You are on page 1of 11

ዑራኤል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛደረጃ ትምህርት ቤት

ተግባራዊ ጥናት እና ምርምር

የ 8 ኛ ሀ ክፍል የሁለት ተማሪዎች በክፍል ዉስጥ መረበሽ እንዴት መቅረፍ ይቻላል?

አዘጋጆች፡ መ/ርት ዮጊት ደምሴ


መ/ርመንግስቱ የሩቅነህ
መ/ር ሹመት ዳኘ

አዲስአበባ, ኢትዮጵያ
ታህሳስ/2015 ዓ.ም
ምስጋና
በመጀመሪያ የትምህርት/ቤት መሻሻል/ም/ር/መ/ር አሰፉ ክብረት በስልጠናና በአስፈላጊ ቁሳቁሶች ድጋፍ ላደረጉልን ልባዊ ምስጋናችንን
እናቀርባለን፡፡
ማውጫገ ገፅ
ምዕራፍ አንድ
መግቢያ…………………………………………………………………….…………………..1
1.2. የጥናቱ ዳራ………………………………………………………………………………2
1.3.የጥናቱ መንሥኤ………………………………………………………………………….3
1.4. የጥናቱ ዓላማ…………………………………………………………………………….3
1.4.1. አጠቃላይ ዓላማ………………………………………………………………………..3
1.4.2. ዝርዝር ዓላማ…..…………….………………………………………………………..3
1.5. የጥናቱጠቀሜታ…………………………………………………………………………3
1.6. የችግሩማላምት…………………………………………………………………….……4
1.7. የጥናቱወሰን……………………………………………………………………………..4
ምዕራፍ ሁለት፡ ተዛማጅ ጽሁፍ

ምዕራፍ ሦስት፡የ ጥናቱ መረጃመሰብሰቢያዘዴ……………………………………………………6


2. የጥናቱ መረጃመሰብሰቢያዘዴ…………………………………………………………….6
2.1. መረጃዎቹየተተነተኑበትመንገድ………………………………………………………..6
ምዕራፍ አራት፡ የመረጃ ትንተና
4.1 መረጃትንተና………………………………………………………………………………….7
ምዕራፍ አምስት፡
4.1. በችግሩ የተነሱነጥቦች………………………………………………………………….12
የተቀመጡ የመፍትሄ ሃሳቦች………………………………………………………………...12
4.2. የጥናቱመፍትሔሃሳብተግባራዊማድረግ…………………...……….…………..….13
4.3. የመጨረሻውጤት (ግኝት)……………………………………………….……….……13
ማጣቀሻ……………………………………………………………………………………….14
ምዕራፍአንድ
1.1 መግቢያ
 ሥነ-ምግባር ለአንድ ሀገር በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ተማሪዎችም በመልካም ሥነ-ምግባር ታንፀው ለሀገር ና ለወገን ታላቅ ስራ
ሰርተው ሊመሰገኑናሊከበሩ ይገባል፡፡ስለሆነም በ 8 ኛሀ ክፍል በሁለት ተማሪዎች በክፍል ወስጥ የሚያሳዩትን ችግር ለማጥናት
በጥናትና ምርምር ተስማምተናል፡፡
 በዚህመሰረትበ 2015 ዓ.ም. በ 1 ኛወሰን ተማሪዎቹ ያሳዩት ክፍተት ለመለየት የተለያዩ መጠይቆች በማዘጋጀት
በአካባቢያቸው ተፅዕኖ የቤተሰብ የልጆቹን ውሎ ባለመከታተል የተለያዩ ዘመኑ ያፈራቸው ከባህል የወጡ ፊልሞች ናየአለባበስ
ተፅዕኖዎች የተለያዩ የአቻ ጓደኞች የሚፈጥሩት ተፅዕኖ ለተማሪዎች የሥነ-ምግባር ችግር እንዲታይባቸው ሊያደርግ የቻለ
ነው፡፡

