Professional Documents
Culture Documents
ምሳሌ
➛ ምንት መጽአ ናሁ? (አሁን ምን መጣ?)
• ከልብ መጽአ። (ውሻ መጣ።)
➛ ምንተ ታፈቅር ? (ምንን ትወዳለህ?)
• አነ አፈቅር ግብር ፡፡ (እኔ ሥራ እወዳለሁ፡፡)
➛ ምንት ገበርከ ናሁ ? (አሁን ምን ሠራኸ?)
• ግብረ ቤት ገበርኩ ፡፡ (የቤት ሥራ ሠራሁ፡፡)
➛ ምንት ገበርኪ ትማልም ? (ትናንት ምን ሰራሽ?)
• አንበብኩ መጽሐፍ ትማልም ፡፡ (ትናንት መጽሐፍ አነበብኩ፡፡)
➛ ምንት ተመሀርክሙ ትማልም? (ትናንት ምን ተማራችሁ?)
• በእንተ አድዋ ተማሀርነ ትማልም፡፡ (ትናንት ስለ አድዋ ተማርን፡፡)
➛ ምንተ ታፈቅሩ አርድእት ? (ተማሪዎች ምንን ትወዳላችሁ?)
• ንሕነ ናፈቅር ተውኔት ፡፡ (እኛ ጨዋታ እንወዳለን፡፡)
ክፍል ፬
፫ . ለጠይቆተ ጊዜ (When - Asking times)
• ማዕዜ - መቼ
• እስከ ማዕዜ - እስከ መቼ
ምሳሌ
➛ ማዕዜ ተወለድከ ? (መቼ ተወለድክ) • በወርኃ መስከረም ፡፡ (በመስከረም ወር)
➛ ማዕዜ ማዕዜ ውእቱ ትምህርተ ግእዝ? (የግእዝ ትምህርት መቼ መቼ ነው)
• ዕለተ ሐሙስ ወ ዕለተ ዓርብ ፡፡ (ዕለተ ሐሙስ ና ዕለተ ዓርብ)
➛ ማዕዜ ውእቱ ፈተና ? (ፈተና መቼ ነው)
• ጌሠም ውእቱ ፈተና ፡፡ (ፈተና ነገ ነው)
➛ ማዕዜ ተሐውሪ ኀበ ቤተ ክርስቲያን ? (ወደ ቤተ ክርስቲያን መቼ ትሄጂያለሽ)
• በዕለተ ሰንበት ፡፡ (በዕለተ እሑድ)
➛ ማዕዜ ይመጽእ መምህር ? (መምህር መቼ ይመጣል)
• ጌሠም ይመጽእ መምህር ፡፡ (መምህር ነገ ይመጣል)
➛ እስከ ማዕዜ ውእቱ ዘትመጽእ ? (እስከ መቼ ነው የምትመጣው)
• እስከ ዘይመጽእ ወርኀ ፡፡ (እስከ ሚመጣው ወር)
ክፍል ፭
፬ . ለጠይቆተ መካን (ቦታ) (Where - Asking place)
• አይቴ ➾ የት
• ኅበ አይቴ ➾ ወዴት
• እም አይቴ ➾ ከየት
ምሳሌ
➛ አይቴ ውእቱ ቤተ ትምህርትከ ? (ትምህርት ቤትህ የት ነው)
• ጎንደር ውእቱ ፡፡ (ጎንደር ነው)
➛ አይቴ ይእቲ እምኪ ? (እናትሽ የት ናት)
• አክሱም ይእቲ እምየ ፡፡ (እናቴ አክሱም ናት)
➛ አይቴ ተወለድኪ ? (የት ተወለድሽ)
• አነ አዲስ አበባ ተወለድኩ፡፡ (እኔ አዲስ አበባ ተወልድኩ ፡፡)
➛ ኅበ አይቴ ተሐውሪ ? (ወዴት ትሄጂያለሽ)
• ኅበ ቤተ ትምህርት ፡፡ (ወደ ትምህርት ቤት)
➛ፍሡሕ አነ በተራክቦትነ…
• በመገናኘታችን ደስተኛ ነኝ።
➛ሰላም ለከ ወፍሡሕ አነ በአእምሮተ ኪያከ…
• ሰላም ላንተ ይሁን አንተን በማወቄ ደስተኛ ነኝ።
፩.፫ ምድብ ተውላጠ ስሞች መራሕያን
