You are on page 1of 13

የ 2013 በጀት ዓመት የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የሥነምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል

መሪ ዕቅድ አቅጣጫዎች

የፌዴራል ሥነምግባርና ፀረሙስና ኮሚሽን

ጥቅምት/2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ

1
ማውጫ ገጽ
1 መግቢያ 3

2 ዓላማ 4

3 በሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የሚታዩ ዋናዋና ችግሮች 4

4 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የ 2013 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ 6

5 ስትራቴጂክ ትኩረት መስኮችና ውጤቶች 6

6 ስትራቴጂያዊ ግቦች 7

7 ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ዋና ዋና ተግባራት 7

የኮሚሽኑን ግብና ዋና ዋና ተግባራትን መሠረት በማድረግ የሥነምግባር


8 9
መከታተያ ክፍሎች ቀጣይ የዕቅድ አቅጣጫዎች

9 የክትትልና ድጋፍ አግባብ 11

10 የሪፖርት ስርአት 11

11 የ 2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ትግበራ መርሀ ግብር 12

12 ማጠቃለያ 14

አባሪ - የዕቅድና የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቅጽ 15

1. መግቢያ

የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሁለተኛውን ሀገራዊ የእድገትና የትራንስፎሜሽን ዕቅድ ለማሳከት የአምስት
ዓመት ስትራቴጂያዊ እቅድ አቅዶ ተግባራዊ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ስኬቶች ተመዝግበዋል፤ ተግዳሮቶችም አጋጥመዋል፡፡
ከተመዘገቡት ስኬቶች መካከል ህብረተሰቡ በፀረ-ሙስና ትግል ተሳታፊ እንዲሆን ለማድረግ የተለያዩ
አደረጃጀቶችን ለመፍጠር መሞከሩ፣ በመንግስት ተቋማትና የልማት ድርጅቶች ውስጥ ለሙስናና ብልሹ
አሠራር የሚያጋልጡ አሠራሮችን በመፈተሽ ምክረ-ሃሳቦችን ለመስጠት ጥረት መደረጉ፣ ሀገር አቀፍ የህፃናትና
ወጣቶች ሥነ-ምግባር ግንባታ ስትራቴጂ መቀረጹና በተወሰነ መልኩም ቢሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ ለወጣቶች

2
የሥነምግባር ትምህርት የሚያግዙ ተግባራት መከናወናቸው፣ የሀብትና ንብረት ምዝገባና ማሳወቅ ተግባራት
መከናወኑ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡

ኮሚሽኑ ከገጠሙት ተግዳሮቶች ውስጥ ደግሞ በፌዴራልና በክልል የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች መካከል የነበረው
ግንኙነት ለአንድ ዓላማ በጋራ የመሥራት ሳይሆን በተናጠል የሚደረግ፣ በመደጋገፍ፣ አቅም በመገንባትና
በተደራጀ መልክ መረጃ በመለዋወጥ ላይ የተመሠረተ አለመሆን፣ በፀረ-ሙስና ትግል ቀጥተኛ ሚና ያላቸውንና
ተጽዕኗቸው ከፍተኛ የሆነ ባለድርሻ አካላትን በተለይም የሲቪክ ማህበራትን በትክክል ለይቶና ትኩረት ሰጥቶ
አለመሥራት፣ በቅንጅት አለመስራት፣ በመልካም ሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥራ ላይ የሚዲያ
ተቋማትን አቅም አሟጦ አለመጠቀምና ሚናቸውን እንዲወጡ አለማድረግ፣ በተቋማት የተቀናጀ የሙስና
መከላከል ስትራቴጂ ትግበራ ውስንነት ያለበት መሆኑ እንዲሁም የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ህጉ በሚፈቅደው
ሥርዓት መሠረት ማስመዝገብ የሚገባቸውን በተሟላ መንገድ መመዝገብ አለመቻል፣ የተሟላ መረጃ
አለመያዝ፣ ያላስመዘገቡትን ተጠያቂ አለማድረግ፣ በመንግስት ተቋማትና የልማት ድርጅቶች ውስጥ
ለሙስናና ብልሹ አሠራር የሚያጋልጡ አሠራሮችን በመፈተሽ የተሰጣቸውን ምክረ-ሀሳብ ተግባራዊ
የማያደርጉትን፣ ግልፅነትን ከማስፈን ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አንፃር ተቋማትን ተጠያቂ የሚያደርግ የህግ
ማዕቀፍ ክፍተቶች መኖራቸው እንዲሁም በተቋማት ዉስጥ የተደራጁ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ሚና
ዉስን መሆን ካጋጠሙ ችግሮች መካከል ግንባር ቀደሞቹ ነበሩ፡፡

