Professional Documents
Culture Documents
Revised MoE 2014 Budget Year Final Report PDF
Revised MoE 2014 Budget Year Final Report PDF
(የተከለሰ)
አዲስ አበባ
0
ማውጫ
ድርሞ (Executive Summary) ..................................................................................................1
ክፍል አንድ ..............................................................................................................................9
1. የትምህርት ዘርፉ ስትራቴጂያዊ መሰረቶች.............................................................................9
ክፍል ሁለት ............................................................................................................................10
2. በትምህርት ሴክተር የተተገበሩ ዋና ዋና የሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ...................................10
ክፍል ሶስት.............................................................................................................................12
3. የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ አመታዊ ዕቅድ አፈጻጸም .........................................................12
ሀ. የትምህርት አስተዳደርና ስርዓት ግንባታ፣ ...........................................................................12
ለ. የትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ..............................................................................................15
ሐ. የትምህርት እና ምርምር አግባብነትና ጥራት ....................................................................16
መ. የትምህርት ፍትሐዊነትና ተደራሽነት፣ ..............................................................................20
ሠ. ከሥራ ጋር የተሳሰረ የጐልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ..........................................26
ረ. የትምህርት መሰረተ ልማትና ፋሲሊቲን ማሻሻል፤ .............................................................28
ክፍል አራት............................................................................................................................29
4. የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ........................................................................................29
ሀ. የትምህርት አስተዳደርና ስርዓት ግንባታ .............................................................................29
ለ. በብዝሃነት ውስጥ ብሔራዊ አንድነት፡- ...............................................................................32
ሐ. የትምህርት እና ምርምር አግባብነትና ጥራት .....................................................................32
መ. የትምህርት ፍትሐዊነትና ተደራሽነት፣ ..............................................................................38
ሠ. የቴክኖሎጂ ዕድገት፣ ሽግግር እና የማኅበረሰብ አቀፍ ስራዎች፣ ..........................................42
ረ. የትምህርት መሰረተ ልማትና ፋሲሊቲን ማሻሻል፤ ..............................................................44
ክፍል አምስት .........................................................................................................................46
5. የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ......................................................49
ክፍል ስድስት .........................................................................................................................57
6. የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን .........................................................................................57
ክፍል ሰባት .............................................................................................................................61
7. የድጋፍና አመራር ዘርፍ .....................................................................................................61
ክፍል ስምንት .........................................................................................................................64
8. የውስጥ ኦዲት እና የዋና ኦዲተር ግኝት ማስተካከያ በተመለከተ ..........................................64
ክፍል ዘጠኝ ............................................................................................................................65
9. የበጀት አጠቃቀም ሪፖርት ..................................................................................................65
ክፍል አስር .............................................................................................................................66
ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተቀመጡ መፍትሄዎችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ .................................66
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች(KPIs) አፈጻጸም ማትሪክስ) ....69
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች(KPIs) አፈጻጸም ማትሪክስ) .......69
0
ድርሞ (Executive Summary)
በትምህርት ሥርዓቱ ባለፉት ዓመታት ከቅድመ አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ተቋማትን
በፍትሀዊነት ተደራሽ በማድረግ እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናትና ወጣቶችን ወደ ትምህርት ቤት
ለማምጣት ከፍተኛ ጥረት መደረጉ፣ የትምህርት ጥራትና ተገቢነት ለማስጠበቅ ሥርዓተ ትምህርቱ ወቅቱ
የሚፈልገውን የመማር ብቃት የተላበሰ እንዲሆን ከተደረጉ ጥናቶች በመነሳት የሪፎርም ስራ መጀመሩ፣
መምህራን ለሚያስተምሩት የትምህርት ደረጃ ብቁ ለማድረግ በመደበኛውና በክረምት መርሃ ግብር
ከዲፕሎማ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ ማሰልጠን የተቻለ መሆኑ፣ ሴት መምህራንን ወደ ትምህርት ሥርዓቱ
ከመሳብና እንዲቆዩ ከማድረግ አንጻር እና የመምህራንን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የተለያዩ ስትራተጂዎች
እና ማሻሻያዎች መዘጋጀታችው፣ አርብቶ አደርና ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎችን የማስፈጸምና የመፈጸም
አቅምን በማሳደግ የትምህርት ተደራሽነት፣ ተሳትፎና ጥራትን ለማሳደግ ጥረት መደረጉ እና የጎልማሶችና
መደበኛ ያልሆነ ትምህርት በመስፋፋቱ በተለይም የትምህርት ብርሃን ምዘና መጀመሩ አጠቃላይ የሰው
ሃብት ልማት ማሳያ /Human Development Index/ እየተሻሻለ መምጣቱ ባለፉት አመታት በአጠቃላይ
የትምህርትን ተደራሽነት፣ ተሳትፎ፣ ጥራትንና ተገቢነት ከማሻሻል አንጻር የተመዘገቡ አበረታች ስራዎች
ናቸው።
ይሁን እንጂ አሁንም በየደረጃው እያጠናቀቁ የሚወጡ ተማሪዎች የሚጠበቀውን እውቀት፣ ክህሎት እና
መልካም ስነ ምግባር በሚፈለገው ደረጃ የተላበሱ አይደሉም። ለአብነት የትምህርት ጥራት መለኪያዎችን
መሰረት ተደርጎ ባለፉት ዓመታት በተካሄዱ ጥናቶች 3ኛ ክፍል የደረሱ ተማሪዎች በተማሩበት ቋንቋ
የማንበብ፣ የመጻፍና የመናገር ክህሎት ለመለካት በተደረገው የናሙና ምዘና የሚጠበቀውን ውጤት
ያስመዘገቡ ተማሪዎች 34% ብቻ ናቸው፤ በተጨማሪም በ2013 ዓ.ም የሙያ ብቃት ምዘና ከተመዘኑ
መምህራን ውስጥ የማለፊያ ውጤት አምጥተው ሰርተፍኬት የወሰዱ 29% ብቻ ናቸው። እንዲሁም ካሉን
47 ሺህ ያህል ት/ቤቶች ውስጥ በትንሹ የሚፈለገውን ስታንዳርድ የሚያሟሉት 10.8% ብቻ ናቸው፤ ይህም
በአጠቃላይ የሀገራችን የትምህርት ጥራት ያለበትን ክፍተት ያመላክታል። እነዚህን ችግሮች በየደረጃው
እየፈቱ የመማር ውጤትን ለማሻሻል የትምህርት ሚኒስቴር የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ አዘጋጅቶ በመተግበር
ላይ ይገኛል። በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ልዩ ልዩ የሪፎርም ተግባራት ታቅደው ተከናውነዋል፡፡ በዚህም
መሰረት ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ተከልሶ የተዘጋጀው ስርዓተ ትምህርት በ2014 ዓ.ም በ589
ት/ቤቶች (ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል) ውስጥ የሙከራ ትግበራ ለማካሄድ ታቅዶ ሙሉ በሙሉ የተከናወነ ሲሆን
በ2015 ዓ.ም ወደ ሙሉ ትግበራ ይገባል፡፡ በ89 የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሙከራ ትግበራ ለማካሄድ እቅድ
ቢያዝም ዝግጅቱ ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቁ የሙከራ ትግበራው ወደ 2015 ዓ.ም እንዲተላለፍ ተደርጓል።
በተማሪዎችና በመምህራን ዘንድ የሚስተዋለውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ለማሻሻል በውጪ ያሉ
የሁለተኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን /SECOND GENERATION DIASPORA/፣ የሰላም ጓዶች /PEACE
CORPS/፣ የብሪታንያ የውጪ በጎ ፈቃደኞች አገልግሎት /VSO/፣ በጡረታ ላይ ያሉ በጎ ፈቃደኞችና አፍ
መፍቻ ቋንቋቸው እንግሊዝኛ የሆኑትን በሃገራችን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማሰማራት ግንኙነት
1
በመፍጠር ውይይት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ የመምህራን አቅም ግንባታ በተመለከተ በአዲሱ
የትምህርት እርከን ለማስተማር በቂ የትምህርት ዝግጅት ያላቸው ቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን 26,800
ታቅዶ አፈጻጸሙ 8759 (32.7%)፤ የአንደኛ ደረጃ እና መካከለኛ ደረጃ መምህራን 146,806 ታቅዶ
አፈጻጸሙ 70,330 (49.9%)፤ እንዲሁም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት 23,269 ለማድረስ ታቅዶ 16,196(69.6%)
ማድረስ ተችሏል፡፡
ውስጣዊ ብቃትን በማሳደግ በኩል በእቅድ ትግበራ ዘመኑ የአንደኛ ክፍል የማቋረጥ ምጣኔ በ2013 ዓ.ም
ከነበረበት 23% ወደ 20% ለማውረድ ታቅዶ 20% ማለትም የእቅዱን 100% ማሳካት ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ከ1ኛ - 6ኛ ክፍል መጠነ ማቋረጥ ወደ 14.4% ለማውረድ ታቅዶ አፈጻጸም 13% ሆኗል፡፡
ይህ አፈጻጸም የሚያሳየው በተሰሩ ስራዎች የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥ እየቀነሰ መሄዱን ያሳያል፡፡
የትምህርት ፍትሀዊነትን በተመለከተ የልዩ ፍላጎት እና አካቶ ትምህርትን ተደራሽ ለማድረግ ከቅድመ
አንደኛ እስከ 2ኛ ደረጃ 200 ሺህ የልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን ለማስተናገድ ታቅዶ 127 ሺህ (63%)
ማሳካት ተችሏል። የልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች በት/ቤቶች ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ 187 የድጋፍ
መስጫ ማእከላት ለማቋቋም (በሰው ሀይልና ቁሳቁስ በማሟላት እና የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት)
ታቅዶ በ164 (87.7%) ት/ቤቶች ውስጥ ተቋቁሞ ለ54 ሺህ ተማሪዎች ድጋፍ እንዲሰጡ ተደርጓል።
2
የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም በተመለከተ 3 ሚሊዮን ጎልማሶችን ለማስተማር ታቅዶ
አፈጻጸሙ 2.4 ሚሊየን (80%)፣ 30,000 ተማሪዎች በርቀት ትምህርት መርሀ-ግብር ለማሳተፍ ታቅዶ
34,165 (114%)፣ በተፋጠነ ትምህርት 10,000 ተማሪዎችን ለማሳተፍ ታቅዶ 24,044 እንዲሁም 150,000
ተማሪዎችን በማታ ትምህርት ለማሳተፍ ታቅዶ 203,417 ከዕቅድ በላይ ማሳተፍ ተችሏል፡፡ በትምህርት
ብርሃን ምዘና 500,000 ወጣቶችንና ጎልማሶችን መዝኖ እውቅና ለመስጠት ታቅዶ 900,753 መመዘን
ተችሏል። ከእነዚህም ውስጥ 518,891 (57.6%) የማለፊያ ውጤት ላመጡ የእውቅና የምስክር ወረቀት
እንዲወስዱ ተደርጓል።
ሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናዎችን በተመለከተ የ2013 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ለመፈተን ከተመዘገቡት
617,991 ተማሪዎች ውስጥ በ2014 ዓ.ም 598,676 ተማሪዎች በሁለት ዙር ፈተናውን ወስደዋል። በሀገር
አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ሪፎርም ምክንያት የአስፈጻሚ አካላትን እንደገና የማደራጀት ስራ መሰራቱ
ይታወቃል፡፡ በዚህ መሰረት የትምህርት ሚኒስቴርም እንደገና መደራጀቱን ተከትሎ የከፍተኛ ትምህርት
ዘርፉን የ10 አመት እቅድ ከመከለስ በተጨማሪ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ጥናት ምክረ ሀሳቦችን
መሰረት በማድረግ በርካታ የለውጥ ስራዎች ተከናውነዋል። ወደ ትግበራ ከገቡ ሪፎርም ስራዎች መካከል
የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተልዕኮና በትኩረት መስክ የማደራጀት፣ የቅድመ ምረቃ
ፕሮግራሞች የትምህርት ጊዜ ላይ ማሻሻያ ማድረግ፣ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ምሩቃን በጥናት የተለዩ
የእውቀትና የክህሎት ውስንነትን የሚያሻሽሉ የአንደኛ ዓመት የጋራ ኮርሶች ቀርጾ ወደ ትግበራ ማስገባት፣
የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ክለሳ ማካሄድ፣ አካዳሚክ ፕሮግራሞች በሀገር ውስጥና
በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የሚያገኙበትን የአክርዲቴሽን ስርዓት ማስተግበር እና በጤናና በህግ
ትምህርት መስኮች ሲተገበር የነበረውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ምሩቃን የመውጪያ ፈተና በሁሉም
የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ላይ ተግባራዊ የማድረግ ስራ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
3
መሰረት ከ2015 በጀት ዓመት ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከዕለት ዕለት ተለምዷዊ የበላይ አካላት
ቁጥጥር ነጻ ሆኖ በአገሪቱ ህግና የከፍተኛ ትምህርት ማዕቀፎች እየተመራ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ
ተልዕኮዎቹን እንዲወጣ ለማድረግ በተለያዩ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን
የሪፎርም ስራዎች ተጠናቀው የራስ ገዝ ማድረጊያው ቻርተር በመገባደድ ላይ የሚገኝ ሲሆን በ2015
መጀመሪያ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ መልሶ እንዲደራጅ ለማድረግ
ስራዎች ተሰርተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የተልዕኮ ልየታን መሰረት በማድረግ ለተልዕኳቸው ስኬት አወንታዊ
አስተዋጽኦ ሊያደርጉ የሚችሉ ከተለያዩ የሙያ ዘርፍ ልምድ ያላቸውን ከፍተኛ አመራሮችና
ባለሙያዎችን ያካተተ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ቦርድ በሁሉም ተቋማት እንደገና በማደራጀት የስራ
መመሪያ ተሰጥቶ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
አደረጃጀቶችን እንደገና በማጥናት ከሃብት አጠቃቀም አንጻር ግልጽ፤ ወጪ ቆጣቢ፣ ተመጋጋቢ እና ሁሉን
አቀፍ ለማድረግ በተልዕኮ ልየታቸው መሰረት ለምርምር፣ ለአፕላይድ፣ ለአጠቃላይ እና ለሳይንስና
ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ተስማሚ የሰው ኃይል አደረጃጀት ተጠንቶ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በማጸደቅ
ወደ ትግበራ ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አጠቃላይ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ቅበላ (በመደበኛና በተከታታይ
ትምህርት) ከ1,141,295 ወደ 1,522,615 ለማድረስ ታቅዶ 1,527,629 (100.3%) ማድረስ የተቻለ ሲሆን
በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመደበኛው ፕሮግራም 642,067 በተከታታይ ትምህርት 139,442
ተማሪዎችን መቀበል ተችሏል። በመደበኛ ፕሮግራም በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ
ምረቃ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከ141,295 ወደ 156,000 ለማድረስ ታቅዶ 160,014 (102.6%) ደርሷል።
እንዲሁም በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም እንደቅደም
ተከተላቸው 285,070 እና 61,000 ነው። በትግራይ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ከመማር ማስተማር ስራው
ውጪ ቢሆኑም ዓመታዊ የቅበላ ምጣኔው ከነበረበት 14.2 በመቶ ወደ 15.2 በመቶ አድጓል። አለም ባንክ
በ2021 ባወጣው ሪፖርት መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ጥቅል ተሳትፎ (Gross Enrollment Rate in
Higher education) በ2020 የአለም አማካይ ተሳትፎ 40%፣ ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገራት 27%
እና ከሰሀራ በታች ያሉ አገራት (በ2019) 9% መሆኑን ያሳያል።
4
በድህረ ምረቃ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተሳትፎ ከነበረበት 83,407 ወደ 107,327 ለማድረስ ታቅዶ
95,280 (89%) ማድረስ ተችሏል፡፡
በድህረ ምረቃ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ተሳትፎ ከነበረበት 4,265 ወደ 5,532 ለማድረስ የታቀደ ሲሆን
5,768 (104%) ደርሷል፣ በህክምና ትምህርት መስክ የስፔሻሊቲ ተማሪዎችን ተሳትፎ ከነበረበት 1,444 ወደ
3,000 ለማድረስ ታቅዶ 2,900 (97%) ደርሷል እንዲሁም የድህረ ስፔሻሊቲ ተማሪዎችን 100 ለማድረስ
ታቅዶ 66(66%) ማድረስ ተችሏል፡፡
በዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት 0.45% ወደ 0.9%
ለማሳደግ ታቅዶ 0.5 (56%) ማድረስ ተችሏል፡፡ በመጀመሪያ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት
34.3% ወደ 37.87% ለማሳደግ ታቅዶ በበጀት ዓመቱ 38.2(101%) ማድረስ ተችሏል፡፡ በዩኒቨርሲቲ
በሁለተኛ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት 15% ወደ 22% ለማሳደግ ታቅዶ 22.7(103%)
ማድረስ ተችሏል፡፡ በዩኒቨርሲቲ በሦስተኛ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት 9% ወደ 13%
ለማሳደግ ታቅዶ በበጀት ዓመቱ 11.5(85.5%) ማድረስ ተችሏል።
በተፈጥሮ ሳይንስ በመጀመሪያ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ 33% ታቅዶ አፈፃፀሙ 33% ደርሷል።
በዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ምጣኔ ድጋፍ የሚሹ ክልሎች ከነበረበት 3.4% ወደ 3.6%
ለማሳደግ የታቀዶ ከ3.4% በላይ ማሳደግ አልተቻለም፡፡
ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት 0.8% ወደ 0.9% ለማሳደግ ታቅዶ ልዩ ልዩ ተግባራት
የተከናወኑ ቢሆንም የበጀት ዓመቱ ክንውን ከ0.8 በላይ ማሳደግ አልተቻለም፡፡ በሳይንስና ቴክኖሎጂ
ፕሮግራሞች የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት 31.6 በመቶ ወደ 32.6 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ
አፈጻጸሙ 33 (101%) ነው። ስኮላርሽፕ ተጠቃሚ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከነበረበት 1% ወደ 1.3%
ለማሳደግ ታቅዶ ልዩ ልዩ ተግባራት የተከናወኑ ቢሆንም የበጀት ዓመቱ ክንውን ከ1 በመቶ በላይ ማሳደግ
አልተቻለም።
5
ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራማሪዎች ለምርምርና ቴክኖሎጂ ማመንጫና ማሳደጊያ የሚሆኑ የሃይ
ፐርፎርማንስ ኮምፒውቲንግና (HPC) የክላውድ አገልግሎቶች ከኢተርኔት ዳታ ማእከል አስፈላጊውን
ሶፍትዌር ዝግጁ በማድረግ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በክላውድ ቴክኖሎጂ የተተገበሩና አገልግሎት የሚሰጡ የተማሪ አስተዳደር
ስራውንና አገልግሎቶችን የሚያሳልጡ የቴክኖሎጂ መተግበሪያዎችን (Enterprise Resource Planning)
አገልግሎት ዝግጁ በማድረግ በዚህ አመት ለመስጠት ከታሰበው የኦንላይን አገልግሎቶች (ተማሪ ቅሬታ
የሚያቀርብባቸው፣ የ12ኛ ክፍል ውጤትና ምደባ የሚያይባቸው፣ ዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ አቅምና የተመደቡ
ተማሪዎችን የሚያዩባቸው…ወዘተ) በማእከል በማልማት አግልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከእቅድ አንፃር
100% ተፈፅሟል፡፡
በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የዘመነና የተቀናጀ የመረጃ አመራር
የማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም Higher Education and Training Management Information
System (HETMIS) የKPI፣ የዳሽቦርድ፣ የዳታ ቤዝ ዲዛይንና የሲስተም ዲቨሎፕመንት ተጠናቆ ስልጠና
በመስጠት ወደ ትግበራ ተገብቷል፣ አፈጻጸም (100%) ነው፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ የተለያዩ የምርምር ጆርናሎች ውስጥ በአለም አቀፍ የጆርናል ኢንዴክሲንግ መረጃ
ውስጥ የተካተቱት በሚመለከት በSCOPUS 4(Ethiopian journal of health sciences, Ethiopian
medical journal, Ethiopian journal of health development, and Bulletin of chemistry በPubMed
እና Web of Sciences 2 (Ethiopian journal of health sciences, Ethiopian medical journal
