Professional Documents
Culture Documents
(የመጨረሻ ረቂቅ)
ሰኔ 2009 ዓ.ም
አዲስ አበባ
መ ግ ቢ ያ
ተቋማት የዕለት ከዕለት ስራቸውን ለማከናወን ከሚገለገሉባቸው የስራ አመራር ዘዴዎች
አንዱ ስብሰባ ነው፡፡ ስብሰባ አዳዲስና የተለያዩ ሀሳቦችን ለማመንጨት፣ ወሳኝ
መረጃዎችን በተገቢው ሁኔታ ለማስተላለፍ፣ ለችግሮች መፍትሄ ለመሻት፣ ጠቃሚ
ውሳኔዎችን ለመወሰን እና በአጠቃላይ በአንድ ሰው ጥረት ውጤት የማያስገኙ ጉዳዮችን
ሁለትና ከዚያም በላይ በመሆን ውጤታማ አድርጎ ለመከወን የሚያስችል ቁልፍ መሳሪያ
ነው፡፡
በመሆኑም የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር 916/2008
በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት ይህን በጥናት የተደገፈ እና ዓለም አቀፍ
ተሞክሮዎችን ያካተተ የፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት አገራዊ የስብሰባ መመሪያና ዝርዝር
የአፈጻጸም ማንዋል አዘጋጅቷል፡፡
1
ዝርዝር የአፈጻጸም ማንዋል የያዘ ሲሆን የስብሰባ መሰረታዊ ህጎች፣ ውጤታማ የስብሰባ
አፈጻጸምን በቅድመ ስብሰባ፣ በስብሰባ ወቅት እና በድህረ ስብሰባ በመክፈል የተዘረዘረ
ሲሆን የመጨረሻው ክፍል አራት የመመሪያውን አጠቃቀም የተመለከተ ነው፡፡
2
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
2. ትርጓሜ
2.9. የስብሰባ መሰረታዊ ህጎች ማለት በስብሰባ ወቅት የታደሙ የስብሰባ መሪና
ተሳታፊዎች ውይይት በሚያደርጉበት ወቅት ሊያስታውሷቸውና
ሊተገብሯቸው የሚገቡ የውይይት ህጎች ማለት ነው፡፡
2.10. አጀንዳ ማለት ቀደም ብለው የተዘጋጁና በስብሰባ ወቅት በቅደም ተከተል
ለውይይት የሚቀርቡ ዝርዝር የውይይት አርዕስት ማለት ነው፡፡
4
2.12. የስብሰባ መሪ ማለት ስብሰባዎችን በኃላፊነት ለመምራት የተሰየመ
ማንኛውም ግለሰብ ማለት ነው፡፡
2.18. የአብላጫ ድምጽ ማለት በአንድ ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ ውሳኔ ለመወሰን
አባላት የውሳኔ ምርጫቸው ተቆጥሮ አብዛኛውን ድምጽ ያገኘው ሀሳብ
ተቀባይነት የሚያገኝበት ነው፡፡
5
ለመወሰን፣ በተለያዩ ጉዳዮች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ወሳኝ መረጃዎችን
ለማስተላለፍና ለመሰል ጉዳዮች በጋራ ተገናኝተው የሚመክሩበት እጅግ ጠቃሚና
አስፈላጊ መሳሪያ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ በልማታዊና ዲሞክራሲያዊ መንግስት
አስተሳሰብ እንደሚመራ ልማታዊ አገር በዋና ዋና የልማት አጀንዳዎች ላይ ከሕዝብ
