Professional Documents
Culture Documents
ስነ_ምግባር
ስነ_ምግባር
መልካም ምግባራት
የምዕራፉ ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ተምረው ካገባደዱ በኋላ
፩ ከክርስቲያኖች የሚጠበቁ መልካም ምግባራትን ይለያሉ፡፡
፪ ለማንና እንዴት መታመን እንዳለባቸው በታሪክ ይማራሉ፡፡
፫ ቅን ስለመሆን በቅንነትም ስለሚገኝ ጥቅም አውቀው ቅን ለመሆን ይጥራሉ፡፡
፬ ታዛዥ ልጆች መሆን እንዳለባቸው በታሪክ ይማራሉ፡፡
(የመክፈቻ ጥያቄዎች)
.፩ ልጆች መልካም ምግባራት ብላችሁ የምታስቡአቸውን ለመምህራችሁ ተናገሩ?
፪ በመጽሐፍ ቅዱስ ከምታውቁአቸው ታዛዥ ልጆች መካከል የአንዱን ተራሪክ
ለመምህራችሁ ተናገሩ?
መልስ፦ ቅንነት ከክርስቲያናዊ ስነ ምግባራት መካከል አንዱ ሲሆን ኅሊና መሞላት፣ መልካምነት፣
ተንኮል የሌለበት ትክክለኛ እሳቤ ማሰብ በድርጊትም መፈፀም ነው፡፡
ጥያቄ፦ ቅን ሰው ምን ያያል?
መልስ፦ የአምላኩ የእግዚአብሔርን ፊት ያያል
ጥያቄ፦ ማስረጃ ጥቅስ ብትነግረን?
መልስ፦ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ “እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና ጽድቅንም ይወድዳል ቅንነት ግን ፊቱን
ታየዋለች” በማለት ተናግሯል፡፡ መዝ ፲፩፥፯
ጥያቄ፦ ቅን ልብ ያለው ልጅ ምን ያደርጋል?
መልስ፦ ቅንልብ ያለው ልጅ በቀና አዕምሮ በንፁህ ልብ ሲጠሩት ይሄዳል ሲልኩት ይታዘዛል፡፡
ጥያቄ፦ ሌላ ምን ያደርጋል?
መልስ፦ ቅን ልብ ያለው ሰው ለሰዎች ብቻ አይደለም ለእንስሳም ጭምር ያዝናል፡፡
ጥያቄ፦ ማስረጃ ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ ቅን ልብ ያላት የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ታሪክ በአንድ ወቅት እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ ሳለች ውኃ ቀድታ ስትመለስ አንድ የተጠማ ውሻ ከመንገድ
አገኘች ውኃን ሊጠጣ ቢፈልግ ሌሎች ሰዎች በቅንንት ውኃ መስጠት ሲገባቸው ሲያባርሩት ተመለከተች
እርሷ ግን ቅን ልቡና ያላት ናትና ካያዘችው ማድጋ (እንስራ) በወርቅ ጫማዋ ውኃ አድራበት ውኃ
እንዲጠጣ አደረገችው፡፡
ጥያቄ፦ ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን?
መልስ፦ እኛም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምንማረው ትልቁ ነገር በቅንነት መኖር ቅን
ነገርን ለሰዎችም ሆነ ለእንስሳት መፈፀም እንዳለብን ነው፡፡
ጥያቄ፦ ሌላ የቅን ሰው ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ ሌላው የቅንነትን ታላቅነት የምንማርበት ታሪክ የአባታችን የአባ አጋቶን ታሪክ ነው፡፡ አባታችን
ከቅንነታቸው የተነሣ በረከትን አግኝተዋል፡፡ ታሪካቸውም በአንድ ገዳም ውስጥ ሰሌን እየሰፉ የሚሸጡ
አባት ነበሩ፡፡ ሰሌኑን ሸጠው በገዳሙ ውስጥ ለሚኖሩ መነኮሳት ነው ምግብ የሚገዙበት ይሄ ትልቅ
ቅንነት ነው፡፡ ታዲያ አንድ ቀን ሰሌኑን ሊሸጡ ከገዳሙ እንደወጡ አንድ የኔ ቢጤ ሰው ‹‹አባቴ ወዴት
ነው የምትሄደው?›› ብሎ ሲጠይቃቸው ‹‹ገበያ ነው የምሄደው›› አሉት የኔ ቢጤውም ‹‹ገበያ የምትሄደው
ለምንድን ነው?›. አላቸው፡፡ መነኩሴው ‹‹ይህንን ሰሌን ልሸጥ›› አሉት የኔቢጤውም ‹‹እኔም ገበያ መሄድ
እፈልጋለሁ ግን መራመድ ስለማልችል አዝለኸኝ ገበያ ውሰደኝ›› ሲላቸው እሺ ብለው አዝለውት ገበያ
ወሰዱት ገበያ ከደረሱ በኋላም ሰሌኑን ሲሸጡ የኔ ብጤው ‹‹ሰሌን ሸጥክ?›› ሲላቸው ‹‹አዎ›› አሉት፡፡
‹‹በስንት ብር ሸጥክ?›› ሲላቸው ‹‹በዚህን ያህል ብር ሸጥኩት›› ሲሉት የኔቢጤው ‹‹ዳቦ ግዛልኝ?
