Professional Documents
Culture Documents
AEPC 202 Module)
AEPC 202 Module)
Epsy 242
ለቅድመ መደበኛ መምህራን ስልጠና የተዘጋጀ ሞጁዩል
ለመጀመሪያ ደረጃ መምህራን ለማሰልጠኛነት የተዘጃጀ ሞጁዩል
i
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
መግቢያ.........................................................................................................................................................1
የትምህርቱ አላማዎች.....................................................................................................................................1
ክፍለ ትምህርት አንድ፡.....................................................................................................................................3
1. የትምህርት ምዘና እና ግምገማ መሰረታዊ ጽንሰ-ሃሳቦች...................................................................................3
1.1 የምዘና፤ልኬታና ግምገማ መሠረታዊ ጽንሰ-ሃሳቦች....................................................................................3
1.1.1. ምዘና፣ ልኬታ እና ግምገማ..............................................................................................................3
1.1.2. የድንገተኛ ሙከራ፣ ሙከራና ፈተና ንጽጽር.......................................................................................6
1.2 መማርን የመመዘንና የመገምገም ዓላማዎች.............................................................................................7
1.3 የመማር ምዘናና ግምገማ ትግበራ መርሆዎች/ Principles........................................................................11
1.4 የምዘና አይነቶች.................................................................................................................................12
1.4.1 ተከታታይ ምዘና (Continuous Assessment)..................................................................................12
1.4.2. የብቃት ምዘና (Authentic Assessment)......................................................................................14
1.5 ሂደታዊ ተከታታይ ምዘና የአተገባበር ችግሮች.................................................................................................15
የምዕራፉ ማጠቃለያ.................................................................................................................................16
የክፍለ ትምህርት አንድ ማጠቃለያ ጥያቄዎች...............................................................................................16
ክፍለ ትምፍርት ሁለት...................................................................................................................................17
2. የቅድመ መደበኛ ትምህርት ምዘና ባህርያት...................................................................................................17
2.1 ተከታታይ ምዘና..................................................................................................................................17
2.1.1. ሂደታዊ ተከታታይ ምዘና (ሂተም)...................................................................................................17
2.1.2 አጠቃላይ ተከታታይ ምዘና (አተም)................................................................................................18
2.1.3 የተከታታይ ምዘና አተገባበር መርሆዎች (ጠቃሚ ነጥቦች).................................................................19
የክፍለ ትምህርት ሁለት ማጠቃለያ ጥያቄዎች..............................................................................................23
ቀጥሎ በቀረቡት የመወያያ ጥያቄዎች ላይ ለ 20 ደቂቃ ያህል ውይይት በማድረግ ለክፍሉ ተማሪዎች በማብራራት
አቅርቡ....................................................................................................................................................23
ክፍለ ትምህርት ሶስት....................................................................................................................................24
3. የቅድመ መደበኛ ትምህርት ምዘና ስልቶች....................................................................................................24
3.1 መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ የምዘና ስልቶች..................................................................................................24
3.2. የብቃት ምዘና ስልቶች (Tools of authentic assessment).....................................................................25
3.3 ግለ ምዘናና የአቻ ምዘና........................................................................................................................26
3.3.1. ግለ-ምዘና/ Self-Assessment.......................................................................................................26
ተከታታይ ምዘና በተገቢ መልኩ ተግባራዊ ሳይደረግ ሁሉም ህጻናት -ተማሪዎች እኩል የመማር እድል እንዲኖራቸው ማድረግ
አይቻልም፡፡ ስለሆነም ይህ ኮርስ የትምህርት ግቦቻችንን ዳር ለማድረስ እና የተሟላ ስብዕና የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት ተከታታይ
ምዘና የሚጫወተውን ሚና በጥልቀት የምንረዳበትና ይሆናል፡፡
የትምህርቱ አላማዎች
ትምህርቱን በሚገባ ተምረው ካጠናቀቁ በኋላ ሰልጣኞች፡
የህጻናትን መማር ምዘናን የተመለከቱ ንድፈ ሃሳቦችን ይረዳሉ፤
የተከታታይ ምዘና መረጃን በመጠቀም የህጻናት መማር እና መዳበር የተሻለ እንዲሆን ጥረት
ያደርጋሉ፣
ተከታታይ ምዘናን በመጠቀም የህጻናትን የመማርና ሌሎች እገዛ የሚሹ ፍላጎቶችን ይለያሉ፣
የተለያዩ የመማር ፍላጎት እና የመማር ስልት ላላቸዉ ህጻናት ተስማሚ የሆኑ የምዘና ስልቶችን
በመምረጥ ይጠቀማሉ፣
ምዘናን ተከትሎ መማርና የህጻናት መዳበርን በተመለከተ ምን መስራት እንዳለባቸው ይለያሉ፣
የህጻናትን መማርና የልጆች መዳበርን በመመዘን ሂደት መምህራን ሊከተሏቸው የሚገቡ የስነምግር
ደንቦችና መርሆዎችን ይረዳሉ፣
ከህጻናቱ እና ከወላጆቻቸው/ አአሳዳጊዎቻቸው ጋር በምን መንገድ ግንኙነት መፍጠር እንዳለባቸው
ይረዳሉ፣
i
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
ይህ ክፍለ ትምህርት የህጻናትን የመማር ሁኔታ በተመለከተ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም መረጃ ማሰባሰብን፣ በመረጃው
መሰረት የህጻናትን መማር የተመለከቱ ውሣኔዎችን መወሰንና ድጋፍ መስጠትን የተመለከቱ ሃሳቦችን የምናይበት ነው፡፡ ውሳኔዎቹም
የመማር ማስተማሩን ሂደት ማሻሻል፤ የተማሪዎችን መሰረታዊ ክህሎቶች የማሳደግ፣ ወይም ብቃታቸውን ከማረጋገጥ ጋር
የተዛመዱ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ይህ ክፍለ ትምህርት ለትምህርቱ ቁልፍ የሆኑ ዋና ዋና ቃላቶችን ትርጉም፤ የተከታታይ ምዘና ባህሪያትንና
ግቦችን በጥልቀት የምንማርበት ነው፡፡
ተግባር፡- በሚከተለው ምስል የምታዩት የአንድ ተማሪን የባህርይ ለውጥን በተመለከተ በምን በምን የመረጃ መሰብሰቢያ
ዘዴዎች መረጃ እንደምናገኝ ነው፡፡
1. ሌሎች ተጨማሪ የምዘና ስልቶችን ጠቁሙ
2. የተጠቀሱትን እና ተጨማሪ ስልቶችን መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ በማለት ፈርጁ፡፡
በክፍል መምህራን የሚደረግ ምዘና ከላይ በህጻን አልማዝ ላይ እንደተደረገዉ ሁሉ የተለያዩ የምዘና ስልቶችን በመጠቀም
መረጃ መሠብሰብ፣ መረጃዉን መተንተን እና ሁኔታዉን ሊያሻሽል የሚያስችል ዉሳኔ መስጠትን የሚያመለክት ጽንሰ
ሃሳብ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ስለህጻኗ የሰበሰብነዉ መጠናዊና አይነታዊ መረጃ ጉብዝናዋን የሚያመላክት ከሆነ ዉሳኔያችን
አልማዝን ለሌሎች ጓደኞቿ የተማሪ አስተማሪ አድርጎ መመደብ አንዱ ሊሆን ይችላል፡፡
የልኬታ (measurement)፡- ልኬታ ወይም ሰፈራ ምንድነው? ልኬታ የህጻናትን እዕምሮአዊ፣ አመለካከታዊ ክህሎታዊ ለውጥ
የተመለከተ መረጃን በመጠን (በቁጥር) የማግኘት ሂደት ነው፡፡ ልኬታ መረጃን በመጠን ለመግለጽ የተወሰነ የአሰራር ህግን
ይጠቀማል፡፡ ለምሳሌ አንድ ህጻን የሩጫ ፍጥነቱን በተመለከተ በሰከንድ ምን ያህል ሜትር እንደሚሮጥ በመለካት መናገር ወይም
መረጃን መያዝ እንችላለን፡፡ የትምህርቱን አላማዎች መሰረት ተደርጎ የተዘጋጀ ሙከራን ወይም ሌላ የብቃት ምዘናን በመጠቀም
የህጻናትን እውቀት፣ ግንዛቤ ወይም ክህሎት በመጠን ወይም በቁጥር እንገልጻለን፡፡ ይኸውም ህጻኑ/ኗ 10 ከ 10፣ 8 ከ 10
ወይም ሌላ አመጣ/ች በማለት ሊገለጽ ይችላል፡፡ ልኬታ መረጃን ለመግለጽና ስርዓት ለማስያዝ ቁጥርን ይጠቀማል፡፡ ልኬታ
መረጃዎችን በአይነት አይገልጽም፤ በተጨማሪም ግምገማ ማድረግን አያካትትም፡፡ ልኬታ “ምን ያህል ነው?” የሚል ጥያቄን
በመመለስ ላይ ያተኩራል፡፡ ስለሆነም ልኬታን ብቻ በመጠቀም ሁሉንም የተማሪዎች የመማር ባህሪ መመዘን አይቻልም፡፡
የግምገማ (Evaluation)፡- ግምገማ ምንድነው? ግምገማ መረጃ በመሰብሰብ ለተሰበሰበው መረጃ ትርጉም የመስጠት
ሂደት ነው፡፡ ግምገማ ተማሪዎች የተነደፉ የትምህርቱ አላማዎችን በምን ያህል ከግብ እንዳደረሷቸው ለማወቅ የሚደረግ
ስልታዊ አካሄድ ነው፡፡
የአንድ/ዲት ህጻን በመማር የመለወጡ/ጧ ሁኔታ ተገምግሞ ከቀደመ የህጻኑ/ኗ የራስ ስራ ጋር (Self-referenced)፣
በቡድኑ ካሉ ሌሎች ህጻናት ስራ ጋር (Norm-referenced) ወይም ከትምህርቱ አላማ (ከመስፈርቱ) አንጻር (Criterion
referenced) ታይቶ/ ተወዳድሮ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ግምገማ የህጻናትን መማር ብቻ ሳይሆን፣ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የመማር
ማስተማሩን ጥራት፣ ጠቃሚነትና አስፈላጊነት ላይም አስተያየት ለመስጠት ይረዳል፡፡
ሐ
ለ
ሀ
ስልታዊ አካሄድን ይከተላል ማለት ግብታዊ፣ ያለእቅድ የሚደረግ አካሄድን ያስዎግዳል፤ የውጤቱን ትክክለኛነት የሚያዛቡ
ተለዋዋጮችን ይቆጣጠራል፤
የትምህርቱ አላማዎች ቀድመው በታወቁበት ሁኔታ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ አላማዎች ቀድመው ሳይታዎቁ የተማሪዎችን መማርና
የጥራት ደረጃ መለካት አይቻልም፡፡
ግምገማ ‘በምን ያህል ጥራት?’ የሚል ጥያቄን ሲመልስ፣ ልኬታ ደግሞ ‘በምን ያህል መጠን?’ የሚል ጥያቄን ይመልሳል፡፡ ግምገማ
ከልኬታ በተሻለ አጠቃላይና ሁሉን አቀፍ ነው፡፡ ይኸውም መጠናዊ እና አይነታዊ መረጃዎችን በመጠቀም ውጤቱን መግለጽ ብቻ
ሳይሆን መረጃውን በመጠቀም ለባህሪው ትርጓሜ ይሰጣል፣ ያወዳድራል፤ ይፈርጃል፡፡ ይሁንና ግምገማና ልኬታ የማይለያዩ የአንድ
ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች እንደሆኑ መረዳት ይቻላል፡፡ ልኬታ በባህሪው የተለመደ ግልጽ አካሄድን በመከተል መጠናዊ መረጃን
ያሰባስባል፤ ግምገማ በልኬታ የተገኘንና ሌሎች መረጃዎችን በመውሰድ ከትምህርቱ አላማዎች ጋር በማገናዘብ እንደ ሁኔታው
እያመዛዘነ በማየት ለባህሪው ደረጃ ያወጣል፣ ያወዳድራል ወይም በቅደም ተከተል ያስቀምጣል፡፡ ስለዚህ ግምገማ ባህሪን
በቁጥር እና በአይነት ከመግለጽ በተጨማሪ ስለስራዉ ጥራት አስተያየት መስጠትንም (Value judgement) ያካትታል፡፡
የመወያያ ጥያቄ
ሀ. -ልኬታ፣ ግምገማና ምዘና አንዱ በሌላው ስር ሊካተት ከመቻሉ አንጻር አይታችሁ ከምስሉ ከተለያዩ ክፍሎች ጋር አዛምዱ፡፡
ለተግባራችሁ ተገቢ ምክንያት ስጡ
ለ. የሚከተሉት ሃሳቦች እያንዳንዳቸው ምዘናን ወይም ግምገማን የቱን እንደሚያመለክቱ በመለየት መልሳችሁን
ለመምህራችሁ ተናገሩ!
