Professional Documents
Culture Documents
የጋራ-መኖሪያ-ቤት-መመሪያ.docx
የጋራ-መኖሪያ-ቤት-መመሪያ.docx
ቁጥር 08/2014
ጥር 2014 ዓ.ም.
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
ማዉጫ
መግቢያ......................................................................................................................................................................3
ክፍልአንድ፡-................................................................................................................................................................4
አንቀጽ 2፡ ትርጓሜ......................................................................................................................................................4
ክፍል ሁለት.................................................................................................................................................................5
ክፍል ሦስት..............................................................................................................................................................10
ክፍል አራት...............................................................................................................................................................12
2
መግቢያ
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ያስቀመጠዉን ራዕይ ከማሳካት አንጻር በመማር ማስተማር፣ በምርምርና ማህበረሰብ
አገልግሎት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር በርካታ ፋይዳ ያላቸዉን ተግባራት እየሰራ የሚገኝ ተቋም ሲሆን የትምህርት ሥራ
በአንድ በተወሰነ ወቅት ተከናውኖ የሚያበቃ ሳይሆን የተከታታይነት ባህርይ ያለው ሥራ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲዉ አሁን
ባሉትም ሆነ ወደፊት በሚያስገነባቸው የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለመምህራን በህግ ላይ ተመስርቶ
በመደልደል፤
ሀ) እየናረ በሚሄደዉ የቤት ኪራይ ወጪ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማድረግና የተረጋጋ ኑሮን በመፍጠር ህይወታቸውን
ለመምራት ለማስቻል፤
ለማጎለበትና ለማሳለጥ፤
ሐ) ለተማሪዎች ትምህርታዊ የምክር አገልግሎት ለመስጠትና በቅርብ የተማሪዎችን ችግር በጋራ ለመፍታት፤
መ) በመምህራን መካከል መቀራረብን፤ መማማርንና የጋራ ተግባቦትን በመፍጠር የሚያጋጥሙ ማህበራዊ ችግሮችን
