You are on page 1of 5

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ

የመዉጫ ፈተና ትግበራ የድርጊት መርሐ-ግብር

ታህሳስ/2015 ዓ/ም
አሶሳ፣ኢትዮጵያ
ማዉጫ
1
1. መግቢያ …………………………………………………………………………………3

2. የድርጊት መርሐ ግብሩ አስፈላጊነት ……………………………………………………3

3. የድርጊት መርሐ-ግብሩ የክንዉን ጊዜ …………………………………………………..4

4. ተግባራት፣ የሚፈጸምበት ጊዜ፣ፈጻሚ አካል እና በጀት ………………………………...4

1. መግቢያ

በከፍፈተኛ ትምህርት ተቋማት ብቃትና ጥራት ያለዉ የሰዉ ኃይል ማፍራት ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊና ሁለተናዊ እድገት
ወሳኑን ድርሻ ይወስዳል፡፡ በተለይም አካባቢያዊ፤ሀገራዊና ዓለማቀፋዊ የሰዉ ሀይል ፍላጎትን ማዕከል ያደረገ ሥርዓተ-ትምህርት
2
ቀረጻ ተግባራዊ ማድረግ ወቅቱ የሚጠይቀዉ ዘመን ተሻጋሪ አሰራር ሁኗል፡፡ ሥርዓተ ትምህርቱን ከመቅረጽ ባለፈ ተማሪዎችን
በአግባቡና ዘመኑ የሚጠይቀዉን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ማስተማርና ዉጤታማ ማድረግን ይጠይቃል፡፡ ስለሆነም በስርዓተ
ትምህርቱ ዉስጥ የተመላከተዉን የምሩቃን ፕሮፋይል ምሩቃን እንዲጨብጡ ት በማድረግ ለገበያዉ ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡

በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ ባለፉት 20 ዓመታት የትምህርት ጥራት ጉዳይ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ለትምህርት
ተደራሽነት የተሰጠዉን ትኩረት ያህል ለጥራቱም የገዘፈ ትኩረት ባለመሰጠቱ ምክንያት ምሩቃን የሚፈለገዉን ብቃት ያሟሉ
አለመሆናቸዉ ከቀጣሪ መ/ቤቶች ሳይቀር በየጊዜዉ ይነሳል፡፡

የምሩቃን በቃትን ለመመዘን ደግሞ ተቋማት በራሳቸዉ የሚሰጡት ብቃትን የማረጋገጥ ተግባር እንደተጠበቀ ሁኖ በአገር
አቀፍ ደረጃ ደግሞ ምሩቃን በስርዓተ ትምህርቱ ላይ የተቀመጠዉን ፕሮፋይል ማሟላቸዉን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

መንግስት የመዉጫ ፈተናዉን አስፈላጊነት በመገንዘብ በህግ ትምህርት እና በተለያዩ የጤና ዘርፎች የሙጫ ፈተናን ተግባራዊ
ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ የምሩቃን ብቃትን በመመዘን ገበያዉ የሚያስፈልገዉን የሰዉ ሀይል ማቅረቡ እንደተጠበቀ ሁኖ
የተመራቂዎች ብቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መጥቷል፡፡ ተማረዎችም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሚኖራቸዉ ቆይታ
ፍሬያማ አድርጓቸዋል፡፡ ስለሆነም ይህን ተሞክሮ ከግንዛቤ በማስገባት መንግስት ከ 2015 ዓ/ም ጀምሮ የመዉጫ ፈተናን
በሁሉም የትምህርት መስኮች(ፕሮግራሞች) ተግራዊ ለማድረግ በተላላፈዉ ዉሳኔ መሰረት የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የመዉጫ
ፈተናን ተግባራዊ ለማድረግ የትግበራ የድርጊት መረሐ ግብር አዘጋጅቷል፡፡

