Professional Documents
Culture Documents
ከባንኮች ብድር ማግኛ መስፈርቶች
ከባንኮች ብድር ማግኛ መስፈርቶች
ሀ) ጊዜ ላይ የተመሰረተ ብድር፡-
የመክፈያ ጊዜ በየወሩ
ይህ የብድር ዓይነት ደንበኛ በባንክ ካስቀመጠው (ካለው) ገንዘብ በላይ እስከተወሰነ መጠን ድረስ
ለእለት እንቅስቃሴው ብር እንዲያወጣ ነው፡፡ ይህ የብድር ዓይነት በጊዜ ላይ ተመርኩዞ ከሚሰጥ
ብድር በሁለት ባህሪያት ይለያል፡፡
ምሳሌ፡–
የወለድ መጠን 9%
ድርጅትዎ የኦቨር ድራፍት የብድር ዓይነት ከተመቻቸለት በኋላ ባልጠበቁት ሁኔታ የገንዘብ እጥረት
ቢገጥምዎ የኦቨር ድሮዋል ብድር እንደገና ሊመቻችልዎት ይችላል፡፡ ሆኖም ግን ለዚህ ብድር
የሚከፍሉት የወለድ መጠን ከላይ ካየናቸው የብድር መጠኖች ከፍ ያለ ነው፡፡
ይህ ዓይነቱ ብድር ሸቀጦች ተገዝተው በግምጃ ቤት ውስጥ ከተከማቹ በኋላ የገንዘብ እጥረት
ሲያጋጥም እነዚህ ሸቀጦች እስከሚሸጡ ድረስ ለሚፈጠር የገንዘብ እጥረት ማቃለያ የሚሰጥ
ብድር ነው፡፡ ለዚህ ብድር በዋስትና መያዣነት የሚያገለግሉት እነዚሁ ሸቀጦች ናቸው፡፡
በክምችት ያሉትም ሸቀጦች በባንኩ እና በድርጅቱ በጋራ የሆነ ቁጥጥር ይጠበቃሉ፡፡ ከዚህ ክምችት
ውስጥ የተወሰነ ሲሸጥ ይኸው ገንዘብ ከነወለዱ ለባንኩ ይከፈላል፡፡
ይህ የብድር ዓይነት ቡና ላኪ ላልሆኑ ላኪዎች የሚሰጥ ብድር ሲሆን ይህም 80% የሚሆነውን
ዋስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ /የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚሰጥ ሆኖ ጥሬ እቃው ተገዝቶ
የምርት ሂደቱን ጨርሶ ያለቀለት ምርት ሆኖ እስከሚወጣ እና ተመልሶ ወደ ውጭ ለመላክ
እስከሚጫን ድረስ የሚያስፈልግ የገንዘብ እጥረት የሚሰጥ የብድር ዓይነት ነው፡፡
ይህ የብድር ዓይነት ለላኪዎች በመቶኛ ተሰልቶ የሚሰጥ ብድር ሲሆን በመቶኛ የሚሰላውም
እቃውን ልኮ ከሚሰበስበው ገንዘብ ላይ ነው፡፡
ይህ የብድር ዓይነት ላኪዎች ከሀገር ውጭ ባለ ገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚሰጥ ብድር ነው፡፡
ይህ የብድር ዓይነት ለቤት እና ለንግድ ግንባታ የሚሆን የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥም ይህንን እጥረት
ለማስወገድ የሚሰጥ ነው፡፡ ይህም የሚከፈለው በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ ብድር ይሆናል፡፡
ይህ የብድር ዓይነት አዲስ የብድር ዓይነት ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ በዱቤ ሽያጭ ለሚያከናውኑ
ነጋዴዎች ነው፡፡ በዚህን ጊዜ ድርጅትዎ የጥሬ ገንዘብ እጥረት ሲያጋጥመው የዱቤ ሽያጭ ውሉን
ለባንኮች በማቅረብ የሚሰጥ የብድር ዓይነት ነው፡፡
የዋስትና ማስያዢያ፡- ይህ ማለት አንድ ተበዳሪ ለሚበደረው ገንዘብ የሚያስይዘው ዋስትና ሲሆን
ይህም ተበዳሪው ባልተጠበቀ መንገድ የወሰደውን ብድር ሳይከፍል ቢቀር ባንኩ የያዘውን የዋስትና
ንብረት ሽጦ ገንዘቡን ይወስዳል፡፡
የዋስትና ማስያዢያ ሽፋን ንጽጽር፡- ይህ ንጽጽር ለዋስትና ያስያዙት ንብረት ከተበደሩት ገንዘብ
ጋር ያለው ንጽጽር ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ ያስያሪት ንብረት
ንጹህ ብድር/ ክሊን ሎን/፡- ይህ የብድር ዓይነት ማንኛውም የብድር ዓይነት ሆኖ የድርጅቱ/
የተበዳሪው/ ጥንካሬ እንጂ ያለው የማስያዢያ ዋስትና ግምት ወስጥ የማይገባበት ነው፡፡
ብድሩን እንደገና ማየት፡- ይህ ማለት የብድሩን ማብቂያ ጊዜ እንደገና መከለስ ሲሆን ይህም
የወለድ መጠኑን በመጨመርና በመቀነስ፣ የብድሩን መክፈያ ጊዜ እና መጠን በመቀየር ማስተካከል
ሲሆን ከዚህ በኋላ እንደገና የተሰራ የብድር አከፋፈል ሰንጠረዥ እንዲደርስዎት ይፈልጋል፡፡ ይህ