ሠ) በወርክ ሾፕ፣ በላቦራቶሪ የሚደረጉ ረጅም ሰዓት የሚወስዱ ሥራዎችን ተረጋግተዉ እንዲሰሩ ለማገዝ፤
ጥራትና ብቃት ያለው እና የሥራ ሂደቱን የተሳካ ለማድረግ ከሚያስችሉ አበይት ተግባራት መካከል የመምህራን የጋራ
መኖሪያ ቤት ችግር ደረጃ በደረጃ በመቅረፍ የሥራ ተነሣሽነትን ማሳደግ አንዱ በመሆኑ፣ ዩኒቨርሲቲው በሶዶ ከተማ
የጋራ መኖሪያ ቤት ህንፃዎችን በራሱ ወጪ በመገንባት እና በመግዛት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለመምህራን ለመደልደል
የሚያስችሉ መመሪያዎችን በ 2006 ዓ.ም፣ 2007 ዓ.ም፣ 2011 ዓ/ም አዘጋጅቶ እየሰራ የቆዬ ብሆንም በአፈጻጻም ላይ
ክፍተቶች የታዩ በመሆናቸዉ ነባሩ መመሪያ እንዲሻሻል ከመምህራን በተለያዩ ጊዚያት ጥያቄዎች በመቅረባቸዉ
ምክንያት፤
ዩኒቨርሲቲው 225 ቤቶችን የያዘ 15 የጋራ መኖሪያ ቤት ህንፃዎችን በሁለት ሳይቶች ከቤቶች ልማት ኤጀንሲ
የገዛቸውን፣
አሁን በቴክኖሎጂና በኦቶና ካምፖሶች አገልግሎት እየሰጡ ያሉ 48 ቤቶችን የያዙ ሁለት ዘመናዊ ህንጻዎችን፣
እና
ዩኒቨርሲቲዉ በቀጣይ የሚገነባቸዉን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ግልፅና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ድልድል ለማድረግ
3
ክፍልአንድ፡-
አንቀጽ 1፡ አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት ድልደላ አፈጻጸም የዉስጥ መመሪያ ቁጥር
08/2014 ተብሎ ይጠቀሳል፡፡
አንቀጽ 2፡ ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ፡ -
2.1. ዩኒቨርሲቲ፡ ማለት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማለት ነዉ፡፡
2.2. ከፍተኛ አመራር ማለት ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ማለት ነዉ፡፡
2.3. መምህር ማለት በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ በተለያዬ ደረጃ ያሉ ተማሪዎችን በቋሚነት በማስተማር፣
በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራ ላይ የሚገኝ የዩኒቨርሲቲዉ አካዳሚክ ሰራተኛ
ማለት ነዉ፡፡
2.4. መካከለኛ አመራር ማለት ዳይሬክተሮች፣ የካምፓስ ዲኖች፣ የኢንስቲትዩት ዋና ኃላፊዎች፣ የኮሌጆች ወይም
ትምህርት ቤቶች ዲኖች እና ሌሎች በተመሳሳይ ማዕረግ የሚሰየሙ ኃላፊዎችን ያካትታል፡፡
2.5. መሠረታዊ አመራር ማለት የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ተባባሪ ዲኖች፣ ምክትል ዲኖች፣ ተባባሪ
ሬጅስተራሮች፣ ረዳት ሬጅስትራሮች፣ አስተባባሪዎች እና ሌሎች በተመሳሳይ ማዕረግ የሚሰየሙ ኃላፊዎችን
ያካትታል፡፡
2.6. የጋራ መኖሪያ ቤት ማለት ለማንኛውም የአካዳሚክ ዘርፍ ኃላፊ ወይም ባለሙያ (መምህር) ለመኖሪያነት
በውድድር ተደልድሎ የሚሠጥ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት ማለት ነው፡፡
2.7. ልዩ ቤቶች ማለት ለሌሎች የማይሰጡ ያለዉድድር በፕሬዚዳንትነት እና በምክትል ፕሬዝዳንትነት ለሚሾሙ
መምህራን የሚሰጥ መኖሪያ ቤት ማለት ነዉ፡፡
2.8. የአገልግሎት ዘመን ማለት በወላይታ ሶዶ ዪኒቨርሲቲ ወይም በአቻ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ወይም የመንግስት
