Professional Documents
Culture Documents
Students Regulation
Students Regulation
ትምህርት ቢሮ
የተሻሻለ ረቂቅ
0
በሀገራችን በየደረጃው የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማፍራት ት/ቤቶች የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
ትምህርት የዕድገት ሁሉ ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ ለሁለንተናዊ ልማት መፋጠን ትልቁን ድርሻ ይይዛል፣
ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊና ባህላዊ ዕድገቶችን የሚያፋጥን መሣሪያ ነው፡፡ በዚህ መሠረት ት /ቤቶቻችን
በሰከነና ቀልጣፋ አመራር የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማከናወን ይቻል ዘንድ የተማሪውን ስነምግባር
በተፈለገው አቅጣጫ ለማነፅ መብቱንና ግዴታዎቹን ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ
የትምህርት ተቋማት አንድ ወጥ የአመራርና የርምጃ አወሳሰድ አፈፃፀም መኖሩ ተገቢ በመሆኑ ይህ
የተሻሻለ የመጀመሪያ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት የተማሪዎች መተዳደሪያ መመሪያ በአዲስ አበባ
ይህ መመሪያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ የቅድመ መደበኛ፤ የመጀመሪያ ደረጃ፤ ሁለተኛ
ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት የተማሪዎች መተዳደሪያ መመሪያ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
አንቀፅ 2፡ ትርጓሜ
1
2.1. #ተማሪ$ ማለት በአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ በሚገኙ በመንግስትና በግል የመጀመሪያ
ደረጃ፣ ሁለተኛ ደረጃ፣ መሰናዶ ት/ቤት በመደበኛ እና በማታ የትምህርት ኘሮግራም በመማር ላይ
የሚገኙ ማለት ነው፡፡
2.2. #ቅጥር ግቢ$ ማለት ት/ቤቱ ከመንግስት ወይም በግል በባለቤትነት ወይም በኪራይ የያዘው እና
ለመማር ማስተማር አገልግሎት ወይም ስራ የሚሰጥበት ክልል ማለት ነው፡፡
2.3. #ትምህርት ቤት$ ማለት ማንኛውም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ የመጀመሪያ
ደረጃ፤ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ማለት ነው፡፡
2.4. #የተማሪ ዲስኘሊን ኮሚቴ$ ማለት ተማሪዎች መልካም ስነ-ምግባር ኖሮአቸው እንዲያድጉ ይቻል
ዘንድ ለማስተካከል በየት/ቤቱ የተቋቋመ ኮሚቴ ማለት ነው፡፡
