Professional Documents
Culture Documents
Ethiopian Capital Market Authority's - Fee Directive
Ethiopian Capital Market Authority's - Fee Directive
996/2016
ባለሥልጣኑ በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 አንቀጽ 108 (2) መሠረት ይህንን መመሪያ
አውጥቷል።
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የክፍያ መመሪያ ቁጥር 996/2016” ተብሎ ሊጠራ
ይችላል።
2. ትርጓሜ
1. “የማመልከቻ ክፍያ” ማለት ለሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ምዝገባ ወይም ለፈቃድ ማመልከቻ
በአመልካች ለአንድ ጊዜ የሚከፈልና የማይመለስ ክፍያ ነው።
3. “የካፒታል ገበያ ግብይት” ማለት በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ፣ ባልተማከለ የጠረጴዛ ዙሪያ
ገበያ ወይም በሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ እና ክፍያ አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያዎች
የሚደረግ ማንኛውም ግብይት ነው።
7. “የፈቃድ እድሳት ክፍያ” ማለት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪ፣ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ
ገበያ፣ ያልተማከለ የጠረጴዛ ዙሪያ ገበያ ወይም የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ እና ክፍያ
አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያ ፈቃድ ሲታደስ ለባለስልጣኑ የሚከፈል ዓመታዊ ክፍያ ነው።
8. ‘’የገበያ መሰረተ ልማት አገልግሎት ሰጪ’’ ማለት ፍቃድ የተሰጠው የሰነደ ሙዓለንዋይ
ገበያ፣ ያልተማከለ የጠረጴዛ ዙሪያ ገበያ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ እና ክፍያ
አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያ ነው።
11. “የምዝገባ ክፍያ” ማለት በአዋጁ አንቀጽ 75 መሠረት ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች በባለስልጣኑ
ሲመዘገቡ የሚከፈል ክፍያ ነው።
12. “የግብይት ክፍያ” ማለት ፈቃድ ባለው የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ፣ ያልተማከለ የጠረጴዛ
ዙሪያ ገበያ ወይም የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ እና ክፍያ አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያ ላይ
በሚደረጉ በእያንዳንዱ ግብይቶች ላይ የሚተገበር ባለሥልጣኑ የሚያስከፍለው ክፍያ ነው።
13. ‘’ሱኩክ ቦንድ’’ ማለት የሼሪአ መርሆዎችን እና የእስልምና ህጎችን የተከተለ የብድር ሰነደ
ሙዓለንዋይ ነው።
14. በዚህ መመሪያ የተገለጸ ማንኛውም ቃል ወይም ሐረግ በአዋጁ የተሰጠው ትርጉም
ይኖረዋል፡፡
3. የተፈጻሚነት ወሰን
ክፍል ሁለት
5. የማመልከቻ ክፍያ
6. የፈቃድ ክፍያ
ሁሉም የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች አመታዊ የፈቃድ እድሳት ክፍያን እንደሚከተለው
ይከፍላሉ።
ክፍል ሶስት
9. የማመልከቻ ክፍያ
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ፣ ያልተማከለ የጠረጴዛ ዙሪያ ገበያ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ
እና ክፍያ አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያ የማይመለስ የአንድ ጊዜ የፈቃድ ማመልከቻ ክፍያ
እንደሚከተለው ይከፍላል።
10 . የፈቃድ ክፍያ
የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ፣ ያልተማከለ የጠረጴዛ ዙሪያ ገበያ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አስቀማጭ
እና ክፍያ አጣሪና ፈጻሚ ኩባንያ የማይመለስ የአንድ ጊዜ የፈቃድ ማመልከቻ ክፍያ
እንደሚከተለው ይከፍላል።
ክፍል አራት
12. አክሲዮኖች
ክፍል አምስት
የግብይት ክፍያዎች
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ
16. የክፍያ ጊዜ
ከአንድ በላይ ፈቃድ ለማግኘት የሚያመለክት አመልካች ለእያንዳንዱ ፈቃድ ሁሉንም አግባብነት
ያላቸውን ክፍያዎችን መክፈል ይኖርበታል።
19. መዛግብት
(1) ከፋዮች ቢያንስ ለአስር አመታት ትክክለኛ የክፍያ ሰነዶችን እና ማህደሮችን ጠብቀው
መያዝ አለባቸው።
20. ባለስልጣኑ በቦርዱ ውሳኔ መሰረት ማናቸውንም ክፍያዎች ለጊዜው ሊተው ወይም ሊቀንስ
ስለሚችልበት ሁኔታ
ባለሥልጣኑ የካፒታል ገበያውን እድገት እና የተሳታፊዎችን አቅም ከግምት በማስገባት እንዲሁም
የገበያ ተሳትፎን ለማሳደግ ሲባል አስቀድሞ ቦርዱ በሚሰጠው ውሳኔ መሰረት በዚህ መመሪያ
የተደነገጉትን ማናቸውንም ክፍያዎች ለጊዜው ሊተው ወይም ሊቀንስ ይችላል።’
አዲስ አበባ
መጋቢት፣ 2016 ዓ.ም
ዶ/ር ብሩክ ታዬ
ዋና ዳይሬክተር
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን።