You are on page 1of 8

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የማህበራዊ ሚዲያ ሞኒተሪንግ ክትትል እና ድጋፍ ዴስክ የሁለት ወራት


አጭር ሪፖርት

መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም


ማውጫ

1. የሪፖርቱ ጭማቂ ሃሳብ


2. መግቢያ
3. ክፍል አንድ
1. የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም
1.1 የቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም ተቋማዊና ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች
4. ክፍል ሁለት
2. የአበይት ተግባራት አፈጻጸም
2.1 የአበይት ተግባራት ግቦችና ዋና ዋና አፈጻጸም
1.1 ከዕቅድ ውጪ የተከናወኑና ታቅደው ያልተከናወኑ
5. ክፍል ሦስት
3. ያጋጠሙ ችግሮች፣የተወሰዱ የመፍትሄዎች፣ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች
3.1 ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች

3.1.1 ያጋጠሙ ችሮች

3.1.2 የተወሰዱ መፍሔዎች

3.2 ጠንካራና ደካማ ጎኖች

3.2.1 ጠንካራ ጎኖች

3.2.2 ደካማ ጎኖች

3.3 ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች


4. ማጠቃለያ

የ 2014 በጀት ዓመት ሁለት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት በአጭሩ

ሪፖርቱ ጭማቂ ሃሳብ


የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ፣ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ባሳለፍናቸው ሁለት ወራት በርካታ ልዩ ልዩ ተግባራትን
ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ከነዚህም መካከል የተቋሙ የ 5 ዓመት ስትራቴጂክ ረቂቅ ሰነድ እና የ 2014 በጀት ዓመት
ዕቅድ ሲዘጋጅ ግብአት በመስጠት የሚዲያ ማደራጃ፣ክትትል እና ድጋፍ ዘርፍ ዕቅድን ማዘጋጀት እንዲሁም
ይህንን መሰረት በማድረግ የዴስኩን ዕቅድ አዘጋጅቶ ለፈጻሚዎች በማውረድ ወደ ስራ ለመግባት ተችሏል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ባሳለፍናቸው ሁለት ወራት ዋና ዋና ግቦችን እና ዝርዝር ተግባራትን መሰረት ያደረገ ልዩ
ልዩ ተግባራቶችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ በዚህም በባለፉት ሁለት ወራቶች የታዩት አፈጻጸሞች ወደ ፊት
ለዴስኩ አስፈላጊው የሰው ሃይልና የግብአት ችግር እየተሟላ ሲሄድ ደረጃ በደረጃ ተቋሙ ያስቀመጠውን
ራዕይ ሊያሳካ ይችላል የሚል እሳቤ አለን፡፡

መግቢያ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተጣለበትን ተልዕኮ በአግባቡ ለመወጣት እንዲያስችለው የተለያዩ የስራ
ክፍሎችን በማዋቀር ወደ ስራ የገባ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የስራ ክፍሎቹ የመንግስትን ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት
በማድረግ በዜጎች መካከል የተሳለጠ የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር በማድረግ የሀገርን መልካም ገጽታ ግንባታ
አዎንታዊ በሆነ መልኩ መገንባት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህን በማድረግ ረገድ የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ፣ክትትልና ድጋፍ
ዴስክ ወደ ስራ ከገባ ጀምሮ የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም አበረታች ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን
በባለፉት ሁለት ወራት ማለትም ሐምሌ እና ነሐሴ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ያከናወናቸውን አበይት ተግባራት
እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ክፍል አንድ

5. የዝግጅት ምዕራፍ አፈጻጸም


5.1 የቁልፍ ተግባራት አፈጻጸም ተቋማዊና ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች

በስራ ክፍሉ ዝግጅት ምዕራፍ ወቅት የተከናወኑ የተለያዩ ተግባራት ተከነውነዋል ለአብነት ያህል የአምስት
ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ (2014-2018) ረቂቅ የሰነድ ዝግጅትን መገምገም፣ ማረምና ማሻሻያ ሀሳቦችን

