You are on page 1of 390

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

መልእክት አንድ
በምድሪቱ ሁሉ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ
ተፃፈ በኅዳር 7 ቀን 1998 ዓ.ም እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር
ይህ የመጀመሪያ የፈጣሪ ውሳኔ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል። ወይም ቢጫ መብራት የታየበት ሊባል ይችላል።

ማስታወሻ

»» መልዕክቱን በጥንቃቄ ያንብቡ


»» ለሌሎች ሲሰጡ ሁሉንም ገጾች ይስጡ። አይቀንሱ፤ አይጨምሩ፤ አያያሻሽሉ። ይህን የሚያደርጉ
አለቅጣት አይታለፉምና!
»» እኔ በነፃ እንደሰጠኋችሁ እናንተም በነፃ ስጡ፤ ፈቅዶ ወዶ ከሰጣችሁ ተቀበሉ። በረከቱ ይበልጣል
ካላችሁ አትቀበሉ።
»» ፋክስ አድርጉት፣ ኢሜይል አድርጉት፣ በድረገጾቻችሁ ልቀቁት፣ በፖስታም ላኩ።
»» በጋዜጣ በመጽሔት አትሙት፣ አሰራጩት በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን ልቀቁት።
»» እንደትእዛዙ ምክር ለማያደርጉ በትእዛዙ ውስጥ የሚገጥማቸውን ያንብቡ።
»» በጎ ለመሥራት ማንም ይከለከልም።
»» መሪ ሆነ ተመሪ ሁሉም የሚመዘነው እንደመፀፀቱና እንደ ቅን ተግባሩ ነው።
»» በጎ ሥራም የሚጀመረው ከትንሹ ነውና!

መልካም የመረዳት ንባብ ይሁንልዎ



ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

ማውጫ
መልእክት አንድ
በምድሪቱ ሁሉ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ማስታወሻ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ሀ/ በአንደኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ ጆሮአችሁን ከፍታችሁ አድምጡ! . . . . . . . . . . . . . . . 2
ለ/ በሁለተኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ! ጆሮአችሁን ከፍታችሁ አድምጡ! . . . . . . . . . . . . . . 8
ሐ/ በሶስተኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይመለከታል። . . . . . . . . . . . . . 9
መ/ ሌላው መልእክቴ ኢትዮጵያንና የሕዝቦቿን መጻኢ ሁኔታና እድል ይመለከታል። . . . . . . . . . . 10
ማጠቃለያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 13
ማስታወሻ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 14

መልእክት ሁለት
በምድሪቱ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ማስታወሻ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
በምድራችን ሁሉ ፊት ተበትኖ ለሚኖር መላው የአዳም ዘር በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . 2
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቃት ከወዴት እንዴት ወዴት . . . . . . . . . . . . . . . . . . 10
ይድረስ! ለፕሮቴሰታንት እምነት ተከታዮች ልብ ብላችሁ አድምጡ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
በእስልምና እምነት ውስጥ ላላችሁ ሁሉ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 13
ሴቶችና ዘመኑ፤ እንዲሁም መጻኢ እድላቸው! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 14
በዉጪ ስላሉ ኢትዮጵያዉያን!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ላለህ ወገኔ በሙሉ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16
የኢትዮጵያ ትንሳኤ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 17
ስለአሁኑ መሪዎቻችንና ስለ እጣፈንታቸው። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 19
አንድ ማሳሰቢያ ለመሪዎቻችን ልገልጽ እወዳለሁ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 21
ስለዚህ መልእክት መሰራጨት . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22

መልእክት ሦስት
በምድሪቱ ሁሉ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ማስታወሻ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
1–ሀ መግቢያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 2
ወደ መንደርደሪያ እንግባና . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 9
መላው የሰው ዘር ሁሉ ልብ ብላችሁ አድምጡ አስተውሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 10
ማሳሰቢያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 11
1 ስለ ሁሉም መልእክቶች የሰዎች አቀባበልና ምንነታቸው። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

1–ሀ በአንደኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች አቀባበል . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12


1–ለ በሁለተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
1–ሐ በሦስተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 13
1–መ በዚህ በአራተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 13
2. በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቃል ተመስርቶ በፈቃዱ ታዘው የቀረቡት መልእክቶች ማንን ይዳኛሉ? በማንስ
ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 14
3. ዓለም በጥቅሉ የሚገጥማት የቁጣ ፍሰት . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16
4. የእምነት ተቋሞች /በዳኝነት ሂደት ውስጥና/ እጣ ፈንታቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 17
4–ሀ ካቶሊክ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 17
4–ለ ፕሮቴስታንት . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 20
4–ሐ እስልምና። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 21
4–መ ቡዲሂዝም ኮንፊሽየስ፣ ሺንቶይዝም እና ሌሎችም ተዛማጅ እምነቶች . . . . . . . . . . . . . . . 21
4–ሠ ሂንዱይዝም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
4–ረ ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
4–ሰ ተዋህዶ ኦርቶዶአክስ እምነትና ቤተ ክርስቲያን . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
5. አሕጉሮች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 24
5–ሀ ሰሜን አሜሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 24
5–ለ ላቲን አሜሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 24
5–ሐ መካከለኛው ምሥራቅ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 25
5–መ አውሮፓ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 25
5–ሠ እስካንድኔቪያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 26
5–ረ ኤሽያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 26
5–ሰ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 26
5–ሸ አውስትራሊያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 27
6–ሀ አሜሪካ /ባቢሎን/ ካናዳ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 27
6–ለ ሜክሲኮ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 30
7–ሀ ኩባ፣ ኒካራጓ፣ ጓቲማላ፣ ኢልሳልቫዶር፣ ኮስታሪካ፣ ሆንዱራስ፣ ጃማይካ፣ ፓናማ፣ ሃይቲ፣ በሃማስ . 31
7–ለ ቬንዝዋላ፣ ኮሎምብያ፣ ሱማትራ፣ ፍሬንች ጊዋና፣ ኤኳዶር፣ ፔሩ፣ ብራዚል፣ ፓራጓይ፣ ቮሊቪ፣ ቺሊ፣
አርጀንቲና፣ ኡራጓይ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 32
8–1 ሶርያ፣ ኢራን . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 32
8–2 ሳውዲ አረቢያ፣ ኩዌት፣ ኢምሬትስ፣ ዱባይ፣ ኳታር፣ ኦማን፣ ባህሬን . . . . . . . . . . . . . . 32
8–3 እስራኤል . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
8–4 ሊባኖስ፣ ኢራቅና ቱርክ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
8–4ሀ ሊባኖስ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
8–4ለ ኢራቅ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

8–4ሐ ቱርክ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
9 ኤሽያ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 34
9–1 ራሽያ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 34
9–2 ታጃክሲታን፣ ኪርጊስታን፤ ሁዝቬክስታን፤ ተርኪሚስታን፤ ጆርጂያ፤ ካዛኪስታን፤ ቤላሩስ፡ . . . . 35
9–3 አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ሞንጎሊያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
9–3ሀ አፍጋኒስታን . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
9–3ለ ሞንጎሊያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
9–3ሐ አርሜንያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
9–3መ ቻይና . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 36
እጣዋ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 36
9–3ሠ በርማ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣ ቬትናም፣ ላኦስ፣ ሰሜን ኮርያ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ኔፓል . . . . . . 36
9–3ረ ጃፓን . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 36
እጣዋ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
10–1 አውስትራሊያ፣ ኒውዚላንድ፣ ፓፓው ጊኒያ፣ ፊጂ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
አሜሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ኒውዝላንድ፣ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
10–2 ማሌዥያ፣ ኢንዶንዢያ፣ ፊሊፒንስ፣ ታይዋን፣ ሲንጋፖር፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
10–3 ህንድ፣ ሲሪላንካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
11 አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 38
11–1 ምዕራብ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 38
11–2 ሰሜን አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
11–2ሀ ግብፅ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
11–2ለ ሊቢያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
11–3ሐ ቱኒዚያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
12 ማእከላዊ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
13 ምሥራቅ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 40
13–1 ሀገሬ ኢትዮጵያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 40
13–2 እምነትና ውጊያ በኢትዮጵያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 41
14–1 ደቡብ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 42
15 አውሮፓ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 43
15–1 እንግሊዝ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 44
15–2 ፈረንሳይ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 44
16 የምትወስደው እርምጃ እንደ ግለሰብ መዝ ዳዊት 18 /19 /8 – 9 . . . . . . . . . . . . . . . . . 45
17 ከቅጣት በኋላ የሚፈጠር መንፈሳዊና ሥጋዊ አኗኗር አስተዳደር ምን ይመስላል። . . . . . . . . . . . 47
18 ዓለም የተሸከመችው የጥፋት መሣሪያ እጣ ፈንታስ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 48
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

ሀ/ የተሸከሙትስ መሣሪያ እጣ ፈንታስ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 49


ለ/ ዓለም በማን ትመራለች ማእከሉስ የት ይሆናል? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 49
19 የአስተዳደር ማእከላት . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
20/ አስተዳደሮች ተዛምዶዎች በመንፈሳዊ ዐይን እንዴት ይጠራሉ። እንዴትስ መልካም ይሆናሉ። . . . . 51
21/ የመሪዎች ማረፊያ ማእከል የት የት ይሆናል? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 52
22/ በመላው ዓለም የሚፈሰው መንፈሳዊ አመራርና አገዛዝ ስርዓትና ፍሰት እንዴት ይሆናል . . . . . . 52
23 የመጨረሻው ማሠሪያ ቃልና ትእዛዝ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 55
24. በመጨረሻም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 56
25–ሀ የተፈጥሮ ኃይሎች፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 56
26.ለ. የኢኮኖሚ ቀውስ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 57
27.ሐ. የፖለቲካ ቀውስ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 57
28.መ. ማህበራዊ ቀውስ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 58
29.ሠ. ወታደራዊ መገልገያዎች፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 58
በእምነት መስመር ያሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 60
የውጭ መንግሥታት በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 60
ወጣቶች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 61
30. ማጠቃለያ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 61
31. ትእዛዝ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 62

መልእክት አራት
ለመላው ህዝበ ክርሰቲያን የተዋህዶ ልጆች በሙሉ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
በተዋህዶ እምነታችሁ በጽናት ለቆማችሁ በመላው ዓለም ፊት ለተበተናችሁ ሁሉ!! . . . . . . . . . . . 1
ለመላው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርሰቲያን ልጅ ለሆንክ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ . . . . . . . . . . . 2
በመላው ዓለም ተበትነህ፣ ከእውነት ጋር ቆመህ፣ በፈጣሪ ታምነህ፣ ተወደህ፣ ለበጎው ቀን በእግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስ ታትመህ ላለህ ወገኔ በሙሉ። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 2

መልእክት አምስት
የሚተነተኑ ርእሶች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 8
ቀደምት መልእክቶችን /1፣ 2፣ 3/ እናም መልእክት 4 / ለኢትዮጵያውያን የተዋህዶ ልጆች/ (ዓለምም
ኢትዮጵያውያንም እንዴት ተቀበሉት) . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 9
ከመልእክቶቹ መውጣት በኋላ ዓለም ምን ገጠማት! አሁንስ በምን ሁኔታ ላይ ትገኛለች! በመልእክቶቹ አንጻር
ቅጣቱ በምን መጠን እየተከናወነ ይገኛል! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 11
ከዚህ ሁኔታ በኋላ መጪው ምንድነው! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 14
ኃያላን መንግሥታትና ቀደምት የወጡትን መልእክቶች አቀባበላቸው፤ እንዲሁም ቀጣዩ እጣ ፈንታቸው። . 14
የተለያዩ የእምነት ተቋማትና ስለመልእክቶቹ ያላቸው አተያይ በመጪው ቀጣይ የ2ኛ ደረጃ የእሳት ማበጠሪያ
እጣ ፈንታቸው። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

ሀ/ ካቶሊክ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16
ለ/ ፕሮቴስታንት /መናፍቃን/ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 17
ሐ/ እስልምና . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 18
መ/ ቡዲሂዝም፤ ታኦይዝም፣ ሺንቶይዝም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 19
ሠ/ የተለያዩ እምነቶች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 19
ረ/ በመላው ዓለም ያሉ የተዋህዶ እምነት ተከታዮችን በተመለከተ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 19
6/ በዚህ ዘመን በመልእክቶቹ የፍርድ ሚዛን ውስጥ የወደቁት መሪዎችና ጭፍሮቻቸው በቀጣዩ እርምጃ ምን
ይገጥማቸዋል! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 20
7/ በመጀመሪያ ደረጃ የእሳት ወንፊት የተደረገ ብጠራና በቀጣዩ ሁለተኛ ደረጃ የእሳት ወንፊት መጪ ሁኔታ
በንጽጽር ሲታይ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 21
2ኛው ዙር የእሳት ወንፊት ከመጀመሪያው ጋር ሲነጻጸር ምን ይመስላል። . . . . . . . . . . . . . . . . 22
8/ አገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የእሳት ወንፊትና በመጭው ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ውስጥ . . 24
1ሀ/ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበት ሁኔታና በሁለተኛው የእሳት ወንፊት እጣዋ . . . . . . . . . 25
ትእዛዞች፤ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 27
2ለ/ በአገራችን ያሉ የተለያዩ እምነቶች በሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚጠብቃቸው እጣቸው። . . . . . 28
2ሐ/ የአገራችን ኢትዮጵያ ገዢዎችና ምንዝሮቻቸው በ2ኛው የእሳት ወንፊት ውስጥ /የነሱ ድጋፍ ሰጪ አዛዥ
መካሪዎችም/ እጣቸው። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 30
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 32
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 36
8ሠ/ እውነተኞቹ ኢትዮጵያውያን የተዋህዶ ልጆችና መጪው እጣቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
9/ አውሮፓና በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበት የመጀመሪያው እሳትና በሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚገጥማት
እጣ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 38
10/ ሰሜን አሜሪካ በመልእክቶቹ አንጻር በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ውስጥና በሁለተኛው የእሳት ወንፊት
የሚገጥማት እጣ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
ትዕዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 40
11/ ኤሽያ በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበት የመጀመሪያው የእሳት ወንወፊትና በአሁኑ የ2ኛው ዙር የእሳት
ወንፊት የሚገጥማት እጣዋ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 41
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 42
12/ አውስትራሊያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 43
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 43
13/ ደቡብ አሜሪካንና የካሬቢያን ደሴቶች በመጀመሪያው የእሳት ወንፊትና እንዲሁም በቀጣዩ 2ኛ ደረጃ
የእሳት ወንፊት የሚገጥማቸው እጣ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 43
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 44
14/ አፍሪካ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 44
15/ መካከለኛው ምሥራቅ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 46
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

16/ የእስካንዲኔቪያን ሀገሮች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 46


ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 46
17/ በተለይ ዓለምን ለመቆጣጠር በታለመ ኒዩክለር፣ ኬሚካል፣ ባዮሎጂካል፣ አልፎም በህዋ ላይ የተጠመዱ
የጨረርንም፣ የኒዩክለርንም መሳሪያ የታጠቁ አገሮች እጣ ፈንታ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 47
ትእዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 47
18/ ስለአባቶች እናቶች ስለወንድሞች፣ እህቶች፣ የተመረጡ የልዑል ባሪያዎች /አገልጋዮች/ ላይ የተፈጸመ
ጥቃትና ከልዑል የተሰጠ የቅጣት ውሳኔ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 48
19/ የእምነት መርከባችን /የኖኅ መርከብ/ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 49
20/ ትንሽ ምክር ለልዑል ባሮች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
21/ በመልእክቶቹ ስርጭት ላይ ስለሚሠሩ ጥፋቶች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
ትእዛዝ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
22/ ሺ ዘመን ምን ይላል፤ ምንስ ያስረዳናል! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 51
23/ ማጠቃለያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 54
ጥብቅ ማሳሰቢያ፡– . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 56
ተፈጸመ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 56

መልእክት ስድስት
መላው ዓለም ለምትገኙ የአዳም ዘር በሙሉ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
አዋጁ ከመቼ ጀምሮ ይፀናል። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 5
የኢትዮጵያ ሃገራችን ወቅታዊ ሁኔታ! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 7
ስለወቅቱ የዓለም ሁኔታ፤ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
ስለድንግል ፍርድ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 13

መልእክት ስምንት
መግለጫ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
በግንባርና በመጨረሻ ገጽ ያሉ ሥእሎች መግለጫ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
በግንባር ያለው ስእል ምንን ይናገራል? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
በጀርባው ያለው ስእል ምንን ያመለክታል? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ዓለምና የፍርድ ቃሉ ትናንት፤ ዛሬ፤ ነገስ ምን እንጠብቅ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 6
የዛሬዋ ዓለማችን ምን ትመስላለች፤ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 17
ዓለም ነገስ ምን ትመስላለች? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 20
አገራችን ኢትዮጵያና የፍርድ ቃሎቹ ትላንት ዛሬና ነገስ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
የትላንቷ ኢትዮጵያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 24
ቤተ ክርስቲያናችን / የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን/ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 33
ብርሃናዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ፦ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 34
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

2/ቤተ ክህነት ፦ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
3/ ቤተ ምርፋቅ /መማክርተ ካህናት ሲሆኑ የሁሉም የበላይ እራስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይሆናል።
ከፍም ዝቅም የሚል ነገር የለም። . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
ራስን ማስመለከና የውድቀት መንገዱ፤ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 37
በአገራችን በኢትዮጵያና በዓለምም የሚወሰድ ቀዳሚ እርምጃና ብርቱ የቅጣት ትእዛዞች!!! . . . . . . . 41
LIST OF MILITARY HARDWARES THAT ARE TARGETED IN THE FIRST DEGREE
PUNISHMENT AND OWNER COUNTRIES . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 49
USA . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 49
ENGLAND . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
FRANCE . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
CHINA . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
RUSSIA . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 50
ማጠቃለያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 54
ማሳሰቢያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 56
የደብዳቤዎች ምንነት መግለጫና መሸኛ ለሁሉም የአዳም ዘር በሙሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . 59
ምስጋና እና ክብር ለሥላሴ ይሁን! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 60
ምስጋና ለእናታችን ድንግል ማርያም ይሁን! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 60

የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
አሜን!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 1
ፈጥነው የሚፈፀሙ ከልዑል የተወሰኑባችሁ ቅጣቶችና ትአዛዞች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 15
ማጠቃለያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 16

መልእክት ዘጠኝ
የመልእክቱ መሠረታዊ ይዘትና ዓላማ! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 3
እነማናቸው የአውሬው አምላኪዎች? ይህንን በግልፅ ልታውቁ ይገባል። . . . . . . . . . . . . . . . . . 6
እስላም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 7
የቻይናዋ እና መሰሎቿ እምነቶች . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 8
ሕንድ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 8
እስራኤል ዘሥጋ እነማናቸው? ምንስ ማለት ነው? ለምንስ እነዲህ ተባሉ? . . . . . . . . . . . . . . . 10
እስራኤል ዘሥጋ ለምን አነሱ? ለምንስ ለትንሳኤው ሳይታመኑ ቀሩ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . 11
እስራኤል ዘነፍስ /ኢትዮጵያውያን/ ለምን ተባሉ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
እስራኤል ዘነፍስ ወይም ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት ነው? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 14
የቀደሙ አባቶች የእምነት አካሄድና ትምህርታቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን

የጥንት አባቶቻችን ሃይማኖት በአጭሩ ምን ነበር? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 23


ምንፍቅናና የኛ አባቶች መልስ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 25
በእውነትና በመንፈስ በማምለክና መንፈሳዊ ምሪት በተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ ምን ይመስላል? . . 27
ኢትዮጵያና ዓለም በንፅፅር! ዓለም ለምን ኢትዮጵያን ይጠላል? ይዋጋል? በአንድ ሃሳብ ቆሞ ይገዳደራል?
ሊያጠፋትም ይጥራል? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 30
እነዚህ በኢትዮጵያ ዙሪያ የሰፈሩ አገሮች እነማናቸው? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 31
በቤተል ለያዕቆብ የተገለፀው መሰላል የት ነው የተተከለው? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 32
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርሰቲያን ዛሬ እምን ላይ ነች? . . . . . . . . . . . . . . . . . . 35
ንቅለ ተከላ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
እነማን ይተከላሉ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 39
ንጉሥ – ነገሥት ቴዎድሮስ ማነው? ስለምን ዓላማ በእግዚአብሔር ታሰበ? የት ነው ያለው? ምንስ ይፈፅማል?
የት ነው የሚነግሰው? የትኛውን ግዛት ይገዛል? ይህ እውነት በማን ተገለፀ? አባቶችስ ስለዚህ ንጉስ ምን
አሉ? . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 42
በአንደኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 58
በሁለተኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 59
በሶስተኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 59
ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 65
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ!! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 65
አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 65
መግቢያ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 65
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስንል ምን ማለታችን ነው! . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 66
የሚፈሱት ቁጣዎች በምድር ላይ ምንን ያስከትላሉ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 70
መልእክት አንድ
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ህዳር 7 ቀን 1998 ዓ.ም ለሕዝብ የተገለጸ ዛሬ በ1/10/2000 በድጋሚ ላልደረሰው እንዲደርሰው የቀረበ

ይድረስ በምድር ላላችሁ የአዳም ዘር በሙሉ!!


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!
የፍጥረት ሁሉ ጌታ ስሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን!!
በምድሪቱ ፊት ሁሉ ተበትናችሁ ለምትኖሩ ሕዝቦች፣ በተለያየ ቋንቋና ዘር ነገድ ተከፋፍላችሁ፣ በአሕጉር
በአገር፣ በቀበሌ፣ በመንደር ለተበተናችሁ የሰው ዘር በሙሉ!!
በዚህ ዘመን ዓለምን ለምትመሩ መሪዎችና ገዢዎች፣ በምድሪቱ ሁሉ ባሉ የእምነት ተቋማት በመሪነት
በአስተዳዳሪነት፣ በሰባኪነት እናም በአደራጅነት፣ ለምትመሩ እንዲሁም እምነታችሁን በማስተማር ለተሰማራችሁ
የእምነት አባቶች ሁሉ!! ለጥበበኞች፣ ለፈላስፎች፣ ለጦር አለቆች፣ ለነገሥታቶች፣ ለዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣
መሪዎች። ዓለምን በጥበባችን፣ በሃብታችን በጉልበታችን እየገዛነው ነው ለምትሉ፤ በተለይ ለታላቋ አሜሪካ
(ባቢሎን) ከሷም ጋር ዘወትር ለሚያመነዝሩ ጋለሞታ ወዳጆቿ፣ አውሮፓውያን፣ ኤሻውያን፣ አረባውያን፣ ላቲን
አሜሪካውያን፣ አፍሪቃውያን፣ እንዲሁም በታላቋ ባቢሎን (አሜሪካና) አውሮፖውያን ተጠፍጥፈው ለተሠሩ
ህዳጣን ጋለሞታ መንግሥታት በሙሉ!!
በዚህ ክፉ ዘመን እራሳችሁን በታላቅ ፈተናና መከራ ውስጥ ለጣላችሁ፣ ስለእምነታችሁ፣ ስለፈጣሪያችሁ
መውደድና መታመን በታላቅ ጉዳት ላላችሁ የእግዚአብሔር ልጆች በሙሉ!!

እኔ ቃል ተመልቻለሁና በውስጤም ያለ መንፈስ አስገድዶኛልና በተሃ ጠጅ እንደተሞላና


ሊቀደድ እንደቀረበ አቁማዳ ሊፈነዳ እንደማይችል እንደ ወይን ጠጅ አቁማዳ እነሆ
አንጀቴ ሆነ ጥቂት እንድተነፍስ እናገራለሁ ከንፈሬን ገልጬ እመልሳለሁ
መጽሐፈ ኢዮብ 32፡ 18 – 20
ከላይ በእግዚአብሔር ቃል እንደተመለከተው ይህንን መልእክት እናገር ዘንድ ግድ ስለሆነብኝ እናገራለሁ።
ላለመናገር ላለመተንፈስ ከራሴም ከፈጣሪየም ጋር ተሟግቻለሁ። እንደ ዮናስም እምቢ ብያለሁ። ይሁንና
ከእግዚአብሔር ኃይል ጋር ተሟግቼ ስላልቻልኩ፣ እየከፋኝ ይህንን ትእዛዝ እፈጽም ዘንድ ግድ ሆነብኝ፤
ስለዚህም እነሆ እናገረው ዘንድ የሚገባኝን የዓለማችንን መጻኢ ሁኔታ እናገራለሁ።
ይህ ማስጠንነቀቂያና መፃኢ ፍርድ ይድረሳችሁ!!
እኔ እጅግ ታናሽ ኃጢአተኛ በእውቀትም ያነስኩ በኑሮዬም ምናምቴ ወዳቂ ኑሮ የምገፋ ነኝ። እናንተ
በድህነቷ የምታውቋት ኢትዬጵያ ዜጋና ድሃ ልጇም ነኝ።
መልእክቱ አራት ክፍሎች አሉት
1ኛ/ ለዘመናችን ጥበበኞች፣ ገዢዎች፣ ባለጠጎች፣ የኃጢአት ባለሃብቶች፣ አመንዛሪዎች፣ ግብረ ሰዶሞች
ነፍሰ ገዳዮች፣ ዘራፊዎች ነጣቂዎች፣ ድሃ አጥፊዎች በጥቅሉ የቀደመው እባብ (ዲያብሎስ) ልጆችና አገልጋዮች
በግልጽ በእግዚአብሔር ሕግና ስርዓት ላይ የማፍረስ ሥራ በመሥራት ፍፁም የጨለማን ሥራ ላነገሱ የዘመኑ
እባቦች ዘንዶዎችና ጊንጦችን ይመለከታል።

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

2ኛ/ በእምነት ካባ ተጠልለው በተለያየ የእምነት ተቋም ራሳቸውን ያደራጁትን ማለትም እንደ ካቶሊክ
ቤተ–ክርስቲያን፣ ኘሮቴስታንት፣ ኦርቶዶክስ፣ አንግሊክና እናም ሌሎች በክርስትና ስም ራሳቸውን ያደራጁ
ተቋማትን ይመለከታል። ሙስሊም፣ ቡዲሂዝም፣ ኮንፊሺያን፣ ሂንዱይዝም እናም ቁጥራቸው የበዛ የእምነት
ተቋማትን ይመለከታል።
3ኛ/ በምድሪቱ ላይ በሰፈነው ብርቱ ኃጢአትና ማእበሉ ዘወትር እየተሰቃዩ ላሉ የእግዚአብሔር ሕዝቦች
ይመለከታል።
4ኛ/ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ገዢዎቿን መጪውን እድሏን ይመለከታል። ባጠቃላይ ዓለምን በሥራና ተግባሯ
ተመስርቶ የሚጠብቃትን ቅጣትና ፍርድ ከዚያም ያለውን መፃኢ ሁኔታ የያዘ መልእክት የምታገኙ ሲሆን ይህንን
መልእክት ለመስማት ባትወዱትም ወይም ባትፈቅዱትም የማይቀር ስለሆነ ፍርዱ በራሳቸው ላይ የሚያርፍ
ይሆናል። የምትታመኑበት እውቀት፣ ጥበብ ብልጽግና ወይም የሃሰት አባታችሁ በፍፁም አያድናችሁምና
»» ለበደለኞች የሙት ፍርድ መርዶአቸውን የሚሰሙበት
»» ለመልካሞች የእግዚአብሔርን ታዳጊነትና የታመነ አባትነቱን የሚያረጋግጡበት ነው።

ሀ/ በአንደኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ ጆሮአችሁን ከፍታችሁ አድምጡ!

የዘመናችን ጉዶች ለመሆኑ እናንተ ማናችሁ! ይላል ጌታ እግዚአብሔር። ራሳችሁን ያሰማራችሁ በትእቢት
የተሞላችሁ ፍፁም የታበያችሁ ምድርንና ሰማይን የዘረጋውንና የፈጠረውን አምላክ የናቃችሁ እኮ እነማን
ናችሁ! የቀደመው እባብ ልጆች በፈጣሪ የተላገዳችሁ፣ እኮ እነማን ናችሁ! እስትንፋሳችሁ ባፍንጫችሁ ስር
የሆነች ብትያዙ የምትጠፉ ለመሆኑ ምንድን ናችሁ! አዎ ትቢያና ከንቱዎች የከንቱም ከንቱ ናችሁ። እስኪ ጌታ
የሚያጠይቃችሁን ስሙ!!

ውሆችን በእፍኙ የሰፈረ፣ ሰማይንም በስንዝር የለካ፣ የምድርንም አፈር በመስፈሪያ


ሰብስቦ የያዘ፣ ተራሮችን በሚዛን ኮረብቶችንም በሚዛኖች የመዘነ ማነው! የእግዚአብሔርን
መንፈስ ያዘዘ ወይስ አማካሪ ሆኖ ያስተማረው ማነው! ወይስ ከማን ጋር ተመካከረ!
ወይስ ማን መከረው! የፍርድንም መንገድ ማን አስተማረው! እውቀትንስ ማን
አስተማረው! የማስተዋልንስ መንገድ ማን አሳየው! እነሆ አሕዛብ በገንቦ እንዳለች
ጠብታ ናቸው። በሚዛንም እንዳለ ትንሽ ትቢያ ተቆጥረዋል። እነሆ ደሴቶችን እንደ
ቀላል ነገር ያነሳል። ሊባኖስ ለማንደጃ እንሰሶችም ለሚቃጠል መስዋእት አይበቁም።
አህዛብ ሁሉ በፊቱ እንዳልነበሩ ናቸው። ከምናምን እንደሚያንሱ እንደከንቱ ነገርም
ይቆጥራቸዋል።
እንግዲህ እግዚአብሔርን በማን ትመስሉታላችሁ! ወይስ በምን ምሳሌ ታስተያዩታላችሁ!
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 40፣12–19
ከላይ ለተጠቀሰው የእግዚአብሔር ቃል ምን መልስ አላችሁ! ምንም የምትመልሱት የለም ነገር ግን ከፈጣሪ
በላይ አዋቂዎች ሁሉን ሻሪ ሁሉን አጽኚ ሆናችኋል። የፈጣሪን ትእዛዝ የናቃችሁ ስለሆናችሁ በራሳችሁ ሕግ
የምትመሩ ናችሁ። የፈጣሪን ሕግ ሽራችሁ የራሳችሁን ሕግ ያጸናችሁ ናችሁ። በትእቢታችሁ በንግዳችሁ
በክህደታችሁ በመታበያችሁ ብዛት የሰው ዘር ከተፈጠረ ጀምሮ ያልታዩ አይነት ናችሁ።
ጌታ እንዲህ ብሎ አላዘዘምን! የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣ የአብርሃም አምላክ፣ የሙሴ አምላክ፣ የነኤሊያስ
አምላክ፣ የነጰውሎስ አምላክ፣ የነዮሐንስ አምላክ ይህንን ታላቅ ትእዛዝ አላዘዘምን!
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ አላለምን!

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

»» ከኔ በቀር ሌሎች አማልእክት አይሁኑልህ


»» የጌታ የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ
»» በላይ ከሰማይ ካለው በታችም በምድር ካለው ከምድርም በታች ከውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ
የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ አትስገድላቸው አታምልካቸውም በሚጠሉኝ እስከ ሶስተኛና
አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶቻችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ ለሚወድዱኝ ትእዛዜንም
ለሚጠብቁ እስከ ሺ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ፣ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ
አምላክ ነኝና፡ የምባላ እሳትም ነኝና
»» በከንቱ ስሜን የሚጠራውን ከበደል አላነጻውም
»» የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ። እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል አርፎበታልና!!
»» አባትና እናትህን አክብር፣ አትግደል፣ አታመንዘር፣ አትስረቅ፣ በባልንጀራህ ላይ በሃሰት አትመስክር፣
የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፣ ባልንጀራህን እንደ እራስህ ውደድ!!
ኦሪት ዘጸአት ምእራፍ 20፡ 1 – 17
ከላይ የተጠቀሱትን የፈጣሪ አምላካችንን ትእዛዝ፣ ናቃችሁ፣ ምንዝርናን እንደ ትክክል ሥራ አጸናችሁ
ፈቀዳችሁ፣ ተገበራችሁ፡ አልፋችሁ ተርፋችሁ ግብረ ሶዶምነትን አጸናችሁ። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አጋባችሁ፣
ተገበራችሁ ለእንስቶቹም እንዲሁ አደረጋችሁ ሴትን በቤተክርስቲያን ሰባኪ ጳጳስ አድርጋችሁ ሾማችሁ።
አትግደል የሚለውን የፈጣሪ ትእዛዝ ጥሳችሁ ለስልጣናችሁ፣ ለሀብታችሁ፣ ለጥቅማችሁ፣ ለክብራችሁ፣
ለንግዳችሁ፣ በትእቢት ተሞልቶ ከፍ ለማለት ላላችሁ ጥማት ስትሉ ገደላችሁ። እንዲያውም የመግደያ
መሳሪያዎቻችሁ አንድና ሁለት ሰው ከመግድል አልፈው በሚሊዮን የሚቆጠርን ሰው የሚያጠፉ መሳሪያዎች
ሰራችሁ። በዚህም ብዙዎችን በአንድ ጊዜ ገደላችሁ፤ ዛሬም እየገደላችሁ ነው። ዛሬ መገዳደልን እንደስልት በብዙ
ትተገብራላችሁ። አያት ቅድመ አያቶቻችሁን ከቃየል ጊዜ ጀምሮ ያስተማረው የቀደመው እባብ ጋድርኤል፤
ዛሬም በአንድ አቤል መግደል የጀመረውን ማስተማር፣ በሚሊዮን እንድትገድሉ አስተማራችሁ። ኒዩክለር፣
ኒዩትሮን፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል፣ ጄት፣ ቦምብ፣ ታንክ፣ ፈንጂ፣ መድፍ፣ ሚሳኤል፣ ምን ስፍር ቁጥር
አለው? ይህን ሁሉ ለሰው መጥፊያ ሰራችሁ። ገደላችሁበት እየገደላችሁም ነው። ለምን? ለስልጣን፤ ለክብር፤
ለሀብት፤ ለዝና!!
አትስረቅ፤ ይህን የጌታ ቃል ሁሉም ሰው የሚጥሰው ነው። በልዩ ልዩ መልክ ሰው ይሰርቃል። ያታልላል።
በሃሰት አትመስክር፤ ይህንንም የፈጣሪ ትእዛዝ እንዲሁ ሁሉም ሰው የሚጥሰው ነው። በየእለቱ ሰው አብዝቶ
ሲዋሽ ይውላል። እንዲያውም መዋሸትን እንደ እውቀት፤ እንደችሎታ ያየዋል። መሪዎች ገዢዎች አስተዳዳሪዎች
እንደዘዴ ዘወትር ይጠቀሙበታል። የፖለቲካ ጥበብ ብለው የውሸትን ስልት እንደ እውቀት ያጠኑታል። ህዝቡንም
ለመንዳት ለመግዛት ለማታለል ይጠቀሙበታል።
ባልንጀራህን መውደድ፤ በፍፁም በፍፁም እንክዋን ሊተገበር ከመሰረቱ የጠፋ ሆኖአል። እንዲያውም
ወንድሙን አጥፍቶ ንብረቱን ሚስቱን ይነጥቃል፣ ይዘርፋል።
እናትና አባትህን አክብር፤ የሚለው ትእዛዝ እንዲሁ ከተሻረ ቆየ። አባትና እናትን እንኳን ሊያከብር፣ ሊሰማ
በተገላቢጦሽ ፈራጅ ምክር ሰጪ አመራር ሰጪ ታናሽ እና ልጅ ሆኗል።
ሰንበትን አክብረው ቀድሰው የሚለውንም ትእዛዝ እንዲሁ እንደጅልነት ስለተቆጠረ ሰው ከሻረው ቆየ።
የፈጣሪን ስም በከንቱ አትጥራ፤ የሚለው አምላካዊ ቃልና ትእዛዝ ሽሮ በውሸት ይምላል። እንዲሁም
እንደዘዴና ብልሀት ተቆጥሮ በመሀላ የፈጣሪን ስም በመጥራት ለመነገድ ለማታለል እንዲውል ተደርጓል።
3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

በመጨረሻም ከኔ በቀር ሌላ አምላክ አታምልክ፤ እኔ ቀናተኛ አምላክ ነኝና! የሚለውን አምላካዊ ትእዛዝ
በመናቅ የሰው ዘር በተለያየ አምልኮ ተጠምዶአል። ይኸውም ገንዘቡን፣ እውቀቱን፣ ክብሩንና ጣኦትን
ያመልካል። ገንዘብ አምላኩ ነው፤ ስልጣን ምሽጉ ነው፣ እውቀት የኑሮ መመኪያው፣ የትዕቢት ምንጩ ነው።
ፈጣሪን የሚጠራው ለአፉ እና ለይምሰል ብቻ ነው። ፈጣሪን የሚጠይቀው ያቀደውን ሊፈጽም የወደደውን
እንዲያጸድቅለት እንጂ ፈጣሪ የፈቀደውን እንዲፈጽም አይደለም። ዛሬ የሚታየው እውነት ይኸው ነው።
የጥበብ መጀመሪያ ፈጣሪን መፍራት ነው። ይህም የሚገለጸው ሕጐችን በመጠበቅና በማክበር ወደተግባርም
በመለወጥ ብቻ ነው። በፍፁም ልብ፣ በፍፁም ሀሳብ፣ ለፈጣሪ በመታዘዝና በመገዛት፤ ብቻ ነው ፈጣሪን
መፍራታችን የሚገለጸው። ይህንን ተግባራዊ የሚያደርግ አንድስ እንኳን የለም።
ታዲያ እናንተ እባቦች ዓለምን በኃጢአት ባሕር አሰጠማችኋት፤ አንድም ስፍራ ሳይቀር ፍፁም የኃጢአት
ሥራ ነገሰ። እንደ ክብርም ታየ። በጨርቃችሁ ተሸፋፍናችሁ ስትታዩ ትልቅ ትመስላላችሁ፣ በየስልጣን
መንበራችሁ ስትታዩ ቅን ፈራጅ ትመስላላችሁ፤ ነገር ግን መቃብር ውጪው እንዲያምር ውስጡ ትል፣ ምስጥ
እንደመላው እናንተም እንደዚያ ናችሁ። ቤታችሁ ከተማችሁ ያምራል። ግን በውስጡ ያላችሁት እባቦች፣
ጊንጦች፣ አውሬዎች ናችሁና! ምድሪቷ ትሸከማችሁ ዘንድ አቃታት። በየብስ፣ በባሕር፣ በአየሩ ሁሉ የእናንተ
ክፉ ሥራ መላ። በየትኛውም የምድሪቱ ፊት የአባታችሁ የዲያብሎስ እባቡ እጅና እግር ያልደረሰበት ያልከበበው
የለም። እናንተ እንዴትስ ተሁኖ ከለመዳችሁት ከኖራችሁበት የኃጢአት ቤታችሁ ትወጣላችሁ? አትወጡም!
ባህሪያችሁ ሆኗል። የእባብ፣ የዘንዶ፣ የጊንጥ ልጅ ያው እባብ ዘንዶና ጊንጥ ነው። ተፈጥሮአችሁ ሰው ይሁን
እንጂ ተግባራችሁ ሁሉ የእባቡ ሥራ ነው። የሰራዊት ጌታ እግዜአብሔር ስለናንተ እንዲህ ይላል።

ምናልባትም መጠቀምም ትችዪ ወይም ታስደነግጪ እንደሆነ ከአስማቶችሽና፣


ከህጻንነትሽ ጀምረሽ ከደከምሽበት ከመተቶችሽ ብዛት ጋር ቁሚ። በምክርሽ ብዛት
ደክመሻል፣ አሁንም የሰማይን ከዋክብት የሚቆጥሩ፣ ከዋክብትንም የሚመለከቱ
በየመባቻውም የሚመጣውን ነገር የሚናገሩ ተነስተው ከሚመጣብሽ ነገር ያድኑሽ።
እነሆ እንደ እብቅ ይሆናሉ። እሳትም ይጥላቸዋል፤ ሰውነታቸውንም ከነበልባል ኃይል
አያድኑም፣ እርሱም ሰው እንደሚሞቀው ፍም ወይም በፊቱ ሰው እንደሚቀመጥበት
እሳት ያለ አይደለም። የደከምሽባቸው ነገሮች እንዲህ ይሆኑብሻል። ከህፃንነትሽ ጀምሮ
ከአንቺ ጋር ይነግዱ የነበሩ እያንዳንዳቸው ወደ ስፍራቸው ይሄዳሉ። የሚያድንሽ
የለም።
ትንቢት ኢሳይያስ 47፣ 12 – 15
ከላይ በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቃል እንደተነገረው የሚያድን የለም፣ የገነባችሁት ሁሉ ይፈርሳል ትቢያም
ትሆናላችሁ። ፋብሪካችሁ ከተማችሁ የስልጣኔ አውታራችሁ፣ ከትንሽ መንግሥትነት እስከ ትልቅ ኃያል
መንግሥትነት ለመድረስ የደከማችሁበት ሁሉ በምትታመኑበት እውቀት፣ ጥበብ፣ ስልጣኔ ድጋፍ አይድንም፣
ትቢያ ይሆናልና።

አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ፤ አህዛብንም


ያዋረድክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥክ፤ አንተም በልብህ ወደ
ሰማይ አርጋለሁ፣ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፣
በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፣ ከደመና ከፍታዎች በላይ አርጋለሁ፣
በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።
ትንቢት ኢሳይያስ 14፣ 12 – 14
አባታችሁ የቀደመው እባብ ህልሙ ከላይ በጌታ እንደተገለጸው ነው። እሱ ያስተማራችሁ ስለሆነ ዛሬ ምድርን
ለቃችሁ ጨረቃ ላይ ማርስ ላይ ከዚያም በላይ እንሂድ ብላችሁ፣ ቤታችሁንም እዚያ ልታደርጉ እየጣራችሁ
4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ነው። መሰሎቻችሁ ለሽርሽር እየሄዱ እየመጡ ናቸው። ነገ ከዚያ ለመኖር የሠሩት መንኮራኩር በየጊዜው
ይሄዳል ይመጣል። አባታችሁ ዲያብሎስ ከፈጣሪ በላይ ሊሆን አይደል እናንተስ የሱ ደቀ መዝሙሮች ከሱ ሃሳብ
በምን ትለያላችሁ? ትጥራላችሁ ከንቱዎች ናችሁ። ከንቱ ትሆናላችሁ።

ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጉድጓድም ጥልቅ ትወርዳለህ፣ የሚያዩህ ይመለከቱሃልና


በእውኑ ምድርን ያንቀጠቀጠ መንግሥታትንም ያናወጠ ዓለሙን ባድማ ያደረገ
ከተሞችንም ያፈረሰ ምርኮኞችንም ወደ ቤታቸው ያልሰደደ ሰው ይህ ነውን? ብለው
ያስተውሉሃል። የአህዛብ ነገስታት ሁሉ በየቤታቸው በክብር አንቀላፍተዋል። አንተ
ግን እንደተጠላ ቅርንጫፍ ከመቃብር ተጥለሃል። በሰይፍም የተወጉት ተገለውም ወደ
ጉድጓድ ድንጋዬች የወረዱት ከድነውሃል። እንደተረገጠም ሬሳ ሆነሃል። ምድርህን
አጥፍተሃልና ሕዝብህንም ገድለሃል ከነርሱ ጋር ከመቃብር በአንድነት አትኖርም። /
አትሆንም/። እንዳይነሱም ምድርን እንዳይወርሱ ስለአባቶቻቸው በደል ለልጆቹ ሞትን
አዘጋጁላቸው።
ትንቢት ኢሳይያስ 14፣ 15 – 21
አባታችሁ ዲያብሎስ የቀደመው እባብ መንግሥታትን ሲያምስ ሕዝብን ሲያስፈጅ በኒዩክለር ከተሞችን
ሲያፈርስ በጀት በመድፍ ሲቀጠቅጥ እናንተም ይህን ስታደርጉ ስታስፈጽሙ ኖራችሁ ነገር ግን ፍጸሜአችሁ
መጠረግ ነው፣ እንኳን እናንት ልጆቻችሁም አይኖሩም።
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይህን ይላል!!

የሰራዊት ጌታ በእነሱ ላይ እነሳለሁ ይላል። የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ከባቢሎን


ስም ቅሬታን ዘርንና ትውልድንም እቆርጣለሁ ይላል እግዚአብሔር። የጃርት መኖሪያ
የውኃ መቆሚያ አደርጋታለሁ በጥፋትም መጥረጊያ እጠርጋታለሁ ይላል፣ የሰራዊት
ጌታ እግዚአብሔር።
ትንቢት ኢሳይያስ 14፡ 22 – 23
እንግዲህ የናንተ ጥፋት ከላይ በተገለጸው መልኩ ነው። ትጠረጋላችሁ፣ ትወድማላችሁ፣ ትቢያ ትሆናላችሁ።
ይህ ይፈጸማል፣ ይህም ይከናወናል፣ ጌታም የታመነ ነው ያደርገዋል። ስለዘመናችን ባቢሎን /አሜሪካ/ ከሷም
ጋር ስለሚነግዱ አብረው ስለሚያመነዝሩ ሁሉ ከዚህ የሚከተለው የጌታ ፍርድ ይፈጸማል።
የሰራዊት ጌታ ይህን ይላል!

በብርቱም ድምጽ ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች! ወደቀች! የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች


የርኩሳን መናፍስትም ሁሉ መጠጊያ የርኩሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ
ሆነች። አህዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቁጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና! የምድርም
ነገስታት ከእርሷ ጋር ሲሴስኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ
ባለጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ።
የዮሐንስ ራእይ 18፡ 2 – 4
ዛሬ ከአሜሪካ ጋር የማይነግድ የለም። ከእንግሊዝ የማይነግድ የለም። የአረብ ነገስታት፣ የአውሮፓ ነገስታት፣
የኤሺያ፣ የላቲን አሜሪካ እናም አፍሪካ ነገስታት ሁሉም ከታላቋ በባሎን /አሜሪካ/ ጋር የሚነግዱ ናቸው። ዛሬ
ከሷ ነግደው የበለጸጉ ናቸው።
እንኳንና ነገስታት ግለሰቦችም አሜሪካ አውሮፓ ሄደው መኖር፣ መነገድ እንደ ክብር፣ ገነት እንደመግባት
ይቆጥሩታል። ምክንያቱም ገንዘቡም አለ፣ ልቅ የሆነው ምንዝርና አለ። የዲያብሎስ ዘመን የእባቡ ጊዜ ስለሆነ

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ሁሉንም በእጅ በደጅ አድርጎላቸዋልና! ስለዚህ ዘወትር ሩጫው ወደእዚያ ነው ወዬላችሁ! ትጠረጋላችሁ!
አታመልጡም።
እነሆ ይህንን ይላል ጌታ እግዚአብሔር ስሙ ሁሉን ቻይ ኤልሻዳይ አምላክ!!

ከሰማይም ሌላ ድምጽ ሰማሁ፣ እንዲህ ሲል። ህዝቤ ሆይ በኃጢአትዋ እንዳትተባበሩ


ከመቅፍትዋም እንዳትቀበሉ ከእርስዋ ዘንድ ውጡ! ኃጢአትዋ እስከ ሰማይ ድረስ
ደርሶአልና! እግዚአብሔር አመጽዋን አሰበ። እስዋ እንደ ሰጠች መጠን ብድራት
መልሱላት፣ እንደሥራዋም ሁለት እጥፍ ደርቡላት። በቀላቀለችው ጽዋ ሁለት እጥፍ
አድርጋችሁ ቀላቅሉባት። ራስዋን እንደአከበረችና እንደተቀማጠለች ልክ ስቃይና ሃዘን
ስጥዋት። በልብዋ ንግስት ሆኘ እቀመጣለሁ ባልቴትም አልሆንም ሃዘንም ከቶ አላይም
ስላለች፣ ስለዚህ በአንድ ቀን ሞትና ሃዘን ራብም የሆኑ መቅሰፍቶች ይመጣሉ።
በእሳትም ትቃጠላለች የሚፈርድባት እግዚአብሔር ብርቱ ነውና!
ከእርሷ ጋር የሴስኑና የተቀማጠሉና የምድር ነገስታት፣ የመቃጠልዋን ጢስ ሲያዩ፣
ስለእርስዋ ዋይ ዋይ እያሉ ያለቅሳሉ። ስቃይዋን ከመፍራት የተነሳ በሩቅ ቆመው
አንቺ ታላቂቷ ከተማ ብርቱይቱ ከተማ ባቢሎን ወዬልሽ በአንድ ሰዓት ፍርድሽ
ደርሶአልና እያሉ ይናገራሉ።
የመርከባችን ጭነት ከእንግዲህ የሚገዛ የለምና የምድር ነጋዴዎች ያለቅሱላታል።
ያዝኑላትማል። ጭነትም ወርቅና የከበረ ድንጋይ እንቁም ቀጭንም ተልባ እግር፣
ቀይም ሃርም፣ ሃምራዊ ልብስ የሚሸትም እንጨት ሁሉ፣ ከዝሆን ጥርስ የተሠራ
እቃም ሁሉ እጅግም ከከበረ እንጨት ከናስም ከብረት ከእብነ በረድም የተሠራ እቃ
ሁሉ ቀረፋም ቅመምም የሚቃጠልም ሽቱ ቅባትም እጣንም የወይን ጠጅም ዘይትም
የተሰለቀ ዱቄትም ስንዴም ከብትም በግም ፈረስም ሰረገላም ባሪያዎችም የሰዎችም
ነፍሳት ነፍስሽ የጎመጀችው ፍሬ ከአንቺ ዘንድ አልፏል። የሚቃጠልና የሚያጌጥም
ነገር ሁሉ ጠፍቶብሻል። ሰዎችም ከእንግዲህ ወዲህ አያገኙአቸውም።
እነዚህን የነገዱ በእርሷም ባለጠጋዎች የሆኑት እያለቀሱና እያዘኑ በቀጭን ተልባ
እግርና በቀይ ሃምራዊም ልብስ ለተጎናጸፈች በወርቅና በከበረ ድንጋይም በእንቁም
ለተሸለመች ለታላቂቷ ከተማ ወዩላት። ይህን የሚያህል ታላቅ ባለጠግነት በአንድ ሰዓት
ጠፍቶአልና እያሉ ስቃይዋን ከመፍራት የተነሳ በሩቅ ይቆማሉ። የመርከቡም መሪ ሁሉ
በመርከብም ወደማናቸውም ስፍራ የሚሄድ ሁሉ መርከበኞችም ከባሕርም የሚጠቀሙ
ሁሉ በሩቅ ቆሙ። የመቃጠልዋን ጢስ ባዩ ጊዜ ታላቂቱን ከተማ የምትመስላት ምን
ከተማ ነበረች? እያሉ ጮሁ በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነስንሰው እያለቀሱና እያዘኑ
በባሕር መርከቦች ያሉአቸውን ሁሉ፣ ከባለጠግነትዋ የተነሳ ባለጠጋዎች ላደረገች
ለታላቂቷ ከተማ ወዮላት! ወዮላት! አንድ ሰዓት ጠፍታለችና እያሉ ጮሁ። ሰማይ
ሆይ! ቅዱሳን ነቢያት ሃወርያትም ሆይ! በእርስዋ ላይ ደስ ይበላችሁ እግዚአብሔር
ፈርዶላችኋልና!!
አንድም ብርቱ መልአክ ትልቁን ወፍጮ የሚመስልን ድንጋይ አንሰቶ ወደ ባህር
ወረወረው። እንዲህ ሲል ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን አንዲህ ተገፍታ ትወድቃለች
ከእንግዲህም ወዲህ ከቶ አትገኝም። በገና የሚመቱና የሚዘምሩም ድምጽ እምቢልታና
መለከትንም የሚነፉ ድምጽ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይገኝም። የወፍጮ
ድምጽም ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም። የመብራትም ብርሃን
ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይበራም። የሙሽራና የሙሽሪይቱም ድምጽ
ከአንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም። ነጋዴዎችሽ የምድር መኳንንት

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ነበሩና በአስማትሽም አህዛብ ሁሉ ስተዋልና፣ በእርሷም ውስጥ የነቢያትና የቅዱሳን


ደም በምድርም የታረዱ ሁሉ ደም ተገኘባት።
የዮሐንስ ራእይ 18፡ 4 – 24
እንግዲህ ስሙ አድምጡ! ታላቂቱ ባቢሎን /አሜሪካ/ እንዲሁም ልጆችሽ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣
ካናዳ፣ ስፔን፣ ደች፣ ፖርቹጋል፣ ጣሊያን፣ ዴንማርክ፣ አየርላንድ፣ ኦስትሪያ፣ አውስትራሊያ፣ ሜክሲኮ፣
ራሺያ፣ ጃፖን፣ ቻይና፣ ቬትናም፣ ህንድ፣ ሲንጋፖር፣ እስራኤል፣ እንዶንዢያ፣ ሊቢያ፣ ኮርያዎች፣ ኩባ፣
ኢራን፣ ሶሪያ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ቤልጂየም፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ፊንላንድ፣ ካታር፣ ኤሜሬትስ፣ ኩዌት
ግብጽ፣ አልጀሪያ ናይጀሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ብራዚል፣ ቺሊ፣ አርጀንቲና፣ ሌሎችም አናሳ መንግሥታት ሁሉ
የተሰናዳላችሁን ጽዋ ትጠጣላችሁ።
ስልጣኔአችሁ ክብራችሁ፣ ሃብታችሁ ሁሉ ይጠፋል። የናንተ ንግስት አሜሪካ ጥፋት የታላላቅ ወዳጆችዋ
መንግሥታት ጥፋት ጢሱ ሰማይ ይወጣል። ትቃጠላላችሁ ትቢያም ትሆናላችሁ። አሻራችሁ ይጠፋል።
መብራታችሁ ፋብሪካችሁ፣ ውብ ከተማችሁ፣ ጌጣችሁ ሃብታችሁ፣ ብራችሁ፣ ምንዝር መፈጸሚያችሁ፣
ዘራችሁ ሁሉ ይጠረጋል። ትቢያም ይሆናል። አውሬ ይዋለድበታል። እንደ ኤፍራጥስ እንደ ግብጽ ስልጣኔ
ምልክት እንኳ አይቀርላችሁም። የቀደመው እባብ አባታችሁ አያድናችሁም ጠበቃ የላችሁም፣ የናቃችሁት
በስሙ የተላገዳችሁበት ጌታ፣ የሰደባችሁት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በእሳት መጥረጊያ ይጠርጋችኋል።
ወዴት ትሸሸጋላችሁ? ወዴትስ ትሸሻላችሁ? በሁሉም ስፍራ ጥፋታችሁ ውድመታችሁ ይከተላችኋል። እናንተ
ያፈረሳችኋቸው፣ እናንተ ያጠፋችኋቸው ድሆች ጎስቋሎች ረሃብተኞች ይወርሷችኋል። የነሱ ከፍታ ይሆናል።
የናንተ ውርደትም ይቀድማል። ከሃዲዎች የእባብ ልጆች፣ ጨካኞች፣ ትእቢተኞች፣ በጥበባችሁ የተመካችሁ፣
ይህ ሁሉ መታመኛችሁ ይጠፋል። እንደ ጢስ ይተናል። የዘር ቅሬታችሁ ይነቀላል። ማንም አያስጥላችሁም።
በሥራችሁ በሃጢያታችሁ ብዛት ሶዶምና ጎመራን ሰባት እጥፍ በልጣችኋል። ሶዶምን የበላው እሳት ሰባት እጥፍ
ሆኖ ይበላችኋል። በሰራችሁት መሳሪያም ትተላለቃላችሁ።
ጥፋታችሁን ውደመታችሁን፣ መጠረጋችሁን፣ ደካሞች፣ የዋሆች፣ ጻድቃን የእግዚአብሔር ሕዝቦች በመልካም
ጥበቃ በጥሩ ስፍራ ሆነው፤ የፈጣሪያችውን ፍርድ /ቅን ፍርድ/ አፈጻጸም ያያሉ ይደነቃሉ ተዘልለውም
ይኖራሉ። ማን ይነካቸዋል? ጠባቂያቸው የታመነው የማያንቀላፋው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነውና!
በጥበባችሁ ትምክህት ስላደረባችሁ ፈጣሪ የለም ትላላችሁ እድሜን የሚለካው የሚወስነው ፈጣሪ መሆኑ
ቀርቶ ስለመሬት ስለሰው ስለልዩ ልዩ ፍጥረቶች ቅሬተ አጽም እየሰበሰባችሁ ሚሊዩን ሺ ወዘተ እያላችሁ
እድሜ ትተምናላችሁ። ጥበባችሁ አስከራችሁ፤ ፍፁምም አሳታችሁ ያልተገደበ ምኞታችሁ ናላችሁን አዞረዉ።
ስለዚህም በትእቢት ሰከራችሁ። ድሃ መንግሥታትና ህዝባቸው ለናንተ አገልጋይ ሆኑ። ለናንተ የሚመቻችሁን
ገዢ በሕዝብ ላይ ጭናችሁ፤ በመከራና በረሃብ ሰንሰለት እንዲሰቃይ ታደርጋላችሁ ሃብታቸውንም ትዘርፋላችሁ
ታዳጊ የላቸውም ትላላችሁ። ምድር በየእለቱ የምትፈጽሙትን ክፉ ሥራ መሸከም አልቻለችም። ስለዚህ
ፍርዳችሁ ፈጠነ። እነሆ በአጭር ጊዜ ይመጣል ይፈፀማል። የት ይመለጣል የፈጣሪያችን ፍርድ ይፈፀማል። ቅን
ፍርዱ ይገለፃል። በቅርቡም ይታያል መጥፋታችሁና ፍርዳችሁም በየደጃችሁ ቆሟል።
አይ ባቢሎን! (አይ አሜሪካ) አይ አውሮፓ! አይ ኤሽያ! አይ አፍሪካ! ወየው ላቲን አሜሪካ! አይ
አውስትራሊያ! አይ ዓለም ወዴት ነው መደበቂያው? ተመዝናችሁ ቀለላችሁ (ማኔ ተቄል ፋሬስ) ስለዚህም
በእሳት ወንፊት ትበጠራላችሁ።
ከውስጣችሁ ንፁሃን ከክፉ ሥራችሁ የራቁ ዘወትር በናንተ ኃጢአትና ክፋት ነፍሳቸውን ያስጨነቁ ይድናሉ።
ያመልጣሉ። የሰራዊት ጌታ ይህንን ያደርጋል ይፈፅመዋል።

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ለ/ በሁለተኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ! ጆሮአችሁን ከፍታችሁ አድምጡ!

በዚህ መልእክት ውስጥ የተጠቀሳችሁ የተለያየ እምነትን ይዛችሁ ይህንንም እምነታችሁን ለምታራምዱ
ይመለከታል።
1. በክርስትና ስም ላላችሁ ካቶሊካውያንና መሪዎችዋ፤ ፕሮቴስታንታውያንና መሪዎችዋ፤ ኦርቶዶክሳውያንና
መሪዎችዋ። እንዲሁም ሌሎች የተለያየ የክርስትና እምነት ለምትክተሉ አናሳ በየሀገሩ ተከልላችሁ
ያላችሁ ክርስቲያኖችና መሪዎችዋ!!
2. ምድሪቱን በስፋት ለሸፈናችሁ የእስልምና እምነት ተከታዮችና መሪዎችዋ በሙሉ!!
3. ኮንፊሺያን፤ ቡዲሂዝም፤ ሂንዱይዝም እና ሌሎችም በምሥራቅ ኤሽያ በስፋት የተንሰራፋችሁ እምነት
ተቋማትና መሪዎችዋ!
የሰራዊት ጌታ ያለ የነበረ የሚኖር ሁሉን ቻይ ሁሉን የሚያሳልፍ ሁሉንም በእጁ የያዘ ጌታ ይህን ይላችኋል!!

እነሆ እግዚአብሔር መአቱን በቁጣ ዘለፋውንም በእሳት ነበልባል ይመልስ ዘንድ ከእሳት
ጋር ይመጣል። ሰረገሎቹም እንደ አውሎ ንፋስ ይሆናሉ እግዚአብሔርም በሥጋ ለባሽ
ሁሉ ላይ በእሳትና በሰይፍ ይፈርዳል። በእግዚአብሔር ተወግተው የሞቱት ይበዛሉ።
ትንቢተ ኢሳይያስ 66፤ 15 – 16
ጌታ እግዚአብሔር ሥራችሁን መዘነ ክፋታችሁ ምድርን ሸፈነ የእምነት መሪ ነን ትላላችሁ ሥራችሁ ግን
የአባታችሁ የዲያብሎስ ሆነ። ፈጽማችሁም የመዳንን መንገድ አጠፋችሁ። ክፉዎችን አመንዝራዎችን ነፍሰ
ገዳዮችን አፀናችሁ። ስለዚህ የሃጢያታችሁ ብዛት ለዓለም ሁሉ ተረፈ። ጌታ በእሳትና በሰይፍ ይጠርጋችኋል።

ስለዚህ እረኞች ሆይ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ! ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል እኔ


ህያው ነኝና እረኛ ስለሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ፤ እረኞችም እራሳቸውን እንጂ
በጎቼን ስላላሰማሩ በጎቼ ንጥቂያ ሆነዋልና! በጎቼም ለምድር አራዊት ሁሉ መብል
ሆነዋልና! ስለዚህ እረኞች ሆይ! የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ ጌታ እግዚአብሔር
እንዲህ ይላል! እነሆ በእረኞች ላይ ነኝ በጎቼንም ከእጃቸው እፈልጋለሁ በጎቼንም
ከማሰማራት አስተዋቸዋለው።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 34፤ 7 – 10
በክርስትና እምነት ስም ተሰማርታችሁ እረኛና መሪ ሆናችሁ ጌታን የምታገለግሉ መስላችሁ ፓትሪያርክ፣
ጳጳስ፣ ቄስ፣ ካህን፣ ዲያቆን፣ ዘማሪ የሚል ማእረግ ይዛችሁ ወደ እራሳችሁ ስምሪትና ንግድ የወረዳችሁ
ወዮላችሁ! ይህ ሁሉ ክብራችሁ ይጠፋል። እናንተም የሰበሰባችሁት የአመፃ ፍሬ ሁሉ ይጠፋል።
እውነትን በአመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በሃጢአተኝነታቸውና በአመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ
ከሰማይ ይገለፃልና።
እግዚአብሔር ስለ ገለጠላቸው ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጥ ነው። የማይታየው
ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱን፤ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ
ይታያልና፤

ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና


ስላላመኑት የሚያመካኙት አጡ ይላል የልዑል ቃል
ወደ ሮሜ ሰዎች 1፤ 18 – 22

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

የዘመኑ የክርስትና እምነት መሪዎች ሁሉን ታውቁ ዘንድ ጌታ ሁሉን አሳውቆአችኋል። ግን ጥበበኞች ነን
ትላላችሁ ደንቆሮ መሆናችሁ ተግባራችሁ ይገልፃል።
በዓለም ላይ ብዙ የተዋቡ ጌጣቸው ስእላቸው የህንፃ ጥበባቸው ድንቅ የሆኑ ካቴድራሎች የእምነት ቤቶች
ሀብት ክብር አላችሁ ትነግዱማላችሁ እጅግ ግዙፍ ኮሌጅ ዩንቨርስቲ አላችሁ በስነ መለኮት ትምህርት በዶክተር
በዲግሪ በመሳሰለው ማእረግ መርቃችሁ ባለእውቀቶች ታወጣላችሁ እጅግ ትላልቅ የመጻሕፍት ቤት በተ መዘክር
ቤተ ምርምር አሉዋችሁ ትመረምራላችሁ ግን ምን ዋጋ አለው ከንቱዎች ናችሁ።

ዳንኤል ሆይ አንተ ግን እስከ ፍጻሜ ድረስ /ዘመን ድረስ/ ቃሉን ዝጋ መጽሐፉንም


አትም ብዙ ሰዎች ይመረምራሉ እውቀትም ይበዛል።
ትንቢተ ዳንኤል 12 ፡ 4
ከላይ በጌታ ቃል እንደተገለጸው፣ ምርምር እውቀት በዝቶአል፤ የእግዚአብሔር ምስጢር ግን በእውቀት
ብዛትና በምርምር ስለማይገኝ ተዘግቶአል ታትሞአል። በየዋህነት፣ በቅንነት፣ በእውነትና በመንፈስ ለሚያመልኩ
ብቻ ይገለጻል። የዘመናችን እባቦች ግን የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት ትለውጣላችሁ በአሁኑ ወቅት ዓለም
በሙሉ በቀደመው እባብ ተግባር ተሸፍናለች። በናንተ ውስጥ፣ በቤተ ክርስቲያንም ፍፁም የዲያብሎስ ሥራ
ነገሶአል። ትነግዳላችሁ፣ ግብረ ሶዶምነትን ታስፋፋላችሁ፣ ታደርጋላችሁ፣ የከፉ መሪዎችን፣ ገዢዎችን መሪዎችን
ታገለግላላችሁ፣ ታበረታታላችሁ። ሰለሃብታችሁ ሁሉንም ክፉ ሥራ ትሰራላችሁ። ስለዚህም እግዚአብሔር
በእሳት ሊጎበኛችሁ ወሰነ። ወዴትም አታመልጡም ሞት ተፈርዶባችኋልና።
ሙስሊም፣ ቡዲዝም፣ ሂንዱይዝም፣ ኮንፊሺያን እንዲሁም ሌሎች መሰል ተቋሞች በተራ ቁጥር፡ 2 – 4
የተጠቀሳችሁ በሙሉ ተረታችሁ ይቀራል፣ ይሻራል። የቅዱሳንን የነቢያትን ደም በከንቱ ለውሸት ትምህርታችሁ
ስትሉ ገድላችኋል፣ እየገደላችሁም ነው። ስለዚህ ከእጃችሁ ደማቸው ይፈለጋል። ፍፁም የጨለማ ሰራተኞች
በመሆናችሁ በእሳት መጥረጊያ ትጠረጋላችሁ። ሁሉም ትምክህታችሁ የገነባችሁት ሁሉ ትቢያ ይሆናል።
የመቆሚያ ስፍራ አታገኙም። ድንገት ወደ ሲኦል ትወርዳላችሁ። ከምድር ፊት ፍፁም አለቅሪት ትጠፋላችሁ።
ይህ ሩቅ አይደለም ፍርዳችሁ ወጥቶአል። የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የጦር እቃውን ለብሶአል። ቁጣውም
እጅግ ጢሶአል። ምድር ወየው በይ! የተበተበሽ እባብ፣ ጊንጥ፣ ዘንዶ ሁሉ በእሳት ባሕር ይዋጣል፤ ይህ እጅግ
በቅርብ ይሆናል። ይፈጸማል። የሰራዊት ጌታ በቃሉ የታመነ ነው። ቃሉ ከሚጠፋ ምድርና ሰማይ ቢያልፍ
ይቀላልና።
አሜን የጌታ ቅን ፍርድ ይገለጥ ስሙም የተመሰገነ ይሁን!

ሐ/ በሶስተኛው መልእክት ለተጠቀሳችሁ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይመለከታል።

በሰራዊት ጌታ ታምናችሁ፤ በጌታ ጸጋና ማዳን ጸንታችሁ፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አጽናኝነት
የወረደባችሁን መከራና ጭንቅ፣ እስራት ውርደትን፣ መራብን ማጣትን፣ እንግልትን ሞትን ሁሉ ታግሳችሁ
በጌታ ቅን ፍርድ መዘግየት ምክንያት ለደከማችሁ ተሰፋ ቆርጣችሁ፣ ፊታችሁን ላዞራችሁ፣ ሁሉ ልዑል
እግዚአብሔር እንባችሁን ሊያብስ ጭንቀታችሁን ሊያጠፋ ተነሳ! አይዞአችሁ ጽኑ!!

የሰላምን ቃል ኪዳን ከነእርሱ ጋር አደርጋለሁ፣ ክፉዎችንም አራዊት ከምድር


አጠፋለሁ። ተዘልለውም በምድረበዳ ይኖራሉ፣ በዱርም ውስጥ ይተኛሉ። እነርሱንና
በኮረብታዬ ዙሪያ ያሉትን ስፍራዎች ለበረከት አደርጋቸዋለሁ። ዝናቡንም በጊዜው
አወርዳለሁ። የበረከት ዝናብ ይሆናል። የምድረ በዳም ዛፍ ፍሬውንም ይሰጣል።
ምድርም ቡቃያዋን ትሰጣለች በምድራቸውም ተዘልለው ይኖራሉ።

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

የቀንበራቸውንም ማነቆ በሰበሩ ጊዜ ከሚገዟቸውም እጅ ባዳንኳቸውም ጊዜ እኔ


እግዚአብሔር እንደሁንሁ ያውቃሉ።
እንግዲህም ለአሕዛብ ንጥቂያ አይሆኑም፣ የምድርም አራዊት አይበሉአቸውም።
ተዘልለውም ይቀመጣሉ። የሚያስፈራቸውም የለም። የዝናን ተክል አቆምላቸዋለሁ።
እንግዲህም ከራብ የተነሳ በምድር አያልቁም። የአሕዛብንም ስድብ ከእንግዲህ ወዲህ
አይሸከሙም። እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው ከእነርሱም ጋር እንዳለሁ እነርሱም
የእስራኤል ቤት ሕዝቤ እንደሆኑ ያውቃሉ፣ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። እናንተም በጎቼ
የማሰማሪያም በጎች ሰዎች ናችሁ። እኔም አምላካችሁ ነኝ ይላል ጌታ እግዚአብሔር።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 34 ፡ 25 – 31
ይህ ቃል በመላው ዓለም ለተበተናችሁት ቅን፣ የዋህ፣ ትሁት፣ ጌታን የምትወዱ በፍፁም ሃሳብና ልባችሁ
ለእግዚአብሔር ላደራችሁ ሁሉ ይመለከታል። የቅዱሳን መላእክትን ተራዳኢነት፣ የእመቤታችንን እናትነትና
ብጽእትነት፣ አማላጅነት አምናችሁ፣ አክብራችሁ ለያዛችሁ ይመለከታል።
ጌታ በኮረብታው ዙሪያ፣ በኢትዮጵያና ዙሪያዋን ባሉ ተራሮች የሚተክለው ብርሃን የሁላችሁም ቅኖች
መሰብሰቢያ ይሆናል።
ልዑል እግዚአብሔር ሀዘናችሁን ወደ ደስታ ይለውጠዋል። የታመነው ጌታ ለልጆቹ የሚነፍገው የለም።
ይህም ደርሷል። በቅርቡም ይሆናል። ራሳችሁን አጽዱ፣ ጽኑ፣ አይዟአችሁ አትፍሩ፣ አትጨነቁ፣ በቁጣው
እሳት የምትጎበኘው ምድር ከናንተ አንዲቷን ጸጉራችሁን እንኳን አይነካም። ባባታችሁ፣ ጌታችን መድሃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ቅን ፍርድም ትደነቃላችሁ።
እግዚእብሄር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ አሃዱ አምላክ ስሙ ይባረክ
አሜን!!

መ/ ሌላው መልእክቴ ኢትዮጵያንና የሕዝቦቿን መጻኢ ሁኔታና እድል ይመለከታል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፈጣሪው በመሸሽ ትእዛዙንም በመናቅ፣ በእንግዳ ባህልና በእንግዳ ትምህርት በመወሰዱ
በከፍተኛ ደረጃ ፈጣሪውን በመበደሉ እነሆ ላልተቋረጠ መከራ ተዳርጎ ይገኛል።
ከፈጣሪው ማግኘት የሚገባውን ምሕረትና እርዳታ፣ ከአሜሪካና አውሮፓ (ባቢሎናውያን) ይፈልጋል።
ይለምናል። ነገር ግን የተገኘ አንዳችም የለም። ምክንያቱም እነሱ እባቦች፣ የዲያብሎስ ልጆች እንጂ የፈጣሪ
ወዳጆች አይደሉም። የሚያስፈጽሙትም የአባታቸውን የዲያብሎስን ፈቃድ ነው።
ዛሬ በኢትዮጵያ የነገሰው ዲያብሎስ ነው። የሚሰራውም ለዚሁ ለቀደመው እባብ ነው። ይህ የሚወገደው
በፈጣሪ ኃይል ነው።

የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ የምድያም አገር መጋረጃዎች ሲንቀጠቀጡ


አየሁ።
ትንቢተ ዕንባቆም 3 ፡ 7
አዎ ለረጅም ጊዜ አገራችን እየተጨነቀች ነው። ይህም ለሥራ ነው፣ እየሰራንም ላለነው ጥፋት የመጣ ቅጣት
ነው። ሌብነት፣ ምንዝርና፣ሃሰት፣ ክፋት፣ በሃሰት መመስከር፣ግድያ፣ ዘረፋ፣ክህደት፣ ዘረኝነት፣ ጭካኔ ምን
ስፍር ቁጥር አለው።ይህ ደግሞ ሕዝቦችም፣ ገዥዎችም የሚሠሩት የየእለቱ ተግባር ነው። በመሆኑም አሁን
እየታየ ያለው መከራ እየወረደ ነው። ይሁንና ጌታ ይህን እንዲያደርግ ልታውቁ ይገባል።

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ከኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ የሚማልዱኝ የተበተኑት ሴቶች ልጆቼ ቁርባኔን ያመጡልኛል።


በዚያን ጊዜ አትታበዩ የሚፎክሩትን ከመካከልሽ አወጣለሁና፤ አንቺም በቅዱስ
ተራራዬ ዳግመኛ አትኮሪምና በዚያ ቀን በኔ ላይ ተላልፈሽ በሰራሽው ሥራ ሁሉ
አታፍሪም። በመካከልሽም የዋህና ትሁት ሕዝብን አስቀራለሁ። በእግዚአብሔር ስም
ይታመናሉ። የእግዚአብሔር ቅሬታ ኃጢአትን አይሠሩም፣ ሃሰትንም አይናገሩም፣
በአፋቸው ውስጥ ተንኮለኛ ምላስ አይገኝም። እነርሱም ይሰማራሉ፣ ይመሰገኑማል፣
የሚያስፈራቸው የለም።
ትንቢተ ሶፎኒያስ 3 ፡ 10 – 13
ጽዮን ሆይ አትፍሪ! እጆችሽም አይዛሉ፤ አምላክሽ እግዚአብሔር በመካከልሽ ታዳጊ
ኃይል ነው። በደስታ ባንቺም ደስ ይለዋል። በፍቅሩም ያርፋል። በእልልታም ባንቺ
ደስ ይለዋል ይባላል። ከጉባኤው ርቀው የሚያዝኑትን ከአንቺም የሆኑትን እሰበስባለሁ፤
ስድብ እንደ ሸክም ከብዶአቸው ነበር፤ በዚያ ዘመን እነሆ ባስጨነቁሽ ሁሉ ላይ
አደርግባቸዋለሁ። አንካሳይቱንም አድናለሁ፤ የተጣለችውንም እሰበስባታለሁ።
ባፈሩበትም ምድር ሁሉ ላይ ለምስጋና ለከበረ ስም አደርጋቸዋለሁ። በዚያ ዘመን
አስገባቸዋለሁ። በዚ ዘመን እሰበስባቸዋለሁ፤ ምርኮአችሁንም በዓይናችሁ ፊት
በመለስሁ ጊዜ፤ በምድር አህዛብ ሁሉ መካከል ለከበረ ስምና ለምስጋና አደርጋቸዋለሁ
ይላል እግዚአብሔር።
ትንቢተ ሶፎኒያስ 3 ፡ 16 – 20
ይህ ከላይ የሰፈረው የጌታ ቃል ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተነገረ ተስፋ በመሆኑ እነሆ በቅርብ ጊዜ መፈጸም
የሚጀምር ነው። ክፉዎች ሁሉ፣ ጠማሞች ሁሉ ሲወገዱ ጨካኞች ሁሉ፣ ዘረኞች ሁሉ፣ አመንዝራዎች፣ ጨካኝ
ገዥዎች፣ ሁሉ ይጠረጋሉ።
ጌታም በምድሪቱ (በኢትዮጵያ) ይነግሳል። ስለዚህ የኢትዮጵያ ሕዝብ በፈጣሪው ብቻ ሊታመን ይገባዋል።
በነጭ ገዥዎችና በባህላቸው፣ በሃብታቸው፣ በእውቀታቸው መታመንን ፍፁም ከልቡ አውጥቶ መጣል አለበት።
እነሱ! ነጭ ገዥዎች ምን እንደተዘጋጀላቸው ቀደም ብዬ በገለጽኩት ሁለት መልእክቶች ውስጥ ተገልጦአል።
በኢትዮጵያ ምድር ያሉ የሃይማኖት መሪዎች የሠሩት ክፉ ሥራም ይጎበኛል። በእሳት ይፈተሻል። የሥራቸውም
ዋጋ ይሰጣቸዋል።
የሃይማኖት አባቶች ሳይሆኑ፣ የሃይማኖት አጥፊዎች ሆነዋል። ጳጳስ፣ ካህን፣ ዲያቆን፣ ቄስ መነኩሴ እነዚህ
ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይነግዳሉ፣ ያመነዝራሉ፣ የመንግሥትን የፖለቲካ ሥራ ይሰራሉ፣ ያታልላሉ፣
ሰዎችን ወደ ጨለማ ይነዳሉ። ወንጌል ጨብጠው ለሰው ልጆች የመዳንን መንገድ ማሳየት ሲገባቸው ወደ
ጥፋት ወደ ክህደት ወደ ጨለማ ሥራ ይመራሉ። ከሁሉም በላይ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ላይ ያላግጣሉ።
ስለዚህም በእሳት ይጠረጋሉ። እውነት የሚናገሩ ባህታዊያንን ያሳድዳሉ። ይገድላሉ። ቀጣፊዎች ስፍራና ቦታ
ገንዘብ ይሰጣቸዋል። የሃሰትን ምልክት ይናገራሉ። እነዚህም ደፋሮች ከውሸት አለቆቻቸው ጋር ይጠረጋሉ።
በዓለም ያሉ የክርስትና እምነትን መሪነት ካባ ያጠለቁ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ሲቀንሱ ሲያሻሽሉ፣
ሲጨምሩ እንደኖሩ ይታወቃል። ሁሉም ለድፍረታቸው ዋጋቸውን ይቀበላሉ።
አባቶቻችን የእምነት አርበኞች፣ አጽንተው፣ ተሰውተው፣ ያቆዩን ሰማኒያ አሃዱ መጽሃፍ ቅዱስ አለን።
ነገር ግን ነጮች የተቀነሰ መጽሐፋቸውን እንደ ትክክል በመቁጠር፤ ያልተቀነሰ ያልተጨመረ ሰማኒያ አሃዱን
መጽሐፍ “የኃይለ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱስ” ነው ብለው እንደ ግለሰብ ድርሰት በመቁጠር ይተቻሉ። ይሳደባሉ።

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

የኃይለ ሥለሴ መጽሐፍ ቅዱስ ነው ላሉት፤ የግለሰቡ የጃንሆይ ሳይሆን የሥላሴዎች፣ የአብ፣ የወልድ፣
የመንፈስ ቅዱስ፣ አሃዱ አምላክ ኃያል የሆነው መጽሐፍ ነው። ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መቀነስ
ያካሄዳችሁ ነጮች ፍርዳችሁን ታገኛላችሁ።
በኢትዮጵያ ምድር የተለያየ መመሪያ ያለው የክርስትና እምነት ለምታራምዱ ሁሉ እንደ ሥራችሁ እንደ
ዘራችሁትም መጠን ታጭዳላችሁ። ከላይ በመልእክት 1 – 2 ለተጠቀሱት ሁሉ እንደተጠቀሰው እነሱ
በሚመዘኑበት አካሄድ ትመዘናላችሁ። ዋጋውንም ትከፍላላችሁ።
ከክርስትና እምነት ውጪ የሆነ እምነት ለምትከተሉ፤ በዓለም ሁሉ ላሉ ቢጤዎቻችሁ እንደሚፈረድ ሁሉ
ለናንተም ይኸው ፍርድ ይከተላችኋል።
በኢትዮጵያ ላሉ ገዥዎችና፣ አስተዳዳሪዎች ሁሉ ማንም እንደሚያውቃችሁ፣ ከሃዲዎች ናችሁ። አታውቁትም
እንጂ እምነታችሁ የአባታችሁ የዲያብሎስ ነው። ስለዚህ ለሰራችሁት ሥራ ሁሉ፣ ላፈሰሳችሁት ደም፣ በብርቱ
ትጠየቃላችሁ። በትእቢታችሁ፣ በክፋታችሁ፣ በተንኮላችሁ ሁሉ ትያዛላችሁ፣ ትመዘናላችሁ፣ ትዋረዳላችሁ፣
ወደ ትቢያም ትወርዳላችሁ። ከመሰረታችሁ ከነሥራችሁ፣ ከነልጆቻችሁ ትጠረጋላችሁ። በመልካሟ ኢትዮጵያ
እንኳን እናንተ ልጆቻችሁም ቢጤዎቻችሁም አያዩት። ረጅም ታስባላችሁ፣ ብዙ ታቅዳላችሁ፣ ዘር ከዘር
ታጋጫላችሁ፣ የጦርነት እሳት ትጭራላችሁ፤ ግን ይህ ሁሉ የምታደርጉት እንኖራለን ብላችሁ ነው? አትኖሩም።
እጅግ በጣም ትንሽ ጊዜ ናት ያለቻችሁ፤ ትጠፋላችሁ።
ባህረ ነጋሽ (ኤርትራ) በተመለከተ ብርቱ ቅጣትን፣ ብርቱም ጥፋትን ተቀብላ ወደ ነበረችበት ትመለሳለች።
ከጥፋቷ የሚያመልጡ እድለኞች ናቸው። በኢትዮጵያ ምድር ላለው ጥፋት እጃቸውን ላስገቡ አገሮች ተጨማሪ
በትርን ይቀምሳሉ።
የሰራዊት ጌታ ይህን ይላል፤

አንተ የእባቦችን ራስ በውኃ ውስጥ ሰበርህ፤ አንተ የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ፤


ለኢትዮጵያ ሕዝቦችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው
የዳዊት መዝሙር 73 (74) 13 – 14
ገዥዎችና መሰሎቻችሁ እባብ ማን ይመስላችኋል? ዘንዶውስ? አዎ እናንተ ናችሁ። ትቀጠቀጣላችሁ፣
ትሰበራላችሁ፣ ትጠፋላችሁ።
ኢትዮጵያም የዋህ፣ ቅን፣ ትሁት ፈጣሪውን የሚወድድ ነጻ ይወጣል። ምግቡንም ያገኛል። ይህ ደግሞ
ሳይርቅ በቅርቡ ይፈጸማል። በኢትዮጵያ በአዲስ የነጭ ባህል የተወሰዱ፣ ፍፁም የተበላሹ ሴቶች የሚበዙ
ናቸው። ሱሪ ለብሰው ይሄዳሉ፣ ሃፍረተ ሥጋቸውን ያሳያሉ፣ ምንዝርናን እንደ ሥራ ይዘውታል። ፍፁም
የዲያብሎስ ሰራተኞች ሆነዋል።
የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል

ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ ወንድም የሴት ልብስ አይልበስ ይህን የሚያደርግ


በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነውና
ኦሪት ዘዳግም 22፤ 5
ይላል የጌታ ቃል። ወንዱም ያው ነው፤ አመንዛሪ፣ አታላይ፣ ነጣቂ፣ ትእቢተኛ፣ ውሸታም፣ ስስታም፣
ሰካራም ጨካኝ ነው። እናንተም ከመጠረግ አታመልጡም። ይኸው ከላይ እንደተጠቀሰው በኢትዮጵያችን
ይፈጸማል። አንዳችም የሚቀር ነገር የለም። ጌታ ከረጅም ጊዜ ትእግስት በኋላ የወሰነው ውሳኔ ስለሆነ፤ ተፈጻሚ
ከመሆን በፍፁም አይቀርም።
12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

ማጠቃለያ

»» በመላው ዓለም ላላችሁ ገዥዎች፣ ነገስታቶች፣ የጦር መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅት መሪዎች
ባለሃብቶች
»» በመላው ዓለም ላላችሁ የእምነት መሪዎች፣ ሰባኪዎችና ተከታዮች፤
»» በመላው ዓለም ላላችሁ ከሃዲዎች፣ ጸረ ክርስቶስ፣ የተረት እምነት ተከታዮች፣ ጸረ ማርያም፣ ጸረ
መላእክት አቋምና እምነት ላላችሁ
»» እግዚአብሔርንና ትዕዛዙን ንቃችሁ በራሳችሁ ተረት ተረት ለምትጓዙ በሙሉ በጥንቆላ በጣኦት ሥራ
ላላችሁ እናንተንም ለሚከተሉዋችሁ
»» በሁላችሁም ላይ እነሆ የኤሊያስ አምላክ በእሳት ይፈርዳል።
ጌታ ከአንድ ታማኙ ጋር ቆመ እንጂ፤ ከነአከአብ፤ ከነኤልዛቤል፤ ከነቡኤል ዘቡኤል፤ ካህናትና የዚሁ
ተከታይ ከሆኑ ሕዝቦች ጋር አልቆመም። በተጻራሪው ከታመነው አገልጋዩ እውነትን ብቻ ከሚያጸናው ባሪያው
ኤሊያስ ጋር ቆመ። መልሱን በእሳት መለሰ ቁጥራቸው ቢበዛም ከሃዲዎች የእሳት እራት ሆኑ እንጂ ከጌታ ፍርድ
አላመለጡም።
እናንተም ቁጥራችሁ በሚሊዮን ቢቆጠር ዋጋ ያለውም፤ ጌታ ከአንድ እውነተኛ ጋር በመቆም በሚሊዮን
ተቆጠሩ በቢሊዮን በእሳት ይፈርድባችኋል።
ቁጥራችሁ በዝቶ ኃጢአትን እንደትክክል አንግሳችሁ ዓለምን ብትሸፍኑ፤ ጌታ ከጥቂት ወዳጆቹ ጋር ሆኖ
እውነትን ያነግሳል። እናንተና አባታችሁ ዲያብሎስ ከነኃጢአትና ወንጀላችሁ እንደገለባ በእሳት ትቃጠላላችሁ።
ይህም ይሆናል የጌታ እግዚአብሔር ትእግስት አልቆ ተፈጽሞአልና። የናንተም ወንጀልና ኃጢአት ሞልቶ
ተርፎ ፈሷልና። የግድ የአመፃን ዋጋ በሕይወታችሁ ትከፍሉታላችሁ። የጌታም ቅን ፍርዱ ይገለጣል፤ አይርቅም
በቅርቡ ይሆናል።
በየትኛውም የዓለም ገጽታ ላይ ኑሩ የሰራችሁት እየሰራችሁት ያላችሁት አመጽ፤ ምንዝርና፤ ነፍስ ማጥፋት፣
ዝርፊያ፤ ውሸት፤ ትእቢት፤ ዘር ከዘር ማፋጀት፤ ዘረኝነት፤ ንቀት እንዲሁም ሴቶች ፍፁም ልቅ ታይቶ
የማይታወቅ ምንዝርና፤ ጽንስ ማጥፋት፤ ወንዱም ግብረ ሶዶምነት ይህ ሁሉ ወንጀላችሁ ዓለምን ፍፁም
በሃጢአት ባሕር እንድትሰጥም አድርጓታል። ስለሆነም ፍፁም ተጠርጋችሁ በእሳት መጥረጊያ ትበተናላችሁ።
ከትቢያ ትቀላቀላላችሁ። ጌታ ይፈጽመዋል ታዩትማላችሁ። የእግዚአብሔር ሕዝቦች የትም ሆኑ የት ጌታ
ደርሶላችሁ የሰራዊት ጌታ ምክር ይድረሳችሁ።
በአመጽ ሰፈር አትገኙ፤ ከክፉዎች ራቁ፤ በሥራቸውም በሃሳባቸውም አትግቡ። ከደም አፍሳሾች ጨካኞች፤
ትእቢተኞች፤ ውሸታሞች፤ አመንዛሪዎች፤ ሰካራሞች ራቁ። ፍፁም ራቁ። ቤተ ክርስቲያን ስትሄዱ ዘወትር
እንጸልያለን በማለት ጌታን ሰቅለው ቁስሉን ከሚወጉ ጋር መስዋእታችሁን አትቀላቅሉ። ብትሄዱም የግላችሁን
ጸሎት ጸልዩ። ዛሬ ሁሉም የእምነት ተቋሞችና መሪዎች ሕይወት ባራኪ ሳይሆኑ ሕይወት አጥፊ ናቸውና።
በቤታችሁ እልፍኛችሁን ዝጉ፣ በእንባ፣ በፍፁም ልባችሁ፣ በፍፁም ሃሳባችሁ፣ ጸልዩ ስለቋንቋችሁ አትጨነቁ።
ልባችሁን የሚመረምር የአብርሃም አምላክ በእውነትና በመንፈስ፣ በተሰበረ ልብ፣ በእንባ ስትነግሩት ይሰማል፤
ትራሳችሁን በእንባ አርሱት እንባችሁን ያብሳል። የታመነውን የሰራዊት ጌታ፣ ይህን የማንም ፍጥረት ህሊና
ሊመረምረው ሊያውቀው ፈጽሞ የማይቻለውን ዓለም በቅጽበት ይሁን ሲል የጸና እንዲሆን ያደረገ አምላክ
ፍፁም ይወዳችኋል። ዋጋችሁንም ይከፍላል።

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አንድ

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ይህን
ይላል።

እስራኤል ሆይ ስማ! አምላካችን እግዚአብሔር አንድ አምላክ (አንድ እግዚአብሔር)


ነው። አንተም እግዚአብሔር አምላክህን በፍፁም ልብህ፣ በፍፁም ነፍስህ፣ በፍፁም
ኃይልህ ውደድ። እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ፤ ለልጆችህም
አስተምረው፣ በቤትህም ስትቀመጥ፣ በመንገድም ስትሄድ፣ ስትተኛም፣ ስትነሳም
ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፣ በአይኖችህም መካከል እንደ
ክታብ ይሁንልህ፣ በቤትህም መቃኖች በደጃፎችህም በሮች ላይ ጻፈው።
ኦሪት ዘዳግም 6 ፡ 4 – 9
ሁሉን ቻይ ፈጣሪ የታመነ ነው። በሺ የተቆጠረ ዘመንን ታገሳችሁ። ደም ሲፈስ፣ ወንጀል ሲሠራ፣ ምንዝርና፣
ውሸት፣ ክፋት፣ ተንኮል፣ ትዕቢትን ስታነግሱ በግሳጼና በመለስተኛ አባታዊ ቅጣት አለፋችሁ፤ ሁሉን የሚችል
አምላክ የነበረ ያለ የሚኖር ሁሉን የሚያሳልፍ ጌታ ሽንገላችሁን አየ፣ ዓለምን የዋጠውን ሃጢያታችሁን አየ፤
ምድሪቱም ጮኸች ትሸከማችሁ ዘንድ አቃታት። ልዑል የጦር ልብሱን ለበሰ። ለሺዎች ዓመታት ከአያት ቅድመ
አያቶቻችሁ ጀምሮ የፈተናችሁት ትዕግስቱ አለቀ። እንግዲህ ወዴት ይሆን መድረሻው? ሰውንም ፈጣሪንም
በድላችኋል፤ ወዴት ነው መሸሸጊያው? እጅግ አስፈሪ ነው። እኔም እጅግ እየከበደኝ ተገድጄ ተናግሬአለሁ።
ስለሚሆነው ሳስብ ፍፁም መድረሻ ይጠፋኛል። ይህንንስ ቁጣ ማን ይመልሰው ይሆን? አዎ ከፈጣሪ ፊት ወዴት
መሰወር ይቻላል?
እንግዲህ መልእክቴ ይኸው ነው።
ትሰሙት ዘንድ ግድ ነው። እንዳይሰማ ማድረግ ደግሞ ባይሳካም በራስ ላይ ትልቅ ጉዳት መጥራት ነው።
ጨረስኩ! ሃሳባችሁም ልባችሁም ከመልእክቱ ላይ እንዲሆን እያሳሰብኩ እኔን ለመፈለግ አትድከሙ አታገኙኝም
ቢሳካላችሁ እንኳ የምረዳችሁ የለኝምና እኔ አንድ ውዳቂ ድሃ ነኝ፣ አንድ ምስኪን ተላላኪ መልእክት አድራሽ
በቃ! ሥራው የኸው ነው። እዚሁ ላይ ያበቃልና!!
አስጀምሮ ላስጨረሰኝ የአብርሃም የይስሃቅ የያዕቆብም አምላክ፣ የነኤልያስ አምላክ፣ የሐዋሪያቶች አምላክ፣
ልዑል እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ስሙ ይባረክ።
ቅን ፈራጅ ጌታ ከፍ ከፍ ይበል።
አሜን!!

ማስታወሻ:–

»» ማንኛውም ይህ ፍርድ አዘል መልእክት የደረሰው ሰው፣ ድርጅት፣ ተቋም፣ ባለስልጣን ለሌላው
የማስተላለፍ ግዴታ አለበት ይጠቀምበታል፤ ያተርፍበታል።
»» ማንኛውም ግለሰብ፣ ተቋም፣ ድርጅት ወደፈለገው ቋንቋ መተርጎም ይችላል፤ ግን መቀነስ፣
መጨመር፣ መለወጥ ክልክል ነው።
»» ማንኛውም ግለሰብ፣ ተቋም፣ ድርጅት፣ መንግሥት፣ ባለሰልጣን ይህን ፍርድ አዘል መልእክት
ካሰናከለ፣ ካገደ የሚገጥመው ቅጣት ለመጸጸት እንኳ እድል የማይሰጠው ይሆናል።

ተጻፈ ቀን ኅዳር 7 ቀን 1998 ዓመተ ምሕረት

14
መልእክት ሁለት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

መልእክት ሁለት
በምድሪቱ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ
ተጻፈ ግንቦት 27 ቀን 2000 ዓ.ም እ. ኢ. አ.
ይህ ሁለተኛ የፈጣሪ ውሳኔ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
ወይም ቀይ መብራት የታየበት ሊባል ይችላል።

ማስታወሻ

»» መልእክቱን በጥንቃቄ ያንብቡ


»» ለሌሎች ሲሰጡ ሁሉንም ገጾች ይስጡ። አይጨምሩ፣ አይቀንሱ፣ አያሻሽሉ፣ ይህን የሚያደርጉ
አለቅጣት አይታለፉምና!
»» እኔ በነጻ እንደሰጠኁአችሁ እናንተም በነጻ ስጡ ፈቅዶ ወዶ ከሰጡአችሁ ተቀበሉ። በረከቱ ይበልጥብናል
ካላችሁ አትቀበሉ።
»» ፋከስ አድርጉት፣ ኢሜይል አድርጉት፣ በድረገጾቻችሁ ልቀቁት፣ በፖስታም ላኩ።
»» በጋዜጣ በመጽሔት አትሙት፣ አሰራጩት በሬድዮን፣ በቴሌቪዥን ልቀቁት
»» እንደ ትዕዛዙና ምክሩ ለማያደርጉ በትዕዛዙ ውሰጥ የሚገጥማቸውን ያንብቡ።
»» በጎ ለመሥራት ማንም አይከለከልም።
»» መሪም ሆነ ተመሪ ሁሉም የሚመዘነው እንደመጸጸቱና እንደቅን ተግባሩ ነው።
»» በጎ ሥራም የሚጀመረው ከትንሹ ነው።

መልካም የመረዳት ንባብ ይሁንልዎ!

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ግንቦት 27/2000 ዓ.ም ተጻፈ

በምድራችን ሁሉ ፊት ተበትኖ ለሚኖር መላው የአዳም ዘር


በሙሉ
ሁለተኛውና የመጨረሻው መልእክት ነው ሌላ የሚመጣ የለም። የተወሰነውን ወደ ተግባር ከሚለውጥ
በስተቀር።
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!

ትእዛዝህን ፈልጌአለሁና አስፍቼ አፄዳለሁ በነገስታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ


አላፍርምም እጅግ በወደድኁአቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል እጆቼንም ወደ
ወደድኁአቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሳለሁ ስርዓትህንም አሰላስላለሁ
መዝ. 118 (119) 44 – 48
እንዳለው ዳዊት ለሁሉም የሰው ዘር! የፈጣሪን የፍርድ ውሳኔና ሂደት እንድታደምጡ እነሆ ታዘዝሁ።
ትእዛዜንም ያለአንዳች ፍረሃት እነሆ የሰው ዘር በሙሉ አድምጥ፣ ጆሮህን፣ዐይንህን ክፈት ብዬ እናገራለሁ።
በአእምሮአችን የሚታወቀውንም፣ የማይታሰበውንም፣ የማይደረስበትን፣ የረቀቀውን፣ ተገለጸውንም፣ የገዘፈውን፣
ያነሰውንም፣ ሁሉንም የፈጠረ አምላካችን ስሙ ይባረክ! ያለ የሚኖር የዘመንም የጊዜም የሁሉ ነገር ፈጠሪ
አምላክ ለስሙ ክብር ይሁን። የብርሃን ፈጣሪና ጌታ እግዚአብሔር ማንም በማይቀርበው ብርሃን ውስጥ ዙፋኑን
የዘረጋ አምላካችን የተመሰገነ ይሁን።
ሰውን ለክብሩ፣ ሊመሰገንበት፣ በራሱ አምሳል አክብሮ የፈጠረ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
ለዘላለም እስከዘላለም ሊመሰገን ይገባዋል። ልንከብር፣ ልንድን፣ የዘላለም ሕይወት ልንወርስ፣ የወደደን ቸሩ
ፈጠሪ ይመስገን። ማንም የማይመክረው፣ ማነም የማያዘው፣ ፈቃዱ የወደደችውን ሁሉ የሚያደርግ አምላክ
ይክበር ይመስገን። በባሕርዩ እውነትን፣ ፍቅርን፣ ቸርነትን፣ ፈጹምነትን የለበሰ፣ ፍፁም የሆነ ጌታ ለክብሩ
ስለ ፈጠረን ልናመሰግነው ይገባል። የዘላለም ሕይወት ልንወርስ ከመንግሥቱ ሙላት በደስታ ልንቦርቅ ፍፁም
የወደደን ማንም በማያልፈው መከራ ሥጋውን በጣጥሶ ደሙን ዘርቶ በታላቅ ሰቆቃ ሞትን ጨልጦ በ 3 ቀን
የሞትን ጀግንነት በትኖ (ድል ነስቶ) እሰከ ምን ርቀት እንደሚወደን አሳይቶን በክብሩና በዙፋኑ ላይ ያለ ጌታ
የተመሰገነ ይሁን!!
መዝሙረ ዳዊት 103 (104)
ከእናታችን ከድንግል ማርያም ሥጋዋን ቆርሶ ደምዋን ወርሶ ፍፁም ሰው ሆኖ፣ የኛ ህመም ህመሙ፣
ቁስላችንን፣ መሰበር፣ መጎሳቆል፣ መድቀቅን ሁሉ ገንዘቡ አድርጎ ልናልፍበት ልንከፍለው የሚገባንን የኃጢአት
ዋጋ ሁሉ ራሱን ሰውቶ ፍፁም ዋጋ ከፍሎ ላዳነን፣ ለክብሩ ላበቃን፣ የገሃነም ደጆች ሊያጠፏት የልቻሏትን፣
የተዋህዶ ኦርቶዶክስን እምነት በዚህ ሁሉ የጥፋት ማዕበል ውስጥ አጽንቶ ላቆመልን፣ አምላካችን ክብር ምስጋና
ውዳሴ በፍፁም ነፍሳችን ከፍፁም ሃሳባችንና ከፍፁም ልባችን ለሱ ይፍሰስ! ስሙ ይባረክ አሜን!!
የዛሬው መልእክቴ የመጨረሻና ማሳረጊያዬ ነው
ደግሜ እላለሁ የመጨረሻው መልእክት ነው
የመልእክቱ ጭብጥ በሁለት ይከፈላል። 1ኛው መልክት በመላው ዓለም ያሉ አገራትንና ህዝባቸውን
የሚመለከት ሲሆን። 2ኛው የአገሬን የኢትዮጵያን ሁኔታ ይመለከታል። ከትእቢትና ንቀት ርቃችሁ ልብ ብላችሁ

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

አድምጡ! የፍርድ ቃልና ውሳኔ ሊፈጸምባቸው የተዘጋጀና በየደጃችሁ መቆሙን እንድታውቁት የታዘዘ ቃል
ነው።
ከኢትዮጵያ ውጭ ላሉ የዓለም ሕዝብ በሙሉ እንዲዳረስ በእንግሊዝኛ ይሄው መልእክትና የፍርድ ቃል
ቀርቧል።
ሰው ሆይ አድምጥ
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 1 ፡ ም 2 ፡ 1 – 10
መዝሙረ ዳዊት 18 (19)
መዝሙረ ዳዊት 32 (33) 16 – 22

ፈጣሪውን ለናቀ ትእዛዙንና ፈቀዱን ላቃለለና በፍፁም የዲያብሎስ ተገዥ ለሆነ ሕዝብ
የግድ ፍርዱን ሊያገኝ የገባል፤ ቢወቀስ ቢገሰጽ ቢገረፍ በፍፁም የማይሰማ፤ ከአንዱ
ጥፋት ወደ ሌላው የሚሸጋገር የፈጠረውን አምላክ ትእግስት የሚፈታተን፣ አልፎም
የሚሳደብ፣ በያዘው እውቀት የሚታበይና እራሱን ከፈጠረው ጌታ በላይ ያደረገ፣
የዘመኑ ሰው የግድ የፈለገውን እሬቱን ሊጋተው ይገባል።
መዝሙረ ዳዊት 10
ከሌሎች ፍጥረቶች ሁሉ ትለያለህና በፈጣሪ አምሳል የተፈጠርክ ሰው ነህና እንደ ስብእናህ አስብና አድምጥ፤
ጆሮህን ክፈት፣ ዐይንህም ይገለጥ፤ በገደል ጫፍ ላይ ቆመሃል፣ ልትተፋ ልትጣል ነው። የዘላለምን ጨለማ
የዚችንም ዓለም እንግድነት በውርደት ልትጨልጥ ነው። አስተውል፣ አስብ፣ ፈጥነህ አድምጥ ይህ መልእክት
የኖቤል ፕራይዝ እያልክ የምትሸላለምበት ድርሰት፣ ልብወለድ እንዳይመስልህ። ይህ መልእክት የፍርድ ነው።
ሰማይና ምድርን የፈጠረና የዘረጋ አንተንም ፈቅዶ የፈጠረ አምላክ ውሳኔ ነው። ከአፉ ወጣ ቃሉ፤ የታዘዘውን
ሰይፈጽም አይመለስም። ቃሉ ከሚታጎል ምድርና ሰማይ ቢያልፉ ይቀላልና!
በምድርም ከንቱ በመጭውም ዓለም ውዳቂ ለምትሆን ላንተ መጥቶብሃልና፤ ምጥ ጀምረሃል። ረሃብ፣
ጦርነት፣ አውሎ ንፋስ፣ ማዕበል፣ እሳተ ገሞራ ሁሉም የፈጠራቸውን የአምላካቸውን ትእዛዝ ለመፈጸም
ተጠንቀቅ ቆመዋል።
መንግሥት ነኝ፣ ድርጅት ነኝ፣ መሪ ነኝ፣ ካቶሊክ ነኝ፣ እስላም ነኝ፣ ፕሮቴስታነት ነኝ፣ ዓለም አቀፍ
ድርጅት ነኝ፣ ፕሮፌሰር ነኝ፣ ዶክተር ነኝ፣ ጀነራል ነኝ፣ ሊቅ ነኝ፣ ባለ ታንክ፣ ባለ ጀት፣ ባለ ኒውክሊየር፣
ብዙ ሀብት አለኝ፤ ለምትል በንቀት፣ በትእቢት፣ በአውቀለሁ ባይነት ለተሞላህ፤ ውሸትን እንደጥበብ ለለበስክ
ጨካኝ ነፍስ ገዳይ ለሆንክ ሁሉ ትቢያ ነህ አትጠራጠር፤ ወደ ትቢያ ትመለሳለህ፣ መና ነህ፣ እንደ ጢስ
ትበናለህ፤ የፈጣሪን ቁጣ የቀሰቀሰው አመፅህ የሚበላህን እሳት ወልዱአል። ይበላሃል አታመልጥም።

የሰራዊት ጊታ እግዚአብሔር ይህን አስቦአል የሚያስጥለውስ ማነው? እጁ ተዘርግታለች


የሚመልሳትስ ማነው?
ኢሳይያስ 14፡ 27
ማንኛውም ይህ መልእክት የደረሰው ሰው ለሌላው ወገኑ ሳያጎል ሳይጨምር ሊያደርስ ይገባዋል። ለሁሉም
እንዲደርሰው አቅምህ የፈቀደውን ሁሉ አድርግ፤ ለፈጣሪ መታዘዝ ማለት፣ ሌላው ወንድምህና እህትህ
የሚድኑበትን፣ ከሞት አደጋ የሚያመልጡበትን ሁሉ ማድረግ ነው። በቅንነት በየዋህነት የፈጠሪውን ትእዛዝ
በማክበር ለሚለፋ ዋጋው ይከፈለዋል። ይህ መልእክት ለሁሉም የሰው ዘር ሊደርሰው ይገባዋል፤ ቢቀበልም
ባይቀበልም፣ ቢሰማም ባይሰማም፣ አንተ ፈጣሪ የጣለብህን አደራ ተወጣ። ንገረው አልሰማ ካለ እጅህን

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

አጨብጭበህ የእግርህን ትቢያ አራግፈህ፤ አንተ እንዳራገፍከው ሁሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርም እንደዚሁ


እንደ ትቢያም ይበትነዋል። ስለዚህ አንተ መልእክቱን አድርስ፤ ቢፈልግ ይጣለው፣ ይቅደደው፣ ይተችም፣
ይመጻደቅም፣ እንደለመደም፣ የክርክር፣ የፍልስፍና አጀንዳም ይክፈትበት፣ ያሻውንም ይበል፣ የሚከፈለው ዋጋ
በእግዚአብሔር እጅ ነው። በመሆኑም ሳይውል ሳያድር ዋጋውን ይቀበላል። አላግጦ ንቆ አሹፎ የሚኖርበት ዘመን
አልቆአልና! ማንኛውም ሰው ይህን መልእክት ካነበበ በኋላ ቀድሞ እራሱን ቢያይ መልካም ነው። ብዙዎች
እንደ ሕይወታቸው ልምድና እንደ እውቀታቸው፣ እንደ ተግባራቸው ሊያዩና ሊተረጉሙ ይችላሉ። ይህ በዚህ
ገሃድ ዓለም በሚፈጠር የሥጋ ጭቅጭቅ የሚፈቀድና የተለመደ ነው።

ስለዚህ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ ድካማችሁ በጌታ እግዚአብሔር ከንቱ እንዳይሆን


አውቃችሁ የምትደላደሉ፣ የማትነቃነቁም፣ የጌታ ሥራ ሁል ጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ!!
ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች – 1 ም 15 – 58
ይህ የምታነበው ቃል ከፈጣሪ ጋር የቀረበ ግንኙነት ባላቸው በተልእኮው በታመኑ አገልጋዮቹና ባሮቹ
የተጻፈ የሚወቅስህ፣ ባትሰማ ባትመለስ ዋጋህን የሚሰጥህ የፍርድ ቃል ነው። በሥጋ ምኞት፣ በግል ስሜት
የመጣ እንዳይመስልህ እዚህ ውስጥ የምትሰማውና የምትረዳው መልእክት አንዱም ነጥብ ሳይወድቅና ሳይለወጥ
ይፈጸማል። ቆሞ ተርፎ ለማየት ያድልህ እንጂ። በእርግጥ መታወቅ የሚገባው እውነቱን አውቀህ ላልተመለስክ
ልክ እንደ ኖኅ ዘመን ሰዎች ጥፋቱ አንገተህ ደርሶ ተፀጽተህ ወደማትመለስበት ጫፍ ሲያደርስህ በዚያ ሰዓት
ብቻ ታውቀዋለህ። ይህ ቃል እውነት መሆኑን ወደ ሞት እየተላለፍክ ለነፍስህ፣ ለራስህ፣ ለውስጥህ ነግረህ
ትከትማለህ ሰለዚህ ስማ!
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ ፡ 2፡ 6 – 22
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ ፡ 5፡ 7 – 30
የአዳም ዘር አድምጥ ፍርድህ ወጥቶአል። ማምለጫ የለም። በ1988 ዓ.ም በህዳር 7 ቀን በኢትዮጵያ
አቆጣጠር በ 21 ገጽ የተከተተ የመጀመሪያው መልእክት የላክሁ ሲሆን ታላላቅ አገርና የዚያም መሪ ነን ለሚሉ
የሥጋው መሪዎች፣ መንፈሳዊ መሪ ነን ለሚሉ በአደራ ፖስታ እንዲደርሳቸው ልኬላቸዋለሁ። በአዲስ አበባ
ለሚገኙ የ17 አገሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እዚህ ባኖሩአቸው ኤምባሲዎቻቸው በኩል በአደራ ፖስታ
በአድራሻቸው ልኬአለሁ። በአገሬ ለብዙዎች በግል እንዲደርሳቸው አደርጌአለሁ። ለመላው ሕዝብም በየቋንቋው
ተርጉማችሁ እንድትገልጹ አሳስቤአለሁ። ኃላፊነትም እንደምትወስዱ ገልጫለሁ። ይህንን ንቃችሁ ይህንን
ሳታደርጉ ቀርታችኋል። የሚገርመው አንድም የመንግሥት ድርጅት፣ መንፈሳዊ ተቋም፣ ተብዩ ለወገኖቹና
ለሚመረው ሕዝብ የገለጸው የለም።
ይሁንና ዛሬ በአለማችን ከ2 አመት ወዲህ እየተከሰተ ያለውን የምጥ ጅማሮ ሰትመለከቱ ቆይታችኋል። ይህም
አይቆጠቆጣችሁም። ስለዚህ የዛሬው የሞት መርዶ መጥቶልሃል!!
የአባታችሁ የዲያብሎስ ሰራ፣ የዘፈን፣የዳንስ፣ የፊልም፣ የስፖርት፣ የፍጅት፣ የአደጋ ዜና፣ ብታገኙ በሰከንድ
በረጫችሁት ነበር። ይሁንና ለኔ አይገደኝም፤ ሊያውቅ የሚገባው በተለያየ መንገድ ደርሶት አውቆታል።
ያላወቀውም አሁን እያወቀው ነው።
በዚህ የመጀመሪያ መልእክት የሚገጥማችሁ በግልጽ ተነግሯል። ሥራችሁም ተገልጧል የእሳት ባሕር
ይጠርጋችኋል። ይህም የዓለምን የሙቀት መጨመር እየተመለከትከው ነው። በሳይንስ ትመልሰዋለህ ጠብቀው።
ለሚያስተውል ራሱንና ወገኑን የት እንዳሉ የሚያይበት መነጽር ነው። አሁን ያ ወቅት ሳትጠቀምበት አልፏል።
2ኛ አመቱን አጠናቋል። መጪው ምንድነው የሚለውን መመልከት ተገቢም አስፈላጊም ነው። በመጀመሪያውም
ሆነ በዚህ በ2ኛው መልእክት የተገለጸው ሁሉ ይፈጸማል። አንዳችም የሚቀር ነገር የለም። ዓለም የተለያየ

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

መጠን ባላቸው ችግር ውስጥ ወድቃለች፤ ሙቀት ጨምሯል፣ረሃብ ነግሷል፣ ግጭት በዝቷል፣ የአየር ንብረት
ተለውጧል፣ ምድር ባህሪዋን ለውጣለች። ይህ ሁሉ ልክ ነው። ይሄው ጥፋት በብዙ መቶ እጥፍ በከፍተኛ
መጠን ይጨምራል። የዲያብሎስ ልጆች በእሳት ባሕር ለመጠረጋችሁ መጠራጠር የለባችሁም። የቻይናን
ምድር ያንቀጠቀጠና ያፈረሰ፣ በርማን የጠረገ፣ የቁጣ ምልክት ምን ይመስላችኋል? እናንተ ጋ አይመጣም?
የሚያግደው አለ? በሺ እጥፍ ይመጣልሃል። እንናተ ሞት ሲውጣችሁ ብቻ ነው የሚገባችሁ። ስለዚህ ጠብቁት።
አንዲት እርጉዝ ሴት ልትወልድ ወሯ ሲገባ ይጎረብጣታል፣ ይወጋጋታል፣ ጭንቅ ጭንቅ ይላታል። ይህም
የምጥ መምጫው ምልክት ነው። ዛሬም በአለማችን የሚታየው ይኄው የጥፋት መምጣት ምልክቶች ናቸው።
ታላቁ ምጥ ገና ይጀምራል። የትስ ታመልጣላችሁ! ከጌታ ወዴት ትሸሸጋላችሁ! እውቀታችሁ፣ ሃብታችሁ፣
ግንባችሁ መኪናችሁ አውሮፕላናችሁ፣ የቆፈራችሁት መደበቂየችሁ፣ ወታደራችሁ፣ ጥበባችሁ ለመሆኑ የቱ ነው
ከፈጣሪ የቁጣ በትር ሸሽጎ የሚያኖራችሁ! ረሃብና የኢኮኖሚው ችግር ለደሃ ብቻ እንደመጣ ትናገራላችሁ፤
ባለጠጎች ናችሁና በወርቃችሁ በብራችሁ እንድናለን ባዮች ናችሁ። ጠብቁ! ውጤቱን ታያላችሁ። ከተደበቅህበት
ፈትሾ ገብቶ የሚበላ እሳት ይመጣልሃል። ኢሳይያስ ም . 13
በእግዚአብሔር ቤት መሸሸግ የሚቻለው ለምኖ ከፈጣሪ ለማስታረቅም ለመታረቅም ለሁሉም የሚበቃ
መንፈሳዊነትና መንፈሳዊ አባቶች ሲኖሩ ነው። ከአለማዊው አመጽ ይበልጥ አመጽ የሚፈጸመው በእምነት
መሪዎች ነው። ሶዶሚያውያን ናቸው፣ አመጸኞችና በጥበባቸው የሚመኩ፣ ለጨለማ ሥራ ድጋፍ የሚሰጡ
የሚያበረታቱ ናቸው። በጥቅሉ ለዲያብሎስ ሥራ የተጉ ናቸው።
ከተጣመመና የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ትምህርትና ፈቃድ፣ ከናቀና ካደፈረሰ፣ ከደለዘና ከለወጠ
የድፍረት ትምህርታቸው በላይ ዐመፃቸው የበረታ ነው። ነፍሰ ገዳዮችን የሚባርኩ፣ በእምነት ሽፋን የፖለቲካን
ሥራ የሚሠሩ፣ ወደ ተለያየም ስፍራ ሲሄዱ በቀሚሳቸው የረቀቀ የዲያብሎስን ተልእኮ ለማስፈጸም የሚተጉ
ናቸው። እናንተና የእግዚአብሔር ትእዛዝ ወዴት ስትተዋወቁ! ህንጻ ቢያምር እውነትን አያሳይ በረቀቀ ጥበብ
ቢሰብክ አያንጽ። ውስጣችሁ በአመጽ የተገነባና ለቢያብሎስ ፈቃድና ለጨለማ አሰራር የተገዛ በመሆኑ እንዴት
መልካም ይወጣችኋል?
ትን ኢሳይያስ 28 ፡ 3 – 29
የካቶሊኩ መሪና የእስልምና መሪዎች እርስ በእርስ በመጽሐፋቸው ሲመራረቁ የታየ ሲሆን የደም አፍሳሾችን
መጽሐፍ እንደ መልካም ከቆጠረና ከዘከረ በምን መልኩ ነው መንፈሳዊ መሪ ሚሆነው? በሚመራቸው የእምነት
ተቋሞች ሰዶማውያን ሞልተውበትና፤ የፖለቲካ ሰራተኛ በሆኑበት የእግዚአብሔር ፈቀድና ትእዛዝ በፈረሰበት
እንዴት ነው ያላመነ የሚያምንበት? በምንስ መልኩ ነው የመንፈስ ስብራቱ የሚጠገንበት? በመጀመሪያው
መልእክት እንደተገለጸው ብዙ የእምነት መጽሐፍትና የመስኩ ጠበብቶች አሏችሁ ብዙ ጽፋችኋል። እንደ ሥጋው
እውቀት እሰከ ዶክተር ማእረግ የሚያደርስ የቲዎሎጂ ትምህርት ማስረጃ ትሰጣላችሁ። ብጹእ፣ በጹእነታቸው
ትባላላችሁ፤ጳጳስ የተከበሩ ትባላላችሁ። የከበሬታ ወንበር በሄዳችሁበት ሁሉ ለናንተ ነው። ልብሳችሁ ያማረ
ነው። ዝማሪአችሁ በብዙ መሳሪያና የሰው ጩኸት የተመላ ነው። ፕሮቴስታንቱ፣ አንጀሊካኑም፣ እስላሙም፣
ቡዲስቱም፣ ሌላውም ሁሉ እንደናንተው ነው። ኤሌክትሮኒክ ሚዲያው የናንተ ነው። መሰብሰቢያው ሁሉ
የናንተ ነው። እጅግ የበዛ ሀብትም ባለቤት ናችሁ። የዘመኑ ሊቀውንት የፖለቲካ መሪዎች ለጥፋታቸው ሲሰማሩ
መርቃችሁ አበረታታችሁ የምትልኩ እናንተ ናችሁ።
የእውቀታቸውም የጥበባችውም አምላኪ ናችሁ። ልባችሁ ከነዚህ ከዲያብሎስ ልጆች ጋር ነው። ጀርባችሁን
ለእግዚአብሔር ሰጥታችኋል። ለጸሎት በሚል ትሰባሰባላችሁ። ሰሚ የላችሁም። ፈጣሪ እናንተን ከሚያዳምጥ
ጆሮውን ከደፈነ ቆየ። እንደ ፋንድያ ጭስ የሚሸተውን ጩኸታችሁን እንኩአን ሊየዳምጥ ሊታገሳችሁና
ሊሸከማችሁ ታክቶታል።
የዳዊት መዝሙር 35 (36) ፡ 1 – 4

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

በአለማችን ላይ መልከ ብዙ እምነቶች ምድርን ሸፍነዋል። የጥፋት መንገድ ሰፊ፤ የመዳን መንገድ ጠባብ፤
መሆኑን ሁሉም የሚያውቀው ነው። ሰፊው መንገድ የዲያብሎስ መንገድ ነው። ስሙን ብቻ በለበሱ በውስጣቸው
እውነት በሌለቸው የዲያብሎስ ልጆች የተሞላ ነው። ስማቸው ብዙ ነው። ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታትን፣ እስላም፣
ቡዲዝም፣ ሺንቶኢዝም፣ ታኦኢዝም፣ ቁጥራቸው የበዛ ነው። አንዳንዶቹ የክርስትና ካባ የለበሱ ውስጠ ባዶ
ናቸው። አንዳንዶቹ ፍፁም ጣኦት የሚያመልኩ ናቸው። ሌሎቹም ፍልስፍና መሰል እምነቶች ናቸው። ከዓለም
6 ቢሊዮን ሕዝብ ቁጥር 90 በመቶ የሚሸፍኑ ናቸው። በድምጽ ብልጫ የፈጣሪን እጅ ሊጠመዝዙ እንደሚችሉ
የሚያምኑና የሚገምቱ የሰይጣን ልጆች ናቸው።
ይህ የሚያስታውሰው ባንዱ የእግዚአብሔር ሰው የሆነው ኤልያስና የእስራኤልን ሕዝብ ይመሩ ከነበሩ
ኤልዛቤልና አከአብ ከነ 400 የበአል ቀሳውስት ጋር የተደረገን ፍልሚያ ነው። በዚህ ፍልሚያ በብዙ ሺ
የሚቆጠሩት የኤልዛቤል ልጆች የአከአብ ሕዝቦች የቡኤል ዘቡኤል ካህናት በአንዱ ኤልያስ ላይ ዘምተው፤ በዚሁ
በአንዱ የእግዚአብሔር የታመነ ባሪያ ተመትተዋል።
በዘህ ንጽጽር ስናይ በዓለም ሁሉ ፊት ከ5 ቢሊዮን በላይ የሚሆነው ሕዝብ የተለያየ ስም አንጠልጥሎ ሁሉም
በቀደመው ዲያብሎስ (እባብ) እየተመራ 99 በመቶ የዓለም ሕዝብ ከፈጣሪውእርቆ ከዚህ የዲያብሎስ አዝማቾች
ጋር ቆሞአል። በተጻራሪው በቁጥርም በሀብትም በሁለመናዋ እጅግ ያነሰችው ሁሌም በነዚሁ የተቀጠቀጠችው
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቆማለች። ኤሊያስ ብቻውን ከፈጣሪው ጋር ቆመ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስን በዓለም ካሉ
ጥቂት ወንድሞችዋ ጋር ከፈጠሪዋ ጋር፣ ከፈቃዱና ከትእዛዙ ጋር ቆማለች። ማን ያሸንፋል ኋላ እናያዋለን።
የተዋህዶ ኦርቶዶክስን እምነት በአሁኑ ሰዓት በታላቅ ፈተና የወደቀች ከውሰጥም ከውጭም በጠላት የተወረረች
በታለቅ ፈተና ላይ ያለች ነገር ግን የማትጠፋ የገሃነም ልጆች ሁሉ የከበቡአት ሆናለች።
የመላው ዓለም የዲያብሎስ ፊት አውራሪና ሰራዊቱ በዚች የተዋህዶ እምነት ላይና የጸና መሰረቷን ባጸናችባት
በአገሬ በኢትዮጵያ ላይ ለዘመናት የቆየና የሸበተ ሁለገብ ጦርነት አካሂደውባታል። እያካሄዱም ይገኛሉ።
ዛሬም በአመራርዋና በውስጥዋ የተቀመጡት ከጠላት የወገኑ የጠላትን ፈቃድ በማስፈጸም ላይ የሚገኙ ሲሆን
ከማእከል እሰከ መንደር ድረስ በዘለቀ እጅና እግራቸው የቤተክርስቲያንዋን መሰረትና ጽናት ለመናድ እየተጉ
ይገኛሉ። የፖለቲካው መሳሪያ በመሆናቸው ከመንግሥት ኃይሎች ጋር በመተባበር እያፈረሱ ለመሆናቸው ሁሉ
የሚያውቀው እውነት ነው። ህዝቡም ፍፁም ስቶ የዘመናችንን የጥፋት ሰዎች ባህልና እምነት ወርሶ የዲያብሎስ
ሰራተኛ ሆኖአል። አመንዛሪ ነው፣ ሌባ ቀጣፊ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ ሃሰት ተናጋሪና መስካሪ ነው።
አምላካችሁ የሆነው የቀደመው እባብ ዲያብሎስ ለጥፋት አላማው ከአያት ቅድመ አያቶቻችሁ ጀምሮ እሰከ
አሁን እየዘለቀ ባለው ጊዜ የተለያዩ የጥፋትና የጨለማ ህጎቹን አስጨብጦአቸዋል። ሰማይና ምድርን የፈጠረውን
አምላክ ፈቃድና ሕግ ንቃችሁ በዲያብሎስ ሕግና ፈቃድ የምትመሩ ሆናችኋል። ማመንዘር መብት ነው፣
መዋሸት ጥበብ ነው፣ የደሃን ፍርድ ማጣመም ትክክል ነው፣ ለባለሃብቱና ለባለስልጣኖች ቆሞ ድሃን ማሳደድና
መበደል፤ አግባብ ነው ብላችኋል። ዘረኝነትን፣ ሰዎችን በዘራቸው የበላይና የበታች ማድረግ፣ ሰዶማዊነት፣
የወሲብ አንዱሰትሪ፣ የድሃን ጉልበትና ልፋቱን መንጠቅ የጥፋት መሳሪያ አዘጋጅቶ ሕዝብን ማፋጀት፤ እኒህ
በሙሉ ትክክለኛ ሥራ ናቸው ብላችኋል!!
ባቢሎን (አሜሪካ)፣ ግልገል ባቢሎናውያን (አውሮፓ) የሚያወጡት ሕግ የአባታቸው የዲያብሎስን በመሆኑ
በዚህ በመመራት በጅምላም ሆነ በነጠላ የማይፈጽሙት ፍጅት የለም።
ትንቢተ ኤርሚያስ ም 23 ፡ 9 – 40
ዛሬ ገንዘብ አምላክ ነው። በገንዘብ የማይገዛ ነገር የለም። የሁሉም ሰው ጣኦት ገንዘብ ነው። ዓለም በሙሉ
ህልውናውን ለገንዘብ ሽጧል። ገንዘብ ደግሞ ዋነኛው የዲያብሎስ መሳሪያ ነው።

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ለዲያብሎስና ለናንተ ለጭፍሮቹ ብቻ የሚጠቅም የዲሞክራሲ መብት ትላላችሁ። አዘጋጅታችሁ ሁሉንም


ሕዝብ በዚህ ትነዳላችሁ፤ ለዚህ ዲሞክራሲ ለሚባለው ብሂልና ህጋችሁ አልገዛም፤ በፈጠረኝ አምላክ ሕግ ነው
የምገዛው ያለውን ሰውም ሆነ ተቁአም ታሳድዳላችሁ፤ ትገላላችሁ፣ ታሥራለችሁ ይህም ዘወትር የምትፈጽሙት
ተግባራችሁ ነው።
በዓለም ላይ እንድንኖር የፈጠረን አምላክ የሰጠንን የፈቃዱን ሕግና ስርዓት በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት
ጸንተው አባቶቻችን አልፈውበታል። ለእግዚአብሔር እውነት ተሰውተውበታል። የሚፈለገውንም ዋጋ ከፍለው
አልፈዋል።
ይኸው ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት በአገሬ ቆማ አልጠፋ ብላችሁ፤ እነሆ እሷንም እንደ ድርጅት ለማጥፋት
የተሳካላችሁ ሆኗል። እንደግል እምነት ግን በየሰው ልብ ውስጥ እግዚአብሔር ስለተከላት አልጠፋ ብላለች።
ቫቲካን፣ ፕሮቴስታንት፣ ሙስሊም፣ ቡዲዝም፣ ሂንዱዚም፣ ኮንፊሽየስ፣ ማናቸውም የእምነት ድርጅቶች ቅርጽ
የያዘ በሙሉ ህልሙም፣ ጥረቱም፣ ዘመቻውም ይህቺን የእግዚአብሔር ቤት የእውነት ደጅ ፈጽሞ ማጥፋት
ነው። ሁሉም የዓለም ገዥዎች፤ የእምነት መሪዎች በመሪያቸው በጨለማው ገዢ እየተመሩ ተዋህዶን ለማጥፋት
ይደክማሉ። የሾሙአቸው፣ ያሳደጉአቸው፣ የኮተኮቱአቸው ጳጳሳት ሥራቸው ይኸው ነው።
ለዚህም ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ቁጥር የበዛ እስላም፣ ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ ሌላም ሌላም የሞላው። ይህ
ሁሉ የእምነት ተቁአምና ድርጅት ከጠዋት እስከ ማታ ዘምቶና አጥፍቶ የሚገባው የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን
ነው።
ዘመቻቸው እመጨረሻው ጣሪያ ላይ በመድረሱ በውጭዎች የተተከሉት ጳጳሳት፣ ዲያቆናት፣ አገልጋይ
ተብየዎች በተለያየ የዲያብሎስ የዘመቻ ስልት ተመርቀውና ተክነው ለሆዳቸው ያደሩ ሆነው የተለያየ የጠላት
ዶክትሪን አንጠልጥለው እንደ ቅባት፣ ጸጋ፣ ተሀድሶ፤ የሚል የዲያብሎስ የረቀቀ ማጥፊያ አዝለው የማፍረስ ሥራ
መሥራት ከጀመሩ ረጅም ዘመን ተቆጠረ። ከዚህ የዘለሉትን በሆዳቸው እንዲያስቡ ተደረገ። ለፖለቲካው መሳሪያ
ሆኑ፣ ለፈጣሪ መገዛት ተዉ። ምዕመኑን ለአውሬ በተኑ። ሆዳቸውን ለመሙላት ከቅርስ ጀምሮ ማናቸውም ነገር
ገንዘብ ያወጣል ብለው ያመኑበትን ሁሉ ሸጡ ለወጡ። አልጠፋም ያላቸው ከሰው ልብ ብቻ ነው። ይህ ሁሉ
የሚቀናበረው ታዲያ ዓለምን እየነዳ ባለው የቀደመው እባብ ነው። ዙፋኑን በአሜሪካ፣በአውሮፓ፣ በኤሽያ፣
በመካከለኛው ምሥራቅ ተክሎ ለተቀረው የዓለም ክፍል እንደየአቅማቸው የሚመጥን ማዘዣ ጣቢየ አደራጅቶ
ዓለምን ወደ ጥፋት እየነዳ ይገኛል። መቀመጫውና ማዘዣው በዓለም የታወቁ ከተሞች ናቸው። ሁሉም ሰው
እንደገነት የሚያያቸው ናቸው። እነኒዎርክ እነዋሽንግተን፣ እነለንደን፣ እነፓሪስ፣ እነብራስልስ፣ እነማድሪድ
እነሊዝበን፣ እነፔኪንግ፣ እነሞስኮ፣ እነቶኪዮ ወዘተ አይደሉም እንዴ! በነዚህስ ከተሞች አይደለም እንዴ
እንደሰናኦር ግንብ የረዘሙትን ህንጻዎችስ የምናየው! በነዚህ ከተሞች ገዝፈው ከሚታዩት የአማሩ ህንጻዎች፤
የነቫቲካን፣ የነፕሮቴስታነት የነአንጀሊካን፣ የነሙስሊም፣ የነቡድሃ አይደሉም እንዴ? የእምነት ዩኒቨርሲቲዎች
ከሚሊዮን መጽሐፍቶቻቸው ጋር ያሉት የት ነው? ከነዚህ ከተሞች ውስጥ አይደለም እንዴ? መቼ ራሳቸውን
ደበቁ በግልጽ የዲያብሎስን ሥራ የሚሠሩ አኮ ናቸው። ዓለምንስ እንመራለን፣ እንዳኛለን፣ እንወቅሳለን፣
እንቀጠቅጣለን፣ እናፈርሳለን እንገነባለን የሚሉትስ መሪዎች፣ ጦረኞች ከነኑይክለራቸው፣ ከነጀታቸው፣
ከነሚሳኢላቸው እዚሁ አይደሉም እንዴ? በነዚህስ ከተሞች አይደለም እንዴ የምንዝርናው፣ የፊልሙ፣ የዘፈኑ፣
አስረህ ምቺው ኢንዱስትሪ የሞላው? አባታቸው ዲያብሎስ ቢሳካለት ገና ሰማይ ላይ ዙፋኑን ሊዘረጋ አይደለም
የሚለፋው? ቋሚው ሳተላይት እስቴሽን ተብየው ለዚሁ ህልም አየደለም እንዴ የሚደክሙበት።
ዓለምን የምታምሱበት የጥፋት መሳሪያዎቻችሁ ዓለም ከተፈጠረች ጀምሮ የሰው ልጅ ያስገነባው አይደለም
እንዴ? ንዩክለር፣ ኒዩተሮን፣ ኬሚካል፣ ባዮሎጂካል፣ ሚሳኤሎች እጅግ የረቀቁ ጀቶች፣ ፈንጂዎች፣ ታንኮች፣

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

መድፎች፣ በህዋ ላይ ደግሞ ኒዩክለር የታጠቁ ሳተለይቶች፣ በጨረር የሚጠቀሙ ማጥቂያ ሳተላይቶች ዓለምን
ደጋግሞ ሊያጠፉ የሚችል መሳሪያ አከማችታችኋል። እየተጠቀማችሁበትም ነው።
እናንተ የአመጽ ልጆች የፈጣሪን ትእግስት ንቃችሁ እንደሌለ እንድትቆጥሩት ሆናችሁ። ፈጣሪ የለምም ብላችሁ
እንድታምኑና እንድታሳምኑ አድርጎአችኋል። ፈጣሪን እስከነመኖሩ ረስታችኋል። በዓለም ሁሉ ምንዝርናን ሥራ
ያልሆነበትና እንደኢንዱሰትሪ ያልተደራጀበት አገር አለወይ? እንኳን ምድር ባህሩም ነጻ ሊሆን አልቻለም።
የምትመሩት በምድርና በባሕር ውስጥ ባለው አጋንንት ብቻ አይደለም፤ በአየርም ከሚከንፈው የጨለማው ገዢ
ጋር ጭምር ነው።
ስለሆነም ይህ ሁሉ ተግባራችሁ ተመዘነ ቀለላችሁ። ዛሬም ትላንትም ከአያት ቅድመ አያቶቻችሁ ጀምሮ
ለ 7000 (ሰባት ሺ) አመታት ስትመዘኑ ሰትለኩ አለፈ። በየመዝገባችሁ የሞላው የአመጽ ሥራችሁ በሁሉም
መስፈርት የሞት ፍርድን ወለደላችሁ። ለምሕረትም የሚያበቃ ነገር ከውስጣችሁ ተፈልጎ ጠፋ! እነሆም ፍርዱ
ወጣ ተወሰነም።
ዓለም አድምጥ!! ከእንግዲህ የናቅሃት ከነጭርሱም የማታውቃት ኢትዮጵያ በሰራዊት ጌታ ፊት የ 7000
(ሰባት ሺ) ዘመን ልፋቷ ታሰበ። ተወደደች። እግዚአብሔር ወደዳት ባለድል ሆነች።
ስማ የሰው ዘር!! ኢትዮጵያ በመንፈሱም በሥጋውም ዓለምን የምትመራ፣ የምትገዛ ሆና በልዑል እግዚአብሔር
ተሾመች!! እንደ ፀሐይ የሚያበሩ የእምነት አርበኞቿ ተቀቡ! ተሾሙ! በአምላካቸው ተወደዱ!!
ደምህን አዝርተህ፣ እምባህን እረጭተህ፣ በጉልበትህ ተንበርክከህ፣ ቅጣትህንና ፍርድህን ተቀብለህ ለምሕረት
የተረፍከው ትውልድ ብቻ እጅህን ለኢትዮጵያ ትሰጣለህ። የኢትዮጵያን ትንሳኤ ታያለህ! ለዚችው ለተባረከች
ምድር ትገብራለህ! የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይህን ያደርጋል! እወቅ የሰው ዘር! ጌታ በከበረው ስሙ
ምሏል። እኛም የታመንን ባሮቹ የውሳኔውን ማህተም ጨብጠናል። አስፈጻሚውም ከደጅህ ቆሟል። እንደ ንስር
ዙሪያህን ይዞራል፤ አታመልጥም መሸሸጊያም የለም።
በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም፤ በእመቤቴ ድንግል ማርያም ስም አረጋግጥላችኋለሁ። ተፈጸመ! ተከደነ!
ትንቢተ ኢሳይያስ ም ፡ 62
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
የሰራዊት ጌታ ስሙ ይባረክ!!!
በኢትዮጵያ ምድር ላላችሁ ከኢትዮጵያም ውጭ ላላችሁ ዜግነታችሁን እምነታችሁን ያልጣላችሁ ወገኖቼ
በሙሉ! ይህ በሕይወታችሁ በአገራችሁ በኑሮአችሁ በዘራችሁ በሃብታችሁ ሁሉ ወሳኝ ሆነውን የአምላካችንን
ፍርድና የመጨረሻው የቅጣት አመጣጥና የማዳኑን ውሳኔ ከዚህ በታች ባለው የመጨረሻው መልእክት
እንድታነቡና ለሁሉም ወገናችሁም ሆነ ለሰው ዘር በሙሉ እንድታደርሱ በፈጠሪ ስም እጠይቃችኋለሁ።
ትንቢተ ኢሳይያስ መዕ – 18
ይህ መልእክት እንደጉዳያቸውና በሕይወታቸው ወሳኝ ጊዜ ላይ መድረሳቸውን ለተገነዘቡ የፈጣሪም ተግሳጽ
ለሚያስደነግጣቸው ወደንስሓ ለሚመልሳቸው (እንደ ነነዌ ሕዝብ ፈጥነው ለሚመለሱ መዳኛቸው ሲሆን)
ለሚንቀው ለሚተቸው ለሚያንጓጥጠው ደርሶ አዋቂ ነኝ ብሎ ለሚመጻደቀው የትችትና የአሽሙር ምላሱን
ለሚያስቀድመው፤ ተውት ለሞት ልጅ አንዴ ለታወረ ምንም ቢሉት አይመለስም። ፈጣሪያችን ከነ ክብሩ
እንኳ ወርዶ ቢያናግረው አይሰማም። ለእሳት የተጻፈ ለእሳት ነው። የኢትዮጵያንና የዓለምን መልካም አያይም!
ከመጪው የበረከት ዘመን አይደርስም! ስለዚህ ለሰው በሙሉ በየትኛውም ዓለም በትኑ! የፍርድ ቃል ነው!
አድርሱ! አውቆ ይዳን! አውቆ ይለቅ ማሳወቅ ብቻ ነው የኛ ግዴታ!!

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

አፌ ጽድቅህን ሁሉ ግዜ ማዳንህን ይናገራል በእግዚአብሔር ኃይል እገባለሁ አቤቱ


ጽድቅህን ብቻ አስባለሁ አምላኬ ከታናሽነቴ ጀምሮ አስተማርከኝ እስከዛሬም
ታምራትህን እናገራለሁ እስካረጅም እስክሸመግልም ድረስ ለሚመጣው ትውልድም
ሁሉ ክንድህን ኃይልህንም ጽድቅህንም እስክነግር ድረስ አቤቱ አትተወኝ
መዝሙር ዳዊት 70 (71) 15 – 18
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። አገራችንን ኢትዮጵያን ፈጣሪያችንና አዳኛችን፤ ለእናቱ
ለድንግል ማርያም የበረከት ልጆች አድርጎ፣ ምድሪቱንም እኛንም የሰጠ ጌታ የተመሰገነ ይሁን። በአባታዊ
ቅጣቱና ማስተማሩ በጸጋው እየሸፈነ ሰው እንድንሆን ለመከረን፣ ለመራን፣ ላኖረን፣ ለቸሩ ፈጣሪያችን ምስጋና
ይድረስ። እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ አሃዱ አምላክ የተመሰገነ
ይሁን አሜን!!
የነበረ ያለ የሚኖር ከመኖር ወደ አለመኖር የሚለውጥ ካልነበረ ወደህያውነት የሚያመጣ ማንም በማይቀርበው
ብርሃን ውስጥ ያለ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን!!

የኢትዮጵያ ሕዝብ አድምጠኝ! አስተውል! ሁሉም ነገር አበቃ የፍርድም ሰዓት ደረሰ።
የቀረችውም ትንሽ ጊዜ አለቀች፤ የመጨረሻው የፈጣሪያችን የአምላካችን መገለጫ
የፍርድ ሰዓት ደረሰ!!

የወደደን በዓለም ሁሉ ፊት ለክብሩ ሊያቆመን ከዘመናት ጀምሮ አያት ቅድመ አያቶቻቸው የከፈሉትን፣
የደከሙበትን፣ የታመኑለትን፣ ለኛ ለልጆቻቸው ሊከፍለን ለወደደው እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ምስጋና ይግባው።

በፈጣሪ ፊት ለተወደደው የኢትዮጵያ ሕዝብ!


በተዋህዶ እምነትህ የጸናህ ውርደትን መከራን የጠጣህ!
በድንግል ማርያም እናትነት ያመንክና በአማላጅነቷ በኢትዮጵያ ባለ ርስትነቷ ታምነህ ለቆምክ!

ውርደቱ ንቀቱ ማጣቱ መገፋቱና መጠላቱ መገደሉ መገረፉ መታሠሩ ሁሉ ሳይበግርህ በፈጣሪህ ታምነህ
ቆመህ እንባህን ላፈሰስክ ወገኔ ሰላም ይብዛልህ፤ ደምና አጥንትህን ለገበርከው የእግዚአብሔር ውድ የኔም
ወንድም፤ ከዚች ቅድስት ምድር አብረን ለበቀልነው ወገኔ፤ በዱር በገደሉ ለምትንከራተተው የሰራዊት ጌታ
የእምነት አርበኞች የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ጀግኖች!!
ከቤተክርስቲያን ተባራችሁ በተኩላ ለተሰደዳችሁ ሁሉ፤ የበይ ተመልካች ሆናችሁ በዘረኞች፣ በአመንዛሪዎች፣
በነፍስ ገዳዮች፣ የእምነት ካባ በለበሱ ቀጣፊዎች ለተረገጣችሁ፣ ቤት ንብረታችሁ ተነጥቆ፣ ትዳራችሁ ፈርሶ፣
ለልመና የተዳረጋችሁ ወገኖቼ!
እንደ ክረምት ሙጃ ሁሉን ቦታ ፈሰውና በቅለው ወፍረው ባበጡ የሙስሊም፣ የፕሮቴስታነት፣ የካቶሊክ፣
የጥንቆላ ሰራዊቶች ለተመታችሁ ለተዋረዳችሁ ወንድሞቼ እህቶቼ!

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

መንግሥት ተብየው በኮለኮላቸው የሆድ አምላኪዎች ዘወትር ለምትገፋና ለምትጨነቁ በሙሉ!


ሰዓት ደረሰ ፍርዳችሁን እንደፀሐይ የሚወጣው የሰራዊት ጌታ እነሆ በደጅህ ለፍርድ ቆሟል። ልትደሰቱ
ህሊናችሁን ልታዘጋጁ ይገባል። ብዙ ወገኖቻችን መልካሙን ቀን ለማየት አየተመኙ የጌታ ፈቃድ አልሆነምና
አልፈዋል። ለአገራቸው ለእምነታቸው ለህዝባቸው ተጨንቀው ተጠበው በጨለማው ገዢ ተረግጠው ተከፍተው
ወደ ጌታችን እቅፍ ሄደዋል። ዛሬ በሕይወት ያለነውም በዲያብሎስ እሥራት ተጠፍረናል። ለረሃብና ለችግር፣
ለሞት ለመንከራተት፣ ለእሥራት ለስደት ተመድበን በዚሁ ሰንሰለት ኖረናል። ብዙዎቻችን አምላካችን ዘገየ
ብለን ተስፋ ቆርጠን ለጠላት እስከመንበረከክ ደርሰናል። እረኛ የሌለው ተቅበዝባዥ በጎች ሆነናል። የተኩላ
እራትም እስከምንሆን ዘልቀናል። ወገኔ! በዘርህ ተለይተህ ተረግጠሃል፣ በእምነትህ ተጠልተሃል፣ በአገርህ
በጠላትነት ተፈርጀሃል፣ ይህችን አገር የማያውቋት ለጥፋቷ ለሚደክሙና ከአያት ቅድመ አያቶቻቸው ጀምረው
ሲያጠፏት የኖሩ የሁሉ ነገር ባለቤት ሆነዋል። ሁሉንም ወርሰዋል፤ ሀብት ንብረት ሰበስበዋል፤ ገንብተዋል፤
ወደ ነጩ ምድርም አፍልሰው አከማችተዋል። ማንም አይነካንም ብለው ራሳቸውን በግንብና በምሽግ ከልለው
ተቀምጠዋል። በጦራቸው፣ በጀታቸው፣በታንካቸው በወታደሮቻቸው ታምነዋል፤ አውሮፓ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣
ህንድ በወዳጆቻቸው ታምነዋል።
ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን! አገራችን መጠለያችን እንድትጠፋ እሷንም የሚወዱ ልጆቿ ከእምነታቸው
እንዲከስሙ ተወስኖ መሥራት ከተጀመረ ብዙ ዘመናትና አመታት አልፈዋል።
አንድ ሕዝብ፣ አንድ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት፣ አንዲት አገር፣ አንዲት አረንጉአዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ
ብሎ ያመነና በዚህ የጸና ወገኔ ወንጀለኛ ነው፤ ስለሆነም ይሳደዳል ይገደላል ይታሰራል ቢዘረዝሩት ብዙ
ነው።ያለቀውና የደቀቀው ማንነትህ ይገልጸዋልና!!
ትግስቱ የማያልቅበት አምላክ አሁን ግን ትእግስቱ አለቀና አበቃ! በሥጋችንም ያመንናቸው ያደራጀናቸው
ተበተኑ። ተስፋችን ጨለመ፤ በመሆኑም መታመኛ ጥበብ ሁሉ አለቀ፤ በመሆኑም ይህን የተመለከተው አምላካችን
ትግስቱ ተሟጧል! የማዳን ክንዱን አነሳ፤ ፍርዱን እንደፀሐይ ሊያወጣ ከሰማይ ማንጎዳጎድ ጀመረ!!

ተስፋህን ዓለምልም ወገኔ አባትህ የታመነው ጌታ ደርሱአል!!! አንተ ባሕርን


በክንድህ አጸናሃት፤ አንተ የእባቦችን ራስ በውኃ ውስጥ ቀጠቀጥህ (ሰበርህ) አንተ
የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ ለኢትዮጵያ ሕዝቦችም ምግብን ሰጠሃቸው
መዝሙረ ደዊት 73 (74) 13 – 14

የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥቃት ከወዴት እንዴት ወዴት

በኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሽጋችሁ ከአለቃ እስከ ምንዝር ላላችሁ በሙሉ!!


የእግዚአብሔርን በጎች አርዳችኋል፣ በልታችኋል፣ ለአውሬ ሰጥታችኋል፣ ሸጣችኋል፣ ለውጣችኋል፣
ለሆዳችሁ፣ ለክብራችሁ፣ ለገንዘባችሁ የእግዚአብሔርን እውነት ለውጣችኋል። በቤተ ክርስቲያን ተሰብስባችሁ
ዘወትር የጌታን ቁስል ትወጋላችሁ። በእመቤታችን ስም ትነግዳለችሁ፤ ታላግጣላችሁ፤ የፖለቲካ ሰራተኛ
ሆናችሁ፤ የተሰጣችሁን መንፈሳዊ ሥራና እረኝነት ለቄሳር ሥራ ለውጣችኋል። ትገላላችሁ ታስገድላልችሁ።
የአምላካችን ሥጋው በሚፈተትበት ደሙ በሚፈስበት ቤተ ክርስቲያን በጎቹን ጠቦቶቹን ግልገሎቹን በሙሉ
አርዳችሁ በልታችኋል! ፍፁም ተኩላ ሁናችኋል።
ሕዝቅኤል ም ፡ 34
ስለዚህ አንድም አታመልጡም፤ ወዴትም መሸሻ የላችሁም፤ ፍፁም ትጠረጋላችሁ! የሰበሰባችሁትን እሳት
ይበላዋል! ለዘራችሁ ለስማችሁ ማረፊያ አታገኙም፤ እንደ ትቢያና አቡአራ ትበናለችሁ!!
10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ተሃድሶ ነኝ! ጸጋ ነኝ! ቅባት ነኝ! እያላችሁ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ላይ ያላገጣችሁ የእመቤቴን
ክብር ለመቀነስ የለፋችሁ፤ የጌታን ፍቅር ክፍያ ያሳነሳችሁ፤ የዲያብሎስ ልጆች ሆይ! ፀሐይ ሲመታው
እንደሚጠፋ ሙጃ ትደርቃላችሁ፤ ለእሳትም ትጣላላችሁ!!
እግዚአብሔር የታመኑ እረኞቹን መርጧል! አዘጋጅቷል! ቀብቷል! ያፈረሳችሁትን ቤት ይገነባል። ተዋህዶ
ኦርቶዶክስ ትታነጻለች፤ እንደ ገና እንደ ፀሐይ ታበራለች። አንተ ተኩላ፣ የሰይጣን ልጅ ትጠረጋለህ አንድህም
አታመልጥም!! ተዋህዶ ኦርቶዶክስ የእውነት እምነት ባለቤት እንጂ የተኩላዎች መሰብሰቢያ አትሆንም!
የመጀመሪያው ጽዳት በእግዚአብሔር ቤት ይጀምራል! እሳት ይበረብርሀል፣ እሳት ያበጥርሃል፣ የዘራኸውን
ታጭዳለህ!!
ያሳደዳችኋቸው፣ ያሰራችኋቸው፣ የጨፈጨፋኋቸው፣ የገደላችኋቸው የእምነት አርበኞች፣ ይፋረዱአችኋል፤
በእሳት ያነደዳችሁት ገዳምና ቤተ ክርስቲያን እጅግ ውድ ዋጋ ያስከፍላችኋል! ዛሬ ዲያብሎስን የምትመርቁና
የምታወድሱ ዲያቆናትና ቄሶች፣ ባህታውያን፣ ጳጳሳት፣ ሥጋችሁን አወፍራችሁ ምላሳችሁን አጣፍጣችሁ
አለሃፍረት ላላችሁ ሁሉ የትም ገብታችሁ አታመልጡም፤ የከፋ፣ የበረታ ቅጣት ትቀበላላችሁ።
የእግዚአብሔር ቤት ትታነጻለች ከተኩላ፣ ከተባይ፣ ትጸዳለች፤ ታሪኩአ ይመለሳል። ክብሯ ይታደሳል፣ ቅርሷ
ይሰበሰባል፣ የእምነት ባለሟሎችና አርበኞች ከተሳደዱበት፣ ከታሠሩበት፣ ከተጣሉበት፣ በክብርና በሙላት
ይመለሳሉ፤ ይፈወሳሉ፣ ይጠገናሉ፣ እንደ ፀሐይ ያበራሉ። እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ይፈወሳሉ!
ይጠገናሉ! በለመለመው መስክ ያድራሉ! በታመኑ እረኞች ይጠበቃሉ!!
ለፈጣሪ ታምናችሁ፣ በድንግል ማርያም ጸንታችሁ፣ ለአገልግሎት ተግታችሁ፣ ከንግድ ሥራና ከሸመታ
እርቃችሁ፣ ለቃሉ የምትተጉ አይዟችሁ፤ ዋጋችሁ በፈጣሪ እጅ ነው። ትደምቃላችሁ! ታበራላችሁ!!
የተዋህዶን እምነት ለሥጋ ትርፋችሁ ያደረጋችሁ ወደ ንግድ ጣቢያነት ለለወጣችሁ ወዮላችሁ!!
ትንቢተ አሞጽ ም 2 ፡ ቁ 13 – 16
ስለጣፈጠው ምላሳችሁ በሕዝብ ፊት የከበራችሁ በውስጣችሁ አመጽና ቅሚያ ለሞላባችሁ ልብና ኩላሊትን
የሚመረምር አምላክ ፍርዳችሁን እንደፀሐይ ያወጣዋል! በሰው ፊት የከበረ በፈጣሪ ይናቃል። በሰው የተናቀ
በፈጣሪ ይከብራል። ሰው እንደሚያይ ፈጣሪያችን አያይም፣ አይቶም አያውቅም። እንደሰው የውጭን ገጽታን፣
ውበትን፣ አለባበስን፣ አነጋገርን አያይም። እሱ የሚፈትሸው ልብና ህሊናን ነው ኩላሊትንም ነው። ፍርዱም
የሚመሰረተው በዚህ መሰረት ነው። በመሆኑም ብዙውን ሰዎች የወደዱትና ያጸደቁት ወይም የመረጡት
ይወድቃል። በተጻራሪው የናቁት ይጸድቃል።
ዳዊትን ከትቢያ ያነሳ፣ ሳሙኤል ብላቴናውን ከኤሊና ከከበሩ ልጆቹ ይልቅ ወዶ የመረጠ፣ አብርሃምን ከጣኦት
አምላኪዎች መሃል መርጦ ያወጣ፣ ሃዋርያትን ከየአሳ ማጥመጃ የመረጠ፣ ከተናቀው የቀረጥ ሥራ የጠራ፣
የከበሩትን የሕግ አወቂዎቹን አነ ገማልያንን ከከበረ ሙክራብ ላይ ያልጠራና ያልመረጠ እግዚአብሔር ሃሳቡ
ከኛ ሃሳብ የተለየ ነው። በኢትዮጵያችንም የሚሆነው ይኸው ነው። የተናቁ በእውቀታቸውም፣ በኑሮአቸውም፣
በሁሉም ነገራቸው እዚህ ግቡ የማይባሉ ተመረጡ!! ተቀብተው ታመኑ! የእግዚአብሔር ምርጫ ነው።
ትቃወሙት ዘንድ ይቻላልን? ምንስ ስለሆናችሁ! ሁሉንም ወደፊት ማየት የተሻለ ነው!! ስለዚህ በመልካም
ሰዓት እግዚአብሔር ሊጎበኘን በቀረበበት ጊዜ በቤቱ የበቀሉ ጠማማና ወልጋዳዎች ይወገዳሉ ይጠረጋሉ!
የዛሬው የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና እረኞች ስሙ አድምጡ! ጊዜው አለቀ፤ የዘራችሁትን
ማጨጃው ሰዓት ደረሰ! አጫጁም እነሆ በደጃችሁ ቆመ። ፈጥነህ ውደቅ አታመልጥምና! በፈጣሪ የታመኑትን
የተወደዱትንና ለቃሉ የሚተጉትን፣ ከጳጳስ እስከ ዲያቆን ያሉትን በገዳማት በገጠር ቤተ ክርስቲያን በማስተማር፣
በቅኔ፣ በድጉአ፣ በዜማ በአቋቋም፣ በተለያየ ትምህርተ ተዋህዶ እምነት አንጸው በማውጣት የተሰማሩትን

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የእግዚአብሔር በጎችና እረኞች ለቅማችሁ አጥፍታችኋል። በናንተ ቤት እግዚአብሔር አያይም ይመስላችኋል?


አሁን ወዴት ታመልጣለችሁ! የፍጸሜአችሁ ቀን ደረሰ። ሥራችሁ ተከተላችሁ። አታመልጡም የፈጣሪ ውሳኔ
አርፏል! የዘራችሁትን ታጭዳላችሁ።
እንሸሻለን፣ አናመልጣለን ብላችሁ አታስቡ፤ ይህ ድሮ ቀረ። ከአሁን በኋላ ሰው አምልጦ የሚድነው ወደ
ኢዮጵያ መጥቶ በመጠለል ብቻ ነው። ስለዚህ ሽሽት ወዴት! እናንተ መሸሸጊያ ይሆናሉ ብላችሁ በሥጋችሁ
ያደራጃችኋቸው እነባቢሎን (አሜሪካ)፣ እነአውሮፓ፣ ወይም ኤሽያ፣ አረቢያም ሁሉም በእዚህም ጽዳት
ይካሄዳል። ምሽጉ የትጋ ነው! ራሳችሁንና ሥራችሁን ይዛችሁ በፈጣሪ እጅ መውደቅ ቅን ፍርዱን መጠበቅ
ብቻ ነው። ተጣምራችሁና እጅና ጓንት ሆናችሁ አባራችኋቸው የምትሠሩላቸውን የፖለቲካ ኃይሎች እጣፈንታም
ከናንተው ይከፋል እንጂ አይለይም። ምሽግ የለም! ሁሉም ተጭኖ መጥቶአል።
ኤርሚያስ 23 ፡ 1 – 6

ይድረስ! ለፕሮቴሰታንት እምነት ተከታዮች ልብ ብላችሁ አድምጡ!!

እናንተ የዘመኑ የጠላት መጠቀሚያዎች እጣ ፈንታችሁ እጅግ ያስደነግጣል። በኢትዮጵያችን ታሪክ የአገሪቱን
የእምነት መሰረት በመናድ፣ ከማንም በላይ የደከማችሁ እናንተ ናችሁ። አገራችን ኢትዮጵያ በእናንተ የጥፋት
ተልእኮ እጅግ ተፈትናለች። የዚችን አገር በእግዚአብሔር የታቀደ ስልታዊ አቀማመጥዋን ልታውቁ ይገባል።
ኢትዮጵያ! በግዮን የተከበበች፣ በምድር ወገብ ሁሉ ብትዞሩ የማታገኙትን ከባሕር ጠለል በላይ በከፍታ
ቦታ የተቀመጠች፣ የማንም ሀገር ስነ ምህዳር ያልጨበጠውን የተለየ የአየር ንብረት የእፅዋት ዝርያ የእንስሳት
አይነት ያቀፈች፣ ያበቀለች ለሰው መኖሪያ ተስማሚነት ያላት አገር ነች። ህዝቧም በመልኩ ለየት ያለ ነው።
በተፈጠሮው ፈጣሪ የቸረው አእምሮውም ያለትምህርት የታነጸ ነው።
እናንተ ደግሞ ከዚሁ ህብረተሰብ ውስጥ በቅላችኋል። በስንዴ አረም እንደሚበቅል፣ በጨለመው ክረምት
ሙጃ እንደሚበዛ፣ አገሪቱን ሸፍናችኋል። ከአጥፊው ስርዓት ጋር ወግናችሁ አገሪቱን ታፈርሳላችሁ፤ ኢትዮጵያዊ
ወኔንም ትሰልባላችሁ፤ እጅና እግሩን ትቀይዳላችሁ፤ አሁን ያለውን መንግሥትም ከምንም በላይ የጠቀማችሁ
የዲያብሎስ ሰራተኞች ናችሁ።
እናንተ የምትንቁአት ይህች ቅድስት ሀገር የእመቤታችን ድንግል ማርያም አገርና ርስቷ ናት፤ በናንተ የረከሰ
አፍ ሁሌ ትነቀፋለች፤ በናንተ የዲያብሎስ ውክልና ቅዱሳን መላእክት እንደ እቃ ዝቅ ተደርገው ይታያሉ።
ምድርና ሰማይ የማይሸከሙትን አምላክ፤ የሚባላ እሳት የሚፈጥረውን አምላክ፤ በማህጸኗ የተሸከመች በነፍሷ
ያሳለፈች፣ ደሟን የለገሰች እናት በናንተ ትነቀፋለች፤ ትሰደባለች፣ ዝቅ ተደርጋም ትታያለች።
የሷን ክብር ለ2000 (ለሁለት ሺ) ዘመን አክብራ፣ አቅፋ፣ ተባርካበት፣ ተወዳበት፣ የኖረችን የተዋህዶ
ኦርቶዶክስን እምነት በናንተ ዘመቻ ተመታለች። በሰርጎ ገቦቻችሁም ትታመሳለች። ቀንን፣ ወርን፣ አመትን ሁሉ
ባለማቋረጥ እንደ ጅረት በሚፈሰው የምስጋና ዜማዋ፣ ቅዳሴና ማህሌት አምላክን፣ እናቱ ድንግል ማርያምን፣
የጌታን ባለሟሎች አክብራ የምታመሰግን ተዋህዶን ልታፈርሱ ከዘመታችሁ ቆያችሁ። እድሜያችሁም የሚለካው
ከጽንሰታችሁ እስከአሁን እድገታችሁ በሰራችሁት አመጽ ነው።
የትኛው የእምነት ተቋም ነው! በዘመን ርቀትም ሆነ፣ ለእምነት ጸንቶ መቆምን፣ በእሳት ማዕበል ማለፍን
ያየ! ያለ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትስ ይህንን የፈጸመ የሚፈጽምስ የት ነው ያለው! የዘመኑ የዲያብሎስ
መጠቀሚያዎች አድምጡ! ማንስ አክብሮ ያኖረውን የእግዚአብሔር ቃል ልታፈርሱ ትነሳላችሁ!
እንደ አርሞንኤም ጠል የሚንጠባጠበውን እንደ ምንጭ ውኃ በሚፈሰው የቅኔ፣ የማህሌት የዜማ ፍሰት
ፈጣሪዋን ያለማቋረጥ የምታመሰግን ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን የሚመስል እስቲ አምጡ! በተግባርም ደሃ

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የሚጠለልባት! ቢከፋው የሚገድምባት! እድሜውን ለፈጣሪው ለሚያስገዛባት ሥጋን በጾም ለማድከም ከ 365
ቀኖች 2/3ኛውን ለጾም በመመደብ የሥጋ ጉልምስናን ለመንፈስ እንዲገዛ በገነቡአቸው መንፈሳዊ ስርዓት
ያሰረጸች ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ናት። እናንተም ካቶሊኩም እስላሙም እምነት አለኝ ፈጠርኩ የሚል ሁሉ በዚች
ተዋህዶ እምነት ላይ ዘምቶ ጦሩን ሰብቆ አናንቆ መንፈሳዊና ሥጋዊ ስብራት አድርሶ ለዘመቻው በዲያብሎስ
ተወድሶ ኖሯል ኖራችኋል።
ዛሬ ግን አበቃ! በሰፈርከው ቁና አስር ዙር ስፍር ሰፍሬ እጠርግሃለሁ ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣
እመቤታችን የድንግል ማርያም ልጅና የደሙን ማህተም የጨበጥኩ፣ የታመንኩት የተወደድኩት የልዑል
ባለሟሎች ሚካኤልና ገብርኤል ለሁሉም ፈጥነው የሚደርሱልኝ፣ በእሳት ቅጥር አጥረው፣ የሚጠብቁኝ የታመንኩ
ወዳጃቸው ነኝ በዚህም የምመካ ነኝ። የአምላኬን ትእዛዝ፣ የእመቤቴን ትእዛዝ፣ የወዳጆቼን ትእዛዝ ልፈጽም
ላስፈጽም የቆምኩ የልዑል ባሪያ ነኝ። ከደፈራችሁ ጠብቁኝ ሂሳቡን እናወራርዳለን ይህን አትጠራጠሩ ምሕረት
ከኔ አታስቡ። ከስንዴ አረም እንደሚነቀል ከኢትዮጵያ ምድር እናንተንና ሥራችሁን አሻራችሁን ማጥፋትና
መጥረግ ዋናው ሥራዬ ነው! የምኖረው ለዚሁ ነው። ጊዜው አልቋል እኔም አጠገብህ ነኝ፤ ከመሃልህ አለሁ።
አኔ ብቻ አይደለሁም። የልዑል ባሪያዎችና የታመኑ ልጆች የደሙን ማህተም የጨበጡ በመሃልህ ቆመዋል።
ለዐይናችሁ አንሞላም ውዳቂዎች ነን፣ በሥጋችን የኮሰመንን ነን። በእምነታችን ቸሩ ፈጣሪያችን በጸጋውና በእሳት
አጥሮ የሚጠብቀን ነን። ሁልህም ተሰናድተህና ወገብህን ታጥቀህ ጠብቀን! የታመንክበትን ሁሉን እናየዋለን
እንደጭስም ሲተን አናየዋለን አብረህም ትበናለህ ፍየልንና በግን አንድ ላይ የምናግድ አይደለንም፤ የተጠራነው
ለበጎች እረኝነት ብቻ ነው። የምንታመነው ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ነው። ጠላትን የሚሸከም ጫንቃ የለንም!!
ሕዝቅኤል 13 ፡ 17 – 23

በእስልምና እምነት ውስጥ ላላችሁ ሁሉ!!

