You are on page 1of 7

ሀገር በቀል መድኃኒት እና ወረርሽኝ

ሰልሞን ተሾመ (ድ/ር)

በተሇያዩ ዘመናት ዓሇማችንን ያስጨነቁ በርካታ ወረርሽኞች ተከስተዋሌ፡፡ በወረርሽኞቹም ሳቢያ በርካታ
ሕዝብ ሇሞት ተዲርጓሌ፡፡ በላልች የዓሇም ሀገራት መነሻቸውን አዴርገው በኢትዮጵያ የተስፋፉና በርካታ
ሕዝብ ሇሞት የዲረጉ ወረርሽኞች በርካታ ናቸው፡፡ ከእነዚህ መካከሌ በተሇምድ የህዲር በሽታ በመባሌ
የሚታወቀው ወረርሽኝ አንደ ነው፡፡ ወረርሽኙ የህዲር በሽታ የተባሇው በኢትዮጵያ በመስከረም ወር
መታወቅ ቢጀምርም በከፍተኛ ዯረጃ የተስፋፋው በህዲር ወር ስሇሆነ ነው፡፡

‹‹
የህዲር በሽታ ስፓኒሽ ፍል›› ወይም ‹‹
ፓንዯሚክ ፍለ›› በመባሌ የሚታወቅ የኢንፊልዌንዛ ወረርሽኝ
ነው፡፡ ወረርሽኙ እ.ኤ.አ ከ1918-1920 ዴረስ በበርካታ የዓሇም ሀገራት የተዛመተ ሲሆን ከ20 እስከ 50
ሚሉዮን የሚገመት ሰው ገዴሎሌ፡፡ ይህ ወረርሽኝ በአገራችንም በ1911 ዓ.ም በህዲር ወር ተከስቶ
ከፍተኛ ቁጥር ያሇውን ሕዝብ ሇሞት ዲርጓሌ፡፡

የህዲር በሽታ በአዱስ አበባ ከተማ ምን ያህሌ ጉዲት እንዲዯረሰና የነበረውን ጭንቀት በስፍራው
‹‹
ተገኝተው የተመሇከቱትን መርስዔ ኀዘን ወሌዯ ቂርቆስ የሏያኛው ክፍሇ ዘመን መባቻ›› በሚሌ
መጽሏፋቸው እንዯሚከተሇው ይገሌጻለ፡፡

በ1911 ዓ.ም የበሽታ መቅሰፍት በኢትዮጵያ ሊይ ወርድ ብዙ ሰው አሇቀ፡፡ በሽታው አዱስ


‹‹
አበባ ዯርሶ በጣም የታወቀው በህዲር ወር ስሇሆነ በህዝብ ቃሌ የህዲር በሽታ›› የሚሌ
‹‹
ስም ወጣሇት፡፡ ፈረንጆች ግን የበሽታውን ስም ግሪፕ›› ብሇውታሌ፡፡ በሀገራችንም
አንዲንዴ ሰዎች ‹‹ቸነፈር›› ብሇውት ነበር፡፡

በሽታው ቀዯም ብል አውሮፓ ሊይ በዓሇም ጦርነት ምክንያት ስሇተነሳና ብዙ ሕዝብ


ስሇፈጀ ይኸው ወሬም ከመስከረም ጀምሮ ተሰምቶ ነበር፡፡ ወዯ አገራችንም በንፋስ
ተዛምቶ መጣና ከጥቅምት ጀምሮ ጥቂት በጥቂት በአንዲንዴ ሰው ቤት መግባትና መጣሌ
ጀመረ፡፡ በህዲር ወር ግን አብዛኛውን ሰው ስሇነዯፈው ከተማው ተጨነቀ፡፡

በሽታው እንዯ ሳሌና እንዯ ጉንፋን አዴርጎ ይጀምርና በበሽተኛው ሊይ ትኩሳት


ያወርዴበታሌ፡፡ ከዚያም ላሊ ያስሇቅሳሌ፣ ነስር ያስነስራሌ፣ ተቅማጥና ውጋት
ያስከትሊሌ፣ አንዲንደንም አእምሮውን ያሳጣዋሌ፡፡ እንዱህ እያዯረገ በሶስት በአራት ቀን
ይገዴሇዋሌ፡፡ ከአራት ቀን ያሇፈ በሽተኛ ግን ከሞት ማፋረሱ ነው፡፡ ሆኖም ከግርሻ
መጠንቀቅ ነበረበት፡፡

