You are on page 1of 36

በአምባሰል ወረዳ የመሬት

መንሸራተት አደጋ የዳሰሳ ጥናት


ጥናቱን ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎች
1. ደባልቄ አዱኛ ከአ/መ/ም/ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት
2. ይማም አህመድ ከውሃና ኢነርጅ መምሪያ
3. ሰዒድ ይመር ከመሬት መምሪያ
4. ግዛቸው ሸዋየ ከግብረና መምሪያ
5. መሃመድ ኑርየ ከአካባቢ ጥበቃ መምሪያ
6. አወል አደም ከቤቶች ልማት መምሪያ
7. እሸቱ ይማም ከጤና ጥበቃ መምሪያ

ታህሳስ 2015 ዓ.ም


ማውጫ
ሰንጠረዠ ማውጫ ii
ምስል ማውጫ iii
አጭር መግለጫ iv
1. መግቢያ 1
1.1. የችግሩ መገለጫ 1
1.2. የጥናቱ አስፈላጊነት /ጠቀሜታ/ 2
1.3. የጥናቱ ወሰን /ስፋት ወይም ሽፋን/ 2
1.4. የጥናቱ ዓላማና ግብ 2
1.4.1. የጥናቱ ዓላማ 2
1.4.2. የጥናቱ ግብ 2
2. የጥናቱ የአጠናን ዘዴ (Methods of Study) 3
2.1. የጥናቱ ቦታ /አካባቢ (Description of the study area) 3
2.2. የሕዝቡ አኗኗርና ማህበራዊ ሁኔታ 4
2.3. የእንስሳት ሀብት 4
2.4. የጥናቱ መረጃ አሰባሰብ ዘዴ 4
2.4.1. የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ 4
2.4.2. የሁለተኛ ደረጃ መረጃ 5
2.5. የመረጃ አተናተን ዘዴ (ስልት) 6
2.6. በጥናቱ ጥቅም ላይ የዋሉ ቁሳቁሶች 6
2.7. የጥናቱ እጥረቶች 6
3. የጥናት ውጤቶችና ማብራሪያዎቹ 7
3.1. አደጋው እንዴት ተከሰተ 7
3.2. ለመሬት መንሸራተት መነሻ መንስኤዎች ዳሰሳዎች 7
3.2.1. ስነ-ምህዳርን (Geology) ሁኔታ 7
3.2.2. የተከሰተው የመሬት መንሸራተት ዓይነት 8
3.2.3. የገፀ-ምድር እና የውሃ መውረጃ ሁኔታ 11
3.2.4. የእጽዋት ሽፋን 11
3.2.5. የአፈር ሁኔታ 11
3.2.6. የመሬት አጠቃቀምና የተፈጥሮ ሃብት ሁኔታ 11
3.3. የችግሩ መንሰኤ 13
3.3.1. ውጫዊ ምክንያቶች 13
3.3.2. ውሳጣዊ ምክንያቶች 13
3.4. በመሬት መንሸራተቱ የደረሱ ጉዳቶች 13
3.4.1. በመሰረት ልማት ላይ የደረሰ 14
3.4.2. በቤቶች ላይ የደረሰ ጉዳት 14
3.4.3. በመሬት ላይ የደረሰ አደጋ 16
3.4.4. በአትክልትና በእፅዋት ላይ የደረሰ አደጋ 17
3.5. በአደጋው ዙሪያ አሁን እየተሰሩ ስራዎች 17
3.6. ትምህርትና ጤና በተመለከተ 17
4. ማጠቃለያና ምክረ-ሐሳብ 18
4.1. ማጠቃሊያ 18
4.2. ምክረ ሃሳብ 19
ዋቢ መጻሐፍት 20
ዕዝል 21

i
ሰንጠረዠ ማውጫ

ሰሠንጠረዠ 1፡ በሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት 13


ሰሠንጠረዠ 2፡ ለአደጋ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍል መረጃ 16

ii
ምስል ማውጫ

ምስል 1፡ ጥናቱ የሚደረግበት ቦታ ካርታ 3


ምስል 2፡ የጥናት ቡድኑ ከማህበረሰቡ እና ከወካይ ቡድኖች ውይይቶች ሲያደረጉ 5
ምስል 3፡በሶስት ቀን ልዩነት የተፈጠረ የመሬት መንሸራተት 7
ምስል 4፡ የመሬት ስብራትን አመለካች የሚገልፅ ∕Indication of fault∕ 8

ምስል 5፡ የመሬት መስመጥ ∕Normql fault∕ 9

ምስል 6፡ ከአንድ አቅጣጫ ብቻ የመሬት መስመጥ ∕Reverse fault∕ 9

ምስል 7፡ የመሬት መምታታት ∕Strike-slip fault∕ 9

ምስል 8፡ የመሬት መሰንጠቅ እና የመሬት መንሸራተት የጀመረበት ቦታ ∕Starting point of fault and Land slide∕ 10
ምስል 9፡ የመሬት ስብራት ያቆመበት ቦታ/Fault ending point/ 10
ምስል 10፡ አስጊ የውሃ ተቋም እና መኖሪያ ቤት ∕Peril water point and house∕ 10
ምስል 11፡ ከሃያ ዓመት በፊት የተፈጠረ የመሬት መንሸራተት 12
ምስል 12፡ የተጉዱ መሰረተ ልማቶች በከፊል 14
ምስል 13፡ የወደሙ ቤቶች በከፊል 15
ምስል 14፡ በከፍተኛ ስጋት ላይ ያሉ ቤቶች በከፊል 15
ምስል 15፡ የተጉዳ መሬትና በስጋት ላይ ያለ መሬት መጠን 16

iii
አጭር መግለጫ

የአምባሰል ወረዳ በአማራ ክልላዊ መንግስት በደ/ወሎ መስተዳደር ዞን ስር ከሚገኙት የምስራቅ አማራ ወረዳዎች ወስጥ አንዱ
ነው፡፡ አምባሰል ወረዳ በጥቅሉ የመሬቱ አቀማመጥ ተራራማና ወጣ ገባ የበዛበት፣ የአፈር ለምነቱም ዝቅተኛ የሆነ፣ የአፈር
መሸርሸር ያለበት፣ በጎርፍ የሚጠቃ ወረዳ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ ለመሬት መንሸራተት ዋነኛ መንስኤ ነው ተብሎ ይወሰዳል፡፡
በአካባቢውም የመሬት መንሸራተት አደጋ አልፎ አልፎ የተከሰተ ሲሆን አሁንም በ01 ሊሞ ቀበሌ የተፈጠረው መሬት መንሸራተት
አደጋ ያደረሰው ጉዳት እጅግ የከፋ በቀላልና ባጭር ጊዜ ሊካካስ የሚችል አይደለም፡፡ አደገጋው በስነልቦናም ሆነ በኢኮኖሚ ላይ
ደረስው እንድሁም የደቀነው ስጋት ከፍተኛ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ መሆኑን መረዳት ይቻለል፡፡ ስለዚህም በደረሳው አደጋ ስነ
ልቦናዊም ሳናነሳ በቅሳዊ ጉዳት ብቻ 35782500 ብር ሙሉ ለሙሉ አሳጥቷል፡፡ 81 ወንድ 86 ሴት 166 ማህበረሰብን ከመኖሪያ
ቦታቸው ሙሉ በሙሉ እንድፈናቀሉ አድርጓል፡፡ ለ137 አባዋራ ለ178 እመዋራ በድምሩ ለ315 ህብረተሰብ ለስጋት አጋልጧል፡፡
መሰረተ ልማቶችን አውደሟል፤108 ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንድስተጓጎሉ ሁነዋል፡፡ የችግሩ ጥልቅት ለአካባቢው
ህብረተሰብ ብቻ ሳይሆን ለውጫሌ ከተማም ቢሆን አስጊ በመሆኑ ከተማውን መታደግ የሚቻለው ለችግሩ ትኩረት ተሰጥቶ ዘላቄ
መፍትሄ በማበጀት መሆኑን ያመለክታል፡፡ በመጨረሻም መሬትን በአግባቡ አለመያዛችንና ከመሸከም አቅም በላይ አላግባብ የምን
ጠቀምባት ከሆነ በቃኝ ብላ አራግፋ አንደምትጥለን ማሳያ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ስለዚህ ይህ አደጋ ብቸኛና ተተኪ የማይገኝለትን
የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን መሬትን ተንከባክበንና ትኩረት ሰጥተን ካለይዝ በቀላሉ ማጣት አንደምንችል የሚያሳይ የደወል ጥሪ
መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ ስለዚህ አደገው የተከሰተባቸው ማህበረሰቦች ሆኑ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን አደጋ
ከመድረሱ በፊት በአፋጣኝ ቦታውን ለቀው እንድ ወጡና በጊዜያውይ መጠለያ የሚሰፍሩበት መንገድ ቢመቻች፡፡ በዘለቄተው
ሊሰፍሩበት የሚችሉ ቦታ በማዘጋጀት በእጃቸው ያለ ሃብትና ንብረት ሳይጠፋ በቋሜነት እንድቋቋሙ ቢደረግ፡፡ አካባቢው ጥለቅ
ጥናት ቢደረግበትና አካባቢው ከሰውና ከእንሰሳት ንኪኪ ተጠብቆ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራዎች ቢሰሩበት እንድሁም ወደ ቋሚ ደን
ልማት ቢሸጋገር፡፡ በጥቅሉ የተደረገው የዳሰሳ ጥናት ችግሩ ፈጣን ምላሽ ከልተሰጠው ችግሩ ቀጣይንት እንደሚኖረውና ተጨማሪ
ጉዳት እንደሚያደረስ ያመልክታል፡፡

iv
1. መግቢያ

የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት በአገራችን ከሚከሰቱ አደጋዎች አንዱ የመሬት መንሸራተት