ይገኙበታል።
6
በሀገራዊ ደረጃ የትስስር ስራን የማስተባበር ኃላፊነት እና ተግባራት አንዱ የሆነውን በከፍተኛ ትምህርትና
ስልጠና ምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪ ትስስር ቀጠናዊ ክላስተር በተመለከተ 400 አምራችና አገልግሎት
ሰጪ ኢንዱስትሪዎች፤ 75 ምርምር ተቋማት እና 104 ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ትስስር ፈጥረው
ተሳትፈዋል፡፡ የተቀዱ፣ የተላመዱ እና የተፈጠሩ ቴክኖሎጂዎችን መለየትና ማጠናቀር እንዲሁም
ለማህበረሰቡ እና ለኢንዱስትሪዉ ከማሸጋገር አንጻር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበጀት ዓመቱ 190
ቴክኖሎጂዎች ለማሸጋገር የታቀደ ሲሆን በ33 ዩኒቨርሲቲዎች 452 መምህራን አማካኝነት አጠቃላይ 120
ቴክኖሎጂዎች ተሸጋግረዋል፡፡
በተጨማሪም 350 የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ለማከናወን ታቅዶ 195 የማህበረሰብ አገልግሎት
ፕሮጀክቶች ማከናወን የተቻለ ሲሆን ይህም የዕቅዱ 55.7% ነው፡፡ ከማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች
ውስጥ 38% ውጤታማ እንዲሆኑ ታቅዶ 28% ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ ሲሆን ይህም የዕቅዱ 73.6%
ነው፡፡
በአጠቃላይ ከላይ የተከናወኑት ተግባራት በበጀት ዓመቱ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ የፀጥታ
ችግር ምክንያት የትምህርት ማህበረሰብ መፈናቀልና የትምህርት ተቋማት መጎዳት ወይም ለመጠለያነት
ማገልገል፣ በትምህርት ማህበረሰቡ ላይ የስነ ልቦናና የአዕምሮ ጤና መረበሽ፣ የአየር ንብረት ለውጥ
ተከትሎ የተከሰተ ድርቅ፣ የCOVID-19 ወረርሽኝ፣ የመፈጸም አቅም ውሱንነት የትምህርት ሴክተሩን
ያጋጠሙት አበይት ተግዳሮቶች ናቸው፡፡
በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የተተገበሩ ስልቶችን በማስፋት ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን
ትምህርት ለማስጀመር የተሻለ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን በላቀ መልኩ
ለማከናወን የሚያስችለን ቁመና ላይ ለመድረስ በሁለቱም ዘርፎች ቀጣይ ተግባራት የሚከናወኑ ይሆናል።
7
መግቢያ
ሁለንተናዊ እድገትን በማምጣት የሕዝቦችን ኑሮ ማሳደግ የሚቻለው በሚኖረው የሰው ሃይል አቅም ነው።
ዛሬ በሳይንስና ቴክኖሎጂ በልጽገው በአገራቸው ልማትን በማምጣት የሕዝባቸውን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ
እና ያረጋገጡ ሀገሮች ልምድ የሚያሳየው ይህንኑ ሀቅ ነው፡፡ በተለይ በቅርብ ዓመታት ከድህነት ወለል
በታች የነበሩና ከዚህ ችግራቸው ወጥተው ከፍተኛ የሣይንስና ቴክኖሎጂ እድገት ላይ የደረሱ ሀገሮች
ተሞክሮ ይህን ያሳያል። እነዚህ ሀገሮች ለትምህርትና ስልጠና በሰጡት ትኩረት የሰው ሀይል ሀብታቸውን
በከፍተኛ ደረጃ በማልማት ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ የሕዝባቸውን ኑሮ ማሻሻል ችለዋል። ከዚህ
የምንረዳው ትምህርት ብቁና በቂ የሰው ሃይል በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ነው።
የሀገራችን ትምህርትና ስልጠና ዋና ዓላማ ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና በማቅረብ አገራችን
በዝቅተኛ፣ መካከለኛና በከፍተኛ ደረጃ የሚያስፈልጋትን ብቁና በቂ የሰው ሃይል በማፍራት ኢትዮጵያ
አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ማሳካትና የሀገራችንን ብልፅግና እውን ለማድረግ የ10
አመት የትምህርት ዘርፍ ልማት እቅድ እና ከዚሁ እቅድ የተወሰደ የስድስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት
መርሀግብር (ESDP-VI) እና ከ10 ዓመቱና ከቀጣይ 5 አመት እቅድ መነሻ በማድረግ፤ መንግስት
የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ባወጣው አዋጅ መሰረት ተከልሶ የ2014 በጀት አመት
እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህም መሰረት በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ፣ የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፣ የትምህርትና
ስልጠና ባለስልጣን እና የትምህርት ስራ አመራር እና ድጋፍ ዘርፍ የ2014 ዓ.ም አመታዊ እቅድ
አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚከተለው በዝርዝር ቀርቧል።
8
ክፍል አንድ
1. የትምህርት ዘርፉ ስትራቴጂያዊ መሰረቶች
1.1. የትምህርት ፍልስፍና /Educational Philosophy/
ለሀገራቸው ብልፅግና የሚተጉ በሁለንተናዊ ስብእናቸው ብቁ የሆኑ ዜጎች በ2022 ለምቶ ማየት፡፡
ፍትሀዊ፤ አካታች እና ተደራሽ የሆነ ጥራቱና አግባብነቱ የተረጋገጠ በመልካም አስተዳደር ላይ የተገነባ
የህይወት ዘመን ትምህርትና ስልጠና አካል የሆነ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርት ከቅድመ አንደኛ እስከ
ከፍተኛ ትምህርት ድረስ ለዜጎች ማቅረብ እና ዘርፈ ብዙ ጥናትና ምርምር በማካሄድ ቴክኖሎጂዎችን
ማሸጋገርና የማኅበረሰብ አገልግሎት መስጠት፡፡
9
ክፍል ሁለት
የትምህርት ጥራት መጓደል ምክንያት ከሆኑት አንዱ ያሉን ትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት አብዛኞቹ
ከደረጃ በታች መሆናቸው ነው። በመሆኑም በትምህርት ሚኒስቴር እና በሁሉም አካላት ተሳትፎ
በሚቀጥሉት ዓመታት ደረጃቸውን የማሻሻል ስራ መስራት እንደተጠበቀ ሆኖ በአገራችን በሁሉም ክልሎች
የሚገነቡ ከአገራችን ከሁሉም አካባቢዎች የሚመጡ ተማሪዎች የሚማሩባቸው 50 ልዩ አዳሪ እንዲሁም 50
ልዩ ሞዴል የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችን ለመገንባት የስታንዳርድ ክለሳ እና አዲስ የግንባታ ዲዛይን
ጽንሰሀሳብ ስራ ተጠናቆ ዝርዝር የግንባታ ዲዛይኖች ተሰርቷል።
የትምህርት መሰረተ ልማትን ከማስፋፋት ጎን ለጎን የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል “አዲስ የኢትዮጵያ
ትምህርት ቤት” የሚል የትምህርት ቤት ዲዛይን የተዘጋጀ ሲሆን ዲዛይኑን በመጠቀም በጦርነቱ ምክንያት
የወደሙ 1335 (አፋር 65፣ አማራ 1028፣ ቤ/ጉሙዝ 55፣ ኦሮሚያ 165፣ ደቡብ 22) ትምህርት ቤቶችን
መልሶ በተሻለ መልኩ ለመገንባት ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ በሌላ በኩል 4882 በከፊል የተጎዱ ትምህርት
ቤቶች ክልሎች በራሳቸው አቅም እንዲያድሱ መግባባት ላይ ተደርሷል።
10
ተጠናቀው የራስ ገዝ ማድረጊያው ቻርተር በመገባደድ ላይ የሚገኝ ሲሆን በ2015 መጀመሪያ አዲስ አበባ
ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ መልሶ እንዲደራጅ ስራዎች ተሰርተዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስራ አመራር ቦርድን እንደ ተቋማቱ ልየታ መሰረት ተቋማቱን ተልእኮ
ሊያግዙ የሚችሉ የተለያዩ የሙያ ዘርፍ ልምድ ያላቸውን አመራሮችና ባለሙያዎችን የያዘ አዲስ ቦርድ
ተቋቁሞ የስራ መመሪያ በመስጠት ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
ከሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቅድመ ምረቃ ሁሉም ፕሮግራሞች ተመርቀው የሚወጡ ተማሪዎች
ከ2015 ዓ.ም ማብቂያ ጀምሮ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) እንዲወስዱ ቀደም ተብሎ በተጀመሩ የጤና
እና የህግ ፕሮግራሞች ላይ ያለውን አሰራር በሁሉም የትምህርት መስኮች ለማስፋት የማስፈጸሚያ
መመሪያ ተዘጋጅቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተሰርቷል።
በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የዘመነና የተቀናጀ የመረጃ አመራር
የማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስስም Higher Education and Training Management Information
System (HETMIS) ለመስጠት የKPI፣ የዳሽቦርድ፣ የዳታ ቤዝ ዲዛይንና የሲስተም ዲቨሎፕመንት ስራ
ተጠናቆ ስልጠና በመስጠት ወደ ትግበራ ተገብቷል፣ አፈጻጸም (100%) ነው።
በትምህርት ፍኖተ ካርታ ጥናት ምክረ ሀሳቦች መነሻነት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን
በተልዕኮና በትኩረት መስክ የመለየት ስራ በተካሄደው መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተልዕኮና
ትኩረት መስክ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል።
11
ክፍል ሶስት
ያልተማከለ የትምህርት አስተዳደር ስርአትን በውጤታማነት ተግባራዊ ያደረጉ ተቋማት ድርሻ በ2013ዓ.ም
ከነበረበት 50% በ2014ዓ.ም ወደ 60% ማድረስ ታቅዶ 53%፤ በየደረጃው የተደራጀና ውጤታማ የሆኑ
የተማሪ ወላጆች ማህበር በ2013 ዓ.ም ከነበረበት 50% በ2014ዓ.ም ወደ 60% ማድረስ ታቅዶ 54%፤
የህብረተሰብ ተሳትፎ አጎልብተው በመጠቀም ውጤታማ የሆኑ ትምህርት ቤቶች በ2014ዓ.ም 100%
ማድረስ ታቅዶ 82% መድረሱ፣ እንዲሁም የብቃት ደረጃውን ያሟሉ አመራሮችና ባለሙያዎች ድርሻ
በ2013ዓ.ም ከነበረበት 60% በ2014ዓ.ም ወደ 75% ማድረስ ታቅዶ 65% ማድረሰ ተችሏል፡፡ ግቡን
ለማሳካት በትምህርት እቅድ አዘገጃጀት፣ አፈጻጸም፣ ክትትልና ግምገማ ዙሪያ ለ1200 ር/መምህራን፣
ሱፐርቫይዘሮች እና የወረዳ ጽ/ቤት ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ለ1190 (99.2%)
የተሰጠ ሲሆን፤ ስልጠናውን ያገኙ የትምህርት ቤት እና የወረዳ አመራሮች ያገኙትን ስልጠና በጉድኝት
ማዕከላት እና በወረዳ ጽ/ቤቶች አማካኝነት ለሁሉም ትምህርት ቤት አመራሮች ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡
፡ ስልጠናው በተሰጠባቸው ትምህርት ቤቶች የሶስት ዓመት እና የአንድ አመት የድርጊት መርሃ ግብር
አዘገጃጀትና የትምህርት ቤት ግለ ግምገማ ሂደት እየተሻሻለ መሆኑን በተካሄዱት የክትትልና ድጋፍ
ስራዎች ማረጋገጥ ተችሏል። በመቀጠል የተከናወነው ተግባር ት/ቤቶች በቅርበት ክትትልና ድጋፍ
የሚያገኙበትን የሱፐርቪዥን አገልግሎት የሚተገበርበት ማዕቀፍ ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን
ማዕቀፉን በማዘጋጀት፣ ከክልሎች ጋር በተካሄደ መድረክ በማዳበር እና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በማከናወን
ለትግበራ ወደ ክልሎች ተሰራጭቷል።
በት/ቤት መሻሻል አተገባበርና አፈጻጸም ዙሪያ ከ120 የትምህርት አመራሩና ባለድርሻ አካላት ጋራ
የምክክር መድረክ ለማካሄድ ታቅዶ 95 (75%) ተሳታፊዎች በተገኙበት ተካሂደል፡፡ በውይይቱ ለቀጣይ
አሰራር ግብዓት የሚሆኑ ሃሳቦችና ተሞክሮዎች ተለይተው ለአፈጻጸም ይረዳ ዘንድ ለክልሎች
ተሰራጭቷል። የትምህርት አመራርና አደረጃጀት፣ የህብረተሰብ ተሳትፎና የፋይናንስ መመሪያ በረቂቅ
ደረጃ ከተዘጋጀው የትምህርት አዋጅና ፖሊሲ፣ ከወቅቱ የትምህርት አሰራርና አደረጃጀትና ሌሎች ወቅታዊ
ሁኔታዎችን ታሳቢ በማድረግ የማሻሻል ስራ ተከናውኗል። ከዚህ አንጻር የዚህ ተግባር አፈጻጸም 90% ላይ
ይገኛል።
12
በሌላ በኩል ብቃት ያላቸው እጩ መምህራንን ወደ ትምህርት ሥርዓቱ ለመሳብ የሚያግዝ፣ የመምህራን
አመላመል ፍትሃዊነትና ወጥነትን የሚያስጠብቅ፣ በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ እየተካሄዱ ካሉ ለውጦች ጋር
የተናበበ ሀገራዊ የመምህራን ምልመላና የርዕሳነ መምህራን ምደባ መመሪያዎች ተሻሽለው ተዘጋጅተዋል።
ለአራቱ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች (ሶማሌ፣ አፋር፣ ጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ጉምዝ) የሚሰጠውን ድጋፍ
ለማጠናከር በበጀት ዓመቱ 30 ባለሙያዎች እና 8 ተሽከርካሪ ለማሰማራት ታቅዶ፡ 24 ባለሙያዎች ከ8
ተሽከርካሪዎች ጋር ከነሙሉ ሎጀስቲክ በማሰማራት የተለያዩ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል። ከተከናወኑት
ተግባራት መካከል በአመቱ መጀመሪያ ሁሉም ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ
ለማድረግ የሚያስችል የትምህርት ንቅናቄ ሰነድ በማዘጋጀት ከክልል እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የሚገኙ
150,000 የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የንቅናቄ ስራ ለማከናወን ታቅዶ ለ129,876 (ወ
65,699፤ ሴ 64,177) 86.6% ተሳታፊዎችን በንቅናቄ ስራ ላይ ማሳተፍ ተችሏል። በተጨማሪም ልዩ
ድጋፍ በሚሹ ክልሎችና አርብቶ አደር አካባቢዎች ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለማምጣትና መጠነ
ማቋረጥን ለመከላከል የሚያስችል ሰነድ፣ በትምህርት ቤት አስተዳደር፣ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎጂ
ልማዳዊ ድርጊቶች ዙሪያ ለተጽእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ ለጎሳ መሪዎችና ለወላጅ-ተማሪ-መምህር ህብረት
ኮሚቴዎች 138 ተሳታፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር ለማከናወን ታቅዶ 126 (91.3%) ተሳታፊዎች
ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል፡፡ በኦሮሚያ እና በደቡብ አርብቶ አደር አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን
የድጋፍ ፋላጎትና በትምህርት አፈጻጸማቸው ዙሪያ ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ የሚያስችል አመላካቾች
የአፈጻጸም ትንተና ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡ የተሻለ አፈጻጸም ካላቸው የትምህርት ተቋማት መልካም ተሞክሮ
በመቀመር ለማስፋት የታቀደ ሲሆን በአራቱም ልዩ ድጋፍ በሚሹ ክልሎች የተሻለ አፈጻጸም ያላቸውን
በክልል ሁለት ትምህርት ቤት በድምሩ ስምንት ትምህርት ቤቶችን በመምረጥ ከአራቱ ክልሎች የተውጣጡ
160 (አፈጻጸም 100%) ባለሙያዎች፣ ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የልምድ ልውውጥ አከናውነዋል፡፡
እንዲሁም በመስክ በተሰማሩ አማካሪ ባለሙያዎች አማካይነት ድጋፍ በሚደረግባቸው የተመረጡ
ወረዳዎችና ትምህርት ቤቶች ለትምህርት አመራር፣ ባለሙያዎች፣ መምህራንና ለወላጅ-ተማሪ-መምህር-
ህብረት አባላት በተከታታይ የሙያ ማሻሻያ እቅድ አዘገጃጀትና አተገባበር፣ የተፋጠነ የትምህርት ቤቶች
ደረጃ ማሻሻያ፣ የመረጃ አያያዝ፣ የህብረተሰብ ተሳትፎ፣ የትምህርት ቤት መሻሻል እቅድ፣ በትምህርት ቤት
ድጎማ በጀት አጠቃቀም መመሪያ፣ በአካባቢና ማህበረሰብ ጥበቃ፣ በወላጅ- ተማሪ- መምህር-ህብረት
አደረጃጀት መመሪያ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለ1000 ተሳታፊዎች ለመስጠት ታቅዶ ክንውኑ
በሶማሌ ክልል 275፣ በአፋር ክልል 62 ፣ጋምቤላ 321፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ 130 ሲሆኑ በጠቅላላው 788
(78.8%) ተሳታፊዎች በስልጠናው ተሳታፊ ሆነዋል።
ባለፉት ዓመታት በስራ ላይ የነበሩትን የተለያዩ የአጠቃላይ ትምህርት ኢንስፔክሽን ሰነዶችን አሁን ካለው
የትምህርት ለውጥ አንጻር ተጣጥሞ ተዘጋጅቷል፡፡ እነዚህ የተከለሱ የኢንስፔክሽን የትግበራ ማዕቀፎች እና
መመሪያዎች ለ120 የክልል እና ከተማ አስተዳደር የኢንስፔክሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የትውውቅ
ስልጠና ለመስጠት የታቀደ ሲሆን ለ70 ተሳታፊዎች (58.3%) ለማከናወን ተችሏል፡፡ የተሳታፊዎች ቁጥር
13
አነስተኛ የሆነበት ምክንያት በሃገሪቱ ካለው የጸጥታ ችግር አንጻር የአንዳንድ ክልል ተሳታፊዎች መገኘት
ባለመቻላቸው ነው። ሰነዶቹ ለክልሎች በሶፍት እና በሃርድ ኮፒ እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
የትምህርት ቤት ድጎማ በጀት አጠቃቀም በተመለከተ በ2011 እና በ2012 ዓ.ም በገለልተኛ አካል
የተካሄደው ኦዲት ምርመራ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ክፍተት መኖሩን አመላክቷል። እነዚህ ክፍተት
በታየባቸው ትምህርት ቤቶች ላይ የእርምት እርምጃ ተወስዷል። የታየው የኦዲት ክፍተት ዳግም
እንዳይከሰት እና ተመሳሳይ ጉድለቶች እንዳይታዩ ለመከላከል ይረዳ ዘንድ ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ
100 የወተመህ አባላት፣ የክልልና የዞን የትምህርት ባለሙያዎች፣ የክልል GEQIP-E አስተባባሪዎች እና
የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር መድረክ ለማካሄድ ታቅዶ 85 ተሳታፊዎች የተገኙ
ሲሆን አፈጻጸሙም 85% ደርሷል።
ከላይ እንደተመላከተው በሁሉም ተግባራት የታሰበውን ዒላማ ማሳካት አልተቻለም፡፡ ለዚህ ዝቅተኛ
አፈጻጸም ምክንያቱ ባጠናቀቅነው በጀት ዓመት በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል እና በሌሎች ውስን አካባቢዎች
የነበረው የጸጥታ ችግር የታቀዱ ተግባራት አፈጻጸም እና ሽፋን ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ዓመታዊ
ግቡን ለማሳካት ፈታኝ አድርጎታል፡፡ የዚህ አፈጻጸም ጉድለት በ2015ዓ.ም ዒላማ ላይ ተጨማሪ ተግባራት
በመሸጋገራቸው ጫና የሚፈጥር ሲሆን በ2017 ዓ.ም 90% ለማድረስ የታቀደውን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ
ርብርብ መደረግ እንዳለበት ያመላክታል።
ይህን ግብ ለማሳካት ከተከናወኑ ተግባራት ውስጥ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የድጎማ በጀት
ለትምህርት ቤቶች የማሰራጨት ስራ አንዱ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የ2014 ዓ.ም የትምህርት ቤት ድጎማ
በጀት ድልድል የ2013 ዓ.ም የትምህርት አመራር መረጃ ስርዓት ስታቲስቲክስንና የትምህርት ቤቶች
ድጎማ በጀት መመሪያን መሰረት በማድረግ ለሁሉም የመንግስት ትም/ቤቶች (ኦ-ክፍልን ጨምሮ) 1.3
ቢሊየን ብር ተሰራጭቷል። ለአራቱ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ (አፋር፣ ሶማሌ፣ ጋምቤላ እና ቤ/ጉሙዝ) ክልሎች
ከአለም ባንክ ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት እስከ DECEMBER 31/2021 ድረስ 70% ለሚሆኑ
ትምህርት ቤቶች ለማድረስ ታቅዶ 87.6% ትምህርት ቤቶችን በወቅቱ ማድረስ በመቻሉ 10 ሚሊዮን
የአሜሪካን ዶላር ማግኘት ተችሏል። የነበረው የድጎማ በጀት መመሪያ ስደተኞችንና በመጠለያ ጣቢያ ያሉ
ትምህርት ቤቶችን የማያካትት በመሆኑ እነዚህን ባካተተ መልኩ የድጎማ በጀት መመሪያ ተሻሽሎ
ተዘጋጅቷል።
ሀገር አቀፍ የወላጆች ህብረት እስከ ወረዳ ድረስ ተደራጅቶ እና ህጋዊ ሰዉነት አግኝቶ ወደ ተግባር
ተገብቷል፡፡ በትምህርት ቤት ደረጃ የሚገኘው ወተመህ (ወላጅ ተማሪ መምህር ህብረት) በማጠናከር
የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማገዝና ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቶችን በእኔነት ስሜት እንዲያግዝ ለማስቻል
በሙያ፣ በገንዘብና በዓይነት ያደረገውን ተሳትፎ ከማሳደግ አንጻር በ2014 የበጀት ዓመት 12 ቢሊዮን ብር
14
የሚገመት ሃብት ለማሰባሰብ ታቅዶ 11.3 ቢሊዮን ብር ማሰባሰብ የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙም 94.1% ላይ
ይገኛል። ግቡ ሲቀመጥ የአማራ፣ አፋር እና ቤ/ጉሙዝ ክልሎች አካቶ ሲሆን በእነዚህ አካባቢ የነበረው
የፀጥታ ችግር በግብ ስኬቱ ላይ ተጽእኖ ፈጥሯል።
ግቡን ለማሳካት ከተከናወኑ ተግባራት መካከል ለአራቱ ታዳጊ ክልሎች እና በጦርነት ምክንያት ስልጠና
ካላገኙ አካባቢዎች ለተወጣጡ 120 የኢንስፔክሽን ባለሙያዎች ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ወንድ 89 ሴት
4 በድምሩ 93 (77.5%) ባለሙያዎች በኢንስፔክሽን መመሪያ፣ የአፀደ ህፃናት፣ የመጀመሪያና መካከለኛ
ደረጃ፣ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ማዕቀፎችና ቼክሊስቶች ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ የተዘጋጀውን የመረጃ ዳታ
ቤዝ ከክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ 50 (100%) የመረጃ ትንተና እና የድጋፍና ክትትል
ባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት አስተያየቶችን በማካተትና በማስተካከል የተዘጋጀው ዳታ ቤዝ በትምህርት
ሚኒስቴር ሰርቨር ላይ ተጭኖ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል።
በግል ባለሀብት፣ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች /የሲቪል ማኅበራት፣ በሃይማኖት ተቋማት ባለቤትነት/
የሚቋቋሙ ትምህርት ቤቶች በክልሎች የሚሰጡ የትምህርት ቤቶች እውቅና፤ ፈቃድና እድሳት እንዲሁም
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚከፈቱ የሌሎች ሀገራት ማህበረሰብ (COMMUNITY) እና ዓለም ዓቀፍ ት/ቤቶች
በተሰጣቸው ፍቃድ መሰረት ሥራቸውን እያከናወኑ መሆናቸውን በ26 ትምህርት ቤቶች ላይ ክትትልና
ድጋፍ ለማድረግ ታቅዶ በ19 ትምህርት ቤቶች ተደርጓል።
በት/ቤቶች ኮድ አሰጣጥ ችግር ያለባቸውን ት/ቤቶች ለማጥራት ለ30 ባለሙያዎች ሥልጠና ታቅዶ ሁሉም
እንዲሰለጥኑ በማድረግ ለ9003 የአንደኛ ደረጃ ትም/ቤቶች የትምህርት ቤት ኮድ /SCHOOL CODE/
የማስተካከል ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ የተዘጋጀውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሁለተኛው ዙር
የኢንስፔክሽን ትንተና ሪፖርትና ኦ ክፍል ኢንስፔክሽን ማዕቀፍ በሶፍት ኮፒ ማሰራጨት ተችሏል፡፡
የ2,160 ምዕራፍ አንድ ት/ቤቶች የኢንስፔክሽን ሥራ ተከናውኗል፡፡በተገኘውም ውጤት ላይ
ከክልሎች/ከተማ አስተዳደር ከተውጣጡ 125 የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር የምክክር አውደ
ጥናት ለማካሄድ ታቅዶ 95 (76%) ተሳታፊዎች በተገኙበት የሪፖርቱን ተገቢነት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 3ኛ ዙር የኢንስፔክሽን አገልግሎት በክልል ደረጃ ያለው
15
አፈጻጸም የሚለያይ ከመሆኑም በላይ ደቡብ ብ/ብ/ህና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ሪፖርት
ባለማቅረባቸው ሃገራዊ አማካይ አፈጻጸሙ ከእቅድ በታች ነው፡፡ በተለይም የሁለተኛ ደረጃው ዝቅተኛ
ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው የአመራሩ ድጋፍና ክትትል እና የባለሙያ የመፈጸም አቅም ጉድለት ያለበት
በመሆኑ ነው፡፡
የመምህራን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና በተመለከተ፡- የመምህራን የሙያ ፍቃድ ምዘና በ2014 ዓ.ም ወደ
85% ለማድረስ ታቅዶ 72% ማድረስ የተቻለ ሲሆን፣ የትምህርት ቤት አመራሮች የብቃት ማረጋገጫ
ምዘና በ2014 ዓ.ም ወደ 65% ለማድረስ ታቅዶ 41% ማድረስ ተችሏል።
በሁሉም ደረጃ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁና የተከለሱ የመማሪያ ማስተማሪያ መጻህፍት
ብዛትን በ2013 ዓ.ም 70% ከነበረበት በ2014 ዓ.ም ወደ 100% ማድረስ ታቅዶ 100% ማድረስ ተችሏል።
በ2014 ዓ.ም አንደኛ ደረጃና የመካከለኛ ደረጃ የመፀሀፍት ተማሪ ጥምርታ ወደ 1፡1 ማድረስ ታቅዶ 1፡1.3
ደርሷል። በሌላ በኩል በአዲሱ ስርአተ ትምህርት የአንደኛ ደረጃ እና የመካከለኛ ደረጃ የሙከራ ትግበራ
የመፀሀፍት ተማሪ ጥምርታ 1፡1 ማድረስ ታቅዶ 1፡2 ደርሷል፡፡ አፈጻጸሙ ሲታይ ዝቅተኛ ነው፡፡
16
ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪ መጽሐፍት እና የመምህር
መምሪያዎችን ለሚያዘጋጁ 4222 አዘጋጆች፣ ኢዲተሮች፣ ኢላስትሬተሮችና ዲዛይነሮች በትምህርት
ሪፎርም፣ በስርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ፣ በመርሃ-ትምህርት፣ በተማሪ መጽሐፍትና በመምህሩ መምሪያ
አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ አፈጻጸሙም ከእቅድ አንጻር 100% ነው፡፡ በዚህ ስልጠና መነሻነት
በአንደኛ ደረጃ እና መካከለኛ ደረጃ በሚሰጡ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተማሪው መማሪያ እና
የመምህሩ መምሪያ መጽሃፍት በሙከራ ትግበራ ላይ ውለዋል፡፡ የአጠቃላይ ትምህርት አዲሱን ስርዓተ
ትምህርት ለመምህራን እና የባለድርሻ አካላት በትምህርት ሪፎርም፣ በአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ
ትምህርት ማዕቀፍ፣ የየትምህርት ዓይነቱ መርሃ-ትምህርት፣ የተማሪ መጽሐፍት እና የመምህር መምሪያ፣
የስርዓተ ትምህርቱ የሙከራ ትግበራ ጉዳዮች ላይ ለ169 ከክልል ለተውጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች
ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ እነዚህ የአሰልጣኞች ስልጠና የወሰዱ ባለሙያዎች ለመምህራን ስልጠናውን
በመስጠት በ589 አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሙከራ ትግበራ ተካሂዷል፡፡ ከሙከራ
ትግበራ በተገኘ ግብዓት መሰረት ሥርዓተ ትምህርቱ ላይ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ተሻሽለው ወደ
ህትመት ተገብቷል፡፡
ክልሎች ለትምህርት ሚኒስቴር ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል የግብረገብ ትምህርት 6 የተማሪው መማሪያ
መጻሐፍት እና 6 የመምህሩ መምሪያ በአጠቃላይ 12 መማሪያ ማስተማሪያ መፃህፍት እንዲያዘጋጅ
በሰጡት ውክልና እና የድጋፍ ጥያቄ መሰረት የመማሪያ ማስተማሪያ መፃህፍት ዝግጅት ተጠናቆ
በባለድርሻ አካላት ለማስተቸትና ለማፀደቅ ዝግጁ ሆኗል።
ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በ2014 ዓ.ም የሙከራ ትግበራ ለማካሄድ እቅድ የተያዘ ሲሆን ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ጋር በተገባው ውል መሰረት 100 መማሪያ ማስተማሪያ መጻሕፍት ተዘጋጅተው በውጪ የገምጋሚ
ቡድኖች ተገምግሞ በወቅቱ ባለመጠናቀቁ ምክንያት የሙከራ ትግበራው አልተከናወነም።
በአዲሱ የትምህርት እርከን አወቃቀር መሰረት ለሚያስተምሩበት የትምህርት ደረጃ የሚመጥን የትምህርት
ዝግጅት ያላቸው መምህራን በተመለከተ በ2014ዓ.ም ዲፕሎማ ያላቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራን
26800፤ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን 146806፤
የማስተርሰ ዲግሪና በላይ ያላቸው የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን 23269 ለማድረስ ታቅዶ ፤
ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን 8759 (32.68%) ፣
17
የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ መምህራንን 70330 (47.9%) ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራንን 16196
(69.6%) ለማድረስ ተችሏል።
በ2014 ዓ.ም ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት
ርዕሰ መምህራን 37747 (86.4%) ለማድረስ ታቅዶ ከጠቅላላው 44589 ር/መምህራን መካከል 25213
(56.5%)፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን 5136 (82.8%) ማድረስ ታቅዶ ከ6510 የሁለተኛ
ደረጃ ር/መምህራን መካከል 2233 (34%) ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት አሟልተዋል፡፡
በተመሳሳይ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው የአንደኛ ደረጃ ክላስተር ሱፐርቫይዘሮች
6611(97.8%) ለማድረስ ታቅዶ ካሉት 7125 ክላስተር ሱፐርቫይዘሮች መካከል 5198 (73%) ደረጃውን
አሟልተዋል፡፡ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው የሁለተኛ ደረጃ ሱፐርቫይዘሮች 100%
ለማድረስ ታቅዶ ካሉት 1031 የሁለተኛ ደረጃ ሱፐርቫይዘሮች መካከል 527(51%) ለደረጃው የሚመጥን
የትምህርት ዝግጅት አሟልተዋል።
ትምህርት ቤትን መሠረት ባደረገ ተግባራዊ የርዕሳነ መምህራን ሥልጠና መርሀ ግብር አፈጻጸም ላይ
ለ334 ለክልል /ለዞን /ለወረዳ ትምህርት አመራሮች እና ለ489 ክላስተር ሱፐርቫይሮች በ31 የስልጠና
ጣቢያዎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት በ10 ክልሎች /ትግራይን ሳይጨምር/ እና በሁለት ከተማ
አስተዳደሮች ብዛታቸው 1238 የሚሆኑ /502 ዋናና 736 ምክትል ርዕሳነ መምህራን/ የሁለት ቀን
የቱቶሪያል ሥልጠና ከመውሰዳቸውም ባሻገር ወደ ትምህርት ቤታቸው ተመልሰው በመሪ አሰልጣኞች
እየተደገፉ የተግባራዊ ሥልጠናውን የመጀመሪያ ሞጁል አጠናቀዋል፣ ይህም የእቅዱ 100% እንደተከናወነ
ያሳያል።
የአፍ መፍቻና እንግሊዝኛ ቋንቋ በተመለከተ የሃገር ውስጥና የውጪ ሃገር የትምህርት ቋንቋዎች አተገባበር
ሦስት፣ የመካከለኛ ደረጃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ላብራቶሪና የክበባት አተገባበር ሁለት ረቂቅ መመሪያዎች እና
የአፍ መፍቻና እንግሊዝኛ ቋንቋ ማዕከላት አጠቃቀም ሁለት ማንዋሎች ለማዘጋጀት በታቀደው መሰረት
ተዘጋጅቷል፡፡ 24000 የእንግሊዝኛና የአፍ መፍቻ ቋንቋ መምህራንን ለማሰልጠን ታቅዶ በበጀት እጥረት
ምክንያት ማሰልጠን አልተቻለም፡፡
18
በአጠቃላይ በ2014 ዓ.ም ለየትምህርት ደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንና
ትምህርት ቤት አመራሮች የማፍራት እቅድ አፈጻጸም ዝቅተኛ ሊሆን የቻለው በትምህርት ስርአቱ
እየተደረጉ ካሉ ለውጦች ጋር ተያይዞ የስልጠና ስትራቴጅዎችን መከለስ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ አዲስ
የስልጠና ስርዓት ትምህርት ዝግጅት እየተከናወነ በመሆኑና የመምህራን ማሰልጠኛ ሥርዓተ ትምህርት
ከመደበኛው የአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ጋር አናቦ ማዘጋጀትና ወደ ሥራ ማስገባት
በማስፈለጉ እንደዚሁም ባለፉት አመታት በተለያዩ የስልጠና ሞዳሊቲዎች (በተለይ በክረምት) ለመምህራን
ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በኮቪድ 19 ወረርሽኝና በጸጥታ ችግር ምክንያት የትምህርት መቋረጡ በዋናነት
ተጠቃሽ ናቸው።
ይሁን እንጂ ከ2014 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ በሀገራችን የሚገኙ ሁሉም የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋማት
እጩ የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ መምህራንን ተቀብለው በዲፕሎማና በዲግሪ መርሀ ግብር
ማሰልጠን ጀምረዋል፡፡ እንደዚሁም ቀደም ሲል በኮቪድና በሀገራችን ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት
ከትምህርታቸው ተስተጓጉለው የነበሩ የክረምት ሰልጣኞች ከ2014 ዓ.ም የክረምት ወቅት ጀምረው
የቀሯቸውን ኮርሶች በማጠናቀቅ ይመረቃሉ፡፡ ይህም ለሚያስተምሩበት የትምህርት ደረጃ በቂ ዝግጅት
ያላቸው መምህራን አቅርቦትን ይጨምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በSTEAM 2014 ዓ.ም ፕሮግራም የሳይንስ ላብራቶሪ የተሟላላቸው የትምህርት ተቋማት ወደ 30%
ለማሳደግ ታቅዶ 25% የተፈጸመ ሲሆን በSTEAM የመምህራን ስራ ላይ ስልጠና 35% ለማሳደግ ታቅዶ
25% ተከናውኗል፡፡ ለ200 ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በ STEAM ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ
ከሁሉም ክልሎች (ከትግራይ በስተቀር) ለተውጣጡ 128(64%) ርዕሰ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች
ሥልጠናው ተሰጥቷል፡፡ ለ160 የፊዝክስ መምህራን ተግባር ተኮር ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ 113
(70.63%) መምህራን ስልጠናውን ወስደዋል፡፡
ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ 734 የሂሳብና ሳይንስ ቁልፍ የ5ኛ እና 6ኛ ክፍል አሰልጣኝ መምህራንን
ለማሰልጠን ታቅዶ 717 (92%) ማሳካት ተችሏል፡፡ የሂሳብና ሳይንስ ትምህርቶች ችግሮችና የመፍትሄ
19
አቅጣጫዎች ላይ ጥናትና ምርምር ጉባኤ ለማካሄድ ታቅዶ 21 ጥናታዊ ጹሁፎች ቀርበው ውይይት
ተደርጎባቸዋል አፈጻጸሙም 100% ነው።
በሳይንስ ፈጠራ ስራ ውድድር በሀገር አቀፍ ደረጃ በፈጠራ ስራ ለ60 መምህራንና ለ60 ተማሪዎች
እውቅና ለመስጠት ታቅዶ 114 የተማሪዎችና የመምህራን የሳይንስ የፈጠራ ስራ ፕሮጀክቶች ለውድድር
የቀረቡ ሲሆን የተሻለ የፈጠራ ስራ ላቀረቡ 28 ተወዳዳሪዎች በፌዴራል ደረጃ እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የፌዴራል ሁለት STEAM የልህቀት ማዕከል ቤተሙከራዎችን በግብዓት ለማሟላት የታቀደ ሲሆን በበጀት
እጥረት ምክንያት መስራት አልተቻለም።
የትምህርት ቤቶች በግብዓት፣ በሂደትና በውጤት ያሉበትን ደረጃ ለመለየት በተዘጋጀው መስፈርት
ተለክተው ደረጃ 3 የደረሱ የቅድመ አንደኛ፣ መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2013 ዓ.ም
ከነበረበት 0%፣ 7.8% እና 16.2% በቅደም ተከተል በ2014 ዓ.ም በሁሉም የትምህርት ቤት ደረጃ 22%
ለማድረስ ታቅዶ ቅድመ መደበኛ 3.6%፣ አንደኛ እና መካከለኛ 8.15% እና ሁለተኛ ደረጃ 18.11%
ማድረስ ተችሏል። ደረጃ 4 የደረሱ የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት
ቤቶች በ2013 ዓ.ም በሁሉም የትምህርት ቤት ደረጃ ከነበሩበት 0% በ2014 ዓ.ም ወደ 6 % ለማድረስ
ታቅዶ የቅድመ አንደኛ 0.11% አንደኛና መካከለኛ 0.02% እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 0.09%
ማድረስ ተችሏል።
አዳዲስ 560 የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት
ታቅዶ አፈጻጸሙ1208 የቅድመ አንደኛ፣ 699 አንደኛና መካከለኛ ደረጃ እና 133 የሁለተኛ ደረጃ
በአጠቃላይ 2150 አዳዲስ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን አፈጻጸሙ ከመቶ ፐርሰንት በላይ ነው፡፡ ልዩ
ተሰጥኦና ችሎታ ያላቸው ከሁሉም ክልሎች ተወዳድረው በመግባት ትምህርታቸውን የሚከታተሉበት 50
ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በሁሉም ክልሎች በተመረጡ ቦታዎች ለመገንባት ታቅዶ
የዲዛይን ስራ፣ የቦታ መረጣና የሃብት ማፈላለግ ሥራ ተከናውኗል፡፡ እንዲሁም ለ200 የቅድመ አንደኛ፣
20
አንደኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እድሳት እና ጥገና ለማካሄድ ታቅዶ 25851
የተጠገኑ ሲሆን 15171 ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች ተገንብተዋል።
537 ትምህርት ቤቶችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ 1557 ትምህርት ቤቶችን
ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ እንዲሁም 374 ትምህርት ቤቶችን የመጸዳጃ አገልግሎት እንዲኖራቸው
ለማድረግ ታቅዶ 2897 ትምህርት ቤቶች መጸዳጃ ቤት ተሰርቶላቸዋል፡፡
በአጠቃላይ ደረጃ 3 እና ደረጃ 4 የደረሱ የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶች አፈጻጸም የተቀመጠውን ግብ ማሳካት እንዳልተቻለ ከሪፖርቱ መረዳት ይቻላል፡፡ ለዚህ
አፈጻጸም ምክንያቱ የአመራሩ ክትትልና ድጋፍ አነስተኛ መሆን፣ በማዕከል የሚሰጡ ስልጠናዎችን
በአግባቡ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ አለማውረድ፣ በየደረጃው የሚገኙ ባለሙያዎችና የትምህርት ቤት
ርዕሰ መምህራን ቁርጠኝነት ማነስ እና መቀያየር ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ለዓመቱ
የተጣለው ዒላማ አለመሳካት በስድስተኛው የትምህርት ልማት እቅድ ማጠናቀቂያ ላይ ደረጃ ሶስት የደረሱ
ትምህርት ቤቶችን 45.2% ለማድረስ እንዲሁም ደረጃ አራት የደረሱ ትምህርት ቤቶችን 10.8% ለማድረስ
የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት አዳጋች ያደርገዋል፡፡
ስፖርትን በተመለከተ
21
መ. የትምህርት ፍትሐዊነትና ተደራሽነት፣
በቅድመ መደበኛ (በመዋዕለ ህጻናትና ኦ ክፍል መርሃ ግብር) የተማሪ ተሳትፎ በ2013ዓ.ም ከነበረበት
2,934,668 (ሴ1,406,083 ወ 1,528,585) በ2014 ዓ.ም ወደ 3,667,803 (ወንድ 1,855,805፣ ሴት
1,811,998) ለማድረስ ታቅዶ 3,547,764 (ወንድ 1,849,179፣ ሴት 1,698,585) ህጻናትን ወደ ትምህርት
ቤት ማምጣት የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙም 96.72% ደርሷል፡፡ ይሁን እንጂ ዕድሚያቸው ለትምህርት
ከደረሱት 8,016,003 ህጻናት አንጻር አፈጻጸሙ ሲታይ 44.3% ነው። የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ
ትምህርት ተሳትፎ በ2013 ዓ.ም ከነበረበት 18,447,497 (ሴ 8,694,105 ወ 9,753,392) በ2014ዓ.ም ወደ
20,924,471 (ወንድ 11,062,517፣ ሴት 9,861,954) ለማድረስ ታቅዶ 19,219,900 (ወንድ 10,125,068፣
ሴት 9,094,832) ህጻናትን ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙም 91.8% ደርሷል።
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በ2013ዓ.ም ከነበረበት 3,540,324 (ሴ 1,681,500 ወ 1,858,824) ወደ
4,320,808 (ወንድ 2,160,404፣ ሴት 2,160,404) ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ 3,867,463
(ወንድ1,988,937፣ ሴት 1,878,526) ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙም
90% ነው፡፡ ይሁን እንጂ ዕድሚያቸው ለትምህርት ከደረሱት 8,522,690 ህጻናትና ወጣቶች አንጻር
አፈጻጸሙ ሲታይ 45.4% መሆኑን ያሳያል፡፡ አጠቃላይ ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ወንድ
13,963,184 ሴት 12,671,943 ድምር 26,635,127 ተማሪዎች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን
አፈጻጸሙም ከእቅድ አንጻር 92% ደርሷል።
ይሁን እንጂ በአንደኛና በመካከለኛ ደረጃ ትምሀርት የተሻለ ተሳትፎ የተመዘገበ ቢሆንም በቅድመ
አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ተሳትፎ በጣም ዝቅተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህም በቀጣይ በሁለቱ
ደረጃዎች የተማሪዎችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡
የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ሽፋን ለማሳደግ በወረዳ ከተሞች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት
ቤቶች ለመክፈት ታቅዶ 1086 አዲስ ተከፍተዋል። በተጨማሪም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ረቂቅ የትምህርት
ፖሊሲ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል።
የትምህርት ተሳትፎና ውስጣዊ ብቃትን ለማሳደግ ከሚያግዙ ስልቶች መካከል አንዱና ዋነኛው የትምህርት
ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማከናወን ስለመሆኑ የትምህርት ፍኖተ ካርታው በግልጽ አስቀምጧል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪም ሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የገባቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች፣ የትምህርት ፖሊሲው፣
የህጻናት ኮንቬንሽኖች፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብርን በስፋት ማካሄድ እንደሚገባ ያሳያሉ፡፡
ከዚህ በመነሳት በ2014 ዓ.ም ከተመዘገቡት የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች
መካከል 30% ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ
1,740,706 (ወንድ 965,657 ሴት 775,049) ተማሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህንን
22
የተማሪዎች የት/ቤት ምገባ መርሃ-ግብር ለማካሄድ በክልሎች 2,697,083,640 ብር በአጋር ድርጅቶች
390,017,515.62 ብር በጠቅላላው 3,087,101,155.62 ብር ተመድቦ ጥቅም ላይ ውሏል። በተጨማሪም
ከ10,000 በላይ የሚሆኑ እናቶች ምግብ በማቅረብና በማብሰል ስራ ላይ እንዲሰማሩ የተደራጁ ሲሆን
ከፍተኛ የስራ እድል ፈጥሯል። በመደበኛና በአስቸኳይ ጊዜ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ሶስት
ጊዜ የመስክ ምልከታ በማካሄድ የሚቀርበው ምግብ ከአካባቢው አርሶ አደሮች የተመረቱና ደህንነቱ
የተጠበቀ፣ በንጥረ ምግብ ይዘቱ የተሟላ ምግብ ለተማሪዎች መቅረቡን በማረጋገጥ ግብረ መልስ
ተሰጥቷል።
ሌላው የታቀደው ተግባር ለትምህርት ቤት ምገባ የማስፈጸሚያ ስትራተጂ የ10 ዓመት እቅድና በጀት
/Costed strategy / ማዘጋጀት ሲሆን በዚሁ መሰረት ማስፈጸሚያ ስተራቴጂውን በማዘጋጀት ከፌደራል
ትምህርት ሚኒስቴር፣ ክልሎችና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም አጋር የልማት
ድርጅቶች ለተውጣጡ 26 ከፍተኛ ባለሙያዎች የፖሊሲ ማዕቀፍንና ስትራቴጂውን የማስተዋወቅ ሥራ
ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም Save the Children International (SCI) ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር
በመተባበር Global Partners fo Education (GPE) በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የትምህርት ቤት ምገባ
በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ የዞን እና የወረዳ አስተባባሪዎች አቅም ግንባታ ስልጠና በትምህርት
ቤት ምገባ ስራ አመራርና ፕሮጀክት ማኔጅመንት ዙሪያ ተሰጥቷል።
በአጠቃላይ በ2014 ዓ.ም ከቅድመ አንደኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል ከተመዘገቡት 18,262,035 ተማሪዎች
መካከል 5,478,610 (30%) ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ
ታቅዶ 1,740,706 ተማሪዎችን በመመገብ የእቅዱን 31.8% መፈጸም ተችሏል፡፡ አፈጻጸሙ ዝቅተኛ
የሆነበት ምክንያት የአማራ ክልል 20 ሚሊዮን ብር ለትምህርት ቤት ምገባ የበጀተ ቢሆንም በጦርነቱ
ምክንያት ለሌላ ተግባር ለማዞር በመገደዱ፣ ቤ/ጉሙዝ ክልል በተመሳሳይ የበጀት እጥረት ያጋጠመው
በመሆኑ እና ሌሎች ክልሎች የእቅዳቸውን ያህል በጀት መድበው ምገባውን ማካሄድ ባለመቻላቸው
የተከሰተ ነው፡፡ ከዚህ መረዳት የሚቻለው በ2017 ዓ.ም 50% ለመድረስ የተቀመጠውን ዒላማ ለማሳካት
ጥረት እንደሚጠይቅ ነው።
23
ግብ 9፡- የትምህርት ፍትሀዊነትና አካታችነትን ማሻሻል
በአመቱ በተከናወኑ ተግባራት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ሴት መምህራን ድርሻ ከነበረበት 81.2% ወደ 83%
ታቅዶ 92%፣ የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት የሴት መምህራን ድርሻ ከነበረበት 41.2% ወደ 42%
ታቅዶ 42%፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሴት መምህራንንም ከነበረበት 19.6% ወደ 21% ለማድረስ
ታቅዶ 20.4%፣ የአንደኛ ደረጃ የሴት ር/መምህራን ድርሻ ከነበረበት 12.73% ወደ 14.26% ለማድረስ
ታቅዶ 12%፣ የሁለተኛ ደረጃ የሴት ር/መምህራን ድርሻ ከነበረበት 7.71% በ2014 ዓ.ም ወደ 8.62 %
ለማድረስ ታቅዶ 7%፣ የአንደኛ ደረጃ የሴት ሱፐርቫይዘሮች ድርሻ ከነበረበት 9.44% ወደ 13.88%
ማድረስ ታቅዶ 7%፣ እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ የሴት ሱፐርቫይዘሮች ድርሻ ከነበረበት 2.8% ወደ 5.6%
ለማድረስ ታቅዶ 7.5% ማድረስ ተችሏል።
የቅድመ አንደኛ ደረጃ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተሳትፎ ከነበረበት 1.3% (ወ 1.5% ሴ 1.2) ወደ 5.22%
(ወ 5.2 ሴ 4.96) ታቅዶ 1% ፣ ጥቅል ከ1ኛ-8ኛ ክፍል የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተሳትፎ ከነበረበት 11%
(ወ 12.3% ሴ 9.7%) ወደ 16.6% (ወ 17.3 ሴ 15.8) ለማድረስ ታቅዶ 11% እንዲሁም ጥቅል ከ9ኛ -
12ኛ ክፍል የልዩ ፍላጎት ትምህርት ተሳትፎ ከነበረበት 2.8% (ወ 3.2 ሴ 2.4) ወደ 6.24% (ወ 6.56 ሴ
5.92) ታቅዶ 3% ማድረስ ተችሏል።
ግቡን ለማሳካት ከፌደራል እስከ ወረዳ በመቀናጀት ከተከናወኑት ዋና ዋና ተግባራት መካከል፡ “ሴት
መምህራንን ወደ ትምህርት አመራርነት ለማምጣት የሚያግዝ የትምህርት ሴክተር ስትራቴጂ ማዘጋጀት”
የሚል ተግባር ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ሌላው በ2014 ዓ.ም በዝግጅት ምዕራፍ በአገሪቱ ውስጥ
የሚገኙ ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ልዩ ፍላጎት ያላቸው ሕጻናት ወደ ት/ቤት እንዲመጡ
ለማድረግ የሚያስችል የሕዝብ ንቅናቄ ተግባራት፣ 187 የልዩ ፍላጎት ድጋፍ መስጫ ማዕከላት ለማቋቋም
ታቅዶ ከትግራይ ክልል በስተቀር 164 (87.7%) ማዕከላትን በመለየት የማቋቋም እና በግብዓት የማደራጀት
ስራ ተከናውኗል፡፡
24
የድጋፍ መስጫ ማዕከላትን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ለ371 የተዘዋዋሪ መምህራንና ርዕሰ መምህራንን
በልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን መለያ መሳሪያ (Screening Tool)፣ በድጋፍ መስጫ
ማእከላት የአተገባበር መመሪያ እና የአካቶ ትምህርት ፅንሰ ሀሳብ ላይ ለማሰልጠን ታቅዶ 348 (93.8%)
ማሰልጠን ተችሏል፡፡
በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ትምህርትን ለማስቀጠል ከአደጋ ስጋት ስራ
አመራር ኮሚሽን ጋር በጥምረት የአደጋ ስጋት መረጃ የማሰባሰብና የትምህርት ዘርፍ ምላሽ እቅድ
ተዘጋጅቷል። በዚህም በአፋር 65፣ አማራ 1028፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 55፣ ኦሮሚያ 165፣ በደቡብ
ብ/ብ/ህ/ክልል 22 በድምሩ 1335 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ውድመት የደረሰባቸው ሲሆን በአፋር
415፣ አማራ 3082፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ 335፣ ኦሮሚያ 919፣ በደቡብ ብ/ብ/ህ/ክልል 131 በድምሩ 4882
በከፊል ጉዳት የደረሰባቸው እንደሆነ ከክልሎች የተጠናቀረው መረጃ ያሳያል። በመሆኑም በእነዚህ
አካባቢዎች የትምህርት አገልግሎትን ለማስቀጠል የሚያስችል የንቅናቄ ስራ፣ የግብአት አቅርቦት
እንዲሁም ከማእከል የትምህርት ባለሙያዎች ለተወሰኑ ወራት በየክልሎቹ ማእከላት ተመድበው የመረጃ
ማሰባሰብ፣ የእቅድ ዝግጅት፣ የቁሳቁስ ስርጭት እና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንዲሰጡ ተደርጓል።
በዚህም በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው ከነበሩ 1.9 ሚሊዮን
ተማሪዎች ውስጥ 1.19 ሚሊዮን፣ በአፋር ክልል ከ50 ሺ ተማሪዎች ውስጥ 43 ሺ ተማሪዎች፤
በቤኒሻኝጉል ጉሙዝ ከ145,076 ሺ ተማሪዎች ውስጥ 70ሺ ያህል ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት
ተመልሰው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ተደርጓል፡፡
በጦርነት ምክንያት በአማራና በአፋር ክልል በመምህራንና በተማሪዎች ላይ የተፈጠረውን የስነ ልቦናና