ጋር እየመከርን፣ የጋራ መግባባትና የባላቤትነት ስሜት እያዳበርን በመሄድ
ላስመዘገብነው ተከታታይ እድገት ስብሰባ እጅግ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
6
እንቅስቃሴ ውስጥ እየተጫወተ ስላለው ወሳኝ ሚናና አስፈላጊነት በቂ የተግባቦት ስራ
አመራሩ አለመስራቱ እንደ ችግር ይጠቀሳል፡፡
በሌላ በኩል የፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት ስብሰባን ለታሰበለት አላማ በማዋል ከስብሰባ
የሚገኘውን ውጤት በተቋማቱ ማረጋገጥና መጠቀም እንዳይችሉ በተለይ በአመራሩና
በሰራተኛው የሚንጸባረቁ ከስብሰባ ጋር የተገኛኙ አሉታዊ አመለካከቶች እንቅፋት
7
ሆነውባቸዋል፡፡ የተወሰነው የፐብሊክ ሰርቪሱ ማህበረሰብ በስብሰባ ውስጥ ትኩረት
ለመሳብ መናገርን የዕድገትና የሹመት ማግኚያ መንገድ አድርጎ ማሰብ፣ ስብሰባ እንደ
መጨረሻ ውጤት መቁጠርና መኩራራት፣ ለሁሉም ችግሮች ስብሰባን እንደ መፍትሄ
መውሰድ፣ አስረዝሞና የፈለጉትን መናገርና ማሰማት የዲሞክራሲያዊነት መገለጫ
አድርጎ ማየት፣ ፐብሊክ ሰርቪሱ በንግግር እንጂ በሌሎች የመግባቢያ መንገዶች
ማለትም በኢሜል፣ በአጫጭር መልዕክቶችና በጽሁፍ ለመነጋገር ገና ነው (Oral
Society) ብሎ በመደምደም በቴክኖሎጂ ዙሪያ አቅምን ለመገንባትና ከስብሰባ ጋር
የተገኛኙ ዘመናዊ አካሄዶችን ለመከተል ካለመፈለግ ጋር የተያያዙ የተዛቡ
አመለካከቶች በየተቋማቱ ስብሰባዎች እንዲበዙና እንዲራዘሙ እንዲሁም የሀብት
ብክነትና የተገልጋይ መጉላላት እንዲያስከትሉ አድርጓል፡፡
8
የተገልጋይ መጉላላቶችና የሀብት ብክነቶች የተጠያቂነት ውሱንነት በመኖሩ ምክንያት
በሰበብ አስባቡ ስብሰባ ሲያበዙ ይታያሉ፡፡
4. የመመሪያው አስፈላጊነት
በመሆኑም በፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት ከላይ በነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳ ከውጤታማ ስብሰባ
ስራ አመራር ጋር ተያይዘው የተገለጹ ችግሮች ከመሰረቱ በመቅረፍና ስብሰባን
በሳይንሳዊ መንገድ በማስተዳደር በየደረጃው የሚደረጉ የተለያዩ ስብሰባዎችን
ውጤታማና ቀልጣፋ በማድረግ ከስብሰባ የሚገኘውን ጥቅም ማግኘት እንዲችሉ
ለማድረግ አንድ ወጥ የሆነ የፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት ውጤታማ የስብሰባ መመሪያና
ዝርዝር የአፈጻጸም ማንዋል ማዘጋጀት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
5. የፆታ አገላለጽ
9
6. የመመሪያው ዓላማ
7. የመመሪያው ግቦች
10
8. የመመሪያው መርሆዎች
የውጤታማ ስብሰባ ባህልን በፐብሊክ ሰርቪሱ ውስጥ ከማስረጽ አኳያ ተቋማት በዚህ