ኮሌጆች በመምህርነት ያገለገሉበት እና በተቋማቱ የሰው ሀብት ጽ/ቤት ማህተም የተረጋገጠ ህጋዊ ማስረጃ የቀረበ
የሥራ አገልግሎት ማለት ነው፡፡
2.9. ጋብቻ ማለት አግባብነት ያለው የሀገርቱ ቤተሰብ ህግ ዕዉቅና ከሰጣቸዉ የጋብቻ አፈፃፀም ሥነ-ሥርዓቶች
በአንዱ መሠረት የተፈጸመ ጋብቻ ቢሆንም በወሳኝ ኩኔት ጽ/ቤት የተረጋገጠ ሆኖ በግልጽ የሚታይ የጥንዶች ፎቶ
ግራፍ ያለበት፣ ያረጋገጠዉ የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት ኃላፊ ፊርማ ያለበት እና የወሳኝ ኩነት ጽ/ቤት ማህተም ያረፈበት
የጋብቻ ሰነድ ማለት ነው፡፡
4
2.10. የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት ደልዳይ ኮሚቴ ማለት በዚህ መመሪያ አንቀጽ 13 ላይ የተዘረዘሩትን
የሚያጠቃልል ነዉ፡፡
2.11. ቤተሰብ ማለት ለዚህ መመሪያ ዓላማ ሲባል በዩኒቨርሲቲዉ የጋራ መኖሪያ ቤት በሚኖር መምህር ስር የሚተዳደሩ
ሰዎች ማለት ነዉ፡፡
2.12. አካል ጉዳተኞ ማለት የአካል ወይም የአዕምሮ ጉዳተኛ ሆነው ማየትና መስማት የተሳናቸዉ፣ በተሽከርካሪ ወንበር
ወይም በክራንች የሚሄዱ ወይም የከፋ የአካል ጉዳት ያለባቸውና ጉዳቱ በዓይነቱ ለረዥም ጊዜ /በዘላቅነት/ የዕለት
ተዕለት ተግባራቸው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያደርስ ማለት ነው፡፡
3.1 ይህ መመሪያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሚገኙ በሁሉም ካምፓሶች ተመድቦ ወይም ተቀጥሮ ለሚሰራ
የአካዳሚክ ዘርፍ ኃላፊ እና ባለሙያ (መምህር) ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
ክፍል ሁለት
4.1 የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ የሚደለደሉት በመማር ማስተማር፣ በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት እና በቴክኖሎጂ
ሽግግር ሥራ ላይ በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ በቀጥታ በመሳተፍ ላይ ለሚገኙ መምህራን ወይም ቤተሰብ ያላቸው
በትምህርት ላይ ለሚገኙ መምህራን ይሆናል፡፡
5.1. በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለመምህራን ቤት የሚሰጠው ምንም ዓይነት አድሎ በሌለበትና አንድ ወጥ ሥርዓትንና
አፈጻጸምን በተከተለ መልኩ ብቻ ይሆናል፡፡
5.2. መምህራን የዩኒቨርሲቲውን ዓላማ በማስፈጸም ረገድ ቀጥተኛ ሚና የሚጫወቱ በመሆናቸው የመኖሪያ ቤት
የማግኘት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡
5
5.3. የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ድልደላ በዋናነት የአካዳሚክ ማዕረግ እና ደረጃ፤ የአገልግሎት ዘመን፣ የሥራ ኃላፊነትን እና
ህጋዊ ጋብቻን እንደ መሰረታዊ መስፈርት በማድረግ ሌሎች ተጨማሪ ነጥቦች የሚሰጡበት መስፈርቶች ታክለውበት
በውድድር የሚፈጸም ይሆናል፡፡
6
6.5.1. የአገልግሎት ዘመን ከፍተኛው 25 ነጥብ የሚይዝ ሆኖ በሚከተለው መልኩ ተተንትኗል፡፡
6.5.1.1. በወላይታ ሶደ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ላገለገሉበት ለእያንዳንዱ አንድ ዓመት አገልግሎት ሁለት