አንዲንዴ ስፍራ ቤተሰቡ በሙለ ይታመም ስሇነበር አስታማሚ በማጣት በርሃብና በውኃ
ጥም ብዙ ሰው ተጎዲ፡፡ ስሇዚህ በአዱስ አበባ ከተማ በየቀኑ ሁሇት፣ ሶስት መቶ ከዚያም
በሊይ ይሞት ጀመር፡፡ በአንዴ መቃብርም ሁሇቱን ሶስቱን ሬሳ እስከመቅበር ተዯረሰ፡፡
አንዲንድቹንም ሰዎች ሬሳ ተሸካሚ በማጣት በየግቢያቸው ውስጥ ቀበሯቸው፡፡

አፍሊው በሽታ ከህዲር 7 እስከ 20፣ ሇ14 ቀን ያህሌ ነበር፡፡ በተሇይም ህዲር 12 ቀን
የህዲር ሚካኤሌ ዕሇት ብዙ ሰው ሞተ፡፡ ….. በዚያ ሰሞን መቃብር የሚቆፍርና ሬሳ
ተሸክሞ የሚወስዴ ሰው ሇማግኘት ችግር ሆነ፡፡ በቤተሰብ ውስጥ ከበሽታው ያመሇጡ
ሲገኙ ሁሇት ሰዎች ሬሳ ተሸክመው እየወሰደ ይቀብራለ፡፡

ባሌ ሚስቱን፣ አባት የሌጁን ሬሳ እየተሸከመ ወስድ ቀበረ፡፡ ዯግሞ አንደ መቃብር


ይቆፍርና ሬሳ ሇማምጣት ወዯ ቤት ሄድ፣ ሬሳ ይዞ ሲመሇስ ላሊው ቀብሮበት ያገኘዋሌ፡፡

ቤተሰቡ በሙለ በታመመበትም ስፍራ ብዙዎቹ በየቤታቸው እየሞቱ አውሬ በሊቸው፡፡


ሇጉዲይ ወዯ አዱስ አበባ የመጣ እንግዲም እየታመመ መግቢያ ቤት አጥቶ በየመንገደ
እየወዯቀ አውሬ በሊው፡፡

በማሇት በወቅቱ የነበረውን አሳዛኝ ሁኔታ ይገሌጻለ፡፡ በተመሳሳይም የህዲር በሽታን አስከፊነት በሏረር
‹‹
ከተማ ያዩት ሌዐሌ ራስ እምሩ ኃይሇሥሊሴ፤ ካየሁት ከማስታውሰው›› በሚሇው መጽሏፋቸው ሊይ
እንዱህ ሲለ ገሌጸውታሌ፡፡

በሺህ ዘጠኝ መቶ አሥራ አንዴ ዓመተ ምህረት በሮፓና በእስያ አዴርጎ የመጣው የንፋስ
(የግሪፕ) በሽታ በኢትዮጵያም በመሊው አገር ገብቶ ብዙ ሰው ሞተ፡፡ ያንጊዜም ሏረር
ነበርኩ፡፡ እዚሁም ሏረርጌ ከህዲር ወር ጀምሮ እስከ ጥር መጨረሻ ሰሞን ዴረስ በጣም
ከፍቶ በከተማው ውስጥ ብቻ እንኳን ከሰማንያ እስከ መቶ ሃያ በየቀኑ ይሞት ነበር፡፡
የታመመው ሰው ሌክ አሌነበረውም፡፡
በሽታውም ትኩሳቱ በጣም እየበዛ፣ እራስ እያዞረ፣ አእምሮ እያጠፋ፣ ዯም እያስታወከ
ነው፡፡ በቶልም ካንደ ወዲንደ የሚተሊሇፍ በመሆኑ ብዙም ቤተሰብ እንዲሇ እየተኛ
አስታማሚው ብዙ ችግር ሆነ፡፡ የነበሩት ጥቂት ሏኪሞች ምንም ያህሌ ሰው ሇማዲን
አሌቻለም፤በሽታው እያጣዯፈ የሚገዴሌ ስሇሆነ፡፡

