Professional Documents
Culture Documents
Abiye Tsome Hudade
Abiye Tsome Hudade
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር በራሱ ፈቃድ
በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጾመ። መጾሙ ግን ኃጢአት ሠርቶ ለስርየት፤ እሴት
ሽቶ ለበረከት አይደለም። ለምዕመናን አብነት ለመሆን ነው። አርባ ቀን መሆኑም ነቢያት አርባ ቀን
ጾመው ትንቢት የተናገሩለት እሱ መሆኑን ለማጠየቅ ነው። (ማቴ 4፥ 1-6)
ከሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ድረስ (መጋቢት 23, ቀን 2010 ዓም እስከ መጋቢት
30,ቀን 2010 ዓም/April 1-8, 2018) ያለው ሰባት ቀን ሰሙነ ሕማማት ይባላል።
በዚህ ሳምንት ውስጥ የጌታን መከራና ሞት የሚያስታውሱ ቅዱሳት መጽሐፍት ይነበባሉ። ስግደትም
በየተወሰነው ሰዓት ይሰገዳል። ልዩ ልዩ የፀሎት ስርዓትም ይካሄዳል። አዳም ከፈጣሪው ጋር ተጣልቶ
የኖረውን የመከራና የጨለማ ዘመን በማስታወስ መንበረ ታቦቱ በጥቁር መጐናጸፊያ ይሸፈናል።
ካህናቱም በዚሁ ሰሞን ለአገልግሎት የሚለብሱት ልብሰ ተክህኖም ጥቋቁር ነው። (ኢዩኤል 2፥21 ፤
ማቴ 21፥18 ፤ ሚክያስ 2፥ 3-13 ፤ኢሳያስ 50፥1 ፤ ሉቃ 13፥23 ፤ ዘፀዓት 19፥1 ፤ ኤርምያስ
17፥1 ፤ መዝ 41፥6)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
ከደብረ ገነት ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን