You are on page 1of 12

/ / //

በደ ብ ብ ህ ክ መንግስት ትምህርት ቢሮ

አርባምንጭ ትምህርት ኮሌጅ

የ 2015 ዓ.ም የተማሪዎች መመገቢያ አደራሽ ግንባታ ፕሮጀክት ዕቅድ፤


ፕሮጀክት ኮድ: አምትኮ 011

ግንቦት 2014 ዓም

አርባምንጭ

ማውጫ

ርዕስ ገጽ
2

የፕሮጀክቱ ስም-------------------------------------------------------------------------------------------------3
የፕሮጀክቱ ባለቤት---------------------------------------------------------------------------------------------3
የፕሮጀክቱ ሁኔታ---------------------------------------------------------------------------------------------3
የፕሮጀክቱ አስፈላጊነት--------------------------------------------------------------------------------------5
ፕሮጀክቱ የሚገኝበት ቦታ -----------------------------------------------------------------------------------6
ለፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገው ጠቅላላ በጀት-----------------------------------------------6
የፕሮጀክቱ ቆይታ ጊዜ----------------------------------------------------------------------------------------7
-የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች-------------------------------------------------------------------------------------7
የፕሮጀክቱ ዓላማ፣ አስፈላጊነትና የሴክተሩን የልማት ፖሊሲ ለማስፈጸም የሚኖረው ድርሻ:-------------------------9
የፕሮጀክቱ ግቦችና በፕሮጀክቱ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት-------------------------------------10

የፕሮጀክቱ ፋይናንሺያል ዝርዝር ዕቅድ ማጠቃለያ---------------------------------------------------13

የክትትልና ግምገማ ስርዓት፣ታሳቢዎችና ስጋቶች -----------------------------------------------------13

የፕሮጀክቱ አጠቃላይ መረጃ(Executive summery)


I. የፕሮጀክቱ ስም፡
ይህ ፕሮጀክት በደ/ብ/ብ/ሕ/ክልል መንግስት በአርባምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ውስጥ የተማሪዎች
መመገቢያ አደራሽ ችግር ለመቅረፍ ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን የፕሮጀክቱም ስያሜ “የተማሪዎች ምግብ
አደራሽ ግንባታ ፕሮጀክት” ተብሎ የሚጠራ ይሆናል::

II. የፕሮጀክቱ ባለቤት፡

የዚህ ፕሮጀክት ባለቤት በደ/ብ/ብ/ሕ/ክልል መንግስት የአርባ ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ሲሆን የተለያዩ
ባለድርሻ አካላትም በፕሮጀክቱ አተገባበር ላይ የጋራ ሚና ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል::

III. የፕሮጀክቱ ሁኔታ፡-

የአርባ ምንጭ ትም/ኮሌጅ በሀገሪቱ ብሎም በክልሉ ውስጥ እያደገ የመጣውን የአንደኛ ደረጃ መምህራን ፍላጎት
ለማሟላት ታስቦ በ 1980 ዓ.ም የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋም ሆኖ የተመሠረተ ሲሆን በ 1996 ዓ.ም የክልሉ
መንግስት በአዋጅ ቁጥር 74/1996 በአንቀጽ 37 እና አስፈጻሚና ፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን
በወጣው አዋጅ ቁጥር 64/1995 አንቀጽ 56 ንዑስ አንቀጽ 1 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ወደ መምህራን ትምህርት
ኮሌጅ ያደገ ተቋም ነዉ::
3