በማሇት የሕመሙን አስከፊነት ይገሌጻለ፡፡ በህዲር በሽታ ምክንያት አዱስ አበባ ከተማ የሞተው ሕዝብ
ቁጥር 9 ሺህ፤ በመሊው ኢትዮጵያ ዯግሞ እስከ 40 ሺህ ይሆናሌ ተብል እንዯሚገመት መርስዔ ኀዘን
ወሌዯ ቂርቆስ ይገሌጻለ፡፡ በዚህ በሽታ ሳቢያ ከሞቱ ታዋቂ ግሇሰቦች መካከሌ በአዱስ አበባ ከተማ ከንቲባ
ወሰኔ ዛማኔሌ፣ በዴሬዯዋ ከተማ ነጋዴራስ አፈወርቅ ገብረየሱስ ይጠቀሳለ፡፡

እነዚህን መሰሌ የዓሇማችን አስጨናቂ ወረርሽኞች በርካታ ህዝብን ጨርሰዋሌ፡፡ ከእነዚህ ወረርሽኞች
በማህበረሰቡ የራሱን ሀገር በቀሌ ዕውቀት መሰረት በማዴረግ በሽታዎችን ሲከሊከሌና ጤንነቱን ሲጠብቅ
ቆይቷሌ፡፡ አሁንም እየተከሊከሌ ይገኛሌ፡፡

ሇፎክልር ጥናት መሰረት የፎክ ዕውቀት (Folk knowledge) ነው፡፡ የፎክ ዕውቀት ማሇት በአንዴ
በተወሰነ ሕዝብ፣ ማህበረሰብ፣ ባህሌ ወይም አካባቢ ውስጥ ያሇ ሌዩ ዕውቀት ነው፡፡ ይህ ዕውቀት
የተሇያዩ ህዝባዊ ቴክኖልጂዎችን፣ ክህልቶችንና ውስብስብ ዕውቀቶችን የሚይዝ በመሆኑ ሇማህበረሰቡ
ህይወት መሰረት ነው፡፡

የፎክ ዕውቀት ማህበረሰቡ በህይወት ዘመን ተመክሮው ያጠራቀመው፣ የትውሌዴን ሌምዴ የሚወክሌ፣
የማህበረሰቡን ማንነትና የእዴገት ዯረጃ የሚያሳይ በመሆኑ ሌዩ ትኩረት ሉሰጠው የሚገባ የዘመን
ሙከራ አሻራ ነው፡፡

በፎክ ዕውቀት ዘርፍ ውስጥ ከሚካተቱ ሌዩ ሌዩ ዕውቀቶች መካከሌ ሀገር በቀሌ የህክምና ዘዳ አንደ
ነው፡፡ በተሇያዩ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚከሰቱ የተሇያዩ የጤና ችግሮች መነሻ ምክንያታቸውን ሇማወቅና
ችግሩንም ሇመፍታት ማህበረሰቡ ባሇው ባህሌ መሰረት ሇረጅም ዘመን የተጠቀመባቸውና አሁንም
እየተጠቀመባቸው ያለ የፎክልር ዕውቀቶች በሀገረሰባዊ ህክምና (Folk Medicine) ዘርፍ ውስጥ
ይመዯባለ፡፡