እነዚህንና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን ግምት ውስጥ በማስገባት ውስጣዊና ውጫዊ ዳሰሳ በማካሄድ እንዲሁም የሀገሪቱን ረቂቅ
መሪ እቅድ መነሻ በማድረግ ኮሚሽኑ ሃገር አቀፍ የሥነምግባር ግንባታና የሙስና መከላከያ መሪ እቅድ ያዘጋጀ ሲሆን ይህን
መሰረት ባደረገ መልኩ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የቀጣይ አመት እንቅስቃሴን የሚያመላክት መሪ ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡

የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችም ይህን መሪ ዕቅድ መነሻ በማድረግና ከራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ጋር
አጣጥመው የራሳቸውን ስትራቴጂያዊ ዕቅድ እንዲያቅዱ ይጠበቃል፡፡
መሠረታዊ የዕቅድ አቅጣጫው ሀገራዊ ራዕይን፣ የኮሚሽኑን ተልዕኮ፣ ራዕይን፣ እሴቶችን፣ ስትራቴጂያዊ
የትኩረት መስኮችንና ግቦችን እንዲሁም በስትራቴጂያዊ ግቦች ሥር የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ያካተተ
ነው፡፡

2. ዓላማ

 ተቋማት የራሳቸውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ዕቅዳቸውን በመከለስ ተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና
መከላከል ስትራቴጂ ዕቅድ እና የ 2013 በጀት ዓመት ዕቅዳቸውን እንዲያዘጋጁ ለማድረግ፣
 በተለያዩ ተቋማት የሚደረገውን የተናጠል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ትግል ከማቀናጀት በተጨማሪ የሚዘጋጁ
ዕቅዶች ከኮሚሽኑ ዕቅድ ጋር ተቀራራቢ ይዘት እንዲኖረው ለማድረግ ነው፡፡

3
3. በሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የሚታዩ ዋናዋና ችግሮች

የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀው የአሥር ዓመት (2013-2022 ዓ.ም)
የሀገር አቀፍ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስትራቴጂያዊ መሪ ዕቅድ መነሻ በማድረግ ለ2013 በጀት ዓመት የሥራ
ዕቅድ የማዘጋጀትና ዕቅዱንም መተግበር በሚያስችል መልኩ እራሱን በአዲስ መልክ አደራጅቷል፡፡
በኮሚሽኑ የተዘጋጀን ይህን ዕቅድ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ደግሞ በተለያዩ ተቋማት የሚገኙ የሥነምግባር
መከታተያ ክፍሎች የማይተካ ሚና አላቸው፡፡ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን አቅም ሙሉ ለሙሉ አሟጦ
ለመጠቀም ደግሞ በቅድሚያ ለሥራቸው እንቅፋት የሆኑ አሠራሮች በመለየት ሊቀረፉ ይገባል፡፡ በሥነምግባር
መከታተያ ክፍሎች ለሥራቸው እንቅፋት እንደሆኑ በተደጋጋሚ የሚነሱ ዋና ዋና ችግሮችን ለመለየት አጠር
ያለ ዳሰሳዊ ጥናት ከማድረግ በተጨማሪ በኮሚሽኑ በተለያየ ጊዜ በተዘጋጁ የውይይት መድረኮች የተነሱ
ሃሳቦችን በማጠቃለል እንደሚከተለው ቀርቧል፤
 ከሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ተጠሪነት ጋር በተያያዘ ወጥ አሠራ አለመኖር፣

 በ JEG ለሥራ መደቡ የተሰጠው ደረጃ ዝቅተኛ መሆን፣

 የተቋማት አመራሮች ለክፍሉ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል አለማድረግ፣

 በተቋም ውስጥ ሊፈጸም የሚችል ሙስናን የመከታተል ኃላፊነት የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ብቻ አድርጎ
ማየት፣
 በአንዳንድ ተቋማት የሥነምግባር መከታተያ ክፍልን የማኔጅመንት ኮሚቴ አባል እንዲሆን አለማድረግ፣