1.2 የጥናቱ ዳራ
 በሥነ-ምግባር ትምህርት ተማሪዎች በምዕራፍ አንድ ግብረ-ገብ በተለያየ ጊዜ ተምረዋል የተለያዩ ፅሁፎች በርዕሱ ዙሪያ
ተፅፈዋል፡፡
 ዑራኤል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛደረጃ ትምህርት ቤትበቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01
በ 1963 ዓ.ም. የተመሰረተነው፡ሰፊ ግቢናማራኪ ውብ ንፁህ አየር የሚነፍስበት ለመማር ማስተማርናለንባብ ምቹ ሲሆን
ተማሪዎች የክፍል የመጫወቻ ሜዳ የተለያዩ የት/ት ቢሮዎች ሲገኙ እንዲሁም የአስተዳደር ቢሮ በፎቆች ላይ የተለያየ
አገልግሎት በመስጠት ይገኛል የቅድመ መደበኛ መማሪያናመጫወቻም ይገኛሉ የተለያዩ ለመማር ማስተማር አገልግሎት
ደጋፊዎች በሙሉይገኛሉ፡፡

1.3. የጥናቱ መንሥኤ


 በሥነ-ዜጋና በሥነ-ምግባር ትምህርት ለየትኛውም ህይወት እጅግ አስፈላጊ ነው ነገር ግን እየታየ ና እየተሰማ ያሉ ችግሮች
ዋንኛዎቹ የሥነ-ምግባር ብልሹነት ነው፡፡ስለዚህ ይህን ጥናት ዋና ችግሩን በመረዳት ችግሩን ለመንቀል (ለመቅረፍ) አቅደን
ተነስተናል፡፡
 ዑራኤል ቅድመ አንደኛ አንደኛ እና መካከለኛደረጃ ትምህርት ቤትበ 8 ኛሀ ሁለት (2) ተማሪዎች የታየ
ችግር
 በተማሪዎች ላይ በተደጋጋሚ የሚታዩ በክፍል አለመረጋጋት
 ተማሪዎች ትምህርቱን አቅለዉ የማየት ችግር
 የሚሰጣቸዉን የትምህርት አይነት ከፍና ዝቅ አድርጎ ማየት ለምሳሌ ለሒሳብ እና እንግሊዘኛ የሚሰጠዉን ትምህርት ለሌሎች
አለመስጠት
1.4. የጥናቱ ዓላማ
ጥናቱን የምንሰራው በሁለት ዓላማዎች ነው፡፡እነርሱም
1.4.1. አጠቃላይ ዓላማ
ተማሪዎቹ በሥነ-ምግባር የተሻሉ ሆነው እንዲገኙ ማድረግ ነው፡፡
1.4.2. ዝርዝር ዓላማ
የዚህ ጥናት ዝርዝር አላማ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ሀ. የ 8 ኛሀ ክፍል የሁለቱ ተማሪዎች የሥነ-ምግባር ባህሪ መሻሻል እገዛ ማድረግ
ለ. አርአያ በመሆን ሌሎችን እንዲማሩ ማዘጋጀት
ሐ.ተማሪዎችን በተለያዩ አጋጣሚዎች ማለትም በክባባት መልኩ መምከር

1.5.የጥናቱ ጠቀሜታ
ይህ ጥናት ለተማሪዎች ለመምህራን ለወላጅ በጣም ጠቀሜታ አለው ። ምክንያቱም ተማሪዎች ካለባቸዉ ችግር ተሻሽለዉ ማየት
ለሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ማለትም በቅድሚያ ለራሱ ከዚያም ለቤተሰብ ,ለወገን ብሎም ለሀገር እድገት አስፈላጊ ስለሆነ ነው።

1.6.የችግሩ መላምት
ለዚህ ጥናት ምክንያት ይሆናሉ ተብሎ በአጠኚዎቹ የታሰበ መላምት
ሀ. ተማሪዎች የመጡበት አመጣጥ (አስተዳደግ)
ለ. ለትምህርቱ ብዙ ቦታ ባለመስጠት
ሐ. ከአሣዳጊ ወይም ከወላጆቻቸው ምክር ማጣት
መ.የመምህሩ የማስተማሪያው ሥነ-ዘዴው ግልጽ አለመሆን
ሠ. የጓደኛ አላስፈላጊ ምክሮችን በመቀበል
ረ. መጤ ባህሎች ኢትዮጵያዊነትን የማያሳዩ ዘመናዊ ለመሆን ከመፈለግ
ሰ. በእኛ ወግ የተነወሩ ፊልሞችን በመመልከት
1.7. የጥናቱ ወሰን(scope of the research)
 ይህ ጥናት ና ምርምር በ 8 ኛሀ በሁለት ወንድ ተማሪዎች በ 2015 የዑራኤል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የሥነ-ምግባር ችግር
ያለባቸው ተማሪዎችን ነው፡፡