2.5. “የደንብ ልብስ” ማለት በት/ቤቱ ማህበረሰብ የጋራ ስብሰባ በስምምነት የተመረጠ ለተማሪዎች
መለያነት የሚያገለግል ተመሳሳይ የጨርቅ ቀለም፤ ቅርፅ፤መጠን፤ጥራት እና አዘገጃጀት ያለው ልብስ
ነው፡፡
3.1. ተማሪዎች 1986 በወጣው የትምህርት እናስልጠና ፖሊሲ መሰረት ተምረው ሀገር ተረካቢ እንዲሆኑ
ለማስቻል፤
3.3. ተማሪዎች በትምህርት ላይ በሚቆዩበት ጊዜ በራስ የመተማመን መንፈስ በጋራ የመኖርና የመረዳዳት
ባህል እንዲያዳብሩ ለማስቻል፣
3.4. ተማሪዎች ለሀገራቸውና ለወገናቸው ተቆርቋሪ ችግር ፈችና መልካም ስነ ምግባር ያላቸው ዜጐች
ሆነው እንዲቀረጹ ለማስቻል፣
3.5. ተማሪዎች፣ የዲሞክራሲ ስርዓት፣ የህግ የበላይነትን፣ እኩልነትን፣ ፍትሐዊነትን፣ የሀገር ፍቅርን፣
የሀላፊነት ስሜትን፣ ጠንካራ የስራ ባህልን፣ ራስን የመቻል፣ የቁጠባ ባህልን ንቁ ህዝባዊ ተሳትፎንና
እውቀትን የመሻት ዕሴቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲችሉ፣
2
3.7. በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ለተመሳሳይ ጉዳዩች የሚሰጡ ውሳኔዎች
መዘበራረቅን በማስቀረት ተቀራራቢና ወጥነት ያለው አሰራር ለመዘርጋት፤
የማታ ተማሪዎችን ጉዳይ ሲታይ ሁለት የማታ ተማሪዎች ተወካዮች በቀን ተማሪዎች ምትክ
በኮሚቴ አባልነት ይሳተፋሉ፣
4.2. የኮሚቴው የሥራ ዘመን ሁለት አመት ይሆናል፤ ሆኖም አባላት እንደገና ሲሰየሙ ለአንድ ተጨማሪ
ዙር ለማገልገል ሊመረጡ ይችላሉ፣
4.4. በጐደለው የኮሚቴ አባላት ምትክ ክፍተት ሳይፈጠር በፍጥነት በየጊዜው እየታየ ይተካል፣
4.6.1. የኮሚቴው ስያሜ የተማሪዎች የዲስፕሊን ኮሚቴ የሚባል ሲሆን፤ ኮሚቴው ተጠሪነቱ ለር/መምህሩ
ይሆናል፡፡
3
በወረዳው ት/ጽ/ቤት ስር የምትሰራ ሴት የትም/ባለሙያ-------------------- አባል
7.1. ተማሪዎችን በሚመለከት የሚከሰቱ ማንኛውንም የዲስኘሊን ጉዳዮች የማየት ስልጣን አለው፣
7.2. ተማሪን ለአንድ አመት ከሚያገሉ ውሳኔዎችና ከነጭራሹ ከት/ቤት የሚያስወግዱ እርምጃዎች
በስተቀር ሌሎች የኮሚቴው ውሳኔዎች የመጨረሻ ይሆናሉ፡፡
7.3. ተማሪን ለአንድ አመት ከትምህርት ገበታ የሚያገሉና ከነጭራሹ ከት/ቤት የሚያስወግዱ የኮሚቴ
ውሳኔዎች የውሳኔ ሀሣብ በር/መምህሩ ቀርቦ ይፀድቃል፣
በወረዳ ደረጃ የተቋቋመው የዲስኘሊን ኮሚቴ በት/ቤት ደረጃ በተማሪዎች የዲስኘሊን ግድፈት ምክንያት
ለአንድ አመትና ከነጭራሹ የተባረሩ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤትን ተማሪዎችን ይግባኝ ይመለከታል፣
ይመረምራል፣ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል/ ያፀድቃል ወይም ይሽራል፡፡ኮሚቴው ተጠሪነቱ ለፅ/ቤቱ ኃላፊ
ይሆናል፡፡
በክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ደረጃ የተቋቋመው የዲስኘሊን ኮሚቴ በት/ቤት ደረጃ በተማሪዎች የዲስኘሊን
ግድፈት ምክንያት ለአንድ አመትና ከነጭራሹ የተባረሩ የሁለተኛ መሰናዶ ት/ቤቶች ተማሪዎችን ይግባኝ
በፍትሐዊነት ይመለከታል፣ ይመረምራል፣ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል/ ያፀድቃል ወይም ይሽራል፡፡ኮሚቴው
ተጠሪነቱ ለፅ/ቤቱ ኃላፊ ይሆናል፡፡
4
10.1. የመማር፣ ጠይቆ የመረዳትና የማወቅ ፣
10.2. በት/ቤቱ የትምህርት ግብዓቶች የመጠቀም ወይም አገልግሎት የማግኘት፣
10.3. የትምህርታቸውን ውጤትና የምስክር ወረቀት በወቅቱ የማግኘት፣
10.4. የት/ቤቱን የክፍል ውስጥ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መመሪያዎችን የማወቅና የማግኘት፣
10.5. ከመምህራን ጋር ተገቢ የሆነ የመማር ማስተማር ግንኙነት በመፍጠር ድጋፍና እርዳታ
የማግኘት፣
10.6. የሚደርስባቸውን በደልና ቅሬታ በየደረጃው ላሉ የት/ቤቱ አካላት የማቅረብ፣
10.7. ስለመምህራን የማስተማር ክህሎት የመገምገም አስተያየት ሲጠየቁ የመስጠት፣
10.8. ከመማሪያ ክፍል ውጭ የሚከናወኑ የተጓዳኝ ትምህርት ኘሮግራሞች ላይ የመሳተፍ፣
10.9. በትምህርት ቤት አደረጃጀቶች ውስጥ ለተማሪዎች ከሚሰጠው ልዩ ልዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ
የመምረጥና መመረጥ፣
10.10. ከት/ቤት ወይም በቅርብ ከሚገኝ የጤና ማዕከል የመጀመሪያ ዕርዳታ የማግኘት፣
10.11. በት/ቤት የዕቅድ ዝግጅትና የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ በተወካዮቻቸው አማካኝነት መሳተፍ፣
10.12. ተወካዮቻቸውን በየደረጃው ላሉ የኃላፊነት ቦታዎች የመምረጥ፣
ተጨማሪ የተማሪዎች መብትና ግደታ ይህንን መመሪያ በማይቃረን ሁኔታ በት/ቤቱ
መቅረብ ይችላል፡፡
11.3. በት/ቤቱ ውስጥና በዙሪያው ተማሪዎች በህይወታቸው ላይ ጉዳት ያደርሳሉ ተብሎ ከተከለከሉ
ሥፍራዎች እራስን ማራቅ፣
11.5. የክፍል ሥራ፤ የቤት ሥራ፤ የቡድን ሥራ የሚሰጡ የችሎታ መመዘኛዎችን ሠርቶ አጠናቆ በጊዜው
የማቅረብ፣
11.6. የት/ቤቱ ኃላፊዎችና መምህራን በአግባቡ የሚሰጡትን ድጋፍ ምክርና መመሪያ መፈፀም፣
5
11.9. ከማንኛውም የቡድን ጠብ አምባጓሮና ጉልበተኝነት ተግባር ራስን ማቀብ፣
11.12. የትምህርት ጊዜን በማይሻማ ሁኔታ ዕውቀቱንና ጉልበቱን ለትምህርት ቤቱና ለአካባቢው
ህብረተሰብ አገልግሎት የማዋል፣
11.14. የት/ቤቱን ንብረት የመጠበቅ / መቀመጫ ወንበሮችን፣ የመማሪያ ክፍሎችን፣ መስኮቶችን፣ ምድረ
ግቢውን በንፅህና መያዝና መንከባከብ/
11.19. በደንቡ አንቀፅ 17 መሰረት የተፈቀደውን ሥነ-ሥርዓት የተከተለ የደንብ ልብስ አለባበስና የፀጉር
አያያዝ መጠቀም፣