መስጠት፤ የ 2015 በጀት ዓመት የዘርፉ ረቂቅ እቅድ እንዲዘጋጅ ተደርጎ የማሻሻያ ሃሳብ እንዲሰጥበት
ለሚመለከተው ሃላፊ መላክ፣ በእቅድ ዝግጅት ሂደቱም ላይ የተቋሙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች እና

ባለሙያዎች እንዲሳተፉና ሀሳባቸውን እንዲሰጡ ማድረግ፤ የዴስክ እቅድ ለፈጻሚዎች በማውረድ (ካስኬድ
በማድረግ) የግል እቅዶቻቸውን እንዲያዘጋጁ የክትትልና ድጋፍ ስራ ተከናውኗል፡፡

ክፍል ሁለት

6. የአበይት ተግባራት አፈጻጸም

6.1 የአበይት ተግባራት ግቦችና ዋና ዋና አፈጻጸም

ስትራቴጂክ ግብ 1:- የህዝብና የተገልጋይ አካላት ዕርካታን ማሳደግ

ለሚነሱ ቅሬታዎች ፈጣን ምላሽ መስጠትን አስመልክቶ በተለያዩ ጊዜያት ከህብረተሰቡ የተነሱ ቅሬታዎችን

መሰረት በማድረግ የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ ቅኝት በማድረግ እና ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ የማህበራዊ

ሚዲያ ዳሰሳ አዝማማያ ትንተና በመስራት ለሚመለከተው የተቋሙ አመራር በጥራትና በወቅቱ መረጃዎች

እንዲደርሱ ተደርጓል፡፡

ስትራቴጅክ ግብ 2:- የበጀትና ፋይናንስ አጠቃቀም ውጤታማነት ማሳደግ፤

ለዘርፉ የተመደበውን ሀብትና በጀት ውጤታማ በሆነ መንገድ ስራ ላይ ማዋል፣ ለዘርፉ የሚያፈልጉትን
ግብዓቶች መጠየቅና ማስፈጸም እንዲሁም ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ተጨማሪ የሀብትና የፋይናንስ ምንጭ
ማፈላለግ በሚል ታቅዶ ለስራ የሚያስፈልጉንን አጠቃላይ ግብአቶች ከማሟላት አኳያ ለግዢ ክፍል የግብአት
አቅርቦት እንዲሟላል ተጠይቋል ፡፡

ስትራቴጅክ ግብ 3:- የባለድርሻ አጋር አካላት ተሳትፎና ቅንጀታዊ አስራር ማሳደግ፤


በአገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ክንውኖች አና ሁነቶች ላይ የማህበራዊ ሚዲያ ክትትል እና አዝማሚያ ትንተና

ማከናወን በሚል ታቅዶ የጀግኖች አትሌቶችን ድል፣የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሃይል ማስጀመርና የውሃ

ሙሌትን፣ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከወጣቶች ጋር ያደረጉት ውይይት፣የኢትዮጵያ

ሙስሊሞች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያካሄዱትን የምክክር መድረክ ወዘተ በተሰኙ የመንግስት ኮሙኒኬሽን
በየጊዜው በሚወጡ አጀንዳዎች/ ሁነቶቹን አስመልክቶ አንዲሁም አገልግሎቱ በሚያወጣቸው

መግለጫዎችን መሰረት በማድረግ የተሰሩ በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ቅኝቶችና የአዝማሚያ ትንተናዎች

ተጠቃሽ ናቸው ፡፡

በሌላም በኩል ህዝቡ የሚያነሳቸዉን ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዩች በማሰባሰብ፣ በማደረጀትና ተንትኖ ለመንግስት

በማቅረብ የሁለትዮሽ ተግባቦትን ማጠናከር በሚል ታቆዶ ከህዝብ መረጃ በመሰብሰብ፣ በመተንተንና

የሁለትዮሽ ግንኙነቱን ለማጠናከር የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ በማድረግ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ

የአዝማሚያ ትንተና ስራ ተሰርቷል፡፡

በተጨማሪም የማህበራዊ ሚዲያው ሚዛናዊና ተገቢ መረጃ በመስጠት ለሠላምና ለሀገር እድገት የበኩሉን

ሚና አንዲጫወት በሚል ርዕስ የሠላም ሚ/ር በተዘጋጀ የጋራ ምክክር መድረክ ላይ ሀለት የዴስካችን

ባለሙያዎች አንዲሳተፉ አድርገናል፡፡ በዚህም በተቋማችንና በሠላም ሚ/ር መካከል መልካም ጅማሮን

የሚያሳይ ቅንጅታዊ አሰራር ለመፍጠር ተችሏል፡፡

በየጊዜው በተቀረፁት መንግስታዊ አጀንዳዎች ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መግባበት

እንዲፈጠር ማድረግ ላይም በየሳምንቱ ተቀርጸው በሚሰጡ ወቅታዊ ሃገራዊ አጀንዳዎች ላይ የማህበራዊ

ሚዲያ ቅኝት በማድረግ እና የአዝማሚያ ትንተና በመስራት ለሚመለከታቸው ሃላፊዎች ዕለታዊ እና

የተጠቃለለ ሳምንታዊ ሪፓርት ማቅረብ ተችሏል፡፡

ስትራቴጅክ ግብ 4:- የመንግስት መረጃ ተደራሽነትና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን አገልግሎትን


አሰጣጥ ማሳድግ፤
በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የማህበራዊ ሚዲያ ስራዎች የህዝብ አስተያየት ደሳሳ
እና የአዝማሚያ ትንተና ማድረግ በሚል ታቅዶ ተጽዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያዎችን በመለየት፣ ዳሰሳ
በማድረግና የመተንተን ስራ ተከናውኗል፡፡
የማህበራዊ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን የመረጃ አያያዝ፣ አጠቃቀምንና ስርጭትን ማሻሻል በተመለከተ የሚዲያ

መረጃ አያያዝ፣ አጠቃቀምና ስርጭትን በዘመናዊ መንገድ ተደራሽ ማድረግ በሚል ታቅዶ በየጊዜው ከስራ
ክፍላችን የሚወጡ መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅተን የመያዝ እና ለሚፈለገው ዓላማም ለማዋል

የሚያስችል አሰራር በመከተል ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡

ስትራቴጅክ ግብ 6 ፡- የተቋሙን አገልግሎት አስጣጥ ቅልጥፍናና ዉጤታማነት ማሳደግ ፤


ዘርፉ ተግባራቱንና ተልእኮዉን ለማስፈፀም የሚያስችለዉ የህግ ማዕቀፎች፣ ልዩ ልዩ የአሰራር መመሪያዎች፣

ማኑዋሎችንና ሰነዶችን በማዘጋጀት የተቋሙን ስራ ማቀላጠፍ በሚል ታቅዶ የ የማህበራዊ ሚዲያ

አጠቃቀም መመርያ ረቂቅ በማዘጋጀት የዘርፉ ሃላፊ አስተያየት እንዲሰጥበት ቀርቧል፡፡

6.2 . ከዕቅድ ውጪ የተከናወኑና ታቅደው ያልተከናወኑ

ከእቅድ ውጭ የተከናወኑ ስራዎች ፤

ኢቲቪ ዳጉ በተሰኝ ፕሮግራም የመንግስት ኮሙንኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ደ/ር ለገሰ ቱሉ በውቅታዊ

አገራዊ ጉዳዮች ዙርያ በቀጥታ ቆይታ ያደረጉበትን ዝግጅት ፣ ክብርት ሠላማዊት ካሳ ከ TALK TO OBN

ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ እንዲሁም ኢትዮጵያ ታመስግን በሚል ርዕሰ ጠ/ሚ/ር አብይ አህመድ

ባስተላለፉት መልዕክት ዙርያ ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የሰጡትን ማብራሪያ አሰመልክቶ
ሪፓርት ቀርቧል፡፡ እነዚህ ሁሉ የሚዲያ ሞኒተሪነግ ስራዎችከሜይንስትሪሙ ሚዲያ በተደረገ ክትትል
የተወሰዱ መረጃዎቹ ናቸው፡፡ ከላይ የተጠቀሱትን ስራዎች አስመልክቶ ምንም እንኳን የስራ ክፍላችን
አጠቃላይ ትኩረቱን የሚያደርገው ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ቢሆንም ጉዳዩ ለዘርፉ እጅግ አንገብጋቢ
በመሆኑ እና በቶሎ ለዘርፉ ኃላፊዎች መቅረብ ስለነበረበት ቅዳሜ ፣እሁድ፣ ሌሊት ሳይባል ተሰርተው የቀረቡ
ስራዎች ናቸው ፡፡