ነው፡፡ የአደጋው ክስተት በተወሰኑ አካባቢዎች ሊሆን እንደሚችል ቢታመንም በአደጋው በአማካኝ
በየአመቱ አንድ ሺህ ሰዎች ተጎጂ እንደሚሆኑና ሶስት ሚሊዬን ዶላር የሚገመት ግንባታዎች ላይ
ጉዳት ያደርሳል (የአለም ባንክ 2019) ፡፡ የመሬት መንሸራተት አደጋ ክስተት ክብደቱ ከቦታ ቦታ
እንደሚለያይ ይታመናል፡፡ የመካከለኛው የአገራችን ክፍል የሚፈጠረው አደጋ ከፍተኛ እንደሆነ
ይታመናል፡፡ ይህ ችግር ከትግራይ ክልል ምስራቃዊ ድንበር ወደ አማራ ክልል የተዘረጋና እና
እስከ ታችኛው የስምጥ ሽለቆ ምዕራባዊ ክፍል የሚደርስ ነው፡፡

የመሬት መንሸራተት አደጋ በበርካታ የአማራ ክልል ቦታዎች እንደሚከሰትና ህብረተሰብን


እንደሚጎዳ ይታወቃል፡፡ ከነዚህም ውስጥ ሀብሩ፣ አምባሰል፣ ጉባላፍቶ፣ ቃሉ፣ ዳውንት፣ ደላንታ፣
ወረባቦ፣ ከታበር፣ ደሴዙሪያ እና ወግዲ ወረዳዎች አደጋው የሚከሰትባቸውና ተጎጂ ወረዳዎች
እንደሆኑ ይገለፃል (ጌትነት እና ፍላጎት፣ 2021) ፡፡

1.1. የችግሩ መገለጫ

አባሰል ወረዳ አባዛሃኛው የመሬት ክፍል ገደላማ በመሆኑ የጉርፍና የመሬት መንሸራተት ችግሮች
ከሚስተዋልባቸው አካባቢዎች አንዱ ሲሆን ለነዚህ አደጋዎች እንዲጋለጥ መነሻ ከሆኑት
ምክንያቶች ውስጥ ዋነኛው ተስማሚ ያልሆነ የመሬት አጠቃቀምና አያያዝ መኖር ነው፡፡ ይህም
በመሆኑ የመሬት የአፈር መሸርሸርና የመሬት መንሸራተት አደጋ በአካባቢው ሊሞ (01) ቀበሌ ልዩ
ስሙ ግራር ገንዳ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የመሬት መንሸራተት ተከስቷል፡፡ በዚህም መሰረት
የችግሩ አሳሳቢነት መገለጫ የሆኑት ጉዳቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
1. አካባቢው ከሰውም ሆነ ከእንስሳት ንክኪ ሙሉ በሙሉ የተጠበቀ ባለመሆኑ የመሬት
መረበሽ ወይም እረፍት ማጣት መኖሩ
2. ህጋዊም ሆነ ህገወጥ ግንባታ በቦታው ላይ እየተካሄደ በመሆኑ መሬት ከሚሸከመው በላይ
በመሆኑ አሁንም እንቅስቃሴው ያልቆመ በመሆኑ
3. የአካባቢው ስሪት አፈር ቀላል እና በውኃ በቀላሉ የሚሸረሸር በመሆን

1
1.2. የጥናቱ አስፈላጊነት /ጠቀሜታ/

ይህ ጥናት በዋናነት የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኝልናል፡፡


 የችግሩን መነሻና ወደፊት ሊያደርሰው የሚችል ጉዳትን ያመላክትል
 ለችግሩ የአጭር ጊዜ እና የረጀም ጊዜ መፍተሔ ያስቀምጣል
 ችግሩ በትትክክል ያደረሰው ጉዳት ለይቶ ለሚመለከተው አካል ያቀርባል

1.3. የጥናቱ ወሰን /ስፋት ወይም ሽፋን/

ጥናቱ የተካሄደው በ 01 ቀበሌ ልዩ ስሙ ግራር ገንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተከሰተው


የመሬት መንሸራተት መነሻ መንስኤውን የመለየት፣ ያደረሰው የጉዳት መጠን የመለየት፣ ወደፊት
ሊያደርሰው የሚችል ጉዳት ማመላከት፣ የመሬት መንሸራተቱ በዘላቂነት የሚያቆምበትን እና
በተለይም ለውጫሌ ከተማ የመሬት መንሸራተቱ ስጋት የማሆንብትን እና ሊወሰዱ የሚገባቸውን
አማራጭ የመፍትሔ ሀሳቦች ማስቀመጥ ያካትታል፡፡

1.4. የጥናቱ ዓላማና ግብ

1.4.1. የጥናቱ ዓላማ

 አደገው የተከሰተባቸው ማህበረሰቦች ሆኑ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ


ክፍሎችንየአጭር እና የረጅም ጊዜ መፍትሔ ማስቀመጥ
 በዘላቂነት የመሬት መንሸራተቱ አደጋ ስጋት እንዳይሆን የአጭር እና የረጅም ጊዜ
መፍትሔ ማስቀመጥ

1.4.2. የጥናቱ ግብ

 በደረሰው የመሬት መንሽራተት አደጋ ያደረሰው የጉዳት መጠን መለየት እና ለሚመለከተው

አካል ማሳወቅ እንድሁም አደጋው ስጋት እንዳይሆን የአጭር እና የረጅም ጊዜ መፍትሔ


ማስቀመጥ

2
2. የጥናቱ የአጠናን ዘዴ (Methods of Study)

2.1. የጥናቱ ቦታ /አካባቢ (Description of the study area)

የአምባሰል ወረዳ በአማራ ክልላዊ መንግስት በደ/ወሎ መስተዳደር ዞን ስር ከሚገኙት የምስራቅ


አማራ ወረዳዎች አንዷ ስትሆን በሰሜን ሀብሩ እና የጉባ ላፍቶ ወረዳ ፣በደቡብ ተሁለደሬ እና
ኩታበር በምስራቅ ተሁለደሬ በከፊል እና የሀብሩ ወረዳ እንዲሁም በምእራብ ደላንታ እና ተንታ
ወረዳዎች የሚያዋስኑት ሲሆን የወረዳው ዋና ከተማ ውጫሌ ስትሆን ይች ከተማ ከአዲስ አበባ
461 ኪ/ሜ ከክልሉ ርእሰ ከተማ ባህር ዳር በ440 ኪ/ሜ እንዲሁም ከዞኑ ዋና ከተማ ደሴ በ60
ኪ/ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች ፡፡ ጆኦግራፊካሊይ ከ390 36" 30' እስከ 390 36" 30' ምስራቅ እና 110
30" 30' እስከ 110 30" 30' ሰሜን ውስጥ ይገኛል::

ምስል 1፡ ጥናቱ የሚደረግበት ቦታ ካርታ

የወረዳው አየር ንብረት ወይና ደጋ ሲሆን የህዝቡ ኑሮ የተመሰረተው በግብርና ስራ ሲሆን በዚህ
መስክ ከተለያዩ ሰብሎች በተጨማሪ አትክልትና ፍራፍሬ ይመረትባታል፡፡ ወረዳዉ በ25 ቀበሌ
የሚለማ መሬት 14360ሄ/ር እና 91217 ሄ/ር የቆዳ ስፍት ያላት ሲሆን ወረዳዉ ከባህል ወለል
በላይ 1450—3600 ሜትር ከፍታ አለዉ የመሬት አቀማመጡ 92.5% ተራራማና ወጣ ገባ 7.5%
ሜዳማ የሆነ ተፈጥሮአዊ የመሬት አቀማመጥ አለው፡፡ እንደ ዳንኤል (1997) ከሆነ የአየር ፅባይ
ሁኔታ በረሃ (<800 ሜትር)፣ ቆላ (800-1500 ሜትር)፣ ወይና ደጋ (1500-2300 ሜትር)፣ ደጋ
(2300-3300 ሜትር) እና ውርጭ (>3300 ሜትር) ተብሎ ሊከፈል ይችላል፡፡ በዚህም መሰረት
የመሬት መንሸራተት የተፈጠረበት ቦታ በወይና ደጋ የአየር ፅባይ ሁኔታ ውስጥ ይገኛል

3
ምክንያቱም ቦታው ከ1786-1884 ከፍታ ውስጥ ሰለሚገኝ፡፡ አደጋው ከደረሰበት ቦታ ቅርብ የሆነው
የሜትሮሎጂ ጣቢያ የውጫሌ ሜትሮሎጂ ጣቢያ ነው ፡፡ ከጣቢያው ከተገኘው መረጃ (2000-2005
ዓ.ም) እንደሚያሳየው የአካባቢው አማካኝ የዝናብ መጠን 922 ሚሊሜትር እንደሆነና ዝቅተኛው
የሙቀት መጠን 90C ከፍተኛው ደግሞ 330C መሆኑን ያመለክታል (2000-2009 ዓ.ም)፡፡

2.2. የሕዝቡ አኗኗርና ማህበራዊ ሁኔታ

በቀበሌው ወንድ 1080 ሴት 283 ድምድ 1303 የሚገመት ህዝብ የሚገኝ ሲሆን የመሬት
መንሸራት በደረሰበት ጎጥ ወንድ 176 ሴት 231 ድምር 407 ህዝብ የኖራል፡፡ ዋነኛ
መተዳደሪያውም የግብርና ሥራ ነው፡፡ በእርሻ ስራው በዝናብ ውሃ በመታገዝ ስንዴ፣ ጤፍ፣
በቆሎ፣ ዘንጋዳና ማሽላ ያመርታሉ፡፡ በግብርና ስራው የሰብል ምርት ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
የፍራፍሬ ዛፎች እንደ ብረቱካን፣ ማንጎ፣ ግራቪሊያ፣ አቡካዶ ወዘተ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም
ከአትክልት ደግሞ ጎመን በብዛት ይመረታል፡፡ ከዚሁ ጋር አነስተኛ ቁጥር ያላቸውን የቤት እንስሳት
በማርባት ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡

2.3. የእንስሳት ሀብት

የመሬት መንሸራተት በደረሰበት ቀበሌ በጎጧ ውስጥ የሚገኝ የእንስሳት ሃብት የቀንድ ከብት 66
በግና ፍየል 132፣ ዶሮ 220፣ የንብ ቀፎ 6 ይገኛል፡፡

2.4. የጥናቱ መረጃ አሰባሰብ ዘዴ

2.4.1. የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ

ቦታዎችን በአካል በመስክ ተገኝቶ የምልከታ ስራ መስራት /Observation/ አንዱ ሲሆን በዚህም
ስለአካባቢው የደረሰው የመሬቱ መንሸራተት በአካባቢው ላይ እያደረሰ ያለውን ችግር ደረጃ እና
ስፋት ለማስተዋል ተችሏል፡፡ ሌላው በዚህም የቅኝት ወቅት በየመሬት አጠቃቀሙ ሊሰሩ የሚችሉ
የአካባቢ ጥበቃ፣ የተፈጥሮ ኃብትና የመሰረተ ልማት ሥራዎች በምን ያህል መጠን እንደተሰሩ

4
ጭምር፣ ምን ያህል ጉዳት እንደደርሰም ለማየት ተችሏል፡፡ ደረሱ ጉዳቶችን በምስልም ሆነ
በተንቀሳቃሽ ምስል ለመያዝ ተችሏል፡፡

ልቅ ጥያቄዎችን /Open-ended Questions/ በማዘጋጀት መረጃን በቀጥታ መሰብሰብ፤ ከላይኛውና

ከታችኛው ተሰሚነት ካላቸው የማህበረሰብ ተወካዮች /key informants/ ጋር ጥያቄዎችን በማንሳት


ውይይት ተደርጓል፡፡ ከወረዳው አመራር፣ ቀበሌው አመራር፣ ከብረተሰብ እና ከህብረተሰብ ተወካይ
ከሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎች የቡድን ተኮር ውይይት /Focus group discussion/ ተካሂዷል፡፡
በአጠቃላይ የመሬት መንሸራተቱ በአካባቢው ላይ እያድረሰ ያለውንና ያስከተለው ተፅዕኖ ምን ያህል
የከፋና ያልከፋ ስለመሆኑ ለመገንዘብና የችግሩ አሳሳቢነት ደረጃ በይበልጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የወደሙ ሃብቶችን ቆጠራና ልኬታ ስራዎችን የተካሄድ ሲሆን ጠቅላላ በመሬት መንሸራተቱ
የተጎዳውን የመሬት መጠን /ስፋት/ ለማወቅ መረጃውን በጂ.ፒ.ኤስ በመውሰድና በጂ.አይ.ኤስ አርክ ማፕ
ሶፍትዌር በመጠቀም ስፋቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ምስል 2፡ የጥናት ቡድኑ ከማህበረሰቡ እና ከወካይ ቡድኖች ውይይቶች ሲያደረጉ

2.4.2. የሁለተኛ ደረጃ መረጃ

እንዴ 2ኛ ደረጃ መረጃነት በመሬት መንሸራተት ዙሪያ የተጠኑ ጥናቶችንና ሶሽዮ-ኢኮኖሚያዊ


መረጃዎችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡ ይህም ስለጥናቱ መነሻ ሀሳብና የመግቢያ ጽሁፎችን ለመፃፍ
ረድቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ማለትም ከወረዳው ግብርና ጽ/ቤት፣
ቤቶች ልማት ጽ/ቤት፣ ከመሬት ጽ/ቤት ጋር መረጃ በመውሰድ የጥናት ሥራውን ማጠናከር
ተችሏል፡፡

5
2.5. የመረጃ አተናተን ዘዴ (ስልት)

ለመረጃ አተናተን ሥራችን የተጠቀምንበት መንገድ የማብራሪያ ትንተና ስልትን (Descriptive


analysis) ሲሆን በዚህ መንገድ የተሳተፉ ሰዎችን የቡድን ውይይትና በአካል ተዳሶ ከታዩት
መረጃን መሰረት በማድረግ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዳውን የመሬት መጠን፣
የአትክልትና የቤቶችን ጉዳት ለመተንተን ጥረት ተደርጓል፡፡

2.6. በጥናቱ ጥቅም ላይ የዋሉ ቁሳቁሶች

ጥናቱ በሚካሄድበት ወቅት ጥቅም ላይ የዋሉ ቁሳቁሶች ጂ.ፒ.ኤስ፣ ሞባይል፣ ሜትር፣ ኮፒተርና
ጅ.አይ.ኤስ ሶፍትዌር ናቸው፡፡

2.7. የጥናቱ እጥረቶች

ለጥናቱ የተሰጠው ጊዜ በማነሱ ምክንያት እያንዳንዳቸውን ችግሮች /የናሙና መጠንን መጨመርና


ከሌሎች ሐገሮች የሚገኙ ልምዶችንና መረጃዎችን በስፋት መጠቀም ይቻል ነበር/ በዝርዝር
ማጥናት ያልተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በርካታ ናሙናዎችን ወስዶ ለመተንተን አልተቻለም፡፡
በተጨማሪም ትክክላኛ መረጃ የማገኘት ችግሮች ነበሩ፡፡ በአጠቃላይ ጥናቱን ለማከናወን ረጅም ጊዜ
የሚያስፈልገውና በጥልቀት ሊሰራ የሚገባው ቢሆንም ባለው የበጀትና የሐብት አቅም ውስንነት
ምክንያት አነስተኛ የሰው ኃይል በመያዝና በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በማተኮር ከተለያዩ ሴክተር
መሰሪያቤቶች የተውጣጡ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች ቡድን በማዋቀር በአጭር ጊዜ ውስጥ
መነሻ ሊሆን የሚችል ሥራ ተሰርቷል፡፡

6
3. የጥናት ውጤቶችና ማብራሪያዎቹ

3.1. አደጋው እንዴትና መቼ ተከሰተ

አምባሰል ወረዳ በጥቅሉ የመሬቱ አቀማመጥ ተራራማና ወጣ ገባ የበዛበት፣ የአፈር ለምነቱም


ዝቅተኛ የሆነ፣ የአፈር መሸርሸር ያለበት፣ በጎርፍ የሚጠቃ ወረዳ ነው፡፡ በአምባሰል ወረዳ በ01
ቀበሌ ሊሞ በውጫሌ ከተማ አቅራቢያ ግራር ገንዳ በሚባል አካባቢ (ጎጥ) ጥቅምት 17/2015 ዓ.ም
በስፋት የመሬት መንሸራተት ቢከሰትም የተከሰተውም የመሬት መንሸራተት አደጋ የዚሁ አካል
ያደርገዋል፡፡ የመሬት መሸራተቱ በፍጥናትና በአንድ ጊዜ የተከሰተ ሳይሆን በየዕለቱ የሚጨምር
መሆኑን በተደረጉ ምልከታዎች መረዳት ተችሏል፡፡ ችግሩ ከቀን ወደ ቀን እየሰፋ በመንጣቱ
የአዳጋው ተጋላጭነትና ተፈናቀቃዮች ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ ችግሩን አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡

ምስል 3፡ በሶስት ቀን ልዩነት የተፈጠረ የመሬት መንሸራተት

3.2. ለመሬት መንሸራተት መነሻ መንስኤዎች ዳሰሳዎች

3.2.1. ስነ-ምህዳርን (Geology) ሁኔታ

የከርሰ ምድር ውሃ (ground water table approach to the surface) በዚያ ቦታ ላይ መኖሩ
አንዱ ለፎልት መፈጠር እንዴ ምክንያት ይጠቀሳለ፡፡ በዚህም በቡድን ውይይት የተገኘው መረጃ
በዚሁ አካባቢ የተለያዩ ምንጮች የገፀ መድረ ውኃ ያሉና እንዴነበሩ እንደሁም እንዴተደፈኑ
ያሳያል፡፡ ሌላኛው ምክንያት ደግሞ የውስጠኛው የመሬት ክፍል የአፈሩ ወይም የአለቱ ጥንካሬ
ከመሬት ስበት ጋር ሲነፃፀፃ አናሳ ሆኖ ከተገኘ የመሬት መሰበርና መታጠፍ (fault or fould)

7
ሊፈጠር ይችላል፡፡ በዚህም ምክንያት የመሬት መንሸራተት (Land slide) ይፈጠራል፡፡ በተደረገው
የዳሰሳ ጥናትና በቡድን ውይይቱ በተገኘው መረጃ መሰረት መሬት መንሸራተት የገጠመው አካባቢ
ከፍተኛ ወጣገባ የሆነ፣ ሸለቆ የበዛበት፣ ከፍተኛ ተዳፋትነት ያለው የመሬት ክፍል በመሆኑ ይህ
ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ (Earthquick) በአካባቢው ለሰከንድ ወይም ለማይክሮ ሰከንድ
በአጋጣሚ ከተፈጠረ ወጣ ገባ የመሬት ክፍል (undulated land surface) ይህንን አደጋ ተቋቁሞ
የመቆየት እድል የለውም፡፡ በዚህም ምክንያት የመሬት መሰበር ወይም የመሬት መታጠፍ (fault
or fould) አደጋ ስለሚያጋጥም ለመሬት መንሸራተት እንደ ምክንያት ይጠቀሳል፡፡ በዚህ የተነሳ
በአካባቢው ያሉ የሰው ልጆች፤ እፅዋቶች፤ መጠለያ እና መሰረተ-ልማቶች በከፊል እና ሙሉ
በሙሉ የመጥፋት አደጋ ይከሰታል፡፡ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድም ችግሩ እንድባባስ በማድረግ
ለሞት እና ለንብረት መውደም አደጋ ያጋልጣል፡፡