ነጥብ አምስት (2.5) ነጥብ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
6.5.1.2. በትምህርት ሚኒስቴር ሥር ባሉ በሌሎች የመንግሥት አቻ ዩኒቨርሲቲዎች ለተሰጠ አገልግሎት
ለእያንዳንዱ ዓመት አንድ ነጥብ አምስት (1.5) ነጥብ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
6.5.1.3. በመንግሥት ኮሌጆች ለተሰጠ አገልግሎት ለእያንዳንዱ ዓመት አንድ (1) ነጥብ የሚሰጥ
ይሆናል፡፡
6.5.1.4. በእነዚህ ሁኔታዎች ረዥም አገልግሎት ላበረከተ መምህር የሚሠጠው ትልቁ ነጥብ 25 ብቻ ይሆናል፡፡
በዩኒቨርሲቲዉ ሰኔት ሌጅስሌሽን አንቀጽ 42.7 እና በስቭል ሰርቭስ አዋጅ ቁጥር 1064/2010 አፈጻጸም መመሪያ
2011 አንቀጽ 58(7) ስር በተደነገገዉ መሠረት ለሁሉም መምህራን በትምህርት ላይ የነበሩበት ዓመት የሥራ
ልምድ ሆኖ አያገለግልም፡፡ ይሁን እንጂ በሥራ ላይ ሆኖ ትምህርቱን ለተከታተለ መምህር ትምህርት ላይ የቆዬዉ
ዓመት ህጋዊ ማስረጃ ሲቀርብ የሥራ ልምድ ሆኖ ይያዛል፡፡
6.6. በዚህ መመሪያ መሠረት ቴክኒካል ረዳቶች ለጋራ መኖሪያ ቤት መወዳደር አይችሉም፡፡
እና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሮች፤
ዳይሬክተሮች፤
6.7.2.6. በሌላ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ በየትኛዉም የኃላፊነት ደረጃ ያገለገለ መምህር ላገለገለበት ለአንድ ዓመት 1.5
ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን በአጠቃላይ የአሥር ነጥብ 80% (8 ነጥብ) የሚያገኝ ይሆናል፡፡ በሌላ የመንግስት ኮሌጅ
7
በየትኛዉም የኃላፊነት ደረጃ ያገለገለ መምህር ለአንድ ዓመት 1 ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን ትልቁ ነጥብ የአሥር ነጥብ
6.8.1. በመካከለኛ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ መምህራን ለምሳሌ፡- ዲኖችና ዳይሬክተሮች ወይም
በእነዚህ ደረጃዎች በኃላፊነት አገልግለው ለነበሩ ኃላፊዎች ለእያንደንዱ ዓመት ሶስት (3) ነጥብ
አገልግለው ለነበሩ ለእያንዳንዱ ዓመት ሶስት (3) ነጥብ የሚሰጥ ሆኖ በአጠቃላይ ለአንድ ዙር
6.9 ከዚህ ከላይ በንዑስ አንቀጽ 6.7.2 እና 6.7.3 የተጠቀሱ ኃላፊዎች በተከታታይ ለሁለት ዙር (terms) ያገለገሉ ከሆነ
የሚያዘው ነጥብ የሁለቱም ዙር ሆኖ መካከለኛም ይሁን መሠረታዊ ኃላፊነት ቦታ ላይ ያገለገሉበት ትልቁ ነጥብ ከ 10
መብለጥ የለበትም፡፡
6.9.1 በሌላ በኩል ከአሁን በፊት በኃላፊነት ቦታ ላይ አገልግለው የነበሩና አሁንም በኃላፊነት
ነጥብ ይያዛል፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት ያገለገለበት የኃላፊነት ቦታ አሁን ካሉበት የተሻለ ከሆነ የበፊቱ የኃላፊነት ዉጤት
የሚያዝ ይሆናል፡፡
8
6.10. አሁንም ይሁን ቀድሞ በመካከለኛ ወይም በመሠረታዊ የሥራ ኃላፊነት ቦታ/ዎች ላይ አገልግሎ የነበረ መምህር
የአገልግሎት ጊዜዉ ከአንድ ሴሚስተር በታች ከሆነ የኃላፊነት አገልግሎት ዉጤት አያገኝም፡፡
6.11. ህጋዊ ጋብቻ ለፈጸሙ መምህራን የሚሠጥ ነጥብ
6.11.1. በአንቀጽ 2.9 መሠረት ህጋዊ ጋብቻ ስለመፈጸሙ በህጋዊ ማስረጃ የተረጋገጠ መምህር 10 ነጥብ ይሰጣል፡፡