ርቦኛል›› አላቸው እርሳቸውም ቅንነት ስላላቸው ሳያንጎራጉሩ ለኔብጤው ዳቦ ገዝተው ሰጡት፡፡ ሁሉንም
ሰሌን ሸጠው ዳቦ ግዛልኝ ሲላቸው እየገዙለት መጨረሻ ላይ ሰሌኑን ሸጠው ከጨረሱ በኋላ ምንም ብር
እጃቸው ላይ አልቀረም፡፡ ለኔብጤው ዳቦ ሲገዙለት አልቋል፡፡ የኔ ብጤውም ‹‹ዳቦ ግዛልኝ?›› ሲላቸው
‹‹ገንዘቡ አለቀበኝ›› አሉት እርሱም ‹‹አሁን ታዲያ ምን ልታደርግ ነው?›› ሲላቸው ‹‹አሁን ወደ በአቴ
ወደ ገዳሜ ልመለስ ነው›› አሉት የኔ ብጤውም ‹‹በቃ እኔንም አዝለኸኝ ውሰደኝና ጠዋት ካነሳኸኝ ቦታ
አድርሰኝ?›› አላቸው፡፡ እሳቸውም እሺ ብለውት አዝለውት ወደ ጠዋቱ ቦታ የገዳሙ በር ላይ ሲደርሱ
‹‹በል አሁን አውርደኝ ደርሻለሁ›› ሲላቸው እሺ ብለው አወረዱት ለካስ ያ የኔ ብጤ መስሎ የተገለጠው
መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነበር እና መርቋቸው ባርኳቸው ሄደ፡፡
ጥያቄ፦ ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን?
መልስ፦ እኛም ለሌላው በጎ ስናደርግ ለእግዚአብሔር እንደምናደርግ አንጠራጠር፡፡ተማሪዎች ሁል ጊዜ
ቅን ሆነን የምንጓዝ ከሆነ አምላክችን እግዚአብሔር መልካም የምንለውን ነገር ለእኛ ይሰጠናል፡፡ ክፉንም
ነገር ያርቅልናል፡፡ “እግዚአብሔር በቅንነት የሚሄዱትን ከመልካም ነገር አያሳጣቸውም” እንዲል መዝ
፹፬፥፲፩
ጥያቄ፦ ከአንድ ክርስቲያን የሚጠበቅ ሦስተኛ መልካም ምግባር ምንድን ነው?
መልስ፦ ታዛዥነት
መልስ፦ ለወላጆች የማይታዘዝ ልጅ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ፣ በሰዎችም ዘንድ መወደድ የሌለው ይሆናል፡፡
ጥያቄ፦ ለወላጆቹ የሚታዘዝ ልጅ ምን ያገኛል?
መልስ፦ ወላጆቹን የሚያከብር ለእነርሱም የሚታዘዝ ልጅ እግዚአብሔር እድሜን ይሰጠዋል፡፡
ጥያቄ፦ ማስረጃ ጥቅስ?
መልስ፦ “አባትና እናትህን አክብር እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር እድሜህ እንዲረዝም” ዘጸ ፳፥፲፪
ጥያቄ፦ ለወላጅ መታዘዝ እንዲገባ ምሳሌ የሚሆነን ማን ነው?