3.2.2. የተከሰተው የመሬት መንሸራተት ዓይነት

መሬት መንሸራተት በተለያዩ ዓይነቶች ሊከፈል ይችላል፡፡ ለምሳሌ፡- በቁስ አይነቱ በስድስት
ሊከፈል ይችላል፡፡ ይኽውም መውደቅ፣ መገንደስ፣ የመሬት መምታታት ፣ መውረድ፣ መዘርጋት
እንዲሁም ሁለትና ከዚያ በላይ ዓይነቶችን ሊይዝ ይችላል፡፡ በዚህም መሰረት በአምባሰል ወረዳ
ሊሙ ቀበሌ የተከሰቱውን የመሬት መንሸራተት በሚከተለው ምስል ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡

ምስል 4፡ የመሬት ስብራትን አመለካች የሚገልፅ ∕Indication of fault∕

8
ምስል 5፡ የመሬት መስመጥ ∕Normql fault∕

ምስል 6፡ ከአንድ አቅጣጫ ብቻ የመሬት መስመጥ ∕Reverse fault∕

ምስል 7፡ የመሬት መምታታት ∕Strike-slip fault∕

9
ምስል 8፡ የመሬት መሰንጠቅ እና የመሬት መንሸራተት የጀመረበት ቦታ ∕Starting point of fault and Land slide∕

ምስል 9፡ የመሬት ስብራት ያቆመበት ቦታ/Fault ending point/

ምስል 10፡ አስጊ የውሃ ተቋም እና መኖሪያ ቤት ∕Peril water point and house∕

10
3.2.3. የገፀ-ምድር እና የውሃ መውረጃ ሁኔታ

የመሬት መንሸራተት አደጋው የተከሰተበት ቦታ የአፋር ሸለቆ ዳርቻና ቁልቁለት አካባቢ


ነው፡፡ቦታው የሚሌ ተፋሰስ ምዕራባዊ ዳርቻና የቁልቁለት ክፍል ነው፡፡ የቦታው ከፍታ ከፍተኛው
1884 ሜትር ሲሆን ዝቅተኛው ደግሞ 1786 ሜትር ነው፡፡ ይህ ማለት የከፍታ ልዩነቱ 98
ሜትር እንደሆነ ያሳያል፡፡ የአካባቢው መሬት አቀማመጥ አባጣ ጎርባጣ የበዛበት ነው፡፡ የመሬቱ
አቀማመጥ ሁኔታው 22.3% ቀስ በቀስ እያጋደለ የሚሄድ፣ 49.7% የሚጋድል እና 28.1% ደግሞ
በመሀከለኛ ዥው ያለ ተዳፋት ነው፡፡ በሌላ በኩል የአካባቢው የውሃ መውረጃ ሁኔታ በትይዩ
የተዘረጉ የዛፍ ቅርጽ ያለው ነው፡፡

3.2.4. የእጽዋት ሽፋን

በአካባቢው የተለያዩ የአገርና የውጭ ዝርያ ዛፎች በጓሮ ዙሪያ ለምተው ይገኛሉ፡፡ ከአገር በቀል
ዝርያዎች የአባሻ ግራር፣ ወይራና ዋንዛ በብዛት ሲገኙ ደደሆና ሌሎች ቋጥቋጦች በሸለቆ ቦታዎች
ይገኛሉ፡፡ ከውጭ ዝርያዎች ደግሞ የተለያዩ የባህር ዛፍ ዝሪያዎችና የፍራፍሬ ዛፎች እንደ
ብረቱካን፣ ማንጎ፣ ግራቪሊያ፣ አቡካዶ ወዘተ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ማሽላ፣ በቆሎ፣ ጤፍ እና
ዘንጋዳ በአካባቢው ይመረታል፡፡ ከአትክልት ደግሞ ጎመን በብዛት ይመረታል፡፡

3.2.5. የአፈር ሁኔታ

የመንሸራተት አደጋ የደረሰበት አካባቢ አፈር ደለል ሆኖ የፍርስራሽ ክምር፣ ቀር አፈርና የደለል
አፈር አይነት ነው ፡፡ የአፈር ቅንጣት ሁኔታው ደግሞ ዋልካማ (100%) ነው፡፡

3.2.6. የመሬት አጠቃቀምና የተፈጥሮ ሃብት ሁኔታ

በዚህ ቀበሌ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ቢሰራለትም በመሬት ላይ የተሰሩ ሰራዎች የሉም፡፡ በዚህም
መሬቱን ከዕለት ከዕለት እራፍት የሚያሳጡ፣ የሚረብሹ ተግባራት ያሉ ሲሆን የተፈጥሮ ሃብት
ስራዎችም በአካባቢው መሬት ላይ የተሰሩ ስራዎች ማገኘት አልተቻለም፡፡ አካባቢው ከሰውና
ከእንስሳት ንክኪ የተጠበቀ አይደለም፡፡ በዚህም አካባቢው ከሚሸከመው በላይ የተለያዩ ህጋዊና

11
ህገወጥ ግንባታዎች ይገነባሉ ተገንብተዋልም፡፡ ነገር ግን የላይኛው የአፈር ንጣፍ ጥቁር አፈር
በመሆኑ ለግንባታ የማይመከር በቀላሉ ሊንሸራተት የሚችል መሆኑን መረዳት ተችሏል፡፡ የአፈር
ሲሪትም ቢሆን በቀላሉ በውኃ ሊቦረቦር የሚችል፤ እርጥበት ሲነካው በወሀ የሚቀልጥ፣ በፀሀይ
የሚሰነጣጠቅ ጥቁር አፈር የአካባቢው መሬቱ የተሸፈነ በመሆኑ አደጋው በቀላሉ ለፈጠር
እንደሚችል መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ ቦታ የአፈር እና የውኃ ጥበቃ ሊሆኑ የሚችሉ ስራዎች
አልተሰሩም፡፡ እንድሁም መሬተ አቃፊ ስር ያላቸው ዕፅዋቶች (ቀርቀሃ፣ ዝሆኔ ሳር ወዘተ) በሆኑ
ተክሎች መሬቱ ያልተሸፈ በመሆኑ እና ከጉርፍ የሚከላከሉ ስራዎች ያልተሰሩ በመሆናቸው
ለተፈጠረው የመሬት መንሸራተት አድጋ መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ ነጥቦች ናቸው፡፡

በተደረገው የመስክ ላይ ጉብኝት እና የቡድን ውይይይት ካላይ የተጠቀሱትን ሃሳቦች የሚያጠናክሩ


መረጃዎች ማገኘት ተችሏል፡፡ ከሃያ ዓመት በፊት በአካባቢው ስፋቱ ዝቅተኛ ቢሆንም ተማሳሳይ
አደጋ ተፈጥሮ የነበረ መሆኑን ለማየት ተችሏል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ካባባድ ማሽኖችና
መኪናዎች የሚንቀሳቀሱ በመሆኑ ለመሬት መረበሽ ምክንያት ለሆኑ የሚችሉ ነጥቦች ናቸው፡፡
የነበሩ የውኃ ምንጮችም መደፈናቸውና ወደ መሬት ውስጥ መስረጋቸው ሌለኛው የመሬቱ
መንሸራተት መነሻ ለሆን ይችላል፡፡ በጥቅሉ ሰፊ ጥናት የሚያስፈልግ ቢሆንም በተደረገው የመስክ
ምልከታ ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች እንዳሉ ሁኖ አካባባቢው ተዳፋትነትም ቢሆን ቀላል ግምት
የሚሰጠው አይደለም፡፡

ምስል 11፡ ከሃያ ዓመት በፊት የተፈጠረ የመሬት መንሸራተት

12
3.3. የችግሩ መንሰኤ

በጥቅሉ የመሬት ምንሸራተት ክስተት ውጫዊ እና ውስጣዊ ምክንያቶች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት
በአምባሰል ወረዳ ልዩ ስሙ ግራር ገንዳ በተበለው ቦታ የተከሰተውን የመሬት መንሸራተት ችግር
መንሰኤዎች ከላይ በተዘረዘሩት መንስኤዎች በመነሳት እደሚከተሉት ቀርቧል፡-

3.3.1. ውጫዊ ምክንያቶች

 የህዘቡ አሰፋፈር በጣም እየተቀራረበ መምጣቱና በርካታ የመኖሪያ ቤቶች በቦታው ላይ


መገንባታቸው
 በአቅራቢው የአውራ ጎዳና መኖሩና በርካታ የከባድ መኪና እንቅስቃሴ መኖሩ
 በጦርነቱ ምክኒያት የከባድ መሳሪያ ድምፅ እና በቦታው ላይ ማለፍ

3.3.2. ውሳጣዊ ምክንያቶች

 የመሬቱ የይዘት ሁኔታ ጠንካራ ያለመሆን


 የውሃ አዘል ጥልቀት እየጨመረ መሄድ፣ ይህን በተመለከተ ከህብረተሰቡ ከተወጣጡ
ሰዎች ጋር የተደረገው ውይይት እንደሚመለክተው በሠፈሩ የምንጭ ውሃ እንደ ነበርና አሁን
እንደደረቀና ታችኛው የመሬት ክፍል ላይ እንደመነጨ ይናገራሉ፡፡

3.4. በመሬት መንሸራተቱ የደረሱ ጉዳቶች

ሰሠንጠረዠ 1፡ በሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት

ተ/ቁ የደረሰ ጉዳት ዓይነት


እድሜ የተፈናቀለ ሞት ሌላ (ይገለጽ)……
ወንድ ሴት ድምር ወንድ ሴት ድምር ወንድ ሴት ድምር
1 0-14 16 16 32 --- --- ----- --- --- ---
2 15-64 61 65 126 ----- ----- ---- --- --- ---