የእግዚአብሔርን ሕዝብ ጨፍጭፎ፣ ቤቱን አፍርሶ፣ በከፋ ጥላቻ ተሞልቶ፣ በህዝበ ክርስቲያን ላይ ዘምቶ፣
መኖር ይቻላል ብላችሁ እጅግ ብዙ ርቃችሁ ሄዳችኋል! እስካሁንም እየሄዳችሁ ነው።
በኢትዮጵያ ምድር በቅንነትና በየዋህነት ብትስተናገዱ ስር ሰድዳችሁ እንግድነትን ረስታችሁ፣ ይህን ሕይወት
የሌለበትን እምነታችሁን በቅድስት ምድራችን ዘርታችሁ የአገሪቱን ከተማና ገጠር የጥቅም አውታራችሁ
አድርጋችሁ፣ ተዋልዳችሁ ከብራችሁ፣ ቤት ንብረት ገንብታችሁ፣ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ሜዳ ላይ ወርውራችሁ፣
ንብረቱን ወራችሁ፣ ተቀምጣችኋል። ይህም አልበቃችሁ የበዙ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ገድላችኋል! እጅግ ብዙ
ንጹህ ደምም አፍሳችኋል። ትክክል እንደሠራ እንደባለመብትም ትፎክራላችሁ። በገዛ ሀገሩ በእምነቱ የተገፋው
የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን የእግዚአብሔርን ፍርድ ሲጠብቅ ቆየ። ያለው የጥፋት አስተዳደር ደግፎአችሁ አድራጊ
ፈጣሪ ሆናችኋል። በዓለም ላይ የሚታየው እልቂት በእናንተው የጥፋት መምህሮች የተቀየሰ ነው። በገዛ ወገናችሁ
ሞት ፈርዳችሁ! አንዱ አክራሪ! ሌላው አላሊ! አንዱ ሱኒ ሌላው ሺያት! እንዲሁም ዋቢያ በሚልና በተለያየ
የጥፋት መመሪያ ታጥቃችሁ ያለቃችሁን የዲያብሎስን ሥራ በግንባር ቀደምትነት በመፈጸም ላይ ናችሁ። አንድ
ሺ አራት መቶ ሰማንያ ሁለት አመት ያሳለፈው የጥፋት ተልእኳችሁ ይደመሰሳል። ከነምልክቱም ይጠረጋል።
እናንተ በፈጣሪ ፈቃድና አሳብ ላይ የዘመታችሁ ናችሁ! የእውነት ጠላቶች ናችሁ! ስለሆነም ፍርዳችሁን ጌታ
እንደ ፀሐይ አውጥቶታል። እንደሌላው ጣኦት አምላኪ ሁሉ የእናንተም እጣ ፈንታ ከምድረ ገጽ መጠረግ ብቻ
ነው።
በኢትዮጵያ ምድር እንኳን ልትኖሩበት ምልክታችሁም አይገኝም። አይታይምም። የሚሆነው ይህ ነው።
አንዲት ሀገር ታላቋ ኢትዮጵያ ትታነጻለች ትቆማለች!! አንድ ሕዝብ ታላቁና የተወደደው በፈጣሪ የታመነው

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የኢትዮጵያ ሕዝብ በዓለም ሁሉ ፊት ይነግሳል፤ እንደ ለመለመ ወይራ ያብባል!! አንዲት እምነት ተዋህዶ
ኦርቶዶክስ ብቻ እንደ ፀሐይ የምታበራበት ምድር ትሆናለች!!
ዓለምን ሁሉ አንቀጥቅጠውና በፈጣሪ ሕግ አስረው የሚገዙ የእግዚአብሔር የታመኑ ልጆችና ባሮች የተዋህዶ
ኦርቶዶክስ አርበኞች የሚነግሱባት ኢትዮጵያን ታያላችሁ! ይህንን የሚያዩት ደግሞ ከውስጣችሁ ተጸጽተው
የሚመለሱ ብቻ ይሆናሉ። ለምስክርነትም ይቆማሉ።
ስለዚህ በተመካችሁበት ሆናችሁ ጠብቁ። ያስተዋላችሁ ደግሞ ለእውነተኛይቱ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት
ነገ ዛሬ ሳትሉ ሳይጨልምባችሁ እጃችሁን ስጡ! በፈጣሪ እጅ ውደቁ! ሌላ ማድረግ የምትችሉት የለም።
ከሁለት አንዱን መምረጥ ብቻ ነው። የዘለዓለምን ሞትና የሥጋንም ሞት። ወይም ደግሞ የዘለዓለምን ሕይወትና
በሥጋም መባረክን! እንዲሁም እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንን! ከዚህ ውጭ ሌላ መንገድ የለም። እኛም
ትዕዛዙን ለመፈጸም ከአምላካችን ብርሃን ኃይላት ጋር ቆመናል። ጨለማ ይጠፋል ብርሃን ይነግሳል፤ አንዱ
ባለበት ሌላው ተጻራሪ አይኖርም!!
ልብ ብለህ አድምጥ! የሰው ዘር በሙሉ!!!
እግዚአብሔር አብ አባታችን፣ እግዚአብሔር ወልድ አባታችን፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አባታችን፣
አንድ አምላክ አባታችን ስሙ ይባረክ! አሜን!
ከረጅም ጊዜ ትዕግስት በኋላ ቅን ፍርዱን እንደ ፀሐይ ያወጣ አምላካችን የተመሰገነ ይሁን። ስሙ ይባረክ!
አምላካችን 2000 (ሁለት ሺ) የምሕረት ዘመን ለገሰ፤ ዐመፃችንን ከደነ፣ ሸፈነ፣ ታገሰ። የታመኑ ልጆቹ
ሲገደሉ፣ ለአውሬ ሲጣሉ የመጫወቻ ሜዳ ማድመቂያና በነሱ ስቃይና ሞት መደሰት እንደመዝናኛ ሆኖ ሲያልፍ
(በሮም ያለው ኮላስየስ ስታዲዮም የቆመ ምስክር ነው) ጌታ ዝም አለ። ከአፉ የወጣውን ቃል የሚያውቅ ጌታ
ጽዋው እስኪሞላ ጠበቀ። አያት ቅድመ አያቶቻችሁ ቅምቅም አያቶቻችሁ ምንጅላቶቻችሁ በእግዚአብሔር
በጎች ደም ሲንቦራጨቁ አገር ሲገነቡ ግዛት ሲያስፋፉ፣ ሀብት ሲሰበስቡ በዐመፃቸው ሲገፉበት በመጠነኛ ቅጣት
ታገሰ።
የቀድሞው እባብ ልጆች በዐመፃቸው ገፉበት፣ አውነትን አጥፍተው፣ ከጌታ የወጣውን ቃል አጣመው፣
የራሳቸውን ሥጋ ፍላጎት ጨምረው፣ ቀንሰው፣ እውነት የሚመሰክሩትን ንቀው፣ አጥፍተው አሳደው፤ በምትኩ
የዲያድሎስን ድርሰት ለዓለም ሁሉ አስተማሩ። እናንተም ልጆቻቸው ከነሱ አብልጣችሁ ተገበራችሁ፣ በዘመናዊ
ጥበብና ዘዴ በዓለም ሁሉ በተናችሁ። አረም ከተመቸው እህልን ይውጣል፣ የጨለማ ጊዜ ለሌባና ለቀጣፊ
ይመቻል። በመሆኑም 2000 ሺ ዘመን የዘለቀ የጨለማ ሥራችሁ፣ አቅማችሁና እውቀታችሁ እስከፈቀደ
ድረስ፣ የዲያብሎስም እውቀቱ እስከ ደረሰበት ድረስ፣ የጥፋት ሥራችሁን፣ ይበጀናል ያላችሁትን ሁሉ ሰራችሁ
ጨረሳችሁ። ዛሬ ግን በቃ፤ ዘመናችሁ ተደመደመ። የማያልፍ፣ የማያልቅ የመሰላችሁ ዘመን አለቀ። ታሪክ ወደ
መሆን ትሸጋገራላችሁ።

ሴቶችና ዘመኑ፤ እንዲሁም መጻኢ እድላቸው!

በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ጎልቶ የሚታየው የዲያብሎስ ዋናው የሥራ መገለጫ ምንዝርና ነው። በአሁኑ
ዘመን የምናየው ምንዝርና ፍፁም ልቅ የሆነና በምድራችን በየትኛውም ትውልድ ያልታየና ወደፊትም ፈጽሞ
ይታያል ተብሎ የማይታሰብ ነው።
በዚህ የምንዝርና ተግባር እጅግ በከፋ መልኩ ተዘፍቀውና ወድቀውበት የሚገኙት ሴቶች ናቸው። በመላው
ዓለም ያለው ሙገሳ፤ ውደሳ፣ ድርሰት ጽሁፍ፣ ፊልም፣ ዘፈን፣ ሆቴል ድርጅት፣ የውኃ ዳርቻ፣ የብስ፣
ባሕር ሁሉም ተደግሶ አልቆ፤ የእግዚአብሔር ቤት ሳይቀር በምድር ላይ አንድም ክፍት ቦታ ሳይተው ሁሉም

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ምንዝርና ማስፋፊያ፣ ማደራጃ፣ ማስፈጸሚያ ወደሚከፋ ደረጃ ማሸጋገሪያ ሆኖአል። ይህ ሁሉ ፀሐይ የሞቀው
እውነት ነው። በዚህ ምግባር ሴቶች ዋንኛውን ስፍራ ይዘዋል። ገላቸውን አራቁተው በጠራራ ፀሐይ በመዞር
ለፍትወት ሁሉን ይጋብዛሉ። ሃፍረተ ሥጋቸውን በማጋለጥ የተቃራኒን ጾታ የፍትወት ስሜት ለመቀስቀስ ከጧት
እስከ ሌሊት ይደክማሉ። የዲሞክራሲ መብት ነው በሚል የዲያብሎስ ሕግ በመመራት አካላቸውን ይሸጣሉ።
መተዳደሪያ አድርገውታል። መሪዎች ታዋቂ ግለሰቦች በሙሉ የምንዝርናን ተግባር በመፈጸማቸው እንደ ነውር
የሚሰማቸው አይደሉም። በዲያብሎስ የተሾሙ ናቸውና! ስለዚህ ምንዝርና የየእለቱ ተግባር ነው። ፈጣሪ
አምላካችን አታመንዝር ያለውን ሕግና ትእዛዝ በመጣስ ከጧት እስከ ማታ መፈጸም የተለመደ ተግባር ሆኖአል።
ነውርን ከማድረግና ከመፈጸም ማፈር ቀርቶ በአምላካችን የተከለከለውን አታመንዝር የሚለውን አለመጣስ
እንደ ነውር ተቆጥሮአል። በትዳር የተወሰነች ገላዋን የሸፈነች ሴት እንደ ውዳቂና አላወቂ ያልሰለጠነች ተብላ
ተቆጥራለች። የማያመነዝር ወንድም እንደ ጅል ከተቆጠረ ሰነበተ።
ወንድና ወንድ፣ ሴትና ሴት በፈትወት ከተቃጠሉ፣ የሰዶምን ሥራ በብዙ እጥፍ በልጠው ከተገኙ ቆየ፤
እንደውም እንደ መብት ተቆጥሮላቸዋል። ይጋባሉም፣ ቤተ ክርስቲያን እመራለሁ፣ አስተምራለሁ፣ ምእመንን
ወደ እውነት እመልሳለሁ የሚል ቄስ፣ ጳጳስ እራሱ ግብረ ሰዶማዊ ሆኖ ተገኘ። እንደ ትክክልም ተግባር
በመቁጠር በአደባበይ ተከራከረበት።
በአገሬ በኢትዮጵያ አጅግ የከፋ የምንዝርና ተግባር ለመፈጸም ፈጻሚውም ተመልካቹም ሁሉም የሚያየው
ያልተሸፈነ የተፈቀደ ተግባር ሆኖአል።
የኛ መንግሥት ስለ ሰዶማውያን ሲጠየቅ የሰጠው መልስ፤ ህገ መንግሥታዊ መብታቸው ነው፤ አንከለክልም
የሚል ነበር። መልሶ እራሱን ከድርጊቱ አድናቂነት ለመሸፈን፤ ቤተ ክርሰቲያን ታስቁም እንጂ እኔን አያገባኝም
ብሎ በተዘዋዋሪ ሳይሆን በግልጽ ይኸው ተግባር እንዲስፋፋ አድርጓል።ሴቶች የተከለከለውን በወንድ ልብስ
ማጌጥ፣ መብታችን ነው በሚል የሰይጣን ብሂል በመነዳት ማንም ሊከለክለን አይችልም ብለው በድርጊቱ
ከተጠመዱ እጅግ ቆዩ። ከወንዱም በፍፁም የማይለዩ ሆነዋል። ከሱሪውም አልፈው መላ ገላቸውን በማሳየት
ከጠዋት እስከ ማታ ዝናብና ፀሐይን ሳይመርጡ ሲዞሩ ይስተዋላሉ።
ኦሪት ዘዳግም ም ፡ 22 ፡ ቁ 5
ምንዝርና ነውር መሆኑ ቀርቶ አለማመንዘር ነውር ሆነ። አንድም ሴት ከነ ክብርዋ መቆየትም ከናቀች
ቆየች፤ ክብርዋን የትም መጣል መሰልጠን ሆነ። በምንም መለኪያ በምንም መንገድ ለዚህ አመንዛሪና
አንጓጣጭ ትውልድ መራራት እጅግ ይከብዳል።እርኩሰታቸሁ ዓለምን አጥለቅልቆታል። በመሆኑም ከአባታችሁ
ዳያቢሎስ ጋ ትጠረጋላችሁ። መልካሙንና ጽድቅን ብትሠራ ላንተ እንጂ ለፈጣሪ ምን ይጠቅመዋል! ምንስ
ይጨምርልታል! ክፉ ብትሠራ እምትጎዳው እራስህን እንጂ ከፈጣሪ ክብር ምንስ እምትቀንሰው አለ! ስለዚህ
ቁጥርህ በረከተ አልበረከተ ምንም ትርጉም የለውም። እንደ ኖኅ ዘመን ትጠረጋለህ! አስታውስ! እጣህ እንደ
ሰዶማዊያን ይሆናል።
በኢትዮጵያ ምድር፤ ከናንተ የበለጠ የቅጣት በትር የሚያርፍበት የለም። መሸሸጊያም የለም! ምንነው
ባልተፈጠርኩ የምትልበት ሰዓት መጥቷል አጥፊአችሁ በየደጃችሁ ቆሞአል። ፈጣሪም ምድርም ተፍታኋለች።
በምንዝርና፣ በውሸት፣ በጭካኔ፣በሌብነት፣በነፍሰ ገዳይነት፣ የተበከልክ ሥራህም ያደረግህ ወንድም ሆንክ
ሴት በፈጣሪ እሳት ትበጠራለህ። ማንም የሚያመልጥ የለም። መልካሙን ዘመን የሚያዩት በፈጣሪአቸው ሕግ
የተመሩ፣የኖሩ፣ ሲወቀሱ ፈጥነዉ ንስሓ የገቡ ብቻ ናቸዉ። ከጥፋት ወደ ጥፋት ለምትነጉደዉ፣ ተግሳጽና ምክር
ለናቅከዉ፣ ለጠፋኸዉ ትውልድ፣ የጨለማ ልጅ ከጨለመ ሥራዉ ጋር ጨለማው ሲጠረግ አብሮ ይወገዳል።
የብርሃን ልጅ ደግሞ በብርሃን ዓለም ተባርኮ ይኖራል።

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

በምንዝርና፣ በክህደት፣ በውሸት፣ በንጥቂያ፣ በቅሚያ፣ በግድያ፣ እናትና አባትን በማዋረድ፣ በስርቆት፣
በዚህ ሁሉ ተክነህ የዘለቅህ ሽማግሌ፣ ወጣት፣ ባልቴት፣ ሁልህም ትፈተሻለህ፣ ትበጠራለህ፣ ቀለህ ስትገኝ
ለእሳት ትጣላለህ። የሚያመልጠዉ ደግሞ አንተ የናቅከዉ፣ ውዳቂ ያደረግከዉ፣ አንተ ከምትሰራዉ ወንጀል
የራቀና ከልቡ ንስሓ የገባ ይሆናል። በምንም ዘዴ የማታመልጠዉን የብርሃን ፍርድ ትቀበላለህ። ሁሉም በደጅህ
ነዉ። ጊዜዉም ተፈጽሞአል።
ምሳሌ ም 6 ፡ 26 – 35 ወደ ሮሜ ሰዎች ምእ ፡ 1
ሕዝቅኤል ምእ 16 ፡ 31 – 34 ምሳሌ ምእ ፡ 7

በዉጪ ስላሉ ኢትዮጵያዉያን!!

በዉጪ በስደት ያላችሁ ወገኖቻችን አገራችሁን እየወደዳችሁ በችግር የሄዳችሁ የችግር ምልክት የሆነዉን
ዜግነታችሁን ያልጣላችሁ ያልለወጣችሁ የፈጣሪዬና የምዩ ልጆች ጊዜዉ ስለመሸ እራሳችሁን እንደ ሎጥ
ከሰዶም ከተማ ለማስመለጥ ከፈጣሪአችሁ ጋር በብርቱ ተነጋገሩ፤ እመቤቴን ጠይቁ፤ ጊዜም አታጥፉ! አጥፊዉ
በመላዉ ዓለም በሁሉም ስፍራ ታዞ በደጅ ቆሞአልና!!
የአገራችሁ ትንሳኤ እነሆ እንደ ፀሐይ ሊያበራ ነዉ። የምዩ ልጆች እውነተኛ ተዋህዶ ኦርቶዶክሶች አይዞአችህ
አምላካችሁ ደርሶአል። በደጅም ቆሞአል ራሳችሁን አዘጋጁ ጊዜ የለም! አትዘናጉ ተፈጽሞአል። በሌላ አኩአያ
ኢትዮጵያዊ የነበርክ ኢትዮጵያዊነትህን የናቅህ ዜግነትህን የለወጥህ ለፍርፋሪ የሸጥህ ብኩርናውን ለምስር ወጥ
እንደ ሸጠዉ ኤሳዉ ክብርህንና ብኩርናህን ለለወጥህ ምንዝርናን የለመድህ ከአህያ የዋለች ጊደር ፈስ ትማራለች
እንደተባለ ምንዝርናን፣ ዉሸትን፣ ንቀትን፣ስስትን፣የተማርክ ተዋህዶ እምነትህን ንቀህ ከፈረንጅና ከአረብ
እምነት የቃረምክና የተቀበልክ፣ መንገድህ ያድንህ፣ ያመንክበት ይከልልህ ለካቶሊኩም፣ ለፕሮቴስታንቱም፣
ለእስላሙም፣ ለሂንዱም፣ ለቡዲሂዝሙም ተከታይ ሁሉ የሚጠብቀው ሁሉ ላንተም ይጠብቅሃል ተዝጋጅተህ
ጠብቅ!!
ሕዝቅኤል ምእ ፡ 14 ፡ 12 – 20 ዘጸአት ምእ ፡ 12 ፡ 21 – 28
ኢሳይያስ ምእ ፡ 40 ፡ 6 – 8 ኢሳይያስ ምእ ፡ 57 ፡ 11 – 13

ከሊቅ እስከ ደቂቅ ላለህ ወገኔ በሙሉ!!

ሁሉም የሚመዘንበት የሚዳኝበት፣ የሚለይበት፣ ሰዓት ተፈጽሞአል የሚቀረው ስንዴውን ወደ ጎተራ


እንክርዳዱን ለእሳት መስጠት ብቻ ነዉ። ሽማግሌ ባልቴት፣ ጎልማሳ ጎልማሲት፣ ወጣት ሴት ወንድ ሁልህም
ልብና ኩላሊትን በሚመረምር አምላክ ተለይተሃል! ለምሕረት የተጻፈዉ በግንባሩ ምልክት በስውር ተደርጎበታል።
ምሕረትን የማያገኘዉ (ለእሳት የተጻፈው) ምልክት አልባ ነው።
በስውር የታተመው ምልክት የጨበጥህና ያልጨበጥህ መሆንህን የሚለዩህ ቅዱሳን መላእክት ስለሚያውቁህ!
የሌለውን ለእሳት ያለውን ወደእረፍትና ወደምሕረት የምታውቀው ደግሞ ስትድን ከመአቱ ስትተርፍ ብቻ ነው።
መዳንህንም በዚህ ታረጋግጣለህ። ከአጠገብህ ያለችው ያለው ሲሸኙ ምልክት አልባ መሆናቸዉን ታዉቃለህ
ትረዳለህ።
እኔ መሪ ነኝ፣ እኔ ሚኒስቴር ነኝ፣ እኔ የእምነት መሪ ነኝ፣ የጦር አለቃ ነኝ፣ ባለኒዩክለርም፣ ባለጠብመንጃ
ብትሆን የዓለም መሪም ሁን፣ የአጥፊዉ ጋሻ ጃግሬ ስለነበርክ፣ አለቃና ምንዝር ስለሆንክ፣ የዘር ሹመኛ
ተጠቃሚ፣ የዘር ፈራጅ ስለነበርክ ምንም ከምንም የሚያድንህ የለም። ሁሉም የዓለም ገጽታ በሙሉ በሞት
ይፈተሻል። የሚያድንህ የልብህ ቅንነት እምነትህና ሥራህ ብቻ ነዉ።

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የሰበሰብከዉ ሀብት፣ ንብረት፣ በምሕረት ለታሰቡት ይቀራል። አንተ እንደዘራኸው ታጭዳለህ፣ ፈጣሪህን
ርስትህን እንደ አምላክ ቆጥረህ የተከለልከዉ በዘረኛ ገዢ ጉያ ነው። እሱ ስለሚሄድ አንተስ ወዴት ትቀራለህ!!
አብረህ ትጓዛለህ። የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም እንደሚባለው ለሆድህም ሆነ ላመንክበት አላማ ያዉ ከሃዲ
የእግዚአብሔር አገር የወገን ጠላትነህ፤ ስለሆነም ስፍራህ መቃብር ብቻ ነው። እንደ ሥራህ መጠን ይከፈልሃል።
የማንም ገዢ አያመልጥም። ራሱንም ሆነ አንተንም አያድንም። ስለዚህ ከፊትህ የመጣዉን የፈጣሪ በትር ሳያበጥር
እንደማይመለስ ተረድተህ ታጥቀህ ጠብቅ! የታዘዘዉ አጥፊህ በየደጅህ ቆሞአልና።
ይህንን መልእክት ስታነብ እንደለመድከው የሥጋ ብልጠትና የፖለቲካ ክህሎት ያዋጣኛል ብለህ እንዳታስብ።
መከራህም ከሚያከብደው በቀር የሚፈይደዉ የለም። ዓለም ገና ከእንቅልፉ አልነቃም፤ በመጣበትም ቁጣ ፈጽሞ
አልደነገጠም ሁሌም እንደሚያስበዉ በእዉቀት በእርዳ ተረዳዳ በገንዘብ እወጣዋለሁ ብሎ ያምናል።
በምድር መንቀጥቀጥ፣ በጎርፍ፣ በማዕበል፣ በሙቀት፣ በረሃብ ሲመታ ኮንፈረንስ ያደራጃል፣ ሳይንሳዊ ዘዴ
ይተልማል፣ የእርዳታ ድርጅት ይሰይማል ደረስኩ ይላል። ይሄ ሁሉ ይቆማል አይረዳም ለራሱ የሚሰጠዉን
መከራና በትር ስለማይቋቋም አንዱ ላንዱ የሚረዳዳበት ወቅት ይጠፋል። ሁሉም እንደ ሥራው በመጣው ጥፋት
ይጠረጋል። እንደ ጪስም ይተናል። ምድራችን እዉነትን በማያዉቁ አመጸኞችና ወንጀለኞች የዲያብሎስ ልጆች
ስለተሞላች በግድ መጽዳት አለባት። ለቅዱሳንም የተመቸችች የበረከት ምድር ልትሆን ይገባል! ስለሆነም
ይኸዉ የፈጣሪ ፈቃድ ይፈጸማል።
በኢትዮጵያ የሚደርሰው የሚፈጸመው ሁሉ እነሆ ይመጣል! እግዚአብሔር የቀባቸው በምድሪቱ ላይ ሲነግሱ
ያኔ ብቻ የእረፍት ጅማሮ ይሆናል። ይህ እስኪሆን ግን ዓለም አይታ የማታውቀውን ጥፋትና ውድመት
ታስተናግዳለች በዚህን ጊዜ ሁሉም የሚጮኸው የፈጣሪ ቁጣ እንዲቆምለት ብቻ ነው። ያ ደግሞ የሚሆነው
የታዘዘው ሁሉ ሲፈጸም የእግዚአብሔርም ሕዝቦች ነጻ ሲወጡ ብቻ ነው።
የታመኑ የፈጣሪ ልጆች በዓለም ሁሉ ፊት የሚያበራውን ከጌታ የተሰጣቸውን ስልጣን ሲያፀኑ! ሁሉም
ሲንበረከክና ለፈጣሪና ላከበራቸው ሲገዛ ብቻ ነው! ሰላም፣ በረከት፣ ቸርነት፣ የሚሆነው ይኸው ሲሆን ብቻ
ነው። ይህ ደግሞ ከብዙ ጉዳት በህዋላ የሚፈጸም ነው። ምክንያቱም የሰው ልጅ ትእቢቱንና አውቃለሁ ባይነቱን
ቶሎ አይጥልምና!! ዓለም ሁሉ በታላቅ እንባና ጩኸት ይሞላል። ከቁጣው ብርታት የተነሳ ዓለም ያለፈች
እስኪመስል ድረስ፤ አሁንም ደግሜ እለዋለሁ! በኢትዮጵያና በዙሪያዋ ባሉ ተራሮች (ሀገሮች) ሁሉ የብርሃን
ዙፋኑን የሚዘረጋው ጌታ ልጆቹን ከዙፋኑ ላይ ሲያስቀምጥ ብቻ ነው ቁጣው መስከን የሚጀምረው ከዚህ ውጪ
የሚመጣ አንዳችም ነገር የለም።
እግዚአብሔር ለምሕረት ያሰባቸው ክርስቲያን ሆኑ እስላም ሆኑ ካቶሊክ ሆኑ ሌላም ሆኑ ድርጅት ውስጥም
ኖሩ አልኖሩ እምነት ይኑራቸው አይኑራቸው፤ ብቻ ልባቸው ቅን የዋህ ትሁትና ደግ ከሆኑ እውነትን የሚወዱ
ከሆነና ፈጣሪን የሚፈልጉ ይሁኑ እንጂ! አምነውና ተጠምቀው በብርሃናዊቷ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጅነት
ተባርከው በብርሃን ጎዳና ይገሰግሳሉ! የምሕረትንም ዘመን ያያሉ ይኖሩበታልም።

የኢትዮጵያ ትንሳኤ!!

ወገኔ የኢትዮጵያ ሕዝብ በፈጣሪህ እጅግ የተወደድክ ሕዝብ እኮ ነህ እጅግ ላከበራት ለእናቱ ለእናታችን
ለድንግል ማርያም ልጅ አድርጎ የሰጠህ ለማንም ያልሰጠውን በረከትና ሕይወት ያዘዘልህ እኮ ነህ!! የእምዬ
(የድንግል) ልጆች ለመሆኑ እንዲህ ለወደዳችሁ አምላክ ምን ትከፍላላችሁ!! ዓለምን ሁሉ ለእናንተ እንዲገዛ
እንዲታዘዝ ወሰነ። እስቲ ወገኔ አስተውል! ያለፉት ለዚች የተባረከች ምድር የደከሙት አባቶቻችንን ድካም
ለ 7500 (ሰባት ሺ አምስት መቶ) ዘመን ሲመዝን፣ ሲለካ፣ ሲመዘግብ ኖሮ ቃሉን በፍፁም የማያጥፍ ጌታ

17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ለኔና ላንተ ላንቺ ብድራትን ሊከፍል መጣ!! ለመሆኑ ምንስ ትከፍለዋለህ!! ጌታ ሌላ አይጠይቅም ከልብህ
የሚመነጨውን ምስጋና ብቻ ነው።
በፈጣሪ ፊት ያለህን ክብር አላወከውም! አሁን ግን ልታውቀው ይገባሃል። በሥራህ አይደለም የወደደህ
አያት ቅድመ አያቶችህ በእምነታቸው ቆመው በጸጋው ያፈሱት በረከት ነው። ለዚህም የትንሳኤ ዘመን ያደረሰህ
የታመነ አምላካችን ሁሌም የታመነ ነው። ከቃሉ የሚጨመር የሚቀነስ የለም።
አድምጥ ደስም ይበልህ!! በዓለም የሚያበራ ክብር ለኢትዮጵያ ተሰቶአታል!! በበረከቱና በቸርነቱ
በፍፁም ፍቅሩም የምትሞላው ኢትዮጵያ በእመቤቴ የእናትነት እቅፍ እና በረከት ታኖርሃለች። ከእንግዲህ
አገርህ ኢትዮጵያ ወደውርደት አትመለስም ለበረከት የታደልከው ወገኔ እንደ አሁኑ ክፉ ትውልድ ፈጣሪህን
እንዳታስከፋው እነግርሃለሁ። አሁን ቁጣውንም ጥፋቱንም ታየዋለህና ከፈጣሪህ ፈቀቅ እንዳትል ከዚህ ጥፋት
በኃዋላ በበረከቱና በቸርነቱ ብዛት ደስታህ እጅግ ስለሚበዛ በሥጋ ምቾት ተጠልፈህ ከፍቅሩና ከቸረህ ጸጋው
እንዳትኮበልል ተጠንቀቅ!!
የተባረከው ወገኔ አንተ መልካሙን ታያለህ ልጆችህም እንዲያዩና ለትውልድ እንዲያዘልቁ አብረን ታምነንና
ለአምላካችን ቃልና ትእዛዙ ተግተን አገራችን በፈጣሪ ፊት እንደታመነች፣ እንደተወደደች፣ እንድትዘልቅ
የሚያደርገውን ሥራ እንሥራ!!
በፍቅሩ ኑሩ የሚጠላውን ጥላ፣ የሚወደውን ውደድ፤ አሁን የምታየውን ዲያብሎስ የዘራውን አመጽና የጥፋት
አዝመራ ከምድርህ አጥፋ፣ እውነትን ብቻ አንግስ። ሙሴ በእስራኤላውያን ክህደት ሲበሳጭ እግዚአብሔር
ያለውን ልታስብ ይገባሃል። ጌታ እንዲህ ነበር ያለው፣ ሙሴ ባሪያው ይህንን ልቡ ጠማማ ሕዝብ ላጥፋው ተወኝ
አንተንም ለታላቅ ሕዝብ መሪ ላድርግህ ነው ያለው፣ ያ ታላቅ ሕዝብ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ሙሴ
አስተዳደርን የተማረው ከኢትዮጵያዊው የሚስቱ አባት ከዮቶር ነበር። ኢትዮጵያ በህገ ልቦና፣ በህገ ኦሪት፣
ዛሬም በህገ ወንጌል ያለውን ስርዓት ሳታፋልስ ትውፊቱን ጠብቃ መጥታለች። እግዚአብሔር አምላካችን በባሮቹ
በኩል ያስተላለፈውን ቅዱስ ቃሉን፣ በጥንቃቄ ጠብቃ ላንተ ለዛሬው ትውልድ አድርሳለች። ሌላው የናቀውን
የጣለውን የደለዘውን የቀነሰውን ተግባር ሳትከተል በትክክል እንደነበር እንደቃሉ ጠብቃ አኑራለች።
ከዓለም ሁሉ በሚለየው የእምነት ስርዓትዋ ዛሬም ሁሌም እንደ ጠል በሚንጠባጠብና እንደ ምንጭ ውኃ
በሚንቆረቆር ዜማዋ ፈጣሪን ታመሰግናለች።
ታላላቅ መሪዎችን እግዚአብሔር ሰጥቶአት ነበር። እነ ካሌብን፣ እነ ኢዛናን፣ እነ አብርሃ ወአጽብሃ፣
እነላሊበላን እነ ዘርአያዕቆብን ወዘተ … በእምነቱም በሥጋውም አገዛዛቸው የገነኑትን አሳልፋለች። ግዛትዋም
እጅግ የሰፋና እስከ የመን የዘለቀ ነበር። በየዘመኑ የተነሱ ጠላቶች ሲቀንስዋት ሲሸርፍዋት መጡ፣ መሪዎቹም
በታሪክ እያነሱ መጡ፣ የቅርቡን ብናነሳ ከዘመነ መሳፈንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ታሪክ በድንበር ጉዳይ ብዙ
የተወሳሰበ ሁኔታ ተፈጥሮና እስከዛሬ ተወሳስቦ እንደቀጠለ እናያለን። በታሪክ ያነሱና አገራቸውን እየሸረፉ
ለጠላት በመስጠት ለስልጣናቸው መደላደል ብቻ የሚደክሙ መሪዎች እነሆ ቆመን እያየን ነው! የታሪክ
ድንክነት ፈጽሞ የማያማቸው ናቸው።
ይሁንና ወገኔ አትጨነቅበት ጠላት በየአቅጣጫው በቃኘው በነደፈው አካሄድ ሁሉ ኢትዮጵያን ከምድረ ገጽ
አጥፍቶአል። ዛሬም የሚችለውን እያደረገ ነው። ይሁንና ፈጣሪ ሁለንተናዊ ጥበቃ ስላደረገ እዚህ ደርሳለች።
ከአሁን በህዋላ ግን ይህ ታሪክ ይቀየራል። ሃፍረትም መሸማቀቅም ለጠላቶች ይሆናል። የጠበበው የተሸረፈው
ወደነበረበት ብቻ ሳይሆን እጅግ በማትገምተው ሁኔታ ሰፍቶ ይንሰራፋል። በነካሌብ ዘመን የነበረው ብቻ ሳይሆን
ከዚያም በላይ ይሆናል። ወገኔ! ይግረምህ አምላክህ ይህንን ያደርጋል፤ ከዚህም አልፎ የሌሎች አገሮች ሁሉ

18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

እድልና እጣፈንታ በሙሉ የሚወሰነው እዚህ በታላቋ ኢትዮጵያ ይሆናል። ዓለምም የኢትዮጵያ ምርኮና በረከት
ይሆናል።
መዝሙር ዳዊት 36 (37) 9 ትንቢተ ሶፎኒያስ ምእራፍ 3
ኢሳይያስ ምእራፍ 57 ኢሳይያስ ምእ 62 ፡ 1 – 5
መዝሙር ዳዊት 57 (58) መዝሙር ዳዊት 56
ወገኔ ልብ ብለህ አስተውል ፈጣሪህ ለክብሩ ሊመሰገንበት በእውነት ወዶሃል ቅን ፍርዱንም እንደፀሐይ
ሊያወጣ ወስኗል። ስለዚህም እኔ ወንድምህ የምመክርህን ታናሽ ምክር አድምጥ!!
ለሰው ልጅ ሁሉ ፍቅር ይኑርህ ክፋትን፣ ጭካኔን፣ ስስትን፣ ምንዝርናን፣ ሌብነትን፣ መልካም ያልሆነውን
ሁሉ ፈጽሞ ከራስህ አርቅ በእምነት ወንድምህ እህትህ ለሆኑ ለአገርህም መታመን ይኑርህ ከዚህ ሁሉ በላይ
ፈጣሪ አምላክህን በፍፁም ልብህ በፍፁም ሃሳብህ በፍፁም ነፍስህ ውደደው!!!

ስለአሁኑ መሪዎቻችንና ስለ እጣፈንታቸው።

ስልጣንስ ወደእግዚአብሔር ልጆችና አገልጋዮች እንዴት ይዞራል! የሚለውን ከዚህ በታች በዝርዝር ስለምናይ
በአንክሮ ተመለከተው።
መላው ዓለም በምስጢርም ሆነ በግልጽ ሲደክም ይህችን የተቀደሰች የተባረከች ምድር ኢትዮጵያን ለማጥፋትና
ከምድረ ገጽ ፈጽሞ ለመፋቅ ነበር። በነበር ቀረ እንጂ! አዝማቹም የቀደመው እባብ ዲያብሎስ ሆን ሁሌም
ዘመቻው የሚያነጣጥረው በእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳብ ላይ እንዲሁም በሰው ዘር ላይ በሙሉ ነው። ማንኛውም
አገር ሰለጠነም አወቀም ከእኩያው ጋር ከሚጋጭ ይልቅ ይህችን ድሃ አገር ማጥፋት ቀዳሚ እቅዱ ያደርጋል።
ይህንንም ሲፈጽም ኖሮአል አሁንም ይህንኑ ተግባር ያለማቅዋረጥ ሲያደርግ ይታያል።
አረቡና የአረቡ ዓለም፣ አሜሪካና ወዳጆችዋ፣ ኤሽያዊውም፣ ጥቁሩ አፍሪካዊም ለኢትዮጵያ ያላቸው ሰሜት
ሁሌም የደፈረሰ ነው ለምን ቢባል ኢትዮጵያ ሃገራችን በሁለመናዋ የተለየች ናትና!! እስቲ ፈረንጁን ከፈረንጁ
አስተያዩት በባህሉ በስብእናው በሁለመናው ተቀራራቢ ነው። አረቡንም እዩት ያው ነው ጥቁሩም ተመሳሳይ
ሁኔታ ነው የሚታይበት፣ በኤሺያዊውም ተመሳሳይ ክስተት ነው የሚስተዋለው። ከዚህ ሁሉ የምትለየው
ኢትዮጵያና ሕዝቦችዋ ብቻ ናቸው። በእምነትም በባህልም በተፈጥሮ ንቃትም በታሪክም በሁሉም ትለያለች
ስለዚህም ሁሉም የዓለም ፖለቲከኞችና መሪ በአንድም ሆነ በሌላ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ጉዳይ ሲመጣ የጋራ
ግንዛቤው በጋራ መጥላትን ነው። ከዚሁ የህሊና ጥመት በሚመነጭ የጥፋትና የክፋት ሥራ መሥራት ነው።
ለምን ይህ ሆነ! ይህ የሆነው ሰዎችን በመንፈሳዊ ህሊናቸው እንዳይገዙ የቀደመው እባብ ሥራውና ተግባሩ
ነውና ከሞላ ጎደል ሁሉንም የዓለም ክፍል በሚሻው መልክ ነድቶ ጠፍጥፎና ቀርጾ እንደሚሻው አድርጎታል።
እሱ ያቀደውንና ያስጨበጠውን እንደ ህልውናና እንደ እውነት ተቀብሎታል። ስለሆነም ለሌላው ዓለም አባታቸው
ዲያብሎስ ስለሆነ የሱ ጠላት ደግሞ ጠላታችን ነው። የጨለማው ገዢ የጨለማ ሥራ መሪ ነው። ስለሆነም የዚህን
ተጻራሪ የሆነውን በኢትዮጵያ የሚታየውን፣ ብርሃናዊ እምነት አይቀበልም።
ኢትዮጵያ የብርሃን ሀገር ናት። ዘመንን ሁሉ ቆርጦ የመጣውን እውነት የጨበጠች ፈጣሪ አምላካችን በየዘመኑ
ያስጨበጣትን የብርሃን ሕግና ቃል አጽንታ የኖረች ናት። በመሆኑም ዓለም ሁሉ ይህንን የእውነት መንገድ
ስቶ በጨለማው የአለማዊ መንገድ በመሄዱና እውነትን በመናቁ ለኢትዮጵያ የተሰጠውን ጸጋ ስለአጣ ሥራው
ይህንን እድልና እውነት የጨበጠችውን ኢትዮጵያን አጥብቆ ይጠላል። በዚህ መንፈስና ስሜት በመገዛት የተለያየ
አይነት ጥቃት ይሰነዝራል። በፈጣሪ ፊት የከበረውን እምነት (ተዋህዶ ኦርቶዶክስን) ያጸናች፣ በኑሮ ስርዓትዋ
በወንድማማችነት ፍቅር የተሞላች ዘወትርም ለፈጣሪያዋ ከልቡዋና ባለማቋረጥ እንደ መልካም ጠል በሚመነጭ
19
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የምስጋና ጸሎት እንደ ጅረት የምታፈስ የቅኖችና የየዋሆች አገር ነች። በዚህም ዲያብሎስ እጅግ ስለተጠላች
የሰይጣን ልጅ ሁሉ ከአያት ቅድመ አያቶቹ ጀምሮ 7000 ሺውን ዘመን በሙሉ በፊታውራሪው ዲያብሎስ
አማካኝነትና አዝማችነት ያለማቋረጥ ሲዘምትባት ኖሮዋል። አሁንም የሚታየው እውነት ይሄው ነው።
በዚህ አስከፊ የመከራና የችግር ወቅት በመፈተን ላይ ያለችው አገራችን ኢትዮጵያ ታላቁን የፈጣሪዋን ተስፋ
ጨብጣ ያለች መሆኑን ሁሉ ያውቃል። ታዲያ የዚች ታላቅ አገር የጥፋትዋ መሪዎች እነማን ናቸው?
የዛሬው መሪዎቻችን ፈጣሪን የማያውቁ፣ በጭካኔ የተሞሉ፣ ይህችን አገር የረገጡ፣ የጠሉ ባህልዋን
እምነትዋን፣ ህልውናዋን የናቁ ናቸው። በሃይላቸው ታምነው የሚገዙ ናቸው። ለጥፋትም የተላኩ ናቸው። ሕዝብ
ለአምላክ አልታዘዝ ሲል ሲያምጽ ለመቅጣት ሲል ፈጣሪ ጨካኝ ገዢዎችን እንዲልክ ሁሉ፣ የኛዎቹም በዚሁ
መስፈርት የመጡ ናቸው እንጂ በራሳቸው ጉልበት የቆሙ አይደሉም። ለነሱ ግን ይመስላቸዋል። ያውቁታልም
ተልዕኮውን ግን አይረዱም። የሚነዳቸውም የሚያዛቸውም ለዚሁ ተግባር የተመደበው አጥፊ መላእክ ነው።
ስለመሪዎቻችን፤ ስለባህሪያቸው ማንሳት ምንም አይጠቅምም። ሁሉም ወገኔ ያውቃቸዋልና፣ ውሸትን በራሱ
በክፉ ሥራ የፀኑ መሆናቸውን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ያውቃል። እጣ ፈንታቸውን ማንሳት ሰዓቱ ስለሆነ
የግድም ተገቢ ነው። እነሱም ካልተረዱት ቢያውቁት መልካም ነውና!!
ልብ ብላችህ አድምጡ! ጊዜው ፍፁም የጨለመባችሁ መሪዎቻችን!! በቅድሚያ የምለው ቢኖር ስለእድል
ፈንታችሁ ነው። ሰው እንደመሆናችሁ መጠን እጅግ አዝናለሁ። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ባትከሰቱ በተሻለ ጥሩ
በሆነላችሁ ነበር!!
ይህ ያለንበት የታሪክ ወቅት በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም እጅግ ትልቅና ቀድሞም ያልታሰበና ያልታየ
ነገር የሚከሰትበትና የሚታይበት ወቅት ነው። የጨለማው 7000 (ሰባት ሺ) ዘመናት ተሸኝተው ለምሕረትና
በረከት የተሰጠው የሰው ዘር ለእረፍት ለ1000 (አንድ ሺ) ዘመን የሚዘልቅበት የመሸጋገሪያ ድልድይ ላይ
እንገኛለን። የሚሻገሩት ውስን ናቸው። የማይሻገሩት ደግሞ እጅግ የበዙ ናቸው።
የዘመናችን የአገራችን አለቃና ምንዝሮች ግን ከሚሻገሩት ሳይሆኑ ከማይሻገሩት ናቸው። እንዲያውም
የሚገርመው በዚህ የመጨረሻ ሰዓት እንኩዋን እራሳቸውን ለማሹለክ የሚያስችላቸውን ሥራ ሲሠሩ አይታዩም፣
አይጸጸቱም ዛሬም ከፈጣሪ ጋር ሊዋጉ ይከጅላቸዋል። የሚገርመኝም ይኸው ነው። የምታሳዝኑትም በዚህ ነው።
ሰው እንዴት አያስተውልም! ሰው እንዴት ከፈጣሪው ጋር ደፍሮ ሊታገል ይሞክራል? ሰው እንዴት ወደ
ረግረግ እየሰጠመ ለመዳን አይጥርም? እምትገርሙ ናችሁ። ሁሉ ከእጃችሁ ይወጣል! ይተናል። አንድህም
አታመልጥም ወዴት ነው የሚመለጠው? በዓለም ሁሉ ያለ ወንጀለኛ፣ አመጸኛና ሓጢያተኛ የዲያብሎስ
ፊትአውራሪ እዚህ ኢትዮጵያ መጥቶ (ተገዶ) በፍርድ አደባባይ ይቆማል!! ቅን ፍርድንም ይቀበላል።
ታዲያ እናንተ ወዴት ትሄዳላችሁ? ተይዞ ፍርዱን ወደሚቀበለው ወደሚጠረገውና ወደሚጠፋው ዓለም፤
እጅግ ያሳዝናል ያልኩትም ለዚህ ነው።
ብዙዎች አለቆች ወገናቸውን በድለውና አጥፍተው ወደሌላው ዓለም መሸሽ የተለመደና ሁሉም መሪ
የሚያውቀው ዘዴ ነው። ይህ ዘዴ ግን መሸበትና ወደ ታሪክ መዝገብ ተጣለ። መሸሻ የለም ቢሸሽም የትም
ስፍራ ቢሆን ከተደበቀበት ተይዞ ተዋርዶ ለፍርድ መቅረብ አይቀርም። ይህን ደግሞ ለመትረፍ ያድላችሁ
እንጂ ታዩታላችሁ። መፍትሄውና የሚሻለው ግን ከዚሁ ከብርሃን ችሎት ቀርቦ ቅን የእግዚአብሔርን ፍርድ
መቀበል ብቻ ነው። ፈራጁም መሃሪውም እንደልባችሁ ምንነት የቅጣት መጠኑን የሚወስነው የሰራዊት ሁሉ
ጌታ እግዚአብሔር ነው።
ጀት ታንክ ጠብመንጃ የታመነ ወታደር ሁሉም አብዋራ ናቸው። አንዳቸውም አያድንዋችሁም። መሪዎቻችን
ከዚህ ሁኔታ የሚያወጣቸው ምንም ዘዴ የለም። የዘራችሁት የአመጽና የክፋት ዘር በህዝበ እግዚአብሔር ላይ
20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

ያደረሰው ጥፋት ብዙ ደም፣ ብዙ እንባ፣ ብዙ የሰው ሕይወት እንዲያልፍበት ሆኖአል። ይህ ደግሞ በፈጣሪ
ተመዝኗል፣ ፍርዱም ወጥቷል። ስለዚህ ወደየትም ማምለጥ አይቻልም። ዛሬ የታመናችሁበት ስልጣን እሳት ሆኖ
ይበላችኋል። ለሱ ብላችሁ የደከማችሁት ድካም ሁሉ መና ይሆናል። የትም አኑሩት የትም ያከማቻችሁትን፣
የገነባችሁትን ለምሕረት የታደለው ይበላዋል። ያከማቻችሁበት አገርና ወገን ይጠፋል። የሚረዳችሁ ሁሉ እንደ
ጪስ ይተናል።
አድምጡኝ፤ ጆሮአችሁንም ክፈቱ፤ ዐይናችሁንም ግልጡ! ይህ ስልጣን በከንቱ ደከማችሁበት ነገ የሚሆነውን
የማይቀረውን ልንገራችሁ።
በርግጥ ነው የምላችሁ፤ ይህንን ስልጣን ዓለምንም ሁኔታ ለማሰረከብ ለምናችሁ፣ ተንበርክካችሁ፣ ጮሀችሁ
ለመላቀቅ ትጥራላችሁ። ነገር ግን በእናንተ ሃሳብና ምኞት አይሆንም። ስልጣን ሰጪ፣ ስልጣን ነሺ ጌታ ስለሆነ
በሚገባ ከተጎዳችሁበት በህዋላ ፈጣሪአችን ሲያዝን ብቻ እንረከባችኋለን እንጂ እኛ የልዑል ባርያዎች ስልጣን
ስጡን ብለን አንለምንምም አናደርገውምም! ደግሞስ ከማን ነው የምንለምነው! ስልጣኑ የአባታችን የፈጣሪአችን
እኮ ነው!! ይህንን ሁላችሁም ልታወቁት ይገባል። በመሆኑም ስልጣኑ ከእናነተ ተነጠቆ ለልጆቹ ይተላለፍ
ዘንድ በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ችሎት ተወሰነ፣ ጸደቀ፣ ታተመ። ቀሪው የሽግግር ጊዜ ነው። ያ ደግሞ ዋጋ
የምትከፍሉበት ወቅት ነው።
ይህ እንዴት ይሆናል! ሲሆን ታዩታላችሁ በደጃችሁ አይደለም እንዴ ሁሉም ነገር! ምን ጊዜ አለና መጠበቅ
ብቻ ነው።
የእምነት ሰው በእምነት ዓይኑ ያያል! ከሃዲና ፈጣሪውን የማያዉቅ የሚያይበት ዐይን ስለሌለው ድንገት
ጨለማ እስከሚውጠው ድረስ እያፌዘና እያላገጠ፣ አሊያም በድንጋጤ ተውጦ ፍጻሜውን ይጠብቃል!
ይህ የፍርድ ቃል መሰራጨትና በሕዝብ መታወቅ ከጀመረ ጀምሮ ጊዜው ስለተፈጸመ ወደ ተግባር መለወጥና
ጠረጋው ይጀመራል!!!
ወገኔ ሁሉ እራስህን አዘጋጅ መጪው ጥፋት በአንደበት እንደሚነገረው ቀሎ የሚያልፍ አይደለምና!! ፈጥነህ
እራስህን በፈጣሪ እጅ ጣል! የመዳኛው መንገድ አንድ ብቻ ነው። እሱን በታመነው ለወደዱት፣ በእሳት አጥሮ
ለሚጠብቀው የሰራዊት ጌታ ጉያ ገብቶ መሸሸግ ብቻ ነው!! በብርቱ እምመክረውም እማስጠነቅቀውም ይህንን
ብቻ ነው።

አንድ ማሳሰቢያ ለመሪዎቻችን ልገልጽ እወዳለሁ!!

መንግሥት እንደ መንግሥት እራሱን ቢያስገዛ መልካም ነው። በግሌ ሀላፊነትን የማውቅና የዚህንም ሸክም
የምረዳ ነኝ። ትዕግስትን ማድረግ ፈጣሪ አስተምሮኛል። ይሁንና ለረጅም ጊዜ ትግስትን የሚፈትን ሥራ ስትሠሩ
ቆይታችኋል። የደህንነት ሰራዊት፣ ወሬና መረጃ ለቃሚ፣ ታጣቂ በማሰማራት ስልታዊ የማጥቂያ ዘዴ ቀይሳችሁ
በኔ ላይ ስትሰነዝሩ፣ ስትዘምቱ ቆይታችኋል።
ትዕግስትም ያልቃል ስለዚህ ከድርጊታችሁ ታቀቡ እላለሁ!! ይህንን የምለው ሰው ምንም ቢሆን ሲጎዳ ማየት
ስለሚከብደኝ ብቻ ነው። አትሳሳቱ፣ እኔ ስለእናነት የማላውቀው የተደበቀ ነገር አለ ብላችሁ እንዳትገምቱ።
ጭለማ ብርሃንን አይመረምርም፤ ብርሃን ግን ጨለማን ይመረምራል። ተሰውራችሁ ማናቸውንም ነገር ስታቅዱ፣
ስትወጥኑ፣ ስትወጡም፣ ስትገቡም፣ ህልማችሁንም፣ ሁሉንም ፍንትው አደርጎ ያሳየኛል። ልብ ልትሉ ይገባል
እኔ መታገሴ እንጂ ፈጣሪን ለመጠየቅና ዋጋችሁን ወዲያው እንዲሰጣችሁ ለማድረግ የጥቂት ሰከንዶች ጥያቄ
ብቻ ነው። እኔ ከመሰለኝ በጎም ሆነ ክፉ አምላኬን ከጠየኩት ምንም የምከለከለው ነገር እንደሌለና ለኔ ለባርያው
ለልጁ ጆሮም ክፍት ዐይኑም በኔ ላይ መሆኑን ልታውቁት እወዳለሁ። ስለዚህ ትዕግስቴን አትፈታተኑ። ስለኔ

21
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

የምገልጽላችሁ ይህን፣ ያንን አደርጋለሁ የሚላችሁ የአየርም በሉት የምድር፣ የውኃም በሉት ወይም ጳጳስም
ደብተራ እንዲሁም ሼኪ ሁሉም ይድከሙላችሁ። የት ድረስ እንደሚሄዱ አውቃቸዋለሁ እነሱም ያውቁታል።
ስለዚህ የዲያብሎስ ሰራዊቶች ላለቀባችሁ ጊዜ አትድከሙ! ቀዩን መስመር አልፋችሁ ለመሄድ ተቃርባችኋልና
ደግማችሁ አስቡ ለኔ አይገደኝም! ዙረያዬን ያለውን የእሳት ግንብና የሚባላ እቶን ያሰፈረው አባቴ የቁጣውን
እሳት እንዳይግታችሁ እነግራችኋለሁ! ከእንግዲህ ድጋሚ የሚያነጋግረን ሰዓት የለምና!!
በመላው ዓለምና በኢትዮጵያም ላለህ ህዝበ ክርስቲያን በሙሉ!
»» ይህንን የጽሁፍ መልእክት ስታነብ የፈጣሪህን ድምጽ መስማትህን እወቅ!!!
»» በስሜት አትገንፍል፣ ራስህን ግዛ፣ ደስታህም በአግባቡ ራስህን በመግዛት ይሁን!!
»» ትህትናን ልበስ፣ ለወንድምህ እዘን፣ በሚደርስበት ጉዳት አትደሰት ቢድን ኖሮ ወንድምህ ነበርና!!!
»» የእግዚአብሔር ሰው በነገር ሁሉ እራሱን ያስገዛለና! አንተም ትዕግስተኛ ሩህሩህ ቸር ሁን!
»» ለሌላው የሚጨነቅ እውነተኛ ነው፤ አንተም ወደ አመጽ አትሂድ፤ ሥራውን ሊሠራ የወጣው
የእግዚአብሔር ኃይል የሥጋ ድጋፍን አይፈልግምና ተጠንቀቅ!!

ስለዚህ መልእክት መሰራጨት

ጌታ አንድ ምሳሌ መስሎአል ለሦስት ሰዎች መክሊት ሰጠ። እንደየአቅማቸው ሰጣቸው እንዲነግዱ፣
እንዲያተርፉ ሶስቱም በየፊናቸው ተሰማሩ፣ ሁለቱ ነገዱ አተረፉ ትርፋቸውንም ይዘው መጡ። ተመሰገኑበት
ተሸለሙበት። አንዱ ግን ሰርቶ ነግዶ ከማትረፍ ይልቅ ደበቀ፤ ጌታ ሲጠይቀውም ያንኑ ጌታ የሰጠውን አንዱን
መክሊት አቀረበ ጌታ ረገመው ተኮነነ፣ እድል ፈንታው ጨለማ ሆነ።
ይኽን ያልክዋችሁ በከንቱ አይደለም ይህንን የሰራዊት ጌታ መልእክት ባላችሁ አቅም ሁሉ ለመላው ሕዝብ
አድርሱ፣ በትኑ!! በዚህ ንስሓ የሚገባ አለ ይድናልም፤ እናንተም ነገዳችሁ፣ አተረፋችሁ፣ ሌላው ደግሞ ይህን
መልእክት ይሰማል፤ ንስሓ ሰለማይገባ አይድንም ይፈረድበታል። በዚህም አትርፋችኋል። ምክንያቱም ፍርድ
ያገኘው ተመክሮ ተነግሮት እንዲመለስ ተመክሮ ስለሆነ በዚህም ለፈጣሪያችሁ ሰለታመናችሁና ሰለታዘዛችሁ
አትራፊ ናችሁ።
ነገር ግን ደብቃችሁ በቤታችሁ ቀብራችሁ ብታኖሩት! እንደ ሃኬተኛው ሰው፣ መክሊት ቀባሪ ትሆናላችሁና
ተጠንቀቁ። እግዚአብሔር የሚወደውና የሚደሰተው የሰማችሁትን አምናችሁ፣ ከተሳሳታችሁበት ፈጥናችሁ
ስትመለሱና ሌላው ወንድማችሁ እንደናንተው እንዲድን ስትጥሩ ብቻ ነው።
»» ለሌሎች ሀገሮች መልእክቱ በአግባቡ ይደርስ ዘንድ በአማርኛም፣ በእንግሊዘኛም አንብባችሁ በውጪ
ላሉት ወገኖቻችሁም ሆነ ለሁሉም የሰው ዘር እንዲደርስ አድርጉ። በዘመኑ ዘዴም ተጠቀሙበት።
»» በፖስታ፣ በኢሜይል፣ በፋክስ ላኩት ይድረሰው ፍርዱን ይወቅ፣ አውቆም ይዳን አሊያም ሞትን
ይቀበላል።
»» ዛሬ ነው የማትረፊያው ሰዓት፣ ነገማ በምሕረት የታሰበው ሁሉ ከምድርም ከሰማይም የሚፈስለትን
በረከት ስለሚያግኝ እምትጨምርለት ምንድነው!!
የፈተናው ሰዓት አሁን ነው እንዲድን መርዳት አሁን ነው። እሳቱ በሙሉ ኃይሉና በታላቅ ቁጣ ከመፍሰሱ
በፊት። ቤት ሲቃጠል ከውስጡ ሰውን ለማዳን እንደሚደከም ሁሉ እናንተም ጣሩ። ላረጋግጥላችሁ የምወደው
ምንም ጊዜ አለመኖሩንና ፍፁም መምዋጠጡን ነው።
እኔና ወንድሞቼን ለማወቅ አትባዝኑ! አጠገባችሁ ስላለን በሥራው ላይ ብቻ አትኩሩ!!
ወደው ሳይሆን ተገደው እንክዋን ለኢትዮጵያ ለባለጉዳዩ ሕዝብ፣ ለመላዉ ዓለም ሕዝብ ባላቸው መገናኛ ዘዴ
ሁሉ በቀን አስር ጊዜ ያወሩታል። የዓለም ሕዝብ ሁሉ መሪም ተባለ ምንም ይሁን ነፍሱን ለመታደግ በጭንቀት
የሚበረው ወደኢትዮጵያ ይሆናል!!

22
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሁለት

እድለኛ የኢትዮጵያ ሕዝብ በእውነት የምትወደድ ሕዝብ ነህ!!


እግዚአብሔር በሥራችሁ ሁሉ ይባርካችሁ!! እመቤቴ ድንግል ማርያም ዘወትር በእቅፍዋ ታኑራችሁ!
ከክቡር ቃሉ የተጠቀሱትን (ከመጽሃፍ ቅዱስ) ጥቅሶች አስተውላችሁ አንብቡ!!
አስጀምሮ ላስጨረሰኝ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይኹን
ዘወትር ከኔ ላልተለየችኝ እናቴ ድንግል ምስጋና ይሁን

ከታመነው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ባሪያና አገልጋይ


ተፈጸመ!!
የገጹ ብዛት 19 (አሥራ ዘጠኝ) መሆኑን አትዘንጋ!!
ስታሰራጭ በፍፁም ከገጽ አታጉድል!!
በፊደል ግድፈት ላይ ሳይሆን በመልእክቱ ላይ ብቻ አተኩር!!
መዝሙረ ዳዊት 36(37)፤ 25 - 40

23
መልእክትሦስት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

መልእክት ሦስት
በምድሪቱ ሁሉ ላለህ የሰው ዘር በሙሉ
ተጻፈ በመጋቢት 19 ቀን 2001 ዓ.ም
ይህ መልእክት የመጨረሻ የአፈጻጸም ውሳኔ ሲሆን የመጀመሪያውንና የሁለተኛውን መልእክት ወደ አፈጻጸም
የሚቀይር ውሳኔ ነው።

ማስታወሻ

»» መልዕክቱን በጥንቃቄ ያንብቡ።


»» ሲሰጡ ሁሉንም ገጾች ይስጡ። አይቀንሱ፥ አይጨምሩ፥ አያሻሽሉ። ይህን የሚያደርጉ አለቅጣት
አይታለፉምና!
»» እኔ በነጻ እንደሰጠኋችሁ እናንተም በነጻ ስጡ ፈቅደው ወደው ከሰጡአቹህ ተቀበሉ። በረከቱ
ይበልጥብናል ካላችሁ አትቀበሉ።
»» ፋክስ አድርጉት፥ ኢሜይል አድርጉት፥ በድረ ገጾቻችሁ ልቀቁት፥ በፖስታም ላኩ።
»» በጋዜጣ በመጽሔት አትሙት አሰራጩት በሬዴዮ፥ በቴሌቭዥን ልቀቁት።
»» እንደ ትዕዛዙና ምክሩ ለማያደርጉ በትዕዛዙ ውስጥ የሚገጥማቸውን ያንብቡ።
»» በጎ ለመሥራት ማንም አይከለክልም።
»» መሪም ሆነ ተመሪ ሁሉም የሚመዘነው እንደ መፀፀቱና እንደ ቅን ተግባሩ ነው።
»» በጎ ሥራም የሚጀምረው ከትንሹ ነውና!

መልካም የመረዳት ንባብ ይሁንልዎ!

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅደስ አሀዱ አምላክ አሜን!


1–ሀ መግቢያ

የፍጥረት ሁሉ ጌታ ስሙ ይክበር ይመስገን፣ በዓይናችን ከምናየው፣ ከምድርና ፀሐይ በብዙ ትሪሊዮን


ክብደት ስፋትና እርቀት የሚበልጡትን ከዋክብቶች የፈጠረ፤ በሰማይ ላይ እንደማይቆጠር አሸዋ የበተነ፣ ሁሉን
ቻይ ፈጣሪ፣ በብዙ ሚሊዮን የሙቀት ዲግሪ ሴሌሺየስ የምትንቀለቀለውን ፀሐይ በአንድ ስፍራ አቁሞ ለምድርና
በውስጧም አልቆ ለፈጠረው ሰውና ፍጥረታት በሙሉ እንድታገለግል፣ ብርሃንና ሙቀት እንድትለግስ ላደረገ
አምላክ ከብርሃን እጅግ በፈጠነ ሩጫ የሚከንፉትን በቅጽበትም ለሚሰወሩት በትልቅነታቸው ከፀሐይ በብዙ
ቢሊዮን የሚበልጡትን ከዋክብት ህልው ላደረገ፣ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ ይክበር ይመስገንና፤
ይህን አምላክ በምን ልክ በምን ቋንቋ በምንስ የፍጥረት ብልሃት ትገልጹታላችሁ? ትመስሉታላችሁ? ጌታችን
ፍፁምና ከሕሊናችን ዕሳቤና ግምት እጅግ የራቀ ነው። በምንም አንመስለውም ስንወደው፣ ስንታዘዘው፣
ስናመልከው ያኔ በቸርነቱ፣ በበረከቱ፣ በአባትነቱ፣ በርሕራሄው፣ በፍቅሩ፣ በቅን ፍርዱ እናውቀዋለን።
ስንንቀው፣ ስንክደው፣ በእርሱ ምትክ ሌላ አምላክ ስናቆም የቁጣውን በትር የሚያሳርፍ ምንም አምሳያ የሌለው
አምላክን በምን ትገልጡታላችሁ?
ከሰው ይልቅ እንስሶች በተሰጣቸው የደመ ነፍስ እይታ የተሰጣቸውን ስርዓተ ሕይወትና አኗኗር ሳያዛንፉ ለሰው
አገልግለው ያልፋሉ። ባጭሩም ሆነ በረዘመ ዘመናቸው ፈጣሪአቸውን ያመሰግናሉ፤ ሰውስ? የከበረው የአዳም
ዘርስ? እንደ ፍጥረት ልቀቱ ነውን? እንድናስተውል አዕምሮ ለሰጠን አምላክ ምስጋና ይገባዋል። ሰውን ለክብሩ
ሊመሰገንበት በራሱ አምሳል እጅግ አልቆ የፈጠረ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ይክበር ይመስገን። በአንድነቱ በሦስትነቱ
የከበረ ጌታ የተመሰገነ ይሁን በማንኛውም ፍጥረት እሳቤና ህሊና የክብሩ፣ የግዝፈቱ፣ የጥልቀቱ፣ የብርሃን
ምንጭነቱ የማይዳሰስ ጌታ ሁሉን ህልው የሚያደርግ፣ ሁሉን የሚያሳልፍ፣ማንም በማይቀርበው ብርሃን ላይ፣
ማንም ሊያየው በማይቻለው የእሳት ፍምና ምንጭ ላይ ዙፋኑን የዘረጋ፣ የገዘፉትንም ያነሱትንም የሚታዩትም
የማይታዩትም ረቂቅ ፍጥረት ሁሉ ቅዱስ! ቅዱስ! ቅዱስ! እያሉ ሌት ከቀን በምስጋናቸው የሚያረሰርሱት እንደ
አርሞንኤም ጠል፣ ሳያቋርጡ ምስጋናው ዘወትር የሚፈስለት ጌታ ይክበር ይመስገን አሜን።
የዳዊት መዝሙር 97 (98)፤
የዳዊት መዝሙር 148
እኔም የሥላሴ ባርያ! እጅግ ባደፈችው አንደበቴ፣ እጅግ በምታንሰው ሰውነቴ ደፍሬ አመሰግነዋለሁ። ቃሉን
ትዕዛዙን፣ ፍርዱን፣ ተግሳፁን፣ ቁጣውን፣ በረከቱን፣ ምሕረቱን ለሰው ዘር በሙሉ ከሁሉ በሚያንሰው በእኔ
ይነገር ዘንድ ፈቃዱ የሆነ አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን አሜን!
መዝ. 18(19)፥7–14
የዛሬው መልእክት አዲስ ትእዛዝ አዲስ መልእክት የሚመነጭበት ሳይሆን ቀድመው በተገለጹት 1ኛ
እና 2ኛ መልእክቶች እንደተገለፀው፣ በልዑል እንደተወሰነው እና እንደታዘዘው እኔም ሳይጨመር ሳይቀነስ
እንደገለጽኩላችሁ ሁለቱም መልእክቶች የሚወቅሱ፣ ፍርዱን የሚገልፁ ናቸው። የሰራዊት ጌታ ፍርድ በመጻኢ
ሕይወታችን ላይ ምን እንደሚመስል በየትኛው ተግባራችን ላይ እንደተመሰረተ ጠቅልሎ የሚገልጽና ፍርዱንም
የሚያሰማ ለንስሓም እድል የሚሰጥ ነው። የቅጣቱንም ሁኔታ የሚገልፅና ጅምሩንም በግልፅ እያሳየ ያለ
ቀጣይነቱንም የሚያሳይ ነው።

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ታዲያ ይህ መልእክት ለምን ተጻፈ? የሚሌ ጥያቄ ሊኖር ይችላል። በእርግጥም ሊጠየቅ ይገባል። በአንደኛው
መልእክትና በሁለተኛው መልእክት የሰፈረው የጌታ ቅን ፍርድና ውሳኔ አፈጻጸሙን ጥልቀቱንም እናም
የሚመጣውን ውጤት የሚገልፅ በመሆኑ ይህ መልእክት ደግሞ የተበተነውን ለመሰብሰብ፣ የተሰበሰበውን
መልካም ፍሬ ለመሸከፍ ነው። በዚህ መልእክት የሁለቱንም መልእክቶች አፈፃፀም በዝርዝር ለመግለፅና በመላው
ዓለም ላሉ ሕዝቦች ሁሉ፣ እንደየ አደረጃጀታቸው የተፈፃሚነቱን ዝርዝር እንዲያውቁ በቅጣቱም ሆነ በምሕረቱ
የተጎበኙ ሁሉ ሊያደርጉ ስለሚገባቸው ዝርዝር መመሪያና ማረፊያ መደምደሚያ ለማስቀመጥ የታሰበ ነው።
በአምላኬም ይህንን እንዳደርግ የታዘዝኩ ስለሆነ ነው።
በዚህ መልእክት ለሁሉም መንግሥቶች፣ ድርጅቶች፣ መንፈሳዊ ተቋሞች፣ ቡድኖች፣ ግለሰቦች፣ ማህበሮች፣
ክፍለ አሕጉሮች፣ አገሮች በሁለቱም መልእክቶች ውስጥ ሲመዘኑ በልዑል ፊት ምን እንደሚመልሱ እንዲያውቁት
የሚያደርግ የሁለቱንም መልእክቶች ዝርዝር ማብራሪያና መመሪያ በመስጠት ዓለም ወዴት መጓዝ እንዳለበት
ከልዑል የታዘዘውን ለማሳወቅ ለሁለም የሰው ዘር ከእንግዲህ ከወዴት የመንፈሳዊንም ሆነ የሥጋዊን አመራር
እንደሚያገኝ የሚያስረግጥ ይሆናል። ሁሉም ልብ ይበል የቀደመው የዓለም ስርዓት ሁሉ ይሻራል። የመዋቀሻው
ዘመን አልፏል። አሁን በዓይናችሁ እንደምታዩት በጀሮአችሁ እንደምትሰሙት ዓለም በምጥ ጅማሮ ውስጥ
ናት። ስለሆነም ከእግዚአብሔር አገልጋዮችና ባሮች መንፈሳዊንም ሆነ ሥጋዊውን አመራር እንደ ልዑል ትእዛዝና
ፈቃድ መስጠት ግድ ነው። የኔም ሆነም የወንድሞቼ ኃላፊነት ግዴታም ነው። ጭንቁ እየበረታ ሲመጣ በጎችን
ማረጋጋት፣ ማፅናናት፣ ማፅናት፣ ወደ መልካሙ ስፍራ መምራት አለብንና!
ለመንጋው መሰማሪያ፣ መመሰጊያ፣ መጠለያ ማሳየት ወደዚያም መምራት የእረኞች ግዳታ ነው። ከበጎች
መቀላቀል የማይገባቸው ፍየሎች፣ ተኩላዎች በፍርድ እንዴት እንደሚጠበቁ ማረፊያቸውንም ያውቁት ዘንድ
የግድ ይላል። ተግሳፅን ንቀው ትዕዛዙን አፍርሰው በአመፅ አድገው፣ በክፋት አርጅተው ለመልካሞቹ እንቅፋትና
ጥፋት ሆነው ሁሌም እንደማይቀጥል ዳኛው ልዑል በቃሉ መሰረት እንደሚፈርድባቸው ሊያውቁት ይገባል።
ይህንን ኃላፊነት የተሸከሙ የበጎች እረኞች ከመንጋቸው ተኩላዎችን ማራቅና በጌታ ቅን ፍርድ ስፍራቸውን
ማስያዝ ይገባቸዋል። በአንድ ባሕርይ ሦስትነቱ ፍፁም የሆነ ልዑል የሰጠንን የእረኝነት ኃላፊነት ልንወጣ በስሙ
ለተጠራን ለታማንን ሁሉ የውዴታ ግዳት ያለብን ነን ለፈቃዱ የምትገዙ ሁሉ።
የእግዚአብሔር ቃል ዘመንን ሁሉ ያውጃል ዓለምንም በየዘመኑ ያፀናል። በየዘመኑ ያሉት ትውልዶቹም ሁሉ
በቃሉ ይፈርዳል፣ ይምራል፣ ይቀጣል፣ ይገስፃል ወደ እውነት መሄጃውን መንገድ ያመለክታል። ለሰው ያለው
ፍቅር መለኪያ የለውም የዚህ ሁሉ ዘመን ትዕግስቱ ለሰው ዘር ሁሉ ያለውን የፍቅር ርቀት ያሳያል። ሰውን
ከጥፋቱ ለመመለስ ወደ መንግሥቱ ወራሽነት በንስሓ እንዲመለሱ ለማድረግ ሁሉም የሰው ዘር የሚያውቀውን
ማንም ሊከፍለው የማይችለውን የኃጢአት እዳ በመክፈል በፍቅሩ ወደ መንግሥቱ እንድንፈልስ አድርጓል።
ለ5500 ዘመን የዘለቀ ትዕግስት፤ ለ2000 ዘመን የዘለቀ የምሕረትና የፍቅር ጥበቃ፣ የአባትነት ተግሳፅና ምክር
ማን ያደርገዋል? ለመሆኑ ይህንን ጌታ በምን ልንመስለው እንችል ይሆን? በየዘመኑ በስሙ ያተማቸውን በቅዱስ
መንፈሱ ያነፃቸውንና የሞላቸውን ነቢያትን፣ ሐዋርያትን፣ እረኞችን፣ ባሕታውያንን፣ መነኮሳትን፣ ከጳጳስ እስከ
ዲያቆን ለአገልግሎት ታምነው በመውጣት ለሰው ዘር በሙሉ የመዳንን መንገድ ሲያሳዩ ወደ ፍቅሩ መንግሥት
ሕዝብን ሲጠሩ፣ ሲወቅሱ፣ ሲያስተምሩ ማን አስተዋለ? እኛ ሰዎች ደፋሮች ነን። ለዲያብሎስም የጥፋት ሥራ
መማሪያ እና ከለላ ሆነናል። ለእውነት የመጡትን የጌታ እረኞች ምን አደረግናቸው ምንስ ከፈልናቸው። አዎ
ሁለም የሚያውቀው ነው። አሰርናቸው፣ አሳደድናቸው፣ ገደልናቸው ይህ የሚታይ፣ የሚዳሰስ፣ የሚዘከር
የጨለማ ሥራችን ነው።
ሰው ሆይ አድምጥ በምድር ላይ ከተበተነው ፍጥረት ሁሉ የምትበልጥ በማስተዋል፣ አስበህ በማደር፣
በማዋል የምትኖር ክፉና በጎን የሚለይ፣ ጥቅምና ጉዳትን የሚያውቅ አዕምሮ የተቸረህ፣ ሁሉም ሕይወት ያለው

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የምድር ፍጥረት ከበታችህ እንዲገዙ ልዑል ያደረገልህ፣ በአምሳል ፈጥሮ፣ በክብር አልቆ፣ በደሙ ዋጅቶ፣
ለማንም ያላደረገውን የፍቅር ፀጋውን ያለበሰህ፣ የሰው ዘር አድምጥ፤ በትዕቢት ተሞልተህ ለምን ትጠፋለህ?
በከንቱ ለምን ትጠረጋለህ? ለምንስ አጥፊህን ዲያብሎስን ትተማመናለህ? ለምንስ ወደ ጨለማው ትገሰግሳለህ?
ስንቶች ሊወቅሱ ወደ እውነት ሊመልሱህ ተነሱ? አንተስ ምን ከፈልካቸው? እንዴትስ ሸኘሃቸው? ለየትኛው
የእግዚአብሔር የታመነ አገልጋይ መልካም መለስክ? አንድም ምስክር የለህም። ሁለንም አሳደሃል፣ ሁሉንም
ገድለሃል፣ ሁሉንም አጥፍተሃል።
ለሚጠፋ ስልጣን፣ ክብር፣ ለሀብትና ገንዘብ ስትል የጥፋት እጅህን አስረዝመሃል። ለመሆኑ በዓለም ላይ
የነገሱ፣ የሰለጠኑ፣ በባለሀብትነት፣ በመሪነት፣ በጦር አዝማችነት ስማቸው ገኖ በሰዓቱና በጊዜው በተሰጣቸው
ትንሽ ዓመታት የዘላለም ስልጣን፣ ሀብት፣ ጉልበት ያፀኑ የመሰላቸው የሰው ዘር በሙሉ የእነሱ ባሪያና አገልጋይ
እንደሆነ በመቁጠር በንቀትና በትዕቢት የተጓዙ በኋላም ሳያስቡት የጨለመባቸው ስንቶች ናቸው።
ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 32 በሙሉ ይነበብ።
ከትላንቶቹ የማይማሩ የዛሬዎቹ ከቀደሙት ጨካኞች ብሰው በእውቀታቸው፣በጦራቸው፣በሃብታቸው፣
በገንዘባቸው ብዛትና በጦራቸው ታምነው ሰውን ለመግዛት በጭካኔ ለመንዳት ምን ያላደረጉት አለ። የዘመኑ
አጥፊዎች በዲያብሎስ በመመራት በእሱ ፈቃድና ትእዛዝ በመነዳት የሚተካከላቸው የሌለ ሆነዋል። በብልጠትም
ፈጣሪን የሚያታልሉ አርገው ያስባሉና።
ዛሬ በየአገሩ ያለ መሪ፣ ባለሀብት፣ ነጋዴ፣ ባለኢንዱስትሪ፣ የጦር አዛዥ፣ የፀጥታ ኃላፊ ቀን እንደ ሰው
ለብሶ የሚንቀሳቀስ የሚሊዮን ከበሬታን ስፍራ ይዞ የሚያዝ፣ የሚናዝዝ፣ ሲሆን ሌት ደግሞ ወደመኝታው
በመሄድና ፈጣሪውን ከማመስገን ይልቅ ወደ ጠንቋይ፣ መጽሐፍ ገላጭ፣ ኮከብ ቆጣሪ፣ ድቤ መቺ፣ ጫት
ቃሚ፣ ሼክ፣ደብተራ፣ ተብታቢ የአየር፣ የምድር፣ የውኃ፤ የጥፋት አጋንንት መላእክቶችን ሳቢ በማሰስ
ደጅ ሲጠና ይውላል ያድራል። ሲጎነበስ ሲሰግድ ሲለምን ያመሻል። የሚያዙትንም ሳያቅማማ ይፈፅማል።
ያስፈፅማል። የመረጃ ምንጮቹ፣ የስልጣን ምሰሶዎቹ፣ የገንዘብ ሰብሳቢዎቹ፣ አድርጎ ስለሚቆጥራቸው፤ አድርግ
የተባለውን ማንኛውንም የከፋ ሥራ ይሰራል።
እነዚህ የጨለማ ሰራተኞች ከተገዙላቸው ለአጭር ጊዜ የሚያገለግል ሲሆን የእግዚአብሔርን መንገድ ሰው
እንዳይከተል በማድረግ ወደ ጥፋቱ ሲነዱ፤ በንስሓ ለንስሓ ሳይበቃ፣ ከፈጣሪው ሳይታረቅ በቁሙ ወደ ውርደት
ቢሞትም ወደ ገሃነም የሚሰድዱት ናቸው። እነሱ ለፍርድ እንደተጠበቁ ሁሉ ሰው የቅጣታቸው ተሳታፊ የዘላለም
የጨለማ ወራሽ እንዲሆን ያደርጉታል። ዛሬ ተመቸኝ የምትል የዘመኑ ፈራጅ ፈላጭ ቆራጭ አዳምጥ! ዛሬ ብዙ
እንዲውም ሁሉም መሪዎች ማየት ይቻላል የዲያብሎስ ተገዥዎች ናቸው። ባለሃብቶች፣ ስለ እውነት የሚያውቁ
የኃይማኖት አባቶች፣ ከተራ ስፍራ እስከ ከፍታ ያሉ ሀብት፣ ስልጣን፤ ክብር ናፋቂዎችና በያዙት ላይም አብዝቶ
ለመጨመር የሚለፉ ሁሉ የዚሁ የጨለማ ገዥ ተገዥ ናቸው።
በእግዚአብሔር ቃል እንደተነገረው በቃሉ ተመስርቶ ከልዑል እስትንፋስ በእኔ በውዳቂው ባርያው የወጣው
አንደኛ እና ሁለተኛ መልእክቶች እንደተገለፀው ማንም ልብ ያለው ያስተዋለው የለም። እናንተ የዘመናችን
የጥፋት ሰዎች ማድመጥ፣መመለስ፣መፀፀት በፍፁም አልዞረባችሁም። እንዲያውም ጊዜ ሲቸራችሁ ወደከፋ
ጥፋት ተሸጋግራችዋል። በመጀመሪያው መልእክት በህዳር 7/1998 ዓ.ም ተፅፎ ፍርዳቸውን እንዲያውቁ
ተሰጣቸው በሁለተኛው መልእክት በግንቦት 27/2000 ዓ.ም እንዲሁ ፍርድንና የመጀመሪያውንም መልእክት
በማፅናት የመጨረሻ የፍርድ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ። ሊደርስ የሚችለውንም ጥፋት አመለከተ ማንም አልሰማም
በተለይ መሪዎች የየአገሩ መሪዎች እነ አሜሪካ፣ባቢሎን፣ አውሮፓ ኤሽያ፣ላቲን አሜሪካ፣መካከለኛው ምሥራቅ
አፍሪካ ሁለም ሰሙ ናቁ ተሳለቁ። አይ የሰው ጥጋብ በሥራው ዓለም ሲመፃደቅ።

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የእምነት መሪዎች ቫቲካን፣ምሥራቅ ክልል ያሉ የቻይና፣ የህንድ ጣዖት አምላኪዎች፣ ፕሮቴስታንቶች፣


ሙስሊሞች ሌሎችም እምነቶች ሁሉም በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ ሰሙ አላደመጡም እንዲገባቸው በዓለም
መግባቢያ በሆነው ቋንቋቸው የሁለተኛው መልእክት በእንግልዝኛ ቀረበላቸው። በመልእክቱ እንደተመለከተው
የኢኮኖሚ ቀውስ፣ የገንዘብ ቀውስ፣ የከፋ ሪሴሽን፣ የበጀት ጉድለት፣ ግጭት፣ ጦርነት፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣
ማዕበል እሳት ሁሉም የከፋው እርምጃ መዘጋጀታቸውን እያሳዩአችው ቢሆንም አልሰማችሁም ታዲያ እነዚህ
መች ይሰማሉ? አመፀኞች ማንን ፈርተው የፈጣሪን ቁጣ ሊቆጣጠሩት ዕቅድ ፕላን ይነድፋሉ። ስብሰባ በስብሰባ
ያደራጃሉ ግን ምንም የፈየዱት የለም። እየተከሰቱ ያሉት ምልክቶች እርምጃዎች የመልእክቶችን አይቀሬነትና
እርግጠኝነት ከልዑል ለመውጣታቸው የሚያረጋግጥ ሲሆን አመፀኞች ሁሉ እንደሚጠረጉ ግልፅ ሆኗል። እኔም
ምንም የተናቀ ሕይወት ብመራም ብተችም በልዑልም ታዝዤ የአገልጋይነት ሥራዬን ለመወጣት የምተጋ፤
እንደሌላው ከዓለም የምሻው የለም። ስለ ስሜ እንኳን ለመግለፅ አልፈለግሁም። ምክንያቱም እኔ ታዛዥ
መልእክት አድራሽ እንጂ ሌላ ምንም እንዳልፈለግሁ ሰው ሁሉ ሊረዳና ወደ ፈጣሪው መልእክት እንዲያተኩር
ስለፈለግሁም ነው።
ዜና መዋዕሌ ቀዳማዊ 16፣21–23 ይነበብ
ከፈጣሪዬም የተማርኩት ትምክህትን አርቆ ትህትናን መልበስን መልካም ስለሆነ ነው እንጂ ለነገርም ሊታሰብ
የማይችል ስጦታውን ጌታ ለእኔ ለትንሹ ባርያው ሰጥቷአል። ትምክህት ከጨለማ ስለሆነ በመመካት አልናገርም
መግለፅ ግድ ካልሆነብኝ በቀር። የሰው ዘር አድምጥ መሪዎችህ ገዥዎችህ በከፍታ ላይ አቁመህ የምታያቸው
የምትንቀጠቀጥላቸው ጣዖቶችህ ክቡር እከሌ፣አዋቂው፣ባለሙያው፣ሊቃውንቱ፣የጦር ባለሙያው፣ኢኮኖሚስቱ፣
ባለሃብቱ፣ቢሊኒየሩ፣ኢንደስትርያሊስቱ፣ የህክምና ጠበብቱ፣መሃንዲሱ፣ የአየር ንብረት አዋቂው፣ የጦር
አለቃው፣ ተመራማሪው፣የፖለቲካ ሳይንቲስቱ፣ ኧረ ምኑ ተቆጥሮ የሊቁ፣ የአዋቂው፣ የአባይ ጠንቋዩ፣ የጦር
ኤክስፐርት ወዘተ እኚህ ሁሉ ምን ፈየዱ? ምንስ ለወጡ? ምንስ አመጡልህ? በየአገሩ ህዝባቸውን በመግዛት፣
በማስጨነቅ፣ ወደ ጥፋት በመንዳት ላይ ያሉ ከመንደር እስከ አገር፣ ክፍለ አሕጉር የተኮለኮሉ ገዥዎች መቼ
ጊዜ ለፈጣሪ ትእዛዝ ጀሮ ሲሰጡ ታየ? የእነሱ ጥፋት ምድርን ሸፍኖ ሰማይን አዳርሷል። የዘመኑን ፊደል ቆጠሩ
ሁሉን አዋቂ ሆኑ። ሰርቆ፣ ነጥቆ፣ ገሎ፣ አመንዝሮ፣ ዋሽቶ፣ አታሎ በየትኛውም ቀን ተሰማርቶ ገንዘብን ሰብስቦ
ሕዝብን አስጨንቆ መኖሩ ህልማቸውና ደስታቸው ከሆነ ዘመናት አለፈም ተቆጠረም።
በወቀሳ፣ በማስተማር በመገሰፅ በመለስተኛ ቅጣት መፍታት ቢቻል ኖሮ 7500 ዘመን ሙሉ ጌታ ያለመታከት
በትዕግስት ሸፍኖታል። የሚያዳምጥ ጠፋ እንጂ!
ጊዜን በሰጡ፣ ምክርን በለገሱ የጥፋትንም ስፋት ባሳወቁ ፍርዱንና ፍፃሜውን በገለፁት ሁለት የጌታ
መልእክቶች ማን ተጠቀመ። መጭውን አስከፊ ጠረጋና የከፋ አደጋ ለሰው ሁለ በመግለፅ በኩል በሃገሬ
ብዙ ባሕታውያን መምህራን ከጌታ የተሰጣቸውን ትእዛዝ በመቀበል ለማዳረስ ጥረዋል እስከ ሕይወት ዋጋም
ከፍለዋል። ግን ማን አስተዋለ? ማንም ተሳለቀ እንጂ!
በእኔ በባርያው የአስተላለፈውን የፍጻሜ መልእክት ማንን አስደነገጠ? በተለይ በትዕቢት በማን አለብኝነት
በአውቃለሁ ባይነት የተወጠሩ የየአገሩ መሪዎች መቼስ ደነገጡ?
በህዳር 7/1998 እና ግንቦት 27 /2000 የተገለጹት መልእክቶች በሕዝብም በመሪዎችም በተለያየ ባህል፣
እምነት፣ የአገዛዝ ስርዓት ውስጥ ያሉ ሁሉ እንዴት ተመለከቱት እንዴትስ አስተናገዱት እንየው አራት አይነት
ሰዎች ተከስተዋል። ከእነዚህ ከአራቱ አይነቶች የሚዘል አልነበረም አይኖርምም ይህንን በዝርዝር መግለጫ
ውስጥ የምታዩት ይሆናል።
ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ 7፣ 27–28

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የአዳም ልጅ እንግዲህ ገላጋይ ወደሌለበት ወደ ብርቱ የቅጣት ማዕበል እየተንደረደርክ ነው። ፍጠን አምልጥ፣
ተባልክ ተነገርክ፣ ተመከርክ ተዘከርክ፣ ትዕቢትህ የበዛ ነውና መልስህ ንቀት ትችት በመልእክቱ ከመጠቀም
ይልቅ ስለ መልእክቱ አድራሽ ማንነት ለማወቅ ደከምክ። አይ የሰው ልጅ ምክንያትህ ምክንያትን እየወለደ፣
ሰበብህ ሰብብን እየፈጠረ ልትጠቀምበት ይገባህ የነበረውን ቀናቶችና ወራቶች ዓመታትንም በከንቱ አሳለፈክ።
ጥቂቶች ግን ተጠቀሙበት ወደ ፈጣሪያቸው ጉያ ገቡ ተሸሸጉ። ቅጥራቸውን አጠበቁ አንተስ? በምን ላይ
አረፍክ? አዝናለሁ ጊዜህ አበቃ! የተከፈተው በር ተዘጋ! ተከረቸመ ዛሬ በዓለም ላይ የሚታየው የቀውስ
አይነት፣የተፈጠሮ አደጋ ብዛት የሕዝብ ግጭት የአገሮች አለመስማማት የታላላቅ መንግሥታቶች ወደ አዘቅት
የመውደቅና የመጥፋት ጉዞ ጅማሮ ከ2000 ዓ.ም ማለቂያ ከነኀሴ መጨረሻ ላይ ከዋናው አምላካችሁና ጣዖታችሁ
ከአሜሪካ (ባቢሎን) በገንዘብ ቀውስ የጀመረ ሲሆን አድማሱን በማስፋት የኢኮኖሚ መቅለጥ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ
ወደ ማህበራዊ ቀውስ እየዘለቀ ይገኛል። ተስማምቶ የሚፈታ ታቅዶና ተተልሞ የሚተገበር ነገር ከእንግዲህ
የማይታይበት ወደ ጨለማ መገስገስ ተጀምሯል። ሁሉንም አዳርስዋል ይቀጥላል በብርቱም ይከፋል።
በመልእክት ቁጥር 2 እንደተገለፀው (በእንግሊዝኛው) የእስትንፋስ ጊዜ አይሰጥም። የኢኮኖሚ ቀውስ፣የገንዘብ
ቀውስ፣የኢንዱስትሪ ቀወስ፣ ሥራ ፈቱ በአጠቃላይ በሁለም ዘርፍ ያለው ቀውስ በከፋ ሁኔታ ይጨምራል።
መፍትሄም አጥታችሁ በልዑል ፊት እስክትወድቁና እስክትንበረከኩ ድረስ። የልዑል ቃል ወጣ አይመለስም
እንደ ቃሉ ያደርጋል እንጂ በከፍታ ላይ ያሉ መንግሥታቶች በሰበሰቡት ገንዘብ፣ ወርቅ፣ ታንክ፣ ጀት፣
ኒውክሊየር፤ የኢንደስትሪ ብዛት፣ የህንጻ ውበት፣ የጀትና የባቡር የመርከብ ግዝፈትና ርቀት በየቀኑ የሚዘቅጠው
ነዳጅ(ዘይት) በማዳበሪያ በጀነቲክ ኢንጂነሪንግ በፈጠሩት የእህል ዘር የሚመኩበት ደሃን በምጽዋት ደልለው
በሚገዙበት ዕቅዳቸው የጨለማ አገዛዛቸውን የጥፋት የምንዝርና የግድያ ህጋቸውን በሚጭኑበት አካሄድ የሚቀጥል
መስሎቸው አምነውበትም ነበር።
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 24 በሙሉ ይነበብ
በዲያብሎስም ፍፁም ታምነው ነበር። ዛሬ ወደ ቁልቁለት ጉዝ ጀምረው ከዚህ ገዞአቸው እጅ አልወጡም
አይወጡም ፍርዳቸው ወጥቷአል። ተግባሩን ጀምሯል። ዛሬ የሚታየው የምጥ ጅማሮ ለውጊያው በማጥፋቱ
የታዘዙት ቅዱሳን መላእክት በመጨረሻው ርምጃ ጠቋሚ የሆነውን የሚያመለክት የልምምድ እርምጃ እያሳዩ
ነው። መቼ ጀመሩ መጪውን የግዳጅ አፈፃፀም ልታየው ነው። ገንዘብ የኃጢአት ስር ነው። ገንዘብ ደግሞ
የዲያብሎስ መጠቀሚያ ነው በመልእክት 2 እንደተገለፀው። ታዲያ ይኸው የዘመኑ ባለጠጎች መሪዎች በልፅገናል
ባይ አገሮች ዋና መታመኛቸው ይኸው በቁጥር ለመግለፅ የሚያታክት ገንዘባቸውና ወርቃቸው ነው። የእርምጃው
ጅማሮ ደም ሥራችን ነው በሚሉት ገንዘብ ላይ በትሩን በማሳረፍ ተጀምሯል ከእጃቸው እንደ ሰም ይቀልጣል
እየቀለጠም ይገኛል። ስለ ትርፍ ብቻ እንጅ ስለ መክሰር ሰምተው የማያውቁ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በእስያ፣
በላቲን አሜሪካ፣ በአፍሪካ ያሉ ታላላቅ ባንኮች ኢንሹራንሶች ከመስከረም ወዲህ እየተመቱ ናቸው። በዓለም
ያለው ቀውስ ምን ይመስላል በዚህ ቀውስ የጉዳቱ መጠን እንዴት ነው? በጥቅሉ በገንዘብ ቀውስ እንደምንሰማው
በአጭር ወራቶች ውስጥ ባንኮች ከሦስት ትሪሊዮን በላይ በአውሮፓና በአሜሪካ ያሉት ብቻ አጥተዋል። ይህ
አሃዝ የኢንሹራንሶችን ክስረት ሳይጨምር ነው። የሞርጌጅ ባንኮች ከመደበኛ ባንኮች በሚቀራረብ መጠን
ከስረዋል። አረቦች ሁለት ተኩል ትሪሊዮን አጥተዋል። ይህ ሂደት ገና አልተገታም አይገታምም። የኢኮኖሚ
ቀውሱ መጠኑንና አድማሱን በማስፋት ሁሉም የምድር ብርቱ ነን ባይ መንግሥታቶች እስኪከስሙ ይቀጥላል።
ትንቢተ ኢሳይያስ 45፣9–10
ዛሬ ይህን አደጋ ለማጥፋት ምን ዕቅድ ተነደፈ ምንስ እየተየረገ ነው ብንል ከመንግሥት ካዝና ያለውን
ከሕዝብ የተሰበሰበውን ፌደራል የገንዘብ ክምችት ላይ በመቀነስ መደጎምን ተያይዘውታል።

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አሜሪካ /ባቢሎን/ በቡሽ ዘመን 700 ቢሊዮን፤


አሜሪካ /ባቢሎን/ በኦባማ ዘመን 879 ቢሊዮን
እንግሊዝ /ትንሿ ባቢሎን/ 90 ቢሊዮን
ሲንጋፖር 13.3 ቢሊዮን
ጀርመን 470 ቢሊዮን
ቻይና 570 ቢሊዮን
ፈረንሳይ 18 ቢሊዮን
ራሺያ 28 ቢሊዮን
ደ/ኮርያ 30 ቢሊዮን
አውስትራሊያ 14 ቢሊዮን
ካናዳ መጠኑ ያልታወቀ
ስፔን መጠኑ ያልታወቀ
ሌሎችም እንዲሁ ከ 2 እስከ 10 ቢሊዮን
ከማእከላዊ ባንካቸው ፌደራል ሪዘርቭ በማውጣት ደጉመዋል (ቤል አውት) አድርገዋል። በድጎማ በእቅድ
በምኞት የሚቆሙ መስሎአቸው ይደክማሉ። ከንቱዎች በመልእክት 1 ሆነ 2 እንደተገለፀው ሕልማቸው
እቅዳቸው ሁሉ ቅዠት ይሆናል እንጂ የሚለውጠው ነገር የለም። ሞርጌጅ ባንኮች መሸቃቀጫ ገቢያዎች
የሚባሉት ሁሉ በታላቅ ክስረት እየተመቱ ሲሆን ከመንግሥት ካዝና የድረሱልኝ ድጋፍና ድጎማ እየተደረገላቸው
ነው። ሆኖም አስር ቦታ እንደተበሳ እንሥራ ውኃ በአናቱ ሲገባ ከስር እንደሚያንዠቀዥቀው ተመልሰው እና
መላልሰው በማፍሰስና በመውደቅ ላይ ይገኛሉ። ታላላቅ የመኪና የኤሌክትሮኒክስ የሸቀጥ ኢንዱስቱሪዎቻቸው
በመክሰር ሰራተኞቻቸውን በማባረር ላይ ይገኛሉ። በታንክና በጠመንጃ የማይፈቱት አደጋ ጅምር እንጂ መቼ
ወደ ከፋው ደርሷል። የእኛ ብልሆች የኋለኛይቱ ዝንጀሮ በፊተኛዋ ትስቃለች ይባላል። እሱ ነው እሱ ነው
ይባባላሉ። ከንቱዎች ከንቱ የሚያደርጋቸውን እርምጃ ጀመሩ እንጂ ገና መቼ ወደ ከፋ ፍጥነት ገቡ ሲፈጥን ያኔ
ሲፈጭህ ታየዋለህ። እስትንፋስህ ሲዘጋ ቱልቱላህ ሁሉ ይቆማል። ኖኅ መርከብን አዘጋጀ እንደታዘዘው ለዘርና
ለምሕረት የታሰቡትን ሰበሰበ እሱም ቤተሰቡም ተጠቃሎ ወደ መዳኛው የእግዚአብሔር እጅ ተጠለሉ።
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 8፣9–10
ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 7፣13–16
ጌታ ከውጭ መርከቡን ዘጋው። የጥፋቱም እርምጃ ተጀመረ። ተጀምሮም አልቀረም የሚጠርገውን ጠራርጎ
ተፈፀመ። ዛሬስ አመንዛሪዎች የጣዖታችሁ የባቢሎን /አሜሪካ/ የአውሮፓ የኤሽያ፣የመካከለኛው ምሥራቅ
መታመኛችሁ ግንቡ መሰንጠቅ ጀምሯል። አይነካንም ብላችሁ የተመካችሁበት የሀብት ክምችት ምንጫችሁ
መንጠፍ ጀምሯል።
በኖኅ ዘመን ዝናቡ ሲጥል ቀስ በቀስ የውኃው ሙላት ምድርን መሸፈን ሲጀምር ሁሉ የአዳም ዘር ይደንሳል፣
ይስቃል፣ ይሣለቃል፣ለነገው ዕቅድ ያወጣል፤እንደደነሰ እንደዘለለ እንደ ፎከረ በኖኅ መርከብና በውስጧ በተጠለሉ
በንቀትና በምናምንቴነት እንደተሳለቀ ዛሬ በእኔና በመሰሎቼ እንደምታደርጉት ከእግሩና ጥፍሩ ስር የነበረው
ውኃ ወደ ጉልበቱ ወደ ወገቡ ሲደርስ አሁንም አልተመለሰም ያላግጣል። ደረቱ ላይ ሲደርስ ግን መደንገጥ፣

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ጥርስ ማፋጨት፣ መወራጨት ይጀምራል ምን ዋጋ አለው ውኃው ሥራውን አላቆመም። አንገቱ ጋር ደረሰ
በስተመጨረሻም እስትንፋሱን ዘጋ። ይህ ነው የዘመናችን አመፀኞች ዕጣ።
ይህ በእግዚአብሔር ቃል የተገለፀ የትላንት ክስተት ለእናንተ ለዛሬዎቹ በ70 እጥፍ ይጨምራል። የኖኅ ዘመን
ሰዎችን በሞት ለምትልቁት ሲነገራችሁ መቼ ደነገጣችሁና።
አንዳንድ ከአውሮፓና ከሌሎችም አገሮች ራሳቸውን ማጥፋት ጀምረዋል ገና በስፋት ይቀጥላል። ሁሌ ሀብት
ማጋበስ፣ ሁሌ ትርፍ፣ ሁሌ ዳንስ፣ ቀንም ሌትም ያለ እረፍት ለስልጣን፣ ለገንዘብ ሩጫ የትም የሚታይ
የትልቅነት ምልክት ነበረ። አሁን ግን ትርፍና ሁሌ በድሃ መቃብር ላይ ማደግና መበልፀግ የለምና! ከበርቴና
ባለስልጣን ድንገት ኪሳራ፣ ሞት፣ በሽታ፣ አደጋ ሲከታተልበት አዕምሮው ስለማይሸከም ሞትን ይመርጣል።
አሁን አልፎ አልፎ የሚታዩ ጠፊዎች ይህችን ዓለም መሰናበታቸው የክብር ሞትን እንደሞቱ ይቆጠራል። ገና
ሞት ይፈለጋል። ራሱን ይሸሽጋል ይህ መጪው ዕጣ ፋንታችሁ ነው።
በአንደኛው መልእክት 7/3/1998ዓ.ም በዝርዝር እንደተገለፀው ተፈፃሚ እንደሚሆን ልትጠራጠሩ አይገባም።
ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 7 በሙሉ
በሁለተኛው መልእክት በአማርኛ እንደተገለፀው በሁለተኛው መልእክት በእንግሊዘኛ እንደተገለፀው በድጋሚ
የመጨረሻ ጊዜ እንደተረጋገጠው ጊዜው መሟጠጡን እንዳበሰረው ሰምታችሁ መቼ ተፀፀታችሁ።
በብዙዎች ህሊና ውስጥ እየተመላለሰና እያሰናከለ ያለው ምንድን ነው? ለምንስ ማስተዋል ጠፋ? ብንል
እርቀን ሳንሄድ መልሱ ቅርብ ነው።
1ኛ እውነትን የሚፈለግ የህሊናና የልብ ውሳኔ ማጣት
2ኛ እውነትን የሚፈለግ ሁለተኛ እምነታችንን መምሰልን እንጂ መሆንን ስላልተላበሰ።
3ኛ አምልኮታችን ጌታ እንደተናገረው በእውነትና በመንፈስ ለማምለክ አለመወሰንና አለመፍቀዳችን።
4ኛ አስቀድማችሁ ፅድቁን ፈልጉ ሌላው ሁሉ ይጨመርላችኋል የሚለውን የልዑል ቃል በዲያብሎስ ፈቃድ
በመመራት ገልብጠን አስቀድመን የሥጋውን ከዚያ በኋላ ስለ እምነት እንደትርፍ ጉዳይ ማሰባችን።
5ኛ ይህን የተጣመመ አካሄዳችንን የጠፋ መንገዳችንን ለማስተካከል ጌታ ባሮቹንና አገልጋዮቹን እየላከ
ሲወቅስ ሲገስፅ አለመስማታችን ብቻ አይደለም መልእክተኞቹን ማሳደድ፣ማሰር፣መግደልችን።
6ኛ በተሰጠን ህሊና የፈጣሪያችንን ፈቃድ ከመፈፀም ይልቅ ዕውቀት ሲበዛ የቁሳቁስ ፍላጏታችን ሲትረፈረፍ፣ገደብ
የሌለው የሥጋ ፍላጎታችን ገንፍሎ በስስት፣በገንዘብ ማከማቸት፣በንፉግነት፣በጭካኔና በተገኘው ሥጋዊ ምቾት
መታበይ በፈጠሪ ሕግ ማሾፍን እንደ እውቀት በመቁጠር ሰማይ የደረሰ ትዕቢት ተላበስን፣ፈጣሪንም ናቅን ካድን
የራሳችን አምላክ አቆምን እውቀትና ገንዘብ ጠመንጃ ትዕቢትን ተካን!
በመልእክት 1 እንደተጠቀሰው ገንዘብ አምላክ ሆነ፣ሥልጣን ዕውቀት መታበያ ሆኑ የሁሉም ሰው ምኞት
ተምሮ ገንዘብ አፍሶ፣ ተሽከርካሪ ሸምቶ፣ ቤት ሰርቶ፣ በድሃው ወንድሙ ላይ ተመፃድቆ፣ ከሆነለትም በደሃው
ላይ የሥልጣንና የክብር መንበሩን ዘርግቶ በደሃው ዕድል ፈንታ ላይ ወስኖ መኖር የሚያረካው የሥጋ ምኞቱ
ሆነ። ሁሉም ሰው የሚጋልብበት ጎዳና የዲያብሎስ ጎዳና ይኸው ከላይ እንዳልኩት ከብዙ በጥቂቱ የብዙዎችን
ህሊና ሰቅዞ የያዘው አለማስታዋል ከላይ በተጠቀሱት ነጥቦች የሚገለፅ ነው።
ኦሪት ዘሌዋውያን 18፣ 1 – 5
በእነዚህ ሃሳብ የተጠመደ ሰው የዲያብሎስ ፈቃድና ሃሳብ ፈፃሚ ከፈጣሪው ፈቃድ ተጋጭ ሆኖ ይቀራል።
ሰው ሲወቀስ ሲገሰፅ ካልሰማ ሲጠፋ ቢሰማ ምን ዋጋ አለው? ሰው በፍርድ ሂደት ክርክር ውስጥ ሲገባ

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ከውሳኔው በፊት ነው የመፀፀቻ ዕድሎቹ ሁሉ ያሉት ከውሳኔ በኋላ ውሳኔው ወደ ማስፈፀም የሚሄዱት ኃይሎች
እንደስማቸው የማይፀፀቱ የአቤቱታ የይቅርታ ጥያቄ አድማጮች አይደለም። ማስፈፀም ብቻ ነው ሥራቸው።
ተልዕኮአቸውም ይኸው ነው። መፀፀትም መመለስም፣ ንስሓ መግባትም ከውሳኔው መሰጠት በፊት ነው። ዛሬ
በተከታታይ እየተወቀሰ አልሰማ ያለ የሰው ዘር ውሳኔው ሲተገበር ቢጮህ ምን ፋይዳ አለው።
መልእክቶቹ የደረሷቸው ሁሉ ከፊሉ ይህ ሰው ከወዴትስ የበቀለ ነው? ማነው? ምን አገባው? ምን ስልጣን
አለው? ማን ሾመው? በየትኛው ጉልበቱና ኃይሉ ነው? የአዕምሮ በሽተኛ ነው ቅዠታም ነው ወዘተ ... እያሉ
ባያውቁኝም ሲያብጠለጥሉኝ ይውላሉ ያድራሉ። ስለ እኔ ማንነት ከሚቸገሩ ይልቅ የመልዕክቱን ሃሳብ ብቻ
ተረድተው ቢጠቀሙበት ምንኛ ባተረፉ ነበር። ከንቱዎች ከከንቱ ሃሳባቸው ጋር ይደናቆራሉ። ይሁንና እኔ
በሁለቱም መልእክቶች ለመግለፅ ሞክሬአለሁ ደግሜም የምናገረው ይህንኑ ነው። ድሃ ነኝ እውቀት የለኝም ከሁሉ
በሚያንስ ኑሮ ውስጥ እኖራለሁ። በማንም ዘንድ ግምት የሚሰጠው የሀብትና የእውቀት ስብዕና የለኝም ራሴንም
አልሰየምኩም የፈጠረኝ አምላክ እንጂ የሾመኝ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው ስልጣኔን ወደፊት ፈጣሪ
ሲገልፅላችሁ ታውቃላችሁ ጉልበቴና ኃይሌ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እሳት ነው። ፀጋው ሽፋንና ከለላዬ
ነው። ብዙዎች ከመንግሥት እስከ በታች ሹም ወይም ከአለቃ እስከ ምንዝር እኔን ሊያጠፋ ያልወደዱ የሉም።
ዛሬም ነጋም ጠባም በእኔ ጉዳይ ትልቅ ስምሪት፣ዕቅድ፣ብልሃት፣ማጥቃት፣ማጥፋት ለመፈፀም ለማስፈፀም
ይወጣሉ ይወርዳሉ። ግን በመልእክት 2 እንደገለፅኩት ከእነሱ የሚበልጠው እነሱን በሚተክለው በሚያጠፋው
የልዑል ኃይል የምጠበቅ ነኝና ምንም ሊሆን አይችልም። ክፉን አላሰብኩም እንዳስብም ፈጣሪዬ አላስተማረኝም።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 12፣ 1 – 3
ከአለቃ እስከ ምንዝር በእኔ ላይ በጓደኞቼ ላይ የጥፋት ሥራ ሲሠሩ ሲያስቡ፣ በከፍተኛ ወጪ ሲሰልሉ በሥጋ
ጥበባቸው ብዙ ሊያደርጉ በያዙት ጠምንጃ ሲመኩ ምንም ያልኳቸው ነገር የለም፣ ታገስኳቸው እንጂ። ምክር
ተግሳፅ ከመሰንዘር በስተቀር ከዚያ አልዘለልኩም ፈጣሪን ብጠይቅ ፍፁም በእሳት እንደሚበሉ ነግሬአቸዋለሁ።
ዛሬም ላረጋግጥላቸው እወዳለሁ ብጠይቅ ተፈፃሚ ነው። በጠረጴዛቸው ላይ ስለ እኔ የሚቀርበው ሪፓርት ዝርዝር
አውቃለሁ። ትምክህት ግን ምን ያደርጋል። አዝንላቸዋለሁ። መልዕክቱ ደርሷቸው ምን እንዳሉ ምን እንደወሰኑ
ሁሉ በግሌ የሚታወቅ ነው። በንቀትም እንደተሳለቁበት እረዳለሁ።
ይሁንና ሳይርቅ ሁሉም ስለሚፈፀም እርምጃቸውን ሁሉ ደግመው ደጋግመው ቢያዩት ለራሳቸው የሚበጅ
በሆነ ነበር። ሆኖም በራሳቸው የሥጋ ሩጫ ስለሚያልሙ ከውድቀታቸው አይመለሱም ይበጀናል ብለው
የሚወጥኑት ሁሉ ወደ ከፋ ጨለማ እያወረዳቸው ይገኛል። አሁንም ቢይዙት ሰከንድ ለማትፈጅ እስትንፋሳቸው
ይመጻደቃሉ። የመንፈሳዊን ሰው ዐይን ንቀው በሥጋቸው ዐይን ሊሰልሉት ይደክማሉ። እስከ ቤቴ ገብተው
እንዲሰልሉ ፈቅጄላቸዋለሁ ከተጠቀሙበት። እውር አይናማውን ሲሰልለው እስቲ አስቡት!
ዓለም በምን ምጥ ውስጥ እንዳለ ወዴትስ እንደሚጓዝ በፊታቸው ያለው የልዑል መልእክት ሲለካቸው
ሲመዝናቸው ለፍርድ ሲያዘጋጃቸው በማይታይ የእግዚአብሔር የብርሃን ሰንሰለት ሲጠፍራቸው አያውቁትም
አይረዱትም በህሊና፣ በሥጋ ዕውቀታቸው ዲያብሎስ በሰጣቸው የውሸት ተስፋ ሲመፃደቁ የተሳካላቸው
እየመሰላቸው ሲያከትሙ አይናማው ያያል።እነሱ ግን እንደ ዕውሩ ወደ ገደል ይወድቃሉ። ለምን አያስተውሉምና
በትዕቢት ተሞልተው አያዩምና።

ወደ መንደርደሪያ እንግባና

ስለዚህ መልእክት ያላችሁን ግንዛቤ መንገድ ለማስያዝ፣ በመልእክት አንድና ሁለት የታዘዘውን እየተፈፀመ
ያለውንና የሚፈፀመውን ትረዱና ታስተውሉ ዘንድ ይህ መልእክት የተፃፈ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ
ተፈፃሚነቱን ብቻ ሳይሆን ዝርዝር መመሪያውን የሚገልጽ ይሆናል።

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕራፍ 8 በሙሉ


በሦስተኛ ደረጃ እያንዳንዱ የዓለም ክፍለ ሀገር፣ ክፍለ አሕጉር ሕዝብ፣ ማህበረሰብ፣ የእምነት ተቋም
የሚገጥመውን ሸክም /ቅጣት/ እስከምን እንደሚሄድ እንዴት ቅጣቱ እንደሚያበቃ፣ በቅጣቱስ ምን በማድረግ
መዳን እንደሚችል ርዕስ በርዕስ እየተነተነ ይገልፃል።
ይህ መልእክት ለሁለም የሰው ዘር ሁሉ እንደ ልዑል ትዛዝና ፈቃድ የተዘጋጀ በሁለቱም መልእክቶች ላይ
መሰረት ያደረገ ዝርዝር የድርጊት መመሪያ ስለሆነ የእግዚአብሔር እውነተኛ አገልጋዮች፣ የታመናችሁ የልዑል
ልጆች በየትኛውም የዓለም ፊት ኑሩ፣ በየትኛውም የሕይወት ጎዳና ተሰማሩ ከመልእክት 1 እስከ 2 እና ይህን
ዝርዝር አመላካች መመሪያ ትጨብጡ ዘንድ ሁሉንም ክንዋኔ ትመዝኑበት ዘንድ በጥብቅ እመክራችኋለሁ
አሳስባችኋለሁ። እንደምረዳው ለበጎ ቀን የተጠበቃችሁ ከጌታ ጋር ግንኙነታችሁ የጠበቀ በእጃችሁ ያለውን
ትእዛዝ ታውቃላችሁ። ፈጣሪ የሰጣችሁን ምልክት፣ ተስፋና ኃላፊነት በማስታዋል በልባችሁ መዝግባችሁ
ተጠባበቁ። ልዑል ቃሉን ሊፈፅም ጥሪው ደርሷችኋልና።
ሁሉንም አካሄዳችሁን መዝኑበት፣ አካባቢያችሁንም፣ የዓለምን ሁኔታ ሁሉ እዩበት ከልዑል የተሰጣችሁ
መነፅር ነውና። ዕውር ዕውር ነው ዕውርነት ስላችሁ መንፈሳዊ ዕውርነትን ነው። የመንፈስ ዕውር የጌታን
የመንፈስ መነፅር ሊያደርግ አይችልም። ምክንያቱም እንደ ሰውነቱ የተገዛው ለጨለማው መንፈስ ስለሆነ
የብርሃን መንፈስን በደባልነት ሊያጠልቀው አይችልም አጥፊው ነውና።
ዕውር በፍፁም ጠቆረም ነጣ መነፅር ቢያደርግ ዕውርነቱን አይሸፍንለትም በመሆኑም ዕውራን የዘመናችን
ታላላቅ ነን ባይ መንግሥታቶች፣ ሹሞቻቸው፣ የእነዚሁ መንግሥታቶች አሽከርና ሎሌ መንግሥታቶች
ከነሹሞቻችሁ አንብቡት፣ እንደለመዳችሁት ወርውሩት ናቁት ተሳለቁበት ችግር የለውም የምትከፍሉትን ዋጋ
ከየዝርዝር መግለጫው ስለምታዩት ትሰፈሩበታላችሁ ትጠረጉበታላችሁ። የናንተ ጉዞ ረግረግ ላይ እስከ ጉልበቱ
ሰምጦ ኳስ እጫወታለሁ የሚልን የዋህ ይመስላል። ስለዚህም ትዕግስቱ ካላችሁ አንብቡት የጥፋታችሁን ሂደትና
ፍጥነት እዩበት።
ለወገኖቼ፣ ለወንድሞቼ፣ ለእህቶቼ፣ ለእናቶቼና አባቶቼ በየትኛውም የምድር ፊት ላላችሁ የእግዚአብሔር
በጎች የሚጠብቃችሁን ክብር፣ በረከት፣ መፅናናትና ደስታ በኔ አንደበት ልገልጽላችሁ ይቸግረኛልና ብቻ ፅኑ
በሚያበጥረው የእሳት ጉዞ ውስጥ ገብታችኋል። እሳቱ እናንተን አይጎዳም ሲድራቅ፣ ሚሳቅ፣ አብዲናጎም
በልዑል የታመነ መልአክ ቅ/ገብርኤል ስለተጠበቁ ምንም እንዳልሆኑ እነሱን ለእሳት የጣሉትን እንደ በላ
በምድሪቱ የበቀሉት የሊባኖስ ዝግባዎች ረዘሙም አጭሩም ልቅም አድርጎ ሲበላ የምትታዘቡ ትሆናላችሁ
ለመጭውም ትውልድ ምስክር ሆናችሁ ትቆማላችሁ እናንተን የሚያስጨንቅ አደጋ አይመጣም።
ወደ ዕብራውያን ምዕራፍ 12 በሙሉ

መላው የሰው ዘር ሁሉ ልብ ብላችሁ አድምጡ አስተውሉ

ከእኔ ዘንድ የደረሳችሁ መልእክት 1 እና መልእክት 2 እና ይህ 3ኛው የመመሪያ የማብራሪያና የአፈፃፀም


የድርጊት ውሳኔ መግለጫ ሁሉ በቸሩ አምላካችን ታዝዤ ያደረግሁት መሆኑን በኔ ዕውቀት ጥበብና ፍላጎት
የመጣ እንዳልሆነ መታወቅ ይገባዋል። እኔ የልዑል አገልጋይ /የሥላሴ ባርያ/ ትዕዛዙን ፈፃሚ እንጂ በራሴ
የማመንጨው አንዳች ነገር የለም።
የክርክር ዘመን አልፏል የእኔ አካሄዴ ትክክል ነው፣ የኔ መስመር፣ የኔ እምነት የተሻለ ነው በሚል ከእውነት
መንገድ የወጣም በእውነቱም የተመሰረተ የእምነት ጦርነት ሁሉ በሺዎች ዘመን አስቆጥሯል። ዛሬም ይኸው
ያለና የሚታይ ነው። ግን አበቃ!

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ሁሉም ሰው በልዑል ፊት ባመነበት ቆሞ ተሟግቷል፣ ሃሳቡንና እምነቱን ለማስረፅ ከቅድመ አያቶቹ ጀምሮ
ተጉዞበታል። ታዲያ ይኸው ሁኔታ የሚቀጥል መስሎአችሁ ሁላችሁም በተመሰረታችሁበት ቆማችሁ በየራሳችሁ
መነፅር ስታዩ ኖራችኋል። ሁሉም ባመነበት በልዑል ችሎት ተሟግቷል። ውሳኔ ተላልፏል። ይግባኝ ተሰምቷል።
ሌላ ይግባኝ የለም።
በኔ በልዑል ባሪያም የተላለፈውን መልእክቶች ሁሉ እንደተወለዳችሁበት፣ እንዳደጋችሁበት ዛሬም
እንደምትኖሩበት ዐይንና ሕሊና እያያችሁት ነው መልካም ነው።
ልብ ልትሉት የሚገባው ግን ያ ዘመን አበቃ። ትእዛዝና ፍርድ ወጣ የአፈፃፀም መመሪያውም ይኸው ወጣ።
የክርክር ዘመን አለፈ፣ተዘጋ። ከማነው የምትከራከሩት በየትኛው ፍ/ቤት የፍርድ ሂደት ክርክር ይደረጋል።
የፈጀውን ጊዜም ይፈጃል በኋላ በዳኛው ውሳኔ ይሰጣል። በቃ!
እየነገርኳችሁ ያለውን የልዑል ውሳኔ ነው። 1–2 ተነግሯችኋል። የዛሬው የውሳኔ አፈፃፀምና መመሪያ
ከነሙሉ ማብራሪያው ቀርቦላችኋል። አበቃ!
ትንቢተ ኢሳይያስ 43፣8 – 13 ለማነፃጸሪያ አንብቡት

ማሳሰቢያ

በየርዕሱ ውስጥ የሚገለፁት ማብራሪዎች መመሪያዎች የአፈፃፀምና የድርጊት ውሳኔዎች ሁሉ ርዕሱን በሚገባ
እንዲገልፁ የታሰበና ያረጋገጠ ነው።
በየርዕሱ የምታዩት የምትረዱት ሁሉ አንድም ሳይወድቅ የሚፈፀምና የእናንተንም የሚዛን ግምት የሚያብራራ
ሲሆን በዚያ ተመስርቶ የሚገጥማችሁን የቅጣት ሂደትና ፍፃሜውንም የሚያስረግጥ ነው።

1 ስለ ሁሉም መልእክቶች የሰዎች አቀባበልና ምንነታቸው።

በመላው ዓለም ፊት ተበትኖ የሚኖረው የሰው ዘር ቁጥር በዝቶ ምድርን መሸፈን ከጀመረ ጀምሮ እንደየአካባቢው
ሁኔታ የሚስማማውን የኑሮ ሕግ መስርቶ በተለያየ የባህል የእምነት የአኗኗር ደንብ እየተገዛ መኖር ከጀመረ ቆየ።
7500 ዘመኖችም አለፉ። ፈጣሪ ከዚህ ምድር አዳምና ሔዋንን ፈጥሮ ለመልካም ቢያስባቸውም በትእዛዝ
ጥሰት ከፊቱ መሸሽና ሞትን የሚያህል ዕዳ ከተሸከሙ በኋላ በምድር ፊት ተበትነው ጥረው ግረው እንዲኖሩ
በመወሰኑ ይኸው ሂደት ቀጥሎ እዚህ ደርሰናል። ፈጣሪ ፈጥሮ አልተወንም ሰው ከሳተና ትዕዛዙን ካጠፋ ጀምሮ
መልሶ የሚድንበትን መንገድ ጌታ አዘጋጀ። እንደ ቃሉ አደረገ ሰው ግን ሁሉንም ትዕዛዙን በማፍረስ የራሱን
የጥፋት ሕግ በማቆም መልካሙን ትቶ መጀመሪያ ጀምሮ ከመንገዱ ያወጣውን የእባብ ምክር /የዲያብሎስ
ምክር/ቭበመስማት እስካሁን እንዳጠፋ ፈጣሪውንም እንዳሳዘነ ይኖራል።
ሸክሙ የቀለለውን ትእዛዝ በማስቀመጥ እዳችንን የከፈለውን ፈጣሪያችን በትዕግስቱ ርቀት ተሸክመን
ብርሃንን ትተን ወደ ጨለማው ስንጓዝ በማዘን ታገሰን ሰው ጌታ አልቆ ሲፈጥረው በአምሳሉ ምሳሌ አድርጎ
ነው። የምድር ፍጥረትም ሲያስገዛለት ለሰው የሰጠውን ክብር ግልፅ ያደርገዋል።
ጥቂቶች ለፈጣሪያቸው ፍቅር ተገዝተው ደምና አጥንት ገብረው የልዑልን ፍቅር ለብሰው ዓለም ንቃቸው
ተዋርደው የሚበልጠውን በመንፈስ አይተው ወደ ፈጣሪያቸው እቅፍ አልፈዋል።
የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ፡ 9 – 28 ለማነፃፀር አንብቡት
የሚበዙት ደግሞ መልካሙን ትተው ወደ ጨለማ ተጉዘው ድንገት ወደ ሲዖል ወርደዋል። የዛሬው እጅግ
ከፍቶ የሚታየው የጥፋት ዘመን ከአለፈው ዘመን የጥፋት ጎዳና ጋር ሲነፃፀር እጅግ የከፋ ነው የሰው ልጅ

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ስብዕናው ወድቆ ከእንስሳ አንሷል በተለያየ የሥጋ ምኞት ተጠልፎ የዲያብሎስ ወዳጅ የፈጠረው አምላክ ጠላት
ሆኗል። ፈጣሪ የሚጠላውን ለማንገስ እጅግ ደክሟል። አመዛሪ ነው፣ ውሸታም ነው፣ ነፍሰ ገዳይ ነው፣ ገንዘብ
አምላኩ ነው። ፈጣሪውን የካደ ነው። የተለያየ ባዕድ አምልኮ ወዳድና ተከታይ ነው። ጣኦት አምላኪ ነው።
ሁሉንም በፈጣሪ የተጠሉትን ክፋቶች ሁሉ እንደመልካም በራሱ ሕግ እንደነፃነት፣ እንደመብት በመቁጠር
ተጀምሮ እስከሚያልቅ የሕይወቱ አካል ያደረጋቸው ናቸው። እንግዲህ በዚህ ሁሉ የፈጣሪ ትዕግስት አልቆ
ከ7/3/1998 ጀምሮ የመጨረሻ ፍርድ እየተገለፀና ለመጨረሻ ጊዜ በድጋሜ የልዑል ውሳኔ በ27/9/2000
የፀናው የመጨረሻው ውሳኔ ለመላው ሕዝብ ቢገለፅም ከውስን ሰዎች በስተቀር የሰማ የለም። ለሕዝቡም በይፋ
የገለፀ መንግሥት፣ የእምነት ተቋም፣ ድርጅት የዜና ማሰራጫ የለም።
ይሁንና መልእክቱ የደረሳቸው እንደምን መልእክቱን ተቀበሉት በመልእክቱ ያላቸው አመለካከት ምን
ይመስላል?

1–ሀ በአንደኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች አቀባበል


በዚህ ክፍል ያሉ ሰዎች መልካም ሰዎች ናቸው። ቀና ልብ አላቸው ትሁትና ቅኖችም ናቸው። በተለያየ
የእምነት መስመር ይጓዙ እንጂ የፈጣሪን እውነት የሚወዱ ናቸው። እነዚህ ቅኖች የፈጠሪን ወቀሳና ግሳፄ
ሁሉ በቅንነት ተቀብለው እራሳቸውን ከስህተት ለመመለስ ፈጥነው እርምጃ የሚወስዱ ናቸው። መልእክቶቹ
እንደደረሳቸው በመልእክቱም መልእክት በመወቀስ ህሊናቸውን ወደ እውነት በመመለስ ለንስሓ ራሳቸውን
ያዘጋጁና በፍጥነትም የተመለሱ ሲሆን ያሉባቸውን ጉድለት በመልእክቱ መነፅርነት በማየት ወደፈጠሪያቸው
ጉያ የተመለሱ ናቸው።

1–ለ በሁለተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች


በዚህ ክልል ውስጥ የሚያርፉ ሰዎች በራሳቸውም ሆነ በቀረቡአቸው ሰውች ዙሪያ የሚያዝ የሚጨበጥ
ባሕርይ የሌላቸው ናቸው። ሁለት እግር ይዘው ሁለት ዛፍ ባንድ ጊዜ ለመውጣት የሚያስቡና የወሰኑ ናቸው።
በማናቸውም ጉዳይ ላይ እምነት የማይጣልባቸው ናቸው። እምነትን ለማመን ከወሰኑም በመምሰል ለመጓዝ
የሚወስኑም ናቸው። ቆርጠው ባንድ አቋም ፀንቶ ጥቅሙንም ጉዳቱን ለመቀበል የሚችልና የሚወስን ህሊና
የላቸውም። አላማቸው ያ ብቻ ነውና በማስተማርም የሚመለሱ አይነት አይደሉም ቢጎዱም ከዋዠቀው አቋማቸው
አይወጡም አላማቸው ያ ብቻ ነው። ጌታ በዮሐንስ ራእይ ላይ እንደተናገረው ሙቀትም ቀዝቃዛነትም የሌላቸው
ለብታን የተላበሱ በመሆናቸው ሊተፋቸው ያስጠነቀቃቸው አይነት ናቸው። በመላው ዓለም በቁጥር በዝተው
የሚታዩና ለማንኛውም ጉዳይ የማይበጁ ናቸው። በመልእክት 1 እንዲሁም በመልእክት 2 የተላለፉትን ወቃሽ
ፈዋሽና ፈራጅ ገሳጭ መልእክቶች ሰምተው ለጊዜው የመደንገጥ ምልክት የሚያሳዩ፣ ቆየት ብለው የተሰጣቸውን
እድሜ በብልጠት ያገኙት አድርገው በመቁጠር ለከፋው የኑሮ ገጽታቸው የአለሁበት ማረጋገጫ የሚሰጡ
በመሆናቸው ተመልሰው እንደ እርያ ወደ ኃጢአት ጭቃ የሚመለሱ በመሆናቸው። በዚህ የፍርድ አፈጻጸም
ውስጥ በእሳት የሚበጠሩ ናቸው። በአብዛኛው የኑሮ ምቾት የእውቀት ብዛት ያነቃቸው ሩጫቸው ባላቸው ላይ
ለመጨመር የሚለፉና ለዚሁ ሁሉ ሌላውን አሳልፈው የሚሰጡ ናቸው። በስልጣንም በንግድም በማናቸውም
ማህበራዊ ኃላፊነት ቢቀመጡ አታለው ለመኖር የሚጥሩ የሾማቸውን በክፉ ሰዓት ጥለው የሚጠፉ አምላካቸው
ሆዳቸው ብቻ የሆኑም ናቸው። ስለዚህም አስቸጋሪ ሁኔታ የሚጠብቃቸው መሆኑን ላረጋግጥላቸው እወዳለሁ።

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

1–ሐ በሦስተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች


በዚህ መስፈርት የሚያርፉት ብዙውን ጊዜ የሚያጠፉትን፣ የሚሠሩትን፣ ማናቸውንም ጉዳይ አምነውበት
ይበጀናል ብለው የሚፈጽሙ ናቸው። ጥፋትን ሲፈጽሙ ትክክል እንደሠሩ በነሱ እምነት ትክክል እንደሆነ
የሚቆጥሩ ለብዙ ሰው የጋራም ሆነ የግል ተቃውሞና ግሳጼ ቦታ የማይሰጡ የኔ ትክክል ነው ብለው የሚያምኑና
በዚህም እስከ መጉዳት የሚሄዱ ናቸው። እነዚህ ሰዎች ዛሬ በአለማችን ላይ በእምነት ውስጥ ለእምነቱ ብርቱ
ተሟጋች ሆነው የሚቆሙ የሌላውን ተጻራሪነት በማናቸወም መንገድ ማስወገድ የሚፈልጉ ሲሆኑ በስልጣን
ጫፍ ላይ ከወጡም ሥልጣኑን ለማቆየት ብቻ ሳይሆን በዚያ ስልጣን ላይ መቆየት አለብኝ ብለው ላመኑበት
ምክንያት ጸንተው የሚቆሙ ናቸው። ከአቅማቸው በላይ የሆነ በግድ የሚያስወግዳቸው ሁኔታ ሲፈጠር ብቻ
አቋማቸውን የሚፈትሹና ከጉዳት በኋላ እውነቱን የሚቀበሉ ናቸው። እነዚህ ሰዎች በዓለም ገጽታ ውስጥ በቁጥር
መስፈርት እንደተመለከቱት አይበዙም በእምነት ስንሄድ ሐዋርያው ጳውሎስን ስናስብ ለፈሪሳዊነቱ ለሕጉ በጽኑ
የቆመ ክርስቲያኖችን በማሳደድ እንቅልፍ ያጣ ሐዋርያቶችን እጅግ ያስጨነቀ ነበር። ጌታ ሲለውጠው እንኳን
በሐዋርያቶች ዘንድ እሱን ለመቀበል ረዘም ላለ ጊዜ የተቸገሩበት ነበር።
ሆኖም አምኖበት ነውና የተለወጠው በክርስቶስ የወንጌል ሥራ ከማንም በላይ ሠርቶ በመስዋእትነት ያለፈ
ጀግና ሐዋሪያ ነው። የቅርቡን በሥጋው ያለፉትን ብንጠቅስ ደግሞ እነአዶልፍ ሂትለር፣ እነሮሜል፣ እነስታሊን፣
ባገራችንም እነበላይ ዘለቀ፣ እነመንግሥቱ ነዋይ፣ እነጀነራል ታሪኩን እጅግ ብዙ ሰዎችን መጥቀስ ይቻላል።
በዚህ ክልል ለክፉ ይሁን ለበጎ፣ በሥጋውም ይሁን በመንፈሳዊ የሚመጡ ሰዎች በግል እጅግ የሚደንቁኝ
ናቸው። ከነዚህ ክልል ወደፊት በመንፈሳዊ ተልእኮም ሆነ በሥጋው ሥራ ብዙዎችን አያለሁ ብዬ ተስፋ
አደርጋለሁ። ጥረቱ መስመር እንዲይዙ እውነትን እንዲጨብጡ መጣር ሲሆን ልዑል ከያለበት ያወጣቸዋል ብዬ
አስባለሁ። እነሙሴን፣ እነአብርሃምን፣ እነያዕቆብን፣ ሁሉንም ሐዋርያቶች፣ ብንወስድ በዚህ ክልል የሚያርፉ
ናቸው። ሙሴ ከክብር ወደአመነበት ወደጭቃና ወደወገኖቹ እስራኤላውያን ሲመለስ ቅርም አላለው የተወው
ሕይወት /የግብፅ ሕይወት/ አልናፈቀውም ፈጣሪውን አወቀ በዚያው ጸንቶ ተጓዘ አለፈ።
አብረሃም አባቱን እሱም ቤተሰቡም የሚያምንበትን ጣኦት ትቶ በሰማው የፈጣሪው ድምጽ አምኖ ሁሉን
ትቶ ወደበረሃ በእምነት ወጣ፤ ማንም ያላገኘውን የእምነት ጽናት በሥላሴዎች ታደለ። ተባረከበት፣ ተቀደሰበት፣
ለሁላችን ተረፈበት፣የዘለዓለምን ሕያወት ወረሰበት። ያዕቆብ ጽኑ የእምነት ታጋይ ነበር፤ ከፈጣሪ የብርሃን
መልአክ ጋር ካልባረከኝ አልለቅህም ብሎ ታግሏል ሹሉዳው ተጎድቶ በጥረቱ የተደነቀው ፈጣሪ በረከቱን
አጎናጽፎታል። ሐዋርያቶችን ብንወስድ ከተለያዩ ከተናቀ ሥፍራ ጌታ ቢሰበስባቸውም ለቃሉ ታምነው፣
በወንጌል ለኛ ሆነው ለትውልድ ተርፈው በታላቅ መስዋእትነት ለድል በቅተዋል። በአገራችን አፄ ቴዎድሮስን
እነላሊበላን፣ እነ ዘርአያዕቆብን፣ እነ አፄ ዮሐንስን ብናስብ የእምነትም የአገርም መሪና ጀግና ሆነው ባመኑበት
ዋጋ ከፍለው አልፈዋል። ስለዚህ በስፋት ያሉ ሰዎች ለጥፋቱም እሰከጫፍ የሚሄዱ ለመልካሙም ብርቱ ዋጋ
የሚከፍሉ ናቸው። በዛሬው አለማችን ባመኑበት የተሰለፉ ብዙ ናቸው። ዲያብሎስ ከነዚህ ሰዎች የህሊና ምርኮኛ
ለማግኘት በብረቱ የሚጥርበት ነው። እስከ ፍፃሜ ባስጨበጣቸው እውነት መሰል ጥፋቱ ስለሚዘልቁ በብርቱ
ይፈልጋቸዋል ይጠቀምባቸዋል።

1–መ በዚህ በአራተኛው ዘርፍ ያሉ ሰዎች


በዚህ መስፈርት የሚከለሉት ደግሞ እጅግ መጥፎዎች ናቸው። እነዚህ በጎን መልካምን ነገር በፍፁም
የማይወዱ፣ በጭካኔያቸው ወደር የማይገኝላቸው ፍፁም ትእቢተኞች ናቸው። ማንኛውም ነገር የሚለኩት
ለራሳቸው የደስታ ምንጭ ይሆናል አይሆንም ከሚል መስፈርት ብቻ በመሆኑ ከተጣመመው ፍላጎታቸው ጋር
የሚጋጭ ሁሉ ቢጠፋ እምነታቸው ነው። እየሞቱም እየተሰቃዩም ቢሆን ከትእቢታቸው፣ ከክፋታቸው፣ መጥፎ

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ከመሥራት የማይመለሱና ባሳለፉት መጥፎ ተግባር መዘከር የሚደሰቱ ስለዚህ ብቻ መስማት የሚወዱ ናቸው።
ለዚህ ምሳሌ ጌታ ስለኛ በደል በመስቀል ሲሰቀል በመጥፎ ሥራቸው ከተሰቀሉት ወንጀለኞች ነፍሰ ገዳዮች
ውስጥ ግራና ቀኝ የተሰቀሉት ፋህታዊ ዘማዊና ፋህታዊ ፀጋምን ነበሩ። ፈያታዊ ዘየማን 70 ነፍስ በመጨረሱ
የተፈረደበት ሲሆን ፀጋም እንዲሁ ብዙ ነፍስ ያጠፋ ነው። ሁለቱም ስለጌታ መከራከር ጀመሩ በስተቀኝ ያለው
ፈያታዊ ዘየማን ስለጌታ ንጹህነት በመመስከር የራሱን ወንጀለኝነት በማመን፣ በመጸጸት ለቅጣቱ አግባብነት
ተከራክሮ ጌታ ግን ንጹህ መሆኑን መስክሮ በመንግሥቱ እንዲያስበው ጠየቀ ምሕረትም አገኘ፣ ገነት ከማንም
ቀድሞ ከጌታ ጋር ገባ። በስተግራ የተሰቀለው ፈያታዊ ፀጋምን ግን ጌታን በመዝለፍ ንጉሥ ከሆነ ራሱን ያድን
እያለ በማፌዝ በትእቢት እንደፀና አለፈ ወደ ጨለማው ነጎደ። በዚህ መስፈርት ያሉ በምንም መንገድ ቢሏቸው
የማይመለሱ በመሆናቸው በፍርድ የሚያገኙትን ቅጣት መቀበል ያለባቸው ናቸው። ባሁኑ ዘመን እነዚህ እጅግ
በዝተው እናገኛቸዋለን።

2. በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቃል ተመስርቶ በፈቃዱ ታዘው የቀረቡት መልእክቶች


ማንን ይዳኛሉ? በማንስ ላይ ተፈጻሚ ይሆናሉ?

የሰው ልጅ ከተፈጠረበት እለት ጀምሮ አክብሮት ሊኖርበት የሚገባ ትእዛዝ ተሰጥቶታል። ይህንን ትእዛዝ
ቢጥስ ደግሞ ቅጣት እንደሚከተለው በግልፅ የፈጠረን አምላክ ደንግጓል። መብትንና ግዴታን መመለሻውን
ድንበርና መሄጃውን መንገድ አመላክቶአል የሰው ልጅ ታዲያ ይህንን የልዑል ትእዛዝ አክብሮ አልኖረም
አባታችን አዳም እናታችን ሄዋን በእባብ ምክር በዲያብሎስ ጠንሳሽነት ትእዛዝን አፍርሰው ከተሰጣቸው ድንበር
ወጡ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ያስቀመጠውን ትእዛዝ በመጣሳቸው አዘነም ተቆጣ በፍርድ ወንበሩ ላይ
ተቀመጠ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት ለአጥፊዎቹ ምክንያታቸውን መሳሳት አለመሳሳታቸውን ጠየቀ።
የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ አዳም በሄዋን ሄዋን በእባቡ እያመካኙ ዛሬ የሰው ልጅ ሲያጠፋ ብዙ ምክንያት
እንደሚደረድረው ሁሉ አላጠፋሁም ብሎ መከራከር ከራስ ላይ የጥፋትን ኃላፊነት ማሸሽ ተጀመረ።
ትእዛዝ (ሕግ) ሲጣስ ቅጣት አለ። ከቅጣቱ በፊት ለዳኝነቱ ትእዛዙን ያወጣው ጌታ በችሎቱ ይቀመጣል።
ክርክር ይካሄዳል ቅጣቱ ይሰነዘራል። አዳም በማዘኑ በልቡ ይግባኝ በማለቱ ቢደመጥም የሞት ቅጣት ተሰንዝሯል
ለአዳም የሰው ዘር እየበዛ ምድርን እየሸፈነ ከመሄዱ በፊት ጌታ ሕግን እንዲጠብቅ በልቡናው ጻፈ ክፉንና
በጎውን እንዲለይ የሚያስችለው ህሊና ቀድሞም ሲፈጥረን ሰጥቶናል፣ በሕገ ልቡና ረዘም ያለ ዘመኖችን የሰው
ዘር ኖረ። በሕገ ልቦና ሰው ተዳኝቶአል። የኖኅ ዘመንን ማሰብ በቂ ነው። ሰዶምና ጎሞራን ማስታወስ ከበቂ
በላይ ነው። በሁለቱም ወቅቶች ጌታ በልባቸው ባስቀመጠው ህገ ልቦና ፍርድ ሰጥቶአል። ዳኝነት ተካሂዷል።
ቅጣቱም ተሰንዝሮ ተፈጻሚ ሆኖአል።
ኦሪት ዘፍጥረት ም2፡ 16 – 17
ኦሪት ዘፍጥረት ም3፡ በሙሉ
ኦሪት ዘፍጥረት ም6. 7 በሙሉ
ጌታ ሰው በዝቶ ምድርን መሸፈን ከጀመረ በኋላ የግድ የተጻፈ ሕግ ያስፈልገው ዘንድ አየ። ፈቃዱም ሆነ
በአባታችን ሙሴ ህገ ኦሪት ተደነገገች በዚህም የሰው ልጅ መብትና ግዴታውን እንዲያውቅ ተደረገ።
ከዚያች ጊዜ ጀምሮ ሰው ሲያጠፋ፣ ሲቀጣ፣ ምሕረት ሲጠይቅ፣ ንስሓ ሲገባ፣ ለጥፋት መስዋእት ሲያቀርብ፣
ምሕረትን በይግባኝ ሲያገኝ በየጊዜው ልዑል ዳኝነት ሲሰጥ ዘመናችንም ሲከንፍ አባቶቻችንም ኖረውበት
ሲያጠፉ፣ ሲማሩ፣ ወደ ምሕረት ዘመን ተደረሰ። ጌታ እንደቃሉ ለአዳም እንደሰጠው የይግባኝ መብትና በዚያም
በጨበጠው ተስፋ ከ5500 ዘመን በኋላ ጌታ ላንዴም ለሁሌም የሰውን የኃጢአት እዳ ለመክፈል መጣ። ቃሉን

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አከበረ፣ ሕግን ፈፀመ ሰው መፈፀም ያቃተውን ትእዛዙን ፈፀመ። ለሁሉም የሰው ልጅ ኃጢአት ንፁህ በግ ሆኖ
ታረደ ተሰዋ በሃጢአታችን የመጣውን የዘለዓለም ሞት በመስቀሉ ሻረ። የዘለዓለምን ሕይወት ለኛ አፀና የልጅነት
ክብርን አጎናጸፈን። ይህ ሁሉ ሆኖ አሁንም ቀሊል የሆነውን ሕግና ትእዛዙን አስቀመጠ።
እንጠብቀው ዘንድ አዘዘ። ስናጠፋ ንስሓ እንድንገባ እንቢ ብንል በችሎት ቀርበን እንደምንቀጣ አረጋገጠ።
ሰው ሞገደኛ ነው ሁላችንም በሥጋችን ተሸናፊ ነን። የምናየው ሁሉ እኛም እራሳችን ሁሌ እንደፈነጨን የምንጓዝ
ይመስለናል። በዚህም ትእዛዝን እንጥሳለን። ንስሓ ገብተን በትእዛዝ ጥሰት የሚሰነዘርብንን ቅጣት በይግባኝ
/በንስሓ/ ምሕረት ማግኘት ስንችል በትእቢታችን በመግፋት እንጎዳለን።
ጌታ ሁሌም ፍቅሩን በመግለጽ በመታገስ ጊዜ በመስጠት፣ በመውቀስ ቀላል አባታዊ ቅጣት በመሰንዘር ወደ
ትክክለኛው መንገድ እንድንመለስ ሁሌ ያደርጋል ይሁንና ሁሉም ገደብ ስላለው የግድ ብርቱ ቅጣት ይመጣል።
የሰው ልጅ ሁላችን የጌታን ሕግ ጥሰን የራሳችንን የሥጋ ሕግ የእግዚአብሔር ጠላት የሆነውን የዲያብሎስ ሕግ
በማጽደቅ የፍቅር ሕጉን ንቀን አታመንዝር ያለውን እንደ መብት በሕጋችን የማመንዘርን ፈቃድ አስቀምጠን፣
አትግደል ያለውን እንገላለን፣ አትዋሽ እንዋሻለን፣ ወንድምህን እንደ ራስህ ውደድ ያለውን ትተን አይ የለም
ወንድም፤ ባልንጀራ ገንዘብ እንላለን። በሁሉም ትእዛዝ አፍርሰን በጭለማ ሕግ መመራት ጀመርን።
በዚህም ምክንያት ሲታገስ የቆየው ጌያ በተለያዩ አገልጋዮቹ አማካኝነት ማስጠንቀቂያ ሰጠ፣ መከረ፣ ዘከረ።
መልእክት 1 መልእክት 2 በቃሉ ተመስርቶ በኔ በትንሽ ባርያው ለሰው ሁሉ እንዲዳረስ አደረገ። ፍርዱን
በመልእክት 1 አሳወቀ የደህንነቱን ትእዛዝ አወጣ ሦስት አመት ታገሶ ይግባኝ ያሉትን (ምሕረት የጠየቁትን)
በምሕረቱ አተመ። የናቁትን፣ ይግባኝ ያላሉትን፣ ፍርዱን ያልተቀበሉትን ወደ አፈጻጸም ውሳኔ በመሻገር
ፍርዱን ለማጽናት ተሻገረ። የእያአንዳንዳችን መዝገብ ላይ በየደረጃው የተካሄደውን የፍርድ ሂደት ጨርሶ ወደ
አፈጻጸም አለፈ። ተወሰነ አበቃ። ፍርድ ምን እንደሚመስል ሁላችንም እናውቃለን።
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፡ 53 በሙሉ
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተፈረደ። ይግባኙ ጠ/ፍርድ ቤት ሄደ። ተወሰነ፤ ከዚያ ወዲያ ወዴት ይኬዳል ወደ
አፈጻጸም ብቻ ይሆናል። በመሆኑም የዛሬው ይህ የፍርድ አፈጻጸምና መመሪያ ከልዑል ችሎት ወጣ። ይግባኝ
የለም ጊዜ የለም፣ ወደ አፈጸጸም የሄደ ውሳኔ በአስፈጻሚዎቹ እጅ ገብቷልና።
መልክቶቹና ፍርድ ሂደት አፈጻጸምና ውጤቱ ወንድሞች፣ እህቶች፣ መላው የሰው ዘር በሙሉ፣ ሰማይና
ምድርን የዘረጋ አምላካችን ሲያዝህ፣ ሲመክርህ፣ ሲወቅስህ፣ ለምን አትሰማም? እሱ የፈጠራቸውን እንደፈቃዱ
የሚሽራቸውን፣ የሚሾማቸውን፣ የሥጋ አለቆች ትፈራለህ። እነሱ ሲሉህ ትደነግጣለህ፤ ሲያዙህ ትታዘዛለህ፣
ፈጽም የተባልከውን ትፈጽማለህ፤ የአምላክህን ትእዛዝ ግን ትንቃለህ፣ ታሾፋለህ፣ ታፌዝበታለህ።
ብዙ አገልጋዮች ከልዑል ታዘው መጡ፤ መልእክቱን ተሸክመው፣ ምክርና ግሳጼውን፣ ቁጣውንና ፍርዱን፣
በረከትና ምሕረቱን ላንተ ለማድረስ የታዘዘውን የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር መልክቶች በመግለጻቸው
ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፣ ተገድለዋል። ይህ ሁሉ የተፈጸመው በዲያብሎስ በመመራት የጨለማን ሕግ
ለማጽናት በመሆኑ በዚህ ድርጊታቸው ገዥዎች ለስልጣናቸው ጥበቃ ሲሉ ሲፈጽሙት የኖሩት ነው። እነሱ
እንደሚሹት መሆን አለበት ባዮች ናቸው።
ይህን ዐመፃቸውን ለመግታት በተከታታይ የማሳሰቢያ፣ የመውቀሻ፣ የማስጠንቀቂያ መልአክቶች፣ ከጌታ
በአገልጋዮቹ በኩል ሲፈሱ ኖሩ። ይሁንና ዓለም ናቀ በራሱ ሕግና ደንብ ሰመጠ፣ ፈጣሪን ወግድ አለ ይህንን
የሺዎች ዘመን ትእግስትም ልዑል ጨረሰና በኔ በባሪያው በኩል በ7/3/1998 ዓ.ም የመጀመሪያውን ምድርና
በውስጧ ያሉትን የሰው ዘር በሙሉ የተመለከተ ውሳኔና ፍርድ አስተላለፈ፣ ተመለሱ አለ 3 ዓመት እያመመው
ጠበቀ ሆኖም ይህንንም አልሰማ ላለው የሰው ልጅ የመጨረሻው ውሳኔ በ27/9/2000 ዓ.ም በኔው በባሪያው

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በኩል ተገለጸ። ለመሪዎችም፣ ለእምነት ተቋሞችም፣ ለግለሰቦችም፣ ለዓለም አቀፍ ተቋሞችም፣ ለመላው ዓለም
አቀፍ የዜና አታሚዎችም ተሰጠ።
ኦሪት ዘፀአት ም. 32 በሙሉ
ትንቢተ ኢሳይያስ ም. 3፡ 8 – 15
አስገራሚ ሕዝብ ነው አንድም መሪ ድርጅት፣ አንድም የሃይማኖት ተቋም ትንፍሽ አላለም። እንደ ኃላፊነቱ
በሚገዛው በሚመራው፣ በእምነት ስም ለሰበሰበው አልገለጸም መረጃ ለሕዝብ አድራሽ ነኝ የሚል ጋዜጠኛ
ማንም አልተነፈሰም። በ7/3/1998 ዓ.ም የጀመረው የፍርድ ሂደት ቀጥሎ በ27/9/2000 ዓ.ም ምሕረት
ለጠየቁትም ለናቁትም ሁሉንም የይግባኝ የፍርድ ሂደት በልዑል ታየ የመጨረሻው ውሳኔ ጸና።
ዛሬ ደግሞ የፍርድ አፈጻጸምና ሂደቱን ለመግለጽ፣ ለማሳወቅ ይህ ትእዛዝ በልዑል ፈቃድ በኔ በትንሹ
ባሪያው እነሆ ለሰው ዘር በሙሉ ወጣ እንግዲህ አበቃ። አፈጻጸም ምን ይሆናል በሚል ሁላችንም ልናስብ
እንችላለን እጅግ ብርቱ ቅጣትን የሚይዝ ነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ 30፡ 8 – 14
ሹሞቻችን ይፈርዳሉ እንደ ፍርዳቸው ያሥራሉ፣ ይቀጣሉ፣ ይገላሉ፣ እነሱም ትላንት ሲፈርዱ ቆይተው
በተራቸው ይፈረድባቸዋል። እንዳሠሩ ይታሰራሉ፣ እንደ ገደሉ ይገደላሉ፣ ይህ የዓለም የሕግ ስርዓት ነው።
ሁሉም የዓለም ስርዓት በቆመው ሕግ በየጊዜው በሚመጡ፣ በሚወርዱ አለቃና ምንዝሮች ይዳኛል እሱም
ሲወድቅ በሌላው ተረኛ ይዳኛል።
ፈጣሪ ይዳኛል እንጂ አይዳኝም ፈጣሪ ፈጠረን፣ ሰራን፣ አበጀን፣ በፍቃዱ እስትንፋስ ዘራብን፣ አእምሮ ሰጠን፣
እኛ ቢሻ የሚያኖረን ባይሻ የሚያተነን ነን። እኛንና በላይዋ የኃጢአት ማዕበል ፈጠረን፤ የምንጨማለቅበትን
ዓለምም በፈቀደው ሰዓት በቃ ቢል ምንተን ነን። የሰው ጥጋብ ግን ወሰን ያለፈ ነው። በወንድሙ ላይ ሲሰለጥን፣
ሲግል፣ ሲቆርጥ፣ ሲያስር፣ ሲያጠፋ፣ ሲዘርፍ፣ በማይጨበጠው እሳት የሚዳብሰውን ጌታ ያቃልላል፣ ይንቃል።
ጨርሶም በትእዛዙም በመልእክቱም ንቀት ይሰነዝራል።
ይህ የአገራችን መሪዎችና ሹሞች በህሊና ማጣት በትእቢት ሲፈጽሙት እያየን ነው። የከንቱ ከንቱዎች
ናቸው። የእግዚአብሔር የፍርድ አፈጻጸም ሲጀመር አይታይም፣ ሲጨርስም አይዳበስም። በፈጣሪ ፍርድ የተያዘ
መሪም ተመሪም ሁሉም የተሰጠውን የፍርድ አፈጻጸም ሊያልፍ አይችልም። የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል
ይላል የጌታ ቃል፤ እስከ ዛሬ ሲወቀሱ አልሰሙም፣ ሲጠፉም አይሰሙም። ውጤቱ በልዑል የተወሰነው እውን
መሆን ብቻ ነው።

3. ዓለም በጥቅሉ የሚገጥማት የቁጣ ፍሰት

ትንቢተ ኢሳይያስ 24፤ 1 – 13


በሁለቱም መልእክቶች እንደተገለጸው ዓለም ከ12/12/2000 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ማበጠሪያው ወፍጮ
ገብታለች። ማበጠሪያው ትልልቁን ቆሻሻ የሚያስወግደው ሰፋ ያለ ቀዳዳዎች ባሉት የመጀመሪያው መሳሪያ
ሲሆን ሁለተኛው ከአንደኛው የጠበበ 3ኛው ከ2ኛው እየጠበበ የሚመጣ የእሳት ወንፊት ጀምሯል። እጅግ ከብዶ
ይቀጥላል።
የልዑል ቁጣ ገና ጅምር አሳየ እንጂ ሲፈስ እጅግ ይከፋል። በሕሊናችን ያልገመትነው፣ ያላሰብነው ቁጣ
ይፈሳል። ቀድሞ እንደነገርኳችሁ አንድም አገር፣ ማህበር፣ ተቋም፣ ግለሰብ አያመልጥም ሁሉም በተዘጋጀለት

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የቅጣት ጎዳና ይጓዛል። ሞት ከሆነ በሞት ለምኖ፣ ተሰቃይቶ ማለፍ ከሆነ ማለፍ፣ በጉዳት መቆም ከሆነ በጉዳት
ባጠቃላይ ሁሉም የተተመነለትን ይቀምሳል።
በእግዚአብሔር የተመረጡት በምሕረቱ የታተሙት ይቀራሉ። ለምሕረት ታስበዋልና ምድርን ይወርሳሉ።
ቀጣፊው፣ ውሸታሙ፣ አመንዛሪው፣ ነፍስ ገዳዩ ትእቢተኛው፣ በእውቀቱ የታበየው፣ በወርቁ በብሩ የተመካው፣
በታንኩ፣ በጀቱ፣ በኑዪክለሩ፣ በወታደሩ ብዛት የተመካው በሰበሰበው የሲሚንቶ ክምር የታበየው፣ በቆርቆሮና
የብረት ክምሮች የተመጻደቀው ሁሉ ወደ ትቢያነት ይለወጣሉ። ፋብሪካ፣ እንዱስትሪ፣ ሲደከምበት የኖሩበት
ሁሉ ለተባረኩት ይቀራል። እሱ የተባረከውን ዘመን ስለማያይ ከነዘሩ ይጠረጋል።
ውጤቱ ከላይ እንደተገለጸው ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪ በየአንዳንዱ የየአገሮች እጣ ፈንታ ርእስ ውስጥ
በዝርዝር ስለሚጠቀስ በዚያ የሚገለጸውን በጥንቃቄ ያንብቡ።

4. የእምነት ተቋሞች /በዳኝነት ሂደት ውስጥና/ እጣ ፈንታቸው

ትንቢተ ኢሳይያስ 5፡ 20 – 25

4–ሀ ካቶሊክ
ሮም /ጣሊያን/ መቀመጫዋን ያደረገችው ይህች እምነት ከተከታዮቿ ብዛት ያላት ናት። አንድ ቢሊዮን
የሚጠጋ አባል እንዳላት ትናገራለች። በዚህ እምነት ውስጥ ያሉት ምእመናን በአብዛኛው የሚገኙት በአውሮፓ፣
በላቲን አሜሪካ ነው። በሌሎች አገሮችም በዋናነት የሚያሰልፍ ቁጥር ባይኖራቸውም በማይናቅ መጠን አሉ።
ካቶሊክ በፖፕ የምትመራ ሲሆን በየሀገሩ እንደየብዛቱ የተሾሙ ጳጳሳት፣ ሊቀ ጳጳሳት፣ ዲያቆናት ወዘተ…
አሉአት። ካቶሊክ ማን ናት? ካቶሊክ በመጀመሪያ ልዑል ካስተማረው የተዋህዶ እምነት በ431 ዓ.ም እ.ኢ.አ.
ተገንጥላ በመውጣት፤ በንስጥሮስ ትምህርት በመወሰድ የክህደት ሥራን፣ የመለያየት ተግባር በማጽናት እንደ
ድርጅት የቆመች እምነት ናት። እስከአሁንም የጨለማ ሥራዋን እንደ መልካም የምትዘከር ናት።
በዓለም ላይ ያሉ በምሥራቅ ኤሽያ በብዛት የሚገኙ ስማዊ ኦርቶዶክሶች፤ ግብራዊ ካቶሊኮች እጅግ ሰፍተው
ይገኛሉ። በቀጥታም በተዘዋዋሪም በሷ የተጠለፉም አሉ። ጠንካሮችም አሉ። በዚህ ፅሁፍ የክርክር ሃሳብ
ለመፍጠር ሳይሆን ፍርድንና አፈጻጸሙን ለመግለጽ የወጣ መልእክት በመሆኑ ከዚህ የሚዘል ሃሳብ አይገለጥም።
ካቶሊክ በሰራዊት ጌታ እንዴት ታየች? ፍርዱስ እንዴት ይታያል የሚለውን እናያለን። ከ1500 ዘመን በላይ
በልዑል ፊት በአንዲት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት የክርክር ሂደት ተካሂዷልም፣ አካሂዳለች። በእምነት ጸንታ
ዓለምን በወንጌል ታረሰርስ የነበረችን የልዑል ቤት ማፍረስ የጀመረች ካቶሊክ ናት። እስከ 431 እ.ኢ.አ.
በታላቅ ፈተና እየጸናች፣ ዋጋ እየከፈለች፣ ሐዋርያቶችን፣ ደቀመዛሙርቶቿን እየገበረች የገሰገሰችው የተዋህዶ
እምነት ያልተበገረችለት ጠላት የመረጠው ዘዴ ከሃዲዎችን መፍጠር ነበር።
ወደ እውቀትና ወደ ፍልስፍና ያዘነበሉትን የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሥራን፤ በሥጋቸው የእውቀት
ትርጉም የተኩትን ጳጳሳት በመመልመል ለረጅም ጥፋት አነሳስታ ተሳክቶላት የተከለችው አረም በዝቶ ዓለምን
ሸፈነ።
ትንቢተ ሕዝቅኤል ም 22፤ 23 - 31
አርዮስን፣ ንስጥሮስን፣ አርጌንስስን፣ መንኪዮስን፣ አብርዮስን፣ አፍተክስን፣ አርሲስና መናፍቃንን፣ ልዮንን፣
መለካውያን፣ ወዘተ ማንሳት በቂ ማስረጃ ነው። እነዚህ በክርስትና ሕይወት ላይ የዘመቱ የዲያብሎስ ምልምሎች
ሲሆኑ ሁሉም የተሰለፉት አንድ ባሕርይ፣ አንድ አካል ብላ በምታምነው ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ነበር።

17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ዛሬም በነሱ አስተምህሮ ላይ ተመስርተው የቆሙት የዘመናችን ካቶሊኮች፤ ለጥፋት የቆሙ እጅግ ብዙ በጎችን
የበሉ፣ ተኩላነታቸውን በለምድ ሸፍነው እያጠፉ ያሉ ናቸው።
በአሁኑ ጊዜ ብዙ የውስጥ ችግር ቢያንቃቸውም በግብፅ፣ በሕንድ፣ በተለያዩ የኤሽያ አገሮች ከተኩላ ተርፈው
ጌታ ባጸናት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ጸንተው የቆሙ አሉ። ይሁንና እነሱም ካቶሊክን ከመሳሰሉ አጥፊዎች ዘወትር
በፈተና እንደተጠመዱ ይታወቃል። እስከ 431 ዓ.ም እ.ኢ.አ. ድረስ በሮም በሐዋርያው ጴጥሮስ መንበር
እየተፈራረቁ ጳጳሳት በተዋህዶነት ጸንተው የኖሩ ሲሆን ከ431 ዓ.ም ጀምሮ በልዮን ትምህርት ተለወጠች።
ከዛ በፊት ግን እውነትን የጸና ተዋህዶን ያቀኑ ሊቃነ ጳጳሳት መሃከል ጥቂቶቹን ባናሳ፤ ቅዱስ ፊሊክስ ሊቀ
ጳጳስ፣ ቅዱስ አቡሊድስ ሊቀ ጳጳስ፣ ቅዱስ አዮክንዲዮስ ሊቀ ጳጳስ፣ ቅዱስ ናጣሊስ ሊቀ ጳጳስ እነዚህን የመሰሉ
የተዋህዶ እምነት ጀግኖች በሮም ጸንተው አልፈዋል። ወንበር ገልባጮች፣ የዲያብሎስ ደቀ መዝሙሮች በልዮን
ግንባር ቀደምትነት እስካፈረሷት ድረስ በአንዲት ተዋህዶ እምነት ልዩነት አልነበራትም።
ዘመቻው ሰፍቶ ዲያብሎስ ደርጅቶ ከ1500 አመታት በላይ ሲያጠፋ፣ ሲያሳድድ፣ ኖሮ አልጠፋ ብላ፣
አልቆረጠም ያለችው በኢትዮጵያ የጸናችው ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ብቻ ናት። የብዙ ሐዋርያት ደም የፈሰሰው የት
ነው? የብዙ ነብያት ደም የተረጨው ከማን አገር ነው? ብዙ የወንጌል አርበኞች የተፈጁት የት ነው? ሮም /
ጣሊያን/ ፣ ሩቅ ምሥራቅ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አፍሪካ ሥራችሁን ታሪካችሁን ፈትሹ! ንጹህ ደም በእጃችሁ
አለና።
ኢትዮጵያ ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ የወንጌል ጀግኖችን ተቀበለች እንጂ አላጠፋችም። ሳያዩ የሚያምኑ
ብጹአን ናቸው። በሩቅ ሰምታ አመነች ዛሬም ድረስ ቆመች። ዛሬ ስለእናንተ የጥፋት አለቆች ብዙ መጻፍ
ይቻላል። እናንተን የተዋጉ ኢትዮጵያዊ የተዋህዶ ጀግኖችን ጥቂቶችን ብቻ አነሳለሁ።
ትንቢተ ኢሳይያስ 47፡ 1 – 15
ትንቢተ ኤርሚያስ 17፡ 5 – 8
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ አለቃ አያሌው፣ እነ ንቡረእድ ኤርምያስ፣ እነ አባ
ተክለማርያም፣ ከምስከየ ሕዙናን እነ አቡነ ተክለሃይማኖት /ሃዋርያ/ ብፁዕ አቡነ ባስሊዮስ፣ ከናንተ የወጡት
አባ ጴንጤሊዮንን፣ አባ ሊቃኖስ፣ ከናንተው ፈልሰው በኢትዮጵያ የኖሩትን መጥቀስ ይቻላል።
ኢትዮጵያውያን የወንጌል ጀግኖች እጅግ ብዙ ናቸው። ለዚህ ሃይማኖተ አበውን ማንበብ ይጠቅማል። ፊት
ለፊት የሚቆም ጠላትን መለየት አያስቸግርም፤ መለየት የሚያስቸግረው የበግ ለምድ የለበሰ ተኩላን ነው
ብርቱም ጠላት ነው።
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስን ለማጥፋት በለምድ ለባሽ ተኩላነት ከተሰለፉት ከካቶሊክ የሚቀድም የለም።
ሌሎቹ የፊት ለፊት ጠላቶች ናቸው። ካቶሊክ ፀጋ፣ ቅባት፣ እያለች በኢትዮጵያ መለያየትን ለመፍጠር ብዙ
የደከመች ናት ዛሬም ከጥፋቷ ያለተመለሰች ናት።
ትንቢተ ኢሳይያስ 5፡ 18 – 25
ካቶሊክ ዛሬ ምን ታደርጋለች? ካቶሊክ ብዙ አጥፊዎችን የፈለፈለች ናት። በመልእክት ቁጥር 1 እና
በመልእክት ቁጥር 2 እንደተመለከተው በሀገሯ፣ በመቀመጫዋ ከሮም ተነስቶ በመላው ዓለም የተበተነን
የኃጢአት ሥራ እያጸደቀች የምታሰማራ ናት።
በእውቀት በመታበይ፣ የጥፋት ታሪኳን እንደበጎ ሥራ በመዘከር፣ ገንዘብ በመሰብሰብ፣ ሶዶማውያንን በውስጧ
በማበልጸግ፣ በቤቷም በማጋባት ነፍሰ ገዳዮችን በመመረቅ፣ የዓለም ቁጥር 1 ወንጀለኞችን ባቢሎንን /

18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አሜሪካንን/ አውሮፓን፣ በጥፋታቸው የምታበረታታ ናት። ካቶሊክ ከምንም በላይ የከፋ የእውነት እንቅፋት
ናት። ወደ እውነት የሚመጡትን የዋሀንን በመጥለፍ የምታጠምድ ተኩላ ናት።
በጌታ ፊት 1500 አመታት በላይ በጥፋት ጎዳና ፀንታ የቆመች ዛሬም በዛው ያለች፣ በዚሁ ልትዘልቅ
የወሰነችም ናት። ፍርዷ 431 እ.ኢ.አ. ጀምሮ ከ1500 አመታት ላላነሰ ጊዜ ሲታይ ኖሯል። ጌታ ሥራዋን
ሲመዝን አካሄዷን ሲለካ በትእግስት ጽዋው ሞልቶ እስከሚፈስ ታገሳት፣ የእውነት ሰዎችም ቢመጡላትም
ስታሳድድ፣ ስታስር፣ ስትገድል ኖረች። ሁሉንም በወንጌል ስም በልዑል ቅዱስ ስም ሽፋንነት ስትፈፅም
ጌታ አየ። በእጇ የሞላውን ንፁህ የደም መጠን ለካ፣ አፏን አጣፍጣ ስንቶችን እንዳጠፋች አየ። ሳታፍር ጌታ
በከፈለው ዋጋ ላይ አላገጠች እምነት ካባ ያጠለቁ፣ በእውቀት የታበዩ፣ በእውቀት እኛ መልካም ነን የሚሉ፣
አምላካቸው እውቀት የሆነ የብዙ ለምድ ለባሽ ተኩላዎች አዘመተች ይህንንም አየ የድንግልን ክብር ቀንሳ
በአርያም የከበረውን ከድንግል የተዋሃደውን ሥጋ ለማራከስ ጣረች፣ በስም የምትጠራትን እናታችንን ድንግልን
በግብር ካደች። ካቶሊክ ተመዘነች፣ ተፈተሸች፣ ተለካች፣ ፍርዷወጣ፣ በመልእክት 1 በ7/3/1998 ዓ.ም
ይግባኙም ታየ። በ27/9/2000 ዓ.ም ፀደቀ ለምሕረት የሚሆን ነገር በረጅሙ ዘመን የፍርድ ሂደት ቢፈተሽ
ጠፋ እንደ ፍርዱም ይህ የመጨረሻ የፍርድ አፈጻጸም ወጣ።
ካቶሊክ አድምጪ ካቶሊካውያንም አድምጡ እንደ ድርጅት፣ እንደ መሪ ተመሪ፣ እንደ ግለሰብ፣ እንደ
አገልጋይ ተገልጋይ፣ በማናቸውም ከፍታም ሆነ ዝቅታም፣ በስውርም በግልጽም፣ ያላችሁ በሙሉ በከፋ እሳት
ትበጠራላችሁ፣ እያንዳንዱ ቤታችሁ፣ መከለያችሁ፣ መታመኛችሁ ሁሉ ይጠረጋል። ጉዳታችሁ እስከዛሬ
ተሰምቶ የማይታወቅ ሞትን የሚያስመኝ ይሆናል። ምልክታችሁ ይጠፋል ተፈልጎም አይገኝ በናንተ ላይ
የሚደርሰው ቅጣት ለሚያየው እጅግ ይዘገንናል።
ዛሬ የምታዩት የገንዘብ፣ የኢኮኖሚ፣ የኢንዱስትሪ ቀውስ፣ የሥራ ማጣት፣ የኢኮኖሚ መጨማደድ፣ ሁሉ
ጅምር እንጂ መቼ ወደዋናው ቅጣት ተገባና! ከእንግዲህ ወደቁልቁለቱ፣ ወደጨለማው፣ ወደአዘቅት ጉዞ ሀ ብሎ
ተጀምሮአል። እስከ መጨረሻው ይቀጥላል። በመልእክት 1 በመልእክተ 2 እንደተመለከተው የመተንፈሻ ጊዜ
አይሰጥም። ጥፋታችሁ በአይነቱ ልዩ ነው፤ ቅጣታችሁም ማንም የማያስበው ይሆናልም ተብሎ የማይገመትም
ይሆናል።
ለመተንፈስ፣ ለመዳን፣ ለመትረፍ፣ የሚቻለው እንደ ድርጅት በካቶሊክነት እቆማለሁ ብሎ ከእንግዲህ
በማለም አይደለም። ሁለመናችሁን ለፈጣሪ ማስገዛት፣ እጃችሁን ለተዋህዶ እምነት ያለምንም ማቅማማት
መስጠት ብቻ ነው። እንደ መሪም፣ እንደ ግለሰብም ሁሉም ስቃዩ ሲበረታበት መዳኛው አንድ ቀዳዳ ብቻ
ነው። በኢትዮጵያ ለምትነግሠው ዛሬ ካሉት ተኩላዎች በምትጸዳ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ስር
በመውደቅ ብቻ ነው።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 34፡ 17 – 19
መንፈሳዊውም ሥጋዊውም አሰራር ለዓለም ሁሉ የሚመነጨው ከኢትዮጵያ ብቻ ይሆናል። ዛሬ በአገራችን
በኢትዮጵያ ያለው መንፈሳዊውም ሥጋዊውም መሪዎች በሙሉ በእግዚአብሔር ፍርድ የታዩ ሲሆን ተመዝነው፣
ተለክተው እጅግ የቀለሉ በመሆናቸው እግዚአብሔር የወሰነላቸውን ቅጣት የቀበላሉ። ከእናንተም በየትኛውም
የአገልግሎት ስፍራ ይኑር ጳጳስም ይሁን ሊቀ ጳጳስ፣ ቄስም ይሁን ዲያቆን ሁሉም ይፈተሻል። ምእመኑም
ይፈተሻል፣ ይበጠራል ከዚህ የሚያመልጠው እድለኛ ነው። ማንም ሰው ሊያመልጥ የሚችለው እስከዛሬ
በተሰጠው ምክር ተጠቅሞ ከሆነ ነው። ይህን ካደረገ በምሕረት መዝገብ ሰፍሮአል ማለት ነው። ካላደረገ ደግሞ
በእሳት እየተበጠረ ወይ ያልፋል ወይ ይድናል ይሄ የጌታ ውሳኔ ነው። እኔ ግን የምላችሁን እየተጎዳችሁም ቢሆን
ራሳችሁን ከመአቱ ለመከለል ለልዑል እጃችሁን በመስጠት አምልጡ ነው።

19
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

4–ለ ፕሮቴስታንት
ይህ እምነት ከካቶሊክ ተገንጥሎ የወጣ እምነት ነው። መሥራቹ ማርቲን ሉተር ከካቶሊክ መሪዎች ጋር
ተጋጨ፣ በዚህም በማመጽ ተለየ /proteset/ አመጽ አደረገ። ስማቸው እንደሚገልጸው አመፀኛ፣ ተቃዋሚዎች
ናቸው። የመጀመሪያው የእምነት ተቃዋሚ ካቶሊክ ስትሆን ከሷ ማህፀን የወጡት ደግሞ ያንኑ ያስተማረቻቸውን
ጨብጠው በተቃውሞ ያደጉት ፕሮቴስታንቶች ናቸው። ካቶሊክ ማህፀኗ የሚፈለፍለው አመፀኛን ብቻ ነው።
ስለዚህም ፕሮቴስት አድራጊዎች ብዙ ናቸው። አንጀሊካን፣ 7ኛው ቀኖች /አድቬንቲስት/፣ ፕሬስባይቴሪያን፣
ጆቫዊትነስ ምን ስፍር ቁጥር አላቸው በአገራችን ብቻ ከ10 በላይ የፕሮቴስታንት ክፍልፋዮች የሞሉ ናቸው።
መካነ ኢየሱስ፣ ቃለ ሕይወት፣ ሙሉ ወንጌል፣ ዋና ዋናዎቹ ናቸው። ልብ በሉ የሰው ልጆች።
አስከ 431 ዓ.ም እ.ኢ.አ. በመላው ዓለም ፀንታ የነበረች ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ናት። በመጀመሪያ ተገንጥላ
ወጪ ደግሞ ካቶሊክ ስትሆን ከካቶሊክ ማህፀን ውስጥ ደግሞ ፕሮቴስታንት፣ ከፕሮቴስታንት ማህፀን ውስጥ
ደግሞ ቁጥር ስፍር የሌለው ተቃዋሚ ተፈለፈለ። እኒህ ሁሉ ዲያብሎስ የሚሰጣቸውን የረቀቀ አጀንዳ ለማራመድ
እየለፉ ያሉ ናቸው።
ትንቢተ ኢሳይያስ 9፡ 13 – 17
እውነቱን በድፍረት ለማጥፋት እንደ ፕሮቴስታንቶች ደፋር የለም። የጌታን ቃል ይሸረሽራሉ፣ ለደህንነታችን፣
ለመማለዳችን፣ ለእናትነት ከልዑል የተሰጠችን በረከት ድንግልን፣ የመድኃኒታችንን እናት በአማላጅነቷ ዓለምን
የምትታደገውን ይንቃሉ። ቅዱሳን መላእክትን በእሳት የተሞሉትን፣ ማንም በይቀርበው ብርሃን ዙፋኑን በዘረጋው
ልዑል ፊት ዘወትር የሚቆሙትን እንደ ተራ ተላላኪ በመቁጠር ክብራቸውን ሲቀንሱ፣ ለሰው ዘር በሙሉ
በመማለድ፣ በማጽናናት፣ ሲወቀስ በመውቀስ፣ ሲያጠፋ በመመለስ፣ ሲባረክ ለመባረክ፣ የሚተጉትን ሲያናንቁ
የሚውሉ የሚያድሩም ናቸው። እኒህ የከይሲ ልጆች የጌታን ክብር ወደ አማላጅነት በማውረድ የሚለመነውን
ጌታ የሚለምን የሚያደርጉ ናቸው። በዚህም መልእክት ከእነርሱ ጋር ክርክር ለማድረግ የታዘዘ አይደለም
የፍርዳቸውን አፈጻጸም እንዲያውቁት እንጂ።
እነዚህ እውነትን በማጥፋት ላይ ከሚተጋ የዲያብሎስ መሳሪያዎች ዋናዎቹ ናቸው። በመላው ዓለም ከካቶሊክ
ቀጥሎም የተንሰራፉ ናቸው። ዋናዋ ባቢሎን /አሜሪካ/ የመንግሥት እምነቷ ፕሮቴስታንት ነው። ገዢዎቿን
ከምትለካበት 7 መለኪያ አንዱ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ መሆንን ነው። ባቢሎን ደግሞ የዛሬው የዓለም
የጥፋቷ ቁንጮ ናት። ደፋሮች ናቸው፣ የጥፋት እናቶችም ናቸው።
አድምጥ ፕሮቴስታንት የሆንክ ሁሉ አለቃም ሆንክ ምንዝር፣ በየትም ዓለም ኑር መርዶህን ስማ። በቁጥር
1 በቁጥር 2 መልእክቶች ፍርድህ ተገልጾአል። የዛሬው መልእክት አፈጻጸሙን ይነግርሃል። ፍፁም ከምድር
የምትጠረጉ እናንተ ናችሁ። በየትኛውም የምድር ፊት ለናንተ የሚተው መደበቂያ የለም። ምሕረት ለእናንተ
የለም። በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ላይ ያላገጣችሁ ናችሁና። በየትኛውም ቀዳዳ፣ በየትኛውም ዘዴ መከለያ
ምሕረት አታገኙም። እናንተን እንደ ድርጅት የሚቀበል አልፎም የሚያናግርም ካለ ከናንተው ይደመራል
ቅጣቱን ይቀበላል።
ትንቢተ ሕዝቅኤል ም13 20 - 23
ተዋህዶ ኦርቶዶክስ በመላው ዓለም ስትጸና የናንተ ማረፊያ ሲኦል ይሆናል። ለናንተ ፀሐይ አይወጣም
ይጨልማል እንጂ።
ስለዚህ ስማችሁ ይሻራል፣ ድርጅታችሁ ይፈርሳል፣ መሰብሰቢያችሁ ሁሉ ይከረቸማል። በየትኛውም ቦታ
በዚህ ስም የምትንቀሳቀሱ ሁሉ መላውን ዓለም እንዲገዛ በተወሰነው መንፈሳዊና ሥጋዊ ሕግ የተዋህዶ ሕግ

20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ትዳኛላችሁ። ለእናንተ በምንም መስፈርት የሚተው የምሕረት ቀዳዳ የለም። ይህ በእናንተ ላይ የሚፈጸም
መሆኑን አውቃችሁ ጠብቁ።

4–ሐ እስልምና።
እናንተ የእምነቱ አራማጆች ልብ ብላችሁ አድምጡ በተደጋጋሚ እየገጠማችሁ ያለውን ውድመት ማስተዋል
ተስኗችኋልና። በዚህ የመጨረሻው የአፈጻጸም ሂደት ምን እንደሚመስል ስሙ ተረዱ። እስልምና ፍፁም
የተሳሳተ ብዙ ሰዎችን ለጥፋት የዳረገ እምነት ነው። እስልምና ተረት መሰል የጠላት ዲያብሎስ ድርሰት ነው
ብንል ከእውነት አንርቅም።
ሰውን አጥፍቶ እኔ እኖራለሁ የሚል፣ በገዛ ወገኑ ሞትን የሚዋጅ፣ ገነት በደም ጨቅይቼ እገባባታለሁ የሚል
ፍፁም የጥፋት እምነት ነው። በዚህም መሰረት ላይ ቆሞ ለሰው ጥፋት መሳሪያ ሰብስቦ በዚሁ ሁሉንም እምነት
ጨፍልቆ በራሴ አምሳል ጠፍጥፌ እሰራለሁ የሚል ድርጅት ሲሆን፤ በውስጡም ያሉት ፍፁም የዲያብሎስ
ሰራተኛ የሆኑ እውነት መስሏቸው yeተሳሳቱ፣ እንደ ባህል የያዙ፣ ከዝርያ ጋር አያይዘው የሚያዩ ሱኒ፣ ሺያት፣
በሚል የዘር ሀረግ የሚፋጁ አንዱ አክራሪ /ዋህቢያ/ አንዱ ሺያት፣ አንዱ ሱኒ እያለ አንዱ ለአንዱ ሞት
እየደገሰ የሚፋጅበት ገንዘብና እምነቱን በአንድ ሻንጣ አስጨብጦ በደሃ አገሮች ላይ የሚዘምትበት የጥፋት
መሳሪያ ነው።
ስለዚህ የዚህ እምነት ተከታዮች በመልእክቱ እንደታየው በሰበሰባችሁት መሳሪያ እራሳችሁ ታልቁበታላችሁ።
እስከምትከስሙ ድረስ፣ ከጥጋብ ተራራ እስክትወርዱ ድረስ፣ አጥታችሁ ነጥታችሁ ትቢያ ላይ እስክትወድቁ
ድረስ የሀብት፣ የመሳሪያ ክምራችሁ በኖ እስኪጠፋ ድረስ፣ ትንፋሽ የማይሰጥ የጥፋት፣ የውድመት እሳት
ታዞላችኋል። ከእናንተ የሚያመልጡት እውነትን ከልባቸው የሚፈልጉ ፈጣሪን ከልባቸው የሚወዱ ቅን፣ የዋህ፣
ትሁት የሆኑ የጥፋት ሥራችሁን የማይወዱ ብቻ ይድናሉ ወደ እውነተኛው የብርሃን መንገድ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ
ቤተ ክርስቲያንርስቲያን ይሰበሰባሉ።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 22፡ 1 – 5
ይህ እድል የሚገጥማቸው በመጪው የሚያበጥረው እሳት አልፈው የሚድኑት ብቻ ናቸው። እስልምናን
የመንግሥት እምነት ያደረጋችሁ አገሮች ሕዝቦች እጣ ፈንታችሁን ከየአገሮቹ ዝርዝር ልታዩ ትችላላችሁ።

4–መ ቡዲሂዝም ኮንፊሽየስ፣ ሺንቶይዝም እና ሌሎችም ተዛማጅ እምነቶች


የዚህ እምነት አራማጆች ባብዛኛው ያሉት፡– በቻይና፣ በቬትናም፣ በጃፓን፣ በላኦስ፣ በታይላንድ፣
በካምቦዲያ፣ በበርማ፣ በኔፖል፣ በመሳሰሉት ሲሆን 1.8 ቢሊዮን ሕዝብን ያቅፋሉ ተብሎ ይገመታል።
በጥቃቅን ጉዳይ ይለያዩ እንጂ ሁሉም መሰረታቸው ቡድሃ ነው። ምልክታቸውም ድራጎን ነው። ይህንንም ቻይና
በኦሎምፒክ ዝግጅቷ እንደ መግቢያ አድርጋ እስከነመቅደሱ ስታሳይ ነበር። የዲያብሎስን ምልክት ምልክቴ ብላ
የያዘች በግልፅ ለዲያብሎስ ሀውልት ያቆመች ሀገር ናት። የዚህ እምነት አራማጆች ፈጣሪ ብለው የሚያምኑት
ዘንዶውን በመሆኑ ይህ እምነት በግልፅ ዲያብሎስ የሚመለክበት ስርዓት ነው።
አድገናል፣ ተመንጥቀናል፣ የሚሉት እኒህ የቻይናና አጎራባቾቿ በርግጥም በሥጋ እድገት መወፈር
ይታይባቸዋል። ዲያብሎስ ከምትጠፋው /ባቢሎን/ ማዘዣ ጣቢያውን ወደፔኪንግ ያዞረ ይመስላል። ነገር ግን
ይህ ሳይሆን ራሱን በተለያየ የጨለማ እምነት መግለጽ የሚችለው ዲያብሎስ አንዱን ከፍ አንዱን ጣል በማድረግ
ዓለምን በቅናት፣ በፍጅት፣ አንድ አንዱን እንዲያናንቅ በማድረግ የሚጠቀምበት ስትራቴጂ ነው።

21
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ስለዚህ ይህ እምነት የዲያብሎስ እምነት እንደመሆኑ መጠን የሚያርፍባቸው እሳት ፍፁም የሚጠርግ
ከመሰረታቸው የሚያጠፋ ይሆናል። በዚህ እምነት የታቀፉ አገሮች ጥፋት ብርቱና ቶሎም የማይጠፋ ነው።
ዝርዝሩን በየአገሮቹ ርእስ ውስጥ ይገኙታል።

4–ሠ ሂንዱይዝም
ይህ እምነት በስፋት እንደሚታየው በህንድ ውስጥ የተንሰራፋ ከ800 ሚሊዮን ያላነሰ ሕዝብ ያቀፈ እምነት
ነው። ይህ እምነት የተለያየ ስም ያላቸው ጣኦቶችን የሚያመልክ እንስሶችን፣ በተለይም ላምን እንደ አምላክ
የሚያከብር እምነት ሲሆን የጥንት ፍልስጤማውያን፣ አማሌቃውያን፣ እያቡሳውያን፣ ሶርያውያን ያመልኩት
የነበረውን ቡኤል፣ ዘቡኤልን ዛሬም ይዘው ያሉ ናቸው። እነዚህ ሕዝቦች ፍፁም በዲያብሎስ የጨለማ አገዛዝ
ያሉም ናቸው። ዲያብሎስ እንደ እቅዱ እንደ ቻይና በሀብት ሊያበለጽጋቸው የሚደክምባቸው ናቸው።
ትንቢተ ኢሳይያስ 2፡ 12 – 22
ትንቢተ ኤርሚያስ 10፡ 2 – 15
ትንቢተ ኢሳይያስ 44፡ 9 – 16
ከጎናቸው ያለው የሳኡዲ አረቢያ መካ የእስልምና እምነት ማእከል ሲሆን ዲያብሎስ በሌላው ቅርጹ
የሚያዘው የጨለማ ጣቢያው ነው። እነዚህ ሕዝቦች እጅግ ብዙ የእግዚአብሔርን አገልጋዮችና ሕዝቦች በታላቅ
ፍጅት በማጥፋት የሚዘክር ታሪክ ያላቸው ናቸው።
ይህ እምነት በማያሻማ መልኩ ዲቢሎስ አገዛዙን ፍፁም ያሰፈነበት ነው። በመሆኑም ይህ እምነት ከመሰረቱ
እስኪጠፋ በእሳት የሚጠረግ ይሆናል። በነዚህ የሚወርደው እሳት ከውስጡ የሰው ዘር ይተርፋል ወይ የሚያስብል
ነው። ከዚህ የቁጣ ማዕበል የሚያመልጡ ምንኛ የተባረኩ ናቸው። የዚህ እምነት አለቃና አራማጅ አገሮች እጣ
ፈንታ ፍጻሜ በየአገሮቹ ሸክም ዝርዝር ውስጥ ታገኙታላችሁ። በዚችው በህንድ ውስጥ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ
እምነት ተከታዮች ያሉ ሲሆን ይህን መልእክት በጥንቃቄ እንዲያነቡትና እንዲይዙት ይመከራሉ።

4–ረ ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ


በሩቅ ምሥራቅ፣ በሩስያ፣ በቡልጋሪያ፣ በሩማንያ፣ በኢስቶኒያ፣ ላትቪያ፣ ዩክሬን፣ ጆርጅያ፣ አርመንያ፣
ኢስቶንያ፣ እና ሌሎችም በብዛት ጎልቶ የሚታይባቸው እምነት ነው። ፍፁም ተዋህዶ ኦርቶዶክስን የጨበጡ
አይደሉምና በተለያየ የካቶሊክ፣ አንጀሊካን፣ ፕሮቴስታንት እምነት መሰረታቸው የተቦረቦረ በመሆኑ
ጉድለታቸውን አርመው ከመምሰል ወደ መሆን እንዲመለሱ በጌታ መላሽ ቅጣት የሚጠብቃቸው ናቸው።
በዓለም ላይ ያሉ የብዙ እምነት መሰል ተቋሞች ያሉ ሲሆን እነዚህም እንዲሁ በልዑል የፍርድ ሚዛን
ተፈትሸው የታዩ ሲሆን ቅጣታቸውን የሚቀበሉበት ሁኔታም ተዘጋጅቷል። ማንም ከልዑል ፍርድ ሾልኮ
የሚያመልጥ የሰው ዘር የለም።
የዮሐንስ ራእይ 3 ፡ 1 – 6

4–ሰ ተዋህዶ ኦርቶዶአክስ እምነትና ቤተ ክርስቲያን


የልዑልን ቃል ተብቃ የምትጓዝ እምነት ከህገ ልቡና ከኦሪት ሕግ ዛሬም በአዲስ ኪዳን ሁሉንም በአግባቡ
ጠብቃ ሳትቀንስ ሳታጎል በታላቅ የፈተና እሳት ያለች እምነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ!