በወሳኝ ኩነት ያልተረጋገጠ የጋብቻ ሰነድ ለጋራ መኖሪያ ቤት ዉድድር ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
6.11.2. ጋብቻ ፊቺ የፈተመ/ች መምህር የጋብቻ ዉጤት አይሰጠዉም፡፡
6.11.3. በዉድድር ወቅት አጠራጣሪ የሆነ የጋብቻ ሁኔታ ከተገኘ የጋራ መኖሪያ ቤት ደልዳይ ኮሚቴ በህጋዊ መንገድ
የሚያጣራ ሆኖ ጋብቻዉ ስህተት መሆኑ ከተረጋገጠ ከዉድድር ዉጪ ሆኖ በመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት የዉስጥ
አስተዳደር ደንብ/መመሪያ መሰረት የሚቀጣ ይሆናል፡፡
6.11.4. ባልና ሚስት በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መምህር ሆነው ለውድድር ሲቀርቡ የሚወሰደው ከሁለቱ የአንደኛው
ከፍተኛ ነጥብ ብቻ ይሆናል፡፡
6.11.5. ቤተሰብ ያለው መምህር ለትምህርት ቢሄድ ቤተሰቡ ማለትም ባለቤቱ እና ልጆች በተሠጠው ቤት እንዲኖሩ
ይደረጋል፡፡
6.12. በልዩ ሁኔታ የሚሰጥ ነጥብ
6.12.1. አካል ጉዳተኛ መምህር በዉድድር ጊዜ በአራቱ መሠረታዊ መስፈርቶች (አንቀጽ 6.1(ከሀ-መ)) ተወዳድሮ
ከመቶ በሚያኘዉ ነጥብ ላይ አካል ጉዳተኛ በመሆኑ 10 (አሥር) ነጥብ ይጨመራል፡፡
6.12.2 ይህ ተደምሮ በአጠቃላይ አካል ጉዳተኛ ተወዳዳር መምህር ባገኘዉ ነጥብ ልክ ለድልድል ከወጡ ቤቶች ዉስጥ
ልያገኝ ከሚችለዉ ተመሳሳይ ቤት ደረጃዎች መካከል ለራሱ የሚመቸዉን የመምረጥ ዕድል ይሰጣዋል፡፡
6.12.3 ሴት መምህሪት በዉድድር ጊዜ በአራቱ መሠረታዊ መስፈርቶች (አንቀጽ 6.1(ከሀ-መ)) ተወዳድራ ከመቶ
በሚታገኘዉ ነጥብ ላይ ሴት በመሆኗ ብቻ ተጨማሪ 7 (ሰባት) ነጥብ ይጨመርላታል፡፡ ነገር ግን ሴት መምህሯ አካል
ጉዳተኛ ከሆነች ከሁለቱ ተጨማሪ ነጥቦች ከፍተኛ ነጥብ የያዘዉ 10 ነጥብ ይያዝላታል፡፡
6.12.4. መምህሩ ህጋዊ ማስረጃ ሲያቀርቡ በአንድ ልጅ 1 ነጥብ የሚያገኙ ሆኖ የጉዲፈቻ ልጅ ወይም የእንጀራ ልጅ
ያለዉ መምህር ህጋዊ ሰነድ ሲያቀርብ የተጠቀሰዉን ነጥብ ያገኛል፤
6.12.5 ባልና ሚስት በዩኒቨርሲቲዉ መምህራን ከሆኑ ከሁለቱ አንዱ ባላቸዉ ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ዉጤት
መሠረት ተወዳድረዉ ቤት የሚያገኙ ሆኖ ከሁለቱ አንዱ የቤት አበል ያገኛል፡፡
9
ክፍል ሦስት
7.1. በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ዪኒቨርሲቲዎች በትምህርት ላይ ያሉ መምህራን በተረጋጋ ሁኔታ ተምረውና
ተመልሰው ዩኒቨርሲቲውን እንዲያገለግሉ ለማበረታታት ሚስቱ/ባሏ ወይም ህጋዊ ልጅ/ የዉድድር ሰነድ ይዘዉ
በመቅረብ ሊወዳደሩ ይችላሉ፡፡
7.2. በሥራ ላይ ሆኖ የሚማር የዩኒቨርሲቲያችን መምህር በቀጥታ በመማር ማስተማር፤ ምርምርና ማህበረሰብ
አገልግሎት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራ ላይ የሚሳተፍ ስለሆነ መወዳደር ይችላል፡፡
ለ). ቤቶቹ የሚገኙበት ወለል/የፎቅ ደረጃ ሲሆኑ በእነዚህ መሥፈርቶች መሠረት የሚከተሉት ደረጃዎች
ወጥቶላቸዋል፡፡
8.2 የመኖሪያ ቤቶች መኝታ ቤት ቁጥር/ብዛት፡-
ለመምህራን የሚደለደሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ካላቸው የመኝታ ቤት ብዛት አንጻር የሚከተለው ደረጃ ወጥቶላቸዋል፡፡
8.2.1. ባለ 3 መኝታ ቤቶች ………………… ደረጃ አንድ