ውስንነት
 ይህን ተግባራዊ ጥናት ና ምርምር ስንሰራ
 መምህራን ቶሎ መገናኘት አለመቻል
 በክፍለ ጊዜ አለመቻቸት
 የተለያዩ መረጃዎችን ለመሰብበሰብ ናለመገናኘት ካለን ጊዜ እጥረት
 እንዲሁም መፃህፍቶችን በሰፊው ያለማግኘት ለዚህ ጥናት ችግሮች ነበሩ፡፡
ምዕራፍ ሁለት
2. የጥናቱ መረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ
 የዚህ ተግባራዊጥ ናትናምርምር መረጃዎች የተሰበሰቡት ለጥናቱ ከተወሰኑት ዋነኛ ተተኳሪዎች ማለትም በናሙናነት
ከተመረጡት የስነ-ምግባር ችግር ካለባቸው ተማሪዎች ከተማሪ ወላጆች እናመምህራን በፅሁፍ መጠይቅ የተሰበሰበ
መረጃ ነው፡፡
2.1. መረጃዎቹ የተተነተኑበት መንገድ
 የተግባራዊ ጥናት አድራጊው ከተማሪዎች ከተማሪ ወላጅና ከመምህራን በፅሁፍ መጠይቅ የተሰበሰበውን በግልፅ
በማሣየት በሚያመች መልኩ ቁጥሮቹን በመጠቀም ለመተንተን ተሞክሯል፡፡

ምዕራፍ ሦስት
3.1 ለመምህራን የተዘጋጁ መጠይቂች ናምላሾች
የዑራኤል መ/ደ/ት/ቤት የሚያስተምሩ መምህራንና 8 ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን የተጠየቁ መጠይቆች ናምላሾች

1. በት/ቤት የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸው ተማሪዎች አሉ ?


ጾታ አዎ የሉም
በቁጥር በፐርሰንት በቁጥር በፐርሰንት
ወንድ 3 33.3% 1 11.1%
ሴት 3 33.3% 2 22.3%
ድምር 6 66.7% 3 33.3%
በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሰውን አዎ ካሉ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ፡፡
የአንዳንድ ተማሪዎች ውጤት መቀነስ የክፍል ውስጥ ተሣትፎ መቀነስ አንዱ የስነ-ምግባር ችግር ነው፡፡

2. እርስዎ የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች በአግባቡ ናበወቅቱ የሚሰጣቸውን የቤት ስራ እና የክፍል መልመጃዎችን


የመስራት ችሎታ ምን ያህል ነው?
ጾታ ከፍተኛ መካከለኛ ዝቅተኛ
ወንድ 2 2 -
ሴት 2 3 -
ድምር 4 5 -
በተራ ቁጥር 2 ላይ ዝቅተኛ ነው ካሉ ምክንያቱን ይፃፉ፡፡
ለመጠይቁ ዝቅተኛ ያሉ የሉም፡፡

3. የተማሪዎችን ሥነ-ምግባር ችግር ለመፍታት በይበልጥ መወሰድ ያለበት እርምጃ ምንድን ነው?አማራጮች፡
 ሀ. የወላጅ ድጋፍ መጠንከር አለበት
 ለ. የት/ቤቱ ደንብ በግልፅ ማስረዳት
 ሐ. የመምህራን ምክር የጎላ መሆን አለበት

4. ተማሪዎችን በስነ-ምግባር የታነፁ እንዲሆኑ ከተማሪዎች ከመምህራን እና ከወላጆች ምን ይጠበቃሉ ይላሉ በዝርዝር
ይፃፉ::
 ከመምህራን የሚጠበቀው
 ከወላጅ ጋር ቀጣይነት ያለው ምክክር ማድረግ
 ተማሪዎች በስነ-ምግባር ለውጥ ሲያሳዩ ማበረታታት
 መምህሩ ተማሪዎቹን እንደልጁ መቁጠር ናበማቅረብ መምከር
 መምህራን ለተማሪዎች አርአያ መሆን
 ከተማሪዎች የሚጠበቀው
 በክፍል ውስጥ ከመረበሽ ይልቅ መምህሩን መከታተል
 ተማሪዎች ለጓደኛቸው ታማኝ ግልፅ መሆን
 የስነበ-ዜጋ ና የስነ-ምግባር ት/ት ለቁጥር ሳይሆን የባህሪይ ለውጥ ለማምጣት መስራት
 ከወላጆችየሚጠበቀው
 የልጆችን ውሎ መከታተል
 ስለልጆቻቸው ውጤት መከታተል ና የሚሰጣቸው መልመጃዎች እንዲሰሩት ማድረግ

