Professional Documents
Culture Documents
አመሠራረት _ታሪካዊ አመ
አመሠራረት _ታሪካዊ አመ
በኢትዮጵያ ዘመናዊ የመንገድ ትራንስፖርት አጀማመር በአፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ
መኪና በ 1899 ዓ.ም ወደ ሀገር ውስጥ መግባትና በ 1928-1933 ዓ.ም በጣሊያን ወረራ ወቅት ከነበረው
የመንገዶች መስፋፋት ጋር የተያያዘ ሲሆን ጣሊያኖች አስተዳደራቸውን ለማስፋፋት በተለይም ደግሞ
የመከላከያ ኃይላቸውን ለማጠናከር እንዲረዳቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ መንገዶችን በመስራትና
ተሽከርካሪዎችን በማስገባት የመንገድ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲጎለብት አድርገዋል፡፡
በ 1933 ዓ.ም የጣሊያን ወራሪ ኃይል ተሽንፎ ከመጣ በኋላ የወራሪው ንብረት የነበሩት ተሽከርካሪዎች
ተወርሰው ለኢትዮጵያውያንና ለውጪ ዜጎች እንዲሸጡ በመደረጉ ለኢትዮጵያውያንና ለውጪ ዜጎች
እንዲሸጡ በመደረጉ ለኢትዮጵያውያንና የውጪ ሀገር ባሀብቶች በትራንስፖርት ንግድ ውስጥ በስፋት
ለመሳተፍ ምቹ ሁኔታን የፈጠረላቸው ሲሆን ውድድሩን በአሸናፊነት ለመውጣት ባደረጉትም ፉክክርም
የትራንስፖርት አገልግሎቱ እድገት አሳይቶ እንደነበረ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ትራንስፖርትን በተመለከተ
በየወቅቱ የወጡ አዋጆችን መዳሰስ ስለትራንስፖርት አጀማመር የበለጠ ግንዛቤ ስለሚሰጥ እንደሚከተለው
በአጭሩ ቀርቧል፡፡
አዋጅ ቁጥር 11/1934፡- ይህ አዋጅ የመንገድ ትራንስፖርትን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ አዋጅ ሲሆን
ዋና ትኩረቱም ስለተሽከርካሪ ማፃፍ የወጣ አዋጅ ነው፡፡
በወቅቱ የነበሩት ማዘጋጃ ቤቶች ተሽከርካሪዎችን እየመዘገቡ (እየፃፉ) ዝርዝሩን ለአገር ግዛት ሚኒስቴር
የማቅረብ ግዴታ እንዳለባቸው አዋጁ ይገልፃል፡፡
አዋጅ ቁጥር 35/1935፡- ይህ ቀጥሎ የወጣው ሁለተኛ አዋጅ የየብስ ትራንስፖርት አዋጅ የሚባል ሲሆን ዋና
አስፈፃሚ አካል የሥራና መገናኛ ሚኒስቴር ነው፡፡ በወቅቱ ትራንስፖርትን ለመቆጣጠር ስድስት አባላት ያሉት
ቦርድ ተዋቅሮ ስራው ይካሄድ ነበር፡፡
በወቅቱ የሥራና መገናኛ ሚኒስቴር ይባል የነበረው መ/ቤት ከጣሊያን ወራሪ ኃይል የተረከባቸውን መጠነኛ
ተሽከርካሪዎችና የመለዋወጫ ዕቃዎች ከ 1935-1943 ዓ.ም ሲያስተዳድር ቆይቶ በ 1944 ዓ.ም በታህሳስ ወር
ለተቋቋመው አክሲዮን ማህበር አስረክቧል፡፡
ይህ አዋጅ የሚያካትታቸው ድንጋጌዎች፡-
በ 1960 ዓ.ም እንደገና በመንገዶች ላይ ጉዞንና ማመላለሻን (ትራንስፖርትን) ለመቆጣጠር አዋጅ ቁጥር 256
ወጥቶ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ በዚህ አዋጅ መሠረት
የሥራና የመገናኛ ሚኒስቴር በመንገዶች ላይ አጠቃላይ ጉዞን ለመከታተልና ለመቆጣጠር ስልጣን የነበረው
ሲሆን አስፈፃሚው አካል የመንገድ ትራንስፖርት አስተዳደር የሚባል መ/ቤት ነበር፡፡
ለንግድና የሕዝብ ማመላለሻ ማህበራትና ተሽከርካሪዎች ፈቃድ መስጠት የመሳሰሉትን ሥራዎች እስከ 1996
ዓ.ም ድረስ ሲያከናውን ነበር፡፡
በዚሁ ወቅትም የባለሞተርና ተሳቢ ተሽከርካሪ ምዝገባን፣ መንጃ ፈቃድን እና ትራፊክን የተመለከቱ ደንቦች
ወጥተው በሥራ ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡
በ 1966 ዓ.ም ከተደረገው የመንግሥት ለውጥ በኋላ የደርግ መንግሥት በ 1969 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 107/69
የመንገድ ትራንስፖርት አስተዳደርን የሚተካ የመንገድ ትራንስፖርት ባለሥልጣን መ/ቤት በአዋጅ ቁጥር ......