መልስ፦ ለወላጆች መታዘዝ እንዲገባ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአጭር ቆመት
በጠባብ ደረት ተገልጦ በተመላለሰበት የልጅነቱ ወራት ለእናቱ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
እየታዘዘ በማገልገል አስተምሮናል፡፡
መልስ፦ ይቅርታ መጠየቅ ማለት አንድን ሰው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በመናገር በመስራት በድለነው
ተናግረነው አስቀይመነው ከሆነ ወንድሜ ይቅር በለኝ እኅቴ ይቅር በይኝ ይቅርታ አድርጊልኝ በድያለሁ
ብሎ ጥፋትን ማመን ማለት ነው፡፡
ጥያቄ፦ ይቅርታ ማድረግ ማለት ምን ማለት ነው?
መልስ፦ ይቅርታ ማድረግ ማለት የበደለን ያስቀየመን ሰው ወደኛ መጥቶ ማረኝ ወንድሜ ማሪኝ እኅቴ
ብሎ ይቅርታ ሲጠይቀን እኛ ደግሞ ችግር የለውም ይቅር ለእግዚአብሔር በመባባል ሰላም ማውረድ እና
ወደ ቀድሞ ፍቅር ወንድማማችነትና ታማኝነት መመለስ ነው፡፡
ጥያቄ፦ ይቅርታ መባባል እንዲገባ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
መልስ፦ ‹‹እርስ በርሳችሁ ትዕግስትን አድርጉ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው ይቅር
ተባባሉ፡፡ ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ፡፡›› ቆላ ፫፥፲፫
ጥያቄ፦ ይቅርታ ስለመባባል የሚያስረዳ ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩ፡፡ ከእነርሱም ታናሹ አባቱን ‹‹አባቴ ሆይ ከገንዘብህ የሚደርሰኝን
ክፍል ስጠኝ›› አለው አባትየውም ገንዘቡንም አካፈላቸው፡፡ ከጥቂት ቀንም በኋላ ታናሹ ልጅ ገንዘቡን
ሁሉ ሰብስቦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ ከዚያም እያባከነ ገንዘቡን በተነ፡፡ ሁሉንም ከከሰረ በኋላ በዚያች ሀገር
ጽኑ ርሀብ ሆነ እርሱም ይጨነቅ ጀመር፡፡ ሄዶም ከዚያች ሀገር ሰዎች ከአንዱ ጋር ተዳበለ እርሱም
እሪያ እንዲያሰማራ ወደ ሜዳ ላከው፡፡ እሪያዎችም ከሚበሉት ምግብ ይበላና ይጠግብ ዘንድ ይመኝ
ነበር ነገር ግን የሚሰጠው አልነበረም፡፡ ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ፦ ‹፣እንጀራ የሚተርፋቸው
የአባቴ ባለሙያዎች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በርሀብ እጠፋለሁ ተነስቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁ
አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም ከሙያተኞችህ እንደ አንዱ
አድርገኝ እለዋለሁ›› አለ ተነስቶም ወደ አባቱ መጣ፡፡ እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለትሮጦም
አንገቱን አቀፈውና ሳመው፡፡ ልጁም ‹‹አባቴ ሆይ በሰማይና በምድር በደልሁ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል
አይገባኝም›› አባቱ ግን በታላቅ ደስታ ሆኖ ባርያዎቹን አለ
የማጠቃልያ ጥያቄዎች
የሚከተሉትን ጥያቄዎች እውነት ወይም ሀሰት በማለት መልሱ
ታታሪነት
የምዕራፉ ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ተምረው ካገባደዱ በኋላ
፩- በነገር ሁሉ ታታሪ ስለመሆንና እንዴት መሆን እንዳለባቸው ያውቃሉ፡፡
፪- ቤተሰብን በስራ ማገዝ እንደሚገባቸው ይረረዳሉ በማገዝም ያገለግላሉ፡፡
፫- በአለማዊውም ሆነ በመንፈሳዊው ትምህርታቸው እንዴት ውጤታማ መሆን
እንዳለባቸው ይረዳሉ፡፡
፬- መጻሕፍትን የማንበብ ልማድ ሊኖራቸው እንዲገባ በማወቅ ልምምድ ያደርጋሉ፡፡
፭- ጊዜያቸውን እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንዳለባቸው ያውቃሉ፡፡
(የመክፈቻ ጥያቄዎች)
የማጠቃልያ ጥያቄዎች
ምዕራፍ ሦስት
ትዕግሥት
የምዕራፉ ዓላማ
ተማሪዎች ይህን ትህርት ተምረው ባገባደዱ ጊዜ
፩ የትዕግሥትን ምንነት ይረዳሉ፡፡
፪ በመታገሥ የሚገኘውን ጥቅም በማወቅ ለመተግበር ይለማመዳሉ፡፡
፫ ባለመታገሥ ጠንቅ የሚመጣውን ጉዳት ያውቃሉ ይጠነቀቃሉ፡፡
(የመክፈቻ ጥያቄዎች)
፩ ልጆች ትዕግሥት ማለት ምን ማለት ነው? የምታውቁትን ለመምህራችሁ
ተናገሩ?