10
8.2.2. ባለ 2 መኝታ ቤቶች ………………… ደረጃ ሁለት
8.2.3. ባለ 1 መኝታ ቤቶች ……………… ደረጃ ሦስት እና
8.2.4. ስቱዲዮ ቤቶች ……………….. ደረጃ አራት በመሆን ደረጃ ተሠጥቷቸዋል፡፡
1 ኛ) አዲስ ዘመናዊ ህንጻዎች በላይኛዉ የሠራተኞች መግቢያ በር ፊት ለፊት ላይ ያለዉ፤ አዲስ ዘመናዊ ህንጻ
ቴክኖሎጂ ካምፓስ እና አዲስ ዘመናዊ ህንጻ ኦቶና ካምፓስ፣
2 ኛ) 4M2 ብሎኮች፤
3 ኛ) 6S2 ብሎኮች እና
11
ይሆናል፡፡ ከዚያም የትምህርት ደረጃቸዉ ይታያል፡፡ በዚህም ሁሉ ተመሣሣይ ከሆኑ አሸናፊው በዕጣ ተለይቶ ቤቱን
ያገኛል፡፡
9.7. ዉድድር የሚደረገዉ ቤቶች በተለቀቁ በ 15 ቀናት ዉስጥ ቤቶቹን ከሚያስተዳድረዉ ክፍል ሪፖርት ከቀረበ በኋላ
ማስታወቂያ በማዉጣት በየሩብ ዓመት ይደረጋል፡፡
ክፍል አራት
10.1.5. በዩኒቨርሲቲው የመምህራን መኖሪያ ቤት ውስጥ የሚኖር መምህር ለሌላ የተሻለ ቤት የመወዳደር መብቱ
የተጠበቀ ነው፡፡ ሆኖም አዲስ የተወዳደረውን ቤት ካላሸነፈ ቀድሞ ሲኖርበት የነበረውን ቤት እንዲለቅ አይገደድም፡፡
10.1.6. በመኖሪያ ቤት ድልደላ ሂደትና አፈጻጸም ቅሬታ ያለው መምህር ውጤቱ በተገለጸ አምስት (5) የሥራ ቀናት
ውስጥ ቅሬታውን በማመልከቻ ለዩኒቨርሲቲዉ አስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
የማቅረብ መብት አለዉ፡፡
10.2. ተወዳድረው ቤት የሚያገኙ መምህራን ግደታ
10.2.1. በውል ከዩኒቨርሲቲው የተረከቡትን ቤት ለሌላ መምህር ማስተላለፍ አይቻልም፡፡
10.2.2. ቤቱን በውድድር ያገኘ መምህር የቤቱን ወለል፤ ግድግዳ፤ በርና ሌሎች መሠረታዊ ክፍሎች በጥንቃቄ
መገልገልና መጠበቅ አለበት፡፡ ነገር ግን በጥንቃቄ ጉድለት የተበላሸ ወይም የተሰበረ ዕቃ የማጠገን ወይም በአዲስ
የመተካት ግዴታ አለበት፡፡
10.2.3. መምህሩ ተወዳድሮ ያገኘውን ቤት ጡረታ ሲወጣ ለአንድ ዓመት እንዲኖር ይፈቀዳል፡፡ ነገር ግን አንድ ዓመት
ጊዜ እንደተጠናቀቀ ቤቱን ያስረክባል፡፡ አንድ መምህር ዩኒቨርሲቲዉን በዝውውርም ሆነ በሌላ ምክንያት ሲለቅ በ 1 ወር
ጊዜ ውስጥ ቤቱን እንዲለቅ ይደረጋል፡፡
10.2.4. ቤቱን ተወዳድሮ ያገኘ መምህር ቤቱ ላይ ጉዳት ማድረስ አይችልም፡፡ ነገር ግን በቤቱ ላይ ማሻሻያ ወይም
ማናቸውንም ዓይነት ለውጥ ካደረገ ያሻሻለበት ወይም የለወጠበት ክፍያ ገንዘብ እንዲመለስለት መጠየቅ አይችልም፡፡
10.2.5. መምህሩ ለትምህርት ሲሄድ የቤት ዉክልና መስጠት የሚችለዉ በቤቱ ውስጥ ለሚቀሩ ለባል ወይም ለሚስት
ሆኖ በልዩ ሁኔታ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሱ ልጆች የሚኖሩበት ከሆነ በዩኒቨርሲቲዉ ዕዉቅና በፍርድ ቤት ወይም
በሌላ ህጋዊ አካል ዉክልና የተሰጠዉ አካል ቤቱን ሊያስተዳድር ይችላል፡፡
12
10.2.6. መምህሩ ከተቋሙ ውጭ ርቆ የሄደ ከሆነና ራሱ ቤቱን ማስረከብ በማይችልበት ሁኔታ ላይ ከሆነ የእሱ ተወካይ
ቤቱን ማስረከብ ይችላል፡፡
10.2.7. የመኖሪያ ቤት በውድድር ያገኘ መምህር ከአስተዳደር ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ፈቃድ ሳያገኝ በራሱ ፈቃድ ቤቱን (የቤቱ ደረጃ ተመሳሳይ ቢሆን እንኳን) መቀያየር ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
በተጨማሪም ቤቱን ከወሰደ በኋላ ከሌላ ቦታ ቤተሰብ በማስመሰል ሌላ ሰዉን አምጥቶ ማስገባትም ሆነ አከራይቶ