22
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የመጀመሪያቱ ጌታ ያጸናት ሐዋርያቶች የተሰውላት፣ ነብያቶች የተፈጁላት፣ በዲያብሎስ የሺዎች ዘመናት


ፈተናና የከበደ መከራ የጸናች የገሃነም ደጆች ያልቻሉአት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት!
እውነተኞቹ፣ በእሳት ተፈትነው ነጥረው እየሞቱ እያለቁ ለልጆቻቸው ያሻገሩአት የእምነት አንበሶች ምሽግ
ተዋህዶ ኦርቶዶክስ፣ ድንግልን በእናትነቷ በአማላጅነቷ፣ ፍፁም በሆነው ፍቅሯ እየተጠበቀች እየተባረከችበት
የዘለቀችበት የእምነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት!
የአምላኳን ሥላሴዎችን ምስጢር ጠንቅቃ ያወቀች ዋጋ የከፈለላትን ጌታ በአንድ ባሕርይ ሦስትነቱን
በማይለያይ፣ በልዕልናው የልዑላን ልዑል፣ በቅድስናው የቅዱሳን ቅዱስ፣ በንጽህናው የንፁሃን ንፁህ፣ በግርማው
ግሩማንን የሚያስፈራ፣ በግዛቱ የገዝዎች ገዢ፣ በሐሳቡ የጥበበኞች ጥበበኛ፣ ስለእርሱ ከዚህ እስከ እዚህ
የማይባል፣ የእግሩ መረገጫ በዚህ፣ ራሱ በዚህ ነው የማይባል፣ መድረሻው እስከዚህ ነው የማይባል፤ በሁሉ ቦታ
ሙሉ ሆኖ ታምራትን የሚደርግ በሰው ህሊና የማይዳሰስ፣ የማይገመት፣ መሆኑን የምታምን፣ ጸንታም የቆመች
ተዋህዶ ኦርቶዶክስ።
በመላው ዓለም ያሉትን የተዋህዶን ልጆች በጽናት ይቆሙ ዘንድ አርአያ ሆና ለሁሉም ከጌታ የተሰጣትን
ብርሃን እያበራች እየተፈጨች፣ እየተቆላች፣ እየነደደች፣ በእሳት ማዕበል ያለፈች የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ
እምነት ዛሬ ልዑል ድካሟን አየ። በፍቅሩ ፍፁም ወደዳት።
የልዑል ታማኞችን የከበሩ መላእክትን፣ ገብርኤልን፣ ሚካኤልን፣ ሩፋኤልን፣ ፋኑኤልን፣ ኡራኤልን፣
ራጉኤልን፣ ሣቁኤልን ሁሉ ታምናባቸው ወድዳቸው፣ በአማላጅነታቸው ተደግፋባቸው፣ በፍቅራቸው ተወዳ፣
በበረከታቸው ተሞልታ፣ በጥበቃቸው ፀንታ የቆመች የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ታሰበች
ተወደደች።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 34፡ 25 – 31
ትንቢተ ኢሳይያስ 40፡ 9 – 11
ዓለም ሁሉ በምርኮ ተሰጣት፣ የወደዳት ጌታ በሷ በኢትዮጵያ ዙፋኑን ሊያጸና ወሰነ ማለ በበረከቱ በቸርነቱ
ሁሌም ሊያረሰርሳት አጸና። ከውስጧ የሚፈሰውን የምስጋና ጸሎት፣ ማህሌት፣ ቅዳሴ፣ ሰአታት እንደ መልካም
ሽቱ ወደደ። የአገሬ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ አርበኞች አባታችሁ መጣ። እየገሰገሰ! በድንግል፣
በገብርኤል፣ በሚካኤል፣ ታጅቦ መጣ። ሆናችሁ፤ ከመምሰል ርቃችሁ፣ ተሰዳችሁ ተርባችሁ፣ ታሥራችሁ
ደህይታችሁ፣ ተነቅፋችሁ ቁጥር ስፍር በሌለው ጠላት እንደ መንግሥት በቆመ ገዥ፣ እንደ ሃይማኖት ድርጅት
በቆሙ ዓለምን በሸፈኑ የዲያብሎስ እምነቶች የደረሰባችሁ የብዙ ሺ ዘመን ሰቆቃ ዋጋ ሊከፈለው በልዑል
ተወሰነ፤ እነሆ አፈጻፀሙ ወጣ።
አባቶቻችን እንቁዎቻችን ደምና አጥንት ገብረው ለልዑል ታምነው በእንባቸው በደማቸው አረስርሰውት ወደ
እቅፉ ቢሄዱም የታመነው ጌታ ዛሬ የሚያደርገውን የቃል ኪዳኑን ውጤት ያዩ ዘንድ በመንፈስ ይመለከቱና ስለ
ድንቅ ጌትነቱ ይፈነጥዙ ዘንድ ሊያደርግ ወሰነ አፀና።
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጆች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዛሬ ብዙ ተኩላ፣ ብዙ የበግ ለምድ የለበሱ
ቀበሮዎች እንደሞሉአት ይታወቃል። በመምሰል ያሉ፣ እምነቱን በሆድ መስፈሪያ የሚለኩ የቤተ ክርስቲያን
ሕግና እምነትን ያፈረሱ የአበውን የእምነት መሰረት የሚሸረሽሩ፣ የሥጋ ሰራተኞች የሆኑ ቤተ ክርስቲያን
ለፖለቲካ ሥራ መጠለያና መጠቀሚያ ያደረጉ በውስጥ የሞሉ ቢሆንም እነዚህ ሁሉ ተኩላና ቀበሮዎች የግድ
ይፀዳሉ። ፈጽመውም በእሳት ይበላሉ። በአገራችን ከውስጥም ከውጭም የጠላትን ዘመቻ በመንፈሳዊ ፅናት
እየመከታችሁ ያላችሁ አባቶች፣ እናቶች፣ ወጣቶች ፅኑ በርቱ ሰዓቱ አልቆ እነሆ የፍጻሜው ውሳኔ አፈፃፀም
ወጣ።

23
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በ2001 የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፅናትና ምንነትን ሁሉም የተመለከተ
ይመስለኛል። በእለቱ በሕዝቡ ፍቅር ጌታ ተደስቶበታል። እንደ እሳት ይፋጅ የነበረውን ፀሐይ በደመና ተክቷል
ከበዓሉም በኋላ ዝናቡን አርከፍክፏል። በዚህም ሁሉም በመሆን የሚጓዝ የተዋህዶ ልጅ በሙሉ አይዟችሁ
የጠላትን ፉከራ ነገ ዋጋ ስለሚከፍሉበት አትጨነቁ የልዑል ባሪያ ያለምሕረት ለጥፋቱ እሰፍርለታለሁ። ብርቱው
አበጣሪው እሳት ሊፈስ ታዟል። ስለዝርዝር ክንዋኔው ስለ ኢትዮጵያ በተጻፈው ርእስ በማስተዋል ያንብቡ።
ትንቢተ ኢሳይያስ 40፡ 3 – 11
ትንቢተ ኢሳይያስ ም. 12 በሙሉ

5. አሕጉሮች

ይህ ርእስ ክ/አሕጉሮችን በጥቅሉና አጠር ባለ መልኩ የምናይበት ሲሆን በዝርዝር የአገሮች ምንነት ላይ
ሁሉም ይገለጻል።

5–ሀ ሰሜን አሜሪካ


ትንቢተ ኤርሚያስ ም. 51 በሙሉ
ይህ አሕጉር በስተምእራብ ሰሜን አትላንቲክ የሚገኝ ሲሆን አሜሪካ /ባቢሎን/፣ ካናዳ፣ ሜክሲኮ የሚገኙበት
አሕጉር ነው። የምንዝርና፣የግድያ፣ የዘረፋ፣ የጥፋት ሁሉ ምንጯ አሜሪካ በዚህ ትገኛለች። ሁለቱ ካናዳና
ሜክሲኮ አንደኛው በደቡብ አንዱ በሰሜን፣ ለአሜሪካ በር ጠባቂ መስለው የቆሙ ሀገሮች ናቸው። ከአውሮፓ
የተሰደዱ ነጮች የአገሬው ተወላጆችን እንደ ሬድኢንዲያንስ፣ እናም ማያስን የመሳሰሉትን በማጥፋት ለረጅም
ጊዜ በስተደቡብ እንግሊዝ በስተ ሰሜን ፈረንሳይ ጦር ልከው ሲፈጁ ኖረው ካናዳና /ኪዊቤክ/ ፈረንሳይ ስትይዝ፣
አሜሪካንም እንግሊዝ ይዛለች። በአሜሪካ በስተደቡብ ያለችውን ሜክሲኮን ደግሞ ስፔን ይዛለች።
ከረጅም ቅኝ አገዛዝ በኋላ ነጻ ወጡ ቢባልም ተወላጆችን አጥፍተው ፈረንሳዊያንን በካናዳ፣ እንግሊዛውያን
አይርሾች አሜሪካንን የራሳቸው አደረጉ። ከፈረንሳይና እንግሊዝም ወጥተው የዛሬ 200 ዓመት ጀምረው
መንግሥት መስርተው ሲኖሩ እንግሊዞቹ በተለይ ወደ ምእራብ አፍሪካ በመዝመት ጥቁሮችን እንደ ከብት
ነድተው ለትምባሆ እርሻቸው በባርነት ተጠቅመውባቸዋል። አሜሪካ የሰፈሩት ጥቁሮች በሙሉ ከአፍሪካ የሄዱ
የተጋዙ ናቸው።
የዛሬ 200 ዓመት ጀምሮ እንደ አገር የበቀለው የምንዝርና ኢንዱስትሪ ምንጩና መነሻው አውሮፓ ቢሆንም
እጅግ ስፍቶና ደርጅቶ ዓለምን ያጥለቀለቀው ከአሜሪካ በመነሳት ነው። እጣ ፈንታቸው ባለ 7 ቀንዳሟ ባቢሎን
እጣ ነው።

5–ለ ላቲን አሜሪካ


በዚህ አሕጉር እነ ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ ቬንዚዌላ፣ ቺሊ፣ ኮሎምቢያ፣ ኢኳዶር፣ ቦሊቪያ፣ ጓቲማላ፣
ኮስታሪካ፣ ኒኳራጓ፣ ኩባ፣ ፓራጓይ፣ ኡራጓይ፣ ጉያና፣ ኢልሳልቫዶር፣ ሆንዱራስ፣ ቤሊዝ፣ ጃማይካ፣ ሃይቲ፣
በሃማስ፣ ሱማትራ፣ ፍሬንች ጉያና፣ ትሪኒዳድና ቶቤጎ የሚገኙ ሲሆን እነዚህ በስፔንና ፖርቹጋል ቅኝ ስር የነበሩ
አገሮች ሲሆኑ ቋንቋቸው ስፓኒሽ ነው። ግሪናዳ፣ ሴንትቪንሰንት፣ ባርቤዶስ፣ ማርቲን /ፈረንሳይ/፣ ጋድላፕ /
ፈረንሳይ/፣ ሴንት ኪንት ኔቪስ፣ አትስ ኔቪስ፣ አንቲጎዋና ባርባዶ፣ አንጉሊያ /እንግሊዝ/፣ ቨርጅን አይላንድ/
እንግሊዝ/፣ እነዚህ ደግሞ ጥቃቅን ደሴቶች ሲሆኑ በደቡብ አሜሪካ በስተሰሜን ምሥራቅ ያሉ በፈረንሳይና
በእንግሊዝ ተጽኖ ስር ያሉ ናቸው።

24
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

እነዚህ አገሮች በአብዛኛው ስነልቦናቸው ተመሳሳይ ነው። በተፈጥሮ ሀብት የበለጸጉ ዝናባማ ናቸው። የሕዝቡ
ቁጥር በድምር ከ200 ሚሊዮን አያንሱም ይባላል በውስጣቸው፡– ካቶሊክ በከፍተኛ ቁጥር የተንሰራፋችበት
ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ፕሮቴስታንት ቀጥሎ እስላም ሲኖር የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በግለሰብም
ሆነ እንደ ቤተ ክርስቲያን የቆመበት የለም። ጃማይካ በራስ ተፈሪያን መሰረት አስጨባጭነት ለኢትዮጵያ ፍቅር
አላቸው። ተዋህዶ እምነት ተከታይ ግን አይደሉም።
በዚህ አሕጉር ምንዝርና ስሩን የሰደደ ነው። ባህላቸውም፣ ድርጊታቸውም፣ ዘፈናቸውም ሁሉ ምንዝርናን
የሚያስፋፋ ነው። በእፅ ተጠቃሚነታቸውና አምራችነታቸው የታወቁ ናቸው። ይህ ክልል በሌላው ሕዝብ ላይ
ያሳደረው አገዛዝ ጭቆና ባይኖርም ከፈጣሪ ሕግ ወጥቶ በዲያብሎስ ሕግ የሚመራ ነው። በመሆኑም እንደ ግለሰብ፣
እንደ አገር ብርቱ ቅጣት የሚፈስበት ነው። የየአገሮችም ሸክም በየአገሮቹ ዝርዝር ውስጥ ታገኙታላችሁ፡

5–ሐ መካከለኛው ምሥራቅ


ይህ አሕጉር የሰው ጥፋት በርትቶ የሚታይበት ነው። በዚህ ክልል እነ ሳኡዲ አረቢያ፣ ሶሪያ፣ ኢራቅ፣ የመን፣
እስራኤል፣ ሊባኖስ፣ ቱርክ፣ አማን፣ ኳታር፣ ኤምሬትስ፣ ኩዌት፣ ዱባይ፣ ባህሬን ይገኛሉ። በነዚህ አገሮች
መሃከል የተወሳሰበ ግንኙነት ይታያል። ለዚህ ክልል ጁዴዝም በእስራኤል፣ እስልምና በሌሎቹ የሚታመንና
የሚኖርበት ሲሆን፤ ሃገሮቹ በተለያየ ተጽእኖ ስር ናቸው። እስልምና ሁለት ገጽታ አለው፡– አንዱን ሺያት
ሲሆን ሁለተኛው ሱኒ የሚባልና የማይጣጣሙ ናቸው። ሁለቱም ደግሞ የጋራ ጠላታቸው የአይሁድ እስራኤል
እምነትና እስራኤል ናት። በዚህ ክልል ትልቅ የግጭት መንስኤ የፍልስጤም ሕዝብ ነው።
የኢኮኖሚ መሰረታቸው የነዳጅ ሀብት ነው። ሁሉም ሲደመሩ ወደ መቶ ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ይሆናሉ።
7ቱ የሱኒ ዝርያዎች የሚበዙባቸው አገሮች ሳኡዲና ባህሬን፣ ኦማን፣ ኤሜሬትስ፣ ኳታር፣ ኩዌት፣ ዱባይ ሲሆኑ
እነዚህ በአንድ የቆሙ በነዳጅ ከፍተኛ ሀብት የሰበሰቡ ናቸው። ኢራቅ ሱኒና ሺያት የሚፋጁበት ሲሆን ኢራን
በኤሽያ ቀጠና ብትሆንም ሺያቶችን የምትደግፍ ናት። ሶሪያም እንዲሁ የሱኒና የሺያቶች ስብስብ ናት። ሊባኖስ
ማሮናይት ክርስቲያኖችን ሽያቶችንም ሱኒንም የያዘች ናት።
በዚህ ክልል የአሜሪካ የአውሮፓ ደጋፊዎች የራሽያ ደጋፊዎች የኢራን ደጋፊዎች የአክራሪ ደጋፊዎች ያሉበት
ሲሆን ከባድ ውድመት እየተካሄደ ያለበትም ነው። በዚህ ክልል ነው እስልምና መሰረቱንና ዙፋኑን ያደራጀበት።
ይህ ክልል ፍፁም ማንም ከሚገምተው በላይ በታላቅ የእግዚአብሔር ቁጣና እሳት የሚጠረግ ነው። በዚህ
ክልል የሚቀር ቢኖር ጥቂት ሰውና የሲሚንቶ ክምር ብቻ ነው። የሁሉም ሸክም በየአገሮቹ ዝርዝር ውስጥ
ተካቷል።

5–መ አውሮፓ
ኢሳይያስ 47፡ 1 – 15
ኤርሚያስ 50፡ 24 – 32
ይህ ክልል የአሕጉሮች እምብርት ነው ማለት እንችላለን። በዚህ ክልል የታቀፉ አገሮች እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣
ስፔን፣ፖርቹጋል፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ዴንማርክ፣ ግሪክ፣ አልባኒያ፣ ኦስትሪያ፣ ፖላንድ፣ ሀንጋሪ፣ ሩማንያ፣
ዩጎዝላቪያ፣ ቼክ፣ ክሮሽያ፣ ቡልጋሪያ፣ ሆላንድ፣ ኢስቶኒያ፣ ላቲቪያ፣ ሊቶንያ፣ ቤላሩስ ወዘተ ናቸው።
አውሮፓ በተለይም እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ፖርቱጋል፣ ቤልጄያም፣ ጀርመን፣ ጣሊያን እነዚህ
ለአውሮፓ ምንነት በጋር የሚጥሩ ናቸው። አውሮፓ የክህደት፣ የፍልስፍና የሳይንስ ግኝቶች የተፈጠረበት ነው።
ክህደት በነካርል ማርክስ፣ እምነትን በፍልስፍናው የሚጻረር ቻርለስ ዳርዊን፣ የተለያዩ የሳይንስ ግኝቶች ከዚህ

25
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ክልል የመነጩ ናቸው። ይህ ክልል ዓለምን በቅኝ ለመግዛት የወጡ ከ7 ያላነሱ ሀገሮች ያለበት ነው። በአንድ
ዘመን ዓለምን በሙሉ ገዝተዋል ማለት ይቻላል።
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን በመጻረር የታወቁ ካቶሊኮች፣ አንጀሊካን፣ ፕሮቴስታንት ከዚሁ የመነጩ
ናቸው። ዛሬም ዓለም የኢኮኖሚና የፖለቲካ ተገዥ ያደረጉ አሜሪካና አውሮፓ ናቸው። የዲሞክራሲ ፍልስፍናን
የተቀበሉና አስገዳጆችም ናቸው። እነሱ የማይወነጀሉበት ሌሎችን የሚወነጅሉበት ለፍርድ የሚያቆሙበት እንደ
ዘሄግ ያለ ፍ/ቤት ያላቸው ናቸው። ማሰሪያም ያደራጁ ናቸው። የአውሮፓ ህብረት የሚባል ድርጅትና ኔቶ
የሚባል የጦር ድርጅት ከባቢሎን ጋር በጋራ አቁመው ሌላውን የሚቀጠቅጡ ናቸው። የተባበሩት መንግሥታት፣
ለእነዚሁ ለአውሮፓና አሜሪካ ውሳኔ የሚገዛ ድርጅት ነው። ድሃን አገሮች እንዲገዙ እንዲነዱ የሚያደርግ
መሳሪያ ነው። የነሱን ምጽዋት በልማት ስም የሚያድል ነው። እነዚህ ባቢሎንና አውሮፓ፣ አይ ኤም ኤፍ፣
የዓለም ባንክ አቋቁመው ሁሉም በነሱ የገንዘብ ሕግ የሚገዛ ነው አበዳሪም፣ መጽዋችም፣ ነፋጊም ናቸው።
የምንዝርና ኢንዱስትሪ የክህደት ጣሪያ፣ የትእቢት ማመንጫ፣ የፍልስፍና እምብርት፣ በሳይንስና እውቀት
የሚመሩ ናቸው። በዚሁ በአውሮፓ ነው የጥንቆላው፣ የኮከብ ቆጠራው መሰረት ያለው። የአውሮፓ ልጆች ናቸው
በአሜሪካ የሰፈሩት። በጥቅሉ እነዚህ ከ400 ሚሊዮን የማያንሱ ሕዝቦች ከነመሪዎቻቸው፣ ከነድርጅቶቻቸው
በታላቅ የእሳት መጥረጊያ የሚጠረጉ ናቸው። አገራቸው ሰው የሚከስምበት፣ አውሬ የሚፈነጭበት፣ አይጥ
የሚረባበት ይሆናል።
የእያንዳንዱ አገር ሸክምና ቅጣቱ በየአገሮቹ ዝርዝር ይገለጻል።

5–ሠ እስካንድኔቪያ
ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ፊንላንድ፣ በቅርበት ግሪን ላንድ፣ አይስላንድ የሚገኙበት ነው። እነዚህም ከአውሮፓ
የማይለዩ በነሱ መስፈሪያ የሚሰፈሩ ናቸው።

5–ረ ኤሽያ
ይህ ክልል ሰፊ የየብስ ክልል፣ ብዙ ሕዝብ ያለበት ክልል ነው። በዚህ ውስጥ የሚገኙ አገሮች ራሽያ፣
አፍጋኒስታን፣ ህንድ፣ ፓኪስታን፣ ተርኪሚንስታን፣ ኢራን፣ ካዛኪስታን፣ ኡዝቤክስታን፣ ኪርጊስታን፣
ታጃኪስታን፣ ማይማር /በርማ/ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣ ቬትናም፣ ቻይና፣ ማሌዢያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ፊሊፒንስ፣
ላኦስ፣ ሆንግኮንግ፣ ታይዋን፣ ሰሜን ኮርያ፣ ደቡብ ኮርያ፣ ጃፓን፣ ሞንጎሊያ፣ ሲንጋፖር፣ ኔፓል፣ ሴሪላንካ፣
አርሜኒያ፣ ይገኛሉ።
ይህ ክልል ግማሽ የዓለምን ሕዝብ ይዟል ተብሎ ይገመታል። ወደ 3 ቢሊዮን የሚጠጋ ሕዝብም ይኖርበታል።
በአብዛኛው ጠኦት አምላኪ ነው። ብዙ የእስልምና ተከታይ አክራሪም በዚሁ ክልል ይገኛል። ኢንዶኔዥያ፣
አፍጋኒስታን፣ በሕንድም ወደ 200 ሚሊዮን የሚጠጋ ሙስሊም ያለ ሲሆን እነ ኢራን የከረረ እስልምናን
በመንግሥትነት ያራምዳሉ። በዚህ ክልል ከ100 ሚሊዮን የማያንስ በራሺያ የሚገኝ ኦርቶዶክስ አማኝ አለ።
ካቶሊክም በስፋት እንዲሁ አለ። በዚህ ክልል ስፋት ያለው እምነት አልባም አለ። በጥቅሉ እጅግ የተወሳሰበ
ባህል፣ እምነት፣ የፖለቲካ ነጸብራቅ የያዘ ነው። በየአገሮች ዝርዝር ውስጥ በጥልቅ ለማየት ሞክሩ።

5–ሰ አፍሪካ
አፍሪካ በአብዛኛው በድህነቱ የሚታወቅ ከ700 ሚሊዮን ያላነሰ ሕዝብ ያቀፈ መሆኑ ይገመታል። ይህ
አሕጉር የተመሳቀለ በፍፁም ለሕዝብ የማይመች አስተዳደር የሸፈነው ነው። የአሜሪካ፣ የአውሮፓ፣ የኤሽያ

26
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የሁሉም ዘርፍ ተጽኖ ያለበት ሲሆን እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ቤልጂየም፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ፖርቹጋል፣ ስፔን፣
ተቀራምተው የገዙት የቀጠቀጡት የዘረፉት ክልል ነው።
ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ሱዳን፣ አልጄሪያ፣ ሊቢያ፣ ሞሮኮ፣ ቱኒዚያ፣ ሶማሊያ፣ ሞሪታኒያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣
ቻድ፣ ማእከላዊ አፍሪካ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ ጋምቢያ፣ ጊኒቢሳው፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ አይቮሪኮስት፣
ጋና፣ ቤኒን፣ ናይጄሪያ፣ ጋቦን፣ አንጎላ፣ ኢኳቴሪያል ጊኒ፣ ዛምቢያ፣ ናምቢያ፣ ቦትሰዋና፣ ደቡብ አፍሪካ፣
ሌሴቶ፣ ስዋዚላንድ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ የሚገኙበት ነው።
ከላይ የተጠቀሱት ቅኝ ገዢዎች በመላው ዓለም ዘምተው በፈጠሩት የቅኝ አገዛዝ አገሮቹን ለቀው ወደ ስውር
አገዛዝ ሲያዛውሩ የአፍሪካውያንን ድንበራቸውን የወሰኑት እኒሁ ያውሮፓ ዘራፊዎች ናቸው።
አፍሪካ የሁሉም እምነት መናኸሪያ ነው። አፍሪካ የአውሮፓና አሜሪካ ኤሽያ የፖለቲካ ተጽእኖ በፍፁም
ጉልበት ያረፈበትም ነው። ይህንን ክልል ለየት የሚያደርገው በዓለም ጥርስ ውስጥ ገብታ ስትገፋ የኖረች ዛሬም
ለዓለም አስደንጋጭ ክስተት የመነጨባት አገሬ ኢትዮጵያ መኖሯ ነው። የዚህም ክልል አገሮች እጣ ፈንታ
በየአገሮቹ ዝርዝር ውስጥ ይመልከቱ።

5–ሸ አውስትራሊያ
ይህ ክልል አንድ የገዘፈ አገር ነው። ጥቂት ደሴቶች የያዘ ነው እነሱም አውስትራሊያ፣ ኒውዚላንድ፣
ፓፓው ጊኒያ፣ ፊጂ ናቸው። ይህ ክልል እንግሊዞች በቅኝ የያዙት ሲሆን የመሰረቱን ሰዎች አቦርጅኖች ፍፁም
አጥፍተው አገልጋዮች አድርገው ወርሰው የገነቡት ዛሬም በነጮች ስር ያሉ ናቸው። አውስትራሊያ ሁለተኛዋ
እንግሊዝ ብንላት ይቀላል። የእነዚህም እጣ በዝርዝራቸው ያገኙታል።
የየአገሮች ዝርዝር እጣ ፈንታ በዚህ ዝርዝር ውስጥ አንድ አንድ አገሮችን ወይም ከዚያ በላይ በጥምር እጣቸው
የሚገለጽ ሲሆን፤ ይህ የሚሆነው የአገሮቹ የፖለቲካ፣ የእምነት፣ የሕዝብ መቀራረብና መመሳሰል፣ የጉርብትናና
የዝውውር ጥልቀት ከታየ በኋላ ነው፤ የሚገለጸውም እጣ ፈንታቸው፣ ሸክማቸው በድምር የተገለጹትን አገሮች
እንደ አንድ ተፈጻሚ የሚሆንባቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው።
ኤርሚያስ 51፡ 1 – 58
ኤርሚያስ 50፡ 24 – 32

6–ሀ አሜሪካ /ባቢሎን/ ካናዳ


በዚህ ርእስ 52 ግዛቶችን ያቀፈችውን አሜሪካንና እጣ ፈንታዋን እንመለከታለን። አሜሪካንን የማያውቅ
በምድራችን ላይ የለም። የተማረውም ያልተማረውም ያውቃታል። የብዙዎች ህልም አሜሪካ መሄድ ነው።
አሜሪካ እንደ ገነት የምትታይ ናት። እርጉዞች ልጅ ለመውለድ ወደዚያ ያቀናሉ የሚወልዱት ህጻን ዜግነትን
እንዲያገኝ፣ ዲቪ ይሞላሉ አሜሪካ ለመግባትና ለመበልጸግ ሁሉም አሜሪካ በመሄድ ይገኛል ባይ ነው።
የዮሐንስ ራእይ ም. 18 በሙሉ
መላው ዓለም ከአሜሪካ ጋር የተያያዘ ንግድ፣ አስተዳደር፣ የባህል ጥምረት ያላደረገ የለም። አሜሪካ የሁሉም
አገሮች እጣ ፈንታ ወሳኝ ናት። የሚመቻትን መንግሥት ታቆማለች የጠላችውን ትጥላለች። የተገዳደራትን
በወታደራዊ ጡንቻዋ ትቀጠቅጣለች፣ አሜሪካ የማትገባበት የአገሮች ጉዳይ የለም። ሁሉም ከሷ የሚመነጨውን
ዲሞክራሲ የሚባል ኪኒን የሚውጡ ናቸው። ከሷ የሚፈሰው መመሪያ፣ ትእዛዝ ሁሉም መንግሥታቶች
የሚፈጽሙት ነው።

27
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አሜሪካ ያልታወጀ አምላክ ናት። ባቢሎን የሰውን ዘር በሙሉ ታይቶም ተሰምቶም ወደማይታወቅ ምንዝርና
ኢንዱስትሪው የከከተተች ናት። ባቢሎን /አሜሪካ/ የምንዝርና፣ የዘረፋ፣ የዘረኝነት፣ የጭፍጨፋ መሃንዲስና
ቀያሽ ናት። አሜሪካ የዓለምን ሁለት ሦስተኛ ሀብት የሰበሰበች ናት። እያንዳንዱ ግዛቶችዋ ቢያንስ የአንድ
መለስተኛ የአውሮፓን ሀገር ኢኮኖሚ የጨበጡ ናቸው።
አሜሪካ ከሷ ተከትለው በሃብታቸው የቆሙትን የደረጁትን እነ ጃፓንን፣ ጀርመንን፣ እንግሊዝን፣ ካናዳን፣
የመሳሰሉትን በስሯ ያደረገች ናት። ዓለም በሙሉ የአሜሪካ አገልጋይ ነው። በድህነት ያሉ አገሮች ከአሜሪካ
በተጨማሪ የሷን ሹሞች የአውሮፓን አገሮችንም የመታዘዝና የመገዛት ግዴታ ያለባቸው ናቸው። በሁለት ጌቶች
የሚገዙም ናቸው። ከዚያም በላይ በቻይና፣ በራሺያ፣ በህንድ ተጽእኖ ስር የወደቁም ናቸው።
ዓለም በሙሉ አሜሪካንን እንደአባቱ እንደ ፈጣሪው ያያል። ዲያብሎስ ትልቁ ማዘዣ ጣቢያውን ያደረገው
በአሜሪካ ነው። ቀጥሎም በአውሮፓ፣ በኤሽያ፣ በመካካለኛው ምሥራቅ እንዲሁ ጽህፈት ቤቱን አደራጅቷል።
ከዚያ በኋላ ለሁሉም እንደ አቅሙ የሚመጥን ማዘዣ ጣቢያ አቋቁሞ ያዛቸዋል። ይገዛቸዋል። አሜሪካ የምንዝርና
ኢንዱስትሪ ምንጭ፣ የሀብት ምንጭ፣ የጥንቆላ፣ የመተት አፍላቂ፣ አሜሪካ የመንግሥታዊ ዘረፋ መሃንዲስ፣
አሜሪካ ጨፍጫፊ፣ አሜሪካ የዘረኞች ምሽግ፣ አሜሪካ የጨለማ ተግባር ሁሉ ማመንጪያ ናት።
ትንቢተ ኢሳኦያስ 34፡ 1 – 15
አሜሪካ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጽ/ቤት ማእከል ናት። ጽ/ቤቱ ከፍተኛ በጀቱ ከሷ የሚፈስለት፣
የተቀረው በአውሮፓ የሚጨመርለት ነው። በሌላ አባባል አሜሪካ ጠበቃና ጉዳይ ፈጻሚ ነው። ዓለም በአሜሪካ፣
በራሺያ፣ በእንግሊዝ፣ በቻይና፣ በፈረንሳይ በዋናነት በጨበጡት ኒዩክሌር፤ ኬሚካል፣ ኒውትሮን፣ የጦር
መሳሪያዎች የጥፋት ጠርዝ ላይ ያሉ ናቸው።
ኔቶ፣ የአሜሪካ አንዱ ክንድ ሲሆን እንዲሁም ሌላው ሲያቶ የአሜሪካ ክንድ ነው። ባጠቃላይ አሜሪካ
በጨረሩ፣ በሳተላይቱ፣ የጦር መሳሪያ፣ በጦር መርከቡ፣ በጀቱ፣ በቦምቡ፣ በገንዘቡ በሁሉም ቀዳሚ አዛዥ ናት።
አሜሪካ የተለያዩ እምነቶች ያሉባት ናት። በዋናነት ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ፣ እስላም፣ ከሃዲ፣ ሁሉም በዓለም
ያሉ እምነቶች የሰፈሩባትም ናት። አሜሪካ የሰው ዘር በምድር ላይ ሲኦልን የሚለማመድባት፣ የዲያብሎስን
አገዛዝ አካሄድና የጥፋት ፍጻሜውን የሚያዩባት ናት። አሜሪካ በጥበቧ የተመካች በሳይንስ የቁስ ውጤቷ
የታበየች በግልጽና በማያሻማ አቋም የልዑልን ሕግ አፍርሳ፣ ከሌላውም ዓለም ጠርጋ፣ በየትኛውም የዓለም
ክልል የዲያብሎስን ሕግ ተክታ ለተካችውም የጨለማ ሕግ ቆማ እየተዋጋች ያለች ናት። የፈጣሪን ልጆች
ከምድር ገጽ ለማጥፋት የተቃረበችም ናት። ውጤቱም በግልባጭ መሆኑ ባይቀርም።
ትንቢተ ኢሳይያስ፡ ም. 47፡ በሙሉ
ለዚህም በ1998 ህዳር 7 በተጻፈ መልእክት ከፈጣሪ እጣ ፈንታዋ ምን እንደሚሆን ተነገራት፣ ከ3 አመት
በኋላ 27/9/2000 የመጨረሻው ማስጠንቀቂያና ፍርድ ተገለጸ እጣ ፈንታዋ ሁሉ በግልጽ ተነገራት። ይህች
አገር የትእቢት ሁሉ ምንጭ በመሆኗ መልእክቶቹን ከእብድ ቃልና ንግግር አብልጣ አላየችውም። እኔም
መልእክት አድራሹንም እንደከንቱ ቅዠታም ቆጥራለች ከሷ የተጠፈጠፉት አውሮፓ፣ ኤሽያ፣ አሜሪካ፣ አፍሪካ
የኔው አገርም መሪም ተሳለቁ፣ ይሁንና ቆይታቸው 3 ወር ብቻ ሄደ እንጂ። በሳቁበት ልክ የአባታቸው የአሜሪካ
የሀብት፣ የገንዘብ ክምር በቀውስ ሲታመስ እንደ ሰም ሲቀልጥ ሳቅ ቆመና ሃዘን ሆነ። እቅድ፣ የአስቸኳይ
ስብሰባ፣ የመፍትሔ ብዛት ተደረደረ ሁሉም ተባለ ራስን ደግፎ ምን ይሻላል ማለት ተጀመረ። እብዱ እኔ
እብድነቴ ለናንተ፣ ባለ አእምሮነቴ ህሊና ለሰጠኝ ለእግዚአብሔር፣ ባሪያነቴ ለፈጠረኝ አምላክ ነው። ዛሬ
ደግሞ ምጥህ ጀመረ፣ ገና መቼ ዘለቀ ባቢሎን /አሜሪካ/ አምላክህ አምላክነቷ፣ ጥበቧ፣ ብልሀቷ፣ ምሽግነቷ፣
የሃብታችሁ ምንጭነቷ እነሆ በከባድ እሳት ይበጠራል። አምላካችሁ ናትና ከናቃችሁት ጌታ ፍርድ፣ የቁጣ እሳት
አታመልጡም። እናነተም ሞክሩ ስታመልጡ ልናይ ነው።
28
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በሁለቱም መልእክቶች እንደተጠቀሰው እስትንፋስ የለም። እቅድ ድርድሩ መላ አደራጁ፣ የዲያብሎስ ልጆች
መቼም ቢሆን ምላሳችሁ አይሞትም፤ አባታችሁ ዲያብሎስ ባሳደጋችሁ መንገድ በጨለማው እየተደናበራችሁ
ወደ መጨረሻው ሞታችሁ ትዘልቃላችሁ እንጂ መመለስ የለም።
»» ከውስጧ የሚወጡ ሰዎች በእሳቱ ሲጤሱና እሳቱ ሲነድ ለዓለም ሁሉ ይታያል ለታመኑ ወዳጆቿም
ይተርፋል።
»» ከውስጡ የሚወጡ ሰዎች ቢኖሩም ለረጅም ጊዜ የፍርሃትና ድንጋጤው ጥላ–አይርቃቸውም።
»» ለጥፋት ያሰናዳቸው መሳሪያ ሁሉ የትም ታኑረው የት ወዳጅ ከምትላቸው ጋር አብሮ ይጠፋል።
ምልክቱም አይገኝም።
»» የሰው ዘር፣ ለመግዣ፣ እምቢ ቢል፣ ለመጨፍጨፊያ ያዘጋጀችው /ያዘጋጃችሁት/ ኒክለር፣ ኬሚካል፣
ባዮሎጂካል፣ መሳሪያ ጀት፣ መርከብ፣ ሳተላይት መርዝ ሁሉም ከነአዛዦቹ፣ ከነአድራጊዎቹ፣
ከወሳኞቹ ጋር አብሮ ይጠፋል።
»» በዚች በባቢሎን አገር የበቀለ ማንኛውም የትኃጢአት ማጎልመሻ፣ ማራመጃ፣ የዲያብሎስ መጠቀሚያ
በሙሉ ይጠፋሉ። በውስጡ ያሉ ሶዶማውያን አመንዛሪዎች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ በሃብታቸው፣ በእውቀታቸው
የሚጨማለቁ ሁሉ የፈጣሪን ሕግ የናቁ ሁሉ የእምነት መሪም ተመሪም ነን የሚሉና እውነትን የናቁ
/ካቶሊክ፣ ሙስሊም፣ ፕሮቴስታንት፣ ቡዲሂስት፣ ኮሚኒስት፣ ሌሎችም/ የጦር መሪ ነን፣ የጸጥታ
ሃላፊ ነን፣ የምክር ቤት አባል ነን፣ ሴናተር ነን፣ አገረ ገዥ ነን፣ ባለኩባንያ ነን፣ ሊቅ ነን፣ የሚሉ
ሁሉ በውስጧ የበቀሉ እሬቶች ሁሉ ይጠረጋሉ ይጠፋሉ።
»» ምድሪቱ ከተሸከመቻቸው ሁሉ አውሬዎች ትጸዳለች ትላቀቃለች።
»» ባቢሎን ለሰው ዘር የደገሰችው ሁሉ ለራሷ የምትጋተው ይሆናል። ቁጣው ሲፈስስ ማን ያመልጣል?
ማንም አያመልጥም እሳቱ ሳይፈትሸው የሚያመልጥ የለም። በግንባሩ ምልክት ካለው ይድናል።
ከሌለው የለም። በቁጥር 2 መልእክት እንደተጠቀሰው የሚድኑ ተለይተዋል የሚጠፉም እንዲሁ።
ኢሳይያስ ም. 24፡ 1 – 13
የዳዊት መዘ. 91 /92/ 7 – 8
»» እንደ ግለሰብ እንደቡድን እንደተደራጀ አመራርም ቢሆን ከዚች ከባቢሎን እንዴት እድናለሁ የሚል
ከሚድኑት የሆነ ልዑል ያሰበው ካለ ደግሞም ስላለ ይህን ማድረግ ይቻላል።
1. መዳኛ ኢትዮጵያ ሀገሬ ናት። አዳኙም በኢትዮጵያ አገልጋዮቹን በዙፋኑ የሚያነግሰው የሰራዊት ጌታ
እግዚአብሔር ነው።
2. እምነቱም የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ነው።
3. በዚችው በባቢሎን የተሰናዱ መጠለያዎች አሉ። እነሱም የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ዜግነታቸውን
እምነታቸውን ያልጣሉ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አገልጋዮች ያዘጋጁት
የመድኃኒዓለም የእመቤታችን፣ የገብርኤል፣ የሚካኤል፣ ታቦታት ያረፉበት ቤተ ክርስቲያን ስላለ
በዚያ ሄዶ እጅን ሰጥቶ ተዋህዶ እምነትን መቀበል ይቻላል። ከዚህ በኢትዮጵያ ለሚቆመው የልዑል
መንፈሳዊና ሥጋዊ አመራር ራስን ማስገዛትና በተዘረጋው የመገናኛ መንገድ መጠቀምና ትእዛዝ
ማክበር የመዳኛ መንገድ ነው። በዚያ የሚገኙ የተዋህዶ ልጆች፣ የድንግል ልጆች በትጋት ለሚመለሱ
እጅ ለሚሰጡ ማገልገል መርዳት ከዚህ የሚፈሰውን መንፈሳዊና ሥጋዊ አመራር ተግባራዊ ማድረግ
ግዴታቸው ነው።
29
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ማንም ኢትዮጵያዊ ለምሕረት የታሰበና የዳነ ሁሉ ለሚድኑ ልዑል ለመለሳቸው በትህትና ማገልገል፣
ማጽናናት፣ እውነቱን ማስጨበጥ፣ የልዑልን ቅን ፍርድ ማሳወቅ፣ ለምን ይህ ቅን ፍርድ እንደተፈረደባቸው
ሁሉንም በግልጽና ያለ ሽንገላ ማስረዳት ከፈጣሪ የታዘዘ ግዴታ ነው።
የኢትዮጵያዊነትን ባህል፣ ጨዋነትን፣ ትህትናን፣ ሰውን መውደድን፣ ከውሸት መራቅን፣ ከምንዝርና ከክፋት
ርቆ የልዑልን ትእዛዝ ጠብቆ ሁሉም ፊት የሚበራ ብርሃን ሆኖ ማገልገል ይገባል። ከሚያበጥረው እሳት
ለመውጣት ሰዎች እንደ ጎርፍ ይመጣሉና አገልጋዮች ሊያደርጉት የሚገባውን ሁሉ ከፈጣሪ ጋር በጸሎት
በመነጋገር መርዳተ ማስረዳት ይገባል።
ከኢትዮጵያ ሀገራችሁ የሚፈሰውን ዝርዝር መንፈሳዊና ሥጋዊ መመረያ ለአገልግሎቱም የተመደቡትን
ከዚህ በመነሳት የሚመጡትን በፈጣሪ ፍቅር መቀበልና ጸንቶ ማገልገል፣ መታዘዝ ግዴታ መሆኑን አብሬ
አሳውቃችኋለሁ።
ትንቢተ አሞፅ 9፡ 6 – 7
ስለግንኙነት መስመር ዝርዝሩ በሌሎቹ ርእሶች ስለሚገለጽ በጥንቃቄ ይመልከቱ። ከባቢሎን /አሜሪካ/
ጋር እጅና ጓንት ሆና የምትጓዘው ካናዳ ለአሜሪካ የተሰናዳውን የቁጣ እሳት ትጋተዋለች። በሁሉም ሥራቸው
ከአሜሪካ የተለየ ምግባር የላቸውምና። አመንዛሪ፣ ቀጣፊ፣ ዘራፊ፣ የባቢሎን የቅርብ ታዘዦች ናቸው። ስለዚህ
በሁሉም መስፈርት ከአሜሪካ የማይለይ መለኪያ ይጠብቃቸዋል።

6–ለ ሜክሲኮ
ይህችም ሀገር የአሜሪካ ደቡባዊ አዋሳኝ ስትሆን ከምንዝርናው ሌላ በእጽ ሱሰኝነት እና ነጋዴነት የተጠመዱ
የሚበዙባት ምንዝርናው እንደ አባትዋ ባቢሎን በምድር ያልታየ ነው። ወንጀል የበረከተባት ጥፋት የነገሰባት
ናት። ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት ሌሎችም እምነቶች የሚበዙባት ናት።
የዚች አገር ነጻነት በተባበሩት መንግሥታት እንደ ነጻ አገር መታወቋ ብቻ ነው። እንጂ የአሜሪካ 53ኛ ግዛት
እንደማለት ናት። በመሆኑም ለአሜሪካ የሚደርሰው ሁሉ ለሷም ሳይጎድል ይደርሳታል።
»» አሜሪካ /ባቢሎን/ በፊልም እንደምታቀናብሩት ሁሉ በናንተው ላይ በፊልሙ የሚታየው ሁሉ
ይፈጸማል።
»» የዘረጋችሁት የረቀቀ መገናኛ መሰለያ፣ ማጥፊያ ሁሉ ይጠፋል።
»» ይጠብቀኛል ብላችሁ ያሰናዳችሁት ምሽግ ሁሉ መቀበሪየችሁ ይሆናል።
»» ለሰው ዘር 200 ዓመት የዘለቀ መጠነ ሰፊ የጥፋት ዘር ዘርታችኋልና እናንተው ታጭዳላችሁ እናንተው
ትቀምሱታላችሁ።
»» የናንተ ጥፋት አውሮፓ ያሉ የአውሮፓ ህብረት አባላት የሆኑ ሁሉ በእኩል የሚጋሩት ይሆናል።
»» በእናንተ ጥፋት ህንድም፣ ቻይናም፣ ራሺያም እንደየተግባራቸው ይጋቱታል እንጂ አያመልጡም።
አብራችሁ ነግዳችኋል፣ መክራችኋል፣ አንዱን አንዱን ሊገዛ ሊበልጥ ለሰው ማጥፊያ ኒኩለር ,፣
ኬሚካል፣ ኒትሮን፣ ባዮሎጂካል፣ መሳሪያዎች ሰርታችኋል። እጅግ የረቀቁ የጥፋት መሳሪያ ባለቤት
ሆናችኋል። በዓለም የምትወስኑ አምስት ኃያላን አገሮች አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ቻይና፣ ራሽያ፣
ፈረንሳይ፣ ከእናንተ በተጨማሪ ህንድ፣ ፓኪስታን፣ እስራኤል፣ ዛሬ ደግሞ ኢራን፣ ሰሜን ኮሪያ
ኒክሌር ጨብጠዋል። ሺ ሰው መግደል ስላነሰ ሚሊዮኖችን በአንዴ ማጥፋት እንደ ዘዴ ተወሰደ።
ሌሎችም የናንተኑ ፈለግ ለመከተል እየጣሩ ናቸው።

30
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የቀደመውን የኒዩኩለር አሻራ ከጃፓን ሳያጠፉ በ10 ሺዎች የሚቆጠር እጅግ ኃይል ያለው ኒዩክለር
ሰብስባችኋል። ዓለም በጦር መሳሪያ ብዛት፣ በተዋጊ ጀት ብዛት፣ በታንክና በሚሳኤል ብዛት፣ በጦር መርከብ
ብዛት፣ በፈንጂ ብዛት የምድር ላይ መጋዘኖች ሁሉ ተጨናንቀዋል። የዲያብሎስ ልጆች አስተማሪያቸው ዲያብሎስ
እዚህ አድርሷችኋል። የተባበሩት መንግሥታት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የኤሽያ ህብረት፣ የላቲን አሜሪካ ህብረት፣
የአፍሪካ ህብረት ሁሉም የእናንተን ጉልበተኝነት የተቀበሉ ናቸው። የሥጋ ሰው፣ በመንፈሳዊ አይኑ የታወረ
ሰው፣ ፈጣሪውን በስም እንጂ በግብር አያውቅም። አምልኮቱ የሥጋ አምልኮት ነው። ፈጣሪን ስሙን ይጥራ
እንጂ የሁሉ ነገር ጌታ መሆኑን ልቡና አእምሮው አይቀበልም። የሚያየውን የሚያምን እንጂ የማያየውን
አይቀበልም። በዚህ ምክንያት ዓለም የሚያየውን መሳሪያችሁን፣ የጥበብ ርቀታችሁን፣ የሀብት ክምችታችሁን፣
የኑሮ ምቾታችሁን ያምናል። ስለዚህ እንደ አምላክ ቆጥሮአችኋል። የእምነት ተቋሞች ሁሉ ፈጣሪን ስሙን በነጋ
በጠባ ይጥሩ እንጂ አምላካቸው እናንተ ናችሁ። የምትሉትን ይሰማሉ የምታዟቸውን ይታዘዛሉ፣ ለእናንተ ሰላም
የላሉ ለዚህ ደግሞ የቫቲካኑ ፖፕ፣ የፕሮቴስታንቱ ቄስ፣ የአንጀሊካኑ ጳጳስ፣ የቡድሃ መነኩሴ፣ የሙስሊሙ
ሙፍቲ /መሪ/ ሁሉም ታዛዦቻችሁ ናቸው።
እንግዲህ ይህን ሁሉ የተመለከተ አምላክ፣ ሰማይና ምድርን በፈቃዱ ያጸና አምላክ፣ ሁሉንም የሚሽር
የሚያጸና እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ትእግስቱ አለቀ
ተሟጠጠ። በ7/3/1998 ዓ.ም በችሎቱ ተቀመጠ፣ ወንጀላችሁ ሁሉ ተመዘነ፣ በጎም ተፈልጎ ጠፋ፣ ምድር
ሁሉ ተፈተሸች በየትኛውም ስፍራ የናንተ ጌታ ዲያብሎስ የጨለማው ገዢ ፍፁም ወርሶታል። አንድም ነገር
ሳይቀር ታየ እጣ ፈንታችሁ ተገለጸ፣ ውሳኔውም ተወሰነ /ተፈረደ/ በፍርዱም የሚጠብቃችሁ ሁሉ ተገለጸ።
የይግባኝም እድል ሰጠ።
በ27/9/2000 ድጋሚ ዓለም ታየች ተመዘነች አንድም የሚፀፅት ከውስጣችሁ ጠፋ ለሕዝቡ የሚገልጽ
ወደፈጣሪ የሚመለስ ጠፋ፣ በይግባኝም ቢታይ ያው ሆነ ጭራሽ ባሰ። የመጨረሻው ውሳኔ ጸና እንደ ውሳኔው
ከ3 ወር በኋላ ምልክቱን ማሳየት ጀመረ። ኢኮኖሚያችሁ ተመታ ምንም አትጸጸቱም፣ ስለዚህ የመጨረሻውን
ውሳኔ ወደ ተግባር የሚለውጠው የአፈጻጸም ውሳኔ ይኸው ወጣ አበቃ! ይገባኝ የለም ሁሉም ተዘጋ! እንግዲህ
የታመንክበት ያድንህ ምሽግህ ይከልልህ፣ እውቀትህ ይርዳህ፣ በተጠንቀቅ የቆሙት የልዑል ኃይሎች የአፈጻጸም
ትእዛዛቸውን ተረክበዋል። አከተመ።
የዳዊት መዝ. 20 /21/፡ 8 – 13
እንግዲህ ዓለም በአምላኩ በአሜሪካ የተከሰተውን የመሪ ቀለም መለወጥ እንደ ትልቅ ዜና ሲቀባበለው
አይተናል። እኝህ ክልስ መሪ ተአምር ይፈጥራሉ እየተባሉ ሰው ሁሉ ወደ አሜሪካ ሲያንጋጥጥ እያየን ነው።
ነገር ግን በፈጣሪ ውሳኔ ላይ የሚለውጠው የለም። የሚያመጣውም ነገር የለም የተለዋጩም ሆነ ሌላው ሁሉም
ተጠያቂ የባቢሎን አለቆች ናቸው።

7–ሀ ኩባ፣ ኒካራጓ፣ ጓቲማላ፣ ኢልሳልቫዶር፣ ኮስታሪካ፣ ሆንዱራስ፣ ጃማይካ፣


ፓናማ፣ ሃይቲ፣ በሃማስ
እኒህ ሀገሮች አብዛኞቹ በውኃ የተከበቡ ደሴቶች ናቸው። በነዚህ አገሮች ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት፣ የሚያንሱት፣
እስላም፣ ሌሎችም የሞሉባቸው ናቸው። በጃማይካ የሚገኙት የራስ ተፈሪያን አምላኪዎች ሲለዩ በስተቀር።
እነዚህ አገሮች የምንዝር፣ የእጽ ወንጀሎች ጎልተው የሚታዩባቸው ናቸው። አብዛኛው ሕዝብ በኃጢአት ማዕበል
የሚዋኝ ነው እነዚህም በግለሰብም ይሁን እንደ ቡድን እንደድርጅት እንደ መንግሥት ለሌላው የሚሆነው
መስፈሪያ ይሰፈርላቸዋል። ተሰፍረዋልም። በእሳት ይፈተሸሉ የሚድነው ይድናል የሚጠፋው ይጠፋል።

31
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

እጅግ ደቃቅ የሆኑት ደሴቶች፤ እነዚህ ደሴቶች ከላቲን ሰሜን ምሥራቅ የሚገኙ ናቸው። ቨረጂን ደሴት
በአሜሪካና እንግሊዝ ስር ያሉ፣ አነጎሊያ/እንግሊዝ፣ አንቲጉዋ፣ ባርበዶዋ፣ ሴነት ቪትሰነቬስ፣ ጓድላፕ/
ፈረነስይ፣ ማረቲን ኩ/ፈረንሳይ/ባርባዶስ/ሲነትቪንተስ ግራናዳስ፣ ግሪናዳ፣ ትሪንዳድ እና ቶቤጎ፣ እነዚህ
ደሴቶች በእንግሊዝ፣ በፈረንሳይ፣ በአሜሪካ ቁጥጥርና ተጽእኖ ስር ያሉ ናቸው። በጌታቸው መስፈርት ይዳኛሉ።
የጌቶቻቸውን ወንጀል ወርሰዋልና። በሁሉም መልኩ ይበጠራሉ።

7–ለ ቬንዝዋላ፣ ኮሎምብያ፣ ሱማትራ፣ ፍሬንች ጊዋና፣ ኤኳዶር፣ ፔሩ፣ ብራዚል፣


ፓራጓይ፣ ቮሊቪ፣ ቺሊ፣ አርጀንቲና፣ ኡራጓይ
እነዚህ የደቡብ አሜሪካ አገሮች ናቸው። እምነታቸው ካቶሊክ የሚበዛ ነው። ከዚያ በመቀጠል ፕሮቴስታንት፣
እስላም፣እምነት የለሽም በማይናቅ ቁጥር ያለበት ነው። ምንዝርና እጅግ በከፋ መልኩ የሚታይበት ነው።
ወንጀል፣ የሰው ሕይወት ማጥፋት የበዛበት ነው። ጥንቆላ፣ መተት እንዲሁ የበዛበት ነው። ከፊሉ በቀጥታ
በአሜሪካ ተጽኖ ስር ሲሆን እንደ ቬንዙዋላ አይነቱ አሜሪካንን የማይደግፍ አለ።
ይሁንና በጥቅሉ ሲታይ ክልሉ ከዋናው አሜሪካ የማያንስ የምንዝርና ሕይወት ስር የሰደደበት ነው። በመሆኑም
እንደ ግለሰብም፣ እንደ ኃይማኖት ተቋምም፣ እንደ መንግሥትም፣ ሁሉም ቅጣቱን ይቀበል ዘንድ ተለይቶ
የተዘጋጀ ነው። ስለዚህ ፍርዱ በእሳት ማበጠሪያ መበጠር ይሆናል። የተጠቀሱት በሙሉ ሰላምን የሚያገኙት
ከእሳቱም ማበጠሪያ መውጫው አንድ ብቻ ነው። ኢትዮጵያ የሚጸናውን የብርሃን እምነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስና
መንፈሳዊና ሥጋዊ አገዛዙን መቀበል ብቻ ነው።

8–1 ሶርያ፣ ኢራን


እኒህ አገሮች በእስልምና ሕግ /የሸሪአ ሕግ/ የሚመሩ አገሮች ናቸው። እነዚህ አገሮች ከባቢሎን /አሜሪካ/
ጋር የሚጋጩ ናቸው። እስራኤል ዋና ጠላታቸው ናት። ሁለቱም የሺአት እምነት የሚከተሉ፣ ያከረሩ አገሮች
ናቸው። ነዳጅ ዋና የገቢ ምንጫቸው ነው። እነዚህ አገሮች ከፈጣሪ ሕግ ጋር ዘወትር በመጋጨት ላይ ያሉ
ናቸው። ከእምነታቸው ከንቱነት ሌላ የምንዝርናው፣ የሰው ሕይወት ማጥፋት፣ ተጨማሪ ወንጀላቸው ነው።
እስላሙ በሚመዛንበት የሚመዘኑ ናቸው። ከመሰረታቸው ፍፁም የሚጠፉ ናቸው። የሚተርፉ እጅግ ጥቂቶች
ናቸው። ስማቸው ብቻ በነበሩ ይታወሳል።

8–2 ሳውዲ አረቢያ፣ ኩዌት፣ ኢምሬትስ፣ ዱባይ፣ ኳታር፣ ኦማን፣ ባህሬን


እነዚህ የሱኒ ዝርያ የሚበዛባቸው ሲሆኑ በመንግሥት የታወጀ ሌላውን ያገደ እስልምና ሕግ የሚመራቸው
ናቸው። የእስልምናው መሰረት ከነቢዩ ተብየው መሃመድ መቃብር ጋር በመካ ሳዑዲ ይገኛል። በአመት በአመቱ
ከ 3 – 5 ሚሊዮን እስላም ወደዚያ “ሊባረክ” ይመላለሳል። ዛሬ ዓለምን የሚያምሰው እስልምና መነሻው
ከዚሁ ስፍራ ነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ ፡ ም ፡ 33፡ 9 – 12
እነዚህ አገሮች በነዳጅ የከበሩ ናቸው። ዲያብሎስ ዋናው ዙፋኑ ያደረገው በዚህ ነው። አገዛዛቸውም የሀብት
ምንጫቸውም፣ ዝርያቸውም ለማቸውም ሁሉ አንድ አይነት ነው። በአገራቸው ምንም አይነት የክርስትና
እምነት አይካሄድም፣ የምንዝርናና የሰካራምነት ቁንጮ ናቸው።
እነዚህ ምን ይገጥማቸዋል? እነዚህ ከውስጣቸው የሚተርፍ ይገኝ ይሆን? ተብሎ ቢታሰብ ይቀላል። በፍፁም
ከምድረ ገጽ የሚጠፉ ናቸው። ከነአምልኮአቸው ከነ ጣኦታቸው የሚጠረጉ ናቸው። ፍርድ ወጥቷል። ሃብታቸው

32
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ለሚቀረው የእግዚአብሔር ሕዝብ ይሆናል። በነበሩ የሚቀሩ የሚወራ ታሪክ ይኖራቸዋል። በዐይን የሚታይ፣
የሚዳሰስ ምልክት አይተውላቸውም። በሕይወት የሚተርፉት እጅግ የወደቁ፣ የተናቁ፣ ፍፁም ጤና የራቀው
ሕይወት ይመራሉ።

8–3 እስራኤል
ይህች አገር በእግዚአብሔር ፈቀድ የተፈጠረች አገር ናት። ሕዝቧም ሂትለር ከጨፈጨፈው 6 ሚሊዮን ያህል
የተረፈ ነው። ይህች አገር ምድሪቱን የወረሳት ልዑል ነው። የአብርሃም ዘሮች ናቸው፣ የሙሴ ዘሮችም ናቸው፣
የታላላቅ ሐዋርያት ዘሮች ናቸው፣ የድንግል ዘሮች ናቸው፣ የጌታም ወገኖች ናቸው። በእነዚህ ሕዝቦች ላይ
የሚያርፈው ቅጣትም ሆነ ምሕረት በልዑል እጅ የተጠበቀ ነው። ነገር ግን ከአህዛብ የተማሩትን የሰበሰቡትን
ሰው ዘር ማጥፊያ መሳሪያ ያጡታል። እንደ አገር እንደ ሕዝብም ይኖራሉ። ልዑልን ያውቁታል። ከውስጣቸው
በቀለውን የሰቀሉትን ጌታ የዓለምን መድሐኒት መልሰው በታለቅ ፀፀት ይረዱታል። ለዚህ የሚታደሉ ባይበዙም
ይህ ይሆናል።

8–4 ሊባኖስ፣ ኢራቅና ቱርክ


እነዚህ አገሮች እጅግ ብርቱ ፈተና ውስጥ ያሉ አገሮች ናቸው። ሊባኖስ ኢራቅና ቱርክ የጎሪጥ የሚተያዩ
ህብረተሰብ ያቀፉ ናቸው። በፍፁም ተጠርገው የሚጠፉ ናቸው።

8–4ሀ ሊባኖስ፡–
ሱኒ ሙስሊም፣ ሺያት ሙስሊም፣ ፍልስጤም ማሮናይት /ድሩዝ / ክርስቲያን ያለበት አገር ነው።
መንግሥታቸው የነዚህ ቅልቅል ሲሆን በትንሽ ግጭት የሚፈርስ ነው። ሁሉም እርስ በእርስ የሚፈጁ ናቸው።
ሂዝቦላህ የኢራንና የሶርያ ወዳጅና ተደጋፊ ነው። ሱኒው በአረቦች /የአሪሪ ቡድን ማለት ነው/ የሚደገፉ ሲሆን
በአሜሪካም ይደገፋል። እስራኤል የጋራ ጠላታቸው ናት። በእነዚህ ሕዝቦች ሌላው በሚታይበት መስፈርት
የሚሰፍሩ ናቸው። በነዚህም ውስጥ የምንዝርና፣ ግድያ ኃጢአት ስር የሰደደ ነው። ከክህደታቸው በተጨማሪ
ስለዚህ ብርቱ የእሳት ማበጠሪያ ያበጥራቸዋል።

8–4ለ ኢራቅ፡–
ይህ ሕዝብ የሺያት ደጋፊ፣ ሱኒ ደጋፊ፣ የኩርድ ደጋፊ ያለበት ነው። ተቧድነው የሚፋጁበት አገር ነው።
እስልምና ባሰናዳው መሳሪያ ራሱን ለመፍጀቱ ጥሩ ምሳሌ ሆነው የሚታዩ ናቸው። የእስልምና እምነት ተከታዮች
ለክርስቲያን የደገሱት መሳሪያ ለራሳቸው መጥፊያ ለመሆኑ ከኢራቅ የበለጠ ማስረጃ የለም። አሜሪካ ለጥቅሙ
ሲል የገባበት ሲሆን ይህ ሕዝብ የሚጠብቀው ቅጣት ከአሁኑ በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ነው።

8–4ሐ ቱርክ፡–
ይህ ሕዝብ ኩርድ ያለበት አብዛኛው የእስልምና ተከታይ የሆነ የምእራብን ሴኩላር አስተዳደር የሚያራምድ
የአሜሪካ የጦር ድርጅት፣ የአውሮፓ የጦር ድርጅት ኔቶ አባል የሆነ አገር ነው። የዚህ አገር ጥፋት ከአሜሪካ
ከአውሮፓ ጥፋት አይለይም። ጉዳታቸው እጅግ የሚከብድ ነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ 47፡ 8 - 15

33
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

9 ኤሽያ፡–
ይህ ሰፊ ክልል ነው በዋናነት ራሽያ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ጃፓንን የመሳሰሉ አገሮች የተካተቱበት ነው። ከዋና
ዋናዎቹ እንጀምር፡–

9–1 ራሽያ፡–
ይህ አገር ከአሜሪካ ቀጥሎ ወታደራዊ ጉልበት ያለው አገር ነው። ራሽያ ከ100 ሚሊዮን የማያንስ የኦርቶዶክስ
እምነት ተከታይ ያለበት ሲሆን እምነቱ በውስጡ ከተዋህዶ የወጣ አካሄድን የሚሄድ በመሆኑ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ
እምነትን በተግባር የማይገለጽበት ወደ ካቶሊክ ስርአተ እምነት ያዘነበለ ነው። በካቶሊኮች ስልታዊ አካሄድ
የተተበተበ ነው።
በሌሎችም በዚሁ በራሽያ ግዛት ውስጥ የነበሩ ተመሳሳይ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ተከታዮች ያሉ ሲሆን ወደ
አውሮፓ በመቀላቀላቸው የካቶሊክ ተገዢ ሆነዋል።
ራሽያ ከአምስቱ ኃያላን አንዱ ስትሆን ለአሜሪካ በንጽጽር በጉልበቷ የምትመጣጠን ናት። በኢኮኖሚ
በመበታተኗ ሳቢያና ከባቢሎን ጋር በተደረገ የበላይነት ፍልሚያ የተጎዳችና አሁንም መልሳ በማገገም ላይ ያለች
አገር ናት። አገሪቱ የኮምኒስቶች /የከሃዲዎች አገርም ናት/።
በባቢሎን የሚታየው ምንዝርና፣ ሶዶማዊነት፣የተደራጀ ዘረፋ፣ ሌብነት ዕብሪተኝነት፣ የሚታየባት አገር ናት።
በዚች አገር የእምነት ሰዎች ቢኖሩም በከሃዲዎች የተዋጡ ናቸው። ይህች አገር እንደ ሌላው ሁሉ የሚያበጥራት
እሳት ያገኛታል። የሰበሰበችውን ኒውክለር፣ ኒውትሮን፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል፣ የጦር መሳሪያ ታንክ፣ የጦር
ጀት፣ የጦር መርከብ፣ ፈንጂ፣ ሁሉም ማጥፊያዎች ከባቢሎን በሁለተኛ ደረጃ ያስቀምጣታል። በመሆኑም
እስክትጥለው ድረስ እሳት ይበላታል።
በአጥቂ ሳተላይቶች፣ በህዋ ላይ የተደራጁ መሳሪያዎች ባለቤትም ናት። ልክ እንደ ባቢሎን ምድሩ አንሷት
ህዋ ላይ የተሰቀለች አገር ናት። ሁሉም ጉልበቷ ይወገዳል። ከዚች አገር ብዙዎች ወደ እውነቱ ወደ ተዋህዶ
ኦርቶዶክስ ይመለሳሉ ይህም የሚሆነው ሁሉም ትምክህቷ ሲጠፋ ብቻ ነው። ያከማቸቻችው የጦር መሳሪያ
በሙሉ ይጠፋል። የትም ይኑር የት እጣው ፈጽሞ መጠረግ ይሆናል።
ትንቢተ ኤርሚያስ ም4፡ ቁ26-31 ለንፅፅር ከ 80 አሀዱ መፀሐፍ ይመልከቱ።
ይችም አገር ጽዋዋን ጠጥታ የሚተርፈው ወደ ኢት/ተ/ኦርቶዶክስ እምነትና ወደ መንፈሳዊውም ሥጋዊውም
ብርሃናዊ አገዛዝ እራሱን ሲመልስ ብቻ ነው ሰላሙን የሚያገኘው። በእምቢታ ከገፋች ደግሞ ከባቢሎን/አሜሪካ
/የማያንስ በትር ይጠብቃታል። ያገኛታልም።
ከሷ የወጡት ወደ ምእራብ አውሮፓ የተቀላቀሉ እነ ፖላንድ፣ ዩክሬን፣ ቼክ፣ ክሮኤሽያ፣ ቦስንያ፣ ሃንጋሪ፣
ቡልጌሪያ፣ ሮማንያ፣ ሁሉም ለአውሮፓ የሚመጣው መስፈሪያ መስፈሪያቸው ይሆናል። ፍፁም ይጠረጋሉ፤
ወደ ትቢያነት ይለወጣሉ። ከአውሮፓ ጋር ሲቀላቀሉ ከካቶሊክ፣ ከፕሮቴስታንት፣ ከሶዶሞች፣ ከፈላስፎች፣
በእውቀታቸው ከሚታበዩ ጋር እድር ገብተዋል። መቀበሪያቸው ይሆናል አብረው ይጠረጋሉ በውስጣቸው ያሉ
ቅኖች በፍጥነት እራሳቸውን ወደ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ መመለስ አለባቸው። ምንም ቀን የለምና። የማምለጫ
ቀዳዳ ሸሽቶ መጠለያ አገሬ ኢትዮጵያ የልዑል የብርሃን አገዛዝ የሚጸናባት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እንደ ፀሀይ
የምትበራባት የድንግል እርስት የሆነችው ብቻ ናት። ማንም የዓለም ክልል መጠለያ አይሆንም በውስጡ
የኢት/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ካለ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብቻ የተጠለለ ይድናል። ሌላ እንደ አገር ከኢትዮጵያ
ውጪ መጠለያ የለም።

34
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

9–2 ታጃክሲታን፣ ኪርጊስታን፤ ሁዝቬክስታን፤ ተርኪሚስታን፤ ጆርጂያ፤


ካዛኪስታን፤ ቤላሩስ፡
እነዚህ አገሮች ማእከላዊ ኤሽያ ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ከራሽያ ተገንጥለው ነጻ ነን ያሉ ናቸው። እነዚህም
በውስጣቸው የሚታየው የተለያዩ እምነት ነው። እስልምና፣ ካቶሊክ፣ ባህላዊ እምነት፣ ፕሮቴስታንት፣ ኦርየንታል
ኦርቶዶክስ፣ ተመሳቅሎ የሚታይባቸው ናቸው። የነዳጅ ሀብት አላቸው የሚባሉም ናቸው። እነዚህ አገሮች እንደ
ሌላው ሕዝብ ሁሉ በአመጽ፣ በምንዝርና የተሞሉ ናቸው። አስተዳደራቸው ወደ ጥፋቱ የስልጣኔ ተብዬ ዓለም
እየገፋቸው ያሉ ናቸው።
የነዚህም እጣ በእሳት መፈተሽ ነው በመሆኑም የሚድነው ይድናል የሚጠፋው ይጠፋል ሥራቸው
ይከተላቸዋል። ይችም አገር ጽዋዋን ተጥታ የሚተርፈው ወደ ኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትና ወደ
መንፈሳዊውም ሥጋዊም ብርሃናዊ አገዛዝ ራሱን ሲመልስ ብቻ ነው። ሰላሙን የሚያገኘው።
ትንቢተ ኤርሚያስ፡ 25 ፡ 27 – 31
ትንቢተ ሕዝቅኤል 22 ፡ 1 – 5

9–3 አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ሞንጎሊያ

9–3ሀ አፍጋኒስታን
ፍፁም እስልምና የሰፈነባት በከረረ የእስልምና እምነት የምትመራ ሲሆን በዚች አገር አክራሪ የመሸገበት ነው
በሚል ኔቶና አሜሪካ በሙሉ ጦርነት ውስጥ የገቡበት ሀገር ናት፣ ሕዝቡ በአጥፍቶ መጥፋትና በሽምቅ እየተዋጋ
ያለበት ሁኔታ ይታያል። አከረሩም አላሉም እስላሞቹ አፍጋናውያን ላመኑበት እየሞቱ ነው በዚህ አገራቸው
ነውና። አሜሪካና ኔቶ ከዚህ የተነሳ ሽብር አስጨንቋቸዋልና ዘምተዋል። ይህም ልክ ነው በእምነት ሲታዩ ሁሉም
የዲያብሎስ መጠቀሚያ ናቸው በተለያዩ መስመር ላይ ያቆማቸውና የሚያፋጃቸው በሁለቱም ያለው የእስልምና
መንፈስና የካፒታሊስቶች መንፈስ ነው።
ስለዚህ የነዚህ ጥፋት በየምክንያቱ የጀመረ ሲሆን ሁሉም ይጠረጋሉ አንድም የሚድን የለም። ጥፋታቸው
ሀ ብሎ እንደጀመረ በብርቱ ጥፋት ዘልቆ ሁሉንም ያጠናቅቃል። ፓኪስታን ከአፍጋኒስታን ምንም የተለየ እጣ
የላትም፤ በአፍጋኒስታን የሚፈጸመው በዚህም ይፈጸማል።

9–3ለ ሞንጎሊያ
ይህች አገር በራሽያና በቻይና መሃከል ያለች የሁለቱም ተጽእኖ ያለባት አገር ነች። በመሆኑም እንደ ሕዝብና
እንደ ግለሰብ በሥራቸው በልዑል ፍርድ ተመዝነው የሚቀጡ ናቸው።

9–3ሐ አርሜንያ
ይህች አገር ከራሽያ ነጻ ወጥታ ያለች አገር ናት። እምነቷ የኦርቶዶክስ እምነት በመሆኑ በቅጡ ተፈትሻ
የሚቀጣውም ተቀጥቶ የሚገሰጸው ተገስጾ ወደ እውነቱ የሚመጣ ይመጣል።

35
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

9–3መ ቻይና
ይህች አገር የዓለምን ¼ ሕዝብ የያዘች ናት ኃያላን ከሚባሉትም 5ቱ አንዷ ናት። በጦር ኃይል ለአሜሪካ
እያሰጋች ያለች አገር ናት በኢኮኖሚዋ እጅግ በፍጥነት በማደግ ላይ ያለች እና የዓለምን ገበያ ሀብት እየሰበሰበች
ያለችም ናት።
ይህች ሀገር ቡድሃ ቡድሂዝም፣ ታኦይዝም፣ ሺንቶኢዝም፣ ኮንፊሺያን የሚባሉ እጅግ ብዙ ፍልስፍና
መሰልና የጣኦት እምነቶች አምላኪ ናት። ብዙ አውሬዎችን እንደ ምልክት የምትጠቀምና የምትታመንበትም
ናት። ድራጎን ዋናው ምልክቷ ነው። ከዚህ ሕዝብ ውስጥ ምንም ሰው አለ ለማለት ይከብዳል። ፍፁም በግልጽ
ለዲያብሎስ ገንዘቡ የሆኑ ሕዝቦች ናቸው። በሃብታቸው፣ በእውቀታቸው፣ በብዛታቸው እየተመኩ ያሉና ዓለምን
በተለይም ድሆችን በማጥለቅለቅ ላይ ያሉ ናቸው።
ትንቢተ ኤርሚያስ 25 ፡ 15 – 38
ቻይና በፈጣሪ ፊት የተፈተሸች፣ የተመዘነች፣ የቀለለች፣ ፍፁምም የተጠላች አገር ናት።

እጣዋ፡–
በቻይና ከሚመጣው ቁጣና እሳት የሚተርፍ እጅግ በጣም ውሱን ነው። የተሸከመችው የጦር መሳሪያ
ኑዩክለር፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል፣ ኒውትሮን፣ የረቀቁ የጦር መሳሪዎች፣ ጀት፣ ተዋጊ መርከብ፣ ሚሳኤል፣
ታንክ ሁሉም ለጥፋት ያዘጋጀቻቸው መሳሪያ በሙሉ፣ እንደ ወዳጇ እንደ አሜሪካ ፍፁም ተጠርጎ ይጠፋል።
ከመሪው እስከ ተመሪው ከጦር አዛዡ እስከ ታዛዡ ሁሉም በእሳት ይጠረጋሉ።
ቻይና ቻይና ነበረች ይባላል እንጂ፣ በህልውና አትኖርም በምድርም ላይ ፍፁም በልዑል ቁጣ ከሚጠፉ አገሮች
ባቢሎን /አሜሪካ/፣ ቻይና፣ ህንድ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ከፊሉ ሲቀር ራሺያ እነዚህ በከባድ ጥፋት የሚወገዱ
አገሮች ናቸው። ጥፋታቸው በፍጥነትም በዝግታም የሚከናወን ነው። የሚፈጥነው ትእቢታቸውን ለመስበር
ዝግታው ስቃያቸውን ለማበርከት ይሆናል። በመልእክቶቹ ያልተጠቀሙ ትእቢተኞች ናቸውና ከጥፋታቸው
የሚቀር ቅሬት አይኖራቸውም።

9–3ሠ በርማ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣ ቬትናም፣ ላኦስ፣ ሰሜን ኮርያ፣ ደቡብ


ኮሪያ፣ ኔፓል
እነዚህ ሕዝቦች ተቀራራቢ ባህል፣ አስተሳሰብና የእምነት አካሄድ ያላቸው ናቸው። ከሰሜን ኮሪያ ኮሚንስትነት
ውጪ የተቀሩት በሙሉ ጣኦት አምላኪዎች የቡድሃ እምነት ተከታዮች ናቸው። በደቡብ ኮሪያ ብቻ ፕሮቴስታንት፣
ካቶሊክ በብዛት ያለ ሲሆን በሌሎቹ በመጠኑ አሉ እንጂ እምነታቸው በቻይና የበቀለው ኮነፊሺያን ትምህርትና
ቡድሃ ነው። በቅርቡ ወሰናቸው ላይ ባለ የቡድሃ መቅደስ በይገባኛል ታይላንድና ካምቦዲያ ጦር ተማዘውበታል
እስካሁንም ያልፈቱት ነው።
ትንቢተ ኤርሚያስ ም25፡ ቁ15-38 ለግንዛቤ ይመልከቱ።

9–3ረ ጃፓን
ይህች አገር ለኤሽያ በስተምሥራቅ ለአሜሪካ በስተምእራብ ያለች ደሴት አገር ነች። የጃፓን ሕዝብ አኗኗር
ከባቢሎን አሜሪካ ምንም ያልተለየ ነው። ጃፓን ከአሜሪካ ቀጥሎ 2ኛዋ የኢኮኖሚ ኃያል ናት። በእውቀት
በኢንዱስትሪ እድገት፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በመኪና ምርት፣ በመድሃኒት፣በብዙ የቴክኖኮጂ ምርቶች ያደገች

36
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የበለጸገች ናት። ሕዝቡ እምነቱ እንደ ጌታዋ አሜሪካ የተመሳቀለ ነው። አብዛኛውም እምነት የለሽ ነው።
ምንዝርና ግብረሶዶም እጅግ የተንሰራፋበት አገር ነው። እንደ አሜሪካ ፍፁም የልዑል ጠላት ሆና የተቀመጠች
አገር ናት።

እጣዋ፡–
ይህች አገር ከአሜሪካ በማይተናነስ ቅጣት ትመታለች የታበየችበት ሀብት፣ ንብረት ይጠፋል። ያከማቸችው
ገንዘብ ወርቅ ፍፁም ይጠረጋል። የሂሮሺማና ናጋሳኪ ጉዳትን በሺ እጥፍ ሆኖ ይመጣባታል እጅግ ጥቂት ሰው
ቢተርፍ ነው፤ ጉዳቷ እጅግ ፈጣንና በዝግታም የሚከናውን ነው። አውቀው እንዲከስሙ የት ድረስ ፈጣሪን
እንደናቁ እንዲረዱ የሚያደርግ እሳት ይጠርጋቸዋል።
ጃፓን ሃብቴ፣ ጃፓን ቅርሴ፣ የኃይል መሰረቴ ነው የምትለው ሁሉ በእሳት ባሕር ይበላል። የሚወርድባት
ጥፋት የማያቋርጥ ፍፁም የሚያስጨንቅ ይሆናል። መዳን የሚቻለው በአንድ መንገድ ብቻ ነው፤ መዳን
የሚቻለው በኢትዮጵያ ለሚቆመው የእግዚአብሔር መንግሥት መንፈሳዊና ሥጋዊ አመራር እጅ ያለምንም
ቅድመ ሁኔታ በመስጠት ነው። በዚህም እንደመንግሥት፣ እንደ ግለሰብ፣ እንደ ድርጅት ራስን ማዳን ይቻላል።
ከዚህ ውጪ የሚመጣ ነገር የለም።

10–1 አውስትራሊያ፣ ኒውዚላንድ፣ ፓፓው ጊኒያ፣ ፊጂ፡–


ይህ ክልል ከኤሽያ በስተደቡብ በሰላማዊ ውቅያኖስና በህንድ ውቅያኖስ መሃል ያሉ አገሮች ናቸው።
አውስትራሊያም ሆነ ኒውዝላንድ የእንግሊዝ ዝርያዎች የሚገዙት የሚመሩት አገር ነው። የመሰረቱ ዜጎች
አቦርጂኖች ተገዢ ናቸው። ክልሉ በተዘዋዋሪ የእንግሊዝ ቅኝ ነው።

አሜሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ኒውዝላንድ፣


ያሉበት የጦር ድርጅት አላቸው። እነዚህ አገሮች ፍፁም የአውሮፓ ተግባር የሚታይባቸው ናቸው። ምንዝርና
ግብረሶዶምነት ከማንም አገር በላይ በግልጽ የሚከናወነወበት ነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ፡ 59 ፡ 3 – 8
እነዚህ ሀገሮች ፍፁም በጣዖት የሚያመልኩ ናቸው። ፈጣሪ ቀናተኛ አምላክ የሆነውን ሁሌ ሲያስቆጡ የኖሩ
ናቸው። በመሆኑም በመከራው እጅግ ይበጠራሉ ልዑል የማራቸው ይተርፋሉ።

10–2 ማሌዥያ፣ ኢንዶንዢያ፣ ፊሊፒንስ፣ ታይዋን፣ ሲንጋፖር፡–


እነዚህ ሀገሮች በአብዛኛው በእስልምና እምነት የተሸፈኑ ናቸው። በብዙ ደሴቶች የታቀፉም ናቸው።
በማእከላዊ የሕንድ ውቅያኖስ የሚገኙ ናቸው። የአክራሪነት አንዱ ምሽግ እነዚህ አገሮች ናቸው። እነዚህም
ፍፁም ጣኦት አምላኪዎች ከመሆናቸውም በላይ በእስልምናውና በጣኦቱ አምልኮ፣ ፍፁም ልቅ በሆነ ዝሙት፣
ሰዶማዊነት የተበከሉ ናቸው። እነዚህም አገሮች በጌታ የቁጣ እሳት የሚመቱና የሚበጠሩ ናቸው። ተራፊው
ጥቂት ጠፊው እጅግ ብዙ ነው።

10–3 ህንድ፣ ሲሪላንካ


ህንድ በዓለም ሁለተኛውን የሕዝብ ብዛት ከቻይና ቀጥሎ ያቀፈች ናት። ወደ 1.1 ቢሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ
አላት። ኢኮኖሚዋ እንደ ቻይና በመመንጠቅ ላይ ያለ ሲሆን በሁለቱም መሀል የገበያ ትግል ይካሄዳል።

37
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ህንድ ሂንዱስታን የ2/3 ሕዝብ እምነት ነው። ወደ 200 ሚሊዮን የሚጠጋ እስልምና እምነት ተከታይ
አላት። ህንድ በግልፅና በማያሻማ መልኩ ጣዖትን ታመልካለች። የሃዋርያትም ደም በውስጧ አለ። ህንድ ላምን
እንደአምላክ ታያለች አታርድም አትበላም።
ሕዝቡ ፍፁም ለጣዖት ተገዢ ነው። ምንዝርና በዚህም ሕብረተሰብ አለ። ኑዪክለርም ታጥቃለች። ምን
ይጠብቃታል።
»» በመላው ህንድ ያሉ የጣዖት አምላኪዎች ይጠረጋሉ።
»» በውስጧም ያሉ ጣኦቶች ተጠርገው ይጠፋሉ።
»» ጉልበቴ የምትለው የጦር መሳርያ ሁሉ ከነአዛዡ እና ከታዛዡ ጋር አብረው ይጠፋሉ። በህንድ
ያለ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ አማኞች ይቀራሉ የተጠለለባቸውም ይድናል። በዚህ በኢትዮጵያ ያለውን
ብርሃናዊ አገዛዝ ስትቀበልና ስትንበረከክ ሰላሟን ታገኛለች። አለበለዚያ በውስጧ የሚነደው እሳት ሁሌ
ያነዳታል እስክትጠፋም ይጎዳታል። ይጠርጋታል። ስሪላንካም በህንድ ያልተለየ እጣ ይጠብቃታል።
ትንቢተ ኢሣኢያስ፡ ም 14 በሙሉ ያንብቡ።
ብዙዎቹ የአውሮፓ አገሮችና የአሜሪካ ግዛቶች ስካንዲኔቪያኖች ሶዶምነትን የፈቀዱ ናቸው። ውርጃ
እንደመብትም በማጽናት ሴቱን ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ያደረጉ ናቸው።
በመሆኑም እነዚህ አገሮችም የአውሮፓ እጣ ፋንታ ይጠብቃቸዋል። አውስትራሊያም ሆነ ኒውዚላንድ ሁሉም
በከባድ እሳትና ማዕበል ይጠረጋሉ። የሚተርፈው እንደሌላው ሁሉ እጃቸውን ለኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ
ቤተ ክርስቲያን እና ለኢትዮጵያ ብርሃናዊ አገዛዝ በመስጠት መንበርከክ ግዴታቸው ይሆናል።

11 አፍሪካ
ይህ ክልል በሁሉም ነገሩ የተጎዳ ክልል ነው። 52 የሚሆኑ አገሮችን አቅፏል። ይህን ክልል አውሮፓውያን
ተቀራምተው ገዝተውታል። እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ፖርቱጋል፣ ስፔን፣ ጀርመን፣ ደች፣ ጣሊያን፣ ቤልጂየም፣
አሜሪካ ተቀራምተው ገዝተዋል።
እንግሊዝ፡– ግብፅን፣ ሱዳንን፣ ሰሜን ሱማሌን፣ የገዛች ሲሆን ስፔኖች፡– እነ ሞሮኮን፣ ሞውሪታንያን፣
ሲገዙ ጀርመን፡– ቱኒዝያን፣ ፈረንሳይ፡– ማእከላዊ አፍሪካን በሙሉ፣ ፖርቱጋል፡ እነ ሞዛምቢክን፣አንጎላን
ሲገዙ
ቤልጄም፡– ኮንጎን ገዝታለች። ጣሊያን፡– ሊቢያን፣ ላጭር ጊዜ ኢትዮጵያን፣ ላጭር ጊዜ ደቡብ ሱማሌን
ገዝተዋል። ደቡብ አፍሪካን ደቾች ገዝተዋል። ዚምባቡዌና ናሚቢያን እንግሊዝ ገዝታለች። አሜሪካ ደግሞ
ላይቤሪያን ገዝታለች።
አፍሪካ ፍፁም የነጮች ተገዢ ነበረች። ለአሜሪካ ርካሽ ጉልበት የተዛቀው ከአፍሪካ ነው። ከከብት ባነሰ
የሚታይ ሕዝብ ነበር። የባሪያ ንግድ ውጤት ዛሬ አሻራው በአሜሪካ የሚታይ ነው።

11–1 ምዕራብ አፍሪካ


ሞሮኮ፣ ሞውሪታንያ፣ አልጄሪያ፣ ሴኔጋል፣ ኬፕቬርድ፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ጊኒ፣ ሴራሊዮን፣
ላይቤሪያ፣ አይቬሪ ኮስት፣ ቡርኪና ፋሶ፣ ጋና፣ ቶጎ፣ ቤኒን፣ እኒህ አገሮች በከፍተኛ ደረጃ የባሪያ ንግድ
የተካሄደባቸው ናቸው። ሞሮኮ፣ ማውርታኒያ፣ አልጄሪያ፣ ሴኔጋል ፍፁም የእስልምና አገዛዝና የእስልምና
እምነት የተንሰራፋባቸው ናቸው።

38
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

እነዚህ አገሮች ሙሉ በሙሉ የአሜሪካና የአውሮፓ ተገዢዎችና ፖሊሲ አራማጆች ናቸው። ምንዝርና
የገነነበት ወንጀል የተንሰራፋበት አክራሪ የሰፈነበት መንግሥታዊ ዘረፋ እጅግ ስር የሰደደበት ፍፁም ውሉ የጠፋ
የሁሉ መራገጫ ክልል ነው።
ይህንን ክልል ብርቱ ቅጣት ይጠብቀዋል። በዚህ ክልል የሚያርፈው የቁጣ በትር ከመካከለኛው ምሥራቅ
አገሮች የማያንስ ነው። ይህ ሕዝብ ምንም የእምነት ጽናት የሌለው ጣኦት የሚያመልክ እስልምናን የሚከተል
ሌሎችም ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት በመጠኑ ያለበት ነው። ብርቱ ቅጣት እጅግ ከባድ ጥፋት ይገጥመዋል። ወደ
እውነት ሲመለሱ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ብቻ ሰላምን ያገኛሉ።

11–2 ሰሜን አፍሪካ


ይህ ክልል የአፍሪካ ሰሜናዊ ግዛት ሲሆን በዚህ ውስጥ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ቱኒዚያ የሚገኙበት ነው። በውስጣቸው
የእስልምና እምነትና አገዛዝ የሰፈነበት ነው። ይህ ክልል በአፍሪካ የእስልምና እምነትን ተፅዕኖ ለማሳረፍ
መንደርደሪያ ሆኖ እያገለገለ ያለ ነው።

11–2ሀ ግብፅ
የግብፅ አስተዳደርና ግብፅ ረጅም ታሪክ ያላት አገር ናት። ህይወቷ ከኢትዮጵያ ምድር የሚፈሰው አባይ
ነው። ለብዙ ሺ አመታት ያጠጣት ያበላት ነው። በዚች አገር ብዙ አይነት ክንዋኔዎች ተፈጽመዋል ቀድሞ
በፈርዖን ትመራ የነበረችው ግብፅ በራሷ የኢትዮጵያ ግዛት ነበረች። ንጉሦችዋም የሚሾሙት ከዚህ ከኢትዮጵያ
/የኩሽ ግዛተ መንግሥት/ ይባል በነበር አገዛዝ ነበር።
ኢትዮጵያ ለዚህ ለአባይ ውኃ ሲባል ለብዙ ዘመን የተቀናበረ ጥቃት በመሰንዘር ለዛሬው የአገሬ ጥፋት በቁጥር
1 የምትሰለፍ አገር ናት። ግብፅ በውስጧ ካለው መጠነኛ የተዋህዶ አማኝ በስተቀር እስልምናን የሚከተል አገር
ነው። በዚች አገር ጥፋት እጅግ ብዙ ዜጎችዋ ይጎዳሉ። በከፋ የረሃብ፣ የበሽታ፣ የፍጅት መከራ ይመታታል።
እንደመንግሥት መቆምም ያቅታቸዋል። የሰበሰቡት መሣሪያ ከነተጠቃሚው ይጠፋል። በኢትዮጵያ ተዋህዶ
እምነት አስተዳደር ስር አሜን ብለው ካልተገዙ ጥፋታቸው ፈፅሞ ከምድር የሚያጠፋቸው ይሆናል።
ትንቢተ ሕዝቅኤል 29 ፡ 1

11–2ለ ሊቢያ
ይህችም አገር በነዳጅ የበለጸገች የእስልምና እምነት ተከታይ አገር ናት። ከግብፅ ጎረቤቷ ያልተለየ እጣ
ይጠብቃታል። ትምክህቷ ሁሉ ይጠፋል ተራፊዎች ጥቂት ይሆናሉ።

11–3ሐ ቱኒዚያ
ይህችም አገር ብዙም ባትበለጽግ ሙሉ በሙሉ የእስልምና እምነት ተከታይ ሀገር ናት። እጣዋም ከግብጽና
ከሊቢያ ያልተለየ ይሆናል።
መ.ነገሥት ካልእ 17 ፡ 7 – 18 ለንፅፅር ይመልከቱ።

12 ማእከላዊ አፍሪካ
ይህ የአፍሪካ ማእከል ማእከላዊ አፍሪካን፡– ናየጄሪያን፣ አንጎላን፣ ቻድን፣ ጋቦንን፣ኮንጎን፣ ኒጀርን
ካሜሩንን፣ ይይዛል። በዚህ ክልል ግጭት የሚበዛበት አካባቢ ነው። ነዳጅ መዐድን ቡና ካካዋ የመሳሰሉትን

39
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በመላክ የሚተዳደር አካባቢም ነው። እምነቱ የተመሳቀለ ነው። ካቶሊክ፣ እስልምና፣ ፕሮቴስታንት፣ እምነት
የለሽ፣ የባህል እምነት፣ ዝርያ አዘል ግጭት የሚበዛበት ነው። እነዚህ ውስጥ ውል ያለው ነገር አይታይም።
ከነጮች የተወረሰ ምንዝርና ሌብነት ግድያ የሰፈነበት ነው። ተጸጽቶ የሚመለስ ሕዝብ እጅግ ጥቂት ነው።
ይህም ክልል መስፈሪያው እሳት ነው። የተመካበት ሁሉ ይጠፋል፣ ረሃብ ይነግሳል፣ በሽታ ይስፋፋል፣ ግጭት
ይበረክታል፣ የሚያስተዳድር መንግሥትም ይጠፋል። መናና ከንቱ ባዶ እስከሚሆን ይቀጣል ይጠረጋል። እንደ
ግለሰብ ለመዳን ለሌላው ሁሉ መፍትሄ የምትሆነው ኢትዮጵያ ብቻ ናት። የዚችን አገር መንፈሳዊም ሆነ ሥጋዊ
አስተዳደር መቀበል ብቻ ነው።

13 ምሥራቅ አፍሪካ
በዚች ክልል አገሬ ኢትዮጵያ ትገኛለች። ስለ ኢትዮጵያ የተጻፈውን መልእክት ለመረዳት በ 13–1
ይመልከቱ።
በምሥራቅ አፍሪካ ከኢትዮጵያ ሌላ ሱዳን፣ ኬንያ፣ ሱማልያ፣ ጅቡቲ፣ ባህረ ነጋሽ /ኤርትራ/፣ ሩዋንዳ፣
ብሩንዲ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛንያ ያሉ ሲሆን እነዚህ አገሮች በታላቅ ፍጅት ውስጥ ያሉ ናቸው። ክልሉም በድህነቱ
የሚታወቅ ነው።
በኢትዮጵያ ካለው የተዋህዶ እምነት ውጪ ሌላው እስልምና፣ ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊክ፣ ፓጋን፣ የባህል
እምነቶች የሕዝብ ለሕዝብ ፍጅትም የሚታይበት ነው።
ምሥራቅ አፍሪካ የልዑል ዙፋን የሚፀናባት በኢትዮጵያ እምብርት ላይ ነው። ዙፋኑም የሚዘረጋ በመሆኑ
እነዚህ አገሮች ከታላቅ መጠረግ በኋላ እድላቸው የሚወሰን ሲሆን በኢትዮጵያ መደበኛ /ፕሮፐር/ ግዛት ውስጥ
የሚካተቱ ናቸው። ከዚህ በፊት ግን ወንጀላቸው የወለደውን ብርቱ ቅጣት ይጋቱታል ከኤርትራም የሚተርፍ
ካለ ድንቅ ይባላል።

13–1 ሀገሬ ኢትዮጵያ


ሀገሬ ኢትዮጵያ በስተምሥራቅ አፍሪካ የምትገኝ ናት። አገሬ የምትታወቀው በረሃብ ነው። ሁሉም ዓለም
ስለረሃብ ሲነሳ ኢትዮጵያን ምሳሌ ያደርጋታል። ለ7500 ዘመን በታላቅ የዲያብሎስ ፈተና የተጨፈጨፈች አገር
ኢትዮጵያ ናት። በጊዮን የተከበበች አገር ኢትዮጵያ ናት።
ዛሬ አገሬ ኢትዮጵያ ከረሃብ ስሟ ሌላ በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነቷ ፅናትና ጥንካሬ የምትታወቅ ናት።
ሁሉንም የመጀመሪያቱን የነቢያቶች፣ የሃዋርያቶች እምነት በጌታ ደም ያፀናችውን እምነት በድንግል ምልጃና
ባለርስትነት የፀናችውን ተዋህዶ እምነት የጨበጠች ናት። አፅንታ በታላቅ የዲያብሎስ ውጊያ ፀንታ ለ7500
ዘመን የቆመች አገር ኢትዮጵያ ናት።
አገሬ ኢትዮጵያ አምልኮን በህገ ልቡና፣ በሕገ ኦሪት፣ በወንጌል ሕግ አፅንታ፣ በማየት ሳሆን፣ በመስማት
ያመነች፣ ላመነችበትም እውነት እስከ አሁን በመላው ዓለም በሚንተከተከው የገሃነም ደጅ የቆመች አገር
ናት። አገሬ ኢትዮጵያ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት አንበሶች፣ የእምነት ጀግኖች ሀገር ናት። የዘመን ፅዋ
እስኪሞላ በታላቅ እሳት የተበጠረች ናት። አገሬ ቀጣፊ ትውልድ እንደሚያስበው፣ አጥታ፣ ለሥራ ሰንፋ
የተራበች አይደለችም፣ አልነበረችምም። የችግሯ ምንጭ የጨበጠችው እውነትና እምነቷ ያስከፈላት ዋጋ ነው።
አባቶቻችን ሁሉም ክህደትን፣ ኑፋቄን፣ መለያየትን ሳያስገቡ በአንዲት ተዋህዶ ፀንተው ኖሩ። አለፉ። በጊዜ
ብዛት ከወደነጭ የበቀለ የጠላት አረም በነጩ ዘሪነት በአዝመራችን መሃል ገባ። ዛሬ፣ ፀጋ፣ ቅባት፣ ነኝ የሚል
በካቶሊክ ከሃዲዎች በቤተ ክርስቲያን ተዘራ። እስልምና በእንግድነት ገብቶ ተንሰራፋ፣ ፕሮቴስታንት በስልጣኔ

40
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አምጭዎች እንደ ሸቀጥ ወደ አገር ውስጥ ገባ። በተለይ በደቡብ ኢትዮጵያ ተንሰራፋ ጆሆቫ፣ ጥንቆላ፣ ትብተባ
ሁሉም የዲያብሎስ ዘርፈ ብዙ መሳሪያዎች ይህችን አገር ወረሩ በዚች አገር የወረደው መከራ በዚህ ብቻ
አላቆመም እጅግ ዘርፈ ብዙ ሆኖ መጣ።

13–2 እምነትና ውጊያ በኢትዮጵያ


ቀድሞ በነበሩ ዘመኖች ውጊያው ባመኑ ሰዎች መሃል ሆኖ በቃሉ ላይ የተደረገ የጨለማና የብርሃንን መንገድ
በማፅናት ላይ የተመሰረተ ፍልሚያ ነበር። ሁሉም ማለት ይቻላል እምነት አለው። በአንድ ፈጣሪ ከሚያምኑ
ጀምሮ በጉኡዝ ነገር የሚየምን የሞላበት ጊዜ ነበር።
ለንፅፅር ትን. ሶፎኒያስ ም3፡ ቁ1-20 ይመልከቱ።
በኢትዮጵያ ከመጀመሪያው ጀምሮ እውነትን፣ ተዋህዶ ኦርቶዶክስን ጌታ ስለተከላት የሚመጡ ነገስታት ስለ
እምነት የቆሙ ነበሩ። ከጥቂት በስተቀር /እነ ዮዲት ጉዲት፣ እነ ግራኝ መሃመድ/ ከፈጠሩት ቀጥታ የእምነት
ጦርነት ሌላው አብዛኛው የመጣው ውጊያ በእምነት ስም የመጣ ዘመቻና ፀንታ በቆመችው ተዋህዶ መሃል አረም
ለመዝራት በጠላቶች የተሠራ ጥፋት ነበር። የኢትዮጵያ ጀግኖች የእምነት አርበኞች እጅግ የበረታ የመከላከል
እርምጃ በመውሰዳቸው ተዋህዶ በእሳቱም በማእበሉም ፀንታ እዚህ ደርሳለች። የጥፋት ልጆችም እስከ አሁን
ሊቋቋሟት አልቻሉም።
ዛሬ ያለው ውጊያ እምነቱን ባልያዘው ትንሽ እውቀት ላይ ባደረገ ውል ባጣ መሰረቱን በማያውቅ፣ ቢያውቅም
በናቀ፣ ከነጭ የተቀበለውን ባህል፣ እምነት፣ የቁስ እድገት፣ እውቀት፣ እንደ አምላክ የሚያይና የሚያመልክ
የጠፋ ትውልድ ጋር የሚካሄድ ትግል ሆኖአል።
ዲያብሎስ ይህንን የጨለመበት ትውልድ በአመራርም በሀብትም በኃይልም እንዲደረጅ ጥሯል። መንግሥት
በራሱ የዲያብሎስ መሳሪያ ሆኖ ይህን የጠፋ ትውልድ ፍፁም እንዲጠፋ ያደርጋል። እያደረገም ይገኛል።
በኢትዮጵያ ተዋህዶ እምነት ላይ ያለው ውጊያ በመልእክት 2 እንደተጠቀሰው እምነት አለን በሚሉ ብቻ
የሚሰነዘር አይደለም፤ እምነቱ በሌላቸው በመንግሥት፣ በውጪ መንግሥታት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣
ባለሃብቶች ጭምር እንጂ።
ሁሉም ይህቺን እምነት ለማጥፋት እስከ አሁን ይሰራሉ። እየሠሩም ይገኛሉ። ሁሉን ለመዘርዘር ሰፊ ቦታ
ይፈጃል። በጠቅላላ በእምነት ውጊያው ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታነት፣ እስላም፣ ጆቫ፣ ሌሎችም ሁሉ በቅንብር
በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ላይ የዘመቱ ናቸው። ሁሉም ዘማቾች ከውጭ በሚደረግላቸው ቀጥታ የገንዘብና
የስልት የቁሳቁስ ድጋፍ የታጠቁ ናቸው። በመሆኑም ፍርዳቸው ቀድሞ ወጣ። አሁን ስለ አፈፃፀሙ በጽሑፍ
መጨረሻ እናየዋለን።
በኢኮኖሚ፣ በባህል የተደረገ ውግያ ከራሱ ከእምነቱ የማያንስ ነው። ድሃ እንድንሆን እንድንራብ እንድንበታተን
ከራስ ባህል ይልቅ በምንዝርና፣ በውሸት በእርስ በእርስ መፋጀት እንድናልቅ፣ በሽታ እንድንረግፍ፣ ባለን ሀብት
እንዳንጠቀም፣ በማድረግ ልማታችን ወደ ጥፋት በማዞር እስከ አሁን ሲሰራበት ኖሯል። በኢትጵያ ላይ በተደረገ
ዘረፈ ብዙ ዘመቻ በጥቂት ግንባር ቀደም የምዕራብ፣ የአረብ አገሮች በመመራት ሁሉም ዓለም የየበኩሉን
ድንጋይ አቀብሏል፣ ወርውሯል ዛሬ ይከፍልበታል።
ለግንዛቤ ዕንባቆም ም3፡ ከቁ2-19 ይመልከቱ።
እንደ መንግሥት ማዳከም መንግሥትን የራስ ጥገኛ ማድረግ፣ በተዋህዶ እምነታችን መሐል ተኩላ በውስጧ
በመሰግሰግ ማዳከም፣ መበተን የተደረገ፤ እየተደረገ ያለ ግልፅ ተግባር ነው። ወገኖቼ በብርሃን ስለምንተያይ

41
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በሰፊው ያኔ እንነጋገርበታለን። በኢትዮጵያ አፈፃፀሙ ምን ይሆናል። በዚች አገር ያሉ ሁሉ ደግም ደጋግሞ


እንዲያስተውል ተመክሯል ተዘክሯል።
አሁን የወቀሳ፣ የመምከሪያ፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ተጠናቋል። ፍርዱ ወደ ፍፃሜ ተሸጋግሯል። ስለዚህ
በልዑል ያልተመዘገበ፣ ለምሕረት ያልተጻፈ፣ ከነ ድንጋይ ልቡ እያፌዘ ያለ፣ በዚህ አፈፃፀም ፍፁም ይጠረጋል
እንጂ አያመልጥም።
በምንዝርና የተነከረ፣ ከንስሓ ያልደረሰ፣ በትእቢት የጸና በጠመንጃው፣ በሃብቱ፣ በጉልበቱ የሚመካ፣ ውጪ
ባለ ወገኑ የተኩራራ፣ በድሃ ያላገጠ፣ የድሃ ንብረት፣ሚስት የቀማ፣ ጓደኛውን የካደ፣ በውሸት የበለፀገ፣ አገርን
የካደ፣ ተዋህዶን ለማጥፋት የደከመ፣ ንብረቷን የዘረፈ፣ ምእመኑን ለተኩላ የበተነ፣ ለባእድ እምነትና መንግሥት
የሰለለ ዋጋም የተቀበለ፣ ምንዝርናን ሥራው ያደረገ፣ ንጹሃንን ያሰገደለ፣ የገደለ፣ የእግዚአብሔር አገልጋዮችን
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት አገልጋዮችን ያሳደደ፣ ያሰረ፣ ያሰቃየ፣ በኢትዮጵያ ምድር የምሕረትን ዘመን ያለ
ቅጣት ያለ ዋጋ መክፈል ፈጽሞ አያይም። የሚያየውም ንስሓ የገባውና የተጸጸተው በመጠነኛ ቅጣት የታለፈው
ብቻ ይሆናል። በኢትዮጵያ ምድር ምንዝርናን በማስፋፋት ሴቶች እጅግ ከፍተዋል፣ ሱሪ ለባሽ ገላዋን ገላጭ፣
በፍፁም የማትመለስ ነውረኛ ሴት ሁሉ በላያቸው ላይ የሚጠርጋቸው እሳት ወጥቷል።
በኢትዮጵያ ከአንዲቷ ከተዋህዶ እምነት ውጪ ሌላ አይረግጥም፣ አይኖርባትም፣ አይጠለልባትም። ከዚህ
አፈጻፀም መውጣት በኋላ በኢትዮጵያ በግልም፣ በመንግሥትም፣ በኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንም፣
በመንግሥት ተቋማትም ስለሚወሰዱት አቋምና እርምጃዎች በቀጣዮች የድርጊት መመሪያዎች ይገለጻሉ።
ለንፅፅር የዳዊት መዝ 145 ይመልከቱ።
መላው አገሬ የኢትዮጵያ ልጆች፣ የተዋህዶ እምነት ልጆች፣ የድንግል ልጆች፣ የገብርኤል የሚካኤል
አንበሶች፣ የኡራኤል፣ የሩፋኤል አርበኞች፣ ባጠቃላይ ቅን የዋህ የሆንከው ኢትዮጵያዊ በሙሉ፣ ባለህበት
ፀንተህ ቁም! ቅድስናህን ጠብቅ! አትደንግጥ፣ አትፍራ እራስህን ለፈጣሪ ስጥ፣ ለታላቅ የልዑል አገልግሎት
እራስህን አዘጋጅ! እስከዛሬ ከሰራኸው ጥፋት በምሕረቱ ሽሮ በቸርነቱ ያሰበህን፣ የኢትዮጵያ አምላክ አስብ፣
አመስግን። ዝርዝር መመሪያዎችን በጥንቃቄ አንብብ፣ አስተውለህም አድርግ። እግዚአብሔር ለክብሩ መርጦሃልና
እራስህን በቅድስናና በትህትና አንጽ፣ ከክፋትም ሁሉ ራቅ።

14–1 ደቡብ አፍሪካ


ይህ ክልል ደቡብ አፍሪካን፣ ናሚቢያን፣ ዚምባብዌን፣ ዛምቢያን፣ ሞዛንቢክ፣ ማደጋስካር፣ ሌሴቶ፣ ማላዊ፣
ቦትስዋና፣ ሞሪሺየስ፣ ኮሞሮስን ይይዛል። ይህ ክልል እጅግ የተጎዳ የቀኝ ተገዢ ነው። በተለይ በዚህ አገዛዟ
መጥፎነት የምትታወቀው እንግሊዝ እስከዛሬ የምትጫነው ክልል ነው።
ሕዝቡ የጌቶቹን እምነት የወረሰ ነው። በደቡብ አፍሪካ፣ በሞዛምቢክ፣ በዚምባብዌ፣ በናሚብያ ዛሬም ጥቁሩን
እየገዙ እየዘረፉ ያሉት ነጮች እዚያው እንደሰፈሩ ናቸው። ስለዚህ ይህ ክልል እንደ አውሮፓዎች የሚመዘን
ነው። በዚህ ክልል ምንዝርናው እጅግ የከፋ ነው። ብዙ እምነቶች አሉ፡– ካቶሊክ፣ አንጀሊካን፣ ፕሮቴስታንት፣
ሙስሊም፣ በስብጥር ያለበት ነው። የተሰባጠረ ቅጣት ይጠብቃቸዋል። በእሳትም ይፈተሻሉ የማያቋርጥ እሳት
ይበረብራቸዋል። ለሁሉም ዓለም እንደሚሆነው እነዚህም ጥቂት የሚተርፍ ስለሚኖራቸው፤ በኢትዮጵያ ተዋህዶ
ኦርቶዶክስ ስር ሲጠለሉ በኢትዮጵያ የሚሰፍነውን ብርሃናዊ አገዛዝ ሲቀበሉ ብቻ ሰላማቸው ይመለስላቸዋል።
ከዚህ ውጪ የመፈጠር መፍትሄም ሆነ ዘዴ አያገኙም። አይኖርምም።
ለንፅፅር አሞፅ 2 ፡ 14 – 16 ይመልከቱ።

42
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

በውስጥ ገጽ የተዘረዘሩት የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች ሸክም እጅግ ከባድ ከብዙ ጥፋትና ውድመት በኋላ
ነው ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ /ለኢትዮጵያ/ አገዛዝ እጃቸውን የሚሰጡት መሰረታቸው ፍፁም ዲያብሎሳዊ በመሆኑ
እሳቱ እየወረደባቸው ጥቂት እስከሚቀሩ የማይመለሱ ናቸው።

15 አውሮፓ
ይህ አሕጉር አውሮፓ ሲሆን በዋናነት እነ እንግሊዝ፣ ጀርመንን፣ ፈረንሳይን፣ ስፔንን፣ ዴንማርክን፣
ጣሊያንን፣ ፖርቱጋልንና ሆላንድን ያቀፈ ሲሆን በቅርቡ ከራሽያ ተገንጥለው ወደሱ የገቡት እንደ ፖላንድ፣ ቼክ፣
ላቲቪያ፣ እስቶኒያ፣ ክሮሽያ፣ ቡልጋሪያ፣ ሩማንያ፣ ሃንጋሪን፣ የሰበሰበ የአውሮፓ ህብረት የሚባል ድርጅት
ያለ ሲሆን ኔቶ ከአሜሪካ ጋራ ተጣምሮ ዓለምን ለመግዛት የሚጥሩና እየገዙም ያሉ ናቸው። በኢኮኖሚያቸው
ከአሜሪካ ቀጥሎ ያል ናቸው።
ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ስፔይን፣ ኦስትርያ፣ እንግሊዝ፣ ሆላንድ፣ ጣሊያንና ፖርቹጋል እነዚህ አገሮች ፍፁም
የጥፋት አገሮች ናቸው። በውስጣቸው ሁሉም የእምነት አይነት አለ፣ ከተዋህዶ እምነት በስተቀር፣ የምንዝርና
ቁንጮ ናቸው፣ የክህደት አገር ነው። በኑሮአቸው ምቾት፣ ባላቸው የኢንዱስትሪና የፍልስፍና አካሄድ እጅግ
የሚመጻደቁ ናቸው። ከእንግሊዝ ቀጥሎ ዓለምን በቅኝ በመግዛት በሰው ዘር ደም የተጨማለቁ ናቸው። ሰውን
አሽከራቸው ሃብቱን ንብረታቸው አድርገው ዘምተው ለረጅም አመቶች ደሃን የፈጁ ናቸው። በእነሱ ውስጥ
ያሉት ካቶሊክ አንጀሊካንና ፕሮቴስታንት እምነቶች ከመንግሥታቸው ጋር እኩል ለሰው ጥፋት የዘመቱ
ናቸው። ከእንግሊዝ አንገሊካን እንደ መንግሥት ሆና የመራችም ነች።
አውሮፓ ፍፁም የዓለም የጥፋቷ ቁንጮ ነው። በአውሮፓ ተፈልጎ የሚገኝ አንድም ለምሕረት የሚያበቃ ነገር
የለም፤ በሓዋርያት ደም የታጠበች፣ በብዙ ክርስቲያኖች ሕይወት ያላገጠች የዲያብሎስ የጥንት ማዘዣ የዛሬው
ከአሜሪካን ቀጥሎ ሁለተኛ ማዘዣ ጣቢያ ናት።
የሚጠብቃት፡–
»» አውሮፓ እንደ አሕጉርም ሆነ በውስጧ እንዳቀፈቻቸው አገሮች በሙሉ በአንድ ሚዛን ትሰፈራለች
»» በዚህ ክልል የአውሮፓ ህብረት አባል የሆኑ 28 የሚጠጉ አገሮች በሙሉ በልዑል የእሳት ማዕበል
የሚጠረጉ ናቸው።
»» ከዚህ ክልል የሚተርፉ ቢኖሩ እጅግ ጥቂት ናቸው እንደ አገር ቀርቶ እንደ መንደር መቆም የማይችሉ
ናቸው።
»» የሰበሰቡት መሳሪያ የራሳቸው መጥፊያ ይሆናል።
»» የአውሬ መርቢያ ይሆናል። ዛሬ እንረዳለን ባዮች ነገ እርዱን የሚሉ ይሆናሉ ከነዚህም የሚተርፍ
የታደለ ነው። ከሚመጣውና ከሚፈሰው የልዑል ቁጣ ከተረፉት መዳን የሚቻለው በአንድ መንገድ
ብቻ ነው። ለኢ. ተ. ኦርቶዶክስ እጅ መስጠት በእምነቱ በአስተዳደሩ እንደ መንግሥትም እንደ
ቡድንም እንደ ግለሰብም በኢትዮጵያ ለሚቆመው ብርሃናዊ መንፈሳዊ የልዑል አገዛዝ ፍፁም እጅ
መስጠት ብቻ ነው። እጅም ቢሰጡ ከልዑል ሲጸናና መታዘዙ ከልብ መሆኑ በልዑል ሲረጋገጥ ነው።
ለማነፃፀሪያ ትን. ኤርሚያስ 51፡1-58
ትን. ኤርሚያስ 50: 24-32 ይመልከቱ።

43
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ከውስጣቸው ለሰው የሚጠቅም ሲቀር ማናቸውም ለጥፋት ሌላውን ለመግዛት ተፈጥሮን ለመጉዳት
ለስግብግብነት ባጠቃላይ ለሰው ዘር ሰላምና ጤና ለምድሪቱም ጤና እንቅፋት የሆነው ሥራችሁ ሁሉ ከመሰረቱ
ተጠርጎ ይጠፋል።
ለንፅፅር የዳዊት መዝሙር፡ 13(14)፡2 – 8 ይመልከቱ።

15–1 እንግሊዝ
ይህች ሀገር የአውሮፓ ቀዳሚ መሪ ናት የዚች አገር ወንጀል እና የኃጥያት ጥፋት ከአሜሪካ በምንም መልኩ
የማይለይና በማናቸውም ታሪኳም ሆነ ሥራዋ ከባቢሎን የምትመሳሰልና ጠበቃ በመሆኗ ከዚህ በተጨማሪ
የክህደት ፈላስፎች የፈለቁባት የእምነታችን ጠላቶች በትልቅ ደረጃ የተስፋፉባት ለአሜሪካ ልጆቿ እዚህ መድረስ
ዋናዋ እሷ ናት። እንግሊዝ ዓለምን በቀኝ የገዛች የጥፋትን ሥራ በሁሉም መልኩ ለዓለም ያስተማረችና የመራች
መሰረት ያስጨበጠች ናት። የዚች አገር እጣ ፈንታ በምንም መልኩ ከአሜሪካ እጣ ፈንታ አይለይም።

15–2 ፈረንሳይ፡–
ይህች አገር ከእንግሊዝ ጋር ተመሳሳይ ታሪክ ያላት በዓለም ቅኝ ገዥነት ከእንግሊዝ ጋር እኩል ትራመድ
የነበረች ናት። ከእንግሊዝ የማይተናነስ ወንጀል በሰው ዘር ላይ የፈፀመች ናት። ከአምስቱ ኃያላን አንዷ ናት።
የኔቶ ቁልፍ አባል፣ የአውሮፓ ህብረት መሥራች ናት። ፈረንሳይ በአገሬ ጉዳይ ጣልቃ የገባች ናት። አገሬን
ወደብ አልባ ካደረጉ አገሮች የቅርቡ ተጨባጭ ጠላት ናት። ጅቡቲን የጦር ስፍራና መናኸሪያ ያደረገችም ናት።
ለሷ የሚደርሰው ጥፋት እጅግ ብርቱ ነው። የሰበሰበችው ሀብት ይጠፋል። ያከማቸችው የጦር መሳሪያ
ኒዩክለር፣ ኬሚካል፣ ባዮሎጂካል፣ ሚሳየል፣ ጀት፣ የጦር መርከብ፣ ሰበ መሪን ሁሉም እንደ ጢስ ይተናል።
ዜጎቿ በሙሉ በእሳት ይበጠራሉ። አጥቶ መንከራተትን መራብን ያዩታል። ለነዚህ መንግሥት ብርቱ ቅጣት
ሳያቋርጥ ይወርድበታል። እናንት በኢትዮጵያ ዛሬም እየሰራችሁት ላላችሁት በደል ለፍርድ ትቀርባላችሁ ቶሎ
ምሕረት ስለጠየቃችሁም አታገኙም።
ለንፅፅር ሚኪያስ 2 ፡ 1 – 3 ይመልከቱ።
ጣሊያን ትናንት ቅኝ ሊገዛ መጣ ዛሬ የለም። እናንት ግን ጉልበተኞች ብዙም ሳይርቅ ጅቡቲን ከእናት
ምድር ነጥላችሁ ነፃ ናት አላችሁ። ጦር ሰፈር አደረጃችሁ። መቀበሪያችሁ ትሆናለች። አገራችሁ የሰውን አገር
እንደበተነች ትበታተናለች። እናንት በኢትዮጵያ ፊት አለፍርድ አትታለፉም ትቢያ ትለብሳላችሁ። በአውሮፓ
ላሉ አገሮች የከፋ የጥፋት ምሳሌ ትሆናላችሁ።
በመላው ዓለም ላለህ የሰው ዘር በሙሉ ልብ ብለህ አድምጥ ልትወስደው የሚገባህ እርምጃ ምንድን
ነው። በዚህ የልዑል ውሳኔ ውስጥ የሁሉንም መልእክቶች በሚገባ የተረዳህ ከሆንክ ከዚህ በታች ያሉትን
እንደመጀመሪያው ሁሉ ከዚህም በኋላ ያሉትን የአፈጻጸም ውሳኔዎች አስተውለህ ተረዳ አድርግም።
ይህ መልእክት መላውን ዓለም የምታይበት የእምነት መነጽርህ ነው። ከራስህ አትለየው የሚፈጸመውን
የልዑል ውሳኔ አስፈጻሚዎች ሲያከናውኑት ልብ ብለህ አስተውል። በምድር ሆነ በህዋ፣ በባሕርም ውስጥ ሁሉ
ሁኑ ይህ የልዑል መልእክት የማይዳኘው ዓለም የለምና ፍርዱን እዩ። ሁሉም የዓለም መሪ፣ ሁሉም የዓለም
ሕዝብ፣ ሁሉም ባለጸጋ፣ ሁሉም ድሃ በብርሃናዊ ፍርድ ይዳኛልና። ልብ ብለህ አድምጥ። እምነት የሌለህ
ጠማማ ትውልድ እስከምትጠረግ ጠብቅ።

44
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

16 የምትወስደው እርምጃ እንደ ግለሰብ መዝ ዳዊት 18 /19 /8 – 9


ሀ/ ማንኛውም የሰው ዘር ይህንን መልእክት 1ኛውን 2ኛውን መልእክት ይህንንም 3ኛ የአፈጻጸም ውሳኔ
ማንበብ መረዳት፣ ማስረዳት እንደ ወሳኝ መመሪያ መጨበጥ ለሌላውም ማስጨበጥ ከፈጣሪ የተሰጠን ግዴታ
ነው።
ለ/ ማንኛውም ሰው በኢትዮጵያ ተ/ኦርቶዶክስ እምነት እንዲጸና እንዲጠለል አምኖ ተጠምቆ እንዲሰበሰብ
በፈጣሪ ታዟልና። አንተም ይህን አድርግ ያመንክ ቀድሞውንም በእምነቱ ካለህ ማናቸውንም የፈጣሪ ትእዛዝ
ጠብቅ ከቅድስናህ አትጉደል!!
ሐ/ ከኢትዮጵያ ውጪ ያለህ ማንኛውም በልብህ ያመንክ በህሊናህ የተለወጥክ ሰው በሙሉ ባለህበት
የትኛውም የዓለም ማዕዘን በጎጆህ /በቤትህ/ ሆነህ ወደ ፈጣሪ መመለስህን፣ መጸጸትህን፣ በእውነት ለተዋህዶ
እምነት መቆምህን ለፈጣሪ በጾም በጸሎት ንገር። ቀጥሎም ማናቸውንም ኢትዮጵያዊ የእምነቱ ሰው ለማግኘት
ጣር።
ዳዊት መዝ 23 /24 /3 – 5
በተዘረጉ የመረጃ መረቦች ለማግኘት ሞክር፣ በአገርህ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲም መረጃ ጠይቅ ከዚህ
ከኢትዮጵያ የሚያገናኝህን አድራሻም ጠይቀህ ሁሉንም አግኝተህ ተመለስ። በነጠላ ቢያቅትህ በህብረት አቅምህን
አስተባብረህ መምጣትና የእምነቱን ስርዓት ፈጽመህ ሕጉን አውቀህ መመሪያ ተቀብለህ መሄድ ትችላለህ። በልቡ
ለተለወጠ ሰው መንገዱ ክፍት ነውና።
መ/ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በየትኛውም ዓለም ያለ ሁሉ መልእክቱን ለማግኘት የሚፈልጉ ሰዎችን መርዳት
ግዴታው ነው። ከብርቱ ቅጣት መፍሰስ ጀምሮ ሰዎች ለመዳን ይጥራሉና! ማምለጫውን ማሳየት ግዴታው
ነው። በዚህም ለመነገድ የሚሞክር ይቀጣበታልና አገልግሎቱን በነጻ ይስጥ።
ውሳኔው ወደ አፈጻጸም ተሻግሯልና ያልጠበቅናቸው አገሮች ሕዝቦች የሚጠፉ ሲጠፉ የሚተርፉ ምሕረት
ሲሹና ማምለጫ ሲፈልጉ በየትም ያለ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጅ በትህትና፣ በቅንነት፣ ራስን ዝቅ በማድረግ፣
መርዳት ዋናው ተግባርና ግዴታው ነው።
»» በትምክህት የሚናገር የሚያደርግ የሚመጸደቅ ብርቱ ቅጣት ይጠብቀዋልና ከዚህ አጸያፊ ሥራ ይቆጠብ።
»» አንዳንድ መንግሥታቶች ቡድኖች ድርጅቶች ይጠቅመናል ባሉት ድርጅቶች የመከለሻ ዘዴ ተጠቅመው
ሊገልጹት ይችላሉና በጥንቃቄ ከያዛችሁት ኦርጅናል መልእክት ጋር አመሳክሩት።
»» ማንኛውም የሀገር መሪ፣ የእምነት ድርጅት መሪ፣ የጦር መሪ፣ የደህንነት ሃላፊ፣ የምክር ቤት አባላት፣
የመወሰኛ ምክር ቤት አባላት፣ የዓለም አቀፍ ድርጅት መሪዎች፣ የእርዳታ ድርጅት መሪዎች፣ ዓለም
አቀፍ የሙያ ማህበሮች ኃላፊነት ያለበት የሕዝብ አመራር የያዘ በሙሉ ይህን ትእዛዝ ያስተውል።
ሀ/ ባለው የወልም ሆነ የግልም ኃላፊነት ትልቅነትና ትንሽነት በዚህ መልእክት መሠረት ስለሚመዘን፣
መረጃን ለሕዝቡ መግለጽ፣ ሕዝቡን ወደ እውነት መመለስና ማስረዳት ግዴታው ነው። ይህን የማያደርግ እንደ
ግለሰብም እንደ መሪነቱም ይጠየቃልና። እንደ ትእዛዙ የሚፈጽም ከሆነ ሸክሙ ይቀላል።
ለ/ በተለይ የአገር መሪዎች የአገሪቱ ሕግ አውጪዎች በሕዝብ ተመርጠናል የሚሉ የስርና የበላይ ም/ቤቶች፣
ይህንን መልእክት በግልጽ ማሳወቅ፣ ማስረዳት፣ ወደኢትዮጵያ መጥተው ለመረዳት ለሚሹ ማገዝ መርዳት፣
መስጠት፣ ከኢትዮጵያ ካሉት ጋር ማገናኘት ግዴታቸው ነው።
መፅሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ 22 ፡ 5

45
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ሐ/ በየትኛውም ሀገር የሚገኝ ዳኛ፣ አቃቢ ሕግ፣ የፀጥታ ሰራተኛ፣ የጦር አባል፣ ቁጣው ሲፈስ ሹመትና
ጉልበት እውቀትና ሀብት አያድነውምና አውቃችሁ ጠብቁ ወይም ፈጥናችሁ ውጡ።
መ/ ማንኛውም ሰው ወይም መንግሥት በቂ መረጃ ሳይሰጥ የሚያፍን ከሆነ በየአቅሙ ብርቱ ቅጣት
ያገኘዋል። በዚህ ድርጊት ምሕረትን አያገኛትም።
ሠ/ ማንኛውም አሰናካይ እንቅፋት ሰው ሁሉ ይፌዝበታል። ሞትን እየለመነ ያልፋል። ይጨልጣታል።
ረ/ በ7/3/1998 የተገለፀውን የመጀመሪያ መልእክት በ27/9/2000 የተገለፀውን ሁለተኛ መልእክት ለሕዝብ
ሳትገልጹ አፍናችሁ ያስቀራችሁ ግለሰቦች፣ የአገር መሪዎች፣ የእምነት ድርጅት መሪዎች፣ የዜና ማሰራጫዎች፣
ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ በአጠቃላይ መልእክቶቹ ደርሶአችሁ የናቃችሁ የቃለላችሁ ያፌዛችሁ ሁሉ አሁንም ይህ
የአፈጻጸም ውሳኔ ቢደርሳችሁ እንደቀድሞው ስተታችሁን ብትደግሙ፣ ደግሞም ታደርጋላችሁና፣ በመጀመሪያ
የቁጣውን እሳት ትጋታላችሁ ይህ ሲደረግ ሌላውም ይማራልና በዚህ ስተት ያለቅጣት አትታለፉም።
ለንፅፅር መጽሐፈ ምሳሌ 16 ፡ 5 ይመልከቱ።
ሰ/ ይህንን መልእክት በመናቅ፣ በማፌዝ፣ እንደ እብድ ንግግር በመቁጠር ከቀደመው ክፋታችሁ፣
ትእቢታችሁ፣ እውቀታችሁ፣ ሃብታችሁ፣ በመመጻደቅ በጨበጣችሁት የመሳሪያ ጉልበት በመመካት ጸንተው
የሚቆሙ መሪዎች፣ አገሮች፣ ቡድኖች፣ ድርጅቶች፣ የእምነት ተቋሞች፣ ግለሰቦች፣ ባለእውቀቶች፣ ፈላስፎች፣
ሊቆች፣ ጄነራሎች አሉና በመልዕክቱ አምኖ የተጸጸተና የተመለሰ ሰው ምንም ይሁን ምን ከላይ ከተጠቀሱት
ፈጽሞ ራሱን ማራቅ አለበት። በክፉ ሥራቸው መተባበር መታዘዝ የለበትም። እነዚህ ለቁጣው ማረፊያ የተሰናዱ
ጠፊ ናቸውና።
ሸ/ በየትኛውም አገር ያለ አገርን የሚጠብቅ መሪ፣ ወታደር፣ እንደተሸከመው የሕዝብ ኃላፊነት መጠን
ቁጣው ሲበረታ አደጋው ሲጨምር ጠረጋው ሲያይል ሕዝቡ ወደ እውነቱ እንዲመለስ መጣር አለበት። በከንቱ
ምክንያት እየደረደረ መፍትሔ አመጣለሁ እያለ ጊዜውን ማባከን የለበትም። ስብሰባ፣ እቅድ፣ ውይይት፣
የመፍትሔ ውሳኔ ድጎማ ሁሉ ይታቀዳሉ እንጂ የሚያመጡት ውጤት ስለሌለ ማንኛውም ሰው በዚህ መልእክት
የታዘዘውን የተነገረውን እንዲፈጽም እንዲረዳ ማድረግ ግዴታ ነው።
ለንፅፅር መጽሐፈ ምሳሌ 12 ፡ 26 ይመልከቱ።
ወደ መልእክቱ ምንጭ ወደ እግዚአብሔር ሕዝቦች ማረፊያ መቀመጫና ማዘዣ ስፍራ /ኢትዮጵያ/ ለመምጣት
መመሪያ ማግኘት ለሚፈልጉ ማናቸውም ሰዎች እንደግለሰብም፣ እንደቡድንም፣ እንደድርጅትም፣ እንደአገርም
በፈለጉት ቅርጽ ሆነው ለመምጣት ቢሹ ያሉበት አገር እና አስተዳደሩ በሁሉም መልኩ መርዳት ይገባዋል።
በአገሬ ያለው መንግሥት ምን ማድረግ እንዳለበት በራሱ የሚያስፈልገው መመሪያ ይሰጣልና በኢትዮጵያ በኩል
ምንም እንቅፋት እንዳይኖር ይደረጋል።
በኢትዮጵያ ያሉ ማናቸውም ድርጅቶች፣ ማህበሮች፣ ተቋሞች፣ የቤተ ክርስቲያን መጠለያዎች፣ አገልጋዮች፣
መዕመኖች ለሚመጣው ሁኔታ ሁሉ እራሳችሁን ማዘጋጀት አለባችሁ። ድርብ ኃላፊነት ይጠብቃችኋል።
ከየትኛውም ዓለም የሚመጣ እንግዳ ወንድም እህታችሁን እግዚአብሔር እንደሰጣችሁ ቸርነት መጠን በቅንነት፣
በንፅህና፣ በትህትና፣ በፍቅር ልዑል እንዳስተማራችሁ ሆናችሁ ማገልገል ግዴታችሁ ነው።
በኢትዮጵያ ተ/ኦ/ቤተ ክርስቲያን መሠረት የታነጻችሁ፤ ውድ አባቶቼ እናቶቼ አበው የተዋህዶ እምነት
መምህራን፣ ሊቀ ሊቃውንት፣ የዜማ፣ የቅኔ፣ የአቋቋም መምህራን፣ የድጓ መምህራን በየጫካው የወደቃችሁ
መነኮሳት፣ ባህታዊያን፣ በየገጠሩ በእምነታችሁ ፅናት ከቤተ ክርስቲያን ተባራችሁ በመንከራተት ያላችሁ
አገልጋዮች ምእመናን በሙሉ ከእንግዲህ የሚጣለው ተጥሎ ለተጋድሎአችሁ ከጌታችሁ ክብርን ምስጋናን
በረከትን ታገኙ ዘንድ ታዟልና በተባረከችው ኢትዮጵያ! ዓለምን በምትመራው ውድ አገራችሁ ኢትዮጵያ!
46
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የልዑል የክብሩ ማረፊያ ኢትዮጵያ! እነሆ ሥራውን ትረከቡ ዘንድ የአፈጻጸም ውሳኔ ተላለፈ። በመሆኑም
ለደስታውም፣ ለመጽናናቱም፣ ለአገልግሎቱም፣ ራሳችሁን አዘጋጁ።
በመላው ዓለም በክብር በፀጋው ተሞልታችሁ ለኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ለድንግል እናታችሁ፣ ለአባታችሁ፣
ለወዳጆቻችሁ፣ ለሚካኤል፣ ለገብርኤል፣ ለሩፋኤል፣ ለፋኑኤል በጥቅሉ ለእውነት እምነታችሁ ለማገልገል
ተዘጋጁ አንበሶች የልዑል አርበኞች ተፅናኑ።
ለንፅፅር መጽሐፈ ምሳሌ ም 30 /6/29 – 31 ይመልከቱ
ትንቢተ ሚልኪያስ፡ ም 3 ፡ 1 – 6
ደ/ መንፈሳዊ አገልግሎትን ወደ ንግድ ለመለወጥ የሚያስቡ ካሉ አሁኑኑ ሌላ ዓለም ለመኖር ቢያስቡ
ይቀላቸዋል። አልምርምና እንግዳችሁን በፍቅር ያለ ዋጋ አስተናግዱ፣ የአባቶቻችሁን ሕግ ተከተሉ ፈቅዶ
በፍቅራችሁ ደስ ብሎት ለሚባርካችሁ፣ ስጦታም ለሚሰጣችሁ በትህትና ተቀበሉ እንጂ እንደ ንግድ የአገልግሎት
ዋጋ አትቀበሉ። ቀድሞም ሥራችሁ ንግድ የሆነ በግልፅ የንግድ ቤት መሆኑን አሳውቁ በተለይ ቤት አከራዮች ቤት
የእግዚአብሔር መሆኑን እወቁ የምታደርጉት ሁሉ ለንግድ ሳይሆን ከፈጣሪ ለሚገኝ በረከት ይሁን። ያለፉትን፣
በቅጣት የተጠረጉትን፣ በክፋት የፀኑትን፣ የማይበሉትን የአመጽ ሀብት የሰበሰቡትን፣ አብረዋችሁ የሌሉትን፣
ሁሉን ትተው ወደ አፈርነት የተቀየሩትን ወገኖች አስቡ። እናንተ የቀራችሁት የነሱን ሥራ ለመድገም አይደለም
ከዚህ ፍፁም ራቁ እኔም አላልፋችሁምና።

17 ከቅጣት በኋላ የሚፈጠር መንፈሳዊና ሥጋዊ አኗኗር አስተዳደር ምን


ይመስላል።
1. ዓለም የሚጠብቃት በትርና እሳት ፈፅሞ አይታው የማታውቀው ነው። በዚህ የቁጣ ፍሰት አመፀኞች
በሙሉ ይጠረጋሉ፤ ምንም መሸሸጊያ ማምለጫ ቀዳዳ ያጣሉ። የሰው ዘዴ ሁሉ ከንቱ ይሆናል። አዲስ
ስርዓት ይፈጠራል፣ አዲሱ አስተዳደር ይዋቀራል።
2. ኢትዮጵያ የዓለም ሁሉ መንፈሳዊም ሥጋዊም መሪ ትሆናለች።
3. በዓለም አንድ እምነት አንድ ጥምቀት መልከ ብዙ አንድ ሕዝብ ይሆናል።
4. ቋንቋ ዛሬ ያለው የዓለም የቋንቋ አጠቃቀም ከስሞ የኢትዮጵያ ቋንቋ አማርኛ የዓለም መግባቢያ ቋንቋ
ይሆናል። መላው ዓለም እንግሊዚኛን እንደሚያጠና ሁሉ ያ ቀርቶ አማርኛ ዋናው መግባቢያ ይሆናል።
የሥራም ቋንቋ ይደረጋል።
5. በኢትዮጵያ የሚቆመው ብርሃናዊ አገዛዝ በመላው ዓለም ሰው ዘር በሙሉ የሚመቸውን የአስተዳደር፣
የፍትህ፣ የኢኮኖሚ፣ የገንዘብ፣ የትምህርት፣ የጤና፣ የመገናኛ ወዘተ አሰራሮች ያሰፍናል።
6. በኢትዮጵያ የሚቆመው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ በመላው ዓለም ያለውን የሰው ዘር መንፈሳዊ
ሕይወት በራሷ ቀኖናና ስርዓት ከልዑል በሚሰጣት ትእዛዝ ትመራለች ቅድስና የተሞላበትን መንፈሳዊ
ሥራ ትሠራለች። ለዓለም ብርሃን ሆና ታበራለች።
7. በቤተ ክርስቲያን የመንፈስ ቅዱስ አመራር የሚሾሙ አባቶች፣አገልጋዮች በመላው ዓለም ይበተናሉ
ሕዝቡን ይመራሉ። ያንጻሉ ያስተምራሉ።
8. መንፈሳዊ አገልግሎት ሁሉ መሠረቱ የሚጣለው በኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ስርአት አሰራርና
ትምህርት ይሆናል። የሚቋቋሙ ቤተ ክርስቲያኖች በቤተ ክርስቲያኗ አመራርና ፈቃድ መሠረት
ይሆናል።
47
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

9. በኢትዮጵያ የሚጸናው የልዑል ዙፋን በሥላሴ የታመኑ የተቀቡ አገልጋዮች የሚቀመጡበትና ከነሱ
በሚፈሰው መንፈሳዊና ሥጋዊ አመራር እንደ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፈቃድና አመራር በመላው
ዓለም በሚዋቀረው ስርአተ አገዛዝ ሕዝብ በሙሉ መንፈሳዊውንም ሥጋዊውንም አመራር ያገኛሉ።
በመላው ዓለም ያለው የወሰን አከላለል ሁሉ ለአስተዳደር፣ ለሕዝብ አኗኗር፣ ለጉርብትናው፣
ለመቀራረቡ፣ ተፋቅሮ ለመኖሩ በሚመች ሁኔታ ይስተካከላል። የቀደመው ቀኝ ገዥዎች አሻራ
ይወገዳል። በመላው ዓለም ያለው የሥጋ አሠራር መንፈሳዊ ሕይወትን የማያዳክም የማይጎዳ መሆኑ
ሲረጋገጥ ተግባራዊ ይሆናል። ዓለም የምትተዳደርበት መንፈሳዊ ሕግና ሥጋዊ ሕግ ወጥና አንድ ብቻ
ይሆናል። ዓለም አንድ ሕገ መንግሥት ብቻ ይኖራታል። በሕገ መንግሥቱ ተመስርቶ በማይቃረን
በማይሻር መልኩ በየዓለሙ ገጽታ ለተዘረጉ የከባቢ አስተዳደሮች ሕጎች ይደነገጋሉ። የሚወጡ ሕጎች
በሙሉ ከዚህ ከኢትዮጵያ ማእከል ቀርበው ይፀድቃሉ፣ ይሻራሉ፣ ይታረማሉ፣ ይሻሻላሉ። የፀጥታ
ኃይሎች በመላው ዓለም በመንፈሳዊ ስነ ምግባር በሕግ አግባብ ታንፀው በቅንነት የሚያገለግሉበት
ስርዓት ይደራጃል። ፍትህ በመንፈሳዊና ሥጋዊ አሰራር ምን እንደሚደረግ ወደፊት ከመንፈሳዊ አባቶች
ከሕግ ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት ወጥ ስርአት ይዘረጋል። እውነትን ብቻ መሠረት ያደረገ የፍትህ
ስርዓት ይደራጃል።
ትንቢተ ሚልኪያስ፡ ም. 4 በሙሉ
ዓለም በውስጧ ብዙ ሕዝብ እንደማቀፏ መጠን የሕዝብን ሀብት ጠቅልሎ በጥቂት ግለሰቦች ሰብስቦ መክተት
ዛሬም የሚታየውን የገብጋቦች ዓለም እንዲወገድ ያደርጋል። በተለይ አሜሪካ አውሮፓ ከብዙ ጥፋት ፍሰት በኋላ
ስለሚንበረከኩ ጉዳታቸው እጅግ ይከብዳል።
በዓለም ያሉ ዛሬ ሲታዩ ትልቆች መሪዎች ባለሃብቶች ሁሉን አድራጊዎች ሊያውቁት የሚገባ ነገር ቢኖር
በኢትዮጵያ በፍትህ አደባባይ ቀርበው ቅን የፈጣሪን ዳኝነት ያገኛሉ። ሥጋዊ አሰራሮች የእለት ተእለት ክንዋኔዎች
ሁሉ ምንዝርናን፣ ሌብነትን፣ ክፋትን፣ ተንኮልን፣ ማታለልን፣ ማጭበርበርን፣ በወንድም ላይ በደል መፈጸምን
ከመንፈሳዊ ሕይወት መስመር መውጣትን የሚያስወግድ ፈፅሞም የማይሸከም ሆኖ ይደራጃል ይዋቀራል።

18 ዓለም የተሸከመችው የጥፋት መሣሪያ እጣ ፈንታስ


1ሀ/ዓለም ለረጅም ዘመን ለመፋጂያ መሣሪያን ስታደራጅ ኖራለች የመጀመሪያው የጥፋት መሣሪያ ድንጋይ
ነበር። ቃየል ወንድሙን በዲያብሎስ ግፊት፣ በቅናት ተነስቶ የገደለው በድንጋይ ነበር፤ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ
የጥፋት መሣሪያ አደራጅቶ ወንድምን መግደል ተዘወተረ።
ለ/የጥፋት መሣሪያዎች አንድ ሰው መግደል ብቻ በማዘውተራቸው ሰው በጠላት ግፊት የመግደያ መሣሪያዎቹን
እያሻሻለ መጣ ከድንጋይ ወደቀስት ከቀስት ወደብረት እያለ አንድ ሰውን መግደል ተለመደ። የሰው ሥጋ ብርቱ
የጠላት መሳሪያ ነውና በሥጋ ፍላጎቱ የማይረካው ሰው ብዙ የተሻሻሉ መሣሪያዎችን ሠራ። ከብዙ ዘመን ጉዞ
በኋላ ሰው ታላላቅ የሰውና የንብረት ጥፋት የተደረገበትን 1ኛው የዓለም ጦርነትን 2ኛው የዓለም ጦርነትን
አካሄደ። አንድ ሰው ከመግደል አልፎ በሰራው ፈንጂ፣ ጀት፣ መድፍና ታንክ በሺና በመቶ መፍጀት ጀመረ።
ይህ መጠን ያላረካው ዲያብሎስ ጥበቡን እንደተሞላ ነውና። የተሻለን የጥፋት መሣሪያ ለሰው አስጨበጠ
ኒዩክለር ተሠራ በጃፓን ተሞከረ ከ300 ሺ ያላነሰ ሰው ፈጀ በዚህ ያልረኩት የዲያብሎስ አሽከሮች የምድርን
ሰው መላልሶ የሚያጠፋ ኑዩክለር በብዛት ሠሩ ይህ አልበቃቸውም የኬሚካል መሣሪያ ሠሩ ሰውን በጣጥሶ
የሚያጠፋ፣ ኒውትሮን ሠሩ። ሕይወት ያለውን ብቻ ለይቶ የሚገድል፣ ባዮሎጂካል መሳሪያ ሠሩ በሽታ አምጪ
ቫይረሶችን ጨራሽ አውዳሚ ባክቴሪያዎችን በላብራቶሪ አደራጁ ስንቱ ሰውን ሊያጠፉት እንዳሰቡ የሚገርም
ነው። ከ9 የማያንሱ አገሮች ይህንን የኒዩክለር መሣሪያ ተሸክመዋል።

48
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ለንፅፅር ትንቢተ ሚኪያስ 5፡– 10 – 15


ትንቢተ ኢሣኢያስ 24፡ 1 –13 ይመልከቱ።
በዚህ አልቆሙም እጅግ ግዙፍና የረቀቁ መርከቦችን፣ ሚሳኢሎችን፣ መድፎችን፣ ታንኮችን፣ አጥቂ
ሳተላይቶችን በጥቅሉ ሰው የማያውቃቸውን የረቀቁ የጥፋት መሣሪዎችን አከማቹ ሠሩ። ተዘጋጁ ወንድማቸውን
ሊገድሉበት የረቀቁ የጥፋት መሣሪያዎችን አከማቹ ሠሩ ተዘጋጁ ወንድማቸውን ሊገድሉበት እንደ ቃዬል
አንዴ አይደለም መልሰው መላልሰው ሊያጠፉበት ዓለሙ ዛሬም በዚያው ሕግና አላማ ውስጥ አሉ። ታላላቅ
መንግሥታት ለሃብታቸው ዋስትና ለወንጀላቸው መሸፈኛ ለድሃ መርገጫ ደሃ መንግሥትና ሕዝብ ለመዝረፊያ
ተጠቅመውበታል ዛሬም እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። የዓለም ዳኛ ነን የሚሉ ታላላቅ ጉልበተኛ መንግሥታት
በዚሁ መሣሪያቸው በሰበሰቡት ሃብታቸው በየቦታው ባደራጁት ተገዥ አሽከሮቻቸው ዓለምን ወደ ፍፁም ጥፋት
እየገፏት ይገኛሉ።
ይህን መሣሪያ የጨበጡት እነዚህ ሀገሮች አሜሪካ ከራሽያ፣ አረብ ከአሜሪካ፣ ኮሪያ ከኮሪያ፣ ሕንድ
ከፓኪስታን፣ እስራኤል ከአረብ ከፍልስጤም፣ አንዱ አገር ከአንዱ አገር በቀኝ ገዥዎች በተከለለ ድንበር
ሲፋጁ ሲነታረኩ የሚታዩበት የዘወትር የዓለም ድራማ ነው። የሰው ልጅ ልብ ብለህ አስተውል ጌታ ባይጠብቅህ
ዲያብሎስ የደገሰልህ ድግሥ ስንቴ ከመቃብር እያወጣ እንደሚገልህ /ቢቻል/ አስብ አሜሪካ 10 ሺ የኒዩክለር
አረር፣ ራሺያ 8ሺ የኒዩክለር አረር፣ ቻይና የኒዩክለር ብዛት በሺ አረር፣ ፈረንሳይ በሺ የሚቆጠር አረር፣
እንግሊዝ በሺ የሚቆጠር የኒዩክለር አረር፣ ሕንድ፣ ፓኪስታን፣ እስራኤል ከዚያም በመቶ የሚቆጠር የኒዩክለር
አረር ተሸክመዋል። ለዓለም ጥፋት የአንዱ አገር በቂ ነው። በዚህ አልቆሙም ይህንኑ መሣሪያ ጠፈር ላይ
ሰቅለዋል። ከዚህ በላይ ወንጀለኛ ምን ይምጣ? ታዲያ ይህ እንዴት ይወገዳል።

ሀ/የተሸከሙትስ መሣሪያ እጣ ፈንታስ?


»» ይህ የጥፋት መሣሪያ የተሸከሙ አገሮች ለራሳቸው የደገሱት ነው።
»» በእግዚአብሔር የተመረጡ የትም ይሁኑ የት ምንም ይፈጠር ምን የሚነካቸው የለም።
»» የተሸከሙት መሣሪያ በሙሉ ከምድረ ገጽ ይጠፋል። ሲጠፋም እነሱኑ የጥፋት አለቆችን ይዞ ይሔዳል።
ለንፅፅር ትንቢተ ሕዝቅኤል ም 26 (27) በሙሉ ያንብቡ።
»» እነዚህ አገሮች በኪሳቸው የሚነድ እሳት የከተተውን ሰው ይመስላሉ።
»» አጠፋፉን ሁሉ የሚያየው ስለሆነ መመልከት ለታደሉት ነው።
»» የሚጠፉ መልካሙን ሳያዩ ከጥፋት መሣሪያው ጋር አብረው ይበናሉ።
»» እንዴት? ያንን ለኃያሉ የሠራዊት ጌታ ውሳኔ አስፈጻሚ የብርሃን መላእክቶች እንተወው።

ለ/ዓለም በማን ትመራለች ማእከሉስ የት ይሆናል?