 የሥነምግባር መከታተያ ክፍል አደረጃጀት የተሟላ አለመሆን፣

 ከሥራ ጋር በተያያዘ በሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ላይ የሚደርሱ አስተዳደራዊ በደሎችን በወቅቱ


ተከታትሎ መቀልበስ አለመቻል፣
 በአንዳንድ ተቋማት በደንብ ቁጥር 144/2000 መሰረት የኦዲት ግኝት ለሥነምግባር መከታተያ ክፍል በግልባጭ
እንዲደርስ አለማድረግ፣
 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን አቅም ለመገንባት የሚስችል ተከታታይነት ያለው የአቅም ማጎልበቻ
ስልጠና አለመሰጠቱ፣
 ኮሚሽኑ በበቂ ሁኔታ ክትትልና ድጋፍ አለማድረጉ ለስራው ቁርጠኛ አለመሆን፣
 የተቋማት የሥራ ኃላፊዎች በሚመሩት ተቋም ውስጥ የሙስና ወንጀል እንዳይከሰት በመከላከል ረገድ
የአንበሳውን ድርሻ እንዲይዙ መደበኛ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በኮሚሽኑ በኩል ያልተመቻቸ ከመሆኑም
በተጨማሪ ግልጽ የሆነ የተጠያቂነት ሥርዓት አለመዘርጋቱ፣
 የተቋማት ኃላፊዎች ስለ ተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና መከላከል እስትራቴጂ ያላቸው ግንዛቤ ዝቅተኛ መሆንና
ለመተግበር ቁርጠኝነት ማነስ፤
 ተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና መከላከል እስትራቴጂ ዕቅዱ ዝግጅትና አተገባባርን በተመለከተ ወጥ የሆነ
የቁጥጥርና የክትትል ሥርዓት በኮሚሽኑ አለመዘርጋት የሚሉና መሰል ሃሳቦች ይገኙበታል፡፡
4
ኮሚሽኑም ከሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ጋር በጋራ በመሆን በተያዘው በጀት ዓመት ለማከናወን የተያዙ ዕቅዶችን
ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር እንቅፋት ሊፈጥሩ በሚችሉ መሠረታዊ ችግሮችን መቅረፍ በሚያስችል መልኩ ይህን
አጠቃላይ የዕቅድ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
4. የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የ 2013 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ

4.1 የኢትዮጵያ ራዕይ፣ የኮሚሽኑ ራዕይ፣ የኮሚሽኑ ተልዕኮ፣ ዕሴቶች


የኢትዮጵያ ራዕይ
 በ 2022 ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ
የኮሚሽኑ ተልዕኮ
 ጠንካራ እና ኃላፊነቱን በብቃት ሊወጣ የሚችል ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር፣ ሙስናን ለመከላከል
የሚያስችል አመለካከትና ግንዛቤ ለመፍጠር የሥነምግባር አስተምህሮዎችን ማስተማር፣ በጥናት ላይ
የተመሠረተ የቅድመ ሙስና መከላከል ሥራዎችን መሥራት፣ በህጉ መሠረት የሀብት ማሳወቅና
ማስመዝገብ ሥራዎችን በብቃት መፈፀም እና ከሌሎች የባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት
ውጤታማነትን ማረጋገጥ፡፡
የኮሚሽኑ ራዕይ
 በ 2022 ሙስና ለኢትዮጵያ ብልጽግና እንቅፋት እንዳይሆን በማድረግ ከአፍሪካ ግንባር ቀደም ተቋም
ሆኖ መገኘት
የኮሚሽኑ እሴቶች
 የመልካም ሥነምግባር ተምሳሌት መሆን
 በጋራ መሥራት
 ለቀጣይ ለውጥ ዝግጁ መሆን
 የተግባር ሰው መሆን

5. ስትራቴጂክ ትኩረት መስኮችና ውጤቶች

ተ.ቁ የትኩረት መስክ ውጤት


1 ሙስና እና ብልሹ አሠራር መከላከል  በተቋማት ውስጥ የግልጽነትና ተጠያቂነት አሠራርን በማሳደግ
ሙስናና ብልሹ አሠራርን መቀነስ፣
2 የመልካም ሥነምግባር ግንባታ  በመልካም ሥነምግባር የታነፀና ሙስናን በጽናት የሚታገል
ህብረተሰብ ማብዛት፣
3 የላቀ የፀረ ሙስና ትብብርና አጋርነት  ያደገ የፀረ ሙስና ትግል ተሳትፎና ባለቤትነት፣
6. ስትራቴጂያዊ ግቦች