11.25. ሲጋራ አለማጨስ መጠጥ ጠጥቶ አለመገኘት ጫትና ሌሎች አደንዛዥ ዕጾችን አለመጠቀም፣
11.27. የስርቆት ወንጀል አለመፈፀም፣ ፈተና መኮረጅ ቁማር መጫወት ከመሳሰሉ ሕገወጥ ድርጊቶችና
ከሌሎተ ጥፋቶች መራቅ፣
6
10.28. በት/ቤት ግቢ መታወቂያ ይዞ መገኘት ሲጠየቅ የማሳየት፣
11.1.4. የክፍል ውስጥ ስነ-ስርዓትን ያለማክበር በክፍል መረበሽ መጮህ፣ መብራት ማጥፋት ወዘተ፣
11.1.5. በተደጋጋሚ ሁኔታ የቤት ሥራዎችን፣ የቡድን ሥራዎችን፣ የክፍል ሥራዎችን ያለመስራት ፣
11.2.1. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 11.1 የተመለከቱትን ጥፋቶች በተደጋጋሚ ለሚፈፅሙ ተማሪዎች የቤተ
ክፍል ሀላፊ የተማሪውን ሥነሥርዓት ለማስከበር ከተመረጡ ተማሪዎች ጋር በመሆን የተማሪውን በቀላል
የጥፋተኝነት ደረጃ በየጊዜው የተመዘገቡትን ጥፋቶች እየተከታተሉ የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ፣
ስለተሰጠው የምክር አገልግሎት መረጃ በተማሪው ማህደር ይቀመጣል፣
7
11.2.2. የተማሪው/ዋ ጥፋት መረጋገጥ በተማሪው የመማር ሁኔታ ላይ ችግር ይፈጥራል ተብሎ
ሲታመንበት ወላጅ በልጁ ጉዳይ እንዲመከርና በቂ መረጃ እንዲኖረው በመጥራት በጋራ እንደጥፋቱ ሁኔታ
በሶስት ተከታታይ ጊዜ የቤተ ክፍሉ ሀላፊ ለተማሪው የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ፣ የተማሪውን/ዋን ችግር
ለይቶ የማወቅ ስራ ይሰራል፣ ወላጅ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ይደረጋል፣
11.2.3. ተማሪው ከወላጁና ከቤተ ክፍሉ ኃላፊ የተሰጠውን የምክር አገልግሎት ተቀብሎ ተግባራዊ
ማድረግ ካልቻለ፣ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጠው ይደረጋል፣ ወላጆችም በአራተኛው የግንኙነት ጊዜ
ይህንን እንዲያውቁ ይደረጋል፣
12.1.የቤተ ክፍል ኃላፊው የተማሪዎቹን የዕለት ከዕለት የባህሪና ትምህርትን የመከታተል ሁኔታዎች
በተመለከተ በቂ መረጃ ከክፍል አለቃዎችና ከመምህራን በመውሰድ ተማሪውን/ዋን ሊገልጻት/ጸው
የሚችል መረጃ ይይዛል፡፡
12.2.ተማሪው/ዋ በት/ቤት ውስጥ ከትምህርት ገበታው/ዋ ሊያስወጣት የሚችል ሁኔታ ሲፈጠር የቤተ
ክፍሉ ኃላፊ ገላጭ የሆነ በየጊዜው የተመዘገበ መረጃ ከወላጁ ጋር የተደረገ ውይይት፣ ተማሪው
የፈረሙበትና ይቅርታ የጠየቁበት፣ ማስጠንቀቂያ የተሰጠ አጠቃላይ የተማሪውን/ዋን ባህሪ ሊገልፅ
የሚችል መረጃ ለት/ቤቱ ያቀርባል፣
12.3.ከላይ የተመለከተውን መነሻ በማድረግ በጊዜው ከተፈፀመ የባህሪ ግድፈት ጋር በማየት የት/ቤቱ
የዲስኘሊን ኮሚቴ በተማሪው/ዋ ላይ አግባብነት ያለው እርምጃ ይወስዳል፣
13.1. ት/ቤቱና ወላጅ ባላወቁት እና አሳማኝ ባላሆኑ ምክንያቶች ከት/ቤት በአመቱ የትምህርት