1. በአመዛኙ የመማር- ማስተማርን ሂደት በማሻሻል ላይ ያተኩራል፤
2. ችግሮችን ከመለየት በበለጠ ነገሮችን በመፈረጅ ላይ ያተኩራል፤
3. ወጥ አሰራርን ከመከተል በበለጠ ሁኔታዎችን እንዳመጣጣቸው ለማየት ይረዳል፤
4. ከማፈካከር ይልቅ በህፃናቱ መካከል መተባበር እንዲኖር ያደርጋል፤
5. ህፃናቱ የሚሰማቸውን ስሜት አውጥተው እንዲያንጸባርቁት ያበረታታል
ተግባር፡-ለመሆኑ ከላይ በተሰጠው የሙከራ ትርጓሜ ውስጥ ስልታዊ አካሄድ፣ እና የተማሪዎች ባህሪ የሚሉት ሀረጋት ምን ማለት
እንደሆኑ ተረድታችኋል?
ለ. ድንገተኛ ሙከራ (Quiz)፡ ከሙከራ ወይም ከፈተና የተለየ ሆኖ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ጥያቄዎችን የያዘ ለህጻናት ሳይታሰብ
የሚቀርብ የመማር ማስተማሩን ሂደት ለማሻሻል የሚረዳ መረጃን ለማሰባሰብ ታስቦ ተግባራዊ የሚደረግ ስልት ነው፡፡
ፈተና(Examination)፡ ፈተና ሰፋ ያለ ይዘትን የሚሸፍን በትምህርቱ ወይም በአመቱ መጨረሻ የሚሰጥ በዋናነት አላማው
የተማሪዎችን ውጤት መወሰን የሆነ በዛ ያሉ ጥያቄዎች የያዘ የምዘና ስልት ነዉ፡፡ ከፈተና የሚገኝ መረጃ ተማሪዎችን ከክፍል ወደ
ክፍል ለማዛወር (Promotion)፣ የምስክር ወረቀት (Certification) እና የሙያ ማስረጃ ለመስጠት (Licensing) እንዲሁም
የአንድን ስርዐተ-ትምህርት ዉጤታማነት ለመፈተሸ ያገለግላል፡፡ ፈተና በቅድመ መደበኛ ትምህርት ፕሮግራም ላይ ተግባራዊ ላይደረግ
ይችላል፡፡
የመወያያ ጥያቄ
1. ከዓላማ፣ ከትግበራ ጊዜ፣ ከጥያቄ ብዛትና አይነት አንጻር የድንገተኛ ሙከራን፣ የሙከራንና የፈተና አንድነትና
ልዩነትን አብራሩ፡፡
2. ሙከራ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማሻሻል ወይም የአጠቃላይ ምዘና አካል የሚሆን ዉጤት ለመመዝገብ ታስቦ
ይሰጣል፡፡ ለሁለቱም አላማ የምናዘጋጀዉ የሙከራ ጥያቄ አንድ አይነት ይመስላችኋል? በቡድን በመወያየት
ማብራሪያ አቅርቡ፡፡
በሌላ አባባል የምደባ ምዘና ወደፊት የሚማሩ ተማሪዎችን ለመማር ያላቸውን መነሳሳት፣ ጥንካሬና ድክመት በመለየት
ለነሱ የሚሆናቸውን የትምህርት ፕሮግራም ለይቶ ለማወቅ፤ ወይም ተማሪዎቹን በተለየ ቡድን ውስጥ በመመደብ
የተለየ ድጋፍ ካስፈለገ ለማመቻቸት የሚረዳ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው፡፡
ለማዘዝ በሽታውን ቀድመው መለየት እንዳለባቸው፣ መምህራንም የአንድን ተማሪ/ ህጻን የመማር ወይም የእድገት
ሁኔታ ለማሻሻል የተማሪውን/ዋን ሁኔታ/ ጥንካሬ/ ችግር በትክክል ቀድመው መረዳት ይኖርባቸዋል፡፡
ተግባር፡ የሂደት ምዘና እና የችግር መርማሪ ምዘና ሁለቱም የህጻናቱን የመማር ችግር ያያሉ፡፡ ለመሆኑ ልዩነታቸው ምንድነው?
የመማር ችግር ምርመሪ ምዘና እና ሂደታዊ ምዘና ተመሳሳይነት ያላቸዉ ቢሆንም የችግር መርማሪ ምዘና ከበድ ባሉና ተደጋግመዉ
በሚከሰቱ የተማሪዎች መማር ችግሮች ላይ ያተኮረ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ህጻናት አንድን ጨዋታ ለመጫዎት የአጨዋዎቱ ቅደም ተከተል
ቢጠፋቸው ችግሩ ቀላል የሚባል፤ አጨዋዎቱን ደግሞ በማሳየት እና እየተሳሳቱም ቢሆን ደጋግመው እንዲሞክሩት በማድረግ ሊፈታ
የሚችል ነው፡፡ ይህን አይነት ችግር በወቅቱ ለመለየት ታስቦ ተግባራዊ የሚደረግ ምዘና የሂደት ምዘና ይባላል፡፡
በአንጻሩ በመማር ማስተማር ሂደት የተግባቦት ችግር ያለበትና በቡድን ዉይይቶች ወቅት አዘዉትሮ ገለልተኛ የመሆን
ባህሪ ያለዉ ከሆነ ከባድ የመማር ችግር ነዉ፡፡ የዚህን አይነት ችግሮችና መንስኤዎቻቸውን ለመለየት ተግባራዊ የሚደረግ
ምዘና የመማር ችግር መርማሪ ምዘና ይባልል፡፡
ቀላል የመማር ችግሮች በጊዜዉ ካልታረሙ በሂደት ከባድ የመማር ችግሮችን ያስከትላሉ፡፡ ለምሳሌ ህጻናት
በእድሜአቸው እንዲያነቡ፣ እንዲጽፉ ካልተደረገ፣ ጥራት ያለው ትምህርት ሳያገኙ ከክፍል ክፍል እንዲዛዎሩ ከተደረገ
የኋላ ኋላ የመማር ችግር ያለባቸው፣ ትምህርት አይገባኝም የሚሉ በራሳቸው የማይተማመኑ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
የተማሪዎችን ውጤት ከመወሰን ባሻገር ስርዐተ ትምህርቱንና የስርዓተ ትምህርቱን ማቴሪያሎች ውጤታማነት
እንዲሁም የመምህራንን የማስተማር ብቃት ለመገምገም ግብዓት የሚሆን መረጃ ከማጠቃለያ ምዘና ሊገኝ ይችላል፡፡
የሂደት ምዘና
የማጠቃለያ ምዘና
ተግባር፡- ከላይ ባየናቸው ሁለት ምሳሌዎች መሰረት በቅድመ መደበኛ ትምህርትቤቶች ተግባራዊ ሊደረጉ የሚችሉ
የመማር ችግር መርማሪ ምዘና፣ የቦታ ምደባ ምዘና፣ የሂደትና፣ የማጠቃለያ ምዘና ተግባራዊ ምሳሌዎችን በተጨማሪ በዝርዝር
በመጻፍ እና በማብራራት አቅርቡ፡፡
ፍትሃዊነት: የምዘና ሂደትና መዛኙ ግለሰብ ተመዛኞችንና የእያንዳንዱን ተመዛኝ ጥቅም ከግምት ውስጥ የሚያስገቡ
መሆን አለባቸው፡፡ ስለሆነም ምዘና ፍትሃዊ ነው የምንለው ሁሉም ህጻናት-ተማሪዎች፡
በምዘናው ሂደት እንዲፈጽሙት ስለሚጠበቅባቸውና ስለምዘናው አይነት የጠራ እውቀት ሲኖራቸው፣
የብቃት መመዘኛ መስፈርቶችን ቀድመው ሲረዱ፣
ሁሉም ተማሪውች በእኩል ሁኔታ ሊመዘኑ ሲችሉ፤
ከመማር ዘይቤዎቻቸው (learning style) እና ልዩ ፍላጎቶቻቸው ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲመዘኑ
ሲደረግና፤
የምዘናውን ውጤት ለማሻሻል እንዲችሉ ብቃታቸው እንደገና የሚታይበትና እንዲያሻሽሉ የሚጠይቁበት
እድል ሲሰጣቸው ነው፡፡
ተግባር፡የሚከተሉትን ጥያቄዎች በቡድን በመወያየት ለክፍሉ ተማሪዎች አቅርቡ፤
1. የተማሪዎች ልዩ ፍላጎቶችና የመማር ዘይቤዎች ምንድናቸው? ምዘናውን እንዴት ሊወስኑ
ይችላሉ?
2. ተማሪዎች ለምዘናው በተለያየ ምክንያት ሳይዘጋጁ ቀርተው ቢወድቁባችሁ ምን እርምጃ
ትወስዳላችሁ? ለምን?