1. የህብረተሰብ ዕይታ
5
1.1. የህብረተሰብና የባለድርሻ አካላት ዕርካታ ማሳደግ
2. የበጀት ዕይታ

2.1. የበጀት አጠቃቀም ዉጤታማነትን ማሳደግ


3. የዉስጥ አሰራር ዕይታ

3.1. የሙስና መከላከል ውጤታማነትን ማሳደግ


3.2. የሙስና መከላከል አቅም ማሳደግ
3.3. የሥነምግባር ግንባታ አቅም ማሳደግ
3.4. በፀረ-ሙስና ትግሉ የተለያዩ አካላት ተሳትፎን ማሳደግ
3.5. የሥነምግባርና ሙስና ጥናትና ምርምር ማሳደግ
4. መማማርና ዕድገት ዕይታ

4.1. የሠው ሀብት ዉጤታማነትን ማሳደግ


4.2. የኢኮቴ አጠቃቀምና አቅርቦት ማሳደግ
4.3. የሥርዓተ ጾታ አካታችነትን ማሳደግ
4.4. የተቋም የመፈፀም አቅም ማሳደግ

7. ስትራቴጂያዊ ግቦች እና ዋና ዋና ተግባራት

1. የህብረተሰብ ዕርካታን በተመለከተ


 የዕርካታ ደረጃን ለማወቅ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ላይ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ መለካት፣
 የአመኔታን ደረጃን ለማወቅ በየአምስት ዓመት መጨረሻ ላይ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ መለካት፣
2. የበጀት አጠቃቀምን ማሳደግ በተመለከተ
 ለበጀት ዓመት የታቀዱት ተግባራት ከበጀት ጋር በማጣጣም ማከናወን፣
 ተጨማሪ የበጀት ምንጭ ማግኘት፣
 ጥቅም ላይ የዋለውን በጀት አዲት በማካሄድ ስለትክክለኛነቱ ማረጋገጫ ማግኘት፡፡

3. የሙስና መከላከል ውጤታማነት ማሳደግ በተመለከተ


 በተቋማት ውስጥ የሙስና ችግር እንዲቀንስ ማድረግ፣
 የህብረተሰብ አከላት የአመለካከት ለውጥ እንዲያመጡ ማድረግ
 የተማሪዎች ስነምግባር እንዲጎለብት ማድረግ፣
 ተባበሪና አጋር አካላት የፀረ ሙስና ትግል ባለቤት እንዲሆኑ ማድረግ፡፡
6
4. የሙስና መከላከል አቅምን ማሳደግ በተመለከተ

4.1.የሥነ ምግባር መከታተያና ሙስና መከላከል


 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን አሠራርና አደረጃጀትን ማሻሻል፣ ማጽደቅና ሥራ ላይ እንዲውል
ማድረግ፣
 ለተቋማት የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የመነሻ መሪ ዕቅድ በማዘጋጀት የዕቅድ ኦሬኔቴሽን
መስጠት፣ወደ ሥራ ማስገባት፣
 በየተቋሙ ያሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የራሳቸውን ዓመታዊ እቅድ እንዲያቅዱ ማድረግ፣
መታቀዱን ማረጋገጥ፣
 የሁሉም ተቋማት ሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን ዝርዝር መረጃ (ፕሮፋይል) መያዝ፣ ወቅታዊ
ማድረግ፣
 በሁሉም ተቋማት ያልተደራጁና የተጓደሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን በመለየት እንዲደራጁና
እንዲሟሉ ማድረግ
 ለሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ፣
 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ለተቋሞቻቸው አመራርና ሠራተኞች በሥነምግባር እና በሙስና
መከላከል ስትራቴጂዎች ላይ ሥልጠና እንዲሰጡ ማድረግ
 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች በተቋሞቻቸው ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ የሆኑ
አሠራሮች ላይ ጥናት በማካሄድ ማሻሻያዎች ተግባራዊ እንዲሆኑ እንዲያደርጉ ማድረግ
 በሁሉም ተቋማት የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች አማካይነት አመራርና ሠራተኞች ሀብትና
ንብረት እንዲያስመዘግቡና እንዲያሳድሱ ማድረግ፣
 በየወሩ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች አፈፃፀም ሪፖርት መቀበልና የጽሁፍ ግብረመልስ መስጠት፣
ደረጃ መመደብ፣
 በየ 6 ወር ከሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ጋር የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ የምክክር መድረኮችን
ማዘጋጀት፣
 በሁሉም ተቋም ያሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ፈፃሚ ባለሙያዎችን ሥልጠና እንዲሰጡ
ማድረግ፣
 ከሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትምህርት ተቋማት
ስለሚሠራው የተማሪዎች የሥነምግባር ግንባታ ሥራ ኮሚሽኑና ሁለቱ ሚኒስቴሮች የስምምነት
ሠነድ ተዘጋጅቶ እንዲፈራረሙ ማድረግ፣
 የመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲዎችን መረጃዎችን ማደራጀትና መያዝ፣

