You are on page 1of 1

ቀን 28/05/2011 ዓ.

የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ

የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሰጪ ፡- አቶ አብዱልፈታ ናስር

አድራሻ ፡- አዳማ ከተማ ቀበሌ ኦዳ የቤት ቁጥር

የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተቀባይ ፡- አቶ አብዱልሰመድ ሰኢድ

አድራሻ ፡- አዳማ ከተማ ቀበሌ 04 የቤት ቁጥር 1170

ይህ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1772 መሠረት የተሰጠ ነው፡፡

በእኔ በአሁኑ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሰጪ እና በአሁኑ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ተቀባይ መካከል ሚያዚያ 25 ቀን 2010
ዓ.ም የትራንሳይክል ሽያጭ ውል ስምምነት የፈጸምን መሆናችን ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ንብረትነቱ የአሁኑ የጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ ሰጪ የሆነውን ትራንሳይክል ባጃጅ የሰሌዳ ቁጥር 1 - 11947 ኦሮ የሆነውን ለአሁኗ የጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ ተቀባይ በብር 90,000 (ዘጠና ሺህ ) ሸጬልዎት ከሽያጩም ገንዘብ ውስጥ በእለቱ የውል ሰነድ
ደረሰኝነት አማካኝነት ብር 80000 (ሰማኒያ ሺህ) ተቀብዬ ቀሪውን ብር 10000 (አስር ሺህ) የባጃጁን ንብረትነት ስም
በእርስዎ በአሁኗ የጽሁፍ ተቀባይዋ እስከ ሰኔ 25 ቀን 2010 ዓ.ም ድረስ ሲዛወር ልቀበልና ላዛውርልዎት መስማማታችን
ይታወቃል፡፡

ይን እንጂ እስከ ዛሬ ቀን ድረስ በስልክና በአካልም ያቀረብኩልዎት ጥሪ አክብረው ስም ለማዛወርና ቀሪውን ብር 10000
(አስር ሺህ) ሊከፍሉኝ ፍቃደኛ ሆነው አልተገኙም፡፡ ስለዚህ ከዛሬ ይህ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከደረስዎት ቀን አንስቶ
በሚታሰብ 8 ቀናት ውስጥ ቀርበው ስም እንዲያዛውሩና የሚፈለግብዎትንም ብር 10000 (አስር ሺህ) የማይከፍሉኝ
ከሆነ ጉዳዩን ለሚመለከተው ፍርድ ቤት አቅርቤ የዳኝነት ወጪ ፣ የጠበቃና የቀላጤ ልዩ ልዩ ወጪዎችን ጭምር
በማስከፈል መብቴን በህግ አግባብ ለማስፈፀም የምገደድ መሆኔን አበክሬ እየገለፅኩ ይህንን የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
የሰጠሁ መሆኔን አሳውቃለሁ፡፡

የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሰጪ ፊርማ

_________________________

You might also like