የዓሇም የጤና ዴርጅት (2001) ስሇሀገረሰባዊ ህክምና ብያኔ ሲሰጥ ሀገረሰባዊ ህክምና ጤና ነክ
ዴርጊቶችን፣ የአቀራረብ መንገድችን፣ ዕውቀትንና እምነቶችን፣ እፀዋትን፣ እንሰሳትን፣ ማዕዴናትን፣
መንፈሳዊ ቁሶችንና መንፈሳዊ ክዋኔዎችን መሰረት በማዴረግ ህመሞችን የማወቅ፣ የመከሊከሌና
የመፈወስ ስርዓት እንዯሆነ ይገሌጻሌ፡፡
በማህበረሰቡ በሕይወት ውስጥ ሇሚያጋጥሙ የጤና ችግሮች መፍትሄ ሇማግኘት በሚሌ የማህበረሰቡ
አባሊት የሚከውናቸው አጠቃሊይ ዴርጊቶች በሀገረሰባዊ ህክምና ውስጥ የሚጠኑ ጉዲዮች ናቸው፡፡
እነዚህ ዴርጊቶችም ማህበረሰቡ ስሇ ህመምና ጤና ያሇው እሳቤ፣ ስሇህመምተኛው ያሇው አመሇካከት፣
ስሇህክምና ባሇሙያዎቹ ያሇው አመሇካከት፣ አንዴን የህመም አይነት ሇመሇየት የሚጠቀምበት ዘዳ፣
ሇበሽታዎቹ መከሊከያ ወይም ማጥፊያ የሚሆኑ መዴኃኒቶችን ከምን ከምን እንዯሚያዘጋጅ፣ እንዳት
እንዯሚያዘጋጅ፣ መቼ እና የት እንዯያሚዘጋጅ፣ የመዴኃኒቶቹ የአወሳሰዴ ስርዓት እና ሇህክምናው
የሚያስፈሌጉ ቅዴመ ሁኔታዎች የመሳሰለትን ነጥቦች ናቸው፡፡

ሀገረሰባዊ ህክምናዎች ማህበረሰቡ በረጅም ዘመን የህይወት ተመክሮው ባካሄዯው ምርምር በአካባቢው
የሚያገኛቸውን ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ግብዏቶችን በመጠቀም የራሱን ሕዝባዊ ዕውቀት መነሻ
በማዴረግ የሚያዘጋጃቸው ናቸው፡፡ ህክምናዎቹም በአካባቢው ሇሚከሰቱ የጤና ችግሮች ሁለ መፍትሄ
የሚሰጥባቸው፣ የጤና ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት የሚዯረጉ ቅዴመ ጥንቃቄዎች፣ ችግሮቹ ዲግመኛ
እንዲይከሰቱ የሚዯረጉ ዘሊቂ መፍትሄዎች ወዘተ. የሚሰጡበት ህዝባዊ ጥበቦች ናቸው፡፡

በዓሇማችን ሊይ በሚገኙ ህዝቦች ዘንዴ በርካታ የሀገረሰባዊ ህክምና አይነቶች አለ፡፡ እነዚህ የህክምና
አይነቶች እንዯማህበረሰቡ ባህሌ፣ ፍሌስፍና፣ ርዕዮተ ዓሇማዊ እይታና መሰሌ ሁነቶች የሚሇያዩ ናቸው፡፡
ሀገረሰባዊ ህክምናዎችን ማህበረሰቡ በሰው፣ በእንሰሳት እና በእፀዋት ሊይ የሚከሰቱ የጤና ችግሮችን
ሇመከሊከሌ ይጠቀምባቸዋሌ፡፡

ድን ዮዯር (1972) የተባሇው ዕውቁ የፎክልር ባሇሙያ ሀገረሰባዊ ህክምናዎችን ተፈጥሯዊ የሀገረሰብ
ህክምና (Natural folk medicine) እና እምነታዊ-ሀይማኖታዊ የሀገረሰባዊ ህክምና (Magico- religious
folk medicine) በሚሌ በሁሇት ይመዴባቸዋሌ፡፡

ተፈጥሯዊ የሀገረሰብ ህክምና የሚባለት ከተፈጥሮ የሚገኙ፣ ሇምግብነትና ሇመዴኃኒትነት ወይም


ሇመዴኃኒትነት ብቻ የሚያገሇግለ የተሇያዩ የእፀዋት ቅጠልች፣ ቅርፊቶች፣ ስራስር፣ ፍራፍሬ፣ ግንድች፣
የተሇያዩ ማዕዴናት፣ የተሇያዩ የእንሰሳት ተዋጽኦ ምርቶችንና የሰውና እንሰሳት ተረፈ ምርቶችን
በግብአትነት በመጠቀም የሚዘጋጁ ናቸው፡፡ እነዚህን ግብአቶች በመጠቀም እንዯማህበረሰቡ ባህሌ ሇሰው
ሌጅ፣ ሇእንሰሳትና ሇእፀዋት የጤና ችግሮች መፍትሄ ይሰጣለ፡፡