• ኮሌጁ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት 34


ዓመታት በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከ 1980 ዓ.ም
እስከ 1998 ዓ.ም ድረስ በሰርቲፊኬት ፕርግራም
በመደበኛ፤ በክረምትና በማታ ወንድ 8084፤ ሴት
3860፤ በድምሩ 11‚944 እጩ መምህራንን
አሰልጥኖ በመምህርነት ሙያ በማሰማራቱ
ለሀገሪቱ በትምህርት ዘርፍ አኩሪ ሚና
ተጫዉቷል፡፡ በአጠቃላይ ኮሌጁ ከተመሠረተበት 1980 እስከ 2014 ዓ.ም ድረስ በመደበኛ፤ በማታ፤ በሣምንት
መጨረሻ፤ በክረምትና በአጫጭር ሥልጠናዎች 58,974 (ሃምሳ ስምንት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ አራት) በ 2014 ዓ.ም
ተመራቂ ተማሪዎችን ጨምሮ 59,635/ሃምሳ ዘጠኝ ሺህ ስድስት መቶ ሰላሳ አምስት/የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
መምህራን፤ ርዕሰ-መምህራን፤ ምክትል ርዕሰ-መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች ማለትም በመምህርነት ሙያ እና
በትምህርት አመራር መስክ በሰርቲፍኬትና በድፕሎማ አሰልጥኖ ያስመረቀ ሲሆን በክልሉ ብሎም በአጎራባች ዞኖች
ልዩ ወረዳዎች እና አርብቶ አደር አካባቢ ማህበረሰቦች ያለውን ከፍተኛ የሆነ የአንደኛ ደረጃ መምህራንን እጥረት
ከመቅረፍ አኳያ እንዲሁም መንግስት የትምህርት ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በሚያደርገው ሁለንተናዊ
ጥረት ላይ የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ በማበርከት አገራዊና ክልላዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ያለ አንጋፋ ተቋም ነው::
ይሁን እንጂ በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ጥናት ውጤት መሠረት ተማሪዎች ከኮሌጅ ግቢ ውጭ
መኖራቸው በተለይም ሴት ሰልጣኞች ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ካላቸው ቤተሰቦች የሚመጡ ተማሪዎች እና ልዩ ድጋፍ
ከሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በሚመጡ ተማሪዎች በመሆናቸው የሚያስከትለውን ውስብስብ ችግሮች
ከማስወገድ አኳያ ኮሌጁ ቅጥር ግቢ ውስጥ ማደሪያና የምግብ አገልግሎት ተሰጥቷቸው እንዲማሩ በመወሰኑ
ምክንያት ይህ የተማሪዎች ምግብ አደራሽ ፕሮጀክት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል::

በመሆኑም ይህ ፕሮጀክት ከላይ የተጠቀሱ ችግር በመቅረፍ ሠልጣኞች ውጤታማ ሆነው እንዲዘልቁ ለማስቻል

ወሳኝነቱ አጠያይቅ ጉዳይ ባለመሆኑ ኮሌጁ ራዕውንና ተልዕኮውን በብቃት ለመፈፀም እንዲያስችለው ወሳኝ ግብዓት

ከመሆኑ አኳያ የክልሉ መንግስትም ፕሮጀክቱን በጥንቃቄ ገምግሞ ምላሽ ይሰጣል የሚል እምነት አለን::

በተጨማሪም የተማሪዎችን በኮሌጁ ግቢ የመኝታና የምግብ አገልግሎት ያገኛሉ ተብሎ ሲታሰብ የተማሪዎች
የሚመገቡበትን የምግብ አደራሽ አብሮ የሚታሰብ በመሆኑ ለተማሪዎች መመገቢያ አገልግሎት በተገቢውን
ማስተናገድ የሚችል አደራሽ በጊዜ ወቅቱን ጠብቆ መገንባት የተማሪዎች ዘርፈ ብዙ ችግሮችን በመፍታት በፍኖቴ
ካርታው ከተያዙ ችግሮች ውስጥ የሚካተት ስለሆነ ኮሌጁም ለዚህ አገልግሎት የሚሆን ህንፃ ባለመኖሩ የዚህ ፕሮጀክት
ግንባታ ወሳኝ ነው::

በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ይህ ፕሮጀክት ኮሌጁ ራዕውንና ተልዕኮውን በብቃት ለመፈፀም እንዲያስችለው ወሳኝ ግብዓት
ከመሆኑ አኳያ የክልሉ መንግስትም ፕሮጀክቱን በጥንቃቄ ገምግሞ ተግባራዊ ያደርጋል የሚል ጽኑ እምነት አለን::
4

IV. የፕሮጀክቱ አስፈላጊነት :-

 ከጤና አኳያ
ንፁህ ለመመገቢያ የተመቸ የምግብ አደራሽ መኖር ለአንድ ከፍተኛ ትምህርት ተ n ም የመማር
ማስተማሩን ሂደትን ጤናማና ሰላማዊ አከባቢ እንዲሆን ከማድረግ በተጨማሪ ንጽህናው የተጠበቀ
ምግብ አደራሽ መኖር ተማሪዎች ለተለያዩ በሽታዎች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ለማድረግ እጅግ በጣም
አስፈላጊ ነው:: በመሆኑም በአሁኑ ጊዜ በአለማችንና በአገራችን የተከሰተውን የኮሮና ወረርሽኝ ሆነ
ሌሎች ምግብና ውሃ ወለድ በሽታዎች በመከላከል የመማር ማስትማሩን ስራ ለማድከድ አስፈላጊ
ነው::
 ከመማር ማስተማር አኳያ
ተማሪዎች ሙሉ ጊዜያቸውን ለመማር ማስተማሩ ስራ በማዋል በትኩረት መማር ሲገባቸው የምግብ
መመገቢያ አደራሽ ያለመኖር ምግብ ላይዘጋጅ ይችላል በዚህ መነሻ ምግብ ፍለጋ ከግቢ ይወጣሉ በዛው
ምክንያት የትምህርት ጊዜ ብክነት ብሎም የተሟላ መስተንግዶ በማጣት ፍለጋ ላልተፈለገ ችግሮች
ልጋለጡ ይችላሉ:: ይህም በአንድ በኩል ለትም/ት ማዋል የሚገባቸውን ጊዜ ያባክናሉ:: በሌላ በኩል
ደግሞ የተሟላ ምግብ ላይገኝ በሚችልበት ወቅት ጥያቄ በማንሳት የመማር ማስተማሩ ሥራ ላይ ጫና
ያሳድራሉ በዚህና በመሰል ምክንያት ፕሮጀክቱ አስፈላጊ ነው::
 ከፖሊሲ ለውጥ አንጻር
ቀደም ስል ተማሪዎች ወርሃዊ የኪስ ገንዘብ እየተከፈላቸው ከግቢ ውጭ የሚኖሩ ሲሆን በአዲሱ የትምህርትና
ስልጠና ፍኖተ ካርታ መሠረት በኮሌጁ ግቢ ውስጥ እየኖሩ የምግብና የመኝታ አገልግሎትን ከግቢ እያገኙ
ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተወሰነ በመሆኑ ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የተማሪዎች ምግብ አደራሽ
ወሳኝ ነው::
በተጨማሪም ተ n ሙ ከዚህ ቀደም የተፈቀዱለት ውስን ካፒታል ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት
በአግባቡ ተጠናቀው አገልግሎ በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ተ n ሙ ፕሮጀክቶችን የማጠናቀቅ ከፍተኛ ልምድ
እና ተሞክሮ ያለው ነው:: ይህም የኮሌጁ አመራር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት
እና ለፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከፍተኛ የሆነ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም ድጋፍ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ልምድ
ያለው ነው:: በመሆኑም ይህ ፕሮጀክት ብጸድቅና ተግባራዊ ብደረግ ጊዜና ውስን የሆነውን ሀብት በአግባቡ
በመጠቀም ለማስፈጸም የሚያስችል በቂ አቅም አለው::

V. ፕሮጀክቱ የሚገኝበት ቦታ :-

ይህ ፕሮጀክት በደ/ብ/ብ/ሕ/ክልል መንግስት በአ/ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኝ ነው::
የአ/ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ በጋሞ ዞን አ/ምንጭ ከተማ የሚገኝ ሲሆን ከአገሪቱ መዲና አዲስ አበባ በስተ ደቡብ አቅጣጫ
5

505 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከክልሉ መቀመጫ ሐዋሳ ከተማ ደግሞ በ 275 ኪሎ ሜትር በስተደቡብ ምዕራብ
ሆኖ በምስራቅ ኩልፎ ወንዝ በደቡብ የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ በሰሜን ወደ አርባ ምንጭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ
የሚውስደው አስፋልት መንገድ እና በምዕራብ ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ የሚወስደው መንገድ የሚያዋስኑትና ግቢው የቦታ
ስፋትም 119,312.5 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ተቋም ነው::ተቋሙም ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የተፈጥሮ ቁሳቁሶች
በከተማ አቅራቢያ የሚገኝ መሆኑ ሌላው እድል ነው፡፡በሌላ በኩል ተቋሙ ለመማር ማስተማር ሂደት ምቹ የሆነ አካባቢ ያለው
ስሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ከኮሌጁ ጋር መልካም መስተጋብር ያለው እና ለትምህርትና ስልጠና ሂደት የራሱን
አስተዋጽኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር በሀገር ደረጃ የሰላም ተምሳሌት አከባቢ በመሆኑ ተማሪዎች ያለምንም ችግር
ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙበት ተቋም ነው::በተጨማሪም ኮሌጁ በሚገኝበት አከባቢ የሚገኙ አምስት ዞኖችና
ሶስት ልዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች የመምህር እጥረት የሚታይባቸው ከመሆናቸው በተጨማሪ አርብቶ
አደር አካባቢ የሚመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ትምህርትና ስልጠና የሚያገኙበት ተቋም ነው፡፡