መጠቀም አይቻልም፡፡
10.2.8. የቤት ድልድሉ ውጤት በአስተዳደርና ተማሪዎች ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ጸድቆ በግልጽ ማስታወቂያ
ሰሌዳ ላይ ተለጥፎ ደብዳቤ ለአሸናፊዎች እስኪገለጽ ድረስ ማንኛውም መምህር በተደለደለበት ቤት ዉስጥ መግባት
አይችልም፡፡ ተወዳድረዉ ቤት ያገኘ መምህር ውጤቱ በተገለጸ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በተደለደሉበት ቤት ካልገባ
አስ/ተ/አገ/ም/ፕ/ጽ/ቤት ቤቱን ለሚቀጥለው ተጠባባቂ መምህር ይሰጣል፡፡
10.2.9. ማንኛውም መምህር የመኖሪያ ቤት ሻወር ቤት ውስጥ ልብስ ማጠብ አይችልም፡፡
10.2.10. መምህራን የሚኖሩበትንም የጋራ መኖሪያ ቤት ግቢ ሆነ የአካባቢውን ጽዳት የመጠበቅና የማስጠበቅ ግዴታ
አለባቸዉ፡፡
10.2.11. የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤት ግቢ ዉስጥ የሚኖር መምህር በሚኖሩበት ህንጻ ወይም ሌሎች ግቢ ዉስጥ
ባሉ ህንጻዎች የሚኖሩ ሌሎች መምህራንና ቤተሰቦችን የሚያዉክ ወይም የመኖር መብታቸዉን የሚጎዳ ማንኛዉንም
ድርጊት ራሱ ወይም ቤተሰቡ መፈጸም የተከለከለ ነዉ፡፡
10.2.12. ማንኛውም መምህር አብረው ለሚኖሩ ቤተሰብ አባላት ዩኒቨርሲቲዉ የሚሰጠዉን መታውቂያ እንዲይዙ
ማድረግ ይኖርበታል፡፡
10.2.13. ማንኛውም መምህር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ ንግድ መንገድ፤ እንስሳትን ማርባትና የነዋሪውን ሰላምና ደህንነት
የሚያውኩ ማናቸውንም ተግባራት መፈጸም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
10.2.15. በዩኒቨርሲቲዉ የጋራ መኖሪያ ቤት ዉስጥ የሚኖር መምህር በመኖሪያ ቤቱ ዉስጥ ያሉ ንብረቶችን
(መብራት፣ ዉሃ፣ ወዘተ) በአግባቡ የመጠቀምና የመንከባከብ ኃላፊነት አለበት፡፡
10.2.16. ቤቱን ተወዳድሮ ያገኘ መምህር ከዩኒቨርሲቲው ጋር ውል ሳይገባ ቤቱን መረከብ አይችልም፡፡
10.2.17. አንድ መምህር ወይም ማንኛዉም ሰዉ ወደ መምህራን መኖሪያ ግቢ በሚገባበት ጊዜ በሚመለከተዉ አካል
ሲጠየቅ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ ማሳየት አለበት፡፡ እንዲሁም ንብረት ይዞ ሲገባም ሆነ ሲወጣ በሚመለከተዉ
አካል ሲጠየቅ ማሳየት አለበት፡፡
10.3 የዩኒቨርሲቲዉ ግዴታ
10.3.1. ዩኒቨርሲቲው የራሱን የጋራ መኖሪያ ቤቶችን 24 ሰዓት ጥበቃ መድቦ የማስጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡
10.3.2. የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ በእርጅና ወይም በዝናብና ሌሎች ተፈጥሯዊ በሆኑ ምክንያቶች እድሳት ወይም ጥገና
ስለሚያስፈልጋቸው ዩንቨርሲቲዉ ዓመታው የጥገና ሥርዓት በመዘርጋት ማሳደስ/ማስጠገን አለበት፡፡
10.3.3. ዩኒቨርሲቲው የጋራ መኖሪያ ቤቶቹን ዙሪያ አጥር ደረጃውን በጠበቀ አጥር ማሳጠር አለበት፡፡
13
10.3.4. የመኖሪያ ቤቶቹ በልዩ ልዩ አትክልቶች የተዋቡ፣ ለመኖር ማራኪና ምቹ እንዲሆኑ የዉበት ዛፎችንና
አትክልቶችን ያስተክላል፤ አትክልተኛን ይመድባል፡፡
10.3.5. ከነዋሪዎች ከተመረጡ ኮሚቴዎች ጋር በመነጋገርና አቅጣጫ በመንደፍ ቆሻሻ በዘመናዊ መንገድ