ማህበራዊ ጉዳት ለመቅረፍ የሚያስችል ለ444 መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል። የአሰልጣኞች
ስልጠና የወሰዱት መምህራን በመጠቀም 4000 መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ለማሰልጠን
ታቅዶ ለ3513 (87.8%) መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ይህ ስልጠና
የመምህራን፣ የር/መምህራንና በአጠቃላይ የትምህርት ማህበረሰቡ ላይ የደረሰውን የስነ ልቦናና ማህበራዊ
ጉዳት ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ በአፋር ክልል በአፍዴራ እና በኮሬ በጊዚያዊ መጠለያ ላሉ ተማሪዎች ከ38
በላይ ድንኳንና የትምህርት ቁሳቁስ ተሰራጭቷል። በተመሳሳይ በድርቅ ምክንያት ከኦሮሚያ እና ሶማሌ
ክልሎች ለተፈናቀሉ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ የሚያስችሉ ተግባራት የምላሽ እቅድ፣
ጊዚያዊ የመማርያ ጣቢያዎች፣ የጽህፈት መሳሪያና ቁሳቁሶች፣ ለመምህራን የስነ ልቦና ዝግጁነት ስልጠና
ተሰጥቷል፡፡ በማያያዝም የምገባ ሂደቱ እስከ መስከረም /2015ዓ.ም ድረስ እንዲቀጥል በማድረግ በግጭት
እና በድርቅ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ተማሪዎች የተስተጓጎለባቸውን ትምህርት ለማካካስ ተጨማሪ
ሀብት ማሰባሰብ ተችሏል፡፡ የትምህርት ማስፋፋትን ከጥራት ጋር ጎን ለጎን ለማስኬድ “አዲስ የኢትዮጵያ
ትምህርት ቤት” የሚል የትምህርት ቤት ዲዛይን ተዘጋጅቷል፡፡ በግጭት ምክንያት የወደሙ ትምህርት
ቤቶችን መልሶ በተሻለ መልኩ ለመገንባት የዲዛይን ዝግጅት ሥራ ተጠናቋል፡፡
25
ከዚህ በተጨማሪ ዝርፊያ የተካሄደባቸውን ትምህርት ቤቶች የጉዳት አይነቶችን በመለየት የውስጥ ቁሳቁስ፣
የትምህርት ቤት ፈርኒቸሮች (የተማሪ ዴስክ፣ የመምህራን ወንበር፣ የኮምፒውተር ላብ ጠረጴዛ፣ የመምህራን
ሼልፍ) እንዲሁም 2000 ኮምፒውተር ለ50 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማሟላት የጨረታ ሂደቱ
ተከናውኗል።
የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በ2009 ዓ.ም ባወጣው መረጃ መሰረት እድሜያቸው 15 ዓመትና ከዚያ
በላይ የሆናቸው መፃፍ፣ ማንበብና ማስላት የማይችሉ ዜጎች ቁጥር ከ21 ሚሊዮን በላይ እንደደረሰ ያሳያል፡
፡ እነዚህን ዜጎች መፃፍ፣ ማንበብና ማስላት እንዲችሉ ለማድረግ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ በሌላ
በኩል ደግሞ ማንበብ፣ መፃፍና ማስላት ችለው ሌሎች ትምህርትና ስልጠናዎችን ማግኘት ለሚፈልጉ
ወጣቶችና ጎልማሶች አጫጭር የሙያ ክህሎት ሥልጠናዎችን በመዘርጋት ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ለማድረግ በርካታ ስራዎች ሲከወኑ የቆየ ሲሆን ከተሰሩ ስራዎች መካከል ከዚህ የሚከተሉት ዋና ዋናዎቹ
ናቸው፡፡
በ2014 እቅድ ዓመት አንድ የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት የሽግግር መመሪያ ለማዘጋጀት
የታቀደ ሲሆን በእቅዱ መሰረት የሰነዱ የመጀመሪያ ረቂቅ ተዘጋጅቷል፡፡ በሌላ በኩል አራት የጎልማሶች
መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም የማስፈጸሚያ ሰነዶችን ከልሶ ለማዘጋጀት በዕቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን
በታቀደው መሰረት የጎልማሶች መሠረታዊ ትምህርት የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ፣ አጥጋቢ የመማር
ብቃት መለኪያ፣ የጎልማሶች መሠረታዊ ትምህርት የማስተግበሪያ መመሪያ እና የጎልማሶች መሠረታዊ
ትምህርት አመቻቾች ምልመላ፣ ሥልጠና፡ ቅጥርና ስምሪት የአፈጻጸም መመሪያ በድምሩ አራት ሰነዶች
ተከልሰው የመጨረሻ ዝግጅታቸው ተጠናቆ ለትግበራ ተዘጋጅተዋል።
የአቅም ግንባታ ስልጠናን በሚመለከት በዓመቱ ሁለት የተለያየ ይዘት ያሏቸው ሥልጠናዎች 40 ለሚሆኑ
የክልል የጎልማሶች ትምህርት ባለሙያዎችና የስራ ክፍል ሀላፊዎች የአሰልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት
ታቅዷል፡፡ በዚሁ መሰረት የመጀመሪያው ሥልጠና የተሰጠው በ2014 ዓ.ም ተከልሶ የተዘጋጀውን
የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት የማስተማር ሥነ-ዘዴ አንጻር፣ የጎልማሶችና መደበኛ
ያልሆነ ትምህርት ፕሮግራሞች ሥርዓት ግንባታ፤ መደበኛ ያልሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞች (በማታ፣
በርቀት፣ በቤት አካባቢና፣ በተፋጠነ ትምህርት) ፕሮግራሞች አተገባበር ዙሪያ አንድ የአሰልጣኞች
ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መረጃ አሰባሰብና አደረጃጀት
ላይ ለ40 የክልል የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት የመሪ አሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል፤
26
አብዛኞቹ ክልሎችም ስልጠናውን ለታችኛው ፈጻሚ እንዲደርስ አድርገዋል፡፡ በመሆኑም በ2014 ዓ.ም
ለዚህ ተግባር ከተቀመጠው ዒላማ አንፃር 100% ተከናውኗል።
በጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ፕሮግራሞች ትግበራ ዙሪያ በ2014 ዓ.ም በሀገር ደረጃ አንድ
የንቅናቄና የሲምፖዚያም መድረክ የሁሉም ክልሎች የዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ባሉበት
ተከናውኗል። ከዚህ በተጨማሪም አንድ የኤሌክትሮኒክ እና አንድ የህትመት ሚዲያዎችን በመጠቀም
የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ተከናውኗል። በጎልማሶች መሠረታዊ ትምህርት እና በተፋጠነ ትምህርት
ፕሮግራሞች ፍላጎት፣ አቅርቦትና ፍትሀዊነት ዙሪያ አንድ የዳሰሳ ጥናት ለማካሄድ ታቅዶ በደቡብ ኦሞ ዞን
በሚገኙ የባጫ ብሄረሰብ ላይ assessment በማካሄድ 12 ወጣቶችን በፍቃደኝነት በማሰባሰብ ከደቡብ
ብ/ብ/ሀ/ ክልል መንግስት ትም/ት ቢሮ ጋር በቅንጅት በመስራት ትምህርት እንዲጀምሩ ተደርጓል።
በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ሁለት ጊዜ በጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት ፕሮግራሞች
ትግበራ ዙሪያ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ ታቅዶ ከትግራይ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎችና ከተማ
አስተዳደሮች ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፡፡
ክንውን
መለኪ የ2014 ዓ.ም አፈፃፀም
የቁልፍ ውጤት አመላካቾች
ያ ዕቅድ በ%
NB፡- የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም የሚለው የጎልማሶች የህይወት ክህሎት ትምህርት
ተብሎ ተቀምጦ የነበረውን ተክቶ የገባ ነው፡፡
27
ሰንጠረዡ እንደሚያሳየው በጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራም በዓመቱ ከታቀደው አንፃር
የተገኘው ውጤት የሚያበረታታ ነው፡፡ ይሁንና በእቅድ አፈጻጸም ወቅት ከፌደራል እስከ ትም/ቤት ድረስ
ወጥ የሆነ አደረጃጀት፣ የሰለጠኑ አመቻቾች እና ኘሮግራሙን ለማካሄድ በቂ ሀብት አለመኖር ቁልፍ
ችግሮች ናቸው፡፡ በትግበራ ወቅት የታዩ ችግሮች በመቅረፍ በ2015 ዓ.ም ተጨማሪ የመማማሪያ
ጣቢያዎች እንዲከፈቱ፣ በቂ አመቻቾች እንዲቀጠሩ፣ የሙያ ክህሎት ትምህርትና ሥልጠና ትግበራ
የሞጁል ዝግጅት ስራዎች እንዲጠናቀቁ በማድረግ ፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረጉ
የማህበረሰብ የመማማሪያ ማዕከላትን በማቋቋም ወጣቶችና ጎልማሶች የሙያ ክህሎት ትምህርትና ሥልጠና
ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲሆኑ መስራትን ይጠይቃል።
ግቡን ለማሳካት ፈጣን በሆነ የብሮድባንድ ኔትወርክ መሰረተ ልማት ተሳስረው የዲጂታል ቴክኖሎጂ
ተጠቃሚ የሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ2013 ዓ.ም ከነበሩበት 100% በ2014ዓ.ም ወደ 100%
ለማድረስ ታቅዷል።
28
ክፍል አራት
የዩኒቨርሲቲ የስራ ሃላፊዎችን የአመራር አቅም ለመገንባት በታቀደው መሰረት የተደራጁ የአመራር
ማሰልጠኛ ክላስተር ማዕከላትን 5 ለማድረስ ታቅዶ ባለው አገራዊ ሁኔታ ምክንያት 3 (60%) ብቻ
ተደራጅተው ወደ ስራ ማስገባት ተችሏል። በተጠናቀቀው የበጀት አመት ከከፍተኛ ትምህርት አመራር
አቅም ግንባታ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር 377 መካከለኛ አመራሮችን ማሰልጠንና እውቅና መስጠት
የተቻለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ የሴቶች ድርሻ 166 (44%) ነው፡፡ እንዲሁም በክላስተር ማዕከላትና በተቋማት
ደረጃ የአመራር አቅም እንዲጎለብት በማዕከል ደረጃ ለ24 ሰልጣኞች የአሰልጣኞች ሥልጠና እና እውቅና
በመስጠት የእቅዱን 100% ማከናወን ተችሏል። በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ከዝግጅት እስከ ማጠቃለያ
ምእራፍ ድረስ ለ548 አመራሮች በስራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን እንዴት እንደሚፈቱ፣ የከፍተኛ
ትምህርት ዓለም አቀፍ ተግዳሮቶችን እንዴት መቋቋምና መፍታት እንዳለባቸው የሚያግዝ የአመራሩን
ክህሎትና ስብዕና ሊያጎለብቱ የሚችሉ ሥልጠናዎች ተሰጥቷል።
ሴቶች በየደረጃው ባለው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የአመራር እርከን ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ
እና በአቅምና በአመለካከት ሙሉ ቁመና እንዲኖራቸው ለማድረግ ለ526 ሴት መካከለኛ አመራሮች
በተቋማት ተልዕኮ ልየታ፣ ክህሎትና ስብዕና ብስለት፣ የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ 1152/2011 እና
1263/2014፣ በፋይናንስ በግዥና የሰው ሃብት አስተዳደር፣ በከፍተኛ ትምህርት ሌጅስሌሽን፣ የጥናትና
ምርምር መመሪያ፣ የአካዳሚክ ደረጃ ዕድገት አወሳሰን ሥርዓት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
29
በበጀት ዓመቱ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የከፍተኛ ሴት አመራሮች (በም/ፕሬዝዳንቶች ማዕረግ እና
ከዚያ በላይ ያሉ አመራሮች) ድርሻን 25% ለማድረስ ታቅዶ አፈጻጸሙ 11.25% ማድረስ ተችሏል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርነት ስልጠና የወሰዱ የተማሪ አመራሮችን ከ20% ወደ 50%
ለማድረስ ታቅዶ፣ በድሬዳዋና በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ለ100 የተማሪ ህብረት ፕሬዝዳንቶች
የሰላም ክለብ እና የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ተወካዮች የምክክር ጉባኤ የተካሔደ ሲሆን በጠቅላላው
በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለ50% ተማሪ ህብረት አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በመስጠት
አፈጻጸሙን 100% ማድረስ ተችሏል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትኩረት መስካቸውን ተከትለው እንዲሰሩ ለማድረግ የዩኒቨርሲቲዎች ልየታ
ትግበራ ስትራቴጂ በማዘጋጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ የተከናወነ ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ በመውጫ
ፈተና ዙሪያ ተመሳሳይ ስራ ተሰርቷል። በዚህም አቅማቸው የጎለበተ ተቋማትን ከ45 ወደ 46 ለማድረስ
ታቅዶ 46(100%) ማድረስ ተችሏል።
ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በእቅድ መሰረት ስራ ላይ የዋለ ሃብት በአግባቡ እንዲጠቀሙ ገቢያቸውን
እንዲያሳድጉ፣ መደበኛ በጀት፣ ከውስጥ ገቢ እና ከተለያዩ ምንጮች የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ
እንዲጨምሩ የአሰራር ስርአት በማጠናከር፣ በ10 ዓመቱ የእቅድ ዘመን መጨረሻ ላይ የበጀታቸውን 50%
በሂደት ከውስጥ ገቢ መሸፈን እንዳለባቸው ሰፊ ግንዛቤ በመፍጠር ከአመራሩ ጋር መግባባት ላይ
ተደርሷል፡፡ የተቋማት ሀብት የማመንጨት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ቢመጣም ከመንግስት
የሚበጀትላቸው በጀት በቂ ባለመሆኑ የውስጥ ገቢያቸውን በተሻለ ደረጃ በማሳደግ እንዲጠቀሙ ለማድረግ
እና ለስራው የሚያስፈልጋቸውን የፋይናንስ፣ የቁሳቁስ እና የሰው ኃይል ግብዓቶች እንዲሟላላቸው በዝርዝር
ለሚመለከታቸው አካላት (ለገንዘብ ሚኒስቴር፣ ለመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣንና ለሲቪል ሰርቪስ
ኮሚሽን) የማቅረብ ስራ ተሰርቷል፡፡ በዚህም መሰረት ደንብና መመሪያ በሚፈቅደው መልኩ አቅርቦ
የማስፈቀድና የመጠቀም ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ መጥቷል፡፡
በኦዲት ግኝት ምንም ነቀፌታ የሌለባቸው (Unqualified audit opinion) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከ0
ወደ 20% ለማድረስ ታቅዶ 2.12% ላይ ማድረስ ተችሏል፡፡ እንዲሁም በኦዲት ግኝት ከጥቂት ጉድለቶች
በስተቀር በአጠቃላይ አጥጋቢ ሆነው የተገኙ (Except…for) ተቋማትን ከ20% ወደ 80% ለማድረስ ታቅዶ፣
34.78% ማድረስ ተችሏል፡፡ ከ33 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተሰበሰብ መረጃ መሰረት በ2012 ዘጠኝ
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት qualified/ except for ላይ የነበሩ ሲሆን በ2013 ወደ 17፣ በ2012 Adverse
የነበሩ 20 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2013 ወደ 10 ማውረድ የተቻለ ሲሆን 7 ከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት በተለያዩ ምክንያት ኦዲት አልተሰራላቸውም። ለአፈጻጸሙ ማነስ ምክንያት የከፍተኛ ትምህርት
የስራ ባህሪ ከግምት ውስጥ ያስገቡ የግዥ አፈጻፀም ስርአት ችግር መኖሩ፤ በዚህም ምክንያት ለመማር
30
ማስተማርና ለምርምር የሚሆኑ ግብአቶችን ለማሟላት በጣም ሰፊ ጊዜ በሚፈጅ የግዥ ስርአት መግዛት
የተማሪዎች ቀለብ እና መድሀኒት ግዥን ጨምሮ የመማር ማስተማሩን እና የምርምር ስራውን
ስለሚያደናቀፍ ብዙ ተቋማት ቀጥታ ግዥን ስለሚጠቀሙ እና እነዚህ ግዠዎች ደግሞ የኦዲት ግኝቶች
ሆነው ተገኝተዋል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ባጋጠመው ጦርነት ምክንያት ጉዳትና ውድመት የደረሰባቸውን በአማራ ክልል
የሚገኙ ሶስት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን እንደገና ስራ ለማስጀመር አገራዊ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ
እየተደረገ ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው ተቋማትም በሙሉ አቅም ወደ ስራ ገብተዋል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ኢንዱስትሪዎች መካከል ትስስርና አጋርነት በመፍጠር የሰው ኃይል
ስልጠና ፍላጎት መለየት የሚያስችል ጥናት በጋራ ለማካሄድ ታቅዶ በተሰራው ስራ 17 ድህረ መሰረታዊ
ሙያ (Post Basic) የጤና ፕሮግራሞች ፍላጎት መኖሩን ማረጋገጥ ተችሏል። ይህም የዓመቱ ዕቅድ
አፈጻጸም ከታቀደው አንጻር 100% መሆኑን ያመላክታል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሰው ኃይል ስልጠና
ፍላጎቱን ከነበረበት 30% ወደ 50% ለማሳደግ ታቅዶ 50% መድረሱን ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን
አፈጻጸሙም 100% መድረሱን ያሳያል።
በኢትዮጵያ የትምህርት ዕድል የሚሰጣቸውን ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ቁጥር 3,500 ለማድረስ ታቅዶ
3,500 ዕድል የተሰጣቸው ሲሆን ዕድሉን መጠቀም የቻሉት ግን 2,361(67.5%) ተማሪዎች ብቻ ናቸው፡፡
የዓለም አቀፍ መምህራን ልውውጥ በበጀት አመቱ 1,500 የውጭ ሀገር መምህራን በሀገራችን ከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት የማስተማር ዕድሉን እንዲያገኙ ታቅዶ 1500 መምህራን ልውውጥ የተደረገ ሲሆን
ይህም አፈፃፀሙ 100% መሆኑን ያሳያል፡፡
በሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች ስኮላርሽፕ የተሰጣቸው የመጀመሪያ ዲግሪ የውጭ ዜጋ የሆኑ ተማሪዎች
ቁጥር ከነበረበት 1,400 ወደ 1,600 ለማሳደግ ታቅዶ 1,767 ተማሪዎችን የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ
የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙ 110% ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል
31
የተሰጣቸውን ተማሪዎች ቁጥር ከነበረበት 328 ወደ 500 ለማሳደግ ታቅዶ 514 ተማሪዎችን የዕድሉ
ተጠቃሚ ማድረግ በመቻሉ አፈጻጸሙ ከዕቅድ አንጻር 102.8% ነው፡፡ እንዲሁም በሶስተኛ ዲግሪ
የትምህርት ዕድል የተሰጣቸውን ተማሪዎች ቁጥር ከነበረበት 35 ወደ 60 ለማድረስ ታቅዶ 60(100%)
ማድረስ ተችሏል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገር ውስጥ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የሚሰሩ የዓለም አቀፍ
ዩኒቨርሲቲዎች ቁጥር ከነበረበት 30 ወደ 35 ለማሳደግ ታቅዶ ወደ 37(106%) ማሳደግ ተችሏል።
ግብ 4፡- በመልካም ሥነ ምግባር የታነፁና ለሥራ ዝግጁ የሆኑ ተማሪዎችን ማፍራትና ማረጋገጥ፣
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ስነምግባርና ባህርይ መሻሻል ላይ ብዙ መስራት የሚገባ መሆኑን
ከትምህርት ልማት ፍኖተ ካርታ ጥናት እና ከአመታዊ ዕቅድ አፈጻጸሙ መረዳት ተችሏል፡፡ በመሆኑም
የተማሪዎችን መልካም ስነ ምግባር የሚያንጹ የአንደኛ ዓመት የጋራ ኮርሶች ውስጥ ተካተው እንዲሰጡ
የተደረገ ሲሆን በቀጣይ አመታትም ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር ይሆናል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ፕሮግራሞች የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ምጥጥንን ጠብቀው
እንዲዘጋጁ ከተቋማቱ ጋር በተደረሰው ስምምነት በትምህርት ዘመኑ የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ምጥጥንን
ጠብቀው የሚዘጋጁ ፕሮግራሞችን ከነበረበት 75 በመቶ ወደ 80 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ ከዕቅዱ 77%
የተከናወነ ሲሆን አፈጻጸሙም 86.5 በመቶ ለማድረስ ተችሏል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በተለያየ ስያሜ
የሚሰጡ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞችን ካላቸው የሥርዓተ ትምህርትና የኮርሶች ተዛምዶ አንፃር
በመቃኘት ተቀራራቢ የሆኑትን ወደ አንድ የፕሮግራም ስያሜ በማምጣት ከ52 ፕሮግራሞች ውስጥ 46ቱን
በማዋደድ ወደ 16 በመቀነስ የፕሮግራም ስያሜ ስራ ተሰርቷል። ቀሪዎቹ 6 ፕሮግራሞች ግን በተፈጠረው
መድረክ ስምምነት ላይ መድረስ ባለመቻሉ በቀጣይ ከሌሎች ተመሳሳይ ችግር ካለባቸው ፕሮግራሞች ጋር
የማስማማት ስራ የሚሰራላቸው ይሆናል።
32
በሌላ መልኩ የትምህርት ጥራትን በየደረጃው ለማረጋገጥ እንዲረዳ የመውጫ ፈተናን በ8 የቅድመ ምረቃ
ፕሮግራሞች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዶ በ8 የጤና መስክ እና በህግ ትምህርት የቅድመ ምረቃ
ፕሮግራሞች ላይ ተግባራዊ ማድረግ የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙን 113% ማድረስ ተችሏል፡፡ የመውጫ
ፈተናዎቹን ውጤታማነት ለማረጋገጥ ከፌዴራል የፍትህና ህግ ኢንስቲትዩት እና ከጤና ሚኒስቴር ጋር
በትብብር ተሰርቷል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ በበጀት አመቱ ተግባራዊ በተደረገው በ8 የጤና እና በህግ የትምህርት ዘርፍ ለሁለት
ጊዜ መውጫ ፈተና ተሰጥቶ የተማሪዎች የማለፍ ምጣኔ ከነበረበት 82.7 በመቶ ወደ 86 በመቶ ለማሳደግ
የታቀደ ቢሆንም ፈተና ላይ ከተቀመጡ 11,544 ተማሪዎች የማለፊያ ነጥቡን ያመጡት 4,459 (38.63%)
ብቻ ሲሆን ከዕቅድ አንጻር ያለው አፈጻጸም 45% ነው፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በመጪው የ2015 የበጀት አመት ለሁሉም የቅድመ ምረቃ ትምህርት ዘርፍ ምሩቃን
የመውጫ ፈተና ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን ተግባሩን በስኬት ለማከናወን
የሚያስችሉ የማስፈጸሚያ መመሪያዎችና ተያያዥነት ያላቸው ማኑዋሎች ማለትም የከፍተኛ ትምህርት
የብቃት ምዘና ማዕቀፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና አፈጻጸም መመሪያ፣ የከፍተኛ ትምህርት
ተመራቂዎች የመውጫ ምዘና አፈጻጸም መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
በሌላ በኩል በሁሉም የመጀመሪያ ዲግሪ ዕጩ ምሩቃን ላይ ተግባራዊ የሚደረገውን የመውጫ ፈተና
በውጤታማነት ለማከናወን በቅድሚያ ፈተናው የሚሰጥባቸውን የትምህርት መስኮች ለመለየት በተደረገው
ርብርብ 70 የሚደርሱ ፕሮግራሞች የተለዩ ሲሆን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች፣ ከሙያ
ማህበራት፣ ከተማሪዎች ህብረት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር አንድ ዐውደ ጥናትን ጨምሮ
ከሰባት ጊዜ በላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የውይይት መድረኮችን ማዘጋጀት ተችሏል። ዩኒቨርሲቲዎችም
ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችና ፈጻሚዎች ተመሳሳይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን እንዲያዘጋጁ
በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ስለ አፈጻጸሙ ለሚመለከታቸው ሁሉ ተገቢውን ግንዛቤ ማስጨበጥ ተችሏል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በጥራት እና ብቃት ላይ በስፋት ለመስራት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን
የሙያ ፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የአመራር እና መምህራን ምዘና
አተገባበር መመሪያዎች ተዘጋጅተው በባለ ድርሻ አካላት ተገቢው አስተያየት ተሰጥቶባቸው ለትግበራ
ዝግጁ ሆነዋል፡፡
33
መሰረት እንዲከለሱ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ቢሆንም የአራት የጤና ፕሮግራሞች የክለሳ ስራን
ግን ማጠናቀቅ አልተቻለም፡፡
የትምህርትን አግባብነትና ጥራት ለማሻሻል በመማር ማስተማሩ ሂደት የኢንዱስትሪና የሴክተር መሥሪያ
ቤቶች ባለሙያዎችን ተሳትፎ ከነበረበት 45 በመቶ ወደ 60 በመቶ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት
ትኩረት ተሰጥቷቸው እንዲከናወኑ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር መግባባት ላይ ተደርሶ በተሠራው
ሥራ 55 በመቶ ማከናወን የተቻለ ሲሆን አፈጻጸሙ ከታቀደው ተግባር አንጻር 92 በመቶ ነው፡፡ የከፍተኛ
ትምህርት ፕሮግራም ተገቢነት መለኪያ የሆነው አንዱ የተመራቂዎች የመቀጠር ምጣኔ ሲሆን የከፍተኛ
ትምህርት ተመራቂዎች የመቀጠር ምጣኔን ከነበረበት 58.5 በመቶ ወደ 67 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ ወደ
59% መድረሱን ማረጋገጥ ተችሏል። በዚህም የዕቅዱን 88% መፈፀም እንደተቻለ ተመልክቷል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ፕሮግራሞች የሀገር በቀል እውቀቶችን አካተው እንዲዘጋጁ
ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ መሰረት በዕቅድ ዘመኑ ከነበረበት 5 በመቶ ወደ 10 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ
ሙሉ በሙሉ ማከናወን ተችሏል፡ አፈጻጸሙም ከዕቅድ አንጻር 100% ሆኗል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ለአገራዊ ልማትና ዓለም አቀፋዊ
ተወዳዳሪነት የሚኖራቸውን ተገቢነት ከማረጋገጥ አንጻር በበጀት ዓመቱ ተገቢነታቸው የተረጋገጡ
ፕሮግራሞችን ከነበሩበት 63 በመቶ 72 በመቶ ለማድረስ የታቀደ ቢሆንም 70 በመቶ የሚሆኑ
ፕሮግራሞችን ተገቢነት ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ይህም ከዕቅድ አፈጻጸም አንጻር 97% መሆኑን ያመለክታል።
በተመሳሳይ መንገድ የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትን ለማስጠበቅ የሚደረገው የአሰራር ሥርዓት አካል
የሆነ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተዘረጋ የውስጥ ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓትን በሁሉም ተቋማት
ተግባራዊ ለማድረግ በታቀደው መሰረት በበጀት አመቱ በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ተችሏል፡፡
ይህም የዕቅድ አፈጻጸሙን 100% ያደርገዋል።
34
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችን የማጠናቀቅ ምጣኔን ለማሳደግ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን
የማጠናቀቅ ምጣኔ ከ85 ወደ 86% ለማድረስ ታቅዶ 68% ማከናወን ተችሏል፡፡ የሁለተኛ ዲግሪ
ተማሪዎችን የመመረቅ ምጣኔ ከነበረበት 80 በመቶ ወደ 81 በመቶ ለማሳደግ የታቀደ ቢሆንም ክንውኑ 56
በመቶ ብቻ ነው፡፡ የቅድመ ምረቃም ሆነ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች የመመረቅ ምጣኔ ከዕቅድ በታች
ሊከናወን የቻለው በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የትምህርት ካሌንደሩ በመዛባቱ ምክንያት በበጀት
ዓመቱ መመረቅ የሚገባቸው ተማሪዎች ኮርሶችን ባለማጠናቀቃቸው አፈጻጸሙ ከዕቅድ በታች ሊሆን
ችሏል፡፡ ነገር ግን በበጀት አመቱ የሶስተኛ ድግሪ ተማሪዎችን የመመረቅ ምጣኔ ከነበረበት 40% ወደ
45% ለማሳደግ በተያዘው ዕቅድ መሰረት ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በመቻሉ የተግባሩ አፈጻጸም
ከዕቅድ አንፃር 100% ነው፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልየታ የትኩረት መስካቸውን መሰረት በማድረግ በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች
የመጀመሪያ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ የተማሪዎች ምጥጥን ከነበረበት 72፡22፡5 ወደ 61፡33፡6፣
በአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ከነበረበት 93.2:6፡0.8 ወደ 92፡7፡1፣ እንዲሁም በአጠቃላይ
ዩኒቨርሲቲዎች ከነበረበት 97.8:1.8:0.4 ወደ 96.8፡2.6፡0.6 ለማሻሻል የታቀደ ቢሆንም የመምህራን ቅጥር
በጊዜያዊነት በመታገዱ እና የተማሪዎች ምደባ ስራ የተቋማትን ልየታ የተልኮ እና ትኩረት መስክ
መሰረት አድርጎ ባለመሆኑ የተማሪዎች ምጥጥን በነበረበት ቀጥሏል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለምሩቃን ስራ የማግኘት ወይም የመፍጠር ዕድልን ለማስፋት ከመደበኛ
ትምህርት ጎን ለጎን ወደ ስራ ዓለም የሚሸጋገሩበትን ስልጠና የመስጠት ልምድ እያደገ መጥቷል። በዚህ
መሰረት በዕቅድ አመቱ ሥልጠና ያጠናቀቁ ተመራቂ ተማሪዎችን 50 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ ሁሉም
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበጀት ዓመቱ ላስመረቋቸው ተማሪዎች ወደ ስራ የመሸጋገሪያ ስልጠና
በመስጠታቸው የዕቅድ ከንውኑ 100% ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የቀጣሪዎች በምሩቃን የስራ አፈጻጸም
ላይ ያላቸውን የእርካታ ደረጃ 55% ለማድረስ የታቀደ ቢሆንም በበጀት ዓመቱ የምሩቃንን የስራ አፈጻጸም
ብቃት ላይ የዳሰሳ ጥናት ማካሄድ ባለመቻሉ የቀጣሪዎች እርካታ ደረጃ መሻሻሉን ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡
35
መካተታቸውን ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን ይህም ከአጠቃላይ (328) ፕሮግራሞች አንጻር አፈጻጸሙ 98.78%
ነው፡፡
የመጽሐፍ አቅርቦትን በማሻሻል መጽሐፍት ተማሪ ጥምርታ በበጀት ዓመቱ በዋና ዋና ማጣቀሻ መጻህፍት
ከነበረበት 1ለ7.4 ወደ 1ለ5 ለማድረስ ታቅዶ 1ለ5 ማሳካት የተቻለ ሲሆን የተግባሩ ዕቅድ አፈጻጸምም
100% ነው፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የረዳት ፕሮፌሰር߹ የተባባሪ ፕሮፌሰርና የሙሉ ፕሮፌሰር ምጣኔን ከነበረበት
13% ወደ 15% ለማሳደግ ታቅዶ ሙሉ በሙሉ ማሳካት የተቻለ ሲሆን የተግባሩ የበጀት ዓመቱ ዕቅድ
አፈፃፀም 100% ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የመምህራንን የትምህርት ደረጃ ምጥጥን በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና
በሶስተኛ ዲግሪ ከነበረበት 17:68:15 ወደ 14፡70፡16 ለማድረስ ታቅዶ 14፡70፡16(100%) መፈፀም
ተችሏል።
በተልዕኮ ልየታ መሰረት በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ የመጀመሪያ፣ የሁለተኛና የሶስተኛ ድግሪ
ያላቸው መምህራን ምጥጥን ከነበረበት 16:63:21 ወደ 11፡65፡24 ምጥጥን ለማድረስ ታቅዶ 11፡65፡24
(100%) መፈጸም ተችሏል። በተመሳሳይ በአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ የመጀመሪያ፣
የሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ ያላቸው መምህራን ምጥጥን ከነበረበት 18:69:13 ወደ 15፡71፡14 ለማድረስ
ታቅዶ 15፡71፡14(100%) መፈፀም ተችሏል፡፡ እንዲሁም በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ
የመጀመሪያ፣ የሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ ያላቸው መምህራን ምጥጥንን ከነበረበት 21:76:3 ወደ 24፡67፡9
ለማድረስ ታቅዶ 24፡67፡9(100%) ማሳካት ተችሏል።
በሀገር ውስጥ በሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት ዕድል የሚሰጣቸው መምህራን ቁጥር ከነበረበት 5,404 ወደ
7,017 ለማሳደግ ታቅዶ 6,842 መምህራንን በሀገር ውስጥ የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም
ከዕቅዱ 88.9% ማከናወኑን ያሳያል። ከዚህ በተጨማሪ ለ262 መምህራን በውጭ ሀገር የሁለተኛ ዲግሪ
36
ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ታቅዶ 190 (73%) መምህራን በውጭ ሀገራት ባሉ ተቋማት ትምህርታቸውን
እንዲከታተሉ ማድረግ ተችሏል።
በበጀት ዓመቱ በሀገር ውስጥ የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል የሚሰጣቸውን መምህራን ብዛት ከነበረበት
3,967 ወደ 5,270 ለማሳደግ ታቅዶ 3,747(71.10%) መምህራንን በሀገር ውስጥ ባሉ ከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት እንዲማሩ ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ለ1,110 መምህራን በውጭ ሀገራት ባሉ ከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል ለመስጠት ታቅዶ 1,071(96.5%) መምህራንን የዕድሉ
ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ የተመዘገበው የዕቅድ አፈጻጸም ደረጃ ከፍተኛ ቢሆንም በውጭ ሀገራት
የሚሰጥ የትምህርት ዕድልን በዕቅዱ ልክ ማሳካት እንዳልተቻለ የተመለከተ ሲሆን ይህም የሆነው በዓለም
አቀፍ ደረጃ ካጋጠመው ኮቪድ-19 ጋር ተያይዞ ሀገራት ፖሊሲዎቻቸውን መቀየራቸውና የውጭ ምንዛሬ
እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት ነው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት መምህራን የትምህርት ደረጃና ክህሎትን
ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት በድህረ ምረቃ (ዶክትሬት ዲግሪ) ፕሮግራም የሴት መምህራንን ተሳትፎ
ከነበረበት 9.4% ወደ 12.9% ለማሳደግ ታቅዶ ወደ 9.75% ማድረስ የተቻለ ሲሆን ይህም የዕቅዱን
75.58% ብቻ ማከናወን እንደተቻለ ያሳያል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት መምህራን ሙያዊ ክህሎትን ለማሻሻል መምህራን የስራ ላይ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና
እንዲወስዱ በዕቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የስራ ላይ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና ላይ የሚሳተፉ
የከፍተኛ ትምህርት መምህራንን ድርሻ ከነበረበት 62% ወደ 70% ለማሳደግ ታቅዶ 67.44% በማድረስ
የዕቅዱን 96.34% ማሳካት ተችሏል፡፡
በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ ማዕከላት ውስጥ ለሚሰሩ 81 መምህራንና ባለሙያዎች ለ22
ማዕከላት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በድምሩ ለ103 ሰዎች በማዕከላት ቤተ-ሙከራ አጠቃቀም ላይ
እንዲሁም በሀገር በቀል እውቀት ማዕከላት አደረጃጀትና አስተዳደር ላይ ያተኮረ ስልጠና ከአዲስ አበባ
ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት በማዕከላቱ የሚገኙ ቤተ-
ሙከራዎች ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡
37
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚደንቶችና ዳይሬክተሮች
ፎረም በማካሄድ በSTEM ማዕከላት እንዲሁም በሀገር በቀል እውቀት ላይ ያሉትን ችግሮች በመለየት
ማዕከላቱ የተጠናከረ ስራ አንዲያከናውኑ መግባባት ላይ ተደርሷል። የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና
ሂሳብ (የሳ/ቴ/ም/ሂ/) ትምህርቶችን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሳ.ቴ.ም.ሂ. ማዕከላት የሚሳተፉ
ተማሪዎችና መምህራን አመራረጥ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት 30
የነበረውን የሳ/ቴ/ም/ሂ/ ማዕከላት በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት ወደ 38 ለማሳደግ ታቅዶ በ8 ዩኒቨርስቲዎች
ውስጥ ማለትም ጋምቤላ፣ ደምቢዶሎ፣ ጂንካ፣ ቡሌ ሆራ፣ መደ ወላቡ፣ አርሲ፣ መቱ፣ ወራቤ እና ኦዳቡልቱም
ዩኒቨርሲቲዎች ማዕከላቱ ተቋቁመዋል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2014 ዓ.ም የሳ/ቴ/ም/ሂ/ ፕሮግራሞች ላይ 300 መምህራን እንዲሳተፉ
ታቅዶ 289 (96%) መምህራን ተሳትፈዋል፡፡ ከነዚህ መምህራን ውስጥ የሴት መምህራን ተሳትፎ 75
ለማድረስ ታቅዶ 56 (74.7%) ሴት መምህራን ተሳትፈዋል፡፡ እንዲሁም በSTEM ፕሮግራሞች ላይ
ለ3,000 ተማሪዎች ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ለ3,634 ተማሪዎች ሥልጠናው ተሰጥቷል፡፡ ከነዚህ
ተማሪዎች መካከል የሴት ተማሪዎችን ተሳትፎ ወደ 900 ለማድረስ ታቅዶ 920 ሴት ተማሪዎች
በሥልጠናው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሴት ተማሪዎችን ለማበረታታት ከአዳማ ሳ/ቴ/ ዩኒቨርስቲ
እና ከSTEM Synergy ጋር በመተባበር በ2014 ዓ.ም ለ10 ሴት ተማሪዎች የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም
ተካሂዷል፡፡
በስታንዳርዱ መሰረት አዲስ የመማሪያ ክፍሎች የገነቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከ10% ወደ 51%
ለማሳደግ ታቅዶ፣ 35 በመቶ በማከናወን 68.6% መፈጸሙን በድጋፍ ክትትል ማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በስታንዳርዱ መሰረት አዲስ የመማሪያ ክፍሎች የገነቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከ10% ወደ 51%
ለማሳደግ ታቅዶ፣ 35 በመቶ በማከናወን 68.6% መፈጸሙን በድጋፍን ክትትል ማረጋገጥ ተችሏል።
እንዲሁም በስታንዳርዱ መሰረት የመማሪያ ክፍሎችን ያደሱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወደ 10
ለማሳደግ ታቅዶ፣ በ10 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ 677 የመማሪያ ክፍላቸውን አድሰዋል በዚህም
የእቅዱን 100% መፈጸም ተችሏል፡፡
ለ10 ፕሮግራም የተዘጋጁ ስታንዳርዶች ጸድቀው ለ45ቱ ዩኒቨርሲቲዎች ተደራሽ ተደርገዋል። እንዲሁም
ለ10 የቅድመ-ምረቃ የትምህርት ፕሮግራሞች የተዘጋጁ ስታንደርዶች እና 105 የቤተ-ሙከራና የወርክሾፕ
ማኑዋሎች ለትግበራ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ተልከዋል አፈጻጻሙ 100% ነው፡፡ ሁሉም የከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት ውስጣዊ የአሰራር ሂደቶችን በመመሪያና በስታንዳርድ በማስደገፍ የአሰራር
ስርአታቸውን እንዲያዘምኑ ታቅዶ 100% ማከናወን ችለናል፡፡
38
ከጀርመን ልማት ባንክ በተገኘ የ400,347 ዩሮ ድጋፍ የልዕቀት ማዕከላት የቤተ-ሙከራ ዕቃዎች ግዥ ዓለም
አቀፍ ጨረታ በማውጣት ግዥ ተፈፅሟል፡፡ በተጨማሪም በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ በቴክስታይልና ፋሽን
ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እየተቋቋመ ለሚገኘው የልዕቀት ማዕከል አገልግሎት የሚውሉ የ800,000 ዩሮ የቤተ-
ሙከራና የወርክሾፕ ዕቃዎች ለመግዛት የሚያስችል ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ 5 አቅራቢ ድርጅቶች
ያቀረቡት የጨረታ ሰነድ እየተገመገመ ነው።
በሦስት የልዕቀት ማዕከላት የፒ.ኤች.ዲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ 23 መምህራን የውጭ ሀገር
አማካሪ ፕሮፌሰሮቻቸው ወደሚገኙባቸው ዩኒቨርስቲዎች የቤተ-ሙከራ ሥራዎቻቸውን እንዲያከናውኑ
ተልከዋል፡፡ የጀርመን መንግስት በጀርመን ልማት ባንክ አማካኝነት ለባዮሜዲካል ትምህርትና ሥልጠና
እያደረገልን ባለው የፋይናንስ ድጋፍ በመጀመሪያው ዙር የ3.6 ሚሊዮን ዩሮ የሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና
ዕቃዎች እና መሳሪያዎች የግዥ ዝርዝር የያዘ የጨረታ ሰነድ ተዘጋጅቶ ጨረታ እንዲወጣ የተደረገ ሲሆን፤
ከአሸናፊው ድርጅት ጋር የውል ሰነድ በመፈራረም የ711 ሺህ ዩሮ አድቫንስ ክፍያ ተፈፅሟል፡፡ ከላይ
የተገለፀው የ3.6 ሚሊዮን ዩሮ የሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና ዕቃዎች እና መሳሪያዎች የሚቀመጡባቸው
ክፍሎች በተሻለ መልኩ ማደራጀትና መጠገን የሚያስችል የውል ሰነድ ተፈርሟል፡፡
በኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ ‘Korea EXIM Bank’ አማካኝነት በተገኘው 86 ሚሊዮን ዶላር በአዳማ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ለሚቋቋመው 5 የልዕቀት ማዕከላት አማካሪ ድርጅት ተቀጥሯል። በኮሪያ
ኢንተርናሽናል ትብብር ኤጀንሲ ‘Korea International Cooperation Agency – KOICA’ ለሁለት
ዩኒቨርስቲዎች ለአርሲ እና ለአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ
ልማትን መሠረት ያደረገ የ550,000.00 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ የሚደገፍ ፕሮጀክት ተቀርፆ እና ዕቅድ ተዘጋጅቶ
ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
በቦረና ዩኒቨርሲቲ በ2013 የበጀት ዓመት አጋማሽ የተጀመረው የማስፋፊያ የህንፃ ግንባታ ሥራ 83% ለማድረስ
ታቅዶ 74.56% ተከናውኗል፡፡ የዋና መሠረተ ልማት ግንባታ ሥራ 46.63% ለማከናወን ታቅዶ 37.15%
ተሰርቷል፡፡ በ3 ተቋራጮች እየተከናወነ ያለው የአጥር ግንባታ ሥራ 85% ለማድረስ ታቅዶ 82% ተከናውኗል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ሥራ ጊዜያዊና ዘለቄታዊ ተብሎ ሲከናወን የቆየ ሲሆን ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ
አቅርቦት ግንባታ ሥራ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ የታቀደ ቢሆንም አብዛኞቹ ሕንፃዎች ኃይል አግኝተው
ከፍተኛ ኃይል ለሚያስፈልጋቸው ሕንፃዎች ተጨማሪ 2 ትራንስፎርመሮች በማስፈለጋቸውና ባለመቅረቡ
አልተጠናቀቀም፡፡
39
የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ግንባታ የመስመር ዝርጋታ ሥራ ከጠቅላላው 12.5 ኪሜ ውስጥ ከ11 ኪሜ በላይ
ተዘርግቷል፡፡ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ የ2 ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ፓምፕ (Two submersible pump) ገጠማ
ሥራ የተከናወነ ሲሆን የውሃ ማጠራቀሚያ ጋን ግንባታ (Pioneer water reservoir) ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ የመቆጣጣሪያ ክፍል እና የጀነሬተር ቤት ግንባታዎች ደግሞ የማጠናቀቂያ ሥራዎች እየተከናወኑ
ይገኛሉ፡፡ አፈፃፀሙን 86% ለማድረስ ታቅዶ 77.57% ተከናዉኗል፡፡ የግንባታ ግብአት ግዥና ሥርጭትን
በተመለከተ ባለፈው በጀት ዓመት ግዥ ለመፈፀም ውለታ ከተገባው 80ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ ውስጥ በሩብ
ዓመቱ የተሰራጨውን 10 ሺህ ኩንታል ጨምሮ እስካሁን ድረስ በጠቅላላው 50 ሺህ ኩንታል ለዩኒቨርሲቲው
እንዲሰራጭ ተደርጓል፡፡ የአርማታ ብረት ደግሞ የ4.3 ቶን ግዥ ተፈጽሞ ለዩኒቨርሲቲው እንዲደርስ ተደርጓል፡፡
የትምህርት መሣሪያና ሌሎች ዕቃዎች ግዥ የ4ቱ (የላብራቶሪ መሣሪያዎች፣ የላብራቶሪ ፈርኒቸር፣ የሶሻል
ሳይንስ መጽሐፍትና የፈርኒቸር ግዥ) የቴክኒክ ግምገማ ሥራ ተጠናቆ የዋጋ ግምገማ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን
የጀኔሬተር ግዥ ደግሞ ዕቃዎቹ ከውጭ ተጭነው ወደ ሀገር እየተጓጓዙ ይገኛሉ፡፡
የከፍተኛ ትምህርት አመታዊ የቅበላ አቅምን ከማሳደግ አንጻር አመታዊ የቅበላ ምጣኔን ከነበረበት 14.2
በመቶ ወደ 15.2 በመቶ ለማሳደግ በተያዘው ዕቅድ መሰረት ሙሉ በሙሉ ማሳካት የተቻለ ሲሆን የዕቅድ
አፈጻጸሙም 100% ነው፡፡ የዓለም ባንክ በ2021 ባወጣው ሪፖርት መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ጥቅል
ተሳትፎ (Gross Enrollment Ratio in Higher Education) በ2020 የዓለም አማካይ ተሳትፎ 40%፣
ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገራት ተሳትፎ 27% እና በ2019 ከሰሀራ በታች ያሉ አገራት ተሳትፎ
ደግሞ 9% መሆኑን ያሳያል። መረጃው እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት የተሻለ ደረጃ
ላይ ብትሆንም መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት የደረሱበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ግን ብዙ መስራት
ይጠበቅባታል፡፡
የ2014 በጀት ዓመት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን የመቀበል አቅም (Intake
Capacity) መረጃ በማሰባሰብ በ2013 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመመደብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት
በማድረግ የመግቢያ መቁረጫ ውጤትን ያሟሉ 160,214 ተማሪዎችን በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የመመደብ ሥራ ተሰርቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በምደባው ላይ ቅሬታ ያቀረቡ ተማሪዎችን
ቅሬታቸውን በመቀበል በመመሪያው መሰረት የማስተናገድ ስራ ተሰርቷል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጠቅላላ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ቅበላ (በመደበኛና በተከታታይ1
ትምህርት) ከ1,141,295 ወደ 1,522,615 ለማድረስ ታቅዶ አፈጻጸሙ 1,527,629 (100.3%) ሆኖ
1
በተከታታይ የሚለው ቃል በማታ፣ በሳምንት መጨረሻ፣ በርቀት እና በክረምት ወቅት የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞችነ የሚያጠቃልል
ነው፡፡
40
ተመዝግቧል፡፡ በመደበኛ መርሀ ግብር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች
ተሳትፎ ከ520,053 ወደ 638,053 ለማድረስ ታቅዶ 642, 067 (101%) ደርሷል። ይህም በመነሻ ዓመት
ከነበሩት 520,053 ተማሪዎች ውስጥ 38,000 ተማሪዎች በበጀት ዓመቱ የተመረቁ ሲሆን ዘንድሮ 160,014
ተማሪዎች አዲስ በመቀበላችን ተሳትፎው ወደ 642,067 ማደግ ችሏል፡፡
በተከታታይ ትምህርት (በማታ፣ በቅዳሜና እሁድ እና በርቀት) በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
መርሃ-ግብር ተጠቃሚ የሆኑ ተማሪዎች ከ 505,686 ወደ 539,492 ለማድረስ የታቀደ ሲሆን አፈጻጸሙ
539,492 (100%) ነው፡፡
በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመደበኛ መርሀ-ግብር የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ተሳትፎ ከ63,855
ወደ 285,070 ለማድረስ ታቅዶ 285,070 (100%) ማድረስ የተቻለ ሲሆን በተከታታይ2 ትምህርት (በማታ፣
በቅዳሜና እሁድ እና በርቀት) መርሃ-ግብር ተጠቃሚ የሆኑ ተማሪዎችን ደግም ከ51,701 ወደ 60,000
ለማድረስ ታቅዶ አፈጻጸሙን 61,000 (102%) ማድረስ ተችሏል፡፡ በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
በመደበኛ ፕሮግራም የመጀመሪያ ዓመት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን ተሳትፎ ከ141,295 ወደ 156,000
ለማሳደግ ታቅዶ አፈጻጸሙ 160,014 (102.6%) ደርሷል፡፡ ከላይ የተገለጹት የአፈጻጸም ደረጃዎች
የሚያሳዩት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ሲሆን ለስኬቱም መንግስት በተለያየ መንገድ ከፍተኛውን ሚና
ተጫውቷል፡፡
ነገር ግን በህክምና ትምህርት መስክ የስፔሻሊቲ ተማሪዎችን ተሳትፎ ከነበረበት 1,444 ወደ 3,000
ለማድረስ ታቅዶ 2,900 ማድረስ የተቻለ ሲሆን የተግባሩ አፈጻጸምም 97 በመቶ ነው፡፡ እንዲሁም በድህረ
ስፔሻሊቲ የተማሪዎችን ዓመታዊ የቅበላ አቅም ከ87 ወደ 100 ለማሳደግ የታቀደ ቢሆንም በኮቪድ 19
ምክንያት የትምህርት ካሌንደር በመዛባቱ በበጀት አመቱ መቀበል የተቻለው 66(66%) ብቻ ነው፡፡
በሌላ መልኩ በበጀት ዓመቱ በመንግስት እና የግል ተቋማት ትብብር የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞችን
ቁጥር 5 ለማድረስ የታቀደ ቢሆንም የአሰራር ማነቆዎችን የሚፈታ የማስፈጸሚያ መመሪያ ተጠናቆ ጥቅም
ላይ ባለመዋሉ ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ ማከናወን አልተቻለም፡፡ ነገር ግን ከውጭ ሀገር ተቋማት ጋር
በጉድኝት/በጋራ ትምህርት የሚሰጡ ተቋማት ቁጥር 5 ለማድረስ ታቅዶ የዕቅድ ክንውኑን 4(80%) ማድረስ
ተችሏል።
2
ተከታታይ የሚለው ቃል በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የክረምት ፕሮግራምን አያጠቃልልም፡፡
41
ከነበረበት 34.3 በመቶ ወደ 37.87 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ በበጀት ዓመቱ 38.2 ማድረስ ተችሏል፡፡
ይህም የዕቅድ አፈጻጸሙን 100.87% ያደርሰዋል፡፡ በሁለተኛ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎ ከነበረበት
15% ወደ 22% ለማሳደግ ታቅዶ 22.7% ማድረስ የተቻለ ሲሆን የዕቅድ አፈጻጸም ደረጃውም 103.2%