Vl) ለፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገው ጠቅላላ በጀት-

ለዚህ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚሆን በጀት የወቅቱን ተለዋዋጭ የገበያ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ
በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ዝርዝር የአዋጭነት ጥናት በባለሙያዎች የሚዘጋጅ ሆኖ
አጠቃላይ ፕሮጀክቱ እስከ 50 ሚሊዮን ብር ሊደርስ እንደሚችል የሚገመት ሲሆን በ 2015 ዓ.ም
ተጠናቅቆ አገልግሎት ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል::

VII) የ 2015 በጀት ፍላጎት፡-

ከላይ ተራ ቁጥር 6 ላይ እንደተመለከተው ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ጠቅላላ በጀት 50 ሚሊየን ብር


ሊደርስ እንደሚችል ታሳቢ ቢደረግም በ 2015 ዓም በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀቱን ማለትም 50
ሚሊዮን ብር በጀት ተፈቅዶ ፕሮጀክቱን የማስጀመርና የማጠናቀቅ ስራ ለማከናወን ታቅዷል::

VIII) የበጀት ምንጭ፡-


ይህ ፕሮጀክት የህዝብ እና የመንግስት ከመሆኑ አኳያ በዋናነት የበጀት ምንጩ ከክልሉ መንግስት
በሚገኝ የካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ በጀት የሚሸፈን ይሆናል::
IX) የፕሮጀክቱ ቆይታ ጊዜ:-
ይህ ፕሮጀክት በአንድ ዓመት /2015 ዓ.ም/ ይጠናቀቃል::
X) የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች:

የዚህ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ማህበረሰብ ክፍሎች ሲሆኑ ተጠቃሚዎቹን በጥቅሉ በሁለት ከፍሎ
ማየት ይቻላል:: ይህም
6