3 > 64 4 4 8 ---- ----- ----- ---- --- ----

ድምር 81 85 166 ---- ---- ----- ---- --- ----

13
በተደረገው የዳሰሳ ጥናት መሰረት በዚህ አደጋ በሰውም ላይ ሆነ በእንስሳት የሞትን የመቁሰል አደጋ
ያልደረሰ ቢሆንም 166 ማህበረሰብን የተፈናቀሉ መሆኑን አረጋግጠናል፡፡ ነገር ግን በንብረት ላይ ያደረሰውን
አደጋ እንደሚከተለው ይቀርባል፡-

3.4.1. በመሰረት ልማት ላይ የደረሰ

ሶስት ኪሎ ሜትር የእግር መንገዶች፣ የውኃ መስመሮች፣ አራት የስልክ ፖሎች መውደቅና የሁለት ኪሎ
ሜትር የመብራት ገመዶች በመበጣጠስ ጉዳት ደርሷል፡፡ በዚህም ዘጠኝ የግለሰብ ቆጣሪ፣ አንድ የውኃ
ቦኖና 2000 ሜትር የውኃ ቧንቧ መስመር ከጥቅም ውጭ ሲሆን 58 የግለሰብ ቆጣሪ፣ አንድ የውኃ ቦኖና
4430 ሜትር የውኃ ቧንቧ መስመር በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ሁኗል፡፡ በጥቅሉ የ38 አባዋራ የ46 እማዋራ
በድምሩ የ84 ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ ያወደመ ሲሆን ለ137 አባዋራ ለ178 እመዋራ በድምሩ ለ315
ህብረተሰብ ለስጋት ተጋልጧል፡፡

ምስል 12፡ የተጉዱ መሰረተ ልማቶች በከፊል

3.4.2. በቤቶች ላይ የደረሰ ጉዳት

በይዞታ መሬት ላይ የተገነቡ 12 ቤቶች እንደሁም 26 የመገንባት ፍቃድ የሌላቸው ቤቶች ሙሉ በሙሉ
በመሬት መንሸራተቱ አደጋ ተጎድተዋል (ፈርሰዋል)፡፡ በዚህም 25 አባዋረዎች 13 እማዋረዎች በድምሩ 38
የማህበረሰብ ክፍሎች ቤት በመፍረሱ ምክንያት 33.6ሚሊየን ብር እንድያጡና ከኑሮው እንደፈናቀል
ሁኖል፡፡ በውስጡም የነበሩ ህፃናት፣ ተማሪዎችና አቅመድካማ ለጭንቀት፣ ለተስፋ መቁረጥ ተጋልጠዋል፡፡

14
ምስል 13፡ የወደሙ ቤቶች በከፊል

በስጋት ላይ የሚገኙ መልቀቅ ያለባቸው ማህበረሰብ ያሉም ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በይዞታ መሬት
ላይ የተገነቡ 17 ቤቶች እንደሁም 3 የይዞታ ማረጋገጫ የሌላቸው ቤቶች ሙሉ በሙሉ በመሬት
መንሸራተቱ ለአደጋ ተጋላጭ መሆናቸው አይተናል፡፡ በዚህም 10 አባዋረዎች 10 እማዋረዎች
በድምሩ 20 የማህበረሰብ ክፍሎች ቤት ቤታቸው ለአደጋ የተጋለጠ በመሆኑ የቤቶቹም የዋጋ
ግምት 21.7 ሚሊየን ብር እንደሚደርስ ተገምተዋል ፡፡

ምስል 14፡ በከፍተኛ ስጋት ላይ ያሉ ቤቶች በከፊል

በ500 ሜትር ውስጥ ያሉ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰብ ያሉም ሲሆን ከነዚህም ውስጥ
በይዞታ መሬት ላይ የተገነቡ 8 ካርታና ፕላን ያላቸው ቤቶች እንደሁም 112 የይዞታ ማረጋገጫ
የሌላቸው ቤቶች ሙሉ በሙሉ በመሬት መንሸራተቱ ለአደጋ ተጋላጭ መሆናቸው አይተናል፡፡
በዚህም 70 አባዋረዎች 51 እማዋረዎች በድምሩ 121 የማህበረሰብ ክፍሎች ቤት ቤታቸው ለአደጋ

15
የተጋለጡ በመሆናቸው የቤቶቹም የዋጋ ግምት ጠቅላላ ሀብት 133.1 ሚሊየን ብር እንደሚደርስ
ተገምተዋል፡፡

ሰሠንጠረዠ 2፡ ለአደጋ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍል መረጃ


ተ ዝርዝር መግለጫ ባለንብረት የቤተሰብ ያንዱ ዋጋ የጠቅላላ የይዞታ
/ በቁ ብዛት የቤቱ ዋጋ የቤት ማረጋገጫ
ቁ ጥር ግምት ግምት ደብተር
እማዎራ አባወራ ወንድ ሴት ብር ብር ያለው የሌለው
በሚሊየን
1 ሙሉ ለሙሉ ቤታቸው 38 25 13 71 63 884,210 33.6 12 26
የፈረሰባቸው ማህበረሰቦች
2 በስጋት ላይ የሚገኙ መልቀቅ 20 10 10 18 22 1,085,00 21.7 17 3
ያለባቸው ማህበረሰብ 0
3 500 ሜትር ውስጥ ያሉ 121 51 70 1,100,00 133.1 8 112
ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ 0
ማህበረሰብ

3.4.3. በመሬት ላይ የደረሰ አደጋ

በመሬት መንሸራተቱ 0.1875ሄ/ር የእርሻ መሬት፣ 0.7ሄ/ር የግጦሽ መሬት፣ 2.557ሄ/ር የደን
መረት እንድሁም 6.2155ሄ/ር መንደር በድምሩ 9.66ሄ/ር መሬት የአደጋው ሰለባ ሲሆን 3.67ሄ/ር
ሙሌ በሙሉ የወደመና 5.99ሄ/ር በከፍተኛ ስጋት ላይ ያለ መሆኑን ተረጋጧል፡፡ 30 አባዋራ፣ 19
እማዋራ በድምሩ 49 የመሬት ባለይዞታዎች ሙሉ በሙሉ የመኖሪያና መሬታቸውን ተጉጅ
ሁነዋል፡፡ 10 አባዋራ፣ 10 እማዋራ በድምሩ 20 የመሬት ባለይዞታዎች በከፊል መሬታቸው ተጉጅ
ሁኗል፡፡

ምስል 15፡ የተጉዳ መሬትና በስጋት ላይ ያለ መሬት መጠን

16
3.4.4. በአትክልትና በእፅዋት ላይ የደረሰ አደጋ

በዚህ አደጋ በምግብ እህሎች ላይ የደረሰ አደጋ ባኖርም በቋሜ አትክልቶች ላይ ከፍተኛ አደጋ ደርሷል፡፡
8720 ባህርዛፍ፣ 21 ዋንዛ፣ 25 ግራርና 8 ወይራ በጥቅሉ በወቅቱ የገባያ ዋጋ 1483400 ብር አሳጥቷል፡፡
በተጨማሪም ቋሜ ፍራፍሬ አትክልቶች ማለትም 32 ፓፐየ፣ 34 ማንጎ፣ 5 አቡካዶ፣ 119 ሙዝ፣ 391
ቡና እና 19 ብርትኳን በመጎዳታቸው በወቅቱ የገባያ ዋጋ 699100 ብር አሳጥቷል፡፡

3.5. በአደጋው ዙሪያ አሁን እየተሰሩ ስራዎች

የዞንና የወረዳ ቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ የተጎጅዎችን መረጃ በጥራት በማጥናት መጠይቆችን
አዘጋጅቶ መረጃዎችን እያሰባሰቡ መሆኑ፡፡ ተጎጅዎች ከአደጋው ቦታ እንድርቁ /እንድለቁ የጥንቃቄ
ምክር ሃሳቡን አሰቀምጧል፡፡ ተጎጅዎች በአደጋው ውስጥ ያሉ መኖሪያ ቤቶችን እንድፈርሱ ንብረት
እንዳነሱ ማድረግ፡፡ አደጋው እየተስፋፋ በመሆኑ እና የት ላይ እንደሚቆም ስላልታወቀ ከአደጋው
መጨረሻ ነጥብ ጀምሮ በ500 ሜትር ራድየስ ስንት ማህበረሰብ እንደሚኖር መረጃ መያዝ ስራ
ተሰርቷል፡፡ አጠቃላይ መሰረታዊ መረጃ በሁሉም በአደጋ መከላከል፣ በጤና፣ በወሃ፣ በከተማ
ልማት መረጃዎችን በመጠይቆቹ መሰረት መረጃ መሰብሰብ ስራ ተሰርቷል፡፡ የተፈናቃይ ጊዜያዊ
መጠለያ የቤት ኪራይ እንድሁም እንዳስፈላጊነቱ በድንኳን እንድሰፍሩ ምክር ሃሳቡን ተቀምጧል፡፡
የተፈናቀሉ ሰዎችን የእለት ድጋፍ ማለትም በአደጋው የአቅመ ደካሞችን ተጎጅዎችን ጊዜያዊ
የመኖሪያ ቤት ማስፈረሻ፣ የማቴሪያል ማጓጓዣ የመኖሪያ ቤት ግንባታና መስፈሪያ ቦታ ከዞንና
ከወረዳ አመራር ጋር በመሆን ማመቻቸት እንድሁም የተራዓድኦ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን
ድጋፍ እንዳደርጉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ስራ መስራት ተጀምሯል፡፡