 ለተማሪዎች የቀረቡ ጥያቄዎች ና የተሰጡ ምላሾች ትንተና


የ 8 ኛ” ሀ “ ክፍል ተማሪዎች በጥናቱ የተካተቱ ወንድ 2 ሴት 0 በድምሩ 2 ተማሪዎች የታዩ የስነ-ምግባር ችግር መንስኤው
ምንድ ነው በሚለው ላይ በዓይነት ናበቁጥር ከዚህ በታች ባለው መረጃ ትንተና ተዘርዝሯል፡፡
1. ለስነ-ዜጋ ና ስነ-ምግባር ት/ት የምትሰጠው (ጪው) ግምት ና ፍላጎት ምን ያህል ነው
አማራጮች ወንድ በፐርሰንት ሴት በፐርሰንት ድምር በፐርሰንት
ሀ. ከፍተኛ 1 33.3 1 33.3 2 66.7
ለ. መካከለኛ 1 33.3 1 33.3
ሐ. ዝቅተኛ - - - - - -
በተራ ቁጥር 1 ዝቅተኛ ነው ካልክ(ሽ) ምክንያቱን በዝርዝር ፃፍ(ፊ) ተብሎ ለተጠቀሰው መጠይቅ ዝቅተኛ ያለ የለም፡፡

2.የስነ-ዜጋ ና ስነ-ምግባር ት/ት ከሌሎች የት/ት አይቶች ጋር ሲነጻጸር ያንተ(ቺ) ውጤት ምን ይመስላል፡፡
አማራጮች ወንድ በፐርሰንት ሴት በፐርሰንት ድምር በፐርሰንት
ሀ. ከፍተኛ 2 40% 3 60% 5 100
ለ. መካከለኛ - - - - - -
ሐ. ዝቅተኛ - - - - - -
በተራ ቁጥር 2 ዝቅተኛነው ካልክ(ሽ) ምክንያቱን ይፃፉ
ለሚለው አንድም ተማሪ ዝቅተኛ ነውያለ የለም፡፡
5. ተማሪዎች የስነ-ምግባር ችግር እንዳይታይባቸው ከተማሪዎች ከመምህራን እና ከወላጆች (ከአሳዳጊዎች) ምን
ይጠበቃል ትላለህ(ሽ)
 በስነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ለማፍራት ከመምህሩ የሚጠበቀው
 ከወላጆች ጋር የልጆቻቸውን ውሎ እንዲከታተሉ መነጋገር
 የግብረ ገብ ት/ት በአግባቡ ማስተማር
 ተማሪዎች ታዛዥ እና ታማኝ እንዲሆኑ መምከር
 የችግሩ ባለቤት ከሆኑት ተማሪዎች ጋር ተከታታይነት ያለው ውይይት ማድረግ
 ከተማሪዎች ምን ይጠበቃል
 የስነ-ዜጋ ና የስነ-ምግባር ት/ትን ለማርክ ብቻ ሳይሆን የስነ-ምግባር ባህሪያትን ተረድተው
 ታማኝ
 ታዛዥ እና
 ቅን መሆን
 የስነ-ምግባር መርሆችን ጠንቅቆ ማወቅና መተግበር
 ማንኛዉንም ማህበረሰብ ማክበር

 ከወላጆች የሚጠበቀው
 ውሏቸውን መከታተል
 የት/ት ግብአቶችን ማሟላት
 የሚሰጣቸውን የቤት ስራዎች እንዲሰሩ መከታተል
 ስለልጆቻቸው ከመምህራን ጋር መወያየት