»» ዓለም ከትቢያ በምትነሳው የረሃብ ምሳሌ በሆነችው በአገሬ ኢትዮጵያ ትመራለች። ትገዛለች።
»» ከታላቁ የቁጣ ፍሰት በኋላ ዓለም በውድም በግድም ይህንን የልዑልን ውሳኔ ይቀበላል። ተግባራዊ
ያደርጋል። ይገዛበታል።
የዓለም አመራር ማእከሉ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ ይሆናል። ዓለም ቸሩ አምላክ ባነገሠው ንጉሠ ነገሥት
ከሱ ጋር አብረው በሚሾሙ የልዑል አገልጋዮች ትመራለች። ንጉሡም በታላላቅ ሽማግሌዎች የእግዚአብሔር
ሰዎች ይከበባል፣ ይመከራል፣ ይታገዛል፡ የዓለምን አመራር የሚይዘው የልዑል ባሪያ በዙፋኑ ላይ ሲሆን
49
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

አብረውት የሚሠሩ በሚሰጣቸው የማእረግ ደረጃ በመሆን ስለመንፈሳዊ ጉዳይና ስለሥጋዊ ጉዳይ የማማከር
ተግባር የሚያከናውኑ ይኖራሉ።
ዓለም ቸሩ አምላክ በቀባው አባት በኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባትና መሪ ከሱም ጋር
አብረው በሚቀቡ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በሚመሩ የእምነታችን አባቶች ትመራለች።
መንፈሳዊ አባቶች በመላው ዓለም ይመደባሉ። መንፈሳዊና ሥጋዊ አሰራሩ ተጣምረው በእግዚአብሔር ፈቃድ
የሚመሩ ስለሆነ እንደየሰው ብዛት እርቀት የአገሩ ስፋት እየታየ የአገልጋዮቹ ምደባ ይፈጸማል። በየደረጃው
የሚመደቡ ሁሉ የራሳቸው የስልጣን ሽፋንና የመወሰን ጣሪያ ይኖራቸዋል። ይህንንም የሚወስን ሕጋዊ አግባብ
ይደራጃል።
በሥጋው ሥራና አገልግሎት የሚመደቡትም ዓለምን በሚገዛው የቅድስናና የፅድቅ ሕገመንግሥት ስለሚመራ
ከዚህ ጋር አግባብ ያላቸው ሕጎች እየወጡ በዚያ መስፈርትና ማእቀፍ የመላው ዓለም የአስተዳደር የአገዛዝ
የአመራር የኢኮኖሚ የገንዘብ፣ የማሕበራዊ አገልግሎት በተያያዥነት ይደራጃል። በልማድ ያደጉ ባህሎችና
የአካባቢ አኗኗሮች ከመንፈሳዊና ሥጋዊ አሰራር ጋር የሚስማማው ተዋህዶ የማይስማማው ተጥሎ የአኗኗር ሁኔታ
መሠረት ይይዛል።
ትንቢተ ዘካሪያስ ም፡ 4 /5/በሙሉ
የዳዊት መዘ. 131 /132/6 – 18

19 የአስተዳደር ማእከላት
በመላው ዓለም የአስተዳደር ተዋረድ በዚህ መልክ ይሆናል።
ሀ/ አፍሪካ ይህ አሕጉር በአራት ይከፈላል 1ኛው ምሥራቅ አፍሪካ 2ኛው ደቡብ አፍሪካ 3ኛው ሰሜን
አፍሪካ 4ኛው ምዕራብ አፍሪካ ሲሆኑ ደሴቶች በሚቀርቡአቸው አካሎች ይካተታሉ።
በዚህ የአፍሪካ 4 አካል እንደ አገር መሪ በእያንዳንዱ ክልል በዋናው ማእከል የሚሾሙ መሪዎች ከሙሉ
መንግሥታዊ ስርዓት ጋር ይደራጃሉ። የተቀረው አስተዳደር ተጠሪነቱ ለዚሁ ማእከል ይሆናል። 4ቱም የአፍሪካ
መሪዎች ተጠሪነታቸው በኢትዮጵያ ላለው ለዋናው ማእከልና የንጉሠ ነገሥት አስተዳደር ይሆናል። የክልል
መሪዎችም የንጉስ ማእረግና የተሟላ መንግሥታዊ ስርዓት ይኖራቸዋል። ይህንኑ ተከትሎ መንፈሳዊው መዋቅርም
ይህንኑ እየተከተለ የራሱን መንፈሳዊ የአስተዳደር የአመራር ስርዓት ያደራጃል።
ለ/ አውሮፓ ይህ ክፍለ አሕጉር ለሁለት ይከፈላል 1ኛ ምሥራቅ ክልል 2ኛ ምዕራብ ክልል ይሆናል።
ሁለቱም የአውሮፓ የክልል መሪዎች እንደ አገር መሪ በየክልሉ ከዋናው ማእከል ይሾማሉ። የተቀረው በሥራቸው
የሚዋቀረው አስተዳደር ተጠሪነቱ ለክልሉ መሪዎች ይሆናል። መንፈሳዊ አመራሩ የአስተዳደሩን አከላለል
ተከትሎ የራሱን አስተዳደራዊ መንፈሳዊ የአመራር ስርዓት ይዘረጋል። ሁለቱም የክልል መሪዎች ተጠሪነታቸው
ለንጉሠ ነገሥቱ ይሆናል።
ሐ/ ስካንዲኒቪያ ይህ ክልል 1 መሪ ይኖረዋል። አወቃቀሩም ከላይ በ ሀ/ለ እንደተጠቀሱት ይሆናል።
መ/ አውስትራሊያ ይህ ክልል በዙሪያው ያሉትን ደሴቶች በሙሉ አካቶ በ1 የክልል መሪ ይተዳደራል።
አወቃቀሩም ከላይ በሀ/ለ እንደተጠቀሰው ይሆናል።
ሠ/ ሰሜን አሜሪካ ይህ ክፍለ አሕጉር በሁለት ይከፈላል በሰሜንና በደቡብ የየክልሉ መሪዎች በሀ/ለ
እንደተመለከተው ይዋቀራሉ።

50
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ረ/ በደቡብና ሰሜን አሜሪካ የሚገኙ ደሴታማ አገሮች ራሳቸውን ችለው በአንድ የክልል መሪ ይተዳደራሉ።
አወቃቀሩም በሀ/ለ እንደተጠቀሰው ይደራጃል።
ሰ/ ላቲን አሜሪካ ይህም በሁለት ይከፈላል 2 የክልል መሪዎች ይኖሩታል። አወቃቀሩም በሀ/ለ እንደተገለጸው
ይሆናል።
ሸ/ ኤሺያ ይህ ክ/አጉር በ7 የክልል መሪዎች ይመራል
ሸ/1 ራሺያ፤ ሞንጎሊያ ክልል 1
ሸ/2 ቻይና፤ ሆንግ ኮንግ ክልል 2
ሸ/3 ጃፓን፣ ኮርያዎች፣ታይዋን ክልል 3
ሸ/4 ህንድ፣ ፓኪስታን ክልል 4
ሸ/5 ቬትናም፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣ በርማ፣ ፊሊፒንስ፣ ኔፓል፣ ባንግላዴሽ፣ ላኦስ ክልል 5
ሸ/6 ካዛኪስታን፣ ታጃኪስታን፣ ኡዝቬክስታን፣ ተርኪሚስታን፣ አርመኒያ፣ አዘርቫጃን፣ ኪርግስታን፣
ጆርጂያ ክልል6
ሸ/7 ኢራን፣ አፍጋኒስታን ክልል 7
ቀ/ መካከለኛው ምሥራቅ ሳኡዲ አረቢያ፣ የመን፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኤሚሪትስ፣ ጆርዳን፣
ኢራቅ፣ ሶሪያ፣ ሊባኖስ በሁለት የክልል መሪዎች ይመራል። በሀ/ለ ባለው አወቃቀር ይደራጃል።
በ/ እስራኤል የኢትዮጵያ አምላክ ልጅ ከአባቷ ቤት ያልገባች በአመፅ ያለች ልጅ ናት። ቢሆንም ከማእበሉ
የሚተርፉት የኢትዮጵያ ታናሽ ወንድም ይባላሉ። አስተዳደራቸው በራሳቸው የውስጥ አስተዳደር መብት
ይተዳደራል። መንፈሳዊ አመራሩን ግን ከኢትዮጵያ ባለው ማእከል ይመራል። ይደራጃል።

20/ አስተዳደሮች ተዛምዶዎች በመንፈሳዊ ዐይን እንዴት ይጠራሉ። እንዴትስ


መልካም ይሆናሉ።
ወገኔ የሰው ዘር በሙሉ ልብ ብለህ በሥጋህ ሳይሆን በመንፈሳዊ ሚዛንና ዐይን እይ! ለማታየው አትይ ዐይን
አለህ አታይምና ጆሮ አለህ አትሰማምና አእምሮ አለህ አታስተውልምና።
ባለብረሃኑ ወገኔ የሰው ዘር አስተውል አድምጥ!
በዛሬው ጠፊ ዓለም መጪውን አትለካ የዛሬ ዓለም የበሸቀጠ በኃጢአት ባሕር የተዋጠ በዲያብሎስ የጨለማ
ሥራ የተተበተበ ነው። ይህ ዓለም ይጠረጋል ይጸዳል። ዲያብሎስ ከነጭፍራው በእሳት ይጠረጋል። የሚተው
የለምና ወደ መልካሙ ዘመን የሚሻገረው የዛሬው ልበ ጠማማ አይደለም ልበ ቅኑ እንጂ ብርሃን የሚያየው
ፈጣሪውን የሚወድድ እንጂ የዲያብሎስ ልጅ አይደለም። ስለዚህ መጪውን ምን ይመስላል ብለህ አትጨነቅ
መጪው ከቅጣቱ በኋላ እጅግ መልካም ይሆናል።
የሰው ልጅ ይዋደዳል፣ ጠብ ክርክር ይጠፋል፣ ሁሉም በአንድ እምነት በተዋህዶ ይቆማል። በአንድ ፈጣሪውን
ያመሰግናል። ሰው ለፈጣሪው ቅርብ ፈጣሪ ለሰውም ቅርብ ይሆናል። ዓለም በቸርነቱ ጠል ትረሰርሳለች ሰው
ከመደሰቱ የተነሳ ፈጣሪውን የሚያመሰግንበት የሚሰራበት የሚደሰትበት የቀኑ ብርሃን ለምን መሸ ይላል። ሌሊቱ
የጣፈጠ እንቅልፍና እረፍት ያለበት ከፈጣሪ ተገናኝቶ መባረኪያ ስለሆነ ለምን ነጋ ይባላል።
ወንድሞቼ እህቶቼ ዛሬ የጨለማ አሰራር ነው ያለው። ያኔ የብርሃን አሰራር ነው የሚሰፍነው። ለማን ትሰጣለህ
ሁሉ አለው። ስለ ችግር ማን ይነግርሃል ሁሉም ከችግር ተላቋል። ይህንን ታያለህ አምላክህን ትለምናለህ
51
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ሁሉንም ይሞላልሃል፡ በዚህ የበረከት ዘመን ፈጣሪ ሰውን እንደዚያ ቅርብ ሆኖ የሰማበት የሚሰማበት ዘመን
አልነበረም አይኖረምም። ስለዚህ ሁሉ ጨለማ ሲገፈፍ እየጠራ ይመጣል።
»» ዓለም አንድ የመገበያያ ገንዘብ ይኖረዋል። የዛሬው ጠንካራ፣ ደካማ ገንዘብ የሚሉት ንግግር ይጠፋል።

21/ የመሪዎች ማረፊያ ማእከል የት የት ይሆናል?


ይህ ከአስተዳደሮቹ አወቃቀር አከላለል በኋላ የሚወሰን ይሆናል። በክልልነት፣ በአገርነት የሚቆሙ ሁሉ
ሊኖራቸው የሚገባ የውስጥ ስልጣን አስተዳደር የመወሰን ርቀት የሥልጣን ተዋረድ ዓለምን በሚመራው ሕገ
መንግሥትና በዚሁ መሠረት በሚወጣው ሕግ ይወሰናል።

22/ በመላው ዓለም የሚፈሰው መንፈሳዊ አመራርና አገዛዝ ስርዓትና ፍሰት


እንዴት ይሆናል
ለንፅፅር መዝሙር 67 ፡ 11 – 35 ያንብቡ
»» ይህ በግልፅ እንደተነገረው ዓለምን የሚመራው የሚያስተዳድረው የሚገዛው አንድ ንጉሠ ነገሥት
ሲሆን በየክልሉ የሚወጡ መሪዎችም ንጉሥ ይሆናሉ። ከነሱ በታች በየአገሮቹ የሚመደቡ መሪዎች
ይኖራሉ /ፕሬዘዳንት፣ ጠቅላይ ሚ/ር፣ ሚ/ር ወ.ዘ.ተ./
»» ይህንን አወቃቀር ተከትሎ ከንጉሠ ነገሥቱ በሁሉም ጉዳይ የማይለዩ በመንፈሳዊ ስርዓት ዓለምን
የሚመሩ መንፈሳዊ አባት ይኖራሉ። በንጉሠ ነገሥቱና በመንፈሳዊ አባቱ በነሱም ዙሪያ ባሉ መንፈሳዊና
ሥጋዊ አማካሪዎች በሚደረግ ምክክር በልዑል ፈቃድ ፀንቶ በየክልሉ መንፈሳዊ አባቶች ይሾማሉ።
በየአገሩም እንዲሁ መንፈሳዊ አባቶች ይሾማሉ። የማእረጋቸው ስያሜ በመንፈሳዊው መሪ አባት
በሚመራው የሲኖዶስ ውሳኔ ይወሰናል።
»» ማንኛውም ሥጋዊ ሥራ መንፈሳዊውን ሥራ በማይጥስ በማያፈርስ መልኩ ይመራል። ይህንን ለማድረግ
በሁሉም ጉዳይ መንፈሳዊ አገልግሎት ሰጪ ኃላፊዎች በውሳኔ ውስጥ ይገባሉ ያልተስማሙበት ጉዳይ
እስከ ጫፍ ድረስ ታይቶ ይወሰናል እንጂ ተቃውሞአቸውን በመጣል የሚደረግ ውሳኔ አይኖርም
ቢደረግም በሕግ አግባብ ቅጣት የሚያስከትል ሲሆን ፈጣን እርምት ይወሰድብታል በፍትህ አሰራርና
ከመንፈሳዊ አካሄድ ጋር ተጣጥሞ ይዋቀራል።
»» ይህን የልዑል ትእዛዝ ለማስፈጸም ተገደውም ሆነ ፈቅደው የሚመጡ ማናቸውም ግለሰብ ቡድኖች
መንግሥታቶች የእምነት ተቋሞች ወዴት መምጣት አለባቸው ዝርዝር መመሪያ ከየት ያገኛሉ እንዴት
የግንኙነት መስመር መፍጠር ይችላሉ።
ሀ/ ማናቸውም የሰው ዘር ተገዶም ሆነ ፈቅዶ የሚመጣው ወደ ኢትዮጵያ ብቻ ነው።
»» እዚህ ለመምጣት ሲገደድ ወይም ፈቅዶ ሲወስን ወዲህ የሚመጠውን መረጃ ማግኘት መሰናዶ ማድረግ
ይገባዋል። ለአጭርም ቆይታ የሚረዳውን ነገር መያዝ ይገባዋል።
»» መረጃ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ በውጪ ካሉ ኢትዮጵያውያንና ከራሱ አስተዳደር መጠየቅ ይቻላል።
»» ይህንን የልዑል ትእዛዝ ያመጡት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ወደፊት በተከታታይ በሚገለጹ ፅሑፎች
አድራሻዎችን ስልኮችን ፈክሶችን ኢንተርኔቶችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ለመላው ዓለም እንዲገለፅ
ያደርጋሉ።

52
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

»» ከዚህ ከመጡ በኋላ ጊዜ ሳይጠፋ የሚያስፈልገውን መረጃ ያገኛሉ ሊያደርጉ የሚገባዎትን ሁሉ


መመሪያ ያገኛሉ።
ለአፈጻጸም ውሳኔው እንቅፋት የሚሆኑ የሚወሰድባቸው ተግሳፅና እርምጃ
ሀ/ በዚህ የእንቅፋት ሥራ የሚሰማሩ ማናቸውም ሰው ቡድን ድርጅት የእምነት ተቋም መንግሥት በመንግሥት
ስር የተደራጁ ወታደራዊና የፀጥታ የምክር ቤት አባሎች ባለሃብቶች ሁሉም የዚህ የእንቅፋት ሥራ ሃሳቢና ፈጻሚ
ሁሉ እንደወንጀላቸው ክብደትና ቅለት እርምጃ ይውስድባቸዋል።
ለ/ ምን እርምጃ ይወሰዳል? በመጀመሪያ የዚህ የጥፋት ሰዎች በልዑል ሰራዊቶች ተለይተዋል። ቅጣቱ
ሲጀምር እነሱን የሚዘል አይደለም፤ ስለዚህ እየተቀጡ ተገደው ይፈጽማሉ። ፈቅደው የሚፈጽሙት የታዘዙትን
ለመፈጸም በልባቸው በግልጽም አቋም በመያዛቸው በዚህ ርዕስ አይታሰቡም።
ለንፅፅር የዳዊት መዝ ፡ 124 (125)፡ 1 ይመልከቱ
ሐ/ ለእምቢተኞች የሚላከው የሚበላቸው እሳት ነው። እየላጨ እየቆላ ሞትን እንዲፈልጉት የሚያደርግ
በመሆኑ እንኳን የሚፈጸምባቸው የሚመለከተውንም እጅግ የሚያስደነግጥ ነው።
»» ለአፈጻጸም የመታዘዝ ግዴታ ለሁሉም ሁሉም የሰው ዘር እንደ መልክቶቹ አግባብ መታዘዝ አለበት
»» የዚህ ዘር ነኝ፣ የዚህ እምነት ተከታይ ነኝ፣ መሪ ነኝ፣ ክብር አለኝ፣ ሀብት አለኝ፣ እኒህ ሁሉ የተረፈ
ሰው ሊያስበቸው የሚገቡ አይደሉምና ይጠንቀቁ። ከሌላው ከምድሪቱ በቁጣ ከተወገደው ወገኑ እሱ
የተለየ አይደለምና፤ የሚለየውም ለምሕረት በመታሰቡ ብቻ ነው።
ለ፡–
ሀ/ ቀደም በ7/03/1998 ዓ/ም የተገለጸውን መልእክት ቀጥሎም በ27/09/2000 ዓ/ም የተገለጸውን
መልእክት አንብቦ ተረድቶ መገንዘብ ያስፈልጋል።
ለ/ የአሁኑ መንግሥታችን በእግዚአብሔር ፊት ምን ይመስላል? በግልጽ የሚታወቅ ነው። አፋቸውን
ሞልተው በመገናኛ ብዙሃን እግዚአብሔር መኖሩን የማያምኑ መሆኑን የተናገሩ ናቸው። የእምነትን አገር
የማያምን የሚመራበት ዘመን ማለት ነው። ስለ ውስጥ ሕይወታቸው ብዙ ቢታወቅም ነገ እግዚአብሔር
ስለሚገልጠው መናገር አያስፈልግም።
እንግዲህ መሪዎቻችን ልታውቁት ይገባል። ያላችሁት በኢትዮጵያ! እየገዛችሁ ያላችሁት በኢትዮጵያ ያለውን
ሕዝብ ነው። ይህ ሕዝብ ደግሞ አናውቀውም በምትሉት በእግዚአብሔር የሚገዛ የተወደደ የተመረጠ ሕዝብ
ነው። የመረጣትን ያጸደቃትን እምነት ተዋህዶን ለብዙ ሺ ዘመን ሕይወቴ ብሎ ተሸክሞ የመጣ ሕዝብ ነው።
ለማታውቁት እግዚአብሔር ማንነቱን በቤቱ የቅናት ቁጣ ሊያሳውቃቸው የወሰነ ስለሆነ ልትዘጋጁበት ይገባል።
ሐ/ ጠመንጃና ታንክ ይመጣል ብላችሁ አትገሠሉ ያ የለም። ከጠመንጃው ሁሉ የሚከፋው ሁሉን ከንቱ
የሚያደርገው የእግዚአብሔር እሳት እዚያው አጠገባችሁ አለ። ስለሆነም ይህ የአፈጻጸም ውሳኔ ለሕዝብ መበተን
ሲጀምር ለእግዚአብሔር የብርሃን ተዋጊ መላእክቶች የልዑል እግዚአብሔር ትእዛዝ ፈጻሚዎች አብሮ ይደርሳል።
ስለሆነም እግዚአብሔር ማንነቱን ካሰወቃችሁ በኋላ እንነጋገራለን ማለት ነው። እስከዚያው በማናቸውም ጉዳይ
አንዴ አይደለም አስሬ መላልሳችሁ አስቡና ተጓዙ፤ ሁሉም ድርጊታችሁ ኃላፊነትን ያሰከትላልና።
ቀደም ባሉት መልእክቶች መተላለፍ ጉዳይ ላይ ማንንም ባለመቃወማችሁ በዚህ መልካም ተግባር ነው
እላለሁ። እስከአሁንም እድሉን ያልነፈጋችሁ በዚህ ነው።

53
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

መ/ ለሕዝብ ለመግለጽ ግድ ነውና እስክትገደዱ ሳትቆዩ መግለጽ ትችላላችሁ። የኔን ማንነት ግን ከኔ ፈቃድ
ሳታገኙ በራሳችሁ መግለጽ አትችሉም። የኢ/ተ/ኦር/ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ እጃችሁን ከማስገባት ተቆጠቡ።
ለንፅፅር የዳዊት መዝ ፡ 115 (በሙሉ) ይመልከቱ።
አነሰም ተለቀም ማንኛውም አገር ያሉ መሪዎች ከሰበሰቡት መሳሪያ ጋር ሕዝብን ከሚነዱበት የጸጥታ ኃይል
ጋር ይጠረጋሉ፤ መደበቂያም ያጣሉ። ከላይ የተዘረዘሩትን እርምጃዎች በሙሉ የሰው ዘር ከተፈጠረ ጀምሮ
ያላያቸው በቅንብር የሚያጠቁ ምንም እረፍት የማይሰጡ እንኳን ለሌላው ለራስ መከላከል የማይችሉ ተደብቆ
ሸሽቶ መሽጎ የማይመለጡ ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱት አጥፊዎች በምሕረት የተሰበሰቡትን፣ በልዑል የተለዩትን፣ ምልክት የተደረገባቸውን፣
የድንግል ልጆች፣ የከበሩ የቅዱሳን መላእክት ልጆች፣ ወዳጆች፣ አይነኩም፣ ወደ እነሱም አይደርሱም።
በእግዚአብሔር የተወደዱ የምሕረት ወገኖች ፈቅደው በታዛቸው፣ በግቢያቸው ያስጠለሉት ይድናል።
በጉልበቱ፣ በኃይሉ ሊጠለል የፈለገ ደግሞ ከታዘዘለት የሚከፋውን አደጋ ይቀበላል። ይህ ሁሉ ይደረጋል፣
ይፈጸማል፣ አንዱም አይወድቅም፣ አንዱም አይቀርም።
“አንድ ማሰታወሻ ብነግራችሁ መልካም ነው።”
ስለ ሰው ልጅ ጥፋትና ክፋት ከልዑል ፊት የተደረገ ሰፊ፣ ረጀም ክርክር፣ ፍርድ ምሕረትና ውሳኔ፤
እንዲሁ ድንገት የተከናወነ አይደለም። የአምላካችንን የትእግስት ርቀት ያሳየ፣ የእናታችንን ጽናት ያስመሰከረ፣
የወዳጆቻችን የከበሩ መላእክት ለሰው ያላቸውን ፍቅርና ወዳጅነት ያረጋገጠ ነው።
በዓመተ ዓለም ሰው በኖረው ኑሮ ሁሌ እያጠፋ እየተቀጣ መጥቶአል። የኖኅ ዘመንን ማሰብ፣ የሰዶምን
ቅጣት ማሰብ በቂ ነው። ከዚያም በላይ የተመረጡ ሕዝቦች በእስራኤላውያን ለእኛ ትምሕርት ሆነው መጥተዋል።
ሲያምጹ፣ ሲቀጡ፣ ሲጸጸቱ፣ሲማሩ፣ በእነሱ እኛ የፈጣሪን ትግስት፣ ርህራሄ፣ ቁጣ አይተናል። እንደ ቃሉ ጌታ
ዋጋን ሊከፍል መጣ፤ ፈጸመ። ለሰው ጸንቶ የቆመ፣ የምሕረትና የዘለዓለምን ሕይወት እንዲወርስ የቆመ፣በደምና
በሥጋው የታተመ ፈቃዱን አጸና። ዛሬ 2000 ዘመን ሲያልፍ በዚህ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰው እንዲጠቀም
እንደተዘረጋም አለ።
የሰው ልጅ ግን ከእለት ወደ እለት ወንጀሉ ሃጢያቱ እየከፋ መጣ፤ የንጹሃን ደም መፍሰስ ጀመረ ሃጢአት
ነገሰ በፈጣሪ ፈንታ ፍጡሩ ዲያብሎስ አምላክ ሆነ የፈጣሪ ሕግ ተሻረ የዲያብሎስ ሕግ ተግባራዊ ሆነ። ይህ ሁሉ
ልዑል እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ በዙፋኑ እየተቀመጠ
ዳኝነት ሲሰጥ ቆየ።
ለግንዛቤ መጽሐፈ አስቴርን በሙሉ ያንብቡ
የዳዊት መዝሙር 105 (106) 13 – 40
በዳኝነቱ (በችሎቱ) ሁሉ፤ ድንግል ለሰው ማማለዷን እንባ ማፍሰሷን ታከናውን ነበር። ቅዱሳን የከበሩ
ዋነኞቹ መላእክትም ሚካኤል፣ ገብርኤል፣ ሩፋኤል፣ ኡራኤል፣ ራጉኤል፣ ሳቁኤል ሁሉ ለሰው ጥፋት
በጥብቅና በአማላጅነት ቆመው ጌታ መሃሪ ነውና ፊታቸውን እየተቀበለ ኖሮአል፤ በትንሽ አባታዊ ቅጣት
ሲያልፍ ኖረ። ሰው እንዲጸጸት ንስሓ እንዲገባ ሁሌ ፈቃዱ ስለሆነ ለ2000 ዘመን ታገሰ። አንድም ቀን
የእናታችንን የወዳጆቻችንን ጥብቅናና መማለድ በችሎቱ አላጠፈም ሁሌም እያመመው ትእግስቱን እየፈተነው
ኖሯል፤ ታግሷል።
ግን ዛሬ እንኳን ጌታ ጠበቆቻችን ሊከራከሩ፣ ሊማልዱ፣ ሊለምኑ አፈሩ። ሰው ፈጽሞ ጠፋ በልዑል ፊት
የሚቀርብ ቁራጭም መልካም አጣ። አብርሃም ከጌታ ሲሟገት 50 ጻድቅ ቢኖር፣ 45 ቢኖር፣ 30 ቢኖር፣

54
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

10 ቢኖር፣ 5 ቢኖር እያለ ምሕረት ለሶዶም ሊያመጣ ተሟገተ በዚህ ሁሉ ቁጥር እሺ አለ ጌታ አንድ ሰው
ብቻ ነበርና፤ አብርሃም ምንም ባለመኖሩ ደነገጠ አፉን ያዘ። ይህም ሆኖ ኖኅ በደረቅ ስፍራ መርከብ ሲሠራ
ሲያፌዙበት እሚሰማው አጣ፤ የልዑል ቁጣ ነዳ ነበርና ከመርከቡ ኖኅን ካስገባ፣ በታዛው የሚጠለሉትን ከሰበሰበ
በኋላ፣ በውጭ ዘጋው ኖኅን ዝጋ አላለም እራሱ ዘጋው።
ዛሬም እንግዲህ ይህ ሁሉ የድንግል ክርክር፣ ልመና፣ የቅዱሳን የከበሩ መላእክት ልመና፣ የቅዱሳን
ልመና፣ ሁሉም ሲፈጸም ሲፈቀድ ኖረና ዛሬ ለምሕረት የሚያበቃ ቁራጭ ተግባር ሲጠፋ ሁሉም አፉን ከደነ።
አበቃ የሰው ልጅ ስማ፣ የልዑል ልጆች በእምነት ድንኳናቸው ገቡ ከውጪም ልዑል ዘጋው ያንተም ጉዳይ
ተደመደመ ተዘጋ።
እጅግ አዝናለሁ ይህን ስል! ይህን መርዶ ስናገርህ እጅግ ይዘገንነኛል ምን ይደረግ አበቃ ተዘጋ። በአብርሃም
እቅፍ እንዳለው አልአዛርና እንደ ባለጸጋው ሁላችንም ተለያየን።
ቸሩ ፈጣሪ ስለቅን ፍርዱ ይመስገን ይከበር ልዑል ኃያል መካር ጌታ እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ የተመሰገነ ይሁን። ፍርዱን እንደ ፀሐይ ብርሃን የሚያወጣ ጌታ
ለዘለዓለም ስሙ ይባረክ። አሜን።

23 የመጨረሻው ማሠሪያ ቃልና ትእዛዝ


»» የማናቸውም አገሮች ሕዝቦች የሕዝብ መሪዎች በመላው ዓለም ተበትናችሁ ያላችሁ የሰው ልጆች
በሙሉ፤ በየትኛውም የአኗኗር ደረጃ ላይ ሁኑ።
»» ይህ ቃል ለሁላችሁም ከታመነው የልዑል ባርያና ታዛዥ የወጣ፤ በልዑል ፈቃድ የጸና ነውና
አድምጡ! ዓለም እነ ጳውሎስን እብዶች ብላለች ዓለም በልዑል ስም የመጡትን እነማንን ተቀበለች፣
ተሳለቀች፣ አሰረች፣ ገደለች፣ አሳደደች እንጂ ዓለም ለእግዚአብሔር ባለ አእምሮ የሆነን ሰው ለእናንተ
እብድ ነው ትላለች። ስለዚህም ሰምታም አታውቅም። በመሆኑም ብትሰማም ስማ ባትሰማ አትስማ!
እንዳላችሁት የእብድ ቃል ስለሆነ አንብባችሁ ሳቁበት ተሳለቁበት! ይመሽ ይነጋ አይምሰልህ በሳቅ
በፌዝ የፈጀኸውን ጊዜ በሺህ እጥፍ አብዛኛውና ያ ጊዜ ያንተ የሞት መለመኛ ይሆናል።
»» የሰው ዘር ስማ እኔ የነገርኩህን ከራሴ አላመነጨሁም ከፈጣሪ የተነገረኝን እንጂ። ስለሆነም ከ7/3/1998
ዓ.ም እስከ 19/7/2001 ድረስ ተነግሮህ አድምጠህ ንቀህ ትተኸዋል። ዛሬ ይህንን የውሳኔ አፈጻጸም
ስትሰማ አሁንም እንደለመድከው ያው ይመስልሃል ንቀህ እንደምትኖር ያ አበቃ። ይህ የውሳኔ
አፈጻጸም ከወጣና ከተፈለገው አቅጣጫ መሄድ ከጀመረ ከመጀመሪያው የመድረሻው ቀን ጀምሮ ዓለም
የጠረጋውን ምንነት በሁሉም የዓለም ገጽታ በሁሉም የሰው ዘር ኑሮ ዙሪያ ታያለች። ከዚያች ዕለት
ጀምሮ በቁጥር 1 በቁጥር 2 የተጠቀሱት የቅጣት ዓይነቶች ይፈሳሉ። ማቆሚያ የላቸውም የትኛውም
ብልሃት ዘዴ አያቆማቸውም እንዲያውም የሰው ልጅ ትእቢቱን ካጸና እጅግ ታይቶ የማይታወቅ ጥፋት
በዓለም ሁሉ ይሆናል።
በዚህ ሰዓት በዓለም ሁሉ ያሉ የአገር መሪዎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ከነሹሞቻቸው/ከነአገልጋዮቻቸው
ግንባር ቀደም ተጠራጊ ይሆናሉ። ሲነገራቸው አልሰሙም ለወገናቸው አላሰሙምና እንግዲህ የሰው ልጅ ይህን
ስነግርህ በተለይ ምንም በማያውቁት ሕፃናት ጉዳት ልቤ ቢከፋም ያንተ የአዋቂው የክፋት ውጤት የጎዳቸው
በመሆኑ ላንተ ላላጋጩ ሲያንስህ ነው። ሕፃናት ቢሄዱም ወደ ጌታ እቅፍ ነው የሠሩት ወንጀል የለምና።

55
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

24. በመጨረሻም
ማንኛውም የአዳም ዘር በሙሉ አድምጥ!
መልእክት አንድን በ7/3/1998 ዓ.ም የወጣውን መልእክት ሁለትን በ27/9/2000 ዓ.ም የወጣውን በሙሉ
እናም ይህንን የአፈጻጸም ውሳኔ መልእክት በሚገባ አንብባችኋል ብዬ አምናለሁ። ሁሉም እንደተረዳው
መጠን አይቶታል፣ የናቀውንም ንቋል፣ የደነገጠውም ደንግጧል፣ የሳቀውም ስቋል ብቻ እንደመሰለው እንደ
ተመሰረተበት አይቶታል ፈጽሞም ባያየው ንቆታል።
አሁንም ባበቃውና ባለቀው ሰዓትም ቢሆን ሁሉንም መልእክቶች ከ1፣2፣3 ያሉትን በአንድ ማስታወሻ አካል
መጽሔት ቀርቦልሃልና አንብበው ካልፈለግህም ምርጫህ ነው አታንብበው ከድንበርህ የምትዘለውም ተሳደብ
አፊዝ እሳት ላይ ቆመህ ነውና ይህን የምታደርገው ለጠፊው አዝናለሁ።
የዳዊት መዝ. 82(83) ለንፅፅር ይነበብ።
ዛሬ በዓለም ምን እየሆነ ነው? የቀደሙት መልእክቶችስ ምን ምልክት እያሳዩ ነው? ታዩ ዘንድ በነሱ
ተመስርተው እየተከናወኑ ያሉትን በግልጽ የሚታዩትን እንደ ምሳሌ እንኳ እንይ
»» የዓለም ኢኮኖሚ በቀውስ ውስጥ መውደቅ በመልእክት 2 እንደተጠቀሰው
»» ሪሴሽን እጅግ መክፋቱ የበጀት ጉድለት እየጨመረ መምጣቱ ሥራ ፈት መጨመሩ
»» የተፈጥሮ አደጋ እጅግ መበርከቱ
»» የምግብ እጥረት ማየሉ፣ የሙቀት መጠን መጨመሩ
»» የበረዶ ግግር በአውሮፓ እጅግ መክፋቱ
»» በአውስትራሊያ ጎርፍና እሳት በአንድ ሲዘምቱ
»» የገንዘብ ቀውስ መቀጠሉ የትላንት ፉከራ ዛሬ ባዶ መሆኑ
እነዚህ ሁሉ የምጥ ጅማሮ ናቸው። በዘመናችን አዋቂዎችና እንደኛው አገር ተፈላሳፊዎች ችግሮች ሁሉ
በመፍትሔ የሚፈቱ ናቸው፣ በእቅድ፣ በዘዴ ማስተካከል፣ የመከላከል እርምጃ በመውሰድ የሚፈቱ ናቸው
ባይ ናችሁ። አይ ሰው አይ የዘመኑ መሪዎች ስልጣን ላይ መውጣት ከማንም በላይ አዋቂ ያደረጋችሁ።
የዘመናችን አዋቂና መሪዎች ጠመንጃ ያጎለበታቸው፣ እንዳሻቸው እንዲናገሩ ያደረጋቸው ናቸው። በራሳቸውም
በሕዝባቸውም የነገ ሕይወት ላይ የሚፈርዱም ናቸው።
› ከዚህ የአፈጻጸም መልእክት መውጣት በኋላ ምን ይከሰታል። በምልክቶቹ ያልደነገጣችሁ ይህንን ደግሞ
ተቀበሉ።

25–ሀ የተፈጥሮ ኃይሎች፡–


»» የተለያዩ ስያሜ ያላቸው ማዕበሎች ባልታየ መጠን ይመጣሉ ይጠርጋሉ።
»» የከበደ ማግኒቲዩድ ያላቸው የመሬት መንቀጥቀጦች ካልጨረሱ አይመለሱምና በተከታታይ ይከሰታሉ
ከባድ እሳተ ጎሞራዎች ታይተው በማየታወቅ ጉልበታቸው ይወጣሉ ሳይጨርሱም አይቆሙም!
»» ታይተው የማይታወቁ ጎርፎች የማያቋርጡ ጠርገው እስከሚጨርሱ የማይቆሙ ይመጣሉ።
»» እጅግ የከፋ የበረዶ ክምርና የጉም አፈና የማያቋርጥ ለረጅም ጊዜም የሚቆይ ይመጣል።
»» ያልታየ ንፋስ የቀላቀለ የዝናም መጠንና አጣጣል ቶሎም የማያቋርጥ ይጥላል ይጠርጋል።
56
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

»» እጅግ በጣም ፈጣን የሆነ የጫካ እሳቶች የከተማ እሳቶች ቶሎም የማይጠፉ ይመጣሉ። እሳቶች
የታዘዙትን ሳያጠናቅቁ የማይቆሙ ይሆናሉ።
»» ታይተውም ተሰምተውም የማይታወቁ ኃይለኛ አውሎ ነፋሶች ብረቱ ቋጥኝን የሚፈነቅል ኃይል
ያላቸው በቶሎ የማይቆም ከተማውንም ገጠሩንም ይጠርጋሉ።
»» የከፋ የአውሬዎች ጥቃት በመላው ዓለም ይዘወተራል። ትንቢተ ሕዝቅኤል 26፡ 8 – 21 ለንፅፅር
ይመልከቱ።
»» በፍፁም የማያስኬዱ የባሕር፣ የውቅያኖስ ማዕበሎች የታዘዙትን ስለሚፈጽሙ የማያቋርጡ በአጠቀላይ
እነዚህ የተፈጥሮ ኃይሎች እጅ በእጅ ሆነው ባንድነት ባልታየ ኃይላቸው ፍፁም የሚያጠፉ ናቸው።
በሙሉ ጉልበታቸውም ይዘምታሉ።

26.ለ. የኢኮኖሚ ቀውስ፡–


»» የኢኮኖሚ መጨማደድ እጅግ ይከፋል
»» የኢኮኖሚ ቀውስ እጅግ ይከፋል
»» የገንዘብ ቀውስ ከአሁኑም እጅግ ይከብዳል
»» ያልታየ ያልተሰማ ሪሴሽን
»» ያልታየ ያልተሰማ የበጀት ጉድለት
»» የመላክና የማስገባት ውድቀት ይመለከታል እጅግም አስቸጋሪ ይሆናል
»» የምግብ ችግር እጅግ ይከፋል ረሃብ ያላያቸው ይራባሉ።
»» ሰጪ የነበሩ ፍፁም ያጣሉ። አጥተውም ይለምናሉ
»» ብርቱ በሽታዎች ይነግሳሉ እጅግ ብዙ ጥፋት ያደርሳሉ
»» ብርቱ ባክቴሪያዎች፣ ቫይረስ ቫይረሶች፣ ታላቅ ተከታታይ ጥፋት ያደርሳሉ የታዘዙትን ሳይፈጽሙ
አይቆሙም

27.ሐ. የፖለቲካ ቀውስ፡–


»» ሁሉም ይደጉም አይደጉም፣ ይጡም አይጡም፣ ያላቸውም የሌላቸውም ሀገሮች እርስ በእርሳቸው
የሀሳብ፣ የፖሊሲ፣የድርጊት፣ የእቅድ አለመስማማት ያነሳሳሉ። በብርቱም ይጋጫሉ።
»» ማናቸውም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እንደ EU, AU, UN, SEATO, LATIN UNITY, ARAB
LEAGUE ሁሉም በግጭት ይሞላሉ ማንም ከማንም መስማት መስማማት ያቅተዋል ድርጅቶቹም
የመፈራረስ የመዳከም እጣ ይገጥማቸዋል። ይበተናሉም።
»» ማናቸውም እቅዶች ስምምነቶች ይፈርሳሉ። በተለይም ትልልቅ ነን የሚሉ ሀገሮች ግጭት እጅግ
ይከፋል።
»» ኃያል የሚባሉ አገሮች እጅግ በከባድ ቀውስ ይቀጣሉ። ዳግምም አያንሰራሩም በዚያው ያከትማሉ።
»» ጦርነት ይነግሳል፣ የሕዝብ ለሕዝብ ፍጅት ይከፋል የሃየማኖቶች ግጭት እጅግ ይከብዳል ብዙም
ያጠፋል።

57
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

»» መሪዎች ይጮሃሉ የሚሰማቸውም ያጣሉ ያደራጁት የጸጥታና የጦር ኃይል አይታዘዝም የመዳከም
የመበተንም እጣ ይገጥማቸዋል። ሕዝቦች ለማንኛውም የመንግሥት ኃይል አይታዘዙም አይፈሩምም
ሕግ የተባለ ሁሉ የሚያከብረው ያጣል።
»» ሰላም ስሙ እንጂ ምግባሩና ምልክቱ ፈጽሞ ይጠፋል።
ለንፅፅር መዝሙረ ዳዊት፡ 78(79) ፡ 6 ይመልከቱ።
ከላይ ያሉ አደጋዎች በሙሉ ይከናወናሉ ሰው በሙሉ በመልእክቱ እንደተጠቀሰው መገዛት አለበት እጅን
ለኢትዮጵያና ለብርሃናዊ ዙፋናዊ መንግሥት እምነቱን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መስጠት
አለበት። ከዚህ ውጭ የሚመጣ መፍትሔ የለም። አደጋዎች፣ ጥፋቶች ሁሉ በነጠላ በስፋት የሚቆሙት
የሚያልፉት እጁን ለሰጠው ብቻ ነው።

28.መ. ማህበራዊ ቀውስ፡–


»» ሥራ ፈትነት ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ሁኔታ በመላው ዓለም ይሰፍናል።
»» ማናቸውም ማህበራዊ አገልግሎቶች በየትኛውም ዓለም ይወድቃሉ።
»» የማህበረሰብ ግጭቶች የዘር ግጭቶች በየትኛውም የዓለም ክፍል ይሰፍናሉ። የእምነቶች ግጭት
ይከፋል።
»» የጤና አጠባበቅ ስርዓት ይጠፋል።
»» ትራንስፖርት ፍፁም ይበላሻል በየትኛውም ዓለም መኪና፣ ባቡር፣ አውሮፕላን፣ መርከብ ሁሉም
ለመገልገል ያስቸግራል አደጋቸውም የበዛ ይሆናል። ለምሕረት ያልታደሉትን ለማጥፋት ሞት ሁሉንም
መገልገያዎች ወደ መግደያነት ይለውጣቸዋል።
»» በየእለቱም የምንገለገልባቸው ሁሉ ለእኛ ማጥቂያ ይሆናሉ።
»» ኤሌክትሪክ መገናኛ ግድብ ሁሉም ይወድቃሉ።

29.ሠ. ወታደራዊ መገልገያዎች፡–


»» ማናቸውም ለፀጥታና ለድንበር ተብለው የተሠሩ ወታደራዊ መሳሪያዎች በሙሉ ከንቱ ይሆናሉ።
የያዛቸውንም ይዘው ይጠፋሉ።
»» ለዚሁ ተብለው የተከማቹ ያከማቹዋቸውም የሚገለገሉባቸውም ሁሉም አብረው ይጠፋሉ።
»» ሁሉም ኃያላን ተብዬዎች የሰበሰቡት መሳሪያዎች በሙሉ ጌቶቻቸውን ስለሚበሉ በታላቅ ድንጋጤ
ይዋጣሉ።
»» ሁሉም የጦር አዛዥ የኒዩክለር ኬሚካል ባዮሎጂካል፣ ኒውትሮን የታጠቁ ሳተላይቶች ሁሉም
ጌቶቻቸውን ይዘው ይጠፋሉ።
ለንፅፅር መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 22፡ 8 – 16 ይመልከቱ።
»» ዛሬ የምታዩት የጥፋት ምልክት እጅግ በከበደ መጠንና ኃይል ሊጠርጋችሁ ወጥቷል። በተለይ እናንተ
የፖለቲካው መሪዎች ሕግ አውጪ፣ ሕግ ወሳኞች የጸጥታ መዋቅሮች፣ ቢሮክራቶች፣ ተቃዋሚም
ደጋፊም ፓርቲዎች፣ ወታደሮች ከነአዛዦች፣ ዳኞች፣ አሳሪ ፈቺዎች፣ የመጀመሪያው የጥፋቱ ሰለባዎች
ትሆናላችሁ። ምንም አይነት የእስትንፋስ ጊዜ አይሰጣችሁም፣ ለማንኛውም ወንጀሎችና ኃጢያቶች

58
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ተጠያቂ ናችሁና። በሂደት የሚበላችሁን ስታዩትና በውስጡ ስትገቡ ልታስታውሱት የሚገባው ይህ


ነው።
»» ትዳኛላችሁ፣ ትቀጣላችሁ፣ ትታሰራላችሁ፣ ይህም የሚሆነው እንደተሸከማችሁት የኃላፊነት ድርሻ
መጠን ነው። በእናንተ ኃላፊነት ስር ያለውም እንደ ድርሻው መጠን ቅን ፍርዱን ያየዋል።
»» ማናቸውም የፍርዱ ሂደቶች ከዚሁ በኢትዮጵያ ይከናወናሉ።
»» በፍቃዳችሁ እዚህ በሚሰየመው ችሎት መቅረብ አለባችሁ። ይኸውም ቅን ፍርድን በአባታዊ ቅጣትና
ምሕረትን ለማግኘት ነው።
»» ወይም አለመምጣትና አለመቅረብ ነው። ስለሆነም በዚያው ሆኖ በራሳችሁ ላይ በሕዝባችሁ ላይ
በአገራችሁ ላይ የሚፈጸመውን መቀበል ነው።
»» በመከናወን ላይ ያሉት የጥፋቶች ምልክቶች እናም መጪው እጅግ ብርቱ ጥፋት ካላጠፏችሁ
የማይመለሱ ናቸው። ስቃያችሁን በማራዘም ሞትን በመንፈግ እንድትለምኑ በማድረግ የሚያጠፏችሁ
ናቸው። መንገድ የለምና።
»» አንዱና ብቸኛው መንገድ ራስን ወዶና ፈቅዶ ፍትሕ ላለበት የፍርድ ሂደት ራስን መስጠት ብቻ ነው።
በኢትዮጵያ በሚቋቋመው ፍ/ቤት በኔው በድሃው ጎጆ።
በዚህ በድሃው፣ የልዑል የታመነ አገልጋይ፣ አእምሮው የተቃወሰ እያላችሁ ከምትጠሩት ቅዠታም
ከምትሉት፣ እብዱ ቤት ለፍርድ ትቀርባላችሁ ትዳኛላችሁ።
እኔ ምንም በሉኝ የፈለጋችሁትን ስያሜ ስጡኝ አዎን ነኝ!
ስድብ ትችት ነቀፋ ልብሴ ናቸውና ጎስቋላ ነኝ፣ አቧራ ብናኝ ነኝ፣ ማንም ቁም ነገር የሚለኝም አይደለሁም፣
አዎን ነኝ መቼስ አይደለሁም አልኩና የምትሉትን ሁሉ ነኝ እርካታ ይስጣችሁ እንጂ ለእኔ ጭንቄ አይደለም።
እውነቱ ግን ሌላ ነው ልብ በሉ በዚህ ድሃና ኃጢአተኛ ላይ የእግዚአብሔር ፀጋና ኃይል ሲጨመርበት ግን
ከአእምሮአችሁ በላይ ከምታስቡትም ውጪ ይሆናል። ይህም ነው እየተከናወነ ያለው። ለእናንተ ከንቱ ብሆንም
ለሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን የሚወደኝ ልጁ ነኝ። ፈጠረኝ፣ አሳደገኝ፣ በእድሜዬ ሁሉ መራኝ።
ለንፅፅር መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ 23፡ 2 – 7 ይመልከቱ።
በበረሃውና በእሳቱ አሳለፈኝ። ሰው ሊገምተው ከሚችለው በላይ በሆነ ሰቆቃ ባልወድደውም ፈቃዱ ነበርና
በዚያም ውስጥ ሞትን ጓደኛ አድርጎ አሳለፈኝ ዝርዝር ታሪኩን ልተወውና።
ዛሬ የማደርገው ሁሉ በተሰጠኝ ትእዛዝና ፈቃድ ብቻ መሆኑን ልታውቁልኝ ይገባል። በቀደሙት ሁለት
መልእክቶች ብዙም ስለራሴ የገለጽኩት ባይኖርም ዛሬ ግን በአባቴ የተፈቀደ በመሆኑ ለአምላኬ ምን እንደሆንኩ
ታውቁ ዘንድ በመጠኑ እገልጻለሁ።
ከሁሉም በላይ ግን አንድ ቁም ነገር ልታውቁ ይገባል። ይኸውም ማንኛውም ሰው በሱ ፊት እኩል መሆኑን
ነው። የተከፈለውም የኃጢአት ዋጋ ለሁሉም የሰው ዘር የተደረገ የፍቅር ዋጋና መስዋእት ነው። ልዩነቱ ያለው
ግን በኛ ፈቃድ ላይ ነው። በፍፁም ልባችሁ ነፍሳችሁና ሃሳባችሁ ካመናችሁትና ከወደዳችሁት የምትወደዱ
ልጆቹ ናችሁ። እውነቱም ይህ ነው።
ከላይ እንዳልኩት እኔ ታናሹ ልጁ የልዑል ባሪያ፣ የሥላሴ ባሪያ፣ የድንግል ባሪያ፣ የአምላኬን በጎች
እጠብቅ ዘንድ በመልካምም ሥፍራ አሳርፍ ዘንድ በአባቴ የታዘዝኩ ነኝ የት ድረስ ነው ስልጣንህ ትሉ
ይሆናል። ልዑል ነው ያዘዘኝ የሚመራኝ ምድሪቱም በኔው በትንሹ በኃጢአተኛው በሥላሴዎች በተወደደው

59
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ባሪያ ትገዛለች ትመራለች። እኔ ለበጎች እኖራለሁ። ለቀበሮች ደግሞ ሞታቸው ነኝ። ቀሪ ሕይወቴ ለአባቴ ክብር
ቃልና ፈቃድ መፈፀም መስዋእት መሆን አለበት። እኔም እንግዲህ ይኸው ነኝ ከኔ ከባሪያው ጋር አብረው
የሚከብሩ እጅግ የተወደዱ፣ የተሾሙ፣ የተቀቡ (የታመኑ) ሁሉ በተፈቀደው ሰዓት ወደብርሃኑ ማማ ይወጣሉ።
ዛሬ በየትም ተጥለዋል፣ በየደጁ ወድቀዋል በረሃብ ጠውልገዋል፣ በሰው ተንቀዋል እንደ ውሻ ተቆጥረዋል።
ወንጌልን በጨበጡ ተተፍተዋል ተስቆባቸዋል። ከሃዲዎች መጨወቻ አድርገዋቸዋል። በአባታቸው ቤት ባይተዋር
ሆነዋል። ይህ ግን አበቃ።
ለንፅፅር የዳዊት መዝ፡ 149 ይመልከቱ።
የልዑል ልጆች ከውርደት ወደ ክብሩ ማማ ሊወጡ በተወደደ አንደበታቸው ባማረ እግራቸው ምድሪቱን
በአምላካቸው ቃል ሊያረሰርሱ ይገባልና ይሆናልም። ማነው የሚነካቸው ማነውስ የብርሃን ልጆቹ ፊት በክፋት
የሚቆመው በቃ!
ለንፅፅር ኢዮብ 5፡ 17 – 26 ያንብቡ።
የተዋህዶ ኦ/ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ እጃችሁን ከማስገባት ተቆጠቡ በውስጧም የሰገሰጋችኋቸው የምን
ጉዳይ ይሁን የምን ሰራተኞቻችሁን /ለእናንተ የሥጋ ሥራ የተሰማሩትን/ አስወግዱ።
»» ቤተክርስቲያን በተመለከተ የሚቀጣት እግዚአብሔር ነው
»» አንድም ሰው እንዲነካት መብት የለውም።
»» ተዋህዶ እምነት ላይ የማይዘምት ማን አለ?

በእምነት መስመር ያሉ
በአገራችን ያሉ፡– ካቶሊክ፣ ሙስሊም፣ ፕሮቴስታንት ሌሎችም በውጪ ያሉ ፡– ካቶሊክ፣ ሙስሊም፣
ፕሮቴስታንት፣ ሂንዱኢዝም፣ ቡዲሂዝም ሁሉም ተቋም ቀስቱ በኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን
ላይ ነው።
በመንግሥት መስመር ያሉ፡– የራሴው መንግሥት እናንተና በኢትዮጵያ ጉዳይ ሁሌ የሚታመሙት

የውጭ መንግሥታት በሙሉ


»» በውጭ ያሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ተቋሞች በሙሉ ዘመቻቸው በኢት. ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
ላይ ነው።
»» በነዚህ በውጭ የሚደገፉ የአገር ውስጥ የተለያዩ ተቋሞች ዘመቻቸው በኢት. ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ
ክርስቲያን ላይ ነው።
ሁሉም ከአያት ቅድመ አያቱ የወረሰውን ተዋህዶን የማጥፋት ዘመቻ ሲፈጽምና ሲያስፈጽም እንጂ ሲጸጸት
አላየንም። ዲያብሎስ ዓለምን ይነዳል የምንለውም ለዚህ ነው። ዓለም በሙሉ የሱ ታዛዥ ነው። የኛም መንግሥት
የት እንደቆመ ስለምናውቅ የማን የዘመቻ ምድብ ውስጥ እንዳለ ጠንቅቄ የማውቅ ነኝና ተጠንቀቁ።
ማንም እምነቴን ሊቀጣ አይችልም።
ቤቱን የማጸዳው እኔው የልዑል ባሪያ ነኝ። ሌባም ይሁን ቀጣፊ፣ ተኩላም ይሁን ምን፣ በኢት.ተ.ቤ.ክ
ውስጥ ያለውን ሁሉ ችግር የሚፈታው በራሱ በፈጣሪዋ እንጂ የሥጋ ዳኛ መብት የለውም። ደግሜ እላለሁ በዚህ
በአባቴም ቤት በእናቴ ቤት በወዳጆቼ ቤት የሚደረገው ጥፋት አይሆንልኝምና አልራራም፣ አልምርምም፣ደጋግሜ

60
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

የማስጠነቅቀው ለዚህ ነው። ስለዚህ ከቤተ ክርስቲያን መሪ እስከ አገልጋይ ስር ድረስ ያሉትን በሙሉ ማንም
ውስጧ እንዳይገባ።
»» ቤተ ክርስቲያን ተዘመተባት እንጂ በማን ላይ ወጣች? ቤተ ክርስቲያን፣ ገዳማት፣ ተቃጠሉባት እንጂ
የማንን እምነት ማምለኪያ ነካች።
ለንፅፅር መዝ፡ ዳዊት፡ 95 (96) ፡13 ይመልከቱ።
»» መነኮሳትም፣ ባህታውያኗ፣ አገልጋዮችም፣ ተፈጁ፣ ተሰዉ፣ ተቃጠሉ እንጂ እሷ ማንን ነከች። ጅማ፣
አሰቦት ገዳም፣ ጅጅጋ፣ ሐረር፣ ድሬዳዋ፣ ወለጋ፣ ሁሉም ምስክር ናቸው። ነገ ቅድሚያ በፍርድ
ወንበር የማየው ይህንን ነው፡
ከአህዛብ እምነት ጋር የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያንን እምነት በመደመር የምትወነጅሉ የመንግሥት ተቋማት ነገ
በምንም መልኩ አትታለፉበትም ፈጥናችሁ ታረሙ።
»» ማንኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ ያለ የእምነት ሰው ሊያውቅ የሚገባው ቢኖር መጪው አደጋ ከፊቱ
የተደቀነው ፈታኝ እሳት ቀላል አይደለም።
ከመሪ እስከ ተመሪ ያለ ሁሉ ይፈተሻል ማን ያመልጣል? ማንስ ይሻገራል? አዎ በቀደምቶቹ መልእክቶች
እንደተጠቀሰው ቅን፣ የዋህ፣ ትሁት፣ ፈጣሪውን የሚፈራ ሰው ይሻገራል።
»» ማንኛውም የተዋህዶ እምነት ተከታይ እንደቃሉ እየኖረ መሆኑን ይመርምር።
»» ተመሳስሎ ማለፍ አይቻልም የሚፈትሽህ የሥጋ ዳኛ እንዳይመስልህ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
እንጂ ይህ ምክር በእሳት እያለፉ ለሚወጡት የሚመለከት ነው።

ወጣቶች
› ሴት ወጣቶች እጅግ ታላቅ ቁጣ በእናንተ ላይ ነው ምንዝርናን፣ ቅጥፈትን፣ ውሸትን፣ ሱሪ መወተፍን፣
ራቁት መሄድን እጅግ የከፋውን ሥራ ሁሉ እየሰራችሁ ላላችሁ ለእናንተ የሚመጣው እሳት እጅግ ከባድ ነው።
› ወንዶችም እንዲሁ አመንዛሪ፣ ቀጣፊ፣ ውሸታም፣ ሌባ፣ እናት አባታችሁን የናቃችሁ፣ ታላቅ ማክበርን
የማታውቁ፣ ስለሆናችሁ የእናንተም እጣ በታላቅ እሳት መበጠር ነውና ተዘጋጁበት።
› ተዋህዶ እምነት የምትከተሉ ወጣቶች ለእምነት መቅናት ጥሩ ነው እምነቱን በተግባር መግለጽ ግን
መሰረታዊ ግዴታ ነው። ስለዚህም ከምንዝርና፣ ከውሸት፣ ከሌብነት፣ ከመጥፎ ሱሰኝነት፣ ሰው ከመናቅ፣
ከማዋረድ፣ ከመጥፎ ተግባሮች ሁሉ ራቁ በእምነቱ ስም ንግድ የምታካሂዱ ሁለገብ የእምነት ነጋዴዎች እጣችሁ
እጅግ መጥፎ መሆኑን እወቁ።

30. ማጠቃለያ፡–
ባለአእምሮ ነኝ፣ አስተዋይ ነኝ፣ አዋቂ ነኝ፣ ሁሉንም እምመዝን ነኝ፣ የምትል የሰው ዘር በሙሉ አድምጥ
ስማ። ምድርና ሰማይን የዘረጋ አምላክ ባርያ እኔ የሥላሴ ባርያ ለእናንተ ደግሞ እብዱ፣ በሽተኛው፣ አእምሮውን
የተነካ ነኝ። አዎ ነኝ።
ለንፅፅር የዳዊት መዝ፡ 123(124) ይመልከቱ።
አባቴ ባከበራቸው፣ በወደዳቸው፣ በሾማቸው፣ በቀባቸው፣ አገልጋይ በጎቹ ላይ እስከዛሬ ያላገጣችሁ ሁሌ
በኔ ፊት እንደማትማሩ እንድታውቁ እፈልጋለሁ። ምሕረትን የምትለምኑት ከገፋችኋቸው የልዑል ልጆች ነው።
እነሱ ሲምሩአችሁ እምራለሁ አለበለዚያ እናንተን የበግ ጸሮች አላልፍም እንግዲህ እኔ ይህ ነኝ በየትኛውም
61
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ዓለም ኑር ሂድ የምታገኘው እኔኑ የሥላሴ ባሪያና አገልጋዩን ነው። እምዳኝም እኔው ነኝ በቃ እወቁት
የኢትዮጵያን ክብር እወቁት የእምነት አርበኞቹን አገር እወቁት የብርሃን ፍርድ ምን እንደሚመስል ተረዱት
ባታምኑም እውነቱ ይህ ነው።
ስለኔ በመጠኑ ተረድታችኋል ብዬ እገምታለሁ ስንተያይ ደግሞ ይበልጥ ሁሉም ይገለጣል። ለዘመናትም
በእድሜዬ ስኖር ይህ የአባቴ የፈቃድ ምስጢር በውስጤ ተሸፍኖ ኖሯል። ዛሬ ጫፉን ገልጫለሁ ቀሪውን ድግሞ
በጊዜው ታውቁታላችሁ።
ለንፅፅር መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ መዕ፡ 18 በሙሉ ይመልከቱ
እንግዲህ ይች ለእናንተ ለክፉዎች መጥፋት የምትተጋው ምድርና ባህሪዋ፣ ለልዑል ልጆች፣ ለድንግል
ልጆች፣ ለከበሩ መላእክት ወዳጆች መጥፋት የምትተጋው ምድር ከቅጣት በኋላ ለሁሉም የእግዚአብሔር
በጎች በረከቷን ትሰጣለች። ደስም በሏት ታደረገዋለች። ለሁሉም የልዑል ደስታ ደስታዋ ነውና። ጠላት ደግሞ
ከናንተው ጋር ወደሲኦል መኖሪያው ይካተታል። ምድር ከክፉዎች፣ ከጠማሞች፣ ከተኩላዎች፣ ከቀበሮዎች፣
ከእባብ፣ ከጊንጦች፣ ከዘንዶዎች ትጸዳለች።

31. ትእዛዝ!!
1. አንድ ነገር እናስታውስ በምድሪቱ ሕግ ንጉሥ፣ ፕሬዚዳንት፣ ጠ/ሚኒስትር፣ ጀነራል፣ ሚኒስትር፣
ዳኛ፣ አቃቤ ሕግ ወ.ዘ.ተ. ሁሉም በተሰጠው የስልጣን ክልል የመወሰን አቅም አለው። የወሰነውንም
ውሳኔ ሕጉ በሰጠው የስልጣኑ ክልል ይወስናል። ተፈጻሚም ይሆናል። ያሥራል፣ ይገላል፣ ያሳድዳል፣
ይወርሳል፣ ያሰቃያል፣ ይሰውራል፣ ወዘተ…
መሪም ከሆነ ጦርነት ያውጃል። ታዲያ ማን ስልጣን ሰጠህ ቢባል፣ ሕዝብ መረጠኝ። ባለው ሕገ መንግሥትና
ሕግ በተሰጠኝ ስልጣን ወሰንኩ የሚል መልስ ይሰጣል። የዓለም ገዢ መልሱ ይህ ነው።
ወደኔ ስንመጣ ግን ማን ስልጣን ሰጠህ ስልጣንህስ የት ድረስ ኃይል አለው? የመሳሰለው ጥያቄ ይነሳል።
ዋጋም ተሰጥቶት ላይነሳ ይችላል። ይሁንና ለሚያየው ይህ ነው መልሱ። የኔ ስልጣን ምድርና ሰማይን ከዘረጋው
ፈጣሪ የተሰጠ ነው። እናንተንም በሚነቅል፣ በሚተክል ጌታ የምታመን ነኝ፤ የምጠበቅም ነኝ። ሁሉን የፈጠረ
ጌታ አገልጋይና ባሪያ ነኝ፣ የተወደድኩም ልጁ ነኝ ስለዚህ በስሙ ያመንኩበትን ከሱ የታዘዝኩበትን ሁሉ ትእዛዝ
እገልጽ ዘንድ ስልጣኑ አለኝ። ከእናንተና ከዲያብሎስ አባታችሁ የአገኘሁት ስልጣን አይደለም። ሁላችሁንም
ሁላችንንም ከፈጠረ፣ ከሚሽር፣ ከሚያጸና፣ የሁሉ ፈጣሪ የተሰጠኝ ስልጣንና መብት ነው።
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፡ 43 በሙሉ ለንፅፅር ያንብቡ።

32. በመሆኑም ከዚህ የሚከተለው ትእዛዝ ወጥቷል

2. በቀደሙት ሁለት መልእክቶችና በዚህ በሶስተኛው የአፈጻጸም ውሳኔ የተገለጡት ቅጣቶች በሙሉ
በመላው ዓለም ተፈጻሚ ይሆናሉ። ማንም የሰው ዘር ከዚህ ውሳኔ ውጪ አይሆንም።
ስለዚህ በአባቴ በፈጣሪዬ ስም ይህን ትእዛዝ ተፈጻሚ እንዲሆን እኔም አጽንቼዋለሁ።
3. በፈጣሪዬ ስም አዛለሁ ሁሉም ቅጣቶች ተፈጻሚ ሲሆኑና ሲከናወኑ እኔ የአምላኬን ምሕረትና ፈቃድ
እስካልጠየቅሁ ድረስ እንዳይቋረጡ ወስኜአለሁ። የአምላኬንም ፈቃድ ጠይቄ አስወስኜበታለሁ።
4. መሪም ተመሪም፣ የእምነት መሪም ተመሪም፣ ነገሥታትም የጦር አለቆችም በምድረ ስልጣን
አለን የምትሉ ሁሉ ከአገሬ መሪ ጀምሮ እግዚአብሔር በቀባቸው ልጆቹ ፊት አምናችሁ ዓለምንም

62
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

ቅድመ ሁኔታ እስክትንበረከኩና የፈጣሪን ልጆች ክብር ልክ እስክታውቁ ድረስ ምሕረት አይኖርም፣
የእስትንፋስ ጊዜ የለም፣ የመትረፍ እድል የለም፣ ሞትንም በቀላሉ ማግኘት አይቻልም። ትእቢታችሁ
ሙልጭ ብሎ እስከሚጠፋና ከንቱም መሆናችሁ እስክታውቁ ድረስ መጠኑን እያከበደ የሚሄደው
ጥፋት አይገታም ፈጽሞ ሊያጠፋችሁ ታዟልና።
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፡ 45፡ 9 – 25
5. በማናቸውም የልዑል ልጆች ላይ የሚቃጣ የጥፋት ሀሳብና እቅድ ገና ሲታሰብ የሚጠረግ መሆኑን
የዚህ ሃሳብ አመንጪ፣ አቃጅ፣ አዛዥ ምንም እድል የማይሰጠው መሆኑን በተጨማሪ ተወስኗል።
6. የፈጣሪ ፈቃድ ሐሳብ፣ ትእዛዝ፣ ውሳኔ፣ ምክር ግሳጼ ሁሉም በዚህ የመጨረሻው ሰዓት በኔ በታመነ
አገልጋዩ በባሪያው ተገልጾአል። በመሆኑም አንድም ሳይቀር ተፈጻሚ ይሆናል። እንዲሆንም ታዟል።
7. ማናቸውም ሚዲያዎች፣ ፕሬሶች፣ መጽሔቶች፣ ጋዜጦች፣ ዌብ ሳይቶች፣ ኢንተርኔቶች፣ ፋክሶች
ሁሉም የፕሮፖጋንዳ መሣሪያዎች፣ በመላው ዓለም እራሳቸውን አንሰራፍታችሁ ያላችሁ ሁሉ ይህንን
መልእክት ሳትጨምሩ ሳትቀንሱ አስተላልፉ ለሕዝብም ግልፅ አድርጉ ይህንን የማያደርግ ማንም
ይሁን ማንም በየትኛውም ዓለም ይኑር ፍፁም በእሳት ይበላል። የተረፉትም ለፍርድ ይቀርባሉ።
ያለምሕረትም ቅጣት ይቀጣሉ።
መልእክቱን በአግባቡ ካስተላለፉ ደግሞ ታዘዋልና በምሕረት ይታያሉ።
8. ሁላችሁም የታመናችሁ የአባቴ ልጆች የኢትዮጵያ ተ/ኦ እውነተኛ ልጆች በየትኛውም ዓለም ያላችሁ
የልዑል ልጆች በሙሉ ይህንን ልታውቁ ይገባል።
ሀ/ ከፈጣሪ ጋር የራሳችሁ ግንኙነት እንዳላችሁ አምናለሁ፣ ስለዚህ በሰው ሁሉ ፊት መብራታችሁ የበራ
ይሁን በየእለቱ በቅድስና ተግባራችሁን ተወጡ።
ለ/ ቅን፣ ታማኝ፣ ትሁት፣ ከዓለም ጉድፍ የራቀ፣ ከስሜታዊነት የጸዳ፣ እውነተኛ ሁሉንም በፍቅር የሚያይ
በማናቸውም የሥራ ዘርፍ የተጋ፣ በሁሉም ኃላፊነት የታመነ ሁኑ።
ሐ/ ለፈጣሪዬ ፈቃድ ትእዛዝና ቃል ትጉ፣ አትፍሩ፣ በጠላት ፊት በጥንካሬ ቁሙ።
9. በመላው ዓለም ለምትገኙ የየትኛውም ተዋረድ ባለሥልጣኖች በሙሉ ሁሉም የፖለቲካ መሪዎች
ሁሉም ባለስልጣኖች፣ የሁሉም ዘርፍ የእምነት መሪዎች፣ የጦር አለቆች፣ የፀጥታ ሃላፊዎች፣ ዳኞች፣
ጠበቆች፣ አቃቢ ሕጎች፣ ባለሃብቶች፣ በከፍታም በዝቅታም የምትገኙ የጥፋት ሠራተኞች በሙሉ
ይህ ትእዛዝ ተፈርሞ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የልዑል የቅጣት እጅ በሙሉ ኃይሉ መለቀቁን እናም
እናንተን ማሳደድና ማጥፋት እንደሚጀምር እወቁ። ይህም በልዑል ሥም ታዟል ማንም ሊያመልጥ
አይችልምና። እኔም በአባቴ ስም በፈቃዱ መሠረት አጽንቼዋለሁ።
ለ/ ለጥቂት ጊዜ በሥልጣናችሁ ብትቆዩ እንኳን በዚያው ትዘልቃላችሁ ማለት አይደለም። በተፃራሪው
ማናቸውም የታዘዙ ጥፋቶች ሁሉ በናንተ ላይ ተፈጻሚ እስከሚሆኑ ብቻ ነው።
ሐ/ ከዚህ ትእዛዝ መውጣት እለት ጀምሮ የማንኛውም አገር ባለሥልጣን በየትም ዓለም ያለ ገዥ ሁሉ
ስልጣኑ ከንቱና የማየሰራም ተደረጓል። እንዲሆንም በአባቴ ስምና ፈቃድ መሠረት አጽንቼዋለሁ። ማናቸውም
ኃላፊነትና ሥልጣኖች በሙሉ በየትኛውም የዓለም ክፍል እውንና ዘላቂ ሥልጣን የሚሆነው አባቴ ሲፈቅድ
በስሙም እኔ ባሪያው ትእዛዙን ፈርሜ ወጪ ሳደርግ ብቻ ነው። ከዚያ ውጪ የምድር ባለሥልጣን ሁሉ ሥልጣኑ
በፈጣሪ አምላኬ ትእዛዝ ተሸሮአል። እኔም የልዑል ባሪያ በፈጣሪዬ ፈቃድና ስም መሰረት አጽንቼዋለሁ።

63
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ሦስት

»» በዚህ አፈጻጸምና በቀደሙት መልእክቶች የተጠቀሱት ማናቸውም መቅሰፍቶች ምድር ላይ የሰፈነውን


ጨለማና ስርአቱን ፈጽሞ ጠርገው እሰከሚያጠፋና በምትኩ የፈጣሪ ፈቃድና ትእዛዝ እንዲሁም
ውሳኔና የብርሃን ስርዓት እስከሚሰፍን የሚወርደው የቁጣ እሳትና በትር እንዳይቆም የሰውም ትእቢት
ፈጽሞ እስከሚጠፋ እንዲቀጥል እኔ የልዑል ባርያ፣ የሥላሴ ባርያ፣ የድንግል ባርያ፣ ምድርና ሰማይን
የዘረጋው አባቴ የሠራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔር በሰጠኝ ስልጣንና ኃላፊነት መሠረት በፈቃዱና
በስሙ ተፈጻሚ እንዲሆን እኔም በከበረው ስሙ ወስኜአለሁ።
መ/በአባቴ ስም በልዑል ስም የማጸናው ጊዜያዊም ሆነ ዘላቂ ሹመት ሁሉ በየትኛውም የዓለም ክልል
ተፈጻሚ ይሆናል። ይህ በሚጸናበት ሥፍራ ሁሉ ሁሉም ነገር ሰላም ይሆናል፤ በረከቱን. ቸርነቱን ሁሉ አባቴ
ያፈሳል። በእውነት የፀናች የጌታም የብርሃን አገዛዝ ትሰፍናለች። ከዚህ ውጭ ከፍም ዝቅም የሚል ነገር የለም።
ያኔ ብቻ ነው እጅግ የጤሰውና የነደደው የልዑል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ቁጣ መስከን የሚጀምረው። ከዚህ
ውጪ የሚጨመር የሚቀነስ ነገር የለም።
አበቃ በእርግጥ ተረዱ አበቃ!! ማንም ከላይ ከተጠቀሱት ትእዛዞች ውጭ ሊሆን አይችልም ቢሞክርም
በእሳት ይጠረጋል።
»» አባቴን ፈጣሪዬን ለኔ ሁሉም የሆነውን አምላኬን አመሰግነዋለሁ
»» ለእናቴ ለድንግል በውጣ ውረዱ በሕይወቴ ሁሉ ያልተለየችኝን ከልቤ አመሰግናታለሁ።
»» ለወዳጆቼ እጅግ ለምወዳቸውም ፈጥነው ለሚያደምጡኝ እንደ አይናቸው ብሌን ለሚጠብቁኝ ሊቀ
መላእክት ገብርኤል፣ ሊቀ መልእክት ሚካኤል፣ ሊቀ መላእክት ሩፋኤል፣ ሊቀ መላእክት ፋኑኤል፣
ሊቀ መላእክት ራጉኤል፣ ሊቀ መላእክት ኡራኤል ሊቀ መላእክት ሳቁኤል ለከበሩ የብርሃን መላእክት
ሁሉ ምስጋናዬን ከልብ አፈሳለሁ።
»» ለአባቶቼ፣ ለእናቶቼ፣ ለወንድሞቼ፣ ለእህቶቼ፣ ለልጆቼ የአባታችን፣ የእናታችን የወዳጆቻችን በረከት
ቸርነት፣ ጥበቃ ፈጽሞ አይለያችሁ። የልዑል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ልጆች ጽኑ፤ አይዟችሁ
ይኸው የተጠበቀው ሰዓት ደረሰ፤ በጸሎት በጾም ትጉ ሁሉን ለሚያውቀው አባታችን ሸክማችሁን ሁሉ
ንገሩ አሳርፉ በአመጽ ውስጥ አትግቡ ሥራው ሁሉ የእግዚአብሔር ነውና የሥጋ ድጋፍ አይፈልግም።

የአብርሃም አምላክ፣ የይስሃቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ የባርካችሁ። አሜን።


ከታመነው ከተወደደው የልዑል ባርያና አገልጋይ
ከታመነው የድንግል ልጅ
ከታመነው የከበሩ መላእክቶች ወዳጅ

ተፃፈ ______________
ቀን 19/7/2001 ዓ.ም
አመሰግናለሁ።

64
መልእክትአራት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ቀን፡ 01 – 06 – 2002 ዓ.ም

ለመላው ህዝበ ክርሰቲያን የተዋህዶ ልጆች በሙሉ!!


በተዋህዶ እምነታችሁ በጽናት ለቆማችሁ በመላው ዓለም
ፊት ለተበተናችሁ ሁሉ!!
በዛሬው መልእክት ውስጥ ስለምታገኙት ከማንሳቴ በፊት ላሳስባችሁ የምወደው ጉዳይ አለ፤የእውነተኛይቱ
የተዋህዶ እምነት ከሌላው ሁሉ ከሚለያት እጅግ ብዙ ነገር ዋነኛው በተግባር ሁሌም የሚገለጸው የእምነት
ጽናቷ ነው።
እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያሰርዳ ነው። ለሽማግሌዎች
የተመሰከረላቸው በዚሁ ነውና። ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደተዘጋጁ፣ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት
እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላልን። ዕብራውያን 11፣ 1 – 3
ያለ እምነት ምንም አይነት መንፈሳዊ ትርፍ የለም። እምነትስ ከሌለን እንዴትስ ከእግዚአብሔር የተሰጠንን
ተስፋና ስጦታ እንቀበላለን። እግዚአብሔር የሰጣቸውን ተስፋ አባቶቻችን በእምነት ተቀብለውም አይተውትም
አለፉ በነሱም የእምነት ጽናት ፈጣሪያችን ተደስቶበታል። ያለ እምነት ፈጣሪን ማስደሰት አይቻልምና! ሞትን
የሚያህል እዳ ሄኖክ ሳይቀምስ ያለፈው በእምነቱ ፈጣሪን ስላስደሰተ ብቻ ነው። በታመነው ቸሩ ፈጣሪ ለበጎው
ቀን የታተማችሁ አባቶቼ እናቶቼ፣ ወንድሞቼ እህቶቼ፣ እንዲሁም ልጆቼ፤ ከ4 አመት በላይ የእግዚአብሔርን
ፍርድ፣ ተስፋና ለታመኑ ልጆቹ የሰጠውን ተስፋ በተከታታይ በወጡት መልእክቶች አይታችሁአል። መልእክቶቹ
ሁሉም የሰው ዘር ያምነዋል ተብሎ አልመጣም። ለጥቂቶቹ ለተመረጡት በሥጋ ዐይን የማያዩትን በእምነት
ግን አጥርተው ለሚያዩት የተሰጠ የልዑል ድምጽ ነው። ስለሆነም ነው በዛሬው መልእክቴ መግቢያ በተግባር
ስለሚገለጥ እምነት ላነሳባችሁ የፈለግሁት። (የዛሬውንም የቀደሙትንም መላእክቶች ሁሉ አንብባችሁትም ሆነ
ሳታነቡት አስቀድማችሁ ታላቅ የእምነትን ምንነት አስረጅ የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዕብራውያን
ምዕራፍ 11 በሙሉ አንብቡት)። እጅግ ብዙዎች በመልእክቱ ተሰናክለዋል። በቁጥር ቢያንሱም ጥቂቶች ደግሞ
አትርፈዋል።
ምኞቴ ሁሉም የሰው ዘር በእግዚአብሔር የሚገኘውን በረከትና ሕይወት ቢያተርፍ ነበር። አልሆነም እንጂ!!
በመላው ዓለም ከተበተነው የሰው ዘር ኢትዮጵያውያን የተዋህዶ ልጆች በዚህ የመጨረሻው ፈታኝ ዘመን
ከአባቶቻችን እምነት በረከት በሰነቁት ስንቅ ባለ ድል ሆነዋል። ሌሎች ግን በሥጋ እውቀታቸው፣ በሃብታቸው፣
በጥበባቸው ሲለኩ፣ ሲፈትሹ፣ ሲተነተኑ፣ የተዘጋባቸውን መንፈሳዊ ጥበብ በዲያብሎሳዊ መነጽራቸው ሊያዩ
ሲሞክሩ ተሰናክለው ቀርተዋል። ወገኖቼ በዓለም ዐይን አትዩ እግዚአብሔር በቸራችሁ የእምነት መንፈሳዊ
ዐይን እንጂ! በዚህ መልእክት ብዙ አይነት ትችቶች፣ ስድቦች፣ ሽሙጦችና ቀጥተኛ ተቃውሞዎች ደርሰዋል።
ለእውነታችን መለኪያውም ይኸው ዲያብሎሳዊ ዘመቻ ነው። እንግዲህ የሁሉም ነገር ማብቃት ወደ ጽሁፉ
ስትገቡ ስለምታረጋግጡት፣ ለውሾች ይህንን የብርሃን ተስፋን አብሳሪ ቃል አትበትኑ። የቀደሙት መልእክቶች
ለሁሉም የሆነው የተፈረደበትም ፍርዱን እንዲያውቅ፤ የተጸጸተም በንስሓ እንዲመለስ፣ ባለድሉም በእምነት
ትርፉ ፈጣሪው የቸረውን አስገራሚ ጸጋ ሊያፍስበት ነው። ስለሆነም የልዑል ብሩካን በሁሉም ነገር ዝግጁ
ሁኑ። ጊዜ ስለሌለ መልእክቱን ይደርሰው ዘንድ ይገባል ብላችሁ ላመናችሁበትና ቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ
እንዳሳሰባችሁ ልክ ለየዋህ፣ ቅን ደግ፣ ቸር ለሆነ የእግዚአብሔር ወገን በፍጥነት አድርሱ። ይፍጠን ያልኩት
ጊዜው በማልቁ መሆኑን ተረዱ።

መልካም የመረዳት ንባብ!!


1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አኀዱ አምላክ አሜን

ለመላው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርሰቲያን ልጅ ለሆንክ


ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ
በመላው ዓለም ተበትነህ፣ ከእውነት ጋር ቆመህ፣ በፈጣሪ
ታምነህ፣ ተወደህ፣ ለበጎው ቀን በእግዚአብሔር መንፈስ
ቅዱስ ታትመህ ላለህ ወገኔ በሙሉ።
የዛሬው መልእክቴ ጊዜው በማለቁ፣ ለሕዝበ ክርስቲያን የተዋህዶ ልጆች ማጽናኛ፣ ማበረታቻ፣ የመልእክቱንም
የስርጭት ሁኔታ ለመግለጽ፣ ባገራችን ያለውን መንግሥታችንን በተመለከተ ከፈጣሪ የተላለፈበትን ውሳኔ
ለማሳወቅና ወገኔ የተዋህዶ ልጆች ስለምታደርጉት ዝግጅት ለማሳሰብና ለመምክር የታሰበ ነው።
አባቶቼ፣ እናቶቼ፣ እህቶቼ፣ ወንድሞቼ፣ እንዲሁም ልጆቼ፤ የልዑል ልጆች፣ የድንግል ልጆች፣ የቅዱሳን
መላእክት ወዳጆች፣ የታመናችሁ የተዋህዶ ልጆች፣ ሠላምታዬ ይድረሳችሁ። መልካሙን ቀን በመናፈቅ
በትእግሰት ቆማችሁ፣ በጾም በጸሎት ተግታችሁ፣ ረሀብን፣ ችግርን፣ እሥራትን፣ ስቃይን፣ ማጣትንና
መንከራተትን ታግሳችሁ፣ ለደረሰባችሁ ብርቱ ፈተና ሁሉ እምነታችሁን መመከቻ አድርጋችሁ፣ ለበጎ ቀን
ለዘላለም ለማይጠፋ የእግዚአብሄር ጸጋ፣ የክብር ወራሽ የሆናችሁበትን ክቡር የደሙን ማህተም ተተግናችሁ
ላላችሁ ለጨበጣችሁ ሁሉ!
በተወደደችው፣ በተመረጠችው የተዋህዶ እምነታችሁ ጸንታችሁ ለቆማችሁ ሁሉ! እንዲሁም በዚች የመጨረሻዋ
ሰዓት ከተለያዩ የጥፋት መንገድና እምነት፣ ለሁሉም የሰው ዘር ይደርስ ዘንድ በተላለፈው የልዑል መልእክቶች
ራሳችሁን በመውቀስ በመጸጸት ወደ አባታችሁ ወደ ቸሩ አምላክ እናም ወደ ተወደደችው ሩህሩሁዋ እናታችን
ወደ ቅድሰት ድንግል ወላዲተ አምላክ እቅፍ የተመለሳችሁ ሁሉ! ከክብራችሁ መገለጫ ማማ ከኢትዮጵያ
ጀምሮ በመላው ዓለም ለተበተናችሁ አባቶቼ፣ እናቶቼ፣ ወንድሞቼ፣ እህቶቼ፣ እንዲሁም ልጆቼ በአባታችን
በቸሩ ፈጣሪ በናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም የአክብሮት ሰላምታዬ በድጋሚ ይድረሳችሁ! ባላችሁበት
ሁሉ፣ የአምላካችንና የአባታችን የእግዚአብሔር አብ የእግዚአብሔር ወልድ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
አኀዱ አምላክ ቸርነትና በረከት፣ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የእናትነት ጸጋ፣ በረከትና አማላጅነት፣
የወዳጆቻችን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ
ሩፋኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ራጉኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ኡራኤል፣
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሳቁኤል፣ የሊቀ መላእክት ቅዱስ አፍኒን ጥበቃ፣ ቸርነት፣ ምልጃና የምሕረት ጥላ
ይክበባችሁ እላለሁ!!
በዛሬው መልዕክቴ
1ኛ/የምትጽናኑበትን፣ የምታርሙትን፣ የምታደርጉትን፣ መሰረታዊ ጉዳይ በማንሳት ለመምክር!
2ኛ/ጊዜው በማለቁና በመፈጸሙ ሁለንተናዊ ዝግጅት እንድታደርጉ ለማሳሰብ!
3ኛ/በአሁኑ ሰዓት አገዛዙን አክብዶ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት እድል ፈንታው መጠናቀቁንና ይህንንም
የእግዚአብሔር ወዳጆች እንድታውቁ በዝርዝር ለማሳወቅ የተዘጋጀ የመጨረሻ የመሰናዶ መልእክት ነው።
ወደ ዝርዝር መልእክቶቹ ከመሄዳችን በፈት ጠቅለል ያለ የመግቢያ ማስገንዘቢያዎችን እናንሳ!
ሁላችሁም እንደምታዩትም እንደሰማችሁትም፣ አለማችን ሲመከር ሲዘከር ሲገሰጽም ቆየ፣ ነገር ግን አላደመጠም

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

እንደውም በንቀቱ ዘለቀ፣ ናቀ፣ የጸባኦትን ቃል አቃለለ። በቸርነቱ፣ በፍቅሩ ወሰን ያልተበጀለት አምላክ
በዘረጋለት ምሕረት ላይ አላገጠ። ተወቀሰ አልሰማም፣ ተገሰጸ አልደነገጠም፣ ተመታም ልቡ አልተሰበረም፣
ታዲያ ምን ይደረግ! ሁሌ በፈጣሪ ላይ ታብዮና አላግጦ መኖር አይቻልም። ትዕግስትም፣ ቸርነትም ሁሉ
ማብቂያ አለው። ስለሆነም የግድ የታበየ ልበ ደንዳና የሚገጥመውን እጣ መቅመስ ነው። ዛሬ የምታዩትን
እያያችሁ ነው። ምድር በየሳምነቱ የመንቀጥቀጥ ምልክቱአን እያሳየች ነው። ሲብስም እንደ ሃይቲና እንደ ቻይና
የጥፋት በትርዋን እያሳረፈች ነው።
የካርቦን ልቀት እንቀንሳለን ብለው የተሰበሰቡ 15ሺ ሊቆች፣ የ195 አገር መሪዎችና አጃቢዎች ተሰብስበው
ሲደናቆሩ ሰምተናል። ደቡብና ሰሜን ጫፍ ያለው በረዶ ቀለጠ፣ የምድር ሙቀት ጨመረ እናቁመው ሲሉ
ሰማን፤ ልብ በሉ፣ መልእክት 1.2.3. ምን እንዳሉት እዩት። እነሱ ይህን ብለው ሲመለሱ ልዑል ጠፋብን
ያሉትን በረዶ በቤታቸው ደጅ በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በኤሽያ የ2 ሜትር ከፍታ ያለው በረዶ ከመረላቸው።
ታዲያ ማነው የአየር ንብረቱ ባለቤት! የዲያብሎስ ሊቃውንትና መሪዎች ወይስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
ህሊናው ያልታወረ ያውቃል፣ የተከደነበት ደግሞ በለመደው የዲያብሎስ ቱልቱላ ይደናብራል። የሚደንቀው
ከተሰብሳቢዎቹ ውስጥ አንድም መሪና የአየር ሊቅ ነኝ ባይ የፈጣሪ ተግሳጽና ቁጣ ነው ሲል አልተሰማም፤ከኛው
አገር ጉድ ጀምሮ። ሁሉም ሊቃውንት ትንታኔ ሲሰጡ ሰምተናል፣ ድሆች መሪዎች ደግሞ፣ ዶሮ ብታልም
ጥሬዋን እንዲሉ በዚህ አጋጣሚ ሰፋ ያለ የልመና አኩፋዳ አሰናድተው ይዘው ቢቀርቡም በተስፋ ሰነድ
ብቻ ተመልሰዋል። ምክንያቱም የጌቶቻቸው ቤት እንደድሮው አፍሶ የሚስጥበት አልሆነም። የገንዘብ ምንጭ
መንፎልፎሉ ቀሪና ጭልጭል ይል ጀምሮአል።
ኢዮብ 38፣ 27–30 መጽሐፈ ሄኖክ 16፣ 18– 37
አወቅን በለጸግን፣ ተመነጠቅን የሚሉ ሁሉ ወደ ጨለማ የሚወስዳቸውን ጎዳና ጀምረዋል። ፍጥነቱም ከእንግዲህ
እጅግ ይጨምራል። ከአንዱ እሳት ወንፊት ወደ ሚጠበው የእሳት ወንፊት (በመልእክቶቹ እንደተገለጸው)
እየተሸጋገሩ የተጻፈላቸውን ጎዳና ተያይዘውታል። እኛም በፈጣሪያችን ጉያ ሆነን የሚሆነውን መታዘብ ብቻ
ነው።
ሰለ መልእክቶቹ (1.2.3.) ስርጭትና የት ድረስ እንደሄዱ ብታውቁ መልካም ነው።
በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀው የተሟላው መልእክት፣ ከዚህ ለሚከተሉት አገሮች ኤምባሲዎች፣ በአደራ
እንዲረከቡ ከነሸኚው ተልኮአል። በሸኚው ደብዳቤ ውስጥ የተጠቀሰው ለየተወከሉበት አገር መሪዎች እንዲሰጡና
ህዝባቸውም እድል ፈንታውን እንዲውቅ እንዲያደርጉ ተገልጾላቸዋል። እነማን እነማን ደረሳቸው፣ ከሞላ ጎደል
ከዚህ የሚከተሉት ናቸው።
የተባበሩት መንግሥታት የአውሮፓ ህብረት፣ አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጃፓን፣ ቻይና፣
ራሺያ፣ ስዊዲን፣ ኖርዌይ፣ብራዚል፣ ህንድ፣ ግብጽ፣ ኢራን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አውስትራሊያ፣ ጆርዳን፣ በቀጥታ
ሲደርሳቸው፤ ሳውዲ፣ ስፔን፣ ፖርቹጋል፣ ዱባይ፣ የመን፣ ኦማን፣ ኤሚሬትስ፣ አርጀንቲና፣ ኮስተሪካ፣ ሃየቲ፣
ፍልስጤም፣ ናይጀሪያ፣ ኮሶቮ፣ ቬትናም፣ አልባኒያ፣ መቄዶንያ ኒዘርላንድ ሆንግኮንግ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣
ግሪክ፣ ቤልጂየም፣ ኬኒያ፤ ቆጵሮስ፣ ሰዊዘርላነድ፣ ማሌዥያ፣ ላኦስ፣ እስኮትላንድ፣ ባንግላዴሽ፣ አየርላንድ፣
ኢታሊ፣ ባቲካን፣ ካናዳ፣ ኦስትሬያ፣ ፓኪስታን፣ ለነዚህና ለሌሎችም በተዘዋዋሪ እንዲደርሳቸው ተደርጎአል።
ከ30 የማያንሱ የታወቁ በአውሮፓ፣ በኤሽያ፣ በአሜሪካ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ያሉ የእምነትና የሙያ
ዩኒቨርስቲዎች፣ ሚዲየዎች፣ ፕሬሶች(ጋዜጣና መጽሔቶች) በኢሜል አድራሻቸው ደርሶአቸዋል። ከነዚህም ዋና
ዋናዎቹን ለመጥቀስ፤

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ሲ. ኤን. ኤን፣ ፕሬስ ቲቪ፣ ቢቢሲ፣ ዘ ኢኮኖሚስት፣ ኒውስ ዊክ፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ሚድል ኢስት
ጆርናል፣ ሚድያ ሱልጣን፣ ደቡብ ቻይና ሞርኒንግ ፖስት፣ ኔት ዎርዝ፣ የመሳሰሉ መጽሄቶች፣ ጆርጅ ታውን
ዩኒቨርሲቲ፣ ኢንተርናሽናል ስኩል ኦፍ ብሬመን (ጀርመን)
ከዩኒቨርሲቲዎች፡– ሴንት ሜሪ ዩኒቨርሲቲ (ካቶሊክ)፣ ብሪቲሽ ስኩል ዋሽንግተን፣ አከስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፣
ግሎባል ሄድ ኦፍ ሴኪዩሪቲ፣ ሴንትራል ኢሮፕያን ዩኒቨርሲቲ፣ አቴንስ ዩኒቨርሲቲ፣ ብሪቲሽ ኮሎምቢያ (ፓስፊክ
ኢንስቲቲዩት ፎር ክላይሜት ሶሉሽን)፣አውስትራሊያ ኢንብሩክ ዩኒቨርሲቲ፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፔንስልቫኒያ፣
እና ሌሎችም።
ከላይ በከፊል የተዘረዘሩትን አገሮች፣ ተቋሞች፣ ሚዲያዎች፣ ፕሬሶች፣ መጽሔቶች፣ ዩኒቨርሲቲዎች
ደርሱአቸው እኔም መድረሱን አረጋግጬ፣ እነሱም ሰምተው ንቀው ትተውታል።
አንድ መጽሔት ብቻ እሱም ዘኢኮኖሚሰት የተባለ አርሞ ቀነሶ ጨምሮ ለማውጣት ፈቀድ ቢጠይቀኝም
የእግዚአብሔር ትእዛዝ አይለወጥም አይሻሻልም ብዬ ቋንቋና የቋንቋ አጠቃቀሙን ብቻ ማስተካከል እንደሚችል
በአክብሮት ገልጨለታለሁ።
ይህ ሁሉ የተበተነው በኔ በኩል ቢሆንም ሌሎች ወንድሞቼና እህቶቼ እንዲሁም በተዋህዶ እምነታቸው
የጠነከሩ አባቶች እናቶችና ወጣቶች እጅግ በብዙ እንዲሰራጭ አድርገዋል። 2/3 ኛው የዓለም ክልል ደርሶታል
ማለት ይቻላል። በመልእክቱ ስርጭት አብዝታችሁ ለደከማችሁ ወንድሞቼና እህቶቼ እንዲሁም ወጣት ልጆቼ
እግዚአብሔር ይባርካችሁ፣ የበጎውን ቀን ወራሽ የድርጋችሁ። አይዙአችሁ እንሆ ጊዜው ተጠናቆአል።
የአገሬ መሪዎች ስለ መልዕክቱ ምን ያህል ያውቃሉ፤ ባጭሩ ሁሉም መልእክት ደርሱአቸዋል። በሚገባም
ያውቃሉ። መልእክት አንድም በመረጃ ሰረተኞቻቸው፣ መልእክት 2ን አማርኛና እነግሊዝኛውን በቀጥታ
ለራሳቸው ለጠቅለይ ሚኒስትር፣ 133 ገጽ ያቀፈውን ሙሉ መልእክት አማርኛውንም እንግሊዝኛውንም እንዲሁ
በቀጥታ ለጠቅላይ ሚኒስትር የደረሳቸው ሲሆን ይህ መልእክት ለህዝበ ክርስቲያኑ ሲሰራጭ ደግሞ ለጠቅላይ
ሚኒስትራችን በዚሁ መልእክት ውስጥ የምታዩትን 3ኛ ደብዳቤ እንዲደርሳቸው ተደርጎአል።
ባጠቃላይ ይህ ለህዝበ ክርስቲያኑ የተዘጋጀ መካሪ፣ አበረታች፣ አዘጋጅና ስለ ወቅቱ አመላካች መልእክት
ስታገኙ ለመንግሥትም የሄዱትን ሸኚ ደብዳቤዎች በሙሉ ታገኙታላችሁ።
እንግዲህ ልብ ልትሉ የሚገባው በግሌም ሆነ በወንድሞቼና እህቶቼ በኩል ከ4 ዓመት ጀምሮ ማለትም
ከ1998 ኅዳር 7 ጀምሮ ለመላው የሰው ዘር የፈጣሪን ፍርድ በተከታታይ ሳሳውቅ ስናሳውቅ ቆይተናል።
ሁሉንም ሂደት እንደተረዳችሁት ይህንን እውነትና የፈጣሪ ፍርድ አንድም መንግሥት፣ አንድም ድርጅት፣
ወይም ሚዲያ፣ ወይም ፕሬስ ትንፍሽ አላለም። በኛ አገር ያልደረሰው የለም (ድርጅት፣ ሚዲያ፣ ግለሰብ፣
መንግሥት፣ የሃይማኖት ተቋም ወዘተ…) ሁሉም ተዳርሱአል። ስለዲያብሎስነታቸው ታዲያ ከዚህ የበለጠ ምን
ማስረጃ ያስፈልጋል።
በቤተ ክርስቲያናችን ያሉትስ! በራሳችን የተዋህዶ ቤታችን ተኮልኩለው በዘመኑ አጠራር ኦርቶ ጴንጤ፣
ጸጋ፣ ቅባት፣ የሚል ስውር ማጥቂያ ይዘው በኛው የእምነት ቋንቋ እየማሉ እንደ ምስጥ የእምነት መሰረታችንን
የሚቦረቡሩ የዲያብሎስ የውስጥ አርበኞች ሆነው ህዝበ ክርስቲያኑን ከአባቶች መንገድ ሊያወጡ እየደከሙ ያሉ
አሉ።
የተዋህዶ እምነታችን የራሷ ቀኖና፣ የራሷ ስርአተ ቤተ ክርስቲያን፣ ስርአተ አምልኮ ያላት ናት። የማስተማር
ስርአቷ፣ የዜማ ስርአቷ፣ የአምልኮ ስርአቷ፣ የአጽዋማት ሰርአቷ፣ የመዘከርና የበአላት አከባበር ስርአቷ ሁሉ
በአባቶቻችን ያልተቋረጠ የእምነት ትግል የተገነባ ነው። ታዲያ ለጥፋቷ የሚዘምቱና የሚሠሩ ከውጪ ያሉ
ብቻ አይደሉም፣ ነገር ግን የበግ ለምድ ለብሰው በራስዋ ቋንቋ እየማሉ ከውስጥ ሆነው የሚቦረቡሩ ሆኑ እንጂ!

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

እነዚህንም የበግ ለምድ ለባሾች በዚህ መልክ እራሳቸውን ሲገልጡ ታውቋቸዋላችሁ። ያሬዳዊ ዜማችንን ሲያጠፉ፣
ትውፊታችንን ሲያናንቁና ሲጥሉ ሲሽሩም፣ የአምልኮ ስርአቱን ሲንዱ፣ አጽዋማትን ስያበላሹ፣ የበአላት አከባበርን
እንደ ኋላ ቀርነት ሲቆጥሩ፣ የአባቶቻችንን ድንበር ሲያፈርሱ ታገኙዋቸዋላችሁ። ከዚህም በላይ በእምነቱ ቤት
የሚያገለግሉት የሚኖሩት ለእምነቱ ከፈጣሪ ለሚገኘው በረከትና ሕይወት ሳይሆን ከአገልግሎቱ ለሚገኝ የሥጋ
ትርፍ (ሳንቲም) ብቻ ነው። እነዚህንም ሳንቲም በወደቀበት ከክብራቸው ወድቀው ሲያንሱ ታዩዋቸዋላችሁ።
ለመሆኑ የትኞቹ አባቶቻችን ናቸው ለገንዘብና ለሆዳቸው ሲሉ፣ ቃሉን፣ ዜማውን፣ ትምህርቱን ሲቸረችሩ
የነበሩ፣ ትምህርቱን፣ ዜማውን፣ ዝማሬውን፣ ከሚወዱትና ከታመኑለት አምላክ የሚመጣውን ወቀሳም ሆነ
በረከት እንዲሁም የፍርድ ቃል ሁሉንም ስለራሳቸው ሥጋ ሳይጨነቁ በነጻ ያገለግሉ አልነበረም፤ እራሳቸውን
ጎድተው ተርበው፣ ተንከራተው ሰመያዊውን ዋጋ በመናፈቅ አልነበረም ወይ የእንግድነት ዘመናቸውን የከደኑት፤
የቱን ሕንጻ ገነቡ፣ የቱን መኪና፣ አሽከረከሩ፣ የቱንስ የጣፈጠ ምግብ በሉ፣ ሁሌ ተረበው፣ ምኔም ተንከራተው፣
አይደለም እንዴ ለዛሬው ዓለምን ያስደመመና ያስገረመ የእምነታቸውን በረከት ያተረፉልን።
ዛሬ ግን የሚያስደንቁ ሰዎች ተፈጥረዋል። ደፋሮች ናቸው። በልዑል ደም ላይ ይረማመዳሉ። መዳኛቸውን
መነገጃ አድርገዋል። የተሰጣቸውን አንደበትና ልሳን ለንግድ ለሥጋ ትርፍ አውለውታል። በርግጥ አይብሉ
አይባልም ለእለት ኑሮአቸው አይድከሙ ማለት አይቻልም፤ የሚኖሩት ለእምነታቸው ከሆነ የእለቱን እንጀራ
ከሸፈኑ በበቃቸው ነበር። እነሱ ግን ፍፁም ለንግድ አውለውታል። ቃሉን እንደ ሸቀጥ እየቆነጠሩ ቁጥር 1፣
ቁጥር 2 እያሉ የማያቋርጥ የፋብሪካ ምርት የሚያወጡ ይመስላሉ።
በግሌ ከልዑል የተላከን መልእክት የላኩላቸው በአሁኑ ሰዓት ታዋቂ ሰባኪያን የሚባሉ ናቸው ለአገልግሎታቸው
ክብር ሰጥቼ በቀድሚያ ነበር ሙሉውን መልእክት የላኩላቸው። ተደስተው የተቀበሉ እንዳሉ ሁሉ ከስውር
የጥፋት ስምሪታቸው ጋር የተጋጨባቸው ደግሞ በመልእክቱ ላይ ያልተገባ ነቀፋና ትችት ሲሰነዝሩ ተሰምተዋል።
እኔ ግድ የለኝም ለግሌም ለሚደርሰው ጉዳት ምንም ስፍራ አልሰጥም፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ታዝዤ
ላስተላለፍኩት መልእክቶች ሁሉ እሚከፈለውን ዋጋ ልከፍልበት ስለሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ እመወደው
በእግዚአብሔር ሥራ ላይ እንቅፋት እንፈጥራለን ብላችሁ ለምትደክሙ ሁሉ ሰዓቱ ስለተፈጸመ ዋጋ መክፈላችሁ
ማይቀር ይሆናል። 133 ገጽ የያዘውን መልእክት በነጻ ስሰጣችሁ፣ በአክብሮት በፖስታ ታሽጎ ለመምህር እከሌ
እያልኩ ነበር። አክብረው ለተቀበሉት አክብሮቴን አየገለጽሁ ለአላጋጮቹ ደግሞ የልዑልን ፍርድ በትዕግስት
ጠብቁ እላለሁ። እኛ ከራሳችን አንናገርም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንደመከረን፣ በአንደበታችንና በልባችን
ፈቃዱን እንዳኖረ መጠን እንጂ!!
ለሁሉም የሚናገሩትን ስሙ፣ ክፉውን ጣሉ በጎውን ጨብጡ፤ እነሱ ለሥጋቸው ይድከሙ፤ እናንተ በእግዚአብሔር
ጸጋ የሚጠቅመውን ያዙ፤ ምንጊዜም ከመንገድ የወጣውን ጣሉ። ራሳችሁን፣ ቤተ ክርስቲያናችሁን፣ የጸናች
የተዋህዶ እምነታችሁን ጠብቁ።
በዚህ አጋጣሚ የእግዚአብሔር ባርኮት የሚገባቸው አሉ። ምንም እንኳን በውስጣቸው የተለያየ አላማ
ያነገቡ፣ ከጠላት ሰፈርም ከማህበሮቹም የተቀደሰ ተግባር ውስጥ እግራቸውን የተከሉ፣ ሁለት ዛፍ ላይ እንደ
መውጣት ያህል እንደአንጋሬ የተወጠሩ ቢኖሩም (በውስጣቸው ያሉ ቅኖች ይበዛሉና) እንደ ማህበረ ቅዱሳን፣
የሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ የጽዋ ማህበራት፣ እንዲሁም የተለየዩ መንፈሳዊ ማህበራት ሁሉ እግዚአብሔር
ይባርካችሁ፣ የአባቶቻችን የእምነት ጽናት ያላብሳችሁ እያልኩ በውስጥም በውጪም ያለ የከፋ የዲያብሎስ
ውጊያ ቢበረታባችሁ ማብቂያው ላይ ናችሁና አይዞአችሁ እላለሁ።
እንዲሁም ለጸናች የተዋህዶ እምነት በጽናት የቆማችሁ፡– አባቶቼ፣ እውነተኛ ባህታውያን፣ በየበረሃው
የወደቃችሁና የምትንከራተቱ መነኮሳት፣ ከዘመኑ የዲያብሎስ አሽከርነት ራሳችሁን በማራቃችሁ ተገልላችሁ፣
ተገፍታችሁ፣ በእንክርት የምትገኙ፣ በከፍታም በዝቅታም ያላችሁ እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

እግዚአብሔር ይባርካችሁ። ቸሩ አምላክ ለበጎው ቀን ያተማችሁ ናችሁና አይዞአችሁ፤ ወጣት የተዋህዶ እምነት
አርበኞች በርቱ፤ ዘወትር በልዑል ቅዱስ መንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ። እኔም አጠገባችሁ ነኝ። ከወንድሞቼና
ከእህቶቼ ጋር በመሃላችሁ አለሁ። ሁሉንም እያየሁ እየታዘብኩ ነው። ደስም ይበላችሁ፣ ሁሉ አልቋልና፣
አብቅቶ አገራችን ኢትዮጵያና ቅን፣ የዋህ፣ ትሁት፣ ልጆቿ ወደ ብርሃን ይሻገሩ ዘንድ ታዟል። ይህም ላለው
መንግሥት ተገልጾለታል። እኛም ለመጨረሻው ሰዓት በጥፍራችን ቆመናል።
በዋናው መልእክት እንደተረዳችሁት ዓለም ዋሾ ቀጣፊ አታለይ የዲያብሎስ ቀጥተኛ አገልጋይ መሆኗን
መስክራለች። መልእክቶቹ የደረሳቸው አገሮች በንቀት ተሞልተው ዛሬም ሶዶምን በህጋቸው እያጸደቁ ነው።
የቅርቦቹን እነ ህንድን መጥቀስ ይቻላል። ይህ ዓለም ምን ያህል እንደ በሸቀጠ ልትረዱ ትችላላችሁ። በጥቅሉ
ከተወሰነ ሰው በስተቀር የሚበዛው እዛው በጭለማ እየዳከረ በአመጽ ገፍቶ የቁጣው እሳት እስከሚበላው እየጠበቀ
ይገኛል።
በመጀመሪያው ገጽ እንደ ገለጽኩት በዚህ መልዕክቴ 3 መሰረታዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ የታሰበ ሲሆን
በአንደኛው ተራ ሰለተጠቀሰው ብናነሳ፣
ሀ/ ሁላችሁም እንደምትረዱት የተዋህዶ እምነታችንን ከሁሉ የሚለያት ልጆቿ ዘወትር በእግዚአብሔር ሕግ
እየተደሰቱ፣ በቅድስና ሕይወት ተሞልተው በዜማው፣ በዝማሬው፣ በማህሌት፣ በወረቡ፣ በቅኔው ረክተው፤
በአምላካቸው በረከት እረስርሰው፣ ትሁት፣ ደግ፣ ቅን፣ የዋህ፣ በሆነ የየእለት ሕይወታቸው፤ አምላካቸውን
መስክረው፣ እውነታቸውን አንግሰው፣ ሃሰትን አርቀው፣ ለበጎ ሥራ ተግተው፤ ቅድስናን ከሚያጎድፍ
ሕይወትንም ከሚያጠፋ ሃጢአት እርቀው፣ ሌብነትን፣ ውሸትን፡ በሃሰት መመስከርን፣ ንቀት ጥላቻን፣ አባት
እናት ያለማክበርን፣ ወንድምን መጥላትን የመሳሰለውን የኃጢአት አዝመራ፣ ከልባቸው ነቅለው እንዲጓዙ
ከአባቶቿ ጀምሮ እያስተማረች ያለች ቤተ ክርስቲያን ናት። ስለዚህ ለበጎ ቀን የታተማችሁበትን ቅዱስ መንፈስ
ከሚያሳዝን ተግባር እርቃችሁ፣ በንስሓ ተፈውሳችሁ፣ በፊታችሁ ለቀረበው በረከት ልትዘጋጁ ይገባል።
ጌታ በእናንተ የሕይወት ምስክርነት በፊቱ በብርሃንነት ልትመላለሱ ወዶአችኋል። አገራችን ኢትዮጵያን
የዙፋኑ ማረፊያ፣ የስሙ መመስገኛ፣ የበረከቱ መፍሰሻ ምንጭ ትሆን ዘንድ ወዷል። ከዓለም ሁሉ አብልጦ
ወደዳችሁ፤ የሚወዳትን እናቱን ለእናንተ እናት ትሁናችሁ አለ። ሚካኤልን፣ ገብርኤልን፣ ሩፋኤልን፣ ፋኑኤልን፣
የሁላችሁም ጋሻና የበረከት መፍስሻ አደረገ።
በፍፁም ልባችሁ፣ በፍፁም ሃሳባችሁ፣ በፍፁም ነፍሳችሁ አምላካችሁን ውደዱ፤ በምልጃዋ ከዚህ
ያደረሰቻችሁን ድንግልን ውደዱ፤ በሕይወት ትኖሩ ዘንድ፣ በምልጃው፣ በጥበቃው የረዷችሁን ቅዱሳን
መላእክትን እነ ገብርኤልን፣ እነ ሚካኤልን፣ እነ ሩፋኤልን፣ እነ ፋኑኤልን፣ እነ ራጉኤልን፣ እነ ኡራኤልን ውደዱ
አክብሩም። ዓለምን አትምሰሉ ከእርኩሰት ሥራቸው ራቁ፤ በተለያየ የሥጋ ትርፍ እየተደለላችሁ ለዲያብሎስ
ካደሩ የጨለማ ሰራተኞች ጋር አትተባበሩ፤ ሁለት እግር ስላላችሁ ሁለት ዛፍ ልትወጡ አትችሉምና ወደ
ፈጣሪያችሁ ብቻ አስቡ።
ዛሬ በአገራችን ያለው ስርዓት ፍፁም ዲያብሎስን ያነገሠ ነው። የመናፍቅ፣ የተረት አማኞች ጠበቃ ነው።
ጥንቆላን ኮከብ ቆጠራን ልዩ ልዩ ትብተባን ያጎለመሰና በዚያም የሚገለገል ነው። ታዲያ ከዚህ ስርዓት ጋር ወግኖ
ነገ ደግሞ የእግዚአብሔርን ቀን አገኛለሁ ማለት ከንቱ ዘዴና ምኞት ነው። ዲያብሎስ እጅና እግሩ ሲቆረጥና
ሲጣል፣ ሰራዊቱም አብሮ ይወገዳል ይጠፋል።
ምሳሌ ላንሳላችሁ መንግሥታችን ዛሬ ምርጫ እያለ ይዳክራል፣ የዚህም ምርጫ መራጭ፣ ተመራጭ፣
አስመራጭ፣ ታዘቢ፣ጠባቂ፣ አስፈጻሚ መሪውም ሁሉ የሚደክሙት ለማነው። የሚለፉት የትኛውን ስርዓት
ለማጽናት ነው። አዎን የጨለማውን ስርዓት። የዲያብሎስን ስርዓት ለማንገስ ነው። ከዚህ የዘለለ ምንም
ተግባር የላቸውም፤ ታዲያ ከዚህ የጨለማ ሥራ ጋር እግዚአብሔር ምን ግኑኝነት አለው። እግዚአብሔርን
6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

የሚሹ፣ በእምነት፣ በጽናት ፈጣሪ የገባላቸውን የተረጋገጠ ተስፋ የቀኑን መድረስ በመናፈቅ፣ የሱን ብርሃናዊ
መንግሥት በጉጉት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ እንጂ በጨለማው አሰራርና የዲያብሎስ የውሸት ተውኔትና ድራማ
እየተጠለፉ፣ በፍርፋሪ እየተደለሉ አይወድቁም። የእግዚአብሔር ሕዝቦች ምርጫቸው እነሱ የሚወዱት እሱም
የሚወዳቸው ቸሩ ፈጣሪ ሊያቆምላቸው የወሰነውን የራሱን ብርሃናዊ አገዛዙን እንጂ፤ ሲፈጫቸው ሲቆላቸው
ለጥቂቶች የዲያብሎስ ውላጆች ቆሞ ሲያሰቃያቸው የኖረውን የጨለማ አገዛዝ አይደለም።
ዲያብሎስ እኮ ትላንት ያያችሁትን የጨለማ ስርዓት በምርጫ ተብዬ የዲሞክራሲ ድራማ መልሶ ለመጫን
ነው የህልም እሩጫ የያዘው። ያ ዘዴ ለረጅም፣ በሺዎች ለተቆጠሩ ዘመናት የእግዚአብሔርን ሕዝብ ሲፈጭበት
ሲቆላበት ኖሯል። ዛሬ ያ ዘመን ዳግም ላይታይ ሞቶ ሊቀበር በልዑል አምላካችን ተወስኖአል። ቅድሚያ የብርሃን
ክብርንና ነጻነትዋን ከመላው ዓለም ካሉ አገሮች ቀድማ ትጎናጸፍ ዘንድ ኢትዮጵያ ታሰበች። ከመልእክቱ
እንደምትረዱት ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ የልዑል አገዛዝ የዙፋኑ ማረፊያ እንድትሆን የተመረጠች በመሆኑ
በቀጣዩ ነጻ ለሚወጡ አገሮችና፣ ሕዝቦች መሰብሰቢያ፣ መደራጃ፣ ሙሉ መንፈሳዊና ሥጋዊ አመራር
ማግኛ ስለምትሆን ያለው የአሁኑ መንግሰት መንግሥታዊ አሰተዳደሩን በልዑል ለተቀቡና ለተሾሙ ሕዝቦች
እንዲያስረክብ ተወስኖአል። የኢትዮጵያ ወደ ብርሃናዊ ክብርዋ መምጣት፣ ለዓለም ደግሞ የሚጠፋው ጠፍቶ
የሚቀረው ቀርቶ ወደ ለዑል በረከትና ጉያ የመሰብሰቡ ምልክት ይሆናል። ዲያብሎስ ለዘመናት የዘረጋውን
የጨለማ ዘመን ለማቆየት ቢያልምም ያ ምኞት እንጂ ከእንግዲህ እውን አይሆንም። የሱ ዘመን ተፈጽሞአል።
በመጨረሻው ሰዓት ከሱ ጋር መወገን ራስን በፈቃድ የማጥፋት ያህል ነው። ለመጪው የብርሃን ዘመን ሳይደርሱ
ከሚቆረጡት እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። ምክርን ብትንቁ ነገ ዋጋ መክፈላችሁ አይቀርምና! ባለቀና በተጠናቀቀ
ሰዓት ከሚጠፉ ጋር መሆን አብሮ ለመጥፋት ብቻ ነው።
የጊዜን ማብቃት ያልተረዱ በሆዳቸው ብቻ የሚያስቡ አንድ ተረት በሚገባ ይገለጽላቸዋል፤ ተረቱም፡
– አንድ እድሜ የጠገበ ጅብ ሁለት ልጆች ነበሩት፣ የአንደኛው ልጁ ስሙ መንሾለላ ሲባል የሁለተኛው
ልጁ ስም ደግሞ መዝሩጥ ይባላል። ታደያ ከእለታት ባንዱ ቀን አያ ጅቦ ሁለቱንም ልጆቹን ይዞ ምግቡን
ሲፈልግ ሳይቀናው ቀይቶ ሌሊቱ ተጋመሶ ከቆየ በኋላ አንድ ጌታው የረሳውን አህያ በጫካ ያገኛሉ። ይህንኑ
አህያ ተጋግዘው ይጥሉታል። ሶስቱም ሊበሉ ሲቀርቡ አባት ጅብ የለም ወደያ ፈቀቅ በሉ አህያውን መስባትና
ያለመስባት ልይ ብሎ ብቻውን ይበላ ጀመር ልጆቹም አባታችን ለኛም እንብላ እንጂ ቢሉት ቆዩ ስባቱን እያየሁ
ነው ካለ በኋላ ለመንሾለላ አንድ ጆሮ ወረወረለት። ለመዝሩጥ ግን ፍፁም ከለከለው። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ
መንጋት ጀመረ። ሁለቱም ልጆች ስለሰጉ አባታችን ነጋ እኮ እንሂድ አሉት። አባት ጅብ መብሉ ስለጣመው
ዝም በሉ የጨረቃን ንጋትና የአህያን ስባት የማውቀው እኔ ነኝ በማለት ማሳሰቢያቸውን ናቀ። እንደተፈራው
አልቀረም የአህያው ባለቤት ጎረቤቶቹን አሰባስቦ ጦርና መጥረቢያ ይዞ ሲፈልግ፣ እጅግ ሆዱ የከበደ ጅብ
በአህያው ላይ ተከምሮ ሲነጭ ደረሰ። በሁኔታው የደነገጡት ሁለት ልጆች በሩጫ ተፈተለኩ። አባት ጅብ አደጋ
ውሰጥ መውደቁን ሲያውቅ ልጆቹን እንዲህ እያለ መጣራት ጀመረ። ልጄ አድነኝ መንሾሎላ ሲል ልጅ ደግሞ
አባቴ ምን ሰጠከኝ ከአንድ ጆሮ ሌላ ብሎት ገሰገሰ። አድነኝ ልጄ መዝሩጥ ብሎ ሁለተኛ ልጁን ተጣራ ልጁም
አባቴ እንደበላህ እሩጥ ብሎት አመለጠ። ሆዳሙ አባት ብቻውን ሲጎስር ብቻውን በመጥረቢያ ተቀጥቅጦ ሞተ።
ይህን ምሳሌ በከንቱ አለነሳሁም። ለዛሬዎቹ አልነጋም ባዮች እጣቸው ይኸው እንደሆነ ስለሚያሳይ ነው።
በሆዳቸው የሚያስቡ በሰፊው ዘርግተዋል፣ የሚጠፋውን ዲያብሎስ ተመክተዋል። አለቅጥም ደረጅተዋል።
አሁን ድንገት ሰዓቱ አለቀ፤ ብርሃን መጣ ጨለማው ሊገፈፍ ነው። ያልበሉት የበይ ተመልካች የሆኑት ቀድመው
አመለጡ፤ነገር ግን ደርጅተው የከበዱት የጨለማውን ስርዓት ተስፋ የደረጉት አሁንም እዛው ባሉበት ናቸው።
መጨረሻውንም እነሆ ሳይርቅ ልናየው ነው።
ስለዚህ የብርሃን ልጆች ከጨለማው ውጡ ራቁ፤ ከእንግዲህ በኢትዮጵያ የሚጸናው አንድ እምነት እስዋም
በልዑል ፊት የከበረች ተዋህዶ፣ የተለያየ ቀለም፣ ቋንቋ ያለው አንድ ሕዝብ፤ አንድ ጌታ እግዚአብሔር አብ
7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ፤ አንድ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም
ወላዲተ አምላክ፤ የከበሩ ተራዳኢ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣
ቅዱስ ፋኑኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ኡራኤል፣ ቅዱስ ሳቁኤል፣ ቅዱስ አፍኒን ምድራችን በዚህ መልክ
እጅግ በረቀቀው የእግዚአብሔር ጥበብና በረከት ጸጋም ትከበባለች።
ለ/ ጊዜው ማለቁን ከላይ ገልጫለሁ። ለመንግሥታችን በተላከው ደብዳቤ ላይ እንደተገለጸው የጊዜ ገደብም
አልፎበታል። በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ይህ ያለው መንግሥት ራሱንና ስርአቱን በእግዚአብሔር ለተቀቡ
እንዲያሰረክብ የሚገልጽ ደብዳቤ ተልኮለታል። ደብዳቤውንም ከዚህ መልእክት ጋር ተያይዞ ታገኙታላችሁ።
ስለሆነም ምን ዝግጅት ማድረግ አለባችሁ።
ከላይ እንደ ገለጽኩላችሁ ራሳችሁን በቅድስና፣ በጽናት ከመጠበቅ አልፋችሁ ከዚህ እንደሚከተለው ልታደርጉ
ይገባችኋል። ይህ ትእዛዝ እውነተኛ የተዋህዶ እምነት ላላቸው ላገራቸውም ለህዝባቸውም ቀናኢ ለሆኑ ብቻ
ነው የሚመለከተው።
… መናፍቃንን በጥንቃቄ ለይታችሁ እወቁ፣ አድራሻቸውን፣ ተግባራቸውን በምንፍቅናቸውም ሆነ
በሥራቸው ዙሪያ በቂ የአድራሻ ሰነድ፣ ማንኛውንም የጥፋታቸውን ርቀት የሚገልጽ ሁሉንም ማስረጃ ያዙ፣
በጥንቃቄ አኑሩ፣ በተለይ በዋናነት ያሉትን በጥንቃቄ አጥኑ። በክረት የሚታወቁትን ተረት አማኞችንም እንዲሁ
በተመሳሳይ መንገድ አጥኑ።
… በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ታላቅ ጥፋት በማድረስ ላይ ያሉትን ኦርቶ ጴንጤን (ተሐድሶ)፣ ጸጋ፣ ቅባት
የሚባሉትን ለይታችሁ እወቁ፤ በማናቸውም እነሱን የተመለከተ ማስረጃ ሁሉ ጨብጡ፣ እንዲሁም ለእምነቱ
ሳይሆን ለፖለቲካ ተልእኮ ያደሩ የበግ ለምድ ለባሾችን በሚገባ ለይታችሁ እወቁ፤ የዘር ልክፍተኞችን፣
ዘራፊዎችን፣ አገሪቱንና እምነታችንን ከማናቸውም መሰረት ተነስተው የሚጠሉና ሀብትና ንብረቷ ላይ ግን
እጅግ የሰለጠኑትን በሚገባ አጥርታችሁ እወቁ።
… ለጨለማው ስርዓት እጅና እግር እንዲሁም መረማመጃው የሆኑትን ሁሉ በሚገባ እወቁአቸው።
… በመላ አገሪቱ የተንሰራፉ የጥንቆላ፣ የቃልቻ፣ ተብታቢ፣ የኮከብ ቆጣሪ ሁሉ በሚገባ ለይታችሁ
መዝግባችሁ ያዙ።
… ከዚህ በተረፈ ለመጪው መልካም ጊዜ የሚረዱ ማናቸውንም ማስረጃ ሳትንቁ በአግባቡ ያዙ።
… በማናቸውም መልኩ ወደ ኃይልና እርምጃ አትሂዱ በነገር ሁሉ ታጋሽ ሁኑ ራሳችሁን ግዙ።
ሆኖም በክፋት ተጭነው ያወጡትን ሕግ ረግጠው ለመጡ ለስንፍናቸው የሚመጥን ዝግጅትና መልስ
ይኑራችሁ።
ጠቢቡ ሰለሞን፣ ሰነፍ ያወቀ እንዳይመስለው እንደስንፍናው መልስለት ይላልና።
ሐ/ ያለው መንግሥት እድል ፈንታ ምን ይመስላል።
በዛሬው መላእክቴ፣ ዋናው ነጥብ የሆነው፣ በዚህ ወቅት ያለው መንግሰት እጣ ፈንታና የእድሜ ጉዳይ
መታወቁ ነው።
በታሪክ እንደምንረዳው ሆነ ከእግዚአብሔር ቃል እንዳወቅነው፣ በእግዚአብሔር ቃል ሲመራ በልዑልም
ፈቃድ መሪውን ሲለውጥ፣ ሲያጸናም የታየው የእስራኤል ሕዝብ ነው። እግዚአብሔር ለዓለም ሁሉ፣ ስለ
መንፈሳዊ ትምህርት፣ እምነት፣ ተጋድሎ፣ ስለ እግዚአብሔር ፍቅር፣ ስለ አምላካችን ማንነት፣ ስለ ፈቃዱ፣
ግሳጼም ሆነ ቁጣው ምን እንደሚመስል፣ ታላቅ አስተምህሮን ለመለው ዓለም ያስጨበጠው፣ በእስራኤል
ሕዝብና በተጎራባች አገሮች የውደቅ ተነሳ ጉዞአቸው አማካኝነት ነው። በእርግጥ ከልዑል ፈቃድ የወጣ ምንም
8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ዓይነት የዓለም ክስተት የለም አይኖርምም። ሁሉም በእርሱ ህልው ከመሆኑ በፊት የተጻፈለትን ጎዳና ተጉዞ
ለዛሬው ወቅት ደርሱአል። ለመጪውም ከሱ እስትንፋስና ቃል ውጪ የሚሆን የለም። የዓለም ጉዞ በቅዱስ
ቃሉ በሰማኒያ አሃዱ መጽሐፍ ቅዱስና በሌሎቹም ገድሎች፣ የቅዱሳን ታሪኮች፣ ድርሳኖች ላይ ተገልጹአል።
ከሁሉም በላይ በቅዱስ ቃሉ፣ በመጽሐፈ ሄኖክ፣ በትንቢተ ዳንኤል፣ በዮሐንስ ራእይ፣ ላይ ስለ ዓለም
ጅማሮ ተጀምሮና ተጀምሮም ሆነ ተጉዞ ስለመጠናቀቅ ዓለም የምታሳልፈውን ውጣ ውረድ በሚገባ ተገልጦአል።
ከዚህም የሚወጣ የወጣም ክንዋኔ የለም። ልብ ልትሉት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር ግን ዛሬ የምታዩአት የድሆች
ተምሳሌት ኢትዮጵያ ከእንግዲህ የእግዚአብሔርን የብርሃን መንግሥት ለሺ አመት በዓለም ሁሉ ገና (ከብራ)
በፍፁም የፈጠሪ ፈቃድ መርታ እምትጓዝ ይሆናል። ዓለምም ከሺ ዘመን ፍጻሜ በኋላ ወደ መጨረሻው
ፍርድን የዓለም መፈጸም ትደርሳለች። ይህን ሁሉ ለምን አወቅህ የሚል በአንዳንዶች ህሊና ሊነሱ ይችላል።
ልታውቁት የሚገባው ስለ ሰዶም ጥፋት እግዚአብሔር ለአብርሃም ደበቀው?፤ አልደበቀውም፤ አስቀድሞ
ነገረው ስለምልጃውም ተለመነው እንጂ እግዚአብሔር ከወደዳቸው፣ ከአከበራቸው፣ ከአጸደቃቸው፣ በክቡር
ደሙ ለገዛቸውና ላተማቸው ልጆቹ ምንም የሚደብቀው ሚስጠር የለም።
ይህንን ሁሉ ያነሳሁት ያለ ምክንያት አይደለም። በልዑል ይሁንታና በታሪክ አጋጣሚ ይህ ያለው መንግሥት
ባላሰበውና ባላደራጀው፣ በፍፁም ባልገመተው የእድል መቋጫና የአዲሱ የብርሃን ዘመን መምጫ መለያያ
መንገድ ላይ ተገትሮአል። ሲነገረው በንቀት ያየን የነበረው መንግሥታችን እስከ አሁን የጠጣትን ተጎንጭቶ
በውን ወደሚያየው ገሃድ እነሆ ደረሶአል። የማምለጫም ቀዳዳም ተትቶለታል እንደ ለመደው በዲያብሎስ ምክር
ወደ መፈጸሚያው ጨለማ ካልሄደ በቀር። በተሰጣቸው አጭር ጊዜ መታዘዝ ወይም አለመታዘዝ ምርጫቸው
እንዲሆን እድሉ ተሰጥቶአቸዋል። ቢታዘዙ በቀደመው ሙሉ መልእክት እንደታዘዘው የምሕረትና የቅጣት
ተጠቀሚ ናቸው፤ ባይታዘዙ ደግሞ ቅጣት ብቻ የእድላቸው መቋጫ ይሆናል። እኔም ይህንኑ የሚያሳውቅ
ጊዜውንም የሚያስረግጥ ዝርዝር ደብዳቤ እንዲደርሳቸው አድርጌአለሁ። ከእንግዲህ በኔና እነሱ መሃከል
የተካሄደው የብርሃንና የጨለማ ውጊያ ወደ መቋጫው ደርሷል።
እኔም ሆንኩ መላው የተዋህዶ ልጅ የምንጠብቀው የፍጻሜ ሰዓት መጥቶአል። እንግዲህ ሁሉም ነገር
ተጠናቆ፣ ባጭር ጊዜ ለበጎው ቀን የታተሙ የልዑል ብርሃናዊ ልጆች እንደ ፀሐይ ሊያበሩ በተጠንቀቅ ቆመዋል።
በቅዱስ መንፈሱ ሙላት፣ አገራችንና የተዋህዶ እምነታችንን፣ እኛም ሕዝቦቿ ድል ጨብጠን፣ የወደደንን
ለክብሩ የመረጠንን አምላካችንን በሐሤት ተሞልተን ለማመስገን፣ ለዚህ ክብር ያበቃችንን እናታችንን ድንግልን
ልናመሰግናት፣ እንዲሁም በግንባር ቀደምትነት የጨለማውን ኃይል ጠርገው ለድል ያበቁንን የከበሩ መላእክት
ልናወድስ እመጨረሻው ሰዓት በመድረሳችን ምስጋናችንን ለፈጣሪ ከልብ እናቅርብ። የያዝነው አብይ ጾምም
ለታላቅ ምስጋና እናውለው።

አቤቱ በልቤ ሁሉ አመሰግንሀለሁ ታምራትህን ሁሉ አነግራለሁ በአንተ ደስ ይለኛል


ሐሤትም አደርጋለሁ ልዑል ሆይ ለስምህ እዘምራለሁ በጠላቶችህ ወደ ኋላ በተመለሱ
ጊዜ ይሰናከላሉ ከፊትህም ይጠፋሉ ፍርዴንና በቀሌን አድርገህልኛልና ጽድቅን
እየፈረድህ በዙፋንህ ላይ ተቀመጥህ አህዛብን ገሰጽህ ዝንጉዎችንም አጠፋህ ስማቸውንም
ለዘላለም ደመሰስህ ጠላቶች በጦር ለዘላለም ጠፉ ከተሞቻቸውንም ለዘላለም አፈረስህ
ዝክራቸውም ባንድነት ጠፋ እግዚአብሔር ግን ለዘላለም ይኖራል እርሱም ዓለምን
በጽድቅ ይፈርዳታል አህዛብንም በቅንነት ይዳኛቸዋል ዙፋኑንም ለመፍረድ አዘጋጀ
ዳዊት መዝሙር 9

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ ለአህዛብም ሥራውን ንገሩ ተቀኙለት


ዘምሩለት ታምራቱን ሁሉ ተናገሩ በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ እግዚአብሔርን የሚፈልግ
ልብ ደስ ይበለው እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም
የዳዊት መዝሙር 104(105)
የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሮቸውንም ፍሬ እየተመለከተ
በእምነታችሁ ምሰሏቸው።
ዕብራውያን 13፣ 7
የእግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ ማጽናናትና
በረከት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም እናታችን አማላጅነት የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት ለልዑል ልጆች
ሁሉ ይሁን! አሜን

ከታመነው የልዑል ባሪያና አገልጋይ ይህ መልእክት እንዲሰጥ የተፈቀደው በተዋህዶ እምነት ውስጥ ላሉና
ለእምነታቸውም ለመጪውም መልካም ዘመን በመንፈሳዊ ተጋድሎና ጽናት ውስጥ ላሉ ብቻ ነው!!
ስትሰጡ ከገጹ አታጉድሉ!!

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ቀን 19 – 10 – 2000 ዓ.ም

ለ ክቡር ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ

በመጀመሪያ የከበረ ሰለምታ በልዑል እግዚአብሔር ስም አቀርባለሁ። ይህ ደብዳቤ የተጻፈው ስለ መልእክቱ


መለስተኛ መግለጫ ለመስጠትና በኔ በኩል ያለውን እንደምታ ለማረጋገጥ ታስቦ ነው። ይህ ደብዳቤዬ የመጀመሪያም
የመጨረሻም ነው። መልእክቱን ጠንቅቀው እንዲያነቡት በአክብሮት እጠይቅዎታለሁ። በህይወቶም በመጭው
ዘመንዎም የሚወስን የልዑልን መልእክት መያዙን እንዲረዱ አስገነዝቦታለሁና! መልእክቱ ሁለት ገጽታ አለው።
በእንግሊዝኛም በአማርኛም የቀረበ ነው። አንደኛው መልአክት የአገራችንን እድል ፈንታ የሚመለከት ሲሆን፣
ሁለተኛው መልእክት የዓለምን ሕዝብ እጣ ፈንታ ይመለከታል።
በኅዳር 7/1998 ዓ.ም የተጻፈው የመጀመሪያው መልእክት በቀጥታ ለእርስዎ ባልክልዎትም በመረጃዎች
በኩል ደርሶታል ብዬ አምናለሁ። ባያምኑበትም ዋጋ ባይሰጡትም። በሌላ በኩል ደግሞ ለሁሉም አገር ተወካዮች
ባልክም ለዋና ዋናዎቹ 17 አገሮች ልኬ፣ የሁሉም መሪ የጋራ ባህሪ ነውና በንቀት ትተውታል። ነገ ከየወረወሩበት
ቆሻሻ መጣያ እንደሚፈልጉት ባውቅም ስለድርጊቱ ብዙም አይገደኝም። ይህ ሁለተኛው መልእክት ለሕዝብ
ደርሷል፤ በበቂም ተዳርሷል ብዬ ሳምን በመጨረሻ እልክላቸው ይሆናል። ዛሬም ወደ እርስዎ ከመላኬ በፊት
ለሕዝብ እንዲበተን አድርጌአለሁ። ለውጪዎቹ መሪዎች በድርጊታቸው ምክንያት አክብሮት ነፍጌአቸዋለሁ።
በግድ ልናውቅ ይገባናል፤ እግዚአብሔር እግዚአብሔር መሆኑን፤ ቃሉም ቃል ማንም የማይሽረው፣ ማንም
የማይለውጠው፣ የወሰነውንም ሆነ የፈቀደውን ከማድረግ በሰማይ ሆነ በምድር የሚያግደው እንደሌለ፣ በሚገባ
ወደንም ሆነ ተገደን እንቀበለዋለን። እርስዎም ከዚህ ውጭ መሆን አይችሉም። ቢንቁ ወይም ወደ አልተገባ
አካሄድ ቢያዘነብሉ እርግጠኛ ነኝ ጉዳቶ እጅግ ይከብዳል። ከመልእክቱ እንደሚረዱት አንዱም ነጥብ ሳይለወጥ
ሳየጨምር፣ ሳየቀነስ ሁሉም ይፈጸማል። የሰራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔር ይከብራል። ከፍ ከፍም ይላል።
ካወቁበት ባለእድል፣ ካላወቁበት የከፋ ተጎጂ ነዎት። ባለ እድል ነዎት ያልኩት የጥፋቷም ቢሆን የዚች አገር
መሪ በመሆንዎ ሲሆን፣ ካላወቁበት ይጎዳሉ ያልኩት የእስካሁኑን ከፈጣሪ ጋራ መጋጨትዎን መቋጨት ካልቻሉ
ነው።
እኔ በፈጣሪዬ በልዑል ታዘዝኩ! ለአገልግሎቱም ታመንኩ እንጂ፣ ስልጣን፣ ክብር፣ ሀብት፣ በኔ ስፍራ
ኖሮትም አያውቅም። የፈጠረኝን፣ የወደደኝን አምላኬን ለመታዘዝና ለማገልገል ግን ሁለመናዬን እከፍላለሁ።
ለፈቃዱም እታዘዛለሁ፣ እገዛለሁም።
በመሆኑም ከእንግዲህ የእርስዎ ጉዳይ ያለው በፈጣሪ እጅ መሆኑን ላረጋግጥሎት እወዳለሁ። በፈጣሪ
የታዘዘውን፣ በልዑል እግዚአብሔር ችሎት የጸናውን ውሳኔ ለማሰፈጸም ከኔ የመታገስ አቅም በላይ፣ ከእናንተም
እንቢተኛ መንፈስ ጋር የተደመረ በመሆኑ፣ እልባት ወደሚሰጠው፣ ለታመነው፣ በልዑል እግዚአብሔር ፊት
ለሚቆመው ለወዳጄ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አሳልፌ ሰጥቻለሁ፤ ከዚህ ደብዳቤ ጋር ከፊተዎ
መጥቶአል። የልዑልንም ውሳኔ እንዴት እንዲያስፈጽም ያውቅበታል። ሁሉንም ነገር በልዑል መልእክት
እንደሰፈረው ይፈጽመዋል።
ሌላው ሊያውቁት የሚገባው ቢኖር (በአማርኛው መልእክት ውስጥ ያገኙታል) በኔና በቤተሰቤ፣ በጓደኞቼ ዙሪያ
በየእለቱ የሚያሰማሩአቸው ቁጥር ስፍር የሌላቸው የደህንነት ሰራዊቶችዎ መፍሰስ ነው። ምን ይጠቅምዎታል፣
ለራሴም ገርሞኛል። በባለሃብቱና በእርስዎ፣ የተወሳሰበ ቁርኝነት ባፀኑ የአገርና የውጪ የመዋቅር አካላችዎ
ወዳጆችዎ ፈሰስ የሚደረግለት ተቋም እንደገነቡ አውቃለሁ። ብዙ የተለያዩ ተሸከርካሪዎች፣ ሴት ወንድ ወሬ

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ለቀሚና ተከታታዮችዎን አሰማርተው አጅበውን ሲዞሩ ይውላሉ። ሁሉንም አውቃቸዋለሁ፣ እነሱን የመለየት
ችግር የለብኝምና! ከከንቱ ተግባረዎ እንዲቆጠቡ አሳስብዎታለሁ።
ስልጣንዎን ለምነው የሚያስረክቡት እንጂ! እኔ በመጠየቅ ሆነ በመጠየቅ እምወስድ አይደለሁም። ቢለምኑኝም
ያለ ፈጣረዬ ትእዛዝ የማልረከውብዎት ነኝ። ለምነው እንደሚያስረክቡ ግን አይጠራጠሩ! ይህንንም ይረዱ!
ከዚህ በተረፈ ሁሉም የመጣው የዓለምን የጥፋት ተግባር መነሻ አድርጎ እድልና እጣ ፈንታውን ለመወሰን
በልዑል እግዚአብሔር ተወስኖ ስለሆነ ከመላው ዓለም መሪዎችና ሕዝቦች ጉዳትና ቅጣት የእርስዎ አይብስምና
እርስዎም በዙሪያየ ያሉ ታማኞቼ፣ወዳጆቼ፣ ድርጅቴ፣ አገልጋዮቼ እንዲሁም ወዳጆቼ፣ ድርጅቴ፣አገልጋዮቼ
እንዲሁም ወዳጆቼ የሚሉአቸው አገሮች ሁሉም የመጣውን የፈጣሪ የቁጣ እሳት ሊያውቅ የገባል። ሲጠረጉ
አይደለም ማሰብ የሚቻለው እድሉ የለምና!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ፍፁም የጥፋት ሰዎች በመሆናቸው ለነሱ አክብሬ
የምልከው መልእክት የለም በሰዓቱ እንገናኛለንና!!

ከሰላምታ ጋር

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር የታመነ አገልጋይ ባሪያ።

1ኛው ሸኚ ደብዳቤ

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ቀን 19 – 08 – 2001 ዓ.ም

ለ ክቡር ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ


አስቀድሞ የአክብሮት ሰለምታዬን አቀርባለሁ። ከዚህ ቀደም ከ10 ወር በፊት የላኩሎትን መልእክት
እያስታወስኩ። ምንም የተጠቀሙበት ስላልሆነና በንቀት ስለተዉት፣ ድጋሚ መላክ አልፈለግሁም ነበር።
ነገር ግን ትዕግስትን ገንዘቤ በማድረግ ይህን ሁሉንም መልእክት በአንድ ጥራዝ የያዘ የእንግሊዝኛውንም
የአማርኛውንም መልእክት ልኬልዎታለሁ።
በባለፈው መልእክት ባይጠቀሙም አሁንም ከዚህ የተለየ ያደርጋሉ ብዬ አላስብም። ይሁንና እንደዚች እንደ
አገሬ መሪነትዎና ኃላፊነትዎ መጠን አክብሬ ልኬልዎታለሁ።
በአሁኑ መልእክት፣ መልእክት አንድን፣ መልእክት ሁለትን፣ እናም መልእክት ሦስትን (የመጨረሻ
የአፈጻጸም ውሳኔ ያገኛሉ)። እርሶም የሚመለከታቸው የሥራና የኃላፊነት አጋሮችዎ በሙሉ እንደ አገር፣
እንደዘር፣እንደግለሰብ ከበስተኋላው ሆነው ሁሉን አቀፍ የጥፋት እገዛ የሚያደርጉ ሁሉ እጣቸውን ይዩበት። እንደ
መልእክቱ ትእዛዝ እንዲጓዙ ዛሬም ባለመሰልቸት እነግረዎታለሁ።
እውቀት፣ ብልጠት፣ ትምክህት፣ ሁሉም በፈጣሪ ፊት ያለብረቱ ቅጣት አይታለፍምና፤ በሽርፍራፊና
በተደመደመ ጊዜዎ ጫፍ ላይ ሆነው መውጫ መንገድዎን ያስቡ።
እኔንም ጓደኞቼንም ቤተሰቦቼንም በተለያየ መንገድ ሲከተሉ የሚውሉ ባለመኪናና እግረኛ የደህንነት
ሰራዊቶችዎን ዛሬም አሰማርተዋል። ምን እንደሚጠቅምዎት ባይገበኝም ቢገርመኝም ይህ ድርጊት ግን ነገ
በኃላፊነት የሚያስጠይቅዎት መሆኑን እንዲረዱት እፈልጋለሁ።
ጊዜ ወስደው ስላነበቡት አመሰግናለሁ።
ከአክብሮት ሰለምታ ጋር
የታመነው የልዑል ባሪያና አገልጋይ
2ኛው ሸኚ ደብዳቤ ነው

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

ቀን 07 - 06 - 2002 ዓ.ም
ለክቡር ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ
በትንቢተ ዳንኤል ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል። ይኸውም ቃል ማኔ ቴቄል ፋሬስ የሚል
ሲሆን ይህንን የፃፈው የልዑል እግዚአብሔር ጣት ነው። ትርጉሙም ማኔ ማለት እግዚአብሔር መንግሥትህን
ቆጠረው ፈጸመውም ማለት ሲሆን ቴቄል ማለት ደግሞ በሚዛን ተመዘንህ ቀልለህም ተገኘህ ማለት ነው።
ፋሬስ ማለት ደግሞ መንግሥትህ ተከፈለ ለባቢሎንና ለፋርስ ሰዎች ተሰጠ ማለት ነው። ይህ የመጨረሻው
ትርጉም ለእርሶ ተለውጦ ከዚህ የሚከተለውን ትርጉም ይዟል። መንግሥትዎ ተሰናብቷል፤ የእግዚአብሔር
አገልጋዮች ቦታውን ይረከባሉ ማለት ነው። ይህም ሁኔታ ዓለም እግዚአብሔር ወደወሰነላት የብርሃን ጎዳና
ጉዞዋን የምትጀምረው ከዚህ ከተባረከችው ኢትዮጵያ ይሆናል ማለት ነው። ይህም የተረጋገጠ እውነትና
ከአባቶቻችን ጀምሮ ሲመሰከርበት የኖረ ሀቅ ነው። የእግዚአብሔር ቃል የማይዳኘው የለምና የናቡከደነፆር ልጅ
ብልጣሶር በአባቱ ቦታ ነግሶ ሁሉን ሲፈልጥና ሲቆርጥ በትእቢትና በማንአለብኝነት በእግዚአብሔር ቤት የክብር
ዕቃ ላይ እርኩሰትን ሲፈፅም በመገኘቱ ከላይ የተጠቀሰው ፍርድ ተፈፅሞበታል። ያንኑ የብልጣሶር ሥራ እርሶም
በዚህ የከፍታ ዘመንዎ በእግዚአብሔር ሕዝብና በቤቱ ላይ እንደፈፀሙት ማለት ነው። ይህንን በትንቢተ ዳንኤል
ምእራፍ 5 ላይ ይገኙታል። ታድያ ይህቺ ታሪካዊ የእግዚአብሔር ጣት ታሪካዊ ተግባሯን ማለትም ፍርዷን
ትፈፅም ዘንድ በእርሶም ላይ ወጣች።
አስቀድሜ የአክብሮት ሰላምታዬን በቸሩ አምላኬ ስም አቀርባለሁ። የዛሬው ደብዳቤ 3ኛ እና ማብቂያው
መሆኑ ነው። በፈጣሪዬ ታዝዤ መላ የሰው ዘር ያውቀው ዘንድ ከልዑል የታዘዝኩትን መልእክቶች ለህዝቡ
እንድገለጥኩት መጠን ለእርሶም በየወቅቱ ልኬዎለታለሁ። በሸኚዎች ደብዳቤዎች ምክሬን ማሳሰቢያዬን ወቀሳዬን
አስተላልፌሎታለሁ። ያዩአቸውም መልእክቶች ምን እየሠሩ እንደሆነ የሚያዩትና የሚሰሙት እውነት ሆኗል።
ዓለም የመጀመሪያ ህመሙን እያየው ይገኛል። እጅግ ወደሚከፋው ጎዳና የሚወስደውን አቅጣጫ ተያይዞታል።
አገሬ ኢትዮጵያም የዚህ ችግር ቀማሽ ሆና ብርቱ ፈተና ብታሳልፍም አሁን ግን በፈጣሪ የታሰበላትን ክብር
ታገኝ ዘንድ እነሆ ሰዓቱ ደርሷል። እሷ ኢትዮጵያ ወደ ብርሃናዊ ክብሯ ማማ ልትገሰግስ ዓለም ደግሞ ቅጣቱን
እየቀመሰው ወደ ጨለማው ሊነጉድ እነሆ ጉዞው ተጀምሯል። አምኖ እጁን ለኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥታዊ
አገዛዝ እስከሚሰጥ ድረስም እጅግ በርትቶ ይቀጥላል። የእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳብ እስከሚፈፀም ድረስ።
የዚህ ደብዳቤ ዋንኛው ጉዳይ ይህንኑ ለመግለጥና የጨለማውን አገዛዝ ማብቃት ለማሳወቅ የታሰበ ነው።
የእግዚአብሔር ሥራ በብርሃን የሚከናወን ግልፅና ከውሳኔው ከፍና ዝቅ የማይል በታሰበለት ጊዜና ሰዓት ምንም
አይነት ኃይል ሳያስቆመው የሚከናወን እውነት ነው። ለዚህም ደግሞ አስተዋይ አእምሮ ላለው በእምነት የተገኘ
ዓይንና ህሊናን ለጨበጠ ሰው ከመጀመሪያው ጀምሮ በተላለፉት የልዑል መልእክቶች የተጠቀሱት የቅጣት
አይነቶች መጪውን የዓለምን ሁኔታና የዘመኑን ትውልድ ዕድል ፈንታ እያመላከቱ መከናወን ላይ መሆናቸውን
ሊረዳ ይችላል። የቅጣቱ ዓይነትና መጠን እየሰፋ ጥፋቱም በብዙ እጥፍ እየጨመረ ይሄዳል እንጂ በፍፁም
የሚቀንስ ነገር አይኖርም አይታሰብምም። የሰው ልጅ በተለይም ቀጥተኛ የሲያብሎስ አገልጋይ የሆነው የዘመኑ
የገዢዎችና የባለሃብቶች ኃይል ቶሎ ዐይንበረከክም። ትእቢቱ ሙልጭ ብሎ እስኪጠፋና እጁን እስከሚሰጥ
ድረስ የሰው ዘር በታሪኩ ያላየውን ጥፋት ገና ሊያጠፋ ይየመጣ ይገኛል።
የሚደንቀው ገና ምንም ሳይመጣ በሺህ ዘመን በሁለት መቶ ዘመን ያልታየ በረዶ፣ ጎርፍ፣ የመሬት
መንቀጥቀጥ፣ እየተባለ በየሚዲያው ሲደሰኮር ሳይንሳዊ ምክንያት ሲደረደርበት ይሰማል። አስተውል የሰው ዘር
ገና መደበቂያ ይጠፋል፣ የእስከአሁኑ ከምልክትነት የዘለለ አይደለምና!
ቁጥር 1፣ 2፣ 3 በያዘው መልአክት እንደተገለጸው ሁሉም የጥፋት አይነቶች መጠናቸውን በመጨመር ላይ
ናቸው። የዘመናችን አዋቂዎች፣ ጥበበኞች፣ የፖለቲካ ትያትረኞችና፣ የዲማጎጂ አርቲስቶች ዓለምን በረቀቀ

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

የውሸት ብርድ ልብስ ሸፍነው የሚዘልቁ መስሎአቸው አሁንም እየማሰኑና እየዳከሩ ይገኛሉ።
የአየር ንብረት እንቆጣጠራለን፣ የሞቀውን እናቀዘቅዛለን፣ የተቃወሰውን ኢኮኖሚ እናስተካክላለን፣ የሁሉንም
ችግር እንፈታለን፣ በጦር በጀት እንከላከላለን ሲሉ፣ የሃይማኖት መሪ ነን ባይ የዲያብሎስ አሻንጉሊቶችም
እንዲሁ ከፖለቲከኛው ጋር ተባብረን እንፈታዋለን ይሉናል። ሁለቱም ክፍሎች እንደ አሮጌ ነጠላ እየተቦጨቀ
በየቦታው የሚፈነዳውን ችግርና አደጋ በማያልቅ የውሸት ድሪቶ ሊጥፉትና ሊጠግኑት ሲደክሙበት ይታያል።
እርሶም እንደ ገዢነትዎ የዚሁ የመሪዎች መድረክ አባል ነዎት። ይህም ለኔም በኢትዮጵያውነቱ ለሚመካውም
እጅግ አሳፋሪ ነው። የዚች ታላቅ አገር መሪ ሆነው ሳለ በዚህ መልክ ሲፈረጁና የእግዚአብሔር ጠላቶች
ማህበርተኛ ሆነው በማየቴ አገሬ በምን የጉዳት መጠን ውስጥ እንዳለች ተረድቼአለሁ፤ ሳስተውልም ኖሬአለሁ።
ከላይ እንደጠቀስኩት መንግሥታዊ ስርአቶንና አገዛዞን ለመውቀስ ለመምክር ወየም ለመገሰጽ የታሰበ መልእክት
የለኝም። ያለኝ መልእክት ስለእድልዎ ስለመንግሥትዎ በሰራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔር የተወሰነውንና
የታዘዘውን ለመግለጽነው። በሰራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔር ፊት ጉዳዩ ታይቶ መንግሥትዎ ከነአለቃና ምንዝሩ
ተፈትሾ በልዑል የፍርድ ሚዛን ተለክቶ እጅግ ቀሎ ተገኝቶአል። ይህም ብቻ አይደለም ፈጣሪን ለመውጋት
የመቻልን ያህል እጅግ ታብየዋል። የእግዚአብሔርን ሕዝብ እጅግ ጎድተዋል፣ ለመከራ ለስቃይ ዳርገዋል፣
በእምነቱ ዘምተዋል፣ እርስ በእርሱ በዘር እንዲለያይ ዘረኝነትም እንዲነግስ አድርገዋል፣ የኢትዮጵያ ፍቅር
የሌላቸውን፣ የተዋህዶ እምነታችንን የሚጠሉ፣ እንዲሁም ለጥፋቷ የሚሠሩትን አንግሰዋል። ታይቶ ተሰምቶ
የማይታወቅ የዲያብሎስ ሥራ እንዲሰፍን አድርገዋል። ባጠቃላይ የዘረጉት መንግሥታዊ ስርዓት፣ በፈጣሪ
ፊት እጅግ አስቆጪና የእግዚአብሔርንም ቁጣ የቀሰቀሰ ሆኖአል። ይህም ብቻ አይደለም በተሰጣችሁ ጊዜም
የመጸጸት ምልክት አላሳያችሁም። እንደውም የረቀቀ የጥፋት ድርጅት በመላ አገሪቱ አደራጅተዋል።
በመሆኑም የእግዚአብሔር ጣት በናቡከደነጾር ልጅ በብልጣሶር ላይ ወጥታ የመንግሥቱን መቆረጥ እንዳሳወቀች፣
በእርስዎም መንግሥት ላይ ይህችው ታሪካዊ ጣት ወጥታለች። ሩቅ አሳቢ ቅርብ አዳሪ ሆነዋል። ጌታ
መንግሥትዎንም ሆነ በስርዓተ መንግሥትዎ ውስጥ ያሉትን ተቃዋሚዎች እንዲሁም ማንኛውንም ስርዓትዎትን
ደግፈው የያዙ ኃይሎችን ሁሉ አሰናብቶአል። በቦታውም የእግዚአብሔር መንግሥት እንዲተካም ታዞአል።
በመልእክቱ የተጠቀሱት የኢትዮጵያ ወደ ክብርዋ፣ ወደ ብርሃናዊ ጎዳናዋ እንድትወጣና ይህም እውን እንዲሆን
ተወስኖአል። በመሆኑም በእጅዎ ከሚገኘው መልእክት እንደሚረዱት፣ ዓለም በሙሉ ከቅጣት አያመልጥም፤
የተራ ጉዳይ እንጂ ሁሉም አገር የተመደበለትን ጽዋ ይጋታል። አንዱ በፍጥነት፣ አንዱም በቀጣይነት፣ ሌላውም
በረጅም ስቃይ እድል ፈንታውን በድርሻነት ይወስዳል። ለየሀገሩ የተሰጠው ሸክምና እጣ ፈንታ ይለያያል።
የእርስዎ ግን አልቆአል ተፈጽሞአል።
ቅጣትና ምሕረት ላስተዋሉ ቶሎም ራሳቸውን በእግዚአብሔር እጅ ለሚጥሉ የተሰጠ እድል ነው። በመጨረሻው
ሰዓት በዚህ አድል መጠቀም አንዱ መንገድና ብልህነት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ለሚያፌዙ፣ ለሚንቁ፣
በጥፋት ጎዳና ለሚዘልቁና በኃይላቸው ለሚታበዩ ምሕረት የሌለበት ቅጣት ብቻ የእድላቸው ማረፊያ ይሆናል።
እንግዲህ በዚህ የመጨረሻው ደብዳቤዬ ብታንስም ቁም ነገር ሊያገኙ ይችላሉ ብዬ አስባለሁ። ከናቁትም
መብትዎ ነው። የትርፉ ባለቤት መሆንዎ ግን አይቀሬ ነው። እኔ እንደተረዳሁትና እንደማውቀው ፈጣሪ አምላኬ
የሚያመጣውን የቁጣ በትር ስለማውቅ እስከያዝነው የአብይ ጾም ፍቺ እለት ድረስ በትዕግስት አይዎታለሁ።
ለተሰጠዎት ማሳሰቢያና ትእዛዝ ሥፍራና የመቀበል ሁኔታ ካሳዩና ካልተረጋገጠ እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ለልዑል
አባቴ በመግለፅ ኃላፊነቱን እንዲሸከሙ አደርጋለሁ። መልካም የማገናዘቢያና የማስተዋል ውሳኔ ላይ መድረስ
ያስችላችሁም እላለሁ።
በእኔ በኩል ያለውን ሁኔታ ብገልፅልዎ መልካም ነው። ከአራት ዓመት በላይ የታገስኩት ያለምክንያት
አይደለም። አባቴ እንዳስተማረኝና እኔም እንደማምንበት ሰው ሲፀፀት ወደ ፈጣሪው ሲመለስ ለፈጣሪው

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

አምላክ ከልቡ ሲገዛ ለማየት ጉጉት ስላለኝ ብቻ ነው። በማንም ሰው ጉዳት አልደሰትም። የሰው ዘር ምንም
አይነት ኃጢአት ሲሠራ ተፀፅቶ ሳያስመስል ከልቡ ተሰምቶት በፈጣሪው አምላክ እጅ ከወደቀ በእኔ በኩል
የሚገጥመው የከፋ አደጋ የለም ማለት ይቻላል። ይህ ደግሞ በግሌ ፈጣሪ አምላኬ የቸረኝ ባህሪዬ ነው።
በቀደሙት መልእክቶች እንደገለፅኩት ሁሉንም መልእክቶች ሳያጎድሉ፣ ሳይጨምሩም ሆነ ሳይቀንሱ ለሕዝብ
መግለፅ ነበረብዎ፤ አላደረጉም። ታላቅ ጥፋት ነው። ለነገሩ ይህንን ድርጊት እርስዎ ብቻ ሳይሆኑ መልእክቱ
የደረሳቸው መንግሥታትና ግለሰቦች፣ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፣ ታላላቅ ተብዬ ዩኒቨርስቲዎች ሁሉም አፍነው
ተቀምጠዋል። ይሁንና ሁሉም ዋጋውን እየቀመሰ የግድ የሚለፈልፍበት ጊዜና ሰዓት ይመጣል፤ መጥቶአልም።
ሁለት ሞት ለመሞት ከሚንደረደሩ እጅግ ብዙ ሚሊዮኖች አለመቀላቀል ለታደሉት ብቻ ነው።
ወደ ተዋህዶ እምነታችንና ቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ ስመለስ፤ በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እንዳትገቡ መክሬና
አስጠንቅቄ ነበር፤ አልሰማችሁም። ይህም ምን እንደሚያስከትል አሁን ለመናገር አልሻም። ነገር ግን የእርስዎን
ስርዓተ መንግሥትና ዓለም አቀፍ ዲያብሎሳዊ ስርዓትና ጥፋትን በማገልገል ላይ የሚገኙት የኢትይጵያ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን የበላይ መሪ ጥፋታቸው ወሰን ስላጣ ከዚህ የሚከተለው ቅጣት ታዝዞላቸዋል።
ሥጋቸውን ሙሉ በሙሉ ዲያብሎስ ይሰለጥንበታል፤ ነፍሳቸው ግን እንዳይነካ ይሆናል፤ ስለፈተቱት የልዑል
ሥጋና ደሙ ምክንያት። ይህ ማለት ባለአእምሮ ሰው አይሆኑም፤ ሥጋቸውም በተለያየ የዲያብሎስ በትር
ይመታል። አጠገባቸው ላሉ የጥፋት ሰዎች የእድላቸው ማመላከቻ ይሆናል። በቀጥታ ለእሳቸው እና ለጋሽ
አጃግሬዎቻቸው የማልፅፈው ሥራቸን ነፍሴ እጅግ ስለምትጸየፈው ብቻ ነው።
በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ የጥፋት ሥራዎች ጎልብተው ወጥተዋል። እድገት በሲሚንቶ ጫካ ብቻ እየተለካ
ነው። ደሀ እየተጣለ እየተገፈተረም ነው። ረሃብ የብዙ ሕዝብ ጓደኛ ሆኖአል። ጥቂቶችና አገሪቷን የማያውቁ
ለጥፋቷ የሠሩና የሚሠሩ በሁለመናዋ ላይ ሰልጥነዋል፤ በእርስዎ ብርቱ ድጋፍ። ደሀ ደግሞ ለፈጣሪው አለቀሰ።
ለሀገራቸው፣ ለተዋህዶ እምነታቸው የደከሙ በየተጣሉበትና በየወደቁበት ሆነው ለፈጣሪ አነቡ። የችግሩን
ብርታት መቋቋም ያቃታቸው ደግሞ አለፉ። የእርስዎን የጭካኔና የብቀላ በትር ሲጠጡ ኖሩ። ፈራጅ የሌለ
ይመስል ፍፁም ተገፉ። በጆሮም እንደሰሙት በዓይንዎም እንዳዩት የተዋህዶ እምነት የማትከስምና የማትደክም
መሆኗን የተረዱ ይመስለኛል። የገፉት ሕዝብ በተለይም ወጣቱ ወደፈጣሪው ጉያ ተመለሰ፤ ለፈጠረው አምላክ
ጮኸ፤ ለክብሩም ከልቡ ተነሳ፤ ፈጣሪን ከመንበሩ ቀሰቀሰ፤ እነሆም ይህንን የመንግሥትዎን እድሜ የሚቆርጥ
ውሳኔ ወለደ። ፈጣሪ አምላካችን የኢትዮጵያን ጎስቋላ፣ የተናቀ፣ የተራበ፣ የታሰረ፣ የታመመ፣ በእርስዎ የጭካኔ
አመራር የተጣለውን ፈጣሪውን ብቻ ተስፋ ያደረገውን አሰበ። እነሆም ወደክብሩ ተራራ ሕዝቡን ሊያወጣ
ወሰነ። የእርስዎም ሆነ የሥርአትዎ የወለዳቸው ተቃዋሚም ደጋፊም እንዲያከትም የእድሉም በር ተቋጨ ተዘጋ።
በተጨማሪም ሁኔታ የፈጣሪን አስገራሚ እርምጃ ዓለምም ሊቀበለው የሚከብድ ውሳኔ መጣ። ኢትዮጵያ
ታሰበች፤ ዓለምም በምርኮ ተሰጣት፤ ዓለምን ሁሉ በብርሃናዊ አገዛዝ በልዑል ሕግ የሚገዙ ተቀቡ ተሾሙ።
ይህንን እውነት ከአራት አመት ጀምሮ ለሕዝቡ ሁሉ ሳሳውቅ ቆየሁ። ዛሬ ደግሞ የእርስዎን እድል ፈንታ
የሚወስነውን ትእዛዝ ለመግለጽ እነሆ ታዘዝኩ።
ስለዚህ ከዚህ በታች የምዘረዝራቸው ትእዛዞች በሙሉ ተፈጻሚ እንዲየደርጉ አሳስብዎታለሁ።
1ኛ/ ከዚህ ደብዳቤ መድረስ ጀምሮ የሚወጡ ማናቸውም የተዋህዶ እምነታችንን፣ የአገሪቱን ህልውና፣
ምልክትና (ሰንደቅ አላማ) የሚነኩ ህጎች፣ ደንቦች እንዳይወጡ፣ የወጡም እንዲታገዱ።
2ኛ/ የሀገሪቱን ሀብት በተለያየ ዘዴ በመዝረፍ በማሸሽ ላይ ያሉ በፍጥነት እንዲገቱ።
3ኛ/ ለበቂ ወቅቱን የተከተለ ካሳና ሃገራዊ ምክንያት ድሆችን ከየቀያቸው ማፈናቀሉና ማባረር በፍጥነት
እንዲቆም።

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አራት

4ኛ/ በተለየ በተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከለይ እስከታች የኮለኮላቸውን ተኩላዎች ከመድረሴ በፊት
በፍጥነት እንዲያነሱ።
5ኛ/ በየክልሉ የሚካሄዱ ዘረኝነትን መሰረት ያደረገ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴና የዘር ልዩነት በፍጥነት እንዲቆም።
6ኛ/ እስከ ያዝነው የ2002 ዓ.ም የአብይ ጾም ፍቺ ድረስ በመንግሥትዎ ዙሪያ ሊያጠናቅቁ የሚገባዎትን
የመሸጋገሪያ ዝግጅት እንዲየጠናቅቁ።
7ኛ/ ከኔ ጋር ለመነጋገርም ሆነ በውሳኔዎቹ ከተገዙ የተሟውን መልአክት፣ (1.2.3) የያዘውን በሁሉም
የመገናኛ መስመር ለሕዝብ በተደጋጋሚ የመግለጽ ግዴታ እንዳለብዎት ይወቁ። ይህን ሳያደርጉ በምንም መልኩ
ላናግረዎት በፍፁም አይቻለኝምና!! ይህንን ትእዛዝ አምነው ለፈጣሪ ተዕዛዝ ተገዝተው ስልጣንዎን ለማሸጋገር
ከወሰኑ ብቻ ነው ከላይ የዘረዘርኩአቸውን ትዕዛዞች የሚፈጽሙት። ንቀው ከተዉት ደግሞ 4 ገጽ ወረቀቶች
ናቸውና ቀደው ይጥሉአቸው ዘንድ መብትዎ ነው። ከጊዜ ገደቡ በፊት ከ15 ቀን በላይ የማይወስድ የመነጋገሪያ
ጊዜ ሰለአሎት በሚሹት ጉዳይ ሊያነጋግሩኝ ይችላሉ።
8ኛ/ ከላይ የተዘረዘሩትን ትዕዛዞች ከፈጸሙ ስልእርስዎም ሆነ አብሮዎት በውሳኔ አሰጣጥ ስለሚሳተፉ ሁሉ
እጣ ፈንታ ልገልጽልዎትና ልንነጋገርበትም እንችላለን።
9ኛ/ ስለኔም ሆነ ወንድሞቼና እህቶቼ ማንነት ከኔ ፈቀድ ከላገኙ መግለጽ አይችሉም።
ባጠቃላይ መንግሥትዎ ከነማንኛውም ይዘትና ገጽታው ጋር በቸሩ አምላካችን የማይለወጥ ትእዛዝ እንዲያከትም
የተወሰነ መሆኑን በድጋሚ እያረጋገጥኩልዎት በቦታው ያለምንም እንቅፋት በእግዚአብሔር የተቀቡና የተሾሙ
አገልጋዮቹ እንዲረከቡም የልዑል ውሳኔ አርፎአል።
እንግዲህ ለማንበብም ለዚህ በአክብሮት ለተላኩት ደብዳቤ ዋጋ ለመስጠትም ንቆም ወይም ቀዶ ለመጣልም
በጥቅሉ ለሁሉም ድርጊት ደግሜ እላለሁ መብትዎ በእጅዎ ነው። የኔም ትእግስት እስከ ያዝነው አቢይ ጾም
ፍቺ ድረስ ብቻ ነው። ከዚያ በኋላ ሁሉም የሚከናወነው የልዑልን ትእዛዝ በሚያስፈጽሙ ቅዱሳን መላእክት
በመሆኑ የኔም ሆነ የወንድሞቼ ድርሻ አፈጻጸሙን ማየትና ስንታዘዝ ስፍራውን መረከብ ብቻ ይሆናል። እኔም
በፈጣሪ የታዘዝኩትን መፈጸም ብቻ ነው። ከዚህ የዘለለ ሌላ የምለው የለም። ከዚህ የመጨረሻው የጨለማው
ዘመን ማብቂያው ሰዓት ላደረሰን ቸሩ ፈጣሪ የማይቋረጥ ምስጋና ይፍሰስለት። አሜን።

ጊዜውን ሰውተው ሰለተመለከቱት አመሰግናለሁ።

ከአክብሮት ሰላምታ ጋር

ከታመነው የልዑል ባሪያ አገልጋይ

17
መልእክት አምስት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

21/01/2004 ዓ.ም

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን


አምስተኛ ክፍል
አንባቢዎች ወደ ዋናው መልእክት ከመግባታችሁ በፊት ከዚህ በታች ያሉትን ማሳሰቢያዎች በማስተዋል
ያንብቡት!
ማሳሰቢያ፡– ይህ መልእክት የቀደሙትን መልእክቶች 1፤ 2፤ 3 4ን ተንተርሶ ከመጀመሪያ ደረጃ ቅጣት፤
ወደ ሁለተኛ ደረጃ ቅጣት የሚያሸጋግር የልዑል ትእዛዝ ያረፈበት ነው። የዚህ የሁለተኛ ደረጃ ቅጣት ሁሉም
የቅጣት አይነቶች በ49 እጥፍ ጉልበት አድገው አዳዲስ ቅጣትንም አካተው የመጡ ናቸውና! አቅልላችሁ
አትመልከቱት!
»» በመጀመሪያውም ሆነ በዚህ መልእክት ስርጭት ላይ ዛሬም ለእንቅፋትነት የተሰለፋችሁ ሁሉ፤
በመልእክቱ ውስጥ ከተጠቀሰው ቅጣት ተጨማሪ መግለጫ የማይሰጥበት ቅጣት ታዞባችኋል።
»» ይህንን መልእክት ቢያንስ ለ3 ሰው የመስጠት መንፈሳዊ ግዴታ አለብዎት፤ ይህን የማያደርጉ ሰዎች
መልእክቱ በእጃቸው ባይገኝ በተሻለ ነበር።
»» በነፃ ስጡ አሊያም የኮፒ ወጪአችሁን ብቻ ውሰዱ
»» ከገጽ አታጉድሉ፡ ይህ አምስተኛ መልእክት 41 ገጾች አሉት። ይህ መልእክት በእንግሊዘኛም
በአማርኛም ተሰራጭቷል። ወደውጪም ጭምር አሰራጩት፣ ቢሰሙም ባይሰሙም ይህ መልእክት
በዋናነት የሚጠቅመው ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ነው። ለተቀሩት የሞት መርዶ ብቻ ነው።
»» በመልእክቱ ተጠቀሙበት እንጂ አትጎዱበት፤ የክርክር ዘመን ስላለፈ አትከራከሩ ቢሻ ያድምጥ ባይሻ
አያድምጥ ላበቃ ጉዳይ አትጨነቁ!
»» በእያንዳንዱ የመልእክቱ የጀርባ ገጽ ላይ በትልቁ የኔ የልዑል ባሪያ ፊርማ አርፎበታል።

ለጥፋት ኃይሎች ሁሉ የተሰጠ ማሳሰቢያ


»» በብዙ ያጥፋት ኃይሎች ዘንድ የሚታሰብ አንድ አስተሳሰብ አለ። ይኸውም ጊዜው ገና ነው ነገም
እንዲሁ እቀጥላለሁ የሚል፤ ይህ እንደማይሆንና ቀዩን መስመር መርገጥህን እወቀው።
»» በግሌ በእኔ ዙሪያ ብዙ የጥፋት ሥራ መሥራት ሞክራችኋል! የምትችሉትንም አድርጋቸኋል፤ ይሁንና
ሁሉንም ፈቅጄ ስለተውኩት በጉዳት ውስጥ አልወደቃችሁም፤ ዛሬ ግን ይህ አብቅቷል። ከእንግዲህ
ወዲያ የኔን ጎጆ ማእከል አድርጎ በሰባት ኪሎ ሜትር ዲያሜትር ውስጥ በእኔም በወንድሞቼም ሁሉ ላይ
አንዳች የቀጥታም ይሁን የተዘዋዋሪ የስለላ የጥቃት እንቅስቃሴአችሁን እንዳይ አልሻምና ባትሞክሩት
ይሻላል። ወደ እናንተ የሚመጣ የለም፤ እናንተው ትለምኑ እንደሁ እንጂ! ስለዚህ በአንዳች የጥፋት
እንቅስቃሴአችሁ ላይ ጥፋት መስሎ ከታየኝ፤ በቀጥታ ለልዑል አቀርበዋለሁ መጪውንም የምታዩት
ይሆናል።
»» ጠላት ዲያብሎስ ከነሰራዊቱ ወደ ሺው ዘመን የገሃነም እሥራቱ እንዲወርድ ተወስኖበታል። ይህ
መልእክት ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆን ዘንድ፣ የልዑል ኃይላት ይነቃነቃሉ። የዲያብሎስና
ሰራዊቱ እድላቸው ተከደነ፤ ስለዚህ መርዶአችሁን በመስማታችሁ ለምትደነግጡ ካላችሁ በእግዚአብሔር

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

እጅ መውደቅ ይሻላልና በጥፋታችሁና በሞታችሁ ውስጥም ቢሆን ምርጫችሁ ብታደርጉት ይሻላል።


ላላጋጮች ግን ፌዛችሁ ይታደጋችሁ።
»» ዛሬ በአገራችን የሚነገረው ስለልማት፣ ስለ ውኃ መገደብ ነው። ይሁንና ይህንኑ ቋንቋ የዛሬዎቹ
ሰለጠንን ባዮችም ተጠቅመውበታል። ግን ሌቦች ናቸው፤ ድሃን አደህይተው ጥቂት ቢሊዮነሮችን
ፈጥረዋል። ድሃም የእነሱ እራት አብሊ የውሸት ተስፋቸውን እንዲበላ ይጥራሉ።
የኛዎቹም የድሃውን ደምና አጥንት ግጠው በውጪ ሀብት አከማችተው፤ ድሃው የተለመደውን የማያልቅበት
የውሸት ተስፋቸውን እንዲበላ ይጥራሉ። ዓለም ከዚህ የሚሻል ለጉስቁል ቦታ የላትም፤ የዲያብሎስ ስልት
ከአያቶቻችን ዘመን ጀምር መልኩን እየቀያየረ የሚተገበር ለባለጸጎችና አገልጋዮቹ የቆመ ስርዓት ነው። ስለዚህ
በምኞት የምትጋልብ ሁሉ፤ ከእንግዲህ ዓለም ሁሉ የልዑል ገንዘብ እንጂ ለተወሰነ ጊዜ በክራይ እንደሚኖር
ሰው በውስጧ አዝዞና ፈልጦ ለኖረው ለዲያብሎስ የሰራት ሃብቱ አይደለችምና ባለቤቱ ልዑል በቃህ ቤቴን
አጥፍተሃል ውጣ ለጥፋትህም ዋጋ ክፈል ብሎ ስለወሰነ የዲያብሎስ ተስፈኛ ሁሉ ዘመንህ መከደኑን እወቅ!
በስተመጨረሻ ለሁሉም የመልእክቱ አንባቢ የምመክረው፤ አስተውሎ ማንበብና መረዳት የሚገባ ሲሆን፤
ለሌላውም ለመንገር፤ ለመምክር ይጠቅማል። ሁሉንም መልእክቶች አንብበህ ተረዳ!!
የዘመናችን ፖፖች፤ ፓስተሮች፤ የኛም ጳጳሳት፤ የተረት አምላኪውም፤ የጣኦት ተገዢውም ሁሉም እስከዛሬ
በገዢዎቻችሁ ተወዳችሁ ኖራችኋል፤ ምክንያቱም በርታ ቀጥል የሚነካህ የለም የምትሉ የበአል ነቢያት ናችሁና!
ሚኪያስን በጥፊ የመቱና ያጉላሉ ምድርን የሸፈኑ የኢዮሳፍጥ ነቢያት ናችሁና! ኤሊያስ በማን ታመነ ሚኪያስስ
በማን ፀና ሁለቱም የተወቀሱት ደግ አይናገሩም ከአፋቸው መልካም ነገር አይወጣም ሁሌም ጥፋታችንን ብቻ
ይናገራሉ፤ ተብለው እንደተዘለፉ ኑረዋል። እኔም የታዘዝኩትን ስለተናገርኩ ክፉ ተናጋሪ ተብዬ እንደተወገዝኩ
አለሁ። ያሻችሁን በሉ የመጨረሻ ፍፃሜያችሁን በማርዳቴ ቅርም አይለኝ!