3.6. ትምህርትና ጤና በተመለከተ

በዚህ በተከሰተው የመሬት ምንሸራተት ምክንያት የተስተጓጎሉ ተማሪዎች ያሉ ሲሆን አጸደ ህጻናት 34 ከ1
እስከ 8ኛ ክፍል የሚማሩ 51 ከ8 እስከ 12ኛ ክፍል የሚማሩ 23 ተማሪዎች በጠቅላላ 108 ተማሪዎች
ትምህርታቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ባለመከታተላቸው ምክንያት የስነ ልቦና ጫና እንደደረሰባቸው ለማየት
ተችሏል ፡፡

17
4. ማጠቃለያና ምክረ-ሐሳብ

4.1. ማጠቃሊያ

የአምባሰል ወረዳ በአማራ ክልላዊ መንግስት በደ/ወሎ መስተዳደር ዞን ስር ከሚገኙት የምስራቅ


አማራ ወረዳዎች አንዱ ነው፡፡ አምባሰል ወረዳ በጥቅሉ የመሬቱ አቀማመጥ ተራራማና ወጣ ገባ
የበዛበት፣ የአፈር ለምነቱም ዝቅተኛ የሆነ፣ የአፈር መሸርሸር ያለበት፣ በጎርፍ የሚጠቃ ወረዳ
ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ ለመሬት መንሸራተት ዋነኛ መንስኤ ነው ተብሎ ይወሰዳል፡፡
በአካባቢውም የመሬት መንሸራተት አደጋ አልፎ አልፎ የተከሰተ ሲሆን አሁንም በ01 ሊሞ ቀበሌ
የተፈጠረው መሬት መንሸራተት አደጋ ያደረሰው ጉዳት እጅግ የከፋ በቀላልና ባጭር ጊዜ ሊካካስ
የሚችል አይደለም፡፡ አደገጋው በስነልቦናም ሆነ በኢኮኖሚ ላይ ደረስው እንድሁም የደቀነው ስጋት
ከፍተኛ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ መሆኑን ከላይ ከተቀመጡት መረጃዎች መረዳት ይቻለል፡፡
ስለዚህም በደረሳው አደጋ ስነ ልቦናዊም ሳናነሳ በቁሳዊ ጉዳት ብቻ በቋሜ አትክልቶች በጥቅሉ
በወቅቱ የገባያ ዋጋ 1483400 ብር፤ በፍራፍሬ አትክልቶች ላይ በደረሰው አደጋ በወቅቱ የገባያ ዋጋ

699100 ብር፤ በአደጋው ከፍረሱ ቤቶች 33.6ሚሊየን በድምሩ 35782500 ብር ሙሉ ለሙሉ


አሳጥቷል፡፡ 81 ወንድ 86 ሴት 166 ማህበረሰብን ከመኖሪያ ቦታቸው ሙሉ በሙሉ እንድፈናቀሉ
አድርጓል፡፡ ለ137 አባዋራ ለ178 እመዋራ በድምሩ ለ315 ህብረተሰብ ለስጋት አጋልጧል፡፡
በመሰረተ ልማቶች ላይም ቢሆን 3 ኪሎ ሜትር የእግር መንገዶች፣ 2000ሜትር የውኃ
መስመሮች፣ 4 የስልክ ፖሎች መውደቅና የ2 ኪሎ ሜትር የመብራት ገመዶች በመበጣጠስ ጉዳት
ደሷል፡፡ በተከሰተው የመሬት ምንሸራተት ምክንያት በጥቅሉ 108 ተማሪዎች ከትምህርት
ገበታቸው እንድስተጓጎሉ ሁነዋል፡፡ የችግሩ ጥልቅት ለአካባቢው ብቻ ሳይሆን ለውጫሌ ከተማም
ቢሆን አስጊ በመሆኑ ከተማውን መታደግ የሚቻለው ለችግሩ ትኩረት ተሰጥቶ ዘላቄ መፍትሄ
በማበጀት መሆኑን ያመለክታል፡፡

በመጨረሻም መሬትን በአግባቡ አለመያዛችንና ከመሸከም አቅም በላይ አላግባብ የምንጠቀምብት


ከሆነ በቃኝ ብላ አራግፋ አንደምትጥለን ማሳያ መሆኑን ያስረዳል፡፡ ስለዚህ ይህ አደጋ ብቸኛና
ተተኪ የማይገኝለትን የተፈጥሮ ሃብት የሆነውን መሬትን ተንከባክበንና ትኩረት ሰጥተን
ካልይዝነው በቀላሉ ማጣት አንደምንችል የሚያሳይ የደወል ጥሪ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
ለችግሩ ፈጣን ምላሽ ከልተሰጠም ችግሩ ቀጣይንት እንደሚኖረው ያመልክታል፡፡

18
4.2. ምክረ ሃሳብ

የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ መፍትሄ ይሆኑ ዘንድ እንደሜከተለው ተቀምጠዋል፡-

ከአጭር ጊዜ
 ከላይ ከተቀመጡት ሃሳብ በመነሳት አደጋው ከዕለት ዕለት እየጨወረ የመጣ በመሆኑ
አደገው የተከሰተባቸው ማህበረሰቦች ሆኑ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን
አደጋ ከመድረሱ በፊት በአፋጣኝ ቦታውን ለቀው እንድ ወጡና በጊዜያውይ መጠለያ
ቢሰፍሩ፡፡
 በዘለቄተው ሊሰፍሩበት የሚችሉ ቦታ በማዘጋጀት በእጃቸው ያለ ሃብትና ንብረት ሳይጠፋ
በቋሜነት እንድቋቋሙ ቢደረግ፡፡
 ጉዳት የደረሰበት መሬት መልሶ እጥቅም ላይ እድውል ህገወጥ እንቅስቃሴ ማስቆም ቢቻል፡፡
የረጅም ጊዜ የመፍትሔ ሃሳብ
 የስነ ምህዳር ጥናት ጥልቅ የሆነ ጥናት ያስፈልገዋል፡፡ ማለትም ለችግሩ መንስኤ ቅርብ
የሆነ የከርሰ ምድር ውሃ መኖር ተብሎ የተቀመጥው የከርሰ-ምድር ውሃ መኖሩን የሚገልፅ
ከቡድን ውይይት መረጃ በተጨማሪ የጅኦፊዚክስ መሳሪያ በመጠቀም ውሃ በአካባቢው
መኖሩን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ በሁለተኛነት እንደመንስኤ የተቀመጠው የአፈሩ ወይም
አለቱ ጥንካሬ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አፈር ምርምር ተቋም ወይም አማራ ውሃ ጥናትና
ድዛይን የአፈርን ጥንካሬ ላቦራቶሪ በመውሰድ ማረጋገጥ ይገባል፡፡ በሶስተኛነት የተቀመጥው
የመሬት መንቀጥቀጥ ሲሆን በዚህ ቦታ ላይ የበላይ ባለሙያዎች ከትልቅ የምርምር ተቋም
በመጋበዝ ጥልቅ የሆነ ጥናት ያስፈልጋል፡፡ በዚህም የተነሳ ከተማውን መታደግ የሚቻለው
ጅኦሎጅስቶች የተሳተፉበት የምርምር ጥናት የሚካሄደው ለስራው የሚያግዝ ወይም ለጥናቱ
የሚያግዙ የመመርመሪያ መሳሪዎች፤ የሰው ሀይል፤ በጀት እና ጊዜ ይፈልጋል፡፡ እነዚህን
አጣምሮ ስራው ካልተሰራ በስተቀር ከተማውንና የዚያን አካባቢ ኗሪ ማህበረሰብ መታደግ
ላይቻል ይችላል፡፡ በዚህም የተነሳ የሚመለከተው አካል ጥናት እንድጠናለት ከትልልቅ
ተቋማት ባለሙያዎችን በመጋበዝ በጀት እና ጊዜ መድቦ ማስጠናት እና ለወረዳውም
ጭምር ዘላቂ መፍትሄ ቢቀመጥ፡፡
 አካባቢው ከሰውና ከእንሰሳት ንኪኪ ተጠብቆ የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራዎች ቢሰሩበት
እንድሁም ወደ ቋሚ ደን ልማት ቢሸጋገር፡፡

19
ዋቢ መጻሐፍት

Daniel Gemechu. (1977). Aspect of climate and water balance in Ethiopia. Addis Ababa
University press, Addis Ababa, 79pp.
Getnet Mewa and Filagot Mengistu (2021).Institute of Geophysics, Space Science and Astronomy,
Addis Ababa University, Ethiopia.
World Bank (2019). The international Bank for reconstruction and Development, theWorld Bank
Group 1818 H Street, NW, Washington, D.C.20433, USA.

