You are on page 1of 11

የመሀረነ አብ ጸሎት በግዕዝ እና በአማርኛ

+ ሃሌ ሉያ ፤

ሃሌ ሉያ፤(ቅድመ ዓለም የነበረ፥አሁንም ያለ፥ድኅረ ዓለም የሚኖር )፤

+ ዘበእንቲአሃ ለቤተ ክርስቲያን


ለቤተክርስቲያን ስትል

+ ተጸፋእከ በውስተ ዓውድ


በአደባባይ በጥፊ የተመታህ

+ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር


አቤቱ ይህን ማድረግህ እር ሷን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡

✟✟✟ ሃሌ ሉያ ዘበእንቲአሃ ለቤተ ክርስቲያን


ተጸፋእከ በውስተ ዓውድ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር

ለቤተክርስቲን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ


አቤቱ ይህን ማድረግህ እር ሷን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡

✟✟✟ ዘበእንቲአሃ ዝግኀታተ መዋቅሕት ፆረ


ወተዐገሠ ምራቀ ርኲሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ
አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ

ለእርሷ ሲል ታስሮ መጎተትን የቻለ፤ የበደለውን በደል ሳይኖር ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሰ
አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ

✟✟✟ሃሌ ሃሌ ሉያ አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ


ረዳኤ ኩነነ ወኢትግድፈነ
መሐረነ መሐከነ እግዚኦ እግዚኦ ተሠሃለነ

ሃሌ ሃሌ ሉያ አቤቱ ይቅርታህን አሳየን ፤እርዳን አትተወን ፤


አቤቱ ማረን ይቅር በለን፡፡
+++ መሐረነ አብ
አባት ሆይ! ማረን

🙏 ሃሌ ሉያ፤
ሃሌ ሉያ፤

+++ ተሣሃለነ ወልድ፥


ወልድ ሆይ! ማረን

🙏 ሃሌ ሉያ፤
፥ሃሌ ሉያ፤

+++ መንፈስ ቅዱስ መሐሪ ተዘከረነ በሣህልከ፤


መሐሪ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! በይቅርታህ አስበን፤
(3 ጊዜ)

+++ ለከ ንፌኑ ስብሐተ ወለከ ነዓርግ አኮቴተ፤


ላንተ ምሥጋናን እንልካለን፥ላንተም ምሥጋናን እናሳርጋለን፤

🙏 መሐረነ መሐሪ ኃጢአተነ አስተሥሪ፤


ይቅር ባይ ሆይ ይቅር በለን፥ ኃጢአታችንንም አስተስርይልን፤

+++ ወአድኅነነ፤
አድነንም፤

🙏 ወተማህፀን ነፍሰነ ወሥጋነ፤


ነፍሳችንንና ሥጋችንን ጠብቅ፤

+++ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር፤


የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ሆይ!

