አባቶች፦የእግዚአብ
ሔር_መልአክ_የተላከው፦ወደ አህዛብ ቤት ነው ወደ ቤተ መቅደስ አይደለም የእርሱን መስዋእት ተቀበለ ይህ የሚያሳየው እግዚአብሔር
የሚቀበለው መስዋእት በፍቅር በመታዘዝ እና በምስጋና የሚደረገውን ነው።

{ 1 ኛ ሳሙ 15÷22 } { ኢሳ 1÷11-15 } { ዕብ 2÷1-ፍጻሜ } { ዕብ 13÷1-2 }

👉5፤አኹንም፡ወደኢዮጴ፡ሰዎችን፡ልከኽ፡ጴጥሮስ፡የሚባለውን፡ስምዖንን፡አስመጣ።

👉6፤ርሱ፡ቤቱ፡በባሕር፡አጠገብ፡ባለው፡በቍርበት፡ፋቂው፡በስምዖን፡ዘንድ፡እንግድነት፡

ተቀምጧል፤ልታደርገው፡የሚገ፟ባ፟ኽን፡ርሱ፡ይነግርኻል።

#በባህር_አጠገብ_ናቁርበት_ፋቂ_መባሉ_መባሉ፦ስምኦን ቁርበት ፋቂ ነውና ለዛ ደግሞ ብዙ የባህር ውሃ ያስፈልጋልና ቤቱን በባህር


አጠገብ አድርጓል ይላሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን።

#አንድም_በአይሁዳዊያን_ዘንድ ቁርበት መፋቅ ንጹህ የሆነ ስራ አይደለም ስለዚህም ያገሉት ነበርና ከሌሎች ሁሉ ቤት እርቆ ተለይቶ
ይገኛል የስምኦን ቤት ይላሉ ሊቃውንቱ።አንድም ቤቱን ለመለየት አይከብድም።
#ስለዚህም_የተናቁትን_የሚያከብር_እግዚአብሔር ሰዎች ባገለሉት በስምኦን ቤት ተገኘ ቅዱስ ጴጥሮስም በተናቀውና ሰው ሁሉ ተጸይፎ
ባገለለው በስምኦን ቤት ተገኘ ይህ ምን ያሳያል እግዚአብሔር ሁሉን እንደሚወድ አንዱን ከአንዱ እንደማይለይ የሁሉ አምላክ የሁሉ ጌታ
ሁሉን በፍቅር አይን የሚያይና የተጠሉ የተናቁትን ከፍ እንደሚያደርግ እንደሚያከብር ያሳያል።

#ግብጻዊያን_አባቶች_ስለመላእክት_ሲናገሩ፦የቅዱሳን መላእክት ዓላማቸው ሁሉም ሰው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በቅድስት ቤተ


ክርስቲያን እንዲገናኙ መምራት ነው ይላሉ።

ስለዚህም እውነተኛዋን እምነት አንድም ክርስቶስን ያገኝ ዘንድ ቆርኔሌዎስን እግዚአብሔር ወደጴጥሮስ አንድም ወደ ቤተ ክርስቲያን
ላከው።

#በባህር_ዳር_አለ፦ጃን አርሳሚ ግምጃ ጠቃሚ ነውና ለመንከር እንዲመቸው።አንተም ቤተሰቦችህም እምትድንበትን ገንዘብ እርሱ
ይነግርሀል አለው ይላሉ ሊቃውንቱ።

👉7፤የተናገረውም፡መልአክ፡በኼደ፡ጊዜ፥ከሎሌዎቹ፡ኹለቱን፥ከማይለዩትም፡ጭፍራዎቹ፡እግዚአብሔርን፡

የሚያመልክ፡አንዱን፡ወታደር፡ጠርቶ፥
8፤ነገሩን፡ዅሉ፡ተረከላቸው፥ወደ፡ኢዮጴም፡ላካቸው።

{ ገላ 1÷15-16 }

#ግብጻዊያን_አባቶች_ለምን_እራሱ_አልሄደም_ስለምን_ሎሌዎቹን_ላከ_ቢሉ፦እርሱና ቤተሰቦቹ ከስሩም ያሉት ጭፍሮች ሁሉ መዳንን


ይዎርሱ ዘንድ ነው።

#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈዎርቅ፦ሌላውን ሰው ለማዳን ከማይጥር ክርስቲያን ከዚህ በላይ የቀዘቀዘ ነገር የለም ይላል።
ስለዚህም ቆርኔሌዎስ ብቻውን መዳን ሳይሆን የፈለገው በዙሪያው ያሉትም ሁሉ እንዲድኑ መፈለጉ።

#ከቄሳርያ_ኤዮጴ_32_ኪ,ሜ_ይርቃል።

በፈረስ የ 6 ሰዓት መንገድ ነው ይላሉ ሊቃውንቱ


ይህንንም ያህል ርቀት ተጉዘው መሄዳቸው መስዋእትነት መክፈላቸው ክርስቶስን ለማወቅ ያላቸውን ታላቅ ጽናትና ጉጉት ያሳያል።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_የነገረውም_መልአክ_አልፎ_ከሄደ_በኋላ፦ከባለሟሎቹ ሁለቱን
👉9፤እነርሱም፡በነገው፡ሲኼዱ፡ወደ፡ከተማም፡ሲቀርቡ፥ጴጥሮስ፡በስድስት፡ሰዓት፡ያኽል፡ይጸልይ፡ዘንድ፡ወደ፡ጣራው፡ወጣ።