መልካም ንባብና መረዳት ይሁንላችሁ!

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ተፃፈ በ21/01/2004 ዓ.ም

መልእክት አምስት
በስመ አብ ወወለወድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ
አሜን!!
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል! በዚህ ቃል ተናግራችኋልና እነሆ በአፍህ
ውስጥ ቃሌን እሳት ይህንንም ሕዝብ እንጨት አደርገዋለሁ ትበላቸውማለች።
ት/ኤርሚያስ 5 ፡ 14
ልብ በሉ ልዑል በቃሉ ተናገረ፤ በባሪያው በኔ በውዳቂው አፍ ውስጥ ቃሉን አኖረ! መጭውም እስከ
ዛሬ እየሆነ ያለውም ውድመታችሁም መጠረጋችሁም ሁሉም እየተከናወነ ያለው ሰዓትና ጊዜውን እየጠበቀ
የሚሆነውም ከመጀመሪያው መልእክት ጀምሮ እሰከ እዚሁ አምስተኛው መልእክት ድረስ ከላይ እንደ ሰፈረው
የልዑል ቃል በመመስረት ነው።

የአዳም ዘር በሙሉ ዛሬም ጆሮህን ክፈት አድምጥ


አስተውልም ስማም እጅግ የከበደው ጥፋትህ መጥቷልና!!!

እኔ እጅግ ከሁሉ የማንሰው ኃጢአተኛው የልዑል ባሪያ ለናንተ እብድ ነኝ፤ ለፈጠረኝ አምላኬ ደግሞ ባለ
አዕምሮ ነኝና ብትንቁኝም የእሳቱ መለብለብ ከእግራችሁ ጀምሯል። ዛሬም በትእቢት ተሞልታችሁ በመልእክቱ
ባታምኑበትም ብትጠሉትም የሚመርር እውነት ነውና ዛሬም አድምጡ፤ የዘራችሁትንም እጨዱ!! ቀጣዩንም
እሳት ካንገታችሁ ሲደርስ፣ ያንጊዜ የናቀችሁትን የእግዚአብሔርን እብድ ምናምንቴውን ትፈልጉታላችሁ።
ተንበርክካችሁም ትለምናላችሁ። ይህንን ደግሞ ትምክህቴና ጋሻዬ ልዑል አባቴ ያደርገዋል። እኔ በፈጠረኝ
አምላኬና አባቴ ብቻ እመካለሁ፤ ብዙዎች ባላወቁት፤ አንዳንዶች ደግሞ ዲያብሎስ ባሳዘላቸው አጀንዳ እኔን
የሚጎዱ መስሏቸው ብዙ አይነት የምላስ ጅራፍ ያሰናዳሉ። ቅዠታም ነው፣ እምሮው የታመመ ተፈላሳፊ ቢጤ
ነው፤ በዘህ ዘመን እግዚአብሔር የሚልከው ሰው የለም፤ ብዘረዝረው እጅግ ብዙ ነው፤ ይሁን ብቻ ማንም
የዘራውን ማጨድ ግዱ እንደሚሆን እንዳይስት፤ መልእክቶቹ ሁሉ በየሰአታቸው ተፈጻሚ ሲሆኑ እብድና
ቅዠታሙ ምን እንደሚሆን እናንተም ምን እንድትመልሱ ከወዲሁ ብታስቡበት ይጠቅማችኋል።
ይህንን የመጀመሪያ መግቢያ ቃል እንዳትዘነጓት ገና ከመልእክቱ መግቢያ በር ላይ አኖርኩላችሁ። ከላይ
ለተገለጸው ቃል ልዑል በቃሉ እንዲህ ይላል።

እግዚአብሔር ለሚወዱት እንደሃሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ


እናውቃለን፤ ልጁ በብዙ ወንድሞች መሃከል በኩር ይሆን ዘንድ አስቀድሞ ያወቀቸው
የልጁን መልክ እንዲመስሉ፤ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤ አስቀድሞ የወሰናቸውን
እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውን እነዚህን
ደግሞ ባረካቸው።
ወደ ሮሜ ሰዎች፤ ም፤ 8፡ 28 – 30

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ከዚህ በታች ያሉት የልዑል ቃሎች የዚህ መልእክትን ሙሉ ገጽ የያዘውን የቅጣት አመጣጥ የሚያሳዩና
አይቀር መሆናቸውን የሚገልጹ ናቸው።

እግዚአብሔር የበቀል አምላክ ነው፤ የበቀል አምላክ ተገለጠ የምድር ፈራጅ ሆይ ከፍ


ከፍ በል ለትእቢተኞች ፍዳቸውን ክፈላቸው።
የዳዊት መዝ 93 ፡ 1 – 2
የእግዚአብሔርን መሰዊያ እንወርሳለን የሚሉትን አምላኬ ሆይ እንደትቢያ በንፋስም
ፊት እንደ ገለባ አድርጋቸው እሳት ዱርን እንደሚያቃጥል ነበልባልም ተራሮችን
እንደሚያነድድ እንዲሁ በቁጣህ አሳድዳቸው በመቅሰፍትህም አስደንግጣቸው
ፊታቸውን እፍረት ሙላው አቤቱ ስምህን ይፈልጋሉ ይፈሩ ለዘለዓለም ይታወኩ
ይጎስቁሉ ይጥፉም። ስምህም እግዚአብሔር እንደሆነ በምድር ሁሉ ላይም አንተ ብቻ
ልዑል እንደሆክ ይወቁ
የዳዊት መዝ 82 ፡ 12 – 18
ለአምልኮቱ የቀናበት፣ የሜዳ ጸብቱን ፈጽሞ ይይዛል፤ ጠላቶቹን ለመበቀል ፍጥረቱን
የሜዳ ጸብት ያደርጋታል። የእውነተኛ ጥሩርም ይለብሳል፤ ማድላት የሌለበት
በርበርቴን ይደፋል። የማይሸነፍ የእውነተኛ ጋሻንም ይይዛል፤ የሚቆርጥ መዓቱ
ሰይፍን ይስላል፤ ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ ግብጻውያንን ተጣልቶ ይዋጋል።
ፈጥኖ ያገኛቸው ዘንድ በሳቱ ግብጻውያን ላይ የሚያስፈራ መአቱ በደል ነጎድ ቀንቶ
ይሄድባቸዋል። ጻድቃን ግን እንደ አማረ ቀስተ ደመና አከባበብ ከበው ረድኤቱን
በማግኘት ያመሰግናሉ። ከመዓቱም በደል፣ ነጎድ፣ ደንጊያም፣ ፈጥኖ በረዶ
ይወርዳል። የባህሩም ውኃ በላያቸው፤ ይበሳጭባቸዋል፤ ፈሳሾችም ተነዋውጠው
ፈጥነው ይከቧቸዋል። ኃይል ያለው ንፋስ ይቀዋወማቸዋል፤ ነፋስ እንደመሆኑ ድርቅ
ያደርጋቸዋል። ኃጢአት ምድሩን ሁሉ ታጠፋለችና፤ ክፉም መሥራት የሃያላኑን
ዙፋን ያጠፋልና ይበትናቸዋል።
መጽሐፈ ጥበብ ም 5 ፡ 18 – 24
የዚህ ዓለም ነገሥታት ስሙ የምድር ዳርቻን የምትገዙ መኳንንትም ልብ አድርጋችሁ
እወቁ።
መጽሐፈ ጥበብ ም 6 ፡ 1
አመፃ ትእቢትን ትቀድማለች። በትእቢት፣ በንቀት፣ የተሞላችሁ የዘመናችን ገዥዎች አለቃን ጭፍራዎች
የልዑልን ምክር፣ ፍርድና እርምጃ ንቃችሁ፣ ዛሬም አንቋቋመዋለን በሚል የአባታችሁ የዲያብሎስን ምክር
ሰንቀችሁ እጅግ ወደ ከበደው እሳትና ጨለማ እየተንደረደራችሁ ትገኛላችሁ። የእግዚአብሔር እጅ አይዝል
አይደክም በከንቱ ትፍረመረማላችሁ እንጂ፤ እየደቀቃችሁ ከመፈጸም አንዳች የሚታደጋችሁ የለም። የሰው
ዘር ልብ ልትል ሲገበህ በአመፃህ ገፍተህበታል። በወቀሳው አልተፀጸትክ፤ በፍርዱ አልደነገጥህ፣ የፍርዱ
የአፈፃፀም የመጀመሪያ ደረጃ እርምጃ ዓለምን ሲያናውጥ ያንተ ድንጋይ ልብ ግን ዛሬም በልዑል ቁጣ ላይ
ነዳጅ ያርከፈክፋል።

ልዑል እንዲህ ይላል! ለሞት የሆነ ወደ ሞት፤ ለሰይፍም የሆነ ወደ ሰይፍ፤ ለረሃብም
የሆነ ወደ ርሃብ፤ ለምርኮም የሆነ ወደ ምርኮ ትላቸዋለህ፤ ስይፍን ለመግደል፣
ውሾችንም ለመጎተት፣ የሰማያትንም ወፎች የምድርንም አራዊት፣ ለመብላትና
ለመጥፋት፣ አራቱን አይነት ጠፋት አዝባቸዋለሁ። ይላል ልዑል ትንቢተ ኤርሚያስ
15 ፡ 2 – 4
4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ይህ ቃል በናንተ ላይ ተፈጻሚ ይሆናል። ዛሬ በምናየው ነገ በሌለው ጥበብ፣ በገዥዎችህ ጉልበት ሀብትና


ገደብ በሌለው የውሸት ተስፋቸው ታምነሃል። የዛሬው መልእክት አዲስ ፍርድ ሊነግርህ አልመጣም። የተሟለው
የፍርድ ቃልና አፈፃፀም ተሟልቶ /ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በሚል ርዕስ መልእክቶች 1፣ 2፣ 3/ በእጅህ
ከደረሱ ከ2 አመት በላይ ሆኖአቸዋል። ይህ መልእክት ደግም የመጣው ካየኸው እያየኸውም ካለው፤ የመጀመሪያ
ደረጃ እሳትና በትር ወደ ሁለተኛው የከፋ የእሳት ወንፊት መሸጋገርህን ለማርዳትና ለምን! እንዴት፣ ምንስ
ተፈጸመ፣ ምንስ ቀረ፣ ዓለም እንዴት መልክቶቹን ተቀበለች። በመጀመሪያ እርምጃ ምን ተፈጸመ፣ ያሁኑስ
መልእክት ለምን መጣ! ጉዳቱስ ጥቅሙስ የሚለውን ሁሉ አጥርተህ እንድታይበት ታስቦ የመጣ ነው። እሰከ
ዛሬ የናቅኸው ሁሉ የዚሁ ሸውራራነትህን ፍሬውንና ቀጣዩን ሸክምህን ታይበታለህ። በመልእክቶቹ የተደሰትክ፤
በጊዜው ርዝመት ብቻ የተከፋህ ሁሉ በሰዓቱና በጊዜው ልዑል በፈቀደበት ሰዓት ተፈጻሚ እንደሚሆን፤
አንዳችም ከመልእክቶቹ ሳይፈፀም የሚቀር እንደሌለ እንድታረጋግጥና በውስጥህ የገባውን ጠላት የዘራብህን
ጥርጣሬ እንድታስወግድ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። የነኖኅ፣ የነአብርሃም፣ የነሙሴ የእምነት ልጅ አምላካችን
የተናገረውን አያደርግም ብሎ አይጠራጠርምና።

ልዑል እንዲህ ይላል! ኖኅ ገና ስለማይታየው ነገር ተረድቶ እግዚአብሔርን እየፈራ


ቤተሰቦቹን ለማዳን መረከብን በእምነት አዘጋጀ፤ በዚህም ዓለምን ኮነነ፤ በእምነት
የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ።
እብራውያን 11፡ 17
ባለመስማትህ፣ ፍርዱንም በማቃለልህ፣ በእውቀትህ፣ በሀብትህ፣ ተመክተህ በመታበይ የመጀመሪያውን
የእሳት ወንፊት እያየኸውና በውስጡም ገበተህ እየተበጠርክ ትገኛለህ። በዋነኞቹ በቀደሙት ሦስት መልእክቶች
/1፣ 2፣ 3/ የተገለፁትን ፍርዶቹንና አፈፃፀማቸውን እንደተገለጸው ሁሉ የመጀመሪያውን እሳት እያየነው
እንገኛለን። ስለቀጣዩ ምን እንደሚሆን መግለጽ የዚህ መልእክት ተልእኮ ይሆናል።
የሰራዊት ጌታ ልዑልና ቸር ይቅር ባይ መሃሪ፤ ለቁጣው የዘገየ የፍቅር ምንጭና የሕይወት ሁሉ ጌታ ስሙ
ይክበር ይመስገን አሜን። ዘመናትን ፍጥረታትን የሚታዩ የማይታዩትን የፈጠረ፤ በእኛ አእምሮ ሚዳሰሰውንም
ሆነ ፍፁም ሊታወቅ የማይቻለውን የፈጠረ፤ ልዑል ጌታ ስሙ ይባረክ ይመስገን። አሜን!! የግለቱ መጠን
በምንም መስፈሪያ የማይለካ፤ የብርሃን መጠኑም በምንም መስፈሪያ የማይመዝነውን፤ የእሳት መፍለቂያ ፈጥሮ
የሚያዝዝ፣ የሚናዝዝ፣ ከአዕምሮአችንም በላይ ለሆነው ልዑልና ኃያል ጌታ ምስጋና ዘወትር ይፍሰስለት! እጅግ
ከከበሩት ቅዱሳት መላእክት እውቀት፣ ኃይል፣ ማስተዋልና መረዳት በላይ ፍፁም የረቀቀ ድንቅ ጌታን ማንም
በምንም መለኪያና አንደበት ገልፆ ሊወስነው የማይቻል አምላካችን ድንቅ ነው። እንዲሁ ብቻ እንደተሰጠን
እውቀት መጠን ስሙ ይባረክ ይመስገን እንላለን።
ዘመንም፣ ጊዜም፣ ስፍራም፣ ሁኔታም፣ ጨለማም፣ ብርሃንም፣ ሌትም ቀንም፣ ሳይገታው ለሱ ለአብ፣
ለወልድ፣ ለመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ከፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ሳያቋርጥ እንደ ንጹህ ምንጭ ውኃ፣ እንደ
አርሞንኤም ጠል ዘወትር ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ሳይቋረጥ ምስጋና ይፍሰስለት አሜን!!
እኔም እጅግ ታናሽ የምሆን ኃጢአተኛ ባርያው በኃጢአት በጨቀየና ባደፈው እንዲሁም ባልታረመው
አንደበቴ አመሰግነዋለሁ። የተሰበረ ልብን ከንጹህ ህሊና የሚመነጭን ምስጋናና ምልጃን የማይንቅ አምላክ ነውና!!
በእናቱ በቅድስተ ቅዱሳን በንጽህተ ንጹሃን ወላዲት አምላክ ምልጃ በፍቅሯ እቅፍ ልጆቹን፤ በደሙ የገዛን
እኛን ባርኮ! ለመልካሙ ቀን ለእራቱ ግብዣ የጠበቀን ሁሌም ምስጋናን ለአምላካችንና ለአባታችን ለሰራዊት
ጌታ እግዚአብሔር ልናቀርብለት ይገባል። እጅግ በሚወዳቸው አልቆ ባከበራቸው የከበሩ ሊቃነ መላእክቶች /
ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣
ቅዱስ ሳቁኤል፣ ቅዱስ አፍንኒኤል፣ ቅዱስ ሰዳክያል፣ ቅዱስ ሱርያል፣ ቅዱስ ሰላትያል፣ ቅዱስ ራሙኤል/

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ወገኖቹን እረኞቹንና ሕዝቦቹን ሌትም ቀንም በእሳት ከብቦ የሚጠብቅ ኃያል ጌታ አሁንም ሁሌም ከዘለዓለም
እስከዘለዓለሙ ምሰጋና ለክብሩ ለስሙ ይፍሰስለት አሜን። የወገኖቹን ጸሎትና ምስጋና በቅዱስ መንበሩ ፊት
ለሚያሳርጉት እጅግ ለከበሩት ቅዱሳን መላእክት አክብሮታችን ፍቅራችንና ምስጋናችን ይድረሳቸው። የኛም
የባሮቹና የወገኖቹ አምላክ የከበሩት ቅዱሳተ መላእክትም አምላክ ነውና ምስጋና ዘወትር ለሱ ይፍሰስ አሜን።
በዚህ ክፉ ዘመን ለምንገኝ የእግዚአብሔር ሕዝቦች በታላቅ መንፈሳዊ ጀግንነት፣ በጽናትና ሰማዕትነት
ያለፉትን ስለኛ በልዑል ፊት የሚማልዱትን ሰማዕቱ ጊዮርጊስን፣ ሰማዕቷ አርሴማን እንዲሁም በቁጥር የበዙትን
ሰማዕት ጀግኖችን ቅዱሳንን በልዑል ፊት ልናከበራቸው ልናመሰግናቸው ይገባናል። የምልጃቸው የዘወትር
የጸሎት ድጋፋቸው ባለእዳ ነንና!!
የአዳም ዘር አድምጥ!! መሪ ሆንክ፣ ተመሪም፣ ሀብትም ሰበሰብክ፣ የጦር ክምችትም አደረግህ፣
ታበይክ፣ ተገሰልክ፣ በውሸት ቱልቱላህ ዓለምን ሸፈንክ፣ በፈለግኸው መንገድና ዘዴ ከነፍክ፣ በረርክ፣ የትም
እንደማታመልጥ ገና በቅንጣቷ እርምጃ ልክህን አውቀሃል፤ ገናም እስከሚያንገሸግሽህ ትጋተዋልህ። ስለዚህ
በጥንቃቄ አንብብ አስተውልም ተረዳ። መልእክቱን ለሕዝብ እንዳይደርስ በማድረግ በስልጣንህ ተመክተህ
በጠብመንጃህ ታብየህ የማምለጫ ቀዳዳህን ደፈንክ!! እንግዲህ መጭውን ደግሞ ስማ!! የደፈርከው የፈጠረህን
አምላክ ነውና!!
ይህ ለአምስተኛ ጊዜ የተሰናዳ መልእክት ለምን መጣ የሚል ጥያቄ በሁሉም የመልእክቶቹ ተከታታዮች
ዘንድ የሚነሳ ጥያቄን እንደሚያስነሳ ግልጽ ነው። የመጀመሪያው ሁለተኛውም ሆነ ሶስተኛው መልእክቶች
ከ7/3/1998 ዓ.ም ጀምሮ የአንድም ሆነ ሁለት አመት ቆይታ እያደረጉ መውጣታቸው በሁሉም ዘንድ
የሚታወቅ ነው። ለ4ኛ ጊዜ የወጣው መልእክት ደግሞ በተለይ ለኢትዮጵያውያን የተዋህዶ እምነት ተከታዮች
የወጣ ሲሆን በበቂ ሁኔታ የተዳረሰም ነው ተብሎ ይታመናል። ስለመልእክቱ አንደምታና ትግበራ አግባብ በሆኑ
ርእሶች ውስጥ እናየዋለን።
የዚህ መልእክት መውጣት በዋነኛነት የሚያተኩረው፤ ለእግዚአብሔር ሕዝቦችም ሆነ በጠላትነት ለቆሙት
ሁሉ ዓለም ያለችበትን ሁኔታና አቅጣጫዋን በእግዚአብሔር ቃልና በመልእክቶቹ ሚዛንነት የምናይበትና
የምንረዳበት እንደሚሆን ሁሉም እንዲያውቀው እናስገነዝባለን። በተጨማሪም በመልእክቶቹ ሚዛንነት ሁሉንም
ነገሮች በማስተዋል የምናይበትና የምንገነዘብበት ነው። በትክክል እየተጓዙ ላሉት የእግዚአብሔር ወገኖች ደግሞ
እንዲበረቱ፤ እንዲፀኑ እንዲሁም የተጣመሙት እንዲቃኑ፣ የሳቱት እንዲታረሙ፣ የደከሙት እንዲነቁ እናም
የበረቱ ለሌላ ወንድማቸው መንፈሳዊ ጉልበት እንዲሆኑ ጭምር በመታሰቡ ነው።
ፍርዱ የሚመለከታቸው የዲያብሎስ ልጆችና የጥፋት ሰዎች በእግዚአብሔር ቃልና በቃሉም መሰረት ለዘመኑ
ትውልድ ከልዑል በኔ እጅግ ታናሽ በሆነው ባሪያው በኩል በተገለጡት 3 ዋነኛ መልእክቶች በመመስረት
ለፍርድ የተጠበቁ ሁሉ ምን ላይ እንዳሉ የሚዳስስም ነው።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በሚለው ሙሉ መልእክቶች መልእክት 3 ገጽ 25 እንዲህ ይላል
በሁለቱም መልእክቶች እንደተገለጸው ዓለም ከ12/12/2000 ዓ.ም ጀምሮ ወደማበጠሪያው ወፍጮ
ገብታለች። ማበጠሪያው ትልልቁን ቆሻሻ የሚያስወግደው ሰፋ ያለ ቀዳዳዎች ባሉት የመጀመሪያ መሳሪያ
ሲሆን፣ ሁለተኛው ከአንደኛው የጠበበ ሶስተኛው ከሁለተኛው እየጠበበ የሚመጣ የእሳት ወንፊት ጀምሮአል።
አጅግ ከብዶም ይቀጥላል። ይላል!!
ከመልእክቱ ጭብጥ እንደምንረዳው የእሳት ወንፊቱ ጅምሩን አሳየን እንጂ ገና ሰልፍና ወረፋ ይዞ የሚጠብቀንን
የጥፋት ማዕበል አላየነውም። በልዑል ግምጃ ቤት ለጥፋትም ይሁን ለበረከት ምንም ዓይነት መጠንና ልኬት
የማይበጅለት በሰውም ይሁን በሌላ ፍጥረት የማይገመት ክምችት አለ። የምንበጠርበት የእሳት ወንፊት ቁጥር

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የለሽ ነው። በቀጣዩ በዝርዝር እንደምናየው የእግዚአብሔር የቁጣ ፍሰት አመጸኞችን፣ ትእቢተኞችን፣ የዲያብሎስ
ደቀመዝሙሮችን፣ ሃሰተኞችን፣ ጨካኝ ገዢዎችንና ምንዝሮቻቸውን በቃሉ የሚነግዱ ደፋሮችን አመንዛሪና
ግብረ ሰዶሞችን፣ ነፍሰ ገዳዮችን፣ ነጣቂ ዘራፊዎችን፣ በሀብትና በእውቀታቸው የተመኩትን ልዑልንና ቃሉን
የካዱና ያቃለሉትን፣ ዘረኞችን በደሙ የገዛቸውን ያስጨነቁ ሁሉ፤ ከምድረ ገጽ እስከሚጠፉ ድረስ፤ እንዲሁም
በፍርድ ተጠርገው እስከሚካተቱ፤ እንዲሁም እንደመልእክቱ አሜን ብለው እጃቸውን ለእግዚአብሔር ባሮች
እስከሚሰጡና እስከሚንበረከኩ ድረስ የቁጣው ፍሰት መጠኑን እየጨመረ ይሄዳል እንጂ አይቆምም።
ከላይ ስለተጠቀሱት አመጸኞች ልዑል ምን አለ . . .
እውነትን በዐመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በኃጢአተኝነታቸውና በዐመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ
ከሰማይ ይገለጣልና እግዚአብሔር ሰለገለጠላቸው ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጽ
ነውና። የሚታየው ባሕርይ እርሱም የዘለዓለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ የተሠሩት
ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና። ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስለአላከበሩትና
ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ። ነገር ግን በሃሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ።
ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ የማይጠፋውን የእግዚአብሔርን ክብር በሚጠፋው ሰውና በወፎች አራት እግር
ባላቸውም በሚንቀሳቀሱትም መልክ መስለው ለወጡ።

ስለዚህም እርስ በእርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት


ወደ እርኩስነት አሳልፎ ሰጣቸው። ይህም የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት ስለለወጡ
በፈጣሪም ፈንታ የተፈጠረውን ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው። እርሱም ለዘለዓለም
የተባረከ ነው። አሜን። ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው
ሴቶቻቸውም ለባህሪያቸው የሚገባውን ሥራ ለባህሪያቸው በማይገባው ለወጡ፤
እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባህሪያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ
በርሳቸው በፍትወት ተቃጠሉ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስህተታቸው
የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ። እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን
እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው። ዐመፃ
ሁሉ፤ ግፍ፤ መመኘት፤ ክፋት ሞላባቸው። ቅናትን፣ ነፍስ መግደልን፣ ክርክርን፣
ተንኮልን፤ ክፉ ጠባይን ተሞሉ። የሚያንሾከሽኩ ሃሜተኞች፣ አምላክን የሚጠሉ፣
የሚያንገላቱ ትእቢተኞች፣ ትምክህተኞች፣ ክፋትን የሚፈላልጉ፣ ለወላጆቻቸው
የማይታዘዙ የማያስተውሉ፣ ውል የሚያፈርሱ፣ ፍቅር የሌላቸው፣ ምሕረት ያጡ
ናቸው። እንደነዚህ ለሚያደረጉት ሞት ይገባቸዋል። የሚለውን የእግዚአብሔርን ሕግ
እያወቁ እነዚህን ከሚያደርጉ ጋር ይስማማሉ እንጂ አድራጊዎች ብቻ አይደሉም።
ወደ ሮሜ ሰዎች ም፤ 1፤ 18 – 32
የሰው ዘር ልብ በል ከጠፋህም ምን ይደረግ እያደመጥከው እያየኸው መጥፋት ነው። ፍርድህን ጉዞህንም
እየተመለከትከው መሄድ ነው።
የዚህ መልእክት ዳሰሳ ሰፊና ማስተዋልን፤ ግንዛቤን፤ ትእግስትን፤ የእምነት ጽናትን፣ ለመላው የእግዚአብሔር
ሕዝብ ለማስጨበጥ እንደታለመ ሁሉ በቃሉም ሆነ በዋናው መልእክት /ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን/ በመልእክት
3 ገጽ 3 እንደተገለጸው የመዋቀሻው ዘመን አልፏል። አሁን በዐይናችሁ እንደምታዩት፣ በጀሮአችሁም
እንደምትሰሙት ዓለም በምጥ ጅማሮ ውስጥ ናት። ስለሆነም ከእግዚአብሔር አገልጋዮችና ባሮች መንፈሳዊውንም
ሆነ ሥጋዊውን አመራር፣ እንደ ልዑል ትእዛዝና ፈቃድ መስጠት ግድ ነው። የኔም ሆነ የወንድሞቼ የኃላፊነት
ግዴታም ነው። ጭንቁም እየበረታ ሲመጣ በጎችን ማረጋጋት፣ መጽናናት፣ ማጽናት ወደ መልካሙ ስፍራ
መምራት አለብንና!!

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ለመንጋው መሰማሪያ መመሰጊያ፣ መጠለያ ማሳየት ወደዚያም መምራት የእረኞች ግዴታ ነው። ከበጎቹ
መቀላቀል የማይገባቸውን ፍየሎች፣ ተኩላዎች በፍርድ እንዴት እንደሚጠበቁ፣ ማረፊያቸውንም ያውቁት
ዘንድ ማድረግ የግድ ይላል። ተግሳጽን ንቀው፣ ትእዛዝን አፍርሰው፣ በአመጽ አድገው፣ በክፋት አርጅተው፣
ለመልካሞች እንቅፋትና ጥፋት ሆነው ሁሌም እንደማይቀጥሉ ዳኛው ልዑል በቃሉ መሰረት እንደሚፈርድባቸው
ሊያውቁት ይገባል። ይህንንም ኃላፊነት የተሸከሙ የበጎች እረኞች ከመንጋቸው ተኩለዎችን ማራቅና በጌታ ቅን
ፍርድ ስፍራቸውን ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3፣ ገጽ 3 ይላልና መልእክቱ ሰዓቱን ጠብቆ የመጣ ነው።

ስለዚህ ወንድሞችን ብታሳስብ በእምነትና በተከተልከው በመልካም ትምህርት ቃል


የምትመግብ የኢየሱስ ክርስቶስ መልካም አገልጋይ ትሆናለህ። ነገር ግን ለዚህ ዓለም
ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት እራቅ። እግዚአብሔርን
ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ። ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት
ይጠቅማልና፡ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣውን ሕይወት ተሰፋ
ስለአለው ለነገር ሁሉ ይጠቅማል።
ወደ ጢሞትዮስ 1 ፡ 4፡ 6 – 8
ይህ ዘመን እጅግ ክፉ ዘመን ነው። በተለይም በአምላካችን የታመኑትን በውጊያው ግንባር ቀደምት
የሆኑትን የልዑል ባሮችና እረኞች በእጅጉ የሚፈትን መሆኑን ልታውቁና ልትረዱ ይገባል። በጎችን መጠበቅ፣
ግልገሎችንና ጠቦቶችንም ማሰማራት ልዑል የሰጠው ታላቅ ኃላፊነት ነው። ዘመናችን ካቶሊኮች፣ መናፍቆች
ተሃድሶዎች፣ ቅባቶች፣ ተረት አምላኪዎች፣ ጣኦትንና ቀጥታ ዲያብሎስን አምላኪዎችን ከመንጋው አርቆ
መጠበቅን የሚሸፍን ታላቅና በልዑል የከበረ ሥራ ነው። ለታመንለት አምላካችን ታዘን ለወገኖቻችን ትክክለኛውን
መንገድ ልናሳያቸው አስፈላጊና ሁሌም የምንተጋበት ሥራችን ሊሆን ይገባል። ተኩላዎችን ደግሞ በፍርዱ ቃል
እንዲገሰጹ፣ ለቅጣቱም እንዲጠበቁ ልዑል በሰጠን መንፈሳዊ ስልጣናችን አስረን ለመጨረሻው የቅጣት ሰዓት
እንዲጠበቁ ማድረግ ማለት ነው።
ከላይ ለመልእክቱ መግቢያ የሚሆነውን ጥቅል ማገናዘቢያ አሰቀድመናል። ቀጣዩ በዝርዝር የምናያቸውን
ርእሶች እያየን ወደ ትንታኔአቸው በማለፍ በዝርዝር ካስቀመጥን በኋላ መልእክቱን እንደመድማለን።

የሚተነተኑ ርእሶች

1. ቀደምት መልእክቶችን /1፣ 2፣ 3/ እናም መልእክት 4 /በኢትጵያውያን የተዋህዶ ልጆች ብቻ/


ዓለምም ኢትዮጵያውያንም እንዴት ተቀበሉት።
2. ከመልእክቶቹ መውጣት በኋላ ዓለም ምን ገጠማት፤ አሁንስ በምን ሁኔታ ላይ ትገኛለች። በመልእክቶቹ
አንጻር ቅጣቱ በምን መጠን እየተከናወነ ይገኛል።
3. ከዚህ ሁኔታ በኋላ መጪው ምንድነው
4. ኃያላን መንግሥታትና ቀደምት የወጡትን መልእክቶች አቀባበላቸውና እንዲሁም ቀጣዩ እጣ ፈንታቸው
5. የተለያዩ የእምነት ተቋማትና ስለ መልእክቶቹ ያለቸው አሰተያየት፤ በመጪው ቀጣይ 2ኛ ደረጃ
የእሳት ወንፊት እጣ ፈንታቸው።
6. በዚህ ዘመን በመልእክቶቹ የፍርድ ሚዛን ውስጥ የወደቁት መሪዎችና ጭፍራዎቻቸው በቀጣዩ እርምጃ
ምን ይገጥማቸዋል።

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

7. በመጀመሪያ የእሳት ወንፊት የተደረገ ብጠራና በቀጣዩ የሁለተኛ ደረጅ የእሳት ወንፊት መጪ ሁኔታ
በንጽጽር ሲታይ።
8. አገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪየውና በመጪው ወንፊት ውስጥ፤ እንዲሁም ገዥና ምንዝር ሹማምንቶች
እጣ ፈንታ
ሀ/ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበት ሁኔታና ቀጣዩ የልዑል እርምጃ ስለመሪዎችዋ፣
ስለካህናቶችዋ፣ ስለወጣቶቹዋ፣ ስለገዳማት፣ ስለ መነኮሳት እንዲሁም ስለምእመኖቹ
ለ/ በአገራችን የተለያዩ እምነቶች ሥራና እንድምታው በመልእክቶቹ ሚዛንነት ቀጣዩ እጣቸው።
ሐ/ የፓለቲካው ስርዓት ተጠቃሚና አራማጆች በአገራችን ላይ እየፈጸሙ ያሉት ጥፋትና መላ አገሪቱን
የዳሰሰ ወንጀላቸው። በሁለተኛ ደረጃው የእሳት ወንፍት ውስጥ ዕጣ ፈንታቸው።
መ/ ኢትዮጵያውን የተዋህዶ ልጆችና በእስካሁን የመጡት ጎዳናና ከጽናታቸው ከልዑል አባታቸው፣
ከእናታችን ድንግል፣ ከቅዱሳን የከበሩ መላእክት የሚፈስላቸው በረከት።
9. አውሮፓና በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበትና በሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚገጥማት ዕጣ
10. ሰሜን አሜሪካና በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበትና በ2ኛው የእሳት ወንፊት የሚገጥማት ዕጣ
11. ኤሽያ በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበትና በ2ኛው የእሳት ወንፊት የሚገጥማት ዕጣ
12. አውስትራሊያ በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበትና በ2ኛው ዙር የእሳት ወንፊት የሚገጥማት ዕጣ
13. ደቡብ አሜሪካ በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበትና በ2ኛው ዙር የሚገጥማት የእሳት ወንፊት
14. አፍሪካ በመልእክቶቹ ምዘና ያለፈችበትና በመጪው 2ኛው ዙር የሚገጥማት የእሳት ማበጠሪያ
15. የእስካንዲኔቪያ አገሮች በመልእክቶቹ አንጻር በመጪው 2ኛው ዙር የሚገጥማቸው የእሳት ማበጠርያ
16. በተለይ ዓለምን ለመቆጣጠር በታለመ ንዩክለር፣ ኬሚካል፣ ባዬሎጂካል፣ ኒዩትሮን፣ አልፎም በህዋ
ላይ የተጠመዱ የጨረር የኒዪክለርም መሳሪያ ለታጠቁ አገሮች እጣ ፈንታ
17. ስለ አባቶች፣ እናቶች፣ ሰለወንድሞች፣እህቶች በጥቅሉ ስለተመረጡ የልዑል ባሮች /አገልጋዮች/ ላይ
የተፈጸመ ጥቃትና በዚህም ላይ ከልዑል የተሰጠ የቅጣት ውሳኔ፣
18. የእምነት መርከባችን /የኖኅ መርከብ/
19. ትንሽ መልእክት ለልዑል ባሮች
20. በመልእክቶቹ ስርጭት ላይ ሰለሚሠሩ ጥፋቶች እናም ጥቀታቸው
21. ሺው ዘመን ም ይላል ምንስ እንደሚሆን ያስረዳናል
22. ማጠቃለያ

1/ ቀደምት መልእክቶችን /1፣ 2፣ 3/ እናም መልእክት 4 / ለኢትዮጵያውያን የተዋህዶ


ልጆች/ (ዓለምም ኢትዮጵያውያንም እንዴት ተቀበሉት)

ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም የላል። በሥራቸው ጎሰቆሉ ረከሱ በጎ ነገርን የሚሠራ
የለም የሚያስተውል ልዑልን የሚፈልግ እንዳለ ያይ ዘንድ፣ እግዚአብሔር ከሰማይ
የሰውን ልጆች ተመለከተ፣ ሁሉ አመጹ፣ በአንድነትም እረከሱ፣ በጎ ነገርን የሚሠራ
የለም፣ አንድም ስንኳ የለም፣ ጉሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው በምላሳቸው
9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ሸነገሉ፣ ከከንፈራቸው በታች የእባብ መርዝ አለ፣ አፋቸው መርገምንና መራራን


ተሞልቶአል፣ ደምን ለማፍሰስ እግራቸው ፈጣን ነው፣ ጥፋትና ጉስቁልና በመንገዳቸው
አለ፣ የሰላምን መንገድ አያውቋትምና፣ እግዚአብሔርን መፍራት በዓይናቸው ፊት
የለም፣ ህዝቤን እንደ እንጀራ የሚበሉ፣ ኃጢአት የሚሠሩ ሁሉ በውኑ አያውቁምን!
እግዚአብሔርን አይጠሩትም፣ በዚያ በታላቅ ፍርሃት እጅግ ፈሩ፣ እግዚአብሔር
በጻድቃን ትውልድ ዘንድ ነውና! የድሆችን ምክር አሳፈራችሁ፣ እግዚአብሔር
ግን ተስፋቸው ነው። ከጽዮን መድኀኒትን ለእስራኤል ማን ይሰጣል፤ እግዚአብሔር
የሕዝቡን ምርኮ በመለሰ ጊዜ ያዕቆብ ደስ ይለዋል፣ እስራኤልም ሐሤት ያደርጋል።
ዳዊት መዝሙር 13(14)
ሁሉን ለናቃችሁ እግዚአብሔር የለም ለምትሉ ምድሪቱን የከደናችሁ ሁሉ አድምጡ!
በ7/3/1998 ዓ.ም ዓለም ሁሉ ያደምጥ ዘንድ ከሰራዊት ጌታ የተላለፈ /መልእክት አንድ/ ለሁሉም የሰው
ዘር የተበተነ ሲሆን፣ በተለይም ለዓለም ኃያላን መንግሥታት በየኤንባሲዎቻቸው እንዲደርሱ ተደርጓል።
መልእክቱ በአማርኛና በእጅ ጽሁፍ የተዘጋጀ ነበር። መልእክት አንድን ሁሉም እድል የገጠመው እያየው እያለ
በ27/9/2000 ዓ.ም 2ኛው መልእክት በአማርኛም በእንግሊዝኛም በኮምፒውተር ሕትመት ተጽፎ በመላው
ዓለም ላሉ ሕዝቦችና መሪዎች ደርሶአል። ከዚህ ክስተት በኋላ ሁለቱም መልእክቶች የልዑልን ፍርድ ያዘሉ
ናቸውና ለሁሉም የሰው ዘር እድል በመስጠት ፈጥኖ ንስሓ እንዲገባ በማስጠንቀቅ በጥፋት ጎዳና እየገሰገሰ ያለውን
የአዳም ዘር ወደ ፈጣሪው ጉያ እንዲሰበሰብ ለማድረግ የተደከመበት ነበር። ሆኖም የሰው ልጅ ከመነሻውም
የፈጣሪውን ምክር፣ ተግሳጽና አባትነት የናቀ ነበርና ለሺዎች ዘመናት የሚፈስለትን የተመለስ ምክርና ተግሳጽ
አይቀበልም። አልተቀበለምም። ምክንያቱ ደግሞ እግዚአብሔርን ለማወቅ የሚፈልገውና የሚደክመው ዓለም
ከልጅነቱ ጀምሮ ባስጨበጠችው የእውቀት መነጽር በመሆኑ ሲሆን፣ ዛሬ የምናየው ጥፋትም ሊቃና ያልቻለው
ብዙ የዘመኑን ትውልድ በምሁርነትና በእውቀት ካባ ሸፍኖ፣ እንዲመጻደቁና በተንሸዋረረ እይታቸው እየዘበቱና
እየተቹ በእውነት እየተሳለቁ ወደ መፈጸማቸው እንዲሄዱ አድርጎአቸዋል። ልዑል የሰራዊት ጌታ የቅርብ አምላክ
እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለም፣ ከእውነት ቃል በመስማት እንዲያው በሞኝነት በማመን በዚያም ጸንቶ በተግባር
አውሎ በተሰበረ ልብ፤ በቅንነት ተጉዞ ለዛሬው መመረጥ ይደርስ ዘንድ ማንም አልከለከለውም ነበር። በየስርቻው
የወደቁ ማንም እዚህ ግቡ የማይላቸው ለበጎው ቀን በልዑል ጸድቀው ታትመዋል።
እግዚአብሔር አንድ አይደለም ሁለት፤ ከ7 ሺ ዓመቶች በላይ ታገሰ ተሸከመ፣ ወቀሰ፣ ገሰጸ፣ ቀጣ፣ ማረ፣
መልሶም መላልሶም የሰውን ልጅ ሁሉ ዓመጻ በምሕረት ከደነ። አያት ቅደም አያቶቻችን አጠፉ፣ ተጸጸቱ፣
ምሕረቱን አፈሰሰላቸው። ዘመኖችን በዚሁ መልክ በምሕረቱ ስፋት፣ በቸርነቱ ብዛት፣ በፍቅርነቱ ጽናት
መለኪያ ባልተበጀለት ትእግስቱ እስከዚች ሰዓት አዘለን፤ ነገር ግን ማን አስተዋለ? ማንም።
ከ1998 ዓ.ም መጀመሪያ ጀምሮ የዓለም የአመጽ ጉዞ የሚገታና የልዑል የዘመናት ትእግስት ማለቁንና
ወደ ፍርድ ሂደት መግባቱን በማሳወቅ፤ ለአዳም ዘር በሙሉ የመጀመሪያው የፍርድ ውሳኔ አሳወቀ። ነገር
ግን መልእክቱ የደረሳቸው የሚበዙት አቃለሉት በመቀጠል ከ2 ዓመት ቆይታ በኋላ በ27/09/2000 ዓ.ም
የመጨረሻ የሆነውን የፍርድ ቃል ገለጸ። የሰው ትእቢት ማለቂያ የለውምና የልዑልን ፍርድ አቃለለ፣ ናቀ፣
እንኳን ሊተገብረው ሊሰማውም ተጸየፈ። ይሁንና የእግዚአብሔር ሥራ ሰውም ሰማ አልሰማ አይቋረጥመና፤
በስተመጨለሻ ፍርዱን ወደአፈጻጸም የሚያሸጋግረውን ሁሉንም የዓለም አካል የሚዳስሰውን የአፈጻጸም ውሳኔ
ከአንድ አመተ ተኩል በኋላ በ19/07/2001ዓ.ም ወጣ። መልእክቱ በአማርኛም በእንግሊዘኛም የወጣ ሲሆን፤
በዚህ መልእክት መውጣት ሰዓት፤ ለየት ያለው ነገር ቢኖር፤ ከመጀመሪያው እስከ አፈጻጸም ያሉት መልእክቶች
በሙሉ አማርኛውም እንግሊዘኛውም በአንድ ጥራዝ በማተት እንግሊዘኛውን በአንድ ጥራዝ፤ አማርኛውም
በአንድ ጥራዝ በማድረግ ለዓለም ሕዝብና ለኢትዮጵያ ሕዝብም በስፋት ለማዳረስ ተሞክሮአል።

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ከዚህ ሁኔታ በኋላ ለኢትዮጵያውያን የተዋህዶ አማኞች ብቻ የተመለከተ 15 ገጽ የያዘ መልእክት


በ1/6/2002 ዓ.ም እንዲወጣ የተደረገ ሲሆን መልእክቱ በስፋት ሊዳረስ ችሎአል። ይህ መልእክት ለ3 ጊዜ
ያህል ለአገሪቱ መሪ የተጻፈላቸውን ብርቱ ማሳሰቢያ የያዘ ሲሆን የተቀረው ግን የአገራችንን አገዛዝ ማብቂያ
ሰዓት መድረሱን በመግለጽ የምሕረትና የቅጣት እድልን ለገዢዎቻችን ሰጥቶ ነበር። ይሁንና በዚህ እድል
ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። ቀጣዩን አጣቸውን በሌሎች ርእስ ውስጥ እናየዋለን። በጥቅሉም፤ ዓለምም ሆነች
አገራችን እንደየእምነት መሰረታቸው፣ እንደየእውቀት ባለቤትነታቸው፣ ሁሉም የየራሱን ግምት አዘልና በዓለም
እውቀት በገበየው መነጽር በማየት ሀሳቡን ሲሰነዝር ቆየቷል።
የዓለም ሕዝብ፣ እንዲሁም ኢትዮጵያውን ላስታውሳችዋሁ! መልእክቶቹ ሁሉ /1፣ 2፣ 3/ ለኢትዮጵያውያን
የተዋህዶ እምነት ተከታዮች /15 ገጽ የያዘ መልእክት/ እንደደረሳችሁ ከላይ ላስረዳችሁና ላስታውሳችሁ
ሞክሬአለሁ። እጅግ ውስን ሰዎች ቢያደምጡም 99 ከ100 ወይም ከ10 ዘጠኙ እጅ ንቆ ትቶታል። እኔንም
አጭበርባሪ፣ ቅዠታም፣ ገዢው መንግሥት የላከው ሰላይ፤ ሌላም እጅግ ጸያፍ ስሞችን ቢለጥፉብኝም፣
ድርጊቱም፣ ቢያመኝም፣ ተደሳቹም ዲያብሎስ ቢፈነጥዝም፣ ለኔ ለግሌ ሽልማቴ፣ ልዑል የሰጠኝ ትንሽ
የመስቀል ሸክሜ ናት። ዓለም የኔን ስብእና ያጠናል። ከአገሬ መንግሥት ጀምሮ የዓለም ኃይላት ጭምር የጋራ
ጠላታቸው አድርገውኛልና ተባብረው ያልተቋረጠ ክትትል ስልታዊ ጥቃት ሲያከናውኑ ኑረዋል። ግን ቀድሞም
ነግሬአቸዋለሁ አማካሪአቸው ዲያብሎስም ብልጥ ነው፤ ጥበብን አልተነጠቀምና። ከቀይ መስመር እንዳያልፉ
በማድረጉ እስከአሁን በጠርዝ ቆመዋል።

አቤቱ አንተን ጠርቻለሁና አልፈር፤ ክፉዎች ይፈሩ፤ በሲኦልም ዝም ይበሉ፤


በድፍረትና በትእቢት በመናቅም፤ በጻድቅ ላይ የሚናገሩ፤ የሽነገላ ከንፈሮች ድዳ
ይሁኑ፤ ባንተ ለሚያምኑ በሰው ልጆች ፊት ያዘጋጀሃት፤ ለሚፈሩህም የሰወርሃት
ቸርነትህ እንደምን በዛች፤ በፊትህ መጋረጃ ከሰው ክርክር ትጋርዳቸዋለህ።
ዳዊት 30 (31)፤ 17 – 20
የሚደረገው ይደረግ ዘንድ ለሁሉም ሰዓት ስላለው በዚህ አልገረምም። የሰው ዘር ብርቱና በቀላሉ የማይሰበር
ልብ አለው። የፈጠረውን አምላክ ክዶ፣ ንቆ፣ ባልሰራው ዓለም፣ ባልሰራው የራሱ ገላ በስብእናው፣ በተሰጠችው
ብናኝ እውቀት፣ በአጭር እድሜው፣ በሰበሰበው ሀብት፣ በያዘው ስልጣን ፍፁም በመታበይ የፈጠረውን
አምላክ ምክርና ተግሳጽ ይንቃል። መልእክቶቹ ሁሉ የመጡት እሱን እንደ ኖኅ ዘመን ሰዎች እንዳይጠፉ እንደ
ሰዶምና ገሞራው እሳት እንዳይበላው ነበር። አልሆነም። ዓለምም ኢትዮጵያውያንም (ዓለም አንድ መንደር
ሆናለችና) አልሰሙም። መልእክቶቹንም ናቁት እንጂ አልተቀበሉትም። ከጥቂቶቹ የታደሉት በስተቀር። ስለዚህ
ያለመስማትን ፍሬ በዚህ የ5ኛው መልእክት ውስጥ ሁልህም የአዳም ዘር በሙሉ ትረደዋለህ። ሰው በደነገገው
ስርዓትና ሕግ ብታምጽ፤ ሰው ፍጡሩ የሰው ዘር የሰራው ስለሆነ ምደራዊና ፈራሽም በመሆኑ የሁሉም ጌታ
በሆነው ልዑል እግዚአብሔር ትዳኛለህ፤ እንደ ፈቃዱ ካደረግህ ታመልጣለህ፤ የራሱን የሁሉ ጌታን ትእዛዝና
ፈቃድ ካቃለልህ ደግሞ የሚታደግህ ኃይል ሰማይም ብትወጣ ምድርም ብትገባ ስለሌለ የሚያድንህ የለም።

2/ ከመልእክቶቹ መውጣት በኋላ ዓለም ምን ገጠማት! አሁንስ በምን ሁኔታ ላይ


ትገኛለች! በመልእክቶቹ አንጻር ቅጣቱ በምን መጠን እየተከናወነ ይገኛል!

መልእክቶቹ በሙሉ ጊዜ ወስደው ሁሉም ሰው ይረዳው ዘንድ በማሰብ፤ ባላቻኮለ ሁኔታ ተልእኮአቸውን
እያረጋገጡ ይገኛሉ። ከመልእክቶቹ መከሰት በኋላ ዓለም ብዙ ጥፋት ገጥሞአታል። የመጀመሪያውን የእሳት
ወንፊት ሁሉም ሰው እያየው ይገኛል። በዓለም ላይ ሁሉ የጫጉላው ዘመን አልፏል። ዛሪ ስለአንድም ሁለትም
ጥፋት ሰምተን ሳናበቃ በሌላ አቅጣጫ ደግም የሌላን አደጋ መከሰት እንሰማለን።

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ዓለም የኢኮነሚው ቀውስ ንጧታል ግሽበት፣ የበጀት ጉድለት፣ የገንዘብ ቀውስ፣ የባንኮችና ኢንሹራንሶች
ክስረት፣ የጅምላ መሸቃቀጫዎች ውዥቀት፣ የመላክና የማስገባት መቀዝቀዝ፣ ጥልቅ የሆነ ኢኮኖሚ መቀዝቀዝ፣
ሥራ ማጣት፣ ረሃብ፣ ስደት፣ የተለያዩ ንግዶች ክስረት፤ መንግሥት እንደ መንግሥት ያለመሆን፣ በየትኛውም
የዓለም ክልል በአሁኑ ሰዓት ያሉ መሪዎች በሙሉ ማለት ይቻላል፣ ዘራፊዎች፣ አዘራፊዎች፣ ውሸታሞች፣
አመንዛሪዎች፣ ጉቦኞች፣ ጨካኞች፣ አታላዮች መሆን በተለይም እንደ አፍሪካ ባሉ አገሮች ከህዝባቸው ሥጋውን
በልተው፣ አጥንቱን ቆርጥመው የጨረሱ መሪዎች በስልጣናቸው መቀጠልና የማያፍሩ መሆናቸው፣ በጭካኔ
የደሃውን ጉሮሮ ዘግተው በውጭ ባንኮች ብር የሚያጉሩ፣ ህዝባቸውን በታንክ በጀት የሚጨርሱ፤ ለስልጣናቸው
ሁሉንም ወንጀል የሚፈጽሙ ዐይን አውጣዎችን እያየን ነው። በሁሉም ዓለም ዙሪያ ገብ የኑሮ ውድነት ሰፍኖ
ኑሮም እጅግ ተመሳቅሎ እናያለን። አዳዲስ ቀውሶችም ፈጥጠው መጥተዋል። ምሳሌም የሚሆነን ዛሬ በኃያላኑ
ውስጥ አግጦ የመጣው የእዳ ቀውስ ነው። የአሜሪካ /የባቢሎን/ የመንግሥት እዳ 16 ትሪሊዮን አልፎአል።
የአውሮፓም በቁጥር አይገለጽ እንጂ ብዙ ትሪሊዮን ሆኖአል። ይህን ተከትሎ ጠንካራ ብራችን የሚሉት
የሚወድቅበት ሁኔታ ተፈጥሮአል። እንደ ቻይናና ጃፓንን የመሳሰሉ አገሮች የጌታቸውን መውደቅ በሥጋት
አየተጠባበቁ ይገኛሉ።
ይህንን የዓለም የጥፋት ጉዞ እያዩ ያሉት የአገራችን መሪዎችና ታዛዦቻቸው በሚጠፉ አገሮች ባንክ
ውስጥ ከዚህ ከደሀ ሕዝብ ግጠው 8.6 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በተለያየ ስፍራ አከማችተዋል። የተባበሩት
መንግሥታት አካል የሆነው ዩ.ኤን.ዲ.ፒ ያወጣው መረጃ ያመለክታል። በምትጠፋው ዓለም በዲያብሎስ
አባታቸው በመታመን የሚሠሩት ወንጀል እስከሚደመደሙ ድረስ የማይቆም መሆኑን ያሳያል።
የዮሐንስ ራእይ 18፤ ከ4 – 24 ይመልከቱ።
እንዲሁም ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 1 ገጽ 4 – 5 ያገናዝቡት።
ዓለም በማህበራዊ ቀውስ እየታመሰች ነው /በየትኛውም የዓለም አካል የእርስ በእርስ ግጭቶች በአብዛኛው
ስፍራ የሚታዩት የየእለቱ ክስተት ናቸው። በእምነት ፍጅት፣ በድንበር ፍጅት፣ በስልጣን ውጊያ፣ ትራንስፖርትና
ጤና መውደቅ፣ የመንግሥት በሕዝብ አመኔታ ማጣትና ሰሚ ማጣት፣ ዘወትር ከተሞች በሕዝብ መተራመስ
የባቡር የአውሮፕላን፣ የመኪና አደጋ መብዛት። በመላው ዓለም የየእለት የኑሮ ወጥቶ የመግባት ዋስትና
ማጣት ዓለም አቀፍ ፍፁም ስብእናቸውን በጣሉ፣ ሰው ቅርጽ በያዙ ልቡሰ አጋንንት እየተመራች መገኘቷ
ለሰው መብት፣ ለስእብናው፣ ለኑሮው የሚጨነቁ፣ የሚያስቡና የሚተጉ መሪዎች፣ ሙሉ በሙሉ ከዓለም
ገጽ መወገድ፤ በምትካቸው ፕሮቶኮላቸውን አሳምረው፣ ውሸትን፣ ጨካኝነትን፣ ራስ ወዳድነትን፣ ስለሌላው
ደንታቢስነትን፣ የቦዘኔ ተግባርና አንደበትን የያዙ መሪዎች መተካታቸው። ሰርቀው፣ ዋሽተው፣ ገድለው፣
የማያፍሩ ናቸውና ዘወትር ለሕዝብ ጥፋትን፣ ጭንቀትን፣ ሞትን፣ ረሃብን፣ ስደትን፣ የሚደግሱለት መሆናቸው።
የራሳቸውን ዲያብሎሳዊ ምኞት የሚያስፈጽሙበት ሕግ አውጥተው ፍርድ ገምድልነት አጽንተው የሚረግጡንን
ማየት ሁሉም ሰው የሚመሰክረው ሆኖአል።
መልእክቶቹ ከዚህ በመለስ የማይባለውን፡ የቅጣት ዓይነት ዓለም እንድታይ አድርገዋል። የቅጣቱ መጠንም
የመጀመሪያ ደረጃ የእሳት ወንፊት መሆኑን የሰው ዘር ልትረዳ ይገባሃል።
መሪዎች በየትኛውም የስልጣን ዘርፍና ዓይነት ይቀመጡ የልዑል የቅጣት ወይም የበረከቱ መሳሪያዎች ናቸው።
ለቅጣት የዋሉትም ከመሰረታቸውም በዲያብሎስ የተቃኙ ናቸውና መልካም የሚባል ነገር በአእምሮአቸው ውስጥ
አልተጻፈም። ለበረከት የዋሉት ድደጎች፣ አእምሮአቸውም ሆነ ስብእናቸው በልዑል እግዚአብሔር መንፈስ
ቅዱስ የተቃኘ ስለሆነ ለሰው ዘር በሙሉ ደስታውና እረፍቱ የሚሳሳላቸው ከልዑል የተሰጡ በረከቱ ናቸው።
እነ ሙሴ፣ እነ ዳዊትን የመሳሰሉትን ማለት ሲሆን፣ በአመጹ ምክንያት ሰው ካጣቸው ሺዎች አመታቶች
ተቆጥረዋል።

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ዓለም በፖለቲካው ቀውስ ውስጥ ናት። ዛሬ የሁላችንም ዓይን እንደሚያየው፣ ጆሮአችንም እንደሚሰማው፣
የፖለቲካ ቀውስ ሁሉንም አገር እያመሰ ይገኛል። ሕዝቦች ገዢዎቻቸውን እጅግ ጠልተዋል። መሪዎቻቸውም
በሕዝብ ፊት የቀለሉ ሆነዋል። የትኛውም ዓለም አቀፍም ሆነ አገራዊ ውሳኔ አክባሪና አድማጭ የለውም።
የምድሪቱ ገዢዎች ያደራጁዋቸው ሚዲያዎች ሁሉ ቀጣፊ በመሆናቸው አድማጭ አጥተዋል። ሁሉም ገዢ
ሳያጭበረብር ስልጣን ላይ አልወጣም። የዘመኑ ገዢዎች ፍፁም ዲያብሎሶች ለመሆናቸው ከሕዝብ ወጥተው
በጠብመንጃ ታምነው ተሸሽገዋል። በየትኛውም የዓለም ገጽታ የተረጋጋ ፖለቲካ የሚባል ነገር ከጠፋ ቆየ።
የሕዝብ አመጽም የየእለቱ ተግባርና የማያቋረጥ ክስተትም ሆኖአል።

ለተግሳጽ ወይም ለምድሩ ወይም ለምሕረት ቢሆን ሰው በሚኖርበት ዓለም ላይ


ያዘዘውን ሁሉ ያደርግ ዘንድ ፈቃዱ ወደመራቸው ይዞራል
ኢዮብ ም፤ 37 ፡ 13
ሰው በልዑል ለመፈራረድ እንዲመጣ ጊዜ አይወሰንለትም። ታላላቆችን ያለምርመራ
ይሰባብራል በእነርሱም ፈንታ ሌሎችን ያቆማል። ሥራቸውን ያው ልና፣ እንዲደቁም
በሌሊት ይገለባብጣቸዋል።
ኢዮብ ም፤ 34 ፡ 23 – 25
የሰው ዘር ልብ በል ከላይ የሚናገርህን ቃል አስተውል የእግዚአብሔርን ትእዛዝና ፈቃድ ከመፈጸም
የሚያግድ ምንም ፍጥረትም ሆነ ኃይል የለም። ለፍርድ እንድትቀርብና የሥራህን ውጤት እንድትቀበል ጊዜ
ቀጠሮ የሚሰጥህ የለም! ሥራህ በልዑል ይታወቃል፤ ፍርድህም ሳታስበው ይመጣል። መጥቶልሃልም።

የህያዋን ሁሉ ነፍስ፤ የሰውም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናት።


ኢዮብ ም፤ 12፤ 10
ዓለም በተፈጥሮ አደጋ መመታቷ የመሬት ነውጥ፣ ጎርፍ፣ እሳት፣ የሙቀት መብዛት፣ በረዶ፣ የመሬት
መንሸራተት፣ ማዕበሎች፣ ቶርኔዶ፣ ሱናሚ፣ ሃሪኬን፣ ታይፉን፣ እንዲሁም ዓለም ስም ያላወጣችላቸው
በሽታዎች ብዙ ዓይነት አደጋዎችን እያየች ሲሆን የመጀመሪያውን ምጥና አሳር እያየች ነው።
ከላይ በከፊል እንደዘረዘርነው ዓለም ከመልእክቶቹ መውጣት በኋላ ዛሬም ያሉ ያልተቋረጠ ሁሉን አቀፍ
አደጋን፣ ቀውስን፣ ጥፋትን እያስተናገደች ትግኛለች።
በእምነት ዙሪያ አስደንጋጭ ነገሮች እየታዩም ነው። /በተረት እምነት ተከታይ አገሮች ውስጥ ሙሉ
በሙሉ ማለት በሚያስችል ሁኔታ ፍጅትና አመጽ ነግሷል፣ እነ ግብጽ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ሊቢያ፣ ባህሬን፣
ቱኒዝያ፣ በመጠኑም ቢሆን አልጀሪያ፣ ሞሮኮ፣ ሳውዲ አረቢያ እናም ሌሎቹም አገሮች በአመጽ ታምሰዋል።
ይህ ጉዞአቸው ጅምር እንጂ በመልእክቱ የተሰጠው ፍርድ እሰከሚፈጸምና ሁሉም የዓለም አገሮች ትልቅም
ሆኑ ትንሽ ተንበርክከው ልካቸውን አውቀው፣ በልዑል መቀመጫ ኢትዮጵያ ለሚነግሱት የልዑል ባሮች
እጃቸውን ካልሰጡ የሚቀጥል ነው። ምድራቸው የምትረጋጋው ይህ ሲሆን። ከዚህ ውጪ መፍትሄ ፍለጋ
የሚያደርጉት ድካም ከመድቀቅና ውድቀታቸው ከመክፋቱ ውጪ የሚመጣላቸው መፍትሄና መልካም ዘመን
የለም። የገዢዎቻቸውን የጭንቀትና የመፍትሄ አመጣሁ ሩጫና ፕሮፖጋንዳ እንደተስፋ በመመገብ ለሌላ የከፋ
መከራ ከመንደርደር የዘለለ ሌላ የሚገኝ ማምለጫ የለም።
ካቶሊኮችና ውርደታቸው፣ በውኑ ጆሮ አይሰማው የለምና ውድቀት ሲጀምር ውርደት የመጀመሪያው ጉዞ
በመሆኑ ከካቶሊኮች እንማራለን። ሁሉም መሪዎችዋ በፍርሃት የተዋጡበት፣ ሁሉም የጠለቁበትን የዲያብሎስ
ዋንኛ ሥራ ይፋ ሆኖአል። ግብረ ሶዶምነት የዚችው ቤተ ክርስትያን መለያ ሆኖአል። ግብረ ሶዶምነት በተለይም

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

እናት አባት የሌላቸውን ህጻናት በመርዳት ስም፣ ሰብስበው ያውም ጳጳሳት፣ አንድ ወይንም ሁለት አይደሉም
በተለያዩ አገሮች በብዛት ተገኝተው የዓለም ሁሉ መሳለቂያ የዜና ሽፋን ማድመቂያ ሆነዋል። ዲያብሎስ
ያረጋገጠው ነገር ቢኖር፣ ካቶሊኩም፣ መናፍቁም፣ ተረትና ጣኦት አምላኪውም፣ ሁሉም የራሱና ገንዘቡ
መሆናቸውን ነው። በመላው ዓለም ጥንት የእምነት ቤት የነበሩ ዛሬ ሙዚቃ ቤት፣ ሲኒማ ቤት ሁነዋል። ከዚያ
በዘለለ በአውሮፓም ሆነ በአሜሪካ እምነት ተረት ሆኖአል። ስለዚህ ጥፋቱ ከዚህ በመለስ ሳይል ጀምሮአል።
በዚህ መልእክት እንደሚገለጸው በብርቱ ከፍቶ ይመጣል። ጠላትንም ትእቢተኛንም የዲያብሎስን ልጅ ሁሉ
ፍፁም ጠርጎ እስከሚያጠፋና እስከሚያንበረክክ ድረስ የሚቀጥል ይሆናል። ባጭሩ ዓለም የገጠማት መከራ
መጠኑም አሁን በምናየው በደረጃ አንድ ውስጥ ይገኛል።
ታላቁና ሁሉም ሊያስተውለው የሚገባው ነገር ቢኖር ይህ ነው። በስካሁኑ የመጀመሪያ ደረጃ እርምጃ ብዙዎች
መሪዎች፣ ዓለምን ያጠፉ የዲያብሎስ ዋንኛ መሳሪያዎች በዘረፉት ሀብት የሰከሩ ሞኖፓሊሰቶች፣ የኢንዱስተሪ
የዓለም አቀፍ ባንክና ኢንሹራንስ ባለቤቶች፣ የዓለምን ምስቅልቅልና ውድመት ከመጋረጃ በሰተጀርባ ሆነው
የሚያቀናብሩ፣ ጨካኝ ገዥዎች ከነእጅና እግሮቻቸው ገና አልተነኩም። እግዚአብሔር አምላክ የፍትህ አምላክ
ነውና ማንም ከቅን ፍርዱ አያመልጥም። ቀድሞ ሕዝቦቹን ይቀጣል። ለዚህም ነው ድሆች ሲመቱ፣ ሲሰቃዩ፣
ሲያጡ ሲነጡ፣ አደጋ ሁሉ ቀድሞ ሲመጣባቸው የምናየው። ልዑል የወደደውን ይቀጣል። በሥጋ ይቀጣል፣
በነፍስም በሥጋም ይቀጣል። ይህ መረዳት የሌላቸው የዘመኑ መሪዎችና ባለ ሃብቶች ከነ ምንዝሮቻቸው
ለምን እንደተጠበቁ አያውቁም። ልጁን ወደ በጎ ለመመለስ ያለ ርህራሄ የቀጣ ጌታ እኒህን የዲያብሎስ ልጆች
ለብርቱ እሳት ማስቀረቱን አይረዱም። ሞትን አንዲጠሙት አድርጎ ሰው በዘመኑ ያላየውን ብርቱ ጥፋት
አዘጋጅቶላቸዋል። ይህንንም በ2ኛው የእሳት ወንፊት ዝርዝር መግለጫ ውስጥ የምናየው ይሆናል።

3/ ከዚህ ሁኔታ በኋላ መጪው ምንድነው!

ከላይ ባነሳናቸው ርእሶች፤ በመጠኑም ቢሆንም ያለውን ሁኔታ ተመልክተነዋል። የእግዚአብሔር ሕዝብ በዚህ
ባለው የመጀመሪያ ምት ወይም እንግዳ የሆኑ የዓለም ክስተቶች ብዙዎች የመደናገጥ ስሜት ይታይባቸዋል።
ጠላት የሚያርፍበትን በትር ምንም ቢያደቀው አለሁ ይላል እንጂ ተጎዳሁ አይልም። በመሆኑም ፉከራውና
ፐሮፖጋንዳው የሚያስደነግጣቸው በእምነታቸው ብዙም ያልፀኑትን ለመሆኑ ጠንቅቀው የተረዱ ይገነዘቡታል።
ከ1998 ዓ.ም በፊት ዓለም ብዙም የነካት ነገር የለም ነበር። ከመልእክቱ መውጣት በኋላ ግን ሁሉም ነገር
ተቀየረ። ይህ የሆን ዘንድ ግድ ነው ጊዜም የተሰጠው፤ በዓለም የተተበተቡ ብዙ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ወደ
አባታቸው ጉያ እንዲሰበሰቡ ብቻ ታስቦ እንጂ፤ እንደ ዓለም ጥጋብ፤ የአንድም ቀን እድሜ መስጠት ባልተገባ
ነበር። አሁን ከምናየው የዓለም ሁኔታ በዚሁ ቢቀጥል እንኳን፤ ዓለም ለረጅም ጊዜ የመቋቋም አቅሙ የላትም።
ይሁንና አመጽን የሚሸከም አነቀልባ ከእንግዲህ ስለሌለ ቀጣዩ ጥፋት ይመጣ ዘንድ እነሆ ግድ ሆኖአል። የዚህ
መልእክት መምታትም ዋነኛው መንስኤ ይኸው ነው።
መጪው ምንድነው። ከዚህ መልእክት መውታት በኋላ ዓለም ወደ ከፋው በሰው ህሊና ወደ ማይገምተው
የዓለም ጥፋት ትሸጋገራለች። ዝርዝሩን በመጪዎቹ ርእሶች ውስጥ ታገኙታላችሁ።

4/ ኃያላን መንግሥታትና ቀደምት የወጡትን መልእክቶች አቀባበላቸው፤ እንዲሁም


ቀጣዩ እጣ ፈንታቸው።

ትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ 26፤ እንዲሁም ምእራፍ 27ን ከዚህ በታች ለተጠቀሱት አገሮች በሙሉና አጃቢ
አገሮች በሙሉ በሁለተኛው የእሳት ወንፊት ውስጥ ከታዘዙት ቅጣቶች በተጨማሪ የሚፈጸምባቸው ይሆናሉና
በማስተዋል ያንብቡት።

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

በዚህ ርእስ ስር የምናያቸው የዓለም ኃያላንን መንግሥታት እነማናቸው!

1. አሜሪካን /ባቢሎን/ 9. ካናዳ 17. እስራኤል


2. ራሽያ 10. አውስትራሊያ 18. ኖርዌይ
3. እንግሊዝ 11. ብራዚል 19. ግሪክ
4. ፈረንሳይ 12. ስዊድን 20. ቱርክ
5. ቻይና 13. ስፔይን 21. ሳውዲ አረቢያ
6. ሕንድ 14. ሆላንድ 22. ግብጽ
7. ጀርመን 15. ጣሊያን 23. ኮርያ /ሁለቱም/
8. ጃፓን 16. ኢራን

እነዚህ በቅደም ተከተላቸው የተቀመጡ አቅም አለን የሚሉ ናቸው። ከነziህ የሚያንሱት ደግሞ በዐመፃቸውም
ሆነ በኃጢአት በተነከረ ተግባራቸው ከበኩሮቻቸው የማይተናነሱ ናቸው።
እነዚህ አገሮች በሙሉ የተሟላው መልእክት በእንግሊዘኛ ተዘጋጅቶ የደረሳቸው ሲሆን ለሕዝባቸው እንዲገልጹ
ማሳሰቢያ የተሰጣቸው ናቸው። ይህ ብቻ ሳይሆን በየአገሮቻቸው ያሉ ዩኒቨርስቲዎችና ሚዲያዎች ደርሶአቸዋል።
ታዋቂ የሚባሉ ሚዲያዎች ሲ ኤን ኤን፣ አልጀዚራ፣ ፕሬስ፣ ቢቢሲ፣ ከደረሳቸው ዋንኞች ሚዲያዎች
ናቸው። ከመጽሄቶች እነ ኒውስ ዊክ፣ ዘ ኢኮኖሚስት፣ ታይም ሁሉ ደርሶአቸው የተነፈሱት ትንፋሽ የለም።
እኒህ ሁሉ ሰምተው፤ በእጃቸው ይዘው ለገዛ ሕዝባቸው የደበቁ የዲያብሎስ ሰራተኞች ከምንላቸው ውጪ
ሌላ ማን ሊባሉ ይገባል! ዛሬም እየሞቱና እየደቀቁ፣ እያዩት እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለች አህያ
ራሳቸውንም ሕዝባቸውንም ይዘው ሊጠፉ የቆረጡ ይመስላል። መሰላቸው እንጂ ከነሱ እውቀትና ብልጠት
ይልቅ የእግዚአብሔር ሞኝነት ይጠበባል።
መጪው እጅግ የበረታ ጥፋት በነዚህ መልእክቶቹን ባፈኑና በንቀትና በትእቢት በታጀሉ የዓለም ጉዶች ላይ
ያነጣጠረ ይሆናል። ሞትን እንዲፈልጉት የሚያስገድድ ስፍር ቁጥር የሌለው በርባሪና አጥፊ እሳት ይላክላቸዋል።
መልእክቶቹንም ቀንም ሌሊትም ባላቸው ሚዲያ ሁሉ ለፍልፈው ምሕረት እንዲለምኑ ያደርጋቸዋል።
መጪው በትርና እሳት ዛሬ ከሚያዩትና ካካለለው ስፋት በላይ፤ በማከል መከራቸው 7 ጊዜ 7 ተባዝቶ 49
ጊዜ እጥፍ ጉልበት አምጥቶ ከምድር ሊጠርጋቸው ይመጣል። ትርጉሙንም በምሳሌ በሌላ ርእስ እናየዋለን።
አልሰማ ላላችሁት ለእናንተ ምድሪቱንና የአዳምን ዘር ያሳታችሁና ለአባታችሁ ለዲያብሎስ እንደመስዋእት
ያቀረባችሁ። ከመምህሩ ደቀመዝሙሩ እንዲሉ፤ ከአባታቸው ከዲያብሎስ የበለጣችሁ ደቀ መዝሙሮቹ ናችሁ።
ስለዚህም ጥፋታችሁ ምንም አይነት ጥበብና ብልሃት የማይከላከለው እስትንፋስ የማይሰጥ የትም ብትሸሸጉ
የማታመልጡት እሳት ታዞላችኋል። በተለይ በፓለቲካውም፣ በእምነቱም፣ በፍርዱም፣ በኃይል ስምሪቱም፣
በመረጃ ስብሰባውም፣ በሀብት ማካበቱም፣ በጥንቆላውም፣ በምንዝርናውም፣ በጭፍጨፋውም በጥቅሉ ልዑል
ባወገዘው የአመጽ የኃጢአትና የትእቢት ሥራ በግንባር ቀደምትነት የተሰለፋችሁ በየትኛውም ደረጃ ያላችሁ መሪ
ተዋናዮቹ ትካተታላችሁ። የጥፋቱን የኃይል መጠን ዝርዝር በሌላኛው ርእስ ስር ታዩታላችሁ።
በሙሉው መልእክት /ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን መልእክት 3 ገጽ 83 /ይህን ይላል

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ይህ የውሳኔ አፈጻጸም ከወጣና ከተፈለገው አቅጣጫ መሄድ ከጀመረ ከመጀመሪያው የመድረሻ ቀን ጀምሮ
ዓለም የጠረጋውን ምንነት በሁሉም የዓለም ገጽታ፣ በሁሉም የሰው ዘር ኑሮ ዙሪያ ታያለች። ከዚች እለት ጀምሮ
በቁጥር 1 በቁጥር 2 መልእክቶች የተጠቀሱት የቅጣት አይነቶች ይፈሳሉ። ማቆሚያ የላቸውም የትኛውም
ብልሃትና ዘዴ አያቆማቸውም። እንዲያውም የሰው ልጅ ትእቢቱን ካጸና እጅግ ታየቶ የማይታወቅ ጥፋት በዓለም
ሁሉ ላይ ይሆናል።
በዚህ ሰዓት በዓለም ሁሉ ያሉ የአገር መሪዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ከነሹሞቻቸው፣ ከነአገልጋያቸው
ግንባር ቀደም ተጠራጊ ይሆናሉ። ይህ ሊሆን ይህ መልእክት መጥቶልሃል።

5/ የተለያዩ የእምነት ተቋማትና ስለመልእክቶቹ ያላቸው አተያይ በመጪው ቀጣይ


የ2ኛ ደረጃ የእሳት ማበጠሪያ እጣ ፈንታቸው።

ሁሉም የመላው ዓለም ሕዝብ እንደሚያውቀው፣ ምድራችን ስፍር ቁጥር በሌላቸው የእምነት ዓይነቶች
የተሞላች ናት። ሁሉም እውነት ከኔ ጋር ናት ይላል። በጥበብ በሀብት በቁጥር ብዛት መስፈሪያ ራሱን ለማጽናት
ሲደክምም ኖሮአል። እውነት አንድ ናት። ስለ እምነት ያለውም እውነት አንድ ብቻ ነው። እሱም ልዑል ዋጋ
የከፈለባት የተዋህዶ እምነት ናት። ሌላ እምነትና እውነት የለም። ከሷ ውጪ ያለው ሁሉ ዲያብሎስ ያደራጀው
የአምልኮት መልክ ያለው፣ በቁጥርም በዝቶ ዓለምን የሸፈነው ወደ ጨለማ የሚወስድ እየወሰደም ያለ የጥፋት
መንገድ ብቻ ነው። እስኪ እነዚህን ዋና ዋናዎቹን ሕዝብን ይዘው እየጠፉ ያሉትን በአጭር በአጭሩ እንያቸው።

እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም። ሰው በስውር ቢሸሸግ


አላየውምን? ሰማይንና ምድርን የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።
ት.ኤርሚያስ 23 23 – 24
የማሰማሪያየን በጎች ለሚያጠፉና ለሚበትኑ እረኞች ወዮላቸው።
ት.ኤርሚያስ 23 1

ሀ/ ካቶሊክ
ይህች እምነት ምን ትመስላለች እጣዋስ! በሙሉው መልእክት ውስጥ በመልእክት 3 ገጽ 26 – 30
ተበራርቶ የተገለጸ ሲሆን በአጭሩ በክርስትና ካባ፣ በፍልስፍናና በእውቀት ተሞልታ ብዙ በእውቀት እምነት
የተሞሉ ልዑልን በጥበባቸው ስለው የሚያመልኩ ሕይወት አልባ የሆኑ፣ ከእውነተኛው አስተምህሮ ከተዋህዶነት
ቀድመው ተገንጥለው የወጡ ዛሬ በቢሊዮን የተቆጠሩ ሕዝቦችን ለዲያብሎስ ምርኮ የሰጡ የልዑልን ኃይል ንቀው
ከሃዲዎች የተሰባሰቡባት ናት። በ431 ዓ.ም የተፈጠረችው ካቶሊክ ዛሬ ልትከፍለው ግድ የሚሆንባት የብዙ
በጎችን ደም ለሀሰተኛ ትምህርቷ ስትል ያፈሰሰች ናት። እንደምንሰማው ውርደቷ ቀድሞአል። ግብረ ሶዶም
ዓለም አቀፍ ነጋዴ የተዋህዶን እምነት ለማጥፋት በረቀቀ ስልት ዛሬም የምትደክም ናት። በተለይ በኢትዮጵያ
ከመናፍቃን ጋር አብራ የተዋህዶ እምነትን በጥበብ፣ በአስተምህሮ ስም በእርዳታ ስም ለማጥፋት እየጣረች
ያለች ናት። በኢትዮጵያ መንግሥት ልዩ ድጋፍ ከሚደረግላቸው ከመናፍቃን ቀጥሎ ካቶሊክ ዋናዋ ናት።
ይህች የእምነት ተቋም ከመጀመሪያው ጀምሮ የመልእክቶቹን መውጣት ተከትሎ ስውር አፍራሽ የዲያብሎስ
ሥራ ስትሠራ ቆይታለች። መልእክቱም እንዳይሰራጭ ከሚደክሙት አንዷም ናት። መልእክቱ በይፋ በሚዲያ
ከወጣ በቢሊዮኖች የተገነባው ቁጥር ቁጥር ብቻ ሆኖ እንደሚቀር በሚገባ ታውቃለች። ይሁን እንጂ ልዑል
በሷ እስር ቤት ከታጎረው በቢሊዮን የተቆጠረ ሕዝብ በሕይወት መዝገቡ ቀድሞም ያሰፈራቸው፣ እጅግ
ጥቂት ወገኖች ስላሉ በንስሓ እንዲመለሱ እስከ አሁን ጠብቆአቸዋል። የዚህን ዘመን ሕይወት አድን እምነት

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መርከብ /የኖኅ መርከብ/ የተሳፈሩትን የተገባቸውን ነጩን ልብስ የለበሱትን አሳፍራ ጉዞ የጀመረች በመሆኑ፣
የአሁኑ ቀጣዩ የከፋው ጥፋት ሲመጣ ግን ያልሰሙት በልዑል እርዳታ፣ ሰምተው በመርከቧ ተንጠላጥለው፣
ይተርፋሉ ተብሎ ይታመናል። የጭንቅ መዳን ልንለው እንችላለን። ከዚህ በተረፈ ካቶሊክ የዘራችውን ታጭድ
ዘንድ፣ እጅግ ብዙ ሚሊዮኖችንና መሪዎችዋን ገብራ ስም አጠራሯ ሳይቀር ከምድር ፊት ይጠረጋል። በጭንቅ
የሚተርፉም ካሉ ትቢያ ነስንሰው ራሳቸውን ፈጭተው በታመነበት ንስሓ ለአንዲቷ የኢትዮጵያ ተዋህዶ እምነት
እጃቸውን ከሰጡ ብቻ ነው በምድሪቱ ማረፊያ የሚያገኙት። የዚህች እምነት ውስጥ በተለይ በዓለሙ ሁሉ
ያሉት መሪዎቿ እምነቱን በጥበብ በፍልስፍና ይዘው ያሉ ናቸው። ብዙ የቲኦሎጂ ኮሌጆች ያላትና በዚያም
የሚበዙት አገልጋዮቿ፣ ቀሚስ ለባሽ ዲያብሎሶች፣ ቃሉን በፍልስፍና በጥበብ ሰንጥቀው፣ በይደውና ደርተው
የተሸከሙ ናቸው። እኒህን እየፈለፈለች ያለች ናት። የኛው አገር የተዋህዶ እምነታችን መሪ ጳጳሳት ዲግሪ
ተቀብለናል፣ ዶክተር ሆነናል፣ እያሉ እንደመልካም ዝና በአውሮፓና በአሜሪካ በሩስያና በአጎራባቾች ካሉ
ቲኦሎጂ ዩኒቨርስቲዎች፣ የለቃቀሙትን ፍልስፍና ለበስ እምነት ተሸክመው መጥተው ለሕዝብ መልካም ነገር
ገብይተው እንደመጡ ሳያፍሩ ይናግራሉ።
ልዑል በየትኛውም ትእዛዙ በጥበብ፣ በፍልስፍና ስበኩኝ አላለም። ሁሉም ሃዋርያት ሁሉም ነበያት
ከፍልስፍናና ከጥበብ ትምህርት ቤት አልወጡም። በፍልስፍና ትምህርት ቤት መግባት አላስመረጣቸውም።
የእምነት ጀግኖቹ እነአብረሃም፤ እነጴጥሮስ፣ እነኤሊያስ፣ እነዮሐንስ እንደምሳሌ ስናያቸው፤ ከየትኛው ኮሌጅ
ወጡ! ዓለምን ያስደመሙ የእምነት ጀግኖች ዛሬም ላሉት የእውነት ምልክቶች ናቸው። ስለዚህ ካቶሊክ
ከነምናምንሽ ከነዝግንትልሽ በበርባሪና በአውዳሚ እሳት ፍፁም ትጠረጊና ምልክትሽ እንኳን እንዳይገኝ ሆኖ፣
በሁለተኛው የእሳት ወንፊት መበጠራችሁ ይፈጸም ዘንድ፣ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል
ትእዛዙ ወጥቶአል።
በዚህ ርእስ ስር ማስታወስ የሚሻን ነጥብ ቢኖር፦ ለኢትዮጵያ መባረክም ሆነ መመረጥ እንደምልክትም
ሆነ እንደበረከት የሚታዩት በየገደሉ፣ በየመቃብሩ፣ በየዱሩ ወንበር ዘርግተው፣ ቅጠል ቀልሰው፣ ዜማውን፣
ቅኔውን፣ ድጓውን፣ መጻህፍቱን በወጣቱ አእምሮ ውስጥ አፍስሰው መተኪያ የሌለውን እድሜያቸውን በሙሉ
ለዚሁ ጌታ ለወደደው ሥራ አውለው ዛሬ አለፈው አልፈው የሚታዩትን የአብነት ትምህርት ቤቶችን ተክለው
አልፈዋል። ምትክ የማይገኝለትን የተዋህዶ እምነታችንን በአለቱ ላይ መስርተው ሄደዋል። ይህንን ንቀው ነው
የዛሬዎቹ ዲያብሎሶች የበግ ለምድ ከለበሰች ተኩላ ሳይንሳዊ እምነት ያመጡልን። ሁላችንም እንደምናውቀው
ድንቅ የሆኑ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን፣ ጳጳሳትን፣ መምህራንን ለተዋህዶ እምነት በጽናት በመቆማቸው ሰርገው
ገብተው ጠመንጃን ይዘው የተዋህዶ እምነታችንን ከሚያጠፉት ጋር ግልጥ ውጊያ ውስጥ በመግባታቸው በተለያየ
ዘዴ /በተቀናበረ የመኪና አደጋ፣ በመርዝ/ እንዲወገዱ ተደርገዋል። በምትካቸውም የዲያብሎስ የመናፍቅ፣
የካቶሊክ ምልምሎች እንዲተኩ ተደርጎአል። ስለዚህ ካቶሊክ የዲያብሎስ መሳሪያ ናትና ፍርዱም ይገባታል።
የጴጥሮስ መልእክት ሁለተኛው፦ ምእራፍ አንድን ሁለትን በሙሉ ጠንቅቀው ይመልከቱ ስለ መናፍቅም ሆነ
ስለካቶሊኮች ምንነት በግልጽ የሚረዱበት የልዑል ቃል ነውና! ፍርዱም በዚሁ ቃል ተመስርቶ የወጣ ነው።

ለ/ ፕሮቴስታንት /መናፍቃን/
ይህ እምነት በስም አጠራሩም እንደሚታወቀው አመጽን እንደመንገድ የሚያዩ፣ በአመጽ የተጠነሰሱ፣ ዛሬም
በአመጽ በሴራ የዲያብሎስ ድርጅታቸውን እያስፋፉ ያሉ ናቸው። በመልእክቶቹ /ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን/
በሚለው መልእክት 3 ገጽ 30 – 32 እንደተገለጸው ከካቶሊክ የተገነጠሉ ዘመናቸውን ሁሉ እንደአሜባ እየተገነጠሉ
የሚባዙ እምነታቸውን ልክ እንደፖለቲካ አደረጃጀት አጭበርብረውና አታለው በመላው ዓለም እራሳቸውን
ያስፋፉ የዲያብሎስ የዘመኑ ድርጅቶች ናቸው። ከካቶሊኮች በሚበልጥ ድርጅታዊ አሰራር ፖለቲካውንም
ተላብሰው ገንዘብን ሰንቀው በመላው ዓለም ለሰዎች ጥፋትን ለዲያብሎስ ግዳይን ዘወትር የሚያቀርቡ ናቸው።
17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ከነዚህ ጋር መጨቃጨቅ ከዲያብሎስ ጋር በአካል የመዋጋት ያህል ነው። መልእክቱንም ሁሉ በሹፈትና በፌዝ
የተመለከቱ ናቸው። የልዑል፣ የድንግል፣ የቅዱሳን መላእክት፣ የሰማዕታትና የነቢያት የሃዋሪያት መሰረታዊ
ጠላቶች በመሆናቸው ከነሱ ውስጥ አንድም ሰው በምሕረት መዝገብ አይታሰብም። በራሴም በተሰጠኝ ስልጣን
በታመንኩለትና ባሪያውም ልጁም ሆኜ በማገለግለው እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስ ስምና በእናቴ በወላዲት አምላክ ስም በወዳጆቼ በገብርኤል፣ በሚካኤል፣ በሩፋኤል፣ በፋኑኤል
ስም ቃሌን አጸናለሁ ከምድሪቱ ሁሉ ካልጠፉ እኔ ለነሱ በፍፁም የማልተኛ መሆኔን አረጋግጥላችኋለሁ። ያውም
በኢትዮጵያ ምድር በልዑል መናገሻ፣ እንኳን እነርሱ በአካል ቀርቶ ምልክታቸውም ሆነ ስም አጠራራቸውም
አይታሰብም።
ስለዚህ ከነዚህ ጋር በማንኛውም መልኩ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያለህ ሁሉ! አብረህ
በእሳቱ ትበላለህና ሰከንድ ሳታጠፋ አምልጥ ሌላ የምልህ የለም። ለነሱ የተደገሰው የሰው ልጅ ያላየው ጥፋት
ነውና። እነዚህን የምትቀበል የተዋህዶ አገር የለችም። በነዚህ የአገራችንም የዓለምም ተዋህዶ እምነታችንም
ጠላቶች የየትኛውም የዓለም ዜጋ ይሁኑ የአገራችን! መናፍቃን እሰከሆኑ ድረስ ምንም አይነት ዘር ምልክት
ሳይተውላቸው ፍፁም ከምድሪቱ ይጠረጋሉ። ያሳደጓቸውም እንስሶች ጭምር በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲኖሩ
አይፈቀድም። አይደረግምም። ስለሆነም በየትኛውም ዓለም ስፍራ ሁሉ መናፍቃን ሁሉ በዚህ መልእክት
በተጠቀሱ መቅሰፍቶች ሁሉ ይጠረጉ ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በካዱአት በእናቴ በድንግል ትእዛዝ በኔም
በልዑል ባሪያ ተፈጻሚ ይሆን ዘንድ ታዞአል። እጅም መስጠት፣ እስትንፋስም ለናንተ የለም። በምንም የሚተው
ቀዳዳ አይኖርም።
ቀዳዳ ለነዳታን እንዳልተተወ ሁሉ፤ የልዑል ቃል እንዲህ ይላል!

ሙሴንም፤ እግዚአብሔር የቀደሰውንም አሮንን በሰፈር ተመቀኙአቸው፤ ምድርም


ተከፈተች ዳታንንም ዋጠችው፤ የአቤሮንንም ወገን ደፈነች፤ በማህበራቸውም እሳት
ነደደች፤ ነበልባልም ኃጥአንን አቃጠላቸው።
መዝሙረ ዳዊት 105 (106) ፡ 16 – 18
መናፍቃን የናንት እጣ ፈንታ ይህ ከላይ ያለው ቃል ነው።

ሐ/ እስልምና
ይህንን እምነት በተመለከተ፤ በሙሉው መልእክት፤ መልእክት 3 ገጽ 32 – 33 በዝርዝር ምታገኙት ሲሆን፤
ይህ እምነት በተረት ዓለም የሚዳክር በመሆኑ፤ ለብዙዎችም፣ ለራሱም ሰዎች ጥፋትን ደግሶ ውድመትን አንግሶ
ራሱንም የነገሰበትንም ምድር ጭምር እያጠፋ ያለ እምነት ነው።
ስለዚህ እምነት በመልእክት 1 ገጽ 7 ላይ እንደተመለከተው፤ ፍፁም ከምድር የሚጠረግ የጥፋት እምነት
ነው። ይህ ጅምሩ ዛሬ በመላው ዓለም ላይ ጎልቶ ቢታይም ከዚህ መልእክት መውጣት በኋላ፤ በ49 ጊዜ እጥፍ
ጨምሮ ሰምተን የማናውቀው የእሳት ማዕበል የሚጠርገው ነው። ከዚህም እምነት እግዚአብሔር የመረጣቸው
ከማእበሉ ሾልከው የሚወጡ አሉ። ራሳቸውን በመጸጸት ወደ እውነተኛይቱ እምነት ወደ ተዋህዶ ይመለሳሉ።
እጅግ በቁጥር ያነሱ ናቸው። ካሁኑ ብዛታቸው አንጻር ምንም አልተረፉም የሚያስብላቸው ናቸው። የተረፉትም
ለአንዲቷ የኢትዮጵያ ተዋህዶ እምነት እጃቸውን ከሰጡ ብቻ ነው በምድራቸው የሚኖሩት።
በዚህ መልእክት በትእዛዞቹ ውስጥ የተጠቀሱት መቅሰፍቶችና ሁለተኛው የእሳት መጥረጊያዎች በሙሉ
ይጠርጓቸው ዘንድ በልዑል ፈቃድ በኔ በባሪያው በኩል ትእዛዙ እነሆ ተገልጾአል።

18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

አቤቱ ጋሻዬ በኃይልህ በትናቸው አውርዳቸውም፣ ስለአፋቸው ኃጢአት ስለ


ከንፈራቸውም ቃል መርገምንና ሃሰትን ስለሚናገሩ፣ በትእቢታቸው ይጠመዱ፣
በቁጣ አጥፋቸው፣ እንደይኖሩም አጥፋቸው፣
መዝሙረ ዳዊት 108 (109)፤ 11 – 13

መ/ ቡዲሂዝም፤ ታኦይዝም፣ ሺንቶይዝም


እነዚህ እና መሰሎቹ በሙሉ በግልጽ ጣኦትን የሚያመልኩ ናቸው። በነዚህም ሙሉ ጥፋትን የምናይ ሲሆን
ስፍር ቁጥር የሌለውን ሕዝባቸውን የሚያጡና፣ ካላቸው ሕዝባቸው ከ20 እጅ 19 ኙን አጥተው የተረፉትም
ቢሆን፤ ለኢትዮጵያ ተዋህዶ እምነትና በዚችው የድንግል አገር ለሚጠናው የልዑል ዙፋን ሲንበረከኩ ብቻ
ነው በምድራቸው በሰላም የሚኖሩት። አለበለዚያ ግን ጉልበቱን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የሚሄደውን ጠረጋ
እስከሚፈጽም ድረስ ያዩታል። የሁለተኛ ደረጃው የእሳት ወንፊት በብርቱ ከሚፈስባቸው አገሮች ግንባር
ቀደምም ናቸውና! ጥፋታቸው የዓለምን ሕዝብ በብርቱ ያስደነግጣል።
በኤሽያ ያሉ አገሮች ናቸውና መልእክቶቹ ለመንግሥቶቻቸውና ለሚዲያዎቻቸው ደርሰዋል። በመሆኑም
በዚህ መልእክት ውስጥ የተጠቀሱት ሁለተኛው የእሳት ወንፊትና ሌሎችም መቅሰፍቶች በሙሉ፤ ይፈስሱና
ያጠፏቸው ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል እነሆ ታዞአል።
ት. ኢሳይያስ ም. 2፤ 12 – 22፤ ት. ኢሳይያስ ም. 24፤ 1 – 13 ትንቢተ ኤርምያስ ም.8፤2–3

ሠ/ የተለያዩ እምነቶች
በዚህ ርእስ ከአባሎቻቸው ቁጥር ማነስ አንጻር ባናነሳቸውም የተለያየ ስምና ዓላማ ያዘሉ፤ እምነት መሰል
የዲያብሎስ መሳሪያዎች ከላይ ከተጠቀሱት የተለየ እጣ የላቸውም ታላላቆቻቸው በእሳቱ ሲበጠሩና ሲጠፉ
እነዚሁ አብረው ይጠፋሉ። በነዚህም ላይ የቅጣት ትእዛዞች ሁሉ ተፈጻሚ ይሆናሉ።

ረ/ በመላው ዓለም ያሉ የተዋህዶ እምነት ተከታዮችን በተመለከተ


ዛሬ እንደምናየው በመላው ዓለም ጎልተው ስማቸው የሚጠቀስ ተዋህዶ እምነት አማኞች ግብጽ ካሉት በቀር
የሉም ማለት ይቻላል። ከእውነተኛይቱ ተዋህዶነት ሸሽተው በተለያየ የዲያብሎስ ትብታብ ተጠልፈው ስሙን
ብቻ ያዘሉ እርግጥ ብዙ አሉ። ስሙን ማንጠልጠል ብቻውን አያድንም በምግባር በትክክለኛውና በቀጥተኛው
የተዋህዶ እምነት ሲፀኑ እንጂ።
ሁላችሁም ልታውቁት የሚገባው ዋናው ቁም ነገር ይህ ነው። በእምነቲቱ መርከብ የተሳፈሩ፤ የትኛውም
የዓለም ክልል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ የሌሎች አገሮች ዜጎች የተገባቸው ስለሆነ፤ የጽድቁን ነጩን
ልብስ ለብሰዋል። በእምነቲቱ የእምነት መርከብ /የኖኅ መርከብ/ ተሳፍረዋል። ቀድመው እንደነዚህ ሊሳፈሩ
የተገባቸው አንዳንዶች ደግሞ በተለያየ የዓለም ትርፍ ስብሰባ ተሰማርተው ኮልኮሌአቸው በዝቶ ታንቀውና
ታግተው ያሉ በተለይም ለዘመኑ የጥፋት አለቆች በእንጀራ ስም እያገለገሉ ያሉ ሁሉ የሰበሰቡት ጠፍቶ፤ ውድ
ዋጋ ከፍለው የሚወዱአቸውን አጥተው እየተጎዱ በጥፋታቸው ሂደት ውስጥ ብርቱ ስብራትን እያዩ ንስሓቸውን
ጨርሰው በመርከቢቱ ውጪ አካል ተንጠልጥለው በታላቅ ጭንቅ የሚድኑ ናቸው። ይህ ሁሉ መልእክት ሲፈስ
በቸልታ በንቀት በጥርጥርም መንፈስ በመሞላት በያዙት ሀብትና ውዳቂ ስልጣን በመታመን፤ ጊዜአቸውን
ስለጨረሱ ነው። ሁሉን አጥተው በሥጋቸው ውድ ዋጋ ከፍለው በጭንቅ የሚድኑትም ለዚህ ነው። ከዓለም
ጥበብና ፍልስፍናን ሲቀላውጡ፤ በእጃቸው የነበረውን እንቁአቸውን ስለጣሉም ነው፤ ይህ ፈተና የሚያገኛቸው።
መጸጸታቸውና ሃፍረታቸው ለረጅም ጊዜ አንገታቸውን እንዲደፉም ያደርጋቸዋል።

19
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ 8፤ ምእራፍ 9 አሰተውለው ያንቡ! የእግዚአብሔር ሕዝቦች ምልክት


በግንባራቸው ላይ ተደርጓል። ያልተደረገባቸው ደግሞ ማንም ለማያስቀረው ለታላቁ እሳት ይጣሉና ይጠረጉ
ዘንድ ተወስኖባቸዋል። ይህም ተፈጻሚ ይሆናል።
የመጀመሪው የእሳት ወንፊት ከመፍሰሱ በፊት የተገባቸው ለሁኑ ሁሉ በየትም የዓለም ስፍራ ቢሆኑም
በግንባራቸው ላይ የልዑል ማህተም፤ በቤተሰባቸውና እንዲድኑላቸው ለወደዱአቸው ሁሉ የእመቤታችንን
የድንግልን ማህተም ተደርጎባቸዋል። ሙሉ ለሆነው ጥበቃ ለራሳቸውም ለቤተሰባቸውም ወደው ላስጠለሏቸውም
በአሥራ ሁለቱም ሊቃነ መላእክት፤ በሚካኤል፣ በገብርኤል፣ በሩፋኤል፣ በፋኑኤል፣ ግንባር ቀደምትነት
በብርቱ እሳትና ጥበቃ ታጥረዋል። የልዑል፣ የድንግል፣ እጅግ የከበሩት የቅዱሳን መላእክት እንቁና የክብሩ
ጌጥ ናቸውና አንዳችም የሚነካቸው ቀርቶ ባለፉበት በረገጡበት መድረስ አይቻልም። በእነዚህ የእግዚአብሔር
እንቁዎች ላይ እስከ ዛሬ ግፍ ለሠሩባቸው ዋጋቸውን በአደባባይ እንዲከፍሉ ይደረጋል። ዛሬም በሞተባቸው ቀን
ከክፋት የማይመለሱ ቢያንስ ለነፍሳቸው መጠለያ ለማግኘት እንኳን የመለመን እስትንፋስ እንዳያገኙ የለመዱትን
ክፋት ሲያስቡና የሚያስቡ ሲከሰቱ ወዲያው በብርቱ ኃይል ይጠፈራሉ። ወደ ሞት ልመናም ይሸጋገራሉ። ሞት
ከተቸራቸው ደግሞ እድለኞች ናቸው።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 1 ገጽ 7 – 8፤ መልእክት 2 ገጽ 14 – 15፤ መልእክት 3 ገጽ 35
– 36፤ ገጽ 61 – 64 በጥንቃቄ አንብብና ተረዳ!!

6/ በዚህ ዘመን በመልእክቶቹ የፍርድ ሚዛን ውስጥ የወደቁት መሪዎችና


ጭፍሮቻቸው በቀጣዩ እርምጃ ምን ይገጥማቸዋል!

ቢመከር ያልሰማ መከራ ይምከረው ይላል የአባቶች ብሂል። በዚህ ዘመን ያሉ መሪዎች ሙሉ በሙሉ
ማለት ይቻላል ፍፁም አውሬነትን የተላበሱ፣ በግልጽም ዲያብሎስን የሚያመልኩና የሚታዘዙ የዘመኑ ጉዶች
ናቸው። መልእክቶቹ ደግመው ደጋግመው መዘኑአቸው፤ እጅግ ቀለውም አገኙአቸው። ድሃ ሲመታ፣ በጎርፍ
ሲጠረግ፣ በማዕበል ሲፈራርስ፣ እንደ ሃይቲ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሲበላ፣ በመሬት ርእደት ሲፈርስ
ዓለም በኢኮኖሚ ቀውስ ስትታመስ፣ ደሃ በረሃብ ሲረግፍ፣ ሲሰደድ፣ ድሀው ወደ ሞት፣ መካከለኛው ወደ
ድህነት ሲቀላቀል፣ በከፍታ ያለው ወደ መካከለኛው እያለ ሲወርድ፣ ውኃ ሲወስድ አሳስቆ እንደሚባለው ጉደኛ
መሪዎች (የፖለቲካውም የሃይማኖቱም) ከነጭፍሮቻቸው፣ ከነአገልጋያቸው፣ በመጀመሪያው በትር ስላልተጎዱ፣
በዘራፍ፣ ተሞልተው ለጥፋታቸው ዛሬም በትእቢት ሲፈነጩ ይታያሉ።
ቀጣዩ እርምጃ ኃይልና ጉልበቱ ሁሉ አሁን ከምናየው በ49 እጥፍ ጨምሮ ተጭኖ መጥቷል። በተለይም
እሰከ አሁን እያላገጡ ባሉ መሪዎች (የፖለቲካውም፣ የሃይማኖቱም፣ የጦሩም፣ የጸጥታውም፣ የሃብቱም) አዛዥ
ናዛዦች ከነጭፍሮቻቸው የትም ቦታ ቢወተፉ በማያመልጡበት እሳት ይጠረጋሉ። ሞትን ይራቧታል፣ ይጠሟታል
አየገኙአትም። ሞት ይሸሸጋቸዋል። ከተገኘላቸውም ብርቱ ስቃይን አሳይቶ ይወስዳቸዋል። ሞትን ስላገኙት
እድለኞች ናቸው ብለው የቀሩት አምሳዮቻቸው ይቀኑባቸዋል። የሰበሰቡት ሃብታቸው ይጠፋል። ቤተሰቦቻቸውም
አብረው ይጠረጋሉ። ለምልክት የሚተውላቸው ነገር በፍፁም አይኖርም። የገነቡትም ይፈርሳል። የሰበሰቡትም
ይበተናል። ወለዱ ዘርም አበዙ፤ ወገን የጎጥ አምሳያቸውንም አደራጁ፤ ያመልጣል ብለው ባሰቡበት የዓለም
አካል ሁሉ ቢሸሸጉ የሚያመልጥ የለም እያዩት በብርቱ እሳት ይበላል። ሁሉንም ጥፋት በቁማቸው ያዩታል።
በስተመጨረሻ እነሱ ዘራቸውም የጥፋቱ መደምደሚያ ይሆናሉ። እነሱ ጠፍተው ፍሬዎቻቸውም ተጠርገው
የዲያብሎስ ምልክቱም ሳይቀር ሁሉም በቁማቸው ወደ ምድሪቱ የእሳት ባሕር ይገባሉ። እንደ ዳታን ምድር
ተከፍታ ጉያዋ ትከታቸዋለች። ምልክትም ታሪክም የማያነሳቸው ይሆናሉ። በዚህ ጥፋታቸው መፈጸም ነፍሳቸው

20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ወደ ሲኦል ለዘለዓለሙ እሳት ወደምትጠበቅበት ትገባለች። ይህ ይፈጸምባቸው ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ
በኔ በባሪያው በኩል በዚሁ መልእክት እንዲገለጽ ተደርጓል።

7/ በመጀመሪያ ደረጃ የእሳት ወንፊት የተደረገ ብጠራና በቀጣዩ ሁለተኛ ደረጃ የእሳት
ወንፊት መጪ ሁኔታ በንጽጽር ሲታይ

ዓለም የመጀመሪያውን የእሳት ወንፊት ከመልአክቶቹ መውጣት ጀምሮ በየጊዜው እያደገ በሚሄደው ምት
እያየችው ትገኛለች። የመጀመሪያው እሳት በሁሉም ዓለም ገጽታ በትሩን እያሳረፈ ይገኛል። በመጠኑም ለማየት
ያህል
»» ርእደ መሬት፡– ቢያንስ በወር አሊያም በሳምንት እየተከሰተ ይገኛል። ሃይቲን፣ ጃፓንን፣ ኒውዚላንድን፣
ቺሊን፣ ጣሊያንን፣ ኢነዶኔዢያን፣ እና ሌሎችንም እየመታ ይገኛል። ይቀጥላልም።
»» ጎርፍና እሳት፡– በተጣመረ አሜሪካንን (ባቢሎንን)፣ አውሰትራሊያን፣ ሜክሲኮን፣ አውሮፓን እየመታ
ነው ይቀጥላልም።
»» ቶርኔዶ፣ ታይፉን፣ ሃሪኬን፣ ሱናሚ፣ ካተሪና እና ሌሎችም ስም የለሽ ማዕበሎች ኤሽያን፣
አሜሪካንን፣ ደቡብ አሜሪካንን፣ አውሰትራሊያን በመጠኑም አውሮፓን እየመታ ሲሆን የማያቋርጥም
ሆኖ ይቀጥላል።
»» እሳተ ጎሞራዎች፡– የተኙ ነቅተዋል። ሰው ያላየውንም ጥፋት ያመጣሉ። አሁንም እያጠፉ ይገኛሉ።
»» ርሃብ፣ ጦርነትና ፍጅት፣ ለአፍሪካ፣ ለነፓኪስታን፣ ለነአፍጋኒስታን፣ ለነህንድ ተሰጥቶ እየሠራ ሲሆን
በቀጣዩም ያልተካተቱ ተደምረው በብርቱ ከፍቶ ይቀጥላል።
»» በሽታ፦ በመጠኑም እያጠፋ ቢሆንም እጅግ ታይቶ በመይታወቅ ኃይልና አይነት ሲመጣ ምልክት
እየሰጠ ይገኛል።
»» ትራንስፖርት በሁሉም ዓለም አደጋ በዝቶበታል።
»» ኢኮኖሚ ተመሰቃቅሎአል፣ የገንዘብ ቀውስ፣ የባንክና የኢንሹራንስ መውደቅ፣ የበጀት ጉድለት፣
ግሽበት፣ ሪሴሽን፣ ሥራ ማጣት፣ የኑሮ ውድነት፣ የየእለቱ ክስተት ሆኖአል። ይቀጥላልም።
»» የሕዝብ አመጽ ከፍቷል፣ ያልደረሳቸውን ጨምሮ ከፍቶ ይቀጥላል።
»» የእምነት ግጭት፣ የዘር ግጭት፣ የድንበር ግጭት ሁሉም አሁን ካሉት ከፍተው ይቀጥላሉ።
»» መንግሥትን እንደ መንግሥት ያቆሙ ኃይሎች፣ ወታደራዊ ኃይል፣ የጸጥታ ኃይል የማይታዘዝ ወደ
መሆን እየገሰገሰ ይገኛል። ይሆናልም።
»» የኒዩክሊየር ቀውሰ መታየት ጀምሮአል። ይቀጥላልም።
»» የሙቀት መጠን እጅግ ከፍቶ ታይቷል። በሪኮርድም ያልታየ ሆኖአል። በአሜሪካ 35 ሰው ገድሎአል
ከፍቶ ይቀጥላል።
በዚህ ጽሁፍ ያልተዳሰሱ ብዙ አደጋዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በተለይም የዘመኑ ሚዲያ ለወሬው ማድመቅ የጎሉትንና ገዢዎቹን የማያጋልጥና የማይጎዳውን ብቻ
ስለሚዘግብ እንጂ ጥፋቱ ማንንም ያልዳሰሰበት አገር የለም። ምሳሌን ብናነሳ ስለኢኮኖሚ የትኛውም ሚዲያ
የሚያነሳው ስለታላላቆቹ አገራት መክስር መውደቅ እንጂ፣ ስለ ትንንሾቹ ማለትም እንደኛ አይነቱ አገር ቦታ
ተሰጥቶት አይዘገብም። ሞቱም ተነሱም በቀበሌ ልክ የሚታዩ በጌቶቻቸው ተደግፈው ያሉ ስለሆነ ማንም
21
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ቦታ አይቸራቸውም፤ በመሆኑም ስለ ቅጣቱ መጠንና መንስኤ የአዳም ዘር እንዳይረዳው የዘመኑ የዲያብሎስ


ልጆች ማንኛውንም የመረጃ መንገድ አጥረው በመያዛቸው እንዲያውም ከነአካቴው በውኑም ይሁን በህልሙ
ያላየው ጥፋት መጥቶለታል። የሚበዛው ህዝበ ዓለም /99 ከመቶ የሚሆነው/ ከአያት ቅድመ አያቶቹ ጀምሮ
የተሸከመውንና እሱም ከደረሰበት ዲያብሎስ ካስጨበጠው ጥበብ ጋር አዳምሮ፤ በዘመን ሂደት የልዑልን ሕግና
ትእዛዙን ሽሮ በስፍራውም የጠላት ዲያብሎስን መመሪያ የህይወቱ መንገድ አድርጎ በመያዙ፤ ቢመከርም
ቢገሰጽም በትእግስት ቢሸከሙትም እንኳን ሊሰማ አልቻለምና። ሙልጭ ብሎ የፈጠረውን አምላክ ክዶ፤ ተረት
ነው፤ ፈጣሪ የለም በሚል አቋሙ ጸንቶአል። በመሆኑም የሁሉም ፍጥረት ባለቤት ልዑልና ኃያል ጌታ ፍርዱን
እንደፀሐይ አውጥቶታል።
አመጸኛው፤ ከሃዲው፤ አመንዛሪው፣ ቀጣፊው፣ ትዕቢተኛው፣ ዘራፊውና ጨካኝ አመጸኛ ትውልድ
የሚፈጭበትና የሚጠረግበት እሳት ውስጥ ገብቶአል። የታመነበት ዲያብሎስ፤ የተሸከመው እውቀትና ቁሳቁስ
ኒዩክለር፣ ጀት፣ ታንክ፣ ሚሳየል ሲታደጉት ልናይለትም ነው።

2ኛው ዙር የእሳት ወንፊት ከመጀመሪያው ጋር ሲነጻጸር ምን ይመስላል።


የሁለተኛው ዙር የእሳት ወንፊት ይመጣ ዘንድ ግድ የሆነው፤ ይህ አመጸኛ ትውልድ፤ በመጀመሪያው
ወንፊት ሲበጠር፤ ሊያደምጥም ሊሰማም ስላልቻለና፤ እንዲያውም ለሕዝቡ ከመንገር ይልቅ አፍኖ በመያዝ፤
በተለይ በገዢነቱ ወንበር ላይ የተቀመጡት፤ ቁብም ስላልሰጣቸው ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ታዞላቸዋል። ይህ
ማበጠሪያ ምን ይመስላል? ማንን ይጠርጋል? እስከምን እርቀት ይሄዳል? ጉልበቱስ ማን ይቋቋመዋል? ይህንን
እናያለን።
ከእንግዲህ የሚመጣው የእሳት ማበጠሪያ፤ ማንም የፍጥረት ኃይል፣ በየትኛውም ጥበብና ኃይሉ የማያቆመው
ሞካሪውንም የታለመለትንም ሳያጠናቅቅና ሳይደመድም የማይመለስ ነው።
ልዑልም ልዑል፤ የፍጥረት ሁሉ ጌታና ፈጣሪ፣ ሊመለክ፣ ሊመሰገን፣ የሚገባው መሆኑን ምድሪቱም
ሰማዩም ገንዘቡ ሰውም የራሱ የእጅ ሥራ እንደሆነ ማረጋገጥ ስለተገባና ላመኑት ለወደዳቸው ለወደዱት በጥፋት
ጎዳና ላልሄዱት፣ ትእዛዙን ለወደዱት፣ በፍቃዱም በፍቅሩም ለተደሰቱት፣ ዋጋቸውን መክፈል አለበትና ይህ
ይደረጋል። የጥፋት ልጅ ሁሉ ደግሞ በጥፋቱ ውስጥ እየተጠረገ በፀፀት ያየዋል፣ ይሄዳልም። እግዚአብሔር
ለልጆቹ የሚያፈሰውን ምድር ከተፈጠረች ጀምሮ ያላየችውን ፀጋውን ሲያድላቸውም፣ በግልፅም ይታያል።
እርጉሞች ደግሞ በአፀደ ነፍስ በሲኦላቸው ወድቀው በአካለ ሥጋ የቀሩም የጥፋት ልጆች ካሉ በስቃይ ማጥ
ውስጥ ወድቀው በእሳት እየተበጠሩ እስከሚሄዱ ድረስ ይመለከቱት ዘንድ የግድ ሆኖአል።
የልዑልን ኃይሉንም ለካዱ፣ የለምም ለሚሉ፣ ዲያብሎስንም ለሚያመልኩ፣ ማንም አይደፍረንም ብለው
በሃይላቸውና በጉልበታቸው እንዲሁም በሃብታቸው ተመክተው ለሚገሰሉ ሁሉ፣ የፈጣሪንም ትእግስት እንደቂልነት
እንደከንቱነት በመቁጠር ለተኮፈሱ፣ ጥበብ ልብሳችን፣ ዲያብሎስ ጋሻችን ብለው ለተቀመጡት ለአንዴም
ለሁሌም መዝገባቸው ተዘግቶ ከአባታቸው ጋር ወደ እሳት መውረድ አለባቸው። ይህም ይሆን ዘንድ በልዑል
ታዞአል። ማንም ሳያግደው ተፈጻሚ ይሆናል። ታሪካቸውም፣ ዝክራቸውም፣ ቅሬታአቸውም፣ ዘራቸውም፣
ከምድረ ገጽ ይጠረግ ዘንድ ታዞአል።
ስለሆነም ይህ የሁለተኛው የእሳት ወንፈት፤ በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ያለተዳረሰውን ሸፍኖ በተለይም
የአመጽ መሪዎችንና የእነሱ ተዋረድ ናዛዥ አዛዥ ታዛዦችን ኢላማው አድርጎ የሚመጣ ይሆናል። ሕዝባቸው
እንዳይሰማ እንደይጸጸት እንቅፋት የሆኑ ገዥዎችም፣ የሚዲያ ሰዎችም፣ በተለይ በዚህ ጉዳይ ውሳኔ ሰጭዎች
የሆኑ ሁሉ፣ ሙሉውን መልእክቶች ለሕዝብ እንዳይደርሱ፤ አቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ መሰናክል በማድረጋቸው
የማይወጡት ፍፁም ያልገመቱት፤ ሞትን እንዲለምኑት እያደረገ የሚፈጫቸው እሳት ታዞላቸዋል። ከህዝቡም

22
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መሃል እየለዩ የሚበሏቸው ዓለም ያላያቸው በምንም መሳሪያ የማይቋቋሙት የአውሬ አይነቶች ይፈሱባቸዋል።
በአሰቃቂ ሁኔታም ምልክት አልባ የሆነውን የአዳም ዘር በሙሉ ይቆረጥሙታል።
ርእደ መሬት ዛሬ ከምናየው በላይ ከሰባት እጥፍ ጀምሮ እስክ 49 እጥፍ ድረስ ጨምሮ ይመጣል።
ከተከሰተበት ስፍራ አገርም ከሆነ አንድ አገር አይኖርም። አካባቢም ከሆነ በላዩ ላይ የሰውም ሆነ የሌላ ምልክት
አይኖርም። በአንድ ጊዜ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሕዝቦች መሰናበት የተለመደ ክስተት ይሆናል።
የኒዩክሊየር ፍፁም ጥፋት በጨበጡት አገሮች ሁሉ ላይ ይሆናል። በጃፓን ከተከሰተው አደጋ ከሚመጣው
ጋር ሲነጻጸር አደጋና ጥፋት እንዳልሆነ ይታመናል።
ማዕበሎች ሁሉ ስም ያወጣችሁላቸውም ሆኑ ያልሰየማችኋቸው፤ እሰከ አሁን ካያችኋቸው በላይ ከሰባት
እጥፍ ጨምሮ እሰከ 49 እጥፍ ጎልብተው ይመጣሉ። ማንም በእርዳ ተረዳዳ አያመልጣቸውም።
አውሎ ነፋሶች ሰው አይቶም በማያወቀው ፍጥነትና ጉልበት ይመጣሉ። ጠርገውም ያለምልክት ያጠፋሉ።
ጉልበታቸውም በ49 እጥፍ ያድጋል።
በረዶዎች እሰከ ዛሬ ከምናውቃቸው የአንድ ግራም ክብደታቸው በላይ እሰከ 50 ኪሎ በሚሆን ክብደት
በተለያየ ቅርጽ ፍፁም ያጠፉ ዘንድ፤ በተመረጡ ቦታዎችና ሰዎች ላይ ይወድቃሉ። ቤትንም መሸሸጊያንም
ያወድማሉ።
ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ሁሉ አሁን ከምናየው ሰፍተው፤ ሁሉንም የምድር አካል
ሸፍነው ከሰባት እጥፍ ተነስተው 49 እጥፍ በሆነ የጥፋት ኃይል ምድርን ይከድናሉ። ገዥና ባለ ሀብት ነኝ፣
የሚልና የነዚህ ጋሻ ጃግሬ ሁሉ፣ ከምድር ገጽ የሚያጠፋቸው በርባሪና ጠራጊ እሳት ታዞላቸዋል።
በሽታዎች እጅግ አደገኛ በሆኑ ቫይረሶች እየፈሉ ይመጣሉ። በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን የአዳም ዘር ምልክት
አልባ የሆኑትን ሁሉ ያጠፋሉ። ለረሃብተኞች ደራሽ ስለማይኖር ሚሊዮኖችን መውሰድ ሥራቸው ይሆናል።
ምልክት አልባው ሁሉ የጥፋቶቹ ሁሉ ኢላማ ይሆናል።
ዓለም ለዘመናት ያደራጀችው መመኪያ ሁሉ ከንቱ ሆኖ ከነ ምልክቱ ይጠፋል። ባጠቃላይ በሙሉው
መልእክት (ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን) በሚለው የአፈጻጸም መልእክት 3 ገጽ 83 – 87 የመጨረሻ ማሰሪያ
ቃልና ትእዛዞች የሚገልጽ ሲሆን፤ እነዚህ የመጨረሻ ትእዛዞች ዓለም በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ሲበጠሩ
እንድናይ አድርጎናል። ዛሬም በዚህ ሁለተኛው የእሳት ወንፊት በትእዛዞቹ ውስጥ የተጠቀሱትን ቅጣቶች ሁሉ፤
በሰባት ጊዜ ሰባት እጥፍ አብዝቶ ይጠርግ ዘንድ በልዑል ፈቃድ በኔም በባሪያው በኩል እነሆ ታዞአል።
ምልክት አልባው፤ ተዋህዶ እምነትህን ንቀህ፤ ከንቱን የተከተልህ በጥበብህ፣ በጉልበትህ፣ በሀብትህ፣
የታመንክ የልዑል ጠላት፤ የእናቴ የድንግል ጠላት፣ የተወዳጆቼ የተከበሩት ቅዱሳን መላእክት ጠላት፤ የተዋህዶ
እምነት ጠላት የት ትደበቃለህ? ወዴትስ ትሸሸጋለህ? እንግዲህ ዛሬም መርዶህን ስማ አብቅተሃል። መጭውን
ጥፋትህን በምን ዘዴ በምንም መንገድ አታልፈውም። መልካም ሰንብት!!
እንዲሁም የየክፍለ አሕጉሮችን የሁለተኛው ዙር የእሳት ወንፊት እጣ ፈንታውን በየራሳቸው ገጽ ማብራሪያ
ይሰጥበታል።

ይህች ከእግዚአብሔር ዘንድ የበደለኛ እድል ፈንታ፤ ግፈኛም ሁሉን ከሚችል አምልክ
ዘንድ የሚቀበላት ርስት ናት፤ ልጆቹ ቢበዙ ለሰይፍ ይሆናሉ፤ ዘሩም እንጀራን
አይጠግብም፤ ለእርሱም የቀሩት በቸነፈር ይቀበራሉ፤ መበለቶቻቸውም አያለቅሱም፤
እርሱ ብርን እንደ አፈር ቢከምር፤ ልብስንም እንደ ጭቃ ቢያዘጋጅ፤ እርሱ ያዘጋጀው
ይሆናል። ነገር ግን ጻድቅ ይለብሰዋል። ብሩንም ንጹሃን ይከፋፈሉታል። የሚሰራው
ቤት እንደ ሸረሪት ድር ይሰራል። ጠባቂም እንደሚሰራው ጎጆ ነው። ባለጠጋ ሆኖ

23
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ይተኛል፤ ዐይኑን ይከፍታል እርሱ የለም፤ ድንጋጤ እንደ ጎርፍ ታገኘዋለች፤


በሌሊትም አውሎ ንፋስ ትነጥቀዋለች፤ የምሥራቅ ነፋስ ያነሳዋል፤ እርሱም ይሄዳል፤
ከቦታውም ይጠርገዋል፤ እርሱ ይጥልበታል አይራራለትም፤ ከእጁም ፈጥኖ መሸሽ
ይወዳል፤ ሰው በእጁ ያጨበጭብበታል፤ ከስፍራውም በፉጨት ያስወጡታል።
መጽ. ኢዮብ 27፡ 13 – 23
የመጀመሪያው የእሳት ወንፊት እያበጠረህ አሁንም ስላልተመለስክ ከላይ በቃሉ እንደምትረዳው ሁለተኛው
እሳት ወንፊት ታዞልሃል።

8/ አገራችን ኢትዮጵያ በመጀመሪያው የእሳት ወንፊትና በመጭው ሁለተኛው የእሳት


ወንፊት ውስጥ

ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን!! የኢትዮጵያ ሕዝብ የወደደህን አምላክ በመናቀህ ከአባቶችህ ብርቱ ዋጋ
ተከፍሎበት የተሰጠህን እንቁ እምነት ጥለህ የባእዳን እምነትና ውዳቂ እምነት ተሸክመህ ላልተቋረጠ ጉዳት
ተዳረግህ። ይህ ብቻ ሳይሆን ዛሬ ምታየውን መጠነ ሰፊ ጉዳት እያየኸው ትገኛለህ። የልዑልን ሁሉንም ህጎች
ጣስክ፤ በባእዳን ባህል እምነት አኗኗር ተጠመድክ። አባቶችህ የገነቧትን ተዋህዶ እምነትህን ጣልክ፤ በምትኩ
የዲያብሎስን እምነቱንና ስርአቱን አነገስህ። ጥንቆላን፣ አምልኮ ባእድን አነገስህ። የመናፍቃንና ወላጆቻቸው፤
እንዲሁም የተረት አምላኪዎች መዘባበቻ ሆንክ፤ እምነቱን ተዋህዶን፣ ዜግነቱን ኢትዮጵያዊነትን ካፈረባት ዜጋ
ምንም ይመጣብናል ብለው ስላልሰጉ ገዥዎችህም ጭምር አላገጡብህ፤ ፈነጩብህ፣ የወደቅህበትን እስቲ እየው።
ስለዚህ እስከ ዛሬ እያየኸው ያለው ጥፋት እንደ ካንሰር ጠፍሮ ይዞሃል። ይህች ምድር የድንግል ምድር ናት።
አመጸኛን የሚሸከም አንቀልባ የላትም። ከተዋህዶ እምነት ውጭ ለሆነ ሁሉ ምድሪቱ አትሸከምም። ሁሉንም
በረከቷን ትነፍግሃለች። ዛሬም እንደምናየው ለክፉ ችግር፣ ለረሃብ፣ ለበሽታ፣ ለድህነት፣ ለጨካኝ አገዛዝ
ተጥለሃል።
የመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ሁለመናህን አበጥሮሃል። እንደ ውጪው አገር ያልተጠረግኸው በኢትዮጵያ
ምድር እውነተኛ የልዑል ሕዝቦች፣ የድንግል ወገኖች፣ የከበሩ የቅዱሳን መላእክት ወዳጆች፤ በጥቅሉ የአንዲቱ
የእውነተኛይቱ ተዋህዶ ልጆች እንደ ቁሻሻ በየስርቻው ወድቀው በጨካኝ አረመኔ ገዥዎች ተሳደውና ተረግጠው
በልመናቸው ቁጣውን ስለተከላከሉልህ እንጂ እሰከ አሁን የሳብካትን አየር አትተነፍሳትም ነበር። ይሁንና በነሱ
ልመና ብቻ እያላገጥህ አገሪቱንም ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንንም እያጠፋህ መቀጠል ስለማይቻል የተሰጠውን
እድልህን ስላመከንከው ወደ ሁለተኛው የእሳት ወንፊት እንድትሸጋገር ታዞብሃል። ተወስኖብሃል።
በሁለተኛው የእሳት ወንፊት አገራችን ኢትዮጵያ ምን ይገጥማታል ለሚለው መልሱ ቅርብ ነው። በየመልእክቶቹ
ሁሉ ስለ ኢትዮጵያ እጣ ፈንታ በሚገባ ተገልጾአል፤ ያንን ደጋግመህ ማየት ይገባል። በመጀመሪያ ነጻ የምትወጣው
አገር ኢትዮጵያ መሆንዋን ተረጋግጦ ተገልጾአል። አሁን በሁለተኛው እሳት ማንም አለቃና ምንዝር፣ ዘራፊና
አዘራፊ፣ ዘረኛ፣ መናፍቅ፣ ተረት አምላኪ፣ ባእድ አምልኮ ተከታይ፣ ኢትዮጵያዊነትን ንቆ ዛሬ ደግሞ ለዘረፋ
በአገሪቱ የተሰማራ፣ አገሪቱን፣ ሕዝቧንም፣ እምነቷንም፣ ታሪኳንም የሚያውቁትን አውቀውም የካዱትን፣
በሕዝብ ላይ ሆኖ የሚገዛ፣ የድሃውን ጎጆ በአለማለሁ ስም የሚያፈርስ፣ ሰርቶ የደከሙትን በተለያየ የቀረጥና
የሕግ ሽፋን የሚዘርፍ በጥቅሉ በአገሪቱ ያለ ጠማማ፣ ወልጋዳ፤ እንቅፋት በሙሉ፣ ገዥና አለቃም ሆነ ምንዝር
የሚጠረግ ይሆናል።
ሁለተኛው የእሳት ወንፊት፣ ምድርም ሆነች በላይዋ የሚኖረው ሰው፤ የሚቋቋመው አይደለም። በእዚህ
በሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚያልፉ በልዑል የታመኑ በግንባራቸው ምልክት ያላቸው ብቻ ናቸው። የተቀሩት
ከመርከቢቱ ውጪ በተጨማሪም ምልክት አልባ የሆኑ እንደ ኖኅ ዘመንና እንደ ሰዶምና ገሞራ መጠረግ ብቻ
24
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ነው። የተተወላቸው እጣ ፈንታም ይኸው ነው። በዘመናት እድሜአቸው የደከሙት፣ ኢትዮጵያንና እምነቷን
ተዋህዶ ኦርቶዶክስን ለማጥፋት ነበርና፤ በዓለም ሁሉ ፈሰው ካሉት የዲያብሎስ ልጆች ወንድሞቻቸው ጋር
የዚህ ፍርድ አፈጻጸም ያርፍባቸው ዘንድ ግድ ይሆናል። ከልዑልም ትእዛዙ ወጥቶአል።

1ሀ/ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበት ሁኔታና በሁለተኛው የእሳት ወንፊት


እጣዋ
ኢትዮጵያ ሃገራችን በልዑል ምርጫ የታደለች፣ የተባረከች ለድንግልና ለቅዱሳን መላእክት በበረከት
የተሰጠች የሰው ልጅ ጠላት በሆነው ዲያብሎስ ደግሞ ቁጥር አንድ ጠላቱና የረገማት፤ ሊያጠፋት ሌትም ቀንም
የሚደክምባት ናት። በመሆኑም ይህችው አንዷ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን በጨለማው ገዥና በብርሃን ገዥ
የሁሉም ጌታ በሆነው ፈጣሪያችን መሃከል ታላቅ ውጊያ የሚደረግባት የጦር አውድማ ናት። የሰው አእምሮ
ታላቁ የውጊያ መድረክ ነው። የሰው ልጅ እንደምርጫው ራሱንም እንደአመነበት ላስገዘው ነገር እራሱን
መስዋእት አድርጎ ያቀርባል። ልዑል እንዳስቀመጠለት ወይ ለክፉ ወይም ደግሞ ለደግ (ለጨለማ ወይም
ለብርሃን) ራሱን ይሰጣል። በዚሁ መሰረት በዓለም ሁሉ እንደሚታየው ለጨለማው የተገዙ በዛሬው ሰዓት
ለታላቁ የቁጣ እሳት ፍሪዳ ሆነው የቀረቡ፤ ለዘመናት ከአያት ቅድመ አያቶቻቸው ጀምረው እውነትን ተጻረው፤
የሥጋ ሃሳብና ፍላጎታቸውን በማራመድ፤ የዲያብሎስ መሳሪያ ሆነው፤ እስከ አሁን በአባታቸው በዲያብሎስ
መሪነት፤ ለጥፋትና ለመጠፋታቸው እየደከሙ ይገኛሉ።
ከነሱ በተጻራሪ ለብርሃን ለእውነት ለፈጠሪያቸው ፈቃድና ትእዛዝ ራሳቸውን ሰጥተው በሰራዊት ጌታ
ግንባር ቀደምትነት እስከ ዛሬ ያልተቋረጠ ውጊያ እያካሄዱ ይገኛሉ። የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ከመሰረቱ
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ የተከለውን እውነት
ጨብጣ በአባቶቿ ደም አጽንታ በብርቱ የጠላት ውጊያ እዚህ ደርሳለች። የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርሰቲያን
የዲያብሎስ ቁጥር አንድ ጠላት በመሆኗ ከውስጧም ከውጪም አፍራሽ ኃይል ተሰማርቶባት በታላቅ ውጊያ
ውስጥ ትገኛለች።
ዘመኑ እስከ አሁን የዲያብሎስ ለሱም የተፈቀደ ስለነበር ጠላት የበላይነቱን ጨብጦ በቤተክርስቲያናችን
በአንዲቷ የተዋህዶ ቤታችን፣ ከአናቷ እስከ እግር ጥፍርዋ ወሮአት ይገኛል። አናቷ በዲያብሎስ የጠመንጃ
ኃይል፣ በድርጅታዊ አሰራር፣ በካቶሊኮች ብርቱ ድጋፍ፣ በመናፈቃን ጋሻ ጃግሬነት፣ በገዥው ቀጥተኛ ጣልቃ
ገብነት የተቀመጠ ፍፁም የተዋህዶ ጠላት፤ የዓለም አቀፍ የመናፍቃንና የካቶሊኮች አባልና መሪ፣ የሆነ ቤተ
ክርስቲያኗን ለመናድ ሲባል በአናቷ ላይ ከተቀመጠባት ሁለት አስርትን አስቆጥሯል። ዲያብሎስ የብሉይንም፣
የሃዲስንም ዘመን የምድር ገዥ ሆኖ እስከተፈቀደለት እስከዛሬ በሁሉም አዛዥ ናዛዥ ሆኖ አየፈጫት አየቆላት
ይገኛል። ይህ ዘመኑ መልእክት ሁለት ከወጣ (ማለትም ከ2000 ዓ.ም) ጀምሮ ወደተዘጋጀለት ወደ ሲኦሉ (ወደ
እሳቱ) እንዲወርድ በመወሰኑ ጉዞውን ጀምሮአል።
ገና እንደበፊቱ እንፈልጣለን እንቆርጣለን የሚሉ የነጋባቸው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጧንም
ሆነ ውጪዋንም ወረው በረከቷን በመጋጥ፣ ምእመኖቿን በመበተን፣ ቀይዶና አስሮ ለመናፍቃንና መሰሎቻቸው
ተኩላዎች በመስጠት የገዥው ሰራተኛና አገልጋይ የሆኑ እምነቱም የሌላቸው አገሪቱን በመዝረፍ ሥራ ላይ
የተሰማሩትን በቤተ ክርስቲያኗ አካል ውስጥ በመሰግሰግ ሽባ እንድትሆን አድርገዋታል። የዚህ ጥፋት ዋነኛ ሞተሮች
ደግሞ ከፓትርያርኩ ጀምሮ ለሱ የታመኑትን ጳጳሳት አካቶ በየደረጃው ያሉ የየአድባራቱን አስተዳዳሪዎችንም
ሆነ አገልጋዮችን ፍፁም የተዋህዶ ጠላት የሆኑትን ሁሉ የሚያቅፍ ሆኖአል። በአብነት ት/ቤቶች፤ ቁልፍ ቁልፍ
ቦታ ላይ ሰላይ የስርአቱ አገልጋዮችን ሰግስጎአል። በስብከተ ወንጌሉ ከአናቱ እሰከ ስሩ ድረስ ስውር መናፈቃንን

25
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

አሰማርቷል። ተሃድሶ፣ ቅባት፣ የሆኑ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናት በሁሉም ስፍራ የበላይነቱን ይዘው በማጥፋት
ላይ ይገኛሉ።
እውነተኞች የተዋህዶ ልጆች እንኳን በየቤተ ክርስቲያኑና አድባራቱ ሊኖሩ እስከ ሸሹበት እሩቅ ገዳማት
ጭምር በመዝመት ማንኛውንም የተዋህዶነት ምልክት የጨበጡትን ለማጠፋት እየሠሩ ይገኛሉ። ማህበረ
ቅዱሳንን በተመለከተ ቀደም በመልእክት 4 (ብዛቱ 15 ገጽ በሆነ) እንደተብራራው ማህበረ ቅዱሳን በውስጡ
ቅኖችና ለተዋህዶ እምነታቸው የቀኑ እንዳሉ ሁሉ፤ ጠላት ያሰረጋቸው እምነት ለበስ የሆኑ ፍፁም የገዥውና
የቤተ ክርስትያኗ አፍራሽ ኃይል ሊያፈርሱአት እያደቡ ይገኛሉ። በውስጡም ራሳቸውን የቀበሩም ሰዓት
ጠባቂዎችም ናቸው።
በዚህ ብቻ አልተገቱም ገዢውም ሆነ የተዋህዶ እምነት ጠላቶች አንድ ያደረጋቸውና ያሰማራቸው መሰረታቸው
ነው። የዓለሙ ገዢ ዲያብሎስ ሁሉም የዓለም መሪዎች በዋንኛነት የኛም፣ በዓለም ሁሉ ያሉ እምነቶች ማለትም
ከተዋህዶ እምነት ውጪ የሆኑ ሁሉ ገንዘቡ ናቸው። ስምሪቱም የሚከናወነው ከዓለም አቀፍ ካቶሊክ፣ ከዓለም
አቀፍ መናፍቃን፣ እንዲሁም ከተረት አምላኪዎች ጭምር ተቀናብሮ፣ በሚያዝዛቸው ገዢዎቹ የኃይል ስምሪት
ተደግፎ ነው። መልእክቶቹም ሁሉንም የዓለም አካል የዳሰሱት ጠላት ዲያብሎስም በሁሉም የዓለም አካል
ስለተንሰራፋ ነው።
የአዳም ዘር በተለይም ኢትዮጵያውያን ልብ ልትሉ የሚገባው ትልቁ ነገር ይህ ነው። የዓለም ጸሐፍት ሁሉ
ይጽፋሉ፣ ስለሥጋው ዓለም ነው። ይህ የዲያብሎስ ችግር አይደለም። እንዲሁም ስለእምነት ብዙዎች የእምነትም
የጥበብም ሰዎች ይጽፋሉ። በራሱ የእምነት ክልል ውስጥ እስካሉ ድረስ ለዲያብሎስ አይገደውም። የሱ ጭንቀት
ስለተዋህዶ እምነት የሚጽፉ በተለይም በእምነቱ የፀኑ ከሆኑ ብቻ ነው። ስለ ዲሞክራሲ ተጻፈ፣ ስለኢኮኖሚ
ተጻፈ፣ ስለአገር ድንበር ተጻፈ፣ ስለፖለቲካው ተፃፈ፣ ይህ ሁሉ ለዲያብሎስ ችግሩ አይደለም። የሱ ችግር
ተዋህዶ እምነትን የሚያጸና ተግባሩም ፅሁፉም እንዲሁም ፅናቱም ሲሰምሩ ካየ ነው። የእምነቱን መሰረት
ጠንቅቀው ያወቁትን አገራችን ኢትዮጵያና እምነቷ ተዋህዶ አምጠው የወለዱአቸውን ብዙ መምህራን፣ ብዙ
ዲያቆናት፣ ብዙ መነኮሳት፣ ብዙ ባሕታውያን፣ ብዙ ጳጳሳት በስውርና በቀጥታ በተለያየ የአደጋ ቅንብር በራሱ
ቤተ ክህነት ውስጥ በተደራጀ ቡድንና በገዢውም የፀጥታ ኃይል እንዲወገዱ ተደርጓል። ይህ ድርጊታቸውን
ደግሞ እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ጠንቅቀን እናውቃለን። በሌላው ርእስ የተወሰነባቸውን እናያለን።
የሁለተኛው የእሳት ወንፊት በኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምን ይፈጸማል የሚለው ዋናው
ጥያቄ ነው። ለዚህ ዛሬ የልዑልን ቤት እያጠፉ ያሉ በውስጧም በውጭም ሆነው ለተዋህዶ እምነት መጥፋት
እየሠሩ ላሉ ሁሉ ከዚህ የሚከተለው ቅጣትና መጠረግ ታዞላቸዋል። ይህ ትእዛዝ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ
ክርስቲያን ፀድታ በልዑል እግዚአብሔር መንፈስ የተቀቡት እውነተኛ እረኞቿ እስከሚረከቧት ድረስ የፀና
ይሆናል። ስለዚህ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፣

በጠላቶቼ ላይ ቁጣየን እፈጽማለሁ፤ የሚቋቋሙኝንም እበቀላለሁ፣ እጄንም ባንቺ ላይ


አመጣለሁ ዝገትሽንም በጣም አነጻለሁ፣ ቆርቆሮሽንም ሁሉ አወጣለሁ፣ ፈራጆችሽንም
እንደ ቀድሞው፣ አማካሪዎችሽንም እንደ መጀመሪያው ጊዜ መልሼ አስነሳለሁ፣ ከዚያም
በኋላ የጽድቅ ከተማ የታመነችም ከተማ ተብለሽ ትጠሪያለሽ፣ ጽዮን በፍርድ ከሷም
የሚመለሱ በጽድቅ ይድናሉ፣ በደለኞችና ሃጢአተኞች ግን በአንድነት ይሰበራሉ፤
እግዚአብሔርንም የሚተው ይጠፋሉ፤ በወደዳችኋት የአድባር ዛፍ ታፍራላችሁና
ስለመረጣችኋትም አትክልት እፍረት ይይዛችኋልና፤ ቅጠሏ እንደረገፈ ዛፍ፤ ውኃም
እንደሌለባት አትክልት፤ ትሆናላችሁና፤ የኋለኛውም እንደተልባ ጭረት ሥራውም
እንደጥላሸት ይሆናል፤ አብረውም ይቃጠላሉ፤ እነርሱንም የሚያጠፋ የለም።
ኢሳይያስ 1፤ 24 – 31
26
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ቃሉን የሚነግረን ትእዛዞቹ ተፈጻሚ ይሆናሉ የሚተርፉ ለመልካም፤ የሚጠረጉ ለሲኦል ይሆናሉ

ትእዛዞች፤
ሀ/ በኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አመራሩ ላይ ላሉት፣ የመናፍቅና የካቶሊክ ጉዳይ ፈጻሚ ለሆኑት።
ተዋህዶ እምነትን ለማጥፋት መድከም ታላቅና ይቅር የማይባል ወንጀል ነው። ያውም የበግ ለምድ ለብሶ
በቤተክርስቲያኗ አናት ላይ ፊጥ ብሎ፤ በጎችን መበተን፤ ማጥፋት፤ ማረድ፤ መግደል፣ የሚያስከትለው
ምን እንደሆነ ሕዝቅኤል 34 ይነግረናል ስለዚህ ሞትን ለናንተ መስጠት ሽልማት ነው። ስለሆነም ሞትን
የምትለምኑበት በሁለመናችሁ ላይ የሚሰለጥን በርባሪ እሳት ታዞአል። ለጥፋት የምትገለገሉበት እጅ፣ ዐይን፤
ጆሮ፣ እግር፣ አእምሮአችሁ የማታዙት፣ የማይታዘዝላችሁ ይሆናል። እንቅልፍ የሚባል እንዳታገኙአት ታዞአል።
ሞት ያባርራችኋል ስትገኙለት ይሸሻችኋል። ሌትም ቀንም የአካልም የኀሊና እረፍት ታጣላችሁ። ልትቀምሱ፣
ልትጠጡ፣ የወደዳችሁት ሁሉ መርዝ ሆኖ ያሰቃያችኋል። ስቃያችሁ ጋብ የሚለው ለጥቂት ደቂቃዎችም ቢሆን
እንቅልፍ የሚያሸልበው፤ በኔ በልዑል ባሪያ የተላለፉትን መልእክቶች፤ ከአንድ ጀምሮ እስከ አሁኑ ሰዓት
የወጡትን መልእክቶች በሙሉ፤ በይፋና በአደባባይ፤ በማስሚዲያ ስታነቧት፤ ሕዝብም ሰምቶ ሲጠግባት ብቻ
ነው፤ በመኝታ ላይ ማረፍ የሚቻለው። ብዙ መሰሎቻችሁ በሚያዩበት ስፍራ በኔ በልዑል ባሪያ የተላለፈውን
ሙሉ መልእክት (ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቁጥር 1፤ 2፤ 3) የያዘውን ጥራዝ፤ ደረታችሁ ላይ በግልጽ
በማስቀመጥ ነው።
ከላይ በተዘረዘረው መልኩ የምታገኙዋት እንቅልፍ ከአንድ ሰዓት በፍፁም አትበልጥም። ይህም እድል
የሚሰጠው በልባችሁም በአደባባይ ተናግራችሁ የሰራችሁትን ስትናገሩ ብቻ ነው። እንዲሁም ያሰራችኋቸውን
የእግዚአብሔር ሕዝቦች ከነካሳቸው ስትለቁ፤ በየገዳሙ፣ በየቤተክርስትያኑ፣ በየገዳማቱ የወተፋችኋቸውን
አጥፊዎች ስታነሱ ብቻ ነው። የአንድ ሰዓቷም እንቅልፍ በቀን አንዴ የምትሰጣችሁ እንጂ ከዛ ውጪ ያለም።
ከውስጣችሁ ለታደሉት ሞት አሰቃይቶ ይወስዳል። ይህ እድል ለዲያብሎስና ከእምነታችን ቤት አናት ላይ
ለተቀመጠው ፓትሪያርክ፤ ከሲኖዶሱ ጀምሮ እሰከስር አጥቢያ ቤተክርስቲያንና ገዳማት ድረስ በመሰግሰግ ለዚህ
ሰው ቅስትና ማገር ሆናችሁ፤ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለአንድ ሰውና መሰሎቹ ተኩላዎች ታምናችሁ ላለችሁ
ሁሉ፤ ለሱ የታዘዘው ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ስቃይ ለናንተም ታዞአል።
ከዚሁ በተረፈ ከላይ እንደታዘዘው የልዑል ልጆች ቦታውን ሲረከቡት ከስቃያችሁ የሚገላግላችሁ ክፉም
ይሁን ደግ ውሳኔ በሰዓቱ ታውቁታላችሁ። እዚሁ የምትደርሱት ግን እጅግ ጥቂቶች ናችሁ። በዚሁ ቅጣት
ከነትእቢታችሁ ለመቀጠል ከዳከራችሁ ቅጣቱ በ49 እጥፍ እንዲያድግ ተወስኖአል።
ለ/ ከስር ለተኮለኮላችሁ በአስተዳደሩም በአገልግሎቱም ላይ ላላችሁ የተዋህዶ እምነትን ታፔላ ለለጠፋችሁ።
ከላይ ላመራሮቻችሁ እንደታዘዘው በእናንተ ላይ ተፈፃሚ ይሆናል። ከእግዚአብሔር ይልቅ በነሱ ታምናችኋልና፤
የነሱ መዝገብ ሲዘጋ የናንተም አብሮ ይከደናል። ይህ ሁሉ እየሆነ፤ ከነድንጊያ ልባችሁ ከጸናችሁ፤ ይኸው ቅጣት
በ7 እጥፍ ያድጋል። በዚህ ካልተረታችሁ 7 ጊዜ 7 እጥፍ 49 ጊዜ እጥፍ ሆኖ ጨምሮ ያጠናቅቃችኋል።
ሐ/ ዲያብሎስ ሁሉንም የዓለም አካሎቹን አስተሳስሮ ስለመግዛቱና የየተዋረድ ትእዛዝና ቅንብሮቹ።
በዓለም ሁሉ ያሉ ገዢዎች በዲያብሎስ መለኪያ ስልጣን ላይ ይወጣሉ። ካልታዘዙት ይወርዳሉ። ከታዘዙት
ደግሞ ይቆያሉ። የሱ አሰራር የሚሰበረው ከላይ የልዑል ትእዛዝ ሲያርፍበት ብቻ ነው። እግዚአብሔርን እንደ
እግዚአብሔርነቱ የሚያከብሩ ሕዝቦች ወይም ግለሰብ ላይ፤ የዲያብሎስ ሕግ አይሰራም። ነገር ግን ከእግዚአብሔር
ሕግ ሲወጡ እስራኤላውያን ይገጥማቸው እንደነበረው ውጣ ውረድ ዛሬም ላሉ ሁሉ ይሰራል። (ዛሬም እንደ
ሕዝብ ለልዑል የሚገዛ ባናይም፤ እንደ ግለሰብ ግን ስላሉ ዲያብሎስ ይፈትናቸዋል እንጂ ሊያዛቸው ሊገዛቸው
አይችልም) የተቀረው ግን ፈጣሪውን በራሱ ምርጫና ውሳኔ የካደና በመምሰል የቆመ፤ በመሆኑ ለዲያብሎስ

27
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

አገዛዝ የተተወ ነው። ማንኛውም ሰው በምርጫው የዚህን ዓለም ደስታና ፈንጠዝያ ከመረጠ የአምላኩን የፍቅር፣
የጽድቅ ትእዛዝ ከናቀ፣ ከካደ፣ ዲያብሎስ የዚች ምድር ጊዜያዊ አዛዥና ፈታኝም ነውና ይረከበዋል። ለዚህም
ነው የሚበዛው የሰው ዘር በጉያው የተወሸቀው። ዓለምን ንቀው፤ ዲያብሎስን ክደው በልባቸው፣ በነፍሳቸው፣
በሥጋቸውም የሰራዊት ጌታን ያነገሱ፤ ምንም ፈተናቸው ቢበዛ በረከታቸውና ተስፋቸው የጸና ነው። ከውጣ
ውረዱ ጋር ዘወትር በአምላካቸው ይጠበቃሉና፤ ከዚህ ውጭ ያለው የሰው ዘር ግን በጨለማ ኃይል ተተብትቦ፤
ለዲያብሎስ ፍርፋሪ፣ ለግብፅ ሽንኩርት ተገዝቶ ይኖራል።
ዲያብሎስ የተገዙለትን በስልጣን፣ በሀብት እንዲጠልቁ ያደርጋቸዋል። ከዚያ የሚያንሱትንም በእለት ተእለት
ሕይወታቸውና በትርፍ ፍለጋቸው በመግባት የራሱ ተገዢ ያደርጋቸዋል። ዛሬ የምናየው እውነት በዚህ መስፈሪያ
የመጣ ነው። የሃይማኖቱም መሪዎች አድርጉ የተባሉትን ያደርጋሉ። የእምነቱ ሕግ ፈቀደም አልፈቀደም፤
ምሳሌ እንይ፤ የአገራችን የተዋህዶ እምነታችን መሪ (በባለ ጠብመንጃው ድጋፍ ተቀመጠ፤ ወይም በዲያብሎስ
የተመደበ) ከተዋህዶ እምነታችን ጋር ምንም የማያገናኛቸውን በመሰረታዊ የእምነታችን መመሪያ የተወገዙትን
ተቀብሎ የዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን ህብረት በሚል ስብስብ ውስጥ በመታቀፍ፤ የክብር ፕሬዘዳንት የሚል
ሹመት መጠሪያ ሆኖ ዘወትር እንሰማለን። ይህ ህብረት የዓለም አቀፍ መናፍቃንን፣ ካቶሊኮችን፣ በዋናነት የያዘ
ነው።
እንዲሁም በአገራችን መናፍቁንም ካቶሊኩንም እስላሙንም በመሰብሰብ ለሰላም የሚል የእምነት ጥርቅም
ፈጥረው የዚሁ ሰብሳቢ ሁነዋል። ሰላም በተዋህዶነት በመፅናት እንጂ በእምነት ካባ የገዢው የፖለቲካ ድራማ
ሰራተኛ በመሆን የሚመጣ አልነበረም። ለዚህም ነው በቤተ ክርስቲያናችን በተዋህዶ እምነታችን ቤት አናት ላይ
ዲያብሎስ ተቀምጦአል የምንለው። ዲያብሎስ ያዛል፤ ጳጳስ ሆነ ፕሬዘዳንት ይታዘዛል። ፈቅደው የተገዙለት
አባታቸው ነውና።
መ/ በቤተ ክርስቲያናችን በተዋህዶ እምነታችን ላይ ለሰራችሁት ወሰን የለሽ ወንጀል፤ ከላይ በ1 ሀ/ሀ እና
በ1 ሀ/ለ ለተጠቀሳችሁት፣ በእምነታችን ላይ ለሰራችሁት ቅጣት፤ በትእዛዞቹ እንዳለ ሆኖ በሥጋው በገዢው
መንግሥት ውስጥ እንደ ተሳትፎአችሁ መጠን ለገዢው ስርዓት የሚታዘዘው ቅጣት ማለትም የሁለተኛ ደረጃ
የእሳት ወንፊት በተጨማሪ በእናንተ ላይ ተፈጻሚ ይሆናል።

2ለ/ በአገራችን ያሉ የተለያዩ እምነቶች በሁለተኛው የእሳት ወንፊት


የሚጠብቃቸው እጣቸው።
በአገራችን ኢትዮጵያ የተንሰራፉ እምነቶች ብዙ ናቸው። ካቶሊክ፣ መናፍቅ፣ ተረት አምላኪ /ሙስሊም/
ሌሎችም እኒህ ሁሉ ታዲያ ሲደክሙ የኖሩትም ልፋታቸውም አንዲቷን የቀናች በልዑል የተወደደችና የተመሰረተች
ተዋህዶ እምነትን ማጥፋት ግንባር ቀደም ሥራቸው ነበር። ዛሬም ሁሉም እንደሚረዳውና እንደሚያየው፤
ገዢውም፤ መናፍቁም፣ ተረት አምላኪውም፤ ካቶሊኩም፤ በቅንብርና በስልት በቤተክርስቲያናችን ቁልፍ
ቦታ ሁሉ መሽገው በተቀመጡት ተልእኮ ፈጻሚ መናፍቃን፤ ተሃድሶ፤ ቅባት፤ በሚባሉ በመታገዝ የጥፋት
ሥራቸውን ያለከልካይ እያከናወኑ ይገኛሉ።
እኒህን የጥፋት ሰዎችና የእምነት ድርጅቶች ምን ይገጥማቸዋል። ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ለነሱ ምን
ይመስላል! ከእንግዲህ ሁልህም የዲያብሎስ ልጅ በሺዎች ዘመናት ስትፈጭ፣ ስትቆላን ኖረሃል። ያ ዘመንህ
አብቅቶአል። ከዚህ በኋላ ጉዞህ ወደሲኦልና ወደጥልቁ እሳት ብቻ ሆኖአል። ከዚህ በኋላ ላንተ ከተገዙ
ዝግንትሎችህ ጋራ በማያቋርጠው የእሳት ወንፊት እየተበጠርክ ትሄዳለህ። ጅማሮውም ታይቶአል! ቀጣዩም
በ49 እጥፍ አድጎ ይቀጥላል። የአሁኑን አታልፈውም እንጂ በሺዎች በሚሊዮኖች እጥፍ ማብዛት የልዑል ችግር
አይደለም። የልዑልን ቁጣ ቀስቅሰህ ካነደድክ ቆይተሃል። ትእግስት የሆነው ላንተ እድሜ አይደለም በጥፋት

28
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ሂደት ውስጥ ይድኑ ዘንድ እጣቸው ለሆነ ሲባል እንጂ። በየጠረጋው ማዕበል ውስጥ በምልክቱ መዝገብ ውስጥ
የሰፈሩ ነገር ግን በተዋህዶ የእምነት መርከብ ውስጥ ያልተሳፈሩ ዲያብሎስና ዓለም ያሳዘለቻቸውን ሸክማቸውን
ዝግንትል ሁሉ በየቁጣው ሂደት ውስጥ እያራገፉ ከወደቁበት በታላቅ ስብራትና በመጸጸት እንዲሰበሰቡ ታስቦ
መሆኑን ሁሉም ሊያውቀውና ሊረዳው ይገባል።
በዋናነት ከሚመጡት ጥፋቶች በተጨማሪ በዚህ ርእስ ለተጠቀሳችሁም ሆነ በሁሉም ርእስ ስር ተጠቅሳችሁ፤
በመላው ዓለም ጭምር ላላችሁ ምልክት አልባ የአዳም ዘር በሙሉ ከዚህ የሚከተለው ታዞባችኋል።
1/ ከተፈጥሮ አደጋው፤ ከማህበራዊ ቀውሱ፤ ከፖለቲካው ትርምስ፤ ከኢኮኖሚውጥፋትና ቀውስ በተጨማሪ
በተለምዶ ከምናውቃቸው መባርቅት ክንዋኔ ውጭ ፍፁም ታይቶም ተሰምቶ በማይታወቅ ጉልበት በብዙ
መቶዎች ጉልበት ጨምረው በማያቋርጥ ፍሰት ምልክት አልባ የአዳም ዘርን ይፈጫሉ። መባርቅቱም በጠራራማ
ፀሐይ ይሁን በደመና ቀንም ይሁን ሌት ጊዜንም ሆነ ሰዓት ሳይመርጡ፤ የተፈለገውን ስፍራ ለማጥፋት
ይወርዳሉ። በተለይም የዘመኑ ገዢዎች፤ የጦርና የጸጥታ ሃላፊና ሰራተኞች፤ ሞኖፖሊስቶች፤ የተዋህዶ እምነት
ጠላቶች ሁሉ ግንባር ቀደም ተመቺ ይሆናሉ። በዚህ የቁጣ በትር የሚመቱ ሞት ከወሰዳቸው እድለኞች ናቸው።
ካልወሰዳቸው ግን የነሱን ስቃይ ማየት ደግሞ ለተመልካቹ ለራሱ አጅግ ጭንቀት የሚፈጥር ይሆናል። በብዙ
ሀገሮች እንደሚታዩት መብረቅ ከዝናብ ጋር፤ ከከባድ ማእበሎች፤ እንደ ቶርኔዶ ከመሳሰሉ ጋር የሚከሰቱ
ቢሆንም መጪዎቹ የተለዩ ናቸው። በአገራችን የ2003 ዓ.ም የክረምት መግቢያ ላይ በመላው ሀገሪቱ የተከሰቱት
መብረቆች ብዙ ከብትን፤ ብዙ የኤሌክትሪክ ተሸካሚና ትራንስፎርመሮችና እንዲሁም ሰዎችን በዝናብና በደመና
ወቅትም አልፎም በደረቅ ፀሐይም በመውረድ ጉዳት አድርሰዋል። እነዚህ መጪውን ለማመላከት የተከናወኑ
ምልክቶች ናቸው። መጪው በጋ ክረምት መፀው የማይል ነው።
እነዚህ መባርቅት ሰውን ለመምታት ብቻ አይደለም የሚመጡት፤ ከዚህም ውጪ ማንኛውንም የዲያብሎስ
መጠቀሚያ ያጠፋሉ። ጦራቸውን፤ ክምችታቸውን የማደራጃ፤ የመፈብረኪያ ስፍራቸውን ድሃን ለመፍጀትና
ለመግዛት የሚጠቀሙበትን የጸጥታም ሆነ የማፈኛ ተቋም ሁሉ ይጠርጋሉ። መባርቅት ቅዱሳን መላእክት
ከጨበጡት ቁጥር የለሽ ኃይል ውስጥ አንዱ ናቸው። እኒህ መባርቅት በተለምዶ ከምናየው የመባርቅት ኃይል
በ49 እጥፍ ጉልበት የማውደም ኃይል ይዘው ይመጣሉ።
2/ የአዳም ዘር! እስካሁን የምታውቀው የቅጣት ማዕበል ሁሉ ከብዶ ቢመጣም በታሪክም በማየትም
በመስማትም ታውቀዋለህ የማታውቀው ፍጥረቱን ምን እንደሆነ የማትለየው የአውሬ አይነት ምድሪቱን ይከድናል።
ከፊል ሰው፤ ከፊል አውሬ፤ አውሬ መሰል አጋንንት፤ የተለየዩ አውሬዎችን መልክ የቀላቀለ አውሬ ሌትም
ቀንም ምልክት አልባውን ለመብላት ይዘምታል። የሰው ልጅ ያደራጀው ማንኛውም መሳሪያ እያጠፋቸውም
ለቅጣቱ የላካቸው የሰራዊት ጌታ እስካላነሳቸው ድረስ! ይህ የሚሆነው ደግሞ የታዘዙትን አጠናቀው ሲጨርሱና
የልዑል ሕዝቦች ሁሉን ተረክበው ሲደላደሉ ብቻ ይሆናል።
የልዑል ሕዝቦች በተወሰነላቸው በየመኖሪያቸው ላይ ምልክትና ጥበቃ ስለሚኖር መግባት አይቻልም።
ፈቅደው ከሚያስጠልሉት በስተቀር።
3/ የሰው ዘር ሰምቶትም አይቶትም ወይም ይሆናል ብሎ ገምቶት የማያውቀው ብዙ ሚሊዮኖችን የሚያጠፋ
የበሽታ ዓይነት ይከሰታል። ያለከልካይም ይጠርጋል።

29
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

2ሐ/ የአገራችን ኢትዮጵያ ገዢዎችና ምንዝሮቻቸው በ2ኛው የእሳት ወንፊት


ውስጥ /የነሱ ድጋፍ ሰጪ አዛዥ መካሪዎችም/ እጣቸው።

የኃጢአተኞችም ወገናቸው እንደ ገለባ ክምር ነው። ፍጻሚያቸውም ለገሃነም ይሆናል።


የኃጢአተኞች ሥራቸው ክፉ ነው ፍጻሜዋም ገሃነም ነው።
መጽኃፈ ሲራክ ም፤ 2 ፡ 9 – 10
ስለ ኢትዮጵያ እጣ ፈንታ እሰከዛሬ በወጡት መልእክቶች ውስጥ በሰፊው ተገልጦአል። ይህ ርእስ የሚዳስሰው
ገዢዎቻችን ምን እየሠሩ ነው! ለሥራቸውስ ምን ይገባቸዋል! የሚለውን ሲሆን፤ ስለ አገዛዛቸው በአገራችንና፤
በሕዝባችን፤ በእምነታችን፤ በታሪካችንም ላይ የሠሩትን በጥቅሉ በመዳሰስ፤ መጪው እጣቸውንም የምናይበት
ርእስ ነው።
አገራችን ኢትዮጵያ በዘመኗ ሁሉ ስትፈተን ኖራለች፤– ነገር ግን ያለፍንበትን የ20 ዓመታት የሚመስል
የጉዳት ዘመን የለም። የዛሬው ገዢዎቻችን እነማን ናቸው? እነዚህ እጅግ የከፉ ሕዝብን፤ አገርን፣ እምነትን
ለማጥፋት ተማምለው የተነሱና ጠፍተውም አጥፍተውም እዚህ የደረሱ ናቸው። ገዢዎቻችን የኢትዮጵያ ህዝብ
ታውቃቸዋለህን? ውስን ሰው ከመሰረታቸው ያውቃቸዋል። የሚበዛው ግን አያውቃቸውም። ልጆቻችን ለራሳቸው
ብቻ አልተፈጠሩም፤ እዚህ ድረስ ለመድረስም ብቻቸውን አልተጓዙም፤ ዛሬም ብቻቸውን አልቆሙም።
እነዚህ ገዢዎቻችን በአገራችን በኢትዮጵያ ላይና በተለይም በተዋህዶ እምነታችን ላይም ፍፁም በደማቸው
የተዋሀደ ከዘራቸው ጭምር የተላለፈ ጥላቻን የተሞሉ ናቸው። ሕዝቡን በጥቅሉ በተለይም ደግሞ ተዋህዶነትንና
ኢትዮጵያዊነትን በጥቅሉ የያዘውን የሰሜኑን ሕዝብ እጅግ ይጠላሉ። ቢቻላቸው እንደ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ
ቢጠፋላቸው ደስታቸው ነው። ይህም ሲባል የትግራይ ሕዝብ የሰሜን ሰው አይደለም ወይ በሱስ አይደለም
ወይ የሚገለገሉትና የሚታገዙት የሚል ስሜት ይጭራል። አዎን ተጠቅመውበታል። አሁንም በጥቂቱ በግሉ
በራሱ በብዙው በስሙ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። ይህም ሲባል አገርን፣ እምነትን አልበደሉም ማለት አይደለም
በተለይ ወጣቱ ለዚህ ጥፋት አድርሶዋቸዋል። ዛሬም አብሮ ህዝቡን የሚዘርፉና የሚያሰቃዩ አሉ። ነገር ግን
የወደቁትን ሴትና ወንድ መነኮሳትን ለማየት እንደ ማስረጃ የሚሆኗችሁ ድንግልን ለመሳለም 15 ቀን በእግራቸው
ተጉዘዉ ግሸን የሚመጡትን ብታዩአቸውና ብትጠይቋቸው በቂ ነው።
በትግራይ ሁለት ገጽታን ትመለከታላችሁ፡– አንደኛ በረሃብ ውስጥ ሆኖ እምነቱን ተዋህዶነቱን አጥብቆ
የሚኖርበትን፣ ሁለተኛው በገዢዎቹ ተመክቶ በታጋይነት ተኩራርቶ በወገኖቹ ደም፣ በኢትዮጵያውያን ርሃብና
ጭንቅ እየተሳለቀ የመጣና አሁንም በዛው ጥፋት ውስጥ ያለው ብዙ ነው። በተጻራሪው በተዋህዶ እምነታቸው
ጸንተው፣ በትግራይ በረሃ የወደቁ ብዙ አባቶች መነኮሳት እንዳሉ ሁሉም የሚያውቀው ነው። የዛሬዎቹ
ገዢዎቻችን የዛሬው ትውልድ ታሪኩንና ተዋህዶ እምነቱን እንዳያውቅ የመጀመሪያውን የማጥፋት ሥራ የሠሩት
በዚሁ በትግራይ ውስጥ ነው። በቁጥር ከ80 የማያንሱ በእምነታቸው በኢትዮጵያዊነታቸው የሚታወቁትን፤
በሃገሬው ሕዝብ ከበሬታ የነበራቸውን፤ ኋላ ቀር ናቸው በሚል ዲያብሎሳዊ ፍልስፍና፣ የትግራይ ወጣት
በድርጅታዊ አሰራር እንዲቀበል በማድረግ፣ ታሪኩንና ተዋህዶ እምነቱን የሚነግረውና የሚያስጨብጠው እንዲያጣ
ለማድረግ እንዲወገዱ አድርገዋል። የጨለማ ሥራ ተሸፍኖ አይቀርም። ዛሬ ስለነሱ ወደር የሌለው የሀገር ጥፋት
አብረዋቸው ውስጥ የነበሩ ለጠላታቸው መጠቀሚያ መሆናቸውን የተረዱ የተፈጸመውን እየተፈጸመም ያለውን
የሀገር ማጥፋት ወንጀል እየነገሩን ይገኛሉ።
ገዢዎቻችን ዛሬ ሙሉ በሙሉ የባህረ ነጋሽ /ኤርትራ/ ተወላጆች ናቸው። ይህ ደግሞ ዛሬ የአደባባይ
ምስጢር ሆኗል። ምን ቢሸፈኑ ልዑል አምላካችን ወደ አደባባይ ወደብርሃን ማንኛውንም የጥፋት ሥራ
ያወጣዋል። አገሪቷን ጠልተው ከሄዱ በኋላ ዓለም አቀፍ ቅንብር በተደረገበት እርዳ ተረዳዳ የአገሪቱን ሀብት