ትክክለኛነት (Validity):- የምዘና ትክክለኛነት ምዘናው ሂደት ወይም መሣሪያው እንዲለካ የተፈለገውን ብቃት መለካት
የመቻል ሁኔታን ይመለከታል፡፡ ይህም እውን የሚሆነው፡
ምዘናው ህጻናት-ተማሪዎች በደረጃቸው ከሚጠበቁ ብቃቶች (ዓላማዎች) ጋር የተጣጣመ መሆን
ይኖርበታል፤
ህጻናት,ተማሪዎች የተማሩትን የሸፈነና በቂ ጥያቄዎችን የያዘ መሆን አለበት፤
የሚሰበሰበው መረጃ ከህፃናት እድሜ የሚጠበቅ፣ ለወደፊት እድገታቸው ፋይዳ ያለው መሆን ይኖርበታል፤
ተከታታይ ምዘና ምንድነው? ምዘና አጠቃላይነት ያለው መረጃን ማሰባሰብን፣ መተንተንና መጠቀምን የሚመለከት ተግባር ሲሆን
ተከታታይ ምዘና በተለይ ከመማር ማስተማሩ ሂደት ጋር የተዛመደ፣ ቀጣይነት ያለውና በክፍል ውስጥ ትምህርቱን በሚያቀበው/
በምታቀርበው መምህር/ት ወይም በተማሪዎች ተግባራዊ የሚደረግ የዓላማውን ከግብ የመድረስ ሁኔታ ለመለየትና
የማሻሻያ እርምጃ ለመውሰድ የሚረዳ ተግባር ነው፡፡ ስለሆነም ተከታታይ ምዘና ህጻናት ወደ ስርዓተ ትምህርቱ የመማር
ውጤቶች (ዓላማዎች) የሚያደርጉትን ግስጋሴ በመመዘን ወይም በመለየት በየዕለቱ ተግባራዊ የሚደረግ የመረጃ ማሰባሰብ፣
ማደራጀት፣ መተንተንና ቀጣይ እርምጃን የመውሰድ ሂደት ነው፡፡
ተግባር፡-1. የብቃት ምዘና ሊባሉ የሚችሉ ሌሎች በአይነታቸው የተለያዩ ሶስት ምሳሌዎችን ስጡ
ሀ.__________________________________________________________
ለ.__________________________________________________________
ሐ.__________________________________________________________
2. የብቃት ምዘና ሊባል የማይችል አንድ ምሳሌ ስጡ ______________________
ምዘናው የሚያተኩረው በቀጥታ በህጻናት ተግባር ላይ ነው፡፡ ስለሆነም በህጻናት የተሰሩ ናሙና ስራዎችን
(portfolio-exhibitions)፣ ቀጥታ የመስራት ሙከራዎችን (performances), የሰርቶ ማሳየት ሂደቶችን
(experiments)፣ ገለጻዎችን (presentations)፣ በመምህር/ት ምልከታዎች (observations) ላይ የሚያተኩር
ተግባር ነው፡፡
የብቃት ምዘና የትምህርት አመቱን በሙሉ ቀጣይነት ያለው የምዘና ሂደት ነው፡፡ በዓመት መጨረሻ ላይ
የተማሪዎችን ውጤት ለመወሰን ተግባራዊ የሚደረግ ሙከራ/ ፈተና የብቃት ምዘና አይደለም፡፡
የስርዓተ ትምህርቱ አንድ አካል ነው፡፡ ህጻናት በስርዓተ ትምህርቱ የተቀመጠውን ተግባር መስራት መቻላቸውን
የምንመዝንበት ሂደት ነው፡፡
በተማሪዎች መካከል እና በመምህራንና ተማሪዎች መካከል መተጋገዝ ወይም መረዳዳት እንዲኖር
የሚያበረታታ የምዘና ተግባር ነው፡፡ ስለሆነም ከመምህር ተኮር ምዘና ባሻገር ሃጻናት በምዘና ሂደት እንዲሳተፉ
የሚፈቅድ ተግባር ነው፡፡
ባለሙያዎችና ወላጆች ስለህጻናት የበለጠ እንዲማሩ በማገዝ ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ ስለሆነም የብቃት ምዘና
አንድ ውስን የህጻኑን/ኗን ባህርይ ለመለወጥ ሳይሆን ሁለንተናዊ የህጻናት መዳበርን ለማምጣት የሚረዳ ተግባር
ነው፣፣ ይህ ማለት የህጻኑን/ኗን ማህበራዊ፣ ስሜታዊ፣ አእምሮአዊ፣ አካላዊ እና የቋንቋ የመዳበር ሁኔታን
አጣምሮ ለመመዘን ያስችላል፡፡
ከተቀመጠው መስፈርት አንጻር የአንድን ህጻን ብቃት በመመዘን ላይ ያነጣጥራል፡፡ አንድን ህጻን ከሌላ ጋር
ወይም ሃጻናትን ከሌሎች ህጻናት ጋር በማዎዳደር ላይ አያተኩርም፡፡
ምዘናን የመማር አካል ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ አንድ ህጻን አንድ ነገር ተመልክታና ሪፖርት ጽፋ ለክፍል ተማሪዎች
እንድታቀርብ በማድረግ የተማሪዋን ብቃት መመዘን በእግረ መንገድም እሷ፣ ሌሎችም ከተግባሩ እንዲማሩበት
ይረዳል፡፡ ማለትም የምዘናው ተግባር በቀጥታ ከተማሪዎች የመማር ተግባር ጋር እንዲያያዝ ያደርጋል፣
ህጻናት ቀድመው ከተቀመጡላቸው አማራጮች ውስጥ እንዲመርጡ ሳይሆን አማራጭ መልስ እንዲሰጡ
ያበረታታል፣
ተማሪዎች የላቀ አስተሳሰብ እንዲኖራቸው ይገፋፋል (ማለትም የመተንተን፣ የማደራጀት፣ የመገምገም)፣
የተማሪዎችን ልዩነት ማለትም የመማር ዘይቤ፣ የቋንቋ ችሎታ፣ ባህል፣ ቅድመ እውቀት እና የክፍል ደረጃ
ልዩነቶች ከግንዛቤ ያስገባል፣
በአንድ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ቁጥር መብዛት የተማሪዎችን የመማር ሁኔታ ለይቶ ለማዎቅ እና ለማገዝ የሚደረገውን
ጥረት አስቸጋሪ ያደርገዋል ተብሎ የሚታመን መሆኑ፤
የመምህራን ተከታታይ ምዘናን የመተግበር ክህሎታቸው አናሳ መሆኑ፣
የትምህርት ምዘና ከተገቢው በላይ ሊፈጸም የሚችል መሆኑ፣ ለምሳሌ የሁሉም የትምህርት አይነት መምህራን የቤት
ስራ በተደጋጋሚ ቢሰጡ ተማሪዎች ስራውን በጥራት ለመስራት በቂ ጊዜ ላያገኙ ይችላሉ፡፡ ይኸውም
የተማሪዎችን መማር ከላይ ከላይ የሚያደርግ መሆኑና፣ በወቅቱ አርሞ ተገቢ ግብረመልስ ለመስጠት
ለመምህሩ/ሯ አስቸጋሪ ሊሆን መቻሉ፡፡
የተከታታይ ምዘናን ውጤት መዝግቦ መያዝ አስቸጋሪ ወይም ለብዙ መምህራን ከባድ መሆኑ፣
ብዙ መምህራን ተከታታይ ምዘናን የስራቸው አካል ሳይሆን ከመደበኛ ስራቸው ተጨማሪ የመጣባቸው ጫና እንደሆነ
አድርገው የሚቆጥሩት መሆኑ፤
ተከታታይ ምዘናን ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከሩ ያሉ መምህራንም ቢሆን ትኩረታቸው በትውስታና ግንዛቤ ፈጠራ ላይ
ባተኮሩ የመማር ውጤቶች ላይ ብቻ መወሰኑ፡፡
ተግባር፡- ከላይ የተጠቀሱ የተከታታይ ምዘና የአተገባበር ችግሮች እንዴት ሊቃለሉ እንደሚችሉ በዝርዝር
በመወያየት ለክፍሉ ተማሪዎች በማብራራት አቅርቡ
የምዕራፉ ማጠቃለያ
ልኬታ የህጻናትን እዕምሮአዊ፣ አመለካከታዊ ክህሎታዊ ለውጥ የተመለከተ መረጃን በመጠን (በቁጥር) የመግለጽ ሂደት ነው፡፡
ምዘና ስለህጻናት መዳበር፣ መማር፣ ጤና፣ ባህርይ፣ የትምህርት ግስጋሴ፣ የልዩ ድጋፍ ፍላጎት እና ስኬት የተመለከቱ
መረጃዎችን የማሰባሰብ ሂደት ነው፡፡ የሚሰበሰበው መረጃ አይነታዊ ወይም መጠናዊ ሊሆን ይችላል፡፡ ግምገማ ዓላማን
መለየት፣ መረጃ የመሰብሰብ እና ለባህርይ ትርጉም የመስጠት ወይም የመፈርጅ ሂደት ነው፡፡ ግምገማ አይነታዊ ወይም
መጠናዊ መረጃ ወይም ሁለቱንም በመጠቀም ከዓላው ጋር በማገናዘብ ህጻናት ባሳዩት የባህርይ ለውጥ ላይ ፍረጃ
ማድረግን ያካትታል፡፡ በዚህ የግምገማ ትርጉም መረጃ መሰብሰብ የሚለው ምዘናን ይገልጻል፤ በመሆኑም በግምገማ
ውስጥ ምዘና ሊካተት ይችላል ማለት ነው፡፡ ምዘና መጠናዊ ወይም አይነታዊ መረጃን ያስገኛል ከሚለው ምዘና ውስጥ
ልኬታ መኖሩን ለማየት ያስችላል፡፡ ስለሆነም ልኬታ በምዘና፣ ምዘና በግምገማ ውስጥ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
በምዘና ሂደት መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስልቶችን ልንጠቀም እንችላለን፡፡
መደበኛ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስልቶች የምንላቸው እንደ ፈተና፣ ሙከራ፣ ፕሮጀክት እና
የመሳሰሉት ሲሆኑ፤ መደበኛ ያልሆኑ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስልቶች የምናላቸው እንደ ድንገተኛ
ሙከራ፣ የቃል ጥያቄ፣ ፅብረቃ፣ ምልከታ፣ ግለ-ምዘና፣ የአቻ-ምዘና እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ጥያቄ 1: ተከታታይ ምዘናን ተግባራዊ በማድረግ ሂደት (በምዘና እና ግብረ-መልስ በመስጠት) ተማሪዎችን ማሳተፍ ምን
አይነት ጠቀሜታ አለው?
ጥያቄ 2: የ”ሂተም” መረጃን መዝግቦ መያዝ ለመምህሩ/ሯ እና ተማሪዎች ምን ጠቀሜታ ይኖረዋል?
ጥያቄ 3: በክፍል ስራ እርማት የተገኘ መረጃ የ”ሂተም” ወይም የ”አተም” መረጃ ነው የሚባለው መቼ ነው?
ህጻናት ምን ቅድመ እውቀት እንዳላቸው ሳናረጋግጥ፣ ትምህርቱን እየተከታተሉ መሆኑን ወይም አለመሆኑን መረጃ
ሳይኖረን፣ በመማሩ ሂደት እያጋጠሟቸው ያሉ ችግሮች ሳናውቅ የመማር ማስተማሩን ሂደት ውጤታማ አያደርግም፡፡
የህጻናቱን መማር በተከታታይ መመዘን በራሱ የማስተማርን ሂደት ጥራት እንዲኖረው አያደርግም፡፡
ተከታታይ ምዘና መረጃ መሰብሰብን፣ ለተሰበሰበው መረጃ ትርጉም መስጠትን፣ እና እርምጃ መውሰድን በተከታታይነት የሚያካትት
ተግባር ነው፡፡ እርምጃ (Action) የህጻናትን የምዘና ውጤትና ግምገማን መሰረት በማድረግ ተግባራዊ የሚደረግ ክንውን
ነው፡፡ ይኸውም ግብረ-መልስ መስጠት፣ ማበረታታት፣ ግንዛቤ፣ እውቀትና ችሎታን ማጎልበት፣ ድጋፍ መስጠት፣ ወዘተ
ሊሆን ይችላል፡፡
ለምሳሌ፡- ምዘና የአንድን ሰው ክብደትን እንደመለካት ብናየው፣ ግምገማ ክብደቱ ከሚገባው በላይ/በታች መሆኑና ለጤና አስጊ
መሆኑን/አለመሆኑን እንደመፈረጅ፤ እርምጃ አካላዊ እንቅስቃሴ ወይም ክብደት የሚቀንስ አመጋገብን እንደመጠቀም
ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከእርምጃውም በኋላ እንደገና መረጃ መሰብሰብ ለውጡን መገምገምና የማስተካከያ ወይም ሌላ
እርምጃ መውሰድ እያለ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
ተግባር፡-እናንተ ከትምህርት ዘርፋችሁ አንድ ምሳሌ ተጠቅማችሁ እንዴት የምዘና፣ ግምገማና እርምጃን ተከታታይነትና
ተግባራዊነት ልታሳዩ ትችላላችሁ?
ደብረማርቆስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ/ ስነ-ትምህርት ትምህርት ክፍል
xv
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
ተግባር፡ የሚከተለው ምስል በተከታታይ ምዘና የተማሪዎችን የማብቃት ሂደትና የዳግም ምዘናን
አስፈላጊነት ሊያሳይ የሚችል ነው፡፡ ምስሉን በጥንቃቄ ተረድላችሁ በምሳሌ ለጓደኞቻችሁ
አስረዱ
ተግባር፡ 1. በዚህ ሂደታዊ ተከታታይ ምዘናን በሚገልጸው ንድፉ ውስጥ የሰፈሩ ነጥቦችን በመመርመር የምዘና፣ ግምገማ እና እርምጃን
ተግባራዊነት በመለየት ተንትናችሁ አስረዱ፡፡
2. ለማንሰራረሪያ፣ ማበልጸጊያና ዳግም ምዘና ትግጓሜ ስጡ
ከሂደታዊ ተከታታይ ምዘና በተመሳሳይ አጠቃላይ ተከታታይ ምዘና ሲታቀድ የሚከተሉት ከግንዛቤ መግባት ይኖርባቸዋል፡
የመማር ውጤቶች ግልጽነት፡- የመማር ውጤቶች በግልጽ ሊነደፉ ይገባል፡፡ የሚጠበቁ የባህርይ ለውጦች
ማለትም የዕውቀት፣ የግንዛቤ፣ ክህሎት፣ ዝንባሌና መሰረታዊ እሴቶች በግልጽ ተብራርተው መታየት
ይኖርባቸዋል፡፡
የመማር ተግባራት ተገቢነት፡- በመማር ማስተማሩ ሂደት የህጻናት ተሳትፎ መኖር የመማር ማስተማሩ ሂደት
ስኬታማ እንዲሆን ይረዳል፡፡ ለምሳሌ በገለጻ የማስተማር ስነ-ዘዴ ብቻ የተማሪዎችን ስብዕና፣ ክህሎታ
የመሳሰሉ አላማዎችን ከግብ ማድረስ አይቻልም፡፡ በገለጻ ስነዘዴን በመጠቀም ብቻ ካስተማርን የህጻናትን
በተግባር ሰርቶ የማሳየት ችሎታ ለመለካት አንሞክርም፣ ምክንያቱም ክህሎቱ እንዲጎለብት በማስተማር
ስልታችን አላደረግንምና፡፡
ደብረማርቆስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ/ ስነ-ትምህርት ትምህርት ክፍል
xvii
ም
ት
የ
ው
ቸ
ባ
ር
ኮ
ተ
ሚ
ስ
ቶ
ይ
ቱ
ጃ
እ
ዱ
ሰ
ወ
ግ
ና
ዘ
ሎ
ክ
፣
ዊ
ሮ
ዕ
፡
ች
ዎ
ማ
ላ
አ
ህ
ል
ከ
ካ
ለ
መ
ታ
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
የምዘና ስልቶች፡- ግልጽነት ያላቸው የመማር ውጤቶች የምዘናውን አካሄድ ቀላል ያደርጉታል፡፡ በሌላ አባባል
የምንመርጠው የምዘና ስልት ከትምህርቱ አላማ ጋር ሊሄድ የሚችል መሆን ይኖርበታል፡፡
በምዘና ሂደት የነዚህ ከላይ ያየናቸው ጭብጦች ሊዛመዱ ወይም ሊጣጣሙ ይገባል፡፡ የቅድመ መደበኛ ህጻናትን ውጤት
ለመወሰን በአብዛኘው የብቃት መመዘኛ ስልቶችን(ለምሳሌ፡ ሰርቶ ማሳየት፣ የክፍል ስራ፣ ምልከታ፣ የመሳሰሉትን)
እንድንጠቀም ይመከራል፡፡
ስለሆነም የምዘና ስልቶች እና የማስተማር መማር ተግባራት መመረጥ ያለባቸው ከትምህርቱ ዓላማዎች አንጻር ነው፡፡
አንድ የምዘና ስልት ወይም የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ በአንድ ቦታ ተገቢ/ የሚሰራ ሆኖ በሌላ ቦታ የማይሰራ/ የማይገባ
ሊሆን ይችላል፡፡ በሌላ አባባል የምዘና ስልት ከመምረጣችን በፊት ልናሳካ ላሰብነው ግብ ተስማሚ መሆኑን መመርመር
ይኖርብናል፡፡
2. ምዘናችን ትክክለኛ እንዲሆን ከአንድ በላይ የምዘና ስልቶችን በመጠቀም መመዘን ያስፈልጋል (triangulation)፡፡
በተጨማሪም የሁሉንም የትምህርት አላማዎች ከግብ የመድረስ ሂደት ለማየት አንድ፣ ብቸኛና ተስማሚ የሆነ
የምዘና ስልት የሌለ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ ነው፡፡
ተግባር 1:- የተማሪዎችን መማር ለመመዘን የተወሰኑትን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ወይም በዛ ያሉ የምዘና
ስልቶችን መጠቀም የሚያስፈልገው ለምንድነው?
1. ____________________________________________________
2. ____________________________________________________
3. የምዘና ስልቶችን በአግባቡ መጠቀም የእያንዳንዱን ስልት ድክመቶች፣ ጥንካሬዎችና ተገቢነት ጠንቅቆ ማወቅን
ይጠይቃል፡፡ ሁሉም የምዘና ስልቶች አንድ ወይም ከአንድ በላይ ችግሮች ይኖሯቸዋል፡፡
4. የተማሪዎችን መማር መመዘን በራሱ ግብ አይደለም፣ ከግብ የመድረሻ መንገድ እንጂ፡፡ ስለሆነም የማሳካው ዓላማ
ወይም ግብ ምንድነው? የሚል ጥያቄን ቀድሞ መመለስ ተገቢ ነው፡፡ በተጨማሪም ሊወሰዱ የሚገባቸውን
እርምጃዎች መለየት ያለብን መረጃ ማሰባሰቢያ መሳሪያው ከመመረጡ በፊት ነው፡፡
5. በምዘና የተገኘን መረጃ በመጠቀም ወላጆች እና ማህበረሰቡ የህጻናትን መማር የሚያሻሽል ድጋፍ መስጠት እንዲችሉ መምህራን
እነዚህን አካላት የማሳተፍ፣ የማስተባበር ወይም የማነሳሳት በአጠቃላይ አብሮ የመስራት ሃላፊነት አለባቸው፡፡
ተግባር፡ የተማሪዎችን መማር በመመዘንና የምዘና መረጃን በመጠቀም ሂደት ወላጆችና መምህራን ሊፈጥሯቸው የሚችሉ
ቢያንስ ሶስት የግንኙነት ሁኔታዎችን በጥንድ በመወያየት ለክፍሉ አቅርቡ፡፡
6. የተማሪዎችን ባህርይ መመልከትና እውቀትና ችሎታቸውን የተመለከተ መረጃ መያዝ የቀን ተቀን ተግባር ሊሆን
ይገባል፡፡ መረጃ ሳንይዝ የተማሪዎችን መሻሻል ለማየት እርምጃ ለመውሰድ አንችልም፡፡ መረጃው ከግላዊ
አስተሳሰብና ጭፍን ጥላቻ የጸዳ ጠንካራ ጎኖችን፣ ድክመቶችን እና የተወሰዱ እርምጃዎችን የሚያሳይ ሊሆን
ይገባል፡፡ የተያዘውን መረጃ እንደአስፈላጊነቱ ወላጆችና ተማሪዎች እንዲያውቁት ይደረጋል፡፡ መረጃ የመያዝ
ተግባር የመምህራን ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችም ተግባር ሊሆን ይችላል፡፡
ተግባር 1፡- የተማሪዎችን መማር የተመለከቱ መረጃዎች በሚከተለው መልኩ ተመዝግበው ሊያዙ ይችላሉ፤
ለእያንዳንዱ ግልጽ ትርጓሜና ምሳሌ/ዎች በመስጠት አስረዱ
የተማሪዎችን መማር በተመለከተ የመምህሩ/ሯ እይታ/ግምገማ፣
የተማሪዎች ግለ-ግምገማ ሪፖርቶች፤
የመምህሩ/ሯ-ወላጆች-ተማሪዎች (ወተመ) የጋራ ውይይት ሪፖርት፤
በተማሪዎች የተሰሩ የናሙና ስራዎች፤
የአቻዎች ወይም ቡድናዊ አደረጃጀቶች የግምገማ ሪፖርት፤
የተማሪው/ዋ ፖርትፎሊዮ፤
በመምህሩ/ሯ የተሞሉ ቸክሊስቶች፣ ሬቲንግ ሰኬሎች፣ ሩብሪኮች
የውጤት ማጠራቀሚያዎች(mark lists)፤ ሪፖርት ካርዶች
ተግባር 2፡ የምዘና መረጃን መዝግቦ መያዝ ሊያስገኛቸው ከሚችሉ ጠቀሜታዎች ቢያንስ ሁለቱን ጥቀሱ
1. _____________________________________________________________
2. _____________________________________________________________
7. የተሻለ ምዘና ተማሪዎች መልካም ስነምግባር እንዲያዳብሩ የሚረዳ ነው፡፡ መልካም ስነምግባርን መላበስ
ከመምህሩም፣ ከተማሪዎችም የሚጠበቅ እሴት ነው፡፡ ለምሳሌ ምዘናን ተግባራዊ ስናደርግ እያንዳንዱ ስራ
የተማሪዎች የራሳቸው መሆኑን ማረጋገጥና የሌላ ሰው ስራ ማቅረብን እንዲጠሉ ለማድረግ መጣር ይኖርብናል፡፡
ተግባር፡ በአንድ በተማሪ የተሰራ ስራ የተማሪው/ዋ የራሱ/ሷ መሆኑን ለማረጋገጥ ምን አይነት ስልቶችን ልንጠቀም
እንደምንችል በጥንድ በመወያየት ለክፍሉ ግለጹ፡፡
_________________________________________________________
8. የእያንዳንዱን ተማሪ የመማር ሁኔታ በመመዘን እና ተገቢ ግብረመልስ በመስጠት ተግባር ላይ ተማሪዎች ንቁ
ተሳታፊዎች ሊሆኑ ይገባል፡፡ ከዚህም አንጻር የምዘና ተሳታፊዎች መምህራን፣ ተማሪው /ዋ፣ አቻዎች ወይም
ቡድኖች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
ተግባር 1: የሚከተሉት በምዘና ሂደት ተማሪዎችን ማሳተፍ አስፈላጊ የሆነባቸው ምክንያቶች
ናቸው፡፡ እያንዳንዱን ነጥብ ካነበባችሁ በኋላ “እንዴት?” ብላችሁ ራሳችሁን በመጠየቅ
ለጥያቄዎቻችሁ በቂ መልስ ስጡ፡፡
1. ግለ-ምዘናና የአቻ ምዘና ተፈጥሮአዊ ናቸው፤
2. የመምህር ግምገማ ትክክለኛነትና አስተማማኝነት ሊጎለው ይችላል፤
3. ግለ-ምዘናና የአቻ ምዘና መማር ጥልቀት እንዲኖረው ይረዳል፤
4. ተማሪዎች መማርን የመመዘን ባህል እንዲኖራቸው ያደርጋል፤
5. ተማሪዎች የራሳቸውን መማር ራሳቸው እንዲመሩ ይረዳል፣
6. ተማሪዎች በትምህርታቸው በቂ ግብረ-መልስ እንዲያገኙ ያደርጋል፤
ከግብ ወይም ከአላማ አንጻር ተከታታይ ምዘና በሁለት ዋና ዋና ምድቦች ተከፍሎ ሊታይ ይችላል፡፡ ሂደታዊ ተከታታይ ምዘና
(ሂተም) እና አጠቃላይ ተከታታይ ምዘና (አተም) በሚሉ፡፡
የሂደታዊ ተከታታይ ምዘና (ሂተም) ዋና ግብ የማስተማር መማር ሂደትን ማሻሻል ሲሆን የአጠቃላይ ተከታታይ ምዘና
(አተም) ዋና ግብ ደግሞ ፍትሃዊና ትክክለኛ በሆነ መልኩ የተማሪዎችን ውጤት መወሰን ነው፡፡
ከታች ካለው ምስል መረዳት እንደምትችሉት በአጠቃላይ የተከታታይ ምዘና ስልቶች መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ በሚሉ ሁለት ምድቦች
ይመደባሉ፡፡ መደበኛ ያልሆኑት እንደገና ያልተደራጁና የተደራጁ በሚል በሁለት ይመደባሉ፡፡ መደበኛ የሆኑ የምዘና ስልቶች በጣም
የተደራጁ ናቸው፡፡ እነዚህን የምዘና ስልቶች በቅድመ መደበኛና በአንደኛ ደረጃ አንደኛ ሳይክል ትምህርትቤቶች የሚማሩ ተማሪዎችን
ውጤት ለመወሰን ተግባራዊ እንዲደረጉ አይመከርም፡፡ በዚህ ደረጃ የሚማሩ የህጻናትን ውጤት መደበኛ ያልሆኑ ነገር ግን የተደራጁ
የሚባሉ ስልቶችን በመጠቀም እንዲወሰን ይመከራል፡፡ እነዚህ የ ተደራጀ አካሄድ ያላቸው መደበኛ ያልሆኑ ስልቶች(ለምሳሌ
ትንሽ ሙከራ፣ የክፍል ስራ፣ የቤትስራ፣ የተግባርስራ፣ ወዘተ) በእቅድ ተግባራዊ የሚደረጉ ከሁሉም ህጻናት መረጃ