 ለወላጆች የቀረቡ መጠይቆችን የተሰጡ ምላሾች ትንተና


በዚህ ጥናት ውስጥ የተማሪ ወላጆች እንዲሳተፉ ተደረገዋል፡፡ስለሆነም የተማሪዎች ስነ-ምግባር በምን አግባብ መሻሻል
እንዳለበት በተጠየቀው መጠይቅ መሠረት ተተንትነዋል፡፡
1. እርስዎ ስለልጆ ባህሪ ከመምህራን ጋር ተወያይተው ያውቃሉ
አማራጮች ወ በፐርሰንት ሴ በፐርሰንት ድምር በፐርሰንት

ሀ. አዎ 2 3 5
ለ. አልተወያየውም 2 2 4
በተራ ቁጥር 1 አልተወያየሁም ለሚለውመጠይቅ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ ለሚለው
 ካለብን የጊዜ እጥረት የተነሳ ነው ያሉት 3 ወላጆች እንዲሁም
 1 ወላጅ ልጄ በቤቴ ውስጥ ጨዋ ስለሆነ ያንን ባህሪ ት/ቤት ውስጥም የሚተገበር መስሎ ስለታየኝ ነው ብለዋል፡፡
2. እርሶ ለተማሪው(ዋ) የት/ት ግብአት አሟልተውለታል(ላታል)
አማራጮች ወ በፐርሰንት ሴ በፐርሰንት ድምር በፐርሰንት
ሀ. አዎ 4 3 7
ለ. አላሟላሁም - - - - - -
በተራ ቁጥር 2 አላሟላሁም ካሉ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ ለሚለው ማንም የለም
3. በት/ቤት አካባቢ አዋኪ ነገሮች አለ ይላሉ
አማራጮች ወ በፐርሰንት ሴ በፐርሰንት ድምር በፐርሰንት
ሀ. አዎን 1 1
ለ. የለም 4 2 6
ሐ. ካለይጠቀስ
በተራ ቁጥር 3 ካለ ይጠቀስ ለሚለው
ከአንድ ወላጅ የተሰጠ ምላሽ በት/ቤቱ አዋኪ ነገሮች የሉም ነገርግን ተማሪዎች ከት/ቤቱ ሲወጡ የተለያዩ ሱቆች ስላሉ
ተማሪዎች በሱስ የተበርዙ ሰዎችን ባህሪ ና መጥፎ ነገር ይጋራሉ ብለዋል፡፡

 ተማሪዎች በስነ-ምግባር የታነፁ እንዲሆኑ ከተማሪዎች ከመምህራን እና ከወላጆች (ከአሣዳጊዎች) ምን ይጠበቃል


ይላሉ::

 ከወላጅ (ከአሣዳጊ) የሚጠበቀው


 የት/ት ቁሳቁስ ማሟላት
 ውሏቸውን መከታተል
 በቤት ውስጥ ታዛዥነትን ቅንነት ታማኝነትን ማስተማር
 ከመምህራን የሚጠበቀው
 ከተማሪ ወላጅ ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት መፍጠር
 ተማሪዎች የስነ-ምግባር ለውጥ ሲያሳዩ (የተሻሉሲሆኑ) ማበረታታት
 የስነ-ምግባር መርሆችን ማስተማር
 መምህሩ ለተማሪዎች አርአያ መሆን

 ከተማሪ የሚጠበቀው
 ታማኝ ቅን ታዛዥ መሆን
 መምህራን የሚሏቸውን በአግባቡ መስማት ና መተግበር
 የስነ-ምግባር ት/ትን ለቁጥር ሳይሆን ለተሻለ ባህሪ መጠቀም
 በቤት ውስጥ እርስ በርስ መከባበር