7
 በዪኒቨርስቲዎች ውስጥ የሥነምግባርና የፀረ ሙስና ክበባት እንዲደራጁና እንዲሟሉ በማድረግ ወደ
ሥራ ማስገባት፣
 ለዩንቨርስቲ ተማሪዎች የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ክበባት የአደረጃጀትና የአሠራር መመሪያና ማኑዋል
ማዘጋጀት፣
 የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች፣ ተቋማትና ዩኒቨርስቲዎች በመመሪያው
መሠረት መለየትና ዕውቅና እንዲሰጥ ማድረግ
 ክትትልና ድጋፍ ለሚደረግላቸው በሁሉም ተቋማት ውስጥ ያሉ የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ፈፃሚ
ባለሙያዎች ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ፣
 የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች፣ ተቋማት በመመሪያው መሠረት ሲለዩና
ዕውቅና እንዲሰጥ ሲደረግ የክትትልና ድጋፍ በማድረግ የተቋማት መረጃ መያዝ፤

8. የኮሚሽኑን ግብና ዋና ዋና ተግባራትን መሠረት በማድረግ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ቀጣይ የዕቅድ
አቅጣጫዎች

 በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በጸደቀ የሰው ኃይል አደረጃጀት መሠረት የክፍሉ የሰው ኃይል እንዲሟላ
ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ማቅረብ መከታተልና ማስተግበር፣
 በሁሉም ተቋማት ውስጥ ተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስትራቴጂ ተግባራዊ እንዲሆን
ማድረግ፣
 በኮሚሽኑ የተዘጋጀን የመነሻ መሪ ዕቅድ መሠረት በማድረግ በሁሉም ተቋማት የሚገኙ የሥነምግባር
መከታተያ ክፍሎች የራሳቸውን ዕቅድ ያዘጋጃሉ ወይም ይከልሳሉ፣
 ለሥነምግባር መከታተያ ክፍል የተሰጠን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያስፈልግ ተግባር
ተኮር የአቅም ማጎልበቻ የሥልጠና ፍላጎትን በወቅቱ ለኮሚሽኑ ማሳወቅ፣
 በኮሚሽኑ በሚዘጋጅ ተግባር ተኮር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና የሚመለከተው ባለሙያ እንዲሳተፍ
ማድረግ እና ስልጠናው በባለሙያው ላይ ያመጣውን ለውጥ በተቋሙ የአፈፃፀም ሪፖርት ውስጥ
በማካተት ለኮሚሽኑ ማሳወቅ፣
 በሥነምግባር እና በሙስና መከላከል ስትራቴጂዎች ላይ ለተቋሞቻቸው አመራርና ሠራተኞች
ሥልጠና መስጠት፣
 ለተቋማት አመራርና ሠራተኞች በሥነምግባር ደንብ ወይም ኮድ ላይ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣
ተግባራዊነቱን መከታተል፣
 ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ የሆኑ አሠራሮችን በመለየት ጥናት ማካሄድ እና በጥናት የተለዩ
የአሠራር ክፍተቶችን ለመቅረፍ የሚሰጡ የመፍትሄ ሃሳቦች ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ፣