የሚጠቅመው
ባንኩ
ማንኛውም የኮንትራት ውል ያጠናቅቃል፣ ምዝገባ ያካሂዳል እንዲሁም የተያዘውን
ቋሚ ንብረት የኢንሹራንስ ሁኔታ ያጣራል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ
የተጨማሪ ክፍያ
የጥሬ ዕቃ ግዢ ብድር
ሕንጻ
ተሽከርካሪዎች
የንግድ ቤቶች
ተቀማጭ የባንክ ሂሳብ በመያዣነት የሚቀበላቸው
የማጠራቀሚያ ሂሳብ
ተንቀሳቃሽ ሂሳብ
የጊዜ ገደብ ተቀማጭ ሂሳብ
የጥሬ ዕቃ ግዢ ማረጋገጫ የማረጋገጫ ሰነድ
በስምምነት የሚቀበላቸው
የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነዶች
የመንግስት ቦንድ
የኢንሹራንስ ፖሊሲ የጥሬ ገንዘብ ዋጋ
ወለድ መጠን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዓመት ባበደረው ገንዘብ መጠን 7.5 በመቶኛ ወለድ
ይሰበስባል፡፡ ባንኩ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በማሰጠው መመሪያ መሰረት በወለድ መጠኑ
ሊለያይ ይችላል፡፡ ሌሎች ባንኮች እንደሚያደርጉት ሁሉ የእፎይታ ጊዜ እንደኘሮጀክቱ ባህሪይ
ታይቶ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ዓይነቶች፡-
የረጅም ጊዜ ብድር
ለ 20 ዓመት የሚቆይ ብድር ማንኛውንም የእፎይታ ጊዜ ጨምሮ
ከ 5-15 ዓመት ባሉት ጊዜያት ተከፍሎ የሚያበቃ ቋሚ የሥራ መስሪያ ካፒታል ብድር
የመካከለኛ ጊዜ ብድር
የሥራ ማስኬጃ ብድር፡- ይህም
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ መንግስት በሰጠው ትኩረት መሰረት ለመካከለኛ እና ለረጅም ጊዜ ወለድ
ቅድሚያ የሚሰጣቸው ዘርፎች፡-
ለግብርና
ለአምራቾች
ለላኪና አስመጪነት ብድር
ለንግድና አገልግሎት
ለግንባታና ኮንስትራክሽን
ለትራንስፖርት
ሕንፃዎች
ተሽከርካሪዎች
የንግድ ቤቶች
በመያዣነት የሚቀበላቸው ተቀማጭ ሂሳቦች
የቁጠባ ሂሳብ
ተንቀሳቃሽ ሂሳብ
በጊዜ ገደብ ተቀማጭ ሂሳብ
የጥሬ ዕቃ ግዢ ሰነድ
በስምምነት የሚቀበላቸው ሰነዶች
የመንግስት የግምት ቤት ሰነዶች (ትሬዠሪ ቢል)
የመንግስት ግዢ ቦንድ
የኢንሹራንስ ፖሊሲ ጥሬ ገንዘብ ዋጋ
የአክሲዮን ማህበር የምስክር ወረቀት
ዋስተና (ባንክ ወይም ግለሰብ)
የጥሬ ዕቃ ግዢ ሰነድ
በስምምነት የሚቀበላቸው ሰነዶች
የመንግሰት የግምጃ ቤት ሰነድ
የመንግሰት ግዢ ቦንድ
የኢንሹራንስ ፖሊሲ የጥሬ ገንዘብ ዋጋ
የአክሲዮን ማህበር የምስክር ወረቀት
ዋስትና (ባንክ ወይም ግለሰብ)
የባንኩ የብድር አገልግሎት ዋነኛ ተጠቃሚዎች በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር ንግድ የተሰማሩ
ነጋዴዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም በተጨማሪ ባንኩ ለሚከተሉት የንግድ ዘርፎች ብድር ይሰጣል፡-
7. ሕብረት ባንክ
የሚሰጣቸው የብድር ዓይነቶች፡- አንበባ ባንክ ብድሩን በማስፋት በሁለቱም ማለትም በጊዜ
ገደብ እንዲሁም በተጨማሪ ክፍያ ለባለሀብቱ (ኢንቨስተሩ) እና ለንግዱ ማህበረሰብ በማንኛውም
መስክ ቢንቀሳቀሱ የብድር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ዋነኛ የባንኩ አገልግሎቶች
የኦሮሚያ የሕብረት ሥራ ባንክ የብድር አገልግሎቱን በማስፋት በሁለቱ ማለትም በጊዜ ገደብ እና
በተጨማሪ ክፍያ በማንኛውም መስክ ለሚሰሩ የንግዱ ማህበር አባላት የብድር አገልግሎቱን
ይሰጣል፡፡ ዋነኛ የሚሰጣቸው አግልግሎቶች፡-
በአገርውስጥ ንግድ
በግብርና
በግንባታ
በውጭ ንግድ
በትራንስፖርትና በመሳሰሉት ለተሰማሩ ነጋዴዎች የብድር አገልግሎት ይሰጣል፡፡
የታገደ ጥሬ ገንዘብ
የእፎይታ ጊዜ፡- ከባንኩ የእፎይታ ጊዜ ለማግኘት ገንዘቡ ለታቀደለት መርሃ-ግብር መዋል አለበት፡፡
እስከ ዓመት የሚቆይ የእፎይታ ጊዜ ባንክ ይሰጣል፡፡