እምነታዊ- ሀይማኖታዊ የሀገረሰባዊ ህክምና የሚባለት ዯግሞ በተቋማዊና ተቋማዊ ባሌሆኑ


ሀይማኖቶች እንዱሁም በሀገረሰባዊ እምነቶች (ሇምሳላ፡- ዛር፣ ጥንቆሊ፣ አስማት ወዘተ.) ውስጥ
መንፈሳዊ ዋጋቸው ከፍተኛ የሆኑ መንፈሳዊ የህክምና ግብዏቶችን መሰረት በማዴረግ ጤና ነክ
ችግሮችን ሇመፍታት የሚከወኑ ዴርጊቶች ናቸው፡፡

በተሇያዩ ማህበረሰቦች ውስጥ በሚገኙ እምነቶችና ሀይማኖቶች የአስተምህሮ ስርዓት መሰረት የተሇያዩ
መንፈሳዊ ቁሳቁሶች እንዯመስቀሌ፣ የሀይማኖት መጽሏፍ፣ ጸበሌ፣ ዘምዘም፣ ክታብ ወዘተ. በመጠቀም፣
በቅደስ ስፍራዎች እንዯቤተክርስቲያን፣ መስጊዴ፣ የጸበሌ ቦታ፣ ሀገረሰባዊ ሀይማኖቶች የሚከወኑበት
ስፍራ ወዘተ. አማካኝነት፣ በሀይማኖቱ ወይም በእምነቱ ስርዓት ውስጥ ትሌቅ ስፍራ በሚሰጣቸው
ግሇሰቦች በሚዯረጉ ጸልቶች፣ ሇፈጣሪያቸው ወይም ላሊ ህመምን ያመጣሌ ብሇው ሇሚያምኑበት አካሌ
በሚያቀርቧቸው መስዋዕቶችና መሰሌ መንፈሳዊ ዴርጊቶች አማካኝነት የተሇያዩ በሽታዎችን የመሇየት፣
የመከሊከሌና የመፈወስ ስርዓቶች ይካሄዲለ፡፡

በተሇያዩ አገራት ከተፈጥሮ በሚገኙ ግብአቶች የሚዘጋጁ መዴኃኒቶችን መጠቀም የተሇመዯ ነው፡፡
በተሇይ በማዯግ ሊይ ባለ አገራት ሰማንያ እጅ (80%) የሚሆነው ህዝብ ከእፀዋት፣ ከእንሰሳትና
ከማዕዴናት የሚገኙ የህክምና ግብአቶችን ሇመጀመሪያ ዯረጃ ህክምናዎች የሚጠቀሙ መሆናቸውን
ጥናቶች ያሳያለ፡፡

ከኢትዮጵያ ህዝብ ውስጥም ሰማንያ እጅ (80%) የሚሆነው ህዝብ በአካባቢው የሚከሰቱ የጤና
ችግሮችን ሇመከሊከሌና መፍትሄ ሇማግኘት ሀገረሰባዊ ህክምናዎችን እንዯሚጠቀም የተሇያዩ ጥናቶች
ይጠቁማለ፡፡

በዓሇማችን ሊይ በሚሌዮን የሚቆጠሩ ህዝቦች ተፈጥሯዊ የመዴኃኒት ግብአቶችን በመጠቀም


ሇህመማቸው መፍትሄ እንዯሚያገኙና ከተፈጥሯዊ ግብአቶችም በአብዛኛው የእፀዋት ሀገረሰባዊ
መዴኃኒቶችን (Herbal lore) ይጠቀማለ፡፡ ሇዚህም ምክንያት በዋናነት ማህበረሰቡ በእፀዋት መዴኃኒቶች
ሊይ እምነት ስሊሇው፣ እፀዋቱ በአካባቢያቸው በቀሊለ ስሇሚገኙ፣ የእፀዋት መዴኃኒት ቀማሚ
ባሇሙያዎችን በማንኛውም ጊዜ ማግኘት ስሇሚቻሌና በህዝቡ የፍሊጎት መጠን በብዛት መገኘታቸው
እንዯምክንያትነት ይጠቀሳለ፡፡