ለማግኘት በተመሳሳይ ለሁሉም ግብረመልስ ለመስጠትና መረጃን መዝግቦ ለመያዝ የሚመቹ ስልቶች ናቸው፡፡
ተግባር፡- በመጀመሪያ መደበኛ ያልሆኑ የሂተም የመረጃ መሰብሰቢያ ስልት የሚባሉ ቢያንስ አምስት የተለያዩ ስልቶችን
በየግላችሁ ዘርዝሩ፤ በመቀጠል ጥንድ በመሆን የዘረዘራችሁትን አጠናክሩ፤ በመጨረሻ ሁለት ጥንዶች አንድ ቡድን (4
አባል) በመፍጠር ሁሉንም በተናጠል የታዩ የሂተም ስልቶችን አደራጅታችሁ የምዘና ስልቱ እንዴትና በምን ሁኔታ
ተግባራዊ እንደሚደረግ በማብራራት ለክፍሉ ተማሪዎች አቅርቡ፡፡
ምዘና ማብራሪያ
ቃለ-መጠይቅ ተማሪዎችን ስለታሪካቸው፣ ስለሚያከናውኑት ተግባር፣ ስለአነቡትና ስለፍላጎቶቻቸው ወዘተ
(Interview) በመምህሩ/ሯ ለሚቀርብላቸው የተደራጀ መጠይቅ የተብራራ ምላሽ በቃል ይሰጣሉ፡፡
ምልልሱ ያለማጨናነቅ፣ አዝናኝ ሆኖ ተግባራዊ ለደረግ ይገባል፣
ከእያንዳንዱ ተማሪ ጋር ቃለ-መጠይቁ በተከታታይ ቀናት ተግባራዊ ይደረጋል፣
በቃለ-መጠይቁ የሚገኘው መረጃ ተመዝግቦ (በአይነታዊ መረጃነት) የሚያዝ
ይሆናል፣
ታሪክ ማውራት ህጻናት በማዳመጥ ወይም በመስማት የተማሩትን ታሪክ መልሰው እንዲተርኩት/
/መተረክ እንዲናገሩት ማድረግ፣
(Story telling) ህጻናት በቃል የሚተርኩትን ሪፖርት ያዘጋጃሉ፣
የብቃት ምዘናው የተናገሩትን ፍሬ-ሃሳብ ወይም የቋንቋ አጠቃቀማቸውን መሰረት
በማድረግ ሊሆን ይችላል፣
የመገምገሚያው መሳሪያው (መከታተያው) ሩብሪክ ወይም ሬቲንግ ስኬል ሊሆን
ይችላል፣
የተግባር ስራ /Project ህጻናት በተማሩት ይዘት ዙሪያ በተናጠል፣ በጥንድ ወይም በቡድን የተግባር ስራ ሰርተው
work ያቀርባሉ፣
ህጻናት በቃል፣ በጽሁፍ ወይም በሁለቱም ስራዎቻቸውን ሊያቀርቡ ይችላሉ፣
የህጻናትን የቃል እና የጽሁፍ ስራዎች እንዲሁም የአስተሳሰብ ብስለት ለማየት
ያስችላል፣
የመከታተያ መሳሪያው ሩብሪክ ወይም ሬቲንግ ስኬል ሊሆን ይችላል፣
የመምህር/ት ምልከታ የህጻናት ባህርይ፣ አትኩሮት፣ ተነሳሽነት፣ ለትምህርት ተግባራት ያላቸው ምላሽ፣ ከሌሎች
Teacher Observation ተማሪዎች ጋር ያላቸውን ተግባቦት ወዘተ በመምህሯ/ሩ በቀጥታ ይታያል፣
ህጻናት ስለራሳቸው እና ስለመማራቸው ሁኔታ በግለ -ምዘና ግንዛቤን ይይዛሉ፡፡ ህጻናት ራሳቸውን
ገምግመው የሚገልጹበት ሁኔታ ምን ያህል በጥራት እየተማሩ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ስለሆነም
የቅድመ መደበኛ መምህራን ህጻናት ራሳቸውን እንዲያዩ እድል ሊሰጧቸው ይገባል፡፡ ብዙውን ጊዜ
ህጻናት የመምህሩን ስራ ከራሳቸው ስራ ጋር በማነጻጸር ራሳቸውን ይገመግማሉ፡፡ በዚህ ሂደት ህጻናት
ከሰሯቸው ስራዎች መርጠው ለሌሎች እንዲያቀርቡ ሊበረታቱ ይገባል፡፡
ደብረማርቆስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ/ ስነ-ትምህርት ትምህርት ክፍል
xxiv
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ልጆች ገና ህጻናት በመሆናቸውና ስራዎችን ገምግመው አስተያየት
የመስጠት ክህሎት ያላጎለበቱ በመሆናቸው የአቻ ምዘና ብዙ አይዘዎተርም፡፡ መምህራን ህጻናትን በቀጥታ
በመምራት ተግባሩን በብቃት እንዲፈጽሙት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ለምሳሌ ህጻናት የእንስሳትን ድምጽ
ሲያሰሙ፣ ሲደንሱ፣ ስዕል ሲስሉ፣ ሲዘፍኑ ወዘተ ምን ያህል ትክክል ነው /ናት በማለት አስተያየት እንዲሰጡ
የመምህሩ/ሯ ጥያቄ ለአቻ ምዘና ሊያበረታታ ይችላል፡፡ ተማሪዎች ለተሳሳቱና ትክክለኛ ምላሾች በምልክት
አስተያየት እንዲሰጡ ማድረግም ይቻላል፡፡
1. መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ የምዘና ስልቶች አንድነትና ልዩነትን በምሳሌዎች በማስደገፍ እንዴት
ይገለጻሉ?
2. ዋና ዋና የብቃት ምዘና ስልቶችን በማሰልጠኛ ሞጁዬሉ ከቀረቡት በተጨማሪ በመዘርዘር በስፋት
በማብራራት አቅርቡ፡፡
3. ግለ-ምዘናና የአቻ-ምዘናን እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል በምሳሌዎች በማስደገፍ
አቅርቡ፡፡
ክፍለ-ትምህርት አራት
በዚህ ክፍለ ትምህርት ቀደም ሲል የተማርናቸውን የምዘና ስልቶች የህጻናት የመዳበር ደረጃዎችን ለመመዘን
ተግባራዊ የምናደርግባቸውን ስልቶች በምሳሌ አስደግፈን እናያለን፡፡ የህጻናት መዳበር ከሚከተሉት አራት
ደረጃዎች አንጻር ሊታይ ይገባል፡ አካላዊ መዳበር (የሰውነት የመጠን ለውጥና የአካል ቅልጥፍና መዳበር)፣
አእምሮአዊ እና የቋንቋ መዳበር (የማሰብ፣ ምክንያታዊነት፣ የማስታዎስ፣ ወዘተ እና የቋንቋ ችሎታ)፣ እና
ስነባህርያዊ-ማህበራዊ መዳበር (ከሌሎች ጋር የመግባባትና የስብዕና ለውጥ) ክህሎቶችን ይይዛል፡፡ ስለሆነም
በዚህ ሞጁል እነዚህን የመዳበር ዘርፎች የምንመዝንባቸውን ስልቶች እናያለን፡፡
የመማር ውጤቶች፡
ከዚህ ክፍለ ትምህርት በኋላ የቅድመ መደበኛ ዕጩ መምህራን:
ልንመዝናቸው የሚገቡ የህጻናት መዳበር ዘርፎችን ይገነዘባሉ፣
የተለያዩ የህጻናት መዳበር ዘርፎችን ለመመዘን የሚያስችሉ የተሻሉ ስልቶችን ይመርጣሉ፤
የመረጡትን የምዘና ስልት በምክንያት ያስረዳሉ፤
የህጻናትን መዳበር ዘርፎችን ለማቃናት የሚያስችል መረጃ ለማግኘት ምዘናን አዘጋጅተው
ይጠቀማሉ፡፡
ተግባር፡-
1. አካለዊ መዳበር ምንድነው?
አካላዊ መዳበር የህጻናት የክብደት፣ የቁመት እና የአካላዊ እንቅስቃሴ ክህሎት ለውጥን ይመለከታል፡፡ ወላጆችና
የቅድመ መደበኛ መምህራን የህጻናት መዳበር አይነቶች ይከሰቱባቸዋል ተብለው የሚጠበቁ ዋና ዋና ጊዜያትን
ለይተው ሊያውቋቸው ይገባል፡፡ የአካላዊ እንቅስቃሴ ክህሎት የህጻናትን የአካል ክፍሎች ለይቶ መረዳትን፣
የአካል ክፍሎችን ቅንጅትን፣ ሚዛን የመጠበቅ ሁኔታን፣ የእጅ ቅልጥፍናን፣ የአይንና የእጅ መስተጋብርን
ይመለከታል፡፡ የሚከተለው ደረጃ መመጠኛ ሰንጠረዥ የቅድመ መደበኛ ህጻናት የአካላዊ እንቅስቃሴ ክህሎት
እንዴት እንደሚመዘን ያሳያል፡፡
የአካላዊ እንቅስቃሴ ክህሎት መመዘኛ ደረጃ መመጠኛ ሰንጠረዥ
የህጻኑ/ኗ እድሜ: ____________________ምልከታው የተደረገበት ቀን ____________
ምልከታውን ያደረገው መምህር ስም: _______________________________________
ማውጫ፡ 4=እጂግ በጣም ጥሩ፣ 3=በጣም ጥሩ፣ 2=በቂ የሚባል፣ 1=ደካማ
1. የአካል ክፍሎችን ለይቶ መረዳት ሚዛን የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
Body Awareness 4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ፡
የአካል ክፍሎቻቸውን በስም መጥራት፣
የአካል ክፍሎቻቸውን መስተጋብር መለየት፤
በተለያየ መንገድ ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ መቻል፤
በስልት መንቀሳቀስ፣ መደነስ፤
እንቅስቃሴን በሚጠይቁ ተግባራትና ጨዋታዎች
መሳተፍ
2. የሰውነት ጡንቻዎችን ማቀናጀት መቻል ሚዛን የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
Muscle Coordination 4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ፡
በትንሽ መሰላል ወይም ደረጃዎች ላይ መውጣትና
መውረድ መቻል፣
ክብ ቁሶችን ማሽከርከር መቻል፣
ቁሳቁሶችን ማቀበል፣ መቀበል እና ኳስ መሰል ቁሶችን
መምታት መቻል፤
ከፍተኛ አካላዊ እቅስቃሴን በቅልጥፍናና በቅንጂት
ማከናዎን መቻል
3. ሚዛንን የመጠበቅ ሁኔታ/ ሚዛን የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
Balance 4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
በአንድ እግር መቆምና መዝለል መቻል፣
በእግር እጣቶች ረጂም ርቀት መጓዝ፤
ሚዛን ጠብቆ በአግዳሚ ጣውላዎች ላይ መሄድ፤
ወደኋላ መጓዝ መቻል
4.የእጅ ቅልጥፍናን/ ሚዛን የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
Manual Dexterity 4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
የመመገበያና መጠቀሚያ ቁሶችን ማጽዳትና በሚገባ መጠቀም
መቻል፤
የመጫዎቻ ቁሳቁሶችን ከጭቃ (የተቦካ ወረቀት) በተለያዩ
ቅርጾች በማዘጋጀት መጫዎት መቻል፤
በሌላ አነጋገር የቅድመ መደበኛ መምህራን የህጻናትን የመዳበር ሁኔታ ለመመዘን የሚያስችል የመገምገሚያ
መሳሪያን በእድሜአቸው ከህጻናት ከሚጠበቁ የመዳበር ለውጦች ጋር በማዛመድ ማዘጋጀት ይቻላል፡፡
ለምሳሌ፡
የአካላዊ መዳበር አመላካቾች/ Physical development indicators
የእድሜ ጠቅላላ እንቅስቃሴ አይነቶች/ ውስብስብ አካላዊ ብቃቶች/
ክልል Gross motor Fine motor
ከ 2-3 በቀላሉ መሮጥ፣ መታጠፍና በፍጥነት መቆም ክብ ምስሎችን መስራት፤
ዓመት መቻል፤ የጠርሙስ እፊያዎችን መክፈትና መግጠም፤
መሰላል መውጣትና መውረድ፣ ትናንሽ የመጫዎቻ ቁሶችን በተገቢ ቦታቸው ለይቶ
በመንሸራተቻዎች ተንሸራቶ መውረድና ማስቀመጥ፤
ያለአጋዥ መልሶ መውጣት መቻል የህጻናትን መጽሃፍ በአንድ ጊዜ አንድ ገጽ በመግለጽ
ሁለት እግርን በአንድ ላይ በማድረግ ማየት መቻል፤
(እንደእንቁራሪት) መዝለል መቻል፤ በትናንሽ መቀሶች/ መቁረጫዎች ለመቁረጥ
ለጥቂት ደቂቃዎች ያለድጋፍ በአንድ እግር መቆም መሞከር፤