#ጴጥሮስም_በቀትር_ጊዜ_ከሰገነት_ወጥቶ_ይጸልይ_ነበረ አይሁዳዊያን ሦስት የጸሎት ጊዜያቶች አላቸው እነሱም፦ ጥዋት ቀትርና ማታ


ናቸው።{ መዝ 55÷17 }

#ግብጻዊያን_የቤተ_ክርስቲያን_አባቶች_ቅዱስ_ጴጥሮስ_ለምን_ወደጣሪያው_ወጣ_ቢሉ፦አንድም ለጸሎት አመች ቦታ ስለሆነ ምድራዊ


ነገር አይረብሸውም ከእግዚአብሔር ጋር ለመነጋገር የተመረጠ እንደሆነ ይገመታል ይላሉ።

👉10 -11፤ተርቦም፡ሊበላ፡ወደደ፤ሲያዘጋጁለት፡ሳሉም፡ተመስጦ፡መጣበት፤ሰማይም፡ተከፍቶ፡ባራት፡ማእዘን፡የተያዘ፡ታላቅ፡ሸማ፡
የሚመስል፡ዕቃ፡ወደ፡ምድር፡ሲወርድ፡አየ፤

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ተርቦ_ነበርና_ሊመገብ_ወዶ_ሳለ_ምግብ_እስኪያዘጋጁለት_ድረስ_አርምሞ_መጣበት_ሰማይ_የተከፈተ
_ሆኖ_አየ።

#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ይህን_ክፍል_ሲያብራሩ፦ሰማይ ተከፈተ ሲል፦ሰይማይ እሚከፈትና እሚዘጋ ሆኖ ሳይሆን አዲስ


ሚስጢር አየ የተዘጋ ደጅ በተከፈተ ጊዜ ያልታየ ነገር እንዲታይ ያልተገለጠ ሚስጢር ተገለጠ

#ባራት_ማእዘን_የተያዘ_ታላቅ_ሸማ_የተባለ ችውን_አባቶች_ሲፈቱ_ቅዱስ_ጴጥሮስ_በራእዩ_ያያት_ይች_ሸማ_የተባለችው፦ዓለም
አቀፍዊ የሆነችው የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነች ።የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሚሳሌ ነች ይላሉ።

#አራት_ማእዘን_መባሉ፦ 👉ሰሜን 👉ምስራቅ 👉ምዕራብ 👉ደቡብን ያጠቅሳል ይህም ሐዋርያትና ነብያት በአራቱም ማእዘነ ዓለም ዞረው
ማስተማራቸውንና ቤተክርስቲያንን ማነጻቸውን የሚገልጽ ነው ይላሉ የኢትዮጵያ ሊቃውንትና የግብጽ ሊቃውንቶች በህብረት።

#አንድም፦አራቱን ወንጌል 👉ማቴዎስ 👉ማርቆስ 👉ሉቃስ 👉ዮሐንስንም ያጠቃልላል።

👉12፤በዚያውም፡አራት፡እግር፡ያላቸው፡ዅሉ፡አራዊትም፡በምድርም፡የሚንቀሳቀሱት፡የሰማይ፡ወፎችም፡ነበሩበት።

#ቅዱስ_ጴጥሮስ_በሸማዋ_ውስጥ_የተለያዩ_እንስሳዎችን_ማየቱ፦#እንሰሳዎቹ_የሚያሳዩት_ምሳሌ፦በዓለም አቀፏ ቤተ ክርስቲያን


ውስጥ የተለያዩ ህዝቦች እንደሚኖሩ ያጠቅሳል አህዛቡም አይሁዳዊውም { ገላ 3÷11 } {ቆሮ 5÷17 } { ቆላ 3÷3 } ይህም ማለት
ቆርኔሌዎስ ወደ ቅዱስ ጴጥሮስ ሲሄድ አህዛብ ነው ብሎ አንተ ሮማዊ ነህ አህዛብ ነህ በዚች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አትገባም እንዳይለው
በፍቅር እንዲቀበለው እግዚአብሔር አምላክ እነዚህን የተለያዩ እሰሳዎች በሸማዋ በውጥ አድርጎ ራእዩን የገለጸለት እኔ የአይሁዳዊያን ብቻ
ሳይሆን የአህዛብም አምላክ ነኝ ሲለው ነው አንድም የኔ ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊት ነች ሁሉን አቅፋ የምትይዝ ነች ሲለው ነው።

👉13፤ጴጥሮስ፡ሆይ፥ተነሣና፡ዐርደኽ፡ብላ፡የሚልም፡ድምፅ፡ወደ፡ርሱ፡መጣ።

#እርቦት_ስለነበር_ተርቦ_ባለበት_ስዓት_ተገለጠለት_መንፈስ_ቅዱስ_ያለበትን_ሁኔታ_ተጠቅሞ_ተነስተህ_አርደህ_ብላ_አለው ጴጥሮስ
ግን ግራ ተጋባ እግዚአብሔር ግን እያለው ያለው አስተምር አህዛብ እሮማዊ ግሪካዊ አይሁዳዊ ሳትል ሁሉን አስተምር ሲለው ነው።