 ቀጥተኛ ተጠቃሚ /Direct Beneficiary/፡-ሰልጣኝ /ተማሪ/ ø ኮሌጁ አመራር


 ተዘዋዋሪ ተጠቃሚ /Indirect Beneficiary/፡- መንግስት ø ¾˜œqp# ማህበረሰብ ø

ሰንጠረዝ 1 : የፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ትንተና

ተ/ቁ የተጠቃሚ አይነት የተጠቃሚው የሚያገኘው ጥቅም ምርመራ


ዓይነት
1 ሰልጣኝ /ተማሪ/ ቀጥተኛ ጤንነቱ የተጠበቀ እና ውጤታማ በመሆን ተገቢውን
የአካዳሚክ ዕውቀት ø የሙያ ችሎታና መልካም ዜጋ
የተላበሰ ብቁ ሰልጣኝ እንዲሆን ማድረግ
2 ተnም ቀጥተኛ የንፁህና ለመመገቢያ ምቹ የሆነ የምግብ አደራሽ ተደራሽ
በማድረግ የተማሪዎች ጥያቄ ምላሽ መስጠት
3 አመራር ቀጥተኛ በምግብ አደራሽ ችግር በኩል የሚነሱ የመልካም አስተዳደር
ችግሮችን ለመፍታት
4 መንግስት ተዘዋዋሪ በአስፈላጊ ግብዓት በማሟላት ፖሊሲና ስትራቴጂ
ለማሳካት ይረዳል ø
5 የአከባቢ ተዘዋዋሪ በግንባታው ወቅት የሥራ እድል ማግኘት
ማህበረሰብ
1. መግቢያ( Back Ground)
ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት እውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ኃይል መሰረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በሣይንስና
ቴክኖሎጂ በልጽገው በሀገራቸው ልማትን በማምጣት የሕዝባቸውን ተጠቃሚነት ያጐለበቱ ሀገራት ልምድም የሚያሳየው ይህንኑ
ነው፡፡ ለዚህም ትምህርትና ሥልጠና ብቁና በቂ የሰው ኃይል ከማፍራት አንፃር ከፍተኛ ድርሻ ስላለው ሀገራችንን በሚቀጥሉት
የብልፅግና ዓመታት ራዕይዋን ለማሳከት በተለያዩ ደረጃዎችና የሙያ መስኮች በዕውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት
የተገነባ ብቁና በቂ የሰው ሀይል ማፍራት መሠረታዊ መሆኑን በመረዳት ለትምህርት ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ
ይገኛል።
በመሆኑም ባለፉት አመታት የትምህርት ተደራሽነትን፣ ፍትሐዊነትን፣ አግባብነትና ጥራትን ለማጐልበት ሰፊ ሥራዎች ሲሰሩ
ቆይተዋል፡፡ የአገሪቱን የትምህርት ፖሊሲ መሠረት ያደረጉ የትምህርት ስታንደርዶች፣ ስትራቴጂዎች፣ የትምህርት ዘርፍ ልማት
ዕቅድ (ESDP I to V) እና የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዶች (GTP I&II) በማዘጋጀት ተግባራዊ ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡
የትምህርትና ሥልጠና ተቋማትን በማስፋፋት የትምህርት ተደራሽነትና ፍትሐዊነትን በማጐልበት በኩል በርካታ
ሥራዎች የተሰሩ ሲሆን አበረታች ውጤቶችም ተመዝግበዋል፡፡
ትምህርት ኮሌጆችም ብቃትና ጥራት ያላቸውን መምህራን ከማፍራት አኳያ ሚናቸውን በመለየት በትጋት
ተወጥተዋል*ኮሌጃችን ብቃትና ጥራት ያላቸውን መምህራን ከማፍራት አኳያ የራሱን ኃላፊነትና ተዕልኮውን
በሚገባ ተወጥቷል፡፡
ይሁን እንጂ ኮሌጁ ባሳለፋቸው 34 ዓመታት ውስጥ ደረጃው አድጎ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ሆኖ ስራውን
ስጀምር የመምህራን ማሰልጠኛነት የተማሪዎች ማደሪያ የነበሩ ህንፃዎችን ጥገናና እድሳት በማድረግ ወደ ሥራ
የገባ ሲሆን እንደሌሎች ኮሌጆች ለደረጃ የሚመጥን መሰረተ ልማት ተሟልተው በተገነቡበት ተቋም አይደለም፡፡
7

በመሆኑም ኮሌጁን በተለየ መልኩ በመሰረት ልማት በኩል ጎድቷል፡፡ነገር ግን በባለፉት ዓመታት ቢሆን ኮሌጁን
በሚለውጥ መልኩ መሰረተ ልማቶች ማስፋፊያ በጀት ተመድቦ በልዩ ሁኔታ መታየት ሲገባው ይህ አልተደረገም፡፡
በመሆኑም ይህ በእንድዳለ ኮሌጁ የመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ ግብር መምህራንን እንዲያሰልጥን በአዋጅ የተደገፈ
ኃላፊነት የተሰጠ ሲሆን ይህንን ተልዕኮ በመወጣት የሀገራዊ እራይ ለማሳካት የተጓደሉ መሰረተ ልማቶችን
በማሟላት የትምህርትና ሥልጠናውን ውጤታማነት ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑና ለኮሌጁ ቁልፍ መሰረተ ልማቶች
አንዱ የሆነውን የተማሪዎች መመገቢያ አደራሽ መገንባት አስፈልጓል፡፡
ስሆነም የመማር ማስተማሩን ስራ ውጤታማ ለማድረግና ብቁ ዜጋ ለማፍራት ለማሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ
ግብዓቶችን በኮሌጁ ውስጥ ማሟላት እንዳለበት የሚታመን ሲሆን በዚሁ መነሻ ይህ ችግር ለመቅረፍ ታስቦ
የተማሪዎች ምግብ አደራሽ ግንባታ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ተዘጋጅቷል፡፡