ነው፡፡ እንደዚሁም በበጀት ዓመቱ በሦስተኛ ዲግሪ የሴት ተማሪዎች ተሳትፎን ከነበረበት 9% ወደ 13%
ለማሳደግ ታቅዶ 11.5% ማድረስ ተችሏል፡፡ በመሆኑም የዕቅድ አፈጻጸሙ 88.46% ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
በመጀመሪያ ዲግሪ የተማሪዎች ምጣኔ ድጋፍ የሚሹ ክልሎች ከነበረበት 3.4% ወደ 3.6% ለማሳደግ
ታቅዶ ልዩ ልዩ ተግባራት የተከናወኑ ቢሆንም የበጀት ዓመቱ ክንውን ከ3.4% በላይ ማሳደግ አልተቻለም።
በተመሳሳይ ሁኔታ በበጀት ዓመቱ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎች ተሳትፎን ከነበረበት 0.8% ወደ 0.9%
ለማሳደግ ልዩ ልዩ ተግባራት የተከናወኑ ቢሆንም የዕቅድ ክንውኑን ከ0.8% በላይ ማሳደግ አልተቻለም፡፡
ስኮላርሽፕ ተጠቃሚ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችንም ከነበረበት 1% ወደ 1.3% ለማሳደግ ዕቅድ የተያዘ
ቢሆንም የበጀት ዓመቱን ክንውን ከ1% በላይ ማሳደግ አልተቻለም፡፡ በተቃራኒ ግን በሳይንስና ቴክኖሎጂ
ፕሮግራሞች የሴት ተማሪዎች ተሳትፎን ከነበረበት 31.6 በመቶ ወደ 32.6 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ
በተከናወኑ ተግባራት የዕቅድ አፈጻጸሙ 33% የደረሰ ሲሆን ይህም ክንውኑን 101.2% እንደሚያደርሰው
በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል የቅድመ ምረቃ ሴት ተማሪዎች የማጠናቀቅ ምጣኔ ከነበረበት 75% ወደ 76% ለማሳደግ
የታቀደ ቢሆንም መፈፀም የተቻለው ግን 75% ነው። እንዲሁም በቅድመ ምረቃ የአካል ጉዳተኛ
ተማሪዎች የማጠናቀቅ ምጣኔን ከ78% ወደ 90% ለማሳደግ የታቀደ ቢሆንም ማሳካት የተቻለው ግን 78%
ብቻ ነው። በተመሳሳይ መልኩ ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎችና አካባቢዎች የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች
የማጠናቀቅ ምጣኔን ከ75.4% ወደ 95% ለማድረስ ቢታቀድም ማድረስ የተቻለው 75.4% ብቻ ነው።
የሀገር ውስጥ ጆርናሎችን ጥራትና ዓለም አቀፍ እይታ ለማሳደግ ጆርናሎችን ለመገምገምና ለመፈተሽ
የሚያስችሉ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ወደስራ እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡ ለሀገር ውስጥ ጆርናሎች እውቅና
የመስጠት ስራ እየተሰራ ሲሆን የጆርናሎች ግምገማና ፍተሻ ስራ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እየተመዘነ
በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና ይገኛል፡፡ በአገር ውስጥ ጆርናሎች ፍተሻ ስራ እውቅና ያገኙ ጆርናሎችን
ከነበረበት 10 ወደ 31 ለማድረስ ታቅዶ ለ33 (106.4%) ጆርናሎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡ እንዲሁም የሀገር
ውስጥ ጆርናሎች ፍተሻና እውቅና ስራን በሶፍት ዌር ለማገዝ የማበልጸግ ስራ ተሰርቷል፡፡ በዚህ መሰረት
22 ጆርናሎች እውቅና ለማግኘት በOnline አመልክተዋል፡፡
42
ወደ ስራ ለማስገባት ከተዘጋጀው ብሄራዊ የምርምር ስትራቴጂና የምርምር ትኩረት መስኮች በተጨማሪ
አስቻይ የሆኑ ሶስት ተጨማሪ ዘርፎችን (ትምህርት፣ ጤናና ገቨርናንስ) እንደ የትኩረት መስኮች ተለይተው
ስራ ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡ በዚህ መሰረት በ2014 ዓ.ም በጀት ዓመት 1,600 መሰረታዊ የምርምር
ሥራዎችን ለማካሄድ ታቅዶ 1,316 መሰረታዊ ምርምሮች ተካሂደዋል፡ አፈጻጸሙም 82.25% ነው፡፡
እንዲሁም 1,000 ችግር ፈቺ ምርምሮች ለማካሄድ ታቅዶ 593 (59.3%) ምርምሮች ተካሂደዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በ2014 የበጀት ዓመት በየሩብ ዓመቱ አንድ ጊዜ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት
ምክትል ፕሬዝደንቶች ፎረም ለማካሄድ ታቅዶ 3 ጊዜ (75%) ተካሂዷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሀገር ውስጥ
የምርምር ጆርናሎች መገምገሚያ መመሪያዎችን ከልሶ ለማዘጋጀት ታቅዶ መመሪያዎቹን የመከለስ ስራ
ተሰርቷል፡፡ በዓመቱ በተቋማት የተዋቀሩ እና የተጠናከሩ የምርምር ስነ ምግባር ቦርዶችን 30 ለማድረስ
የታቀደ ሲሆን ክንውኑ ግን 7 ተቋማት (23.3%) ብቻ እንደሆነ ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡ ሰባቱ ተቋማትም
የአርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሜዲካልና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ የአክሊሉ ለማ
ፓቶባዮሎጂ ኢንስቲቱዩት ፣ ደቡብ ክልል ህብረተሰብ ጤና (SNNPR PHI) ፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (DDU)
እና የሀዋሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ናቸው፡፡
በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በብሔራዊ የምርምር ስነ-ምግባር ቦርድ ተፈትሸውና የምርምር ስነ-ምግባርን
ጠብቀው በተመራማሪዎች እየተሰሩ ያሉ ምርምሮች ከታቀደው 90 ውስጥ 98 (108.9%) ፕሮቶኮሎች
ተገምግመው አልፈዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የምርምር ስነ-ምግባርን ጠብቀው በየተቋማቱ የተሰሩ
ምርምሮች መረጃዎችን ባሳለፍነው አንድ አመት ከ13 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና ከሌሎች
የምርምር ተቋማት (የኢትዮጵያ ሶሾሎጂስትና ሶሻል አንትሮፖሎጂስት ማህበር) መረጃዎችን በማሰባሰብ
ከ13 ዩኒቨርሲቲዎች 1247 ከአንድ የምርምር ተቋም 17 ሲሆኑ እንደ አጠቃላይ በከፍተኛ ትምህርትና
ሌሎች የምርምር ተቋማት የተሰሩ 1362 ፕሮቶኮሎች (ጥናቶች) ተገምግመው አልፈዋል፡ አፈፃፀሙም
100% እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
በሌላ መልኩ ደግሞ በምርምር ስነምግባር ዙሪያ ከተለያዩ ዩኑቨርሲቲዎች እና ከተለያዩ ማህበራት
(በኢትዮጲያ ሶሾሎጂስትና ሶሻል አንትሮፖሎጂስት፣ በኢትዮጲያ የአንስቴዥያና ነርሶች ማህበር)
ለተውጣጡ 300 ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል። ይሁን እንጂ ብሔራዊ የምርምር ስነ-ምግባር ኮሚቴ
በማዋቀርና በማጠናከር ዙሪያ የተከናወነ ስራ የሌለ ሲሆን ይህም የሆነበት ምክንያት ከምርምር ስነምግባር
መመሪያው ህትመትና ስርጭት በኋላ መከናወን እንዳለበት የጋራ መግባባት ላይ በመደረሱ ነው፡፡
43
ግብ 12፡- የተቋማት ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ማሻሻል
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና፣ የምርምር ተቋማት እና የኢንዱስትሪ ትስስር ቀጠናዊ ክላስተር በበጀት
ዓመቱ 400 አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪዎች፣ 75 የምርምር ተቋማት እና 104 ቴክኒክና ሙያ
ስልጠና ተቋማት በጋራ ችግር ፈቺ ምርምር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የጋራ የተግባር ስልጠና እና የማማከር
ስራዎች ላይ ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ትስስር ፈጥረዋል፡፡ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የመንግስት ተቋማት አዲስ አደረጃጀት
መሰረት አዳዲስ ተቋማትን የመለየት ነባር እና የታጠፉትን በአዲስ የመቀየርና መዋቅራዊ ለውጡን
በመፈተሽ የብሔራዊ ካውንስል አባላት፣ የቀጠናዊ ክላስተር እና ንዑስ ቀጠናዊ ክላስተር የመለየት
ሥራዎች ተከናውኗል፡፡
የጋራ ችግር ፈቺ ምርምሮችን በተመለከተ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከተከናወኑት አጠቃላይ ችግር
ፈቺ ምርምሮች መካከል የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪ ትስስር እንዲሰሩ
ከታቀዱት 100 የጋራ ችግር ፈቺ ምርምሮች 75ቱ (75%) ተከናውኗል። በትስስር የሚከናወኑ የቴክኖሎጂ
ሽግግር ስራን ለማሳደግ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከተሸጋገሩ 120 ቴክኖሎጂዎች መካከል በከፍተኛ
ትምህርትና ስልጠና ምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪ ትስስር 14ቱ (12%) እንዲሸጋገሩ የታቀደ ሲሆን 18
ቴክኖሎጂዎች ለኢንዱስትሪው ችግር ፈቺ ሆነው ተሸጋግረዋል፡፡ ይህም አፈጻጸሙን 120% ያደርሰዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትስስር የሚሰጡ የማማከር አገልግሎቶችን ለማጠናከር 22%ቱ ተቋማት
የማማከር አገልግሎት እንዲያከናውኑ ታቅዶ 36.9%ቱ ማለትም 17 ዩኒቨርሲቲዎች ለኢንዱስትሪዎች
የማማከር ስራ ሰርተዋል፡፡ አፈጻጸሙም በጣም ከፍተኛ ሆኖ ታይቷል፡፡ በዚህም 74.8 ሚሊዮን ብር ገቢ
ተገኝቷል፡፡
የአቅም ግንባታ ስራን አስመልከቶ በትስስሩ የተሸጋገሩ ቴክኖሎጂ፣ የጋራ ምርምር ስራዎች፣ የማማከር
አገልግሎቶች፣ የጋራ ትምህርት ፕሮግራሞች፣ የተግባር ልምምድና አቅም ግንባታ ስልጠናዎች ልየታ
በማድረግ በአራት ዙር ለዩኒቨርሲቲዎች፣ ለ71 ኢንዱስትሪዎች፣ ለቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ እና ምርምር
ተቋማት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተጨማረም 612 ልምድ ያካበቱ የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ወደ ከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት በመምጣት የአጭር ጊዜ የክህሎት ስልጠና ለመምህራንና ለተማሪዎች እንዲሰጡ
ተደርጓል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ስልጠናና ምርምር ተቋማትና ኢንዱስትሪ ትስስር ረቂቅ ፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፎች
ላይ ለዩኒቨርሲቲዎች፣ ለቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት፣ ለኢንዱስትሪዎች፣ ለምርምር ተቋማት እና
ለሴክተር ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የግንዛቤ
ማስጨበጫ ስልጠና እና ግብዓት ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡
44
በየተቋማቱ የኢንኩቤሽን ማዕከላትን ለማጠናከር ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ከጅማ
ዩኒቨርሲቲ እና ሥራተራ3 ቢዝነስ ኢንኩቤሽን ድርጅት ጋር በመተባበር በግብርና ዙሪያ ሰባት
የኢንኩቤሽን ማዕከል ለማቋቋም እና ለማጠናከር የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ስራ ተገብቷል።
ኢንኩቤሽን ማዕከላትን ለማጠናከር መሰረታዊ ቢዝነስ ኢንኩቤሽን እና ጀማሪ የሀብት ፈጠራ (Start-up)
ስራ ክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና ከ12 ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ ሠልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በመሆኑም በበጀት ዓመቱ 32 ኢንኩቤሽን ማዕከላትን ለማቋቋም ታቅዶ 21(65.6%) ተቋቁመዋል፡፡ የዕቅድ
አፈጻጸሙ ዝቅ ያለበት ምክንያት ባለው ሀገራዊ ችግር ስልጠናውን ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ማዳረስ
ባለመቻሉ ነው፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቴክኖሊጂ ሽግግር ስራን በተመለከተ የተቀዱ፣ የተላመዱ እና የተፈጠሩ
ቴክኖሎጂዎችን መለየትና ማጠናቀር እንዲሁም ለማህበረሰቡ እና ለኢንዱስትሪው 334 ቴክኖሎጂዎች
ለማሸጋገር የታቀደ ሲሆን በ33 ዩኒቨርሲቲዎች በ452 መምህራን አማካኝነት 120(35.9%) ቴክኖሎጂዎች
ተሸጋግረዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 55ቱ የተቀዱ፤ 41ዱ የተሻሻሉ እና 24ቱ አዲስ የተፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች
ናቸው፡፡ ከዚሁ ጋር በተገናኘ በቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደት ላይ የሴቶችን ተሳትፎ 10 በመቶ ለማሳደግ
ታቅዶ 10.5 በመቶ ለማሳደግ ተችሏል፡፡ በዚህም ከተሸጋገሩት 120 ቴክኖሎጂዎች መካከል 11ዱ በሴቶች
አማካኝነት የተሸጋገሩ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ተማሪዎች ከመማር መመራመር በተጨማሪ
በአካባቢያቸው ላለው ህብረተሰብ እና ኢንዱስትሪው ቴክኖሎጂን በመቅዳት፣ በማላመድና በመፍጠር
እንዲያሸጋግሩ ይጠበቃል፡፡ በመሆኑም ከተሸጋገሩት 120 ቴክኖሎጂዎች 16 ቴክኖሎጂዎች በተማሪዎች
የተሸጋገሩ ናቸው፡፡
3
በቢዝነስ ኢንኩቤሽን ስራ የተሰማራ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው
45
ረ. የትምህርት መሰረተ ልማትና ፋሲሊቲን ማሻሻል፤
በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የዘመነና የተቀናጀ የመረጃ አመራር
የማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሥርዓት Higher Education and Training Management Information
System (HETMIS) ለመስጠት የሪካይረመንት፣ የKPI፣ የዳሽቦርድ፣ የመረጃ ቋት ዲዛይንና የሥርዓት
ዝርጋታ (System Development) ተጠናቆ ስልጠና በመስጠት ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ አፈጻጸሙም
(100%) ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ክህሎትን ለማስፋፋት ተግባራዊ
የሆኑ ፖሊሲዎችንና ስታንዳርዶች በማውጣት ተግባራዊ ተደርጎ ስራ ላይ ውለዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ክህሎትንና መሰረተ ልማት ለማስፋፋት እና
ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ የሚያስችል የአይሲቲ ዝግጁነት ኢንዴክስ (ICT Readiness Index) ጥናት
ከUNESC ጋር በመሆን ጥናቱ እየተካሄደ ይገኛል። የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና የዲጂታል ክህሎት
ፕሮግራሞች የኢኮኖሚውን የሙያና የሥራ ፍላጎት ያማከለና ያስተሳሰረ እንዲሆን ለማድረግ የከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት በመካከለኛ ደረጃ (Intermediate level) የዲጂታል ክህሎት እንዲሰጡ ለማድረግ
ስታንዳርድ የሆነ ሞጁል ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል፡ የዕቀድ አፈጻጸሙም 96% ደርሷል።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በadvanced የዲጂታል ክህሎት ፕሮግራሞችን ማሻሻያ ለማድረግ ከተቋማቱ
ጋር 2 የአይሲቲ ትምህርት አይነቶችን በመለየት ወደ ትግበራ ገብቷል፣ አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡ የከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት መምህራን የትምህርት አይሲቲ አጠቃቀምና የዲጂታል ክህሎት በማጠናከርና
በማስፋፋት፣ የመማር ማስተማር ስራዉን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ መምህራንን በዲጂታል ክህሎት
ለማሰልጠን NVIDIA Artificial Intelligence ከተበለ አለም አቀፍ ድርጅት ጋር በመተባበር ለመምህራን
ስልጠና ለመስጠት የሞዱሎችና የድርጊት መርሃግብር በማዘጋጀት ስልጠናውን ለመስጠት መምህራንን
ኦንላይን እየመለመልን እንገኛለን፣ አፈጻጸሙ (86.6%) ነው።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ የተከታታይ፣ የርቀትና የመደበኛ ትምህርቶችና በኦን
ላይን ትምህርት ለሚሰጠት የሚያስችል የዲጂታል ፕላትፎርም (LMS) በኢተርኔት ዳታ ማእከል በየጊዜው
በማሻሻል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፣ (https://courses.ethernet.edu.et/)፣ በተጨማሪም የ O.365 Class
notebook, OneNote እና Teams የክላውድ አገልግሎቶችን ዝግጁ በማድረግ በቀጣይ ስልጠና በመስጠት
አገልግሎቱን ለተጨማሪ 10 ተቋማት ማስፋፋት ተችሏል፣ አፈጻጸሙ (100%) ነው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የመማር ማስተማሩና የስልጠና ሂደቱ በበቂ የቴክኖሎጂ ግብዓት አቅርቦት እንዲሟላ ለማድረግ፣
የመማር ማስተማር ስራውን በቴክኖሎጂ ለማገዝ በመማሪያ ክፍሎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን እየያስፋፉና
እያያሻሉ ይገኛሉ፣ አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡
46
ለዲጂታል ኮንተንት ማልማት አገልግሎት የሚዉል ስታንዳርዱን የጠበቀ የዲጂታል ስቴዲዮ ተግባራዊ
ያደረጉና የዲጂታል ኮንቴንት ማበልጸግ የቻሉ ተቋማትን ቁጥር 3 ደርሷል፤ አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአይሲቲ ባለሙያዎችን የመማር ማስተማሩን ስራ በቴከኖሎጂ ለማገዝ
የዲጂታል ክህሎት ለማጠናከርና ለማስፋፋት፣ የመማር ማስተማር ስራውን በልዩ ሁኔታ ለማገዝ የሚስችል
የትምህርት ዲጂታል ቴክኖሎጂ የአይሲቲ ባለሙያዎች እንዲሰለጥኑ ተደርጓል፣ አፈጻጸሙ 100% ነው።
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮች እንዲሁም የመመረቂያ ጥናቶችን በጥራትና
በተገቢው መንገድ እንዲሰሩና ለተጠቃሚው ማህበረሰብና ለኢንዱስትሪው እንዲደርሱ ለማስቻል
የተደራጀውን ሃገራዊ የመረጃ ቋት (National Academic Digital Repository of Ethiopia (NADRE)
ስፍትዌሩን upgrade በማድረግና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሰሩ ከ13,000 በላይ አዲስ የምርምር
ይዘቶችን በቋቱ በማስገባት ለተጠቃሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፣ አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡
ከዓለም ባንክ የDigital Foundation ፕሮጀክት በተገኘ ድጋፍ ጥራት ያለውና ተደራሽ የሆነ የብሮድ-ባንድ
ኢንተርኔት ኮኔክቲቪቲ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመስጠት እንዲቻል አስፈላጊ ግብአቶች ለተቋማቱ
እንዲሟሉ የቴክኒክ ፍላጎት ዝርዝር ሰነድ በማዘጋጀት ግዢው በሂደት ላይ ይገኛል፣ አፈጻጸሙ 60%
ደርሷል። በተጨማሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከአለም አቀፍ የትምህርትና ምርምር ተቋማት ጋር
ለማገናኘት ከኢትዮ ቴሌኮምና ከጂቡቲ ቴሌኮም እንዲሁም አለም አቀፍ የቴሌኮም ኩባንያዎች ጋር
በመሆን ከአለም ባንክ የDigital Foundation ፕሮጀክትና ከEU የAfricaConnect 3 በተገኘ ድጋፍ
የዲዛይን ስራው ተጠናቆ ወደ ትግበራ ምእራፍ ተገብቷል፡፡ አፈጻጸም 60% ነው፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የኔትዎርክ ባንድዊድዝ ለማሰዳግና ከዚህ በፊት የከፍተኛ ብርድባንድ
ተጠቃሚ ያልሆኑትን ዩኒቨርሲቲዎች የፋይበር ባክቦን ዝርጋታ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ስራዉ
ተጀምሯል፡፡ አፈጻጸም 50% ነው፡፡ የመማር ማስተማር፣ የምርምርና አስተዳደር ስራውን በበቂ የቴክኖሎጂ
ግብዓት አቅርቦት በማሟላት በስታንዳርድ መሰረት የውስጥ ICT መሰረተ ልማቶችን (ግሪንና ስማርት
ካምፓስ ኔትዎርክ) እያሟሉ ይገኛሉ፣ አፈጻጸም (100%)፣ የኢተርኔት የባክ አፕ ዳታ ማእከል የሲቪል
47
ስራው ተጠናቆ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች በመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በኩል
መሳሪያዎቹ ወደ ሃገር ውስጥ ገብተው ለተከላ ዝግጁ ሆነዋል፡፡ አፈጻጸሙ 100% ደርሷል።
48
ክፍል አምስት
ከፈተና ዝግጅት አንጻር ለ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና ደረጃቸውን የጠበቁ ጥያቄዎችን
ማዘጋጀት በዋነኛነት በእቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም የ2013 ዓ.ም ፈተና በተለያዩ ምክንያቶች ተገፍቶ ወደ
2014 ዓ.ም በመዛወሩ የዝግጅት ሥራው በእቅዱ መሰረት በወቅቱ ባይጀመርም የ2013 የትምህርት ዘመን
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የ10 የትምህርት ዓይነቶች የመልስ ቁልፍ በጥንቃቄ በማዘጋጀት ለእርማት
አገልግሎት ወደ ሲስተም እንዲገባ ተደርጓል።
የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዝግጅት የፈተና ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የሚያስችል ሰነድ
በእያንዳንዱ የትምህርት ዓይነትና የክፍል ደረጃ መርሀ ትምህርቶች (Syllabus) ላይ ያሉትን ድርጊት
አመልካቾች ክለሳ ለማድረግ የየትምህርት ዓይነት የዩኒቨርሲቲ መምህራንና የፈተና ዝግጅት ባለሙያዎች
በቡድን በማድረግ በብሉም ስርዓት (Bloom Taxonomy) ምደባ መሰረት እንደገና በመከለስ በአስሩም
የትምህርት ዓይነቶች ተዘጋጅቷል፡፡
የ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዝግጅት ቢጋር (Blue Prinit /Table of
Specification) በማዘጋጀት ጥያቄዎችን ለመጻፍ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቆ እና ለፈተና ጸሐፊዎች
ገምጋሚዎች እና ለኤጀንሲው የፈተና ዝግጅት ባለሙያዎች ስለ ፈተና ዝግጅት ደህንነት በኢንፎርሜሽን
መረብ ደህንነት ባለሙያዎች አማካኝነት ሥልጠና በመስጠት እና የደህንነት ፍተሻ በማካሄድ ወደ ተግባር
ተገብቷል፡፡
የMELQO የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች በማደራጀትና በመተንተን ለዋና መረጃ ስብሰባ (main data
collection) ዝግጁ የተደረገ ሲሆን የተዘጋጁት የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎችንወደ ታብሌት መጫን
/upload/ በማድረግ በተመረጡ እና ስልጠና በወሰዱ 168 የትምህርት ባለሙያዎች ዋናውን መረጃ ከመስክ
መሰብሰብ ተችሏል።
የEGRA ጥናት ሰነድ ዝግጅት መግቢያ የአጠናን ስነ ዘዴ ክፍል፣ የመረጃ ትንተናና ጥናት ሪፖርት
ዝግጅት ሙሉ ለሙሉ ማጠናቀቅ ተችሏል፡፡ ይህ 2ኛ ና 3ኛ ክፍል ተማሪዎች የንባብ ክህሎት ምዘና
/EGRA/ ጥናት ውጤት ከትምህርት ልማት እቅድ አንጻር የታቀደው 36% እና 48% በቅደም ተከተል
ቢሆንም የተማሪዎች ውጤት ከብቃት ደረጃ አንጻር ሲታይ 13% እና 23% ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም
መሰረት የጥናቱ ዋና ዋና ግኝቶች እንደሚከተለው በግራፍ ቀርቧል።
49
በሰዓት የተገደቡና ያልተገደቡ ንዑስ ተግባራት የንባብ ውጤት በሀገር ደረጃ፡
ግራፍ 4 የሚያሳየው ተማሪዎች በሰዓት ያልተገደቡ ንዑስ ተግባራት ማለትም ድምጽ መለየት፣ አንብቦ
መረዳትና አዳምጦ መረዳት አስመልክቶ ከቀረበላቸው ጥያቄዎች መካከል በመቶኛ ምን ያህል
እንደመለሱት ነው። በዚህ መሰረት የሁለቱም የክፍል ደረጃ ተማሪዎች ድምጽ በመለየትና አዳምጦ
መረዳት ተግባራት ላይ በሀገር ደረጃ የጎላ ችግር የሌለባቸው መሆኑን ያመለክታል። ነገር ግን ትልቁ ችግር
አንብቦ መረዳት መሆኑን ከግራፉ ላይ መመልከት ይቻላል። ይህውም 2ኛና 3ኛ ክፍል ተማሪዎች
በቅደም ተከተል በደቂቃ ከአነበቡት ውስጥ መረዳት የቻሉት 7.6% እና 15% ብቻ መሆኑን ጥናቱ
ያሳያል። ሆኖም በሁሉም ንዑስ ተግባራት የ3ኛ ክፍል ውጤት ከ2ኛ ክፍል ተማሪዎች ተሽሎ ተገኝቷል።
50
ከግራፍ 5 እና 6 መረዳት እንደሚቻለው በሁለቱም የክፍል ደረጃዎች በሁሉም በሰዓት በተገደቡና
ባልተገደቡ ንዑስ ተግባራት የወንድ ተማሪዎች ውጤት በመጠኑም ቢሆን ከሴት ተማሪዎች ውጤት ተሽሎ
ታይቷል። ነገር ግን በሁለቱም ጾታ፤ የተማሪዎች የፈጠራ ቃላት ንባብና አንብቦ መረዳት ውጤት በጣም
ዝቅተኛ ነው። በአንጻሩ በሁለቱም ጾታ፤ የተማሪዎች ፊደልና ድምጽ መለየት እንዲሁም አዳምጦ
መረዳት ውጤት የተሻለ ሆኖ ታይቷል፡፡
51
ግራፍ 9 በእያንዳንዱ የቃል ንባብ የብቃት ደረጃዎች የሚገኙ የተማሪዎች ብዛት
በመቶኛ ከዓመት ዓመት ሲነጻጸር
150
ግራፍ 7 የሚያመለክተው በእያንዳንዱ የቃል ንባብ የብቃት ደረጃዎች የሚገኙ የተማሪዎች ብዛት በመቶኛ