መመሪያና ዝርዝር የአፈጻጸም ማንዋል መሪነት ስብሰባዎችን በሚያከናውኑበት ወቅት
ስብሰባው የሚከተሉትን መሰረታዊ መርሆዎች መሰረት ያደረገ ይሆናል፡-
8.5. ተጠያቂነት፡-
ስብሰባን ለታለመለት አላማ ከማዋልና ውጤታማ ከማድረግ አኳያ
በስብሰባ ምክንት በሚፈጡሩ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፣
11
አላስፈላጊ የሀብት ብክነት እና የተገልጋይ መጉላላት ጋር በተያያዘ
አመራሩና ፈጻሚውን ተጠያቂነት ባረጋገጠ መልኩ የሚከናወን ይሆናል፡፡
8.6. ስለተሳታፊዎች፡-
9. የተፈፃሚነት ወሰን
12
ክፍል ሁለት
የስብሰባ አፈፃፀም
13
10.7. ማንኛውም አይነት ስብሰባ የተቋማትን ጊዜ እና ሌሎች ሀብቶችን በማያባክንና
ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ብቻ መከናወን ይኖርበታል፤
10.9. ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮችን በተመለከተ በጋራ መግባባት ወይም በአብላጫ ድምጽ
ውሳኔ ማሳለፍ ይገባል።
10.11. በፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት በሚደረግ ማንኛውም ስብሰባ የተነሳ ለሚፈጠር የኪራይ
ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፣ አላስፈላጊ የሀብት ብክነት፣ የተገልጋይ መጉላላት
እና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ችግሮች አመራሩ፣ ፈጻሚውና ሌሎች
የሚመለከታቸው አካላት በተቋማት አሰራርና በህግ መሰረት ተጠያቂ ይሆናሉ፡፡
14
ክፍል ሶስት
ዝርዝር የስብሰባ አፈፃፀም ማንዋል
15
12. የውጤታማና ቀልጣፋ ስብሰባ አካሄድ
ስብሰባን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ ቀጥሎ በንዑስ ርዕስ 12.1፣ 12.2 እና 12.3
ስር የተዘረዘሩትን በቅድመ ስብሰባ፣ በስብሰባ ወቅትና በድህረ ስብሰባ መደረግ
የሚገባቸውን ጉዳዮች በሚገባ መረዳትና በትክክልና ሙሉ ለሙሉ መተግበራቸውን
ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡
12.1. በቅድመ ስብሰባ
12.1.1.የስብሰባውን አላማ ማስቀመጥ፡- ስብሰባው ያስፈለገበትን ዓላማ በግልጽ
ማስቀመጥ
12.1.2. አጀንዳ መቅረጽ፡- ወቅታዊ የሆኑ ለውይይት መቅረብ የሚገባቸውን
አርዕስት አስቀድሞ ማዘጋጀት ሲሆን አጀንዳው የሚከተሉትን ያካትታል።
o የስብሰባውን አላማ
o በቅደም ተከተል የውይይቱን አርዕስት
o ከመወያያ አርዕስቱ የሚጠበቅ ውጤት (መረጃ ማስተላለፍ፣
ግልጽነት መፍጠር፣ መግባባት ላይ መድረስ፣ ውሳኔ ማሳለፍ፣ ችግር
መፍታት)
o ስለ አጀንዳው ግብረ መልስ መቀበልና ማስተካከያ ማድረግ