2. የፕሮጀክቱ ዓላማ፣ አስፈላጊነትና የሴክተሩንና የልማት ፖሊሲ ለማስፈጸም የሚኖረው ድርሻ


2.1 ዓላማ ፡
የዚህ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ዋነኛ አላማ በ 2015 ዓ.ም የበጀት ዓመት ጀምሮ ተማሪዎች ምግብ
የሚመገቡበት አደራሽ ፕሮጀክት በኮሌጁ ውስጥ መገንባት ሲሆን የሚከተሉት ዝርዝር አላማዎች
ይኖሩታል::
 ደረጃውና ንፁህና የተጠበቀ የተማሪዎች ምግብ መመገቢያ አደራሽ ግንባታ በማካሄድ
በተማሪዎች ሊነሳ የሚችለውን ጥያቄ መመለስ፣
 የኮሌጁን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም ማሳደግ
 እንደተ n ም የማህበረሰብ አገልግሎት ተልዕኮውን በብቃት መወጣት
2.2. ሰንጠረዝ .2:- የሚከናወኑ ተግባራት

ተ.ቁ ዝርዝር ተግባር መለኪያ ብዛት ለስራው


የሚያስፈልግ ወጪ
(በብር)
2 የፕሮጀክት ዲዛይን ዝግጅት በቁጥር 1
3 ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረግ ውይይት በወር 1
4 የዕቅድ ዝግጅት በቁጥር 1
5 ክትትል ግምገማና ግብረ መልስ በወር 1
6 በጀት ማስፈቀድና በሚመለከተው አካል ስረጋገጥ ክፍያ በቁጥር 4
መፈጸም
7 የሳይት ዝግጅት ስራ በቁጥር 1
8 ግንባታው ስጠናቀቅ ርክክብ መፈጸምና ለታለመለት አላማ በቁጥር 1
መዋሉን ማረጋገጥ
9 የኤሌክትሪክና የውሃ መስመር ዝርጋታ ማከናወን በቁጥር 1
8

2.3. የሴክተሩን የልማት ፖሊሲ ለማስፈጸም የሚኖረው ድርሻ:-


መንግስት በቀጣይ አስር አመታት ለማሳካት ከያዛቸው የብልጽግና ዕቅዶች መካከል ጥራትና ብቃት
ያለው ትምህርትና ስልጠና መስጠት ዋነኛው ሲሆን ይህንን ዕቅድ ለማሳካት የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የሚጫዎቱት ሚና ከፍተኛ ነው:: በመሆኑም ከላይ የታሰበውን ዕቅድ ማሳካት የሚቻለው
ተቋማት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሠረት አገልግሎት በሚሰጡ ህንፃዎችና በትምህርት
ግብዓቶች ስደራጁ ነው:: በዚህ መሠረት የዚህ የተማሪዎች ምግብ አደራሽ ፕሮጀክት ተግባራዊ
መሆን መንግስት ቀጣይ ተማሪዎችን ወደ ግቢ ለመመለስ የወሰነውን ውሳኔ ከማስፈጸም አንጻር
የማይተካ ሚና ይኖረዋል::

2.4. የፕሮጀክቱ አፈፃፀም፡


ይህ ፕሮጀክት በ 2015 የበጀት ዓመት ተጀምሮ የሚጠናቀቅ ሲሆን በበጀት ተደግፎና ጸድቆ ሲመጣ
ዝርዝር የአፈጻጸም ዕቅድ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ባሳተፈ መልኩ ተዘጋጅቶ የሚተገበር
ይሆናል::
3. የፕሮጀክቱ ግቦችና የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

3.1. በፕሮጀክቱ የሚጠበቁ ዋና ዋና ግቦች


 ንፁህናው እና ደረጃው የጠበቀ የተማሪዎች የምግብ አደራሽ በመገንባት የኮሌጁ አቅም
ማሳደግ፣
 በትምህርትና ሥልጠናው ሥራ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ማስቀረት፣

3.2. በፕሮጀክቱ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት(Implementation)

 የፕሮጀክት ዲዛይን ዝግጅት

 ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረግ ውይይት

 የዕቅድ ዝግጅት

 ክትትል ግምገማና ግብረ መልስ

 በጀት ማስፈቀድና በሚመለከተው አካል ስረጋገጥ ክፍያ መፈጸም

 የሳይት ዝግጅት ስራ

 ግንባታው ስጠናቀቅ ርክክብ መፈጸምና ለታለመለት አላማ መዋሉን ማረጋገጥ

 የኤሌክትሪክና የውሃ መስመር ዝርጋታ ማከናወን


9

4. የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ዓመት ስራ ማስኬያጃ ወጪዎች

ተ/ቁ ተግባራት የሚያስፈልገው ወጪ ምርመራ

1 የሳይት ዝግጅት ስራ 12,000


2 የዲዛይን ስራ ማሰራት 18,000
3 ጨረታ ሂደት 5,000
4 ቅድመ ክፍያ መፈጸም 10,000,000
5 በሚመለከተው አካላት ተዘጋጅቶ በሚመጣ 48,965,000
ሰርተፍኬት መሰረት የሚፈጸም
ክፍያግንባታው ስጠናቀቅ ርክብክብ
መፈፀም፣
50,000,000
10