8
 የመጀመሪያ ምዝገባ፣ የእድሳት ምዝገባና የአገልግሎት ማቋረጥ ምዝገባ የሚመለከታቸው የተቋሙ
ሠራተኞች ምን ያህል እንደሆኑ በመለየት ለኮሚሽኑ ማሳወቅ፣
 ሁሉንም የተቋሙን አመራርና ሠራተኞች ሀብትና ንብረት መመዝገብ፣ ከተመዘገቡ ሁለት ዓመት
የሞላቸውን ሀብት አስመዝጋቢ ሠራተኞች እንዲያሳድሱ ማድረግ እንዲሁም የአገልግሎት ማቋረጥ
ምዝገባ ማካሄድ፤
 ለፌደራል ሥነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ወርሀዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ወር በገባ እስከ ሦስተኛ ቀን
ድረስ በጽሁፍ ተዘጋጅቶና በተቋሙ የበላይ አመራር ተፈርሞ እንዲቀርብ ማድረግ፣
 በወራዊ አፈፃፀም ሪፖርቶች ላይ በኮሚሽኑ የሚሰጥ ግብረ መልስን መሠረት በማድረግ ቀጣይ
አሠራሮች እንዲስተካከሉ ማድረግና የተከናወኑ ሥራዎችን የሚያሳዩ መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅቶ
መያዝ፣
 በኮሚሽኑ በየ 6 ወር በሚዘጋጅ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የተሞክሮና ልምድ ልውውጥ
የምክክር መድረክ በንቃት መሳተፍ እንዲሁም ለሌሎች ተቋማት በተሞክሮነት ሊተላለፉ የሚችሉ
አሠራሮችን በአግባቡ ቀምሮ መያዝ፣
 በኮሚሽኑ የተዘጋጀን የተማሪዎች የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ክበባት የአደረጃጀትና የአሠራር መመሪያ
መሠረት በማድረግ በዪኒቨርስቲዎች ውስጥ የተማሪዎች የሥነምግባርና የፀረ ሙስና ክበባት
እንዲደራጁና እንዲሟሉ በማድረግ ወደ ሥራ ማስገባት፣ (ከዩኒቨርሲቲ የመጡ የሥነምግባር
መከታተያ ክፍሎችን ብቻ የሚመለከት ይሆናል)፣

 ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ውስጥ የተለያዩ የመልካም ሥነ ምግባር
አስፈላጊነትን እና የሙስና አስከፊነትን የሚያስገነዝቡ መርሀ ግብሮችን ማዘጋጀትና ማካሄድ፡፡

 ጥቆማዎችና ማጣራትና ለሚመለከተዉ ህግ አስፈጻሚ ተቋም እንዲደርሱ የማድረግ፣

 የተማሪዎች የተሞክሮና ልምድ ልዉዉጥ መድረክ የማዘጋጀት፣

 ሙስና በመከላከልና መልካም ሥነምግባር በማስረጽ የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ አካላትን እዉቅና
እንዲያገኙ ማድረግ

9. የክትትልና ድጋፍ አግባብ

 በእለት ከለት ሥራዎች ለሚቀርቡ የድጋፍ ጥያቄዎች አመቺ በሆነ አግባብ የማማከርና
የመደገፍ ሠራ በተቀናጀ መልኩ ማከናወን
 ወርሃዊ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት የማሰባሰብና የጽሁፍ ግብረመልስ ሥርአት ይኖራል
 በአካል ጉብኝት በማድረግ የተገኙ ተሞክሮዎች ለሌሎች ማስተላለፍ፣
9
 በጋራ መድረክ በተቀመጠው ቀጣይ አቅጣጫ መሰረት ተግባራዊ ስለመሆኑ ክትትልና
ድጋፍ ይደረጋል፣
 በተቀናጀ የሙስና መከላከል ስትራቴጂና/ሥነምግባር ግንባታ ሥራ ላይ የመፈጸም አቅም
ማጎልበቻ ሥልጠና መስጠት፣
 በሙስና መከላከል ስትራቴጂዎች ላይ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና መስጠት፣
 የልምድ ልዉዉጥ መድረክ የማመቻቸትና ማስተባበር

10. የሪፖርት ስርዓት

 የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች በየወሩ የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለፌዴራል


የሥነምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ይልካሉ፣
 በየወሩ ከሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የተሰበሰበውን የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በማንባብ የጽሁፍ ግብረመልስ ይሰጣል፣
 በዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መሰረት በኮሚሽኑ የአፈፃፀም ደረጃ ይሰጣል፡፡