፪ ልጆች በመጽሐፍ ቅዱስ በመታገሣቸው ብዛት የተጠቀሙ ሰዎችን ለመምህራችሁ
ተናገሩ?
ትዕግሥት
ጥያቄ፦ ትዕግሥት ምንድን ነው?
መልስ፦ ፩ ትዕግሥት መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ክርስቲያን በሕይወቱ ሊያደርጋቸው ከሚገቡ የመንፈስ
ፍራ ብሎ ከጠቀሳቸው መልካም ሥራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ (ገላ ፭፥፳፪)
፪ ትዕግሥት መከራን ወይንም ችግርን እንዲሁ የትኛውንም የሚገጥመን ውጣ ውረድ ያለ
ምንም መሰላቸትና ብስጭት መቀበል መቻል
፫ ትዕግሥት መልካም ልመናችንን የምንቀበልባት ታላቅ ሥጦታችን ናት፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ
ጻድቁ አባታችን አብርሃም ከእግዚአብሔር ዘንድ ‹‹ዘርህን እንደ ምድር አሸዋ እንደ ሰማይ ከዋክብት
አበዛልሃለሁ›› ተብሎ የተነገረውን የተስፋውን ቃል ምኞቱ የተፈጸመለት ሃያ አምስት ዓመታት ጠብቆ
በመቶ አመቱ ይስሐቅን በመውለድ ነው፡፡ ይህም የሆነለት ትዕግሥትን በማብዛቱ ነው፡፡
ጥያቄ፦ የትዕግሥት ጥቅም ምንድን ነው?
መልስ፦ ዋነኛውና መሠረታዊው ነገር የነፍስ ድኽነት ነው፡፡ ትዕግሥተኛ ሰው ትዕግስቱ ነፍስና ሥጋውን
ያድናል፡፡ ይህንንም መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹በመታገሳችሁ ነፍሳችሁን ታድናላችሁ›› ሲል ይነግረናል፡፡
(ሉቃ፳፩፥፲፱)
ጥያቄ፦ ለዚህ አብነት የሚሆነን ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ አብነት የሚሆነን ታሪክ ታላቁ አባታችን ኢዮብ ነው፡፡ ኢዮብ ላይ ሰይጣን ቀንቶበት በእግዚአብሔር
ፈቃድ በልጆቹ፣ በሀብት በንብረቱ፣ እንዲሁ በገዛ ሰውነቱ ላይ እያፈራረቀ ፈተና ቢያመጣበት እርሱ
ግን የሚስቱን ምክር ሰምቶ አምላኩን ከመስደብ ይልቅ ትዕግሥትን አበዛ እንጂ ለአንዲት ቀንም
የምሬት ቃልን አልተናገረም፡፡ እግዚአብሔር ደግ አምላክ ነውና ለኢዮብ ከፊተኛው ይልቅ በኋለኛው
በታላቅ በረከት ጎበኘው ይህም በረከት እጥፍ ድርብ ሆነለት፡፡ ይህን ሁሉ ያገኘው ግን በመታገሱ ነው፡፡
ማጠቃለያ ጥያቄዎች
ምዕራፍ አራት
ጾም
የምዕራፉ ዓላማ
ተማሪዎች ይህን ትህርት ተምረው ባገባደዱ ጊዜ
፩ የጾም ምንነትን እንዲሁ ተገቢነትን በሚገባ ይረዳሉ፡፡
፪ እንዴት መጾም እንዳለባቸው በሚገባ ይረዳሉ፡፡
፫ በጾም ስለሚያገኙት ጥቅም አውቀው ይጾማሉ፡፡
(የመክፈቻ ጥያቄዎች)
፩ ስለ ጾም የምታውቁትን ተናገሩ?
፪ በጾም ከማናገኛቸው ጥቅሞች መካከል የምታውቁትን ተናገሩ?