የሚወገድበትን ስልት ይነድፋል፡፡ ለአፈጻጸሙም አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል፡፡
10.3.6. ለጋራ መኖሪያ ቤቶች የውሃ ታንከሮችን፤ የጋራ ኩሽናዎችን፤ የጋራ ልብስ ማጠቢያ ገንዳዎችን ሁሉን
ተጠቃሚዎችን ባማከለ ሁኔታ ያዘጋጃል፡፡
10.3.7. የመማር መስተማር፣ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ወቅትን የተከተለ እና ሁል ጊዜ አዳዲስ
መረጃዎችን የሚፈልግ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ የዋይ.ፋይ (WI-FI) አገልግሎት ያሟላል፡፡
10.3.8. ዩኒቨርሲቲው ለመምህራን ቤት ሲያከራይ ሙሉ ጥገና ወይም እድሳት በማድረግ በሮች ከተሟሉ ቁልፎቻቸው
ጋር ሙሉ መሆናቸዉን፤ የበርና የመስኮት መስተዋቶች ያልተሰበሩ፤ የኤሌክትሪክና የውሃ መስመሮች የተሟሉ፣
ያልተበላሹ እንዲሁም ግድግዳና ወለል ንጹህ መሆናቸውን አረጋገግጠዉ በጋራ ስምምነት ውል ላይ በግልጽ ተጠቅሶ
በሚደረግ የውል ስምምነት የቤት ኪራዩን የማከናወን ግዴታ አለበት፡፡
10.3.9. ለመምህራን አመቺ የመኖሪያ አካባቢን ለመፍጠር የሚያስችሉ ሌሎች ተመሳሳይ ተግባራትን ያከናውናል፡፡
14
12.2. በጋራ መኖሪያ ቤቶቹ አስተዳደራዊ ጉዳዩች፤ ዲሲፒሊንና ሌሎች ተያያዥ ነገሮችን ዩኒቨርሲቲው የመወሰን መብት አለው፡
13.1. በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉትን ቤቶች ሁሉ ሁሉም ካምፓሶች ደረጃ ቤት ደልዳይ ኮሚቴ በሚከተለው ሁኔታ
ይዋቀራል፡፡
13.2. የዩኒቨርሲቲው የበላይ አካል በሴኔት ሌጅስሌሽን መሠረት የቤት ደልዳይ ኮሚቴ በማዋቀር የቤት ድልደላ ሂደቱን
የማስፈጸም ግዴታ አለበት፡፡
ክፍል አምስት
15
አንቀጽ፡-14 ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
14.1.1. በዚህ መመሪያ ላይ የተገለጹትን ግዴታዎችን ተላልፎ የሚገኝ መምህር ይህንን መመሪያ ለማስፈጸም
በሚወጣዉ በዩኒቨርሲቲዉ የመምህራን የጋራ መኖሪያ ቤቶች አስተዳደራዊ ልዩ መመሪያ መሰረት ተጠያቂነት አለበት፡፡
15.1. የአፈጻጸም ክፍተቶች ሲኖሩ ወይም ለሚመለከተው አስተዳደር አካል ጥያቄ ቀርቦ ሲወሰን ይህ መመሪያ ሊሻሻል ይችላል፡፡
16.1. ይህንን መመሪያ የሚቃረኑ ማንኛቸውም ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የመኖሪያ ቤቶች ጋር የሚገናኙ አሠራሮችና ቀደምት
መመሪያዎች በዚህ መመሪያ ስለተተኩ ተፈጻሚነት አይኖራቸዉም፡፡
ፊርማ-------------------
ፕሮፌሰር ታከለ ታደሠ
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
ፕሬዝዳነት
16
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ማመልከቻ ቅጽ፤
1. ስም ከነአያት _______________________________
በዩኒቨርሲቲው (ወሶዩ)___
በመንግሥት ኮሌጅ____
5. ሥራ፡-
6. የጋብቻሁኔታ
ያገባ _____
ያላገባ _____
የልጆችብዛት_____
ስም_____________________ ስም _____________________
ቀን______________ቀን________________ ማህተም
ማሳሰቢያ፡-
ትክክለኛመረጃ ብቻ ይሙሉ፣
17
በትምህርት ላይ የቆዩበት ጊዜ በአገልግሎት ዘመን ውስጥ አይካተትም፣
አዘጋጆች
ማጠቃቃሻ የተጠቀምናቸዉ
18
19