ፕሮጀክቱ የሚከናወንበት የኮሌጁ አመራር አካላት

የኮሌጁ ዲን

ም/ዲንና መም/ትም/ባለ ዳይ/ት ም/ዲንና ትም/መሣ/ስ/የቴክ/ስ/ዳይ/ት

የል/ዕቅድና/የበ/ዝግ/ዳይ/ት እንስፔ/የውስጥ ኦዲ/ዳይ/ት የግ/ፋ/ን/አስ/ዳይ/ት


11

ሥነ-ምግባር/ፀ/ሙስና ሥራ ክፍል ሥርዓተ-ፃታ ፀረ-ኤድስና/ኤች/አይ-ቭ ሜን/ግ

5. የፕሮጀክቱ ፋይናንሺያል ዝርዝር ዕቅድ ማጠቃለያ

ፕሮጀክቱ የሚከናወንበት ጊዜና

የወጪ አርዕስት መለያ ቁጥር 011 የገንዘብ መጠን ግምት ድምር


የመጀመሪያ
ዓመት
የሳይት ዝግጅት ዲዛይንና ግንባታ
10,035,000
የማስጀመር ስራ
ግንባታና የማጠቃሊያ ስራ 48,965,000
ድምር 50,000,000

6. ታሳቢዎች(Assumption)
 ሠልጣኞች ከ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ማደሪያ ተሰጥቷቸው ግቢ መኖር የሚጀምሩ መሆናቸው ፣
 በትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታው ላይ እንደተመለከተው ትምህርት ኮሌጁ በድግሪ መርሃ
ግብር እንዲያሰለጥኑ መደረጉ፣
 ኮሌጁ የተሻለ የፕሮጀክት አፈጻጸም ክትትል ልምድ ያለው መሆኑ፣
 የአካባቢው ማህበረሰብና አስተዳደር ጋር ከኮሌጁ ጤናማ የሥራ ግንኙነት በመኖሩ ፕሮጀክቱን
በባለቤትነት ስሜት የሚደግፈው/የሚያየው /መሆኑ፣
 ከፋብርካ ዕቃዎች ውጪ ያሉ የግንባታ እቃዎች ቦሌጁ አከባቢ በቅርበት መኖሩ፣
7. ስጋቶች(Risk)
 የግንባታ ቁሳቁሶች የዋጋ ንረት መኖር፣
 የመንግስት የበጀት አቅም ውስንነት፣
 የቁሳቁስ አቅርቦት እጥረት መኖር፣
 በተቋራጮች በኩል የሚስተዋል የቁርጠኝነት እና የአፈጻጸም ውስንነት፣
8. የክትትልና ግምገማ ስርዓት(Monitoring & Evaluation)
የኮንስትራክሽን ዘርፍ በሀገራችን በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ያለ እና ውስብስብ ሲሆን የተለያዩ ብልሹ አሰራሮችና
ማጭበርበሮች ያሉበት እንደሆነ ይታመናል:: በመሆኑም ተ n ሙ ይህንን ጉዳይ ታሳቢ በማድረግ ከፍተኛ የሆነና
ስልታዊ የክትትልና ግምገማ ስርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ የሚያደርግ ይሆናል:: በተጨማሪም በግምገማው ሂደት
12

የሚገኙ ክፍተቶችን እያረመና አስፈላጊውን የእርምት እርምጃዎች እየወሰደ ዝርዝር እቅድ ተዘጋጅተው
በጥንቃቄ የሚመራ ይሆናል::

9. የፕሮጀክቱ ቀጣይነት (Sustainability)


ፕሮጀክቱ በተከታታ ወደ ኮሌጁ ለሚገቡ ሰልጣኝ /ተማሪዎች/ የምግብ መመገቢያ አደራሽ በመሆን
ከማገልገሉ ባሻገር ለተማሪዎች የተለያዩ መዝናኛና መሰብሰቢያ አገልግሎት በመስጠት ያለው ድርሻ
ከፍተኛ መሆኑ፣

You might also like