You are on page 1of 1

ሰው ምንድን ነው ?

ሰው ማለት ነፋሳዊነት፣ እሳታዊነት፣ ውኃዊነት፣ መሬታዊነት ባሕርያት ያሉት በነፍስ ተፈጥሮውም ነባቢት ለባዊትና ሕያዊት
የሆነች ነፍስ ያለችው ፍጥረት ነው፡፡ እንዲህ ብለን ግን የሰውን ተፈጥሮ ጠቅልለን መናገር አይቻለንም፡፡ ምክንያቱም ሰውን
ከሌሎች ፍጥረታት ይልቅ እጅግ ልዩ በሆነ መልኩ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል ተፈጥሮአልና፡፡ ስለዚህም ቅዱሳን አባቶች
እንዲህ ብለው ሰው ለሚለው ስያሜ ትርጓሜ ይሰጡታል፡፡

ከስጋ አንጻር

ሰው ከሥጋ አንጻር በባህርይው ከ አራቱ ባህሪያተ ሥጋ ማለትም ከ እሳት መሬት ውሃ እና ነፋስ የተፈጠረ በመሆኑ የጊዜ
ገብደ የተቀመጠለት የሚራብ የሚጠማ የሚደክም የሚዎድቅ የሚነሳ እንደሁም የሚሞት ባህርይ ያለው ፍጥረት ነው፡፡

መልክ (አርአያ) ማለትም ነው

መልክ (አርአያ) ማለት ሰው እግዚአብሔር አምላኩን ይመስል ዘንድ በተፈጥሮ የተሰጡት ባሕርያት ናቸው፡፡ እነዚህ ባሕርያት
ከሰው ፈጽሞ የሚወሰዱ አይደሉም፡፡ ብዙ ቅዱሳን አባቶች መልክ (አርአያ) ለሚለው ቃል ትርጉም ሲሰጡ ሲለያዩ ይታያሉ፡፡
ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዘፍጥረትን በተረጎመበት ድርሳኑ ላይ መልክ (አርአያ) ማለት ለሰው በተፈጥሮ ፍጥረታትን
ለሚገዛበት ባሕርይው የተሰጠው ስያሜ ነው ይላል እርሱ (ሙሴ) በእግዚአብሔር መልክ ሲል በምድር ያሉትን ሁሉ ሰው
የሚገዛቸው መሆኑን የሚያመለክተን ነው፡፡ በምድር ላይ ከሰው በላይ የሆነ ፍጥረት የለውም ይላል፡፡

You might also like