➛ መራሕያን : መርሐ = መራ መራሒ = የመራ መራሕያን = መሪዎች ወይም መርሖ = ቁልፍ መራሕያን =
ቁልፎች ማለት ነው፡፡
➛ ስፍን ውእቱ ? ስንት ናቸው ? = ዐሠርቱ ውእቱ፡፡ 10 ናቸው፡፡
➛ ባለቤት መራሕያን
ውእቱ = እርሱ ወንድ፣ ነጠላ ፣ሩቅ
አንተ = አንተ ወንድ፣ ነጠላ፣ቅርብ
ውእቶሙ = እነርሱ ወንዶች፣ብዙ፣ሩቅ
አንትሙ = እናንተ ወንዶች፣ቅርብ፣ብዙ
ይእቲ = እርሷ ሴት፣ነጠላ፣ሩቅ
አንቲ = አንቺ ሴት፣ ነጠላ፣ቅርብ
ውእቶን = እነርሱ ሴቶች፣ብዙ፣ሩቅ
አንትን = እናንተ ሴቶች፣ቅርብ፣ብዙ
አነ = እኔ ነጠላ
ንሕነ = እኛ ብዙ
➛ በመደብ ሲከፈሉ የሚከተለውን ይመስላሉ፡፡
፩. አነ = እኔ
ንሕነ = እኛ
፪. አንተ = አንተ
አንትሙ = እናንተ
አንቲ = አንቺ
አንትን = እናንተ
፫. ውእቱ = እርሱ
ውእቶሙ = እነርሱ
ይእቲ = እርሷ
ውእቶን = እነርሱ
1ኛ መደብ ሩቅም ቅርብም አይደሉም፡፡ ምክንያቱም ሩቅ ቅርብ ለማለት ንጽጽር ያስፈልጋል። 2ተኛ መደብ
ቅርብ ናቸው፡፡ 3ተና መደብ ሩቅ ናቸው፡፡
፩. ፬ ነባር አንቀጽ ( የመሆን ግስ )
➛ ግስ : ድርጊትን የሚገልጡ ቃሎች ናቸው፡፡
ምሳሌ፦ ሞተ = ሞተ (የነፍስ ከሥጋ መለየትን)
መስየ = መሸ (መዓልቱ አልቆ ሌሊቱ የመተካቱ)
ሀበነ = ስጠን ( ልመናን )
ጸልዩ = ጸልዩ ( የአምላክ ትእዛዝን ያመለክታል )
ምሳሌ፦
ሰበከ፣ኀደገ፣መርሐ፣ቶስሐ፣ሴመ፣ሴጠ፣በርሀ፣አጸንሕሐ፣ተንበለ፣ጦመረ፣ዖደ፣ዐደመ(ቀጠረ)፣አደመ፣ሬመ
መለከ፣ነጸረ፣ዘመረ፣መነነ፣ረድአ፣ኀደፈ፣ሠረቀ፣ደፈነ፣ፈተለ፣ሰደደ፣ሰገደ፣ዐረበ፣ገብረ፣ወጽአ፣መስየ፣ኀረየ
ውህዘ፣ሴመ፣ሰተየ፣ሴሰየ፣መርሐ፣አኀዘ፣ቆመ፣ከብደ፡፡
እነርሱም ፦ አድራጊ
አስደራጊ
አስደራራጊ
ተደራራጊ
ተደራጊ
➛ ሁሉም የግእዝ ግሶች ሥርወ ግስ (መነሻ ግስ) አላቸው፡፡ እነዚህም መነሻ ግሶች በ 7ቱም ሆሄ ሊጀምሩ
ይችላሉ የሚጨርሱት ግን በግእዝ ወይም በመጀመርያ ሆሄ ነው፡፡
ምሳሌ ፦ ሥርወ ግሥ ማለት ይበላል ይብላ ወ.ዘ.ተ ከማለቱ በፊት ሁሉም የመጡበት በላ የሚለው ቃል ነው፡፡
ይሄዳል ሄዶ ሲሄድ መሄድ አካሂዶ የሄደ የሄደች ………… ሄደ የሚለው ቃል ነው፡፡
በተመሳሳይ በግእዙም ሰገዱ ስግዱ ሰገድክሙ ሰገዳ ሰጊድ ስግደት ንስግድ …. ሰገደ የሚለው ቃል ነው፡፡
ቡሩክ ቡሩካን ቡርክት መባረክ ባራኪ ቡራኬ ባርኮ ….. ባረከ የሚለው ቃል ነው፡፡
፩) ዝንቱ፣ዝ___ይህ
፪) ዛቲ፣ዛ_ይህች
፫) ዝኵ፣ዝስኵ፣ዝክቱ____ያ
፬) እንታክቲ፣ እንትኵ____ያች
፭) እሉ፣ እሎንቱ___እነዚህ
፮) እላ፣እሎን፣ እላንቱ፣__እነዚህ (ሴ)
፯) እልኰን፣ እልክቶን___እነዚያ(ሴ)
፰) እልኵ፣ እልክቱ____እነዚያ