የክፍያ ጊዜ፡- በየወሩ ወይም በየዓመቱ ሊከፈል ይችላል እንዲሁም በአንድ ጊዜ ክፍያ ሊሆን
ይችላል፡፡
ባንኩ የሚያቀርባቸው የብድር ምርቶች፡- ብርሃን ባንክ በሀገራችን አዲስ ከተቋቋሙት ባንኮች
አንዱ ሲሆን በጊዜ ገደብ ብድርንና ከተቀማጭ ሂሳብ በላይ ተጨማሪ ክፍያ አገልግሎቶችን
በተለያዩ ዘርፎች ለሚሠሩ ነባርና አዲስ ደንበኞቹ ያቀርባል፡፡ ባንኩ የሚሰጣቸው ዋና ዋና የብድር
አገልግሎቶች አብዛኞቹ የንግድ ባንኮች ከሚሰጧቸው ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡
የማስያዣ ሽፋን መጠን፡- እያበበ ያለ ንግድ ከሆነ ያለዎት ከጠየቁት ብድር 20% ያህሉን
በማስያዣነት ሊጠየቁ ይችላሉ፡፡
የንግድ ዕቅድን ማቅረብ፡- የንግዱ ዳራ፣ በገቢና ወጪ ማመሳከሪያ (በባላንስ ሺት) የተደገፈ የመጪ
ጊዜ የገንዘብ ዕቅድ፣ የገንዘብ ፈሰትና የገቢ መግለጫዎች የተካተቱበት የንግድ ዕቅድ ያስፈልጋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የታሰበው ንግድ የፍላጎትና የአቅርቦት መጠን ሊገለፅ ይገባል፡፡
ለተበዳሪው የሚሰጥ ምክር፡- ብድሩ ተከፍሎ እስከሚያልቅ ድረስ ብድሩን ከታሰበለት ዓለማ ውጪ
መጠቀም አሳሳቢ እንቅስቃሴ ነው፡፡
ለጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ድርጅቶች የተዘጋጀ ልዩ መመሪያ፡- እስከ አሁን ድረስ በባንኩ ለንግድ
ድርጅቶቹ የሚሠራ ልዩ መመሪያ የለም፡፡ ነገር ግን ብርሃን ባንክ ከጀርመን ድርጅት ጋር ስምምነት
ተፈራርመው ለንግድ ድርጅቶቹ ከፊል የብድር አገልግሎት ከሚሰጡት ባንኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
ባንኩ የሚያቀርባቸው የብድር ምርቶች፡- ቡና ባንክ በሀገራችን አደስ ከተቋቋሙት ባንኮች አንዱ
ሲሆን የጊዜ ገደብ ብድርንና ከተቀማጭ ሂሳብ ተጨማሪ የሚከፈል አገልግሎትን በተለያዩ ዘርፎች
ለሚሠሩ ነባርና አዲስ ደንበኞቹ ያቀርባል፡፡ በምርት ዓይነትና በዘርፍ ባንኩ የሚሰጣቸው ዋና ዋና
የብድር አገልግሎቶች እላይ ከተጠቀሰው የኦሮሚያ የህብረት ሥራ ባንክ ኢ.ማ ከሚሰጣቸው ጋር
ተመሳሳይ ናቸው፡፡
የማስያዣ ሽፋን መጠን፡- ቡና ባንክ ማስያዣ ሲያቀርቡ ማስያዣዎ ከ 85% እስከ 115% ሊገመት
ይችላል፡፡
የብድር ሒደት አንቅስቃሴዎችና መስፈርቶች፡- እላይ ከተጠቀሰው ከብርሃን ዓለም አቀፍ ባንክ
አ.ማ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡
ባንኩ የሚያቀርባቸው የብድር አይነቶች፡- አዲስ ባንክ የጊዜ ገደብ ብድርንና ከተቀማጭ ሂሳብ
ተጨማሪ የሚከፈል አገልግሎትን በተለያዩ ዘርፎች ለሚሠሩ ነባርና አዲስ ደንበኞቹ ያቀርባል፡፡
የኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ከሚያቀርባቸው የብድር አገልግሎቶች በተጨማሪ አዲስ ባንክ
ከመተማመኛ ሰነድና ከሽያጭ ኮንትራት ቅድሚያ የሚሰጡ አገልግሎቶች (አድቫንስ አጌንስት
ሪቮኬብል ኤልሲ እና አድቫንስ አጌንስት ሴልስ ኮንትራክት) አሉት፡፡
የእፎይታ ጊዜ፡- ለመሥሪያ ካፒታልነት የተለቀቀ ብድር ላይ ምንም የእፎይታ ጊዜ የሌለ ሲሆን
ለግንባታ ግን እስከ አንድ ዓመት የእፎይታ ጊዜ ይሰጣል፡፡
የማስያዣ ሽፋን መጠን ከአዲስ ባንክ ብድር ለማግኘት ያቀረቡት ማስያዣ በ 95%፣ 90%፣ 70%
እና 65% ቅናሽ ሊኖረው ይችላል፡፡ ለምሳሌ፡- ሕንፃው አደስ ከሆነ ከፍተኛው ቅናሽ የሆነውን 95%
ሊያገኝ ይችላል፡፡
የግብአት ብድር “ “
አዲስ ለሚጀምሩ ንግዶች ለማበደር ያለ ፈቃደኝነት፡- ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያቋረጡ፣ የካሌጅ
ተመራቂዎችና ተመሳሳይ ቡድኖች
የቁጠባ አይነቶች፡- የቁጠባ ደብተር ሂሳብ (6% ወለድ) እና የጊዜ ተቀማጭ (6-7%)
የብድር አገልግሎቶች/ምርቶች፡-
1ኛ እስከ 2000
2ኛ 3000