🙏 አምላክነ፥
አምላካችን

+++ ወመድኃኒነ
መድኃኒታችን

🙏 ኢየሱስ ክርስቶስ ተሣሃለነ፤


ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ይቅር በለን፤

+++ በብዝኃ ምሕረትከ፤


በምሕረትህ ብዛት፤

🙏 ደምስስ አበሳነ፤
በደላችንን አጥፋልን፤

+++ ወፈኑ ሣህለከ ላዕሌነ፤


ይቅርታህንም ወደኛ ላክልን፤

🙏 እስመ እምኀቤከ፤
ባንተ ዘንድ ነውና፤

+++ ውእቱ ሣህል፤


ይቅርታ፤

🙏 ሃሌ ሉያ፥ መሐረነ አብ መሐሪ፤


ሃሌ ሉያ፥ ይቅር ባይ አባት ሆይ ማረን፤

+++ ወተሣሃለነ፤
ይቅርም በለን፤

🙏 ሀብ ሣህለከ መሐሪ ፤
ይቅር ባይ ሆይ! ይቅርታህን ላክ፤

+++ ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፤


ያለፈው በደላችንን አስበህ አታጥፋን፤

🙏 በምህረትከ፤
በይቅርታህ፤

+++ እስመ መሐሪ አንተ፤


አንተ ይቅር ባይ ነህና፤

🙏 በብዙኅ ሣህልከ ለኩሎሙ እለ ይጼውዑከ፤


ለሚጠሩህ ሁሉ ይቅርታህ ብዙ ነው፤

+++ ይጼውዑከ በጽድቅ፤


በእውነት ለሚጠሩህ፤

🙏 ሰማዒ ወትረ፤
ሁልጊዜ ሰሚ ነህ፤
+++ ከሃሊ ዘውስተ አድኅኖ፤
በማዳን ጊዜ ቻይ ነህ፤

🙏 ከሃሊ፤
ቻይ፤

+++ ዘውስተ አድኅኖ፤


በማዳን ጊዜ፤

🙏 ለአምላክነ እስመ ጽድቅ ቃሉ፤


የአምላካችን ቃሉ እውነት ነው፡፡

+++ ንስአሎ ለአብ፤


አብን እንለምነው፤

🙏 ይፈኑ ለነ ሣህሎ፤
ይቅርታውን ይልክልን ዘንድ

+++ እስመ አብ የአክል ለዘሰአሎ፤


አብ ለለመነው ሁሉ ይበቃልና፤

🙏 ሃሌ ሉያ፤
ሃሌ ሉያ፤(ቅድመ ዓለም የነበረ፥አሁንም ያለ፥ድኅረ ዓለም የሚኖር )፤

+++ ስብሐት ሎቱ ይደሉ፤


ለርሱ ምስጋና ይገባል፤

🙏 ሃሌ ሉያ፥ አኮቴት ሎቱ ይደሉ፤


ሃሌ ሉያ፥ለርሱ ምስጋና ይገባል፤

+++ ሃሌ ሉያ ፤
ሃሌ ሉያ ፤

🙏 ለክርስቶስ ለእግዚአ ኵሉ፤


ለሁሉ ጌታ ለክርስቶስ ፤

+++ ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ፥ ሃሌ ሉያ፤


ሃሌ ሉያ፥ ሃሌ፥ ሃሌ ሉያ፤

🙏 ወይእዜኒ፤
አሁንስ(እንግዲህስ)
+++ መኑ ተስፋየ?
ተስፋየ ማን ነው?

🙏 አኮኑ
አይደለምን፤

+++ እግዚአብሔር፤
እግዚአብሔር

🙏 ውስተ እዴከ እግዚኦ አመኀጽን ነፍስየ፤


አቤቱ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ፤

+++ ኀበ አምላከ ምሕረት፤


ወደ ምሕረት አምላክ

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

+++ ኀበ ንጉሠ ስብሐት፤


ወደ ምስጋና ንጉሥ፤

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

+++ በእግዚእየ ወአምላኪየ፤


በጌታየና በአምላኬ፤

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አስጠብቃለሁ፤

+++ እምኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለኀፍስየ፤


ነፍሴን ከክፉ ሥራ ሁሉ አድናት፤

🙏 ኀበ አምላከ ምሕረት፤
ወደ ምሕረት አምላክ

+++ አመኀጽን ነፍስየ፤


ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

🙏 ኀበ ንጉሠ ስብሐት፤
ወደ ምስጋና ንጉሥ፤

+++ አመኀጽን ነፍስየ፤


ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

🙏 በእግዚእየ ወአምላኪየ፤
በጌታየና በአምላኬ፤

+++ አመኀጽን ነፍስየ፤


ነፍሴን አስጠብቃለሁ፤

🙏 እምኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለኀፍስየ፤


ነፍሴን ከክፉ ሥራ ሁሉ አድናት፤

+++ ኀበ አምላከ ምሕረት፤


ወደ ምሕረት አምላክ

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

+++ ኀበ ንጉሠ ስብሐት፤


ወደ ምስጋና ንጉሥ፤

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ፤

+++ በእግዚእየ ወአምላኪየ፤


በጌታየና በአምላኬ፤

🙏 አመኀጽን ነፍስየ፤
ነፍሴን አስጠብቃለሁ፤

+++ እምኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለኀፍስየ፤


ነፍሴን ከክፉ ሥራ ሁሉ አድናት፤

🙏 ሀቡ፤

+++ ንስአሎ፤
እንለምነው፤
🙏 ንስአሎ
እንለምነው፤

+++ ናስተምህሮ፤
ራራልን እንበለው (እንማልደው)፤

🙏 ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ ፤


እውነተኛ የሆነው አምላካችን ቃሉ እውነት ነውና፤

+++ ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ፤


ሁሉን የሚችል የሚሳነው ነገር የሌለ፤

🙏 አምላከ ነዳያን ናዛዜ ኅዙናን፤


የድሆች አምላክ ያዘኑትን የምታጽናና ሆይ!

+++ ንሕነ ኀቤከ ተማኅጸነ፤


እኛ ባንተ ተማጽነናል፤

🙏 ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ፤


ሁሉን የሚችል የሚሳነው ነገር የሌለ፤

+++ አምላከ ነዳያን ናዛዜ ኅዙናን፤


የድሆች አምላክ ያዘኑትን የምታጽናና ሆይ!