#አርደህ_ብላ_የሚለው_ቃል፦አስተምረህ በወንጌል ፍቅር ግደል አስተምረህ ወደ ቤተ ክርስቲያን ጨምር ሲለው እንጅ ሌላ ነገር እረድ
ወይም ግደል ሲል አይደለም። {

👉14፤ጴጥሮስ፡ግን፦ጌታ፡ሆይ፥አይኾንም፤አንዳች፡ርኵስ፡የሚያስጸይፍም፡ከቶ፡በልቼ፡አላውቅምና፡አለ።

#ጴጥሮስ_አይሁዳዊ_ነውና፦የተጻፈውን ህግ ያውቃል ይህን ብላ ይህን አትብላ የሚለውን { ዘሌ 11 } { ዘዳ 14 } ላይ በነዚህ የሙሴ


መጽሐፍት ላይ የተጻፉትን የሙሴን ህግ ተላልፌ አላቅም ሲል ነው አንዳች እርኩስ የሚያጸይፍ ከቶ በልቸ አላውቅምና ያለው።
ምክንያቱም አህዛብ በአይሁዳዊያን ዘንድ እርሱስ ንጹሀን ያልሆኑ ተብለው ስለሚታሰቡ አብረው እንኳን አይቀመጡም አብረው
አይበሉም ህብረት አያደርጉም ነበር አይሁዳዊያን አህዛብን ይጸየፏቸው ነበርና።

👉15፤ደግሞም፡ኹለተኛ፦እግዚአብሔር፡ያነጻውን፡አንተ፡አታርክሰው፡የሚል፡ድምፅ፡ወደ፡ርሱ፡መጣ።

#እግዚአብሔር_እርኩስ_ያላላውን_አንድም_እግዚአብሔር_የቀደሰውን_አንተ_እርኩስ_አትበል አትከልክል አህዛብን ቅዱሱ


እግዚአብሔር ተቀብሏቸዋል አንተም ተቀበል ሲለው እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው አለው።{ ሮሜ 9÷25 }

👉16፤ይህም፡ሦስት፡ጊዜ፡ኾነ፥ወዲያውም፡ዕቃው፡ወደ፡ሰማይ፡ተወሰደ።

#ሦስት_ጊዜ_መላልሶ_መናገሩ፦የሦስትነቱ ቃሉ እንደማይለወጥ ያጠቅሳል

#ስለምን_ራእዩ_ለቅዱስ_ጴጥሮስ_ሦስት_ጊዜ_ተገለጠለት_ቢሉ፦የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት ሚስጢር ያጠቅሳል።


#አንድም፦ ሐዋርያትና ነብያት በአራቱም ማእዘነ ዓለም ዞረው ባስተማሩ ጊዜ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቁ ወደ ቤተ
ክርስቲያን መጨመራቸውን ያሳያል ይላሉ አባቶች።

#አንድም፦በአራት_ማእዘን_መባሉ_ና_ራእዩ_ሦስት_ጊዜ_ለቅዱስ_ጴጥሮስ_መገለጡ፦4×3=12 መሆኑ የ 12 ቱ ሐዋርያት ምሳሌ ነው


ይላሉ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ወደሰማይ_ሲያርግ_ማየቱ፦ይነዚህ ሁሉ በአንድ በወንጌል አምነው ወደ ገነት ወደ መንግስተ ሰማይ


የመግባታቸው ምሳሌ ነው።
ማለትም በምሳሌ ቤተ ክርስቲያን ወደ ሰማይ ሲወሰድ ማየቱ የእግዚአብሔር ቤተ መንግሥት ለአይሁዳዊያን ብቻ ሳይሆኑ አህዛብም
እሮማዊያንም እስራኤላዊያንም ሁሉ በአንድ በወንጌል ላመኑ ሁሉ መኖሪያ መሆኗን ሲገልጽለት ነው።{ ኤፌ 2÷14-15 }

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ተመልሶ ወደሰማይ ሲያርግ አየ ሰፊ መጋረጃ የወንጌል በአራት ወገን መያዟ ወንጌል በአራቱ ማእዘን

የመነገሯ ማለትም👉በሰሜን በምስራቅ በደቡ በምዕራብ የመነገሯ ሚስጢርን ሲያስረዱ በአራቱ ክፍል ሆና የመጻፏ ማለትም👉ማቴዎስ
ማርቆስ ሉቃስ ዮሐንስ ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ስዕል_አዕዋፍ_የነብያት_የካህናት_ስዕለ_አራዊት_የምዕመናን_አህዛብ_ስዕለ_እንስሳት_የምዕመናን_እስራ
ኤል_ሪያውንም_አርደ_ብላ_ማለቱ_አህዛብን_አስተምር_ሲለው_ነው።

👉17፤ጴጥሮስም፡ስላየው፡ራእይ፦ምን፡ይኾን፧ብሎ፡በልቡ፡ሲያመነታ፥እንሆ፥ቆርኔሌዎስ፡የላካቸው፡ሰዎች፡ስለስምዖን፡ቤት፡ጠይቀው፡ወደ፡
ደጁ፡ቀረቡ፤