በዓረፍተ ነገር ባለቤት ሆነው ሲያገለግሉ ለምሳሌ ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ ለዓለም።ትርጉሙ ለዘለዓለም ማረፊያየ ይች
ናት ማለት ነው። ቅጽል ሆነው ሲያገለግሉ ዳህንኑ ዝስኵ አቡክሙ ይላል። ትርጉሙ ያ አባታችሁ ደህና ነውን ማለት
ነው። ተሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ። አፍቅር ዛተ ቢል ያችን ውደዳት ማለት ነው።
።
የ"ዘ፣እለ፣እንተ" አስሩ ዝርዝርም ተናበው አመላካች የሚሆኑበት ጊዜ አለ። ትርጉማቸውም እንደሚከተለው ነው።
፩) ዚኣሁ/እንቲኣሁ___የእርሱ
፪) ዚኣሆሙ/እንቲኣሆሙ__የእነርሱ
፫) ዚኣሃ/እንቲኣሃ___የእርሷ
፬) ዚኣሆን/እንቲኣሆን__የእነርሱ
፭) ዚኣከ/እንቲኣከ___የአንተ
፮) ዚኣክሙ/እንቲኣክሙ__የእናንተ
፯) ዚኣኪ/እንቲኣኪ___የአንቺ
፰) ዚኣክን/እንቲኣክን___የእናንተ
፱) ዚኣየ/እንቲኣየ____የእኔ
፲) ዚኣነ/እንቲኣነ_የእኛ
ሲናበቡ አመልካች ቅጽል ይሆናሉ። ለምሳሌ ሀገረ ዚኣነ ቢል ትርጉሙ የእኛ ሀገር ማለት ነው። ሕይወተ ዚአኪ ሲል
የአንቺ ሕይወት ተብሎ ይተረጎማል። የእኔ ሀገር ለማለት ዚኣየ ሀገር አይባልም። ከዚያ ይልቅ ሀገረ ዚኣየ ይላል እንጂ።
እንተ ለሴት ሲሆን፣ ዘ ደግሞ ለሴት ለወንድ ለአንድ ለብዙ ይሆናል። እለ ለብዙ ይሆናል።ሲዘረዘርም እንደሚከተለው
ነው።
፩) እሊኣሁ___የእርሱ
፪) እሊኣሆሙ__የእነርሱ
፫) እሊኣሃ____የእርሷ
፬) እሊኣሆን___የእነርሱ
፭) እሊኣከ____የአንተ
፮) እሊኣክሙ___የእናንተ
፯) እሊኣኪ____የአንቺ
፰) እሊኣክን___የእናንተ
፱) እሊኣየ____የእኔ
፲) እሊኣነ____የእኛ
ይላል። ለምሳሌ እልመክኑን ወረደ ውስተ ዓለም ወእሊኣሁ ሰቀልዎ ሲል ትርጉሙ ጌታ ወደ ዓለም ወረደ የእርሱ
ወገኖችም ሰቀሉት ተብሎ ይተረጎማል።
ምዕራፍ ፪
፪.፩ ሰላምታ አሰጣጥ በግእዝ
ሰላምታ
በግእዝ ቋንቋ ሰላምታ ለመለዋወጥ የምንጠቀማቸው ቃላት:-
ጠዋት ላይ:-
እፎ ኀደርከ__እንዴት አደርክ
እፎ ኀደርኪ__እንዴት አደርሽ
እፎ ኀደርክሙ__እንዴት አደራችሁ
እፎ ኀደርክን__እንዴት አደራችሁ
እፎ ኀደርክን የምንለው ሴቶች ብቻ ካሉ ነው። ሴቶችና ወንዶች ተቀላቅለው ካሉ በአንትሙ እፎ ኀደርክሙ ይሄዳል።
ከሰዓት ደግሞ:-
እፎ ወዐልከ___እንዴት ዋልክ
እፎ ወዐልኪ___እንዴት ዋልሽ
እፎ ወዐልክሙ__እንዴት ዋላችሁ
እፎ ወዐልክን___እንዴት ዋላችሁ
ምሽት ሲሆን ደግሞ እፎ አምሰይከ፣ እፎ አምሰይኪ፣ እፎ አምሰይክሙ፣ እፎ አምሰይክን ይላል ማለት ነው። ለዚህ ሁሉ
መላሹ "እግዚአብሔር ይሰባሕ" ይላል። እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ነው። ሌላ የሰላምታ ዓይነቶችም አሉ:-