30
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

እየዘረፉ ይገኛሉ። መንግሥት የራሳቸው፣ ደኀንነቱ፣ ወታደሩ፣ ሚኒስቴሩ፣ ኮምሽነሩ፣ ሁሉም ስልጣን የተባለች
በሙሉ በራሳቸው ተጠቃሎ ተይዟል። የሀገሪቱ ባንክ፤ ኢንሹራንስ፣ ግንባታ፣ ኢንቨስትመንት፣ አስመጪ
ላኪነት ሁሉም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በነዚሁ ሰዎች ተይዞ ሕዝቡ በሙሉ በሕግ ሽፋን በልማት ሽፋን በሚወጡ
መመሪያዎችና ማስገደጃዎች እየተነጠቀና እየተዘረፈ ይገኛል።
የነዚህ ደጋፊዎች ደግሞ ካናት ካለችው ባቢሎን ጀምሮ የተወሰኑ የአረብ ሀገራትን አካቶ እንደ ቻይናና ህንድ
የመሳሰሉትን የአጋንንትና ጣኦት አምላኪዎች ጨምሮ ይህቺን አንዲት የተዋህዶ እምነት ሀገር ለማጥፋት እስከዛሬ
እየደከሙ አሉ። ሕዝቡን በዘር ከፋፍለዋል! ኢኮኖሚውን ወርሰዋል፤ ቤቱን አፍርሰዋል፤ በቦታው የራሳቸውን
ህንጻ ገንብተዋል፤ በግብር ስም ያላፈራውን ያላገኘውን ውለድ ብለው ኑሮውን አፍርሰው ለረሃብ ሰጥተውታል።
በአገሪቱ ለነሱ የታመኑ፣ በሆዳቸው የሚያስቡ፣ ሰለአገር፣ ስለእምነት ቦታ የሌላቸውን መልምለው በመላ አገሪቱ
ፈሰው ለነሱ እንዲሰልሉ የነሱን አገዛዝ እንዲጠብቁ አድርገዋል።
የአገሪቱን ታሪክ የተዋህዶ እምነቱን የአባቶቹን መሰረቱን ለማጥፋት ቅርሱን ይዘርፋሉ፣ በርዘው ከልሰው
ስለተዋህዶ እምነቱ ስለአገሩ ታሪክ ምንም እንዳያውቅ በሁሉም ሕይወቱ ዙሪያ የተደራጀ መምሪያ አደራጅተው
እያጠፉት ይገኛሉ። የተለያየ የተበረዘ ስለታሪካችንም፣ ስለተዋህዶ እምነታችንም የተደለዘ ጽሁፍ ይበትናሉ።
አገራችንን በማጥፋቱ ሥራና ውጥን ውስጥ እነግብፅ፣ እነባሕረ ነጋሽ፣ እነሱዳን፣ እነጅቡቲ፣ እኒህ ሁሉ
ኢትዮጵያን የማጥፋቱ አካሎች ናቸው። ትላንት ደግሞ የኛው ግዛት የነበሩ ናቸው።
በኢትዮጵያ ላይ የሚካሄደው ዘመቻ በዋናነት እነአሜሪካ፣ ከአውሮፓ፣ እነእንግሊዝ፣ እነፈረንሳይ፤ ከኤስያ
እነሕንድ፣ እነቻይና፣ ከአረብ አገራት የሆኑም የሚሳተፉበት ነው። ስለነዚህ አገራትም ሁሉ ስለሁሉም የቀደሙትን
መልእክቶች ማየት እጅግ ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም የሁሉም አገሮች ሥራቸው የተመዘነበት ፍርዳቸው
ሰፍሮ ይገኛልና። ለመንደርደረያ ያህል ይህን ካልን በመጪው የሁለተኛው የእሳት ማበጠሪያ ገዢዎቻችንና
ምንዝሮቻቸው እንዲሁም በዙሪያችን ያሉ ለጥፋታችን እየሠሩ ያሉ አገሮችስ በ2ኛው የእሳት ማበጠሪያ እጣቸው
ምንድነው?
በገዢዎቻችንና ቁጥራቸው በሚሊዮን የሚቆጠር አገልጋዮቻቸው ላይ የተወሰነ ፍርድ በቀደሙት መልእክቶች
እንዳለ ሆኖ በሁለተኛው እሳት ይበጠሩ ዘንድ ይህ ትእዛዝ በልዑል ፈቃድ ወጥቶአል።

አምስተኛውም መልአክ ነፋ፣ ከሰማይም ወደምድር ወድቆ የነበረ ኮከብ አየሁ፤


የጥልቁም ጉድጓድ መክፈቻ ተሰጠው የጥልቁን ጉድጓድ ከፈተው፣ ጢስም ከታላቅ
እቶን እንደሚወጣ ጢስ ሆኖ ከጉድጓድ ወጣ፤ ፀሐይና አየርም በጉድጓዱ ጭስ
ጨለሙ፤ ከጢሱም አንበጣዎች ወደ ምድር ወጡ፤ የምድርም ጊንጦች ስልጣን
እንዳላቸው ስልጣን ተሰጣቸው፤ የእግዚአብሔር ማህተም በግምባራቸው ከሌለባቸው
ሰዎች በቀር በምድር ያለውን ሳር፣ ቢሆን ወይም ማናቸውንም የለመለመ ነገር ወይም
ማናቸውንም ዛፍ እንደይጎዱ ተባለላቸው፣ አምስት ወርም ሊያሰቃዩአቸው ተሰጣቸው
እንጂ ሊገድሉአቸው አይደለም፣ እነርሱም የሚያሰቃዩት ስቃይ ጊንጥ ሰውን ነድፎ
እንደሚያሰቃይ ነው በዚህም ወራት ሰዎች ሞትን ይፈልጋሉ አያገኙትምም፣ ሊሞቱም
ይመኛሉ ሞትም ከነርሱ ይሸሻል፣ የአንበጣዎችም መልክ ለጦርነት እንደተዘጋጁ ፈረሶች
ነው፣ በራሳቸውም ላይ ወርቅ እንደሚመስሉ አክሊሎች ነበሯቸው፣ ፊታቸውም እንደ
ሰው ፊት ነበረ፣ የሴቶቹን ጠጉር የሚመስል ጠጉር ነበራቸው፣ ጥርሳቸውም እንደ
አንበሳ ጥርስ ነበረ፣ የብረት ጥሩር የሚመስልም ጥሩር ነበራቸው፣የክንፋቸውም
ድምጽ ወደጦርነት እንደሚጋልቡ እንደ ብዙ ፈረሶች ሰረገላዎች ድምጽ ነበረ፣ እንደ
ጊንጥም ጅራት ያለ ጅራት አላቸው፣ በጅራታቸውም መውጊያ አለ፤ ሰዎችንም

31
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

አምስት ወር እንዲጎዱ ስልጣን አላቸው፣ በእነርሱም ላይ ንጉስ አላቸው፣ እርሱም


የጥልቅ መልአክ ነው፣ ስሙም በእብራይስጥ አብዶን በግሪክ አጶልዮን ይባላል፣
የዮሐንስ ራእይ ም. 9፤ 1 – 11
ስለሚመጡት ጠራጊዎች ታውቁ ዘንድ እኒህም ጠራጊዎች ከሌሎች ጋር ሆነው ሁሉንም የሰው ዘር ምልክት
የሌለውን ሁሉ ሊያጸዱ፣ ሊያሰቃዩ፣ ሊገሉ፣ሊቆረጥሙ ስልጣን አላቸው ከዚህ በታች ያለው ትእዛዝም እነዚህን
መቅሰፍቶች ያካተተና የልዑልን ትእዛዝ ለመፈጸም በተጠንቀቅ የቆመ ነው። የሚጠብቀውም የዚህን መልእክት
መውጣት ብቻ ነው። የቅጣት ትእዛዝም በወጣባቸው ሁሉ ላይ ትእዛዙን ተከትለው ለአፈጻጸሙ በምድሪቱ ሁሉ
ላይ የሚዘምቱ ኃይሎች ናቸው።

ትእዛዞች
»» አገራችንን ኢትዮጵያን ባሁኑ ጊዜ በመግዛት ላይ የሚገኙት፡– ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ፕሬዚዳንት፣
በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩ ሚኒስትሮች፣ ም/ሚኒስተሮች፣ ሚኒስትር ደኤታዎች፣ ኮምሽነሮች፣
የፌደራል ሃላፊዎች፣ የየክልሉ የፀጥታ አስተዳደር፣ የፍትህ መሪዎች፣ ስርአቱን በኃይልነት ደግፈው
ያቆሙ ኃይላት /ፖሊስ፣ ወታደር፣ መረጃ/ እንዲሁም ስርዓቱ ላቆመው መንግሥት በአባልነት ቅጽ
ሞልተው ላሉ ሁሉ፣ በስወርና በግልጽ በተቃዋሚነት ስም የቆሙ መስለው ለስርአቱ ታማኝ አገልጋይ
ለሆኑ፣ በየቀበሌው ፈሰው ለአገዛዙ በታማኝነት ቆመው የሕዝቡን የየእለት ሕይወቱን ጭምር ለገዢው
ስርዓት እንዲገብር የሚያደርጉ፣ በተለያየ ምክንያት ከራሱም ከልጆቹም አፍ እየነጠቁ የሚወስዱ
ሁሉ፣ እንደ ሕዝብ ተደራጅተው የኢትዮጵያን ሕዝብ እንደ መሰረታዊ ጠላት ቆጥረው ለዘመቱበት
ሁሉ፡–
»» ተዋህዶ እምነታችንን ለማዳከም ከመናፍቃን፣ ከተረት አምላኪዎች፣ ከካቶሊኮች፣ ከጥንቆላና አምልኮ
ባእድ አምላኪዎች ጋር በመመሳጠር፣ ስልጣናቸውን በመመካት ለተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን መጥፋት
ለሚሠሩ ሁሉ፤
»» ኢትዮጵያዊነትን ክደው፣ ከአካልነታቸው ተገንጥለው፤ ተመልሰው በስርአቱ አጋፋሪነት የአገሪቱን
ተዋህዶ እምነት፣ ለማጥፋት ለሚሠሩ፣ በአገሪቱ ኢኮኖሚውን ተቆጣጥረው የሚዘርፉ፣ በዘረኛነት
ተቧድነው የሌላውን ኢትዮጵያዊ ወገናቸውን አግልለው፣ የዘር ቀጠና ፈጥረው ምድሪቱንም ለዘር
ቡድናቸው የሚሸነሽኑ፣ ለስርአቱ ከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ አስፈፃሚ የሆኑ፣ በዚህም የበለፀጉ ንብረት
ሀብት በውጭ ያከማቹ፣ ይኽንኑ የአገርና የተዋህዶ እምነት ጥፋት ከውጭ ሆነው የሚያበረታቱ፣
የሚደግፉ፣ በድርጊቱም የሚሳተፉ ሁሉ፤
»» አገሪቱንና የጸና ተዋህዶ እምነቷን ለማጥፋት፤ ከአገሪቱ አናት፣ እጅ፣ እግርና መላ አካሏን ወረው
እያጠፉ ላሉ ከበስተጀርባ ሆነው፤ በአገርም በውጪም በጨበጡት የዳቢሎስ ስልጣን ተመክተው
አመራርና፤ የሁሉን አቀፍ እገዛ ለሚያደርጉ ሁሉ
»» በማዘዙ በመወሰኑ ላሉት ከዋናው መሪ ጀምሮ እስከ ስር ድረስ፤ ከዚህ የሚከተለው ቅጣት በልዑል
ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል ተፈጻሚ ይሆን ዘንድ ታዞአል።
ሀ/ ሞት እረፍት ነው። ለአገሪቱ 20 ዓመታትን ሙሉ ለሞቷ ስትደክሙ ኖራችኋል። ስለሆነም ሞት
አይሰጣችሁም። ሞትን ትለምናላችሁ አይሰጣችሁም፤ ትፈልጉታላችሁ አታገኙትም፤ ይቀርባችኋል፤ ነገር
ግን ካልታዘዘ አይወስዳችሁም፤ ይህንንም ሁሉ የሚያስመኛችሁ በርባሪ እሳት ታዞባችኋል። እንቅልፍም
በዐይናችሁ አይዞርም። መኝታችሁ እሳት ሆኖ ይበላችኋል። እራሳችሁን ለማጥፋት ትሻላችሁ አይቻልም። ማረፍ

32
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ትፈልጋላችሁ አይታሰብም። ለመደበቅ፣ ለመሸሽ ትደክማላችሁ በፍፁም አይቻልም። የትኛውም ያደራጃችሁት


ሀብት ንብረት፣ ኃይል በሙሉ ይጠፋል፤ ዘራችሁ ከናንተ የመነጨ ነውና አይቀጥልም። ያለውም እጣው
በናንተው ሥራ ይወሰናል። ከዚህ በፊት ያልታዩ ሰምታችሁትም የማታውቁ የተቀላቀለ ገጽታና አካል ያላቸው
አውሬዎች ምልክት አልባውን ለመቆረጣጠም በመላው ዓለም በኛም አገር ይፈሳሉ። በምንም አይነት ኃይል
አይጠፉም። ሌሊትም ቀንም ይሰማራሉ። ምንም ምሽግ ምንም አይነት ቤት፤ አጥር አያግዳቸውም። በወላዲተ
አምላክ፣ በከበሩት ቅዱሳን መላእክት፣ በቤታቸው ላይ ምልክት (መሃተም) ያረፈባቸውን አይደፍሩም። ቤቱም
ድንግል ባሰማራቻቸው ቅዱሳን የብርሃን መላእክት ይጠበቃሉና። ገዳማት፣ አድባራትም እንዲሁም በልዑል
ሰራዊት በቅዱሳን መላእክት ይጠበቃሉ። ማንም ወደ ተጠበቁት ቤቶች መግባት አይችሉም። ካልተፈቀደለት
በስተቀር፤ በኃይል የሚሞክሩ ይመታሉ። በገዳማትም ለመግባት ፍፁም አይቻልም በውስጣቸው ያሉ ምልክት
አልባዎችም ይጠረጋሉ፤ በገዳማት የቀራችሁት የእግዚአብሔር ሕዝቦች ስርአቱ ሳይጎድል በቀራችሁት ቁጥር
አገልግሎታችሁን መቀጠል አለባችሁ።
ለ/ መባርቅት በ49 እጥፍ ጉልበት ይመጡባችኋል፤ የትኛውም ምሽግ ውስጥ ተወተፉ ያጠፉአችኋል።
ከመሃላችሁ በመባርቅት ሞትን ያገኘውን እድለኛ ነው ብላችሁ ትቀኑበታላችሁ። በአመጽ አድጋችሁ በአመጽ
ላረጃችሁ ለናንተ ሲኦልንና ገሃነምን በሕይወት ቆማችሁ ትለማመዱታላችሁ። ወደ ውጭ እሸሻለሁ የለም
እዚያም ይኸው ትእዛዝ በብዙ እጥፍ ኃይል የጸና ነው። መሸሸጊያ የሚባል በምድር ላይ የለም ሁሉም የልዑል
ገንዘቡ የእጁም ሥራና ታዛዦችም ናቸውና። ሽባና ምናምንቴ የሚያደርጉ ሰምታችሁ የማታውቋቸው መድሃኒት
አልባ በሽታዎች ይይዟችኋል። ምንጫቸውም በምንም ዘዴ አይታወቅም። መዳኛም የላቸውም። በስልጣናችሁ
ተመክታችሁ፤ የድሃውን ሕዝብ ሥጋውን በልታችሁ፤ አጥንቱን በመቆርጠም ላይ ያላችሁ፤ ይህም አንሷችሁ
በባእድ ሀገር ሀብት ያከማቻችሁ ሁሉ፤ የናንተም ተባባሪ ሸሻጊ የሆኑ መንግሥትና ድርጅቶች ሁሉ ከላይ
የተጠቀሰው ቅጣት ተፈጻሚ ይሆንባችኋል።
ሐ/ ለዓለም ሕዝብ የታዘዘው (በመልእክቶች 1፤ 2፤ 3) የተጠቀሰው ቅጣት በአገራችንም ለማንም ሰው
በልኩ ልብስ እንደሚያሰፉለት ለኢትዮጵያ አገራችንም በጥቅሉ በአቅሟ ቅጣቱ ይፈሱበታል።
መ/ በመልእክት 4 የታዘዙ ትእዛዞች እንዳሉ ሆነው ያገራችን መሪ የጊዜ ገደብ ተደርጎ ስልጣናቸውን
እንዲያስረክቡ ተነግሮአቸው ነበር። በዚህ እድል ሳይጠቀሙ ቀርተዋል። እግዚአብሔር አምላካችን ማንም
ሰው በሃጢያቱ እንዲጠፋ ፈልጎ አያውቅም ሰው በራሱ ምርጫ ከዲያብሎስ ጋር ሁኖ ይጠፋል እንጂ። ይህን
ሁሉ ወንጀል በአገራችን፣ በእምነታችን፣ በሕይወታችን፣ በንብረታችን ላይ የፈጸመ ያስፈጸሙ መሪና ምንዝሩ
የንስሓና የመጸጸቻ እድል ተሰጠው ናቀ፤ ተሳለቀ፤ በጥፋቱም በማንአለብኝነት እነሆ ገፋበት። መልእክት 4
የጊዜውን ማለቅ አብስሮአል ይህ ከተገለጸም አንድ አመት ከስድስት ወር ሆነው። ጊዜው የረዘመ ሊመስለን
ይችላል። ይሠሩ ዘንድ የሚገባቸው ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። በራስህ ሕይወት ዙሪያ ያለውን እሳት
እይ፣ ኑሮህን መርምረው፣ መንገዱ እየተጠረገ ነው፣ አንዳች ሳየፈጸም የሚቀር የለም። ልዑል በወሰናት ሰዓት
ትከናወናለች። መሪዎቻችንም ትእቢታቸው የወለደላቸውን ብርቱ ጥቃት በዚህ መልእክት መታዘዙን ከላይ
ባሉት ርእሶች መስፈራቸውን ተረጋግጦአልና ይወቁት።
መልእክት 4ን በትክክል ሊረዱት ያልቻሉ ቅን ወገኖች እንዳሉ ሁሉ አንዳንዶች የመልእክቱን አንድ አንድ
አካል ባልተባለ ባእድ ቃል የመልእክቱን አቅጣጫ ሊያስቱ ሞክረዋል። ለነዚህ የሚታዘዘው ቅጣት ታዞላቸዋል
በየግላቸው ያገኙታል። መልእክት 4 የሚያሳየን ገጽታ ሙሴ እስራኤላውያንን ነጻ የማውጣት ሥራውን ሲያከናውን
በፈርኦንና በመሰሎቹ የታየን ሁኔታ የሚመሳሰል መልክ ይታይበታል። ፈርኦን የእስራኤልን ሕዝብ እንዲለቅ
ሙሴ ሲጠይቀው መልሱ የትእቢት፣ የንቀት ነበር። ከ7 ያላነሱ ቅጣቶች ሲፈሱ በትእቢት ፀንቶ ነበር። ሁዋላ ላይ
የታመነበትን ሰራዊት ሲያጣ ግን የእግዚአብሔርን ምንነት አወቀ። የኛ መንግሥት ተነገረው ናቀ፤ በሁሉም ዘርፍ
በኢኮኖሚውም፣ ፖለቲካውም፣ ማህበራዊ ሕይወቱም ተመታ ደቀቀ አልሰማም። ስለሆነም እነሆ ዛሬ ብርቱ
33
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ቅጣት በራሱም በሁሉም መገልገያው ላይ ታዟል። የዛሬው ከፈርኦን ዘመን በላይ እንደ ተጨማሪ የሚወሰደው
ቅጣት አለ። ያኔ ፈርኦን የእግዚአብሔርን ምንነት አይቶ አምኖአል። በራሱ ላይ በደረሰው ጥፋት ከቀድሞውም
እምነት ባይኖረውም የፈጣሪውን ያህል አምኖ ተቀበለ። የዛሬዎቹ የኛው ሸክሞች ግን የፈርኦንን ታሪክ ያውቃሉ።
በራሳቸውም በደረሰባቸውም ያለውን ያያሉ። ገናም እሳቱን ተግተው ይደመደማሉ።
በፈረኦን ሶካር! ዛሬ ለእነሱ ስሙን በቀየረው በትላንቱም ያው፣ በዛሬውም ያው የሆነውን ዲያብሎስ
ወይም የዘመኑን ሶካር ያምናሉ ይታመናሉ። ሶካር ድረስልን፣ ፍጭልን፣ ቁላልን እያሉት ነው። በዚህ ልንደነቅ
አይገባንም። ሙሴ የእግዚአብሔርን ጸጋና ጉልበት ለብሶ ከፈርኦን ጋር የነበረውን ትግል በድል አጠናቋል።
የፈጀውን ጊዜ ይፍጅ ታሪኩ ከፈርኦን ጋር የተካሄደውን ትግል ምን ያህል ጊዜ እንደከደነ ባይነግረንም፤ ድል
ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ ትሆናለች። ስለዚህም በጥርጥር የተሞላህ ወገኔ ጠላት የዘራብህን አረም ከልብህ
ንቀልና አውጣ በፈጠረህ አምላክ በገባልህም የማይናወጥ ቃል ኪዳን ታመን። እግዚአብሔርን ማስደሰት
የሚቻለው በእምነት ብቻ ነው። እምነትም ያላየነውን ነገር ግን እንደእግዚአብሔር ፈቃድና ቃል ይሆናል ብለን፤
በተስፋው ጸንተን የምንቀበለው ማለት ነው።
ስለኢትዮጵያ የቅጣት ፍሰትና ስለ ትእዛዞቹ ማጠቃለያ፡–
በዚህ የሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚወርዱት ቅጣቶች ሁሉ፤ የቀደሙት መልእክቶች ሁሉ (1፤ 2፤ 3)
እንዲሁም በመልእክት 4 ውስጥ የተጠቀሱት ፍርድና አፈጻጸማቸው እንደሚያረጋግጡት፤ የአዳም ዘር በሙሉ
ከጥቅቶቹ በስተቀር፤ ንቆ ዛሬም እያፌዘ ስላለና በልዑል ትእግስትም በማላገጡ፤ ይህ የሁለተኛው የእሳት
ወንፊት በልዑል ፈቃድ በኔ በባሪያው በኩል ትእዛዙ እነሆ ተገልጾአል።
በአሁኑ እሳት ውስጥ ማንም ምልክት አልባ አያልፍበትም። ሁሉንም ወንጀላቸውን፣ ሥራቸውን በአደባባይ
በማናቸውም የዜና ማሰራጫ፤ በጋዜጣ፤ በመጽሔት፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን ሳያቋርጡ መናዘዝን፣ ሙሉውን
መልእክት ይኽንንም 5ኛውን መልእክት ጨምሮ በሁሉም መገናኛ ብዙሃን፤ ቀንም ማታም አንዲት ቃል
ሳትጎድል መግለፅ አለባቸው። ከሚፈስባቸውም እሳት የአንዲት ሰዓት እረፍት ለማግኘት፣ የነሱ ስቃይ ከታዘዘው
የእሳት ወንፊት ወጥቶ ወደ መደበኛ የቅጣት ዓለም መሸጋገር የሚቻለው፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ጸንቶ፤
ባሮቹ ልዑል ባዘጋጀላቸው ዙፋን ላይ አርፈው የፍርድ ውሳኔአቸውን ሲያፀኑ ብቻ ነው። ከዚህ ሂደት ቀድሞ
ማንኛውም የዓለም ሀገራት መሪና ምንዝሮቹ፤ እጃቸውን በኢትዮጵያ ለሚጸናው በአንዲት ተዋህዶ እምነት ለጸና
መንግሥት መስጠትና በፍርድ መካተት ይጠበቅባቸዋል። ተጨማሪና ተከታታይ ትእዛዞችን መፈጸምም ግድ
ይላቸዋል። ከዚህ ውጪ ማንኛውም አገር፣ ሕዝብ፣ ግለሰብ፣ ድርጅት፣ ቡድን፣ መፍትሄ አገኛለሁ ብሎ ማሰብ
የለበትም። ቢታሰብም ሰሚ የለውም፤ ለአሳቢውም ከንቱ የሆነ፣ የራሱንም፣ የወገኑንም፣ የሕዝቡንም መከራና
የእሳት ፍም መጋምና ማጋል ብቻ ይሆናል።
በቅጣቱ የወደቁ ሁሉ ዛሬም ስለዋናው ጉዳይ ስለገጠማቸው ፍርድ አምነውበት ቢድኑም ባይድኑም
በፈጣሪያችን በሰራዊት ሁሉ ጌታ ፊት ወድቀው ፍርዱን በፀጋ ቢቀበሉ በተሻላቸው ነበር። ምንም ይሁን ምን
በልዑል እጅ መውደቅ የተሻለ ነውና እኔ እንደራሴ አምላኬና እናቴ ወዳጆች የከበሩት መላእክት እንዳስተማሩኝ፣
እንደመከሩኝ እንደአሁኑ ከአቅም በላይ /በትእግስት ከሚታለፈው/ ፍፁም ባለፈ ባይሆን ኖሮ እሰካሁንም ልዑል
እንደሰጠኝ ትእግስት ባያቆየኝ ኖሮ አይቻልም ነበር። የሆነ ሆኖ ዛሬ የልዑልም፣ የድንግልም፣ የከበሩት ቅዱሳን
መላእክትም ትእግስት ተጠናቆ ካበቃ ቆየ።
የአዳም ዘር አድምጥ፣ ስማ ጆሮህን ጭው የሚያደርግ፣ በድንጋጤም ልብህን የሚሰነጥቅ እንኳን ወደ ሁለተኛው
ወፍጮ መግባት ገና ጅምሩን ስታየው እምትደርስበት ይጠፋሃል። የትኛውም ዓለም አይሸሽግህም። ዓለም ሁሉ
የጨለማ (የዲያብሎስ) ልጅ አሽቀንጥራ ለሚበላውና ለሚቆረጥመው አውሬ (እሳተ ጎሞራ እንደሚተፋው ዓይነት

34
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የቀለጠ የእሳት ፈሳሽ) ውስጥ ትጥልሃለች። በቁምህ ገሃነምን ታየዋለህ። ክፉ ሥራህ ያመጣው ፍርድ ነውና
መቀበል ብቻ ነው።
መ/ ስለ ኢትዮጵያውያንና ስለ ባህረነጋሽ (ኤርትራ) አሁኑ ገዥዎቻችን የተቀናጀ ኢትጵያውያንና ተዋህዶ
እምነቷን ማጥፋት ተልእኮ
በኢትዮጵያ ሃገራችን ላይ የሚካሄደው፤ ሁሉን አቀፍ ሕዝብና ሃገራችንን የማጥፋት ሥራ፤ እየተከናወነ
ያለው እጅግ በተቀናበረ፣ በግንባር ቀደም የኢትዮጵያና የባህረነጋሽ መሪዎች የሚመሩት የጥፋት ሥራ ነው።
ኢትዮጵያ ዛሬ ለደረሰችበት ድቀት፣ ድህነት፣ የአገር መሸራረፍ፣ የሕዝብ እልቂት፣ የተዋህዶ እምነቷን እንደ
ምስጥ መቦርቦርና ጭርሱን ማጥፋት፤ ኢኮኖሚዋን በሙሉ ተቆጣጥሮ መዝረፍ ማዘረፍ፤ ሕዝቧን እርስ በእርስ
በማፋጀት፣ ማንኛውም የታሪክ መሰረቷን ማጥፋት፤ ታሪኳን በማያውቁ መርገጥ፣ መግዛት፤ የብሄር ጥላቻን፣
ዘረኛነትን የታጠቁ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ አንዳችም የሀገር መከላከል ውለታ የሌላቸው ህዳጣን ሰዎችን የጥላቻ
መንፈስ አስታጥቆ፣ መርገጥ፣ መግዛት፣ መዝረፍ፣ የሀገሪቱን ቁልፍ፣ ኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የእምነት፣
የማህበራዊ ሕይወት፣ማከናወኛ ስልጣኖችን በሙሉ፤ በነዚህ ሰዎች ማስያዝ፤ ታሪኩን፣ የእምነቱን ባለቤት
በመላ ሕይወቱ ላይ በመዝመት የማፍረስ፣ የማሳደድ፣የመግደል፣ የማሰር፣ ያልተቋረጠ ጥፋት ማካሄድ፤ እንደ
ሥራ በእቅድ ማካሄድ ዋና ሥራቸው ነው። የባህረነጋሽ ሰዎች እንደ ቡድን ሳይሆን እንደ ሕዝብ ተዋቅረው፤
በዚች ሀገር ላይ ያልተቋረጠ ዘመቻ አካሂደዋል። እነዚህ ሰዎች ነጻ ነን ብለው፤ ከአገሪቱ 99 በመቶ ድምጽ
ሰጥተው፤ የሄዱ ሲሆን፤ በዚህ ድርጊታቸው ያልከበዳቸው እንደገና ለዲያብሎስ የተመቸ አካሄድ ይዘዋልና፤
የዚች ሀገር የጥፋቷ መሃንዲሶች ደግሞ እነዚህን ሰዎች በመሰረትነትና የኃይሉም የጸጥታውም የኢኮኖሚውም
ተረካቢ አድርገው በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ከጫኗቸው 20 ዓመት አልፏቸዋል። በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ
ሕዝብ አናት ላይ ጠመንጃና ታንካቸውን ተመክተው ከላይ ሁሉንም የሀገሪቱን ሕይወት በማነቅ፤ በነዚሁ እንደ
ሕዝብ በተደራጁ ኤርትራውያን እጅ ገብቶ፤ ኢትዮጵያም ሆነች ዓለም በታሪካቸው ያላዩት አመጽ፤ ዘረፋ፣
በመንግሥትነት፣ በሕግ ሽፋን፣ በግብር፣ በልማት፣ ስም ኢትዮጵያዊ ወገኔ ሥጋው ተበልቶ አጥንቱ በመቆርጠም
ላይ ይገኛል። የዚህ የጥፋት ቀዳሚ መሃንዲስ ጠቅላይ ሚንስትራችን ሲሆኑ ከመጋረጃ በስተጀርባ ደግሞ
አመራሩንም ዘረፋውንም የሚመሩት የባህረነጋሹ (ኤርትራ) መሪና አገልጋዮቻቸው ናቸው።
እኒህ ደፋሮችና ጨካኞች በዚህ በአንድ ተዋህዶ እምነቱ በጸና ሕዝብ ላይ ዘምተው ለዲያብሎስ የየቀን ግዳይ
የሚጥሉ ናቸው። ማናችንም በዓይናችን እንደምናየው እንደምንሰማው፤ የሀገሪቱ ሀብት፤ ቅርስ፤ አለኝ የምትለው
ሁሉ ተዘርፎ በውጭ ተከማችቷል። በየገዥው ቡድን አባላት የመሸሸጊያ ጎሬ በብዙ ስፍራ ተወትፎአል።
ይህ የሀገር ጥፋቶች ከደቡብ፣ ከኦሮሚያ፣ ከምእራቡም ከምሥራቁም ተሰበሰቡ ስለኢትዮጵያ ታሪክ አንዳች
የማያውቁ ሲጠየቁም ስለብሄራቸው መጨቆንና ነፃ መውጣት ገድል የሚነግሩን ምርኩዛቸው ሲሆኑ፤ ይህ
ሽፋናቸው እንጂ እንዲያጠፉ አገሬ ኢትዮጵያ የሚለውን ሰው፤ በሥራውም በንብረቱም ገብተው እንዲወስኑ
አድርገዋል። የሁለቱ ገዢዎቻችን ስትራተጂ ተግባሪዎችም ናቸው። ይህ ሁሉ ጥፋት በነባቢሎን የመናፍቁ ጌታ፣
በነተረት አምላኪዎች፤ የዲያብሎስ ነፍሰ ገዳዮችን የአረብ አገራት፤ በድራጎንና ጣኦት አምላኪዎች ሁሉን አቀፍ
ድጋፍ ሰጪነት የሚከናወን ነው።
ለዚህ ሁሉ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ እንደ ሕዝብ ዘምቶ ዘርንና ምልክትን፣ አሻራንና ታሪክን፣
ኢኮኖሚንና ቀጣይ ዘርን የመግደል ሥራ፤ በትእግስት ብዙ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ወደፈጣሪያቸው በማመልከት
በእንባቸውና በማያቋርጥ ጩኸታቸው ኃያሉን ጌታ ከመንበሩ በመቀስቀስ የልዑልን ውሳኔ አስገኝተዋል። ማንም
አይታደገውም እንፈጨዋለን እንቆላዋለን ብላችሁ ጌታዋን ተማምና ላቷን እውጭ እንዳሳደረችው በግ በዚህ ምስኪን
ሕዝብ ላይ ተንሰራፍታችሁ፤ ጥፍርና እግራችሁን ዘርግታችሁ፤ በማን አለብኝነት ተቀምጣችኋል። በቃችሁ
የእምነት ጀግኖች ተፈጥረዋል። ዓለም ሰምታም የማታውቀውን እሳት ተጭኖ መጥቶላችኋል። የደከማችሁለት
ስልጣን፤ የሰበሰባችሁት ሀብት የደሃ ደምና አጥንት የተመካችሁበት ዘር አስተማርነው ከበረልን በዓለም በትነን
35
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መሰረት አስይዘነዋል፤ የምትሉት ዘራችሁ፤ ወገናችሁ፤ መሸሸጊያ ያላችሁት በሙሉ፤ ለእሳት ተጠብቆ፤ ከዚህ
በታች ያለው የቅጣት ዝርዝር መግለጫ፤ በናንተና በሁለቱም ሀገር ገዥና አለቃ ምንዝሮቻችሁ እንደ ሕዝብ
ተቧድኖ፤ የዘመተው፣ ዘራችሁና ተባባሪያችሁ ሁሉ ላይ፤ ተፈጻሚ ይሆን ዘንድ የልዑል ፈቀድና ትእዛዝ
አርፎበታል። ተፈፃሚም ይሆን ዘንድ የልዑል ትእዛዝና ፈቃድ በኔ በባሪያው በኩል ከዚህ በታች ተዘርዝሯል።

ትእዛዞች
የኢትዮጵያ ገዥዎችና የባህረነጋሽ (ኤርትራ) ገዥዎች ከነሱ ስር ሆነው የኢትዮጵያን ህልውና፣ ታሪክ
የተዋህዶ እምነት፤ ኢኮኖሚ አጠቃላይ ሕይወቷንና ገጽታዋን በሙሉ የማጥፋት ከውጭ በዚሁ ዘርፍ ከተሰለፉ
ጋር የመቀናጀት ሥራ መሥራትን እንደ እለት ከእለት ሥራቸው የደረጉ ሁሉ ወንጀላቸው አንቀጽ ያልተበጀለት፤
ሰውም በህሊናው ይፈጥረዋል ያልተባለ፤ የዓለም ምርጥ የዘር፣ የሀገር፤ የተዋህዶ እምነት መግደል ሥራ ስለሠሩና
እየሠሩም ስላሉ የመጀመሪያውንም ሆነ ሁለት ሦስት መልእክቶች ያቀፈውን (ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን) በሚል
የተገለጸውን ፍርድና አፈጻጸም እያወቁ ከመጸጸት ይልቅ በጥፋታቸው እንደ ዓላማቸው ገፍተውበታል።
የእግዚአብሔር የተመረጠን የክብር ሀገር ለማጥፋት መድከም እራሱን የምድርና የሰማዩን ባለቤት አጠፋለሁ
ብሎ መዝመት እንደ ሆነ ማንም የሚረዳዉ ነው። ስለሆነም የእግዚአብሔር ቃል እንደሚነግረን (ከእግዚአብሔር
ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉ) ይላል። እነዚህ ጉዶች ግን ከመጣላት በላይም፤ ዲያብሎስ እንኳን መንበሩን ሊወርስ
ነው የተመኘው፤ እነዚህ ደግሞ ከመምህራቸው ከዲያብሎስ በላይ ልዑልን ፈቃዱን ትእዛዙን ሁሉ እናጠፋለን
ብለው የተነሱ ናቸው። ስለሆነም ለነዚህ ሞት ቶሎ አይሰጥም። ሞት እጅግ በጥቂቱ ለተሳተፉ የሚሰጥ
ብቻ ነው። በጥፋቱ ጠልቀው ለገቡት ግን ሞት እንደሚመኙት እንደሚሮጡለት ሃብት፣ ስልጣን፣ በቶሎ
አያገኙትም። ስለዚህ ሌትም ቀንም ቢሹት አያገኙትም። አይቻልም። በሕይወት ሆነው የሰበሰቡትን ይሆነኛል
ያሉትን ሁለመናቸውን ያጡታል። ፍፁም እድል የማይሰጥ በርባሪ፣ ቆርጣሚ እሳት በባህሪያቸው ይሰለጥናል
ምንም ማድረግ የማይችሉ ሽባዎች ይሆናሉ። በመላ አካላቸው ላይ ሁሉም በሽታዎች ይከድኑአቸዋል። እረፍትና
እንቅልፍ ምድሪቱን እስከሚለቁ አያገኙአቸውም። ዓለምን በግርምት የሚያስደምም እሳት ቆርጥሞ ይጨርሳቸዋል።
በዓለም ላይ በተለይ በነአሜሪካ፣ በነአውሮፓ፣ በነኤሽያ ላይ ተፈጻሚ ይሆኑ ዘንድ የታዘዙት ቅጣቶች በዚህ
ርእስ ውስጥ ለተጠቀሰው ወንጀል ተጠያቂ በሆኑ ላይ ሁሉ ተፈጻሚ ይሆናሉ። የነሱ የጥፋት ተባባሪ የሆኑትም
እንደ ተሳትፎአቸው የሚመጥነውን ቅጣት ይቀበላሉ። ኤርትራም ወደፊት የሚታወቅ ወይም የሚታወስ ምንም
ቅሬት አይኖራትም። ሰው ያለ ማረጋገጫ በነበር ብቻ የሚያነሳት እንደ አፈ ታሪክ የሚያስቆጥር ወሬ ብቻ ሆና
ትቀራለች።
ዓለም በቅጣቱ ክብደት የሚደነግጥበት ይሆናል። የትኛውም የነሱ ዘር፤ በየትኛውም የዓለም ክፍል ይሸጎጡ
እንደሠሩት ወንጀል ክብደት ቅጣቱ ተፈጻሚ ይሆናል። በተለይ ይህቺን የተመረጠች ሀገር ሳትበድላቸው
በድለዋታልና። ሀገሪቱን ለባህረነጋሽ ሰዎች በዘመኑ ሁሉ በአናቷ ላይ አስቀምጣ ስቡን አብልታ ማርና ወተቱን
አጠጥታ የቅምጥል ልጅ አድርጋ አኑራቸዋለች። ሌሎች የሀገሪቱ ዜጎች በልመና፣ በማጣት፣ በእለት ተእለት
ኑሮ ተቀይዶ ሲሰቃይ፣ እነዚህ ቅምጥሎች ግን በሁሉም የሀገሪቱ ሀብት ተጠቃሚ ሆነው ኖረዋል። እንዲህም
ሆኖላቸው ነው ዛሬ ይህችን አገር በመዝረፍና በማፍረስ ላይ ያሉት፤ ስለዚህ በዚህ መልእክት ያልተካተተ፤
ለሰውም እንግዳ የሆነ፤ ዘግናኝ ብርቱ ቅጣት ነው እድላቸው። ሌላ እድል የላቸውም። በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ
በኔ በባሪያው በኩል እነሆ ተገልጾአል። ታዞላቸዋል። እስትንፋስ የሚገኘው ምንአልባትም ቢሆን እንደበላየሰብ
ራስን በፈጣሪ እጅ በመተው ብቻ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ከሚፈላው እሳት በልዑል ምሕረት አግኝተው
በመዳናቸው ለሰው ግርምት የሚያጭሩ በጣት የሚቆጠሩ ይታዩ ይሆናል።
የመልእክቱ አስተዋይ አንባቢዎች፤ ከላይ ለተጠቀሰው ርእስ፤ መጽሐፈ አስቴርን በሙሉ እንድታነቡና
እንድትረዱት እያሳሰብኩ፤ የዛሬ መርዶኪዮሶች፤ እንስት አንበሳ አስቴሮች አይዞአችሁ። ስለሀማና ጭፍሮቹ
36
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የግፍ ሥራ ወሰን የለሽ በደል የሚመስሉአቸው እንዲያውም የሚበልጡአቸው የሃገራችን ገዢዎችና እንደ ቡድንና
እንደ ሕዝብ ተደራጅተው፣ የእግዚአብሔርን ሕዝብ፣ በተዋህዶነት የጸናውን ወገን፣ ያጠፉ ዘንድ የዘመቱ
የባህረ ነጋሽ ሕዝቦች፣ የሀማና ወገኖቹ እጣ ፈንታ ተሰጥቶአቸዋል። የነሀማ እጣ ፈንታ የኢትዮጵያ ገዢዎች
ከነምንዝሮቻቸው፤ የባህረ ነጋሽ ሕዝቦች በነገዢዎቻቸው በብዙ እጥፍ ሆኖ የሚቀበሉት ነው።

8ሠ/ እውነተኞቹ ኢትዮጵያውያን የተዋህዶ ልጆችና መጪው እጣቸው


ቀንና ጊዜ ባለፈ ቁጥር ሥጋ ለባሽ በመከራ ክብደት ይደክማል። ኃያል ጌታ ግን ለበረከቱ፣ ለምሕረቱ
ያተማቸውን ልጆቹን ያጸናል። የሰጠውን (የገባውን) ቃል ኪዳን ያከብራል። ሰው በድካም ዝሎ የተገባለትን
ተስፋ ሁሉ ይተዋል። በብርቱ ድካም ዝሎ ይወድቃል። ልዑል ግን ያኔ ድካሙን ሁሉ ከድኖ አድሶ በብርታት
ሞልቶ በደስታ እንዲቦርቅ ያደርገዋል። የታመንበት የሰራዊት ጌታ ሁሌም እስከዘለዓለሙ የታመነ ነው።
የእግዚአብሔር ፍቅሩ፣ መታደጉ፣ በረከቱ ልቡን የሞላው ዳዊት እንዲህ አለ።

አይኖቼን ወደ ተራራ አነሳሁ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ ረዳቴ ሰማይንና ምድርን ከሠራ
ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም የሚጠበቅህ አይተኛም
እነሆ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም እግዚአብሔር ይጠብቅሃል
እግዚአብሔርም በቀኝ እጅህ በኩል ይጋርድሃል ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም
በሌሊት እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል ነፍስህንም ይጠብቃታል ከዛሬ ጀምሮ
እሰከ ዘለዓለም እግዚአብሔር መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።
የዳዊት መዝሙር 120 /121/
እግዚአብሔር ወገኖቹን እንደ ዐይን ብሌን ይጠብቃቸዋል። በማንኛውም የዲያብሎስ ዘዴ ይወድቁና ይጠፉ
ዘንድ በፍፁም አይፈቅድም። ወገኔ የልዑል ልጅ፤ የድንግል ልጅ፣ የቅዱሳን የከበሩት መላእክት ልጆች ብዙ
ብተሰቃዩም ደረሳችሁ የተገባችሁን ነጭ ልብስ ለበሳችሁ። አገራችን ኢትዮጵያ ልዑል ዙፋኑን የሚዘረጋባት፣
ልጆቹን እንቁዎቹን በዙፋኑ የሚያኖርባት፣ ድንግል ልጆችዋን በበረከቷ፣ በፍቅሯ የምታረሰርሳት፣ ኢትዮጵያ
ቅዱሳን የከበሩት መላእክት ዙሪያዋን በእሳት አጥረው የሚጠብቁአት፣ የሚባርኳት ኢትዮጵያ፣ የፀናችው
አንዲቷ የተዋህዶ እምነት እንደፀሐይ የምታበራባት ኢትዮጵያ ለልዑል የሰራዊት ጌታ ሌትም ቀንም ለክብሩ
ለስሙ ምስጋና እንደጅረት የሚፈስባት ድንግልና ቅዱሳን የከበሩት መላእክት፣ ቅዱሳን ሰማዕታት፣ ነቢያት፣
ሐዋርያት፣ ስማቸው የሚከብርባት፣ የሚመሰገኑባት ኢትዮጵያ በክብሯ ጥግ ማንም የማይደርስባት የእግዚአብሔር
የስስት ልጁ ናት።
ከዚህ ድንቅ አገር የተፈጠራችሁ፣ ለአባታችሁ ለልዑል፣ ለእናታችሁ ለድንግል፣ ለከበሩት ቅዱሳን
መላእክት፣ ለአንዲት ተዋህዶ እምነታችሁ፣ ለእንቁዋ ለአገራችሁ ኢትዮጵያ ዋጋ ከፍላችሁ በጭንቅ እዚህ
ለደረሳችሁ ወገኖቼ እንኳን ደስ ያላችሁ። በእምነት ድሉን ተቀዳጅታችኋልና!
የእሳቱ ብርቱ ግለት ተጭኖ ደረሶአልና በሁሉም ነገር ቁጥብ አስተዋይ ታጋሽ ሁኑ። ከአህዛብ ጋር፣
ከመናፍቃን ጋር፣ ከካቶሊኮች ጋር፣ ከተረት አምላኪዎች ጋር፣ ከአምልኮ ባእድ ተከታዮች ጋርና በግልፅ
ዐይናችሁ በሚያየው ሰውን እየጎዱ ካሉ የስርአቱ አገልጋዮች ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ። ቅድመ
ጥንቃቄ ይኑራችሁ አደጋው በአካባቢያችሁ ሲከሰት እናንተም በፈርኦንና በአገልጋዮቹ ላይ ሞት ሲወርድ ሙሴ
በሩን ዘግቶ ሞትን ከነወገኖቹ በምስጋና እንዳሳለፈ ሁሉ በራችሁን ዝጉ በበራችሁም ላይ የድንግልን ማህተም
የቅዱሳን መላእክት ጥበቃና ፈጣሪያችሁን በማመስገን አሳልፉ። ሳታስቡት በውጪ የጥፋቱ ኃይል ሲመታና
ሲጠርግ ስታዩ አትደንግጡ ምልክት አላችሁና እናንተን አይነካም። በጥቅሉ ዓለም በመልእክቶቹ እየተሰፈረች፣
እየተበጠረች እናም ወደማይቀረው አዘቅት እየወረደች ትገኛለች። ዛሬ እንደምናየው ዓለም በተለይም ባቢሎንና

37
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መሰሎችዋ ኃያላን የመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ከመጀመሪያው መልእክት መውጣት ጀምሮ ሥራውን
እየሰራባቸው አናሳዎቹን አገሮችንም አብሮ እየፈጨ ይገኛል። ከእግር ጥፍር የተነሳው ውኃ ከፍታውን እየጨመረ
ዛሬ እወገብ ላይ ደርሶአል። ዛሬ ደግሞ ይህ መልእክት መውጣት ጀምሮ ጉልበቱን ያልታየ ኃይልና ፍጥነቱም
መቼም ያልተገመተ ሆኖ ይጨምራል። እስትንፋስን ለመዝጋት አፍንጫ ስርም ደርሶ ያጠናቅቃል። የግድ
ካልተጠረገ የማይሰማው ይህ የዲያብሎስ መንግሥትና ዓለም ተገድዶ የፊጢኝ ተወጥሮና አፍንጫው ተሰንጎ
በኔ በምስኪኑ በባሪያው በኩል ልዑል የፈረደው ሙሉ ቃል በመልእክቶቹ እንደተገለጸው ሁሉም ተፈጸሚ
ሁነው፤ በምድሪቱ በሙሉ አባታችን፣ አዳኛችን፣ ትምክህታችን፣ ሁለንተናችን የሆነው የልዑልና የሁሉ ፈጣሪ፤
ኃያል የሰራዊት ጌታ፤ ቅድስተ ቅዱሳን፤ ንጽህተ ንጹሃን እናታችን ድንግል፤ እጅግ የከበሩት አሥራ ሁለቱም
ሊቃነ መላእክት፤ በታላቅ ተጋድሎና ሰማዕትነት ያለፉት ሰማዕቱ ጊዮርጊስ፤ ሰማዕቷ አርሴማ፤ እናም እጅግ
የተከበሩት በሰማዕትነትም በቅድስናም ያሉት ነቢያት፣ ሐዋርያት ሁሉም የተዋህዶ ጀግኖች የሚከብሩባት ዓለም
ትጸናለች። እንደ ፀሐይም ታበራለች።

9/ አውሮፓና በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበት የመጀመሪያው እሳትና በሁለተኛው


የእሳት ወንፊት የሚገጥማት እጣ

አውሮፓ፡– በመጀመሪያውም በሁለተኛውም በሶስተኛውም የአፈጻጸም መልእክቶች ሁሉ በሁሉም


አቅጣጫ የተመዘነችበትን፤ በውስጧም ያቀፈቻቸው አገሮች በሙሉ፤ እጣ ፈንታቸውን የተመዘኑበትንም
ሁሉ እንዲያውቁት ተደርጓአል። ከዚህ ሁኔታ ጀምሮ እሰከዚች ወቅት ድረስ በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት
እየተበጠሩ ይገኛሉ። አንዲት ተዋህዶን የማጥፋት ሥራ የተጀመረና የተስፋፋባት፤ የጥፋት እምብርት አውሮፓ
ናት። እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ፖርቹጋል፣ ስፔይን፣ ቤልጂየም፣ ደች /ሆላንድ/ በዋናነት
ዲያብሎስ ቀድሞ የነገሰባቸው በአውሮፓ ታላላቅ ተብለው የሚጠሩ ናቸው። አውሮፓ ዛሬ ወደ ራሽያ ጎራ
ሄደው የነበሩትን ሰብስባ ከ28 በላይ አገሮችን የአውሮፓ ሕብረት በሚል ጥላ አሰባስባ የያዘች አሕጉር ናት።
ይህች ክፍለ አሕጉር በሙሉ መልእክቶች ተመዝና ጥፋትና ፍርዷ ተገልጾላታል። ሙሉ መልእክቱ በእንግሊዝኛ
ተዘጋጅቶ ባለው መንገድ ሁሉ መንግሥታቶቹና፤ ሚዲያዎቹ፤ ዪኒቨርስቲዎቿ የጥፋቷ ቁንጮና የእምነቷ መሪ
ካቶሊክ ከደረሳቸው ዋነኞቹ ናቸው። አልፎ አልፎ ግለሰቦችም ደርሷቸዋል። ለሕዝቡ እንዲገልጹ ቢነገራቸውም
ማናቸውም ትንፍሽ አላሉም።
ቢያንስ ጥፋቱ ከጀመረ በኋላ እንኳን ሕዝብ ከሚያምንበት መንገድ ላይ እንዳያርፍ እስከ አሁን አፍኖ ጥፋቱን
እንዲጎነጭ እያደረጉት ይገኛሉ። አውሮፓ የመናፍቃን አገር እንደመሆንዋ በዲያብሎስ አባቷ የተወደደች
የምንዝርና፣ የክህደት፣ የፍልስፍና፣ የግብረሰዶም፣ የጨካኞች፣ የዘረኞች፣ አገር ናት። መሆኑም የተሰጣትን
መልእክቶች የልዑል ፍርድን የያዙ መሆናቸውን እያወቀች ፍርዱን ወደ አፈጻጸም መሸጋገሩን ተረጋግጦ
ተነግሮአት በንቀትና በፌዝ አልፋዋለች። ባታምንበትና ዛሬም ባባትዋ በዲያብሎስ ምክር ሳይንሳዊ መፍትሄ
አገኝለታለሁ ብላ በመደናበር ላይ ትገኛለች።
የመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ምን እያከናወነ ይገኛል። ኢኮኖሚዋ በታላቅ ቀውስ ተመቶባታል፤ የኢኮኖሚ
እድገት መቀዝቀዝ፣ ግሽበት፣ የበጀት ጉድለት፣ የገንዘብ ቀውስ፣ ሥራ ፈትነት፣ የባንክና ኢንሹራንስ መውደቅ፣
መክሰርና ሌሎችም የኢኮኖሚ ህመሞች ወጥረው ይዘዋታል። የተፈጥሮ አደጋ፣ የሙቀት መጨመር፣ ጭጋግና
በረዶ መከመር፣ አውሎ ነፋስ፣ ጎርፍና የመሬት ርደት መተዋታል። ማሕበራዊ ቀውስ፣ ትራንስፓርት በአደጋ
የተሞላ ሆኖአል። ብዙ የመደጋገፊያ ተቋማት ወድቀዋል፣ የሕዝብ አመጽ በብርቱ ተስፋፍቷል፣ አዳዲስ
በሽታዎች ተከስተው ሕዝቡን አስጨንቀዋል። የኃይል አቅርቦት ፈተና ገጥሞታል። የእሳተ ጎሞራ ብናኝ
በኢኮኖሚውም በአየር ትራንስፖርትም ቀውስ አስከትሏል። ሌሎችም ባይጎሉም ብዙ አደጋዎችና ጥፋቶች
ተከስተዋል። ይህ ጅምር እርምጃ ወደሁለተኛው ምእራፍ ለመሸጋገር የዚህን አምስተኛ መልእክት እየተጠባበቀ
38
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ይገኛል። ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቃሉ። አውሮፓም ትእቢቷና የጥበብ ትምክህቷ ተሟጦ እሰከሚረግፍ
ድረስ ጠረጋው ይቀጥላል። የልዑልን ማንነት ፍርዱንና እኛም አገልጋይ ባሮች ምን እንደሆንን እየጠፋች
የሺዎች ዘመናትን የጥበብና የቁሳቁስ አድጌአለሁ ክምርዋን ስታጣው ታውቀዋለች። ልዑል ማን እንደሁነ ያኔ
ትረዳዋለች።
ሁለተኛው እሳት ወንፊት ከዚህ የሚከተለውን ያካተተና ሌሎችንም ጨምሮ ይመታል። ኢኮኖሚው አሁን
ከሚታየው ቀውሱ በ7 ጊዜ 7 49 ጊዜ እጥፍ አድጎ ፍፁም ይደረማመሳል። መንግሥታትም ባለ ሃብቱም
ባጠቃላይ በሕዝብ አናት ላይ የተቀመጠ ሁሉ በእጁ የያዘውን ሁሉ ያጣል። ሕዝቡም ከጭንቁ የተነሳ አይኑ
እያየው ቤቱ ንብረቱ ስለሚፈርስ፤ ሞትን አይፈራም። ስለሆነም በመንግሥትም ሆነ በሚታመንበት ኃይል ላይ
ዘምቶ መተላለቅ ይሰፍናል። ትራንስፖርት ይፈራርሳል፣ የጦር የጸጥታ የፖሊስ ኃይል የመሳሪያ ክምችትና
ማምረቻው በተለያየ መንገድ ይወድማሉ። የፍትህ ሥራ ይቆማል፣ ግሽበት፣ የበጀት ጉድለት፣ ማንም የማይፈታው
ጥፋት ያስከትላል። ማንምም አይፈታውም። መሸቀጥ፣ መላክ፣ ማምጣት ፍፁም ይወድቃል ይቆማል። ማምረቻ
ድርጅቶች ይከረቸማሉ። ማንም የማያንቀሳቅሳቸው ይሆናሉ። እንደ ጃፓን አይነቱ የኒውክሌር ጥፋት በ49
እጥፍ ሆኖ በሚሊዮኖች ላይ ፍፁም ውድመትንና የሚሊዮኖችን ሞት ያስከትላል። ርእደ መሬት እሰከአሁን
ሆኖ በማይታወቅ ማግኒቲዩድ ተደጋግሞ ይከሰታል። የተከሰተበት ስፍራ ላይ ለምልክት የሚታይ አንዳችም
የሰውም ሆነ የቁሳቁስ ወይም ፍርሥራሽ ብናኝ አይገኝበትም። የተለያየ ስም የሰጣችኋቸው አውሎ ንፋሶች፣
ሱናሚ፣ ቶርኔዶዎች፣ ሃርኬኖች፣ ካትሪናዎች ሌሎችም አሁን ከምናውቃቸው ጉልበታቸው በ49 እጥፍ ጉልበት
አድገው ይመጣሉ። ጎርፎች ታይተው በማይታወቅ መጠን ይመጣሉ። ይጠርጋሉ። እሳቶች ከተነሱ የማይጠፉ፤
አውሎ ነፋስ አዘል ሆነው ብዙ ከተሞችን ያወድማሉ። መብረቆች በ49 እጥፍ ጉልበት ይመጣሉ። በተለይ
ገዢዎችን፣ ባለ ሃብቶችን፣ የወታደር አለቆችን፣ የጸጥታ ኃላፊዎችን፣ የኒውክሊየር፣ የኬሚካል፣ የባዮሎጂካል
ክምችቶችን፣ መፈብረኪያዎችን፣ የመረጃ መረቦችን፣ ሳተላይቶች /የተለያዩ የጥፋት ተልእኮ ያላቸውን/ ቋሚ
ሳተላይቶችን ሁሉ ያወድማሉ። ግማሽ ሰው ግማሽ አውሬ ቅርጽ ያላቸው አውሬዎች ይፈሱባችኋል። ምንም
ምሽግ አይከለክላቸውም። በምንም ዘዴ አይጠፉም። የካቶሊክ፣ የመናፍቅ፣ የተረት አምላኪዎች፣ ቀጥተኛ
የዲያብሎስ አምላኪዎች በሙሉ በአውሬዎቹና በመባርቅት ትጠረጋላችሁ። ይህ ጥፋታችሁ እስትንፋስ እንኳን
የማይሰጥ በመሆኑ የታዘዛችሁትን ለመፈጸም ስትወስኑ፤ ቀድማችሁ ለህዝባችሁ ከአንድ ጀምሮ እሰከ ሦስትና
ይህንን አምስተኛውን መልእክት በሁሉም ቋንቋ በዓለም አቀፍም በብሄራዊ የቴሌቭዥን፣ የሬዲዮ፣ የሳተላይት
እንዲሁም በማናቸውም የመረጃ መረብ በጋዜጣ፣ በመጽሄት በየቀኑ ማስተላለፍ አለባቸው። ከዚህ በኋላ እጃችሁን
በኢትዮጵያ ለሚጸናው የልዑል እግዚአብሔር መንግሥት ዙፋን ላይ ለሚሆኑት ባሮቹ ስትሰጡ የታዘዛችሁትን
ሁሉ ስትፈጽሙ ብቻ መፍትሄ የማግኛ መንገድ ይከፈትላችኋል።
ሁሉም መቅሰፍቶች በአውሮፓ ላይ ይፈሳሉ፣ በዮሐንስ ራእይ 9፤ 1 – 11 እንዲሁም በዮሐንስ ራእይ 9፤
13 – 19 እኒህ በእናንተ ላይ ያርፋሉ።

10/ ሰሜን አሜሪካ በመልእክቶቹ አንጻር በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ውስጥና


በሁለተኛው የእሳት ወንፊት የሚገጥማት እጣ

ሰሜን አሜሪካ ሁላችንም እንደምናውቃት የዘመኑን የኃጢአት አዝመራ የምታመርትና እንደ እለት ከእለት
ምግብና ውኃ ለመላው ዓለም በግድም በውድም የምታከፋፍል የምታራግፍና በዲያብሎስ ዋና አስፈጻሚነቷ
የምትታወቅ አገር ናት። አሜሪካ /ባቢሎን/ ይህንን ክፍለ አሕጉር በዋናነት የያዘችው ሲሆን በስዋ ተዘዋዋሪ
አገዛዝ ስር የሆኑ ካናዳና ሜክሲኮ በሰሜንና በደቡብ ዘብ የቆሙላት አገር ነች። አሜሪካ ሁሉንም የዓለም ሀገራት
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በስሯ አድርጋለች ማለት ይቻላል። የዓለም ኃያላን ከሚባሉት ውስጥ ራሽያ፣
ቻይና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ በዋናነት አምስቱ ኃያላን ተብለው ይጠቀሳሉ። እነዚህ ኃያላን በራሳቸው በአሜሪካ
39
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የቀጥታም ይሁን የተዘዋዋሪ ተገዢ ናቸው። እንደ ምሳሌ ብናይ ራሽያ ትልቁ ገቢዋ የተፈጥሮ ጋዝ መሸጥ
ነው። ሁሉም የሚረከቧት አውሮፓውያን ናቸው። የአውሮፓውያን ኢኮኖሚ ድግሞ በአሜሪካ ስር ነው። በሙሉ
መልእክት እደታዘዘው ቅጣቱ ሲሰነዘር የዓለም ኢኮኖሚ፣ የባንክ፣ የሞርጌጅ ባንክ መውደቅ ሀ ብሎ የተነሳው
ማፌና ማዩ የሚባል የአሜሪካን ሞርጌጅ ባንክ ሁለት ትሪሊዮን ከሰርኩ ብሎ ዘጋ። ባንኮቹም፣ ኢንሹራንሶቹም
ሁሉም ከሠሩ፤ ወዲያው ተቀጣጥሎ አውሮፓ በክስረትና በቀውስ ተጥለቀለቀ። ከዚህ ነጻ ያልነበረችው ራሽያ
በመጀመሪያ 28 ቢሊዮን፣ ቀጥሎ መጠኑ ያልታወቀ የአሜሪካን ብር ድጎማ በማድረግ የደረሰባትን ቀውስ
ለመቋቋም ታግላለች። ቻይና 500 ቢሊዮን በላይ የአሜሪካን ብር ክስረቷን ለማካካስ ኢኮኖሚዋን ደጉማለች።
በአጠቃላይ ጌታቸው ባቢሎን ስትመታ የነሱም ጓዳ ዝብርቅርቁ ወጣ። አሜሪካ ከሞተች ሁሉም አብረው
መሞታቸው ነው። ለቅሶአቸውም አብሮ ነው።
የዮሐንስ ራእይ ገጽ 18 በሙሉ አስተውለው ያንብቡ! የባቢሎን እጣ ፈንታ ይህ ነውና። ኢትዮጵያ
የዓለሙ ብርሃን በሚለው የቀደሙት ሦስት መልእክቶች እንደተገለጸው ሁሉም የሰለጠንን፣ ያደግን፣ በማደግ
ላይ ያለን ነን የሚሉ ሀገሮች በሙሉ፤ ግብይታቸው ሁሉ ከዚችው እንደ አምላካቸው ከሚያዩአት ባቢሎን /
አሜሪካ/ ጋር ሲሆን እስዋ ከሌለች የሉም ማለት ይቻላል። የእኛው ሀገር ቡናዋን፣ ቆዳዋን፣ ሰሊጧን የሚገዛ
የበለፀገ አገር ቢጠፋ የዛሬው እቅድ እድገት ተወነጨፍኩ ያዙኝ ልቀቁኝ ከወዴት ይመጣል። ስለዚሁም ነው
ባቢሎን ያዘዘችው ዲሞክራሲ የሚሉት ከዲያብሎስ ዋናው መስሪያ ቤት ወይም ዋናው ማዘዣ ጣቢያ የተዘጋጀ
ኪኒን ሁሉም ሀገራት ለመውሰድ ግድ የሚሆንባቸው። ከእሷ እጅ ቢሸሹ ከሌላኛው የእጅ አዙር እጇ መሸሽ
አይቻልም ስለዚህም ነው በመጀመሪያ የእሳት ወንፊት ባቢሎን ስትመታ ሁሉም የዓለም ሕዝብ መውሸልሸል
የጀመረው። ዓለም በሙሉ ሊያውቅ የሚገባው ቢኖር አሁን ባለበት የጥፋት ጎዳና እንዲጓዝ ዘመናዊ መሃንዲስና
አስተዳዳሪው የሆነችው፤ እንደ አምላኩም የሚያያት ባቢሎን ናት። የምንዝርናው፣ የግብረሶዶሙ፣ የነጣቂው፣
የዘራፊው፣ የመናፍቁ፣ የካቶሊኩ፣ የተረት አምላኪው፣ የጣኦት አምላኪው በዓለም ሁሉ ያለ ገዢ ሁሉ እንደ
አምላኩና እንደ ቤተክርስቲያን የሚሳለማት ይህቺው ባቢሎን ናት።
የመጀመሪያውን እሳት አይታዋለች ዛሬም በዛው ውስጥ እቋቋማለሁ ብላ እየዳከረች ነው። ረግረግ ውስጥ
እንደጠለቀ ሰው፤ በዚህ ርእስ ስለሷ በመዘርዘር ጊዜ አናጠፋም የቀደሙት 3 መልእክቶች ፍርዷንም አፈጻጸሙን
ስለነገሩን እነሱን ማስተያየት በቂ ነው። ይህ መልእክት ትኩረት የሚያደርገው ስለሁለተኛው የእሳት ወንፊት
መመታቷን ለመግለጽ ነው። አሜሪካ /ባቢሎን/ መልእክቶች ሁሉ፤ ለመንግሥቷ፣ ለሚዲያዎቿ ደርሷል።
ስላልሰማች እንደፍርዱ የመጀመሪያውን የእሳት ወንፊት እየማሰነችበት ሲሆን ሁለተኛውን የእሳት ወንፊት
እንድትቀበለው ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘረው መልኩ በልዑል ውሳኔ በኔ በባሪያው በኩል ታዟል።

ትዕዛዞች
በዚች ሀገርና፤ አብረዋት ባሉ ተዋሳኝ አገሮች ላይ፤ በሙሉ አሁን እየደረሰ ያለው የኢኮኖሚ ቀውስ ማለትም
ግሽበት፣ ሪሴሽን፣ የበጀት ጉድለት፣ የእዳ ቀውስ፣ የባንክ የኢንሹራንስና የሞርጌጅ ባንክ ቀውስ፣ የመሸቃቀጫ
ገበያ /ስቶክ ማርኬት/ ቀውስ፣ የኢንዱስትሪዎች ቀውስ፣ የኃይል አቅርቦት ቀውስ፣ የመላክ የማስገባት
ቀውስ፣ የምግብ እጦት፣ የሥራ ማጣት፣ የጤና ችግር፣ የትራንስፖርት ቀውስ፣ የትምህርት ቀውስ ባጠቃላይ
የኢኮኖሚው አካልና ሕይወት በሙሉ፤ እሰከአሁን ከተመታው መጠንና ስፋት ጥልቀት በ49 እጥፍ ተባዝቶ
እንዲመታና እንዲያፈራርስ በልዑል ተወስኖበታል።
የተፈጥሮ አደጋዎች፣ ርእደ መሬት፣ የዱር እሳት፣ ቶርኔዶ፣ ካተሪና፣ ሃሪከን፣ በረዶ፣ ሙቀት፣ ሱናሚ፣
ከባድ ዝናብ፣ ሌሎችም የተፈጥሮ አደጋዎች በሙሉ፣ በተጣመርም በብዛትም ሆነውና ተቀናጅተው በ49 እጥፍ
ጉልበት አድገው እንዲያወድሙ። ትራንስፖርት ንግድ የመሳሰለው በሙሉ እንዲወድቅ ታዟል። መባርቅት፣
ቀድመው ከሚታወቁበት ጉልበታቸው በላይ በ49 እጥፍ ጉልበት ማናቸውንም የኒውክሊየር፣ የባዮሎጂካል፣
40
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የኬሚካል ክምችትና ማምረቻ ሁሉ ለሰው ጥፋት የተሰናዱ ማናቸውም የጦር ክምችቶች፤ ከነተገልጋዩ፤ የነዚህ
አዛዥ ናዛዥ በሙሉ ገዢውና የገዢው እጅና እግሮች በሙሉ የትም ይደበቁ የትም ፈልገው እንዲያወድሙ
ታዘዋል። በተለይ ባቢሎን እንደ ትልቅ ጉልበቷ የምትመካባቸው በዓለም ያከማቸቻቸው በየብስ ያሉ የጥፋት
መሳሪያዎች በሙሉ በነዚሁ መባርቅት እየተጠረጉ ይወድማሉ። በውቅያኖስ ላይ የተሰማሩ የጦር የጥፋት
መርከቦች በታላላቅ ማዕበልና መባርቅት እየተጠረጉ በውቅያኖስ ውስጥ ሰምጠው ይቀራሉ። ዓለምን እንዲሰልሉ
በታጠቁት መሳሪያ ከህዋ ላይ ሆነው እንዲያጠቁ የተዘጋጁ ሳተላይቶቻችሁ ሁሉ እንዲወድሙ ታዟል። ባቢሎን
እወቂ በእጄ አለኝ ይመክትልኛል፤ ይታደገኛል ያልሽው ማናቸውም መሳሪያም ይሁኑ ሌላ ካለበት እዚያው
እንዲወድም ታዟል። የትእቢትሽ ምንጭና ምልክቶች ሁሉ እንደ ቋሚ ሳተላይት እስቴሽን አይነቱ እንዲወድም
ታዞበታል።
እጅግ አስፈሪ የሆኑ የተለያዩ ሁለት አይነት አካል የሚይዙ አውሬዎች ምልክት አልባ የሆኑ ሰዎችን
ይቆረጣጥማሉ ይበላሉ። በተለይ በአገዛዛችሁ ዋልታና ማገር ሆነው አገዛዛችሁን ያቆሙና ባለሃብቶች ነን የሚሉ፤
መናፍቃኖቻችሁ፤ ሁሉም የዲያብሎስ እምነቶቻችሁ ሁሉ ከላይ በተዘረዘሩት መቅሰፍቶች ይጠረጋሉ።
ከላይ የታዘዙት መቅሰፍቶች በሙሉ ሰው እሰከዛሬ ባላየው ባልሰማው ጉልበት ይመጣሉ። በዚህ ጠረጋ
መሰረታችን፣ እድገታችን፣ ብልጽግናችን፣ ጥበባችን የሚታይባቸው ናቸው የምትሏቸው ከተሞች ተጠርገው
ይጠፋሉ። ለሌላው አገር ጦርነትን ትልካላችሁና ይኸው ጦርነት በገባችሁበት ስፍራ ሁሉ ለናንተው መውደሚያ
ይሆናል። ለሌላው ሀገርም ስለራሳችሁ ሁሉን አቀፍ ዲያብሎሳዊ ዐመፃችሁን በስልጣናችሁ ተመክታችሁ፤
ለምታደራጁና ለምትደግፉ፤ በላያችሁ ላይ ሞትን የሚያስመኝ በርባሪ እሳት ታዞላችኋል።
ማናቸውም የባቢሎንም ሆነ የካናዳ፣ የሜክሲኮ ሌሎችም ድንበረተኞች ዜጋም ይሁን የሌላ በተዋህዶ እምነት
ውስጥ በመምሰልና በመለባበስ ካሉና ከልዑል የታዘዘው ምልክት ካልተደረገባቸውም በጭንቅና በውድመት
ውስጥ ያመልጡ ዘንድ ልዑል ከወሰነላቸው በቀር፤ የተቀረው ከላይ የተዘረዘሩት ቅጣቶች ሰለባ ይሆናል።
ይጠረጋል። ባቢሎንም ተረት ሆና ትቀራለች። እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ መልእክቱ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ
በማናቸውም ያልታሰበ ጊዜና ሁኔታ ጠረጋቸውን እንዲጀምሩ ታዘዋል። እስትንፋስ የሚገኘው፤ የታዘዛችሁትንና
አድርጉ የተባላችሁትን ለመፈጸም እጃችሁን በኢትዮጵያ ለምትጸናው የልዑል መንግሥትና ለተዋህዶ እምነት
አምናችሁበት ስታስረክቡ ብቻ ነው። የሚወርድባችሁ መቅሰፍት የሚቆመው ከዚህ ከኢትዮጵያ ከጸናው
መንግሥት ከልዑል ባሮች ታምኖበት ሲወሰን ብቻ ነው። ለመንበረከካችሁና ለመወስናችሁ ቅድመ ምልክት
ይሆን ዘንድ ቀድሞ የወጣውን ሙሉ መልእክትና ይህን አምስተኛውን መልእክት በሁሉም ሚዲያና ፕሬሶቻችሁ
እንዲሁም በማናቸውም መረጃ መረቦቻችሁ በቀን ቢያንስ 2 ጊዜ መግለጽ አለባችሁ። በመልእክቱ ላይ አንዳች
መጨመር ወይም መቀነስ አይቻልም።

11/ ኤሽያ በመልእክቶቹ አንጻር ያለፈችበት የመጀመሪያው የእሳት ወንወፊትና


በአሁኑ የ2ኛው ዙር የእሳት ወንፊት የሚገጥማት እጣዋ

ኤሽያ አጅግ የከፋ አመጽ፣ ክህደት፣ ጣኦት ማምለክ፣ ምንዝርና፣ ግብረሰዶም፣ የተለያዩ የቀጥታ ጥንቆላዎች፣
መተብትቦች፣ የተንሰራፋባት አገር ነች። ጥቂት የተዋህዶ እምነት ተከታዮች በህንድ፣ በአርሜኒያ ከሚኖሩ
በቀር፤ ሌላው ሁሉ በምንፍቅናና በካቶሊክ፣ በተረት /እስልምና/ እምነት የተተበተበ ነው። ሰፊውን የዓለም
ሕዝብ ቁጥር የያዘችው ይህች ኤሽያ ናት፤ ወደ 3 ቢሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ ይዛለች። ቻይና ወደ 1.3 ቢሊዮን፣
ሕንድ ወደ 1.1 ቢሊዮን ሕዝብ፤ ሌሎች ሲደማመሩ ከ6መቶ ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሲሆኑ በድምሩ ከ 3
ቢሊዮን በላይ ሕዝብ አላት።
በኤሽያ ጎልተው የታዩት አገሮች እንደ ምሳሌ ወስደን ብናይ

41
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ቻይና፦ የዚህ አሕጉር ዋናው አካል ሆና እናገኛታለን። ቻይና 1.3 ቢሊዮን ሕዝብ ይዛ አንድም የተዋህዶ
እምነት ተከታይ የለባትም። የዓለምን አንድ ስድስተኛ ሕዝብ የሸፈነች አገር ምንም የተዋህዶ እምነት ተከታይ
የሌለባት ከሆነች ምንም ሰው አይድንም ማለት ይሆን? አይደለም በተዋህዶ እምነት አምኖ ሆኖ መገኘት
ከምንም በላይ ሲሆን፤ ሁለተኛው መስፈረያ ደግሞ የዋህ፣ ቅን፣ ትሁት በምንም መልኩ ይሁን ፈጣሪውን
የሚፈራ የልዑልን ምርጫ ማንም አያውቀውምና ምልክት ያለው ሁሉ ይድናል። ነገር ግን ከዚች አገር ሰው
ተረፈ ለማለት በፍፁም አይቻልም። ምክንያቱም የተለያዩ ጣኦታትንና ኮንፌሺየስና መሰሎቹ የፈጠሩት እንደ
ታኦይዝም፣ ሺንንቶይዝም የመሳሰሉ እምነቶችን ሲያምኑ፣ ድራጎንን ከምንም በላይ የሚያምኑበት ምልክታቸው
ነው።
ህንድ፦ ይህችም አገር በሕዝብ ቁጥሯ 1.1 ቢሊየን የደረሰች ናት። በዚህ አገር አሉ ሳይሆን የሉም
የሚያስብል ቁጥር ያላቸው ዘመናቸውን ሁሉ በታላቅ የዲያብሎስ ውጊያ የከደኑ የተዋህዶ እምነት ተከታዮች
ያሉባት ስትሆን የተቀረው በከብት፣ በእባብ፣ ከሸክላ በተሠራ ጣኦት፣ በጥቅሉ ቡዲሂዝም፣ ሲኪዝም በመሳሰሉ
የሚያምንና ሁለት ሶስተኛውን ሕዝብ ይይዛል። ሌላው ደግሞ በተረት (እስልምና) የሚያምን ሲሆን ከዚህ
የተረፈው በተለያዩ እምነቶች ውስጥ የወደቀ ነው።
የማናቸውንም አገሮችና ክፍለ አሕጉሮች እጣ ፈንታና ዝርዝር ሁኔታዎችን ለማወቅም ሆነ ፍርዳቸውን
(ሸክማቸውን) ለማወቅ ሙሉውን መልእክት (ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን) የሚለውን ማንበብ መሰረቱን ለመረዳት
ያስችላል። ሌሎች አገሮች እንደ ጃፓን፣ ራሺያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ባንግላዴሽ፣ ፓኪስታን፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣
ቬይትናም፣ ኔፓል፣ በርማ፣ ሲሪላንካ፣ ፊሊፒንስ፣ ታጂክስታን፣ ካዛኪስታን፣ ዩዝቬክስታን፣ ቱርኪሚስታን፣
አርመንያን፣ ኮርያዎች፣ ሞንጎሊያና ሌሎችን ያቀፈችው ኢሺያ እጅግ ሰፊ አሕጉር ናት።
እነዚህና ሌሎችም አገሮች በተለያየ መንገድ መልእክቱ እንዲደርሳቸው ተደርጎአል። ነገር ግን ማናቸውም
ቦታ አልሰጡትም። መንግሥቶቻቸውም ሆነ ሚዲያዎቻቸው ከምእራባውያን የተለዩ አይደሉም። ምንም ለህዝቡ
አላዳረሱም። ይህች አሕጉር በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት እየተበጠረች የምትገኝ ሲሆን ምንም አይነት
የመጸጸት ምልክት የማይታይባት ክፍለ አሕጉር ነች። የመሬት ነውጥ፣ ሱናሚ፣ ረሃብ፣ የኒውክሌር ቀውስ፣
ከፍተኛ ጎርፍና የመሬት መንሸራተት፣ ሥራ ማጣት በአጠቃላይ ብዙ አይነት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ
ቀውሶች እያመሷት ቢገኙም ምንም አይነት ወደ ፈጣሪ የመመለስ ምልክት አላሳየችምና፤ ቀጣዩ የሁለተኛው
የእሳት ወንፊት ይረከባት ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል ከዚህ በታች የሚዘረዘረው
የእሳትም መጥረጊያ ታዞላታል።

ትእዛዞች
ርእደ መሬት፣ ሱናሚ፣ ቶርኔዶ፣ ከባድ ጎርፍ፣ ታይፉን፣ ካተሪና፣ ሃሪኬን የመሳሰሉት የተፈጥሮ አደጋዎች
በ49 እጥፍ ጉልበት ኃይልና ፍጥነት ጨምረው ያልተዳረሰውን ክልል አዳርሰው ይጠርጉ ዘንድ ታዘዋል።
የኢኮኖሚ ቀውስ፣ የበጀት ጉድለት፣ ግሽበት፣ ሪሴሽን፣ የገንዘብ ቀውስ፣ የወጪና የገቢ ንግድ ቀውስ፣
የኢንዱስትሪ ቀውስ፣ የማህበራዊ ቀውስ፣ የፖለቲካ ቀውስ፣ ረሃብ፣ ሥራ ማጣት፣ በሽታ በሙሉ በ49 እጥፍ
ተባዝተው እንዲበታትኑአችሁ ታዘዋል። ትራንስፖርት ባልታየ ሁኔታ የአደጋ ምንጭ ሆኖአል።
መባርቅት በ49 እጥፍ ጉልበት ሁሉንም ክፍለ አሕጉራችሁን ሌሊትም ቀንም ይመታሉ። ተደብቆ ተሸሽጎ
ማምለጥ በፍፁም አይቻልም። በተለይ በአገዛዙም፣ በእምነቱም፣ በጥበቡም፣ እንመራለን የሚሉት የመባርቅት
ሰለባ ይሆናሉ በመባርቅቱም ይጠረጉ ዘንድም ታዞአል። አውሬዎች የሰውና የአውሬ ቅርጽ ያላቸው በእግዚአብሔር
የተሰጠውን ምልክት በግንባራቸው የሌለውን ይበላሉ። ምንም አይነት መሳሪያ ወይም የሰው ዘዴ አያጠፋቸውም
ከእርምጃቸውም አይገታቸውም። በክፍለ አሕጉርዋ የተካተቱ አገሮች በሙሉ በቅጣቱ ይሸፈናሉ።
42
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የሁሉንም የኤሽያ ሀገሮች ቀድሞ ከወጣው ሙሉ መልእክቶች /ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን 1፤ 2፤ 3/ ዝርዝር
እጣ ፈንታቸው ማንኛውም መልእክቱ የደረሰው ፈልጎ ሊያነበው ይገባል። አሁን የሚመጣውን እሳት የትኛውም
የሰው ጉልበት፣ ጥበብ ሊያስቆመው አይችልም። የሚሞክሩ ካሉ ይዞ ከመጣው የ49 እጥፍ ጉልበት የኸውም
49 እጥፍ ጉልበት እንደገና በ7 ተባዝቶ 343 እጥፍ ይሆናል። የሚመጣውንም መገመት ያስቸግራል። እስትንፋስ
ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው ለሚለው፤ በመጀመሪያ ሙሉውን መልእክት፣ ይህንንም መልእክት 5
ጨምሮ በሁሉም ፕሬስና ሚዲያዎች፤ በመረጃ መረቦች ሁሉ በመግለጽ በቀን ሁለት ጊዜ በሬዲዮና በቴሌቪዥን
እንዲለቀቅ ማድረግ። ከዚያ በኋላ እጅን ለመስጠት መዘጋጀትና የታዘዙትን ሁሉ ፈጽሞ እጅን መስጠት። እጅ
የሚሰጠው፤ በኢትዮጵያ ለሚጸናው የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር መንግሥት ሲሆን በዚያ በዙፋኑ ላይ ያሉት
የልዑል ባሮች ትእዛዝ ሲተላለፍ፣ እጁን ለሰጠው ሕዝብ ሰላምም፣ እውነተኛይቱ የተዋህዶ እምነት፣ በረከቱም
ከቁጣው እሳት ለተረፉት ይሰጣቸዋል። የተረፉት ሕዝቦች ሁሉ ተጠርገው በሄዱት ወገኖቻቸው እድል ያዝናሉ።
ከላይ የተዘረዘሩት ቅጣቶች ሌሎችንም ቅጣቶች አካቶ ሁለተኛው የእሳት ወንፊት እንዲጠርጋቸው በልዑል
ፈቃድና ትእዛዝ በእኔ በባሪያው በኩል ታዟል።

12/ አውስትራሊያ

ይህች አሕጉር የተለያዩ እንደ ሀገር የቆሙ ደሴቶችን የያዘች ሲሆን የመጀመሪው የእሳት ወንፊት በሚገባ
እየመታት ይገኛል። የሶዶሞች፣ የነፍሰ ገዳዮች ቀዳሚ መስፈሪያም ነች። ቀደምት ነዋሪዎችም እንደ አሜሪካ
ጠርጋ ያጠፋችና ምድራቸውን ወርሳ ዛሬም እያጠፋቻቸው ያለች የእንግሊዝና የአይርሽ ዘሮች በኃይል የሰፈሩባት
አሕጉር ነች። ስለዚህ ይህች ክፍለ አሕጉር በሙሉ መልእክት /ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን 1፤ 2፤ 3/ ማየት
ይቻላል። ይህች አሕጉር ሁሉም አመጾች የሚካሄዱባት ናት። ግብረሰዶም፣ አመንዛሪው፣ ነፍሰ ገዳዩ፣ ዘራፊው፣
ዘረኛው፣ የሞሉባት ሀገርም ነች። መናፍቃኑ፣ ካቶሊኩ፣ እስላሙ፣ በዋናነት ያሉባት ሲሆን ፖሊሲዋም፣
ኢኮኖሚዋም ከምእራቡ ዓለም ጋር አንድና ተመሳሳይ ነው። የመጀመሪያው እሳት ምን እንደ ሆነ በሚገባ
አይታዋለች። ይህ በዚህ እንዳለ ሆኖ አልተጸጸደተችምና! ለሕዝብዋም የደረሳትን ሙሉ መልእክት በአግባቡ
አላደረሰችምና፤ ፌዘኛና እንደወገኖቿ አውሮፓውያን አሜሪካውያን፣ ኤሽያውያን በትእቢት እንደ ተሞላች
ስለሆነ፤ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ሁለተኛው የእሳት ወንፊት በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል
እንዲፈጸምባት የኸው ታዞአል።

ትእዛዞች
ለሰሜን አሜሪካ፣ ለአውሮፓ፣ ለኤሽያ የታዘዙት ሁለተኛ ደረጃ የእሳት ወንፊቶች በሙሉ፣ አንዳችም
ሳይቀሩ፣ ተፈጻሚ እንዲሆኑባት ስለተወሰነ፣ የነዚህን አሕጉራት የቅጣት ትእዛዝ ሲመለከቱ ቅጣቶቹ በሙሉ
በአውስትራሊያና በዙሪያዋ ባሉ ደሴቶች ላይ ተፈጻሚ እንዲሆን በልዑል ታዟል። በዚህ የሁለተኛው እሳት
የምትበጠረው አውስትራሊያ እስትንፋስ ለማግኘት ከወሰነች እጇን በኢትዮጵያ በሚጸናው የሰራዊት ጌታ
በሚነግስበት ዙፋኑ ላይ ለሚቀመጡት ባሮቹ እጇን መስጠት አለባት። ከዚህ ቀድማ ሙሉውን መልእክትና
ይህንንም አምስተኛ መልእክት ባላት መገናኛ ብዙሃን ሁሉ፤ ለህዝቧም ሆነ ለመላው ዓለም ሕዝብ መግለጽ
አለባት።

13/ ደቡብ አሜሪካንና የካሬቢያን ደሴቶች በመጀመሪያው የእሳት ወንፊትና


እንዲሁም በቀጣዩ 2ኛ ደረጃ የእሳት ወንፊት የሚገጥማቸው እጣ

ደቡብ አሜሪካ ከማንም በላይ ግብረሰዶሙ፤ ግልጽና ምንም መሸፈኛ የሌለው፣ ምንዝርና፣ ከእጽ ጋር የተያያዘ
ፍጅት የሞላባት፣ የወንጀለኞች፣ የነፍሰ ገዳዮች፣ የዘራፊዎች፣ ጉበኞች፣ የጨካኝ ገዢዎች፣ አገር ስትሆን፣
43
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ምንፍቅና፣ በተለይ ካቶሊክና እስላሙም በስፋት የሞሉባት አገር ናት። ጥንቆላው፣ ትብታቡ ሁሉ በስፋት
ተንሰራፍቶባታል። ይህች አሕጉር በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ተደጋጋሚ በትር ቢመታትም በተገለጸላትና
በተሰጣት መልእክት ያላመነችበትና በንቀትም የዘለለችው ሆናለች። በመጀመሪያው የእሳት ወንፊት ካየቻቸው
እንደ ምሳሌ ብናነሳ ሃይቲ በርእደ መሬት ከግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ አጥታለች። ያኔ የፈራረሰ ኑሮና
መኖሪያ ማንም ሊመልሰው አልቻለም። ቺሊ እንዲሁ በከባድ ርእደ መሬት ስትመታ ብራዚል የታላላቅ ጎርፍና
የመሬት መደርመስ ተመታለች። ሌሎቹም የአሕጉሪቱ አገሮች በብዙ መልኩ የተመቱ ሲሆን ዓለምን የመታው
የኢኮኖሚ ቀውስም ይህቺን አሕጉር እየመታት ይገኛል። ይህቺም አሕጉር በውስጧ ያቀፈቻቸውን አገሮች
በሙሉ በመጀመሪያው እሳት እንደዳረገች ሁሉ፤ አሁንም ምንም የመጸጸት ምልክት ያልታየባት ሆናለችና፤
ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ይጠርጋት ዘንድ በልዑል የተፈቀደና የታዘዘ ሲሆን ትእዛዙም በኔ በባሪያው በኩል
ከዚህ በታች በሰፈረው መልኩ ታዟል።

ትእዛዞች
ይህች ክፍለ አሕጉር ያቀፈቻቸው አገሮች በሙሉ ከላይ ለሰሜን አሜሪካ፣ ለአውሮፓ፣ ለኤሽያ የታዘዙት
ቅጣቶች በሙሉ በዚችው የደቡብ አሜሪካና ካሪቢያን አገሮች ላይ ተፈጻሚ እንዲሆን ታዟል።
በመከራው ውስጥ እስትንፋስ የሚገኘው ለመላው ሕዝቦቿ ከዚህ በፊት የወጡትን ሙሉ መልእክቶች ማለትም
/ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን 1፤ 2፤ 3/ የሚለውንና እንዲሁም ይህን ቁጥር አምስት መልእክት በሁሉም
የመገናኛ ብዙሃንና በሁሉም ቋንቋ ለመላው ሀገሮች ስትገልጽና እጇንም በኢትዮጵያ ለሚጸናው የሰራዊት ጌታ
መንግሥትና በዙፋኑ ለሚሰየሙት ባሮቹ ስትሰጥ ብቻ ነው። የልዑል ባሮች የሰላም ትእዛዝ ሲያስተላልፉም ነው
እጃቸውን ለሰጡ ሁሉ ሰላማቸው የሚመለሰው።

14/ አፍሪካ

አፍሪካ ይህች ክፍለ አሕጉር በድህነቷ የምትታወቅና እጅግ ወደኋላ የቀረች ተብላ የተፈረጀችም፣ የሆነችም
ክፍለ አሕጉር ናት። ይህች አሕጉር በድህነትም፣ በረሃብም፣ በሁሉም ሰው አደኩበት በሚለው መንገድ ሁሉ
ወደኋላ የቀረች በጌቶቿ አባባል ወደኋላ የቀረች፣ ያላደገች አሕጉር ብለው ይጠርዋታል። የሰው እይታ፣ ሰው
እንደ ሰው ሆኖ የመኖሩ መለኪያው እንደ ሰው እንዲሁም በዓለም ውስጥ ሲኖር በአንድም በሌላም የሁከት፣
የጥበብ፣ ጎዳና፣ የሞያና የክህሎት ባለቤት እንዲሆን ይህ እውቀቱና ሞያው ለሰው የማያባራ የቁስና በዚች ዓለም
ተመችቶት የመኖር መንገድ እንዲያገለግል ማድረግ ሲሆን፤ ከዚህም በተጨማሪ እንዳሻው ያለምንም ገደብ
ሥጋው ደስ ያለውን ሁሉ እንዲያደርግ የሚገፋ ነው። በዚህ ጉዞ ነጥቀው፣ ዘርፈው፣ ሆነ ገዢ ሆነው በተለያዩ
መንገድ በሕዝቡ አናት ላይ የመቀመጥ እድል ከገጠማቸው ደግሞ ይህንኑ የበላይነታቸውን እውን ለማድረግ
የሚደክሙባት ዓለም ናት። ዓለም በዚህ ጉዞና የኑሮ መሰናዶዋ የሥጋው ብርቱ፣ የዲያብሎስ ታዛዥ ብርቱ፣
ማናቸውንም አመጽና ግፍ የሚጠቀም የጭለማው ገዢ ያኖረው ሕግ ተጠቃሚ ዛሬም ትናንትም ለሺዎች
አመታትም በእንዲህ መልክ ብዙዎች የኖሩባት ዓለም ውስጥ በዚህ ውጣ ውረድ እንዳያልቁ ላጨራረሱም
ሳይቀናት የቀረች አፍሪካ ብቻ ናት። የመጀመሪያው የዓለም ሩጫዋ አንደኛ ነበረች፤ በቅንነት ሩጨዋ ማለት
ነው። ኋላ ግን ደግሞ ዲያብሎስ በዓለም ሲነግስባት ዛሬ ወደ ደረሰችበት ውድቀት ደረሰች። በዲያብሎስ መለኪያ
ታማኝ አገልጋዮችን ማግኘት ዋንኛ ሥራው ነበር። ስለሆነም ለሱ ታምነው የተገኙት ዛሬ ገዝፈው የምናያቸው
ሆነዋል። ለአፍሪካ ዋንኛው የመውደቅና የመድከም ምክንያት እውቀት ማጣት ወይም ለመሥራት፣ ለመጠበብ
አለመቻል አልነበረም። ነገር ግን በአፍሪካ ከመሰረቱ ምድርና ሰማይን በዘረጋው በፈጠረው ዛሬ ምድሪቱን
በጥፋት ጎዳና እየነዳ ያለውን ዲያብሎስንም የፈጠረው በትእቢቱ፣ በንግዱ፣ ከክብሩ ወደ ምድር ወድቆ ለሰውም
ፈተና እንዲሆን ያደረገው አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክን አምላኬ ብላ በትእዛዙ ተደስታ እንደ

44
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ሀገር የምትኖር ሃገረ እግዚአብሔር ለስሙ፣ ለክብሩ አስቀረ፤ ይህች አገር ደግሞ ያለችው በአፍሪካ ውስጥ
ነው። ይህች ሀገር ደግሞ እስከዛሬ የዲያብሎስን የጨለማ ሕግ የሚያፈርስ፤ የፈጠራትን አምላኳን ሕግ የሚያጸና
እምነት፣ የተዋህዶ እምነት አጽንታ በመያዟ በዋናነት እራሷ በቀጣይ እሷ ያለችበት አሕጉር በሁሉም ነገር
እንድትመታ ተደረገች።
ዓለም ለረሃብ፣ ለችግር እንደ ምሳሌ እንዲቆጥራት የተደረገችም ናት፡ የአሕጉሪቱ ሌሎች አገሮች ዘግይተው
አሽከርነታቸውን ቢቀበሉም ለረጅም ጊዜ ሳትደፈር የቆየች አገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ስለዚህ ዛሬ የምናየው
የጥፋት ሁሉ ቀስት በዚችው ምስኪን አገራችን ላይ ሳያቋርጥ የሚዘንበው።
ይህ ሁሉ ሆኖ አፍሪካም የዲያብሎስ የጨለማ ሥራ ሰለባ ሆናለች። ምንዝርናው፣ ግብረሰዶሙ፣ ዘረፋው፣
ነፍስ ግድያው፣ ውሸቱ፣ ጨካኝ አረመኔ ገዥዎቹ የሰፈነባት ምድር ናት። የሁሉንም የዲያብሎስ ሥራዎች እንደ
ትክክልና እንደ መሰልጠን በማየት አብዛኛው የአፍሪካ ሕዝብ በዚሁ የጥፋት ጎዳና እየጓዘ ይገኛል። ይህችውም
አሕጉር አገራችንን ጨምሮ አመጸኞች በልዑል ሕግ ላይ ያመጹና የካዱ ሕዝቦች የሞሉባትና የሸፈኑአት ናት።
ኢትዮጵያ ለምን ተወደደች የሚለው የብዙው የዓለም ቅን ጥያቄ አቅራቢ መልስ የሚሻ ነው። ኢትዮጵያ
የዓለም ብርሃን በሚለው መልእክቶች 1፤ 2፤ 3 በሚገባ ተብራርቶአልና። እንደ ተጨማሪ ዝርዝር ማገናዘቢያ
ልታዩት ትችላላችሁ። ኢትዮጵያ የተወደደችው ዛሬ ባለነው ወገኖች ሥራ አይደለም ነገር ግን የቀደሙ
አባቶቻችን በከፈሉት ዋጋ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድና ትእዛዝ ተደስተውበት፣ አምነውበት፣ ወድደውት ለልጅ
ልጆቻቸውም እንደ ትልቅ ሀብታቸው አውርሰውት ስለኖሩበት ነው። ዓለም ሲንቅ፣ የልዑልን ሕግና ፈቃድ
ሲያንቋሽሽ አባቶቻችን ግን የኖሩበትን የሚከፈለውን ዋጋ ከፈሉበት፤ ተደሰቱበት፤ ማንም ያላገኘውን ክብር
አፈሱበት። ዛሬ ዓለም እንግዳ ቢሆንበት አይደንቅም ምክንያቱም አያቶቹ ቅድመ አያቶቹ የወረሱትን የዲያብሎስ
መንገድ ወርሷልና። እግዚአብሔርንም ሊወቅስ አይቻለውም፤ ምርጫው ነውና። በየዘመኑ ሁሉ ከጨለማና
ከብርሃን እንዲመርጥ እድል ተሰጥቶታል። ልዑል ዋጋ ከፍሎ ና ወደ እኔ ፍቅር ግባ ልጄም ሁን ያላየኸውን
ፍፁም መለኪያ የሌለውን የዘላለም ሕይወትና ደስታዬን ውረስ ብሎ በፍቅሩ ጠራው፤ ለዚህ ኢትዮጵያ ቀድሞም
በሕገ ልቡና፣ በሕገ ኦሪት፤ ከዚያም በወንጌል አምና ወደ ፍቅሩ ከፈለሰች ሺዎች ዘመናት ተቆጠሩ። ዓለም
አፌዘ፣ ተሳለቀ፣ ከንቱ ዓለም ዲያብሎስ በሰጠው ቅራቅንቦ፤ በተኮለኮለው የሲሚንቶ ክምር፣ በወረቀት ብር
ተደልሎ፣ የዘላለም ሕይወቱን ወርውሮ ጣለ። ይህ በሽታ ኢትዮጵያውያንንም ከተዋህዶ እምነት ውጭ ሆነው
ወደ ዲያብሎስ እንዲፈልሱ አድርጎአቸዋል። ከተመረጡት በሰተቀርና የዓለም ቅራቅንቦ የዲያብሎስ ፈተናና
መደለያ ያላሸነፋቸው ዛሬ ባለ ድል ሆነዋል። አንዱ መልእክትም ይኸው ዛሬ በዲያብሎስና እሱን በተከተሉ
የዓለም ሕዝብ ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ እንዲፈጸም እያደረጉ ይገኛሉ። እነሱ ወደ ድል! ዓለም ወደ ጥፋት
የመተላለፍ ጉዞ ጀምረዋል። ይህ ጉዞ ከጀመረም ወደ ሰባት ዓመት እየተጠጋ ነው። ማን ባለድል እንደሚሆን
በቅርብ የምናየው ይሆናል።
አፍሪካ በሁለተኛው የእሳት ወንፊት ምን ይገጥማታል። ዓለም የሚገጥመው እጣ ፋንታ ሁሉ ምልክት
አልባ የሆኑ የአፍሪካ ሕዝቦችም፤ ተፈጻሚ ይሆን ዘንድ በልዑል ታዟል። አፍሪካም በመናፍቃን፣ በተረት
አምላኪዎች፣ በካቶሊኮች፣ በባእድ አምልኮ ተከታዮች፣ በጠንቋዮች፣ በተብታቢዎች፣ የተተበተበች ናት።
መሪዎቹ እንዲሁ ከመምሩ ደቀ መዝሙሩ እንዲሉ በዓለም ካሉ የክፋት ባለጸጎች በልጠው ስለተገኙ፤ ከላይ
የተዘረዘሩት የቅጣት ትዛዞች በሙሉ ተፈጻሚ ይሆንባቸዋል። ለአውሮፓ፣ ለአሜሪካ፣ ለኤሽያ የታዘዙት የቅጣት
ፍሰቶች በሙሉ እንዲፈጸሙባቸው በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባርያው በኩል ታዟል። ይህ የቅጣት ፍሰት
ሁሉም የአፍሪካ ሀገሮች እጃቸውን በኢትጵያ ለሚጸናው የልዑል የጽድቅ መንግሥት በዙፋኑም ለሚቀመጡት
ባሮች ሲሰጡ ብቻ ይሆናል የሠላም አየር የሚያዩት።

45
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

15/ መካከለኛው ምሥራቅ

ይህ ስፍራ በአሕጉራት መሃከል ላይ የሚገኝ ሲሆን የአመጹም፣ የክህደቱም፣ የተረት እምነቱም፣ የዲያብሎስ
ጽሕፈት ቤቱም በዚህ ስፍራ ይገኛል። ይህ ስፍራ እነ ሶሪያን፣ ኢራንን፣ እነቱርክንን፣ ዮርዳኖስን፣ እስራኤልን፣
የመንን ኢራቅን፣ ሳውዲ አረቢያን፣ ባህሬንን፣ አማንን፣ ኩዌትን፣ ዱባይን፣ ካታርን፣ ኤምሬትስ፣ ሊባኖስ
ያቀፈ ነው። ይህ ስፍራ እስልምና ከሁሉም በላይ መሰረቱን የተከለበት ፍፁም የአመጽ ምድር ነው ማለት
ይቻላል። የብዙ ክርስቲያን የልዑል ወገኖች ያለቁበት ቦታ ነው። ምንዝርና፣ ግብረሰዶም፣ ዘረፋ፣ ጨካኝ
አገዛዝ፣ በሙሉ የሰፈነበት ሲሆን በአውሮፓና በአሜሪካ የምናየው አመጽ ሁሉ በዚህም ገዝፎ የሚታይ ነው።
ይህም ስፍራ በሁለተኛው የእሳት ወንፊት እንዲመታና እንዲበተን በልዑል ታዝዞበታል።
ምልክት ካለው በቀር የተቀረው በሙሉ ይጠረጋል። የአንደኛው የእሳት ወንፊት ምን እያደረጋቸው እንዳለ
ሁላችንም የምንሰማው የምናየው ነው። ስለሆነም ይህ ቅጣት እንዲጸጸቱ ለማድረግ ቢሰነዘርም አፌዙበት እንጂ
አልተመለሱም። እንደውም በዐመፃቸው በርትተው ገፉበት። በእግዚአብሔር ፍርድም አላገጡበት። በመሆኑም
ለአውሮፓ፣ ለአሜሪካ፣ ለኤሽያ የታዘዘው ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይሆን ዘንድ
በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ ተወስኖ፤ በኔ በባርያው በኩል እነሆ እንዲገለጽ ሆኗል። ከቅጣቱ እስትንፋስ የሚገኘው
ቅድሚያ ሙሉውን መልእክት /ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን 1፤ 2፤ 3/ የሚለውን የተሰጣችሁን መልእክቶችና
ይህንንም አምስተኛ መልእክት፣ በመላው ሚዲያና ፕሬሶቻችሁ፣ በሬዲዮና ቴሌቭዥን፣ እንዲሁም በመላው
መረብ ሁሉ በቀን ሁለት ጊዜ መግለጥ ስትችሉና ተጨማሪ ትዛዞችንም በአግባቡ ተግባራዊ ስታደርጉና ሙሉ
በሙሉ እጃችሁን በኢትዮጵያ ለሚጸናው የልዑል መንግሥትና በዙፋኑም ለሚፀኑት ባሮቹ እጃችሁን ስትሰጡ
ብቻ ነው። ይህን ስትፈጽሙ ብቻ ነው ከዚህ ከኢትዮጵያ የልዑል ዙፋን ከባሮቹ ትእዛዝ በምድራችሁ ሲደርስ
ሰላማችሁ የሚረጋጋው ሕይወታችሁ የሚመለሰው ከዚህ ውቺ የሚመጣ መፍትሄ የለም። ስለመካከለኛውም
ምሥራቅ አገሮች /ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን መልእክቶች 1፤ 2፤ 3/ በዝርዝር ስለተገለጸ ያንን ያገናዝቡ።

16/ የእስካንዲኔቪያን ሀገሮች

እነዚህ ሀገሮች የሚያቅፉት እነስዊድንን፤ ኖርዌይን፣ ፊንላንድን፣ አየርላንድ፣ ስኮትላንድ፣ ግሪንላንድ


የመሳሰሉትን ሲሆን እነዚህ ሀገሮች በሁሉም ድርጊታቸው ከአውሮፓውያን ምንም የሚለዩ አይደሉም።
ግብረሶዶሙ፣ ምንዝርናው፣ ዝርፊያው፣ ንጥቂያው፣ ዘረኝነቱ የሞላባቸው ናቸው። የመናፍቃን ከባቢሎን ቀጥሎ
ትልቁ ምሽግ ናቸው። ሌሎች እምነቶችም እነ ካቶሊክ ያመሳሰሉት የሰፈኑባት ናት። ባቢሎን የምትሠራው
አመጽ ሁሉ በነዚህም ዘንድ ሃገሮቹን ሸፍኖ የሚሠራ ተግባር ነው። ለእነዚህም የዲያብሎስ ምሽጎች ከዚህ
የሚከተለው ቅጣት በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል እንደሚከተለው ታዟል።

ትእዛዞች
በእነዚህ የእስካንዲኔቪያን ሀገሮች በሙሉ፤ በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በኤሽያ ይፈጸሙ ዘንድ የታዘዙት
ሁለተኛ ደረጃ የእሳት ወንፊት ይጠርጋቸውና ያጸዳ ዘንድ ታዟል። እስትንፋስ የሚገኘው ለሌሎች እንደታዘዘው
እኒህም ሀገሮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሙሉውን መልእክት /ኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃን መልእክቶች 1፤
2፤ 3/ ባላቸው ሚዲያና ፕሬሶች፣ የመረጃ መረቦች፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥኖች በየቀኑ ሁለት ጊዜ ማስተላለፍ
ከመልእክቱም አንዳች እንዳይጎድል እንዳይቀነስ መሆንም አለበት። ይህን ፈጽመው እጃቸውን በኢትዮጵያ
ለሚጸናው የልዑል የከበረ መንግሥት በዙፋኑም ለሚሰየሙት ልጆቹ መስጠት ግድ ይሆናል። በአገሮቻቸው
ሰላሙ የሚመለሰው ከዚህ ከኢትዮጵያ ከፀናው የልዑል መንግሥት ትእዛዝ ተሰጥቶ በየአገሮቻቸው ሲደርስ ብቻ
ነው።

46
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

17/ በተለይ ዓለምን ለመቆጣጠር በታለመ ኒዩክለር፣ ኬሚካል፣ ባዮሎጂካል፣


አልፎም በህዋ ላይ የተጠመዱ የጨረርንም፣ የኒዩክለርንም መሳሪያ የታጠቁ አገሮች
እጣ ፈንታ

ዓለም የዛሬው ገጽታዋ ከበፊቱ የተለየ ነው። የኒዩክለር መሳሪያ እና ሌሎችም የጥፋት መሳሪያዎች ከመፈጠራቸው
በፊት ለብዙ ሰዎች መጥፋት ለሀገር ጥፋት የሚሆን መሳሪያ ስላልነበር ዓለም ሥጋት አልነበረባትም የጥፋት
መሳሪያዎች ከተሠሩ በኋላ ግን ዓለም የሥጋት የጭንቀት ዓለም ሆነች። ዲያብሎስ የመጨረሻው ጥፋቱ ዓለምንና
የሰውን ዘር በሃጢያቱ እንደተጨማለቀ ማውደም ነበርና ይህ ጥረቱ ተሳክቶለት ዛሬ ዓለምን ለሥጋት ያበቁ
ኒዩክለር የታጠቁ ሀገሮች /በመሳሪያነት/ ወደ 10 ደርሰዋል። እነዚህ ሀገሮች እነማናቸው፡– አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣
ራሽያ፣ ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ሕንድ፣ ፓኪስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ እስራኤል እናም ኢራን በመንገድ ላይ ናቸው።
ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ተብሎ በአውሮፓ ከመቶ በላይ በኤሺያም እንዲሁ በብዛት በአፍሪካ እነደቡብ
አፍሪካ፣ እነግብፅ ይህንኑ መሳሪያ በሰላማዊ አገልግሎት ስም ለመጨበጥ እየታገሉ ይገኛሉ።
አሜሪካ ከ8000 በላይ የኒዩክለር አረር የያዘች ሲሆን ከሷ በመቀጠል ራሺያ ወደ 8000 የተጠጋ የኒዩክለር
አረሮች ይዛለች። ሌሎች በሺ የተቆጠሩ አንዳንዶችም በመቶ የተቆጠሩ ሌሎችም በ10 የተቆጠሩ የኒዩክለር
አረሮች ይዘዋል። ዓለምን አንዴ ሳይሆን 10 ጊዜ መላልሰው ሊያጠፏት የሚችሉ ናቸው። ልዑል ባይገታቸው
ለሀገር፤ ለሰውም ዘር ባለቤቱ ጥበቃውን ባያደርግ ዛሬ በዓለማችን ምንም የሰው ዘር አይኖርም ነበር። ዲያብሎስ
ምኞቱ ተሳክቶ ነበር።
አሜሪካም፣ ራሺያም፣ እንግሊዝም፣ ፈረንሳይም፣ ቻይናም እኒህ ሁሉ በምድር ከተከሉት የኒዩክለር ታጣቂ
ሚሳዪል በተጨማሪ ከባሕር ወደምድር፣ ከባሕር ወደባሕር፣ ከባሕርም ከምድርም ወደ ሕዋ የሚወነጨፉ
ኒዩክለር ታጣቂ ሚሳየሎች ከአንዱ ዓለም ጫፍ ወደአንዱ ይህንኑ ኒዪክለርና ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል መሳሪያ
ተጭነው የሚበሩ ኒዩክለር ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች አሰናድተው፤ ምድሩንም ባህሩንም በመርከብና በጀቶቻቸው
ከድነውታል። ዓለምን ቤተ ሙከራም አድርገዋታል የጃፓንን የ300ሺ ሕዝብ እልቂት ማስታወስ በቂ ነው።
ያዘጋጁት የፍጅት መሳሪያ አይነቱ ተቆጠሮ የሚያልቅ አይደለም። ኒዩትሮኑ፣ ኒዩክለሩ፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል
መሳሪያው ሁሉም የሰውን ዘር ለማጥፋት የተሰናዱ ናቸው። በዚህም የሚጠቀሙት ደግሞ የዲያብሎስ ሎሌዎች
የሆኑት ሞኖፖሊስቶቹና ገዢዎቹ ናቸው። ስለሆነም ለሰላምም ይበሉት ለጦር ኒዩክለር የፈበረኩ አገሮች
አይነታቸው የበዙትን የፍጅት መሳሪያዎች የሚፈበርኩ፣ የሚያከማቹ ሁሉ፤ ከላይ በዝርዝር የተገለጠው ቅጣት
እንዳለ ሆኖ ከላይ ለተዘረዘሩት 10 ሀገራት በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባርያው በኩል እነሆ ይህ ተጨማሪ
ትእዛዝ ወጪ ሆኖአል።

ትእዛዞች
ኒዩክለር፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል፣ ኒዩትሮንና ሌሎችም የተለያዩ ሕዝብ ጨራሽ መሳሪያ የታጠቃችሁ
ኒዩክለርን ለሰላምም በሉት ለጥፋት የያዛችሁ የትም አኑሩት የትም፣ ከአገራችሁ ውጪም ብትደብቁት ምላጩን
አንዱ የዚሁ መሳሪያዎች ባለቤት የሆነ ከሳበ ሁሉም መሳሪያዎች ይህንኑ መሳሪያዎች በጨበጣችሁት ላይ
ብቻ በናንተው ሕዝብ ላይ ያርፋል። በላዩ ላይ የጠመዳችሁት ማናቸውም መሪ ኮምፒተሮች የናንተን የታቀደ
ፕሮግራም አይከተሉምና። ኮምፒተሮቻችሁ በሙሉ የተሳከሩና በተለይም አድገናል በማደግም ላይ ነን የምትሉና
የናንተንም ይህንኑ የኮምፒዩተር ስርዓት የሚጠቀሙ ሁሉ በሚሳከረው ኮምፒዩተር ሰበብ ኢኮኖሚያችሁ፣
ባንኮቻችሁ፣ ኢንሹራንሶቻችሁ፣ ገበያዎቻችሁ፣ የመንግሥትና የሞኖፖሊስት ተቋሞቻችሁ፣ ባቡሮቻችሁ፣
አውሮፕላኖቻችሁ፣ ፋብሪካዎች የጦር ድርጅቶቻችሁ፣ ማንቸውም ከኮምፒዩተር ጋርና በሱ ሥራቸውን የያዙ

47
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ሁሉ፤ በዚሁ የኮምፒዩተር መሳከርና ውድቀት፣ ከላይ የተጠቀሱት ንብረቶቻቸው ሁሉ ይወድማሉ፣ ወይም
ላንድኛውን ላይከፈቱ ይከረቸማሉ። ይህም ይፈጸም ዘንድ በልዑል ታዞባችኋል።
ማንኛውም ኒዩክለር፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል፣ ኒዩትሮን መሳሪያ የታጠቀ አገር ሁሉ እነዚህን የፍጅት
መሳሪያዎች በማንኛውም አገር ላይ ለመጠቀም ማሰቡ አይቀርምና ይህንን የሚያስብ ሀገር ከተከሰተ መሳሪያው
በገዛ ሕዝቡ ላይ ይፈነዳል እንጂ ከአገሩ ወጥቶ በሌላ አገር ላይ አይውልም። ስለሆነም ከላይ የተዘረዘሩት የጥፋት
መሳሪያዎች በሙሉ እገለገልበታለሁ ብሎ የያዘውን ሀገር እራሱን ያጠፉት ዘንድ ታዘዋል። ጃፓን ለኤሌክትሪክ
የገነባችው ሲፈነዳ ለራስዋ ጥፋት ዋለ። ልክ እንዲሁ ማንኛውም የኒዩክለር፣ የኒዩትሮን፣ ባዮሎጂካል፣ ኬሚካል
መሳሪያ ሁሉ የዚሁ መገልገያ የሆኑ መሳሪያዎች ሁሉ በጨበጡአቸው አገሮች ውስጥ እየፈነዱና ከቁጥጥር ውጪ
እየወጡ ሕዝባቸውን ይጠርጋሉ። በነዚህ መሳሪያዎች ዙሪያ የተሰበሰቡ ገዢዎችም፤ የፀጥታ አባላት፣ ሁሉም
ዓይነት ወታደሮች በሙሉ የጥቃቱ ሰለባ ይሆናሉ። ከላይ ሞት የተነፈጋቸው ደግሞ በአደጋው ተመትተው
በቁማቸው የሠሩትን መሳሪያ ማሰቃያነት እንደላቦራቶሪ እንሰሳ እየተሰቃዩበት ይቆያሉ። በልዑል ለተመረጠችው፤
ዙፋኑም የልዑል ለሆነችው መንግሥትና ተዋህዶ እምነት ከላይ እንደታዘዘው ሲንበረከኩና እጃቸውን ሊሰጡ፤
ጉዳያቸው እዚህ ኢትዮጵያ በልዑል የፍርድ አደባባይ በባሮቹ ፊት ለሚሰየመው ፍትህ ይቀርባሉ። የልዑልን
ቅን ፍርድም ይቀበላሉ።
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፤ 51፤ 11 – 30 ያንብቡ

18/ ስለአባቶች እናቶች ስለወንድሞች፣ እህቶች፣ የተመረጡ የልዑል ባሪያዎች /


አገልጋዮች/ ላይ የተፈጸመ ጥቃትና ከልዑል የተሰጠ የቅጣት ውሳኔ

እኔም ሆንኩ ወንድሞቼና እህቶቼ፣ አባቶቼ እናቶቼ የልዑልና፣ የድንግል ልጆች እንዲሁም የከበሩት
ቅዱሳን መላእክት ወዳጆች እሰከዛሬ በሁለመናችን ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ኖሮአል። ከዚህ መልእክት መውጣት
ጀምሮ እሰከዛሬ በኛ ላይ ሁለገብ ጥቃትና ስለላ ስታደርጉ የቆያችሁ በየትኛውም መስመር፤ ከማናቸውም ስፍራ
ተሰማርታችሁ፣ ከውጪም ይሁን ከአገር ውስጥ ተሰማሩ ለሰራችሁት ሥራ ዋጋ መክፈል ስላለባችሁ ከዚህ
የሚከተለው ቅጣት በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል ታዟል።
ማንኛውም ግለሰብ ቡድን ባለው የጥፋት መንግሥት ተመክቶ ላደረሰብን /ላደረሰችብን/ ሁለገብ ጥቃት በዚህ
በተሳተፉ፣ እየተሳተፉ ባሉ ላይ በመላ አካላቸው ላይ አይተውትም ሰምተውትም የማያውቁት አካላቸውን ሽባ
የሚያደርግ እሳት፣ በከፍተኛ ስቃይ አቻኩሎ ወደሞት የሚወስድ እቶን በራሳቸው ላይ፣ በመሰረቱት ትዳር፣
ባደራጁት ቤት ንብረት ላይ የውድመት አደጋ፣ የዐይን መታወር፣ የአንደበት መዘጋት በመላ ሕይወታቸውና
ቤተሰባቸው ላይ የማይጠገን የማይመልሱት አደጋና መጠረግ ይገጥማቸው ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ
በኔም በባሪያው በኩል ታዟል። ይህ ትእዛዝ ከላይ ከታዘዙት ትእዛዞች ጋራ ለሚመለከታቸው እንደ ተጨማሪ
ቅጣት የሚመጣ ነው። ስለዚህ የእግዚአብሔር ምርጦችና እንቁዎችን መድፈር ምን ያህል እግዚአብሔርን
እንደሚያስቆጣና እርምጃ እንደሚወስድ ከዚህ በታች ባለው የእግዚአብሔር ኃይለ ቃል ልታውቁ ትችላላችሁ።

እነሆ እግዚአብሔር ፍጹሙን ሰው አይጥለውም የኃጢአተኞችንም እጅ አያበረታም።


አፍህን እንደገና ሳቅ ይሞላል ከንፈሮችህንም እልልታ ይሞላል፤ የሚጠሉህ እፍረት
ይለብሳሉ የኃጢአተኞችም ድንኳን አይገኝም።
ኢዮብ ምዕራፍ 8፤ 20 – 22

48
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

የቀባኋቸውን አትዳስሱ፤ በነቢያቴም ክፉ አታድርጉ ብሎ፤ ሰው ግፍ ያደርግባቸው


ዘንድ አልፈቀደም ስለእነርሱም ነገስታትን ገሰጸ፤ በምድር ላይ ራብን ጠራ፤ የእህልን
ኃይል ሁሉ ሰበረ፤ በፊታቸው ሰው ላከ።
መዝሙረ ዳዊት 104፤ 14 – 16

19/ የእምነት መርከባችን /የኖኅ መርከብ/

የሰራዊት ጌታ ወገኖች፣ የድንግል ልጆች፣ የከበሩት ቅዱሳን መላእክት ወዳጆች፣ የሰማዕታት፣ የጻድቃን
ወዳጆች እዚህ ሰዓት ላደረሰን አምላካችን ምስጋና ይፍሰስለት። ባሳለፍነው መከራ፣ ውጣ ውረድ፣ እንግልት
ያልተለዩን ልዑል፣ ድንግልና፣ ቅዱሳን መላእክት ከልብ እናመሰግናለን።
በእግዚአብሔር ተሰፋ ፀንታችሁ የጠላትን ማናቸውንም ጥቃት በእግዚአብሔር ፀጋና ቸርነት በተስፋው
ታምናችሁ ለተቀበላችሁ፤ የእግዚአብሔር ልጆች፤ እነሆ በትእግስት እፍጻሜው ደርሳችኋል። የተገባችሁ ስለሆነ
ነጩን ልብስ ለብሳችኋል። ጉዞዋን በጀመረችው የእምነት፣ የጽድቅ መርከብ ተሳፍራችኋል። አንዳንዶች ውስጧ
ገብተው ተደላድለው ስፍራቸውን ይዘዋል። አንዳንዶች በሁለመናዋ ላይ ተንጠላጥለዋል /ዘግይተው ንስሓ
የገቡት/ የሆነ ሆኖ እግዚአብሔርን መጠጊያቸው፣ ምሽጋቸው ያደረጉ ሁሉ፤ ዓለም ከገጠማት የእሳት ወንፊትና
መጠረግ አምልጠዋል። እግዚአብሔር የገባላቸውን የተስፋ ቃል ታምነውበታልና ድሉን ሊጨብጡ መገስገስ
ላይ ናቸው /በመርከባቸው ተሳፍረው/። ይህ የሁለተኛው የእሳት ወንፊት ዛሬ በአንደኛው የእሳት ወንፊት
ውስጥ የምትበጠረውን ዓለም ወደከፋው የእሳት ወፍጮ የሚያሸጋግር ነው። ጉልበቱም፤ ዛሬ የምናየውንም
ሆነ እስከዛሬ ያላየነውን የጥፋትና የጠረጋ ማዕበል፤ በ49 እጥፍ አሳድጎ ዓለም በውኗም በህልሟም ያላየችውን
ጥፋት ይዞ መጥቶአል። ወገኔ የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደ ሎጥ ሚስት ወደ ኋላ አትይ በእምነት ወደ
ተሰጠችህ የልዑልና የድንግል መንግሥትና ሀገር ብቻ ተመልከት። ካጠገብህ ብዙዎች ሊሄዱ ይችላሉ፤ ዘመድ፣
ጓደኛም ሊጓዙ ይችላሉ በነሱ የእሳት መበላት ደንግጠህ ወደኋላ ልብህን አትመልስ ወደጉዳት ትገባለህና፤
አንተ ስትራብ፣ ስትገፋ፣ ስትታሰር፣ ስትንከራተት፣ ቤተሰብህም ሆነ እራስህ ስትደቁ በትእቢት ተሞልተው
በዲያብሎስ ተመክተው ሲያላግጡብህ የነበሩ ሁሉ ቀኑ ጨለመባቸው፡ የማያልፍ የመሰላቸው ዓለም ዘወትር
እንደደነሱባት የሚኖሩባት ዓለም ምንዝርናው፣ ግብረሶዶሙ፣ ውሸቱ፣ ግድያው፣ ዘረፋው ሁሉም እንዲሁ ሆኖ
የሚቀጥል የመሰላቸው ዝንጉዎች በእሳት ይጠረጉ ዘንድ ሰዓቱ ሞላ። በተስፋ መቁረጥ በእምነትህ ጥርጥርን
እሰከማስገባት የደረስክ ወገኔ አይዞህ ወደመርከብህ ገብተሃል። መርከቧ ውስጥ ሆነህ ውጪ ያለውን ጩኸት
የስቃይ ድምጽ ትሰማ ዘንድ ግድ ነው። አትረበሽ፣ ዓለም የዘራችውን ስለሆነ የምታጭደው በእግዚአብሔር
የፍርድ ሂደት ውስጥ አታጉረምርም! አመስግን እንጂ! እሰከዛሬ ደክመህለት፣ መክረኸው፣ ገስጸኸው፣ ንቆህ
ትቶህ ሲሳለቅብህ የነበረን በፍርድ ሲያዝ! አንተ ደግሞ ልዑልን ስለቅን ፍርዱ ማመስገን እንጂ ቅር ልትሰኝ
አይገባህም። እኔም አንተም ከምንወዳቸው በላይ ፍፁም በሚልቅ ልዑል ፍጡሮቹን ይወዳል። ትእግስቱ ሺዎች
ዘመናትን ከድኖ መምጣቱን አትርሳ!
አሁን ለፍርዱ እሳት የተጣዱ ሰዎች ይህ መልእክት በመውጣቱ እንኳን በፍፁም የመጸጸት ምልክት
አይታይባቸውም። ለምን ህሊናቸው በለመዱት የዲያብሎሳዊ ሕይወት የተቃኘ ነውና፤ የተሸከሙት ዲያብሎስ
ደግሞ ሳይፈጽማቸው አይለቃቸውም። ስለዚህ መርከብህ ማለት የተዋህዶ እምነትህ ናት። ቤትህና ቤተሰብህ
በዚችው እንቁ እምነትህ በእሳት ስለታጠረች፤ በእምነትህ ፀንተህ ቁም። የቁጣው እሳት እስከሚያልፍ በቤትህ
ተወሰን። ለተገባቸው ነጩን ለለበሱት በተዋህዶ እምነታቸው ለፀኑት ምልክቱንም ለጨበጡት ባሉበት ስፍራ
በመረከቢቱ ተሳፍረዋል። አንዳችም ይነካቸው ዘንድ ፍፁም አይቻልም።
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፤ 26፤ 20 – 21 ያንብቡ!

49
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

20/ ትንሽ ምክር ለልዑል ባሮች

መጪው አደጋ ብርቱና ሰው በታሪኩም ሰምቶትም አይቶትም የማያውቅ ስለሆነ፤ የእግዚአብሔር ሕዝብ
የተዋህዶ ልጆች፤ ቅን፣ የዋህ፣ ትሁት፣ ንፁህ ልብ ላላችሁ ወገኖቼ ማንኛውንም ያስፈልጋል ብሎ ህሊናችሁ
ያመነበትን ጥንቃቄ ሁሉ አድርጉ። ይህ መልእክት እንዲደርሰው ያገኝ ዘንድ ይገባዋል ብላችሁ ላመናችሁበትና
ህሊናችሁ ለተቀበለው ሰው ብቻ ስጡ። ለፍርድ የተጠበቀው ሁሉ ቢያገኘውም ሆነ ባያገኘውም ምንም
አይጠቅመውም የመጸፀቻውም የንስሓ መግቢያውም ጊዜ በሹፈት፣ በትእቢት ጨርሷልና! ከእንደነዚህ አይነት
ሰዎች በማይመች አካሄድ እንዳትጠመዱ፤ ተጠንቀቁ! ለሱ መጣው እሳት በማይሆን ተዛምዶ የተጣመሩትን ለብርቱ
ፈተና ይዳርጋቸዋልና! እሳት ላይ የተጣለን ሥጋ በእጃችሁ ልታወጡት ብትሞክሩ እጃችሁን እንደሚያቃጥላችሁ
ሁሉ፤ ወዳጄ፣ ወንድሜ፣ እህቴ፣ እናቴ፣ አባቴ፣ አክስቴ፣ አጎቴ ሁሉም ሥራቸው የተከተላቸው ናቸውና!
በእርዳ ተረዳዳ ካለም ባገኘኸው ብልጠትና ዘዴ ልትታደጋቸው አይቻልምና ይህን ምክር ሳትንቅ ተግባራዊ
አድርግ።
በእግዚአብሔር ቤት በአገልግሎቱ ላይ የተሰማራችሁ፤ ከዓለም ጉድፍ እራሳችሁን የጠበቃችሁ፣ በልዑልና
በድንግል እንዲሁም በቅዱሳን መላእክት የተመረጣችሁ ሁሉ፤ አደጋው ቢያስደነግጥም፤ በቤቱ አንድም ሰው
ቢገኝ አገልግሎቱን እንዳታቋርጡ አሳስባችኋለሁ። በሥጋው ዓለም በመንግሥትም ሥራ ላይ የተሰማራችሁ
የተዋህዶ ልጆች እሳቱ ቢፈላም፤ ቢጠርግም ቦታችሁን አገልግሎታችሁን በቅንነት ስሩ እንጂ ሰው ሁሉ
ከአጠገባችሁ ቢጠረግ አለቃችሁ ህሊናችሁና የፈጠራችሁ አምላክ ነውና! ከፊቱ በበለጠ ሁሉንም ሸክም
እንደራሳችሁ እንደእምነታችሁ ግዴታ ቆጥራችሁ ስሩ። በአንድ ቦታ፣ በቤተክርስቲያን፣ በገዳም ወይም መስሪያ
ቤት አንድ ወይም ምንም ላይገኝ ይችላልና! ለምትቀሩት ወሰን የሌለው ሸክም ቢሆንም ግድ ነውና! አቅማችሁ
እሰከሚችል መሸከም ይኖርባችኋል። የልዑል ባሮች በአምላካችሁ፣ በእናታቸውና በእናታችሁ፣ እየተመሩ
ሁሉንም እስከሚያስተካክሉ ድረስ! ሸክሙ ሁሉ የልዑል ልጆች ሁሉ ይሆናል። ከቁጣው እሳት፤ ከመጠረግ
ብዙውን የሚድኑት ህፃናት ስለሆኑ በምድሪቱ ሁሉ ከእሳቱና ከማዕበሉ የተረፋችሁ ማንኛውም ሰው የእከሌ ነው
የእከሌ ነው ሳይል፤ ሁኔታዎች እስከሚስተካከሉ ድረስ መንከባከብ ይገባቸዋል። ይህ ከልዑል የተሰጠ ግዴታና
ትእዛዝ ነው። የልዑል ባሮች ስፍራቸውን ሲይዙ ታስረክባላችሁ።

21/ በመልእክቶቹ ስርጭት ላይ ስለሚሠሩ ጥፋቶች

መልእክቶቹ እንዳይሰራጩ ለማድረግ መልእክቱ በዝግጅት ላይ መሆኑን ዲያብሎስ እንደነገራችሁ


እናውቃለን። ለዚህም ብላችሁ መልእክቱ በሄደበት አካባቢ የመልእክቱ ፈላጊ በመምሰል፣ ለመልቀም ወይም
ያሰራጩታል ያላችሁትን ሰው በሌላ ጥፋት ስም በመወንጀል ለሌላ ሰው እንዳያደርስ ለመከላከል ሌሎችም
ዘዴዎች እንደምትቀይሱ እናውቃለን። ለእሳቱም ቀርባችሁ የመጣው እሳት የማትሸከሙት ሆኖ እያለ ሌላም
ጨምርልን የምትሉ ትመስላላችሁ። ስለሆነም በዚህ ሙከራ ላይ ለምትሰማሩ ሁሉ አዛዡም ታዛዡም አንዳች
እንቅፋት ለመፍጠር ብትሞክሩ እንደሞከራችሁት ሁሉ ገና በጅምራችሁ ይህ ቅጣት ይይዛችሁ ዘንድ በልዑል
ፈቃድና ትእዛዝ በኔ በባሪያው በኩል ታዞባችኋል።

ትእዛዝ
1/ በየትኛውም ዓለም ለሚበተነው የቀደሙትም ሆነ የአሁንን መልእክቶች ስርጭት ለማደናቀፍ የሚጥሩ
ግለሰብም ይሁን ቡድን መንግሥት በጥቅሉ፣ ግለሰብና ቡድኖች በየራሳቸው ላይ የሚፀና በፍፁም የማያራምድ፤
በሰው ሁሉ የተጠላን ነገር በአደባባይ የሚያስደርግ፤ በጭንቀት በህመሙ ብዛት፤ እንደ አውሬ ሆኖ የሚያስጮህን
ጥሎም ለረጅም ጊዜ የሚያንፈራፍር፣ ዐይንንም ህሊናንም የሚያሳውር ነገር ግን የማይገል በሽታና ጨካኝ

50
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መናፍስት የተቀላቀሉበት በርባሪ እሳት ታዞባችኋል። ይህ ቅጣት በሌሎች ጥፋቶች ላይ የተገኙት እንደተጨማሪ
ይታክልባቸዋል እንጂ ይህ ቅጣት ሌላውን አያስቀርላችሁም። በተለይ መንግሥት ማን እንደሆነ እስከአሁን
የሰራውን ወደር የለሽ ጥፋቱን ስለምናውቅ በትእቢት ተሞልቶ አሁንም ባገኛት ትንሽም እስትንፋስ ጥፋትን
ብቻ የሚያልም ቀጥተኛ ዲያብሎሳዊ መንግሥት ነው። የሆነ ሆኖ እንደገና ከዚህ መልእክት መውጣት በኋላ
መደምደሚያቸውን ስለምናውቅ አያሰገርመንም። ከሚደንቀው ሥራቸው ውስጥ እኛን፣ የልዑል ባሮች እናወካን፣
እናስጨንቃለን፣ ኢኮኖሚያቸውን እንመታለን፣ በአጠቃላይ ዲያብሎስ የሰጣቸውን የቤት ሥራ ሲሠሩ ቀንም
ማታም እናያቸዋለን። በትንንሽ ጎጆአችን ዙሪያ በምንገባበት በምንውልበት ስፍራ ሁሉ መጠኑን ለመግለጽ
የሚታክት የእግረኛ ሰላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ በተለያየ ታርጋ የሚሰማሩ መኪኖች፤ በውስጣቸው የተለያየ
መከለያና ምልከታን የማሳቻ ዘዴን የሚጠቀሙ ሰዎች አሰማርተው ሰልለን ዋልን ብለው ይደክማሉ። የሆነ ሆኖ
እነሱም ሲደክሙ እኛም በሥራቸው እየተደነቅን እንደሲኒማ ተግባራቸውን ሁሉ ስናይ እንውላለን። የሆነ ሆኖ
ያለዋጋ የሚታለፍ ማናቸውም ሥራ በልዑል ፊት የለምና ሥራቸው የወለደላቸውን እነሆ በዚህ መልእክት
አፍሰውታል። አይዞህ የሚሏቸው የዲያብሎስ መንግሥትም በዚህ መልእክት ትርፋቸውን ዝቀውበታል።
በሥራቸው በነውራቸው ለሆኑ የዘመናችን ጉዶች በትንሽ የእሳት ወንፊት ሲበጠሩ ዘራፍ እንቋቋመዋለን
ብለው በትእቢት ቆመዋል። ለዚሁ ትእቢታቸው በ49 እጥፍ ተባዝቶና ያልታሰበና ያልታየ ጉልበት የተጫነው
ሁለተኛው የእሳት ወንፊት ታዞላቸው ደርሷል። ከዚህ መልእክት መውጣት ጀምሮ በሥራ ላይ ይውላል።
መልእክቱ ለጥቂቱም ደረሰው ለብዙው ሥራው ስርጭቱን አይጠብቅም፤ የሚፈለገው የመልእክቱ አድራሽ
የልዑል ባሪያ እጅ መውጣት ብቻ ነው። መልእክቱ ባሻው ይሄዳል። ቅጣቱም ወደመሰለው አቅጣጫ ይሰማራል።
በቃ!
አላደመጥክም አልተመለስክም። ጧትም ማታም ሌትም ቀንም ያለማቋረጥ ዲያብሎስ የሚወሸክተውን
ፕሮፖጋንዳ ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት ይህን አለ ያን አለ እያልክ፤ በእህል መሙላት የሚገባህን
ሆድህን በወሬ ብዛት ትሞላለህ። እውነትን የሚያወራ አንዳች መንግሰት በመላው ዓለም በሌለበት ተስፋን
ከዲብሎሶች መንግሥት ስትጠብቅ እድሜህን ጨርሰሃል። የዛሬ መንግሥታት የኛን መንግሥት ጨምሮ ሁሉም
የዲያብሎስ ደላሎች ናቸው ብንል የሚቀል ምሳሌ ነው። ደላላ አንድን ነገር ለመሸጥ ውሸትን እንደ ስልትና
ትክክለኛ መንገድ ይጠቀምበታል። ይህንንም ውሸቱን የሚሸፍንበትና የሚናገረው እውነት እንደሆነ እንዲታመንለት
ውድ ልብሶችን፣ መኪናዎችን፣ የንግግር ብሂሎችን ይጠቀማል። ለዚህ የድለላ ሥራ ጉዳቱ ያሳመማቸው ሰዎች፤
እንዲህ ብለው ገጠሙለት /የደላላ ሃብቱ ልብሱና ውሸቱ/። ዛሬም የኛን መንግሥት በስሩም ያሉትን ሁሉ
ብታዩአቸው ከዘረፉት ሕዝብ ከሰበሰቡት ገንዘብ ጥሩ ልብስ ይለብሳሉ፣ ጥሩ መኪና የተዋበ ቢሮ ይዘው ገደብ
የሌለውን ውሸት ይደረድራሉ። ለዚህ ደግሞ ጥሩ ምሳሌዎች ገዥዎቻችን ናቸው። በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ
ብለው ሁሉን እንደሚፈጽሙ፣ ሁሉን አዋቂ እንደሆኑ፣ ከነሱ የሚሰወር መላ እንደሌለ ሲናገሩ እንደ ፈጣሪ ቆጥሮ
የሚያያቸው የሚሰማቸው ቁጥሩ ብዙ ነው።
በጥቅሉ የእግዚአብሔርን ሥራ ማደናቀፍ ያለ ዋጋ ክፍያ ይታለፋል ማለት ስህተት ነው። የእግዚአብሔር ሥራ
ማንም በሥጋ ጥበብና ጉልበት ሊያደናቅፈው የሚቻል አይደለም። ሲሞክርም ቅጣቱ ይሰነዘራል።

22/ ሺ ዘመን ምን ይላል፤ ምንስ ያስረዳናል!

ሺው ዘመን በእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል።

የጥልቁን መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ።
የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፤ ሺ
ዓመትም አሰረው። ወደ ጥልቁም ጣለው አህዛብንም ወደፊት እንዳያስት፤ ሺ ዓመት

51
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

እስኪፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማህተም አደረገበት፤ ከዚያም በኋላ ለጥቂት


ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።
ከዚህም በኋላ ዙፋኖች ተዘርግተው የሰው ልጅ በላያቸው ተቀምጦ አየሁ። ስለ ኢየሱስና
ስለ እግዚአብሔር ቃል ስለ ሞቱ ሰዎች ቅን ፍርድን ፈረደለቸው። ለአውሬውና
ለምስሉ ያልሰገዱትን ምልክቱንም በግንባራቸው በእጃቸውም ላይ ያልተቀበሉትን
አየሁ፤ ከክርስቶስም ጋር ሺ ዓመት ኖሩና ነገሱ። የቀሩቱ ሙታን ግን ይህ ሺ ዓመት
እሰኪፈጸም ድረስ አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሳኤ ነው። በፊተኛው ትንሳኤ
እድል ያለው ብፁእና ቅዱስ ነው። ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ስልጣን የለውም።
ዳሩ ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ። ከእርሱም ጋር ይህን ሺ አመት
ይነግሳሉ። ሺሁም ዓመት ሲፈጸም ሰይጣን ከእሥራቱ ይፈታል። ባራቱም በምድር
ማእዘን ያሉትን አህዛብ ጎግንና ማጎግን እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያስከትታቸው
ይወጣል። ቁጥራቸው እንደ ባሕር አሸዋ የሚያህል ነው። ወደ ምድርም ስፋት ወጡ
የቅዱሳንንም ሰፈርና የተወደደችውንም ከተማ ከበቡ እሳትም ከሰማይ ከእግዚአብሔር
ወርዳ በላቻቸው። ያሳታቸውም ዲያብሎስ፤ አውሬውና ሃሰተኛው ነቢይ፤ ወደ
አሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ። ለዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ቀንና ሌሊት
ይሰቃያሉ።
ታላቅና ነጭ ዙፋን በእርሱም ላይ የተቀመጠውን አየሁ፤ ምድርና ሰማይ ከፊቱ
ሸሹ። ስፍራም አልተገኘላቸውም። ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ ፊት
ቆመው አየሁ። መጽሐፍት ተከፈቱ ሌላም መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት
መጽሐፍ ነው። ሙታንም በመጽሐፍት ተጽፎ እንደነበረ እንደሥራቸው ተከፈሉ።
ባሕርም በሱ ውስጥ ያሉትን ሙታን ሰጠ፤ ሞትና ሲኦልም በእነርሱ ዘንድ ያሉትን
ሙታን ሰጡ፤ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን ተከፈለ። ሞትና ሲኦልም በእሳት
ባሕር ውስጥ ተጣሉ። ይህም የእሳት ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው። በሕይወት መጽሐፍ
ተጽፎ ያልተገኘው ማንኛውም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣለ።
የዮሐንስ ራእይ፤ ምዕራፍ 20 በሙሉ
ከላይ ያለውን የልዑል ቃል በሚገባ ለሚያስተውለውና በእውነተኛይቱ የተዋህዶ እምነት ውስጥ ያለ ሰው
መንፈሱም የልዑል ነውና ጠንቅቆ ይረዳዋል ብለን እናምናለን። ብዙ የዘመኑ ፈላስፎችና እምነት ለበስ ካባ
ያጠለቁ ቃሉን ፍፁም በተዛባ ሁኔታ በመተርጎም “በምድር ላይ ክርስቶስ አይነግስም፤ ቃሉ የሚለው ያው
የመጨረሻ ዓለም ስትሰበሰብ ልዑል በሚሰጠው ፍርድ የዘላለም ሕይወት ወይም የዘላለም ሞት ይሆናል፤ ሁለት
ትንሳኤ የለም፤ ያው አንዱን ትንሳኤ መጀመሪያ ስናምን ስንጠመቅ የመጀመሪያው ትንሳኤ፤ ከሞት በኋላ
ሲፈረድ ሁለተኛው ትንሳኤ ማለት ነው” የሚል ቃልን በራሳቸው የምሁርነት ዲያብሎሳዊ መነጽር በመመራት
ከላይ ለነጽፅር ቃል በቃል ያስቀመጥኩትን የልዑልን ቃል አንድ ትንሳኤ እንጂ ሌላ የለም የሚል ድምዳሜ
ይሰጣሉ። ዓላማው ዛሬ በመጨረሻው ሰዓት እውነቱ መገለጫው ላይ በመድረሳችን ይህንን የተዛባ ትንታኔ
የሚሰጡን መናፍቃንና፣ ካቶሊካውያን፣ ምሁር ተብየዎች ናቸው። በቅርቡ አንዳንድ ጸሐፍት ነን፤ የተዋህዶ
እምነት ተከታይ ነን የሚሉ፤ በማህበረ ቅዱሳን ውስጥ ያሉ፤ ይህንኑ ጽሁፎቻቸውን ማህበሩ ባዘጋጀው ተዘዋዋሪ
መሸጫ ላይ ሲሸጡ በማስረጃነት ይዠዋለሁ። የፍጻሜውም ዘመን የሚል ርእስ የያዘ ነው። ፈልጋችሁ ማየት
ትችላላችሁ። ጽሁፎቻቸው የሺውን ዘመን ትንሳኤ የሚቀበሉትንና እንደ ልዑል ቃል የተረዱትን የሳይንስ ስያሜ
ይሰጡአቸዋል። በዚህ ዘመን ሳይንሳዊ ትንታኔ በእምነት ላይ አክሎ መጻፍ የዚህ ዘመን የዲያብሎስ ከእውነት
ማስወጫ ዘዴ ነው። ልብ በሉ ዲያብሎስ ወደ ጥልቁ ወርዶ ሊጠፈር ሰዓቱ ሞላ፤ እንዴት ብሎ ነው ለሺ ዘመን
ልታሰር ነው ብሎ የሚነግረን። ሙሉውን መልእክቶች ጠንቅቃችሁ ስታነቡ፤ መልእክቶቹ የያዙት እውነት ዛሬ
ሊፈጸም ስለቀረበው የልዑል መንግሥት ዘመን ነው አስረግጠው የሚነግሩን። እንደ ቀደሙት እንደ መልክቶቹ
52
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ከላይ በንጽፅር የቀረበው ቃሉም የሚያረጋግጥልን ይህንኑ ነው። ሰማይና ምድር ይሸከሙት ዘንድ ያልቻሉት
ኃያል ጌታ እንዴት በምድር ላይ ዙፋን ይዘረጋል! አብረውትስ የሚነግሱት ቅዱሳን ልጆቹ እንዴት አብረውት
ይነግሳሉ! የሚለው ጥያቄ ለብዙዎች ግር ሊል ይችላል። ልዑል ከነ ክብሩ ትሸከም ዘንድ ምድር አትችልም።
ሰማይ ዙፋኔ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ምን አይነት ቤት ለኔ ትሰራለህ ብሎ ጌታ ለዳዊት ቤትህን እሰራለሁ
ጥያቄ መልሱን በጥያቄ፤ የመለሰበትን ስናስብ፤ ለልዑል ዙፋንም ለእርሱ ማረፊያ ቤት ማዘጋጀት አይቻልም።
ቃሉ የሚለው “በፊተኛው ትንሳኤ እድል ያለው ብፁእና ቅዱስ ነው፤ ሁለተኛው ሞት በሱ ስልጣን የለውም፤
ነገር ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ። ከእርሱም ጋር ይህን ሺ ዓመት ይነግሳሉ” ይላል።
ከላይ ያለው ሙሉው ቃል የወሰድኩት ቃል፤ ካህናቱ እድለኞቹ! የተመረጡት፣ የተወደዱት፣ በእግዚአብሔር
መንግሥት ዐይን የሚታዩት እንቁዎቹ የሚላቸው፤ በምድሪቱ ላይ እግዚአብሔር አብን፣ እግዚአብሔር ወልድን፣
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ይለብሱታል። በአንደበታቸው ይፈርዳል፤ በቁጣቸው ይገስጻል፣ በፍርዳቸው
እንደፍርዳቸው ቃሉን ያጸናል። የወደዱትን ይወዳል፣ የጠሉትን ይጠላል። ቃሉን ትዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ በራሱ
በከበረው መንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ናቸውና የራሱን ፈቃድ ብቻ የፈጽማሉ።
በዚህ ሁኔታ ሺው ዘመን እስኪፈጸም ድረስ በዙፋኑ ላይ ከኒሁ የታመኑት ልጆቹ ይነግሳል። ስለዚህም
በምድሪቱ ላይ ልዑል በወደዳቸው ባከበራቸው ልጆቹ ክብር መንፈሱን አዋህዶ ይነግሳል። ለዚህ ሰዓት የሚበቁት
/ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክቶች 1፤ 2፤ 3/ እንዳረጋገጡልን እጅግ ጥቂቶች ናቸው። ዓለም 7ቢሊዮን
ሕዝብ ተሸክማለች። ነገር ግን 99 በመቶው የዲያብሎስ ተስፈኛና ተጠዋሪ ነው። ስለዚህ ስንት ሰው ለዚህ
ይበቃል። መልሱ አጭር ነው፤ እጅግ ጥቂት ሰው የታደለው /በኔ ግምት እንደ ጌታ ቁጥሩን ባላውቅም በጥቂት
ሚሊዮኖች የሚቆጠር ሕዝብ ከተረፈ በኔ ድል እንጂ ጉዳት ነው አልልም። በጌታ ግን ሊያንስም ሊጨምርም
ይችላልና! የሚጸናው የአባቴ ፈቃድና ውሳኔ ብቻ ነው።/ ስለዚህ በየዋህነት ስለ ሺው ዘመን የተዛባ ጽሁፍ
የምትጽፉ፤ የምታመጡት ጉዳት ባይኖርም ለራሳችሁ ከጥፋታችሁ ተመለሱ። ለጥፋቱ በዲያብሎስ ታዛችሁ፣
ተመክራችሁ በምሁርነት ካባ ተጀቡናችሁ ለጥፋት ለምትዳክሩ የፖለቲካና የሆዳችሁ ፍርፋሪ ያሸነፋችሁ
ደካሞች፤ በዚህ መልእክት ፍርዳችሁ ስለወጣ፤ ለማታዩት ትንሳኤ ብትጽፉ፣ ባትጽፉ የምታመጡት እንደሌለ
ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ። መልእክቱ ውስጥ ይህን ያህል ስፍራ የተሰጠው፤ ስለ ተጠራጊዎቹ ሳይሆን የልዑልን፣
የድንግልን፣ የቅዱሳን መላእክት ወዳጆችን፣ ለመጀመሪያዪቱ ትንሳኤ የታደሉትን ከናንተ ዲያብሎሳዊ አረም
ለማጽዳት ታስቦ ብቻ ነው።
ቃሉን ማሳከር የሚያነበውንም ሰው ማሳሳት፤ ለመረዳት የሚቸግረውን ሰውም ኢላማ አድርጎ የጥፋት ሥራን
መሥራት ታላቅ ወንጀል ነው። “ሺው ዓመት እስከሚፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማህተም አደረገበት፤
ከዚያም በኋላ ለጥቂት ዘመን ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።” ዲያብሎስ ለዘላለም እስከ ዘለዓለም ተጠናቆ ወደ
ገሃነመ እሳት ከመውረዱ በፊት ከፊታችን ያለውን ሺውን ዘመን በከባድ ሰንሰለት ታስሮ ያሳልፋል። እሱ ታስሮ
ብፁእና ቅዱስ የተባሉት የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይነግሳሉ። ከላይ ያለው ቃል እንደሚነግረን ይህ ፊተኛው
ትንሳኤ ለነዚህ ለታደሉት ብቻ የተሰጠ ነው። “ስለ ኢየሱስና ስለ እግዚአብሔር ቃል ስለሞቱ ሰዎች ነፍስ ቅን
ፍርድ ፈረደላቸው፡” ዛሬ ያለን ሰዎች ስለነዚህ ቅዱሳን ሰማዕታት ብዙም አንረዳም በቃሉ ተፈጭተዋል፣
ለአውሬ እንደመጫወቻ ተጥለዋል፣ ዛሬ ሁለቱም ገዳዩም ለእውነት የተሰዋውም በመቃብር ውስጥ ሲሆኑ ቅዱሳኑ
በገነት፣ ነፍሰ ገዳዮቹም በሲኦል ፍርዳቸውን ይጠባበቃሉ። ዋናውና ሁሉም ምድርም ሰማይም ተጠቅልለው
የመደምደሚያው ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት፤ ለነዚህ ሰማዕታት ደም ፍርዱ ይሰጣል። የወንጀለኞቹ፣ የነፍሰ ገዳዮቹ
ልጆችና ድርጅት ዛሬም ዓለምን እየነዱ እየፈጩ ለመሆናቸው፤ አንተም እኔም እነሆ ምስክር ነን። ይህ ሁሉ
ፍርድና አፈጻፀም የመጣው የአያት ቅድመ አያቶቻቸውን ዛሬም እየፈጸሙ ያለውን ወንጀላቸውን በቅን ፍርድ
ለመክደን፤ ከ6 ዓመት በፊት ጀምሮ የሚፈስልህን ቅን የልዑልን ፍርድ እሰከ ዛሬ በወጡት መልክቶች ስትሰማ
ቆይተሃል። ፍርድ ተሰጥቷል በተግባርም ሙሉ በሙሉ ይፈጸማል። የሰማዕታቱ ጀግኖች ደም ብድራቱም

53
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

ይከፈላል። የነሱ ፍሬ የደማቸው ዋጋ የሆኑት ልጆቻቸው የሞቱላት የተሰውላት የተዋህዶ እምነታቸው ባለድል
ትሆናለች። “ለአውሬውና ለምስሉ ያልሰገዱለትን ምልክቱንም በግንባራቸውና በእጃቸው ላይ ያልተቀበሉትን
አየሁ። ከክርስቶስም ጋር ሺ ዓመት ኖሩና ነገሱ። የተቀሩቱ ሙታን ግን ይህ ሺ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ
በሕይወት አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሳኤ ነው።”
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ፣ እነ ሰማዕቷ አርሴማ፣ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ሰማእታት ሁሉ፤ በገነት ሆነው በአጸደ
ነፍስ የልዑልን ፍርድ ሰምተዋል። ረክተውም አፈጻፀሙን እየተመለከቱ ይገኛሉ። ዛሬ የአውሬውን ምልክት
በግንባራቸው በእጃቸውም ያላደረጉ ተለይተው የልዑልና የድንግል ማህተም ተደርጎባቸዋል። እጅግ በቁጥራቸው
ትንሽ ናቸው። የነፍሰ ገዳዮቹ የአውሬው ልጆች ግን ከ6 ቢሊዮን በላይ ቁጥር ይዘው ምድርን ሸፍነው የመጨረሻ
ፍርዳቸውን በዚህ መልእክትና በቀደሙት መልእክቶች ሰምተዋል፤ እየሰሙም ነው። ባይሰሙም አይጨንቀንም
አይገደንም ነገ ለማይኖሩት! ሥራቸው ላጠፋቸው! የልዑል ቅን ፍርድ ለያዛቸው ለምን ይገደናል! ሲሄዱም
ወደ ሲኦል፤ ዓለም ከሺው ዘመን በኋላ ስትፈጸም ደግሞ ወደ ገሃነማቸው ይገባሉ። የልዑል ልጆች ደግሞ
የዛሬዎቹ ከጀግኖች አባቶቻቸው የወረሱትን የተዋህዶ እምነታቸውን ጨብጠው በአባቶቻቸው በእናቶቻቸው
ሰማእትነት ባለ እድል ሁነው ዛሬ ተመርጠው ለሺው ዘመን ሊነግሱባት እነሆ ተዘጋጅተዋል። የዮሐንስ ራእይ
20 ያስጨበጠን ታላቅ ምስጢር ይኸው ከላይ ያየኸው ነው። ከዚህ ወጪ የሚጻፈው ሁሉ በይሆናልና በራስ
ሃሳብ፤ የልዑልን ቃል እንደ ፈቀዱ በመተርጎም የሚከናወን በመሆኑ ሃሰተኛ ነው።

23/ ማጠቃለያ

ለዚህ ሰዓትና ጊዜ እንደቃሉ እንደገባልን ተስፋ፤ በእምነት እንደጠበቅነው ያደርግ ዘንድ፤ ፍርዱንም
እንደፀሐይ ያወጣ ዘንድ፤ ልዑል የሺ ዘመን ትእግስቱን ጨረሰ። ከኅዳር 7 ቀን 1998 ዓ.ም ጀምሮ ዓለም
ፍርዱን ታውቅ ዘንድ በኔ ባንድ ውዳቂ የተናቀ ባሪያው በኩል ተናገረ። እንዲሁም ደግሞ ለፍርዱም ለቅሬታም
ለንስሓም ሁሉም የአዳም ዘር ይተጋበት ዘንድ ሁለት ዓመት ተኩል፤ በትእግስት ጠብቆ፣ ቅር ላለውም፣
ለተደሰተበትም፣ በግንቦት 27/9/2000 ዓ.ም የመጀመሪያውን ውሳኔ ያጸና ፍርዱ በኔው ውዳቂ ባርያው በኩል
ገለጸ።
ከዚህ በኋላ ውሳኔው ወደ ተግባር መሸጋገሩን የሚያረጋግጥ የፍርድ አፈጻፀም ውሳኔ በመጋቢት 19 ቀን
2001 ዓ.ም አሁንም በናቃችሁት፤ በኔ ባንድ ውዳቂ ባሪያው በኩል እንዲገለጥ ሆነ። ይህ ሁሉ የሰውን ልጅ
አላስደነገጠውም፤ በቁጥር እጅግ ጥቂት ከሆኑ በስተቀር። እንኳን ለጸጸቱበት እና ንስሓ ሊገቡበት፤ በመልእክቶቹ
ማፌዝን ጨምሮ እንደ እብድ ቃል በመቁጠር ዋጋ ሳይሰጥ ቀረ።
ዓለም! ምን ይደረግ! በምንስ ቢነግሩህ ይገባህ ይሆን? ተደከመ፣ ተቆየ አልሆነም። የመጀመሪያ የእሳት
ወንፊት ቢያንስ ከእንቅልፍ ያነቃል፤ ሰው እንዴት እንደጌኛይቱ በዲያብሎስ፣ ህሊናውን፣ ጆሮውን፣ ፊቱን
ተሸብቦ ሲነዳ አይነቃም። ለኔ በግሌ ዘመኔን ሁሉ ሲገርመኝ የሚኖር ነው። የእግዚአብሔርም የትእግስቱ
ብዛት እንዲሁ ሲያስደምመኝ ይኖራል። ያም ሆነ ይህ እፍጻሜው ደርሰናል። አሁን ተመለስ አትመለስ ብሎ
የሚያነጋግረን ነገር የለም። አይኖርምም። የዚህ መልእክት መውጣት ዋናው ጉዳይ የቅጣቱን ጅማሮ ያበሰረውን
አሁንም በድርጊቱ ላይ ያለውን የመጀመሪያውን የእሳት ወንፊት የአዳም ዘር ሊደነግጥበት ሲገባ፤ የለም
በሳይንሳዊ ዘዴዎቼ /ዲያብሎስ ባስታጠቀኝ/ ብልሃትና እውቀቴ በሳይንሱም ባፈራኋቸው ቁሶቼ የመጣውን
ሁሉ እመክታለሁ፤ እየመከትኩም ነው፤ በሚል ፕሮፖጋንዳ ራሱንም መላውን ዓለምም እያደናገረ በመሆኑ
ድራማዎቹና ተውኔቶቹ ሁሉ፤ እውነት መስለው ብዙውን ሰው፤ በተለይም የእግዚአብሔርን ሕዝቦች መንፈስ
በማበሳጨቱና በማቁሰሉ፤ በትእቢቱም በጥፋቱም አንዳችም ወደ ሁዋላ ማለት ስላላሳየ ይህ ሁለተኛ የእሳት
ወንፊት ከልዑል ታዞ ወጣ። ትእቢታችሁ የልዑልን ፍፁም ቁጣ ቀሰቅሶ ከመንበሩ በቁጣ እንዲነሳ አደረገ።
ከአሁን በኋላ ይህንን ሁለተኛውን የእሳት ወንፊት የሚቋቋም አይደለም። ገና ከጅምሩ ሁሉም የሰው ዘር፤
54
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

መቆሚያና መደበቂያ አጥቶ በጭንቀትና በምጥ በሞት ጥላ ውስጥ የሚወድቅበት ነው። እንኳን በሙሉ ኃይል
መጥቶ ይቅርና! እንግዲህ ይህ መልእክት ደርሷችሁ የምታነቡ የእግዚአብሔር ወገኖች እንዲሁም ጠላቶች ለሰው
አድርሱት ይስማው ይወቀው እናንተም አገልግሎት ነውና ተባረኩበት። በልዑል ተስፋ ለጸናችሁ በጊዜያዊ
ችግር ራሳችሁን አታውኩ። ስለ ብዙ አታስቡ፤ ስለ እለቱ ብቻ ይበቃል። ምን ያደርግላችኋል። የሚሸኙት እኮ
እጅግ ብዙ ናቸው። ሁሉንም ትተውት ነው የሚሄዱት። ተለምናችሁ ነው የምትሹትን ሁሉ የምትወስዱት።
በመልካም ሰዓት ሰው እንቁ ነው። የተወደደም ነው። እንኳን ሊቸገር ሊሰጠው የሚቀበለው ያጣል። ሁሉ ስላለው
ማንም ለምንም እንደዛሬው ስለችግር በማውራትና በመጨነቅ አያሳልፍም። ዛሬም የምታዩዋቸው ተጠራጊዎች
ገንብተዋል ኮልኩለዋል በሀብት በብልጽግና ማማ ላይ ናቸው። በናንተም እየተሳለቁ! እንደፈረኦን ሰራዊት ዳግም
አታዩአቸውም። ታሪካቸው ይከደናል። ዓለምን ቀይደው የያዙት የተባበሩት መንግሥታት፣ የአውሮፓ ህብረት፣
የአፍሪካ ህብረት፣ የአረብ ሊግ፣ የደቡብ አሜሪካ ህብረት የኔቶ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት፣ የጂ ስምንት ሀገሮች፣
የጂ 20 ሀገሮች፣ ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሚባሉ ሁሉ ዲያብሎስ ደራጃቸው መጠቀሚያዎቹ ስለሆኑ
ወደ ትቢያነት ይጣላሉ። የጨነቃቸው ስለሆኑ፤ በውጪ በአገር ውስጥ በተለያየ ጎሬ የዘረፉትን ያከማቹትን
ለመሸሸግ በየዓለማቱ ሲንቆራጠጡ ታያላችሁ። የትም አያደርሱትም፤ ምድርን የሚወርሱ የእግዚአብሔር ሰዎች
ናቸውና! በባንክ ቢያኖሩትም ባያኖሩትም ባንኩም ኢንሹራንሱም ሞርጌጅ ባንኩም፤ ሌላውም መደበቂያ ሁሉ
ይዞ ይወድማል። እቤታችሁም አታኑሩት ቤቱም እናንተም ጠፊ ናችሁ። ለልጆቼ አትሉት የእነሱም እጣ
እንደናንተው ነው። ከተመረጡት ምንም ከማያውቁት ሕፃናት በስተቀር፤ ስለዚህ ፍርድህን መጠበቅ ብቻ ነው።
ለማነፃፀር በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጊዜና ከዚያ በፊት የታተመና የተፃፈውን ግዕዙንም ሆነ አማርኛውን
መጽሐፍ ቅዱስ /ሰማኒያ አሃዱ/ ብቻ ተጠቀሙ።
አስጀምሮ ላስጨረሰኝ፤ ፈቃዱንና ተእዛዙን ለሰው ዘር እገልጥ ዘንድ ከትቢያ አንስቶ ወድዶ ለላከኝ
ለእግዚአብሔር አብ፤ ለእግዚአብሔር ወልድ፤ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፤ አሃዱ አምላክ፤ በኃጢአት
ባደፈው አንደበቴ ምስጋናዬን አፈስለታለሁ!
ለእናቴ ለእናታችን ለእመብርሃን፤ ለንጽህተ ንጹሐን፤ ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ወላዲተ አምላክን
አመሰግናታለሁ፤ በሁሉም በእናትነት እቅፏ ይዛኛለችና፤
እጅግ ለከበሩት ለቅዱሳን ሊቀ መላእክቶች /ለሚካኤል፣ ለገብርኤል፣ ለሩፋኤል፣ ለፋኑኤል፣ ለዑራኤል፣
ለራጉኤል፤ ለሳቁኤል፤ ለአፍንንኤል፣ ለሰዳካኤል፣ ለሰላትያል፣ ለሱርያል፣ ለራሙኤል/ የኔ ብዬ የምላቸው
ወዳጆቼ ሁሉ አመሰግናቸዋለሁ።
ለታመኑለት እኔም ለታመንኩለት ጌታ ለቅን ፈራጁ አምላካችን ምስጋና ለስሙ ሁሌም ከፍ ከፍ ለሚለው
ክብርና ስሙ ምስጋና ከዘለዓለም እስከዘለዓለሙ ይፍሰስለት!!! አሜን!

ሃሌ ሉያ! እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት፤ በአርያም አመስግኑት፤ መላእክቱ


ሁሉ አመስግኑት፤ ሰራዊቱ ሁሉ አመስግኑት፤ ፀሐይና ጨረቃ አመስግኑት፤
ከዋክብትና ብርሃን ሁሉ አመስግኑት፤ ሰማየ ሰማያት አመስግኑት!!
መዝሙረ ዳዊት፤ 148፤ 1 – 4
አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ለማድረግ አስተምረኝ፤ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ
ምድር ይምራኝ፤
መዝሙረ ዳዊት፤ 142፤ 10

55
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አምስት

አምላኬ ንጉሴ ሆይ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ስምህንም ለዘለዓለም ዓለምም እባርካለሁ፤


በየቀኑ ሁሉ እባርክሃለሁ፤ ስምህንም ለዘለዓለም ዓለምም አመሰግናለሁ!!!
መዝሙረ ዳዊት፤ 144፤ 1 – 2

ጥብቅ ማሳሰቢያ፡–

»» ይህ መልእክት የደረሳችሁ ሁሉ በማስተዋል አንብቡት፤ ደጋግማችሁ ተረዱት፤ ቃሎቹንም ከሰማንያ


አሃዱ መጽሐፍ ቅዱስ በመመልከት ለመረዳት ሞክሩ፤ በፍፁም ለክርክር አትታደሙ!! ያ ዘመን
አልፏል።
»» በብልጠት የማያልፉት፤ በማናቸውም ዘዴ የማይመክቱት፤ እጅግ ብርቱ ጥፋትና ጠረጋ ስለመጣ የለም
ገና ነው፤ ቆይ እደርሳለሁ በሚል የተዘናጋ አካሄድ አትራመድ፤ ህሊናህ ባመነበት ሁሉ ተሰናዳ!!
»» ጾምና ጸሎት ገንዘቦችህ ይሁኑ፤ ከዘመኑ ገዢዎች የጥፋት ጉባኤና ምክር ራስህን ፍፁም አርቅ፤
በተለይ ሰባራ ምክንያት /ሥራ ነው ትዳር ነው እያልክ/ በማያድንህ ምርኩዝ አትደገፍ!! ከተችዎች፤
ከአላጋጮች፤ እናም ከዲያብሎስ ሰራተኞች ተጠበቅ!! ከእሳት እራቶች ጋር ምን እጣስ አለህ! ምንስ
ያገናኝህና!!
»» በስተመጨረሻም ሁሉንም በትእግስት ተሸክመህ እንደመጣህ ዛሬም ክንዋኔውን በትእግስት ተከታተል፤
በሺዎች መላእክት የምትጠበቅ የልዑል ልጁ ነህና! ራስህን አሕዛብ በሚለኩበት የሥጋ መስፈሪያ /
ገንዘብ፣ ሀብት፣ ስልጣን፣ ቤት፣ እውቀት፣ጥበብ/ አትለካ፤ እነርሱ ሃብታቸው ከዚህ ዓለም የገበዩት
እውቀት፤ የዘረፉት ሀብት፣ ምንዝርናው ውሸቱ ነውና አትምሰላቸው። ይህ መልእክት በውስጡ ገብተህ
እንደተመለከትከው በልዑል የተፈቀዱና የታዘዙ ቅጣቶች ለግዳጅ አፈጻጸም ስለሚወጡ፤ ህሊናህን
አረጋግተህ በትእግስት ጠብቅ የደነገጡትን በማበረታታት፤ ያዘኑትን በማጽናናት የእረኝነት ሥራህን
ተወጣ። ለዚህ ሰዓት ያደረሰህን ቅን ፈራጅ አምላክ አመስግን!! በጠላቶች የፕሮፖጋንዳ ማዕበል
ልብህ አይወሰድ! ውሸትና ምላስ ከዲያብሎስ የተሰጣቸው ትልቁ መሳሪያቸው ነውና የእግዚአብሔር
ሰው ግን በነገር ሁሉ ራሱን የገዛና ቁጥብ በመሆኑ በስሜት አትወሰድ! ይህ አምስተኛው መልእክት
የያዘው ብርቱ ትእዛዝን ነውና አፈጻጸሙ ከጀመረ የሚገኝ የእስትንፋስ ጊዜም የለምና! መልእክቱ
እንደደረሰህ ልዑል እንዳሳሰበህ ራስህን አሰናዳ!!

ተፈጸመ
ከልዑል ባሪያና አገልጋይ የድንግል ልጅና አገልጋይ የቅዱሳን የከበሩት መላእክት ወዳጅና ታማኝ

ቀን 21/1/2004 –––––––––––––
ፊርማ __________________

በመስከረም 21 ቀን 2004 ዓመተ ምሕረት ተዘገጅቶ ለአዳም ዘር ሁሉ ቀረበ!!

56
መልእክት ስድስት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ቀን 19/04/2007 ዓ.ም

በመላው ዓለም ለምትገኙ የአዳም ዘር በሙሉ!!


ይህ መልእክት ስለ ሰባተኛው መልእክት ለመግለፅና ለማወጅ የመጣ አዋጅ ነጋሪ ስድስተኛው መልእክት
ተብሎ የሚጠቀስ ነው!!

አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ!

ስማ! ልብ ብለህ አድምጥ! ላልሰማም አሰማ!


የአዋጅ ነጋሪ ቃል!

የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ ለአምላካችንም ጎዳና በበረሃ አስተካክሉ፣


ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይላል ጠማማውም
ይቀናል፤ ስርጓጉጡም ሜዳ ይሆናል፤ የእግዚአብሐርም ክብር ይገለጣል ሥጋ ለባሽም
ሁሉ በአንድነት ያየዋል የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና!!
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 40፤ 3 – 8
ከላይ በርእሱ እንደተመለከተውና ቀጥሎም በእግዚአብሔር ቃል እንደተረጋገጠልህ ዛሬ ከሦስት ዓመት
ቆይታና ትእግስት በኋላ ልዑል በሙላት መጣ!!!
ለሦስት ዓመት የተደረገው ቆይታ አኛ መልእክት አድራሾች እንደ እናንተ ፉከራ ስለጠፋን አይደለም።
የልዑል ጥበቃ ወዴት ሄዶ? ትእግስትና እድል መስጠት የእግዚአብሔር እጅ ሥራውን ተወ ማለት አይደለም፥
እንዲህ ሆኖም አያውቅም። ኃያሉ ጌታ አይደክም አይታክት ሁሌም ፈቃዱን ለመፈጸም ሁለመናው ሥራ ላይ
ነው። በቁጥር የማይደረስባቸው ኃይላት ቅዱሳን መላእክትም ያለምንም ዝንጋታ ሁሌም በሥራ ላይ ናቸው።
እኛም ባሮቹ ሥጋ ለባሽ ነንና በሰው ያለ ድካም እኛንም ቢይዘንም የቆምነው በልዑል ፀጋ ነውና፤ ብንደክም
ብንዝል ብናንቀላፋ ያኔ እንዳውም ብርቱ እንሆናለን ምክንያቱም በእኛ ድካም የልዑል ኃይልና ክብር ይገለጻልና!
የዛሬው አዋጅ ነጋሪና ዋናው አዋጅ ሊመክርህ ወይም ዛሬም ፍርድን ሊያሰማህ ወይም ደግሞ ማስጠንቀቂያ
ሊሰጥህ የመጣ እንዳይመስልህ ይህ ሁሉ ሆኖ አልፏል፤ የሰማ ሰማ የናቀም ናቀ የተፈረደበትም ፍርዱን
ተሸከመ። ለበጎው ቀን የታተመበትም ማረጋገጫውን በእጁ ከጨበጠ ሰነበተ።
በብዙ ምሳሌ በብዙ የእግዚአብሔር ባሮች ያልተደከመ ያልተፈነቀለ መንገድ የለም አንተን ለማዳን፤ አልሆነም
እንጂ ይሁንና እጅግ ጥቂቶች አምልጠዋል። እጅግ የሚበዛው ቀልጧል። ምን ይደረግ ሁሉም ነገር ማብቂያ
አለው። አበቃ!! አሁን የምትሰማው ስለመጠረግህ አይደለም ያ ተረጋግጦ ሰዓትና ደቂቃዎች እየተቆጠሩ ነው።
በማናቸውም ሰዓት ልዑል ባወቃት ጊዜ ተፈፃሚ ይሆናል።
ስለአዋጁ ከዚህ በሚከተለው መልኩ ቀርቦልሃል።
ስለምን የመጣ አዋጅ ነው? ማነው አዋጁን ያወጣው? የሚል ጥያቄ እንደሚነሳ ግልጽ ነው። አዋጁ ለአንተ
ሰማይንና ምድርን ከዘረጋ የሠራዊት ሁሉ ጌታ እግዚአብሔር ዘንድ የመጣ ነው። ሁሉን ቻይ ከሆነው እግዚአብሔር

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ዘንድ በኔ በአንድ እጅግ ታናሽና
በደለኛ በምሆን ባሪያውም በኩል ዛሬ ለአንተ የሰው ዘር /መልካሙ ሰው/ ትሰማው ዘንድ ታውጆአል!!!
አዋጅ የሚወጣው ለወቀሳና ለምክር ወይም ተው ተመለስ ለማለት አይደለም፤ አዋጅ ከአንድ የማስተዳደር
የመምራት ወይም የመግዛት ሥልጣን ካለው አካል የሚወጣ የሚገዛውንና የሚያስተዳድረውን ሕዝብ እንዲገዛበት
እንዲመራበት የሚወጣ፤ ይገዙለት ዘንድ ግድ የሆነ ሕግ ደንብና ሥርዓት ነው። ዛሬ በዓለማችን ሕገ መንግሥት
ተብሎ እንደሚጠራው ማለት ነው። የዛሬው አዋጅ እንግዳ የሚሆንብህ ሁሉን ከፈጠረ ኃያሉ ጌታ ዘንድ
መውጣቱ ነው። አንተ የለመድከው ሰዎች ጠመንጃና ታንክን ይዘው ጦር አደራጅተው ሕግ ዘርግተው ገዢህ ነን
ብለው በግድህ እንድትገዛላቸው አድርገው ስለሚነዱህ ነው።
የዛሬው አዋጅ ከየት እንደመጣ ካወቅህ፤ ዓላማው ደግሞ ምን እንደሆነ ከዚህ እንደሚከተለው ልትረዳው
ትችላለህ።
የአዋጁ ዓላማ፦ አዋጁ ለአንተ ለሰው ልጅ ከልዑል ዘንድ የተላከ ሲሆን ወደ ትንሳኤው ዘመን መሸጋገርህን
ላወቅኸው በተጨማሪም ወደሽግግሩ ዘመን ለምትደርሰውም ሁሉ ትተዳደርበት ዘንድ የሚገባ የዓለምን ሁሉ
ገጽታ የሚሸፍን የሽግግር ጊዜ ሕግጋተ ሥላሴና በዘመነ ትንሳኤው ነግሶና ከብሮ ዓለምን ሁሉ የሚያስተዳድረውን
የሚገዛውን ቋሚውን ሕግጋተ ሥላሴ መታወጁን እንድትሰማ ለማድረግ ታስቦ ነው።
አዋጁ አሥራ ሁለት ርዕሶችን የያዘ ሲሆን በ100 ገጽ የተሸፈነ ነው። ርዕሶቹም
»» መግቢያ
»» ክፉ ሰው
»» መልካሙ ሰው
»» ዕውቀትና ጥበብ፤ እምነትና ማስተዋል
»» ቀደምት ስለተገለጹት አምስት ተከታታይ መልእክቶች
»» ወደ ትንሳኤው ተሻጋሪው ሰው
»» ሥላሴን እኛ ስንረዳ
»» ቅድስተ ቅዱሳን እናታችን ድንግል ማርያምን ስንገልጻት
»» ስለተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ
»» የሽግግሩ ጊዜ ሕግጋተ ሥላሴና አፈፃጸሙ
»» የትንሳኤው ዘመን የዓለም ገዢ ሕግጋተ ሥላሴ
»» ማጠቃለያ
ከላይ የዘረዘርናቸው ርዕሶች ሁሉ በአዋጁ ውስጥ ተዳሰዋል። የሽግግሩ ጊዜ ሕግጋተ ሥላሴ በውስጡ 5
ምዕራፎችን 5 አንቀፆችን 19 ንዑስ አንቀፆችን የያዘ ነው። እንረዳ! በዚህ የሽግግር ጊዜ አዋጅ፥ ሁሉም
ሀገሮች ሁሉ ያልፉበት ዘንድ ግድ ነው። ቅድሚያ ነፃ የምትወጣው ኢትዮጵያ ስትሆን የሽግግሩም ጊዜ ሕግጋት
በኢትዮጵያ ላይ ሥራውን በመጀመር በአዋጁ ውስጥ የተጠቀሱትን ሕጎች በሙሉ ተግባራዊ ያደርጋል። በፊቱ
መሰናክልና ማደናቀፊያን አደራጅተው ለመቋቋም እንወጣለን ለሚሉት ሁሉ ከልዑል ዘንድ ታዘው ሕጉን
ለማፅናት እርምጃዎችን የሚወስዱ ቅዱሳን መላእክትና የልዑል ባሮች እንደ አልታሰበ ታይቶም ተሰምቶም
የማይታወቅ የእሳት ትንታግ ሆነው ይነሳሉ። እምነታችንና ልዑልን የናቁ፣ በዘመኑ ደርጅተውና በትእቢታቸው

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ፀንተው በሰበሰቡት የዘመነ ወታደራዊ ጡንቻቸው ታምነው ፍፁም የዲያብሎስን ሕግ አፅንተው ልዑልን ሊዋጉና
ዛሬም የጨለማ ሕጋቸውን ሊያፀኑ ለቆሙ ኃይሎች ሁሉ ከምድሪቱ ፍፁም መጠረጋቸው የግድና አይቀሬ ነው።
አዋጁም በፊቱ ያለውን ሰውኛ ጉልበቶችና ጥበቦች ሁሉ አክስሞ የልዑልን ትእዛዝና አዋጅ በምድሪቱ ተፈፃሚ
እንዲሆን ማድረግ አለበት ይደረጋልም። ይህም መወሰኑን አዋጁ ያረጋግጥልሃል።
ዓብዩ ሕግጋተ ሥላሴ በዋናነት ተፈፃሚ ይሆን ዘንድ በልዑል የፀና ሕገ እግዚአብሔር ነው። በሕጉ ውስጥ
የተዘረዘሩ 8 ምዕራፎች 50 አንቀፆች 83 ንዑስ አንቀፆች የያዘ ነው። ሕግጋተ ሥላሴ ፀንቶ የሚቆመው በፊቱ
ለዘመናቶች የተተከሉትን የዲያብሎስ የጥፋት ተክሎችን በእድሜም ያረጁትን በጥፋት ሥራቸው የገረጀፉትን
ሁሉ ከምድሪቱ ጠርጎ ካስወገደ በኋላ ነው። የቀደመው እባብና ክፉ ሥራው ፍፁም ምድሪቱን የሸፈነ ስለሆነና
ምንም አሱ ያልዳሰሰው ሥፍራ ስለሌለ በጠረጋውና በማፅዳቱ ተግባር የማይዳሰስ ሥፍራ የለም። ዲያብሎስ
ባቆመው ሥራና መሠረት ላይ የእግዚአብሔር ቤት አይታነፅም። በመሆኑም አዋጁ የመጣው ከፊቱ ያለውን
የጥፋት ዓለም የሚያፀዱ መጥረጊያዎቹን በማስቀደም ነው።
የሽግግር ጊዜ ያስፈለገው ለምንድንነው የሚል ጥያቄ ማስከተሉ አይቀርም። ይህ አግባብ ያለው ጥያቄ ነው።
ዓለማችን በጥፋት ኃይሎችና ሰራዊቶች መሪነትና የተቀናጀ የጥፋት ሥራ ሲከናወንባትና ስታስተናግድ ኖራለች።
በዚህ ሂደት ደግሞ ያልተተከለ የጥፋት ተክል የለም። የወሰደውም ጊዜ በሺዎች የተቆጠሩ ዓመታትን እንደሆነ
ማንም አስተዋይ ሰው ይረዳዋል ተብሎ ይታመናል። በመሆኑም የጥፋትን ሥራ ለመንቀልና ለማጽዳት ጊዜ
አስፈላጊ ነው።
መንቀል፣ መጥረግ፣ ማጽዳት ብቻ ሳይሆን በምትኩ መልካሙን ማብቀል፣ መትከል፣ መኮትኮት የሚካሄድበት
ወቅት በመሆኑ ይህ ሥራ በሚፈጀው ጊዜ የሚከናወነው በሽግግር ሕጉ በተቀመጠው መሰረት ይሆናል። ይህ
ከተከናወነ በኋላ ዋናው የሚጠበቀው የትንሳኤው ዘመን እንደንጋት ጮራ ልዑል በወደዳቸው፣ በመረጣቸው
ባፀደቃቸውና በባረካቸው ባሮቹ ታጅቦና ደምቆ ወደ ዘመኑ መግቢያ ንጋት ይዘልቃል። ከሽግግሩ ሂደት ወደ
ትንሳኤው ንጋት በመዝለቅ ውስጥ ታላላቅ የልዑል እርምጃዎች ይወሰዳሉ።
በዋናው ሰነድ /በሰባተኛው የአዋጁ ሰነድ/ የተዘረዘሩት ርእሶች ለባለመብቶቹ የልዑል ምርጦችና የተወደዱ
ባሮቹን ያንፁ ዘንድ፤ በሚገባ ከልዑል ቃል ጋር ተገናዝበውና ተደጋግፈው የቀረቡ ሲሆን፤ ማናቸውም
የትንሳኤው ዘመን ሙሽራዎች ሁሉ እራሳቸውን በመፈተሽ ሳያስተውሉም ሆነ አስተውለውት ነገር ግን በማቅለል
የተመለከቱትን በላያቸው ያሉና የበቀሉ ጉድፎችና እሾሆችን ነቅለው በንስሓ ራሳቸውን የሚያፀዱበትን መንገድ
ያመላክታቸዋል ተብሎ በማሰብ የተዘጋጀ ነው። ከአዋጁም ቀድመው በሰነዱ ውስጥ እንዲቀርቡ የተደረጉት በዚ
ራስን ለበጎው ቀን የማዘጋጀት ሥራን ሁሉም የልዑል ብሩካን እንዲፈጽሙት ለማድረግ ነው።
ይህን አዋጅ ነጋሪ ስድስተኛው መልእክት ሁሉም ሰው ቢያገኘውም ምንም አይደለም። የቀደሙት አምስት
መልእክቶች ማንንም ሰው ሳይለዩ ለሁሉም ይደርሱ ዘንድ የተፈቀዱና እንዲያውም ዛሬ በዓለማችን ነግሰው ያሉ
ገዢዎች ሚዲያዎች ፕሬሶች በአብዛኛው አግኝተዋቸዋል። ቢያገኙአቸውም ማንም ዋጋ ሰጥቶ ለሕዝብ አልገለፀም።
ይህ ደግሞ የሚያሳየው የማናቸውም የሰው እንቅስቃሴ ፍፁም በዲያብሎስ ቁጥጥር ሥር ያለ በመሆኑ ማንም
ስለመልእክቶቹ የተነፈሰ ሚዲያም ፕሬስም መንግሥትም እንዲሁም ድርጅትም የለም። በዝምታ እንዲያልቁ
ዲያብሎስ በመላው ዓለም ሕዝብ ላይ ከፈረደባቸው ቆይቷል። የቀደሙት መልእክቶች በተከታታይ ለአምስት
ጊዜ ሲወጡ፤ ለመላው ዓለም ሕዝብ የልዑልን ፍርድን ምክርን ማስጠንቀቂያን መጪውንም ያለውንም አደጋ
በሙሉ በማንሳት ሁሉም ሰው እንዲሰማው የተደከመበት ነው። በዚህ እጅግ ጥቂቶች ብቻ ተጠቅመውበታል
ተብሎ ይታመናል። በንቀታቸው የፀኑት ደግሞ ለዛሬው የመጨረሻ የማይሻር ፍፁም የመጠረጊያ ሰዓት ላይ
ደርሰዋል።

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

እንደቀድሞው ዛሬ ስማኝ ብሎ የሚለምንህ ወይም የሚጠይቅህ መልእክት አይደለም። ይልቅስ ሰማህም


አልሰማህም ያ ተመዝኖና ታውቆ ተለይቶ ማንነትህ በልዑል ኃይላት የመለያ ምልክት ተደርጓል። በመልካሙ
ሰው፣ ለበጎው ለትንሳኤው ዘመን ይደርስ ዘንድ በተመረጠው ሰው ግምባር ላይ ምልክት ተደርጓል። ምልክቱን
ያላገኙት በሙሉ ለታላቁ የቁጣ አሳት ቀርተው ተጠብቀዋል። የልዑል ቃልም እንዲህ ያረጋግጥልሃል።
ተፈፃሚነቱም በማያወላዳ ሁኔታ የተረጋገጠ ነውና እንዲህ ያውጅልሃል!

እርሱም እያንዳንዳቸው የሚያጠፉ መሣሪያን በእጃቸው ይዘው ከተማይቱን የሚቀስፉ


ይቅረቡ ብሎ በታላቅ ድምፅ በጆሮዬ ጮኸ፤ እነሆም እያንዳንዳቸው አጥፊውን
መሣሪያ በእጃቸው ይዘው ስድስት ሰዎች ወደ ሰሜን ከሚመለከተው ከላይኛው በር
መንገድ መጡ። በመካከላቸውም የበፍታ ልብስ የለበሰ የፀሐፊም ቀለም ቀንድ በወገቡ
የያዘ አንድ ሰው ነበረ። እነርሱም ገብተው በናሱ መሰዊያ አጠገብ ቆሙ።
የእስራኤልም አምላክ ክብር በላዩ ከነበረበት ኪሩብ ተነስቶ ወደቤቱ መድረክ ሄዶ
ነበር። በፍታም የለበሰውን የፀሐፊውንም ቀለም ቀንድ በወገቡ የያዘውን ሰው ጠራ።
እግዚአብሔርም በከተማይቱ በኢየሩሳሌም መካከል እለፍ በመካከልዋም ስለተሰራው
እርኩሰት ሁሉ በሚያለቅሱና በሚተክዙ ሰዎች ግንባር ላይ ምልክት ፃፍ አለው።
እኔም እየሰማሁ ለሌሎቹ እርሱን ተከትላችሁ በከተማይቱ መካከል እለፉ ግደሉም
ዐይናችሁ አይራራ አትዘኑም ሽማግሌውንና ጎበዙን ቆንጆይቱንም ሕፃናቶችንና
ሴቶችን ፈጽማችሁ ግደሉ። ነገር ግን ምልክቱ ወደ አለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ
በመቅደሴም ጀምሩ አላቸው። በቤቱም አንፃር ባሉ ሽማግሌዎች ጀመሩ። እርሱም
ቤቱን አረከሱ በተገደሉትም ሰዎች አደባባዮችን ሙሉ ውጡ አላቸው። እነርሱም
ወጥተው በከተማይቱ ገደሉ። ሲገድሉም እኔ ብቻዬን ቀርቼ ሳለሁ በግምባሬ ተደፍቼ
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ወዮ! መዓትህን በኢየሩሳሌም ላይ ስታፈስ የእስራኤልን
ቅሬታ ሁሉ ታጠፋለህን ብዬ ጮኽሁ።
እርሱም የእስራኤልና የይሁዳ ቤት ሃጢአት እጅግ በዝቷል፤ ምድሪቱም ደም
ከተማይቱም አመፅን ተሞልታለች፤ እነርሱም እግዚአብሔር ምድሪቱን ትቶአል፤
እግዚአብሔርም አያይም ብለዋል። እኔም ደግሞ በአይኔ አልራራም፤ አላዝንምም
መንገዳቸውንም በራሳቸው ላይ እመልሳለሁ አለኝ። እነሆም በፍታ የለበሰው የቀለም
ቀንድም በወገቡ የያዘው ሰው ያእዝኸኝን አድርጌአለሁ ብሎ በቃሉ መለሰ።
ትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ ዘጠኝ በሙሉ
አመፃንና ግፍን በማድረግ ምድሪቱን ያከረፉ የሀገራችንም ሆነ የመላው ዓለም ሕዝብ ዛሬ በመጨረሻው
ልትደመደሙ ሆነ። ምልክት ማግኘት የቻሉ ጎበዞች በእንባና በለቅሶ ዘሩ ዛሬ በደስታ ያጭዳሉ። ቅን የልዑል
ፍርድ ምንግዜም አይዛነፍም። ዳኝነቱም ፍፁም ነው። ማንም በመሸምገል ወይም ሕፃን በመሆን ከፍርድ
ማምለጥ አይቻልም ከቤቱም እንደሚጀምር በቃሉ አረጋግጧል።
ዛሬ አዋጁን እንድትሰማ ሆኖአል። አንድን ነገር በስእላዊ መግለጫ ብታየው በአካሉና በሕይወት እስትንፋሱ
ስለማታየው እድለቢስ ነህ። ምክንያቱ ደግሞ ግልፅ ነው። አንተና መሰሎችህ በጥፋት መጥረጊያው ስለምትሸኙ
ለማትኖርበት ዓለምና ሕግጋተ ሥላሴ /ሰነዱን/ ማግኘትህ ምን ይጠቅምሃል። ምንም አይጠቅምህም። ለማየትም
ሊያኖርህም የሚያበቃ ቅድስና የለኽም ስለዚህ መታወጁን ሰምተህ ለቢጤህም አሰምተህ ፍፃሜህን መጠበቅ ነው።
የዘራኸውን ነውና የምታጭደው እኛም በምርጫህ ባገኘኸው ኪሳራህ እያዘንን ከዛሬ ጀምሮ እኛም ተሰናብተንሃል።
ልዑል ተሸከመህ እስከዚህም ዘመን ታገሰህ መከረህ ገሠፀህ ቀጣህ ናቅኸው ካድከው አቃለልከው የሰጠህን ዘመን
ለበለጠ አመፅና ጥፋት አዋልከው በእርግጥ ናቅኸው ስለዚህ ዘመንህን ሁሉ የተከተለህ ፍርድ ዛሬ ሊጨርስና
መዝገብህን ሊዘጋ ከፊትህ ተሰደረ፤ የማይመለሰውን ቅጣትህን ስላየነው ነው የተሰናበትንህ!!!

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

አዋጁ ከመቼ ጀምሮ ይፀናል።

አዋጁ ለአንተ ትሰማው ዘንድ ግድ ስለሆነ፣ የተወሰነ ጊዜ ለስርጭቱ ለመስጠት ተብሎ ከዚህ የአዋጁ ኒጋሪ
መልእክት ከወጣ ጀምሮ ከሁለት ወር ያላነሰ ጊዜ የተሰጠህ ሲሆን፤ መፅናት የሚጀምረው የያዝነው ዓመት
ዓብይ ጾም አልቆ የትንሳኤን ፍቺ እንደዋለ ከሚያዚያ ሰባት ቀን ሁለት ሺ ሰባት ዓመተ ምሕረት ጀምሮ የፀና
ይሆናል። ከዚህ እለት በኋላ ከማናቸውም ጊዜና ሰዓት ጀምሮ በአገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውንም ሆነ
በመላው ዓለምም የሰፈነውን የጨለማው ዓለምና ዝግኑትሉን መጥረግና ማጽዳት ይጀምራል።
የዓለም የጥፋት ተክሎች የሊባኖስ ዛፎች አድገው ያረጁባት የገረጀፉባት መሆኗን ሁሉም ተዋናዩ የሰው ልጅ
ሁሉ ያውቀዋል። ድንጋጤህ ብርቱና እማትቋቋመውም ሊሆን ይችላል። ዓይንህ እያየ ጆሮህም እየሰማ፤ ትላንት
የምታውቃቸው ምኞትህ ተሳክቶልህ ሄደህ የኖርከባቸው የጎበኘኻቸው የተማርከባቸው አገሮች ከተሞች በእርግጥ
ነበሩ ወይ ተፈጥረውስ ነበር ወይ እስከምትል ድረስ አሻራና ምልክት ሳይተውላቸው በታላቅ ቁጣ ይጠረጋሉ።
ዛሬ ከዚህ አዋጅ መውጣት በሁዋላ ምንም ዓይነት የቅጣት ደረጃና ገደብ የለም። ሁሉም ቅጣቶች ማናቸውንም
የዲያብሎስ ሥራና ምልክቶች ፍፁም ለመጥረግና ለማስወገድ በመላው ዓለም ያለምንም እውክታ ይዘምታሉ።
ምልክት አልባ የአዳም ዘር በሙሉ በጠረጋው አብሮ ይጠረጋል በእሳቱም ይበላል።
ታላላቅ የሚባሉ አገሮች በሰው ደምና አጥንት የከበሩ በዲያብሎስ የተወደሱና የተሸለሙ ዛሬም ለድሃ አገሮች
እንደአምላክ ያህል የሆኑ፤ እንደምሳሌም ብናነሳ እነባቢሎን እነሜሪካ፣ እነእንግሊዝ፣ እነቻይና፡ አነራሺያ፤
እነፈረንሳይ፣ እነጀርመን፣ እነጃፓን፣ እነስፔን እነፖርቱጋል እነሕንድ እነስካንዲኔቪያ ሀገሮች፣ እነካናዳ፣
እነብራዚል፣ እነአውስትራሊያ፣ እነኢራን፣ እነሳኡዲ አረቢያ አነግብፅ፣ እነደቡብ አፍሪካ፣ እነእስራኤል፣
እነቱርክ፣ እነኦስትሪያ፣ እናም ሌሎችም የነዚህኑ ፈለግና መንገድ የተከተሉና በነሱም የሚታመኑ ሁሉ አብረው
ይጠረጋሉ። አንዳንዶችም እንደአገር ነበሩ ወይ የሚል ጥያቄ እስከሚያሰነሱ ድረስ ምልክትና አሻራ ሳይተውላቸው
ከምድረ ገጽ ፍፁም ይጠፋሉ።
በተለይ ለዲያብሎስ ዋናው ተጠሪና ፈፃሚ ሆነው በግንባር ቀደምትነት ዲያብሎስ በኢትዮጵያ ላይ ያዘመታቸው
አገሮች እንግሊዝን አሜሪካንን ቻይናን ሕንድን ጀርመንን የመሳሰሉ አገሮች ፍፁም ኢትዮጵያን በማጥፋት ሥራ
ላይ የተሰማሩ ናቸው። በመላው ኢትዮጵያ የተቀናጀ ዘመቻን ከሚያከናውኑ እምነቶች ባብዛኛው ዓለም አቀፋዊ
ጉልበት ካላቸው እነካቶሊክ እነፕሮቴስታንት /መናፍቃን/ እነ ዓለም አቀፍ አስልምና እና ሌሎችም ባላቸው
አቅምና ጉልበት ሁሉ በመዝመት ቤተ ክርስቲያናችን የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በመውረር ፍፁም
ሽባና የማትላወስ አደርገዋታል። አሁን እምነቱ ያለው በሕዝበ ክርስቲያኑ /በምእመኑ/ ልብ ውስጥ በመሆኑ
ሊያጠፏት አልተቻላቸውም። ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ነው። አገልጋዩ በቁሙ ሞቶ በቁጥር
ቢያንሱም ውስን ምእመናንና በየበረሃው የወደቁ አባቶች ፍፁም ፀንተው የቆሙ በመሆናቸው ለዲያብሎስ
የጉሮሮ አጥንት ሆኖበታል።
የቀደመውት መልእክቶች እንደነገሩህ ዛሬ መደምደሚያ ሰዓት ላይ ደርሰሃል። የልዑል ውሳኔ እስካሁን
ምድርን ያላነደደው ብትመለስ ብትፀፀት ተብሎ ቢሆንም አንተ ግን የበለጠ የኃጢአትና የጥፋት ማምረቻ
የጨለማ ሥራን ማዘመኛ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ቅን ሕዝቦች ፍፁም ማጥፈያ አደረግኸው። በሰጠህ ጊዜ
እግዚአብሔር እንዲፀፀት ሆኗል። ለዚህም ነው ዛሬ በዓለም ሁሉ ጣኦት የሆኑ የልዑልን ክብርና መመለክ
ለራሳቸው ያደረጉ ሁሉ ምን ትልቅ ቢሆኑ ከምድረ ገጽ እንዲጠፉ የታዘዘው።
በመላው ዓለም ታላላቅ መንግሥታት የተባሉ ነገር ግን ፍፁም የዲያብሎስ አገዛዝና መጽሐፈ ጽልመትን
ያነገሱና በሱም እየተመሩ ያሉ የሚያመልኩትም ምን ምክንያት ሊሰጡ ይቻላቸዋል? ምለው ተግዝተው
ለዲያብሎስና ለፈቃዱ ተገዝተው ሊኖሩ ወስነው ረጅም እድሜን አስቆጥረዋል። ልዑልን ያስቀኑትም ዘንድ ለልጅ
ልጆቻቸው ክህደትን ዲያብሎስን እንደትክክል እምነት ሲያወራርሱ ኖረዋል። በሱም በመፅናት በማናቸውም
5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

የዓለም ገጽታና ፊት ሕጉን አፍርሰው ስርአቱንና ፈቃዱን አቃለውና ንቀው በምትኩ የዲያብሎስን ድርሰት
አፅንተዋል።
ደፋሮቹና በንቀትና በትእቢት የተሞሎት በአገኙትና በጨበጡት ዲያብሎሳዊ እውቀት ፍፁም ታምነው
የጥፋት አዝመራን ሲያዘምሩ ይውላሉ ያድራሉ። ልዑል በፀባኦት በመንበሩ ሆኖ ይስቅባቸዋል። ቀናቸው ማለቅና
መቆረጡን ስለሚያውቀው። ዛሬ ታላላቅ ተራሮች ናቸው፤ ነገ ግን አቧራና ብናኝ ትቢያ ናቸው። ከምድር ትቢያ
የተፈጠረ በከበረው መንፈስ ላይ ሲታበይ! እንዳልነበረም አድርጎ ፍፁም ሲክድ ከዚህ በላይ ምን ዓይነት ወንጀል
ሊወዳደረው ይቻላል? ልዑል ቅን ፈራጅ፣ እውነተኛ ዳኛ ነው። በፍርዱ ሕፀፅ የለም ኖሮም አያውቅም። ልዑል
ባህሪው ፍፁም እውነት ብቻ ነው። ሁሉ በራሱ የተፈጠረ ስለክብሩም ይሆን ዘንድ የሚኖር ነው።
ማናቸውም ፍጥረት በልዑል ትእዛዝና ፈቃዱ ላይ አንድም ግዜ ወጥተው ከመንገዱም ስተው አያውቁም።
ሁሌም በተሰጣቸው ስርእትና ሕግ የሚጓዙ ናቸው። ሰው ግን ፍፁም ሕግና ትእዛዙን በመናቅና በማፍረስ
ተወዳዳሪ አልተገኘለትም። እንዲያም ሆኖ ቸሩ አምላክ ትእግሥትን ምን ያህል ገንዘቡ አንደሆነ ዛሬ እኛ
ባሮቹ እየመሰከርን ነው። እራሱም ፍቅር መሆኑን ለሰው ልጅ በመታገሥ ብቻ ሳይሆን እስከሞት በመውደድና
ፍቅሩንም እስከ መቃብር በመውረድ አሳይቶናል። ታዲያ ይህን ያወቁ ልጆቹ በአመፀኞች ሰፈጩ ሲቆሉ ልዑልን
ስለትእግስቱ ቢደንቃቸውም በዛው ልክ ደግሞ ዳኝነቱን ፍትህን እንዲሁም ንፁህ ደማቸውን በቅን ፍርዱ
እንዲያካትት ዘወትር በእንባና በጩኸት ከመጠየቅ በርከው አያወቁም።
የትንሳኤው ዘመንም የቅን ፍርዱና የፍፁም ዳኝነቱ ውጤት ነው። ለዚህ መድረስ የተገባቸው ባሮቹ ደግሞ
ቀድምም በሱ ዘንድ የታሰቡ ናቸው። ስለሆነም ዛሬ ባሮቹን ሊክስ ሊባርክ፤ ወንጀለኞችን በደለኞቸን ወደ ሲኦል
ሊልክ ዛሬ በሙላት መጣ! መድሃኔዓለም አባታቸን እናቱንና እናታችንን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግልን አስከትሎ
በቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ታጅቦ ፍርድን እንደ ፀሐይ ሊያመጣ እነሆ ደረሰ!
እኔም አንድ ምናምንቴ ባሪያው ዛሬ የሰማኸውን አዋጅና አዋጅ ነጋሪውን መልእክት እንዲሁም ለዘጠኝ
ዓመታት ስትሰማና ስታደምጥ የቆየኸውን 5 መልእክቶች ሁሉ ላንተ ለሰው ዘር አስተላልፍና እነግር ዘንድ
የተሰጠኝን ትእዛዝ፡ በአቅሜ ልክ ልዑል እንደሰጠኝ ጉልበት መጠን ላደርስልህ ጥሬአለሁ ለእንደኔ አይነቱ
ደካማና ታናሽ ባሪያው ይህንን የከበደ ኃላፊነቱን ቢጭንብኝም በራሱ አከናወኖታል ብዬ አምናለሁ። ስሙ
የተመሰገነ ይሁን።
እንግዲህ ከአዋጁ መወጣት በኋላ መጪው ጊዜ እጅግ አስጨናቂ እንደሚሆን ይታመናል። በልዑል ታምናችሁና
ተወዳችሁ በእንባችሁ ዘርታችሁ በደስታ ልታጭዱ የተገባችሁ ስለሆነ ከታመናችሁለት አምላክ የተሰጠ እድል
ስለሆነ በውጣ ውረዱ የሚያስጨንቃችሁ ነገር የለም። ምልክት አልባ የሆኑት ደግሞ በደስታ ዘርተዋል ፍሬውንም
በልተው በአመፅ ትርፋቸው ተደስተው ኑረዋል ዛሬ ደግሞ በዚህ የልዑል ቅን ፍርድ ሊካተቱ ግድ ስለሆነ በእንባ
ጥርስ በማፋጨት በሽሽት በመፍረስ በመሞት በመጠረግ በእሳት በተለያዩ መቅሰፍቶች ሊከደኑ ግድ ስለሆነ
ትርፋቸውን ማፈስ ይገባቸዋል።
አዋጁ እራሱን ለማፅናት ብዙ እርምጃዎችን ስለሚወስድ በፊቱ እሳትን የለበሱ የእሳት ትንታግና ማዕበል
የሆኑ አንዳች ኃይል የማይቋቋማቸው ቅዱሳን መላእክትና፤ ቀሳፊ መላእክት እንዲሁም ከልዑል ኃይልን የተላበሱ
ምርጥ እቃዎቹ በተጣመር ለእርምጃው ይዘልቃሉ።
አዋጁ ከኢትዮጵያ መነሻውን አድርጎ በሽግግሩ ሂደት ውስጥ የሚነቃቀለውን የሚጠረገውን የሚፈርሰውን
ሁሉ ከነግሣንግሱ በማስወገድ በአኳያውም የሚተከለውን በመትከል የሚስተካከለውን በማሰተካከል ብርሃናዊውን
ዓለም በማዋለድ የሽግግር ጊዜ ሕግጋትን በመጠቀምና በማጽናት በኢትዮጵያ ብርሃናዊውን አገዛዝና የልዑል
ሥርዓት በፀና መሰረት ላይ መትከል አለበት። በሂደት በአዋጁ እንደተመለከተው ለዋናው ሕግጋተ ሥላሴ
ጥርጊያውን በመፈፀምና በማስተካከል ዋናውንና የትንሳኤውን ዘመን ማልዶ መውጣትን በማስረገጥ አስረክቦ
6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

የሽግግሩ ጊዜ ሕግጋት ሥራቸውን ይጨርሳሉ። ይህ ሂደት በሌሎችም የዓለም ገጽታዎች እንደልዑል ፈቃድና
ትእዛዝ ተፈፃሚ ይሆናሉ።

የኢትዮጵያ ሃገራችን ወቅታዊ ሁኔታ!

ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ በብርቱ ፈተና ውስጥ እንዳለች ሁሉም ስለሚያውቀው እንግዳ የሆኑትን ሁኔታዎች
እንመለከታለን። ዓለም የሚደመምበት ፍፁም የአውሬን ባሕርይ የተላበሰ ገዢ ኢትዮጵያን ቀይዶ ይዞእታል።
የሰው ሕይወት ፍፁም ዋጋ አጥቷል። ሰው ይኖር ዘንድ የሚያስፈልጉት መሰረታዊ ፍላጎቶቹ፤ እንደ መጠለያ፣
እንደ ምግብ፣ ሥራ፣ ልብስ እነዚህ አንድ ሰው ይኖር ዘንድ የሚያስፈልጉት መሰረታዊ ፍላጎቶቹና በአለው
መንግሥት ይሟሉለት ዘንድ የሚገባ ግዴታዎች ናቸው። ይህንን ያልተወጣ መንግሥት በምንም መስፈርት
መንግሥት ነው ለማለት አይቻልም።
በዚህ መነሻነት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ ፍፁም የተቃረነ ነው። በመላው አገሪቱ ያለው ሕዝብ
በጣት ከተቆጠሩ የአንድ መንደር ልጆች በስተቀር በረሃብ፣ በሥራ ማጣት፣ በበሽታ፣ በስደት፣ በመኖሪያ
እጦት፣ በዘር ልዩነትና ግጭት ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ የኑሮ ውድነት፣ በተለይ የተዋህዶ እምነት
በመከተላቸው በአማራ ዘርነታቸው ተለይተው መንግሥት በሚያቀናብረው ጥቃት የተመቱ የሞቱ የተጠረጉ
ቤታቸው ንብረታቸው የፈረሰባቸው የተወረሰባቸው፣ በልማት ስም ከዋናው ከተማም ሆነ ከገጠሩም ቤታቸው
ንብረታቸው መሬታቸው የተነጠቁ የተባረሩ ቤታቸው ይቁጠራቸውና በፍርደ ገምድል ፍርድ በየወሕኒ ቤቱ
የተጣሉ እነዚህ ሁሉ በኢትዮጵያ የነገሱ ስር የሰደዱ ችግሮች ናቸው።
ያለው መንግሥት እንደመንግሥት የማያስብ፣ ስለዜጎች ምንም የማይገደው በአንድ መንደር ስሜት አእምሮው
የተሸፈነ በመሆኑ ከአነዚህ ምንም የሚገኝ ትርፍ እንደሌለ ሁሉም የተረዳው ይመስለኛል። በሁሉም የሕይወት
ገጽታ የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ የመላው ዓለም ሕብረተሰብ በታላቅ ቀውስ ውስጥ መውደቁን ሁሉም ያወቀው
እውነት ሆኗል። መፍቻ የጠፋለት የምናየውና እያለፍን ያለንበት መከራ ብርቱ እሳት ሆኖ እየበላ ነው። በኑሮ
ውድነት እሳት፣ በበሽታ እሳት፣ በሰላም ማጣት እሳት፣ በመኖሪያ ማጣት እሳት፣ በስደት እሳት ሌሎቹም
እሳቶች ቁጥራቸው የበዛ ሰውን እንደአሻሮ እየቆሉት ነው።
ይህ ሁሉ የሆነው የቀደሙት መልእክቶች አንደነገሩህ ደረጃ በደረጃ የቅጣት ማእበሉና እሳቱ እየጨመረ
ይሄዳል አንጂ አይቀንስም። ይህ እንደማይሆን ደግሞ ሁሉም መልእክቶቹ አረጋግጠውልሃል። ከደረጃ አንድ
ተነሰቶ በሰባት እጥፍ እየተባዛ እሳቱ ይጨምራል እንጂ የዛሬ ገዢዎች /በመላው ዓለም ያሉ ሁሉ/ እንደሚሉት
ባለን እውቀት ጉልበት ገንዘብ ሀብትና ዘዴዎች ሁሉ ተጠቅመን እንቋቋማዋለን በማለት፣ ዓለምን ከድኖ በያዘው
ሚዲያና ፕሬሳቸው እንዲሁም ፕሮፓጋንዳቸው ሲለፍፉ ይውላሉ ያድራሉ። ዛሬ ማንም የማይክደው እውነት
አለ። በመላው ዓለም ያለው ሕብረተሰብ የቁርስና የምሳው ያህል ወሬንም ከገዢዎቹ እንዲፈስለት የሚወድና
የለመደም ነው።
የልዑል ቅጣት ለምን በረታ የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም። ለነዚህ ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ጥቂቱን
ብናነሳ፦
በመጀመሪያ የሚወርደው እሳት የልዑልን ልጆች /ወርቅ/ በእሳት በተደጋጋሚ እንደሚቀቀልና እንደሚጠበስ
እነሱንም በእሳቱ ውስጥ እየነጠሩ እንዲወጡ ለማድረግ ታስቦ እየተፈፀመ ያለ ነው። ብርቱና የማይበገሩ እንዲሆኑ
ለማድረግ ስለሚያስፈልግ! ለመጪው የትንሳኤው ዘመን የበረቱና በተዋህዶ እምነታቸው የፀኑ ኃላፊነትን
በቅንነትና በታማኝነት ሊወጡ የሚችሉ አገልጋዮችን ለማነፅም ነው። የልዑል ዩኒቨርሲቲና ትምህርት አሰጣጡ
የሚከናወነው አንደሥጋው ዓለም በአንድ ቤት ውስጥ በወንበር ላይ ተቀምጦ ከፊትም አንድ መምህር ተሰድሮ
በሚሰጠው አንድና ሁለት ሲደመር ሲቀነስ በሚል አይደለም። የእግዚአብሔር ትምህርት ቤት ከጥቃቅኗ የእለት

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ከእለት የኑሮ ውጣ ውረዳችን ጀምሮ እስከ ትልቁ ፈታኝ የሕይወት መቸገር መራብ መጠማት መሳደድ መታሰር
መፈተን የሚጨምር ነው። ዩኒቨርሲቲው እንዲህ ነው። በዚህ እሳት እየለበለበና እየጠበሰ ወርቁን የተዋህዶ
አርበኛ ያወጣል። የብቃት ማረጋገጫው የሚሠጠው ምድርና ሰማይን ከዘረጋው የሰራዊት ጌታ እጅ ሲሆን የፍቅር
ማረጋገጫዋን የምትሰጠው ደግሞ ድንግል ናት አቅራቢዎቹ ደግሞ ሊቃነ መላእክቱ እነሚካኤል እነገብርኤል
ናቸው።
የዚች ዓለም የትምህርት ቅኝት ለሥጋው ለሥጋው የሚል ነው። የእግዚአብሔር ትምህርት ቤት ግን መንፈሳዊነት
ይቅደም ሥጋ ለመንፈስ ይገዛ የሚል ነው።
ሁለተኛውና የማያቋርጠው እሳት ደግሞ እምቢ ብለው በእሳቱ እየተለበለቡ መፍቻ ዘዴ ሲያጡ በግድ
ተሰንገው የጠፉበትን መንገድ ተረድተው ወደ እውነተኛይቱ እምነታቸው እንዲመለሱ የሚያደርግ ነው።
በሦስተኛው ምከንያት እሳቱ የሚለበልባቸው ደግሞ እነዚህ የማይመለሱ ሁሌም ከዲያብሎስ መዝገብ /
መፅሐፈ ጽልመት/ መፍትሄ የሚሹ በመሆናቸው እየሞቱም ከከደናቸው የጨለማ መንገዳቸው ስለማይመለሱ
በዚያው የሚያከትሙ ናቸው።
ቤተ ክርስቲያን፤ የተዋህዶ ቤታችን ፍፁም በዲያብሎስ ተወራለች። በውስጧም ለዲያብሎስ አገልጋይ የሆኑ
ወርሰዋታል። ሁሉም አንዱ ቅባት ሌላው ፀጋ አንዱ ደግሞ ተሃድሶ፣ እንዲሁም መናፍቅ፣ ካቶሊክ በሚል
ዶግማ ወጥረው ይዘዋታል። ሁሉም መለያቸው ደግሞ አንድ ለአምስት በሚል የዲያብሎስ አገልጋይ መንግሥት
ባዘጋጀው መረብ የተተበተቡ መሆናቸው ነው። የመንግሥት ተብዬው አባል ያልሆነ የለም ቢባል ይቀላል።
መጪው ጠረጋ የሚከብደው ሂያጁ ስለሚበዛ ነው። ተራፊው እጅግ ጥቂት ነው የሚባለውም ያለምክንያት
አይደለም።
ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የሚሳተፉ ሊያውቁት የሚገባ ቢኖር ቅዳሴው ማሕሌቱ ኪዳኑ ሁሉ ከቤተ ክርስቲያኑ
ጣሪያ እንደማያልፍ ነው። ሊያውቁት ይገባልና እንዲያስተውሉ ይመከራሉ። ምክንያቱ ሺ ጊዜ ተነግሯል።
አልስማ ላለ ሲያይና ሲሰማ ቅበረው እንደሚባለው ተረት ይሆንባቸዋል። በቤተ እምነታችን ውስጥ የተሰገሰጉት
የዲያብሎስ ተጠዋሪዎች ጌታን ሰቅለው ቁሰሉን የሚወጉ ናቸው። ጨለማ ከብርሃን ጋር ምን ሕብረት አለው
ዛሬ መስዋእታቸውን ከዲያብሎስ አገልጋዮች ጋር ቀላቅለው መስዋእት አቀረብን አስቀደስን የሚሉ ሁሉ ጌታን
ከአመፀኞች ጋር ሰቅለው ቁስሉን የሚወጉ አንደሆኑ ይወቁ! በግላቸው እንደኤልያስ መስዋእታቸውን ማቅረብ
ይችላሉ። ለዲያብሎስ እጅ ከሰጡ ጋር ከሱም ፍርፋሪ ከሚለቅሙ ጋር የፖለቲካው ታማኝ ከሆኑ ዲያቆናትና
ቀሳውስት ጋር አብሮ የሚደረግ ጸሎት ማረፊያው ከዲያብሎስ እጅ ነው። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ስትሄዱ በግል
የግል ፀሎታችሁን አድርሱ አሊያም ሰላም ለኪ እምዬ ቤተ ክርስቲያን አምሳለ እየሩሳሌም ብላችሁ ተሳልማችሁ
ተሰማሩ! በቂ ነው።
አንድ ምሳሌ እንውሰድ
የብርሃን ሠራዊት የሆኑ ለውጊያ የተዘጋጁ በስተቀኝ ግንባር ሲሰለፉ በስተግራ ግንባር ደግሞ የጨለማ
ሰራዊቶች ተሰልፈዋል። በሁለቱ መሃል የተተወ የፈሪ ምድር የሚሉት ሥፍራ አለ፤ በሁለቱ ሀይላት እንፃር
ድጋፍ የሚሰጡ ወይም የሚተባበሩ ስፍራቸውን ከየሚደግፉት ሰራዊት ጎን ቆመው ውጤቱን ይጠባበቃሉ።
አንድ እንግዳ ነገር በፈሪው ምድር ላይ ይታያል። ውስን ቁጥር ያላቸው ሰዎች በዚያ በተተወ ምድር ላይ ወደ
ሥራቸው ይሄዳሉ ውለውም በዚያው ይመለሳሉ። በማናቸውም ሰዓት ውጊያ በሚነሳበት የውጊያ ወረዳ ላይ
የሰላም ቀጠና ሳይሆን በነዚህ ሰዎች ግን ምንም የማይከሰትበት ምድር ነው ብለው ያምናሉ። ውጊያው ሲነሳ ግን
ከማንም በላይ አደጋ ውስጥ የሚወድቁ እነዚህ የዋሃን አለአስተዋዮች ናቸው። ዛሬ በቤተ ክርስቲያን ለቅዳሴወም
ለኪዳኑም ማልደው የሚገኙ ሰዎች በቅንነት የሚያደርጉት ቢሆንም ከዚህ አዋጅ መውጣት በኋላ ከሥፍራው
ራሳቸውን ቢያርቁና የግል ፀሎታቸውን በቤታቸው ቢያደርጉ መልካም እንደሆነ ይመከራሉ።
8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

የእግዚአብሔር እርምጃ የሚጀምረው ከቤቱ መሆኑን ሁሉም ሊያስተውሰው ይገባል። በተለየ ሴቶች አናቶች
ቤተ ክርስቲያን የሚሄዱት የእልልታ ጥማታቸውን ለማርካት ይመስላል። የዲያብሎስ ጭፍሮች ገንዘብ ሲሰበሰቡ
እከሌ በዚህ ምክንያት ይህን ያህል ብር ሰጠ እልል በሉ! እልል! ቤተ ክርስቲያንን አፍርሰን ልንሠራ ነው
እልል! ወዘተ የእልልታ ሰራዊት አስነዋሪ ትውልድ የጠፋ ሰው ልንል እንችላለን።
ታላላቅ ገዳማትን አፍርሰው አባቶችን ደብድበው አስደብድበው ገለው እሳስረው እንደዋልድባ የመሳሰሉትን
ገዳማት አፍርሰው ዛሬ ደግሞ እልል በሉ ሲሏችሁ እልል እምትሉ ቤተ ክርስቲያንን አስፈርሰው የተጉ አባቶችን
ደብድበውና ገለው አስረው የመጨረሻ የተዋህዶ አባቶች መካተቻና ወደ ፈጣሪ መሰብሰቢያ የሆኑትን ገዳማት
ፍፁም አፍርሰው እነዚህ በነገሱበት ቤተ እምነት አብረው እንቀድሳለን እናስቀድሳለን የሚሉ ስለእውነተኛይቱ
ተዋህዶ የሞቱትን የተጋዙትን የታሠሩትን ንቆ ለከሃዲው እምነት አልባው የአምልኮ ባእድ አምላኪው ከቆሙ
የቡኤል ዘቡኤል የዘመኑ ካህናት ጋር መሰለፍና አብሮ መስዋእት ማቅረብ ለማን ክብር ነው? ለዲያብሎስ ብቻ
ነው። በቤተ ክርስቲያን የስለላ መዋቅር ዘርግቼ በሚገባ እየተቆጣጠርሁ ነው የሚለው ስሙን እንኳን ማንሳት
የሚቀፍ ዲያብሎሳዊው መንግሥት ለዚህ ካደሩለት ሰራዊቶቹ ጋር መሰለፍ ማለት ምን ማለት ነው? በቃ!
ከሥፍራው እንዳትገኝ አስጠነቅቅሃለሁ።
የዚህ ጉደኛ የኢትዮጵያ መንግሥት ተብዬ አባል የሆናችሁ ከማናቸውም ጥቅማችሁ ወይም ጭፍን ስሜት
ተነስታችሁ የምትደግፉት በዘረኝነት የተተበተባችሁ በተለያየ ዲያብሎስ በደረሰውና በፈጠረው እምነት
ውስጥ ያላችሁ ሁሉ መጥረጊያው የማያልፋችሁ መሆኑን ላሰገነዝባችሁ እወድዳለሁ። አይቀሬ መሆኑንም
አረጋግጥላቸኋለሁ።
ኢትዮጵያና ተሰዳጅ ወገኖቻችንን ስናስብ ደግሞ እጅግ የሚያም ውርደት ሆነ፣ በዛሬው ወቅት በተለይ
በሳኡዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የተፈፀመው ግፍና በደል ማንም ኢትዮጵያዊ እጅግ የሚያመው አንደሆነ
በግልፅ አይተናል።
ብዙዎቹ ወገኖቻችን በአሁኑ ወቅት በሳኡዲ ብቻ ሳይሆን በሌሎቹም ሀገሮች በተለይም በአረብ ሀገራት ሃበሻ
ጠላታችን ነው ብለው የሚሠሩት ግፍ ወሰን አጥቶእል። ዓለም በየትኛውም ሥፍራ የሃበሻን መበተን መስካሪ
ናት። ይሁንና እንደ ከፉ ጠላት /እንደ እባብ/ መቀጥቀጥ በምን ምከንያት ይታለፋል በምንም አይታለፍም።
እዚሁ ላይ ላረጋግጥላችሁ የምወድደው በሺ እጥፍ ዋጋ ትከፍሉበታላችሁ። ይህ ፍፁም የማይቀር ነው። የልዑል
ባሪያ ይህንን ተናግሬአችኋለሁ።
የእግዚአብሔር ባሮች ይህን ሁሉ ግፍ በየባእታቸው ሆነው በቁጭት እያዩት ነው። መንስኤው በኛ እምነት
ምሽግና መጠለያ የምትሆናቸውን አንዲቷን የተዋህዶ እምነት ጥለው ከሥጋ ገበያ መፍትሄ ሲፈልጉ የተጎዱ
መሆናቸው ግልፅና የማያሻማ እውነት ነው።
በኢትዮጵያዊነት ላይ በተዋህዶ እምነት ላይ የዘመታቸሁ የዓረብ ሀገራት ሁሉ እናንተም፣ በመላው ዓለም
ያለውም የዘመኑ ትውልድ ሃበሻን /ኢትዮጵያዊ/ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን ባነሱ ቁጥር፣ እጅግ እንደሚጠሉን
እናውቃለን። ግን ዛሬ ልናበሥራችሁ እንወዳሰን መጪው ዘመን የእኛ መሆኑን በመቃብራችሁ ላይ ታላቂቱ
ኢትዮጵያና ተዋህዶ እምነቷ በመላው ዓለምም ፀንቶ እንደሚቆም እወቁ! አዋጁም ይህንኑ ሊያበስርና ሊገልፅ
የታወጀውንም ሕግጋት ሊያፀና እጅግ ብዙዎች ጠላቶቻችን ከምድረ ገጽ ሊጠራርግ በታላቅ የእሳት ማዕበልና
ጎርፍ ተጭኖ መጥቶልሃል። ማማምለጫ የለም መሸሻ መደበቂያ በምድር ላይ የለም። በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራትም
ተመሳሳይ ግፍ ይፈፀማል። እንደነጂቡቲ አንደነሱዳን እንደነኬንያ የመሳሰሉ ሀገራት ኢትዮጵያዊውን እንደውሻ
በመቁጠር ባለበት በደረስበት አያነቁ ለሚገለው መንግሥት ሲሰጡትና ሲያጠፉት እያየን ነው። እናንተም ካለው
ዲያብሎሳዊ የኢትዮጵያ መንግሥት ጋር አብራችኋልና አብራችሁ ትከደናላችሁ። ትጠረጋላችሁም፤ ይህ ሁሉ
በደል ሲፈፀም ከምንም ያልቆጠረው የኢትዮጵያ መንግሥት ተብዬው በየበረሃ ለወደቁት በባሕር ለሰጠሙት

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

በአረብ ሀገራትና በአፍሪካ ሀገራት በእኖራለሁ ጥረት ወጥተው ለቀሩት ሁሉ ሙሉ ኃላፊነትዋን ይወስዳታል።
እነሱ በአመፅ አልፈዋል። የቆመው መንግሥትና ከጀርባው ሆነው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ያደረጉለት እያደረጉለትም
ያሉ ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት የተዋህዶ እምነታችን ጠላቶች ሁሉ ልብ በሉ ልብም አድርጉ
እስከዛሬ የሰፈራችኋት ግፍና በደል በሺ እጥፍ ትከፍሏታላችሁ የልዑል ባሪያ ይህንን አረጋግጥላችኋለሁ። ቃል
ወጥቶእል ተፈፃሚነቱ እንዳይቀር ደግሜ በልዑል ሥም አረጋግጥላችኋለሁ።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሰላማዊ ተቃሚዎች ጦር የጨበጡ ተቀዋሚዎች ሁሉም በድምሩ ያለውን መንግሥት
ሊጥሉ እየደከሙ ለመሆናቸው እየሰማን ነው። በዓላማቸው ዲሞክራሲን እናሰፍናለን የሚሉ ናቸው። ይህ
ፍልስፍና ከእውነተኛው የተዋህዶ እምነታችን ጋር ፍፁም የማይገናኝና የሚፃረር ነው። ዲያብሎስ ያረቀቀው ይህ
ድርሰቱ ሁሉም ሃይማኖቶች እኩል ናቸው የሚል አባበል ያለው ሲሆን ሶዶምነትንም እንደመብት ከሚቆጥሩት
ምእራባውያን ጋር የተመሳሰለ ነው። ብዙ ቅኖች በዚህ ውስጥ ተሰላፊ ሆነዋል። ለኢትዮጵያ አገራቸው ያላቸውን
ቀናኢነት ስለሁሉም ተቃዋሚዎች አክብነሮት ቢኖረንም በተለይ በሰላማዊ ትግል የተሰለፉት ውስጥ የሚበዙ
ሆድ አደሮች እንደሞሉበት የሚታወቅ ነው። ዛሬም በሕዝብ መከራ የሚነግዱ ከለየለት አውሬው ገዢ ቡድን ጋር
በሕዝብ ደም የሚነግዱ ሁሉ መማረፊያቸው ቀለብ ከሚሰፍርላቸው መንግሥት ተብዬ እንደማይለይ ሊያውቁት
ይገባል። ሌሎች ደግሞ በበረሃ ጠብመንጃ ተሸክመው ሕይወታቸውን ሊሰው ለወደዱት ስለወገንና አገራቸው
ኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር ብናከብርም የሁሉም ዳኛ ልዑል እግዚአብሔር ለሁሉም እንደመንገዱና እንደቅን
ልቡናው ስለሚፈርድ የሚያምናቸውን የወደዳቸውን ያከበራቸውን ልጆቹን ሲያነግሥ ሁሉም በየእጣ ክፍሉ
ይቆማል። በዚህ ጉዳይ ከዚህ የዘለለ ሊባል የሚችል ነገር የለም ሁሉንም የሚለየው የልዑል ቅን ፍርድ ብቻ
ስለሆነ!
ልዑል እንዲህ ብሏል፦

በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ።


በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች። ወደ እርሱም እየመጣች ከባላጋራዬ
ፍረድልኝ ትለው ነበር፤ አያሌ ቀንም አልወደደም ከዚህ በኋላ ግን በልቡ ምንም
እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር ይህች መበለት ስለምታደክመኝ፣ ሁልጊዜም
እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። ጌታም አለ – ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን
ስሙ። እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ለሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሳቸውም
ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? እላችኋለሁ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው
ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?
የሉቃስ ወንጌል ም 18 ፥ 2 – 8
ከላይ የልዑልን ቃል ልብ ብላችሁ ተመልከቱ፤ በዛሬው ዘመን ወንጀለኛ ዳኞች በመላው ዓለም በፍርድ ወንበር
ተቀምጠው ፍርደ ገምድል ዳኝነታቸውን ሲሰጡ እንደሚውሉ እንደሚያድሩ በግልፅ እንረዳለን፤ እግዚአብሔርን
አያምኑም አይፈሩም ይልቅስ በወንበሩ ላይ የጎለታቸውን የፖለቲካና ጠመንጃ የጨበጠ ባለስልጣንን ይታዘዛሉ
ያከብራሉ። የሆዳቸው ጌታ ስለሆነ፤ በዛሬው ዘመን በአገራችን የነገሱ ዘረኛና ፍፁም አጥፊ ገዢዎች በዚች
አገራችን ላይ እየሠሩ ያሉትን ግፍ የተሸከመው ሕዝብ ያውቀዋል። ይህ ሁሉ እየሆነ ደግሞ እውነተኛ
የእግዚአብሔር ምርጦች እግዚአብሔርን ፍረድልን ብለው ይጮሃሉ ያነባሉ። ይህንንም ዛሬ በአገራችን ፍንትው
ብሎ የምናየው ሀቅ ነው። እነሆ መምጣቱ እውን ሆነ። ታድያ በእርግጥ በእምነት ውስጥ ነን ብለን እራሳችንን
ብንጠይቅ መልሱን እናገኛለን። በጣት የተቆጠሩ ብቻ በእምነታቸው እንደሚገኙ እርግጥም ነው። እነሆ በዚህ
አዋጅ መታወጅ ባለድል መሆናቸው ተረጋግጧል። ድልን ለጨበጣችሁ እውነተኛ የልዑል ምርጦች እንኳን ደስ
አላችሁ። ክፉዎች ደግሞ መጣባችሁ ጨለመባችሁ ዳግም ላይነጋላችሁ ሆነ!

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ከእንግዲህ ወደኋላ አእምሮአችሁን እንዲያስብ አድርጉት የዘራችሁትን አመፅና ክፋት ታዩታላችሁ፤


የታመናችሁበት ዲያብሎስ ወርውሮአችሁ ለታላቁ እሳት ዳርጓችሁ ሄዷል። ያመኑት ፈረስ በደንደስ እንዲጥል
ፈረሳችሁ ዲያብሎስ ለእሳት ጥዶአችሁ ሄደ። በመሆኑም ከዚህ በኋላ የፍርዱ ማረፊያ ስለሚወሰን ጠብቁ!
ስለፍርደ ገምድሎች አንድ ምሳሌ እናንሳ፦
በአንድ አገር አንድ ፍርደ ገምድል ዳኛ ነበር ይባላል። ይህ ዳኛ በመሰለው የሚፈርድ ስለሆነ በዘመኑ የሱ
ፍርድ አስጨናቂና ንፁሆችን የሚጎዳ ነበር። በሱ ፍርድ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰዎች ሲጎዱ
ታይተዋል። አንድ ቀን አንድ ጉዳይ ከተሰየመበት ችሎት ደረሰ። ጉዳዩ ሲገለፅ ከሳሽ እንዲህ ብሎ አቀረበ፦
ጌታው ክቡር ዳኛ እግዚአብሔር ያመልክትዎ፤ ወንድሜን አንድ ጎበዝ ጉልበታም በመንገድ ጠብቆ ቀጥቅጦ
ገደለው እነሆ ፍርዶን እሻለሁ የወንድሜን ደም ሕግ ይፋረድልኝ አለ። ዳኛውም ወንጀለኛው ነፍሰ ገዳዩ ተይዞ
እንዲመጣ አዘዘ ተይዞም መጣ! ዳኛው እንዲህ ተብለህ ተከሰሃል ብሎ ወንጀሉን ነገረው እሱም ነውረኛ ስድብ
ስለሰደበኝ ደሜ ፈልቶ ገድየዋለሁ አለ። ዳኛውም በግፍ ገለኸዋልና በስቅላት ትቀጣለህ ብሎ ፈረደ። መስቀያው
ተዘጋጀ ወደዚያም ተወሰደ ወንጀለኛው እጅግ ረጅም ሰለነበረ መስቀያውን በአንገቱ ሲያስገቡ መሬት ላይ ቆሞ
ከመስቀያው እኩል ሆነ። ሰቃዮቹም ወደ ዳኛው ሄደው ከመስቀያው መርዘሙንና መስቀል አለመቻላቸውን
ገለፁለት። ፍርደ ገምድል ዳኛ እንዲህ ብሎ አዘዘ። የወንጀለኛውን የቅርብ ዘመድ ፈልጉ ቁመቱም አጠር ያለ
ይሁን እሱን በሱ ፈንታ ስቀሉ ብሎ አዘዘ። አንድ የከሰተበት ዘመዱ ተገኘና በእጥረቱ ምክንያት ተሰቀለ።
የዘመኑ ዳኝነት ወንጀለኛውን ሳይሆን ከወንጀሉ ያልተናኙትን ፈልጎ ማጥፋት ነው። ዛሬ በፍርደ ገምድሎች
ቤቱ ያልፈረሰ ንብረቱና ገንዘቡ ያልተወረሰ የለም። በማናቸውም የአስተዳደር የዳኝነት ሂደት ውስጥ በሃስት
መከሰስ የውሸት ምሰክር ማሰናዳት ያውም በራሱ በመንግሥት የሚከናወያን የዘወትር ትእይንት ነው።
የኢትዮጵያ አገራችን ችግር አጅግ ተበራክቶና ገዝፎ እየታየ ያለው በሁሉም ኢትዮጵያዊ ሕይወት ውስጥ
ያለው የመንግሥት ችግር ፈጣሪ እጅ ነው። ፍርደ ገምድሎችን በየቦታው ሰግስጎ ያነገሰው ይህ ዲያብሎሳዊ
መንግሥት ዛሬም አልተማረም። በቁጥር 4 መልእክት ማስጠንቀቂያ የደረሳቸው የቀድሞው ባለራእዩ መሪ ቅርብ
አዳሪ ሆነዋል ይታረሙ ተብለው ለንስሓ ተጋበዙ፤ ትእቢት መጥፎ ናትና በታላቅ ቁጣና ትእቢት ተሞልተው
ፎከሩ! ምን ዋጋ አለው ብዙም ሳይቆይ መጥፎው እድል ገጠማቸው። የእሳቸው አባሪና ተዋህዶን እያወቁ
የናቋት ፓትርያርክም ተከትለው ሄዱ ለሁለቱም የደረሰው ማስጠንቀቂያ ተቀባይ ስላጣ ውሳኔው ተግባራዊ ሆነ።
ዛሬም የምናያቸው ደግሞ ከበፊቱ የከፋ ጥፋትን እየፈፀሙና እያስፈፀሙ በመሆናቸው የመጣውን ሁሉ በኃላፊነት
ይሸከማሉ። ከተከሰተው አልተማሩምና።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ጥፋት ዘርዝረን አንጨርሰውም። በመላው ዓለም ያሉ ታላላቅ የተባሉ አገሮች
በመሪያቸው ዲያብሎስ በሚገባ የተሳሉ የጥፋት መሣሪያዎቹ ስለሆኑ በምድር ላይ ያለውን መዉ የልዑል ፍርድ
እጅግ ስለሚፈራና ስለሚጨንቅ ሁሉንም ባሮቹን ስለአደጋውና ስለጥፋቱ ይነግራቸዋል። በተቻላቸው መጪውን
ጥፋታቸውን እንዲቋቋሙ የሚያስችል ሥራ ሥሩ ይላቸዋል። ከዚህ የጨለማው መንፈስ በመነሳት እነሱም
ሲደከሙ እናያለን፤ ምን ምን ጥረት ያደርጋሉ አንዳንዱን እንየው
»» ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት የታመነ የዲያብሎስ አገልጋይ በመሆኑ ሁሉም መንግሥታት
ትልልቆቹም ትንንሾቹም ባላቸው አቅም ሁሉ ከሥልጣኑ እንዳይወርድ እንዲያደርጉ ቀጭን የዲያብሎስ
ትእዛዝ ወርዶላቸዋል። በመሆኑም ገንዘብ ብድር መሳሪያ ምክር ምንም አይነት ሕግ ሳያግዳቸው
የሕዝባቸውንም ጩኸት ቸል በማለት ይረዱታል። የሚቃወሙትን ተቀዋሚዎች ያሳድዱለታል
ካመቸም ይዘው ይሰጡታል። ለዚህም ነው ዛሬ በኢትዮጵያ ያለው መንግሥት በሙሉ ልብ ያሻውን
የሚያደርገው።

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

»» በመላው ዓለም ያለውን መፃኢ ሁኔታ የሚያረጋግጠውን ከልዑል የታዘዘውን ለዘጠኝ አመት የተላለፈን
መልእክት ከኢትዮጵያ ተነስቶ እስከ መላው ዓለም ድረስ አንዲደርስ ቢደረግም በአንዲትም የመንደር
ጋዜጣም እንኳን አልተገለፀም። ይህም የዛሬው አዋጅ ነጋሪ ሲገለፅ ከዚህ የተለየ እንደማይሆን ግልፅ
ነው። የሰው ልጅ ብርቱ ሞገደኛ ነው የሚባለውም በዚህ መንስኤ ነው። ምድሪቱም የተሸፈነቸው
በዲያብሎስ ተጠዋሪዎች መሆኑ እስከአሁን እየተደረገ ያለው ሁኔታ ያረጋግጥልናል።
»» በኢትዮጵያ ያሉትን በልዑል የተወደዱትን እሱም የሚወዳትን ያፀናትን እምነት ተዋህዶን የጨበጡትን
በማሳደድ በመግደል ታቦታቱን በመዝረፍ፤ ቅርሳቸውን በማሸሽ፤ ቤተ እምነታችንን ገዳማትን
በማፍረስ መጠመዳቸውን የምናየው እውነት ነው። ማንም የውጪ መንግሥት ተዋህዶ እምነት ላይ
ዘመቻ ሲካሄድ የተነፈሰ የለም ምክንያቱም አዝማቾቹ እራሳቸው ዓለም አቀፍ የዲያብሎስ ተቋማት
በመሆናቸው ነው።

ስለወቅቱ የዓለም ሁኔታ፤

ዓለማችን በቀደሙት ተከታታይ አምስት መልእክቶች በመዳኘት ላይ መሆኗን እያስተዋልን ነው። የአለማቱ
ገዢዎች መልእክቶቹ ዓለማትን ሁሉ መዳኘታቸውን እያወቁ፤ የመጥፋታቸውን ፍርድ በመግለፁ ምክንያት
በአንድም ቀዳዳ እንዳይነገር የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። በግል ብዙዎች እንዳገኙት ይታመናል። ከመልእክቱ
መውጣት በኋላ ዓለማችን በየደረጃው በእሳቱ ወንፊት በመበጠር ላይ ነች። እንደትእቢቷ መጠንም እሳቱና
የእሳት ወንፊቱ በሰባት እጥፍ እየተባዙ ማድቀቃቸውንና ማክሰማቸውን ይቀጥሉበታል። ዓለም ሁሉ አሜን ብሎ
እስከሚንበረከክ ድረስ!
ሸሸጉትም አልሸሸጉትም መልእክቶቹ ውስጥ የተጠቀሱት ፍርድና ቅጣቶቹ በታዘዙት ጊዜና ሰዓት ሥራቸውን
ያከናውናሉ እንጂ ከፍርድና ቅጣቱ አንዳች የሚቀር ነገር የለም።
በመልእክት ሁለት እንደተጠቀሰውና፤ በመልእክት ሦስት እንደተመለከተው አፈፃፀም፤ ሁሉም እርምጃዎች
ወረፋቸውን እየጠበቁ ይከናወናሉ። እየተከናወኑም ነው። የዓለም ሙቀት ይጨምራል እየጨመረ ነው፤ የምድር
ሰሜንና ደቡብ ጫፎች ያሉ የበረዶ ግግሮች ይቀልጣሉ የውቅያኖስም ከፍታ ይጨምራል ይህም እየተፈፀመ
ነው፤ በዓለም ጦርነትና ፍጅት ይነግሳል ይህም ሁላችንም የምመሰከረው እውነት ሆኗል። የተፈጥሮ አደጋ፣
የትራንስፖርት አደጋ፣ የመሬት ነውጥ፣ የሃይማኖትና የዘር ግጭትና ፍጅት ሁሉም እየተከናወነ ነው። በየትኛውም
የዓለም ገጽታ መሪዎች ተረጋግተው በሰላም የሚገዙበት የሚወጡበት ጊዜ መጥፋቱ ከመልእክቱ መዳኘት ጀምሮ
እየተከናወነ ነው። ዓለም ከፈጣሪዋ የተጣላችና የካደች በመሆኗ አየደቀቀች ወደ ከፋው ድቀትና ሞት እየገሰገሰች
ነው። እርምጃው መጠንና ኃይሉን በሰባት እጥፍ እያባዛ ያለምንም ፋታ ይቀጥላል። ሰውና ትእቢቱ፤ ንቀቱና
ውሸቱ፤ አብረውት ያሉት የዲያብሎስ እምልኮና ባሕርያት ሳያጠፉት እንደማይቀር እውነት ሆኖአል። ዛሬም
እፊቱ ቆሞ ዓለም የጨለማ ኃይላትና ሰራዊቱንም ፍፁም ከምድረ ገጽ ሲያሰወግድ በዓለሙ ሁሉ ፊት ቆሟል።
ዛሬ ደግሞ የግድ ጨለማው ተጠርጎ የብርሃኑ ዘመን ይተካና የእግዚአብሔር ሕዝቦችም በምድሪቱ ይነግሡ
ዘንድ ልዑል በገባው የማይታጠፍ ቃሉ መሰረት ተፈፃሚ ሊያደርግ ገዢ የሆነውን አዋጅ እንዲታወጅ ሆኖአል።
ዓለም ምን ይበጅሃል ተመክረህ ነበር አልሰማህም! ተቀጥተህ ነበር አልደነገጥከም ግሳጼወም አልመለሰህም
ሁሉም ጥረቶች በአንተ እንደሞኝነት ተቆጠሩ። አልፈህ ተርፈህ ልዑልን ፍፁም ካድከው ዲያብሎስንና
ትምህርቱን አነገሥህ፤ ምን ቀረህ ምንም የቀረህ የለም። በየደረጃው እየጨመረ የሚተምመውን ጥፋትህን
ልትለማመደው ትሞክራለህ፣ ሳይንሳዊ መፍትሄም አበጅለታለሁ ትላለህ እንጂ ከንቀትህና ክህደትህ እንዲሁም
ትእቢትህ የሚመልሰህ ብልሃትም ዘዴም አልተገኘም። በስተመጨረሻ የዛሬውን መደምደሚያህ የሆንውን ውሳኔ
ወለደልህ። ታከትምና ከምድሪቱም ፊት ትጠረግ ዘንድ፣ በቦታህም ብርሃን ይነግሥ ዘንድ የልዑል ፈቃድ ሆኖ

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

እነሆም በመቃብርህ ላይ እውን እንዲሆን ታወጀ። የዛሬውን የዓለም ጥፋት በመዘከር እንጨርሰወም፡ ሁሉም
ነገር በመመሰቃቀል ላይ ሲሆን አንደተጎለጎለ ልቃቂት ውልና መጨበጫው ጠፍቷል።
አንዳንድ አገሮች ወደመጥፋት ደርሰዋል። የአመፃ ሰራዊቶች መናኸሪያ ሆነዋል። ታላላቅ የተባሉ ሀገሮች
ችግር መፍታት አቅቶአቸው እራሳቸው የችግሩ አካል ሆነዋል። ዩክሬን፣ ኢራቅ፣ ሶሪያ ሌሎችም የኃያላን
ሀገሮች የአቅም መፈተሻ ሆነዋል። ውሾች እርስ በእርስ ቢጣሉ ጅብ እስከሚመጣ ድረስ ነው፤ እሱ ከመጣ
እጣቸው ሁሉንም የሚያጠፋ ስለሆነ በጋራ ይጮሃሉ። በጋራም ይሸሻሉ። የዛሬው ዓለም ታላላቅ ተብዬ
ሀገራት እርስ በእርሳቸው በመፋጀት ላይ ሲሆኑ እነሱን የሚያስተሳስሩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች /የተባበሩት
መንግሥታት፤ የአረብ ሊግ፤ የአፍሪካ ሕብረት/ በአባሎቻቸው አለመግባባት መወሰን አቅቶአቸዋል። መከራና
መጠረጋቸው በላይ በላዩ እየተደመረ በመሄድ ላይ ሲሆን ሳያከስማቸው እንደማይመለስ እርግጥ ሆኗል። ዛሬ
እኛም የልዑል ባሮች መፈፀሚያቸው መድረሱንና መቆረጡን ልናረጋግጥላቸው እንወዳለን።
ልዑል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ሌትም ቀንም ሲሰድቡትና ሲያቃልሉት የሚውሉና የሚያድሩት
የዲያብሎስ ደቀመዛሙርቶች ላንዴም ለሁሌም እንዳይመለሱ ሆነው ይከደናሉ።

ከኔ ጋር ያልሆነ ይቃወመኛል፤ ከኔ ጋርም የማያከማች ይበትናል፤ ስለዚህ እላችኋለሁ


ኃጢአትና ስድብ ሁሉ ለሰዎች ይሰረይላቸዋል ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን ለሰደበ
አይሰረይለትም፤ በሰው ልጅ ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ በመንፈስ ቅዱስ
ላይ ግን የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለም ቢሆን ወይም በሚመጣው አይሰረይለትም።
የማቴዎስ ወንጌል ምእራፍ 12፡ 30 – 32
ቃሉም እንደሚያረጋግጥልን ዛሬ በአለማችን በልዑል ቃልና ፈቃዱ ላይ ያልዘመቱ የሉም። የውሸት
ድርሰት ደርሰው በመላው ዓለም ሃሰትን ያነገሱ እምነቶችን ፈጥረው፣ ዛሬ ዓለምን ሁሉ የሚመለከተውን
የሚያስተምረውን የሚወቅሰውን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን በመስደባቸው አይደለምን? አዎን ነው። ስለዚህ
ፍርዱን ይሸከሙታል። ሳይውል ሳያድር በሕይወታቸው ይከፍሉታል።
ባጠቃይ ዓለም በአሁኑ ሰዓት በቀደሙትም ሆነ እነሆ አሁን በታወጀው አዋጅ እጣ ፈንታዋ በግልፅ
ተረጋግጦአል። አዋጁ እነዚህ ለዘመናት ያለከልካይ እንዳሻቸው ሲፈነጩ መኖራቸው በግልፅ የተረጋገጠላቸውን
ሸክሞች ከፊቱ ባስቀደመው መጥረጊያው ፍፁም ሊጠርጋቸው ወጥቷል። የተመዘዘ ሰይፍ አይመለስም። የግድ
ሊቆረጥ የሚገባውን ሁሉ ይቆራርጣል። እንግዲህ ሰለዓለም ይህን ያህል ከተረዳን ይበልጥ ደግሞ የቀደሙትን
አምስት ተከታታይ መልእክቶች ደግማችሁ አስተውሉ አላለሁ። ይህ የወጣ አዋጅ የቅጣት አይነቶቹን ሁሉ
ይጠቀምባቸዋልና፤ የቅጣቶች ዓይነትና ምንነት በቀደሙት መልእክቶች ተገልፀዋል። እነዚያን ማገናዘብ
ያስፈልጋል።
አዋጁ ከፀና እለት ጀምሮ በማናቸውም ሰዓትና ጊዜ መጥረጊያው የፅዳት ሥራውን ይጀምራል። በመሆኑም
ይህ አዋጅ ነጋሪ መልእክት በእጁ የደረሰው ሰው ህሊናው ለተቀበለው ሰው ሲሰጥ ይችላል።

ስለድንግል ፍርድ

በዚህ አዋጅ ነጋሪ መልእክት ውስጥ ትሰማው ዘንድ አስፈላጊ ከሆነው አንዱ የድንግል ፍርድ ነው። ዓለም
ያለድንግል አማላጅነት አይድንም ሲባልና ይህንን ያለመታከት ለረጅም ዓመታት ሲያውጁ የነበሩና ያሉ
የድንግል ልጆች እንደምናምንቴ ተቆጥረው የሰማቸው እንደሌለ ራሱ እያንዳንዱ ሰው ልቡናው ያውቀዋል።
ስለዚህ ለናቅኸው ዛሬ ሰማህም አልሰማህም ትርጉም የለውም። የተሰጠህን ዘመን በከንቱ ጨርሰኸዋል። ይህ
አዋጅ ለጠበቀው፣ ለተሰነናዳው፣ በተስፋና በእምነት ፀንቶ ለቆመው ብቻ ነው ታስቦ የመጣው።

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ድንግል ለጠበቋት ልጆቿ ለታመኑባት ወዳጆቿ እንዲህ ፈርዳለች።


አንደኛ በዲያብሎስ በሁለመና ሕይወታችሁ እንዳትላወሱ፤ ደክማችሁ ለፍታቸሁ ራሳችሁን አሸንፋችሁ
ትኖሩ ዘንድ በምትወጡበት በምትወርዱበት ሁሉ በመንቀሳቀስ ድካማችሁን በመንጠቅ ከንቱ በማድረግ ባዶ
እጃችሁን በመስደድ የናንተን ድካም ለሌላው ክፉው ሰው በመስጠት እንድትራቡ እንድትጠሙ የተደረጋችሁ
ልጆቼ ሁሉ፤
ሁለተኛ በተለያዩ በሽታዎቸና ደዌዎች ተመትታቸሁ የዲያብሎስ ማሰቃያ ሰለባ የሆናችሁ በአልጋ ቁራኛ
በደዌ ዳኛ የተያዛችሁ ልጆቼ ሁሉ
ሶስተኛ በጠነከረ የተዋህዶ እምነታችሁ ፀንታችሁ በመቆማችሁ በጠላት የተጋዛችሁ የታሰራችሁ ልጆቼ
ሁሉ አዋጁ ከሚፀናበት ከሚያዚያ ሰባት ሁለት ሺ ሰባት ዓመተ ምሕረት ጀምሮ በኔ በእናታችሁ ምልጃና
ፍርድ በልጄም ፈቃድ ከእሥራታቸሁ ከሕመማችሁ ከረሃባችሁ ተፈትታችኋል። ለዚህ ያበቃችሁን ልዑልን
አመስግኑ!!!
ወዳጆቼ ዛሬ አንድ ትንሽ የልዑልና የድንግል ባሪያ በሆንኩት ምስኪን ድሃ በኩል ለእናንተ ታላቁን
አዋጅ እና ይህንን አዋጅ ነጋሪ ቃል ላደርስ እድል ተሰጥቶኛል። ይህ ክብር ለኔ የተገባ አልነበረም የልዑልም
የድንግልም ፈቃድ ሆነና በእንደኔ አይነቱ በደለኛ መልእክቶቹን ዛሬም አዋጁን አበስር ዘንድ ስለተፈቀደልኝ
በአደፈ አንደበቴም ቢሆን አምላኬንና እናቴን ከልብ አመሰግናለሁ። አንተም የታደልከው ወገኔ ባለድል ሆነሃል።
ከትቢያና ከአቧራ ሊያነሳህ ልዑል ዛሬ በከበረው ስሙ ወሰነ። ሲጠበቅ የነበረው አዋጅም እነሆ ፀና። ዓለም
እስከዛሬ በዲያብሎስ አገዛዝ ሥር ሆነሽ የእግዚአብሔርን ሕዝቦች ለረሃብ ለሞት ለስደት ለድህነት ለእሥራት
ለጭንቀት ለበሽታ ዳርገሽ ነበር። በጥቅሉ ለክፉዎች ገነት ነበረሽ ለመልካሞቹ ደግሞ ሲኦል ነበርሽ። ዛሬ
እምነግርሽ ከሕግጋተ ሥላሴ መፅናት ጀምሮ ተሰንገሽ ለልዑል ባሮች ትገዣለሽ ይህም የልዑል ውሳኔ ነው።
ይህንን አዋጅ ነጋሪ ስድስተኛ መልእክት የደረሳቸሁ ከመልካሞቹም የተመደባችሁ፣ በልዑልም ለመልካሙ
ቀን ለታተማችሁ ሁሉ አዋጁን ለምን አላገኘነውም ብላችሁ አትታወኩ ይህ የሆነው ለጥንቃቄ ነው እንጂ
ልትነፈጉት አይደለም። ይህንን መልእክት እስካገኛችሁ ድረስ ዋናውንም አዋጅ ታገኛላችሁ። እናንተ ለበጎው
ቀን የተወደዳችሁና የተመረጣችሁ ሁኑ እንጂ! ለዲያብሎስና ለተስፈኞቹ እንዲሁም ለጨለማው ዘመን መቆየት
ዛሬም ለሚደክሙና ለሚያልሙ ግን አዋጅ ነጋሪው መልእክት ቢደርሳቸውም ባይደርሳቸውም የሚጠቅማቸው
አይደለም ዋናው አዋጅም ቢደርሳቸው ምን ይጠቅማቸዋል አይኖሩበት አያዩት መልካሙ ዘመን /የትንሳኤው
ዘመን/ አያውቃቸውምና። በተጨማሪም ስለጥፋታቸው ቢሰሙ አይደነግጡም የሚታመንበት ዓለምና ዲያብሎስ
ገና አብረዋቸው አሉና! አይዞህ ባይ ገዢአቸው በመቃብር እስከሚከደኑ ድረስ እናም ከመቃብሩ አፍ ደርሰውም
አንኳን ቢሆን መውረዳቸውን እስካላረጋገጠ እንደማይተዋቸውና በተስፋና በለመደው ማሰሪያው ጠፍሮ
ይጨርሳቸዋል። ስለዚህ አዋጁን አያዩትም አይኖሩበትም ብርሃናዊው ዓለምም ፍፁም አያውቃቸውም።
እንግዲህ ስናጠቃልለው አዋጁ የያዘውን ጥቅል ገጽታውንና ስእሉን ስናየው በመጀመሪያ ክስተት የሚመጣው
የሽግግሩ ዘመን ሲሆን በጥቅሉ መፍረስ መናድ መጠረግ መክሰም ሁሉ ይከናወናል። ይህ እርምጃ በቁስም
በሰውም ላይ የሚፈፀም ነው። ምንም የዲያብሎስ ተክል አለመኖሩን ፍፁም መረጋገጥ አለበት።
ዋናው ሕግጋተ ሥላሴ የፀዳውን መሰረቱም ለልዑል ፈቃድና ትእዛዝ መመቸቱን የሽግግሩ ሕግጋት
ካረጋገጠለት በኋላ ዋናው ሕግጋተ ሥላሴም እየተረጋገጠ ይመጣል። የጧት ጀምበር ማለዳ ከወደ ምሥራቅ
እንድምትዘልቅ ሁሉ ብርሃናዊው ዘመን መዝለቅ ይጀምራል።

በዚያን ዘመን ይላል እግዜእብሔር ለአሥራኤል ወገኖች ሁሉ አምላክ እሆናቸዋለሁ


እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡– እስራኤል ማረፊያ ሊሻ
በሄደ ጊዜ ከሰይፍ የተረፈው ሕዝብ ሞገስ አገኘ፤ እግዚአብሔርም ከሩቅ ተገለጠልኝ
14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

እንዲህም አለኝ፤ በዘለዓለም ፍቅር ወድጄሻለሁ ሰለዚህ በቸርነት ሳብሁሽ የእስራኤል


ድንግል ሆይ እንደገና እሰራሻለሁ፤ አንቺም ትሰሪአለሽ፤ እንደገናም ከበሮሽን አንስተሽ
ከዘፋኞች ጋር ወደ ዘፈን ትወጫለሽ እንደገናም በሰማሪያ ተራሮች ላይ የወይን
ቦታዎችን ትተክሊያለሽ አትከልተኞች ይተክላሉ በፍሬውም ደስ ይላቸዋል።
ትንቤተ ሕዝቅኤል ም 31፣ 1 – 6
በመጨረሻ ይህን ልናውቅ ይገባል
የምሥራች ለልዑል ሕዝቦች፤ ምክንያቱም ደግሞ ዛሬ ይህንን አዋጅ ነጋሪ መልእክት እንድትሰሙና ይህንንም
እንድታውቁ እንድትረዱ ስለወደድሁ ነው። እናንት የእግዚአብሔር ወዳጆች እንኳን ለዚህ ንጋት አበቃችሁ!
በልዑል ምርጫ፤ በድንግል ምልጃና ፍቅር ተወደዳችሁ ለትንሳኤው ዘመን የሚያበቃችሁንና ባለመብትም
ያደረጋችሁን የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ እነሆ ተሠጥቶአችኋል። ትኖሩበት ትሠሩበት ትባረኩበት ትደሰቱበት
ትወልዱና ትበዙበት ዘራችሁም ሁሉ ይባረክበት ዘንድ፤ የልዑልም ብሩካን ካህናት አገልጋዮችና እረኞች
ትሆኑ ዘንድ የተመረጣችሁበትን የምድሪቱ ወራሽ ትሆኑ ዘንድ መወደዳችሁን የሚያረጋግጠውን መለያችሁን /
መታወቂያችሁን/ እነሆ ከአዋጁ መፅናት ጀምሮ ትረክባላችሁ። ለዚህ ያበቃችሁ ልዑል የተመሰገነ ይሁን!
እነሆ መርዶ ለጥፋት ሰዎች! አመፃን ገንዘብ አድርጋችሁ የዚህን ዓለም ትርፍ ታምናችሁ እግዚአብሔርን
ክዳችሁ የዲያብሎስን ፈቃድና ሃሳቡን ታምናችሁ በሱ ጥበባዊ ድርሰት ተተግናችሁ፣ በሃብቱ በገንዘቡ በምድሪቱ
ሁሉ ቦርቃችሁ በዲያብሎስ ድጋፍ በናንተም የአመጽ የኃጢአት የትእቢት የክህደት የምንዝርና የጨካኝነት የዘረፋ
የነፍሰ ገዳይነት የዘረኝነት መውደድ ለተለከፋችሁ እንቁዋን እምነት ተዋህዶን አፍርሳችሁ እሳዳችሁ ገላችሁ
በዚህም ተደስታችሁ፤ ከዓለም አቀፍ ወዳጆቻችሁ የዲያብሎስ ሹመኞች ጋር በመተባበር ፍፁም ጨለማን
እንግሳችሁ፤ ዛሬም በአገሬ በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም በተዋቀረ እጅና እግራችሁ የእግዚአብሔርን
ሕዝብ /አልጠፋ አላችሁ እንጂ!/ እውቀታችሁ አቅማችሁ ዘዴአችሁን ሁሉ በመጠቀም አለከልካይ የነገሳችሁ
የዲያብሎስ ልጆችና ተጠዋሪዎች እንዲሁም ተስፈኞችና የይቆይልን እድሜ ለማኞች ዛሬ ለናንተም መርዶው
ይድረሳችሁ። በቃ በታላቅ ቁጣ ከምድረ ገጽ ትጠረጉ ዘንድ ፍፁም ወደትቢያነት ትመለሱና ላንዴና ለሁሌም
በመቃብራችሁ ትከደኑ ዘንድ ተወሰነ። አዋጁ እናንተን በመጥረግ ምድሪቱን በማጽዳት ብርሃናዊው መልካሙና
የትንሳኤው ዘመን ይዘልቅ ዘንድ ተወስኖአልና የተሳካ የጨለማ ጉዞ ያድርግላችሁ። የታመናችሁበት ዲያብሎስም
በሲኦል እናንተን ወገኖቹን እንግዶቹን ለመቀበል እየተጣደፈ መሆኑንም አረጋግጥላችኋለሁ!!!
ይህን አዋጅ ነጋሪ መልእክት ደርሶአችሁ መስማቱን እድል ለገጠማችሁ ሁሉ መጪው እውነት ይህ ነው።
ተወደደም ተጠላ አዋጁ ታውጇል። እሚመለስ እሚለወጥ ነገር የለም። በእግዚአብሔር ውሳኔ መፀፀት የለምና፤
ተፈፀመ።
አዲስ ብርሃናዊ ዓለም መልካም ዘመን ልዑል የሚነግሥበት ብርሃናዊ አገዛዝ የሚሰፍንበት ዘመን ላይ ትደርሱ
ዘንድ ለታደላችሁ የልዑልና የድንግል ልጆች ደግሜ እንኳን ደስ ያላችሁ እላለሁ።
ለእግዚአብሔር አብ ለእግዚአብሔር ወልድ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ከዘለዓለም እስከ
ዘለዓለም ክብር ምስጋና እንደማያቋርጥ ጅረት ይፍሰስለት!!! አሜን! አሜን! አሜን!
ለእናታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ምስጋና ይድረሳት!!! የዳንከው ሁሉ የእንባዋ ውጤት ነህና
አመስግናት ውደዳት!
ሁሌም ላልተለዩን ለረዱን ለጠበቁን ለአማለዱን ለታገሱን ለተሸከሙን ቅዱሳን ሊቃነ መላእከት ለቅዱስ
ሚካኤል፣ ለቅዱስ ገብርኤል፣ ለቅዱስ ሩፋኤል፣ ለቅዱስ ፋኑኤል ለቅዱስ ኡራኤል፣ ለቅዱስ ራጉኤል፣

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስድስት

ለቅዱስ ሳቁኤል፣ ለቅዱስ አፍኒንኤል፣ ለቅዱስ ሰላትያል፣ ለቅዱስ ሰዳክያል፤ ለቅዱስ ራሙኤል፣ ለቅዱስ
ሱሪያል ሁሉ ምስጋና ይድረሳቸው!!
ለሰማዕቱ ጊዮርጊስ ለሰማዕቷ አርሴማ በምልጃቸው ለተራዱን ሁሉ ለሁሉም የልዑል ቅዱሳን አባቶቻችን
ሁሉ ምስጋናችን ይድረስ!!
ይህ አዋጅ ነጋሪ መልእክት በዛሬው እለት በአሥራ ዘጠኝ እለተ ክብረ ገብርኤል ቀን በታሕሳስ ወር ሁለት
ሺ ሰባት ዓመተ ምሕረት ተፅፎና ተዘጋጅቶ ወጣ!!!

የልዑልና የድንግል ባሪያ የቅዱሳን መላእከትም አገልጋይ ከሚሆን ታናሽ ባሪያ ተላከ!!!

16
መልእክት ስምንት
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

መግለጫ
በግንባርና በመጨረሻ ገጽ ያሉ ሥእሎች መግለጫ

በግንባር ያለው ስእል ምንን ይናገራል?


»» ሰንደቅ ዓላማው የኢትዮጵያ ሕዝብ መለያውና ምልክት መሆኑን በተለይም በመነሻነት ከልዑል ጋር
ቃል ኪዳን መፈፀሙን የሚያረጋግጥ መሆኑን ይገልፃል።
»» ኢትዮጵያና ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት የማይነጣጠሉ መሆናቸውን ያመለከታል።
»» በአረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅ ዓላማችን ላይ ባእድ ምልክት መለጠፍ በኢትዮጵያዊነት በተዋህዶ
እምነት ላይ እና በሃገረ ድንግል ላይ የሆነ የጠላት ጥቃትና ብርቱ ወንጀል መፈፀሙን ያመለከታል።
አንበሳው ስር ያለው ሉል ዓለምን ይወከላል። መልእክቱም በዓለም ሁሉ ላይ ተፈጻሚ ይሆናል።
»» አንበሳው የዘለዓለሙን ንጉሥ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የምድሩም የሰማዩም ገዢነቱን
ያሳያል። መስቀሉም በአንበሳው አናት ላይ ያለውና በበትረ መስቀሉ ጫፍ ላይ ያለው የመዳናችን
የመሰረታዊ እምነታችን እንዲሁም ሃይላችን መስቀሉ መሆኑን ያረጋግጣል። ዘውዱ በሰማይም
በምድርም ሥላሴ ገዢ ፈጣሪ መሆኑን ፈቃዱም ሃሳቡም ትእዛዙም ማንም የማያግደው ተፈፃሚ
መሆኑን ያረጋግጣል።
»» ሰንደቅ ዓላማውን የያዘው የብረት ዘንግ ጫፉ መስቀል ያለበት ሥልጣንና ኃይልን የሚያሳይ ሲሆን
በኢትዮጵያ ምድር የሚፀና ከዚህም ማእከል ተነስቶ መላውን ዓለማችንን የሚገዛ የሚነግሥ መሆኑን
ያረጋግጣል። የተዋህዶ እምነታችን የኢትዮጵያዊነታችን ጽኑ መግለጫ መሆኑን ያሳያል።

በጀርባው ያለው ስእል ምንን ያመለክታል?


በስእሉ ውስጥ ከአናቱ ላይ ያለው ሥላሴ በመንበራቸው ሆነው ሲሆን ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ በግራና በቀኝ
በመንበሩ ዙሪያ ሆነው ሁሌም ያለማቋረጥ የሚያመስግኑት መሆናቸውን የሚገልፅ ነው። መንበሩንም አርባእቱ
እንስሳ ሱራፌል ኪሩቤል ተሸክመውት ይታያል። ከመንበሩ ሥር ሰባቱን ሊቃነ መላእክትን ያሳያል።
በመሃል ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ያሳያል። በዙሪያውም የቤተ ክርስቲያንን ሰባቱን ባሕሪያት
የሚገልፁትን ሰባቱን መቅረዞች የሚገልፅ ሲሆን በዮሐንስ ራእይ የተገለፀውን ማለት ነው ሌላው፤ በእጁ
መፃፊያና ሰሌዳ የያዘውን አባት የሚያሳይ ሲሆን ከሥላሴ መንበር የሚፈሰውን መልእክት ትእዛዝና ፈቃድ ለሰው
ዘር ለማድረስ ሲከትብ ይታያል። የዓለም ካርታውም ከልዑል የሚፈሰው መልእክት በመላው ዓለም ላሉ ሰዎች
ሁሉ የተላከ መሆኑን ያመለክታል።
በጥቅሉ፡
ሥላሴ አክብረው ለፈጠሩት የሰው ልጅ በየዘመኑ ይናገራሉ። ሰው አያስተውልም እንጂ። ሰማያትም፣
ምድርም፣ እንስሳትም ደቂቅ ነፍሳትም ግዑዙ አካልም ሁሉም ይናገራሉ። ላስተዋለው የልዑልን ፈቃድ፣
ትእዛዝ፣ ሃሳብ፣ ውሳኔ ሁሉ፣ በየእለቱ በሚከውኑት የሕይወት መስተጋብራቸው ይናገራሉ። ለማን? – ለሰው
ልጅ!! ማስተዋልን፣ አስቦ ማድረግን፣ አውጥቶ አውርዶ መወሰንን የሚችል እእምሮ የተሰጠውን አምሳለ
ልዑልን የሆነውን የአዳምን ዘር ይመለከታል።

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ታኅሣሥ 21 ቀን 2011 ዓመተ ምሕረት

ተፃፈ ፡ በአንድ ታናሽ የልዑል ባሪያና


ከኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመን
አንዱ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ለሁሉም የአዳም ዘር!

ከሁሉም በላይ ለተወደዱት ፀንተው ለተገኙት


ለእግዚአብሔር ሕዝቦች የተላከ!
ማሳሰቢያ፦
»» ወገኖቼ! መልእክቱን ይገባዋል ብላችሁ ላመናችሁበት ሁሉ አድርሱ!
»» ቢያንስ ለ3 ሰው ብታደርሱ መልካም ነው! በማስተዋል አንብቡ!
»» የቀደሙትን 6 መልእክቶች ብታነቡ ይበልጥ ለግንዛቤአችሁ ይረዳል!
»» ይህንን መልእክት ካደረሱላችሁ ስለቀደሙትም መልእክቶች ብትጠይቁ ሊረዷ66ችሁ ይችላሉ!

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

መልእክት ስምንት
ቀን ታኅሣሥ 21 ቀን 2011 ዓ.ም

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!!


የፍጥረት ሁሉ ጌታ የአባቶቻችን አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን!
ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል እናታችን ስሟ የተመሰገነ ይሁን!

ወገኖቼ ሕዝበ ክርስቲያን!


ወገኖቼ መላው የአዳም ዘር!
ማሳሰቢያ፦ ይህን መልእክት ለማንበብ እድል የገጠማችሁ ወገኖቼ!! የእምነት ሰዎች ከሆናችሁ፤ በየትኛውም
የእምነት ተቋም ውስጥ ብትሆኑም በዚህ መልእክት በእጃሁ መገኘት የመጀመሪያችሁ ከሆነ ልትገረሙ ወይም
ልትረበሹ ትችሉ ይሆናል። ሆኖም ምንም አይደለም። ይልቅስ የቀደሙትንም 6 መልእክቶች አግኝታችሁ የ13
ዓመቱን ሂደት ብትገነዘቡበት የግል ውሳኔ ለመውሰድ ይረዳችኋል ብዬ እገምታለሁ። ለማታምኑበት ለምታላግጡት
ከነጠላው ፍርድ ይልቅ ድርብ ፍርድን በራሳችሁ ባትጋብዙ መልካም ነው። እንኳን ለተደራረበ ፍርድና ቅጣት
ለአንዱም የመሸከም አቅም የላችሁም። ስለዚህ አንብባችሁ ከምታፌዙና ለብርቱ ቅጣት እራሳችሁን ከምትጥሉ
ባታነቡት ይሻላል ብዬ እመክራችኋለሁ።
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል

እነሆ ክፉ ነገር ከሕዝብ ወደ ሕዝብ ይወጣል። ጽኑም አውሎ ነፋስ ከምድር


ዳርቻ ይነሳል። በዚያም ቀን የእግዚአብሔር ግዳዮች ከምድር ዳር ጀምሮ እስከ
ምድር ዳር ድረስ ይሆናሉ። አይለቀስላቸውም፤ በምድር ላይ እንደ ጉድፍ ይሆናሉ
እንጂ አይከማቹም አይቀበሩም። ትታረዱና ትበተኑ ዘንድ ቀናችሁ ደርሶአልና!
እንደተወደደም የሸክላ እቃ ትወድቃላችሁና እናንተ እረኞች አልቅሱ! ጩኹም!
እናንት የመንጋ አውራዎች በአመድ ውስጥ ተንከባለሉ ሽሽትም ከእረኞች ማምለጥም
ከመንጋ አውራዎች ይጠፋል። እግዚአብሔር መሰማሪያቸውን አጥፍቶአልና! የእረኞች
ጩኸት ድምፅ የመንጋ አውራዎችም ልቅሶ ሆኗል። ከእግዚአብሔር ጽኑ ቁጣ የተነሳ
የሰላም በረት ፈርሷል። እንደአንበሳ መደቡን ለቋል፤ ከአስጨናቂውም ሰይፍና ከፅኑ
ቁጣው የተነሳ ምድራቸው ባድማ ሆናለችና
ትንቢተ ኤርሚያስ ም 25፤ 32 – 38
ይህ የመልእክቱ መግቢያ የልዑል ቃል! መልእክቱ ለምን እንደመጣ ጥልቅ የሆነ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ታስቦ
ነው መግቢያው ላይ የሰፈረው።

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወገኖቼ በብዙዎች ዘንድ ይህ መልእክት ለምን መጣ? አዋጁ ታውጆ አብቅቶ የለም እንዴ? ለምን
ሁሉም ነገር ተደበላልቆ አይጠናቀቅም? የሚል ስሜት በብዙ ወገኖች ዘንድ ይነሳል። አንዳንዶችም ጊዜ
ለመስጠት በመዘግየቱ የቀረ የማይሆን መስሎአቸው ከእምነታቸው ጎለው ጠላት በሚፈጥረው መልከ ብዙ ሴራና
እጅግ የረቀቀ ጥበቡ፤ በዓለም በዘረጋው የፕሮፖጋንዳ! ሚዲያ ፕሬስ፤ ሶሻል ሚዲያ ቴሌቪዥን፤ ሬዲዮና
ሌላም ተመሳሳይ የስርጭት መረቡ፤ ተስፋ አስቆራጭ! ድርጊትና ንግግሩ፤ በአታቸውን ስለለቀቁ፤ ለአሁኑ
መልእክትም ያላቸው ቅቡልነት ደካማ እንደሆነ እረዳለሁ። አንዳንዶች አሁንም ትላንትም ከተቃኙበት የጠፋና
ከንቱ አቋማቸው በመነሳት መልእክቱን የሚነቅፉ አሉ። ብቻ ሁሉም እንደ ታየው እንደመሰለው አስተያየት
ይሰጣል ብዬ እገምታለሁ ለደከማችሁት የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል

ያዕቆብ ሆይ እስራኤልም ሆይ መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ


አልፋለች፤ ለምን ትላለህ፤ ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ፤ አላወቅህምን አልሰማህምን፤
እግዚአብሔር የዘለዓለም አምላክ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው። አይደክምም አይታክትም
ማስተዋሉም አይመረመርም፤ ለደካማ ኃይልን ይሰጣል ጉልበት ለሌለውም ብርታትን
ይጨምራል። ብላቴኖች ይደክማሉ ይታክቱማል ጎበዛዝቱም ፈጽሞ ይወድቃሉ።
እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ሃይላቸውን ያድሳሉ። እንደንስር
በክንፍ ይወጣሉ ይሮጣሉ አይታክቱም ይሄዳሉ አይደክሙም። ይላል ልዑል እኔም
ገና በመልእክቴ መግቢያ እይዞህ ደከምክም ወደቅህም ትነሳለህ!! እኔም ይህንኑ
እልሃለሁ! አይዞህ! ትነሳለህ
ትንቢተ ኢሳይያስ ም ፡ 40 ፡27 – 31
ከሁሉም በላይ፤ ወገኖቼ! በርግጥ ልታውቁ የሚገባው ቁም ነገር አለ። ዛሬ ይህ መልእክት የመጣው
በዋናነት፤ የደከሙትን ለማፅናት፤ የበረቱትንም፤ ይበልጥ እንዲተጉ ለማድረግ ነው። እናም አልደረሰም ዘገየ
የት አለ? ለሚሉት ለሚያፈዙት አሁን! በአንገታቸው ላይ ስለሆነ ከፌዛቸው ይጠግቡታል። ስለነሱ ገዶኝ
አይደለም፤ ይህ መልእክት የማደርሰው። እነሱ ትቢያ ናቸው ወደተጠበቀላቸው እሳት ይገባሉ። የእግዚአብሔርን
ሕዝቦች! ከፊታቸው የደረሰው የቁጣው እሳት እንደሚታሰበው ሳይሆን፤ ከሰው ሕሊናና ግምት በላይ ስለሆነ
የእግዚአብሔር ሕዝቦች : እንዳይታወኩ ፡ ለማፅናት ነው። የምነግራችሁም – የልዑልን የአባታችንን የእናታችንን
የድንግልን የማይናወፅ ቃል ነው። ሁለቱም ቃላቸው ባጭሩ ይህ ነው። ልጆቻችን አይዞአችሁ ደርሰናል!።
አትፍሩ አትታወኩ!። ፅኑ!። አትደንግጡ! የነጣውን ለብሳችሁ! በጥፋት ማዕበል ውስጥና መሀል ብትጎማለሉ፤
አንዲቷን ፀጉራችሁን እንኳን የሚነካ የለም። ልጆቻችን ዙሪያችሁ በእሳት የታጠረ ነው። ሊጎዳችሁ ያሰበ
ገና ሃሳቡ በአእምሮው ሲፈጠር እናንተም ጋር ሳይደርስ ይወገዳል! አሁን ደርሳችኋል ስለአመፀኞች ጥፋት፤
ስለፍርዳቸው አፈፃፀም ተመልካቾና ተደማሚ ናችሁ እንጂ ማን ጥጋችሁ ይደርሳል? ሁሉም ተመዝኗል ዋጋው
በእጄ ነው እንደ እጣ ክፍሉ ይከፈለዋል። ይላል የሁለቱም /አባት እናታችሁ/ ቃል።
እንደምን ከረማችሁ! የሠራዊት ጌታ ስሙ የተመሰገነ ይሁን! አኑሮን ጠብቆን ዘመንን እያቀዳጀ ለዚህ
ቀን አድርሶናል። የእግዚአብሔርን ቸርነት ትእግሥትና ፍቅሩን የተረዳ ሁሉ ዛሬ ላይ ሆኖ ልብ ያልተነፈገው
ማስተዋልን ገንዘቡ ያደረገና ጥበብን የለበሰ የፈጠረውን ጌታ ከልቡ ያመሰግናል። በመልእክቶቹና በ6ኛው
መልእክት ከተገናኘን 4 ዓመት ሆኗል።
ሁላችሁም እንደምታስታውሱት 6ኛው መልእክት ዋናው መልእክቱ የነበረው በ7ኛው መልእክት የወጣውን
አዋጅ ለመግለፅ ነበር። አዋጁ እንዲነበብ አልተፈቀደምና አልተሰራጨም ነበር። በዛሬው መልእክቴ ስለአዋጁ
ጥቂት ላስታውሳችሁ የወደድኩት ያለምክንያት አይደለም። አዋጁ ከታወጀበት ከሚያዚያ 7 2007 ዓ.ም
ጀምሮ ራሱን ለመትከል እንደ ልዑል ፍርድ ዓለምን በየደረጃው እያበጠራት ይገኛል። ለዚህ ምስክሩ አገራችን

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ኢትዮጵያ ዛሬ ያለችበት ሁኔታ ነው። ቀድማም ነፃ የምትወጣውና በአዋጁ የተገለፀው የሽግግሩም ሆነ ቋሚው
ሕግጋተ ሥላሴ በመጀመሪያ የሚፀናው እዚህ ኢትዮጵያ አገራችን ላይ ነው። የእግዚአብሔር ሕግጋተ ሥላሴ
በአገራችን ዙሪያ ባሉ አገሮችም ጭምር የሚፀናና ለመላው ዓለም እንደፀሐይ የሚያበራ ሆኖ ይቆማል። ይህንን
ለማየት በውስጡም ለመኖርና እድሜን ለመቀዳጀት የሚታደለው ማን እንደሆነ የሚያውቀው ማንም አይደለም
ልዑልና ድንግል በግንባሩ ያተሙበት ብቻ ነው። ለዛሬው ከሃዲ ትውልድ ይህ ተረት ነው። ለዚህ ነው አዋጁም
የማይገለፀው፤ ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች በእምነት አሻግራችሁ ለማየት የታደላችሁ ወንድም እህቶቼ
እናንተ ተስፋችሁ የፀና የማይናወፅ ነው። ራሳችሁን ከዚህ ዓለም ጉድፍ ስለጠበቃቸሁ ሕይወታችሁ ሥጋዊ
ኑሯችሁ በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሆነ እኔም የምመሰክረው ነውና ፅኑ እንጂ አትናወጡ።
የሚጠፋው ጠፍቶ፣ የሚሻገረው ደግሞ የተፈቀደለት ብቻ ይሆናል። የመከራው ክብደት ተስፋን ያጨልማል
ሥጋ ነንና እንደክማለን እንወድቃለን ነገር ግን የምንታመንበት አምላክ የምንወዳት እናታችን በቃላቸው የታመኑ
ስለሆኑ ብንወድቅ ያንሱናል፤ ብንቆስል ብንጎዳ ይጠግኑናል። ስለ ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች በአንድ ርእስ
ወደኋላ ስለምናየው ለመግቢያ ያህል ያልኩትን በዚህ ልግታና ወደጉዳዩ ቀጥታ ልግባ።

እግዚአብሔር ማዳኑን አስታወቀ፤ በአሕዛብም ፊት ጽድቁን ገለጠ፤ ለያዕቆብ


ምሕረቱን፤ ለእስራኤልም ቤት እውነቱን አሰበ።
መዝሙረ ዳዊት ፡ 97(98) 2–3
የዛሬው መልእክት አዲስ ነገር አዝሎ የመጣ እንዳይመስልህ። የተውከው የረሳኸው እየፈጨኽ፤ እየቆላህ፤
እንደፍርዱ እያካተተህ የመጣውን የፍርድቃል ሊያጠናቅቅህ ከአጠገብህ ተሰድሯልና መለስ ብለህ እንድታይ
የመፈፀሚያ ጉዞ መጀመርህን እንድትረዳ፤ ያለህበት ሰዓት ምን እንደሚመስል እንድታውቅ እጣህንም
እንድትገነዘበው ለማድረግም ነው።
ለ13 ዓመት ለ6 ጊዜ የተላለፉትን መልእክቶች ለመሆኑ ታስታውሳቸዋለህ? ትዝስ ይሉሃል ወይ? ማንን
ፈርተህ! እንኳን ልታስታውስው ዛሬ በዚህ መልከ ሰላነሳሁብህ የምን መልእክት? የምን እግዚአብሔር? እያልክ
እንደምታፌዝ ሳይታለም የተፈታ እውነት ነው። ዛሬ ትውልዱ የጠፋ በተለያዩ ባእድ አምልኮቶች፤ ሱሶች፤
ፍፁም የረከሰ ጠባይ እንዲሁም ከእንስሳም ያነሰ የሶዶምነት ባህሪይ የተጠመደ መሆኑ ማንም የማያስተባብለው
ሃቅ ነው።
በኔ በታናሽ ባሪያው በኩል ልዑል ለሁሉም የአዳም ዘር ሲያስተላልፍ የቆየውን የፍርድ ቃል፤ ምክር፤ ግሳጼ፤
ተስፋ ስትሰማው ቆይተሃል። የናቅኸው ናቅህ የተቀበልከው ተቀበልህ። ምርጫህ ነው፤ መልካም አደረግህ።
ውጤቱንም ከዚሁ መልእክትም ሆነ ከቀደሙት የፍርድ ቃል መልእክቶች ሰምተኸዋል ዛሬም የመፈፀሚያህን
መርዶና የተዘጋጀልህን ማጠናቀቂያ ትበሠራለህ!!
የልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ ይላል፤

ፌዘኞች ፈዝን ይፈቅዳሉ፤ ሰነፎችም እውቀትን ይጠላሉ። ወደ ዘለፋዬ ተመለሱ እነሆ


መንፈሴን አፈስስላችኋለሁ፤ ቃሌን አስተምራችኋለሁ፤ በጠራሁ ጊዜ እምቢ ስላላችሁ
እጄን በዘረጋሁ ጊዜ ማንም ስላላስተዋለ፤ ምክሬን ሁሉ ግን ችላ ስላላችሁ፤ ዘለፋዬንም
ስላልፈቀዳችሁ፤ እኔም ስለዚህ በጥፋታችሁ እስቃለሁ፤ ጥፋታችሁም በመጣ ጊዜ
አላግጥባችኋለሁ። ድንጋጤ እንደጎርፍ በደረሰባችሁ ጊዜ፤ ጥፋታችሁ እንደ አውሎ
ንፋስ በመጣ ጊዜ፤ ጭንቅና መከራ በወረደባችሁ ጊዜ፤ የዚያን ጊዜ ይጠሩኛል
እኔ ግን አልመልስም። ተግተው ይሹኛል። ነገር ግን አያገኙኝም፤ እግዚአብሔርን
መፍራት አልመረጡምና፤ ምክሬን አልፈቀዱምና ዘለፋዬንም ሁሉ ንቀዋልና ስለዚህ
የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ። ከራሳቸው ምክር ይጠግባሉ፣ አላዋቂዎችን ከጥበብ

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

መራቅ ይገድላቸዋልና። ሰነፎችንም ቸልተኛ መሆን ያጠፋቸዋልና፤ የሚሰማኝ ግን


በእርጋታ ይቀመጣል። ከመከራም ሥጋት ያርፋል።
መጽሐፈ–ምሳሌ ምእራፍ 1፡ 22 33
ተጠበቅህ፤ ተዘለፍህ፤ ተመከርህ፤ ተገሰጽህ እንኳን ልትሰማ፤ ከላይ የልዑል ቃል እንደሚነግርህ! አፌዝህ፤
ናቅህ፤ እውቀቴንም ሁሉ ጠላህ ይላል የልዑል ቃል። ይህንን እውነትስ ወዴት ታደርገው! ሰማይና ምድርን፣
አንተንም! ማንም የማይመረምረውን ዓለምም የፈጠረን አምላክ የምታቃልል አንተ ማነህ? አቧራና ብናኝ ሆነህ
የምትቀረው ልዑልን ልትገዳደር የደፈርክ እኮ አንተን ማን እንበልህ? ሁላችን እንደምናየው ልቡና ያለው ሰብአዊ
ፍጥረት ሁሉ እንደሚመስከረው ትእቢትህ ከምድሪቱ አልፎ ሰማይን ዘለቀ። እሱ በሰጠህ አእምሮ መልስህ ሰሪህን
ልትቅ ልታቃልል ልታፌዝ የደፈርክ፤ ቅዱስ መንፈሰን በትእቢት ተሞልተህ የተሳደብህ እኮ ማን ትባል?
እንደ አንተ ዓይነት ደፋርን በምን ቃል እንግለፀው? ለነገሩ ሁሉም ስላበቃ፤ መዋቀሻ ጊዜም ስላልሆነ!
ወደሚሆነው እናተኩር። አሁን ከቃሉ እንደሰማኸው፤ መከራህ እንደጎርፍ ደርሶአል፤ ጭንቅና መከራህ
ተደርበውብሃል ሌሎችም የመከራና የጥፋት ዓይነቶች እኔ ልቅደም እኔ ልቅደም ወረፋ ይዘዋል። አንተን
ከመጥፋት! የሚያስጥልህ የሚታደግህ የለም። ከእንግዲህ ልዑልም ድንግልም ብትጠራቸው አይሰሙህም፤
ተግተህም ብትፈልግ አታገኛቸውም፤ ስለሆነም ውጤትህን ከፈጻሚዎቹ ታገኛለህ።
ዛሬ እንደቃሉ ዓለም በምን ሁኔታ ውስጥ ነች? ለ13 ዓመት ያ ሁሉ መልእክት ሲፈስ ወንድሜ ወዴት
ነበርክ?
»» ዓለምና የፍርድ ቃሉ ትናንት ዛሬና ነገስ፤ ምን እንጠብቅ?
»» አገራችን ኢትዮጵያና የፍርድ ቃሉ ትናንት ዛሬስ ነገስ?
»» የዚህ መልእክት ዋናው ዓላማ የእግዚአብሔር ሕዝቦችን ለማፅናት፤ የታላቁን የቁጣ ቀን መድረሱን
ለመግለጽ ሲሆን፤ የተዋህዶ አርበኞች ወዳጅ ወገኖቼ እናንተስ ምን ማድረግ ይጠበቅባችኋል?

ዓለምና የፍርድ ቃሉ ትናንት፤ ዛሬ፤ ነገስ ምን እንጠብቅ?

የልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ ይላል፤

አባቱን የሚረግም፣ እናቱንም የማይባርክ ትውልድ አለ፤ ለራሱ ንፁህ የሆነ


የሚመስለው፤ ከእርኩሰቱ ያልጠራ ትውልድ አለ! ከፍ ከፍ ያሉ አይኖች ያሉት፤
ሽፋሽቶቹም ወደላይ የሚያዩ ትውልድ አለ፤ ድሆችን ከምድር ላይ ችግረኞችንም
ከሰው መካከል ያጠፋና ይጨርስ ዘንድ፤ ጥርሶቹ ሰይፍ መንጋጋዎቹ ካራ የሆኑ
ትውልድ አለ፤ አልቅት –– ስጠን ስጠን የሚሉ ሁለት ሴቶች ልጆች አሉት፤ ሶስቱ
የማይጠግቡ አራቱም በቃን የማይሉ ናቸው፤ እነርሱም – ሲኦልና፤ የማትወልድ
ማሕፀን፤ ውኃ የማትጠግብ ምድርና፤ በቃኝ የማትል እሳት ናቸው። በአባትዋ
የምታላግጥን፤ የእናቷን ትእዛዝ የምትንቅን ዓይን የሸለቆ ቁራዎች ይጎጠጉጡአታል
አሞራዎችም ይበሉአታል።
መጽሐፈ ምሳሌ ፡ ም ፡ 30 ፡11 – 17
አንተ እጅግ የከፋህ ትውልድ፤ ጨካኝ ዘረኛ ሆድ አምላኩ አረመኔነትን ነውረኝነትን፤ አታላይነትን ንቀትን
ትእቢትን እንደ ጌጥ የለበስክ ትውልድ! በውኑ አንተን የመሰለ የዲያብሎስ መገለጫ በምድር ታይቶ ያውቃል?
በፍፁም!!

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ዲያብሎስን ፈቅደህ ፡ በራስህ ላይ ያነገስህ ትውልድ፤ ከንቱ የከንቱዎች ሁሉ ቁንጮ የሆንክ በእውቀትህ
በሰበሰብከው ሀብት ንብረት ገንዘብ ሥልጣን የተመካህ፤ ድሃውን ሕዝብ በዘር ከፋፍለህ በተለያየ እምነት
አቧድነህ አርቲፊሻል ድንበር ፈጥረህ ጨካኝ አውሬነት የተላበሱ ሰራዊት አደራጅተህ ዓለምን የምትፈጭ
የምትቆላ የሉሲፈር አሽከር፤ በአገራችን ኢትዮጵያ ከጌቶችህ ከአለቆችህ ከነአሜሪካ ከነእንግሊዝ ከነአረብ
የዘይት አለቆች ተጣምረህ የእባብነትህን ቆዳ ቀይረህ ህዝቡን ልትገዛ የተገሰልክ፤ ጨካኝ ዘረኞችን ሸክፈህ ያለህ
ዘረኛ ትውልድ በቃሉ ላብስርህ አላጋጭ ነህና ክፉ ጥፋትን አሟሟትን ትሞታለህ የቁራዎች የአሞራዎች ቀለብ
ትሆናለህ። ይህ ደግሞ ሳይውል ሳያድር የሚመጣብህ ፍርድህ ነው። በጀርባህ ያዘልከው የተሸከምከው ነውርህ
አጠንብቶሃልና ከንቱ ትውልድ ገና ብዙ ጉድህ አለና ፍፃሜህን አድምጥ!!!
ዛሬ ያለሃፍረት በመንግሥት ቅየራ ሥም አንዱን ዘረኛ በሌላው ዘረኛ ተክቶ ጋላቢውን ሳይሆን የደከመውን
ፈረስ በሌላ መልክ የቀየረ ፈረስ ሰይማችሁ ያን የሺዎች ዘመን ሙት የዲያብሎስ አገዛዝ ለመተካት የምትደከሙ
ከንቱዎች ናችሁ። የምትደሰኩሩለት ዲሞክራሲ በጌቶቻችሁ ሕይወት እየተመሰከረና እየታየ ነው። ዛሬ
የሕይወትን ጣእም ከልዑል የተሰጠውን ጥሎ፤ በዲያብሎስ ተክቶ የሚኖረውን የከረፋ ፍፁም የጠፋ ትውልድና
የነጩን ዓለም ለሁሉም ነገር መድሃኒት ነው ብላችሁ የምትወትውቱ በእርግጥ ነው የምነግራችሁ አብራችሁ
ትጠረጋላችሁ የምትታመኑባቸውም እነእንግሊዝ አሜሪካ ፈረንሳይ ጀርመን ቻይና ሳኡዲ አረቢያ ኤሜሬትስ
ሌሎችም የትላንቱም ደጋፊዎች የዛሬውም አዋላጆች ከእንግዲህ በኢትዮጵያ ለደረሰው ጥፋት ሁሉ ተጠያቂዎች
በመሆናቸው ይጠረጋሉ እንጂ ማንም የሚያመልጥ የለም።
አስቀድሜ በመግቢያዬ ስለመጨረሻ እጣችሁ የተናገርኩት እንደክፋታችሁ እንደጭካኔያችሁ እንደ
ትእቢታችሁ፤ እስካአሁኗ ሰዓት ድረስ በፀና የጥፋት ተግባር ላይ ስለሆናችሁ ነው፤ ፍርዳችሁ እንደ ፀሐይ
የወጣው! ይህ መልእክት እየደረሰም እንኳ ከመጥፎ ሥራችሁ የማትገቱ ናችሁ። አጥፊያችሁ እናንተን ለመጥረግ
በፈጣን እሩጫ ላይ ነው። ጅማሮውንም እያያችሁት ነው።
ዛሬ ስለዓለም ስናነሳ ትላንት ምን እንደነበር ካልቃኘነው ለዛሬው መንደርደሪያ አናገኝም። ዓለማችን ለብዙ
ዘመናት /በሺ ለተቆጠሩ/ ስትመከር ስትማር፤ ስትገሰፅ፤ ስትቀጣ ኖራለች። ብዙ የእግዚአብሔር አገልጋዮች፤
ከቸሩ አምላካችን ቅዱስ ትእዛዙን በመቀበል! ለመምክር ለመገሰፅ ለማስተማር በመላው ዓለም ተሰማርተው
የታዘዙትን ለመፈፀም በብርቱ ደክመዋል ነገር ግን እጅግ ጥቂቶች ሰምተው ንስሐ ገብተው የተጠቀሙባቸው
ሲሆን፤ በአንጻሩ ደግሞ እጅግ በቁጥር የበዙት አለመቀበል ብቻ አይደለም አሳደዋቸዋል፣ አስረዋቸዋል፤
ገለዋቸዋል። እኔም የቅርቡ የልዑል ታናሽ መልእክተኛ ለ 13 ዓመት ከዚህ መልእክት ጋር ለ7 ጊዜ
የታዘዝኩትን መልእክት ለማድረስ ሞክሬአለሁ። እንደ አባቶቼ ባይሆንም የአቅሜን ዋጋ ከፍያለሁ። ይሁንና
ይህም ሆኖ ተጎድተንም ቢሆን ምን አለ ትውልዱ በመልእክቱ ተጠቅሞ ቢሆን ነበር በማለት ዛሬ ላይ ሆነን
በታላቅ ቁጭት እናዝናለን።
ዓለም ገና ከጅምሩ አምላኳን የሰቀለች የናቀች፤ ድንግልን የናቀች የካደች ያቃለለች ከመሆኗ በላይ የሄደችበት
መንገድ የቀደመው እባብ በቀደደላት ጎዳና ስለነበር የማንንም የልዑል መልእክተኛ ምክርም ሆነ ጩኸት
አልሰማችም። በራሷ ፈቃድ ዲያብሎስን አነገሰች እንጂ የሁሉንም ቅን ምክር አልተቀበለችም። በመካዷና
በጥላቻዋ በንቀቷ ብቻ አልቆመችም። ብዙ የእግዚአብሔርን ሕዝቦች ገደለች አሳደደች አሰቃየች፤ ድርጊቷን
ከልጅ ወደ ልጅ እያሸጋገረች እንደመልካም ነገር እያወራረሰች ኖረች። ብዙ የውሸት እምነት ፈለፈለች
ኮተኮተች አሳደገች የምድርን ገጽ ሁሉ ከደነች። እነካቶሊክ፤ እነእስላም፤ እነቡዲሂዝም፤ እነሺንቶኢዝም፤
እነፕሮቴስታንት እንዲሁም በራሽያ በቡልጋርያ በሩማንያ ጆርጂያ ወዘተ በግሪክ በምሥራቅ አውሮፓ የተንሰራፋው
ኦርየንታል ኦርቶዶከስ /ውስጡ በምስጥ እንደተበላ እንጨት በካቶሊኮች በዲያብሎስ ስውር ሰራዊቶች ተበልተው
ያለቁት/ እኒህ ሁሉ አምነት ተብዬዎች ምድርን ሽፍነው፣ እነሱም አንሰው፤ አንድም ሰው ወደ እግዚአብሔር
ፊቱን እንዳይመልስ አድርገው የአዳም ዘርን በሙሉ ቀይደው ለዛሬው የመጨረሻ የልዑል የቁጣ እርምጃ
7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ላይ እንዲደርስ አብቅተውታል። ዲያብሎስ የፈጠራቸው መንግሥታት በየዘመኑ የየድርሻቸውን የኃጢአት


አዝመራ አምርተው ውጤቱንም ተቀብለው በፍርድ ተካተዋል። ዛሬም ያሉት የዲያብሎስ ኃያል መንግሥታት፤
(የሉሲፈር አገልጋዮች ታማኞች)፤ እግዚአብሔርን ሊዋጉ ተዘጋጅተው በሙሉ ጉልበታቸው ቆመዋል። ዓለም
በዚህ ሁሉ እድሜዋ ያላየችውን የጥፋት መሳሪያ ዓይነት ሰርተው ምድርንም ሰማይንም የውጊያ ወረዳ ሊያደርጉ
ማሟሟቅ ጀምረዋል። ልብ በሉ ሊዋጉ ነው፡ ዝግጅታቸውም ለዚሁ ነው። ማንን? የፈጠራቸውን ምድርንም
ሰማይንም ፍጥረትን ሁሉ እውን ያደረገውን አምላካችንን! እንግዲህ ዓለማችን፤ በነማን ለጥፋት እንድትቆም
እንደተደረገች ስላለፈው የትላንት ጉዞዋ የተፃፉትን ማንበብ ስለሚቻል በዚህ ጊዜ አናጠፋም። ስለዲያብሎስ
ሥውርም ገሃድም ተግባር ብዛት መፃሕፍት ተፅፈዋል።
የሃያላኑ ሴራ በኢትዮጵያ ላይ፤ ስለኢሉሚናቲ አሰራር አደረጃጀት፤ ምድርን እንዴት እንደተቆጣጠሯት
የሚነግሩን ስለሆነ ማንበቡ አስፈላጊ ነው።
እጅግ በትንሹ በእኔ በታናሽ ባሪያው በኩል ልዑል ያስተላለፈውን፡ የትላንቱን የመጀመሪያ የፍርድ ቃል
ብናይ እንዲህ የሚል ኃይለ ቃሎች እናገኛለን።

የመጀመሪያው መልእክት በሕዳር 7 ቀን 1998 ዓ ም ወጣ!


በእጅ ጽሕፈት 21 ገጽ በኮምፒዩተር 11 ገጽ ያለው ነው።
አንዱ አንቀጽ እንዲህ ይላል?
መልእክቱ አራት ከፍሎች አሉት
»» ለዘመናችን ጥበበኞች፤ ገዢዎች ባለጠጎች፤ የኃጢአት ባለሃብቶች፤ አመንዛሪዎች ግብረ ሶዶሞች
ነፍሰ ገዳዮች፤ ዘራፊዎች ነጣቂዎች ድሃ አጥፊዎች፤ በጥቅሉ የቀደመው እባብ /ዲያብሎስ/ ልጆችና
አገልጋዮች በግልጽ በእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ላይ የማፍረስ ሥራ በመሥራት ፍፁም የጨለማን
ሥራ ላነገሱ የዘመኑ እባቦች፤ ዘንዶዎችና ጊንጦችን ይመለከታል።
»» በእምነት ካባ ተጠልለው በተለያየ የእምነት ተቋም ራሳቸውን ያደራጁትን ማለትም እንደ ካቶሊክ ቤተ
ክርስቲያን፤ ፕሮቴስታንት፤ ኦርቶዶክስ፤ አንገሊካን እና ሌሎችን በክርስትና ስም ራሳቸውን ያደራጁ
ተቋማትን ይመለከታል። ሙስሊም፣ ቡዲሂዝም፤ ኮንፊሺያን፤ ሂንዱኢዝም፤ እናም ቁጥራቸው የበዛ
የእምነት ተቋማትን ይመለከታል።
»» ምድሪቱ ላይ በሰፈነው ብርቱ ኃጢአትና ማእበሉ ዘወትር እየተሰቃዩ ላሉ የእግዚአብሔር ሕዝቦች
ይመለከታል
»» ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ገዝርዎቿን መጪውን እድሏን ይመለከታል።
»» ባጠቃላይ ዓለምን በሥራና ተግባሯ ተመስርቶ የሚጠብቃትን ቅጣትና ፍርድ ከዚያም ያለውን መፃኢ
ሁኔታ በአጠቃላይ የያዘ መልእክት የምታገኙ ሲሆን ይህንን መልእክት ለመስማት ባትወዱትም
ወይም ባትፈቅዱትም የማይቀር ስለሆነ ፍርዱ በራሳችሁ ላይ የሚያርፍ ይሆናል። የምትታመኑበት
እውቀት ጥበብ ብልፅግና፤ ወይም የሃሰት አባታችሁ በፍፁም አያድኗችሁምና! ለበደለኞች የሞት
ፍርድ መርዷቸውን የሚሰሙበት፤ ለመልካሞቹ የእግዚአብሔርን ታዳጊነትና የታመነ አባትነቱን
የሚያረጋግጡበት ነው።
ከላይ ያያችኋቸው በመልእክት አንድ ውስጥ ከመጀመሪያው ገጽ ላይ የሚገኝ ቃል ነው። መልእክቱ በሕዳር
7 ቀን 1998 ዓ.ም የዛሬ 13 ዓመት ገደማ የተፃፈ ነው። መልእክቱ በእጅ ፅሑፍ በ21 ገጽ በኮምፕዩተር ዕሑፍ
11 ገጽ ያለው ነው። መልእክቱ የልዑልን ትእግሥት አልቆ የመጀመሪያው የፍርድ የተገለጠበት ነው።

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

መልእክት ሁለትስ?
ይህ መልእክት ግንቦት 27 ቀን 2000 ዓም የተፃፈ ነው። ይህ መልእክት የሰው ልጅ በፍርድ ሂደት ሲሟገት
በሂደቱም ቢረታ እንደገና ይግባኝ ብሎ ስለፍርዱ ቅሬታውን የሚገልጽበት ነው። ልክ እንደዚሁ እንደሰውኛው
የፍርድ ሂደት ሁሉ በልዑልም ፊት የመጀመሪያው መልእክት እንደወጣ ሰዎችም ቅዱሳን መላእክትም በምልጃ
ምሕረትን የጠየቁበት ነው። ሆኖም የሰው ልጅ በፍርዱ ከመደንገጥ ይልቅ ወደማፌዝ ወደመናቅ ወደትእቢት ሄደ
እንጂ ደንግጦ ወደ ንስሐ አልገባም። በመሆኑም ልዑል ዳግም ውሳኔውን አፀና በዚህም መሰረት ይህ ሁለተኛው
መልእክት ወጣ። 11 ገጽን የያዘው ይህ መልእክት ያልዳሰሰው ነገር የለም። ለአብነት ያህል አንድን አንቀጽ
እንመልከት
በዚያ የመጀመሪያ መልእክት የሚገጥማቸውን በግልጽ ተነግሯል ሥራችሁም ተገልፆአል የእሳት ባሕር
ይጠርጋችኋል። ይህም የዓለምን የሙቀት መጠን መጨመር እየተመለከትነው ነው። በሳይንስ ትመልሰዋለህ
ጠብቀው። ለሚያስተውል ራሱንና ወገኑን የት እንዳሉ የሚያይበት መነጽር ነው። አሁን ያ ወቅት ሳትጠቀምበት
አልፏል። 2ኛ ዓመቱን አጠናቋል። መጪው ምንድነው የሚለውን መመልከት ተገቢም አስፈላጊም ነው።
በመጀመሪያውም ሆነ በዚህ በሁለተኛው መልእክት የተለፀው ሁሉ ይፈጸማል። አንዳችም የሚቀር ነገር የለም።
ዓለም በተለያየ መጠን ባለው ችግር ውስጥ ወድቃለች። ሙቀት ጨምሯል፣ ረሃብ ነግሷል፣ ግጭት በዝቷል።
የአየር ንብረት ተለውጦአል። ምድር ባሕርይዋን ለውጣለች። ይህ ሁሉ ልክ ነው። ይኸው ጥፋት በብዙ መቶ
እጥፍ በከፍተኛ መጠን ይጨምራል። የዲያብሎስ ልጆች በእሳት ባሕር ለመጠረጋችሁ መጠራጠር የለባችሁም።
የቻይናን ምድር ያንቀጠቀጠና ያፈረሰ፤ በርማን የጠረገ የቁጣ ምልክት ምን ይመስላችኋል? እናንተጋ አይመጣም?
የሚያግደው አለ? በሺ እጥፍ ይመጣልሀል። እናንተ ሞት ሲውጣችሁ ብቻ ነው የሚገባችሁ። ስለዚህ ጠብቁት
ይላል።
በዚህ መልእክትም ያለውን ሁሉ ለመጥቀስ ስለሚያስቸግር ፈልጋችሁ አንብቡት።

ወደ ሶስተኛው መልእክት እንሂድ፤


ይህ መልእክት በሌላኛው አጠራሩ የአፈጻጸም መልእክት ተብሎ የሚጠቀስ ነው። የወጣው በመጋቢት 19
ቀን 2001 ዓ.ም ነው። ይህ አፈፃፀም 95 ገጽ የያዘ ሲሆን፤ በመላው ዓለም ያሉ ሀገሮችን እጣ ፈንታ /በሁለቱ
መልእክቶች አንፃር ምን እንደሚከናወን/ የሚገልጽና ይህንን መልእክት ማግኘት ትናንት ዛሬ ነገም የሚሆነውን
ከልዑል የተቆረጠውን ፍርድና አፈፃፀሙን መመልከት የሚያስችል መሆኑ ነው።
ቁጥር አንድም ቁጥር ሁለትም አብረውት የተካተቱበት መጽሐፍ አክልም ነው።
በዚህ መልእክት ውስጥ የዋና ዋና የእምነት ተቋማትን ምንነትና የሚገጥማቸውን እጣ ፈንታቸውን
የተብራራበትና የተገለፀበትም ነው። በዚህ መልእክት ውስጥ ስለሰው ባሕርያት፤ ስለኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ
መንግሥትነትና መሪነት የሚያረጋግጥም ነው። በመላው ዓለም እንደአገር የሚታወቁ አገሮች ሁሉ ፍርዳቸው
የተገለጠበት ነው። ይህንንም ፈልጎ ማንበብ ይጠቅማል።

አራተኛው መልእክትን ደግሞ ስናይ


ይህ መልእክት በአብዛኛው የሚያተኩረው በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ነው። የወጣው የካቲት 1 ቀን 2002
ዓ.ም ነው። በዚህ መልእክት ስለተዋህዶ እምነታችንና በእምነታቸው ፀንተው ስለቆሙ የተገለፀበት አንዱ
ሲሆን ከሁሉም በላይ በወቅቱ የአገሪቱ ዘረኛ መሪ በቀጥታ ለግላቸው የተፃፈላቸውን ሦስት ደብዳቤዎች የያዘም
ነው። ለሳቸው የተፃፈው ደብዳቤ ከሥልጣናቸው ስለመወገዳቸው ከልዑል የተሰጠውን ውሳኔ የሚገልጽላቸው
ሲሆን በተጨማሪ የቤተ ክርስቲያን መሪ ለነበሩት ፓትርያርክ በላያቸው ላይ ዲያብሎስ በሥጋቸው እንዲሰለጥን
የታዘዘውም ሌላው ውሳኔ የተገለፀበት ነው። ይህ መልእክት የዘረኛውን ጨካኝ መንግሥት ያፍረከረከና ዛሬም

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወደውድቀታቸው እየነዳቸው ያለ ለመሆኑ ይህ መልእክት ሲወጣ የነበረውንና አሁን የደረሱበትን በግልፅ


የምናይበት ነው።
ከዚሁ አራተኛው መልእክት ለማስታወሻ ያህል አንድን እንቀፅ ላንሳ
በዛሬው መልእክቴ ይላል –
1ኛ/ የምትፅናኑበትን የምታርሙትን መሰረታዊ ጉዳይ በማንሳት ለመምክር
2ኛ/ ጊዜው በማለቁና በመፈፀሙ ሁለንተናዊ ዝግጅት እንድታደርጉ ለማሳሰብ
3ኛ/ በአሁኑ ሰዓት አገዛዙን አክብዶ ያለው የኢትዮጵያ መንግሥት እድል ፈንታው መጠናቀቁን ይህንንም
የእግዚአብሔር ወዳጆች እንድታውቁ በዝርዝር ለማሳወቅ የተዘጋጀ የመጨረሻ የመሰናዶ መልእክት ነው። ይላል።
በተረፈ በቂ ግንዛቤ ለመጨበጥ የምትፈልጉ ፈልጋችሁ ማንበብ ይጠቅማችኋል።

አምስተኛው መልእክትስ ምን ይላል?


አምስተኛው መልእክት በመስከረም 21 ቀን 2004 ዓ.ም ነው የተፃፈው። 41 ገጽም ያለው ነው። መልእክቱ
ለመላው የአዳም ዘር የተፃፈም ነው። መልእክቱ ቀደሞ በወጡት መልእክቶች የታዘዙትን ቅጣቶች ወደ ከፍተኛ
ደረጃ እንዲያድግ የታዘዘበትም ነው።
ለማገናዘቢያ እንዲረዳ ከመልእክቱ አንድን አንቀፅ እናነሳለን።
አመፃ ትእቢትን ትቀድማለች። በትእቢት፤ በንቀት፤ የተሞላችሁ የዘመናችን ገዢዎች አለቆችና ጭፍሮች
የልዑልን ምክር ፍርድና እርምጃ ንቃችሁ፤ ዛሬም እንቋቋማለን በሚል የአባታችሁ የዲያብሎስን ምክር ሰንቃችሁ
እጅግ ወደከበደው እሳትና ጨለማ እየተንደረደራችሁ ትገኛላችሁ። የእግዚአብሔር እጅ አይዝል አይደክም
በከንቱ ትፍረመረማላችሁ እንጂ እየደቀቃችሁ ከመፈፀም አንዳች የሚታደጋችሁ የለም የሰው ዘር ልብ ልትል
ሲገባህ በአመፃህ ገፍተህበታል። በወቀሳው አልተፀፀትክ፤ በፍርዱም አልደነገጥህ የፍርዱ የአፈፃፀም የመጀመሪያ
ደረጃ እርምጃ ዓለምን ሲያናውጥ ያንተ ድንጋይ ልብ ግን ዛሬም በልዑል ቁጣ ነዳጅን ያርከፈክፋል።
ለማስታወሻ ያህል ከላይ ያነሳሁት አንድን አንቀጽ ብቻ ሲሆን ሁሉንም ብታነቡት ስለመልእክቶቹ በቂ
ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ያደርጋል።

ወደ ስድስተኛው መልእክት ስንዘልቅ ደግሞ


ስድስተኛው መልእክት፦ ይህ መልእክት የወጣው በታህሣሥ 19 ቀን 2007 ዓ.ም ነው።
መልእክቱ በዋናነት አዋጅ ነጋሪ ነበር። አዋጁ በመጪው የትንሳኤው ዘመን ዓለምን በበላይነት
የሚያስተዳድረውን የሽግግር ሕግጋተ ሥላሴ እና ቋሚውን ሕግጋተ ሥላሴ ለማወጅ የተዘጋጀ ነው። አዋጁ
ለሕዝብ አልተገለፀም ምከንያቱ ደግሞ፤ የተዘጋጀውም የሚገለጠውም ለትንሳኤው ዘመን ለሚደርሱትና
በዚያው ዘመን ይኖሩበት ዘንድ እድሉ ለተቸራቸው ብቻ ነው።
ዛሬ የምናየው ትውልድ /በመላው ዓለም ያለው ሁሉ/ ፈጣሪውን የካደ፤ በተለያዩ የዲያብሎስ ድርሰት
እምነቶች ውስጥ የሰመጠ፤ አመንዛሪ፣ ግብረሶዶም፣ ትእቢተኛ፣ ውሸታም፣ አታላይ፣ ከሃዲ፣ ጨካኝ፣ ነፍሰ
ገዳይ፣ ዘረኛ፣ አምልኮ ባእድ የሚወድ ተብታቢ፤ ሌባ ወዘተ ነው።
ይህ ትውልድ ደግሞ ቢነግሩት የማይሰማ፤ ቢወቅሱት ቢገስፁት የማይለማ ከእንስሶች በታች አድርጎ ራሱን
የጣለ ነው።

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ከላይ ከ1– 6 የተጠቀሱት መልእክቶች ሁሉም ይህን የጠፋና በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የወደቀ ትውልድ
ለማዳን፤ ከመጣበት እሳትና ቁጣ እንዲድን ለመምክር ነበር ሲገለጹ የኖሩት። ግን ሁላችሁም የልዑል ባሮች
እንደምትመስከሩት በመላው ዓለም ሰፍሮና እየኖረ ያለ ትውልድ በፍፁም የማይደነግጥ የታበየ ከሃዲ ቁስ
አምላኪ ውሽታምና ዘረኛ ትውልድ ነው። ፈጣሪውን ከናቀና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን የሚሳደብ ለጥፋቱ
የሚተጋ ትውልድ በመሆኑ ለዛሬው የመጨረሻው ሰዓት ደርሶአል።
እንግዲህ ስለቀደመው ዓለማችን ስለመልእክቱ፤ የሰው ልጅ በንቀት ሳይጠቀምበት በመቅረቱ የመጣውን
ይሆን የመጨረሻ ቁጣ ለማየት የሚያስችል መጠነኛ ግንዛቤ አግኝታችኋል ብዬ አምናለሁ።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች!!
በጥፋቱ ጎዳና በመገስገስ ላይ ያላችሁ የአዳም ዘር ሁሉ!!
ዛሬን በምንም መልክ እንየው በምንስ እንመስለው ለሁላችንም የሚታይ የሚዳሰስ፤ ያልተሸፈነ እውነት
የምናይበት የምንመሰከረው እንደሆነ ክርክር የሚያስነሳ አይደለም።
ዓለም ዛሬ ምን ላይ ነች? ወዴትስ እየገሰገሰች ነው? በምድሪቱ የተበተነው የአዳም ዘር ሁሉ ዛሬንም ነገንም
እንዴት ያያል? የዓለማችን መንግሥታት፤ ታላላቅ ነን ባይ እምነቶችስ ምን ይሰራሉ? ስለወቅቱስ ምን ይላሉ?
ለሚከተላቸው ሕዝብስ ምን አስጨብጠውታል? ይህን ሁሉ ከዳስስን በኋላ፤ ስለእውነተኞቹ የእግዚአብሔር
ሕዝቦች ጥቂት አንስተን ዓለም ከሚሸነግሉአት ይልቅ ለፈጣሪያችን ቅርብ ከሆኑና ከታመኑ የልዑል ባሮች በኩል
የልዑል እርምጃ ምንድነው፤ የሚለውን እንሰማለን።

ጩህ የሚል ሰው ቃል ምን ብዬ ልጩህ አልሁ – ሥጋ ለባሽ ሁሉ ሳር ነው።


ክብሩም ሁሉ እንደ ምድረ በዳ አበባ ነው። የእግዚአብሔር እስትንፋስ ይነፍስበታልና!
በእውነት ሕዝቡ ሳር ነው። ሳሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል። የአምላካችን ቃል
ግን ለዘለዓለም ጸንታ ትኖራለች።
ትንቢተ ኢሳይያስ 40 ፡ 6 – 8
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች፤ ልዑል ሊያደርግ የወሰነውን ነገር ለልጆቹ ሳይገልፅ አንዳች ነገር አድርጎ
አያውቅም /እነአብርሃም፤ እነኖኅ፤ እነሙሴ ወዘተ/ ቋሚ ምስክሮቻችን ናቸው።
ታሪክ እራሷን ትድግማለች ይላሉ እንዳንድ ጸሐፍት፤ አባታችን ኖኅ ስለጥፋት ውኃ መምጣት ለሰው ልጅ
ሁሉ በመግለፅ ሲጮህ ሰሚው ጠፊ ትውልድ ኃጢአት ያጠለቀው ትውልድ እንኳን ሊሰማው ቀርቶ፤ ለራሱና
ሊድኑ ለተፈቀደላቸው መጠለያ መርከብ ሲያበጅ ሲመለከቱ በድርጊቱ በመደነቅ ዛሬ እንደምናየው /ሲኒማና
ትያትር ሳይከፍሉ/ ይዝናኑና ይስቁ ነበር። እጅግ ተደስተውም ያፌዙ እንደነበር ሁላችሁም ከልዑል ቃል
የሰማችሁት እውነት ነው።
ኖኅ አባታችን በፌዛቸው ሳይደነቅ ስለአጠፋፋቸው በማዘን ዘወትር ተመለሱ በማለት ብዙ ዓመታትን አሳልፎ
ነበር። ዛሬስ? ብዙ ኖሆች፣ ብዙ አብርሃሞች፣ ብዙ ኤልያሶች፣ የዛሬውን /ለመጨረሻው ጥፋት የደረሰውን
ትውልድ/ ጨካኝ፣ ስብእናውን ከእንስሳ በታች የጣለ፤ የጠፋ ዘር ለመመለስ ያልጣሩት ያልደከሙበት መንገድ
አለ? የለም። ማን ይስማ፤ ራሱ ልዑል ቢመጣ ያልተመለሰ ትውልድ ልዑልም ድንግልም ቅዱሳን መላእክትም፤
ሰማዕታትም ቢጨመሩበትም አልሰማም። እንግዲህ ሥላሴም ድንግልም ለሰው ካላቸው ፍቅር ተነስተው በጉጉት
አንድ ቀን ይጸጸታል በማለት ያልታገሱበት የዘመን ክስተት የለም አልነበረምም።
አባታችን ኖኅ ቁጣው ሲመጣ ጠፊዎቹ ቢያፌዙበትም እሱ ግን ከመንገዱ ፈቅ ሳይል እነሱም ከእልቂታቸው
ሳይድኑ ለአንዴም ለመጨረሻውም ተከደኑ።

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወገኔ የዘመናችን ትውልድ፥ ስትመከር ሥትገሰፅ ስትቀጣም የማትሰማ አላጋጭ ፌዘኛ ትውልድ ከጠፋው
የኖኅ ዘመን ትውልድ በብዙ እጥፍ የምትበልጠው ከንቱ ትውልድ ምን ይበጅሃል? ልዑል እጁን ዘርግቶ
ና ልጄ ብሎ በታላቅ ትእግስት ስንት ዘመን ጠበቀህ? ታውቀዋለህ? 2011 የምሕረት ዘመን 5500 የሕገ
ልቡናና የሕግ ዘመን በጥቅሉ ከ7500 ዓመታት በላይ ጠበቅህ፣ ታገሰህ፣ መከረህ፣ ገሰጽህ፣ ቀጣህ ብትመለስ
ብሎ እጅግ ውድ ዋጋ ከፈለልህ። ልጆቹን ስትጨርስ፤ ስትገል ስታሳድድ! ስታስር እየቆሰለ ታግሷል ተስፋ
እስከሚቆርጥበት ድረስ እድሜን እየሰጠ ታገሰህ። ይህ ሁሉ ሆኖ መቼ ፍንክች ልትል ዲያብሎስን ታምነሃላ፤
ምድርን ቅራቅንቦህን አለኝ እምትለው ጥበብህን እሱው በፈጠረልህ አእምሮ ተጠቅመህ በሰራኸው ሰው ጨራሽ
መሳሪያ፣ እንዲሁም በሕዋ ላይ በሰቀልከው ሳተላይት ልትዋጋውም ወስነሃል እንግዲህ መልሱ ምን ይሁን
አንተም ታውቀዋለህ ወገብህን ታጥቀህ መጠበቅ ነው። ታየዋለህ እኛም የልዑል ባሮች በሱ ታምነን ያለን
ሁሉ፤ ከአንተ ጥፋት እንዴት እንደሚታደገን እንዴትስ ልጆቹን እንደሚያከብር ወደከፍታውም እንደሚያወጣ
ትመለከተዋለህ። አተንም የዲያብሎስ ታማኝና ተስፈኛ እንዴት እየቀቀለህ በእሳት ባሕር እየጠረገ ከታመንክበት
ኩታንኩትህ ጋር ወደትቢያነት እንደሚቀይርህ ታየዋለህ!
አሁን የመዋቀሻ፤ ተመለስ አትመለስ፤ ተገሰፅ ተወቀስ፤ ተለመን ተብሎ የሚጠየቁበት የሚዘከሩበት ጊዜ
አይደለም። ይህም ሁሉ አልፎ ለ13 ዓመት ፍርድ ተሰጥቶ ተጠብቆ ውጤት ጠፍቶ ከተደመደመ በኋላ ከልዑል
እንደ እሳተ ጎሞራ ከሚነደው ቁጣው መሃል የሚቆም የሚሸመግል የሚዳኝስ ማነው? ሁሉ ሰማያዊውም
ምድራዊውም ዘዴና መፍትሄ አልቋል። መላው የልዑል ባሪያ ሁሉ እግዚአብሔር ወደመራው መጠለያው
ተሸሽጎአል። ለራሱ ፈርቶ ሳይሆን ያንተ የዲያብሎስ ተስፈኛ አጠፋፍ እጅግ አስደንጋጭ በምድራችን ታሪክም
ያልታየ ያልተሰማ በመሆኑ መመልከቱም መስማቱም ሰቅጣጭ ሕሊናን የሚሰቅዝ እጅግ የሚያብረከርክ በመሆኑ
እንደኖኅ አባታችን ቤቱን ዘግቶ መከተት ብቻ መሆኑን አውቆ የተቀመጠ ነው።
በሶዶም ዘመን ልዑል ሶዶምን ሲጎበኝ ደፋሮቹ ሶዶማውያን በሎጥ ቤት የተገኘትን ቅዱሳን መላእክትን ሎጥ
እንዲያወጣላቸው የጠየቁ ጉዶች ነበሩ። ወዲያው የመጣው መልስ ምን እንደ ነበር ታውቃላችሁ ሁሉም ሶዶማዊ
የእሳት እራት ሆኗል። ትውልድ እንዲማርበት ዛሬ ድረስ ያ ቦታ የዮርዳኖስ ሸለቆ ተብሎ በውስጡም ያለው
የሙት ባሕር ተብሎ ይታወቃል። የወቅቱ ሶዶማውያን እንደ ፌዛቸው፤ እንደ እርኩሰታቸው፤ እንደጥጋባቸው
እሳት በላቸው፤ ሎጥና ልጆቹ ግን ከቁጣው አምልጠዋል።
አንተስ የዘመናችን ሶዶም ሶዶማዊ!! ሌዝቢያን አመንዛሪ፤ ከእንስሳ በታች ሰብእናህን ያወረድክ ማን
ያስጥልሃል? በወንጀልህ ሶዶምን ያጸደቅህ እኮ ነህ!! እነሱስ ሶዶማዊ ነበሩ አንተ ግን እነሱ የተኮነኑበትን እንደ
አንድ ትንሽ ጉዳይ ደርበኸዋል። ሶዶምነት በሕግ አፅድቀሃል፤ ያልተከተሉን አገሮች አስገድደህ እንዲቀበሉ
አድርገሃል። ምንዝርናን ኢንዱስትሪ አድርገሃል። የሰውን ልጅ እንደሸቀጥ ቆጥረሃል። ክቡሩን የሰው ልጅ
ለምትታመንበት ዲያብሎስ ዘወትር መስዋት /ጭዳ/ አድርገሃል። በተረት እምነቶችህ፤ በፍልስፍና የተሽሞነሞኑ
ሃይማኖትህ፣ በግልጽና ቅንጣት ሃፍረት ባጣ ትእቢናት ክህደትህ ዲያብሎስን የሚያሞግሱ የሚያወድሱ
የሚያስመልኩ ስመ ብዙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችን ፈጥረሃል። አሁንም ድረስ ታምነህበታል አንግሰሃል፤
ሕዝብና ሕዝብን አፋጅተህ ዘረኝነትን በየዘርፉ ተክለህ ሕዝብና ሕዝብን አጫርሰሃል ዛሬም መጠንና ዓይነቱን
አራቅቀህ ተግብረሃል፤ ያንተ የዛሬው ትውልድ ጉድ ተዘርዝሮ መማለቂያ የሚበጅለት አይደለም ይህን በዚህ
ገታ ላድርግና!! ስለአባታችን ሙሴ እንመልከት።
በዘመነ መሴ ልዑል የእግዚአብሔር ሕዝቦችን እስራኤላውያንን ሲታደግ፤ እጅግ በሚደንቅ ትድግናው
እስራኤላውያንን ከፈርኦን ሰንሰለት ነፃ አውጥቶአቸዋል። የነሱ ነፃ መውጣቱ ብቻ ሳይሆን የሚደንቀው የፈርኦን
አለቃና ምንዝሩ የደረሰባቸው ጥፋት ትእቢትና ልበ ደንዳናነት አንዲሁም ጣኦት አምላኪነት በእግዚአብሔር ፊት
ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍሉ ከመስረት እንደሚነቅሉ የታየበት የታሪካችን ክስተት ሆኖ አልፏል። ያንን ሁሉ
ድንቅ የማዳን ሥራ ደጋግመው ሲንቁ ሲያቃልሉ የነበሩ እስራኤላውያን ለኛ ለዛሬው ትውልዶች ምን ትምህርት
12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

እንደሚሰጡን የሁሉም ሕሊና ይመርምረው። እስራኤላውያን ነጻ ከወጡበት የግብጽ ምድር ሲወጡ በአስፈሪነት
በምርኮ በሀብት በብር በወርቅ ስጦታ ታድለው ነው። ልዑል ከዚህም በላይ የኤርትራን ባሕር ከፍሎ እነርሱን
አሻግሮ በትእቢቱ እንደገና ገንፍሎ የመጣውን የፈርኦን ጦር በኤርትራ ባሕር አስጥሞ የአምላክነቱን የታዳጊነቱን
ኃይል አሳይቶአቸዋል።
ጠማማው የእስራኤል ሕዝብ ግን ለክህደት ጊዜ አልፈጀበትም። እንደገና ግብጽን ተመኘ፤ ፈጥኖም
ወደግብጻውያን አምልኮ ባእድ ተመለሰ። ልብ በል ወገኔ ተአምሩን ትድግናውን ቸርነቱን ያየው ያ የእስራኤል
ሕዝብ በክህደቱ የልዑልን ትእግስት በብርቱ በመገዳደሩ ልጆቹ የተገባለትን ምድር ወረሱ እንጂ እሱ ግን
በበረሃው ቀረ። ጧትም ማታም ከልዑል ፈቃድ ጋር መጋጨት ሥራው ነበርና ፍጻሜው በበረሃ መቅረት ሆነ።
እግዚአብሔርን የሚገዳደር የሚፈትን ትውልድ ፍፃሜው በበረሃ መቅረት ነው። ልክ የዛሬው ትውልድ መጥቶ
መጥቶ ከገደሉ አፍ ላይ እንደቆመ ሁሉና በትእቢት ተሞልቶ መገፍተሩን እንደሚጠብቅ ሆኖ ላለነው የመጥፋት
ምንነት ምስክር ሊሆን ቀርቧል።
እንግዲህ ወገኔ ስለስንቱ እናንሳ ስለእያሱ፣ ስለኤልያስ፤ ስለነዳዊት ሁሉንም ታውቃቸዋለህ፤ ልብ ብለህ
አድምጥ፤ ምንም መጥፊያህ ላይ ብትደርስም በሞትህ ጉዞ ውስጥ እውነትን እየሰማህ ወደመደምደሚያህ
መድረስ አለብህ። ባንተ ቀሪው የልዑል ሕዝብ የሚማርበትን ታሪክና ገድል ከአንተ ተሞከሮን ይጨብጣል።
ለሕይወቱና ለልጆቹ ማስተማሪያ ግብአት እንዲሆን ወደትንሳኤው ዘመን ይዞትም ይሻገራል። አንተም እንደ
እስራኤላውያን አባቶች በጥመታቸው በክህደታቸው በየበረሃው ወድቀው እንደቀሩት ትሆናለህ። መላው የአዳም
ዘር! አንተ የዛሬው ትውልድ ምን እንበልህ ምንም ማለት እንችልም በቃ! አከተመ! ተደመደመ! ስለአንተ
ማሰብም መስማትም የማይቻልበት ፍፁም የሚዘገንንበትም ወቅት ላይ ደርሰናል። እንግዲህ ዲሞክራሲህን፤
የዲያብሎስ ድርሰትህን የታበይክበት ሥልጣኔህን የከመርከው መሳሪያና ሀብትህን ሁሉም ላይታደጉህ ሲተኑ
አንተም ዘር ማንዘርህም ከአባትህ ከዲያብሎስ ጋር እሁኑኑ ስትካተት ታየዋለህ። እውነቱ ይህ ነው።
የእግዚአብሔር ሕዝብ መፋረጃ ነው። ብትወደውም ብትጠላውም አንዳንተው ሰው ነው፤ ልዩነቱ እሱ
በፈጠረው አምላኩ ይታመናል አንተ ደግሞ በፍጡሩ ዲያብሎስ ትታመናለህ ትመካለህ። ልብ በል የእግዚአብሔር
ሕዝብ፤ በልዑል ፊት የከበረ የሚወደድ ነው። ቁጥር በእግዚአብሔር ዘንድ ትርጉም የለውም። በዘመነ እስራኤል
በኤልዛቤልና በአከዓብ ንግሥና ዘመን የእስራኤል ሕዝብ አግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ የተመረጡት ካሕናት ሁሉ
እግዚአብሔርን ክደው ቡኤል ዘቡኤልን አንግሰው በሚያመልኩበት ዘመን የታመነው የእግዚአብሔር አገልጋይ
ኤልያስ ብቻ ነበር፤ በአደባባይ ወጥቶ በአምላኩ በሠራዊት ሁሉ ጌታ ስም የተፋለማቸው። ታዲያ እግዚአብሔር
ቁጥር ገደደው በፍፁም፤ በቃሉ የታመነው አምላካችን ከኤልያስ ጎን ቆመ እንጂ በቁጥር ምድርን ከሸፈኑት
እስራኤላውያን ጎን አልቆመም። እግዚአብሔር እውነት ነው ስሙም ያው እውነት ነው፤ ቅንም ነው እውነተኛ
ዳኛም ነው፤ ለማንም ፊት አይቶ የማያዳላ ነው። ፍቅርም ነው ስሙም ያው ፍቅር ነው። እንዲያ በመሆኑ ነው
7500 ዓመታትን የተሸከመን ቸር ነው እየበደልነው ተሽከሞ እኑሮናል ከዘመን ዘመን አሸጋግሮናል።
ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ሕዝብ ውኃ ልክ ነው መፋረጃም ነው። መለኪያ ነው። ስለመርዶክዮስ ስሰነዳንኤል
ስለነሕዝቅኤል ስለነዳዊት ወዘተ ... በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንደከዋክብት የሚያበራ
ሆኖ ተመዝግቧል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ውኃ ልክ ነው። ለሌላው የአዳም ዘር ሁሉ እኩል የተዘራውን
የእግዚአብሔር ቃል የሰማ ቢሆንም በትክከል የተቀበለው እንደቃሉ ሆኖ በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ፀንቶ፤
ከመላው ዓለም ሕዝብ አንፃር በቁጥር ኢምንት ቢሆንም በልዑል ፊት ግን የተወደደ ሆኖአል። ብዙ እምነት
እንደጎርፍ የሚፈስባት ምድራችን ሁሉንም አንግሣ የተዋህዶ እምነትን ብቻ እንደጠላት ስታሳድድ ኖራለች።
ያ የምታሳድደው ሰው ደግሞ እግዚአብሔርና ቃሉን በሕይወታቸው አንግሰው በእለት ተእለት ሕይወታቸው

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

የሚመላለሱ ናቸው። ብርሃናቸው በሰው ሁሉ ፊት እንዲበራና ምሳሌም እንዲሆን ተደርጎ በልዑል የተቀረፀ
በመሆኑ ዛሬም በእግዚአብሔር በስስት የሚታዩ ልጆቹ ናቸው።
ኖኅ ምድርንና በወቅቱ የነበረውን አመፀኛ ሕዝብ በእምነቱ ዕናት እየኮነነ እግዚአብሔርም በዚህ በእውነት
ላይ በቆመ ውድ ባሪያው በኩል ለማይታዘዘው ለአመጸው ትውልድ ፍርዱንና ወቀሳውን ሲያስተላልፍ ኖሯል።
ውኃ ልኩ ኖኅ በጽድቅ ሥራው ዓለምን ኮንኗል።
የልዑል ባሪያ ታማኙና ቀናኢው ኤልያስ በዘመኑ ውሀ ልክ ሆኖ አልፏል። ኤልያስ እስራኤላውያን እጅግ
ባመፁበት ዘመን ስለእግዚአብሔር ቃል ፀንቶ በመቆም እንደ ፀሐይ ያበራ የእምነት ጀግና ነው። በጽድቅ ሥራው
እንደፀሐይ በሚያበራ ሕይወቱ ልዑልን በሕይወቱ ያነገሰ ጀግና ነው። ኤልያስ በዚያ ክፉ ዘመን ስደቱንም
ረሃቡንም ሁሉንም የጠላት ጥቃት የተቀበለ የልዑል ባሪያ ነው።
እስራኤላውያን በዘመናቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ ማመጽን የሚያዘወትሩ ነበሩ። በንግሥት ኤልዛቤልና
በንጉሥ አካብ ዘመን ሁሉንም ካሕናት ጨምሮ መላው የእስራኤል ሕዝብ አምላኩን ክዶ ነበር። እግዚአብሔር
በስውር ከጠበቃቸው የታመኑ ልጆቹ በስተቀር ሁሉም እስራኤላውያን ቡኤል ዘቡኤልን የሚያመልኩና ንጉሱም
ንግስቲቱም በዚሁ ጣኦት ፍቅር የተለከፉ ነበሩ።
የልዑል ቃል በመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ፤ ምዕ 18 ፡ 15 – 40 እንዲህ ይላል!