👉18፤ድምፃቸውንም፡ከፍ፡አድርገው፦ጴጥሮስ፡የተባለው፡ስምዖን፡በዚህ፡እንግድነት፡ተቀምጧልን፧ብለው፡ይጠይቁ፡ነበር።

👉19፤ጴጥሮስም፡ስለ፡ራእዩ፡ሲያወጣ፡ሲያወርድ፡ሳለ፥መንፈስ፦እንሆ፥ሦስት፡ሰዎች፡ይፈልጉኻል፤

👉20፤ተነሥተኽ፡ውረድ፥እኔም፡ልኬያቸዋለኹና፡ሳትጠራጠር፡ከነርሱ፡ጋራ፡ኺድ፡አለው።

#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ_ቤተ_ክርስቲያን_ሊቃውንት_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ_መንፈስ_ቅዱስ_ሦስት_ሰዎች_ይሹሀል_አለው_ይ
ላሉ።
#ግብጻዊያን_የቤተክርስቲያን_አባቶች_ደግሞ_መንፈስ_ቅዱስ_ሥራ_እንዲጀምር_አዘዘው_ይህም_የመንፈስ_ቅዱስ_ትእዛዝ_ነው_ይላ
ሉ።

👉21፤ጴጥሮስም፡ወደ፡ሰዎቹ፡ወርዶ፦እንሆ፥የምትፈልጉኝ፡እኔ፡ነኝ፤የመጣችኹበትስ፡ምክንያት፡ምንድር፡

ነው፧አላቸው።

👉22፤እነርሱም፦ጻድቅ፡ሰው፣እግዚአብሔርንም፡የሚፈራ፥በአይሁድም፡ሕዝብ፡ዅሉ፡የተመሰከረለት፡የመቶ፡

አለቃ፡ቆርኔሌዎስ፡ወደ፡ቤቱ፡ያስመጣኽ፡ዘንድ፥ከአንተም፡ቃልን፡ይሰማ፡ዘንድ፥ከቅዱስ፡መልአክ፡ተረዳ፡አሉት።

#ቆርኔሌዎስ_በእግዚአብሔር_የተወደደ #አንድም፦ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው መሆኑን ገለጹለት እርሱ አህዛብ ቢሆንም ሮማዊ
ቢሆንም ነገር ግን እግዚአብሔርን የሚፈራ ደግ ሰው መሆኑን ነገሩት።

#ቆርኔሌዎስ_በእግዚአብሔር_የተወደደ_መባሉ፦ፈሪሐ እግዚአብሔርነቱ በምግባር የተገለጠ በመሆኑ በምግባሩ በእግዚአብሔር


የተዎደደ ተባለ።

👉23፤ርሱም፡ወደ፡ውስጥ፡ጠርቶ፡እንግድነት፡ተቀበላቸው።በነገውም፡ተነሥቶ፡ከነርሱ፡ጋራ፡

ወጣ፥በኢዮጴም፡ከነበሩት፡ወንድሞች፡አንዳንዶቹ፡ከርሱ፡ጋራ፡ዐብረው፡ኼዱ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦ አሁን ጴጥሮስ ያየው ራእይ እየተገለጸለት ነው እንዴት አንድ አይሁዳዊ ከአህዛብ ጋር ህብረት ያደርጋል

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦በሦስተኛውም ቀን ኢዮጴ በሚባል ሀገር ያሉ አንዳንዶች ክርስቲያኖች ተከተሉት ስድስት ብሎ ኋላ


ያመጣቸዋል

#ከጴጥሮስ_ጋር_ስድስት ክርስቲያኖች አብረውት ነበሩ { የሐዋ ሥራ 11÷12 }

ስለምን ስድስት ሰዎች ጴጥሮስን ተከትለውት ሄዱ ቢሉ፦የዓይን እማኞች ይሆኑ ዘንድ ነው።

👉24፤በነገውም፡ወደ፡ቂሳርያ፡ገቡ፤ቆርኔሌዎስም፡ዘመዶቹንና፡የቅርብ፡ወዳጆቹን፡ባንድነት፡ጠርቶ፡
ይጠባበቃቸው፡ነበር።

#ግብጻዊው_አባት_ፍዘር_ቴዎድሮስ_ማላቲ፦ምናልባት የእግር ጉዞ ነው ያደረጉት።

#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ይህንን_ክፍል_ስተረጉሙ_በመገረም_እንዲህ_ይላሉ፦ መልካም ጓደኛ አማኝ ሰው ነው እሱ ብቻ


ሳይሆን ጓደኞቹ ከዚህ በረከት እንዲካፈሉ ጠርቷቸዋል ይላሉ።{ ሉቃስ 5÷17-26 }

👉25፤ጴጥሮስም፡በገባ፡ጊዜ፡ቆርኔሌዎስ፡ተገናኝቶ፡ከእግሩ፡በታች፡ወደቀና፡ሰገደለት።

#ቆርኔሌዎስ_ጴጥሮስን_ለማግኘት_ከመጓጓቱ_የተነሳ፦ወጥቶ ይጠባበቅ ነበር ይላሉ አባቶች።

#ሊቁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ፦ቆርኔሌዎስ መቶ አለቃና ታላቅ ስልጣን ያለው ሆኖ ሳለ ለጴጥሮስ መስገዱ ትህትናውንና