11. የ 2013 በጀት ዓመት ዕቅድ ትግበራ መርሀ ግብር

የክንውን ጊዜ በሩብ ዓመት

1 ኛ ሩብ 2 ኛ ሩብ 3 ኛ ሩብ 4 ኛ ሩብ ምርመራ
ተ ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት
መለኪያ

ዒላማ

. የሚከናወኑ ተግባራት

በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በጸደቀ የሰው ኃይል አደረጃጀት መሠረት የክፍሉ


የሰው ኃይል እንዲሟላ ለሚመለከተው አካል ጥያቄ ማቅረብ መከታተልና
ማስተግበር፣

በኮሚሽኑ በሚዘጋጅ ተግባር ተኮር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና


የሚመለከተው ባለሙያ እንዲሳተፍ ማድረግ እና ስልጠናው በባለሙያው
ላይ ያመጣውን ለውጥ በተቋሙ የአፈፃፀም ሪፖርት ውስጥ በማካተት
ለኮሚሽኑ ማሳወቅ፣

ተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስትራቴጂ ዕቅድ እንዲዘጋጅ ማድረግ

በተቋማዊ የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስትራቴጂ ላይ በየደረጃው ለሚገኙ


የተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ሥልጠና መስጠት፣

10
የክንውን ጊዜ በሩብ ዓመት

1 ኛ ሩብ 2 ኛ ሩብ 3 ኛ ሩብ 4 ኛ ሩብ ምርመራ
ተ ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት

መለኪያ

ዒላማ
. የሚከናወኑ ተግባራት

የአመራርና ሠራተኞች የሥነምግባር ደንብ ወይም ኮድ ማዘጋጀት

ለተቋሙ አመራርና ሠራተኞች በሥነምግባር ደንብ ወይም ኮድ ላይ ግንዛቤ


ማስጨበጥ፣

የሥነምግባር ደንብ ወይም ኮድ ተግባራዊነትን መከታተል፣

ለሙስና እና ብልሹ አሠራር ተጋላጭ የሆኑ አሠራሮችን በመለየት ጥናት


ማካሄድ

በጥናት የተለዩ የአሠራር ክፍተቶችን ለመቅረፍ የሚሰጡ የመፍትሄ ሃሳቦች


ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረግ፣

የመጀመሪያ ምዝገባ፣ የእድሳት ምዝገባና የአገልግሎት ማቋረጥ ምዝገባ


የሚመለከታቸው የተቋሙ ሠራተኞች ምን ያህል እንደሆኑ በመለየት
ለኮሚሽኑ ማሳወቅ፣

ሁሉንም የተቋሙን አመራርና ሠራተኞች ሀብትና ንብረት መመዝገብ፣

ጥቆማዎችና ማጣራትና ለሚመለከተዉ ህግ አስፈጻሚ ተቋም እንዲደርሱ


የማድረግ፣

የተማሪዎች የተሞክሮና ልምድ ልዉዉጥ መድረክ የማዘጋጀት፣

ከተመዘገቡ ሁለት ዓመት የሞላቸውን ሀብት አስመዝጋቢ ሠራተኞች


እንዲያሳድሱ ማድረግ እንዲሁም የአገልግሎት ማቋረጥ ምዝገባ ማካሄድ፤

ለፌደራል ሥነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ወርሀዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ወር


በገባ እስከ ሦስተኛ ቀን ድረስ በጽሁፍ ተዘጋጅቶና በተቋሙ የበላይ አመራር
ተፈርሞ እንዲቀርብ ማድረግ፣

በወራዊ አፈፃፀም ሪፖርቶች ላይ በኮሚሽኑ የሚሰጥ ግብረ መልስን


መሠረት በማድረግ ቀጣይ አሠራሮች እንዲስተካከሉ ማድረግና የተከናወኑ
ሥራዎችን የሚያሳዩ መረጃዎችን በአግባቡ አደራጅቶ መያዝ፣

በኮሚሽኑ በየ 6 ወር በሚዘጋጅ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች የተሞክሮና


ልምድ ልውውጥ የምክክር መድረክ በንቃት መሳተፍ እንዲሁም ለሌሎች
ተቋማት በተሞክሮነት ሊተላለፉ የሚችሉ አሠራሮችን በአግባቡ ቀምሮ
መያዝ፣