(እዝል አንድን ይመልከቱ፡-የአጀንዳ መቅረጫ ናሙና ቅጽ)
12.1.3. ለውይይት ጊዜ መመደብ፡- እንደየ አጀንዳው ክብደት በቂ የጊዜ ግምት
መመደብ
12.1.4. የስብሰባ ጊዜ፣ ቦታና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶችን ማዘጋጀት፡- ስብሰባው
የሚካሄድበትን ምቹ ጊዜና ቦታ እንዲሁም ለስብሰባው አስፈላጊ የሆኑ
ግብዓቶችን አስቀድሞ ማመቻቸት
12.1.5. ተሳታፊዎችን መምረጥ፡- ከመደበኛ አባላት ውጪ የሚያስፈልጉ
ተሳታፊዎች ከስብሰባው አላማ ጋር ባላቸው ግንኙነትና ለስብሰባው አጀንዳ
በሚያበረክቱት አስተዋጽዖ ብቻ ሊመረጡና ሊጋበዙ ይገባል፡፡
12.1.6. ጥሪ ማስተላለፍ፡-
16
- ምቹ ዘዴ (በቃል፣ በማስታወሻ፣ በደብዳቤ፣ በማስታወቂያ ሰሌዳ፣
በኢሜል፣ በስልክ፣ በመልዕክት) በመምረጥ ስብሰባው
ከሚካሄድበት ከ2-3 ቀናት ቀደም ብሎ ጥሪ ማስተላለፍ እና
- በዚህ ወቅት የውይይቱን አጀንዳ ማስታወቅ እንዲሁም እንዲነበቡ
የሚፈለጉ ተጨማሪ ሰነዶችን (ካሉ) ማያያዝና ማሰራጨት
ይገባል፡፡
12.1.7. በቂ ዝግጅት ማድረግ፡- በስብሰባው አጀንዳ ዙሪያ አስፈላጊ የሆኑ
መረጃዎችን አደራጅቶና የተላኩ ሰነዶችን (ካሉ) አንብቦ ግብዓት መስጠት
በሚያስችል መጠን ተዘጋጅቶ መምጣት፡፡
12.2. በስብሰባ ወቅት
12.1.1. ተሳታፊዎችን መመዝገብ፡- የተገኙ ተሳታፊዎችን ፊርማ መውሰድና
ያልተገኙና ፍቃድ የተሰጣቸውን መመዝገብ።
12.1.2. ምላተ ጉባኤ መሟላቱን ማረጋገጥ፡- ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ምላተ
ጉባኤ መሟላቱን ማረጋገጥ፡፡
12.1.3. ስብሰባውን መክፈት፡- የተሳታፊዎችን ስሜት በሚያነቃቃና መልካም
ድባብ በሚያላብስ ሁኔታ ስብሰባውን መጀመር
12.1.4. ያለፈውን ስብሰባ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ፡- ከዚህ ስብሰባ ቀደም ብሎ
የተደረገውን ስብሰባ ቃለ ጉባኤ አቅርቦ ማጽደቅ።
12.1.5. የስራ ሪፖርቶችን ማዳመጥ፡- በግለሰብና በቡድን ደረጃ ከዚህ ስብሰባ
ቀደምሲል በነበረው ስብሰባ ወቅት የተሰጡ ስራዎች (ካሉ) የደረሱበትን
ደረጃ ማዳመጥ።
12.1.6. የዕለቱን አጀንዳ ማጽደቅ፡-በይደር ለተላለፉ ቀሪ አጀንዳዎች ቅድሚያ
በመስጠት የዕለቱን አጀንዳዎች ማጽደቅ።
12.1.7. ቃለ ጉባኤ መመዝገብ፡- በስብሰባ ወቅት የተነሱ አንኳር ነጥቦች፣
የመጨረሻ ውሳኔዎች፣ የልዩነት ሀሳቦችንና የተግባራትን ክፍፍል በጠራ
መልክ በቃለ ጉባኤ መመዝገብ።
17
12.1.8. የስብሰባን መሰረታዊ ህጎች መከተል፡- በንዑስ ርዕስ አስር
የተዘረዘሩትን የስብሰባ መሰረታዊ ህጎች ተከትሎ ውይይቱን
መምራትና በውይይቱ መሳተፍ።
12.1.9. የተግባራት ክፍፍል፡- በቀጣይ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ
የሚከናወኑ ተግባራት (ካሉ) ተገቢውን ግለሰብ ወይም ቡድን የጊዜ
ገደብ በማስቀመጥ ጭምር በግልጽ መመደብ።
12.1.10. ስብሰባውን በአግባቡ መደምደም፡- የዕለቱን ስብሰባ ዋና ዋና
ነጥቦች ባጭሩ በመከለስ ስብሰባውን መደምደም።
12.1.11. ቀጣዩን የስብሰባ ቀን በጋራ መወሰን፡- የቀጣይ ስብሰባ ቀን፣ ሰዓትና
መነሻ አጀንዳ በጋራ መወሰን።
12.1.12. ማስታወቂያዎች፡- በመጨረሻም መተላለፍ የሚገባቸው ልዩ ልዩ
ማስታወቂያዎች ወይም መልዕክቶች (ካሉ) ማስተላለፍና ማሰናበት።
19
13.1.11. ውይይቱ አጀንዳው ላይ ብቻ ያተኮረ እንዲሆንና ሀሳቦች ያለአግባብ
እንዳይደጋገሙና እንዳይረዝሙ ማድረግ።
13.2. የተሳታፊዎች ሚና
13.2.1. አስቀድሞ የተላከውን የስብሰባ አጀንዳ ማንበብ እና
አስተያየት ካለ በጊዜ መስጠት።
13.2.2. በስብሰባው አጀንዳ ዙሪያ አስፈላጊ የሆኑ
መረጃዎችን አደራጅቶና ሰነዶችን (ካሉ) አንብቦ በስብሰባው
በሚጠበቀው ደረጃ መሳተፍ በሚያስችል መልኩ ተዘጋጅቶ መምጣት፡፡
13.2.3. ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ካጋጠመ ቀደም ብሎ ለሰብሳቢ
ወይም ለፀሐፊ ማሳወቅ።
13.2.4. በስብሰባው ላይ ያልተገኘ ተሳታፊ በስብሰባው የተወሰኑ
ጉዳዮችን ተግባራዊ የማድረግ ኃላፊነት አለበት።
13.2.5. ከስብሰባው ሰዓት አምስት ደቂቃ ያህል ቀደሞ በስብሰባ ቦታ
መገኘት።
20
13.2.6. በግልም ሆነ በቡድን እንዲከናወን የተሰጠ ተግባር ካለ
አጠናቆና የተደራጀ ሪፖርት ይዞ መቅረብ።
13.2.7. የስብሰባ መሰረታዊ ህጎችን ተግባራዊ ማድረግ።
13.2.8. የሌሎችንና የራስን ትኩረት ከሚያሳጡ አላስፈላጊ ተግባራት
(ከጎንዮሽ ወሬ፣ ገባ ወጣ ከማለት፣ ተንቀሳቃሽ ስልክና ሌሎች
ቴክኖሎጂዎችን ከመጠቀም) መቆጠብ።
13.2.9. በጋራ የተወሰኑ ጉዳዮችን በእምነትና በጠንካራ ስነ ስርዓት
ተቀብሎ መተግበር።
13.2.10. በስብሰባ ወቅት የተስተዋሉ ችግሮችን በዕለቱ ከተገኘ ተሳታፊ
ጋር በመወያየት በሚቀጥለው ስብሰባ የመፍትሄ ሀሳብ ይዞ
መቅረብ።
13.3. የፀሐፊ ሚና
13.3.1. ለተሳታፊዎች ጥሪ ማስተላለፍ፣ አጀንዳና የውይይት ሰነዶችን
ማሰራጨት እና ሌሎች በቅድመ ስብሰባ የተዘረዘሩ ተግባራትን
ከሰብሳቢው ጋር በመሆን ማከናወን።
13.3.2. የተገኙ ተሳታፊዎችንና ተጋባዥ እንግዶች ፊርማ መውሰድና
ያልተገኙና ፍቃድ የተሰጣቸውን መመዝገብ።
13.3.3. በስብሰባ ወቅት የተነሱ አንኳር ነጥቦች፣ የመጨረሻ ውሳኔዎች፣
የልዩነት ሀሳቦችንና የተግባራት ክፍፍልን በጠራ መልክ በቃለ
ጉባኤ መመዝገብ።
13.3.4. ከስብሰባ በኋላ ባሉት ከ2-3 ቀናት ውስጥ ተሟልቶ የተጻፈ
ረቂቅ ቃለ ጉባኤ ለእያንዳንዱ የስብሰባው ተሳታፊ