ሰላም ለከ___ሰላም ለአንተ ይሁን
ሰላም ለክሙ_ሰላም ለእናንተ ይሁን
ስላም ለኪ__ሰላም ለአንቺ ይሁን
ሰላም ለክን__ሰላም ለእናንተ ይሁን
ይላል ማለት ነው። በተጨማሪም እንዴት አደርክ እንዴት ዋልክ ሰላም ነህ ወይ ለማለት አንድ ቃል አለ። ይኽውም:-
።
በሐከ_እንዴት ዋልክ/አደርክ፣ሰላም
በሐኪ_እንዴት ዋልሽ/አደርሽ፣ሰላም
በሐክሙ_እንዴት ዋላችሁ/አደራችሁ፣ ሰላም
በሐክን_እንዴት ዋላችሁ/አደራችሁ፣ ሰላም
፪.፪ ግእዝ ንባብ
ፍኖተ ንባብ ዘልሳነ ግእዝ
{የግእዝ ቋንቋ የንባብ መንገድ)
-ይህንን ማወቅ ግእዝ ቋንቋን ለመናገርና ለማንበብ ይጠቅማል
-ይህም የሚዳብረው ሕጉን ተምሮ መጻሕፍትን ሲያናብቡበት ነው
-ለዚህም ልምምድ ከመዝሙር ዳዊት ላይ በምልክት ስለተቀመጠ እርሱን መላልሶ ማንበብ ነው
-እነዚህ የተቀመጠው ጉልህ የሆነው ሕግ ነው
-ውስጣዊ ሕጎች በየትምህርቱ ይገኛሉ
ንባብ ግእዝ
ምዕራፍ ፫
አገናዛቢ ዝርዝር
ተሳቢ መራሕያን አገናዛቢ መራሕያን
ኪያሁ = እርሱን ዚአሁ(ዘዚአሁ) = የእርሱ(ን)
ኪያከ = አንተን ዚአከ(ዘዚአከ) = ያንተ(ን)
ኪያሆሙ = እነርሱን ዚአሆሙ(ዘዚአሆሙ) = የእነርሱ(ን)
ኪያክሙ = እናንተን ዚአክሙ(ዘዚአክሙ) = የእናንተ(ን)
ኪያከሃ = እርሷን ዚአሃ(ዘዚአሃ) = የእርሷ(ን)
ኪያኪ = አንቺን ዚአኪ(ዘዚአኪ) = ያንቺ(ን)
ኪያሆን = እነርሱን ዚአሆን(ዘዚአሆን) = የእነርሱ(ን)
ኪያክን = እናንተን ዚአክን(ዘዚአክን) = የእናንተ(ን)
ኪያየ = እኔን ዚአየ(ዘዚአየ) = የእኔ(ን)
ኪያነ = አኛን ዚአነ(ዘዚአነ) = የእኛ(ን)
ሊተ = እኔን በ = በ
ለሊሁ = እርሱ እራሱ ቦቱ = በእርሱ
ለሊከ = አንተ እራሱ ብከ = ባንተ
ለሊሆሙ = እነርሱ ራሳቸው ቦሙ = በእነርሱ
ለሊክሙ = እናንተ ራሳችሁ ብክሙ = በእናንተ
ለሊሃ = እርሷ እራሷ ባቲ = በእርሷ
ለሊኪ = አንቺን ራስሽ ብኪ = በአንቺ
ለሊሆን = እነርሱ ራሳቸው ቦን = አላቸው
ለሊክን = እናንተ ራሳችሁ ብክን = በእናንተ
ለልየ = እኔ እራሴ ብየ = በእኔ
ለሊነ = አኛራሳችን ብነ = በእኛ
አልቦ = የለም በእንተ = ስለ
አልቦቱ = የለውም በእንቲአሁ = ስለእርሱ
አልብከ = የለህም በእንቲአከ = ስለአንተ
አልቦሙ = የላቸውም በእንቲአሆሙ = ስለእነርሱ
አልብክሙ = የላችሁም በእንቲአክሙ = ስለእናንተ
አልባቲ = የላትም በእንቲአሃ = ስለእርሷ
አልብኪ = የለብሽም በእንቲአኪ = ስለአንቺ
አልቦን = የላቸውም በእንቲአሆን = ስለእነርሱ
አልብክን = የላችሁም በእንቲአክን = ስለእናንተ