በዘመናዊ የህክምና ሳይንስ መፍትሄ ያሌተገኘሊቸው ወይም ውስብስብ የህክምና ስራ የሚጠይቁ በርካታ
በሽታዎች በዓሇማችን ሊይ አለ፡፡ ነገር ግን የተሇያዩ የአገራችን ማህበረሰቦች ከእነዚህ በሽታዎች ሇመዲን
ተፈጥሯዊ መዴኃኒቶችን በሀገር በቀሌ ዕውቀት በመጠቀም መፍትሄ ያገኙሊቸዋሌ፡፡
በአገራችንም በሚገኙ በተሇያዩ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እነዚህን ተፈጥሯዊ የመዴኃኒት
አይነቶችን በመጠቀም በአካባቢያቸው ሇሚከሰቱ የተሇያዩ በሽታዎች መፍትሄ በመስጠት የራሳቸውን፣
የእንሰሳትንና የእፀዋትን ጤና ሇረጅም ዘመን ሲጠብቁ ቆይተዋሌ፡፡

የህዲር በሽታ በ1911 ዓ.ም ተከስቶ ከፍተኛ ጉዲት ባዯረሰብን በዚያ አስጨናቂ ወቅት ማህበረሰቡ ሀገር
በቀሌ መዴኀኒትን በመጠቀም ከበሽታው ተፈውሷሌ፡፡ ሌዐሌ ራስ እምሩ ኃይሇ ሥሊሴ በወቅቱ
ሇተከሰተው የህዲር በሽታ መዴኃኒት ምን እንዯሆነ እንዯሚከተሇው ገሌጸውታሌ፡፡

በሏኪሞቹም ምክር የ‹‹ካሉፕቱስ›› ቅጠሌ በየበሽተኞቹ ቤት እየተቀቀሇ በሊበቱ አየሩን


በመሇወጥና ትኩሱንም ውኃውን በማጠጣት ብዙ ሰው አሻሇ፡፡ በየቦታውም በሞተው ሰው
መቃብር ሊይ ኖራ በብዙ ተረጨበት፡፡ ይኸውም በሽታው እንዲይተሊሇፍ የሚያግዝ ነበረ፡፡

እሳቸው የ‹‹ካሉፕቱስ›› ቅጠሌ በሚሌ የገሇጹት የባህር ዛፍ ቅጠሌ ነው፡፡ የባህር ዛፍ ቅጠሌን በውኃ
በመቀቀሌ በመታጠን፣ ውኃውንም በመጠጣት ከወረርሽኑ ዴነዋሌ፡፡ የባህር ዛፍ ቅጠሌ፣ የሀረግሬሳ
ቅጠሌ፣ የዲማከሴ ቅጠሌ በሙቅ ውኃ ቀቅል መታጠን ከጉንፋን ጋር ቀረቤታ ያሊቸው መሰሌ
የኢንፊልዌንዛ ሕመሞች ፍቱን መዴኀኒት ነው፡፡ ማህበረሰቡ አሁንም ሇጉንፋንና መሰሌ ሕመሞች
እነዚህን እጸዋት ይጠቀማሌ፡፡

በአሁኑ ወቅትም ዓሇምን እያስጨነቀ የሚገኘው የኮሮና በሽታ (ኮቪዴ-19) ሇበርካታ ሕዝብ የሕይወት
ማሇፍ ምክንያት ሆኗሌ፡፡ በአገራችንም ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯሌ፡፡ ይህን ጽሐፍ በማዘጋጅበት ወቅት
በአገራችን 19 ሰዎች በበሽታው ተይዘዋሌ፡፡ የኢትዮጵያ ኢኖቬሽን እና ሳይንስ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ
ምሁራን በመሰራት ሊይ ያሇ ተስፋ ሰጪ ሀገር በቀሌ መዴኀኒት በሙከራ ሊይ መሆኑን ገሌጸዋሌ፡፡

ይህ ትሌቅ ተስፋ ነው፡፡ የራሳችንን ሀገር በቀሌ ዕውቀቶች ዕውቅና መስጠታችን፣ ሇእኛም ሆነ ሇዓሇም
መዴህን እንዯምንሆን አምነን ወዯ ተግባር መግባታችን እጅግ ዯስ ያሰኛሌ፡፡ ሇኢትዮጵያ ክብርም ነው፡፡