በማሰራጨት ተገቢውን ግብረ መልስና እርማት መቀበል፡፡
21
13.3.6. በዕለቱ በተገኙ ሁሉም ተሳታፊዎች ፊርማ መጽደቁ የተረጋገጠ
ቃለ ጉባኤና ሌሎች ከስብሰባው ጋር ተያያዥነት ያላቸውን
ሰነዶች በመዛግብትነት ማስቀመጥ፡፡
14.1. የቃለ ጉባኤ ቁጥር፣ ስብሰባው የተደረገበት ቀን፣ ሰዓት፣ ቦታ፣ የስብሰባው
አጀንዳ እና የተሳታፊዎች ስም ዝርዝር፣
14.2. በስብሰባ ወቅት የተነሱ አንኳር ነጥቦች፣ የመጨረሻ ውሳኔዎች፣ የልዩነት
ሀሳቦችና የተግባራት ክፍፍል በተነሱበት ትክክለኛ አግባብ፣
14.3. የመጨረሻ የልዩነት ሀሳብ ማስመዝገብ የፈለገ ተሳታፊ ካልኖረ በስተቀር
የሀሳብ ሰጪ ተሳታፊዎች ስም አይመዘገብም።
(እዝል ሁለትን ይመልከቱ፡- የቃለ ጉባኤ መመዝገቢያ ናሙና ቅጽ)
በዚህ ንዑስ ክፍል ውሳኔ ለመወሰን መከተል ከሚገቡ የውሳኔ አወሳሰን ዘዴዎች
መካከል በጋራ መግባባት እና በአብላጫ ድምጽ የውሳኔ አሰጣጥ በዝርዝር የቀረቡ
ሲሆን በውሳኔ አሰጣጥ ጊዜ እንደ ጉዳዩ ሁኔታ አንዱን በመምረጥ መወሰን
ይቻላል።
23
15.2.2. የተለያዩ የውሳኔ አማራጮችን አመዛዝኖ የሚጠቃለሉበትን ሁኔታ
ማመቻቸት።
15.2.3. ከጉዳዩ ጋር የተገናኙና ድምጽ ለመስጠት የሚረዱ ማንኛውንም መረጃ
ለተሳታፊዎች ግልጽ ማድረግ።
15.2.4. ተሳታፊዎች በጉዳዩ ዙሪያ ያላችውን ሀሳብ እንዲያካፍሉና ጥያቄ
እንዲጠይቁ እድል መስጠት።
15.2.5. የስብሰባው መሪ ወደ ድምጽ አሰጣጥ ስነ ስርዓት ከመኬዱ በፊት
ሁሉም ተሳታፊ ጉዳዩን በግልጽ መረዳቱን ማረጋገጥ ይኖርበታል።
15.2.6. ከተሰጠው የድምጽ ውጤት ሀምሳ በመቶ ሲደመር አንድ ድጋፍ
ያገኘ የውሳኔ ሀሳብ ተቀባይነት ይኖረዋል።
15.2.7. የተሰጠው የድምጽ ውጤት እኩል በሚሆንበት ጊዜ የስብሰባ መሪው
ድምጽ እንዲሰጥና የመሪውን ድጋፍ ያገኘው የውሳኔ ሀሳብ
ተቀባይነት እንዲያገኝ ይደረጋል።
24
16.1.4. በተመሳሳይ አጀንዳ ላይ በተለያየ ጊዜ ተመሳሳይ ኃላፊዎችና
ሰራተኞች የሚሳተፉበትን የስብሰባ ድግግሞሽ በቅንጅት በመስራት
ማስወገድ።
16.1.5. የስብሰባ አይነቶችን፣ ለውይይት መቅረብ የሚገባውን የአጀንዳ
አይነትና ሊፈጅ የሚገባውን ተገማች ጊዜ ለይቶ ማስቀመጥና
ተግባራዊ ማድረግ።
16.1.5.1. እለታዊ ግንኙነት፡-
- አላማው በየዕለቱ ጠዋት ጠዋት የቡድን አባላት በእለቱ
ስለሚያከናውኗቸው ዕለታዊ ተግባራት መረጃ መለዋወጥ
ነው።
- ከ 5 - 20 ደቂቃ በላይ መፍጀት የለበትም።
- መጠባበቅ አያስፈልግም።
- አባላት ስላልተሟሉ መሰረዝ የለበትም።
16.1.5.2. ሳምንታዊ ስብሰባ፡-
- አላማው ሳምንታዊ የስራ አፈፃፀምን እና የቀጣይ ሳምንት
ዕቅድን መገምገምና ከስራ ጋር የተያያዙ ያጋጠሙ ችግሮችን
መፍታት ነው፡፡
- ከ 1-2 ሰዓት በላይ መፍጀት አይጠበቅበትም።