አልብየ = የለብኝም በእንቲአየ = ስለእኔ
አልብነ = የለብንም በእንቲአነ = ስለእኛ
እለ እንተ = የ ከመ = እንደ
እሊአሁ (እንቲአሁ) = የእርሱ ከማሁ = እንደ እርሱ
እሊአከ (እንቲአከ) = የአንተ ከማከ = እንደ አንተ
እሊአሆሙ (እንቲአሆሙ) = የእነርሱ ከማሆሙ = እንደ እነርሱ
እሊአክሙ (እንቲአክሙ) = የእናንተ ከማክሙ = እንደ እናንተ
እሊአሃ (እንቲአሃ) = የእርሷ ከማሃ = እንደ እርሷ
እሊአኪ (እንቲአኪ) = ያንቺ ከማኪ = እንደ አንቺ
እሊአሆን (እንቲአሆን) = የእነርሱ ከማሆን = እንደ እነርሱ
እሊአክን (እንቲአክን) = የእናንተ ከማክን = እንደ እናንተ
እሊአየ (እንቲአየ) = የእኔ ከማየ = እንደ እኔ
እሊአነ (እንቲአነ) = የእኛ ከማነ = እንደ እኛ
ኀበ = ወደ እምነ = ከ
ኀቤሁ = ወደ እርሱ እምኔሁ = ከእርሱ
ኀቤከ = ወደ አንተ በእንቲአከ = ስለአንተ
ኀቤሆሙ = ወደ እነርሱ በእንቲአሆሙ = ስለእነርሱ
ኀቤክሙ = ወደ እናንተ በእንቲአክሙ = ስለእናንተ
ኀቤሃ = ወደ እርሷ በእንቲአሃ = ስለእርሷ
ኀቤኪ = ወደ አንቺ በእንቲአኪ = ስለአንቺ
ኀቤሆን = ወደ እነርሱ በእንቲአሆን = ስለእነርሱ
ኀቤክን = ወደ እናንተ በእንቲአክን = ስለእናንተ
ኀቤየ = ወደ እኔ በእንቲአየ = ስለእኔ
ኀቤነ = ወደ እኛ በእንቲአነ = ስለእኛ
እለ እንተ = የ ከመ = እንደ
እሊአሁ (እንቲአሁ) = የእርሱ ከማሁ = እንደ እርሱ
እሊአከ (እንቲአከ) = የአንተ ከማከ = እንደ አንተ
እሊአሆሙ (እንቲአሆሙ) = የእነርሱ ከማሆሙ = እንደ እነርሱ
እሊአክሙ (እንቲአክሙ) = የእናንተ ከማክሙ = እንደ እናንተ
እሊአሃ (እንቲአሃ) = የእርሷ ከማሃ = እንደ እርሷ
እሊአኪ (እንቲአኪ) = ያንቺ ከማኪ = እንደ አንቺ
እሊአሆን (እንቲአሆን) = የእነርሱ ከማሆን = እንደ እነርሱ
እሊአክን (እንቲአክን) = የእናንተ ከማክን = እንደ እናንተ
እሊአየ (እንቲአየ) = የእኔ ከማየ = እንደ እኔ
እሊአነ (እንቲአነ) = የእኛ ከማነ = እንደ እኛ
መንገለ = ወደ ምስለ = ከ….ጋር
መንገሌሁ = ወደ እርሱ ምስሌሁ = ከእርሱ ጋር
መንገሌከ = ወደ አንተ ምስሌከ = ካንተ ጋር
መንገሌሆሙ = ወደ እነርሱ ምስሌሆሙ = ከእነርሱ ጋር
መንገሌክሙ = ወደ እናንተ ምስሌክሙ = ስለእናንተ
መንገሌሃ = ወደ እርሷ በእንቲአሃ = ስለእርሷ
መንገሌኪ = ወደ አንቺ በእንቲአኪ = ስለአንቺ
መንገሌሆን = ወደ እነርሱ በእንቲአሆን = ስለእነርሱ
መንገሌክን = ወደ እናንተ በእንቲአክን = ስለእናንተ
መንገሌየ = ወደ እኔ በእንቲአየ = ስለእኔ
መንገሌነ = ወደ እኛ በእንቲአነ = ስለእኛ