2. የድርጊት መርሐ ግብሩ አስፈላጊነት

የመዉጫ ፈተናዉን ከ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ለማድረግ መንግስት በወሰነዉ መሰረት ከወዲሁ በርካታ የቅድመ
ዝግጅት ሥራዎች መከናወን ይኖርባቸዋል፡፡ ስለሆነም በ 2015 ዓ/ም መጨረሻ ላይ ለሚሰጠዉ ፈተና የሚመለከታቸዉ
የዩኒቨርሲቲዉ አካላት ሚናቸዉን በመገንዘብ እንዲሁም ከወዲሁ የቅድመ የዝግጅት ሥራዎችን በመለየት የራሳቸዉን
የድርጊት መርሐ-ግብር አዘጋጅተዉ እንዲገብሩ ማድረግ አስፈላጊ ነዉ፡፡ በመሆኑም ይህ የመዉጫ ፈተና ዝግጅት ምዕራፍ
የድርጊት መርሐ-ግብር የሁሉንም ተሳትፎ በሚያረጋግጥ መልኩ ተዘጋጅቷል፡፡ ስለሆም በፈተናዉ ደርሻ ያላቸዉ አካዳሚክ
ዳይሬክቶሮች፣የተቋማዊ ጥራት ዳይሬከተር፣የኮሌጅ/ትም/ቤት ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ትምህርት ክፍል
ኃላፊዎች፣መምህራን፣ላብራቶሪ ቴክኒሽያን፣የተማሪዎች ህረት እና ተፈታኞች ሚናቸዉን በመለየት ለፈተናዉ
ዉጤታማነት ከወዲሁ አቅደዉ ወደ ተግባር ለማስገባት የድርጊት መርሐ-ግብሩ በዩኒቨርሲዉ በኩል ተዘጋጅቷል፡፡

3. የድርጊት መርሐ-ግብሩ የክንዉን ጊዜ

በ 2015 ዓ/ም መጨረሻ ላይ የሚሰጠዉን የመዉጫ ፈተናን በተያዘለት ጊዜ ለመስጠት እንዲቻል የቅድመ
ዝግጅት ስራዎችን በዕድ መምራት ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም ፈተናዉ ግንቦትና ሰኔ ወራት ዉስጥ እንደሚሰጥ

3
ታሳቢ ተደርጎ ከታህሳስ 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ/ም ድረስ የሚከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች
ተለይተዉ ታቅደዋል፡፡

4. ተግባራት፣ የሚፈጸምበት ጊዜ፣ፈጻሚ አካል እና በጀት

በሚቀጥሉት 6 ወራት ተግባራዊ ይደረጋሉ ተብለዉ የታቀዱት ተግባራት በዕቅዱ የሚያሳኩ


ተግባራት፣የሚፈጸምበት ጊዜ፣ፈጻሚ አካል እና በጀት በዚህ ክፍል ዉስጥ በአግባቡ ተተንትነዋል፡፡

ተ.ቁ ተግባራት የሚፈጸምበት ጊዜ ፈጻሚ አካል የሚያስፈልግ በጀት

1. የመዉጫ ፈተናን ተግባዊ ከታህሳስ 01-03/2015 አካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት


ለመድረግ ዓ/ም ፣ኮሌጅ/ትም/ቤት ዲኖች እና
በአካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች
፣በኮሌጅ/ትም/ቤት ዲኖች እና
በትምህርት ክፍል ኃላፊዎች
የሚመራ ኮሚቴ ማቋቋም

2. ለመዉጫ ፈተና የተለዮ ከታህሳስ 03-15/2015 አካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት፣አካ/ፕ/መ/ል/


ኮርሶች ለሌጅ/ትም/ቤት ዓ/ም ዳይሬክተር፣የኮሌጅ/ትም/ቤት
ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ለትምህርት
ክፍል ኃላፊዎች
ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች
እና ለተማዎች መድረሱን
ማረጋገጥ

3. የመዉጫ ፈተናን ከታህሳስ 15-20/2015 ካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት እና


በሚመለከት ለሌጅ/ትም/ቤት ዓ/ም አካ/ፕ/መ/ል/ዳይሬክተር
ዲኖች፣ አስተባባሪዎችና
ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች
ግንዛቤ መፍጠር

4. የመዉጫ ፈተናን ከታህሳስ 20-30/2015 አካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት፣አካ/ፕ/መ/ል/