እግዚአብሔርን ማመስገኑን ያሳያል ይላሉ።

👉26፤ጴጥሮስ፡ግን፦ተነሣ፤እኔ፡ራሴ፡ደግሞ፡ሰው፡ነኝ፡ብሎ፡አስነሣው።

#ግብጻዊያን_አባቶች፦ቆርኔሌዎስ ለጴጥሮስ በሰገደለት ጊዜ ጴጥሮስ እኔ ሰው ነኝ ማለቱ፦ አምልኮት ነው ያቀረበለትና እሱ እኔ ሰው ነኝ


አምላክ አይደለሁምየአምልኮ ስግደት አይገባኝም የአምልኮ ስግደት እሚገባው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ሲል ነው።

#አንድም፦ቆርኔሌዎስ_ጴጥሮስን_ሲያየው_መሲሁ_መስሎት_ነበር_ለዚህ_ነው_የሰገደለት።

#የኢትዮጵያ_ሊቃውንት_ደግሞ፡ከግሩ በታች ወድቆ ሰገደለት የአክብሮ ስግደት ነው እንዳንተ ያለሁ ፈራሽ በስባሽ አይደለሁምን ስለምን
ለእኔ ትሰግዳለህ ብሎ አስነሳው ይላሉ።

👉27፤ከርሱም፡ጋራ፡እየተነጋገረ፡ገባ፥ብዙዎችም፡ተከማችተው፡አግኝቶ፦

👉28፤አይሁዳዊ፡ሰው፡ከሌላ፡ወገን፡ጋራ፡ይተባበር፡ወይም፡ይቃረብ፡ዘንድ፡እንዳልተፈቀደ፡እናንተ፡ታውቃላችኹ፤ለእኔ፡ግን፡እግዚአብሔር፡
ማንንም፡ሰው፡ርኩስና፡የሚያስጸይፍ፡ነው፡እንዳልል፡አሳየኝ፤
#ጴጥሮስ በቆርኔሌዎስ ቤት የተቀመጡትን ብዙ የተለያዩ ሰዎች ባየ ጊዜ እግዚአብሔር በራእይ የገለጸለት ሚስጢር እየገባው መጣ ይላሉ
አባቶች ።

{ ዮሐ 3÷16 } { ኤፌ 2÷13-17 }

👉29፤ስለዚህም፡ደግሞ፡ብትጠሩኝ፡ሳልከራከር፡መጣኹ።አኹንም፡በምን፡ምክንያት፡አስመጣችኹኝ፧ብዬ፡እጠይቃችዃለኹ፡አላቸው።

👉30፤ቆርኔሌዎስም፡እንዲህ፡አለው፦በዚች፡ሰዓት፡የዛሬ፡አራት፡ቀን፡የዘጠኝ፡ሰዓት፡ጸሎት፡በቤቴ፡እጸልይ፡ነበር፤እንሆም፥የሚያንጸባርቅ፡
ልብስ፡የለበሰ፡ሰው፡በፊቴ፡ቆመና፦

👉31፤ቆርኔሌዎስ፡ሆይ፥በእግዚአብሔር፡ፊት፡ጸሎትኽ፡ተሰማ፥ምጽዋትኽም፡ታሰበ።

👉32፤እንግዲህ፡ወደ፡ኢዮጴ፡ልከኽ፡ጴጥሮስ፡የተባለውን፡ስምዖንን፡አስጠራ፤ርሱ፡በቍርበት፡ፋቂው፡

በስምዖን፡ቤት፡በባሕር፡አጠገብ፡እንግድነት፡ተቀምጧል፡አለኝ።

👉33፤ስለዚህ፥ያን፡ጊዜ፡ወዳንተ፡ላክኹ፥አንተም፡በመምጣትኽ፡መልካም፡አድርገኻል።እንግዲህ፡አንተ፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡የታዘዝኸውን፡
ዅሉ፡እንድንሰማ፡እኛ፡ዅላችን፡አኹን፡በእግዚአብሔር፡ፊት፡በዚህ፡አለን።

ጴጥሮስም በጠየቀ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ጴጥሮስን ያስጠራው እግዚአብሔር አዞት መሆኑን ነገረው።


ሁላችን_አሁን_በእግዚአብሔር_ፊት_አለን፦ሲል እሱና ቤተሰቦቹ ጓደኞቹንም ሁሉ ነው።

👉34-35፤ጴጥሮስም፡አፉን፡ከፍቶ፡እንዲህ፡አለ፦እግዚአብሔር፡ለሰው፡ፊት፡እንዳያደላ፥ነገር፡

ግን፥በአሕዛብ፡ዅሉ፡ርሱን፡የሚፈራና፡ጽድቅን፡የሚያደርግ፡በርሱ፡የተወደደ፡እንደ፡ኾነ፡በእውነት፡
አስተዋልኹ።

#የቅዱስ_ጴጥሮስ_አፍ_በአህዛብ_ላይ_ተከፈተ ይህም ማለት ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ማለት ነው።