3ኛ 4000
4ኛ 5000
5ኛ 5000
1ኛ 5000
2ኛ 6000
3ኛ 7000
4ኛ 9000
5ኛ 10000
የብድር ጊዜ፡- ከፍተኛው የብድር ጊዜ 36 ወራት ሲሆን ዝቅተኛው የብድር ጊዜ ደግሞ 7 ወራት
ነው
የንግድ ዕቅድን ማቅረብ፡- አዲስ የብድርና ቁጠባ አ.ማ ተበዳሪዎች እንደ ንግድ ዕቅድ ሊያገለግሉ
የሚችሉ የማመልከቻ ፎርሞች እንዲሞሉ ይጠይቃል፡፡
ከፍተኛ
ዝቅተኛ ከፍተኛ የመድህን
የምርት የብድር የወለድ የአገልግሎት
መስፈርት መጠን መጠን መጠን/
ዓይነት ጊዜ መጠን ክፍያ
(በብር) (ብር) ዓመት
(ወራት)
በአነስተኛ
ንግድ፣ ምግብን
ጥቃቅን በሒደት ውስጥ
ብድር ማሳለፍ ወዘተ 700 5000 24 9% 2% 1%
የተሰማሩ
መነሻ ካፒታሉ
ከ 5000 ብር
በላይ የሆነ፡፡
አነስተኛ
የሥራ ዕድል
ብድር 5000 250000 36 9% 2% 1%
ለሚፈጥሩ
ንግዶች ቅድሚያ
ይሰጣል፡፡
በቡድን ማስያዣ
የፍጆታ ብድር ይሰጣል፡፡ 700 1000 24 10% — 1%
ብድር ለመንግሥት
ቋሚ ሠራተኞች
እንስሳት እርባታ፣
የግብርና
ማደለብ፣ ግብርና 700 250000 18 9% 2% 1%
ብድር
ወዘተ
ግለሰቦች፣
የጥቃቅን
ቡድኖች እና
ኪራይ — 250000 36 9% 2% 2%
የህብረት ሥራ
ብድር
ማህበራት
በማንኛውም
የአጭር ሕጋዊ ንግድ ላይ
30000 100000 6 1.5/ወር — 1%
ጊዜ ብድር የተሰማሩ
ግለሰቦች
የቤቱ ሕጋዊ
የቤት
ባለቤትነትና ቋሚ 700 50000 60 10% 2% 2%
ብድር
ገቢ
የጓደኛ ተፅዕኖ ማስያዣ፡ ይህንን የዋስትና አማራጭ የሚጠቀሙ የብድር ደንበኞች ከ 3 እስከ 5
አባላት ያሉት ቡድን ማቋቋም ይጠበቅባቸዋል፡፡ በዚህ አሠራር እያንዳንዱ የቡድን አባል
ማንኛውም የቡድን አባል ያልከፈለው ቀሪ ብድር ላይ ኃላፊነት ይወስዳል፡፡
ጥቃቅን የክራይ ብድር ዋስትና፡ በማንኛውም ሶስተኛ ወገን ወይም ደንበኛ በስምምነት ከተወሰነ
ቦታ ለማሽን/ለመገልገያዎች እንቅስቃሴ ከለላ የሚሰጥ ግለሰብ፣ ድርጅት ወይም ማንኛውም
ሌሎች ተቋማት
የግል ዋስትና፡ በቀጣሪው የጽሁፍ ስምምነት ላይ ተመስርቶ ብድሩ ለደንበኛው ይሰጣል፡፡ ልዩ ውሳኔ
ካልተሰጠ በስተቀር በዚህ መንገድ የሚሰጥ ብድር ከ 50 ሺህ ብር አይበልጥም፡፡
የንብረት ማስያዣ፡ በንብረት ማስያዣ ላይ ተመስርቶ ብድር ይሰጣል፡፡ የዚህ ዓይነቶ ማስያዣ
የተለያዩ አማራጮች አሉ፡-
የቁጠባ ማስያዣ፡ ሁሉም የተቋሙ የቁጠባ ደንበኞች ቁጠባቸውን እንደ ማስያዣ በመጠቀም
ብድር ሊወስዱ ይችላሉ፡፡ በዚህ መንገድ የሚሰጠው ብድር መጠን ከቁጠባው 125% በላይ መሆን
አይችልም፡፡
ቼክ ከሌላ ማስያዣ ጋር፡ ይህ ዓይነቱ ማስያዣ ለአጭር ጊዜ የብድር ዓይነት ብቻ ይፈቀዳል፡፡ በዚህ
አሠራር የብድር ደንበኛው ወይም ማንኛውም ሌላ ሰው ብድሩ ተከፍሎ ማለቅ ባለበት ቀን
ለአዲስ የብድርና ቁጠባ ተቋም የሚከፈል ቼክ ይፈርማል፡፡ ፈራሚውም በሒሳብ ውስጥ የተወሰነ
የገንዘብ መጠን በየብድሩ የጊዜ ገደብ ማለቂያ ላይ ማጠራቀም ይኖርበታል፡፡
የትምህርት ማስረጃ አብሮ ከሚፈርም ቤተሰብ ጋር፡ የቴክኒክና ሙያ ት/ቤት ወይም ማንኛውም
ሌላ የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂዎች የትምህርት ማስረጃቸውን እንደ ማስያዣ በመጠቀም
እስከ 5 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ሊበደሩ ይችላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኮሌጁ አዲስ የብድርና
ቁጠባ ተቋም እስኪነግረው ድረስ ለብድር ደንበኛው ዋናውን የትምህርት ማስረጃ ሰነድ
እንደማይሰጥ ለተቋሙ ለማረጋገጥ ፈቃደኛ መሆን አለበት፡፡ ከዚህም በላይ የብድር ደንበኛው
ቤተሰብ ኃላፊነት ለመውሰድ ፈቃደኛ መሆን አለበት፡፡
የመድህን ቦንድ፡ አንድ ደንበኛ ታዋቂ ከሆነ የመድህን ድርጅት የዋስትና ሽፋን ያለው ከሆነና
የመድህን ድርጅቱ ደንበኛው በተያዘው ዕቅድ መሠረት መልሶ መክፈል ባይችል ያልተከፈለውን