- ስትራቴጂክ አጀንዳዎች ላይ መወያየት አይጠበቅም።
16.1.5.3. ወርሀዊ ስትራቴጂክ ስብሰባ
- አላማው በተቋሙ የረዥም ጊዜ ስኬት ላይ ተጽኖ ሊያሳድሩ
የሚችሉ ወሳኝ ጉዳዮችን በተመለከተ ውይይት ማድረግ ነው።
- ከ 2 - 4 ሰዓት በላይ መውሰድ አይጠበቅበትም።
- የአጀንዳውን ቁጥር አለማብዛት።
- በጥናት ላይ የተመሠረተ ሙሉ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ።
16.1.5.4. የሩብ ዓመት ስብሰባ
25
- ይህ ስብሰባ አጠቃላይ በሩብ አመቱ የተከናወኑ ተቋማዊ
ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸሞችን በተጨማሪም የተቋሙን
አጠቃላይ ከስራ ሂደቶችና ሰራተኞች ጋር የተገናኙ ቁልፍ
ጉዳዮችን ለመገምገም የሚውል ነው፡፡
- ከአንድ ቀን መብለጥ የለበትም። ለተገልጋዩ አስቀድሞ
መገለፅ አለበት።
16.1.5.5. የግማሽ ዓመት ስብሰባ
- ይህ ስብሰባ አጠቃላይ በግማሽ አመቱ የተከናወኑ ተቋማዊ
ስትራቴጂክ ዕቅድ አፈጻጸሞችን በተጨማሪም የተቋሙን
አጠቃላይ ከስራ ሂደቶችና ሰራተኞች ጋር የተገናኙ ቁልፍ
ጉዳዮችን ለመገምገም የሚውል ነው፡፡
- ከአንድ ቀን ተኩል በላይ መብለጥ የለበትም። ለተገልጋዩ
አስቀድሞ መገለፅ አለበት።
16.1.5.6. ዓመታዊ ስብሰባ
- ዓመታዊ ዕቅድና የእቅድ አፈጻጸም የሚገመገምበት ሲሆን፣
- ከ1 – 2 ቀናት መብለጥ የለበትም። ለተገልጋዩ አስቀድሞ
መገለፅ አለበት።
26
27
ክፍል አራት
መመሪያውን ስለ መጠቀም
17. ስልጠና
የፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት አመራርና ሰራተኛ በስብሰባ ዙሪያ ተከታታይነት
ያለው የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሊያገኙ ይገባል።
የሰው ሃብት ሥራ አመራር የሥራ ክፍሎች እና የተቋማት የውስጥ ኦዲት በዚህ መመሪያና
ማንዋል የተቀመጡ የአሰራር ሥርዓቶች በአግባቡ ተግባራዊ መሆናቸውን በመከታተል
ለተቋሙ የበላይ አመራርና የማኔጅመንት ኮሚቴ ሪፖርት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
28
21. መመሪያውን ስለማሻሻል
ከስብሰባ ጋር የተያያዙ ሌሎች ችግሮችና ክፍተቶች ሲስተዋሉና ችግሮቹን
መፍታት አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኝ የፐብሊክ ሰርቨስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር
ይህን መመሪያ ሊያሻሽለው ይችላል፡፡
አዲስ አበባ
29
እዝል 1፡ የስብሰባ አጀንዳ ቅጽ
እዝል 2፡ የስብሰባ ቃለ ጉባኤ ቅጽ
እዝል 3፡ የስብሰባ ውጤታማነት ዳሰሳ (Meeting Effectivness Assesment)
መጠይቅ
30