ከዓመት ዓመት ሲነጻጸር ነው። ይኽውም ከ2006 እስከ 2013 ዓ.ም የተከናወኑ የታችኛው ክፍሎች የንባብ
ክህሎት ምዘና (EGRA) መሰረት በማድረግ ነው። ከዚህ አንጻር ምንም ማንበብ ያልቻሉ (Zero Readers)
የተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን መረዳት ጥናቱ ያመላክታል። ስለዚህ ምንም ቃል ማንበብ ያልቻሉ
ተማሪዎችን ቁጥር መቀነስ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው። ከግራፉ መመልከት እንደሚቻለው በአራቱም
ዓመታት የንባብ ክህሎት ምዘና (EGRA) ጥናት፤ በሙሉ ቅልጥፍናና መረዳት ማንበብ የቻሉ ተማሪዎች
ብዛት በመቶኛ ወደ 6% ብቻ ሲሆን ይህም ከሞላ ጎደል አዝማሚያው ባለበት መቀጠሉን ያሳያል። በበጀት
ዓመቱ በ4ኛ እና 8ኛ ክፍሎች ላይ ለሚደረገው የ7ኛው ዙር የምዘና ጥናት የመረጃ መሰብሰቢያ
መሳሪያዎችን የመከለስ አዳዲስ በናሙና ምክንያት የተጨመሩ ቋንቋዎች የማስተርጎም ስራ ተሰርቷል፡፡
በተመሳሳይ 7ኛው ዙር የ4ኛና 8ኛ ክፍሎች (NLA) መረጃ መሰብሰብ በታቀደው መሰረት የናሙና መረጣ፣
የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች ክለሳና ትርጉም፣ ለህትመት ዝግጁ የማድረግ ስራ ተከናወኗል።
በአለም አቀፋዊ የትምህርት ምዘናዎች (PISA/TIMSS) ለመሳተፍ እንዲቻል በመስክ ሙከራ የተገኙ
የጥናት ሪፖርቶችን በመገምገም ለውሳኔ ሀሳብ ለማቅረብ በዚህ እቅድ ዓመት 100% እንደሚከናወን
የታቀደ ሲሆን ሶስት የጥናት ሰነዶች ማለትም የ4ኛና 8ኛ ከፍል TIMSS እንዲሁም የ15 ዓመት ተማሪዎች
PISA ሪፖርቶች በባለሙያዎች ተገምግሞ ግብዓት እንዲሰጥ ተደርጎ ዝግጁ ሆኗል።
የሀገር አቀፍ ፈተና ደህንነት ሥጋቶች እና መፍትሔዎችን በተመለከተ የ2013 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና
ዙሪያ ጥናት እንዲጠና ተደርጓል፡፡ የጥናት ውጤቱም ለፈተና መውጣት (leakage) መሰረታዊ ችግሮች
በሁሉም የፈተና ሂደቶች ከዝግጅት ጀምሮ እሰከ አሰጣጥ ባሉት የፈተና ሂደቶች ተለይተዋል፡፡ በተመሳሳይ
የፈተና ደንብ ጥሰትን አጠቃላይ አፈጻጸም ለመለየት በተካሄደው የዳሰሳ ጥናት የደንብ ጥሰት ችግሮችም
በቅደም ተከተል በሚከተለው ግራፍ ቀርበዋል፡፡
52
70% 63%
59% 59% 58% 58% 56% 57% 56%
60%
50% 41% 41% 42% 42% 44% 43% 44%
37%
40%
30%
20%
10%
0%
አለ የለም አለ የለም አለ የለም አለ የለም አለ የለም አለ የለም አለ የለም አለ የለም
ሞባይልና ፈተና ክፍል ፈተና ዋና ዋና የፈተና ወረቀት የፈተና መልስ የፈተና ለሌላ ሰው
ሌሎች ውስጥ ጎበዝ ከተቀመጠበት ይዘቶችን የያዘ አውጥቶ መልሱ ነው ብለው አስፈጻሚዎችን መፈተን / ሌላ
ኤሌክትሮኒክስ ከሚባሉ ቦታ መስረቅ/ ብጣሽ ወረቀት ተሰርቶ ከሚሸጡ በመደለል ሰው ማስፈተን
መሳሪየዎችን ተፈታኞች ለመስረቅ ይዞ ፈተና እንዲገባ ግለሰቦች ገዝቶ ወይም
ተጠቅሞ ፈተና መኮራረጅ ሙከራ ክፍል መግባት ማድረግ ለመጠቀም በማስፈራራት
መስራት ማድረግ መሞከር ለመኮራረጅ
መሞከር
ግራፍ 10፡-የ2013 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ የዳሰሳ ጥናት ሪፖርት
የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ዝግጅት ማዕቀፍ እና የአፈጻጸም መለኪያ ስታንዳርድ ለማዘጋጀት ታቅዶ የ2014
በጀት ዓመት የ12ኛ ክፍል ፈተና ዝግጅት የአፈጻጸም መለኪያ ስታንዳርድ ማዘጋጀት ተችሏል፡፡ ይህም
የፈተና ስርዓት የአሰራር ማዕቀፎች ለመዘርጋት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡
የታችኛው ክፍሎች (2/3) የንባብ ክህሎት ምዘና ጥናት (EGRA) ሶስት ቋንቋዎችን (አፋር፣ኑዌርና በርታ)
ለስታንዳርድ ሴትንግ አውደ ጥናት (standard setting workshop) ዝግጁ በማድረግ ከእያንዳንዱ ቋንቋ
ዘጠኝ ባለሙያዎች ያሳተፈ የደረጃ መለያ መቁረጫ ነጥብ /Bench Marking Standard/ እንዲወሰን
ተደርጓል ይህም ዕቅዱን 100% ማከናወን ተችሏል። በተመሳሳይ የምዘና ሥርዓቱን የአሰራርና የፖሊሲ
ማዕቀፍ (Assessment Policy Framework) እና የአጠቃላይ ምዘና አሰራር ማዕቀፍ (Comprehensive
Assessment Framework) በማዘጋጀት ለባለሙያዎች የማስገምገም እና ግብአት የመሰብሰብ ስራ
ተከናውኗል፡፡
53
5.3 የትምህርት ምዘናና የፈተና ውጤት መረጃዎችን ተደራሽነት ማሳደግ
የታችኛው ክፍሎች የንባብ ክህሎት ምዘና (EGRA) መረጃ ተተንትኖ በ30ኛው የትምህርት ጉባዔ ላይ
የጥናቱ ዋና ዋና ረቂቅ ግኝቶች ለትምህርት ባለድርሻ አካላት እና ለትምህርት ባለሙያዎች ቀርቦ
ውይይት ተደርጎበታል።
በ2014 ዓ.ም የተሰጠው 2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስተዳደር በተመለከተ በየፈተና
ጣቢያዎች ተዘጋጅቶ በተላከው የደንብ ጥሰት መረጃ መሰረት ተሞልቶ የመጣውን የደንብ ጥሰት መረጃ
በማሰባሰብና በጥፋቱ ዓይነትና ደረጃ በመለየት የውሳኔ ሃሳብ ቀርቦ 80 የሚሆኑ ተፈታኞች የቅጣት ውሳኔ
ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ 41(51.5%) የሚሆኑት ሞባይል በመጠቀም ደንብ ጥሰት የፈፀሙ ናቸው፡
፡ በቅጣት ውሳኔው 60 (75%) የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ ውጤታቸው የተሰረዘ ሲሆን 20 (25%) ደግሞ
የደንብ ጥሰት የፈጸሙባቸው የትምህርት ፈተና አይነቶች ብቻ ተለይቶ ውጤታቸው እንዲሰረዙ ተደርጓል።
የ8ኛ ክፍልን ክልላዊ ፈተና ደረጃ (Standard) ለማስጠበቅ የሚከናወኑ ተግባራትን ለሁሉም ክልሎች
ተደራሽ ከማድረግ አንጻር ተገቢነታቸውና ስታንዳርዳቸውን ጠብቀው የተዘጋጁ የ8ኛ ከፍል ክልላዊ ፈተና
ዝግጅት ቢጋር (Test blue print) ክልሎችን ባሳተፈ መልኩ ሥልጠና በመስጠት እና ስታንዳርዱን ጠብቆ
በማዘጋጀት ለክልሎች በሶፍት ኮፒ በመስጠት ደረጃውን የማስጠበቅ ሥራ ተሰርቷል፡፡
ከተፈታኞች ምዝገባ አንጻር የ2013 ዓ.ም የተፈታኞች ምዝገባ መረጃ ለማጣራትና የሁሉም ክልል አዲስ
አስፈታኝ ት/ቤቶች የት/ቤት መለያ ኮድ ለመስጠት ከአዲሱ የምዝገባ ሲስተም ወደ ነባሩ የDRS ሲስተም
እንዲገቡ ተደርጓል። በአዲሱ የDermalog ሲስተም የ11ዱም ክልል ተፈታኞች ምዝገባ በማከናወን
የ620,730 ተፈታኝ ዳታ ወደ DRS ሲስተም ማስገባት ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ዳታዎችን ከDermalog
ሲስተም ወደ DRS ሲስተም በማዘዋወር (Data migration) ዳታ ማጥራቱም (Adjucation and
confirmation) ሥራ በሁሉም ክልሎች ተሠርቷል፡፡ የ620,730 ተፈታኞች መረጃን በማጣራትና የፈተና
አዳራሽ መግቢያ ካርድ (Admission card) ለክልሎች እዲደርስ ተደርጓል፡፡ በመጀመሪያው ዙር
3,515,179 በሁለተኛው ዙር ደግሞ 349,071 በአጠቃላይ 3,864,256 የመልስ ወረቀቶችን በማንበብ
(answer scanning)/ የእርማት ስራውን በማከናወን ውጤቱን ይፋ ማድረግ ተችሏል፡፡
የ2014 ዓ.ም የኦንላይን ምዝገባ በአጠቃላይ ለ315 የክልል የት/ቢሮ ምክትልና የክልል ት/ቢሮ የፈተና
ክፍል ሃላፊዎች እና የICT ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
54
ግራፍ
11፡- የ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈታኞች ምዝገባ አፈጻጸም
የምዝገባ አፈጻጸሙ ከእቅዱ አንጻር ዝቅ ያለበት ምክንያት በበይነ መረብ ለመመዝገብ ታቅዶ
የመመዝገቢያ ኪት፣ ላብቶፕ፣ የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ እና የግል ተመዝጋቢዎች የተገመተውን
ያህል ወደ ምዝገባ ጣቢያ በወቅቱ ተገኝተው አለመመዝገባቸው በዋነኝነት ይጠቀሳሉ፡፡ በቀሩት ቀናት ወደ
ምዝገባ ጣቢያ ተገኝተው እንዲመዘገቡ ማድረግ በመገናኛ ብዙሃን የማስተዋወቅ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በሌላ በኩል 34,871 ለሚሆኑ ደንበኞች የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ አገልግሎት (178.8%)፣ 34,864
የድጋሜ ሰርተፊኬት አገልግሎት(99.7%) እና 1,727 በስም ላይ የፊደላት ግድፈትን ማስተካከል ሥራ
(94.68%) በድምሩ ለ69,462 ተገልጋዮች አገልግሎት በመሰጠት ተደራሽ ማደረግ ተችሏል፡፡ መንግስታዊ
እና መንግስታዊ ካልሆኑ መስርያቤቶች ከመጡ 1109 የትምህርት ማስረጃዎችን ውስጥ 173 (15.5%)
ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡
በፈተና ምዘናና ፈተና ስርዓቱ አዎንታዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አካላት ለመስጠት በተያዘው እቅድ
መሰረት የፈተና ጥያቄዎች ሲዘጋጁ የልዩ ፍላጎት፣ የስርዓተ ጾታን፣ ዓይነ-ስውራን ያካተተ ሀኖ እንዲዘጋጅ
ተደርጓል፡፡ በዚህም በ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሚወስዱ 620,730
ተፈታኞች መካከል 409 የሚሆኑት የዓይነ ስውር ተፈታኞች እና 2 የእጅ እንቅስቃሴ ችግር ያለባቸው
ተፈታኞች በድምሩ 411 ፈተና እንባቢዎችና ፀኃፊዎች በመመደብ ድጋፍ እንዲያገኙ እና በመመሪያው
መሰረት ለፈተናው ከተያዘው ሰአት ውጪ ተጨማሪ ሰአት ተጠቅመው እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡
5.5 የፈተናና ምዘና ስርዓቱን ለማዘመን የዲጂታል ቴክኖሎጂን አጠቀቃምን ማሻሻል የተፈታኞች
ቁጥር ከዓመት ዓመት እየጨመረ በመምጣቱ ቀደም ብለው በ2012 ዓ.ም በቂ ናቸው ተብለው ተሟልተው
የነበሩት ለኦላይን ፈተና የሚረዱ ተጨማሪ ግብአቶች ማለትም 12,000 ላፕቶፖች፣ 13,500 ዋይፋዎች፣
55
1,040 የቪሳት መሳሪያዎችና የ200 መመዝገቢያ ኪቶች በማስፈለጋቸው ተጨማሪ ለመግዛት በሂደት ላይ
ይገኛል። ተፈተኞችን በኦላይን ለመፈተን የሚያስፈልጉ ታብሌቶች ከውጭ አገር ባለመግባታቸው
የተፈታኞችን ሙሉ ዳታ/ የ617,991 ተፈታኝ/ ከአዲሱ ሲስተም /Dermalog/ ወደ ነባሩ ሲስተም /DRS/
በማዟዟር ጥቅም ላይ እንዲውል ተደርጓል። የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና
በሚሰጠበት ወቅት በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ የሚተላለፉ የፈተና ስርቆት እና ኩረጃን ለመከላከል
ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የአይሲቲ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር የሚዲያ ሞኒተሪንግ ስራ
ተሰርቷል።
56
ክፍል ስድስት
በዚህም መሰረት ለ10 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአካል በመገኘት በውስጥ ጥራት ማረጋገጫ አሰራር
ላይ ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ አፈጻጸሙ ለ6 (60%) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስልጠና በመስጠት
የጥራት ማረጋገጫ አሰራራቸውን ማሻሻል ተችሏል፡፡
ለ35 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ኦዲት በማከናወን የሚጠበቅባቸውን ተቋማዊ የጥራት ትኩረት
መስክ መስፈርቶችን እንዲተገብሩ ለማድረግ ታቅዶ በእቅዱ መሰረት ለ11 የከፍተኛ ትምህርት ተቋም
ተቋማዊ ኦዲት በማከናወን በጥራት መስክ የታየባቸውን ክፍተት እንዲያሟሉ በማድረግ 31.43% መፈጸም
ተችሏል፡፡ ይህ ስራ በእቅዱ መሰረት ያልተከናወነበት ምክንያት በሃገሪቷ በተፈጠረ የጸጥታ ችግር
ማለትም፡- ትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ፣ አማራ ክልል በከፊል፣ አፋር ክልል በከፊል፣ ኦሮሚያ ክልል
በከፊል እና ቤንሻንጉል ክልል በከፊል የጸጥታ ችግር ስለተፈጠረባቸው ነው፡፡
15 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ድህረ ኦዲት ክትትል በማድረግ ሪፖርት ማድረግ ታቅዶ በእቅዱ
መሰረት 5 (33.33%) ድህረ ኦዲት ክትትል በማድረግ ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ይህ ተግባር በእቅዱ
መሰረት ያልተከናወነው በሃገሪቷ በተፈጠረ የጸጥታ ችግር ምክንያት ነው፡፡
የትምህርት ማስረጃ አቻ ግመታ እና ማረጋገጥ አሰራር ስርዓትን ማሻሻል በተመለከተ በሀገር ውስጥ
ከሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተገኙ 15,000 የትምህርት ማስረጃዎችን ትክክለኛነት በማረጋገጥ
ለመስጠት ታቅዶ 11,403(76.02%) በመፈጸም የትምህርት ማስረጃዎችን ትክክለኛነት በማረጋገጥ በዋናነት
በህገወጥ መንገድ የሚያስተምሩና ሀሰተኛ ማስረጃ የሚሰጡትን ተቋማት መቆጣጠር መቻሉ እና
የአመሳስሎ የመስራትና ወንጀሎች እንዳይስፋፉ መቆጣጠር ተችሏል፡፡ ይህ ቁልፍ ውጤት ከእቅድ በላይ
ሊሰራ የቻለበት ምክንያት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በተፈጠረው ጠንካራ የሥራ ግንኙነት መሠረት
ቀደም ሲል የጤና ትምህርት ምሩቃን የትምህርት ማስረጃቸው ሳይረጋገጥ ወደ ሥራ ይሰማሩ የነበረውን
በማስቀረት የትምህርት ማስረጃቸውን እንዲረጋገጥ በመደረጉ ነው፡፡
57
የአቻ ግመታ አገልግሎትን በማሳደግ የፕሮግራም አግባብነትን በማረጋገጥ 800 የአቻ ግመታ የትምህርት
ማስረጃዎች ለመስጠት ታቅዶ 1075 (134.38%) ተገልጋዮች የፒኤችዲ፣ የማስተርስ ዲግሪ እና
የመጀመሪያ ዲግሪ ማስረጃቸው ተገምግሞ የአቻ ግመታ ተሠርቶላቸዋል፡፡ እንዲሁም የ2ኛ ደረጃ
ትምህርታቸውን ውጪ አጠናቀው ቀጣይ ትምህርታቸውን በሀገር ውስጥ ለመቀጠል የፈለጉ ማስረጃቸው
ተገምግሞ ተገቢው አገልግሎት ተሰጥቷቸዋል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ እየተሠራ ባለው ከፍተኛ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ የፌደራል መንግሥት መ/ቤቶች
የሰው ሀይል ቅጥር ሲፈጽሙም ሆነ ለደረጃ ዕድገት ሲያወዳድሩ የትምህርት ማስረጃዎቻቸው ትክክለኛነት
በቅድሚያ እንዲረጋገጥ እያደረጉ ይገኛል፡፡ በመሆኑም 85 መሥሪያ ቤቶች የሠራተኞቻቸው የትምህርት
ማስረጃ እንዲጣራ ጥያቄ አቅርበው ማስረጃቸው እየተጣራ ተገቢው ምላሽ ተሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት
በሀገር ውስጥ ከተገኙ የትምህርት ማስረጃዎች ሲረጋገጡ ህገወጥ ሆነው የተገኙ በአጠቃላይ 502 ሲሆኑ
የሲኦሲ ችግር ያለባቸው 272፣ የመቁረጫ ነጥብ ተገቢነት ችግር ያለባቸው 154፣ የዲፕሎማ ተዛማጅነት
ችግር ያለባቸው 51 እና ሌሎች ችግሮች ያሉባቸው 25 ናቸው፡፡ ከላይ የተገለፀው አጠቃላይ ክንውን
ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ክንውን ጋር ሲነጻጸር የሚታየው ዘጠኝ እጥፍ ለውጥ መኖሩን
ያሳያል፡፡ ይህ ውጤት የተገኘበት፣ በአንድ በኩል በቀጣሪዎችና በተገልጋዮች ዘንድ ከፍተኛ ግንዛቤ
መፈጠሩን በሌላ በኩል በሰራተኞች የስራ ቁርጠኝነት እየተፈጠረ መሆኑን ያመላክታል፡፡
የእውቅና ፍቃድ እና እድሳት አሰጣጥ ስርዓትን በማሻሻል የትምህርት እና ስልጠና አግባብነትና ጥራትን
ማረጋገጥ በተመለከተ
በዚሁ መሰረት፡-
በድህረ ምረቃ መርሀ-ግብር 21 ካምፓሶች በ40 የትምህርት መስክ እውቅና ያገኙ ሲሆን 70 ካምፓሶች
በ136 የትምህርት መስክ እውቅና ማግኘት ያልቻሉ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል 9 ካምፓሶች በ17 የትምህርት
መስክ እድሳት ያገኙ ሲሆን 19 ካምፓሶች በ45 የትምህርት መስክ እድሳት አላገኙም፡፡
58
በቅድመ ምረቃ በመደበኛ መርሀ-ግብር 76 ካምፓሶች በ166 የትምህርት መስክ እውቅና ያገኙ ሲሆን 60
ካምፓሶች በ141 የትምህርት መስክ እውቅና ማግኘት አልቻሉም፡፡ በሌላ በኩል 54 ካምፓሶች በ114
የትምህርት መስክ እድሳት ያገኙ ሲሆን 6 ካምፓሶች በ15 የትምህርት መስክ እድሳት ያላገኙ ናቸው፡፡
በቅድመ ምረቃ በርቀት መርሀ-ግብር በ118 የትምህርት መስክ 35 ካምፓሶች እውቅና ያገኙ ሲሆን በ141
የትምህርት መስክ 60 ካምፓሶች እውቅና ያላገኙ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል በ128 የትምህርት መስክ 99
ካምፓሶች እድሳት ያገኙ ሲሆን በ24 የትምህርት መስክ 10 ካምፓሶች እድሳት ያላገኙ ናቸው፡፡
በድንበር ተሻጋሪ መርሀ-ግብር እድሳት ያገኙ በካምፓስ 1 የትምህርት መስክ 1 እንዲሁም እውቅና
ያላገኘ 1 በካምፓስ 7 የትምህርት መስክ እንዲሁም አንድ ተቋም በበይነ መረብ በድንበር ተሻጋሪ በ3
የተለያዩ ፕሮግራሞች እውቅና ጠይቆ ተገምግሞ ሪፖርት በዝግጅት ሂደት ላይ ነው።
በድህረምረቃ መርሀግብር 2 ካምፓሶች በ2 የትምህርት መስክ እውቅና ያገኙ ሲሆን 3 ካምፓሶች በ14
የትምህርት መስክ እውቅና ያላገኙ ናቸው፡፡ በቅድመምረቃ መርሀግብር 2 ካምፓሶች በ8 የትምህርት
መስኮች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡
በሌላ በኩል የደረጃ ስያሜ (Status) ስርዓትን በማጠናከር ለ9 ተቋማት የደረጃ ስያሜ ለመስጠት ታቅዶ
ለ2 (22.22%) ለመስጠት ተችሏል፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ24 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በእውቅና ፈቃድና እድሳት ሪፖርት ላይ 24
ቅሬታዎች የቀረቡ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 3 ቅሬታዎች አግባብነት ያላቸው ሆነው ስለተገኙ ውጤት ላይ
ለውጥ ያስከትሉ ሲሆን ለሌሎቹ ቅሬታዎች ደግሞ እንደ አግባብነታቸው ተገቢው ምላሽ ተሰቷቸዋል።
የህግ አገልግሎት ስርዓት ለማሻሻል በተሰራው ስራ ባለስልጣኑ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ
በተሰጠው ስልጣንና ተግባር መሰረት ስራውን ሲያከናውን እንዲሁም በድጋፋዊ ክትትል የመስክ ምልከታ
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ህግና መመሪያ ተከትለው መስራታቸውን መቆጣጠር የህግ ማስከበር ስራን
ለመስራት የተቋማቱ ብዛት ከባለስልጣኑ አደረጃጀት ጋር ሲነፃፀር እጅግ ብዙ ቢሆኑም ባለስልጣኑ
ከአገልግሎት ጋር በተገናኘ በሚሰጣቸው አስተዳደራዊ ውሳኔዎች በተገልጋዮች በሚነሱ አቤቱታዎች
ጉዳያቸውን ለተለያዩ መስሪያ ቤቶችና መደበኛ ፍ/ቤቶች ሲያቀርቡ ምላሽ በመስጠትና ቀርቦ በመከራከር
የህግ ማስከበሩን ስራ በተገቢው ጥረትና ትጋት እያከናወነ ይገኛል፡፡ በዚሁ መሰረት፡-
59
ተማሪዎች ዕውቅና ወዳላቸው ወደ ሌሎች ተቋማት ተዛውረው ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ አስተዳደራዊ
ውሳኔ ቢሰጠውም ኮሌጁ በመስሪያ ቤታችን ላይ ባቀረበው የፍትሐብሔር ክስ ጉዳዩ በአዳማ ልዮ ዞን
ከፍተኛ ፍ/ቤትና በኦሮሚያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ክርክሩ ሲታይ ቆይቶ ውሳኔ የተሰጠ ቢሆንም በውሳኔው ላይ
ቅሬታ ባለስልጣኑ ስላለው በይግባኝ ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰበር አቤቱታ አቅርበው ጉዳዩ ወደ
ሰበር አያቀርብም ተብሎ በመወሰኑ አቤቱታ በባለስልጣኑ ከተወከሉ ጠበቆችን ጋር በመሆን ጉዳዩን ወደ
ህገመንግስት አጣሪ ኮሚሽን ለማቅረብ የአቤቱታ ይዘት እየቀረበ ይገኛል፡፡
60
ክፍል ሰባት
የትምህርት ዘርፍ ኤችአይ ቪ መከላከልን በተመለከተ፡- የትምህርት ሴክተሩ ከችግሩ በመታደግ በኩል
ያለውን ጉልህ ሚና በመረዳት ሃገራዊ የሴክተሩ መድረኮቻችን ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ቢሮዎች ጋር
የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ስምምነት ተደርሶ ወደ ትግበራ ገብተናል። በፖሊሲና ፕሮግራሞች፣
ሜይንስትሪሚንግ፤ በክትትልና ግምገማ ዙሪያ ለክልል የትምህርት ተቋማትና ለ78 የከፍተኛና መካከለኛ
አመራሮች የምክክር መድረክ የኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ አስተባባሪዎች የአሰልጣኞች
ስልጠና ተሰጥቷል። በተጨማሪም በትምህርት ዘርፍ የኤችአይቪ/ኤድስ እና ስነ-ተዋልዶ ፕሮግራሞችን
በተገቢው ሁኔታ ለመተግበር የሚያስችል ተናባቢ ተቋማዊ አደረጃጀት በሁሉም ደረጃ መዋቅር የማጠናከር
ስራ ተሰርቷል።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን በተመለከተ፡- ሀገራችን አለምአቀፉ ማህበረሰብ በአረንጓዴ ኦኮኖሚ ልማት
ዙሪያ የገባችው ቃል መሰረት ለመተግበር እንዲቻል በ2014ዓ.ም የትምህርት ተቋማት በዕቅድ ውስጥ
እንዲካተት የማድረግ፣ አመራሩ ትኩረት እንዲሰጠው እንዲሁም ተከታታይነት ያለው ክትትልና ድጋፍ
ተደርጓል። በዚህም መሰረት ተቋማት በትግበራ ሂደት በአካባቢያቸው ካሉ የመስተዳድር አካላት ጋር
በመተባበር ስራዎችን ሰርተዋል።
ስደተኞችና አካባቢ ማህበረስብ የትምህርት አቅርቦት በተመለከተ፡- ሀገራችን ኢትዩጵያ ለአለም አቀፉ
ማህበረሰብ ቃል ከገባቻቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ በጎረቤት አካባቢዎች ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች
ምክንያት ለሚሰደዱ ህብረተሰቦች በማስተናገድ የማህበራዊ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ማድረግ ነው። በዚህም
61
መሰረት በ2014ዓ.ም በ88 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች 132,563 (ወ 79,170 ሴ 53,393)፣ በ18 የሁለተኛ
ደረጃ ት/ቤቶች በድምሩ 11,665 (ወ 5,961 ሴ 1,704) እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
በአጠቃላይ 3,130 ያህል ስደተኞችን በስኮላርሺፕ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
ሀብት ማፈላለግ በተመለከተ፡- በቀጣይ አምስት ዓመታት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተደራሽነትን
ለማሻሻል ለ1459 አዲስ የሚገነቡ፤ ለ485 እድሳት (Re-innovation} እና ለ1,328 ደረጃቸውን ለማሳደግ
የ118.9 ቢሊዮን ብር ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ሀብት የማፈላለግ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም
የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል ከሚሰሩ ተግባራት አንድ አካል የሆነው በቀጣይ ሁለት
ዓመታት ውስጥ የሚገነባ የ50 አዳሪ (Boarding schools) ለመገንባት የሚያስችል የ10.7 ቢሊዮን ብር
የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ሀብት ማፈላለግ ስራ የተሰራ ሲሆን እካሁን 3
ቢሊዮን ብር የማሰባሰብ ስራ የተሰራ ሲሆን በቀጣይ ሀብት የማሰባሰቡ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
በቦሰተን (Boston) ከሚኖሩ ኢትዮጵያን በሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ለሚገነባ አንድ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት
ቤት ግንባታ የ25,547,709.77 ሚሊዮን ብር የግንባታ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል በመቅረጽ ወደ ተግባር
ለመግባት የሚያስችሉ ስራዎችን ለማከናወን ከዲያስፖራዎቹ ጋር የውይይት ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡
በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ በተገኘ ድጋፍ በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ የሚገነባ
አራት (4) ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች ለመገንባት የሚያስችል የ155,727,985.32 ሚሊዮን ብር
የትምህርት ቤቶች ግንባታ ፕሮፖዛል በማዘጋጀት እና ከዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ቦርድ ጋር ተደጋጋሚ
ውይይቶችን በማድረግ በዲያስፖራ ቦርድ በኩል ፕሮፖዛሉና የስምምነት ሰነዱ ተቀባይነት በማግኘቱ
ስምምነቱን በመፈራረም ወደ ስራ የተገባ ሲሆን ግንባታውን ለማስጀመር የሚያስችል የግንባታ ዲዛይን
በኢትዮጵያ አርኪቴክቶች ማህበር በኩል በመሰራት ላይ ሲሆን ክልሎች የቦታ መረጣ በማድረግ ለይተው
እንዲልኩ በመደረግ ላይ ነው፡፡
62
አርባ ሺህ ብር) የተሰራጨ ሲሆን በዚሁ መሰረት 90 በመቶ እና በላይ ለሚሆኑ ትምህርት ቤቶች በወቅቱ
ማድረስ በመቻሉ 13 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ያሳካን ሲሆን ሪፖርቱ ለሦስተኛ ወገን ለማረጋገጥ
ለኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት እንዲገመገም ተልኳል፡፡
በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ለተጎዱ ትምህርት ቤቶች ግብዓት ማሟያ የሚውል በጀት ብር