ቀሪ እንደሚከፍል የጽሁፍ ማረጋገጫ የሚሰጥ ከሆነ ደንበኛው የመድህን ሽፋኑን 75% እንዲከፍል
ይፈቀድለታል፡፡
ሕጋዊ ተቋማት፡ እድሮች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ወይም ማናቸውም ሕጋዊ ተቋማት
ብድር መውሰድ ወይም ዋስ መሆን ይችላሉ፡፡
ሌሎች አገልግሎቶች
የቁጠባ አገልግሎት
አስገዳጅ ቁጠባ፡ ይህ ቁጠባ የብድር ደንበኞችም ሆኑ የብድር ያልሆኑ ደንበኞች የተቋሙን የብድር
አገለግሎቶች ለማግኘት ብቁ ለመሆን ማድረግ የሚጠበቅባቸው ቁጠባ ነው፡፡ አስገዳጅ ቁጠባ
የደህንነትና ወርሀዊ ቁጠባ ሊሆን ይችላል፡፡
የኮንዶሚኒየም የቅድሚያ ክፍያ ቁጠባ፡ ለኮንዶሚኒየም ቤት የተመዘገቡና ቢደርሳቸው የቅድሚያ
ክፈያውን ለመክፈል አቅም የሚያጥራቸው ሰዎች ለዚህ ዓላማ በተቋሙ ቁጠባ ያላቸው ከሆነ
ብድር ይሰጣቸዋል፡፡ ደንበኛው የአስገዳጅ ቁጠባውን 1% በየወሩ ቢያንስ ለ 12 ወራት መክፈልና
የቅድመ ክፍያውን ቀሪ በአንዴ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
ተበዳሪ ደንበኞች፡- ሁሉም የተቋሙ ደንበኞች ለብድሩ የተሰጣቸውን የሒሳብ ደብተር በመጠቀም
በመደበኛነትም ሆነ በሌሎች መንገዶች በተቋሙ ቁጠባ ሊያካሒዱ ይችላሉ፡፡
የቁጠባ ሳጥን፡- ተቋሙ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ደንበኞች ከእንጨት የተሰሩ የቁጠባ ሳጥኖችን
ያቀርባል፡፡ ይህ አገልግሎት የቀን ገቢያቸውን የተወሰነ መጠን ሊያጠራቅሙ የሚፈልጉ ግለሰቦችና
ትናንሽ የንግድ ድርጅቶች ላይ የሚያተኩር ነው፡፡
የማስቀመጫ ጊዜ፡- ቢያንስ ለሶስት ወራት የተጠራቀመ ቁጠባን ይመለከታል፡፡ በመሆኑም ቁጠባው
በዓመት ቢያንስ 4.5 በመቶ ወለድ ይጨምራል፡፡
የንብረት መድህን፡- ይህ መድህን የቤት ብድር ደንበኞችን የሚሸፍን ነው፡፡ የመድህን አገልግሎቱ
የሚሰጠው ቤቱ ላይ አደጋ ሲደርስ ወይም ተበዳሪው ሲሞት ነው፡፡ የዚህ መድህን ተጠቃሚዎች
የብድሩን 2 በመቶ በዓመት መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡
የፈንድ አስተዳደር፡- ጡረታ የወጡ የመንግሥት ሠራተኞች የማህበራዊ ደህንነት ፈንድ ክፍያ፣
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የአገልግሎት ክፍያ ስብሰባ፣ መንግሠታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ዓለም
አቀፋዊ መንግሥታዊ ኤጀንሲዎች ፈንዶችን ማስተዳደር እና ሌሎች ከዚህ ጋር የተያያዙ
አገልግሎቶችን የሚያካትቱ የሦስተኛ ወገን የፈንድ አስተዳደር አገልግሎቶች በፈንድ አስተዳደሩ
ስር ይካተታሉ፡፡ ዝርዝር ስምምነቶቹ በተቋሙና በሦስተኛው ወገን መካከል ይደረጋሉ፡፡
ተዛማጅ ገፆች
የራስዎን ሥራ ይጀምሩ
o የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
o መነሻ ገንዘብ
o ድርጅትዎን ይክፈቱ
የራስዎን ሥራ ያስተዳድሩ
o ድርጅትን ማስተዋወቅ
o የንግድ ወጭ ስሌት
o ገንዘብ አያያዝ
የራስዎን ሥራ ያስፋፉ
o ስለ ቫት፣ደረሠኝ እና ከቀረጥ ነፃ
ነፃ ጠቃሚ ሰነዶች
o የመንግስት ተቋማት
o ባንኮች
o ኢንሹራንሶች
o ነፃ ኦንላይ ኮርሶች
ስኬታማ ታሪኮች
o ለማሸነፍ የተቀባ
o በተተከለበት የሚያድግ
o የነካው ሁሉ ወርቅ
o ታሪክ
o ሳይኮሎጂ
Search
Search for:Search …
Recent Posts
Archives
April 2020
October 2019
April 2019
February 2019
የብድር አሰጣጥ ሂደቶች ከባንክ ባንክ የተለያዩ እንደመሆናቸው የብድር መመሪያዎችና ፖለሲዎችም እንዲሁ
ከተቋም ተቋም በተወሰነ ደረጃ የተለያዩ ናቸው፡፡ ነገር ግን ባንኮች የብድር ማመልከቻ ከመቀበል ጀምሮ ደንበኛ
ወይም ተበዳሪ የሚፈልገውን የብድር መጠን ለመፍቀድ እንዲሟላ የሚፈልጉት፣ የጋራ መሠረታዊ ቅድመ