ጾም
መልስ፦ ጾም ማለት ለተወሰነ ጊዜ እህል ከመብላት ውኃም ከመጠጣት መከልከል ከጥሉላት (ከፆም)
ምግቦች መከልከል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪ ጾም ማለት ራስን መግዛት ፣ ሥጋዊ ስሜትን ማሸነፍ
ለሥጋ ፍላጎት በመከልከል ለነፍስ ፍላጎት እንድትገዛ ማድረግ ነው፡፡
መልስ፦ በአዳምና በሔዋን በኩል የጠቀበልነው የመጀመሪያ ትዕዛዝ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ
የሰውን ልጅ ከፈጠረ በኋላ በኤዶም ገነት እንዲኖሩ አደረጋቸው ለዛም ሦስት እፅዋትን ሠጥቷቸው
የነበረ ሲሆን አንደኛው እንዲበሉ የተሰጣቸው ሁለተኛው ብሉም አትብሉም ያልተባሉት እንዲሁም
ሦስተኛ ደረጃ እንዳይበሉ የጠነገራቸው እፀ በለስ ነበረች እግዚአብሔር እፀ በለስን እንዳይበሉ ስለምን
ከለከላቸው (አዘዛቸው) ከተባለ ፆምን መተው መከልከልን ሲያስተምራቸው ነው፡፡
ጥያቄ፦ የጾም ጥቅም ምንድን ነው?
መልስ፦ በነፍስና በሥጋ ድኅነትን እናገኛለን፡፡
ጥያቄ፦ በፆም ድኅነተ ሥጋን ካገኙ ሰዎች መካከል ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ስሟ ተጠቅሶ የምናገኛት አስቴር አንዷ ናት፡፡ አስቴር በወገኖቿ ላይ
የተላለፈውን የሞት ፍርድ ይሻር ዘንድ ያደረገችው ትልቅ ነገር ሁሉም ወገኖችዋ እንዲፆሙና እንዲጸልዩ
ነበር፡፡ በዚህም ፆም ምክንያት በወገኖቿ ላይ የተላለፈው የሞት ውሳኔ ወደ ሕይወት እንዲቀየር
አድርጓል፡፡ (መ.አስ ፬፥፲)
ጥያቄ፦ በፆም ድኅነተ ነፍስ ካገኙ ሰዎች መካከል ታሪክ ብትነግረን?
መልስ፦ ሌላው በፆም ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስ ካገኙ ሕዝች መካከል የነነዌ ሕዝቦች ዋነኞቹ ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ሊያመጣባቸው ካለው መከራ በፍፁም መፀፀት በንስሐ፣ በመፆም፣ በመጸለይ ከመቅሰፍት
ድነዋል፡፡ (ት.ዮናስ ፫)
ማጠቃለያ ጥያቄዎች
በተማራችሁት መሠረት ትክክለኛውን መልስ ምረጡ
ምዕራፍ አምስት
ጸሎት
የምዕራፉ ዓላማ
ተማሪዎች ይህን ምዕራፍ ተምረወስ ሲጨርሱ
፩ ስለ ጸሎት ምንነት ይረዳሉ፡፡
፪ ጸሎት በማድረግ የሚያገኙትን ጥቅሞች ያውቃሉ፡፡
፫ እንዴትና ስለምን መጸለይ እንዳለባቸው ይለያሉ እነርሱም ጸሎትን የሚያረጉ
ይሆናሉ፡፡
(የመክፈቻ ጥያቄዎች)
፩ ልጆች እስቲ በጸሎታችሁ ስለ ምን እንደምትጸልዩ ለመምህራቹ ተናገሩ ?