🙏 ንሕነ ኀቤከ ተማኅጸነ፤


እኛ በአንተ ተማጽነናል፤

+++ ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ፤


ሁሉን የሚችል የሚሳነው ነገር የሌለ፤

🙏 አምላከ ነዳያን ወተስፋ ቅቡፃን፤


የድሆች እና ተስፋ ለቆረጡ አምላካቸው፤

+++ ንሕነ ኀቤከ ተማኅጸነ፤


እኛ ባንተ ተማጽነናል፤

🙏 ወበከመ ዐቀብከነ እምነግህ እስከ ሠርክ ዕቀበነ እግዚኦ እምሠርክ እስከ ነግህ፤
ከጧት ጀምሮ እስከማታ እንደጠበቅከን ከማታ እሰከ ጧት ጠብቀን፤
✟✟✟(፫ ጊዜ በል በቅብብል)
+++ ተሣሃልከ እግዚኦ ምድረከ፥ሃሌ ሉያ፥ስማዕ ጸሎተነ ወስዕለተነ፥ ወስረይ ኵሎ
ኃጢአተነ፥ስማዕ ጸሎተነ ወስዕለተነ፥ዘሰማዕኮ ጸሎቶ ወስዕለቶ ለዕዝራ፥ተወከፍ
ምህላነ፥ሰላመከ ኀበነ ወእማዕከሌነ ኢትርሐቅ።

አቤቱ ርስትህን ይቅር በል፥ሃሌ ሉያ፥ጸሎታችንን እና አስተብቍኦታችንን ስማ፥ኃጢአታችንንም


ሁሉ አስተስርይልን፥የዕዝራን ጸሎትና ልመና የሰማህ ሆይ! ምህላችንን ተቀበል፥ሰላምህን
ስጠን፥ከመካከላችንም አትራቅ።

🙏 ወሚጥ መዓተከ እምኔነ፥ሃሌ ሉያ፥ንዒ ኀቤየ እንቲአየ፥ሠናይት ርግብየ፥መዓዛ አፉሃ ከመ


ኮል ወኵሉ ነገራ በሰላም።

አቤቱ ከኛ መዓትህን መልስ፥ሃሌ ሉያ፥ያማረች ርግቤ የአፏ እስትንፋስ እንደ እንኮይ ያማረ
ነው፥ንግግሯም ሀሉ ሰላማዊ ነው፥ርግቤ ሆይ! ወደ እኔ ነይ።​

+++ አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ ሃሌ ሉያ መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል፥ሰአል ወጸሊ


በእንቲአነ ፥አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ አቢይ።

የሰላማችን መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ!ስለኛ


ለምን፥ጸልይም፥ጸሎታችንንም ከታላቁ ንጉሥ መንበር ፊት አሳርግልን፡፡

🙏 ገብርኤል አብሠራ ለማርያም፥ወይቤላ ትወልዲ ወልደ፥ወይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም


ወአልቦ ማኅለቅት ለሰላሙ።

ቅዱስ ገብርኤል ድንግል ማርያምን አበሠራት፥እንዲህም አላት፥ልጅን


ትወልጃለሽ፥ለዘለዓለሙ ለያዕቆብ ቤት ይነግሣል፥ለመንግቱም ፍጻሜ የለውም።

+++ ዮሐንስ ክቡር ነቢየ ልዑል ብእሴ ሰላም ዘንብረቱ ገዳም

🙏 ሰዓል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ፥ሀረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ


ሥጋሁ ከመ ሐመድ፥ወወሰድዎ ኀበ ሰብዓ ነገሥት ፥ረገጸ ምድረ አባ ጊዮርጊስ አንሥአ ሙታን
፥በሰላም አደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! ወደ እግዚአብሔር ለምንልን፥ስለኛ ለምን፡፡


አረዱት፥ቆራረጡትም፥ሥጋውን ፈጭተው እንደ ትቢያ በተኑት፡፡ወደ ሰባ ነገሥታትም
ወሰዱት፥ምድርን ተረገጠ፥ሙታንን አስነሣ፡፡አባታችን ጊዮርጊስ በሰላም ከሞት ወደሕይወት
ተሻገረ፥ርስት መንግሥተ ሰማያትንም ወረሰ፡፡

+++ ብፁዐ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ በኀበ እግዚኡ፥ ይንሳእ እሴተ፥ቦአ
ገዳመ ደብረ ሊባኖስ በፍስሐ ወበሰላም።
ብፁዕ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በጌታው ዘንድ ዋጋን ያገኝ ዘንድ ወደ ገዳማት
የገሰገሰ፡፡በደስታና በሰላም ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገባ ፡፡

🙏 ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዝግባ ዘሊባኖስ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኖመ


ኖመ ኢየሩሳሌም በፍሥሐ ወበሰላም

+++ ሣህል ወርትዕ ተራከባ ጽድቅ ወሰላም ተሳዐማ አመ ተሰምዓ ዜናከ በዓለም ዜና
ማርቆስ ክቡር መምህረ ሰላም ዘህላዌከ ገዳም

🙏 ባርከነ አባ እንሣእ በረከተከ፥በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን፥ ሳሙኤል አባ


ባርከነ እንሣእ በረከተከ።

አባ ሳሙኤል ሆይ! በረከትህን እቀበል ዘንድ ባርከኝ፥ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም ስትል
ባርከኝ፥በረከትህንም እቀበላለሁ።

+++ ባርከነ አባ ንንሣእ በረከተከ በእንተሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዘርዓ ቡሩክ አባ


ባርከነ ንንሣእ በረከተከ

አባ ዘርዓ ብሩክ ሆይ! በረከትህን እቀበል ዘንድ ባርከኝ፥ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም
ስትል ባርከኝ፥በረከትህንም እቀበላለሁ።

🙏 ባርከነ አባ ንንሣእ በረከተከ በእንተሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕፃን ሞዓ አባ ባርከነ


ንንሣእ በረከተከ

አባ ሕፃን ሞአ ሆይ! በረከትህን እቀበል ዘንድ ባርከኝ፥ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም


ስትል ባርከኝ፥በረከትህንም እቀበላለሁ።

+++ ማህደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ፥እሞሙ ለሰማዕት፥ወእኅቶሙ ለመላእክት፥ንዑ


ንስግድ ኵልነ ኀበ ማርያም እምነ።

አቤቱ ቸርነትህን አሳየን፥ሃሌ ሉያ፥የሰላማችን ማደሪያ የተቀደስሽ ድንኳን፥የሰማዕታት


እናታቸው፥የመላእክት እኅታቸው፥ኑ፤ሁላችንም ለእናታችን ለድንግል ማርያም እንስገድ።

🙏 መስቀል ብርሃን ለኩሉ ዓለም መሠረተ ቤተከርስቲያን ወሀቤ ሰላም መድኃኔዓለም


መስቀል ለእለ ነአምን መድኅን(ሰላመከ ሀበነ)

ለዓለም ሁሉ መስቀል ብርሃን ነው፡፡ የቤተክርስቲያን መሠረት እርሱ ነው፡፡ ሰላምን የሚሰጥ
ዓለምን የተቤዘህ አምላክ ሆይ ሰላምህን ስጠን፡፡

+++ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፥ሃሌ ሉያ፤


ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስ ቅዱስ የሃሉ ማዕከሌክሙ አኃው

የአብ ሰላም የወልድ ሰላም የመንፈስ ቅዱስ ሰላም በመካከላችሁ ይኑር፡፡

🙏 ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስ ቅዱስ የሃሉ ማዕከሌክሙ አኃው


የአብ ሰላም የወልድ ሰላም የመንፈስ ቅዱስ ሰላም በመካከላችሁ ይኑር፡፡

+++ ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስ ቅዱስ የሃሉ ማዕከሌክሙ አኃው

የአብ ሰላም የወልድ ሰላም የመንፈስ ቅዱስ ሰላም በመካከላችሁ ይኑር፡፡

✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟

ይ.ካ. ሰላመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወፍቅራ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ
አምላክ ሞገሰ መስቀሉ ወሀብተ ረድዔቱ የሃሉ ምስለ ኵልነ ሕዝበ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም።

✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ

በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ

✟✟✟በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ሰአሊ ለነ ማርያም ምሕረተ ወልድኪ የሐውጸነ


ማርያም። ሰአሊ ለነ ማርያም ለለሰዓቱ ተግባረ እደዊሁ ለወልድኪ ኢንጥፋ በከንቱ። ኲሎ
መዓልተ ወኲሎ ሌሊተ ብዙኃ ኃጢአተ ዘገበርነ በእንተ ማርያም እምከ ተማኅጸነ።

✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟

ሥመር እግዚኦ ከመ ታድኅነነ። ኢታርምም እግዚኦ ወኢትጸመመነ ተዘከር እግዚኦ ከመ መረት


ንሕነ።

እግዚኦ ዕቀባ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ።


እግዚኦ አእርፍ ነፈሳተ አግብርቲከ ወአእማቲከ ኲሎሙ ክርስቶሳውያን።
እግዚኦ አድህን ለኩልነ ሕዝበ ክርስቲያን።
✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟✟
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፥ሃሌ ሉያ፤
ለዓለምና ለዘለዓለም፥ሃሌሉያ፤

You might also like