ሁኔታዎች እንዲሁም መስፈርቶች አሉ፡፡ አነዚህን መስፈርቶችና ጉዳዮች በሚገባ መገንዘብና አስፈላጊውን
ቅድመ ሁኔታ በሂደት ማሟላት የብድር ጥያቄ ውድቅ እንዳይሆን ከማገዝ ባለፈ፣ የሚፈለገውን የብድር መጠን
ሳይቀናነስ ከባንኮች የማግኘት ዕድልን ያሰፋል፡፡ በተጨማሪም የብድር ጥያቄ ከቀረበ በኋላ አስፈላጊ ሰነዶች
እንዲሁም ቅድመ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው ምክንያት በመመላለስ የሚባክነውን የአበዳሪ ተቋሙንም ሆነ
ከሌሎች የብድር ተቋማት በተለየ ሁኔታ፣ ባንኮች ከተለያየ አቅጣጫ ሊመጣ የሚችል አደጋን (Risk) ለመለየትና
ብድሩ አደጋ ላይ እንዳይወድቅ (Credit Risk) ቀድሞ ለመከላከል፣ በርካታ ገንዘብ-ነክ እና ገንዘብ-ነክ ያልሆኑ
የትንተና መሣሪያዎችንና ዘዴዎችን (Trend Analysis, Ratio Analysis, Fund Flow & Cash Flow Analysis,
SWOT Analysis, Business Plan Analysis, PESTEL, 5C’s, Market Analysis etc) ይጠቀማሉ፡፡
እንዲሁም የብድር ትንተናና ግምገማ ጥልቀትና ስፋቱ እንደ ብድሩ ዓይነትና መጠን እንዲሁም ድርጅቱ
እንደሚገኝበት ዘርፍ የተለያየ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ የብድር ጥያቄው ለአዲስ ፕሮጀክት ወይም ለነባር ፕሮጀክት
ማስፋፊያ በሚሆንበት ወቅት፣ ተበዳሪው ከሚያቀርበው የአዋጭነት ዝርዝር ጥናት በመነሳት ለሌሎች ብድሮች
ከሚደረገው የመመዘኛ ትንተና በተለየ ወይም በተጨማሪ ስለ ገበያ ሁኔታ፣ በፍላጎትና በአቅርቦት መካከል ስላለው
አቅርቦት መኖር፣ ስለ ምርቱ ወጪና ዋጋ፣ ስለ ህጋዊነቱና ትርፋማነቱ፣ በአጠቃላይ ስለ ንግዱ አዋጭነትና
ቀጣይነት ሠፊና ጥልቅ ጥናት ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም እንዲቀርቡ የሚፈለጉት ሰነዶች
እንዲሁም እንዲሟሉ የሚጠበቁት መስፈርቶች ለባንኮች የብድር ትንተና ግብዓትነት የሚያገለግሉ ወይም
የሚወሉ ናቸው፡፡
ሌላው አበዳሪ ተቋማት በብድር አሠጣጥ ሂደት ያላቸው የትኩረት አቅጣጫ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ አነስተኛ የብድር
ያተኮረ ሂደት የሚከተሉ ሲሆን፣ ባንኮች በበኩላቸው የሚሠጡት ብድር ንብረትን በመያዝ ስጋቱ (Risk)
እንዲሸፈን ቢፈልጉም፣ ዋና ትኩረታቸው ግን አስተማማኝ የገንዘብ ፍሰት (Cash Flow) መኖሩ ላይ ነው፡፡
ስለሆነም የተበዳሪውን የገንዘብ ፍሰት ትንበያን በመተንተን ተበዳሪው በየወቅቱ የሚኖረውን የመክፈል አቅም
ይመዝናሉ፡፡ በአጠቃላይ ለባንኮች የብድር መያዣ፣ ከደንበኛው የመክፈል አቅምና ፍላጎት እንዲሁም የንግዱ
አዋጭነት ቀጥሎ የሚመጣ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እንዲሁም በርካታ የብድር አገልግሎቶች የመኖራቸውን
ያህል እያንዳንዱ የብድር አገልግሎት የራሱ የሆነ (Specific) ተጨማሪ ቅድመ ሁኔታዎችን፣ መስፈርቶችንና
ሰነዶችን ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም፣ ለዛሬ እንደ መነሻ ንግድ ባንኮች በብድር አሠጣጥ ሂደት በመሠረታዊ ደረጃ
ትኩረት የሚየደርጉበትን ጉዳዮች፣ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሁም የሚከተሉትን የብድር አሠጣጥ ሂደትን ብቻ
ከብድር ክፍያው ጋር በተገናኘ ባንኮች መረዳት ከሚፈልጉት ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋነኛው የተበዳሪው የብድር
ታሪክ (Credit history) ሲሆን፣ በዚህም ከዚህ በፊት ምን ዓይነት የብድር ልምድ እንዳለው፣ ከየትኞቹ ተቋማት
እንደተበደረ፣ ምን ዓይነት ብድር እንደወሰደ፣ የብድር ክፍያውን በወቅቱ ይፈፅም እንደነበረ፣ ከዚህ በፊት ተበድሮ