217,000,000 (ሁለት መቶ አስራ ሰባት ሚሊዮን ብር) ለክልሎች ተልኳል፡፡
የሰብዓዊና ቁሳዊ ሀብት አጠቃቀም በተመለከተ፡- የትምህርት ሴክተርን ስትራቴጂክና ዓመታዊ ዕቅድን
ለማስፈፀም ብቁና ተነሳሽነት ያለው አመራርና ፈጻሚ ማሰማራት ይጠይቃል። በዚህም መሰረት በ2014
ዓ.ም ሁለቱን የቀድሞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን በአደረጃጀት፣ በሰው ሀይል፣ በዕቅድ እና በሀብት ደረጃ
የማዋሀድ ወደ ስራ እንዲገባ ተደርጓል።
ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ የተመደበውን በጀት የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው የወጪ ቅነሳ መመሪያ መሰረት
ለመጠቀም ጥረት ተደርጓል። በሌላ በኩል በአዲሱ የሚኒስቴር መስረያቤቱ አደረጃጀት መሰረት ፍትሀዊና
ክህሎትን መሰረት ያደረገ ምደባ ከፍተኛ አመራሩ በጥብቅ ዲስፕሊን በመምራት ምደባ ተደርጓል። ይህም
በቀጣይ ሚኒስቴር መስሪያቤታችን ያቀዳቸውን የሪፎርም ስራዎች በተሻለ አቅም እና የአፈፃፀም ደረጃ
ለመፈፀም የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል።
63
ክፍል ስምንት
የሀገር ውስጥ ተከፋይ ሂሳብ ብር 52,258,836.61 ሲሆን ተሰብሳቢ ሂሳብ ደግሞ 164,543,304,838.56
መታየቱ በኦዲት የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል። በተጨማሪም የውጭ ሀገር ተሰብሳቢ ሂሳብ በተለያዩ ሀገራት
ሲታይ ከ2008 እስከ 2011 በጀት ዓመት ሲታይ በህንድ 407,496፤ በቱርክ 442,206.88 እና ደቡብ
አፍሪካ 5,375,664 በአጠቃላይ የውጭ ሀገር ተሰብሳቢ ሂሳቦች ጠቅላላ ድምሩ $6,225,366.88 የወጪ
ማስረጃ እና ገንዘቡ ስለመድረሱ የተረጋገጠበት ማስረጃ አለመኖሩ በኦዲት ተረጋግጧል።
የግዥ አፈፃፀም ሂደትን በመንግስት የተፈቀዱ የግዥ ዘዴዎች መፈፀማቸውን እና የተሽከርካሪ አያያዝ እና
የነዳጅና ቅባት አጠቃቀም ሂደትን በኦዲት የማረጋገጥ ስራ ተሰርቷል፡፡
በዚህም መሰረት በዋና መስሪያ ቤት በወጪ፣ በተሰብሳቢ፣ በተከፋይና በጀት ሂሳቦች እንዲሁም በግዥና
በሰራተኞች ቅጥር ላይ የተሰጡ አስተያየቶች ላይ ምላሽ ከመሰጠቱም በላይ የማስተካከያ እርምጃና እርምጃ
የሚወሰድበትን መርሀ ግብር በዝርዝር በማዘጋጀትና በመተግበር ላይ እንገኛለን።
በሌላ በኩል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኦዲት ግኝትን ምንም ነቀፌታ የሌለባቸው (Unqualified audit
opinion) ከ0 ወደ 20% ለማድረስ ታቅዶ 2.12% ላይ ማድረስ ተችሏል።እንዲሁም በኦዲት ግኝት ከጥቂት
ጉድለቶች በስተቀር በአጠቃሊይ አጥጋቢ ሆነው የተገኙ (Except…for) ተቋማትን ከ20% ወደ 80%
ለማድረስ ታቅዶ፣ 34.78% ማድረስ ተችሏል፡፡
64
ክፍል ዘጠኝ
NB፡- በፕሮግራም ማስፈፀሚያ ሰነዱ መሠረት የPforR እና የIPF ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የሚቀርበው ሩብ ዓመቱ
ባለቀ በ90 እና በ60 ቀናት ውስጥ እንደቅደምተከተላቸው በመሆኑ የተቀመጠው የበጀት አፈፃፀም የPforR የ6 ወር
እና የIPF የ9 ወር አጠቃቀም ነው፡፡
65
ክፍል አስር
የፈተና ደህንነት ጉዳይ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተወሳሰበ መምጣት፡፡ የ2013/14 12ኛ ክፍል ብሔራዊ
ፈተና እጅግ ፈታኝ ነበር፡፡ በወረዳ ደረጃ በነበረው የፈተና ስርጭት ወቅት ሽፍቶች አድፍጠው
በፈተናና በፈተና አስፈጻሚዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸው፣ ከፈተና መልስ ላይም ባልተለመደ ሁኔታ
መንገድ ላይ ጥቃት መፈጸሙና የፈተና አጃቢዎች የህይወት መስዋዕትነት መክፈላቸው፣ በእያንዳንዱ
የፈተና ቀን የፈተና መልስ በማህበራዊ ሚዲያ መለቀቅና ለቁጥጥር እጅግ ፈታኝ መሆን እና
የእርማት ችግር ያጋጠመ መሆኑ በጉልህ የተስተዋሉ ችግሮች ናቸው፡፡
በትግራይ ክልል በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩ
ተማሪዎች እንዲሁም በክረምት መርሃ ግብር ለደረጃ ማሻሻያ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ መምህራን
እና የትምህርት ቤት አመራሮች በመፈናቀላቸው ምክንያት ትምህርታቸውን ለማስቀጠል ፈታኝ
ሁኔታዎች ማጋጠማቸው፤
በሚ/ር መ/ቤቱ በተደረገው አዲስ የመዋቅር ጥናት የሰራተኛ ምደባ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ
ወደስራ አለመግባት፤
66
ለችግሮቹ የተቀመጡ መፍትሄዎች
በጸጥታ ችግር፣ በጎርፍና በድርቅ ምክንያት በትምህርት ተቋማት ላይ የደረሱ ጉዳቶች በመለየት
በፌዴራልና በክልሎች የሚከናወኑ ተግባራት በጋራ ውይይት ተለይተው ወደ ተግባር ተገብቷል፤
በችግሮቹ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች ባሉበት አካባቢ ትምህርት እንዲቀጥሉ ጥረት
ተደርጓል፣
የአጠቃላይ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ያለበትን የፈተና አስተዳደር ችግር ለመቅረፍ የ2014ዓ.ም
ፈተናው በሃገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ስምምነት ላይ ተደርሷል፤
በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩ መደበኛ ተማሪዎችን እና የክረምት መርሃ
ግብር ሰልጣኝ መምህራን ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ በመመደብ የተቋረጠ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ
ተደርጓል፣
በውጪ ሀገር ለሚማሩ ተማሪዎች የውጪ ምንዛሪ ከመንግስት በማፈላለግ መላክ፤
በሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን እየተካሄደ ያለውን የሰራተኛ ድልድል የበላይ አመራሩ የቅርብ ክትትል
ተደርጎበት እየተጠናቀቀ ይገኛል፤
በሥርዓተ ትምህርት ላይ እየተደረገ ያለውን ሪፎርም በማስቀጠል የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ
ደረጃ ትምህርት ወደ ሙሉ ትግበራ ማስገባት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት (9-10ኛ) ሙከራ ትግበራ
ማካሄድ እና በቴክኖሎጂ ማስደገፍ፣
የልዩ አዳሪ፣ አዳሪ እና የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን ግንባታና እድሳት ለማካሄድ ከውጪ እና ከሃገር
ውስጥ ሃብት በማፈላለግ ግንባታ ማካሄድ፣
በግጭትና በድርቅ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ውጪ የሆኑ ህጸናትና ወጣቶች (ልዩ ፍላጎትን
ጨምሮ) ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ በመሥራት፣ የትምህርት ቤት ምገባን ማጠናከር
የ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን ደህንነቱን በጠበቀ ሁኔታ ለመስጠት
የሚያስችል ሥራ መስራት፣
67
በጦርነት ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ስራ የተመለሱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ቤተ-ሙከራዎች፣ ቤተ-
መጽሐፍትን እና ወርክ-ሾፖችን በተሟላ ሁኔታ በማደራጀት ወደ ቀድመ ቁመናቸው መመለስ፣
የታሪክ ትምህርት የጋራ ኮርስን ጨምሮ በትምህርት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ጥናት የቀረቡ ምክረ
ሀሳቦችን ከማስፈጸም አቅም ጋር በተመጣጠነ ሁኔታ ወደ ስራ ማስገባት፤
68
አባሪ 1፡- የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPIS) አፈጻጸም ማትሪክስ)
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
ግብ2፡- የሀብት በትምህርትና ሥልጠና ዘርፉ የመንግስት በጀትድርሻ በመቶኛ 68.86 69.70 DNA
72.30
ምንጭና
በትምህርትና ስልጠና ዘርፉ የሚታየውን በመቶኛ 19.74 18.48 DNA
አጠቃቀም የሀብትጉድለት ለመሙላት የአጋር ድርጅቶች ድርሻ 14.7
69
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
70
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
ግብ 5፡- የትምህርት አመራሩን ለደረጃው የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በቁጥር 8759 32.68%
15000 26800 44,500
የሚመጥን ቤት መምህራን
እና የመምህራን አቅርቦት፣
የትምህርት
ስነምግባር፣ ተነሳሽነትና ዝግጅት ያላቸው የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ በቁጥር 70330 47.91%
102,315 146806 324,770
ትምህርት ቤት መምህራን
ብቃትን ማሳደግ፣
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በቁጥር 16196 69.6%
11,635 23269 58,171
መምህራን
71
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
በሁሉም ደረጃ የሙያ ፍቃድ ምዘና መምህራንና በመቶኛ 0 35% 29% 82.8% 58.5
ያለፉና እውቅና ያላቸው
መምህራንና የትምህርት ቤት የት/ት ቤት በመቶኛ 72.5%
0 40% 29% 70
አመራሮች አመራር
72
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
የአንደኛና በመቶኛ 0 6
0.02% 0.3 10.8
የመካከለኛ ደረጃ
73
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
ንጥር የ1ኛ ክፍል ቅበላ ወ በመቶኛ 76.2 97.28 97.3 100.2 98.45
74
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
ጥቅል ከ1ኛ-6ኛ ክፍል አማራጭን ጨምሮ ሴ 97.3 107 101.2 97.78 104
75
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
76
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
ከ9-12ኛ ክፍል የስርአተ ጾታ ምጥጥን በምጥጥን 0.92 0.88 0.97 108.99 0.91
የመጀመሪያ ደረጃ የሴት ር/መምህራን ድርሻ በመቶኛ 6.8 14.26 12. 84.15 18.85
የሁለተኛ ደረጃ የሴት ር/መምህራን ድርሻ በመቶኛ 4.0 8.62 7 81.21 11.35
የመጀመሪያ ደረጃ የሴት ሱፐርቫይሮች ድርሻ በመቶኛ 4.7 13.88 7 50.43 27.2
የሁለተኛ ደረጃ የሴት ሱፐርቫይሮች ድርሻ በመቶኛ 11.9 5.6 7.5 133.93 14
የሴት የት/ት ባለሙያዎች ድርሻ በመቶኛ 0 8.8 79.5
22.66 22
የቅድመ 1ኛ ደረጃ የልዩ ፍላጎት ትም/ት ወ በመቶኛ 1.9 5.2 1 19.23 10.75
77
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
78
የ2014 አፈጻጸም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም የ2017ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም (ESDP-VI) ኢላማ
በመቶኛ
79
አባሪ 2:- የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPIS) አፈጻጸም ማትሪክስ)
ግብ1፡- ያልተማከለ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሴቶች አመራሮች ተሳትፎ በመቶኛ 20 25 25 100% 34
የትምህርት አመራርና
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተለዩ የልቀት ማዕከላት በቁጥር 3 45 5 11% 45
አስተዳደርን
ማጠናከር፣ ከትኩረት መስካቸው አንጻር አቅማቸው የጎለበተ ተቋማት በቁጥር 45 46 46 100 45
በስራ ላይ ስልጠና አመራርነት ክህሎትና ስብዕና ብስለት ስልጠና በመቶኛ 20 100 100 100 55
የወሰዱ
80
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በኦዲት ግኝት ከጥቂት ጉድለቶች በስተቀር በአጠቃሊይ አጥጋቢ በመቶኛ 0 80 36.2 45 35
ሆነው የተገኙ (Except….for) ተቋማት
የተዘረጋ የጥቅል በጀት ስርዓት በቁጥር 0 1 0.6 60% -
የተዘጋጀ መመሪያ
81
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በቲዎሪናበተግባር ተመጣጥነው የተዘጋጁ ፕሮግራሞች በመቶኛ 75 80 77 96 100
በኢንደስትሪ ፍላጎት መሰረት የተከለሰ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሮግራሞች በቁጥር 305 328 324 99 397
82
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በተቋማት የተዘረጋ የውስጥ ጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት በመቶኛ 100 100 100 100 100
በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች የመጀመሪያ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ በመቶኛ 97.8:1.8:0.4 96.8:2.6:0.6 97.8:1.8:0.4 78 91፡8፡2
ተማሪዎች ስብጥር
ለደረጃ ስያሜ የተገመገሙና ፍቃድ ያገኙ ተቋማት በመቶኛ - 100 - 0 100
ግብ 6. የትምህርት መምህር ተማሪ ጥምርታ የመጀመሪያ ዲግሪ መንግስት በመቶኛ 1:18 1፡19 1፡18 99 1፡17
83
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
አመራሩንእና መምህር ተማሪ ጥምርታ ድህረ-ምረቃ (የመንግስት) በመቶኛ 1:12 1፡17 1፡12 96 1፡5
የመምህራን
የረዳት ምሩቅ ɪ߹ ረዳት ምሩቅ ɪɪ߹ እና የረዳት ሌክቸረር ብዛት በመቶኛ 22 20 21 95 17
አቅርቦትና ብቃትን
የሌክቸረር ብዛት በመቶኛ 66 65 65 100 61
ማሳደግ
የረዳት ፕሮፌሰር߹ የተባባሪ ፕሮፌሰርና የሙሉ ፕሮፌሰር ምጣኔ በመቶኛ 13 15 15 100 23
በትምህርት ደረጃ (ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ) የመምህራን ምጥጥን በመቶኛ 17:68:15 14፡70፡16 14፡70፡16 100 06፡76፡19
በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች የሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ መምህራን በመቶኛ 16:63:21 11፡65፡24 11:65:24 100 70፡30
ስብጥር በመቶኛ
በአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች የሁለተኛ፣ ሶስተኛ ድግሪና በመቶኛ 18:69:13 15፡71፡14 15፡71፡14 100 80፡20
ኢንዱስትሪ መምህራን ስብጥር
በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች የሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ መምህራን በመቶኛ 21:76:3 24፡67፡9 24፡67፡9 100 15፡70፡15
ስብጥር
በዲጂታል ክህሎትና ቴክኖሎጂ ሰልጥነዉ ሰርቲፋይድ የሆኑ በመቶኛ 5 15 - - 90
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን
በሀገር ውስጥ ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት እድል የተሰጣቸው በቁጥር 5,404 7,017 6842 98 6000
መምህራን
በሀገር ውስጥ የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እድል የተሰጣቸው በቁጥር 298 262 190 73 7670
መምህራን
በውጭ ሀገር ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት እድል የተሰጣቸው በቁጥር 3,967 5,270 3747 71 150
መምህራን
በውጭ ሀገር የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት እድል የተሰጣቸው በቁጥር 1,251 1,110 1071 96 600
መምህራን
የስራ ላይ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና የተሳተፉ መምህራን በመቶኛ 62 70 68 97 100
84
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በተቋማት ትብብር ሀገር በቀል የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርት በቁጥር - 5,000 - - 5000
ፕሮግራም መምህራን ተሳትፎ
በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመምህር በመቶኛ - 1፡18 - - 1፡17
ተማሪ ጥምርታ
በምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በድህረ- ምረቃ ፕሮግራም የመምህር በመቶኛ - 1፡12 - - 1፡5
ተማሪ ጥምርታ
በአፕላይድ ዩኒቨርሲቲዎች በቅድመ-ምረቃ ፐሮግራም የመምህር በመቶኛ
- 1፡18 - - 1፡17
ተማሪ ጥምርታ
ግብ 7- የአገር በቀል የተዘጋጀ የሀገር በቀል እውቀት የሚለማበትና የሚመራበት ፖሊሲ በቁጥር 0 1 1 100 -
እውቀትና ማህበረሰብ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተደራጁ የሀገር በቀል እውቀቶች በቁጥር
35 - - 75
አቀፍ ሥራዎችን ማዕከላት
ማጠናከር
በአገር በቀል እውቀት ላይ የተካሄዱ ምርምሮች በቁጥር 120 290 200 69 1
85
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በዩኒቨርስቲዎች የሳይንስ ቴክኖሎጂ ምህንድስናና ሂሳብ በቁጥር
0 100 56 56 1
ፕሮግራሞች የተሳተፉ ሴቶች ሰልጣኞች
ግብ 8.የትምህርት በስታንዳርዱ መሰረት አዲስ የመማሪያ ክፍሎች የገነቡ የከፍተኛ በመቶኛ 10 51 35 0.686 40
ተቋማትን ለመማር ትምህርት ተቋማት
ማስተማር፣ ምርምርና በስታንዳርዱ መሰረት የመማሪያ ክፍሎችን ያደሱ የከፍተኛ በቁጥር - 10 10 100 10
ፈጠራ ሥራ ምቹ ትምህርት ተቋማት
የትኩረት መስክና ተልኮ መሠረት አድርገው ስታንዳርድ የዲጂታል በመቶኛ - 10 - - 55
ማድረግ ቤተ-መፃሕፍት የገነቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
የትኩረት መስክና ተልኮ መሠረት አድርገው ስታንዳርድ የቤተ- በመቶኛ - 10 - - 100
ሙከራዎች የገነቡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
የተዘጋጁ 10 ስታንዳርዶችን አጸድቆ ለ45 ዩኒቨርሲቲዎች ተደራሽ በቁጥር በ10 ዓመቱ
10 10 100 -
ማድረግና በዚሁ መሰረት እንዲሰሩ ማድረግ ዕቀድ
ግብ 9- የትምህርት የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች አመታዊ የቅበላ እድገት በመቶኛ 14.2 15.3 15 100 18
ተደራሽነትን ማሳደግ
በግል የተከፈቱ አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች በቁጥር 288 - - - 363
86
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በመንግስትና በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጠቅላላ የቅድመ በቁጥር
1,522,615 1,527,629 100.3 100.3 1,972,798
ምረቃ ተማሪዎች ቅበላ (በመደበኛና መደበኛ ባልሆነ)፣
የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ቅድመ ምረቃ ጥቅል ተሳትፎ በቁጥር 520,053 700‚000 642,067 92 1,424,798
ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎች ተሳትፎ በመቶኛ 0.8 0.9 0.8 88.9 1.5
87
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎችና አካባቢዎች የቅድመ ምረቃ በመቶኛ
75.4 95 75.4 79.37 92
ተማሪዎች ማጠናቀቅ ምጣኔ
የተፈጠሩና የተሻሻሉ የማህበረሰብ ችርግ ፈቺ ምርምሮችና በቁጥር 1467 1600 1,909 119 8,500
ቴክኖሎጂዎች
በመሰረታዊ ምርምር ላይ የተካሄዱ ጥናቶች በቁጥር 2,490 2,500 1,316 53 3,000
ጥራታቸው የጎላና እውቅና ያገኙ የሀገር ውስጥ ምርምር ጆርናሎች በቁጥር 16 31 31 100 50
እውቅና ባለው ዓለም አቀፍ አሳታሚ ላይ (Journal Indexing data በቁጥር የለም 1 3 300 40
ግብ 11. የምርምርና base) የተካተቱ የሀገር ውስጥ ጆርናሎች
ፈጠራ ስራዎችን በፈጠራና ምርምር ውጤት ዙሪያ የተመዘገቡ አዕምሮዓዊ ንብረቶች በቁጥር 3 7 24 343 3
ማካሄድ (patents)
ያደገ ሀገራዊ የምርምርና ልማት በጀት (GERD/GDP) በመቶኛ - 0.4 - - 0.7
88
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
በተቋማት የተዋቀሩ እና የተጠናከሩ የምርምር ስነ ምግባር ቦርዶች በቁጥር 25 40 7 18 1
በሀገር በቀል እውቀት፤ በስቴም፤ በምርምርና ምርምር ስነምግባር በቁጥር - 1000 236 24 1
3000
ላይ ተከነማወኑ ስልጠናዎች
ግብ12፡- የተቋማት የተቋቋሙ የኢንኩቤሽን ማዕከላት በቁጥር 20 35 21 60 45
ትስስርና ቴክኖሎጂ በትስስር የተተገበሩ ችግር-ፈቺ ምርምሮች በመቶኛ 105 100 75 75 250
ሽግግርን መሻሻል
በትስስር የተተገበሩ ትምህርቶች በመቶኛ 0 25 0 0 75
89
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
የማህበረሰቡን ፍላጎት ያገናዘበና ያቀፈ የቴክኖሎጂ ሽግግር በመቶኛ
5 15 - - 30
ስራዎች
ከአጠቃላይ መምህራን ውስጥ በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ ተሳተፉ በመቶኛ 7,500 12,000 6,530 54 25000
መምህራን
በማህበረሰብ አገልግሎት የተሳተፉ ሴት መምህራን በመቶኛ 6 12 8.8 73 20
90
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
የመማር ማስተማር ስራዉን በቴክኖሎጂ ለማገዝ በመማሪያ በመቶኛ 5 40 20 50% 80
ክፍሎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን (ስማርት) ያሰፉና ያሻሻሉ
ግብ 13፡ የትምህርት
መሰረተ ልማት፣ ለዲጂታል
ተቋማት ኮንተነት ማልማት አገልግሎት የሚዉል ስታንዳርዱን ቁጥር
2 3 3 100% 20
ፋሲሊቲንና የጠበቀ የዲጂታል ስቴዲዮ ተግባራዊ ያደረጉና የዲጂታል ኮንቴንት
የዲጂታል ክህሎት ማበልጸግ የቻሉ ተቋማት
ቴክኖሎጂ የመማር ማስተማር ስራዉን በልዩ ሁኔታ ለማገዝ የሚስችል በቁጥር
አጠቃቀምን 30 50 50 100% 15
የትምህርት ዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰለጠኑ የከፍተኛ ትምህርትና
ማሻሻል፤
ስልጠና ተቋማት የአይሲቲ ባለሙያዎች
91
የ2014 አፈጻጸም የ2017ዓ.ም
የ2013 ዓ.ም የ2014 ዓ.ም
ስትራቴጂክ ግብ የቁልፍ ውጤት አመላካቾች መለኪያ (ESDP-VI)
መነሻ ዒላማ ክንውን አፈጻጸም
ኢላማ
በመቶኛ
ከፍተኛ ፍጥነትና ተመጣጣኝ የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚ በመቶኛ - 15 - - 70
የሆኑ የከፍተኛ ተቋማት
በስታንዳርድ መሰረት የዉስጥ ICT መሰረተ ልማቶችን (ግሪንና በመቶኛ
5 40 20 50% 90
ስማርት ካምፓስ ኔትዎርክ) ያሟሉ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና
ተቋማት
ከኢተርኔት ጋር በኔትዎክ የተሳሰሩ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና በመቶኛ - 15 - - 70
ተቋማት
ለሁሉንም ከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት አገልግሎት በመቶኛ 30 40 40 100 100
ለመስጠት አቅሙ ያደገ የኢተርኔት ዳታ ማእከልና ኮር ኔትዎርክ
ለትምህርት፣ ምርምርና ቴክኖሎጂ ማመንጫና ማሳደጊያ በማእከል በመቶኛ
አገልግሎት ከሚሰጥ የሃይ ፐርፎርማንስ ኮምፒዉቲንግ (HPC) 12 15 15 100% 70
መሰረተ ልማት ተጠቃሚ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና
ተቋማት
የምርምር ጥራትና አስተዳደርን ለማሳለጥ በማእከል ከሚሰጡ በመቶኛ 15 40 40 100% 100
የዲጂታል አገልግሎቶች ተጠቃሚ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርትና
በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰለጠኑ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና
ስልጠና ተቋማት በመቶኛ 30 50 50 100% 100
ተቋማት የአይሲቲ ባለሙያዎች
92
ማጠቃለያ
በበጀት ዓመቱ ዕቅድ ትግበራ ሂደት የአሰራር ስርዓቱን የሚያቀላጥፉ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣
ማዕቀፎችና ስትራቴጂዎች ተዘጋጅተዋል፡፡ በተጨማሪም በሁሉም ደረጃ በትምህርት ተደራሽነት፣
ፍትሀዊነት፣ ጥራት እና ተገቢነት አንጻር ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል።እንዲሁም
በምርምርና በማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ የሚያሻሽሉ ውጤት
የተመዘገበባቸው ስራዎች በበጀት ዓመቱ ተከናውነዋል፡፡
93