መቻል፤ ስምንትና በላይ ኩቦችን በመደራረብ ማስቀመጥ
ወደፊት በጀርባ መንከባለል (ሮል ማድረግ) መቻል፣
መቻል፤ እንደ አንድ ጎልማሳ ቾክ በእጅ በመያዝ መጻፍ
ቁሶችን ተራምዶ ማለፍ መቻል መቻል
ራስን ችሎ ደረጃዎችን መውጣትና መውረድ
መቻል
ከ 3-4 በሩጫ ጊዜ መንገድ ላይ ያሉ ቁሶችን/ እንቅፋቶችን አግዳሚና ቋሚ መስመሮችን መሳል፣
ዓመት በመዝለል ማለፍ መቻል ሙሉ ክብን መሳል/ ከሌላ አይቶ መሳል፤
ባለሶስት ጎማ ብስክሌቶችን ማሽከርከር መቻል፤ በኩቦች የቤት፣ የድልድይ ወይም የመኪና ሞዴሎችን
ያለድጋፍ በአንድ እግር መቆም መቻል መስራት፣
በአንድ እግር ቢያንስ ሁለት ጊዜ ያለድጋፍ መዝለል በመቀስ ወረቀቶችን አስተካክሎ መቁረጥ፣
መቻል አቋራጭ የሆኑ ሁለት መስመሮችን መሳል፣
ዘጠኝ እና በላይ ተገጣጣሚ መጫዎቻዎችን( puzzles)
በስልት ማስቀመጥ፣
ከ 4-6 ያለድጋፍ በአንድ እግር በመዝለል ቁሶችን መዞር፣ ትርጉም ያለው ስዕል መሳል መቻል፤
ዓመት ከሌላ ህጻን ጋር ሌባና ፖሊስ መጫዎት፤ አራቱ ማዕዘን በግልጽ የሚታይ ካሬ/ አራት ጎን
ኳሶችን መወርዎርና መቅለብ መቻል፤ መስራት፤
ንድፍን ተከትሎ ወረቀትን በመቀስ መቁረጥ መቻል፤
ቢያንስ ሶስት ግልጽ ያካል ክፍል ያለው (ምሳሌ ራስ፣
እግር፣ እጅ ወይም ሌላ) ሙሉ የሰው ምስል መሳል
መቻል፤
መስመር ሳያልፉ የምስሎችን ውስጥ ቀለም መቀባት
መቻል፤
አቅዶና በስልት ስዕል መሳልና ቀለም መቀባት
መቻል፣
ተግባር:
1. የአዕምሮአዊ እና ቋንቋ መዳበር ምንድን ናቸው? (ልዩነትና አንድነት)
2. የህጻናት የቋንቋ መዳበር እንዴት ይመዘናል?
ቁጥሮችን ማዎዳደር፣
መስፈር/ መለካት መቻል(ውሃ፣ አሸዋ ወዘተ)፣
2. ቅርጽን መለየት እና ቦታን መረዳት/ Shapes / Spatial Skills ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ቅርጾችን ማስታዎስ፣ መጥራትና መግለጽ መቻል፤
ሚገጣጠሙ ቀላል መጫወቻዎችን መገጣጠም፤
አቅጣጫን እና ቦታን መግለጽ፤
ተመሳሳይ ቅርጽ ያላቸውን ቁሶች መመደብ፤
የአንድ ነገር ክፍሎችን ከዋናው አካል ጋር ማዛመድ፤
3. በቅደም ተከተል/ በስርዓት ማስቀመጥ/ ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
Patterns/ Sequences 4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ቀላል አሰላለፎችን (patterns) ማስታዎስና መልሶ
መስራት፤
መሰረታዊ የጊዜ ሃሳቦችን መረዳት፤
ቁሶችን/ ስእሎትን መቅደም ተከተላቸው ማስቀመጥ፤
በአካባቢ የተከሰቱ ለውጦችን ማስታዎስ፤
4. መመደብ መቻል/ Classification ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
የሚመሳሰሉ ቁሶችን ማዛመድ፣
በቁሶች መካከል ያለ ልዩነትንና አንድነትን መግለጽ፣
ቁሶችን በባህርያቸው (attributes) መምረጥ፣
ግራፎችን በመስራትና በመጠቀም ሂደት ማገዝ፣
5. ችግር ፈችነት/ Problem Solving ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ችግሮችን ለመፍታት ምልከታ ማካሄድ፣
ሳይንሳዊ የችግር መፍቻ ቁሶችን መጠቀም፣
ምክንያትና ውጤትን ለመለየት መመራመር፣
ከቀደመ ልምድ በመነሳት ውጤትን መተንበይ፣
ሳይንሳዊ ቃላትና ሃረጋትን መጠቀም፡፡
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ታሪክን ማዳመጥና ምላሽ መስጠት፣
ለተጠየቁ ጥያቄዎች መልስ መስጠት መቻል፣
ትዕዛዝ መቀበልና መፈጸም፣
መረጃን መልሶ ማስታዎስ መቻል፣
2. መስማት/ Auditory ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ዜማዊ ቃላትን መለየት፣
ፊደል ድምጾችን ከቅጾች ጋር ማዛመድ መቻል፣
በመነሻ ድምጽ ቃላትን መለየት፣
ድምጾችን በአናባቢዎቻቸው መክፈል መቻል፣
3. መናገር መቻል/ Speech Production ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
አዳዲስ ቃላትን በንግግር ውስጥ መጠቀም መቻል፣
ጥያቄ መጠየቅ መቻል፣
ሙሉ አረፍተ ነገር በመስራት መናገር፣
ፊደላትን በትክክል መጥራት፣
4. ማንበብ መቻል/ Reading ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ለራስና ለሌሎች አንብቦ ለማሳየት መሞከር፣
ምልክቶችን ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር ማዛመድ መቻል፤
አነባበብን (ከግራ ወደቀኝ እና ከላይ ወደታች እንደ ሚነበብ)
ማዎቅ፣
ፊደላትን እና የተለመዱ ቃላትን መገንዘብ፤
5. መጻፍ መቻል/ Writing ሚዛን ቁጥር የተመዘነው ብቃት እና የተሰጠ ግብረ
4 3 2 1 መልስ
ምሳሌ:
ቀላል ቅርጾችን አስመስሎ መሳል ወይም መኮረጅ መቻል፣
የሰዎችን አጻጻፍ አስመስሎ መጻፍ፣
ጽፎ ለማሳየት (ለጎልማሶች) ቁርጠኛ መሆን፣
የሰሙትን ፊደላትና የተለመዱ ቃላትን መጻፍ መቻል፣
የቅድመ መደበኛ ህጻናትን የአዕምሮአዊና የቋንቋ መዳበርን ለመመዘን የሚከተሉትን የባህርይ ጠቋሚዎች
በማገናዘብ መጠቀም ይኖርብናል
የአእምሮአዊና የቋንቋ መዳበር ጠቋሚዎች /indicators ሚዛን ቁጥር
ምርመራ
3 2 1
ደብረማርቆስ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ/ ስነ-ትምህርት ትምህርት ክፍል
xxxii
የትምህርት ምዘናና ግምገማ በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች
በጽሑፍ ፈተና አዘገጃጀት ላይ ጥናት ያደረጉ ምሁራን እንደሚሉት ጥራት ያላቸዉ የፈተና ጥያቄዎች በዘፈቀደ የሚጻፉ
ሳይሆኑ ጥብቅ ህግጋትን በመከተል በጥንቃቄ የሚዘጋጁ ናቸዉ፡፡ በመሆኑም በፈተና አዘገጃጀት ሂደት የመጀመሪያዉ
ተግባር ማቀድ ነዉ፡፡ ፈተናን በማቀድ የጽሑፍ ፈተና አዘገጃጀት እርከን የሚከተሉት ንዑሳን ቅደም ተከተሎች
ይካተታሉ፡፡
1. የፈተናዉን አላማ መወሰን፣
2. ዝርዝር የመማር ማስተማር አላማዎችን መምረጥ፣
3. የጥያቄ ብዛት መወሰን፣
4. ዝርዝር ሠንጠረዥ ማዘጋጀትና፣
5. የፈተና ጥያቄ አይነቶችን መምረጥ፡፡
መምህራን የሚያዘጋጁት የፈተና ጥያቄ ባህሪ ለምሳሌ ቅለትና ክብደት፣ የሚሸፍነዉ የይዘት ስፋት …ወዘተ ጥያቄዉ
የሚዘጋጅበትን አላማ መሰረት በማድረግ ይወሰናል፡፡ ለግንዛቤ እንዲረዳችሁ የሚከተለዉን ሠንጠረዥ ተመልከቱ፡፡
መምህራን ፈተና ለማዘጋጀት ሲነሱ ፈተናዉን ለምን አላማ እንደሚያዘጋጁት መረዳት ተቀዳሚ ተግባራቸዉ ነዉ፡፡
ምክንያቱም ከላይ ከቀረበዉ ሠንጠረዥ እንደምንረዳዉ የፈተናዉ ባህሪ የሚወሰነዉ ፈተናዉ ከሚዘጋጅበት አላማ
አንጻር በመሆኑ ነዉ፡፡
ፈተና ሁሉንም አይነት የባህሪ ገጽታዎች አይለካም፡፡ ለምሳሌ ተማሪዎች በመማር ማስተማር ሂደት ያዳበሩትን ክህሎት
(Psychomotor domain) ወይም ያዳበሩትን ፍላጎት፣ የዝንባሌ፣ የአመለካከት (Affective domain) ለዉጥ በጽሑፍ
ፈተና ጥያቄዎች መለካት ያስቸግራል፡፡ የጽሑፍ ፈተና ሊለካ የሚችለዉ የተማሪዎችን የማስታወስ፣ የመገንዘብ፣
የመተግበር፣ የመተንተን፣ የማቀናበርና የመገምገም በአጠቃላይ አዕምሮአዊ (Cognitive domain) ችሎታን ነዉ፡፡
ስለሆነም በሴሚስተሩ ከተተኮረባቸው የመማር ማስተማር ዝርዝር አላማዎች ዉስጥ በፈተና ሊለኩ የሚችሉ
ባህሪያትን መለየት በሁለተኛነት የሚመጣ የፈተና ዕቅድ ክፍል ነዉ፡፡
የፈተና ዝርዝር ሠንጠረዥ (Table of Test Specification or Test Blue Print) ዝርዝር የመማር ማስተማር
አላማዎችን በፈተናዉ ልናካትታቸዉ ካሰብናዉ ይዘቶች ጋር የምናዛምድበት ሠንጠረዥ ነዉ:: ብያኔዉን በይበልጥ
ለመረዳት የሚከተለዉን ምሳሌ ተመልከቱ፡፡
ከእያንዳንዱ ይዘት ውስጥ በፈተናችን ልናካትተዉ የምንፈልገዉን የጥያቄ ብዛት የምንወስነዉ በዋናነት ይዘቱን
ለማስተማር የተጠቀምንበትን የክ/ጊዜ ብዛት መሠረት አድርገን በሚከተለዉ መንገድ በማስላት ነዉ፡፡
ነገር ግን ከሂሳባዊ ስሌቱ በተጨማሪ መምህራን አንደኛዉ ይዘት/ የመማር ማስተማር ዓላማ ከሌላኛዉ ይልቅ
ለተማሪዎች ቀጣይ ህይወት አስፈላጊ ነዉ ብለዉ ካሰቡ የራሳቸዉን ግምገማ በማካሄድ (Using Personal Judgement)
ከእያንዳንዱ ይዘት የሚያዘጋጁትን የጥያቄ ብዛት ማመጣጠን ይችላሉ፡፡
በእያንዳንዱ የማሰብ ደረጃ (Process objective) አንጻር የሚካተት የጥያቄ ብዛትን ደግሞ የመማር ማስተማር ዝርዝር
አላማ ባህሪን ግምት ዉስጥ በማስገባት የጥያቄዎችን ብዛት ማመጣጠን ይቻላል፡፡
የተግባር ስራ
ከዚህ በታች የሰፈሩት የመማር ማስተማር አላማዎች የተጻፉባቸዉን ድርጊት አመልካች ግሶች በመመልከት በየትኛዉ የማሰብ
ደረጃ ላይ ጥያቄዉ ሊካተት እንደሚችል ለክፍል ጓደኞቻችሁ ተናገሩ፡፡ የፈተና አረገጃጀት ደረጃዎችን ከተማሩ በኋላ
ሠልጣኞች፡
1. የጽሑፍ ፈተና አዘገጃጀት ደረጃዎችን በቅደም ተከተሎች ይዘረዝራሉ፣
2. በመጀመሪያ ደረጃ መምህራን የተዘጋጁ ጥያቄዎችን ጥንካሬና ድክመት ይገመግማሉ፣
3. ዝርዝር ሠንጠረዥ ማዘጋጀት ለፈተናችን ጥራት ያለዉን ፋይዳ ያብራራሉ
4. የጽሑፍ ፈተና አዘገጃጀት ህግጋትን ጠብቀዉ 2 የምርጫ ጥያቄዎችን ይጽፋሉ፣
5. የተለያዩ የፈተና ጥያቄ አይነቶችን ደካማና ጠንካራ ጎን ይተነትናሉ፣
6. በመረጡት አንድ የትምህርት አይነት ላይ ዝርዝር ሠንጠረዥ ያዘጋጃሉ፣
…. መምህር እባክዎ ሌሎችንም ምሳሌዎች በመጨመር ይህን ተግባር ያለማምዷቸዉ!