#ይህ_ክፍል_እሚያሳየው፦እግዚአብሔር አምላክን ያመነና ትእዛዙን የሚፈጽም ሰው ከአህዛብም ወገን ቢሆን የተመረጠ እንደሆነ
ጴጥሮስ መረዳቱን ነው።አንድም እግዚአብሔር አምላክ የሁሉ አምላክ የሁሉ ጌታ መሆኑን መረዳቱን ያሳያል።{ ዮሐ 3÷16 }
#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲተረጉሙ፦እግዚአብሔርን የሚፈራው የሚወደው የሚያመልከው ትእዛዙን የሚፈጽም
በእርሱ ዘንድ የተመረጠ እርሱ ነው።ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን አስተዋለ።{ ሮሜ 2÷11} { ያዕቆብ 2÷ 1} { ኤፌ 6÷6-11 }

👉36፤የዅሉ፡ጌታ፡በሚኾን፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ሰላምን፡እየሰበከ፡ይህን፡ቃል፡ወደእስራኤል፡ልጆች፡ላከ።

#የሁሉ_ጌታ_ሲል፦ለአይሁዳዊያን ብቻ ሳይሆን ለአህዛብም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ የሁሉ አምላክ የሁሉ ጌታ መሆኑን ሲናገር ነው።

👉37፤ዮሐንስ፡ከሰበከው፡ጥምቀት፡በዃላ፡ከገሊላ፡ዠምሮ፡በይሁዳ፡ዅሉ፡የኾነውን፡ነገር፡እናንተ፡ታውቃላችኹ።

#ግብጻዊያን_አባቶች_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ፦ቅዱስ_ጴጥሮስ_በቆርኔሌዎስ_ቤት_ባሉ_በቤተሰቦቹና_በጓደኞቹ_በአህዛብ_ፊት_ቆሞ_ሚ
ተርክላቸው_ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ከተጠመቀ በኋላ ሐዋርያትን መረጠ አገልግሎቱን ጀመረ እያለ
እየገለጸላቸው ነው።

#ቅዱስ_ዮሐንስ፦ያጠምቅ የነበረው የንስሃ ጥምቀት ነው ታዲያ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ ነውር የሌለበት ንጹህ
ቅዱስ ጌታ ለምን በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ ቢባል ይህንን ሲፈቱ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፦ለእኛ ጥምቀትን ያስተምር ዘንድ አርአያ
ይሆነን ዘንድ ተጠመቀ ይላሉ።

#ቅዱስ_ጴጥሮስ ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳ ሁሉ የሆነውን ነገር እናንተ ታውቃላችሁ ማለቱ፦ቆርኔሌዎስ ከቤተሰቦቹ ጋር የሚኖረው
በቂሳርያ ነው ከቂሳርያ ገሊላ 65 ኪ,ሜ ነው ርቀቱ ይህም ማለት ብዙ አይርቅም እና ቅዱስ ጴጥሮስ ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ የሰራውን
ሁሉ ተአምር በእርሱ የተደረጉትን ብዙ ድንቅ ድንቅ ነገሮች ታቃላችሁ አንድም አይሁዳዊያን ለሮማዊያን አሳልፈው እንደሰጡት
በሮማዊያን መገደሉንም ሁሉ ሰምታችኋል ታውቃላችሁ ሲላቸው ነው።{ ማቴ 10÷1 ሙሉውን }

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳም የሆነውን ሁሉ ነገር እናንተ ቅሉን ታቃላችሁ።

👉38፤እግዚአብሔር፡የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡በኀይልም፡ቀባው፥ርሱም፡መልካም፡እያደረገ፡

ለዲያብሎስም፡የተገዙትን፡ዅሉ፡እየፈወሰ፡ዞረ፥እግዚአብሔር፡ከርሱ፡ጋራ፡ነበረና፤

#እርም_እሚለው፦ እግዚአብሔርን ነው

#የተቀባ_ሲል የተመረጠ ሲል ነው።


#ቀባው_ሲል፦መረጠው ነገር ግን መረጠው ስንል የእግዚአብሔር አብ ምርጫ ብቻ ሳይሆን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ምርጫ ነው
አንድነት ሦስትነታቸውን የሚገልጽ ነው።

{ ማቴ 14 ሙሉውን } { ዮሐ 3÷16 }

ሌሎች የተመረጡ የተቀቡ የምንላቸውም አሉ ነገር ግን ጌታን የተቀባ ስንል ቅዱሳን ሰዎችን የተቀቡ ስንል ሰፊ ልዩነት አለው ይህም
እነርሱ የተቀቡት በሰው ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን በእግዚአብሔር አብ የተቀባ ነው ይህም የሚያሳየው እራሱ እግዚአብሔር መሆኑን
ነው።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህንን_ክፍል_ሲፈቱ ዮሐንስ ስለናዝሬቱ ሰው ስለ ኢየሱስ ካስተማረው ጥምቀት በኋላ፦እግዚአብሔርነቱ


ኃይሉ ህይዎቱ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ የመረጠው የሾመው።

#ለዳዳቢሎስም_የተገዙትን_እየፈወሰ_ዞረ፦ተአምራትን አደረገ ወንጌልን በኃይል ገለጠ በአጋንት እስራት ውስጥ የታሰሩትን እየፈታ
በኢየሩሳሌም አውራጃ ዞረ ።

{ ሉቃስ 11÷14 } { ማር 1÷34-35 } { ሉቃስ 4÷35 } {ማቴ 9÷33 } ማቴዎስ ከምዕራፍ 8 ጀምሮ እስከ ምዕራፍ 12 እያንዳንዱን
ምዕራፎች ሙሉ ሙሉውን ማንበብ እንዳይዘነጋ!!