በኮሚሽኑ የተዘጋጀን የተማሪዎች የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ክበባት


የአደረጃጀትና የአሠራር መመሪያ መሠረት በማድረግ በዪኒቨርስቲዎች
ውስጥ የተማሪዎች የሥነምግባርና የፀረ ሙስና ክበባት እንዲደራጁና
እንዲሟሉ በማድረግ ወደ ሥራ ማስገባት፣ (ከዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ የመጡ

11
የክንውን ጊዜ በሩብ ዓመት

1 ኛ ሩብ 2 ኛ ሩብ 3 ኛ ሩብ 4 ኛ ሩብ ምርመራ
ተ ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት

መለኪያ

ዒላማ
. የሚከናወኑ ተግባራት

የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎችን ብቻ የሚመለከት ይሆናል)፣

ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ


ውስጥ የተለያዩ የመልካም ሥነ ምግባር አስፈላጊነትን እና የሙስና
አስከፊነትን የሚያስገነዝቡ መርሀ ግብሮችን ማዘጋጀትና ማካሄድ

በተቋም ደረጃ ሙስናን በመከላከልና መልካም ሥነምግባርን በማስረጽ


የተሻለ እንቅስቃሴ ስላደረጉ አካላት የሚያሳይ መረጃ በአግባቡ አደራጅቶ
መያዝ

በተቋም ደረጃ ሙስናን በመከላከልና መልካም ሥነምግባርን በማስረጽ


የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ አካላትን እዉቅና እንዲያገኙ ማድረግ

12. ማጠቃለያ

ኮሚሽኑ ለ2013 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ የማዘጋጀትና ዕቅዱንም መተግበር በሚያስችል መልኩ እራሱን
በአዲስ መልክ አደራጅቷል፡፡ ይህን ዕቅድ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች
ያላቸውን አቅም ሙሉ ለሙሉ አሟጦ መጠቀም የማይተካ ሚና ይኖረዋል፡፡ ስለሆነም በተለያዩ ተቋማት
የሚገኙ የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች በኮሚሽኑ ከተዘጋጀው መሪ ዕቅድ ጋር የተናበበ የራሳቸውን
ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ዕቅድ እንዲያዘጋጁ ይህ መሪ ዕቅድ ተዘጋጅቷል፡፡

አባሪ
የዕቅድና የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቅጽ
ቅጽ- 1
የሚከናወኑ ተግባራት ዕቅድ ማቅረቢያ ቅጽ
ዕቅዱ የሚሸፍነዉ ጊዜ ከ--------------------- እስከ--------------------
የክንውን ጊዜ በሩብ ዓመት
ተቋማዊ የተቀናጀ 1 ኛ ሩብ 2 ኛ ሩብ 3 ኛ ሩብ 4 ኛ ሩብ ምርመራ
ተ ዓመት ዓመት ዓመት ዓመት
መለኪያ

የሙስና መከላከል
ዒላማ

. የሚከናወኑ ዝርዝር ተግባራት


ስትራቴጂ ዕቅድ
ሐምሌ
ነሐሴ
መስከረም
ጥቅምት
ህዳር
ታህሳስ
ጥር
የካቲት
መጋቢት
ሚያዚያ
ግንቦት
ሰኔ


ተግባራት

12
ዕቅዱን ያዘጋጀው የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ዳይሬክተር / ባለሙያ
ስም-------------------
ፊርማ--------------
ቀን--------------

ቅጽ -2
የሥነምግባር መከታተያ ክፍሎች ወርሃዊ የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ
ሪፖርቱ የሚሸፍነዉ ጊዜ ከ--------------------- እስከ--------------------

የአፈፃፀም ሪፖርት
ተቋማዊ የተቀናጀ
የሙስና መከላከል
ተ.ቁ ያጋጠመ
ስትራቴጂ ዕቅድ
ዋና ዋና / ዝርዝር ችግርና
ተግባራት መለኪያ ዒላማ ክንውን ንጽጽር
ተግባራት የተወሰደ
መፍትሄ

የአፈፃፀም ሪፖርቱን ያዘጋጀው የሥነምግባር መከታተያ ክፍል ዳይሬክተር / ባለሙያ


ስም-------------------
ፊርማ--------------
ቀን--------------

13

You might also like