በአገራችን ከሚገኙ የተፈጥሮ መዴኃኒቶች አማካኝነት ሌክ እንዯ ኮሮና በሽታ ሁለ መዴኀኒት


‹‹
ባሌተገኘሊቸው በሽታዎች የተጠቁ ሰዎች እንዯሚፈወሱ ይታመናሌ፡፡ አረጋ እሸቱ የእኛን ለእኛ
መድኃኒት፤ የባህላዊና ዘመናዊ መድኃኒቶች ስብስብ›› በሚል ርዕስ ባሳተሙት መጽሐፍ ውስጥ ለካንሰር
ህመም መድኃኒት መኖሩን ገልጸዋል፡፡ መድኃኒቱም የቀይ ስር ቅጠሌ ጭማቂ ወይም የካሮት ስርና
ቅጠሌ በየቀኑ መጠጣት ወይም ጥሬ ቀይና ነጭ ሽንኩርት አዘውትሮ ከምግብ ጋር መመገብ ነው፡፡
በማሾላ ብሔረሰብ ሇቢጫ ወባ ባህሊዊ መዴኃኒት የበሶቢሊ (ኤፊያ) እና ‹‹ቀሸውሉታ›› ቅጠሌ በፀሏይ ሊይ
ካዯረቁ በኋሊ በሙቀጫ አንዴ ሊይ በመውቀጥ ደቄቱን ከውኃ ጋር በማዯባሇቅ በሽታው የያዛቸው
ሕጻናት ጠዋት በማሇዲ ምንም ምግብ ሳይቀምሱ እንዱጠጡ ይዯረጋሌ፡፡ የቢጫ ወባ የያዛቸው አዋቂዎች
ዯግሞ ይኸው የበሶቢሊ እና የ‹‹ቀሸውሉታ›› ቅጠሌ በዯንብ ከዯረቀ በኋሊ ተወቅጦ ደቄቱ በሲጃራ መሌክ
እንዱያጨሱት ይዯረጋሌ፡፡

‹‹
በጋሞ ብሔረሰብ ዯርዯሬ›› እና ‹‹
አክርሳ›› የሚባለ ተክልች ስር በአንዴ ሊይ በመውቀጥ ጭማቂውን
በጉበት በሽታ ሇተጠቁ ሰዎች እንዯ እዴሜያቸው በተሇያየ መጠን ይሰጣቸዋሌ፡፡ የጉበት መዴኃኒቱንም
‹‹
ጠላ›› በሚሌ ስያሜ ይጠሩታሌ፡፡

እነዚህንና መሰሌ ሀገር በቀሌ መዴኀኒቶች በሳይንሳዊ መንገዴ ማጥናት አስፈሊጊ ነው፡፡ የኮሮና በሽታን
ሇመከሊከሌ ነጭ ሽንኩርት፣ ዝንጅብሌ፣ ፊጦ፣ ልሚ፣ ዲማከሴ፣ የባህር ዛፍ ቅጠሌ ወዘተ. ይጠቅማለ
ብል በስማበሇው በመሻማት ከመጠቀም መታቀብ ይኖርብናሌ፡፡ በተቃራኒው ዯግሞ እነ ነጭ ሽንኩርት
ምንም ጥቅም የሊቸውም ብል ዜና ሇመስራት ከመሯሯጥ መቆጠብ ይኖርብናሌ፡፡

በእነዚህና መሰሌ ሀገር በቀሌ መዴኀኒቶች ሊይ ሰፊ ምርምር በማዴረግ ያሊቸውን ዘርፈ ብዙ


ጠቀሜታዎች ማወቅና መጠቀም አሁን ሊይ ግዳታችን ሆኗሌ፡፡ አሁን የኮሮና የስጋት ዯመና በአገራችን
ያንዣበበት ወቅት ነው፡፡ በመሆኑም በትክክሇኛ መረጃና ማስረጃ የምንመራበት እንጂ በአለባሌታ
የምንተራመስበት ወቅት አይዯሇም፡፡

You might also like