Professional Documents
Culture Documents
Prosperity Party Constitution Book Size - 281119233727
Prosperity Party Constitution Book Size - 281119233727
(ብልጽግና)
መተዳደሪያ ደንብ
(ረቂቅ)
ኅዳር 8 ቀን /2012 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
መግቢያ
በኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር(ኢሕአዴግ) እና በአጋር ድርጅቶች
አመራር በሀገራችን ያስመዘገብናቸውን ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ለውጦችን
አስጠብቆ ለማስፋት፣ ስሕተቶችን ለማረም እና የዛሬውንና የመጪውን ትውልድ ጥቅምና
ፍላጎት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የድርጅታችንን ቅርጽና ይዘት ወቅቱ ለሚጠይቀው ትግል
በሚመጥን መልኩ ማሻሻል በማስፈለጉ፤
የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶችና አጋር ድርጅቶች ሀገር በመራንባቸው ዓመታት በአመዛኙ
ተመሳሳይ የፖለቲካ ዓላማ፣ ፕሮግራም እና መሠረታዊ አቅጣጫ እየገነባን የመጣን በመሆኑ፤
ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል እና ስሕተቶችን በማረም ወደ ሚቀጥለው የትግል ምዕራፍ
ለመሸጋገር አስቻይ ዐቅም ያለን እንዲሁም የምናካሂደው ውሕደት እያንዳንዱ ድርጅት
የነበረውን የዓላማና የተግባር ውሕደት በአዲስ መንፈስ ይበልጥ በማጠናከር የተሻለ ኃይል
እንድናሰባስብ የሚያስችለን በመሆኑ፤
በኢሕአዴግ ድርጅታዊ ጉባኤዎች የፓርቲ ውሕደት አጀንዳ በተከታታይ ቢነሣም ሳይወሰንና
ሳይፈጸም መቆየቱን ግምት ውስጥ በማስገባት 11 ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ የዝግጅት ሥራዎች
በፍጥነት ተጠናቀው ድርጅቶቹ ወደ ውሕደት እንዲሸጋገሩ ያስቀመጠውን ውሳኔ ለመፈጸም
በማስፈለጉ፤
ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የተለያዩ ማንነቶች በጋራ
ባካበቱት ዕሴት የተገነባችና የጋራ ራእይ ያላቸው ሕዝቦች መኖሪያ ኅብረ ብሔራዊት ሀገር
መሆኗን በመገንዘብ፣
የሀገራችን የኢትዮጵያን ዕድገትና የጋራ ብልጽግና እውን ለማድረግ ጠንካራና ቅቡልነት ያለው
ሀገረ መንግሥት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ፣
አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት ልማትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን
የሚያረጋግጥ አካታች የኢኮኖሚ ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት፣
ቀጣይነት ያለው ብልጽግናን የሚያረጋግጥ ሁለንተናዊ ማኅበራዊ ልማትና ሀገራዊ ክብርን
ማዕከል ያደረገ የውጭ ግንኙነት መመሥረት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት፣
የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሲ የሰፈነባት፤ የግለሰብና ቡድን መብቶች በሚዛኑ የሚከበሩባት፤
የበለጸገች፣ ኅብረብሔራዊ ማንነቷ የዳበረና አንድነቷ የተጠናከረ ኢትዮጵያን በቁርጠኝነት
ዕዉን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት፣
በመደመር አስተሳሰብና በአንድነት ቅኝት በመነሣት፣ ልናያት የምንፈልጋትን የላቀች
ኢትዮጵያን ለመገንባት የእያንዳንዳችንን ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑን በመረዳት የበኩላችንን
ሚና ለመጫወት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ተሰባስበን ለመታገል በማስፈለጉ፣
የኢሕአዴግ 11 ኛው ጉባኤ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት የኢሕአዴግ ምክር ቤት እና አጋር
ፓርቲዎች የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ
ቁጥር 1162/2011 ባከበረ መልኩ የብልጽግና ፓርቲ (ብልጽግና) መተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል፡፡
ምእራፍ አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌዎች
አንቀጽ 1. አጭር ርእስ
ይህ መተዳደሪያ ደንብ “የብልጽግና ፓርቲ (ብልጽግና) መተዳደሪያ ደንብ” ተብሎ
ሊጠቀስ ይችላል።
ይጠየቃል፣
መ) ማንኛውም አመራር ወይም አባል የሐሰት ሪፖርት መስጠትም ሆነ
መጠቀም ክልክል ነው፣
ሠ) በፓርቲው ውስጥ አንጃነት እና ቡድነተኝነት መፍጠር ወይም ማስፋፋት
ክልክል ነው፣
ረ) ማንኛውም አባል የሌላ ፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆኑ ከተደረሰበት ከፓርቲ
አባልነቱ ይሰረዛል፣
ሰ) የፓርቲው አባላትና እጩ አባላት የሚፈጽሟቸው ጥፋቶች ክብደት እየታየ
የሚከተሉት እርምጃዎች ይወሰዳሉ፤
1. ለሙሉ አባል
ሀ) ተግሳጽ፣
ለ) የቃል ማስጠንቀቂያ መስጠት፣
ሐ) የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት፣
መ) ከኃላፊነት ማገድ፣
ሠ) ከኃላፊነት ማነሣት፣
ረ) ከአባልነት ማገድ፣
ሰ) ከአባልነት መሠረዝ፤
2. ለእጩ አባል
ሀ) ፌዴራል፣
ለ) ክልል፣
ሐ) ዞን/ከተማ፣
መ) ወረዳ/ልዩ ወረዳ/ከተማ፣
ሠ) ቀበሌ ናቸው፡፡
2) ፓርቲው የሚከተሉት ተቋማዊ መዋቅሮች ይኖሩታል።
ሀ) ጉባኤ፣
ለ) ማዕከላዊ ኮሚቴ፣
ሐ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ
መ) ፕሬዚዳንት
ሠ) ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣
ረ) የቁጥጥርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን፣
ሰ) የፓርቲው ዋና ጽሕፈት ቤት
ሸ) የፓርቲው የክልል ፓርቲ ጽሕፈት ቤቶች፣
ቀ) የፓርቲው የዞን፣ የከተማ፣ የወረዳና የቀበሌ ጽሕፈት ቤቶች፣
አንቀጽ 16. የፓርቲው ጉባኤ፣ የክልል፣ የዞን፣ የከተማ፣ የወረዳና የቀበሌ የኮንፈረንሶች
አወቃቀር
1) የፓርቲው ጉባኤ በፌዴራል ደረጃ ይቋቋማል፤
2) በክልል ደረጃ ክልላዊ ኮንፈረንስ የሚኖር ሆኖ፤ እንደአስፈላጊነቱ
በየደረጃው ከዞን እስከ ቀበሌ ኮንፈረንሶች ሊዋቀሩ ይችላሉ፣
3) የኮንፈረንስ ውክልና በዋናነት የአባላትን ብዛት መሠረት ያደረገ ሆኖ፤
አነስተኛ የሕዝብ ብዛት ቁጥር ያላቸውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች
አባላት ውክልና ባረጋገጠ መልኩ ይዋቀራል፤
4) በመደበኛ ጉባኤና በእያንዳንዱ ኮንፈረንስ ወቅት ከሚመረጡ ጉባኤያተኞች
እና የኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ብቃት ያላቸውን አዳዲስ አባላት ያካተተ
ይሆናል።
ምዕራፍ አራት
የፓርቲው የክልል አደረጃጀት
አንቀጽ 25. የፓርቲ አደረጃጀትና አወቃቀር
1) ለፓርቲው ዋና ጽሕፈት ቤት ተጠሪ የሆኑ፤ የክልል የፓርቲ ጽሕፈት ቤቶች
የክልል ስያሜ በመያዝ እንደሚከተለው ተቋቁመዋል፡፡
አንቀጽ 35. የፓርቲው የሰው ሀብት፣ ንብረት፣ ፋይናንስና የሂሳብ መዛግብት የአሠራር
ሥርዓት
1) የፓርቲው የሰው ሀብት፣ ፋይናንስና ንብረት ማዕከላዊ ኮሚቴ
በሚያወጣው መመሪያ መሠረት የሚተዳደር ይሆናል፤
ሀ) በፕሬዚዳንቱ ወይም
ለ) በማዕከላዊ ኮሚቴው 1/3 ድምፅ ድጋፍ ሲያገኝ ወይም
ሐ) በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው አብላጫ ድምፅ ድጋፍ ሲያገኝ ወይም
መ) በቁጥጥር እና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን አባላት 1/ 2 ድምፅ ድጋፍ ሲያገኝ
ወይም
3) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) መሠረት የቀረበ የማሻሻያ ሐሳብ ለፓርቲው
ጉባኤ መቅረብ የሚችለው በማዕከላዊ ኮሚቴው በአብላጫ ድምፅ ድጋፍ ካገኘ
ነው።
4) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3) መሠረት በማዕከላዊ ኮሚቴ በቀረበው
የማሻሻያ ሐሳብ ላይ የፓርቲው ጉባኤ በአብላጫ ድምፅ ከወሰነ መተዳደሪያ
ደንቡ ይሻሻላል፡፡