ተማሪዎች! ዝርዝር ሠንጠረዥ ማዘጋጀት ለምን ያስፈልጋል? የተለያዩ የመስኩ ምሁራን እንደገለጹት ዝርዝር
ሠንጠረዥ ማዘጋጀት የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት፡፡
የይዘት ትክክለኛነትን (Content Validity) ለማረጋገጥ ይጠቅማል፣
ተማሪዎች ለፈተና የሚዘጋጁበትን አግባብና አቅጣጫ ለመጠቆም ያግዛል፣
መምህራን ፈተናቸዉን ሲያዘጋጁ እንደ ካርታ ሆኖ ያገለግላቸዋል፣
የመማር ማስተማርን ተግባርን ከምዘና ተግባር ጋር ለማስተሳሰር ጉልህ አስተዋጾ አለዉ
ተማሪዎች! እያንዳንዱ ጠቀሜታ ምን ማለት እንደሆነ በቡድን በመወያየት ጽብረቃ አቅርቡ፡፡
በአንድ የጥያቄ አይነት ሁሉንም የመማር ባህሪያት መለካት ያስቸግራል፡፡ መምህራን የተለያዩ ጥያቄ አይነቶችን
በፈተናቸዉ የሚያካትቱት የተለያዩ የመማር ባህሪያትን ለመለካት ነዉ፡፡ ለግንዛቤ እንዲሆናችሁ የሚከተለዉን
ሠንጠረዥ ተመልከቱ፡፡
ቀጣዩ ተግባር የሚሆነዉ ከላይ የቀረቡትን የተለያዩ የፈተና ጥያቄ አይነቶች መሠረት በማድረግ የሚከተለዉን የፈተና
አይነት ዝርዝር ሠንጠረዥ ማዘጋጀት ነዉ፡፡
የተግባር ስራ፡- ቀጣዩን ክፍል ከማንበባችሁ በፊት ከክፍል ጓደኞቻችሁ ጋር በመወያየት ማብራሪያ ስጡ
1. መምህራን የፈተና ጥያቄዎችን ሲያዘጋጁ ሊከተሏቸዉ የሚገቡ አጠቃላይ እና ዝርዝርዝ መርሆዎች ምን ምን ናቸዉ?
2. እነዚህን አጠቃላይና ዝርዝር መርሆዎች በጽሁፍ ፈተና ዝግጅት ወቅት ተግባራዊ ማድረግ መምህራን ለሚያዘጋጁት
የፈተና ጥያቄ ጥራት ያለዉ ፋይዳ ምንድን ነዉ?
3. የእያንዳንዱ የጥያቄ አይነት ጠንካራና ደካማ ጎኖች ምን ምን ናቸዉ?
4. የተለያዩ የፈተና ጥያቄ አይነቶች የትኛዉን የመማር ባህሪ እንደሚለኩ ማብራሪያ ስጡ
ጠንካራ ጎን ደካማ ጎን
ለማረም ቀላል ነዉ ለግምት የተጋለጠ ነዉ /50%/
ለማዘጋጀት አይከብድም የመለየት አቅሙ /discrimination power/ ደካማ ነዉ
በርካታ ይዘቶችን ለመሸፈን ያስችላል ከፍተኛ የማሰብ ደረጃን አይለካም
ተማሪዎች በፍጥነት መመለስ ይችላሉ አስተማማኝነቱ (Test reliability) ዝቅተኛ ነዉ
ለ. የማዛመድ ጥያቄዎች
ጠንካራ ጎን ደካማ ጎን
ለማዘጋጀት በጣም ቀላል ነዉ በብዛት ከተጠቀምንበት ተራ ሽምደዳን ያበረታታል
መልሱን በግምት የማግኘት እድልን ይቀንሳል ከሌሎች ዉስን መልስ ካላቸዉ ጥያቄዎች ለማረም አስቸጋ ነዉ
ምን፣ማን፣የት፣መቼ አይነት ይዘቶችን ለመጠየቅ ምቹ በጥንቃቄ ካልተዘጋጁ አንድ ዉስን መልስ ላይኖራቸዉ ይችላል
ነዉ
የተማሪዎች የአጠናን ስልት እንዲሻሻል ያደርጋል፣
መለኪያዎች ለሚያስፈልጓቸዉ የመማር ማስተማር ዉጤቶች ለምሳሌ የራስ ዳሽን ተራራ ርዝመት መለኪያ
አሃዱን ጨምሮ መግለጽ፣
ጠንካራ ጎን ደካማ ጎን
የተለያዩ የመማር ዉጤቶችን ለመለካት ያስችል/Versatile/ ከሁሉም የጥያቄ አይነቶች ለማዘጋጀት ከባድ
የተማሪዎችን መማር ለመለካት ዉጤታማ ነዉ/Effective/ ነዉ
በርካታ ይዘቶችን ለመመዘን ያስችል ተመሳሳይ አሳሳቾችን ለማግኘት ያስችግራል
ለማረም ቀላል ነዉ
የጥያቄዉ ግንድ አንድ ሐሳብ ብቻ የያዘ፣ የተሟላ፣ ግልጽና ትክክለኛዉን መልስ ከሚጠቁሙ አመልካቾች የጸዳ
መሆን አለበት፣
ተማሪዎች በከፊል እዉቀት መልሱን ማግኘት እንዳይችሉ “ሁሉም መልስ ነዉ” የሚል አማራጭ አለመጠቀም፣
“መልስ የለም” የሚለዉን አማራጭ ሲያስፈልግ ብቻና በጥንቃቄ መጠቀም፣
አሳሳቾችን (Distractors) ከትክክለኛዉ መልስ ጋር የተቀራረቡ ማድረግ (Plausible)
አማራጮችን እርስበርስ የሚጋጩ ወይም ተመሳሳይ ሃሳብ የሚያስተላልፉ አለማድረግ፣
ሁለት አሉታዊ ቃላትን በአንድ ላይ አለመጠቀም፣ከተቻለ ጥያቄዉን አወንታዊ በሆነ መንገድ ብቻ መጻፍ፣የግድ
ካስፈለገ ደግሞ አሉታዊ ቃላትን/ሃረጋትን ማስመር፣ማድመቅ ወይም ሌላ የትኩረት መሳቢያ መንገድ መጠቀም፣
አማራጮችን ስርዓት ባለዉ መንገድ መደርደር፤ለምሳሌ አማራጮቹ ዓ.ም ከሆኑ ከበፊቱ ወደአሁኑ ወይም
ከአሁኑ ወደቀደምቱ፣ ቁጥር ከሁኑ ከትንሹ ወደትልቁ ወይም ከትልቁ ወደ ትንሹ…ወዘተ መደርደር፣
ትክክለኛ ምላሾችን በተመጣጠነ እና በተዘበራረቀ መንገድ መደርደር፣
እያንዳንዱ ጥያቄ አንድ ዉስን የመማር ማስተማር ዓላማ እንዲለካ ማድረግ፣
አማራጮችን በራሳቸዉ አዲስ መስመር ላይ መደርደር
የአንድ ጥያቄ ግንድም ሆነ አማራጮች በአንድ ገጽ ላይ እንዲሰፍሩ ማድረግ፣
ቢያንስ ሦስት ራሳቸዉን የቻሉ (independent) አማራጮችን መጠቀም፣አራት ቢሆኑ ይመረጣል
እነዚህ አይነት ጥያቄዎች ከላይ ባየናቸዉ ዉስን መልስ ባላቸዉ (Objective items) ጥያቄዎች ለመለካት ያልቻልናቸዉን
የመማር ዉጤቶች ለመለካት ስንፈልግ የምንጠቀምባቸዉ ናቸዉ፡፡ ለምሳሌ ከፍተኛ የማሰብ ደረጃን የሚጠይቁ እንደ
መተግበር፣ መተንተን፤ ማቀናበር እና መገምገም ያሉ የመማር ዉጤቶችን በዚህ መንገድ መለካት እንችላልን፡፡ነገር ግን
ለማረም አመቺ ባለመሆናቸዉ የመጀመሪያ ደረጃ መምህራን ከላይ ያየናቸዉን የጥያቄ አይነቶች ያህል ሲጠቀሙባቸዉ
አይታዩም፡፡
ጠንካራ ጎን ደካማ ጎን
ለግምት የተጋለጠ አይደለም ለማረም በጣም አስቸጋሪ ነዉ
ለማዘጋጀት በጣም ቀላል ነዉ ሠፊ ይዘት ለመሸፈን ያስቸግራል
ተማሪዎች የተሻለ የአጠናን ስልት እንዲኖራቸዉ በእርማት ወቅት ለተመሳሳይ ስራ የተለያየ ዉጤት
ያበረታታል ልንሰጥ እንችላለን
ከፍተኛ የአዕምሮ ደረጃ የሚጠይቁ የመማር ዉጤቶችን ለሁለት የሚታረም ከሆነም በአራሚዎች መካክል
ለመለካት ምቹ ነዉ መመሳሰል ላይኖር ይችላል
ተማሪዎች ሐሳባቸዉን በነጻነት በጽሑፍ እንዲገልጹ
እድል ይሠጣል
ለተማሪዎች በቂ ጊዜ መስጠት፣
ተማሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን እንዲሰሩ አለመፍቀድ፣
የጥያቄዉ አቀራረብ ተማሪዎች ምን መስራት እንዳለባቸዉ በግልጽ የሚያመለከት መሆን ይኖርበታል/ማብራራት
ከሆነ እንዲያብራሩ፣ማወዳደር ከሆነም እንዲያወዳድሩ…./
የተለያዩ የመስኩ ምሁራን መምህራን ያዘጋጁትን የፈተና ጥያቄዎች ለተማሪዎቻቸዉ ከመፈተናቸዉ በፊት ራሳቸዉ
መፈተን አለባቸዉ ይላሉ፡፡ ለምን አንደዚህ እንደሚሉ ከጓደኞቻችሁ ጋር በመወያየት ምላሽ ስጡ፡፡
የፈተና ጥያቄዎች አደራደር ከቀላል ወደ ከባድ በሆኑን ማረጋገጥ ሁለተኛዉ የክለሳ የትኩረት ነጥብ ነዉ፡፡ በዚህም
መሠረት የፈተና ጥያቄ አይነቶች በሚከተለዉ ቅ/ተከተል ቢቀመጡ ለተማሪዎች ምቹ እንደሚሆን በርካታ የመስኩ
ምሁራን ይስማሙበታል፡፡
የእዉነት/ሐሰት ጥያቄዎች
የማዛመድ ጥያቄዎች
የአጭር መልስ መስጠት/ባዶ ቦታ መሙላት ጥያቄዎች
የባለብዙ ምርጫ ጥያቄዎች
የማብራራት/ሠርተህ/ሽ አሳይ ጥያቄዎች
በእያንዳንዱ የጥያቄ አይነት ስር ያሉ ዝርዘር ጥያቄዎችም ከቀላል ወደ ከባድ መደርደራቸዉን ማረጋገጥ በክለሳ ወቅት