አልቦ = የለም ኅየንተ = ስለ
አልቦቱ = የለውም ኅየንቴሁ = ስለ እርሱ
አልብከ = የለህም ኅየንቴከ = ስለ አንተ
አልቦሙ = የላቸውም ኅየንቴሆሙ = ስለ እነርሱ
አልብክሙ = የላችሁም ኅየንቴክሙ = ስለ እናንተ
አልባቲ = የላትም ኅየንቴሃ = ስለ እርሷ
አልብኪ = የለብሽም ኅየንቴኪ = ስለ አንቺ
አልቦን = የላቸውም ኅየንቴሆን = ስለ እነርሱ
አልብክን = የላችሁም ኅየንቴክን = ስለ እናንተ
አልብየ = የለብኝም ኅየንቴየ = ስለ እኔ
አልብነ = የለብንም ኅየንቴነ = ስለእኛ
ሊተ = እኔን ኅየንተ = ስለ
ሎቱ = ለእርሱ ኅየንቴሁ = ስለ እርሱ
ለከ = ለእርሱ ኅየንቴከ = ስለ አንተ
አልቦሙ = የላቸውም ኅየንቴሆሙ = ስለ እነርሱ
አልብክሙ = የላችሁም ኅየንቴክሙ = ስለ እናንተ
አልባቲ = የላትም ኅየንቴሃ = ስለ እርሷ
አልብኪ = የለብሽም ኅየንቴኪ = ስለ አንቺ
አልቦን = የላቸውም ኅየንቴሆን = ስለ እነርሱ
አልብክን = የላችሁም ኅየንቴክን = ስለ እናንተ
አልብየ = የለብኝም ኅየንቴየ = ስለ እኔ
አልብነ = የለብንም ኅየንቴነ = ስለእኛ
፫.፪ አገናዛቢ ቅጽሎች
አገናዛቢ ቅጽል መራሕያን (possessive adjective pronouns) ደግሞ ቅጽል (adjective) ሲሆኑ ከስም
በፊት እየመጡ የባለቤትነትን ወይም ባለንብረትነትን ይገልጣሉ። ሁልጊዜ ከስም በፊት ይገኛሉ።
እሱም የሚከተሉት ናቸው ፦
፩) ዘዚአየ=የእኔ=My
፪) ዘዚአነ=የእኛ=Our
፫) ዘዚአከ=የአንተ=Your
፬) ዘዚአኪ=የአንቺ=Your
፭) ዘዚአክሙ=የእናንተ(ወ)=Your
፮) ዘዚአክን=የእናንተ(ሴ)=Your
፯) ዘዚአሁ=የእሱ=His
፰) ዘዚአሃ=የእሷ=Her
፱) ዘዚአሆሙ=የእነሱ(ወ)=Their
፲) ዘዚአሆን=የእነሱ(ሴ)=Their
ምሳሌ ፩፦ ወልድ=ልጅ (ስም)
ሀ) አነ ውእቱ #ዘዚአሃ ወልድ => እኔ #የእሷ ልጅ ነኝ፡፡
ለ) አንተ ውእቱ #ዘዚአየ ወልድ => አንተ #የእኔ ልጅ ነህ፡፡
ከምሳሌ ሀ) እንደምናየው "አነ ውእቱ ዘዚአሃ ወልድ".. ዘዚአሃ የሚለው አገናዛቢ መራሕያኑ "ወልድ" ከሚለው
ስም በፊት ነው የመጣው።
በምሳሌው መሠረት ሦስት ዓረፍተ ነገር ሥሩ።
የተሰጠን ስም፦ ብዕር = ብዕር (እስከብሪቶ)፣ መጽሐፍ = መጽሐፍ
የተሰጠን ግስ፦ ወሰደ = ወሰደ
ውእቱ ወሰደ #ዘዚአየ ብዕር => እርሱ #የኔን እስክብሪቶ ወሰደ።
አነ ወሰድኩ #ዘዚአከ መጽሐፍ => እኔ #የአንተን መጽሐፍ ወሰድሁ
እነዚህ መራሕያን ራሳቸው እንደ ስም ያገለግላሉ እንጅ ስም አይከተላቸውም፡፡
ምሳሌ
ሀ) ዝንቱ መጽሐፍ #ዚአሃ ውእቱ፡፡
ይህ መጽሐፍ #የእርሷ ነው
This book is #Hers.