ምዕራፍ አራት
4.1 በችግሩ የተነሱ ነጥቦች
ሀ. አንዳንድ ወላጅ/አሳዳጊ የልጆቹን ባህሪ በደንብ አለመረዳታቸው
ለ. ወላጆች ተማሪዎቹን በት/ት ላይ በሚገባ አለመረዳት
ሐ. ወላጅ ልጆቹን በት/ትም ሆነ በሥነ-ምግባር አለማነፅ ሁሉንም መምህር ላይ ብቻ
በመጣል ችግሮቹ በክፍል እንዲታዩ አድረጓል፡፡
መ. በክፍል ውስጥ ፀጥታ እንዲከበር ሁሉንም ተማሪ የሚገዛ ደንብ ከተማሪዎች
ጋር ተመካክሮ በጋራ ማውጣት
 የተቀመጡ የመፍትሔ ሃሳቦች
ሀ. ለተማሪዎች መልካም ስነ-ምግባር ግንባታ ለጤናማ የት/ት ክትትል ውጤት ከወላጆች
እኩል የተፈለገውን ያህል አልተገኘም ስለዚህ ወላጆች ለመማር ማስተማሩ ሂደት
ስኬታማነት የቅርብ ክትትል ቢያደርጉ
ለ. አንድ ተማሪ ወይም ተማሪዎች የሥነ-ምግባር ችግር ቢፈጥር (ሩ) ችግር ፈጣሪዎችን
ለይቶ እርማት መስጠት ናማስተማር እንጂ ሁሉንም ተማሪዎች በጠቅላላ አለመቆጣት
ወይም አለመቅጣት ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል
ሐ. የተማሪዎች የስነ-ምግባር ችግር ጉዳዩ የአንድ ወገን ሥራ ብቻ ባለመሆኑ
የሚመለከታቸው ሁሉ በጋራ በመሆን ችግሩ የሚቃለልበት መንገድ ቢፈለግ ትኩረት ቢሰጥበት
መ. በክፍል ውስጥ ፀጥታ እንዲከበር ሁሉንም ተማሪ የሚገዛ ደንብ ከተማሪዎች ጋር
ተመካክሮ በጋራ በማውጣት በሚታይ ቦታ በትልልቁ በመፃፍ መለጠፍ ቢቻል እና ደንቡን
የተላለፈ ተማሪ በቂ ቅጣት መስጠት ነው፡፡

4.2 የጥናቱ የመፍትሔ ሃሳብ ተግባራዊ ማድረግ


 በ 8 ኛ”ሀ” ክፍል ውስጥ ካሉት የጥናት ተተኳሪ ወንድ 2 ሴት 0 ድምር 2 ተማሪዎች ላይ የዚህ ጥናት አካል የሆኑት
የ 8 ኛክፍል የስነ-ዜጋ ናየስነ-ምግባር መምህራን ከላይ በተሰጡት የመፍትሔ ሃሳቦች መሰረት የተማሪዎች የስነ-
ምግባርችግር ለመፍታት በተቀየሰው መፍትሔ መሰረት ተንቀሳቅሰዋል፡፡በዚህም የመጀመሪያው ስራ የችግሩ ሰለባ
የሆኑ ተማሪዎችን ለብቻ ጊዜ በመመደብ ስለችግሮቻቸው የመመካከር ስራ ሰርተዋል በሌላ በኩል በወቅቱ
መረጃውን ሞልተው ከላኩ ወላጆች ጋር ስለልጆቻቸው ባህሪ ሁኔታ አስመልክተው ሰፊ ውይይት ተደርጎ ድርሻን
የመከፋፈል ስራ ለመስራት ተችሏል፡፡
4.3.የመጨረሻ ውጤት (ግኝት)
 ልጆች ጊዜ ተሰጥቷቸው በቂ ምክር ና ማበረታቻ ከቤተሰቦቻቸው እያገኙ ማደግ ለጥሩ ስነ-ምግባር መነሻ ነው፡፡
 ልጆች ከቅድመ- መደበኛ ት/ቤት ጀምሮ ተረቶች ናመዝሙሮች በሥርዓት ተዘጋጅቶላቸው መማር አለባቸው
የመስክ ጉብኝት ፕሮግራም ተይዞላቸው የአካባቢውን ተፈጥሮ ናውበት እንዲያደንቁ እንዲያውቁ ማድረግ
ስለጀግኖች አባቶች ናእናቶች ታሪክ የሚናገሩ ተረቶችን ማንበብ ስለሰንደቅ ዓላማ ያለንን ክብር ማሳወቅ ማስተማር
ና ወደ ጥሩ ሥነ-ምግባር ማምጣት አለብን ይህም የሁሉም ባለድርሻ ናኃላፊነት ነው፡፡
 በመጨርሻም በዚህም መሰረት የተማሪዎች ባህሪ ባደረግነው ጥረት 2 ቱም ተማሪዎች የባህሪ ለውጥ አምጥተዋል
ከዚህ የተረዳነው በጋራ በመስራት የማይፈታ ችግር እንደሌለ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