የምናረጋግጠዉ ተግባር ነዉ፡፡
በአጠቃላይ መምህራን ምንም እንኳ የፈተና ጥያቄወቻቸዉን ከላይ የሰፈሩ የፈተና አዘገጃጀት ህግጋትን መሠረት
አድርገዉ ቢያዘገጇቸዉም ፈተናዉን ከመፈተናቸዉ በፊት ራሳቸዉ እንደተማሪዎች ሆነዉ መልሱን
ማዉጣት/መፈተናቸዉ በፈተና ጥያቄዎቻቸዉ ዉስጥ ጉልህ ስህተት እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ ጥያቄዉ ይህን ደረጃ ካለፈ
በኋላ በፈተና ወቅት በየክፍሉ በመዘዋወር ማስተካከያ /Correction/ መስጠት የፈተና አዘገጃጀት ህግጋትን የሚቃረን
ተግባር ነዉ፡፡
ከፈተናዉ በፊት ተፈታኞች ፈተናዉ ስለሚያካትተዉ የጥያቄ አይነት፣ ስለሚሸፍነዉ ይዘትና የትኩረት አካባቢ፣ በፈተና
ወቅት ስለሚያስፈልጉ ቁሳቁሶች፣ ስለፈተናዉ ቦታና ቀን መረጃ ሊኖሯቸዉ ይገባል፡፡
ፈተና ማረም
በዚህ ምዕራፍ ክፍል 3.1.2 እንደተመለከትነዉ የጽሑፍ ፈተና ጥያቄዎች ዉስን መልስ ያላቸዉና የማብራራት/ሠርቶ
የማሳየት ጥያቄዎች ተብለዉ ይከፈላሉ፡፡ በፈተና እርማት ሂደት ዉስን መልስ ያላቸዉ ለምሳሌ የእዉነት/ሐሰት፣
የማዛመድ፣ የአጭር መልስ መስጠት፣ የባለብዙ ምርጫ ጥያቄዎች ለማረም ብዙም የማያስቸግሩ ናቸዉ፡፡ ነገር ግን
የማብራራት ጥያቄዎች ተማሪዎች የፈለጉትን ሃሳብ እንዲጽፉ እድል ስለሚሰጡ እና እያንዳንዱ ተማሪ ጥያቄዉን
በተረዳበት አግባብ ዝርዝር ትንታኔ ስለሚሰጥ ለማረም በጣም አስቸጋሪ ናቸዉ፡፡
ዉስን መልስ የሚሹ ጥያቄዎችን ለማረም መምህራን መጀመሪያ የራሳቸዉን ትክክለኛ መልስ (Answer key) ማዘጋጀት
አለባቸዉ፡፡ ይህንን የመልስ ወረቀት መሠረት በማድረግም የተማሪዎቻቸዉን ስራ በፍጥነት ማረም ይችላሉ፡፡ አንዳንድ
ጊዜ የማረሚያ ስቴንስል (Scoring stencil) በመጠቀም የፈተና ወረቀቶች ይታረማሉ፡፡
የማብራራት/ሠርቶ የማሳየት ጥያቄዎችን ለማረም ግን ሁለት አይነት አስተራረሞችን ይጠቀማሉ፡፡
ሀ. አንጻራዊ መንገድ (Relative scoring)፡- የሁሉንም ተማሪዎች ምላሽ በማንበብ የስራዉን የጥራት ደረጃ መሠረት
አድርጎ በተለያዩ ምድቦች መመደብ፤ በዚህ ሂደት ተመሳሳይ መልሶች በአንድ ቡድን ዉስጥ ይመደባሉ፡፡ በመጨረሻም
የሌሎች ቡድኖችን ስራ ለማረም ጥያቄዉን የተሻለ የሞከሩትን ተማሪዎች (ምድብ አንድ) ስራ እንደ ትክክለኛ መልስ
በመቁጠር የሌሎች ምድቦች ስራ ይታረማል፡፡
ለ. ፍጹማዊ መንገድ (Absolute scoring) ፡ ይኸኛዉ የማረሚያ መንገድ ደግሞ የፈተና ወረቀቶችን ከማንበባችን
በፊት ትክክለኛ መልሶችን እናዘጋጃለን፡፡ በመቀጠል የእያንዳንዱን ተማሪ ስራ በቅድሚያ ከአዘጋጀነዉ መልስ ጋር
በማወዳደር ዉጤት እንሰጣለን፡፡
ዉጤት መመዝገብ
ከእርማት ቀጥሎ የሚመጣዉ ተግባር ዉጤት መመዝገብ ይሆናል፡፡ ከጽሑፍ ፈተና የሚገኘዉ ዉጤት አብዛኛዉን ጊዜ
የአጠቃላይ ተከታታይ ምዘና ተግባር በመሆኑ የተለያዩ አስተዳደራዊ ዉሳኔዎችን ለምሳሌ ከክፍል ክፍል ዝዉዉርን
ለመስራት ስለሚያገለግል አመዘጋገቡም በዚሁ አግባብ ይሆናል፡፡ ተማሪዎች! እናንተ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ ት/ቤቶች
በመሄድ መምህራን የጽሑፍ ፈተና ዉጤትን እንዴት እንደሚመዘግቡ መረጃ ይዛችሁ በመምጣት ለክፍል ጓደኞቻችሁ
አንጸባርቁ፡፡ ለበለጠ መረጃ መጽሐፍትን አንብቡ፡፡
ትዕዛዝ 1. በ’ለ’ረድፍ ያሉትን የተለያዩ የጥያቄ አይነቶች ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ በ”ሀ” ስር ከተዘረዘሩ የጥያቄ አይነቶች
ጋር በማዛመድ፣ ተዛማጁን የያዘውን ፊደል ከአዛማጁ በግራ ባለው ክፍት ቦታ ላይ ጻፍ/ፊ፡፡ አንድ ተዛማጅ
ሁለት ጊዜ ሊመረጥ (መልስ ሆኖ ሊጻፍ) ይችላል፡፡
ረድፍ-ሀ ረድፍ-ለ
_____1. ጥያቄዎችን ለማዘጋጀት ተመሳሳይ ጉዳዮች ማግኘት የግድ ይላል፤ ሀ. ማዛመድ
_____2. ሰፊ ይዘትን የሚሸፍኑ በብዛት ጥያቄዎችን ለማካተት አያስችልም፤ ለ. ማብራራት
_____3. ለአንድ አይነት ምላሾች የተለያየ ውጤት እንድንሰጥ ያደርጋል፣ ሐ. እውነት ሀሰት
_____4. መልስ ለመስጠት ተማሪዎች የሚፈጅባቸውን ጊዜ ይቆጥባል፣ መ. ባለብዙ ምርጫ
_____5. በማደራጀት ተማሪዎች በነጻነት ሃሳብ እንዲሰጡ ያበረታታል፣ ሰ. አጭር መልስ መስጠት
_____6. አማራጮች ተመሳሳዮች ካልሆኑ ጥያቄው ቀላል ይሆናል፣
_____7. በብዛት ስንጠቀምበት ተራ ሽምደዳን ያበረታታል፣
_____8. ከሌሎች በተሻለ ከፍተኛ የማሰብ ደረጃን ይለካል፣
_____9. በትንሽ ቦታ ሰፊ ይዘትን ለመሸፈን ያስችላል፤
_____10. ለማዘጋጀት ረጂም ጊዜን ይጠይቃል፣
ትዕዛዝ 2. እያንዳንዱን ጥያቄ በሚገባ ካነበባችሁ በኋላ የተብራራ መልስ ስጡ!
ጥያቄ 11: የሚከተሉትን ተግባራት ከቀዳሚው ወደ መጨረሻው የፊደል ተራውን በቅደም ተከተል አስተካክላችሁ አስቀምጡ፡
ሀ. ፈተና ማረም ረ. የፈተናውን ጥያቄዎች ጥራት መፈተሽ
ለ. ፈተና መፈተን ሸ. የፈተና ጥያቄዎችን ማዘጋጀት
ሐ. የፈተና ጥያቄዎችን መከለስ ቀ. የፈተና አይነትና ጥያቄዎችን ከቀላል ወደ ከባድ ማደራጀት
መ. የፈተና እቅድ ሰንጠረዥ ማዘጋጀት በ. የትምህርቱን ዓላማና ይዘት በዝርዝር መለየት
ሠ. የጥያቄውን አይነት መምረጥ
ጥያቄ 12፡ የሂሳብ መምህር የሆነው አያሌው ለሚያስተምረው ትምህርት አምስት ዋና ዋና ርዕሶች እንዳሉት በማረጋገጥ
በየርዕሶች ስር ያሉትን የትምህርቱን ዓላማዎች ከመርሃ ስርዐተ ትምህርቱ በዝርዝር ከለዬ በኋላ ትምህርቱን
አስተምሮ ሲጨርስ 50 ጥያቄዎችን የያዘ ፈተና በማዘጋጀት የተማሪዎችን መማር ለመመዘን ወስኗል፡፡
ፈተናውን ለማዘጋጀት እንዲረዳው የትምህርቱን ዓላማዎች ማስታዎስን፣ ማገናዘብን፤ እና መተግበርን
የሚመለከቱ በማለት በሶስት መድቧቸዋል፡፡ በተጨማሪም አምስት ዋና ዋና የትምህርቱን ርዕሶች (ሙሉ
ቁጥሮች፣ ክፍልፋዮችና አስርዮሾች፣ ልኬቶች፤ የጠለል ምስሎች እና ጠጣር ምስሎችን) ለማስተማር በቅደም-
ተከተል 12፤ 20፣ 16፣ 10 እና 8 በድምሩ 66 ክፍለ ጊዜያት እንደተመደበላቸው መርሃ-ስርዐተ-ትምህርቱን
በማየት አረጋግጧል፡፡ የተሰጠውን መረጃ መሰረት በማድረግ አያልው ሊያዘጋጀው የሚችለውን ዝርዝር
ሰንጠረዥ በሚከተለው ሰንጠረዥ ያሉትን ክፍት ቦታዎች በመሙላት አሳዩ
የአላማዎች አይነት/ፍረጃና ብዛት
ማስታዎስ ማገናዘብ ትግበራ
1 ሙሉ ቁጥሮች
2 ክፍልፋዮችና አስርዮሾች
3 ልኬቶች
4 የጠለል ምስሎች
5 ጠጣር ምስሎች
ድምር
ጥያቄ 13: የግለጹ ጥያቄዎች ከአማራጭ ሰጭ ጥያቄዎች በተሻለ ተመራጭ የሚሆኑት መቼ ነው?
ጥያቄ 14፡ የፈተና ጥያቄዎች ዝርዝር ሠንጠረዢን (Table of test specification) የማዘጋጀት ዋና ዋና ጠቀሜታዎች ምን ምን
ናቸው?