20
ዕዝል
.የመረጃ መሰብሰቢያ ፎርማቶች
I. የመሬት መንሸራተት ጉዳት መረጃ መስብሰቢያ ፎርም
1.አጠቃላይ መረጃ
1.1 የወረዳ ስም----------------
1.2 የተከሰተበት ቀበሌ-------------
1.3 የተከሰተበት ጎጥ ስም---------------
1.4 የተከሰተበት ቦታ የመሬት ከፍታ ከፍተኛ---------------------- ዝቅተኛ-----------
1.5 አመታዊ የዝናብ መጠን------------ሚሚ
2.የመሬት ሁኔታ
2.1 ችግሩ የተከሰተበት ቦታ የአፈር ዓይነት
ተ/ቁ የአፈር ዓይነት ስፋት (ሄ/ር) ስፋት ከጠቅላላው (%)
1 አሻዋማ
2 ዋልካማ አሸዋማ
3 ደለላማ ዋልካ
4 ዋልካ
5 ሸክላማ ዋልካ
6 ሸክላማ
7 ከባድ ሽክላ

2.2 ችግሩ የተከሰተበት ቦታ የተዳፋት ሁኔታ


ተ/ቁ ተዳፋት መጠን የተዳፋት ክፍሎች መጠን (ሄ/ር) ስፋት ከጠቅላላው (%)
ገደብ %
1 0-2 ሜዳ ወይም ወደ ሜዳነት የተጠጋ
2 2-8 ቀስ በቀስ ያጋደለ
3 8-15 ያጋደለ
4 15-30 በሀከለኛ ዥው ያለ
5 30-50 ዥው ያለ
6 >50 በጣም ዥው ያለ

2.3 ችግሩ ሊከሰትበት የሚችል መሬት በአጠቃቀም

21
ተ/ቁ የመሬት አጠቃቀም ሁኔታ ስፋት (ሄ/ር) ስፋት ከጠቅላላው (%)
1 የታረሰ መሬት
2 የሳር/ ግጦሽ መሬት
3 የደን መሬት
4 ቁጥቋጦ መሬት
5 በመንደር
6 ሌላ (ይገለጽ)……………….
7 ድምር

ማሳሰቢያ፡- እያንዳንዱ የመሬት አጠቃቀም ስፋት በጂ ፒ ኤስ በመጠቀም የሚሰራ ሆኖ የእያንዳንዱ


የመሬት አጠቃቀም ኮርዲኔት ይስፈልጋል
2.4 በአካባቢው እሰከሁን የተሰሩ የደን ልማትና የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች
ተ/ቁ የስራ ዝርዘር መለኪያ መጠን

3. የሶሾ-ኢኮኖሚክ መረጃ
3.1. የተጋላጭ ህዝብ መረጃ
የቤተሰብ ተጠሪ ጠቅላላ ህዝብ በአማካኝ የዕድሜ ሁኔታ
የቤተሰብ
መጠን
አባወራ እማወራ ድምር ወንድ ሴት ድምር እስከ 14- 18- 36- ከ 55 አመት
13 17 35 55 በላይ
በቁጥር
(%)

3.2 በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት


ተ/ቁ የደረሰ ጉዳት ዓይነት
እድሜ የተፈናቀለ ሞት ሌላ (ይገለጽ)……
ወንድ ሴት ድምር ወንድ ሴት ድምር ወንድ ሴት ድምር

22
1 0-14
2 15-64
3 > 64
ድምር

3.3 የተማሪዎች ሁኔታ


 አፀደ ህፃናት የሚማሩ _____
 ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሚማሩ _____
 ከ8 – 12ኛ ክፍል የሚማሩ _____
3.4. የቤት እንስሳት ይዞታ

ተ/ቁ የቤት አንስሳት ዓይነት መጠን (በቁጥር) አማካኝ ይዞታ በአባወራ ከጠቅላላው ያለው
ድርሻ በፐርሰንት
1 በሬ
2 ላም
3 ጥጃ
4 ጊደር
5 ፈረስ
6 በቅሎ
7 አህያ
8 ፍየል
9 በግ
10 ዶሮ
ሌላ ካለ ይገለጽ……
ድምር

3.5 በቤት እንስሳት ላይ የደረሰ ጉዳት መረጃ


ተ/ቁ የቤት አንስሳት ዓይነት የደረሰ ጉዳት ዓይነት የተጎዳ አባወራ

ሞት ስብራት ሌላ (ይገለጽ)…… ወንድ ሴት ድምር


1 በሬ
2 ላም

23
3 ጥጃ
4 ጊደር
5 ፈረስ
6 በቅሎ
7 አህያ
8 ፍየል
9 በግ
10 ዶሮ
ሌላ ካለ ይገለጽ……

3.6 ጉዳት የደረሰበት መሬት


ተ/ቁ መሬት አጠቃቀም ስፋት የተጎዳ አባወራ ብዛት
(ሄ/ር) ወንድ ሴት ድምር
1 የሚታረስ መሬት
2 የሳር/ ግጦሽ መሬት
3 የደን መሬት
4 ሌላ -------- (ካለ ይገለጽ)

3.7 የመሬት መንሸራተት ያጠቃቸው አርሶ አደሮች የጉዳት


ተ/ የጉዳት መጠን ድምር
ቁ ሙሉ በሙሉ ከፊል መሬታቸውን ምንም ጉዳት
መሬታቸውን ያጡ ያልደረሰበት
ያጡ
1 አባወራ
2 እማወራ
3 ድምር

3.8 የምግብ እህልና እጽዋት ጉዳት መረጃ


ተ/ የምግብ እህል መለኪያ መጠን የአንዱ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ የተጎዳ አባወራ ብዛት
ቁ ዓይነት
ወንድ ሴት ድምር

24
1 የምግብ እህል ኩ/ል
ጤፍ
ማሽላ
ዘንጋዳ
ሌላ (ይገለጽ)
2 የፍራፍሬ ዛፍ ቁጥር
ፓፓያ
ጊሽጣ
ሌላ (ይገለጽ)
3 አትክልት
ጎመን
ሰላጣ
4 የደን ዛፍ
ባህር ዛፍ
ዋንዛ
5 ቅመማ ቅመም
6 ሌሎች (ይጠቀስ)

3.9 የመኖሪያ ቤት ግንባታ መረጃ


ተ/ቁ ዝርዝር ጉዳት የጉዳት መጠን አባወራ እማወራ ድምር
የደረሰበት ሙሉ ከፊል
ቤት ብዛት በሙሉ
1 በይዞታ መሬታቸው ላይ
የገነቡ
2 የመገንባት ፍቃድ
ያላቸው ብዛት
3 የመገንባት ፍቃድ
የሌላቸው ብዛት----------
3.10 የቤት ቁሳቁስ የጉዳት መረጃ
ተ/ቁ የቤት ቁሳቁስ መለኪያ መጠን የአንዱ ጠ/ዋጋ የተጎዳ አባወራ ብዛት

25
ዓይነት ዋጋ ወንድ ሴት ድምር

3.11 የተዘጋጀው መሬት አጠቃቀም ዕቅድና የተሠጠ ምክረ ሃሳብ ምን ነበር------------------


3.12 የተዘጋጀው መሬት አጠቃቀም ዕቅድና በተሠጠ ምክረሃሳብ ወደ ተግባር ተግብቷል ሀ/ አዎ
ለ/ አልተገባም
3.13 የእዚህ አካባቢ መሬት እረፍት ሊያሳጣ የሚችሉ ተግባሮች ምን ምን ተፈጽመዋል? (X)
ምልክት ያድርጉ
ተ/ቁ የተግባር ዓይነት አዎ የለም
1 ህገ ወጥ አስተራረስ
2 ደን ጭፍጨፋ
3 ህገ-ወጥ ግንባታ
4 ከባድ ማሽኖች እና መሳሪያዎች እንቅስቃሴ መኖር

5 ሌላ ካለ ይካተት

4) መሰረተ ልማት
4.1)የውሃ ተቋማት ሁኔታ
 የወደሙ የውኃ ተቋማት አይነትና ብዛት በዝርዘር ይገለጽ?
 የተበላሹና የወደመ የውኃ መስመሮች አሉ ወይ? 1) አለ 2)የለም
 ከለይ ለተገለታ ጥያቄ መልሱ አዎ ከሆነ በመጠን ይገለጽ
 የተበላሸ አንዲሁም የተሰበረ የውሃ ቆጣሪ ብዛት ይገለጽ? ምን ያህል ቆጣሪ ከቦታው ይነሳል?
 የባከነ ወሃ መጠን እና በከተማ ታሪፍ በገንዘብ ሲተመን ስንት ይሆናል?
 በኤሌክትሮ መካኒካል ፣የጥበቃ ቤት፣ጀነረተሮች፣ የውሃ መለዋጫና ጥገና መሳሪዎች የደረሰ ጉዳት
ካለ ቢገለጽ

26
 በቦታው ምን ያህል የውሃ ማዳያ (ቦኖ) አለ? የውሃ ማጣራቀሚያ ጋን በቦታው አለ? የሚያዝ
መጠኑ ስንት ነው?
 በጉዳቱ ሰለባ የሆነ አባወራና እማወራ ብዛት ቢገለጽ
 ጉዳት የደረሰበት የመስኖ ተቋም አይነትና ብዛት በዝርዘር ቢገለጽ
 ጉዳት የደረሰበት የእንስሳት ውሃ ማጠጫ ገንዳ ብዛት--------------------
4.2መንገድ
 የተጎዳ የእግር መንገድ-------------ኪ/ሚ
 የተጎዳ የመኪና መንገድ---------ከ/ሚ
4.3 የመብራት መስመር
 የተጎዳ የመብራት ፖል ብዛት--------
 የተጎዳ የመብራት መስመር----------------ኪ/ሚ
4.4 ባዪ ጋዝ
 በአካባቢው ባየጋዝ አለ? በተቋሙ ላይ የደረሰ ጉዳትስ አለ? የጉዳቱ መጠን ይገለጽ…………..
4.5 መኖሪያ ቤት
1/ የግንባታው ባለቤት ሙሉ ስም አቶ/ወ/ሮ
2/ ግንባታው የሚገኝበት አድራሻ ከተማ ……. ቀበሌ …. ልዩ ሰፈር …………………………..
3 / የግንባታው አይነት …………………………………….. አገልግሎት …………………………...
4/ የግንባታ ካርታና ፕላን ሀ/ ያለው ለ/የሌለው ሐ/ ሌላ ማስረጃ ካለ ይጠቀስ……
5/ ግንባታው በአሁኑ ሰዓት ያለበት ደረጃ …ሀ/ የፈረሰ ለ/ ያልፈረሰ ሐ/ በከፊል ተጎዳ
6/ የግንባታው ልኬታ በሜትር ርዝምት……….. ወርድ…………... ቁመት ……….የቤቱ /የግንባታው
ወለል ስፋት በካ/ሜ……
7/ የቤቱ ዙሪያ በድንጋይ ግንብ ሀ/የታሰረ ለ/ያልታሰራ ሐ/ በደረቅ ካብ የታሰራ መ/ ምንም
የሌለው
8/የተሰራ ከሆነ ልኬታ ይቀመጥ ………………………………………………..
9/ ግንባታው የተሰራበት ማቴሪያል ሀ/ በብሎኬት ለ/ በጭቃ ሐ/ በቆርቆሮ መ/ በሌላ
ከሆነ ይጠቀስ ……………….
10/ ግንባታው የውጭ ግድግዳው በአሽዋና ስሚንቶ ሀ/ ሽምብራ ግርፍ የተገረፈ ለ/ የተለሰነ
መ/ያልተለሰነ ሠ /ሀ እና ለ
11/ ግንባታው የውጭና የውስጥ ግድግዳ በተቦካ ጭቃ ሀ/ የተለሰነ ለ/ የተመረገ መ/በምንም
ጭቃ ያልተመረገ
12/ ግንባታው የውስጥ የግድግዳ ቀለም ሀ/ የተቀባ ለ/ ያልተቀባ ሐ/ በጂብሰም
የተሰራ