ለ) ስመ ዚአየ == #የኔ ስም
ሐ) ዝ ግብር #ዚአሁ ውእቱ፡፡
ይህ ሥራ #የሱ ነው፡፡
መ) አነ ውእቱ ወልደ #ዚአከ፡፡
እኔ የእንተ #ልጅ ነኝ።
እነዚህ መራሕያን ባለንብረትነትን ይገልጣሉ። ከላይ ካየናቸው አገናዛቢ ቅጽል መራሕያን የሚለዩት ራሳቸውን ችለው
የሚቆሙ ከስም በኋላ የሚገኙ መሆናቸው ነው።
፩) ዚአየ=የእኔ=Mine
፪) ዚአነ=የእኛ=Ours
፫) ዚአከ=የአንተ=Yours
፬) ዚአኪ=የአንቺ=Yours
፭) ዚአክሙ=የእናንተ(ወ)=Yours
፮) ዚአክን=የእናንተ(ሴ)=Yours
፯) ዚአሁ=የእሱ=His
፰) ዚአሃ=የእሷ=Hers
፱) ዚአሆሙ=የእነሱ(ወ)=Theirs
፲) ዚአሆን=የእነሱ(ሴ)=Theirs
በበይናት = በመካከል እርስ በርስ፤ በበይናቲነ/ እርስ በርሳችን /፤ በበይናቲሆሙ / እርስ በርሳቸው/፤ በበይናቲክሙ / እርስ በርሳችሁ/
ምሳሌ
ዘትፈቅድ ለርእስከ ግበር ለካልእከ = ለራስህ የምትፈልገውን ለሌላው አድርግ፡፡
ሰማእክሙ ዘተብህለ ለቀደምትክሙ / ተብህለ = ተባለ/
ቀደምትክሙ ሰገዱ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ
ክልኤሆሙ ሖሩ ወብልዑ ኅብስተክሙ
ተፋቀሩ በበይናቲክሙ
ተማከርነ በበይናቲነ
ተሰአሉ በበይናቲሆሙ / ተሰአለ፣ ተጠያየቀ/
ኩልነ አግብርተ እግዚአብሔር ንሕነ
መጽኡ ኩሎሙ ወሰአሉ በእንተ ንጉሦሙ
ሑሩ ኩልክሙ ኀበ ቤትክሙ ለክሙ
ኩሎሙ ነቢያት አስከ ዮሐንስ ተነበዩ
መጻእኩ እምብሔር ርኁቅ ባሕቲትየ
ዝንቱ ብእሲ ነበረ ውስተ ቤቱ ለባሕቲቱ
ዘበልዐ ባሕቲቶ ይመውት ባሕቲቶ
ነጠላ ብዙ
ሊተ = የእኔ ፣ ለእኔ ፣ ልኝ ለነ = ለእኛ
ለከ = ላንተ፣ ልህ ለክሙ = ለእናንተ ላቹሁ
ለኪ = ላንቺ፣ ልሽ ለክን = ለእናንተ / ለሴት/ ላቹሁ
ሎቱ/ሎ/ = ል፣እርሱ ሎቶ/ሎቶሙ/ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንድ/
ብየ = በኔ፣ ብኝ፣ አለኝ ብነ = በእኛ ብን አለን
ብከ = በአንተ፣ አለህ ብክሙ = በእናንተ፣ ባችሁ ፣አላችሁ
ብኪ = በአንቺ አለሽ ብክን= በእናንተ፣ ባችሁ አላቹሁ/ለሴቶች/
ቦቱ/ ቦ/ = በት አለው ፣ በእርሱ ቦኑ/ ቦቶሙ/ = አላቸው፣ አላችሁ ባቸው/ለወንዶች/
ባቲ/ ባ/ = ባት ቦን / ቦቶን/ = አላቸው፣ አላችሁ፣ ባቸው /ለሴቶች/
ላቲ= ለእርሷ ሎሙ = ለእነርሱ / ለወንዶች/ ፣ባቸው
ምሳሌ
ምዕራፍ ፮ መስተአምር