ክፍል ሦስት

7. ያጋጠሙ ችግሮች፣የተወሰዱ የመፍትሄዎች፣ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ትኩረት


የሚሹ ጉዳዮች
7.1 ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሄዎች
7.1.1 ያጋጠሙ ችሮች
ለዘርፉ ስራ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ያልተደራጁ መሆኑ፤
የሰው ሀይል የተሟላ አለመሆኑ፤
ስራዎችን በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በተለያዩ ጊዜያዊ ተግዳሮቶች ምክንያት
ሳይከናወኑ መቅረታቸው፤
የአቅም ውስንነቶች መኖር፤

7.1.2 የተወሰዱ መፍትሔዎች


ስራዎችን በስታንዳርድ መሰረት ለመፈጸም የግብዓት እና የሰው ኃይል ችግርን
ለመቅረፍ ከዘርፉ ሀላፊ ጋር በመነጋገር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑ፤
ከግዢ ጋር ተያይዞ ለስራ ሂደቱ የሚያስፈልጉ ግብአቶች በወቅቱ ተሟልተው
እንዲገኙ ለማድረግ የግዢ ፍላጎት መቅረቡ፤
የአቅም ክፍተቶችን ስልጠና በመስጠት ደረጃ በደረጃ ለመቅረፍ መጠነኛ ጥረት
እየተደረገ መሆኑ፤

7.2 ጠንካራና ደካማ ጎኖች


7.2.1 ጠንካራ ጎኖች

ባለው የሰው ሃይል በትብብር በቅንጅት መስራት መኖሩ/strong team sprit/


ባለው ግብአት ተጠቅሞ ስራን የመስራት ሁኔታ መኖሩ፤
የአገልጋይነት ስሜት መኖሩ፤
የአሰራር ስርዐቶችን በየጊዜው ለማሻሻል ጥረት መኖሩ/ continual improvement/

7.2.2 ደካማ ጎኖች

ለስራ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን በፍጥነት ማቅረብ አለመቻሉ፤


የሰው ኃይሉን በማሟላት በሚጠበቀው ልክ ስራ መስራት አለመቻሉ፤
በቴክኖሎጂ የታገዘ የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ ክትትልና ድጋፍ አለመኖር ፣
ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የአቅም ግንባት ስልጠና አለመሰጠቱ፤

7.3 .ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች


የግብአትና የሰው ሃይል እጥረት ችግሮችን መፍታት፤
ከስራው ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የአቅም ግንባት ስልጠና አንዲሰጥ ማድረግ፣
በቴክኖሎጂ የታገዘ የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ ክትትልና ድጋፍ አንዲኖር ማድረግ ፣

8. ማጠቃለያ

የማህበራዊ ሚዲያ ዳሰሳ ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ባላፉት ሁለት ወራት ወደ ስራ የገባ ቢሆንም በዚህ በጣት
በሚቆጠሩ ጥቂት ወራት የማይናቁ ስራዎችን መስራቱን ሪፓርቱ ያሳያል፡፡በ 2015 በጀት ዓመት ባለፈው
የነበሩንን ጥንካሬዎች በማጎልበት እና ድክመቶታችንን በማረም በሙሉ ተነሳሽነት እና በቁርጠኝነት እጅ
ለእጅ በመያያዝ ስራዎችን በጥራት ለመከወን እንጥራለን፡፡

የማህበራዊ ሚዲያ ሞኒተሪንግ ስራዎችን ሪፓርት ለማድረግ የምንጠቀምባቸውን ፎርማቶችን


በማዘጋጀት ስራ ላይ ከማዋላችን ባሻገር ሌሎችም እንደ ምርጥ ተሞክሮ በመውሰድ የሞኒተሪነግ
ስራዎች አንዲሰሩበት ተደርጓል፡፡

You might also like