መልስ፦ ክርስቲያን ስለሚጸልየው ነገር አስቀድሞ ማወቅና ማዘጋጀት አለበት፡፡ ስለምን እንደምንጸልይ
የማያውቅ ሰው ፍላጎቱን የማያውቅ ደካማ ሰው ነው ስለዚህ ለጸሎት በቆምን ጊዜ
ሀ. ስለራሳችን እንጸልይ
ስለ ራሳችን ስለ ምንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወታችን ማለትም ትምህርታችንን እንዲገልጥልን፣ ሥራችንን
እንዲባርክልን፣ጤና እንዲሰጠን፣ ኃይል ጉልበት እንዲሆንነን አጥብቀን ልንጸልይ ይገባል፡፡
ለ. ስለ ቤተሰቦቻችን እንጸልይ
እግዚአብሔር ቤተሰቦቻችንን ማለትም እናትና አባታችንን እህት ወንድሞቻችንን በእድሜ በጤና
እንዲጠብቅልን ሰላምና ፍቅርን እንዲያድልልን ሥራቸው እንዲቃናላቸው፣በመንፈሳዊ ሕይወት
ሐ. ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቃት ዘንድ አገልጋዮቿ የሚሆኑ
ካህናትን ሁሉ ይጠብቅ ዘንድ ስለ ፍፁም አንድነቷ፣ ስለ ሥርዓቷ መጠበቅ ዘወትር ሊለምኑ ይገባል፡፡
መ. ስለ ሀገር
የሁሉ መኖሪያ ስለሆነች ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ስለ ህዝቦቿ አንድነትና ፍቅር እንዲሁ እግዚአብሔር
ሰላሟን ይጠብቅ ዘንድ መለመን ይገባል፡፡ በተጨማሪ ሰላሟን ለመጠበቅ በየድንበሩ ላሉ ሠራዊቶች
ህዝቦቿን ይመግቡ ዘንድ ስለሚታትሩ ስለ ገበራዎች ዝናብን ይሰጥ ዘንድ አብዝ መጸለይ ይገባል፡፡
ሠ. ስለ ዓለም
ክርስቲያን ሁሉ ወገኑ ለሁሉም የየሚያስ ነውና እግዚአብሔር ዓለምን በውስጧ ያሉ ህዝቦቿን ሁሉ
ከርሀብ፣ ከቸነፈር፣ ከተፈጥሮና ከድንገተኛ አደጋ፣ ከእርስ በእርስ ጦርነት ይጠብቅ ዘንድ ዘወትር
ለጸሎት በቆምን ጊዜ ልንጸልይ ያስፈልጋል፡፡
ጥያቄ፦ እንዴት እንጸልይ?
መልስ፦ ለጸሎት በእግዚአብሔር ፊት የሚቆም ማንኛውም ክርስቲያን ጸሎቱን እንዴት ማቅረብ
እንዳለበት ሊያውቅና አውቆ ሊቆም ይገባዋል፡፡ አንዴት መጸለይ እንዳለባቸው ባለማወቅ ብዙዎች
እግዚአብሔርን አሳዝነዋል ጸሎታቸውም ተቀባይነት አላገኘም፡፡ ክርስቲያች ግን እንዴት እንጸልይ ቢሉ?
ሀ. በእምነት መጸለይ
እግዚአብሔር አምላካችን ስለሚደንና ስለሚያስብልን ልመናችንን ስለሚሰማንና የሚጠቅመንን ነገር
እንደሚያደርግልን የተሻላንም ነገር እንደሚሰጠን በፍፁም ልባችን አምነን ንልጸልይ ይገባል፡፡ መጽሐፍ
ቅዱስ “አምናችሁ በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ” ማቴ ፳፩፥፳፪ እንዲል በእምነት ከጸለይን
የለመነው ይሳካልናል የፈለግነውም ይሰጠናል፡፡
ለ. በማስተዋል መጸለይ
ለጸሎት በእግዚአብሔር ፊት በምንቆምበት ጊዜ ሁሉ ከውስጣችን የምናወጣው ማናቸውም ቃልና
የምናደርገው ማንኛውም ዓይነት እንቅስቃሴ በማወቅና በማስተዋል መሆን አለበት፡፡ ይህምእንዲሆን
ዘወትር “አንተ የመድኃኒቴ አምላክ ነህና በእውነት ምራኝ አስተምረኝም ቀኑን ሁሉ አንተን ተስፋ
አድርጌያለሁ” ልንለው ይገባል፡፡ መዝ ፳፭፥፭
ሐ. በትሕትና
አንድ ክርስቲያን በክርስቲያንነቱ ሊያሟላቸው ከሚገቡ መልካም ምግባራት መካከል ትሕትና እጅግ
አስፈላጊ ነው፡፡
ታዲያ በእግዚአብሔር ፊት ለጸሎት የሚቆም ሠው ትሁት ሊሆን ይገባል፡፡ ምክንያቱም ትህትና
ዲያቢሎስን ድል ማድረጊያ መንፈሳዊ መሳሪያ ነውና፡፡
ማጠቃለያ ጥያቄ