ሙሉ በሙሉ የዘጋቸው ብድሮች መኖራቸውን ጭምር የሚዳሰስበት ሲሆን ይህንንም አሁን ላይ የእንዳንዱ
ተበዳሪ ዝርዝር መረጃ (Credit Information)፣ ከጋብቻ ሁኔታ ጀምሮ፣ ምን ዓይነት ብድር መያዣ እንዳቀረበ፣
የት ባንክ ላይ ምን ዓይነት ብድር እንደጠየቀና አሁን ላይ ምን ያህል ያልተከፈለ ቀሪ የብድር መጠን እንዳለበት፣
የብድሮቹ ጤነኝነት ጭምር በብሔራዊ ባንክ የብድር መረጃ ቋት ውስጥ ስለሚገኝ፣ ከብድሩ ጋር የሚነካኩትን
ግለሶቦች (ያገባ ከሆነ የባለቤቱን እንዲሁም የብድር መያዣ ንብረቱን ዋቢ አድርጎ የሚያቀርብለትን ግለሰብ)
የታክስ መለያ ቁጥር በመጠቀም መረጃዎችን ለማግኘት የሚችሉበት አሰራር በመኖሩ፣ ባንኮች ተበዳሪው ለብድር
እያንዳንዱ ከብድር ጋር የተገናኘ እንቅስቃሴ፣ ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ማካሄድ እና ተበዳሪው ቃል በገባውና
ብድር ውል ላይ በሰፈረው መሠረት ክፍያዎችንና ግዴታዎችን በአግባቡ መፈጸም፣ ከማንኛውም አበዳሪ ተቋም
ጋር በቀጣይ ለሚኖር የብድር ግንኑነት ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ በርግጥ ከፀባይ ጋር በተገናኘ በዚህ ብቻ አይወሰንም፡፡
ሌሎች የተበዳሪው ግልጽነት፣ መረጃ የመስጠት ፍላጎት፣ የትብብር መንፈስ፣ ክህሎት፣ የግል ታሪክ እና ዝና
ምንም እንኳን ባንኮች የሚከተሉት ገንዘብ ፍሰት ላይ ትኩረት ያደረገ (Cash-flow based lending) አካሄድ ነው
ተብሎ ቢታሰብም፣ እስከተቻለ ድረስ የብድር መያዣን እንደ ሁለተኛና የመጨረሻ አማራጭ ሲገለገሉበት
ይታያል፡፡ የብድር መያዣ፣ አንድ ተበዳሪ ለተበደረው ገንዘብ ዋስትና ወይም ብድሩ ስለመከፈሉ መተማመኛ ይሆን
ዘንድ የሚያቀርበው ወይም የሚያስይዘው ንብረት ሲሆን ይህም በዋናነት ቤት፣ ህንፃ፣ ማሽን፣ መጋዘን፣
የማምረቻ ቦታ እንዲሁም መኪና ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህም ተበዳሪው በራሱ ስም የተመዘገበ ንብረትን
በመያዣነት ሊያቀርብ የሚችል ሲሆን በተጨማሪም ለሚበደረው ብድር ሌላ በሶስተኛ ወገን ተመዝግቦ የሚገኝ
ንብረትን ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ባንኮች፣ የብድር መያዣው በማንና በምን ይዞታ ላይ እንደሚገኝ እንዲሁም አሁን
ላይ በገንዘብ ምን ያህል ይገመታል የሚለውን ጥያቄ የተለያዩ ባለሙያዎችን በመጠቀም የሚያስጠኑ ሲሆን፡፡
ለዚህም ባንኮች ለእያንዳንዱ የብድር መያዣ ንብረት የራሳቸው የሆነ የሚመሩበት የግምት መመሪያ (Valuation
Manual) አላቸው፡፡ መመሪያውም፣ ለምሳሌ ንብረቱ ማሽን ከሆነ ለተለያዩ ዓላማዎች የሚውሉ በመኖራቸው
ምክንያት የትኛው ማሽን ተቀባይነት ይኖረዋል (ከተመረተ ምን ያህል ጊዜ) ከሚለው ጀምሮ በርካታ ዝርዝር
ነገሮች የተቀመጡበት ነው፡፡ ከብድር መያዣ ጋር በተገናኘ ከባንኮቹ የግምት መመሪያ በተጨማሪ በብሔራዊ ባንክ
በኩል የተቀመጠ ሁሉም ባንኮች የሚተዳደሩበት የበላይ የሆነ መመሪያም ይገኛል፡፡ ነገር ግን ንግዱ ከሚገባው በላይ
አዋጪ ሆኖ በተገኘ ጊዜና ሁኔታ እንዲሁም ከላይ የተጠቀሱት መስፈርቶች በበቂ ሁኔታ የተሟሉ ሆኖ ሲገኝ
3。ካፒታል (Capital)
ካፒታል አንድ የሚጠቁመው ነገር የድርጅቱ ባለቤት ለንግዱ ወይም ለሥራው ያለውን ቁርጠኝነት እና በሥራው
ያለውን መተማመን ሲሆን፣ ስለዚህም የድርጅት ካፒታል አስተማማኝና ሥራውን የሚመጥን ሆኖ እንዲገኝ
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የብሄራዊ ቁጠባችን ትንሽ መሆን ላይ ከፍተኛ የብድር ፍላጎት ተጨምሮበት በባንኮች እጅ የሚገኘው ገንዘብ
ውስን ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን ውስን የህዝብ ሀብት በአግባቡ ለመጠቀምም ጭምር ባንኮች አንድ ሌላ ማረጋገጥ