👉39፤እኛም፡በአይሁድ፡አገርና፡በኢየሩሳሌም፡ባደረገው፡ነገር፡ዅሉ፡ምስክሮች፡ነን፤ርሱንም፡በዕንጨት፡ላይ፡ሰቅለው፡ገደሉት።

#ግብጻዊያን_የቤተክርስቲያን_አባቶች፦እግዚአብሔር አምላክ አስቀድሞ ለአይሁዳዊያን ላከው እነርሱም አይሁዳዊያን ገደሉት።

መድኀኒት የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መድኀኒትነቱን አንቀበልም ብለው ሮማዊያን ገደሉት ሲል ነው ቅዱስ ጴጥሮስ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦ቅዱስ ጴጥሮስ እያለ ያለው እኛ ግን በአይሁድ ሀገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን
ማለቱ፦ባስተማረው ትምህርት በሰራው ቱርፋት ባደረገው ተአምራት ማለቱ ነው። በእንጨት ሰቅለው እንደገደሉት እግዚአብሔር ግን
በሦስተኛው ቀን ከሙታን ለይቶ እብዳስነሳው እኛ ምስክሮች ነን።

አይሁዳዊያን ዘለዓለማዊ ህይዎት የሚሰጠውን ብርሃን የሆነውን ጌታ ህይዎትን እናጠፋለን እናዳፍናለን ብለው በቀራንዮዮ መስቀል ላይ
ገድለው ቀበሩት እነርሱ ግን አላወቁም ዘለዓለማዊ ህይዎትን እናጠፋለን ብለው የራሳቸውን ህይዎት አጠፉ ይላሉ ሊቃውንተ ቤተ
ክርስቲያን።

👉40፤ርሱን፡እግዚአብሔር፡በሦስተኛው፡ቀን፡አስነሣው፡ይገለጥም፡ዘንድ፡ሰጠው፤
#እግዚአብሔር_አስነሳው_ሲል፦ከሦስትነተ አይጎልም በአባቱ በአብ ፈቃድ በራሱ ፈቃድ በባህሪ ህይዎቱ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ
ከሙታን መካከል ተለይቶ መነሳቱን የሚገልጽ ነው አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በአንድነትና በሦስትነት መተካከላቸውን የሚገልጽ ነው

{ ሮሜ 8÷11 } { ዮሐ 2÷19-25 }

#ይገለጥም_ዘንድ_ሰጠው፦በአባቱ ፈቃድ በራሱ ፈቃድ በባህሪ ህይዎቱ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ

መገለጡን ሲነግራቸው ነው።መገለጡ ግን ለህዝቡ ለሁሉም አይደለም 👇👇

👉41፤ይኸውም፡ለሕዝብ፡ዅሉ፡አይደለም፥ነገር፡ግን፥በእግዚአብሔር፡አስቀድሞ፡የተመረጡ፡ምስክሮች፡

ለኾን፟፡ለእኛ፡ነው፡እንጂ፤ከሙታንም፡ከተነሣ፡በዃላ፡ከርሱ፡ጋራ፡የበላን፡የጠጣንም፡እኛ፡ነን።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህንን_ክፍል_ሲፈቱ፦ፈጽሞ ይገለጥ ዘንድ መገለጥን ሰጠው ሲል፦ መገለጡ ለህዝብ ሁሉ አይደለም


ለታመኑት ምስክሮቹ ለሆኑት ከጥንት ጀምሮ ለመረጣቸው ትንሳኤውን ለሚመሰክሩ ለመቶ ሀያ ቤተሰብ ነው እንጅ { ሉቃስ 24÷1-
ፍጻሜው } { 1 ኛ ቆሮ 15÷ 1 -ፍጻሜው}

#ከሙታንም_ከተንፕሳ_በኋላ_ከእርሱ_ጋርል_የበላን_የጠጣን_እኛ_ነን_ማለቱ፦መንፈስ ነው እንዳይሉ ጌታ አሳ ከማር ወለላ ጋር ወስዶ


መብላቱን ይናገራል { ሉቃስ 24÷36-43 }

👉42፤ለሕዝብም፡እንድንሰብክና፡በሕያዋንና፡በሙታን፡ሊፈርድ፡በእግዚአብሔር፡የተወሰነ፡ርሱ፡እንደ፡ኾነ፡እንመሰክር፡ዘንድ፡አዘዘን።

#በህያዋንና_በሙታን_ሊፈርድ_በእግዚአብሔር_የተወሰነ_እርሱ_እንደሆነ_እንመሰክር_ዘንድ_አዘዘን_ማለቱ፦በመጨረሻው ዘመን
ዳግም የሚመጣው ለጻድቃን የሚፈርድላቸው በኀጥአን ላይ የሚፈርድባቸው እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ማለት ነው { ዮሐ
5÷22÷23 }