27
13/ግንባታው የውጭ ግድግዳ ቀለም ሀ/ የተቀባ ለ/ ያልተቀባ ሐ/ በኳርቲዝ የተሰራ
14/ግንባታው የወለል ስራ በስሚንቶና አሽዋ ማንኪያ ሊሾ ሀ/የተሰራ ለ/ ያልተሰራ
15/ ወለሉ በሌላ የግንባታ አቃ የተሰራ ከሆነ ይጠቀስ …………………………….
16/ለግንባታው ኮርኒስ ሀ/ የተሰራ ለ/ ያልተሰራ
17/የተሰራ ከሆነ ኮርኒሱ የተሰራበት የእቃው አይነት ይጠቀስ……………………
18/ ግንባታው / በር ሀ/ የተገጠመ ለ / ያልተገጠመ የተገጠመ ከሆነ የበሩ ብዛት
በቁጥር ………………………
19/ የበሩ አይነት ይጠቀስ ……………………………………….በካሬ………………………
20/የበሩ አይነት ይጠቀስ …………………………………….በካሬ……………………
21/መስታወት የተገጠመ ከሆነ ስፋቱ በካ/ሜ ይገለጽ ……………………….
22/ መስኮት ሀ/ የተገጠመ ለ / ያልተገጠመ የተገጠመ ከሆነ የመስኮቱ ብዛት ……
23/የመስኮቱ አይነት ይጠቀስ……………………………………………በካሬ……………
24/ የመስኮት አይነት ይጠቀስ ………………………….በካሬ………………………
25/መስታወት የተገጠመ ከሆነ ስፋቱ በካ/ሜ ይገለጽ ……………………….
26/ ግንባታው ዙሪያ የእግር መረማመጃና የውሀ መፋሰሻ ሀ/ የተሰራ / ለ/ ያልተሰራ ሐ/ የተሰራ
ከሆነ በምን ……………
27/ የኤሌክትሪክ መብራት የተሰራ ከሆነ በቁጥር ………… ሶኬት የተገጠመ ከሆነ በቁጥር ……
ማሳሰቢያ ፡- 1/ የፎቶ ግራፍ ማስረጃ መያዝ አለበት
2/እያንዳንዱ ግንባታ መረጃው መሞላት አለበት
3/ተጨማሪ ስለግንባታው ከተዘረዘረው ሌላ ማብራሪያ ካለ ይጠቀስ

የግንባታው ባለቤት /ወይም ተወካይ ስም--------------------- ፊርማ ቀን


መረጃውን ያጠናቀረው ባለሙያ ስም ፊርማ ቀን

28
5. የጤና መረጃ መሰብሰቢያ

የተፈናቃይ የቤተሰብ ሁኔታ አጥቢ እስከ 2 ነፍሰ- ቲቢ የግፊት የስኳር የአእም


ተ.ቁ ስም እድሜ ጾታ (እማዋራ፤አባዋራ፤ሚስት፤ልጅ) አመት ጡር ታካሚ ታካሚ ታካሚ ህመም

II. ከህብረተሰቡ ከተውጣጡ አካላት ጋር ለመወያየት የተዘጋጀ ቸክሊስት


1. የችግሩ መነሻ ምንድ ነው?
2. በአካባቢው ላይ ምን አይነት ሥነ- አካላዊ ሥነ- አውንታዊ ሥራዎች ነበሩ?
3. በችግሩ የደረሠ ጉዳቶች ምን ምን ናቸው?
4. የችግሩ መፍትሄ ምን ቢሆን ይሻላል ትላላችሁ?

III. የድረጊት መረሐ-ግብር


ተ/ቁ ዝርዝር ተግባር የሚፈፀምበት ጊዜ
1 የወረዳ አመራሩን በማገኘት የተፈጠረውን ችግር መሰረት በማድረግ ማዋያየት 03/04/2015 ዓ.ም
2 በዞኑ ኮሚቴ ትይዩ የወረዳ ኮሚቴ ማዋቀር 04/04/2015 ዓ.ም
3 ችግሩ በተከሰተበት ቦታ በመገኘት የቅኝት ስራ መስራት 04/04/2015 ዓ.ም
4 በወረዳ የተዋቀረውን ኮሚቴ በችግሩ ዙሪያ ማወያየት 05/04/2015 ዓ.ም
5 ችግሩን ለመዳሰስ የሚስቸል የመረጃ መሰብሰቢያ ፎርም ማዘጋጀት 05/04/2015 ዓ.ም
6 የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማወያየት እንዲመች መሪ ሀሳቦችን በቸክሊስት ማዘጋጀት 05/4/2015 ዓ.ም
7 የመረጃ ማሰባሰቢያ ፎርማቶችን በወረዳ ደረጃ ለተዋቀረው ኮሚቴ ግልጽ ማድረግ 06/4/2015 ዓ.ም
8 በተዘጋጀው ቸክሊሰትን በመጠቀም ከህበረተሰብ ከተውጣቱ ክፍሎች ጋር ውይይት ማድረግ 06/4/2015 ዓ.ም
9 የመረጃ ማሰባሰቢያ ፎርማቶችን መሰረት በማድረግ በኮሚቴው መረጃዎች እንዲሰባሰቡ 7-8/04/2015 ዓ.ም

29
ማደረግ
10 የተሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ የማጣቃሊያ ሪፖርት ማዘጋጀት 09/04/2015 ዓ.ም
11 ከማጣቃሊያው ሪፖርት በመነሳት የአጭርና የረጀም ጊዜ መፍተሄ ማስቀመጥ 10/04/2015 ዓ.ም
12 የተጠቃለለውን ሪፖርት ለወረዳ አመራሩ ማቅረብ 10/04/2015 ዓ.ም
13 የተጠቃለለውን ሪፖርት ለዞን አመራሩ ማቅረብ 11/04/2015 ዓ.ም

IV. የጥናት ቡድኑ አባላት

ተ/ቁ የባለሙያው ስም መምሪያ የስራ ኃላፊነት ፊርማ


1 አቶ ደባለቄ አዱኛ
2 አቶ መሃመድ
3 አቶ ሰይድ
4 አቶ አወል ከተማና መሰረተ ልማት
5 አቶ እሸቱ
6 አቶ ይማም
7 አቶ ግዛቸው ሽዋዬ ግብርና መምሪያ የአ/ው/ጥ ባለሙያ

የደቡብ ወሎ ዞን ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ


በአምባሰል ወረዳ በ01 ቀበሌ ሊሞ ግራር ገንዳ ገጥ በመሬት መንሸራተት ምክኒያት የፈረሰ ፣በስጋት ላይ ያለ ፣እና

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ የቤቶች ብዛት በአማካኝ ዝርዝር ግምት

ተ ዝርዝር መግለጫ ባለንብረት የቤተሰብ ያንዱ ዋጋ የጠቅላላ ዋጋ የይዞታ ምር

/ በቁ ብዛት የቤቱ ግምት የቤት ግምት ማረጋገጫ መራ

ቁ ጥር ደብተር

እማ አባወ ወን ሴ ብር ሳ ብር ያለ የለለ

ዎራ ራ ድ ት ው ው

1 ሙሉ ለሙሉ ቤታቸው 12 26

የፈረሰባቸው ማህበረሰቦች 38 25 13 71 63 ጥቅል ግምት


በአማካኝ የቤቶቹ ሁኔታ

30
 ውሀ ልክ የታሰራ 884,210 33,600,000

 የተለሰነ ጭቃ

 የውስጥ ወለል ሊሾ

የተደረገ ከውስጥም

የተቀባ ሙሉ ቤት

ኮርኒስ ያለው

2 በስጋት ላይ የሚገኙ መልቀቅ

ያለባቸው ማህበረሰብ ጥቅል ግምት


በአማካኝ የቤቶቹ ሁኔታ 3
20 10 10 18 22 17
ውሀ ልክ የታሰራ

የተለሰነ 1,085,000 21,700,000


ኳርቲዝ የተቀባ

ከውጭም ከውስጥም የተቀባ

ሙሉ ቤት

ኮርኒስ ያለው

3 500 ሜትር ውስጥ ያሉ

ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ጥቅል ግምት

ማህበረሰብ
በአማካኝ የቤቶቹ ሁኔታ 121 51 70
112
ውሀ ልክ የታሰረ 1,100,000 133,100,000 8
በጭቃ የተለሰነ፣

በስሚንቶ የተገረፈ ካርታና

ፕላን
ኳርቲዝ የተቀባ
ያላቸ
ከውጭም ከውስጥም ቀለም ው

የተቀባ

ሙሉ ቤት ኮርኒስ ያለው

ሊሾ የተሰራ የተሟላ ቤት

31

You might also like