ማጣቀጫ
ከሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ማሰልጠኛ ሞጁል የፌደራል ሥነ-ምግባር ናየፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሚያዚያ 2008
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሠ/ማ/ጉ/ቢሮ ካዘጋጀው ሞጁል ላይ ስለ ሥነ-ምግባር 2009 ዓ.ም. የተወሰደ

በዑራኤል የመጀ/ደ/ት/ቤት በስነዜጋ ና ስነምግባር ዲፓርትመንት ክፍል የተዘጋጀ መጠይቅ


ለወላጆች የቀረቡ መጠይቆች
1. እርስዎ ስለልጆ ባህሪ ከመምህራን ጋር ተወያይተው ያውቃሉ?
ሀ. ከፍተኛ ለ. መካከለኛ ሐ. ዝቅተኛ
በተራ ቁጥር 1 አልተወያየሁም ለሚለው መጠይቅ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ
2. እርሶ ለተማሪው(ዋ) የት/ት ግብአት አሟልተውለታል(ላታል)?
ሀ. አዎ ለ. አላሟላውም
በተራቁጥር 2 አላሟላሁም ካሉ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ
3. በት/ቤት አካባቢ አዋኪ ነገሮች አለ ይላሉ?
ሀ. አዎ ለ. አላሟላውም ሐ. ካለይጠቀስ
በተራ ቁጥር 3 ካለ ይጠቀስ
ተማሪዎችየስነ-ምግባርችግርእንዳይታይባቸውከተማሪዎችከመምህራንእናከወላጆች(ከአሳዳጊዎች) ምንይጠበቃልትላለህ(ሽ)

በዑራኤል የመጀ/ደ/ት/ቤት በስነዜጋና ስነምግባር ዲፓርትመንት ክፍል የተዘጋጀ መጠይቅ


ለተማሪዎች የቀረቡ መጠይቆች
1. ለስነ-ዜጋናስነ-ምግባርት/ት የምትሰጠው (ጪው) ግምትና ፍላጎት ምን ያህል ነው?
ሀ. ከፍተኛ ለ. መካከለኛ ሐ. ዝቅተኛ
በተራ ቁጥር 1 ዝቅተኛ ነው ካልክ(ሽ) ምክንያቱን በዝርዝር ፃፍ(ፊ)
2. የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ት/ት ከሌሎች የት/ት አይቶች ጋር ሲነጻጸር ያንተ(ቺ) ውጤት ምን ይመስላል?
ሀ. ከፍተኛ ለ. መካከለኛ ሐ. ዝቅተኛ
በተራ ቁጥር 2 ዝቅተኛ ነው ካልክ(ሽ) ምክንያቱን ይፃፉ
3. ተማሪዎች የስነ-ምግባር ችግር እንዳይታይባቸው ከተማሪዎች ከመምህራን እና ከወላጆች (ከአሳዳጊዎች) ምን
ይጠበቃል ትላለህ(ሽ)?

በዑራኤል የመጀ/ደ/ት/ቤት በስነዜጋ ና ስነምግባር ዲፓርትመንት ክፍል የተዘጋጀ መጠይቅ


ለመምህረን የቀረቡ መጠይቆች
1. በት/ቤት የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸው ተማሪዎች አሉ ?
ሀ. ከፍተኛ ለ. መካከለኛ ሐ. ዝቅተኛ
በተራ ቁጥር 1 የተጠየቀውን ዝቅተኛ ነው ካሉ ምክንያቱን በዝርዝር ይፃፉ
2. እርስዎ የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች በአግባቡ ናበወቅቱ የሚሰጣቸውን የቤት ስራ እናየክፍል መልመጃዎችን
የመስራት ችሎታ ምን ያህል ነው?
ሀ. ከፍተኛ ለ. መካከለኛ ሐ. ዝቅተኛ
በተራ ቁጥር 2 ላይ ዝቅተኛ ነው ካሉ ምክንያቱን ይፃፉ፡፡ለመጠይቁ ዝቅተኛያሉ
የሉም፡፡
3. ተማሪዎች የስነ-ምግባር ችግር እንዳይታይባቸው ከተማሪዎች ከመምህራን እና ከወላጆች (ከአሳዳጊዎች) ምን
ይጠበቃል ትላለህ(ሽ)?

You might also like