የሚፈልጉት ጉዳይ ቢኖር ብድሩ የሥራ ዕቅድ ላይ በተቀመጠው መሠረትና ባንኮቹ ለተስማሙበት ትክክለኛ
ዓላማ መዋሉን ነው፡፡ ለዚህም ተበዳሪው በብድር የሚያገኘውን ገንዘብ ለምን ዓላማ እንደሚያውለው፣ የጠየቀው
ብድር በምን መልኩ ጥቅም ላይ እንደሚውል፣ ብድሩን ቢያገኝ የድርጅቱ የገንዘብ ፍሰት ምን እንደሚመስል፣
ዘርፉ ውስጥ የሚኖረውን የገበያ ድርሻ፣ በምን ስልት ዕቅዱን እንደሚያሳካ፣ የቢዝነሱ ዋና አቅራቢዎችና ደንበኞች
ማን እንደሆኑ እንዲሁም ሌሎች የሥራ ዕቅዱ ማካተት የሚኖርበትን ነገሮች ሁሉ ባንኩን በሚያሳምን መልኩ
በሚገባ በጽሑፍ አዘጋጅቶ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ይህ የሥራ ዕቅድ ለብድርም ሲባል ብቻ ሳይሆን፣ አንድ ድርጅት
የግድ ሊኖረው የሚገባ እንደ የጉዞ ካርታ የሚያገለግለውና በየጊዜው ሊዘጋጅ የሚገባ በመሆኑ፣ የሥራ ዕቅድ
መጻፍና ማዘጋጀትን ልማድ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በአጠቃላይ የሥራ ዕቅድ ለባንኮች ዋናና ጠቃሚ የብድር ትንተና
ብድርን ለመክፈል የሚያስችል የገንዘብ ፍሰት ወይም ሃብት መኖሩን ማረጋገጥ ሲሆን ይህንንም የዕዳ ክፍያን
ከገቢ ጋር በማነፃፀር የሚታይ ነው፡፡ ለዚህም የገንዘብ አስተዳደር ስርዓትን በየጊዜው ማሻሻልና ማጠናከር ተገቢ
ነው፡፡
ባንኮች የደንበኞችን የብድር ስጋት ደረጃ ለመለየት የሚጠቀሙበት ስርዓት ሲሆን፣ በዋናነት ተበዳሪው ወይም
ደንበኛው በብድር ውሉ መሠረት ቃል የገባውን ግዴታ ሳይወጣ ቢቀር ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት (loss)
የሚመዝኑበት ነው፡፡ በውስጡም የተበዳሪ ድርጅቱ አስተዳደር ስጋት (Management Risk) ጨምሮ፣ ከዚህ ጋር
በተገናኘም በድርጅቱ ውስጥ ተተኪ ወይም የመተካካት ዕቅድ (Succession Plan) መኖሩን፣ ተተኪው አሁን ላይ
በድርጅቱ ውስጥ የሚገኝበት ቦታ፣ በአስተዳደሩ ላይ የሚገኙ ግለሰቦች ከሥራው ጋር የተገናኘ ልምድና
የትምህርት ዝግጅት፣ ለድርጅቱ ስልት (Strategy) ስኬት አስፈላጊ የሆነው የሠራተኛውና የአስተዳደሩ ግንኙነት፣
የደንበኛው የገንዘብ አስተዳደር ስርዓት ጥንካሬ፣ የሒሳብ መግለጫ (Financial Statement) ጥራት፣ የደንበኛው
ታማኝነትና የትብብር መንፈስ፣ እስከ አሁን ድረስ ያለው የብድር ሒሳብ አጠቃቀም፣ ድርጅቱ የሚገኝበት ዘርፍ
በምን ሁኔታ እንደሚገኝ፣ የገበያ ፉክክሩ እንዲሁም የገበያ ድርሻው እና የድርጅቱ አጠቃላይ የሥራ አከናወን
(Business Performance) ተገምግሞ ደረጃ ወይም ነጥብ የሚሠጥበት ሂደት ሲሆን ተበዳሪው ወይም ደንበኛው
እዚህ ጋር የሚያገኘው ደረጃ ወይም ነጥብ (Score) የተለያዩ መብቶችና ጥቅሞች የሚያሰጠው ወይም
የሚያሳጣው ነው፡፡ ሆኖም የዚህ ውጤት ምንም ይሁን ምን ባንኮች ለሀገር ለወገን እጅግ ይጠቅማል ብለው
የሚያምኑበትን ብድር ወይም ተበዳሪ (Case) በመመሪያቸው ወይም በፖሊሲያቸው ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው በልዩ
የብድር ማመልከቻ
የተመዘገበ ቃለ ጉባኤ
የሽርክና ሰነድ
ዋስትና
ከላይ የተጠቀሱት ቅድመ ሁኔታዎችና ሠነዶች እንደ ብድሩ ዓይነትና አሰፈላጊነት ዝርዘሩ ሊጨምርና ሊያንስ
ይችላል፡፡ እንዲሁም አብዛኞቹ ባንኮች ለእያንዳንዱ የብድር አገልግሎት አስፈላጊ ሠነዶችና ቅድመ ሁኔታዎችን
በዝርዝር የያዘ ቼክ ሊስት (Check List) አዘጋጅተው የሚሠጡ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር በተገናኘ የተወሰኑ ባንኮች
ለደንበኞች ወይም ለተበዳሪዎች ልዩ አማካሪ (Financial Advisor and Relationship Manager) አላቸው::
አለማየሁ ስሜነህ