👉43፤በርሱ፡የሚያምን፡ዅሉ፡በስሙ፡የኀጢአቱን፡ስርየት፡እንዲቀበል፡ነቢያት፡ዅሉ፡ይመሰክሩለታል።

#በእርሱ_የሚያምን_ሁሉ_ሲል፦በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሁሉ ሲል ነው። { ኢሳ 53÷1-ፍጻሜ ሙሉውን } { ኤር 31÷34 }


#ቅዱስ_ጴጥሮስ_ነብያት_ሁሉ_ይመሰክሩለታል_ሲል፦እኛ ሐዋርያት ብቻ ሳንሆን ነብያትም ስለ ክርስቶስ ኢየሱስ ይመሰክራሉ ሲል
ነው።

👉44፤ጴጥሮስ፡ይህን፡ነገር፡ገና፡ሲናገር፡ቃሉን፡በሰሙት፡ዅሉ፡ላይ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ወረደ።

#ይህ ክፍል ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን ነገር ገና ሲናገር ቃሉን በሰሙት፦በሮማዊያን ላይ መንፈስ ቅዱስ እንደወረደ ይናገራል። { የሐዋርያት
ሥራ 15÷8 }

👉45፤ከጴጥሮስም፡ጋራ፡የመጡት፡ዅሉ፡ከተገረዙት፡ወገን፡የኾኑ፡ምዕመናን፡በአሕዛብ፡ላይ፡ደግሞ፡የመንፈስ፡ቅዱስ፡ስጦታ፡ስለ፡ፈሰሰ፡
ተገረሙ፤

#የዓይን_እማኝ_ይሆኑ_ዘንድ_ከቅዱስ_ጴጥሮስ_ጋር_የመጡት፦ስድስት ከተገረዙት አንድም ከአይሁድ ወገን የሆኑት ናቸው።

#ተገረሙ_መባሉ፦በአይሁዳዊያንና በሮማዊያን በአህዛብ መካከል የነበረው ያየጥል ግድግዳ ሲፈርስ ባዩ ጊዜ አንዱ እግዚአብሔር
አምላክ ለአይሁዳዊያም ለአህዛብም አንድ አምላክ አድሎ የሌለው መሆኑን አይተው በሐዋርያት ላይ የወረደው መንፈስ ቅዱስ በአህዛቡ
በቆርኔሌዎስ ቤት በአህዛቦች ላይም ሲወርድ ባዩ ጊዜ ተገረሙ ።

👉46፤በልሳኖች፡ሲናገሩ፥እግዚአብሔርንም፡ሲያከብሩ፡ሰምተዋቸዋልና።

#ሊቁ_አውገስጢኖስ፦መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ በህዝቦች ልሳን መናገራቸው ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ ቋንቋ መናገር እንዳለባት ያሳያል
ይላሉ።
#አንድም፦ ቤተ ክርስቲያን ኩላዊት ሁለገብ አንድም ዓለም አቀፋዊት መሆኗን ያሳያል።

👉47፤በዚያን፡ጊዜ፡ጴጥሮስ፡መልሶ፦እነዚህ፡እንደ፡እኛ፡ደግሞ፡መንፈስ፡ቅዱስን፡የተቀበሉ፡እንዳይጠመቁ፡ውሃን፡ይከለክላቸው፡ዘንድ፡
የሚችል፡ማን፡ነው፧አለ።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን_ይህን_ክፍል_ሲፈቱ፦ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ እኛ መንፈስ ቅዱስን ገንዘብ ካደረጉ እንደ እኛ የመንፈስ


ቅዱስን ጸጋ ከተቀበሉ እኛ በተለያየ ቋንቋ እንደተናገርን እነሱም እንዲሁ ከተናገሩ በኋላ በውኃ እንዳይቀበሉ ማነው እሚከለክል።
👉48፤በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ስምም፡ይጠመቁ፡ዘንድ፡አዘዛቸው።ከዚህ፡በዃላ፡ጥቂት፡ቀን፡እንዲቀመጥ፡ለመኑት።

#ስለምን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም_እንዲጠመቁ_አዘዘ_ቢሉ፦ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ስለሆነ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም


እንዲጠመቁ አዘዛቸው።

#ሊቃውንተ_ቤተ_ክርስቲያን፦በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምናችሁ ተጠመቁ አላቸው ከዚህ በኋላ ጥቂት ቀን ከእኛ ዘንድ
ሰንብት ብለው ማለዱት።

እግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ጴጥሮስ ወደ ቆርኔሌዎስ ቤት እንዲሄድ ያዘዘበት ምክንያት

1 ኛ ወንጌልን እንዲሰብክላቸው ነገረ ክርስቶስን እንዲያላብሳቸው ነው ቆርኔሌዎስን ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲያስተምረው እርሱን ብቻ
ሳይሆን ቤተሰቦቹን ጓደኞቹንም ጭምር።

2 ኛ እንዲጠመቅ ያደርገው ዘንድ { ማር 16÷16 }

ስብአት ለአብ🍀 ስብአት ለወልድ🍀 ስብአት ለመንፈስ ቅዱስ 🍀ወለዓለም ዓለም አሜን

You might also like