አቋቋመ፡፡ ይህ አዋጅ ከወጣ በኋላ፡-
በመሆኑም በወቅቱ የነበረው አሠራር የነፃ ገበያ አሠራርን የማያስተናግድ ከመሆኑም በላይ የእዝ ኢኮኖሚን
የሚያራምድ ስለነበረ የትራንስፖርቱ ኢንዱስትሪ እንዳይስፋፋና እንዲቀጭጭ አድርጎት ቆይቷል፡፡
ከደርግ መንግሥት ውድቀት በኋላ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት ዘርፉን በተሻለ
መልኩ ለማደራጀትና የተሟላ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት እንዲቻል የመንገድ ትራንስፖርት
ባለስልጣንን እንደገና ለማቋቋም አዋጅ ቁጥር 14/84 በማውጣት ቀድሞ የነበሩትን የተዛቡና ለእድገት አመቺ
ያልሆኑ መዋቅሮችንና አሰራሮችን በተስተካከለ መዋቅርና አሰራር እንዲተኩ ከማድረጉም በላይ ለዘርፉ
መጎልበት ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል፡፡
በኢህአዴግ የሚመራው መንግሥት በ 1983 ዓ.ም ስልጣን ከያዘ በኋላ በአዲሱ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መሰረት
በ 1984 ዓ.ም የመንገድ ትራንስፖርትን ለመቆጣጠር አዋጅ ቁጥር 14/84 የወጣ ሲሆን አስፈፃሚው አካልም
የመንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን ነበር፡፡
የአዋጁ ዓላማ፡-
ቀልጣፋና ኢኮኖሚያዊ የመንገድ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲኖርና በተመጣጠነ ሁኔታ እንዲዳረስ ማድረግ፣
የተሳፋሪው ሕዝብ ደህንነትና ምቾት እንዲሁም የሚጓጓዘው ጭነት በሚገባ መጠበቁንና የትራንስፖርት
አገልግሎት ሳይቋረጥ አስተማማኝ በሆነ ስርዓት ለተገልጋዩ ሕዝብ መድረሱን ማረጋገጥ ናቸው፡፡
በህዝብ የንግድ የመንገድ ማመላለሻ ሥራ ላይ የተሰማራ ሰው በግል ወይም በማህበር ተደራጅቶ መስራት
መቻሉንና የመሳሰሉትን ያካተተ ነበር፡፡
አዋጅ ቁጥር 14/84 ከሽግግሩ ወቅት ጀምሮ ለ 13 ዓመታት በስራ ላይ የቆየ ሲሆን የአሰራር ክፍተቶችን
ለመዝጋትና እንደገና ለማሻሻል እንዲሁም ለፌዴራል መንግሥት ተጠሪ የሆኑ ከተሞችን የመንገድ
ትራንስፖርት እንዲሁም የውሃና የባቡር ትራንስፖርትን ከፌዴራል መንግሥት ትራንስፖርት ጋር ማደራጀት
አስፈላጊ በመሆኑ ነባሩን አዋጅ ያሻሻለው አዋጅ ቁጥር 468/97 ሐምሌ 30 ቀን 1997 ዓ.ም ወጥቷል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 468/97 ትራንስፖርትን ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ አስፈፃሚ የትራንስፖርት ባለሥልጣን
መስሪያ ቤት በአዲስ መልክ ተቋቁሟል፡፡