ካላንደር 2 ዐ% አለመገኘት፣
8
13.8. የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመጠቀም ተገቢ ያልሆነ ተግባር ማከናወን (ተማሪ የሚያወናብዱ
መረጃዎች ማስተላለፍ፤ኩረጃ ወዘተ)
አንቀፅ 14፡በማንኛውም ጥፋት በተደጋጋሚ የቤተ ክፍሉና ወላጅ ያደረጉትን ጥረት ተግባራዊ ባለማድረግ
በአንቀፅ አስራ አንድ ላይ በንዑስ አንቀፅ 11.2.3 ላይ የተመለከተውን የማስጠንቀቂያ ጽሁፍ
ተቀብሎ መስተካከል ያልቻሉ ተማሪ ለአንድ አመት ከት/ቤት ይታገዳል፣
15.4. በት/ቤት ውስጥና አካባቢ ሴት ወይም ወንድ ተማሪዎችን መድፈር ወይም ለመድፈር መሞከር፣
15.5. ያልተፈቀዱ ስብሰባ፤በዓላት የማክበር ስነ-ስርዓት ማድረግ፣ ሁከት መፍጠር፤ ማሳደምና ከደንብ
ልብስ ላይ ተገቢ ያልሆነ ፅሁፍ መፃፋና ቀጥሎ ማሰፋት
15.9. የተማሪን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥልና እስከ ህይወት ማጥፋት የሚያደርስ ድርጊት
ጊዜ ይሆናል፡፡
9
17.1. የተማሪዎች የደንል ልብስ የጨርቅ ዓይነት፤ጥራት እና ቀለም በትምህርት ቤቱ
አስተዳደር፤ተማሪዎችና ወላጆች የጋራ ስብሰባ በውይይት የሚወሰን ይሆናል፡፡
17.2. የወንድ ተማሪዎች የደንብ ልብስ አዘገጃጃት የሱሪ ቬሎ መጠን ከ 18 ኢንች ያነሰ ሊሆን አይችልም፡፡
ሱሪ የሚለብሱ ሴት ተማሪዎችም በዚሁ መጠን የሚያዘጋጁ ይሆናል፡፡
17.3. የሴት ተማሪዎች የደንብ ልብስ አዘገጃጃት የቀሚስ መጠን ከጉልበት በታች የታፋቸውን 2/3 ኛ
ክፍል የሚሸፍን መሆን ይኖርበታል፡፡
17.4 ማንኛውም ተማሪ በጋራ ከተወሰነው የደንብ ልብስ ዓይነት፤ጥራትና ቀለም ውጪ መጠቀም
አይፈቀድም፡፡
17.5. ከት/ቤቱ ፈቃድ ውጪ ማንኛውንም ዓይነት ፅሁፍ ማሳተም፤ሌላ የጨርቅ ዓይነት ቀጥሎ ማሰፋት
እና ያልተፈቀደ የደንብ ልብስ ዓይነት ፤ቅርፅና ይዘት መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡
17.6. በህግ በሀይማኖት ምክንያት ከተፈቀደ የደንብ ልብስ ውጪ ማንኛውንም ዓይነት አልባሳት ወደ
ትምህርት ቤት ግቢ ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
18.5.ለሴት ተማሪዎች ተንጠልጣይ የጀሮ ጉትቻ/ጌጥ/ ማድረግ አይፈቀድም፡፡ ለወንድ ተማሪ ምንም
ዓይነት የጀሮ ጉትቻ/ጌጥ/ ማድረግ አይፈወድም፡፡
19.2.ከአንድ ት/ቤት በዲስኘሊን ግድፈት የተቀጣ ተማሪ ትምህርት ቤቱን ለቆ ሲሄድ ወይም መልቀቂያ
ሲጠይቅ ስለተማሪው ሁኔታ በግልፅ በትራንስክሪኘቱ ላይ ይገለፃል፡፡
10
19.4. በመመሪያው ውስጥ የተጠቀሱ የዲስኘሊን ጥፋቶች የዲስኘሊን ኮሚቴ ከሚወስነው ውሳኔ
በተጨማሪ እንደየጥፋቱ ሁኔታ ፍርድ ቤት ሊያስጠይቅ ይችላል፡፡
አንቀፅ 21
የትምህርት ቢሮ
አዲስ አበባ
11