በሚመለከት ለሁሉም ተማሪ ዓ/ም ዳይሬክተር፣የኮሌጅ/ትም/ቤት
ተወካዮች እና ለተመራቂ ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ለትምህርት
ተማሪዎች ግንዛቤ መፍጠር ክፍል ኃላፊዎች

5. የመዉጫ ፈተናን ጥር 13/2015 ዓ/ም አካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት፣አካ/ፕ/መ/ል/


በሚመለከት ለተከታታይና ዳይሬክተር፣የሬጅስትራር አገልግሎት
ርቀት ትም/ት ፕሮግራም ዳይሬክተር፣የቤተ-መጽሐፍትና
ተማሪዎች ግንዛቤ መፍጠር ዶክመንቴሽን ዳይሬከተረና
የተከታታይና ርቀት ትም/ት
ፕሮግራም ዳይሬክተር

6. የመዉጫ ፈተናን ጥር 17/2015 ዓ/ም አካ/ጉ/ም/ፕሬዝዳንት፣አካ/ፕ/መ/ል/


በሚመለከት ለመምህራንና ዳይሬክተር፣የሬጅስትራር አገልግሎት
4
ለላብራቶሪ ቴክኒሽያን ዳይሬክተር፣የቤተ-መጽሐፍትና
ግንዛቤ መፍጠር ዶክመንቴሽን ዳይሬከተርና
የተከታታይና ርቀት ትም/ት
ፕሮግራም ዳይሬክተር

7. የመዉጫ ፈተና የተለዩ እስከ ጥር 17/2015 የኮሌጅ/ትም/ቤት


ኮርሶችን የማጠናከሪያ ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
ትም/ት የሚሰጡ መምህራን ክፍል ኃላፊዎች
መመልመል

8. ለመዉጫ ፈተና አጋዥ የሆኑ እስከ ጥር 25/2015 የቤተ-መጽሐፍትና ዶክመንቴሽን


ማቴራሎችን/ቁሳስ/መለየት ዓ/ም ዳይሬከተር፣ የተከታታይና ርቀት
ትም/ት ፕሮግራም
ዳይሬክተር፣የኮሌጅ/ትም/ቤት
ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ለትምህርት
ክፍል ኃላፊዎች

8. የመዉጫ ፈተና የተለዩ እስከ ጥር 20/2015 የኮሌጅ/ትም/ቤት


ኮርሶችን የማጠናከሪያ ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
ትም/ት ለመስጠት ፕሮግራም ክፍል ኃላፊዎች
ማዘጋጀት

9. የመዉጫ ፈተና የተለዩ ከጥር 20 እስከ ግንቦት የኮሌጅ/ትም/ቤት


ኮርሶችን የተሻሉ ተማሪዎች 15/2015 ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
የማጠናከሪያ ትም/ት ክፍል ኃላፊዎችና የማጠናከሪያ
እንዲሰጡ ማድረግ ትም/ት የሚሰጡ ተማሪዎች

10. የመዉጫ ፈተና የተለዩ ከጥር 20-ሰኔ የኮሌጅ/ትም/ቤት


ኮርሶችን የማጠናከሪያ 20/2015 ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
ትም/ት መምህራን እንዲሰጡ ክፍል ኃላፊዎችና መምህራን
ማድረግ

11. የመዉጫ ፈተና እስከ ሚያዝያ በተቋቋሙ ኮሚቴዎች


በቴክኖሎጂ/በኦላይን/ 30/2015 ዓ/ም
ለመስጠት ማመቻቸት

12. የመዉጫ ፈተና አጋዥ ሞዴል ከግንቦት 15-20/2015 የኮሌጅ/ትም/ቤት


ፈተና ማዘጋጀት ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
ክፍል ኃላፊዎችና መምህራን

13. ሞዴል ፈተና መስጠት ከግንቦት 25-30/2015 የኮሌጅ/ትም/ቤት


ዓ/ም ዲኖች፣አስተባባሪዎች፣ ትምህርት
ክፍል ኃላፊዎችና መምህራን

You might also like