ሆኖም የእግዚአብሔር ባሪያ ኤልያስ ስለአምላኩ ታላቅ ቀናኢ ነበርና በስሩ


ከሚያገለግለው አንዱ የሆነውን አብዲዩን ኤልያስ እንዲህ አለው! በፊቱ የቆምሁት
ሕያው እግዚአብሔርን እኔ ዛሬ ለእርሱ እገለጣለሁ /ለአክአብ/ አለ።
አብድዩም አክአብን ሊገናኘው ሄደ፤ ነገረውም። አክአብም ኤልያስን ሊገናኘው መጣ።
አክአብም ኤልያስን ባየው ጊዜ እስራኤልን የምትገለባብጥ አንተ ነህን? አለው።
ኤልያስም፦ እስራኤልን የምትገለባብጡ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትታችሁ በዓሊምን
የተከተላችሁ አንተና የአባትህ ቤት ናችሁ፤ እንጂ እኔ አይደለሁም። አሁንም ልከህ
እስራኤልን ሁሉ በኤልዛቤልም ማእድ የሚበሉትን አራት መቶ ሃምሳ የበአልን ነቢያት
አራት መቶም የማምለኪያ አፀድን ነቢያት ወደ እኔ ወደ ቄርሜሎስ ተራራ ሰብሰብ
አለ።
አክአብም ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ ልኮ ነቢያቱን ሁሉ ወደ ቄርሜሎስ ተራራ ሰበሰበ።
ኤልያስም ወደ ሕዝቡ ሁሉ ቀርቦ፦ እስከመቼ ድረስ በሁለት ሃሳብ ታነክሳላችሁ፤
እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ፤ በአል ግን አምላክ ቢሆን እርሱን
ተከተሉ አለ። ሕዝቡም አንዲት ቃል አልመለሱለትም። ኤልያስም ሕዝቡን አለ፦
ከእግዚአብሔር ነቢያት እኔ ብቻ ቀርቻለሁ፤ የበአል ነቢያት ግን አራት መቶ ሃምሳ
ሰዎች ናቸው። ሁለት ወይፈኖችን ይስጡን እነርሱ አንድ ወይፈን ይምረጡ እየበለቱም
ይቁረጡት በእንጨትም ላይ ያኑሩት በበታቹም እሳት አይጨምሩ፤ እኔም ሁለተኛውን
ወይፈን አዘጋጃለሁ በእንጨቱም ላይ አኖረዋለሁ። በበታቹም እሳት አልጨምርም
እናንተም የአምላካችሁን ስም ጥሩ እኔም የእግዚአብሔርን ስም እጠራለሁ ሰምቶም
በእሳት የሚመልስ አምላክ እርሱ አምላክ ይሁን ሕዝቡም ሁሉ ይህ ነገር መልካም
ነው ብለው መለሱ።
ኤልያስም የበአልን ነቢያት፦ እናንተ ብዙዎች ናችሁና አስቀድማችሁ አንድ ወይፈን
ምረጡና አዘጋጁ የአምላካችሁንም ስም ጥሩ በበታቹም እሳት አትጨምሩ አላቸው።
ወይፈኑንም ወስደው አዘጋጁ። ከጠዋትም እስከ ቀትር ድረስ በአል ሆይ ስማን እያሉ
የበአልን ስም ጠሩ። ድምጽም አልነበረም፤ የሚመልስም አልነበረም። በሠሩትም
መሰዊያ ዙሪያ እያነከሱ ያሸበሽቡ ነበር። በቀትርም ጊዜ ኤልያስ፦ አምላክ ነውና
14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

በታላቅ ቃል ጮሁ ምናልባት ሃሳብ ይዞታል ወይም ፈቀቅ ብሏል። ወይም ወደ


መንገድ ሄዷል። ወይም ተኝቶ እንደሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል። እያለ አላገጠባቸው።
በታላቅም ቃል ይጮኹ፤ እንደ ልማዳቸውም ደማቸው እስኪፈስስ ድረስ ገላቸውን
በካራና በቀጭኔ ይቧጭሩ ነበር። ቀትርም ካለፈ በኋላ መስዋእተ ሰርክ እስኪደርስ ድረስ
ትንቢት ይናገሩ ነበር። ድምጽም አልነበረም የሚመልስና የሚያደምጥም አልነበረም።
ኤልያስም ሕዝቡን አለ፦ ወደ እኔ ቅረቡ አላቸው ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ ቀረቡ
የነበረውንም የእግዚአብሔር መሰዊያ አበጀ። ኤልያስም፦ ስምህ እስራኤል ይሆናል
የሚል የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ደረሰለት እንደ ያዕቆብ ልጆች ነገድ ቁጥር አሥራ
ሁለቱን ድንጋዮች ወሰደ። ከድንጊያዎቹም ለእግዚአብሔር ስም መሰዊያ ሰራ፤
በመሰዊያውም ዙሪያ ሁለት መስፈሪያ እህል የሚይዝ ጉድጓድ ቆፈረ። እንጨቱንም
በተርታ አደረገ ወይፈኑንም በብልት በብልቱ ቆረጠ። በእንጨቱም ላይ አኖረና
አራት ጋን ውኃ ሙሉ በሚቃጠለው መስዋእትና በእንጨቱ ላይ አፍስሱ አለ።
ደግሞም ድገሙ አለ። እነርሱም ደገሙ። እርሱም ሶስተኛ አድርጉ እለ። ሶስተኛም
አደረጉ፤ ውኃውም በመሰዊያው ዙሪያ ፈሰሰ። ደግሞም ጉድጓዱን በውኃ ሞላው።
መስዋእተ ሰርክ በሚቀርብበት ጊዜ ነብዩ ኤልያስ ቀርቦ – አቤቱ የአብርሃምና
የይስሐቅ የእስራኤል አምላክ ሆይ፤ አንተ በእስራኤል ላይ አምላክ እንደሆንህ እኔም
ባሪያህ እንደሆንሁ ይህንንም ሁሉ በቃልህ እንዳደረግኸው ዛሬ ይገለጥ። አንተ አቤቱ
አምላክ እንደሆንህ ልባቸውንም ደግሞ እንደመለስህ ይህ ሕዝብ ያውቅ ዘንድ ስማኝ
አቤቱ ስማኝ እለ። የእግዚአብሔርም እሳት ወደቀች፤ የሚቃጠለው መስዋእቱንም
እንጨቱንም ድንጋዮቹንም አፈሩንም በላች በጉድጓዱ ውስጥ ያለውንም ውኃ ላሰች።
ሕዝቡ ሁሉ ያንን ባዩ ጊዜ በግምባራቸው ተደፍተው እግዚአብሔር እርሱ አምላክ
ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ አምላክ ነው አሉ። ኤልያስም ከበአል ነቢያት አንድ ሰው
እንዳያመልጥ ያዙ አላቸው። ያዙአቸውም ኤልያስም ወደ ቂሶን ወንዝ ወስዶ በዚያ
አሳረዳቸው።
ይላል የልዑል ቃል! የእምነት አርበኛው ኤልያስ ማን እንደነበር በጥቂቱ አየን።
ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ሕዝቦች! ይህ መልእክት ስለእናንተ ተፃፈ እንጂ ስለ ጠፋው የዛሬው ትውልድ
አይደለም። ቢመከር ቢዘከር፤ ቢወቀስ ቢገሰፅ፤ ቢቀጣ ቢመታ፤ ምንም መስሚያ ያጣ ጉደኛ በሰው ታሪክ
ያልታየ ትውልድን ከእንግዲህ ለመመለስ ታስቦ አይደለም። ያሁሉ ሆኖ አልፏል። ስለ ውኃ ልኩ የእምነት
አርበኛው ኤልያስ ቢነገር ቢዘከር አይጠገብም። ወግኖቼ! ያ ሁሉ ነቢያት አልቆ ብቻውን የቀረው የእምነት
አርበኛው ኤልያስ ሥፍራውን አለቀቀም መላው የመንግሥት ኃይል ሁሉ ቢሰማራበት እንደ የአሰፈላጊነቱ
የመንፈሳዊ ውጊያ ስልቱን በመቀያየር ሲበረታ ለማጥቃት ሲዳከም የመከላከል ሥፍራ በመያዝ ጠላቱን ሁሉ
ሲፋለም አሳልፏል በመጨረሻም የድል ባለቤት ሆኖአል። እምንታምንበት አምላክ ከቃል ኪዳኑ አይዘንፍም፤
እርግጥ በኛ እሳቤ የዘገየ ይመስለናል አይደለም ቀድሞም ባላትና ፈቃዱ ባፀናት ሰዓት ይደርሳል። አሁንም
እነሆ ደርሷል።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ምርጦች አንዱን የእምነት አርበኛ ላንሳ፤ ብዙውን እንደምሳሌ የማነሳቸው የእምነታችን
አርበኞች ለዛሬው ለምናየው መከራና ፈተና በምሳሌነት ይመስላል ያልኩትን ብቻ እንጂ ሁሉን ለማንሳት በዚች
አጭር ጽሑፍ አይቻልም። መርዶክዮስን ላንሳውና ወደ ሌላ ጉዳያችን እንመለስ።
መርዶክዮስ የእስራኤል ሰው አይሁዳዊ ነበር። በዘመኑ እስራኤላውያን በናቡከደነፆር ተወረውና ተማርከው
ተበትነውም በከባድ ሕይወት ውስጥ ይኖሩ ነበር። መርዶክዮስ የተማረከው የእስራኤል ንጉስ ወታደር ነበር።
ከተማረኩትም ወታደሮች አንዱ እሱ ነበር። እናትና አባቷን በወረራው ያጣችው ሀደሳ /አስቴር/ በአጎቷ
በመርዶክዮስ እጅ ያደገችም ነበረች። መርዶክዮስ ኑሮውን በዚያው አድርጎ ነበር። ንጉስ አርጤክስስ በአንድ
15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወቅት ሚስቱ ስለናቀችው እሷን ካስወገደ በኋላ ልጃገረዶች ሲመለመሉ አስቴር እድል ገጥሞእት ተመልምላ
ገባች። ንጉሱ ባያት ጊዜ ከዚያ ሁሉ ልጃገረዶች ወደዳት። ባጭሩ ንግሥት ሆነች ሆኖም አይሁድነቷ አይታወቅም
ነበር። መርዶክዮስ ከአደባባዩ የማይጠፋ ስለአስቴርም የሚከታተል ነበር። በዚህ ወቅት ንጉስን ለመገልበጥ
ገበታና ታራ አሲረው ነበር፤ ቀድሞ ጉዳዩ ለመርዶክዮስ ደርሶ ስለነበር መርዶክዮስ ለአስቴር ነግሮ አስቴርም
ለንጉሱ ነግራ ጉዳዩ ተመርምሮ እውነት ሆኖ በመገኘቱ ሰዎቹ በስቅላት ተቀጡ ይህም በንጉሱ መዝገብ ሰፈረ።
ከዚህ በኋላ ንጉስ እርጤክስስ ሀማን ከፍ ከፍ አደረገው በሁሉም ላይ ከፍ አድርጎ አሰለጠነው። በአደባባይም
ሁሉ ለሀማ የማይሰግድ አልነበረም ከመርዶክዮስ በስተቀር። ሆኖም አብረውት በአደባባዩ የነበሩት ጓደኞቹ ለሀማ
ለምን አትሰግድም ብለው ቢጠይቁት እንደማይሰግድ በማወቃቸው ስለአይሁድነቱና ስለአለመስገዱ ለሀማ ነገሩት
ሀማም እጅግ ጠላው ሊሰቅለው ወሰነ። መላውን አይሁድ ሁሉ ሊያጠፋ ወሰነ።
ሀማ ለንጉስ አርጤክስስ አይሁድ ለሕጉ እንደማይገዙና እንደማይታዘዙ በመንገሩ ሁሉም አይሁድ እንዲገደሉ
ንጉሱ ወስኖ በሀማ እጅ ትእዛዝ /አዋጅ/ አወጣ በሱሳ ግንብም ታወጀ። መርዶክዮስ ወዲያው ለንግሥት
አስቴር እንዲነገራት አደረገ እሱም በታላቅ ሃዘን በጾም በጸሎት ወደቀ ሁሉም አይሁዳዊ በሃዘን ውስጥ ወደቁ።
አስቴርም የአዋጁ ቅጂና የሆነውን ሁሉ ከአጎቷ በመልእክተኛዋ ተረዳች። ወደ ንጉሱም ልትገባ ወሰነች
ገባችም። ንጉስ ሳይጠራ መግባት ክልክል ነበርና አደጋውን ብታውቅም ስለ ሕዝቧ የመጣውን ለመቀበል ወስና
ገባች ንጉስ ሲያያት ደነገጠ አብዝቶም ወደዳት ዘንጉንም ዘረጋላት። አስቴርም በንጉሱ እጅግ ተወዳ ነበርና
ንጉስ ንግሥት ሆይ ምን ፈለግሽ የምትሽውን ሁሉ አደርጋለሁ የመንግሥቴን እኩሌታም ቢሆን አላት። እሷም
ንጉሥ ቢወድድ ወደማዘጋጀው ግብዣ ከሀማ ጋር ይምጣ አለች። ንጉሥም ደስ አለው ሊሄድም ወሰነ። ሀማ
በአስቴር መጠራቱ አስደስቶት ነበር። ነገር ግን ጠላቴ የሚለው መርዶክዮስ ከአደባባዩ ባለመናወፅ ተቀምጦ
ሲያየው ስለማይሰግድለትም ወደ ቤቱ እንደደረሰ ለቤተሰቡ ስለመርዶክዮስ ነገራቸው፤ ስቀለው ብለው መከሩት
መስቀያውን አዘጋጀ ለማስፈቀድም ወደንጉሡ ገባ። ንጉሥ ሌሊቱን እንቅልፍ ከልከሎት ነበርና እሱን ከግልበጣ
ስላዳኑት ሰዎች ምን ተደረገ ብሎ ባለሟሎቹን ጠየቀ። እነሱም ምንም እንዳልተደረገ ነገሩት ሀማን ጥሩልኝ
ብሎ ሲናገር ንጉሥ ሆይ ሀማ በአዳራሹ ቆሟል አሉት። እንዲገባ አዘዘ ገባ ንጉሥ ለሀማ እንዲህ አለው ለመሆኑ
ለንጉሥ መልካም ላደረገ ምን መደረግ አለበት ሲል ሃማ ከራሱ በላይ ማንም የለም ብሎ በማሰብ ለንጉሥ እንዲህ
አለ። ንጉሥ ሆይ ለዚህ ሰው የንጉሥ ልብስ የንጉሥ ፈረስ የንጉሥ ዘውድ ተደርጎለት በአደባባዩ አዋጅ እየተነገረ
ንጉሥ ሰደደው ላከበረው እንዲህ ይደረግለታል አለ፤ ንጉሥም በል ያልከውን ሁሉ በሱሳ ግንብ በአደባባዩ
ለተቀመጠው ለመርዶክዮስ ምንም ሳታጎድል አድርግለት ብሎ አዘዘው። ሀማም በድንጋጤ ተውጦ የተባለውን
አደረገ። ወደቤቱም ሮጦ ሄዶ ለሚስቱና ለቤተሰቡ የሆነውን ነገራቸው እነሱም በፊቱ መውደቅ የጀመርክለት
ሰው ከአይሁድ ወገን ስለሆነ ትወድቅለታለህ እንጂ አታሸንፈውም ብለው ነገሩት።
የአስቴር የግብዣው ሰዓት በመድረሱ እንዲደርስ ሀማን አስቸኮሉት። ሀማም ደረሰ። ንጉሥ በግብዣው
ተገኘ፤ አስከትሎም ለአስቴር ምንድነው የምትሽው የመንግሥቴም እኩሌታም ቢሆን ይደረጋል ሲል ተናገራት።
ንግሥት አስቴርም ንጉሥ ሆይ በፊትህ ሞገስ አግኝቼ ከሆነ እነሆ በአይሁድ ላይ የታወጀው የሞት አዋጅ
ይገልበጥ ቤተሰቤና ዘመዶቼ ሁሉ ይሞቱ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል አለች። ንጉሥ አርጤክስስም እነሆ ሀማንና
ቤተሰቡን ቤቱንም ባንቺና በመርዶክዮስ እጅ እንዲወድቅ አዝዣለሁ። ስለወገኖችሽ ግን ሌላ ደብዳቤ ይዘጋጅ
ይገልበጥም ብሎ ወሰነ። ሀማም ደነገጠ ቤቱ ባዘጋጀው ግንድም ተሰቀለ። አይሁድም ሞታቸው ተገልብጦ
በመላው አገሮች ላይ ሁሉ በበላይነት ሰለጠኑ።
ስለመርዶክዮስና አስቴር ጀግንት የእምነት ፅናት በአጭሩ ባቀረብኩት ፅሁፍ ተገንዝባችኋል ብዬ አስባለሁ።
ዋናው ነጥቤ ግን እንዲህ ልግለፀው። ወገኖቼ መርዶክዮስ ለየት ያለ የእምነት አርበኛ ነው። አገሩ ፈርሶበት
ተዋርዶ፤ ህዝቡንና አገሩን ባፈረሱ ጠላቶቹ ተማርኮ በአደባባያቸው የውርደት ኑሮ እየኖረ! በሕይወቱ እምነቱን
ወገኑን ፈጣሪውን የሚወድድ ነበር። የመጣበት አደጋ ቢያዝንም በጾም በጸሎት አመድ ነስንሶ በመውደቅ
16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወደፈጣሪው አመለከተ። አስቴርም ስለወገኖቿ ህይወቷን ለአደጋ አጋልጣ ሰጠች እግዚአብሔር ግን ሁሉንም
ውርደታቸውን ሞታቸውን ገለበጠ። ለክብር ለታላቅነት አደረገው። ወገኖቼ እግዚአብሔርን ማስደሰት የሚቻለው
በአንድ ነገር ብቻ ነው። ከዚህ ውጪ ሌላ መንገድ የለም፤ እሱም እምነት ነው። መርዶክዮስ የእምነት አርበኛ
ነው። አስቴርም እንዲሁ፤ ስንቱን እንዘርዝር እነኢያሱ ለፈጣሪው የታመነ የእምነት ተዋጊ፤ ከሃዋሪያት እነጴጥሮስ
እነዮሐንስ እነጳውሎስ እነማቴዎስ ወገኖቼ ስንቱን ላንሳ ስለማልዘልቀው ልግታው። እነዚህ ሁሉ የልዑል ባሮች
ከጨለማ ብርሃንን መርጠው፤ ከእሳቱ ይልቅ ወደውሃው እጃቸውን ሰደው፤ ከጨለማ ይልቅ ብርሃንን አንግሰው
ለሁሉም የእውነት የፍቅር የተስፋ የፅናት ምሳሌ መለኪያ ውኃ ልክ ሆነው አልፈዋል። ልዑል ለአመንበት
የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነው የሚለውን ከባድ ሸክም ከላያችን ላይ አንስቶ ጣለ። ሕይወትን የዘለዓለሙን ሰጠ።
የመንግሥቴ ወራሽ የክብሬ አወዳሽ ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ጌጤ ሁኑ አለ። ፍቅሩን እስከሞት ድረስ ሄዶ
ገለጠ። ወገኖቼ ከዚህ በላይ ምን ይደረግ? ከሞት በፊት ያ ሁሉ መቀጥቀጥ መሰቀል መወጋት መቸንከር በዚህ
ሁሉ ውስጥ ስለኔና አንተ ፍቅር መጨከን ሞትን መጎንጨት መቀበር ይህ ነበር የፍቅር ዋጋ ልዑል ስላንተ
የከፈለው፤ ተሰቅሎ እየተቀጠቀጠ ልጆቼን አለእናት አልተውም ብሎ በሞት ጣር ውስጥ ሆኖ የሚወዳት እናቱን
ለእኛ ለልጆቹ እናት፣ በረከት፣ አማላጅ፣ መፅናኛና ለሁሉም ፍላጎታችን መልስ ትሁን አለ። ወገኔ ለዚህ አባትህ
ለዚህ አምላክህ ለድንግል ለእናትህ ምን አደረግህ? አዎን አይካድ ጠላሃቸው ካድካቸው ነቀፍካቸው ሰደብካቸው
በትዛዛቸው በፍቅራቸው ላይ ዘመትክባቸው ይሕን ሁሉ አድርገህ ታገሱህ ተሽከሙህ ጠበቁህ ከ2000 ዓመት
በላይ መታገስ ከዚህስ በላይ ምን ይደረግ? አኔና አንተ ግን ሌላ አምላክ አቆምን ዲያብሎስን አምላክህ አደረግህ
እሱ የሰጠህን ድርሰት እምነቴ አልክ እውነተኞቹን ልጆቹን ገደልክ አጠፋህ አሳደድክ ዛሬ ድረስ በጥፋትህ
እየጨመርክ እያዘመንክ አዳዲስ የኃጢአት ማምረቻ እየፈጠርክ ዓለሙን ሁሉ ይዘኸው ጠፋህ!!

በመልካም ፈንታ ክፉን፤ በወደድኋቸውም ፋንታ ጠላትነትን መለሱልኝ፤ እንዲል!


መዝሙረ ዳዊት 108 /109/፤ 5

የዛሬዋ ዓለማችን ምን ትመስላለች፤

ዛሬ ዓለማችን በኃጢአት ባሕር ሰምጣለች። በክህደት ተውጣለች። የእግዚአብሔርን ሕግ ከምድር ሁሉ ሽራለች


የዲያብሎስ የሆነውን ሁሉ አንግሳለች። የእግዚአብሔር ሕዝቦች አንኳን በነፃነት ሊያመልኩ የሚረግጡትን ምድር
እንኳን ተነፍገዋል።
በመላው ዓለም ሶዶማዊነት ከመስፋት አልፎ ሴቱም ከሴት ወንዱም ከወንድ እንዲጋባ፤ በአሜሪካና በእንግሊዝ
በፈረንሳይ ፊት አውራሪነት በየምክር ቤታቸው እንዲወሰን በማድረግ ሁሉም አገሮች በሕጋዊነት ሥራ ላይ
እንዲያውሉ በማስገደድ እንዲተገብሩ አድርገዋቸዋል። እርዳታ ብድር የሚሰጠው ይህን ለፈፀሙና ለሚያስፈጽሙ
ብቻ እንዲሆን ደንግገዋል። በዚህም መሰረት ሁሉም መንግሥታቶች ለጌቶቻቸው ተንበርክከዋል። ምንዝርና
ኢንዱስትሪ ሆኗል፤ በየትኛውም የዓለም ክፍል ምንዝርናን እንደሥራ የማይተገብር የለም። በአገራችንም
ተስፋፍቶ የሚታይም ሆኖአል። በአውሮፓና በአሜሪካ እግዚአብሔር የፈጠረውን ፍጡር በእያንዳንዱ ዜጋቸው
ላይ የኮምፒተር ቺፕስ /ሴል/ በገላቸው ውስጥ እንዲቀበር በምክር ቤት ወስነው ለተግባሩም እየተንደረደሩ ነው።
ዓለማችን በጥቂት ሞኖፖሊስቶች ቁጥጥር ሥር ሆናለች። የምድሪቱ ሀብት ንብረት ሁሉ በቁጥር 100
የማይሞሉ ሞኖፖሊስቶች የያዙት ሆኗል። እነዚህ ሞኖፖሊስቶች ኢሉሙናቴ፤ ጀሲዩት ኦርደር፤ ፈሪሜሶን
ወዘተ የሚባሉ በግልጽ ሰይጣንን ለማምለክ የተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ድርጅት ከመሰረቱና ሁሉንም ኢኮኖሚ
ገንዘብ ሥልጣን በአባሎቻቸው ቁጥጥር ሥር እንዲሆን ካደረጉ ከ500 ዓመታት በላይ አስቆጥረዋል። የዛሬዎቹ
ሞኖፖሊስቶችም የነዚሁ ድርጅቶች አባላት ናቸው። በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ዓለማችንን የተቆጣጠረው

17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ይኸው አይነተ ብዙ የዲያብሎስ ድርጅት ነው። በየትኛውም ዓለም የዲያብሎስ ድርጅቶች ከዋናው ማእከላቸው
ሆነው የማይቆጣጠሩት መንግሥትና አገር የለም።
ዓለም እጅግ ሰልጥናለች /ሰይጥናለች/ ኢንዱስትሪው፤ መገናኛው፤ የጦር መሳሪያ አይነቱና ብዛቱ፤ የማጥፋት
አቅሙ ከግምት በላይ የሆነ ጥፋት የሚያመጣ መሆኑ፤ የዘመናዊ ከተሞች መብዛት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያው
መርቀቅ፤ ዓለማችን ላይ የሚርመሰመሰው የተሽከርካሪ ብዛትና ዓይነት፤ በምድርም በሰማይም የሚራወጠው
ባቡር አውሮፕላን የከተሞች ሕንፃና ዓይነቱ ብዛቱ እጅግ ብዙ ነው። በህዋው ላይ የሚርመሰመሰው የሚዲያው
የመገናኛው የምርምሩ የስለላው የአጥቂው ሳተላይቶች ብዛት ሰማዩን አጣበውታል። የመገናኛው መርቀቅ
የሕንፃው ብዛት ዓይነት የኢንዱስትሪው ብዛት ዓይነት ዓለም መንደር ሆናለች። ዛሬ ያሉ ዋና ዋና በዓለምም
ተወዳዳሪ የሆኑ ኢንዱስትሪና ስፔሻላይዝድ የማምረቻ ተቋሞች ከ200 ሺ በላይ አልፈዋል። ወገኖቼ በመጨረሻው
ገጾች አካባቢ ከ168 በላይ ዓለምን በሁለመና አቅማቸው የተቆጣጠሩትን ኩባንያዎች አስፍሬላችኋለሁ።
ታውቋቸው ዘንድ እናም እንደትእዛዙ ፍርዳቸው ሲከናወን እንድታዩ /ለታደሉት/ ወገኖቼ የአዳም ዘሮች
ሁሉ!! በውኑ እግዚአብሔርን ምን ያህል እንደበደልነው ይታወቀን ይሆንን? በፍፁም አልተገነዘብንም! በዘመኔ
ሁሉ ሲገርመኝም ሲያስደምመኝም የኖረ እውነት ቢኖር የእግዚአብሔር ፍቅና የትእግሥቱ እርቀት መለኪያው
ማንኛችንም ያላወቅነው መሆኑ ነው። ልብ በሉ ወገኖቼ 7500 ዘመናትን ሁሉ የሰውን ዘር ከነከፋ በደሉና
ሀጢያቱ ያለመታከት መሸከሙ፤ ያም ብቻ አይደለም የከበደ እዳውንና ሸክሙን ሞትን እስከመሞት ድረስ
ሄዶ ነፃ ማውጣቱ፣ እድሜን ሰጥቶ አኑሮ አብልቶ አጠጥቶ ዘርን ሰጥቶ ይህ ልጄ አንድ ቀን ይመለሳል ብሎ
ሁሌም በጉጉት መጠበቁ እኒህን ሁሉ እናንተም እኔም ስንመለከተው በውኑ ሕሊና ላለው አያስገርምም? ዓለም
በለፀገ ተጠበበ ሃብቱንም እንደ ተራራ ከመረ፤ ከምድር አልፎ በሰማዩም ሮጠበት እንደእንቦሳ ዘለለበት በዚህ
ሁሉ ልዑል ምንም አላለም፤ በፈቃዱ የሰጠውን ምድር መጠቀማችን ቅር አላለውም ያ አይደለም ያስከፋው
ምላሻችን እንጂ!!
ወገኖቼ ለምን? በውኑ ለምን? ምን በደለንና? ምን ነፈገንና በምንስ አጎደለብንና? ምድርን በእንግድነታችን
ዘለዓለማዊ ሕይወትን በክብሩ ዙሪያ እንደከዋክብት መድመቅን ለዘለዓለም መኖርን በመስጠቱ ምላሹ እንዲህ
ይሁን? ክህደት፣ ሌላ አምላክ ማምለክ፤ ትእዛዙን ማፍረስ፣ ጭርሱንም ስሙን ሁሉ ከምድር ለማጥፋት
መትጋት፣ ቤቱን ማፍረስ የታመኑበትን ማጥፋት፣ ፍፁም ጨለማን ማንገስ፣ ፈጣሪነቱን ክዶ እሱ የፈጠረውን
ማምለክ፣ በብርቱ እንዲቀና ማድረግ የዛሬው ትውልድ መገለጫ ሆኗል። ስለዚህ ወገኖቼ በዚህ ዛሬ ከፊታችሁ
እንደብርቱ ማዕበል ተጭኖ በመጣው የእሳት መጥረጊያው ልንገረም አይገባንም። እራሳችን ምክርን ግሳፄን
ቅጣትን ዘለፋን ሁሉ ንቀንና አቃለን ነው እንጂ ሌላ ማን አመጣው? በቃ ወገኖቼ!! በቃ! ትእግስቱም
እስከጠርዝ ገፍተን እኛው ቀበርነው። በቃ! ተዘጋጅተህ ጠብቅ! ሁልህም እንደ እጣ ክፍልህ ትቆማለህና
እንደምርጫህ ይሰፈርልሃልና!! ወገን ስማ ደግሜ ደጋግሜ አሁንም ልንገርህ በቃ ተደመደመ!!!
በመሰልጠኑ ልክ ረሃብተኛው፤ የእርስ በእርስ ግጭቱ፤ የሃይማኖት ጦርነቱ፤ ዘረኝነቱ፣ የድንበር ጦርነት፤
የመቻቻል ባሕል መጥፋት፤ ስደት፤ በየስብሰባው ያለው አለመግባባት፤ በተለይም የትላልቆቹ አገራት
ስግብግብነት ስስት ሰብስቦ አለመጥገብ ሁሉንም የሰው ዘር በራስ ቁጥጥር ሥር ለማድረግ እስከ ኒዩከለር ጨብጦ
መዛዛት፤ የመቻቻል ጉዳይ ከምድሪቱ መጥፋት፤ የሰው ደም በየምክንያቱ መፍሰስ፤ በስውርም በግልፅም ሰውን
እንደከብት ለዲያብሎስ ግብር ማቅረብ፤ ሰው ሰውነቱ ተረስቶ እንደእቃና የግል ንብረት መቆጠሩ፤ ከፈጣሪ
በትክክል የምታገናኝ እምነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ነበረች እሷንም ከምድረ ገጽ አጥፍተው ጨርሰዋል። በጣም
በጥቂቱ ያለችው እዚሁ አገራችን ኢትዮጵያ ሲሆን እሷም አንደተቋም እንዳትቆም የዓለማችን ኃያል የዲያብሎስ
እምነቶች ውስጧ ወኪሎቻቸውን ሰግስገው ቅባት ፀጋ ተሃድሶ እያሉ ሽባ አድርገዋታል። እግዚአብሔርም
እምነቷን ካጠፉ አገልጋዮች አንስቶ በምእመኑ ልብ ላይ ተከሎአታል። ዛሬ ብዙዎች አውነተኞቹ የልዑል ባሮች
ከጠላት ጥቃት ብዛት የተሰደዱ ያጡ የነጡ የታሠሩ በተስፋ መቁረጥ የሚበሳጩ ከፈጣሪያቸው ፍትህ ፍለጋ

18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ጧት ማታ እንባቸውን የሚያፈሱ ሆነዋል። ዓለም እንደመሰልጠኗ ሁሉ ሙሉ በሙሉ በዲያብሎስ አገልጋዮች


ቁጥጥር ሥር ሆናለች።
በአገራችን በኢትዮጵያ ሰልጥኖ የበላይነቱን የጨበጠው ዲያብሎስና ምንዝር አገልጋዮቹ አገሪቱን የጠፋች
አድርገዋታል። በአገሪቱ ዘረኝነት ጭካኔ ዘረፋ አምልኮ ባእድ ንቀት ጥላቻ ነግሶአል። የተዋህዶ ኦርቶዶክስ
እምነትን ሁሉም ዘሮች ማለት ይቻላል ጠልተዋታል። ከአንድ ዘር በስተቀር ከሱም ውስጥ የተዋትና ሌላ እምነት
የሚከተሉ ብዙ ናቸው። እንዲህም ሲባል ሌሎችም ብሔር ተብለው በሚጠሩ ውስጥ እግዚአብሔርን የሚወዱ
ተዋህዶንም ያመኑና የሚኖሩበት በቁጥር ይነሱ እንጂ አሉ። እነሱም ውስጥ ተዋህዶ ኦርቶዶክስን እያመኑ
እምነቱን መልሰው የዘር እምነት ሊያደርጓት የሚተጉ አሉ። አንዳንዶች በተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ
ክርስቲያን ይሆኑና ቤተ ክርስቲያን ለቀው ሲወጡ ዘረኛነትን የሚያራምዱም ናቸው። እውነተኞቹ የእግዚአብሔር
ሰዎች የብሔር ድንበር፤ የጥላቻ ልክፍት የለባቸውም። የፀኑ ኢትዮጵያውያንም ናቸው። በዚህ አይደራደሩም።
የዓለም ጥፋት በዚህ አጭር ጽሑፍ ተዘርዝሮ አያልቅም። የዛሬን እውነት ሁሉም ትውልድ የሚያየው ስለሆነ
መንገሩ ለቀባሪው ማርዳት ብቻ ነው።
ይህን ሁሉ የዓለም ጥፋት የሚመለከተው እግዚአብሔር በሰው ልጅ አለመመከር አለመገሰጽ እጅግም
አበሳጭቶታል። ክህደትና ጥፋታቸው አንሶ፤ ሌላ አምላክ እሱም ዲያብሎስ የሰውም የእግዚአብሔር ጠላት
የሆነውን አንግሰው ይህም ሳያቆማቸው የእግዚአብሔርን ሕግና ቤቱን ማፍረስ እንደሥራ አድርገውታል።
እግዚአብሔር መከረ ዘከረ ቀጣ ማንም አልሰማም። እንዲያውም ምክሩን ግሳፄውን የተለያየ ምክንያት በመስጠት
ሳይንሳዊ ትርጉም በማቀረብ እግዚአብሔር እንደሌለ በመስበክ የተጠመዱ ናቸው። ዛሬ ሰው ሁሉ የሚያደምጠው
ሚዲያው ፕሬሱ፤ ሞባይሉ ኢንተርኔቱ ባጠቃላይ መገናኛው ሁሉ ዓለም አቀፍም ሆነ የአገር ውስጥ ሁሉም
በዲያብሎስ ሰራተኞች፤ አምላኪዎች ተጠዋሪዎች የተያዘ በመሆኑ አንድም የእግዚአብሔር ቃል፤ መልእክት
እንዳይተላለፍ አድርገዋል።
ዛሬ የሰው ልጅ ጠፍቶአል የምንለው ከምንም ተነስተን አይደለም።
እስቲ ስለኳስ አናንሳ!! በምድራችን በተለይም አደግን በሚሉ አገሮች ኳስ ሁሉንም ሰው ተቆጣጥሮታል።
ሁሉም ዓይነት እስፖርቶች ኢንዱስትሪ ሆነዋል። ለምሳሌ ያህል በቅርቡ በራሺያ የተካሄደውን የዓለም ዋንጫ
ብናይ ልብ ብላችሁ አስተውላችሁ ከሆነ ማንኛውም ጨዋታ ሊጀመር ሲል አንድ የታየ የመግቢያ ምስል ነበር።
ምስሉ በቀይና በወርቃማ ቅርፅ ሆኖ ክንፍ ያለው ደራጎን ኳሷን በአፉ ስቦ እየበረረ ከላይ ሁኖ መጫወቻ ሜዳው
ውስጥ ይጥላታል። ከዚያ ጨዋታው የሚጀመርበት ስርዓት ይከናወናል። ጨዋታውም ይካሄዳል። በሁሉም
ጨዋታዎች ይህ ስርዓት ተከናውኗል። እንግዲህ ወገኖቼ ኳስ ጨዋታ የማነው ማንስ ያሰረፀው ነው። እንደገናም
የዓለም አትሌቲክስ በፔኪንግ ሲካሄድ በተመሳሳይ ድራጎኑ ከቤቱ ሲወጣ በከንፉ በጨዋታው መከናወኛ ዙሪያ
ሲሽከረከር ይታይ ነበር። ኳስም ሆነ አትሊቲክስ ከ7ቢሊዮን በላይ የሆነው ሕዝብ በስቴድዮም በቤቱ በቴሌቪዥን
አፍጦ ሲያይ ይውላል ያድራል። ዓለም አንኳን ፈጣሪውን ሊያስብ ሊያመልክ ከነመኖሩም ረስቶታል ከሕሊናው
ወጥቶአል የኳሱ ንጉስ ዲያብሎስ ነግሶበታል ዓለም ጠፋች ፈጣሪዋን ፍፁም ከሕሊናዋ አወጣች።
ወገኖቼ ዓለም እንዲህ ናት። የዛሬውን መልእክት ጨምሮ ለሰባት ጊዜ በኔ በታናሽ ባሪያው በኩል ልዑል
ፍርዱን ግሳፄውን ቁጣውን ነግሮ አስጠንቅቆ ቢናገርም የስማም የለማም የለም። ለ13 ዓመት እኔ እንኳን
ፍቃድና ምክሩን ትእዛዙን ፍርዱን አድርሻለሁ፤ ማን ሰምቶ! እንግዲህ በዚህ አጭር ጽሑፍ የዓለምን ሁሉ
ገጽታ ለማየት ስለማይቻል ለማገናዘቢያ የሚሆነውን ከላይ ለማቅረብ ሞክሬአለሁ።

19
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ዓለም ነገስ ምን ትመስላለች?

እንግዲህ ስለዓለም በእምነት በተዋህዶ አንፃር ትላንት ምን እንደነበረች፣ ስለእውነተኛይቱ ተዋህዶ እምነት
ተጋድሎ በውስጧም እንደኮከብ አብርተው ስላለፉት የተዋህዶ አርበኞች ስለ ስድስቱም መልእክቶች አጠር
አጠር ያለ ገላጭ አንቀጽ በመጥቀስ የሞከርን ሲሆን፣ የዛሬውን ምንነቷንም በመጠኑ ዳሰናል።
በእምነት አካሄድ የነገው መሆናችን፤ መድረስና መገኘታችን የሚወሰነው በልዑል ነው። የሱም ውሳኔ
እምነታችንን፤ በእውነትና በመንፈስ እሱን መታመናችን፤ አካሄዳችንን እምነት ምግባራችንን ያያል ልብን
እዕምሮን ይመረምራል ውሳኔም ይሰጣል።
ይህ መልእክት የመጣው አለምክንያት አይደለም። የሚሆኑ ነገሮች ሁሉ እድሜ አላቸው ሰከንድም ቅጽበትም፤
ደቂቃም ሰዓትም፤ ቀንም ወርም፤ ዓመት ዓመታትም ይፍጁ እንጂ እንደጅምራቸው ማብቂያ አላቸው።
ሂደታቸውም ሲያልቅ የምናስተውላቸው የማናስተውላቸው አሉ። ባለቤቱ ልዑል ግን እንደፈቃዱ በወስነው
መሰረት ይጀመራል ያበቃል። እኛም ሰዎች በዚሁ መልክ የምንከወን ነን።
በጨለማም ሮጥን፤ በብርሃንም ገስገስን ያ ሁሉ በልዑል ዘንድ የተመዘገበ ነው። እንደምርጫችን ልንኖር
ልዑል ከመጀመሪያው ፍቃዱን አስቀምጧል። በወደድነው ሄደናል። በውጤቱ ደግሞ ወይ ተጠቅመናል አሊያም
ተጎድተናል።
ይህ መልእክት የቀደሙትን በማስታወስ የተደከመውን ሁሉ በማሰብ ሰው ምን ያህል ተጠቀመበት፤ ወይስ
አልተጠቀመበትም በሚለው መጠነኛ ዳስሳ አድርጎአል። አዎን ዛሬ ላይ ሆነን የትላንቱን ድካም ጥረት የምናስበው
ፍርዱም ቅጣቱም፤ መመስገኑም መባረኩም የሚያርፉበት አላቸውና ያንን ለመግለፅ ግድ ስለሆነ ነው። ልዑል
አባታችን በማይናወፅ ቃሉ ያለውን ስናስብ እንዲህ ነበር ያለው፦

ዓመፀኛው ወደፈት ያምጽ እርኩሱም ወደፊት ይርከስ፤ ጻድቁም ወደፊት ጽድቅ


ያድርግ ቅዱሱም ወደፊት ይቀድስ አለ። እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም
እንደሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከኔ ጋር አለ። አልፋና ኦሜጋ ፊተኛውና
ኋለኛው መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
የዮሐንስ ራእይ ም 22 ፡ 11 – 13
እንግዲህ የብዙዎች ትርጉም /ከላይ ለተጠቀሰው የልዑል ቃል/ እንደሥጋቸው እንጂ እንደሱ ሃሳብ አለመሆኑን
በድርጊታቸው ሲያረጋግጡ ኖረዋል። የልዑል ቃል በኛ ሰውኛ የሥጋ ትርጉም የምንለው እንዲህ ነው። ዓለም
ስታልፍ ሁሉም ሲያበቃ ነው ፍርድ የሚሰጠን ስለዚህ ጊዜ አለን እስከዚያው እንደንስ እናምፅ ከሆነም በመጨረሻ
የእድሜአችን ጫፍ ስንደርስ ንስሓ እገባለን ብለው እንደይሁዳ ቀጠሮ ይሰጣሉ በአመፃቸውም ይቀጥላሉ። ጌታ
እንደሌባ እመጣለሁ አለ እንጂ የቀን ቀጠሮ አላስቀመጠም። የእግዚአብሔር ቃል ዘመንን ሁሉ ይዳኛል እንጂ
ይህ ዘመን የኔ ነው ያ ዘመን የናንተ ነው በሚል እጁን አጣምሮ አይመለከትም።
በሰውኛው አኗኗር ሰው ያለሕግ ያለፍርድ ቤት ያለወታደር ወጥቶ መግባት አይችልም። አመጸኛውን ለመግታት
ለፍርድ አቅርቦ ለማስተካከል ለመቅጣት ሁሉም መሥራት አለባቸው። በመንፈሳዊውም የእግዚአብሔር ቃል ሕጉ
ነውና በዚያ ተመስርቶ በደቂቃውም በሰዓቱም በየዓመታቱም በየዘመኑም በፍርድ የሁሉም ፍጥረት እንቅስቃሴ
ይዳኛል። በፊቱ የተወደደውና ፍቃዱ የሆነውን ያጸናል። የሚወገደውን ያስወግዳል። አዲስ የሚመጣውም
ይመጣል። የዓለምና የሰው ልጅ እንቅስቃሴ ሁሉ በፍቃዱ ሥር ነውና የሰውን ተግባር፣ ሃሳብና አፈፃፀሙን
በሙሉ ከእይታው ውጪ አይደለም። በመሆኑም ፍርዱ አብሮት እንደጥላ ይከተለዋል። ይፈፀም ዘንድ ሲታዘዝ
ይፈፀማል።

20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች፣ የአዳም ዘሮች! ዓለማችን ከዚህ መልእክት መውጣት በኋላ የሚጠብቃት
ምንድነው የሚለው ነጥብ ዋናው የመልእክቱ ጭብጥ ነው። መልእክቱም እንዲወጣ ግድ የሆነው ዓለምም
አገራችንም ወደ ከፋ የጥፋት አቅጣጫ እየሄዱ በመሆናቸው፤ ይህ ደግሞ የሆነው እየሆነ ያለውም በዓለምም
በአገራችንም ከሰራዊት ጌታ ከድንግልም ለረጅም ዘመን የተላለፈውን ምክር፤ ትምህርት ግሳፄ፤ ዘለፋ፤ ቅጣት
ተቀብሎ ለመመለስ ይህ ትውልድ ካለመፍቀዱም በላይ የእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ በማጥፋት ላይ መሰማራቱ
ነው። በየዘመኑ ሁሉ የተደከመውን ድካምም ሆነ ጥረት እንደከንቱ በመቁጠር ሁሉም የአዳም ዘር ንቆ በገዛ
ፈቃዱ ተጓዥ ሆኗል። ጥቂት ልባሞች ምክሩን ሰምተው በተሰጣቸው ምክር አትርፈዋል። እንግዲህ እየሆነ ያለው
ዓለምንና በእግዚአብሔር ፈቃድ ጸንተው የቆሙትን፤ ዲያብሎስ ባነደደው እሳት ተለብልበው ተጨፍጭፈው፣
መቆሚያ መቀመጫ አጥተው በታላቅ ጉዳት ውስጥ በመውደቃቸው በድካምም ዝለው በመገኘታቸው፤ የግድ
ልዑል ልጆቹን መታደግ ነፃ ማውጣት ምድሪቱንም ለልጆቹ ማውረስና እንዲፅናኑ ማድረግ ስላለበት ይህንን
ተግባራዊ ለማድረግ ነው። ለዲያብሎስ ታማኞችም በፍርድ ተካተው የሚከደኑበትን ሁሉ መደረግ ስላለበት ይህ
መልእክት ይህንኑ ለማረጋገጥና የሚፈፀሙ ቅጣቶን ወዴት? እንዴት? በምን ደረጃ? በማን ላይ እንደሚፈፀሙ
ለመግለፅ ምን ውጤት መምጣት እንዳለበት እስከመቼ እንደሚዘልቁ ለማረጋገጥ የመጣም ነው።
የዛሬው መልእክት እንደቀደሙት ስድስት መልእክቶች ጊዜ የሚሰጥ አይደለም። ጊዜ ዘመን የሚሰጠው
ለሚጠቀምበት እንጂ ከከፋ ጥፋት እጅግ ወደከረፋ ጥፋት እንዲሸጋገሩበት አይደለም። የቀደሙት ስድስት
መልእክች 13 ዓመታትን ሲዘልቁ ንስሓ ለሚገባው እንዲገባ እምቢ ያለውም እንደምርጫው እንዲጓዝ ልዑል
ጊዜን ሰጥቶ ነበር። አልሆነም እንደታሰበው ውጤት አልተገኘም። በመልእክቶቹ ምንም ያልተገለጸ ነገር የለም።
ከአለቃ እስከምንዝር እድል አግኝቶ ነበር። እምቢ አላውቅህም አለ። የዲያብሎስን እምነቶች፤ ድርሰቶች፤
የሳይንስ ትንታኔዎች፤ ፍልስፍናዎች ገንዘቤ ናቸው አለ። የእግዚአብሔርን ሕግም ሆነ መልእክቶች ራሱንም
የፈጠረውን አምላክ አላቃችሁም አለ።
የልዑል ቃል እንዲህ ይላል፦

የሰው ልብ ከሁሉ ይልቅ ተንኮለኛ እጅግም ክፉ ነው ማንስ ያውቀዋል፤ አኔ


እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ እንደመንገዱ እንደሥራው ፍሬ አስጥ ዘንድ ልብን
እመረምራለሁ ኩላሊትንም አፈትሻለሁ።
ትንቢተ ኤርሚያስ ም 7፤ 9 – 10
ልዑል የምታየውን የሰማኸውን ቃል ይተገብረዋል። ትመረመራለህ የውጤቱም ባለቤት ትሆናለህ!!
የዛሬው መልእክት የመጣው ክፉ የቁጣ መርዶ ይዞ ነው።
እንግዲህ አላውቀውም ያልከው አምላክ አምላክነቱን ያሳይሃል። የታመንክበትን ሁሉ ትቢያ ሲያደርግ
አንተንም ወገን ዘርህንም ለእሳት እራት ሲያደርግ አሁን ታየዋለህ እያየኸውም በእሳት ባሕር ውስጥ ትጠልማለህ።
የሰው ልጅ ልብ ብለህ አድምጥ!! የምድርን ስብ በላህ፤ ሥጋህ ከምቾቱ የተነሳ ምድርም ጠበበው ሰማዩም
አነሰው፤ ጠገብህ! ትእቢትህም ሰማያትን ነካ። ልዑል እንዲህ ይልሃል!
ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ፤ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ፣ ከንፎቹን ዘርግቶ
ወሰዳቸው፤ በክንፎቹም አዘላቸው፤ እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር
ሌላ አምላክ አልነበረም፤ በምድር ከፍታ ላይ አወጣው፤ የእርሻውን ፍሬ በላ፤ ከአለትም
ድንጋይ በሚገኝ ዘይት አጠበው፤ የላሙንም ቅቤ የመንጋውንም ወተት፤ ከጠቦት ሥጋ
ጋር፤ የባሳንንም አውራ በግ ፍየሉንም ከስንዴ እሸት ጋር በላህ፤ ከወይኑም ደም ያለውን
ጠጅ ጠጣህ፤ ይሹሩን ወፈረ ረገጠ፤ ወፈረ ደነደነ ሰባ የፈጠረውንም እግዚአብሔርን
ተወ፤ የመድሃኒቱንም አምላክ ናቀ፤ በሌሎች አማልእክት አስቀኑት በእርኩሰታቸውም

21
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

አስቆጡት እግዚአብሔር ላልሆኑ አጋንንት ለማያውቋቸውም አማልእክት በቅርብ


ጊዜ ለተነሱ ለአዲሶቹ አባቶቻቸውም ላልፈሩአቸው አማልእክት ሰዉ፤ የወለደህን
አምላክ ተውህ፤ ያሳደግህን እግዚአብሔርን ረሳህ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆችም
ስላስቆጡት እግዚአብሔር አይቶ ጣላቸው፤ እርሱም አለ – ፊቴን እሰውርባቸዋለሁ
ፍጻሚያቸው ምን እንደሆነ አያለሁ ጠማማ ትውልድ ያልታመኑም ልጆች ናቸው።
አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ በምናምንቴዎቻቸውም አስቆጡኝ እኔም ሕዝብ ባልሆነው
አስቀናቸዋለሁ በማያስተውል ሕዝብ አስቆጣቸዋለሁ እሳት ከቁጣዬ ትነድዳለችና!
እስከ ሲኦል ድረስ ታቃጥላለች ምድርንም ከፍሬዋ ጋር ትበላለች የተራሮች መሰረትን
ታነድዳለች፤ መከራን እጨምርባቸዋለሁ፣ በፍላጾቼም እወጋቸዋለሁ፤ በራብ በንዳድ
ይጠፋሉ፤ በንዳድና በመራራ ጥፋት ያልቃሉ፤ የአራዊትን ጥርስ፤ የምድርንም እባብ
መርዝ እሰድድባቸዋለሁ። ጎልማሳውን ከድንግል ሕፃኑንም ከሽማግሌ ጋር በሜዳ
ሰይፍ በቤትም ውስጥ ድንጋጤ ያጠፋቸዋል።
ኦሪት ዘዳግም ም 32፤ 11 – 25
እስራኤላውያን በክህደታቸው በጥጋባቸው የተሸከማቸውን አምላክ እንዴት በቁጣው እንደሞሉት ከላይ
በቃሉ ያያችሁት ነው። የእግዚአብሔር ቃል የዘመን ሁሉ ዳኛ ነው። ዛሬ ደግሞ ከቀደሙት እስራኤላውያን
የእናንተ በብዙ መቶ እጥፍ አይበልጥም! እጅግ ይበልጣል። በመሆኑም በብዙ እጥፍ ያነደድከውን የልዑል ቁጣ
ባልታየው ዘርፈ ብዙ የእሳት መጥረጊው ትጠረጋለህ ትደመደማለህ። እውነቱ ይህ ነው።
ይህ መልእክት የትእግስት መደምደሚያው ማረጋገጫው ነው። ስለ እርምጃዎቹ ዝርዝር በመልእክቱ
መደምደሚያ ላይ የሚገለፁ ይሆናል።

አገራችን ኢትዮጵያና የፍርድ ቃሎቹ ትላንት ዛሬና ነገስ!!

አገራችን ኢትዮጵያ በዚህ መልእክት ወስጥ ስንዳስሳት ምን ትመስላለች በሚለው ሃሳብ ተነስተን የቀደመውን
በመጠኑ አይተን የዛሬውንም ቃኝተን የወደፊት እጣ ፈንታዋን ተመልክተን ወደ ቀጣዩ ርእስ እንዘልቃለን!
ከላይ በመግቢያዬ አካባቢ እንደገለጽኩት አዲስ መልእክት የለም። የነበረውን ለመግለጽ የጥፋት መጠኑ በብዙ
እጥፍ እንደሚጨምር ለማረጋገጥ ይህም የጥፋት ብርታት የእግዚአብሔርን ፈቃድ፣ ትእዛዝና ለልጆቹ ለወገኖቹ
ለየዋሆቹ ለቅኖቹ ለታዘዙት ለጠበቁት ምድርን እስከሚያወርስ እስከሚያስገዛ የሚቀጥል ነው። መልእክቱም
አዲስ የማይሆነው በቀደሙት ስድስት መልእክቶች ያልተዳሰሰ ጉዳይ የለም። ያልተገለፀ መጪ ቁጣ የበትር
ዓይነትም የለም። ዛሬ ግን እነዚህ ሁሉ ተገልጸውም እርምጃውም ቀጥሎ ባለበት ሰዓት ወንፊቱም የብጠራ
ሥራውን ከጀመረ ቢቆይም ውጤቱ ገና የሚፈለገውን እስካላመጣ ድረስ ታይተው ተሰምተው የማይታወቁትን
የጠረጋ ዓይነት እየጨመሩ ይቀጥላሉ እንጂ የሚበርድ ነገር የለም። በዚህም ሁሉ ውስጥ የእግዚአብሔር ሕዝቦች፤
ቅን የዋህ ሕዝቦች፤ የተዋህዶ ልጆች፤ እውነተኛ የኢትዮጵያ ፍቅር ያላቸው ወገኖች ሁሉ እንዳትደናገጡ ይህ
መልእክት ሊያረጋግጥላችሁ ነው የመጣው። በሚነደው እሳት ውስጥ ነጭ ለብሰህ በመሃሉ ብትንጎራደድ የሚነካህ
የለም። የሚታደግህ የሚጠብቅህ ሲድራቅ ሚሳቅ አብዲናጎምን የታደገ በሁሉም ዘመን ለቃሉ ታማኝ የሆነው
አምላክ ነው። እናትህ ድንግል ልጆቿን አሳልፋ እምትስጥ አይደለችምና አትደንግጥ አትፍራ!!
ኢትዮጵያ አገሬ! ምስጢር ናት። የሥላሴ ምስጢር፤ የአገሮች ሁሉ መለኪያ ውኃ ልክ ናት። ዛሬ እሷን
ለማጥፋት በተራቀቀ የጥፋት በትር የመበተን ዘዴ እናጠፋለን ብለው እጅግ በሚገርምና በሚያስደነግጥ ሁኔታ
እያመሷት ይገኛሉ። ግን አይሆንም። እነሱ ይበተናሉ እነሱ እንደ ጭስ ይበናሉ እንጂ ምንም ሊያደርጓት
አይችሉም። በአሁኑ ሰዓት ከመሪዎችም አንደበት ከድርጅቶችም የዘወትር ንግግር ከአብዛኛውም ሕዝብ
የሚወራው የሚነገረው ኢትዮጵያ ልትፈርስ ነው ልትበተን ነው የሚል ነው። ማነው የሚበትናት ማነውስ
ለጥፋቷ እየተጋ ያለው ሁሉም ይታወቃሉ። በሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ!
22
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ኢትዮጵያ የድንግል እርስት የስስት ምድር ናት ሁልህም የምትመዘነው የምትለካው ስታንስ የምትጣለው በሷ
ውኃ ልክነት ነው። ዲያብሎስ ያደነቆረህ ፎቅ ላይ ሰቅሎ ሱፍ አልብሶ የሱ ታላቅ ተብዬ አገር ሥልጣን ላይ
አውጥቶ በትረ ዲያብሎስ አስጨብጦ መሪ መሪ እያለ ቢያንቆለጳጵስህ ምድርና ሰማይን የጨበጥህ መሰለህ! አይ
ሰው! ዛሬም እወቅ! አሁንም ቢገባህ ይግባህ – ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ናት። ኢትዮጵያ የዓለም ገዢ ናት።
ኢትዮጵያ የተወደደች በልዑልም በድንግልም በስስት የምትታይ እንቁ ምድር ናት። በሷ መጥተሃል ልታጠፋ
ደክመሃል፤ ይህ ድርጊትህ በልዑልና በድንግል ዓይን መምጣት መሆኑን አሁንም አልገባህም ደንቁረሃል፤
አዎን! መስሚያህም ማሰቢያህም በዲያብሎስ መልከ ብዙ ፕሮፓጋንዳ ዘመንክ በምትባልበት ዘመናዊ ቅራቅንቦ
ተደፍኗል። አንተን ለመለወጥ ስላልተቻለ ከታመንክበት መልከ ብዙ ጌታህ ጋር ላንዴም ለሁሌም ትቀበራለህ።
ይህ ሊያጠራጥርህ አይገባም።
ወገኖቼ የአዳም ዘሮች! አገሬ ኢትዮጵያ ምስጢር ናት። የልዑል ምስጢር፤ የድንግል ምስጢር፤ ማንም
የማይሰብረው ማንም ሊያየው ያልቻለ። አገሬ ምስጢር ናት። ሊያጠፉት ያልቻሉ የዛሬው ኃያል ሀገራት
ስልታቸውን እየቀያየሩ ቢለፉም ቢሽራርፏትም አልጠፋችም አትጠፋምም፤ ይልቅስ እጃቸውን ባረዘሙ
ስልታቸውን በቀያየሩ ቁጥር የተሳካላቸው ቢመስላቸውም በሚቆፍሩት ሁሉን ዓይነት ጉድጓድ እንደራሳቸው
ዓይነትና ብዛት ራሳቸው ይቀበሩበታል እንጂ ሌላ የሚፈጠር ነገር የለም።
ይህ መልእክት በዝግጅት ላይ እያለ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የውጪውና የውስጡ በሚል
በወያኔ የክፋት ሲራ የተከፈለ ሲኖዶስ እንደገና በአዲሱ መሪ አደራዳሪነትና ግፊት እንዲዋሃዱ መደረጉን
ሁሉም የሚያስታውሰው ጉዳይ ነበር። እኔ ስለውህደቱ አስተያየት ለመሥጠት አልሻም። ከዚህ ይልቅ ሁለቱ
ፓትሪያርኮች በተገኙበት መንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ላይ በተደረገው የአቀባበል ዝግጅት
ላይ ከውጪ የመጡትን አባት በመወከል ንግግር ያደረጉ አንድ አባት /የአውሮፓ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
አባት ስማቸው እርግጠኛ ባልሆንም አቡነ ኤልሳዕ የሚባሉት/ የተናገሩት እጅግ የሳበኝና የገረመኝ ሁለት ነጥብ
ተናግረዋል።
አንደኛው – ኢትዮጵያ የሥላሴ የምስጢር አገር ናት። ማንም ይህን ምስጢር በቀላሉ አይደረስበትም ያሉት
አንዱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አውሮፓውያን የኛን ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እጅግ እንደሚጠሉና ሊያጠፏት
ያልተቋረጠ ትግል እንዳደረጉ አሁንም እያደረጉ እንዳለ የሰጡት ምስክርነት ሲሆን እኝህን አባት በግሌ
አከብራቸዋለሁ። ረጅም እድሜ ከጤና ጋር ይስጣቸው እላለሁ። ተኩላና ቀበሮ በነገሰበት ሰዓት ጥቂት በቁጥር
ያነሱ አባቶች እንዳሉ እያሰብኩ ሁሉንም እግዚአብሔር ይጠብቃቸው ለትንሳኤው ዘመን ያብቃቸው እላለሁ።
ወገኖቼ!! ዛሬ በመላው ዓለም የሰፈኑትን እምነቶች እነካቶሊክ፤ እነእስላም፤ እነፕሮቴስታንት፤
እነሂንዱኢዝም፤ ሺንቶኢዝም ሌሎችም ለቁጥር የሚያታክቱ እምነት ተብየዎችን ስናስባቸው የሚያስገርመው
ባሕርያቸው ሁሉም ስለመጪው መጥፎም በጎም ዘመን የሚገልጹት እውነት የሌላቸው መሆኑ ነው። ተዋህዶ
እምነታችን እውነት ላይ የተመሰረተች እጅግ ውድ ዋጋ የተከፈለባት ዛሬም እየከፈለች ያለች እምነት ናት።
እውነተኛ ልጆቿ ከአምላካቸው ጋር የሰመረ ግንኙነት ያላቸው በመሆናቸው ልዑል ስለፍርዱም ሰለወቀሳውም
ሊያደርግ ስላሰበውም ቀድሞ ለታመኑት ባሮቹ ይናገራል። ወደ ሕዝቡም ሁሉ ይልካቸዋል። ይህም ዛሬ እየሆነ
ያለ ነው። እነአብርሃም፤ እነኖኅ፤ እነኤልያስ፤ እነኤልሳ፤ እነዳንኤል፤ እነወንጌላዊው ዮሐንስ እጅግ ብዙዎች
በዚህ ሕይወት አልፈዋል ለኛም ምስክር ሆነዋል። እውነተኞቹ የእግዚአብሔር ልጆች ዘንድ ዛሬም ምስጢር
የለም። ልዑል አይደብቃቸውምና። ስለእውነተኛይቱ እምነታችን ይህን ካልን ምድርን ስለሸፈኑት ካቶሊክ
እስላም መናፍቅ የምሥራቆቹ እምነት ሺንቶኢዝሙ ቡዲህዝሙ ሂንዱኢዝሙ እኒህ ሁሉ ዘጠና አምስት
ከመቶውን ሕዝብ የሸፈኑትን በአገራችን ያሉትም ማሕበርተኞቻቸው እስላሙም መናፍቁም ካቶሊኩም ዋቄ
ፈታውም ተብታቢውም መተተኛውም እስቲ ይንገሩን መቼም አዋቂ ነን ባዮች ናቸው።

23
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ትውልዱን ሁሉ በውሸት፤ በተረት በፍልስፍና በተደረተ የሚያማልል ቋንቋቸውና ንግግራቸው የሰውን ሥጋዊ
ፍላጎት በመኮርኮር በተካኑበት ችሎታቸው ከፖለቲካውም ከንግዱም ከፍልስፍናውም ከዝርፊያውም ከዘረኝነቱም
ከዲያብሎስ አምላኪነቱም ከሁሉም ውስጥ የጠለሙ በመሆናቸው አናውቅም የሚሉት ነገር በፍፁም የለም። ዛሬ
ብቻ ሳይሆን ለ13 ዓመት ለ6 ጊዜ ያ ሁሉ የልዑል ፍርድ ሲገለጥ በተግባርም እንደ መልእክቱ ምድር ስትበጠር
ዛሬም እጅግ ለከፋው ቁጣ ስትጣድ ለምን ሕዝባቸውን አይታደጉትም፤ ለምን መፍትሔ ከሚታመኑበት አምላክ
አያመጡም። እኛ እንደምንረዳው ከጧት እስከማታ መስዋእት ዘርግተው በአል ሆይ ስማን እያሉ የጮሁትን
የቡኤል ዘቡኤል ካህናትን የተኩ ናቸው። ለውጡ በዘመነ እስራኤል በነአካብ በነኤልዛቤል ዘመን መከናወኑ ሲሆን
የዛሬውም ከ7 ቢሊዮን በላይ ቁጥር መሸፈኑ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የዘመናችን የበአል ካህናት ከነኤልዛቤል
የበአል ካህናት የወረሱትን እምነታቸውን የዘመናዊነት ካባ ማልበሳቸውና በዛው መንገድ መሄዳቸው ነው
እውነቱ። ወገኖቼ የበአል ካህናት ከጧት እስከ ማታ ቢጮሁ ሰሚ አጥተው በቂስ ሸለቆ ለማለቅ በቅተዋል።
ራሳቸውን አላዳኑ የደገፈቻቸውን ኤልዛቤልንም መንግሥቷንም አልታደጉ ሁሉም አልቀዋል። እውነትን ጨብጦ
የተዋጋቸው ሁሉም እንደሚያውቀው እድሜውን በእንክርት በስደት በፈተና የጨረሰው ኤልያስ ነበር።
ዛሬም ኤልያሶች፤ ኢያሱዎች፤ ዳዊቶች፤ የተጉ ቅዱሳን ማንም ባያውቃቸውም በየትቢያው ላይ ወድቀው
በእውነቱ መንገድ ላይ አሉ። ዛሬ ይህ መልእክት እያስገመገመ መጣብህ በጠበቅኸው የበአል ትምህርትና
ትምክህት ጩህ! ሺዎችን ዘመናት ከንቱ ሆነ ጩኸት አሳልፈሃል። ዛሬም ያው መስሎህ ከሆነ አትሳሳት ዛሬውኑ
እጣ ፈንታህን ትቀበላለህ። በእንቅልፍ ላይ ይሁን፤ ወይ መንገድ ሄዶ፤ ወይም በሌላ ጉዳይ ተጠምዶ በርታና
ጩህ በአል ታደገኝ በለው። ሉሲፈር፤ የቀደመው እባብ ያላደራጀልህ የድርጅት እምነትና ማምለኪያ የለም።
በዚህ ዘመን እቋቋመዋለሁ የማይለው ነገር የለም። ስለዚህ የታመንክበት ያድንህ!
ኢትዮጵያ የተዋህዶ አርበኞች ምድር፤ ኢትዮጵያ የተዋህዶ እምነት የምስጢር ምድር፤ የዛሬ ጉዳቷ
ሁሉ የቀደመውን ግዛቷን ብቻ አይደለም የሚመልሰው ከዚያም በላይ ዓለም ሁሉ በምርኮ ተሰጥቶአታል።
እንዴት ይሆናል? እድሉ የለህም እንጂ በጥፋትህ ሂደት ውስጥ ሆነህ ጫፍ ጫፉን ታየዋለህ። ተዋህዶ ማለት
ብርቱ የእግዚአብሔር ፈቃዱና ትእዛዙ ቃሉም ዘብ ናት። ከላይ እንደነገርኩህ በአል ይታደግህ!! እኛ ደግሞ
በምንወደው በቅጽበትም በሚሰማን በእሳት አጥሮ በሚጠብቀን ከፊታችንም ቀድሞ እንደትንታግ እሳት ጠላትን
ሁሉ በሚጠርግልን አምሳያ በሌለው የሰራዊት ሁሉ ጌታ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ስም
እንመካለን እንታመናለን። እሱ በሰጠን እጅግ በሚወዳት በእናቱ ለኛም መተኪያ የሌላት እናት በሆነችው
ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም አንመካለን እንታመናለን። የልዑል ቃል እንዲህ ይላል

ክፉ አድራጊዎች ይጠፋሉና እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን


ይወርሳሉ፤ ገና ጥቂት ኃጢአተኛም አይኖርም፤ ትፈልገዋለህ ቦታውንም አታገኝም፤
ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ። በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል። ኃጢአተኛ ፃድቁን
ይመለካከተዋል ጥርሱንም በእርሱ ላይ ያንገጫግጫል! እግዚአብሔር ይስቅበታል።
ቀኑ እንደሚደርስ አይቶአልና!
መዝሙረ ዳዊት 36(37)፤ 9 - 13

የትላንቷ ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ሀገራችን የዛሬው ገጽታዋን ከመያዟ በፊት የነበራት ማናቸውም ነገሯ ሁሉ ለዛሬው ትውልድ
ቢነገረው ተረት እንጂ ፍፁም እውነት አይመስለውም። የዛሬዋ ኢትዮጵያ ከቀደመው ግዛትዋ ያላት ኢምንት
ነው።

24
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

አገራችን ኢትዮጵያ በምድራችን ከነበሩት ቀዳሚ መንግሥታት እኩል የምትጠራ የምትታወቅም ነበረች።
በነአቴና፤ በነሮማን በነባቢሎን በግብፃውያን ዘመን በነአዝቴክስ ዘመን ኢትዮጵያ በታላቅነቷ የምትታወቅ ነበረች።
በነካሌብ ዘመን ደግሞ ከአፍሪካም አልፋ የመንን ጨምራ በሃይሏ በኢኮኖሚዋ በንግድ መረቧ እጅግ የገነነች
ነበረች። ይህ ደግሞ በታሪክ ጎልቶ ስለተከሰተ ሊሸፍኑት ያልተቻለ እውነት ነው። የዛሬዋ ኢምንት የትናንቷ
ገናናዋ ኢትዮጵያ በእግዚአብሔርም ፊት የምትወደድ ነበረች። ምድሯም ለምና እጅግ ያማረ ነበር። ክርስትና
ወደኢትዮጵያ ዘልቆ ከገባ በኋላ ኢትዮጵያ በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነቷ የፀናች በመሆኗ ይበልጥ በልዑል
በመወደዷ ጌታም፤ ድንግልም፤ የእምነት አርበኞቹ ሃዋሪያትም በፍቅር የተመላለሱባትም ነበረች። በሙሴ ዘመን
ደግሞ በታላቅ ሕዝብነቷ በልዑል የተመሰከረላት ነበረች።
ወገኖቼ ኢትዮጵያውን ከ2000 ዓመት ወደዚህ ያለውን ከማነሳና የዚህን መልእክት ገጽ ከማጣብብ ቀደምት
የሆነውን ባነሳ ይሻላል። ምክንያቱም በአብዛኛው የተመዘገበና የተፃፈ በመሆኑ፤ በቀላሉም የተፃፉ መፃሕፍቶችን
ማግኘት ይቻላል ብዬ ስላመንኩበትም ነው።
ኢትዮጵያ አገራችን ዛሬ በምናያት ቅርፅና ይዘት በቀደምቱ ዘመን አልነበረችም። አሕጉረ አፍሪካ፤ የአሁኑ
መካከለኛው ምሥራቅ እስከ ሕንድ ያለው ግዛት የኢትዮጵያ መደበኛ የግዛት አካል ነበር። በ16 ኛው መቶ ክፍለ
ዘመን የተሥራ አንድ ካርታ በአሁኑ ጊዜ በፓሪስ ይገኛል በዚህ ካርታ የተመለከተው አፍሪካ በሙሉ እንዲሁም
መካከለኛው ምሥራቅ የኢትዮጵያ ግዛት መሆናቸውን ያረጋግጣል። የዛሬው አትላንቲክ ውቅያኖስ የኢትዮጵያ
ውቅያኖስ ተብሎ ይጠራ እንደነበር ያረጋግጣል።
ወገኖቼ! ይህ ስለ ግዛትና ስለሥልጣኔ ስለንግድና ገናናነት ብዙም ባያስደንቅም፤ ሌሎችም በየዘመኑ የተነሱ
ታላላቅ መንግሥታት የሄዱበት ሆነውም ታሪክ ሆነው የተደመደሙበት በመሆኑ ብዙን ላይገርመን ይችላል።
የኔ ነጥብ ይህ አይደለም፤ ስለ ኢትዮጵያ ሀገራችን ሊነሳ የሚደንቀኝ የሚገርመኝ ድብቁ፤ ነጩም ሌላውም
የሚደብቀው እንዲነሳ የማይፈልገው ታሪኳ ነው።
ወገኖቼ! በአሁኑ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያ እጅግ ብርቱ ፈተና ላይ ብትወድቅም እግዚአብሔር በክብር
እንዲሚያነሳት ጠላቷም ወዳጇም ልረዱት ይገባል። ርስተ ድንግል ኢትዮጵያን፤ ተዋህዶ እምነትን መለያዋ
አረንጓዴ ቢጫና ቀይ ምንም ያልተለጠፈበት ሰንደቋን፤ አንድ ሕዝብ አንድ ተዋህዶ ሃይማኖትን አንድ ሀገር
መሆኗን ያልተቀበለ፤ ያላመነ፣ ይህንንም እውነት ለማጥፋት የደከመ፤ ዛሬም ከዚህ እውርነቱ ያልተላቀቀ፤
በሥልጣን ላይ ተቀምጦ ዛሬም ለዲያብሎስ የዘር ክልል የድንበር መለያ እየፈጠረ ሕዝብን ከሕዝብ እያጋጨ
የመኖር ሕልም የሚያልም ሁሉ የሞት መርዶውን ዛሬ ይስማ!! በዚች ምድር እንኳን ሊኖርባት ዘሩም
ያለምልክት የሚቀበርባት አገር መሆኗን ዛሬ ላረጋግጥልህ እወዳለሁ።
ዘረኝነትን ያዘልክ፤ በተለይ ለዚች አገር እጅግ መጎስቀል ከ27 ዓመት በላይ እንደሕዝብ እንደድርጅት
ተቧድነህ፤ የዘረፍክ የገደልክ፤ ያፋጀህ ዛሬም በዚያው መንገድ እየሄድክ ያለህ ለአገሩ ኢትዮጵያ አንድነት
የተሰማራውን ኢትዮጵያዊ ወታደር ነፃ ልወጣ ነው በሚል እቅድህ ስትፈጀው የነበርክ ሁሉ ልብ በል እግዚአብሔር
የፅድቅ፤ የእውነት ፈራጅ እንጂ ሸንግለህ የምታልፈው አምላክ አይደለም ስለዚህ ለሚመጣብህ ቁጣና የእሳት
ጠረጋ ተዘጋጅተህ ጠብቅ። አዎን ጠብቅ! የማታልፈው ፈርጀ ብዙ ሰይፍና እሳት መጥቶብሃል!!
ኢትዮጵያ የድንግል እርስት! ኢትዮጵያ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነታችን መሰረት ብርቱ ዘብ ተፈጭታ
ተቆልታ ተሸርፋ ተሸራርፋ አልጠፋ ብላ ሺዎችን ዘመን ለልዑል እውነት በእቶን ስትቃጠል ኖራለች።
ዲያብሎስ የየእለቱ የዘመቻው ኢላማ አድርጎአት የኖረችው ኢትዮጵያ በሕገ ልቡና ጊዜ ምን ያህል በእምነት
ብርቱ እንደነበረች ወደ ኋላ መለስ ብለን ብናይ ለግንዛቤ ይረዳናል።
ከጠላቶቻችን የነጮች ዓለም የምንሰማውና ያደመጥነው ታሪክ በአብዛኛው አገራችንን የሚያሳንስ፤ በብዙ
መንገድም ምንም የእምነት ታሪክ፤ የታላላቅ መንግሥታት ታሪክ ወይም ገድል እንደሌለን አድርገው ሲነግሩን
25
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ኖረዋል። ዛሬም የሚነግሩን የተቀመመ፤ የተደለዘ፤ የተሸረፈ፤ የተለወጠ ድርስታቸውን እንደታሪክ መሰረትና
እውነት አድርገው ነው።
የነጩ ዓለም ሰዎች እጅግ ደፋሮች ፍፁም የዲያብሎስ ውላጆች ናቸው። ለዚህም የሚደግፈን እውነት ቢኖር
ክቡር የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስን ቀንሰው ከልሰው ዛሬ ላይ ፍፁም ከመሰረቱ የወጣ የተቀነሰ የተዛባ ቅርጽና
ይዘት እንዲኖረው አድርገዋል። የጥቁሩን ታሪክ ሰሪነት ለማጥፋትና ለማደብዘዝ፤ የነጩን ዓለም ለማወደስና
ለማንገስ ያልሄዱበት መንገድ የለም። ደፋሮች ናቸው። ፈጣሪን የናቁ ናቸው። የዲያብሎስ ተገዢ ናቸው።
ስለኛው ታሪክ መለስ ብለን ስንመለከት፤ እነሱ ጠፍቶአል ብለው የረሱት በአጋጣሚ ልዑል በፈቀደው
መሰረት ከፍርሥራሽ የወጡ ታሪኮች በአንዳንድ የተጉ የተዋህዶ ልጆች ከሳባ ቋንቋ ወደ ግእዝና ወደ አማርኛ
ተተርጐመው ለንባብ በቅተዋል። ዛሬ የማነሳው የአቶ መሪራስ አማን በላይ ጽሑፍን ሲሆን – የጥንቷ ኢትዮጵያ
ትንሳኤ – መጽሐፈ ሱባኤ – በተባሉት የታሪክና እውነተኛ ክስተት የተገለጠበት መጽሐፋቸው ውስጥ ከሳቡኝ
ከአስደነቁኝ ታሪኮች የሚከተሉት ናቸው።
በቀደሙት ዘመናት ልዑል ለአባቶቻቶን ራሱን በመጠኑ፤ እጅጉን በጥቂቱ ነበር የገለጸላቸው። በዛችው ጥቂቷ
የብርሃን ብልጭታ አባቶቻችን እጅግ በመደነቅ በምላት ይፈልጉትና ሊያገኙት ይደክሙ ነበር።
ልዑል በገለጠላቸው በትንሿ መገለጥ አብዝተው የፈለጉት አባቶቻችን በታሪካችን አስደናቂውን ዘመን
ሸፍነው ለኛም የሚገርም ታሪክን ትተው አልፈዋል።
ከጌታ ልደት በፊት ከ 4500 ዓመተ ዓለም ቀደም ብለው ከነገሱት ኢትዮጵያውያን አፄዎች /ንጉሠ ነገሥቶች/
መሃል አፄ ሰንደቅ አልማን ብናይ
አፄ ሰንደቅ ዓልማ በዘመኑ መላውን አፍሪካ ሩቅ ምሥራቅን፤ ኤሽያን፤ በከፊል አውሮፓን በመዝለቅ 150
አገራትን ፀጥ እረጭ አድርጎ አስገብሮ ከተማውን ሳባ ብሎ በጊዮን ወንዝ መነሻ ላይ መስርቶ ይገዛ ነበር።
በሚሊዮን የሚቆጠር የተለያየ ሰራዊት የነበረው ንጉሥ ነበር። እኒህን ሁሉ እንዲገዛ ከ450 ዓመት ያላነሰ እድሜ
እንዲኖር የፈቀደለት ልዑል አምላካችን ነበር።
ዛሬ ተረት ቢመስልም ሆኖ ያለፈ የተከናወነ ታሪካችን ነው።
ንጉሠ ነገሥት ሰንደቅ አላማን አምላካችን አጋዕዝተ ዓለሙ ሥላሴ ምን ያህል ቢወዱት ነው እንዲህ የባረኩት።
እንዲህም ያፀኑት። በዘመኑ ቋንቋው ሳባዊ ነበር። በእግዘአብሔር የተወደደው አፄ ሰንደቅ አልማ የሚፀልየው
ጸሎትን ብንመለከተው፤ ልብ በሉ በዚያን ዘመን የዓለምን ሁለት ሶስተኛ የሚገዛ ንጉሠ ነገሥት በልዑል ፊት
ምን ይል እንደነበር ዛሬ ላሉ ትውልዶች አምልኮት ውኃ ልክ /መለኪያ/ ስለሚሆን ነው ላነሳው የወደድኩት።
አፄ ሰንደቅ አልማ በአምልኮቱ ምን ያህል እውነትን እንዳገስ እናያለን፤ የምስጋና ጸሎቱ እንዲህ ይላል –
አልፋኤል – አኤል … የመጀመሪያው እውነተኛው መንፈስ፤ በአምላክነትህ ታምኜ ማንኛውንም የሰብአዊውን
ሥራ ስጀምር ፈጣኑ ኃይልህ ረዳቴ ነውና ለዘለዓለም ከኔ ጋር ይኖራል።
የንኤል – አኤል … ሥርዓትን በሥርዓት ጊዜን በጊዜ የምትቀይርና አዲስን ድንቅ የሆነውን የምትሰጥ
እውነተኛው መንፈስ፤ በአንተ ታድሼና አምሬ በዓለም ፊት እታያለሁ። ፀጋንና ክብርን በኃይልህ እቀበላለሁ፤
እውነትህንም እታጠቃለሁ።
አማኑኤል – ኤል … እውነተኛው መሪ መንፈስ በአንተ ስላለሁና ስለቆምኩ በሰላምና በክብር ለሕዝብህ ፀጋና
ረድኤት እሆናለሁ፤ በኃይልህም ከፍ ከፍ እላለሁ፤ በሥልጣንህም የሕዝብን ተቃራኒ ሁሉ ድል አደርጋለሁ።
አንተ በኔ አድረህ ፈቃድህን ፈፅመሃልና አመሰግንሃለሁ።

26
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ኤል – ኢኤል ... አድራሽና ፈፃሚ የሆንክ ታላቁ መንፈስ፤ በአንተ ስላመለኩና ስለፀለይኩ ፍቅሬንና
መስተዋድዴን ነፍስ በተሰጠው ሥጋ ለባሽ ልብ ሁሉ ላይ ፃፍላቸው። በሕሊናቸው እመላለሳለሁና ነፍሴ በአንተ
ከበረ።
ኢያስጴድ – ኤል – ኢኤል … ለዘለዓለም ነዋሪና መስረት የሆንከው ረዳቴ ፈጣኑ መንፈስ በአንተ
ስለከበርኩና ስለታውቅሁ መንፈሴን በመንፈስህ ምራው በኃይልህም አጠንክረው ነፍሴ ስላንተ ሥራ ደስ ተሰኘ።
ኡዳኤል – ኡል … በሰማያትና በምድር በአየርና በባሕር በውስጥና በውጪ የምትገኝ ቅርብ የሆንክ
እውነተኛ መንፈስ በአንተ ስለሚኖር ሥጋዬ የፈለገውን የተመኘውን መባውን ሰብስብለት አስገብርለት ነፍሴንም
በፀጋህ ደስ አሰኘው ለዘለዓለሙ ከአንተ ጋር በክብር ይኖራልና!
ኤልኦቴ – ኡዩኤል … የሚታይና የማይታየውን ረቂቅ ተንቀሳቃሽ ሁሉ የፈጠርክና ያስገኘህ ለዘለዓለም
የምትመሰገን የአምላኬ መንፈስ፤ ወፍ ጎጆዋን ሰው ማደሪያውን እንደሚሠራ እኔንም አንተ ሰርተኸኛልና
በኃይልህ አድሰኝ በሥልጣንህም አንፀባርቀኝ፤ የአንተ ማደሪያህና ማረፊያህ ነኝና አታሳፍረኝ፤ እውነተኛው
መንፈስ ያለበት ሁሉ ለዘለዓለም ፀንቶ ይኖራል። ሕያው ሆኖ በአንተ ፊት ይከብራል።
አውኤል – ኤኋኤል … ክቡርና ምስጉን የሆንከው የታላላቆች ታላቅ እውነተኛው መንፈስ ፍቅርና ሰላምን
እድሜና ጤናን አድለኝ እነዚህ ለሥጋዬ ፀጋ ለነፍሴ ክብር ይሰጠዋልና! ስለዚህ መንፈሴ በአንተ እየተመራ
በእውነት ጎዳና ይጓዛል።
ኡዋውኤል – ኢዋኤል … ግሩም መንፈስ በአስደናቂ ኃይልህ፣ በረቀቀ ሥልጣንህ ለሕይወቴ መከታ ለነፍሴ
አለኝታ ሁነኝ። ከሚቃወመኝ አድነህ ተቃዋሚዬን ከምድር ፊት አጥፋልኝ በፈጣን ኃይልህ ደምስሰልኝ መንፈሴ
በአንተ ተጠብቆ ለዘለዓለም ይኖራል ስለአንተ በአንተ ነፍሴ ደስ ተሰኘች።
አማጋኤል – አኤል ... መፈፀሚያና መጨረሻ የሆንከን ቅዱስ መንፈስ ለዘለዓለም የምትኖር ተወዳዳሪ
የሌለህ ምስጉን ክቡር ነህና ፈቃድህ በአንተ እንደሆነ በኔ በማደሪያህ ይሁን። የመንፈሴም የሥጋዬም የነፍሴም
ደስታ ስጠኝ፤ በአንተ እኖራለሁ። ለዘለዓለም በአንተ ድል አድርጋለሁ። በሥልጣንም ከፍ ከፍ እላለሁ፤ አንተ
የመንፈሴ መሪ የሥጋዬ ክብር የነፍሴ ሕይወት ነህና ለዘለዓለም አመስግንሃለሁ።
የመጀመሪያዎቹ ቃሎች ሳባውኛን ቃል የሚገልፁ ናቸው።
ወገኖቼ! አፄ ሰንደቅ አልማ የዓለምን ሁለት ሶስተኛ የገዛ ንጉሠ ነገሥት ፈጣሪውን እንዴት እንደሚያመሰግን
እንደሚፀልይና እንደሚያከብር አየን። ያውም በሕገ ልቡና ዘመን! በይበልጥም ልዑል በጥቂቱ ራሱን
በገለጠበት ዘመን! በታላቅ ክብርና ግርማ ላይ ያለ ንጉሥ ይህን ሲል – ዛሬ ላይ ሆነን የዘመናችንን ገዢዎችና
ሕዝቦች አምልኮታቸውን ስናጤነው ምን ያህል የወደቅን ምንስ ያህል ከፈጣሪ የተጋጨን እንደሆንን አብዝቶ
ይመሰክርብናል።
እስኪ በተጨማሪ ከአፄ ሰንደቅ አልማ በኋላ የነበረውን እንዲሁ እንደአባቱ የከበረውን የገነነ ንጉሠ ነገሥት
አፄ አፊላስን እንመልከት
ከ 4589 ዓመተ ዓለም በፊት የዓለም አባት እስከመባል የደረሰው የአፄ አፊላስ ተግባር ምንድነው። ከአባቱ
ከአፄ ሰንደቅ አልማ በኋላ የነገሰው አፄ አፊላስ በመረዌ በአክሱም ከተማውን አድርጎ ብዙ ነገሥታትን አስገብሮ
ይኖር ነበር። እንዲሁ እንደሱ ብርቱ ባይሆንም በመካከለኛው ምሥራቅ በታላቅነቱ የሚታወቀው የባቢሎን ንጉሥ
ናቡከደነፆር እንዲሁ በሥሩ ብዙ መንግሥታትን ሕዝቦችን ይገዛ ነበር።
በአንድ ወቅት አፄ አፊላስ ስርዓተ ንግስናውን በጊዮን ሳባ ከተማ ሲያከብር ለሁሉም መንግሥታትና ሕዝቦች
በበዓሉ እንዲገኙ የክብር ጥሪ አድርጎ ነበር። በዚህ ጥሪው መሰረት የተገኙም ያልተገኙም ነበሩ። ከተገኙት

27
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ውስጥ በናቡከደነፆር ሥር የነበሩ ከአይሁድና ሶሪያ ጎረቤት የነበሩ ሕዝቦች ነበሩ። አፄ አፊላስ ላዘጋጀው በዓል
ጥሪውን አክብረው ተገኝተውም ነበር። በዓሉ ካለቀ በኋላ እነዚሁ ሕዝቦች ስለአስገባሪያቸው ናቡከደነፆር
ጨካኝ አገዛዝና በነሱ በተለይ ያደረሰባቸውን በደል ገልጸው ነግረውት ነበር። አፄ አፊላስ በዘመኑ እውነትን
ያነገሰ ቅንነትን የሚወድ መንፈሱም እግዚአብሔርን በመፍራት የተሞላ ስለነበረ አዘነ። በዚህ ብቻ አልቆመም
ለናቡከደነፆር ደብዳቤ ፃፈ። ደብዳቤውም እንዲህ የሚል ነበር።
በዚያን ጊዜ ኃያላን የሆኑ ፀዌ ሠራዊት አፄ አፊላስ ልኮ ግብፃውያንን መታ፤ በቃዴስ የሚኖሩትን መንደሮች
አቃጠለ የሚል ወሬ ለከለዳ ንጉስ ለናቡከደነፆር ደረሰው። የከለዳው ንጉስም ለሱሳ ንጉስ ለጢሮስ ለአሶር
ንጉሶች እንዲህ ብሎ ላከ።
የሱባያ ንጉስ በሰራዊቱና በአምላኩ ተመክቶ እኛን ለመውረር የትምክህት ደብዳቤ ላከልኝ ደብዳቤውም
እንዲህ ይላል። የከለዳ ንጉስ ናቡከደነፆር ሆይ ሕዝብህን ሳያጠፋ የምታጠፋ ከሆክ በነሱ ስም ሆኜ አጠፋሃለሁ።
ሕዝቡ የሚበላው ሳያጣ የምታስርብ ከሆንክ ያለርህራሄ አስሬ በረሃብ እገድልሃለሁ። ሕዝቤ መኖሪያ ሳያጣ
ማረፊያ ስለከለከልከውና ክፉ ተግባርን ስለጣልክበት መጣሁብህ የሚል ደብዳቤ ላከብኝ። አሁን ደግሞ ግብፅን
መታ! በቃዴስ ያሉትን መንደሮች አቃጠለ የሚል ወሬ ሰማሁ። ስለዚህ ኑ እንሰብሰብና ተማክረን እንግጠመው
አለ። የሱባና የአሶር ንጉሶችም ይህ የምትለው ቃል ሁሉ ልክ አይደለም በኛና በአንተ መካከል በሰማርያና
በኢየሩሳሌም የሚኖሩ አይሁድ ሁሉ ሰላምን አጥተው ሰላምን ፍለጋ ወደግብፅ ወደሱባ ሄደው ተቀምጠው
ሳለ ስለነገሩት እንጂ፤ ይህ የታላቅ ሕዝብ ንጉስ ከኛ ይልቅ ሕዝባችን ስለወደደው ብንገጥመው ድል አድርጎ
ይመልሰናል ያጠፋናል። ስለዚህ የሚለንን ሰምተን ማድረግ እንጂ ሌላ ነገር አታስብ የሚል መልስ ላኩበት።
ናቡከደነፆርም አማካሪዎቹን ሰብስቦ እነርሱም ስላልደገፉት በአንድ መቶ ሽማግሌዎች ስጦታ አሲዞአቸው
ወደመረዌ ላካቸው። የመረዌ ንጉስም ለአፄ አፊላስ ወደአክሱም ላካቸው። ልመናቸውን ተቀብለ። አፄ አፊላስም
የዓለም አባት ተባለ።
ወገኖቼ የዚህ ታሪክ ባለቤት መሆናችንን እናውቃለን? ከራሳቸው አልፈው ስለሌላው አገር ሕዝብ የሚጨነቅ
የሚያዝን መሪ!! ልብ በሉ የዛሬዎቹን ማፈሪያዎች ድንክዬ መሪ ተብየዎች እንኳን ለሕዝብ ሊቆሙ ሕዝቡን
በመፍጀት የሚኩራራ በሴራና በክፋት በጭካኔ የተሞሉ በኢምንት ግዛታቸው እጅግ የታበዩትን እስኪ ከቀደሙት
ጋር አወዳድሯቸው!!!
አፄ አፊላስ ብዙዎችን ካስገበረ በኋላ የአባቶቹን የነመልከፄዴቅን፤ የነኢትኤልን፤ ሕግና ሥርዓት እንደገና
እንዲታደስና እንዲፀና አደረገ። ለሚገዛቸወም አገሮች ሁሉ እንዲህ ሲል አዋጅን አፅፎ ላከ። ይህንን አዋጁን
ልብ ብላችሁ ተመልከቱት ከ4500 ዓመተ ዓለም በፊት የታወጀ ነው።
እንዲህ ይላል!
የነገሥታት እራስ የጠቢባን ልብ አፄ አፊላስ እንዲህ ይላል – በዚህ ዓለም ምድር የምትኖሩ ነገስታትና
አዛውንት ቃሌን ስሙኝ ትእዛዜንም ፈፅሙ፤ የምላችሁን ሁሉ አድርጉ ቃሌን ሰምታችሁ ትእዛዜን ፈፅማችሁ
ብትገኙ ለእናተ ክብር ለወገናችሁ ደስታ ለልጅ ልጆቻችሁ ደህንነት ለጎሳችሁ ሰላምና ፍቅር ይሆናል። ኤል ብዬ
የምጠራው አምላኬ በሰማይ እርሱ በአየር የሕይወት መንፈሱ በምድር የምሥራች ቃሉ ለዘለዓለም የሚኖር እርሱ
ብቻ ነው። ስሙም ቅዱስ አምላክ ለዘለዓላም ነው። አንደሌሎች አማልእክት አይመስልም ተወዳዳሪ ፈፅሞ
የለውም። ባሕርዩ የማይገመት መልኩ ሊያዩት የማይቻል ስውር ሊቀርቡት የማይቻል የቃልና የመንፈስ ኃይል
ነው። የምሥራች ቃሉ ግን ከሰው ልጅ ሰው ሆኖ የሚታይበት የሚዳሰስበት ቀን ይመጣል። ለዚያ ትውልድ
ያየው ባለማየቱ ወዮለት!! የሕይወት መንፈሱ በዛን ጊዜ ለእያንዳንዱ የሰው ልጅ ሕይወትን ከማስተዋል ጋር
ይስጥ ዘንድ በቃል ይመራል። ለሰው ልጆች የተዘጋጀውን ሁሉ ያድላል።

28
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ይህ ሊሆን ግድ ነው ይላል፤ የሕይወት መንፈስ፤ እናንተ አሕዛብ በባሕር ዳር የምትኖሩ በዋሻ የምትቀመጡ
ስሙኝ አድምጡኝ የምትታመኑበት መሳሪያና አምልኮት ሁሉ ይሰበራሉ ይደቅቃሉ። አንዱን በአንዱ መልክ
አትመስሉት ወዮላችሁ! ታፍራላችሁ መኸረምን በጨረቃ፤ ብህ ጢቅን በኮርማ ወይፈን፤ ሃደርን በላም በዛፍ፤
ክሊኑምን በበግ፤ ሚዛንን በተኩላ፤ ሰቡንን በጉጉት አሞራ፤ ስታርን በኮከብ፤ ሃሩስን በጆፌ አሞራ፤ ገዲን
በንስር፤ ሄፌርቱንምና ሆትን በእባብ፤ ሴቤቅን በዘንዶ በአዞ፤ ቡባስቴናን በነብር፤ ቡቀን በእንሽላሊት፤ አምንን
በፀሐይ፤ ቡዳሃን በነፋስ፤ ሺባንና ሂንዱህን በእሳት፤ ሳርህንና አጵሌን በተራራና በኮረብታ – የምትመስሉና
የምታመልኩ አሕዛብ ሆይ! ይህ ሁሉ እናንተ ስለሰራችሁትና ስለመሰላችሁት እንደእናንተ ፈራሽ ነውና!
ወደማይፈርሰውና ወደማይጠፋው የሕይወት መንፈስ የምሥራች ቃሉ ነው። እሱ እራሱ ሁሉን ይገልጥላችኋልና፤
ይሰጣችኋልም ይህን ብታደርጉ እናንተን ይቀድሳል። እናተም እንደርሱ እርሱም አንድ ነው እናንተም በአንድ
ትሆናላችሁ። አሁን ግን ያላችሁት በሞትና በሕይወት መሃከል ናችሁ። አባቶቻችን ቢበድሉት ታናናሾች አባቶች
የታላላቆችን አባቶች ሕግና ትእዛዝ አፈረሱ ይኸውም አባትነትን ያጠፉ ዘንድ ነው። እኔ ግን አባትነትን አኖር
ዘንድ የሁሉንም ሕግና ትእዛዝ መርጬ ልኬላችኋለሁ።
አዳም የፈጣሪውን ትእዛዝ ባይፈጽም ከሕይወት ተሻረ። የማይጠፋ ሞትን አገኘ። ኖኅ የአምላክን ቃል ሰምቶ
መርከቡን ቢሠራ ከዓለም ጥፋት አምልጦ ዘርን አተረፈ። መልከፄዴቅ የተባለው የኢትኤልና የሃመራቢያ አባት
የአዳምን ሞት አይቶ በሕይወቱ አምላኩን በፈጣሪው የሕይወትንም ቃል በሚሰዋው መስዋእት መሰለው።
ስለዚህ ስሙ የሰላም ንጉሥ የደህንነት ካህን ተባለ። ልጁ ኢትኤል የአባቱን ምክር ተቀብሎ የፈጣሪውን ሕግና
ትእዛዝ ቢያደርግ እንደ አባቱም እንደመልከጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህን ቢሆን አባትነትን አገኘ። ይህችን ምድር
እርስትህ ብሎ ሰጠው። ከዘሩም ጭን ታላቁን የሕግ ንጉሠ ነገሥት አፄን አስነሳለት።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! እናንተ ይገባቸኋል። ምክንያቱም በውስጣችሁ ያለው እውነተኛው መንፈስ
– እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና! የቀደሙት አባቶቻችን የደመቁ የተወደዱ የተከበሩ አስደናቂ የእምነት
ተጋድሎ የነበራቸው ናቸው።
የነዚህን ከላይ በመጠኑ ያነሳኋቸውን ከ4500 ዓመተ ዓለም በፊት የነበሩ ታላላቅ ኢትዮጵያዊ ነገሥታት ሙሉ
ታሪካቸውን እኔም አላገኘሁትም።
መሪራስ አማን በላይ በገጠማቸው እድል የተቀበሩና የተረሱ ሳባዊ ሰነዶችን በማግኘታቸው፤ ከሱባ ወደ ግእዝ
ከግእዝ ወደ አማርኛ የመለሱትን መጠነኛ ታሪክ እንጂ፤ እኛ ስንስማ የኖርነው በቅርብ የነበሩ ኢትዮጵያውያን
ነገሥታትን ታሪክ ሲሆን የሩቁን ግን አልሰማንም። ለዚህም ነው በዚህ መልእክቴ ላይ ልገልፀው የሳበኝ።
የቅርቡን ታሪካችንንም ቢሆን ነጮች ዘርፈውናል። ቅርሳችንን አሻግረዋል፤ ደልዘዋል፤ ደብቀዋል፤ አቃጥለዋል።
የራሳቸውን የውንብድና ታሪካቸውን ቀባብተውና አሳምረው እንደታላቅ ገድል ለመላው ዓለም አስተምረዋል።
የዚህ መሃንዲስ ከነጮችም እንግሊዝ ቀዳሚውን ሥፍራ ትይዛለች።
በዚህ ዘመን የዘለቀ የነጮች ዘረፋና ውንብድና ሳያገኘው በሱዳን ውስጥ ከፍርሥራሽ ውስጥ መሪራስ አማን
ያገኘው ዣን ሸዋ የሚል የቀድሞ የአባቶቻችን ታሪክ ብዙ ቁም ነገር አስጨብጦናል። ወገኖቼ! እነዚህ ሁለት
ታላላቅ መንግሥታት የነበሩበት ዘመን ሰው በሕገ ልቡና የሚተዳደርበት ወቅት ነበር። እግዚአብሔር በተወሰነ
መጠን ቢገለጥላቸውም እንደ ሕገ ኦሪቱ እንደ ወንጌሉ የምሕረት ዘመን በሙላት አልተገለፀም። በጥቂቱ
ቢናገራቸው አብዝተው ፈለጉት ወደዱት ታመኑበት በእርግጥም ፀኑበት አንፀባረቁበት ልዑል እንዲህ ነው
የሚያደርገው። ለታመኑበት ለወደዱት በማናቸውም ዘመን ተገልጦ የሚያፀና ድንቅ አምላክ ነው። የአፄዎቹን
ጸሎት ሁላችሁም ልብ ብላችሁ ካስተዋላችሁት ስለ ሕገ ኦሪት ስለ ወንጌል አያውቁም ነገር ግን ድንቅና
አስገራሚ ፀሎታቸውን ስታስተውሉት በእውነትና በመንፈስ ማምለክ ምን እንደሆነ በትክክል ትረዳላችሁ።

29
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

የዛሬው ትውልድ፤ የዛሬው መሪዎች በነዚህ ነገሥታቶች የእምነት ፅናትና መንፈሰ ብርቱነት ፈጣሪያቸውን
መውደድ ሲለካ ሚዛኑ ላይ ሲያርፍ እንዴት እንደሚቀል እዩት።
ታላላቆቹ ነገሥታት በሺዎች ከተቆጠሩ አመታት በፊት በግዮን ዳርቻ በሳባ በአክሱም የነገሱ ዓለምን ያስገበሩ
እንዲህ ከላይ እንደሰማችሁት ፈጣሪያቸውን ወደውታል። ሕዝባቸውን በሥራቸው የነበሩትን ነገሥታትን ሁሉ
በደነገጉት ሕግ ለአንዱ አምላክ ኤል ብለው ለጠሩት አስመልከዋል። አስገዝተዋል።
ልዑል በጥቂቱ በራእይ እየተገለጠ በተመረጡ አባቶች እነመልከጼዴቅ፤ ኢትኤል፤ ኢትዮጵ፤ እየተገለፀ
ትንቢት እንዲናገሩ እያደረገ መርቶአቸዋል። አኑሮአቸዋል፤ ባርኮአቸዋል። በጥቂቱ ተገልጾ ታውቆአቸዋል። እነርሱ
ግን በሙላት በብርቱ ፈልገውታል። ታምነውበታል ወደውታል፤ አክብረውታል። ለሕጉም ለፈቃዱም በደስታ
ተገዝተዋል። ምድርን ያንቀጠቀጡ መሪዎች ወድቀው ሰግደውለታል። አመስግነውታል። አስመልከውታል።
ወገኖቼ፤ እግዚአብሔርን ማስደሰት የሚቻለው በምንም አይደለም በማመን በመታመን ብቻ ነው።
እንደነሱ እጅግ በጥቂቱ ያውም በራእይ የተነገራቸውን በማመን እንዴት እንደወደዱት እንደታመኑበት እሱም
እንዳስደሰታቸው እንዳላሳፈራቸው አይታችኋል። ዛሬስ፤ ለነሱ እራሱን የከለለው አምላካችን፤ በተለይ ህገ ኦሪትን
በጣቱ ዕፎ በግልፅ ደንግጎ፤ በአካል መጥቶ ከክብሩ ወርዶ የደነገገውን ሕግ ፃድቅነት እንደበግ ተሰውቶ አፅድቆ
የዘላለምን መድህን አቁሞ ቀሊሉን ሸከም ወንጌሉን /የምሕረት ዘመኑን/ አጎናፅፎናል። ግን እንዴት ተቀበልነው?
ነቢያት ሃዋሪያትን እንዴት አደረግናቸው? ሥራችንን ስለምናውቅ እኛው ምስክር ስለሆንን መድገም አያሻም።
እሱ በሙላት ሲፈልገን በጥቂቱም እንኳን አልፈለግነውም። አልሰማነውም! አልተቀበልነውም። እንዲያውም
ካድነው በተሰጠን እውቀትና ጥበብ ታምነን ካድነው። በሱ ቦታ ይቺ ልቅምቃሚ እውቀታችንን ሥልጣኔያችንን
ሃብታችንን ሥልጣናችንን አመለክን፤ እንዲያውም በእርሱ ፈንታ በእርሱ የተፈጠረውን ከክብር ይልቅ ውርደት
የመረጠውን ዲያብሎስን አመንን በሥራና በፈቃድም መሰልነው እንደሱም ሆንን። የአባቶቻችንን የትላንቱን
በዚሁ ልግታው እጅግ ብዙ አስደማሚ የልዑል አርበኞች እንደፀሐይ አብርተው አልፈዋል።
ወደዛሬው እውነታ እንመለስ።
ወገኖቼ! አባቶቻችን የራሳቸውን ግዳጅ ተወጥተው እንደኮከብ አንፀባርቀው አልፈዋል። በነሱ ጫማ ልንተካ
ሲገባን ከንቱ ሆነን ስለቀረነው ስለእኛ ስናነሳ ብዙ ጉድ የተሸከምን ሆነን እንገኛለን።
አባቶቻችን እንደዛሬው ትውልድ የእድሜ ፍርፋሪ ተቀበለው አልኖሩም። በረቀቀ ሕክምና አልተደገፉም።
በእምነት ፅናታቸው የእድሜን ከፍታ ልዑል አጎናፅፎአቸዋል። ከላይ እንደምሳሌ ያነሳሁላችሁ ሁለቱም ነገሥታት
ከ450 ዓመት ያላነሰ እድሜን ሁሉ ተወደው ተከብረው ኖረዋል። በክብርም አልፈዋል። ውኃ ልኮቹ ሚዛኖቹ
እንላቸዋለን። የዛሬ መሪዎች የሃገራችንም የውጪውም በመንደር እልቅናችሁ እጅግ የምትጎፈሉ፤ ትእቢታችሁ
ወሰን ያጣ፤ ክህደታችሁን ፈጣሪን መካድ እንደእውቀት፥ በአደባባይ እየገለፃችሁ በድርጊታችሁም የአዋቂነት
መለኪያ አድርጋችሁ በተዋህዶ እምነት ፀንቶ ያለውን ስትነቅፉ ስትሳደቡ ስታቃልሉ ቅርም የማይላችሁ።
መዳቡን ወርቅ ወርቁን መዳብ ያደረጋችሁ። ተመዘናችሁ ተለካችሁ ያው ናችሁ። ጊዜ ተትረፍርፎ ተሰጥቷችሁ
እንኳን ልትፀፀቱ ንስሓ ልትገቡ ጭራሽ የትአለ እግዚአብሔር? እስኪ እንየው? የምን ማስጠንቀቂያ የምን
ምክር? እያላችሁ የምታፌዙ፣ የእግዚአብሔርን ትእግሥት አጠናቃችሁ የበላችሁ። ምን ዓይነት ጉደኛ ትውልድ
ናችሁ፤ምንዝርና ማጭበርበር፤ ማታለል ንቀት ሌብነት ዘረፋ ዘረኝነት በባዶ መኮፈስ ትእቢት፤ እኔ ብቻ
አውቃለሁ ባይነት ታላላቆችን ማዋረድ መናቅ መስደብ፤ በእምነቱ /በተዋህዶ/ የፀናውን ማዋረድ ማሳደድ ምን
ሥፍር ቁጥር አለው ይህ ሁሉ የቀንም የሌሊትም ምግባራችሁ ሆኗል።
ኢትዮጵያ አገራችን በዘመኗ ሁሉ ካፈራችው ትውልድ እንደ አሁኑ የወደቀና የረከሰ የጠፋ ትውልድ ከማህፀኗ
ወጥቶ አልታየም። በሁለመናው የተውሸለሸለ አገሩን የናቀ፤ በተለያዩ አምልኮ ባእድ የተጠመደ /የዲያብሎስ

30
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ድርሰት በሆኑት የሃሰት እምነቶች የተጠመደ ሆኗል። የሚገርመው ይመለሳል ተብሎ በትእግሥት ሲጠበቅ እንኳን
ሊመለስ ያለውን እጅግ ጥቂት የሆነውን እያወከ እያናወፀ በመውሰድ ወደጥፋት እየቀላቀለ ይገኛል።
ፈጣሪ ፍፁም ተክዷል። ዲያብሎስ ነግሷል። የእግዚአብሔር ትእግስት እስከመጨረሻው ጠርዝ ተገፍቷል።
የተዋህዶ እምነት እውነተኛውን አማኝ ማግኘት ፍፁም አዳጋች ሆኗል። ስለአገራችን ስንሰማ ከሁሉም በላይ
የሚገርመን ቅጣቱ እየወረደበት መመለስ መፀፀት ፍፁም በልቡ ያለመኖሩ ሲሆን፤ የሚገርመው ምሁር
ተብዬው ጋዜጠኛው መሪ ተብየው እንደአሸን የፈላውን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ያጥለቀለቀው ወጣት ዲያስፖራ
እያሉ የሚያንቆለጳጵሱት ትውልድ ሁሉም ማለት ይቻላል መፍትሄ እያለ በፍለጋ የተጠመደው ከምእራቡ
ዓለም የዲሞክራሲ ፍልስፍና ነው። ተቀዋሚ ተብየው ፕሮፌሠሩ ዶክተሩ በየሚዲያው ቀርበው ከሽነው በሰላ
ምላሳቸው ሲደሰኩሩ ከሰማይ መና የሚያወርዱ የሚመስሉ ናቸው።
መላው ሕዝብ በረሃብ በኑሮ ውድነት በዘር ፍጅት በስደት በጭንቀት ሰላምን በማጣት ለመኖሪያውም
ለእለቱም መጠለያ አጥቶ ሲጨነቅ ሲጠበብ መልሳቸው ዲሞክራሲ ስላልተጋትክ ነው። ነገ ስንግትህ ትድናለህ
የሚሉትን ነው የሚያዳምጠው። ራሱ ሕዝቡ በጉዳትና በጭንቀት ተውጦ የየእለቱን ፕሮፓጋንዳቸውን እንደምሳና
ቁርስ ጆሮውን ተክሎ ሲያዳምጥ ሲውል ማደሩ ነው።
ልብ በሉ ወገኖቼ! ከስድስት ጊዜ በላይ ያ ሁሉ ምክር ግሳፄ ፍርድ ሲፈስ ማን ሰማ? ዐይናችሁ እያየ
ጆሯችሁ እያደመጠ ፍርዱ እንደታዘዘው እየቀቀላችሁ እሳት ባሕር እያጠለማችሁ / የረሃብ እሳት የዘር ፍጅት
እሳት የዋስትና ማጣት እሳት የሥራ የመጠለያ ማጣት እሳት ምን ስፍር ቁጥር አለው ይህ ሀሉ እየወረደባችሁ
ማን ሰምቶ! የትኛው መንግሥት? የትኛው ሚዲያ ፕሬስ የትኛው ተቃዋሚ? የትኛው ምሁር የትኛው መሪ፣
ስለመልእክቱ ተናገረ። በፍፁም። መልእክቱ እየለካህ እየሰፈረህ እየነቀለህ እያነደደህ እየጠረገህ የታዘዘውን
ጥፋት ሁሉ በየደረጃው እያሳዳገ ሲያጠፋህ ትስቃለህ ታፌዛለህ የኖኅ ዘመን ሕዝቦች ልክ እንደአንተው ነበር
በኖኅ ጩኸት ሲያፌዙ የነበረው። እጉልበታቸው ሲደርስ ወገባቸው ሲደርስ ያው ያፌዙ ነበር እንጂ መች ሰሙ፤
አንገታቸው ጋ ሲደርስ ግን ቢጮሁ በሽርፍራፊ ሰከንዶች መፍትሄ አይመጣ አከተሙ አንተም ለታሪክ ትርክት
እንደምሳሌ ትቀርብ እንደሆን እንጂ ሌላ ምን ትርጉም አለህ!
ዛሬ በአገራችን ያለው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ እንደሆነ እንኳን በልዑል የሚታመነው ቀርቶ የጠፋውም ትውልድ
ግራ ገብቶት እንደ ውኃ ላይ ኩበት ሲዋልል እየታየ ነው። አገራችን ልትፈርስ ነው : በዘር ልትገነጣጠል ነው
እርስ በእርስ ልንጫረስ ነው እየተባለ ሁሉም በድንጋጤ የተዋጠበት ዘመን ነው። ሁሉም እንደሚያውቀው
አገራችን ኢትዮጵያን ወደዚህ ደረጃ ያደረሳት ዛሬ ጥግ ይዤአለሁ የሚለው ሁሉም የሚጠራው ወያኔ በሚለው
ስሙ እኔም የማውቀው ዘረኛ ቡድን ነው። 27 ዓመት ሙሉ ሲፈጭህ ሲቆላህ የቆየው ክፉ ወፍጮ ከአጠገብህ
ሳይርቅ በሩቅ መቆጣጠሪያ እየተቆጣጠረህ ግራ ተጋብተህ እንደ አሻሮ ትቆላለህ፤ መፍትሄ የለውም። እሱን
ተክቶ የመጣው ከራሱ ማሕፀን የወጣው መንግሥት ደግሞ ችግርህን ከድጡ ወደማጡ አድርጎብሃል።
አንዱን ዘር በአንዱ ላይ እያናከሰ የዘራው ዘር አሁን ፍሬው ደርሶ እሬቱን እየተጎነጨኸው ነው። በመላው
አገሪቱ የተቀጣጠለው የዘር ግጭት እራስህን በልቶ ይጨርስሃል እንጂ አሸንፎ መውጣት የለም። እግዚአብሔርንና
ምክሩን ስለናቅህ፤ በአምልኮ ባእድ፤ በራስህ የኤቢሲዲ እውቀትህ ስለታመንክ፤ ለማመን ብትሞክርም ነጩና
አረቡ ውስጥ የመሸገው ዲያብሎስ በረቀቀ ድርሰቱ በፈጠረው እንደ ካቶሊክ፤ ፕሮቴስታንት፤ እስላም በመሳሰሉት
እምነት ተሸሽገህ የመፍትሄ ያለህ ትላለህ! ቀጣፊ ትውልድ፤ ሌባ! አመንዛሪ ትእቢተኛ፤ አገሩን የጠላ
ትውልድ! ፈልግ መፍትሄ! ከሰማይ እንደ ደመና ታወርድ ይሆናል። መቼም ይሳነኛል የምትለው ነገር የለም።
ከንቱ ትውልድ! ምን ተነካህ ገና ምንም ሳይደርስብህ! እዚህም እዚያም በማያቋርጠው ግጭት ጥቂት ስዎች
ስለሞቱ፤ ስለቆሰሉ፤ ስለተሰደዱ ትደነቃለህ አገር ፈረሰ ትላለህ! መቼ ተጀመረ! ከዚህ መልእክት መውጣት
በኋላ ጉድህን ታየዋለህ።

31
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

በከተማችን አንድን ዘር ለማንገስ በቀደሙት መልእክቶች የተሰጡትን ማስጠንቀቂያዎች ንቃችሁ የድሃው ቤት


አፍርሳችሁ የተለያየ የማጭበርበሪያ ስም ለጥፋችሁ። ከንጉሠ ነገሥቱ ጀምሮ በገንዘባቸው ገዝተው የኖሩበትን
የመኖሪያ ይዞታ ሰነድ አልባ በሚል ስታስጨንቁ ስትበድሉ ስትነጥቁ የማይሸከሙትን የገንዘብ ክፍያ ስትጥሉ
ሊዝ ግባ የሚል የሕግ ሽፋን የተሰጠው ንጥቂያን ስትተገብሩ፤ የወደዳችሁትን ቦታ ድሃውንና ጎጆውን በልማት
ስም በዶዘር ስታፈርሱ፤ በምትኩም የራሳችሁን ዘር ፎቅ እንዲገነባ ስታደርጉ፤ ሁሉንም የአገሪቱን ባንክ
ኢንሹራንስ በቁጥጥራችሁ ሥር አድርጋችሁ ለዘራችሁ ያለመያዣ ብሩን በገፍ ስታድሉ፤ የገበሬውን መሬት
ነጥቃችሁ የራሳችሁን እርሻ ስታደራጁ፤ በሜጋ ፕሮጀክቶች ስም ሁሉንም በራሳችሁ የዘር ቡድን አድርጋችሁ
ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ዘረፋ ስታደርጉ የራሳችን ከተማ ባላችሁት የአገሪቱን ሀብት ሁሉ በጠራራ ፀሐይ ያለማቋረጥ
ዘርፋችሁ ስታከማቹ በውጪ የውጭ ምንዛሪ ስታከማቹ ድሃውን ወደመጨረሻው ድህነት ስትነዱ፤ መላውን
ትውልድ ለስደት ስትዳርጉ በየባሕሩ ሰምጦ እንዲቀር ስታደርጉ፤ የሚበዛውን የተቃወማችሁን ስታፍኑ ስትገድሉ
ስትሰውሩ ሃይ የሚላችሁ ጠፍቶ ዛሬም ለጊዜው ጥግ ብትይዙም ገና ብርቱ እዳ አለባችሁና አታመልጡም።
በሰውኛ ታክቲካል ማፈግፈግ ትሉት ይሆናል /ዛሬ ያለውን ሁኔታ/። አታውቁትም ድሮም ንቃችሁታል ልዑል
እግዚአብሔር ዛሬ ያለውን ነገም የሚሆነውን ቀድሞም ተናግሮአል ያም ይሆናል ዛሬም እየሆነ ነው። እናንተም
በቅን ፍርዱ ትጠረጋላችሁ እንጂ በዚች ምድር ምሽግም ሆነ መከለያ የላችሁም። ለናንተ ሽፋን የሚሰጡ
ከለላ ያደረጉላችሁ የውጪውም የአገር ውስጥም የሆኑ ሁሉ እንዲሁ በቅን የልዑል ፍርድ ይደመደማሉ እንጂ
አያድኗችሁም። መልካም ሥራ እንጂ መልካም ምላስና ብልጠት የሽንገላ አንደበት በምንም መስፈርት ዘላቂ
መፍትሄ አያመጡም። የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም።
የድሃ ደም ፡ የድሃ እምባ ፡ በማንአለብኝነት የፈሰሰ የቅኖች ደም የእግዚአብሔር ሕዝቦች ደም ሁሉም
የሚያስከፍሉ ታላቅ እዳዎች ናቸው። ፍቅር የአውሬዎችና የደም አፍሳሾች መሸፈኛ አይሆንም። ወንጌላዊው
ዮሐንስ በአንደኛ መልእክቱ ሞት ለሚገባው ምህረትን አለምንም ያለው ወዶ አይደለም። ስለእግዚአብሔር
የምሕረትና የቅጣት አካሄድ በሚገባ ስለሚያውቅ እንጂ!
የዘመኑ ወገኖቼ!! የእግዚአብሔርም ህዝቦች የአዳም ዘሮች
በከተማችን አንድ ትልቅ ቄራ አለ። የወፈሩ የጠገቡ የሰቡ በሬዎች ከዚህ ቄራ ገብተው ይታረዳሉ። ይበለታሉ።
ይከፋፈላሉ። እንግዲህ ወገኖቼ በድሃ ደም፣ በዘረኝነት፣ በዝርፊያ፤ በሥልጣን በጠመንጃ የተመካህ፤ የትላንቱም
የዛሬውም አለቃና ምንዝር የሆንከው ሁሉ እንኳን ደስ አለህ ቄራ ደርሰሃል። እንደአረድክ እንደዘረፍክ እንደፈነጨህ
መዝለቅ የለምና ስላበቃ እንደበሬዎቹ እግዚአብሔርም ላንተ ቄራ አዘጋጅቶልሃል። በዚያ ትደመደማለህ።
ኢትዮጵያን የጠላ፤ ድንግልን ተዋህዶን እምነት የጠላ፤ ባንዲራዋን የጠላ ሁሉ ይጠረጋል እንጂ በፍፁም
አይድንም። ማምለጫም መዳኛም መንገድ ፍፁም የለውም። በሰሜን በምእራብ በምሥራቅ በደቡብ የመሸጋችሁ
አገራችንን እንደ አንጋሬ ቆዳ ወጥራችሁ ያስጨነቃችኋት ሁሉ በከፋ እሳት ትጠረጋላችሁ እንጂ ከእንግዲህ
እድሜ የላችሁም ፡ የሚጠቅማችሁን ጊዜ በደል በበደል ላይ፣ አማጽ በአመጽ ላይ እየጨመራችሁ መጣችሁ
እንጂ ቅንጣት የመጸጸት ምልክት አልታየባችሁም። በመሆኑም ስታፌዙ ጊዜው አለቀ ተከደነ። የመጣውን
መቀበል ብቻ ነው።
ስለአገሩ በየድንበሩ የወደቀውን ወገን፤ ስለኢትዮጵያ የተሰዋ፤ የቆሰለ፤ እንደ የኔ ብጤ የተጣለ ዳግም ፍርድን
ያገኛል እንጂ ውለታው አይጣልም። አንተ ደሙን ያፈሰስክ የትላንቱም የዛሬውም ብርቱ እዳ አለብህ በብዙ
እጥፍ ትከፍላለህ። በደም ከጨቀየው ማንነትህ ጋር በተለይም በሰሜን የመሸግህ የእዳ መክፈያ ሰዓትህ ደርሷልና
ተዘጋጅ ይልሃል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር። አገር ቆርሶ ለባእድ መሥጠት ቦታ ለማስፋት ዘርን ማጥፋት
መጨፍጨፍ ሁሉም ዛሬ እጫፍ ስለደረሱ ያንተ መጥፎ ትውልድ ከታመኑብህ ምንዝሮችህ ጋር ትቀበራለህ፤
ታሪክም ትሆናለህ።

32
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

በጥቅሉ በአገሬ በኢትዮጵያ ያለህ በውጪም ያለህ! ከእውነተኛይቱ ተዋህዶ እምነት የወጣህ፤ ይህችን
ብሩክ ምድር የድንግል ምድር፤ ልዑል በስስት የሚያያት ምድር፤ የጠላሃት፤ ለጥፋቷ የደከምክ፤ በባእድ
አምልኮ የታመንክ፤ አመንዛሪ ሌባ ዘረኛ ትእቢተኛ ጨካኝ ትውልድ፤ እስላም፤ መናፍቅ፤ካቶሊክ፤ ተብታቢ፤
ድግምተኛ፤ ጠንቋይ ባለውቃቢ፤ ዋቄ ፈታ መተተኛ ሁሉ ከኢትዮጵያ ምድር ትጠረጋለህ። አንተ ከተጠረግህ
በኋላ ኢትዮጵያ የዓለም ሁሉ ጌታ መጠለያ የቅን ሕዝቦች መፅናኛ ትሆናለች። የልዑል ቃል እንዲህ ይላል!

_ በኢትዮጵያ ወንዞች ማዶ ላለች ክንፍ ያላቸው መርከቦች ላሉባት መልእክተኞችን


በባሕር ላይ የደንገል መርከቦችንም በውኃ ላይ ለምትልክ ምድር ወዮላት! እናንተ
ፈጣኖች መልእክተኞች ሆይ ወደረጅምና ወደ ለስላሳ ሕዝብ ከመጀመሪያው አስደንጋጭ
ወደሆነ ወገን ወደሚሰፍርና ወደሚረግጥ ወንዞችም ምድራቸውን ወደሚከፍሉት ሕዝብ
ሂዱ። በዓለም የምትኖሩ ሁሉና በምድር የምትቀመጡ ሆይ ምልክት በተራሮች ላይ
በተነሳ ጊዜ እዩ! መለከትም በተነፋ ጊዜ ስሙ!!!
እግዚአብሔር በፀሐይ ጮራ እንደ ደረቅ ትኩሳት በአጨዳም ወራት እንደ ጠል ደመና
ሆኜ በማደሪያዬ በጸጥታ ተቀምጬ እመለከታለሁ ብሎኛልና። እርሱ ከመከር በፊት
አበባ በረገፈ ጊዜ የወይኑን ፍሬ ጮርቃ ሲይዝ የወይኑን ዘንግ በማጭድ ይቆርጣል
ጫፎቹንም ይመለምላል ያስወግድማል። በተራራ ላይ ላሉ ነጣቂዎች ወፎች ለምድርም
አውሬዎች በአንድነት ይቀራሉ ነጣቂዎችም ወፎች ይባጁባቸዋል። የምድርም
አውሬዎች ሁሉ ይከርሙባቸዋል። በዚያን ዘመን ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር
ከረጅምና ለስላሳ ሕዝብ ከመጀመሪያው አስደንጋጭ ከሆነ ወገን ከሚሰፍርና ከሚረግጥ
ወንዞችም ምድራቸውን ከሚከፍሉት ሕዝብ ዘንድ እጅ መንሻ የሰራዊት ጌታ
የእግዚአብሔር ስም ወደሚገኝበት ሥፍራ ወደ ጽዮን ተራራ ይቀርባል። ትንቢተ
ኢሳይያስ ምእራፍ 18 በሙሉ

ቤተ ክርስቲያናችን / የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን/

ወገኖቼ! የተዋህዶ እምነታችን፤ ቤተ ክርስቲያናችን ዛሬ ምን ላይ ነች የሚለውን በመጠኑ እንመልከት።


ባጭሩ ቤተ ክርስቲያን የተዋህዶ ቤታችን በዘርፈ ብዙ ጥቃት ተመታ በታላቅ አደጋ ውስጥ ነች።
የሕይወት ቤት፣ የድንግል ቤት፤ ራሷ የሆነው የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት፣ የተዋህዶ
ሕዝበ ክርስቲያን ቤት ነበረች። ዛሬ ግን በውስጧ የመሸጉት እነተሃድሶ፣ እነፀጋ፤ እነቅባት እነመናፍቅ እግርና
እጇን ተብትበው መንጋውንም ለአውሬ ሰጥተዋል። ድንቋ ቤተ ክርስቲያናችን ዛሬ ሽባ ሆናለች። ወገኖቼ!
ቤተክርስቲያን የንግድ ማእከል፤ ፎቅ ሰሪ አከራይ ነጋዴ ሆናለች። አገልጋዮቿ በአብዛኛው እንደ አፍኒንና
ፊንሀስ ያሉ በመሆናቸው እርኩሰትን አንግሰዋል። የወፈረውን በግ አርደው በሊታ ሆነዋል የከሳውን ደግሞ
የሚወረውሩም ናቸው። ወገኖቼ በተጉ አባቶች ሰማዕትነት ተጋድሎ የፀናችው ቤተ ክርስቲያናችን የፖለቲካ
ሹመኛ መጫወቻ ሆናለች። የሚበዙቱ አባቶች በፍርሃት የተሸበቡ ለግዢው የተንበረከኩ ናቸው። ዘረኝነትን
የመንግሥት ሰላይነትን የለበሱ የከበረውን ቀሚስ ጥምጣም መስቀል ለመከለያ ጨብጠው አለሃፍረት የሰፈሩባት
ሆናለች። በቅዳሴአቸው በማህሌታቸው በወረባቸው በኪዳን ሁሉ ጌታን ሰቅለው የሚወጉ ሆነው ተገኝተዋል።
እግዚአብሔርን በከፍተኛ ደረጃ ለቁጣ ቀስቅሰዋል በቅናትም እንዲነሳ አድርገዋል።

ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ሁለት ፓትርያርክ አንግሳም አታውቅ። ነገር ግን ለፖለቲካው ለመንግሥት ድጋፍና
ሕልውና ሲባል የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ይጣሳል። ቤተ ክርስቲያናችን ለአገራችንም ለዓለምም ሚዛን ውኃ
ልክ ናት ። ሁሉም በሷ ልክ ይመዘናሉ። ዛሬ የአባቶቻችንን ድንበር ያፈረሱ ምንፍቅናን ያነገሱ የኮተለኩ፤

33
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

የድንግልን ክብር የቀነሱ፤ ጌታ የከፈለውን ውድ ዋጋ ያራከሱ እነዚህ ነጋዴዎች፤ ስለሆዳቸው ስለደሞዛቸው ብቻ


የሚገዳቸው፤ ቤተክርስቲያናችን አይታም ሰምታው በማታውቀው ጥፋት የጣሏት የዲያብሎስ የውስጥ አርበኞች
ፍርዳቸው ወጥቷል።
በቤተ ክርስቲያናችን ነፍሳቸውን አስጨንቀው ተገፍተው፤ አንገታቸውን ሰብረው፤ ለባለጊዜዎቹ ስፍራቸውን
ለቀው ለሚያዝኑት ለሚያለቅሱት ወገኖች ልዑል ድንግል ደርሰዋል። ፍርዳቸውንም እንደ ፀሐይ ያወጡታል።
በሕዳር ወር ውስጥ ለያዛችሁት ምህላ መልሱ ይኸው መልእክት መሆኑን እንድታስተውሉና መልስ ለሚጠብቀው
ከልዑል የተቆረጠውን እውነት ልትነግሩት ይገባችኋል።
በአሁኑ ሰዓት ቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ ሰማዕትነትን የተቀበሉ አገልጋዮቿን አፍልሳለች። በጅጅጋ ያለቁት
የተዋህዶ አርበኞች ከልዑል የሕይወት አክሊልን ተቀዳጅተዋል። ዛሬ ተዋህዶን የጠሉ መናፍቃን፤ ዋቄ
ፈታዎች፤ እስላሞች፣ ካቶሊኮች፣ ተብታቢ መተተኞች ባጠቃላይ በዚች በዘመን ሁሉ በፀና ተጋድሎት የገሃነም
ደጅ ያልቻሏት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችንን ለማጥፋት ብትደከሙም አሸንፋችኋለች። በእሷ ላይ የዘመታችሁ፤
የጠላችኋት ያሳደዳችኋት ያፈረሳችኋት ሁሉ በዚህ መልእክት የማረጋግጥላችሁ ፍፁም የእግዚአብሔር የድንግል
ጠላቶች ስለሆናችሁ በሙሉ ያለርህራሄ ከምድረ ገጽ ትጠረጋላችሁ ለእሳትም ትጣላላችሁ። ወደዳችሁም
ጠላችሁትም የተዋህዶ አርበኛ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምድርን ይወርሳሉ። ይነግሳሉ ዓለምን ይገዛሉ። ሁልህም
በምርኮ ለጀግኖቹ የተዋህዶ አርበኞች ተሰጥተሃል። እንዴት ይሆናል፤ እድሉ ካለህ ታየዋለህ። ከዚህም ውጪ
የሚሆን አለ ብለህ አታልመው። የዐመጽ ብድራትህን ትከፍላለህ። በድሃ ደም በቤተ ክርስቲያናችን በተዋህዶ
አርበኞቻችን ደም የጠመከውን ጠላ ትጋተዋለህ። ትደመደማለህ ትቀብራለህ።
ቤተ ክርስቲያናችን የተዋህዶ አርበኞች ቤትን ንቃችሁ በውስጧ የተሰገሰጋችሁ ተኩላዎች እንደኤሊ
አንገታችሁ ተጠምዝዞ ትወገዳላችሁ። ሌሎችም ዲያቆን ቄስ ካህን ጳጳስ ራሳችሁን ያሰማራችሁ በአፍኒንና
በፊንሀስ ጫማ የተገኛችሁ በሙሉ ታልቃላችሁ። የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን እንደጌታዋ
እንደመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብሩን በሥላሴና በድንግል በሊቃነ መላእከትም ኃይል አፍርሳ
ትነሳለች። በምድር ሁሉ ላይ ትነግሳለች። የእምነታችን መሪም ትሆናለች። የሚነግሱት ምድርንም የሚመሯት
የእግዚአብሔር አገልጋዮች አምጣ የወለደቻቸው ልዑል ባርኮ ያነገሰላት ልጆቿ ናቸው። ምድርን በልዑል ብርቱ
ክንድ ፀጥ እረጭ አድርገው በእውነትና ፍትህን በማንገስ የሚገዟትም ናቸው። ቤተክርስቲያንን እንደአይናቸው
ብሌን የሚጠብቋት የሚታዘዙላትም ናቸው።
ወገኖቼ! የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመላው ዓለም የእምነቱ መሪ ትሆናለች። ሌላ እምነት በምድር
ዳግም አይሰራም። ተዋህዷችን መንፈሳዊ አባትነቷ ምድርን ሁሉ ይከድናል። በበቁ አባቶች ትመራለች።
ትባረካለች። በሦስት ዓይን ትጠበቃለች።

1 ብርሃናዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ፦


መጪው የትንሳኤው ዘመን ከተወደደችው ኢትዮጵያ ተነስቶ አፍሪካን፤ መካከለኛው ምሥራቅን ጨምሮ
በመደበኛ ግዛትነት አካቶ የሚያበራ ልዑልም ድንግልም የሚነግሡበት የተራራዎች ሁሉ አናት ነው። በሕግጋተ
ሥላሴ የሚፀናው ብርሃናዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ዓለምን ሁሉ በበላይነት የሚገዛ የሚያስተዳድር ነው።
በተዋህዶ እምነታቸው የፀኑ በልዑልም በድንግልም የተመሰከረላቸው እረኞች ናቸው በመላው ምድር የልዑልን
ሕግ የሚዘረጉት። ለተዋህዶ እምነትም ዘብ ከሚቆሙት ሶስቱ አካላት አንዱም ነው።

34
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

2/ቤተ ክህነት ፦
ቤተ ክህነት በመጪው የትንሳኤው ዘመን እንደ አዲስ በአባቶቻችን መንገድ በፀናችው የተዋህዶ እምነታችን
የምትታነፅ ናት። በበቁ አባቶች፤ ዛሬም በውስጧ ሆነው ነገር ግን ፍፁም በዲያብሎስ ተረግጠው ያሉትን
አቅፋ፤ ከውስጧም ተገፍተው በውጪው /ከቅጥሯ ውጪ/ ሆነው ወድቀው በእንክርት በእሥራት በመራብ
በመሰደድ በጥቅሉ በታላቅ ጉዳት ውስጥ ሆነው ያሉትን ጨምራ ልዑል በሚያውቃቸው በቀባቸው ባፀደቃቸው
በወደዳቸው የክህነቱንም ሥልጣን በቅድስና ያለነቀፋና ሕፀፅ የጨበጡትን በመሪነት አስቀምጣ ዓለምን ሁሉ
የምትመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክህነት ናት። ወገኖቼ! ዛሬ የምታዩአት ቤተ እምነታችን
በዲያብሎስ በነገሱ የጨለማው እምነቶች ፍፁም ተመትታለች። ቀበሮ ተኩላ እባብ ጊንጥ ወርሷታል። ክብሯ
ተግስሶአል። ንግድ፤ ገንዘብ መውደድ፤ ትእቢት፤ ኑፋቄ፤ ራስን ማስመለክ፤ ምእመኑን ለአውሬ መስጠት፤
የገዢዎች መሳሪያ መሆን ይህን ሁሉ በሕይወታቸው ያነገሱ ተኩላዎችን ሹማና አንግሳለች። በከሃዲዎች
ተሞልታለች ስሟ እንጂ ከአገልጋዮቿ ሕይወት ያለው እምነት ጠፍቷል። ይህ ሁሉ ግን ቀደሞም አሁንም በዚሁ
ስምንተኛ መልእክት የሚረጋገጠው ተዋህዶ እንደገና በክብር በታላቅ ግርማ አምላኳን ድንግልን አንግሳ ተኩላና
ቀበሮውን ጠርጋ ትነሳለች። ተዋህዶ እምነታችንን በቀጥታ እንደ አይኗ ብሌን ትጠብቃለች ትመራለች።

3/ ቤተ ምርፋቅ /መማክርተ ካህናት ሲሆኑ የሁሉም የበላይ እራስ እግዚአብሔር


መንፈስ ቅዱስ ይሆናል። ከፍም ዝቅም የሚል ነገር የለም።
ቤተ ምርፋቅ ፡ – ቤተ ምርፋቅ ይህ አካል ራሱን ችሎ በቤተ ክህነቱም በመንግሥታዊ አስተደደር ተቋማት
ጎን ለጎን የሚቆም አካል ነው። ሥራው የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማዋን ቀኖናዋን ጠብቃ መጓዟን እለት
በእለት የሚከናወነውን ሥርአተ አምልኮውን በሕጉ በስርአቱ አለሕፀዕ መከናወኑን የሚከታተል አካል ነው።
ይህ አካል ከሁለም በላይ በበቁ አባቶች ሥላሴም ድንግልም በመሰከሩላቸው የሚዋቀር ነው። ሁሉም አባቶች
የክህነት ሥልጣናቸውን የጠበቁ የሚሆኑበትም ነው። በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ከፍታውን የጨበጡ
መሆንም የሚገባቸው ናቸው። በአባቶቻቸን አጠራር አራት ዓይናማዎቹ የሚባሉትን ማለት ነው። በመንፈሳዊው
እውቀቱ ብቻ ሳይሆን ለሥጋውም እውቀት ከሌላው የማይተናነስ አጠቃላይ እውቀት የጨበጡም ናቸው። በዚህ
አካል የሚመደቡ አባቶች እጅግ የከበሩ በመንግሥትም በቤተ ከህነትም የሚወደዱ የሚከበሩ የሚፈሩም ናቸው።
በሕዝብም እንዲሁ የሚወደዱም ናቸው። በሕግጋተ ሥላሴ በታወጀው ሥርዓተ አገዛዝ ውስጥ ሥልጣናቸውና
ኃላፊነታቸው የተገለፀና የሠፈረ ስለሆነ ከዚህ በላይ መግለፁ አስፈላጊ አይደለም። በጥቅሉ ሶስተኛው ዓይን
ናቸው። የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን በሦስት ዓይን ትጠበቃለች ተብሎ በጥቅሉ የተገለፀው ለዚህ ነው።
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፡– ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ኢትዮጵያ በሥላሴ በድንግል የተወደደችው
የነገሰችው – ኢትዮጵያ! ሕይወቷ የሆነችው ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን – የብርሃናዊው መንግሥት አገዛዝም
የሁሉም እራሳቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በመሆኑም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
የሁሉም –ዓለምን የሚመሩ የሚገዙ የልዑል የድንግል ባሮች መንግሥታት ንጉሳን ሁሉ መሪያቸው ዳኛቸው
አስተማሪያቸው ነው። ይህ ሁሉ በሥላሴ ኃይል ይፈፀም ዘንድ ተወስኗል። እንግዲህ ጠፊው ትውልድ ሩቅ
አልመህ ቅርብ ያደርከው ከሃዲ ከንቱ ትውልድ ብታምነውም ባታምነውም ሰምተኸውም ከሆነ ሰማኸው
እንጂ አታየውም። እንዳፌዝክ እንደተፈላሰፍክ እንደዘለፍክ ላንተም በዚሁ መልክ በብዙ እጥፍ ይሰፈርልሃል፡
በውርደት በከባድ ሰቆቃ ከምድረ ገጽ በአስጨናቂ መላእከ ሞት ትወሰዳለህ እጣህ ይህ ነው። የብርሃኑን ዓለም
አንተም ዘርህም በፍፁም አታዩትም።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች!!

35
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

በመልካሙ ዘመን አምልኮተ እግዚአብሔር በእውነትና በመንፈስ እንጂ በዘልማድና በስሜት አይሆንም።
አባቶቻችን የተዋህዶ እምነትን መሰረት ሲያሲዙ ሁለመናቸውን ሰውተው እንጂ እንደ ልማድ ሥራ በመሥራት
አልነበረም። እንዲሁም አንዴ ግለው በትንሽ ፈተና የሚቀዘቅዙ አልነበሩም። እምነታቸው እውነትን ማስመሰል
ሳይሆን መሆንን የለበሰ ነበር። በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተመሉ በልባቸውም በነፍሳቸውም በሃሳባቸውም
ፍፁም አምላካቸውን የወደዱ ነበሩና ሌትም ቀንም ፈጣሪያቸውንና ትእዛዙን በልቡናቸው የሚያመላልሱ ነበሩ።
ቅንነትን ትህትናን ቸርነትን እውነተኝነትን ደግነትን ወንድምን መውደድን መታመንን ቅድስናን የተላበሱ ነበሩ።
ሃሰትን ምንዝርናን አምልኮ ባእድን ጥንቆላን ተብታቢነትን እጅግ የሚጸየፉ ነበሩ። ዛሬ ትውልዱ እምነት
የሌለው ቀጣፊና አታላይ ዘረኛ ትውልድ በመሆኑ እንደ ስልጣኔው እንደ ህክምናው መራቀቅ እድሜን አላገኘም።
አባቶቻችን ከመቶው ዘለው እየኖሩ ኑሯቸውን እንደ እንግድነት ቆጠሩት እንጂ እንደዛሬው ትውልድ የዘለዓለም
ነዋሪ መስለው አላሰቡትም። እንደ አሁኑ ትውልድ መጠነ ብዙ የበሽታ ዓይነት አያውቁም ነበር። መቶን እድሜ
መድረስ ከዚያም አልፎ አለመኖር የመቀሰፍን ያህል ይቆጥሩት ነበር። የዛሬው ትውልድም/ ሁሉም የዓለም
ሕዝብ መቶ ዓመት ቀርቶ ሃምሳ ዓመትን ለመኖር የሰማይ ያህል እርቆታል። ወገኖቼ! ዛሬም ይህ የጠፋ
ትውልድ የኖኅን ዘመን የጥፋት ትውልዶች በብዙ በልጦና አሻሽሎ የተካ በመሆኑ የተቀደሰውን መልካም ቃል
ለውሾች አትጣሉ እንዳለው የልዑል መልእክትን ለከንቱዎቹ ሰጥታችሁ በፌዛቸው ባትቆስሉ መልካም ነው።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ፡ ይህን መልእክት በትእግስት በፅሞና እንደምታነቡ እርግጠኛ ነኝ! መልካም
መንፈስ ያለበት ሁሉ መልካምን ያውም ከልዑል የሆነውን ለማንበብ ጉጉቱ ከፍ ያለ እንጂ የታከተ ስሜት
የለውም።
እንግዲህ ወደአባቶቻቸን ልመለስ! – አዳም አባታችን የፈጣሪን ትእዛዝ ባይፈፅም ከሕይወት ተሻረ።
የማይጠፋ ሞትን አገኘ። ኖኅ የአምላክን ቃል ሰምቶ መርከቡን ቢሠራ ከዓለም ጥፋት አምልጦ ዘር አተረፈ።
መልከጼዴቅ የተባለው የኢትኤልና የሃሚራቢያ አባት የአዳምን ሞት አይቶ በሕይወቱ አምላኩን በፈጣሪው
የሕይወትንም ቃል በሚሰዋው መስዋእት መሰለው። ስለዚህ ስሙ የሰላም ንጉሥ የደህንነት ካህን ተባለ።
ልጁ ኢትኤል የአባቱን ምክር ተቀብሎ የፈጣሪውን ሕግና ትእዛዝ ቢያደርግ እንደአባቱም እንደ መልከጼዴቅ
የእግዚአብሔር ካህን ቢሆን አባትነትን አገኘ። ይህችን ምድር እርስትህ ብሎ ሰጠው። ከዘሩንም ጭን ታላቁን
የሕግ ንጉሠ–ነገሥት አፄን አስነሳለት።
እንግዲህ ልብ በሉ ወገኖቼ! አባቶቻችን ማን እንደነበሩ ቀደም ባለው ገጾች የሁለቱን ታላላቅ አፄዎች
ታሪክ ሰምተናል። በእውነትና በመንፈስ ልዑል በሙላት በፅናት በመታመን የፈለጉ፤ ሕዝቦቻቸውን በፈቃዱ
ሕግ /በሕገ ልቡና/ የገዙ የዓለምን ሁለት ሶስተኛ በሰላም ያስገዛላቸውም የምድራችን የሰላም አባት ተባሉ።
እግዚአብሔር በትንሹ ራሱን ቢገልፅላቸው እጅግ አብዝተው የወደዱት የፈለጉት በሕጉም የተደሰቱ የእምነት
ጀግኖች ነበሩ። ወገኖቼ በእውነትና በመንፈስ ማምለክ ሚስጥሩ ጥልቅ ነው። ከልብ ልዑልን ለሚፈልጉ ብቻ
ነው የሚገለጥላቸው። አባቶቻችን እንደፈለጉት ሁሉ ወደዳቸው እድሜን ክብርን አለበሳቸው። የታመነው ጌታ
/የአብርሀሙ ሥላሴ፣ የእኛ ሥላሴ/።
በእውነትና በመንፈስ ያመለኩት አባቶቻችን ዛሬ ከወደቀችውና የዲያብሎስ ውላጆች መራገጫ ከሆነችው
ኢትዮጵያ ተነስተው ነበር ዓለምን የገዙት የመሩት ያስገበሩት። እስኪ የትኛው የነጭ ዓለም ነው ይህን የመሰለ
በእውነትና በመንፈስ አምላኩን የፈለገና ያከበረ መንግሥት? የለም። የውሸት ድርሰት ሕይወት እንደማይሆን
ከአባቶቻቸው የዲያብሎስ አገልጋዮች የተቀበሉትን የጥፋት ምግባርና የክፋት አባትነት እያየን እዚህ ሰዓት
ደርሰናል። እነሱም ዛሬ ፍርዱ ሲገለጽ ከፊታቸው የቆመውን እድል ፈንታቸውን ሊቀበሉት ቆመዋል።
ወገኖቼ! ዛሬ የምናያቸው ነጮች የማያውቁትን ከአባቶቻቸው ያልተቀበሉትን መሰረት እንኳ ያላበጁላቸውን
ደርሰው የሃይማኖት መሪ! ኃያል መንግሥት፤ የዓለም ገዥ ሆነው የጨለማው መንፈስ ቢያነግሳቸውና አብረውትም

36
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ቢነግሱ ልዑልና ፍቃዱን የደመሰሱ መሰላቸው። ልብ በሉ ወገኖቼ ከአባቶቻችን ጀምሮ ከሕገ ልቡና እስከ
ወንጌሉ ድረስ በታላቅ ተጋድሎ የፀናችውን እምነታችንን ለማጥፋት ያልሄዱበት ጎዳና አለ ወይ? የለም። አዎን
አይካድም ጎድተውናል። ጥቂቶች የተዋህዶ ልጆች በልዑል ጥበቃ ለዘር ይትረፉ እንጂ የሚበዛውን አጥፍተዋል።
ዛሬ እዚህ መድረሳችንን አይደለም ማየት ብዙ የልዑል ልጆችን ገብረናል። ማን እራራላቸው? ማንስ
አዘነላቸው? በእውነትና በመንፈስ ማምለክ ዋጋ ቢያስከፍልም መንገዱ እሱ ብቻ ነው። በዚህ ንግግሬ መነሻነት
በእውነትና በመንፈስ ማምለክን በይበልጥ እንድትረዱት መንደርደሪያ ሃሳብ ይሆናችኋል ብዬ አስባለሁ።

ራስን ማስመለከና የውድቀት መንገዱ፤

ባሳለፍነው የጥፋት ዘመን ያሳለፍነው የአምልኮ ሁኔታችን እጅግ የጠፋ ነበር። በብዙ ንግግሬ እንደተረዳችሁት
ቀደምት አባቶቻችን አምልኮታቸው በእውነትና በመንፈስ ነበር። ራሳቸውን ዝቅ አድርገው አምላካቸውን
ያከብሩና ያስመልኩ ነበር።
ዛሬስ? ዛሬ ብዙ ጳጳሳት ካህናት ዲያቆናት አገልጋዮች ራሳቸውን የሚያስመልኩ ፡ የከበሬታ ወንበር
የሚፈልጉ ራሳቸውን ብቻ የሚያሰማሩ የወፈሩ በጎችን አርደው የሚበሉ የከሱትን የሚጠሉ የሚገፉ የሚያሳድዱ
ሆነው ተገኝተዋል። ያውም ክርስቲያን ነን ብለው ካባውን ያጠለቁ ናቸው። ፈጣሪ አምላካቸውን ከልባቸው
ክደው ሆዳቸውን አንግሰው ዲያብሎስን በልባቸው ተክለው የሥጋ ትርፋቸውን አምላክ አድርገው ይመላለሳሉ።
በአፋቸው ግን የከበረ ስሙን ለክፉ ሥራቸው ሁሉ መሸፈኛ ያደርጉታል።
ወገኖቼ እንደተዋህዶ ክርስቲያን የሥጋ ስብእናችንን ብቻ ገንብተን፤ ቤተ እምነታችን ያላስጨበጠችንን ክቡር
የእግዚአብሔር ቃል ያልተናገረንን በሕይወታችን እንግሰን እንዴት ክርስቲያን እንሆናለን : ራሳችንን ለተለያዩ
ክፋቶችና ሃጢያቶች ካስገዛን እንዴት የልዑል ልጆች እንሆናለን?
ራስን መውደድ! ለሥጋ ትርፍ ብቻ መድከም! መናቅ ትእቢት ማን አለብኝነት ጭካኔ ውሸታምነት ዘራፊነት
እግዚአብሔርን አለመፍራት አንግሰን የምንመላለስ ከሆነ ራሳችንና የለበስነውን ሥጋ አመለክን እንጂ ለልዑል
አይደለም ራሳችንን ያስገዛነው።
ስለእምነት ስናነሳ እጅግ ወሳኝ የሆነውን ርእስ ማየታችን ስለሚሆን በመጠኑ ዳስሼ አልፌዋለሁ። ምክንያቱም
በዚህ ጠባብ ሥፍራ ለትምህርት የታሰበ አይደለም መልእክት ለማድረስ ብቻ እንጂ!
ስለእምነት በልዑል ቃል በእብራውያን በምእራፍ 11 የተገለፀውን በሙሉ አንብቡት።
የተዋህዶ አርበኞች የእግዚአብሔር ሕዝቦች!!

እነሆ እግዚአብሔር የሚገሥፀው ሰው ምስጉን ነው፤ ስለዚህ ሁሉን የሚችለውን


የአምላክህን ተግሳጽ አትናቅ! እርሱ ይሰብራል ይጠግንማል፤ ያቆስላል እጆቹም
ይፈውሳሉ ፡ በስድስት ክፉ ነገር ውስጥ ያድንሃል፤ በሰባትም ውስጥ ክፋት አትነካህም
፡ በራብ ጊዜ ከሞት ፡ በሰልፍም ከሰይፍ እጅ ያድንሃል ፡ ከምላስ ጅራፍ ትፈወሳለህ
፡ ጥፋትም ሲመጣ አትፈራም! በጥፋትና በራብ ላይ ትስቃለህ ፡ ከምድረበዳ
ከአራዊትም አትፈራም ፡ ቃል ኪዳንህ ከምድረ በዳ ድንጋይ ጋር ይሆናል፤ የምድረ
በዳም አራዊት ከአንተ ጋር ይስማማሉና፤ ድንኳንህም በሰላም እንዲሆን ታውቃለህ ፡
በረትህን ትጎበኛለህ አንዳችም አይጎድልብህም ዘርህም ታላቅ እንዲሆን፤ ትውልድህም
እንደ ምድር ሳር እንዲሆን ታውቃለህ፤ በወራቱ የእህል ነዶ ወደ አውድማ እንዲገባ፤
በረጅም እድሜ ወደ መቃብር ትገባለህ። እነሆ ይህችን መርምረን የሰማነውም ይህ
ነው። ይላል የልዑል ቃል።
መጽሐፈ ኢዮብ ምእራፍ 5 ፡ 17 –27
37
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወገኖቼ የእግዚአብሔር ምርጦች አይዟችሁ! እንባችሁ ይታበሳል፤ ቁስላችሁ ይፈወሳል፤ ያለአባት ያለእናት
አይደላችሁም። የሰፈራችሁትን መከራ፤ ያለፋችሁበትን የጨለማ ዓለም፤ ዲያብሎስ ያደረሰባችሁን እስር እንግልት
ማሳደድ ርሃብ ስቃይ ውርደት ሁሉም በልዑል ፊት በድንግል ፊት በቁጭት ታስበዋል። ብድራቱን ይከፍላሉ፤
የሆነው ሁሉ ለእናንተ ለበጎ ነው። አባታችሁም እናታችሁም ሁለቱም አሁን ደርሰዋል። ከአጠገባችሁም ናቸው።
እንደ ጥጃ የምትቦርቁበት ዘመን እነሆ ከፊታችሁ ነው። ሁለመናችሁ ይፈወሳል። ስለእናንተ ቅዱሳን መላእክት
ሁሉ ይተጋሉ።
የጠላቶቻችሁን ጥፋት በመልካም ሥፍራ ሆናችሁ ትመለከታላችሁ። ብድራታቸውን በሰፈሩት አስር እጥፍ
ሊሰፈርላቸው ነውና ታያላችሁ። ምድሪቱንም ትወርሳላችሁ። ከምርኮውም ፍፁም ትጠግባላችሁ። ቀኑም ሌቱም፤
ምድሪቱም ማህፀኗም ስለእናንተ ያላቸውን ሁሉ ይሰጣሉ። የተወደዳችሁ በእሳት የተፈተናችሁ እንቁ የልዑል
ልጆች ናቸሁ ፡ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ አርበኞች እንዲሁም ባላችሁበት ባእታችሁ በቅንነታችሁ፣ በየዋህነታችሁ፣
እግዚአብሔርን በመፈለጋችሁ የታጎዳችሁ ሁሉ ዛሬ ታስባችኋል። አትፍሩ አትደንግጡ።።
ወገኖቼ ይህንን ለእናንተ እናገር ዘንድ በዋናነት የታዘዝኩበት ነው። ከእንግዲህ አትፍሩ አትደንግጡ ያለፈው
መከራ ትውስታው አያስበርግጋችሁ። ሁላችንም ከየወደቅንበት ከታሰርንበት እንፈታለን እንነሳለን። ልዑል፣
ድንግል፣ ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት የጠላትን ምሽግ የትምከህታቸውን ክምር የጥፋት እጃቸውን እርዝመት
ሊቆራርጡት ሊያጠፉት ሊደመስሱት በጠላቶቻችን አናት ላይ ቆመዋል። ለአንዴም ለሁሌም ወደገሃነማቸው
ይወርዳሉ። ምን ልበላችሁ ወገኖቼ፣ ወንድም እህቶቼ፣ አባት እናቶቼ፣ እንዲሁም ልጆቼ፤ ድንቅ ናቸሁ።
ለእናንተ ልዑል ያዘጋጀላችሁን ድንግል ያሰናዳችውን ብትመለከቱት ይህ ሁሉ ለእኔ፤ ማን ስለሆንኩ ምንስ
ያህል ፈጣሪም ድንግልም ቢወዱኝ ነው ብላችሁ ከመደመማችሁ የተነሳ የደስታ እምባችሁ የማትገቱት እንዲሆን
ልግለፅላችሁ እወዳለሁ።
የዛሬው የጠፉ ትውልዶች በተለይም ወጣቶች፤ ተምረዋል የሚባሉ ምሁሮች፤ አገር እንመራለን ብለው
በሥልጣኑ ዙሪያ የተኮለኮሉ ሰዎች፣ ጠመንጃ የጨበጡ የተለያዩ ኃይሎች ሁሉንም ስናያቸው በምን ጎዳና ላይ
ናቸው፤ ምንስ ጥፋት ውስጥ ወድቀዋል ስንል ብናነሳው እጅግ ብዙ ነው።
ዛሬ ምንዝርና፣ ሌብነት፣ ዘረኝት፤ ውሸት፣ አምልኮ ባእድ፣ ሱሰኝነት፤ ጫት ቃሚነት፣ ሰካራምነት
ጨካኝነት፣ ክህደት ፡ ትእቢተኝት፣ ነፍሰ ገዳይነት፣ ሰነፍነት፣ ተብታቢነት፤ አታላይነት፣ የአብዛኛው ትውልድ
መገለጫ ሆኗል።
እውነት እምነት ጠፍቶ በምትኩ የውሸት እምነት ነግሷል። በአገራችን የነገሱት ዘረኝነት በራሱም በመንግሥት
ተብዬው በመሆኑ አንዱ አንዱን እንዲጠላና በጠላትነት እንዲተያይ ተደርጓል። እስልምና ምንፍቅና ኩትልክና
ዋቄ ፈታ ጣኦት አምላኪ፣ ተብታቢ፣ መተተኛ፣ ጠንቋይ አስጠንቋይ፣ ውቃቢ የመሳሰሉ ትወልዱን ይዘውት
የጠፉ ሆነዋል።
ዛሬ በምናየው መንግሥታዊ አርቴፊሻል ለውጥ የሚመጣ አንዳች ነገር የለም። እግዚአብሔር ያለው ቀድሞም
የተናገረው ፍርዱንም ያሳወቀው ኢትዮጵያ ወደትንሳኤው እንድትሻገር ነው። አብሯት የሚሻገሩትም ዛሬ
በእምነቱ ስም የሚነግዱትን ቀጣፊዎችን ተኩላዎችን አይደለም። ራሱ ኮትኩቶ ደክሞ በእሳት አንጥሮ ተሸክሞ
በማእበሉ ሁሉ ያሳለፋቸውን አገልጋይ ባሮቹን እንጂ!
ወገኖቼ!! ልትረዱት ይገባል፤ ልታደምጡም፤ ልትዘጋጁም ይገባችኋል። የምድሪቱ ወራሾች የክብሩ ቀዳሽ
አወዳሾች እናንተ የልዑል ማሕተም ያረፈባችሁ ናችሁ።
ቤተ ክርስቲያናችን የተዋህዶ ቤታችን እግዚአብሔር በወደዳቸው በአከበራቸው ባፀደቃቸው ልጆቹ እንደገና
የውርደትና የጥፋት ካባዋን አውልቃ እንደ አዲስ ትነሳለች እንጂ!! ሌባ ተኩላ የበግ ለምድ ለብሶ ሁሌም

38
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

የሚፈነጭባት አትሆንም። አመጽን፤ ማፍረስን በቤተ እግዚአብሔር /በተዋህዶ/ ላይ ሲፈጽም ሲያስፈጽም የነበረ
የአገርም የውጪም ጠላት ሁሉ ለአንዴም ለሁሌም እንዳይነሳ ሆኖ በእሳት ባሕር ይከደናል።
የተዋህዶ አርበኞች ከዚህ በታች ያሰፈርኩት ሁሌም የምትሰሙት ምሳሌ ነውና እንደልዑል ታማኝ አገልጋይ
ሊቀ መላእክት ገብርኤል ፀንተን እንቁም!
በአንድ ወቅት ልዑል ቅዱሳን መላእክትን ፅናት ይመለከት ዘንድ በዙሪያው ካሉ ሊቃነ መላእከቶች ራሱን
ሰወረ። በወቅቱ ከከበሩት መላእክትም በክብሩም በሥልጣኑም ከልዑል ቀጥሎ ይታይ የነበረው ሳጥናኤል ነበር።
ልዑል ራሱን ሲሰውር ሁሉም ተደናገጡ ፈጣሪያችን ማነው ወዴትስ ሄደ ብለው ታወኩ። ሳጥናኤል ቀድሞም
በልቡ ሥልጣንን እነጥቃለሁ ብሎ ሃሳብ በልቡናው ያሳደረ በመሆኑ፤ ከመላእክቱም በከፍታ ያለ በመሆኑ
መልስ ሰጪ ሆኖ በመቅረብ እኔ ነኝ አምላካችሁ ብሎ መለሰላቸው። በዚህ ወቅት ከከበሩት መላእክት አንዱ
የሆነው ገብርኤል የሳጥናኤልን ድርጊት በመቃወም እሱን አትስሙት እሱም እኛም የእግዚአብሔር ፍጡሮች
ነን፤ ስለዚህ አምላካችን ተገልጦ እስከሚረከበን ድረስ ባለንበት ፀንተን እንቁም አላቸው። ብዙም ሳይቆይ
ልዑል ራሱን ገለጠላቸው። ሳጥናኤልና የተከተሉት ተፈረደባቸው። ተዋጉም ለውርደት ለጥፋት ለፍርድ
ለሰው ልጅ ፈተና ይሆኑ ዘንድ ወደምድር ተጣሉ። ዛሬ እንደምናየው የሰውን ዘር በሙሉ ለማለት በሚያስችል
ቁጥር በቁጥጥራቸው ሥር አድርገው የፈቃዳቸው ተገዢ አድርገውታል። ዛሬም ለመጣው ፍርድና ቅጣት
ማረፊያ እንዲሆን አድርገውታል። በጊዜውም አለጊዜውም እንደ ሊቀመላእክት ቅዱስ ገብርኤል ፀንቶ መቆም
ለእግዚአብሔር ሕዝቦች ሁሉ የምሰነዝረው ምክር ነው። እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ስንደክም ኃይለኞች ነን።
በድካማችን የልዑል ጥበብ ነውና አምላካችን ሥራው ይበረታል።

በዚያን ጊዜም የእውሮች ዐይን ይገለጣል የደንቆሮችም ጆሮ ይከፈታል በዚያን ጊዜ


አንካሳ እንደ ሚዳቋ ይዘልላል፤ የዲዳም ምላስ ይዘምራል፤ በምድረበዳ ውኃ በበረሃም
ፈሳሽ ይፈልቃልና፤ ደረቂቱ ምድር ኩሬ የጥማት መሬት የውኃ ምንጭ ትሆናለች። ቀበሮ
የተኛበት መኖሪያ ልምላሜና ሸንበቆ ደንገልም ይሆንበታል። በዚያም ጎዳና መንገድ
ይሆናል። እርሱም የተቀደሰ መንገድ ይባላል። ንፁሃንም ያልሆኑ አያልፉበትም፤
አንበሳም አይኖርበትም ነጣቂ አውሬም አይወጣበትም ከዚያም አይገኙም የዳኑት
ግን በዚያ ይሄዳሉ፤ እግዚአብሔር የተቤዣቸው ይመለሳሉ፤ እየዘመሩም ወደ ፅዮን
ይመጣሉ፤ የዘለዓለም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል። ሐሤትንና ደስታን ያገኛሉ።
ሃዘንና ትካዜ ይሸሻሉ።
ትንቢተ ኢሳይያስ ፡ 35 ፡5–10
ወገኔ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚጠብቅህ ከላይ ያየኸው ቃል ነው።
ስማ! የአዳም ዘር አድምጥ! ልብ ብለህ አድምጥ! ላንዴም ለመጨረሻ ጆሮህን ከፍተህ አድምጥ!
የሠራዊት ሁሉ ጌታ! የፍጥረት ሁሉ ጌታ! የነበረው ያለው አልፋና ኦሜጋ የሆነው የሰማዩም የምድሩም
ጌታ! የሌለውን እንዲኖር ሕልው የሚያደርግ! ያለውን ወደሌለነት የሚለውጥ! ከነበረ ወደአልነበረ፤ ከአልነበረ
ወደነበረ የሚለውጥ ሁሉን ቻይ አምሳያም አኳያም የሌለው ሁሉም በእጁ የሆነ ኃያል ጌታ!! መጣሁብህ
ይልሃል!!
በቁጣው የነደደው ልዑል!! እንደእቶን እሳት በታላቅ ቁጣ እየጤሰ ያለው የሰራዊት ጌታ ደረስኩ ይልሃል!!
እንግዲህ ወገብህን ታጥቀህ ጠብቀኝ ፡ እኔው ፈጥሬሃለሁ፤ እኔው አኑሬሃለሁ ከነከረፋው ምድርንም ሰማይን
ካጠነባው ኃጢአትህ ጋር መሽከሜ አንሶ እኔኑ ወጋህ! ስለሰው ያፈሰስኩትን ደሜን ረጋገጥህ! በደሜ ተንቦጫረቅህ!
የተወጋው ጎኔን፤ የተቸነከረው እጅና እግሬን መልሰህ ወጋህ! ከከፉት አይሁዶችም በላይ ሆንክ! በብዙ እጥፍም
በለጥህ! እኔው በፈጠርኩት ነገር ግን እኔን ሊዋጋ እኔንም ሊወርስ ያላፈረውን፤ ለታላቁ ቁጣዬና ፍርዴ

39
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

የጣልኩትን የቀደመውን እባብ ዲያብሎስን እነገስህ አከበርህ አመንክ ታመንክበት ያዘዘህን ሁሉ ፈፃሚ ሆንክ!
በፍፁም ልብህ የሰራሁህን የወደድኩህን የሞትኩልህን የፍቅር እጄን የዘረጋሁልህን የክብሬ ወራሽ የስሜ አወዳሽ
ቀዳሽ ያልኩህን አንተን ካድከኝ! ፍፁም ጠላኸኝ ዘመትክብኝ በታላቁ ቅናቴም አነደድከኝ ከፍጥረት መጀመሪያ
ጀምሮ ባለተከሰተ ትእቢትህ ክህደትህ ፌዝህ ንቀትህ እስከዛሬም ያልታየውን የቅናት ቁጣዬን አነደድከው!!
እንግዲህ ሁሉን አዘጋጅተህ የለ? /ሚሳየሉ ጀቱ ኒኩለሩ፤ የጦር መርከቡ ጠመንጃው ታንኩ፤ ኬሚካሉ አጥቂ
ሳተላይቱ ምንም የቀረህ የለም ጧትም ማታም እሱኑ ስታመርት ትወላለህ ታድራለህ! ልትዋጋ ተለማምደሃል
ተዘጋጅተሃል / ወገብህን ትጥቅህን አጥብቀህ ጠብቀኝ!! የምጠርግህ የምባላው እሳት በቅናቴ ቁጣ እንደጢስ
የማተንህ የሰራዊት ሁሉ ጌታ መጣሁብህ!! ይላል እግዚአብሔር መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ!!
ተመልከት ወገኔ! እንግዲህ አደመጥከው አይደል፤ መጣ ኃያሉ ጌታ፤ እኛን ስትፈጭ ስትቆላ፤ ነበርክ፤
ማንም ያልመከተህ ነበርክ፤ መግቢያ መውጫ ያሳጣኸን እንልሰው እንቀምሰው ያሳጣኸን በገዛ አባታችን
ንብረት ሀብት አንተ አዛዥ ናዛዥ እኛ እስረኞችህ ዘወትር መጫወቻህ ነበርን። ውርደትን መናቅን ማሰደድ
መንከራተትን መሞት መታሰርን መቀጥቀጥን እንደዘወትር ቀለብ የሰፈርክልን የልዑል ባሮች /ልጆች/ እኛ
ነበርን። ዛሬ የሰፈርከውን በትእቢትህ በንቀትህ በማንአለብኝነት የዘራኸውን ሊያሳጭድህ ሊያስቅምህ፣ አስር
እጥፍ ብድራትህን ሊከፍልህ መጣለህ! ያውም በሙላት! እንደብርቱ ማዕበልና እንደሚንተከተክ እሳተገሞራ
እንደሚገተለተለው ጭስ ጢሶ መጣብህ!! ምን ይባላል ተቀብለው!! ስለእናንተ በእውነት እኔንም አስጨነቀኝ።
መፍቻ የሌለው ጉዳይ!!
ይህ ስምንተኛ መልእክት የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሊያፀና እንደወጣ ሁሉ የመጨረሻው ሰዓት ላይ በመደረሱ
ለተሰናባቹ የጠፋ ትውልድ የሚፈስበትን የእሳት ማዕበል ሰይፍ እንዲያውቀው ለማድረግም ነው። ኢላማቸውንም
ለማሳወቅ ነው። የመነሻ ጊዜአቸውንም የሚገለፅበት ነው። አሁን ያለው ጅማሮ የአገራችንም ሆነ የዓለም ጥፋት
ብዙም ትርጉም ያለው አይደለም። ከተዘጋጀልህ ብርቱና ህሊና ከሚሸከመው በላይ የሆነ ጠረጋ እስከ አሁን
ያየኸው ኢምንት ነው። እንዲያውም ሰላም ነው የሚያስብል ነው። ከላይ ሰማኸው አይደል! ቃል በቃል ነው
የልዑልን ታላቅ ቁጣ ያሰፈርኩልህ።
ወገኖቼ! ቁጣው በሙሉ ኃይሉ መፍሰስ ከጀመረ፤ የሚያስቆመው ምንም ኃይል አይኖርም በአንድ ነገር ብቻ
ሊቀንስ ወይም ሊጨምር ይችላል። ልዑል እንዳሰበው፤
ሀ/በመጀመሪያ በኢትዮጵያና በዙሪያዋ ባሉ ሀገሮች ሁሉ ላይ የቀባቸው የመረጣቸው የአከበራቸው ታማኝ
አገልጋዮቹ መንበረ ሥልጣኑን መጨበጥ አለባቸው። ያውም ተለምነው ደጅ ተጠንተው በብዙ እንባና ጩኸት
ተወትውተው፤ ይሁንታንም ከልዑል ተቀብለው (ከድንግልም ተባርከው ሲረከቡና እነሱም ለቀረው ሕዝብ
ከታላቁ ቁጣ ላመለጠው ሕዝበ ክርስቲያን የልዑል ቁጣ እንዲበርድ ልመናና ምልጃ ሲያቀርቡ ብቻ፤ ያኔ
የአንደኛው ሰይፍ /የልዑል ሰይፍ/ ከእርምጃው መቀዝቀዝ ይጀምራል ይቆማል አላልኩም ከከፍታው ወደዝቅታው
እንደሁኔታው ይቀንሳል። ይህም ማለት አበቃ ማለት አይደለም ሁለተኛው ሰይፍ ይጀምራል። ይህ ሰይፍ
የታመኑት አገልጋዮቹ ሰይፍ ሲሆን በመላው ዓለም የልዑል አገዛዝ እስኪሰፍን ድረስ እርምጃው የሚቀጥል
ይሆናል። እግዚአብሔር ባሮቹን በኃይል ያስታጥቃል። የዚህን ዘመን ጥበብ እውቀት የዲያብሎስን የዘመናት
ዝግጅት ሁለት ሶስተኛውን እጅ በልዑል ቀጥተኛ እርምጃ ይደመሰሳል። ቀሪውን አንድ አራተኛ ለባሮቹ የሚተው
የማጽዳት እርምጃ ነው። የልዑል ባሮች ዓለም ላይ ሁሉ ከልዑል ዘንድ በይሁንታው ያፀደቀውን ሕግጋተ ሥላሴ
አፅንተው ብርሃናዊ አገዛዛቸው ሲሰፍን ያኔ ብቻ ነው የልዑል የቁጣ እጆች ወደሰገባቸው የሚመለሱት። በምትኩ
የምሕረት የበረከት የፍቅር የደስታ የብልፅግና የጤና የረጅም እድሜ በረከቶቹ ሁሉ መፍሰስ የሚጀምሩት።
ለምሕረት ያስቀራቸውን የወደዳቸውን ያከበራቸውን የሚጠግንበት የሚያስደስትበት የሚያከብርበት ወቅት
ይሆናል። በፍቅር እንባቸው ከልብ በመነጨ ምስጋናቸው በፊቱ በደስታ ይቀርባሉና ምስጋናቸው ለልዑልም
ለድንግልም ለሊቃነ መላእክትም ለቅዱሳንም ለሰማዕታት ሐዋሪያት ነቢያትም እንደማያቋርጥ ጅረት ይፈሳል።
40
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

እሱም እናታችን ድንግልም በረከታቸውን ያለማቋረጥ በልጆቻቸው ላይ ያፈሱታል። እውነቱ ይህ ብቻ ነው።


ፈላስፎችህም ስለቤተክርስቲያናችን እንቶ ፈንቶ የአሮጊቶችን ተረት መሰል እየፃፉ ቢያደነቁሩህም ራሳቸው
ለሠሩት አመፅ ብርቱ እዳ ከፋይ ናቸው።
ወገኖቼ!! ከዚህ በታች የሚሰፍረው የቅጣት ዓይነትና ምንነት ሲሆን እንደበፊቱ መልእክቶች አገላለፅ ጥቅል
ትእዛዝ ሳይሆን፤ የአሁኑ ብርቱ የቅጣት ትእዛዝ በመሆኑ በየደረጃው የሚከናወነውን የሚገልፅ ምንስ ውጤት
እንዲመጣ እንደሚፈለግም የሚያረጋግጥ ነው። ቅጣቱ የሚያርፍባቸው እንደግለሰብ፤ እንደመሪ፣ እንደ ቡድን፣
እንደማህበረሰብ፣ እንደድርጅት፣ እንደ ተቋማት፣ እንደጎሳ፣ እንደብሄር እንደ ሕዝብ፣ እንደአገር፣ እንደአሕጉር
በጥቅሉ ሁሉም በምድራችን ላይ ያለ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ሰብአዊ ፍጡር ሁሉ በመጪው ቁጣ
የሚጎበኝ ነው። ለምሕረት የታሰበ ቀድሞም የተመረጠ በግንባሩም ምልክት የተደረገበት ብቻ ነፃና አንዳች
የሚነካው የሌለ ሲሆን እንዲሁም በየትኛውም አገር ውስጥ ያለ የዋህ ቅን ደግ እግዚአብሔር በወሰነው መሰረት
የሚሰበሰብበት የሚታረምበት በቅጣት የሚመለስበት እርምጃም ይወሰዳል። ከእንግዲህ ዓለማችን አሁን ባለችበት
የጨለማ ሕይወት፤ የዲያብሎስ የንግሥና ዘመናት አትቀጥልም። እሱም ለሺዎች ዘመናት የዘራው የአመጽ፣
የጥፋት፣ የኃጢአት አዝመራውም ከነአለቃና ምንዝሮቹ፤ በመልከ ብዙ ቅርጽ ምድሪቱን ከከድኑት ሕዝቦቹ ጋር
በእሳት ማዕበል ይጠረጋል።
ወገኖቼ!! ከዚህ በታች የምታነቡት ኢላማውን ያወቀ የተረጋገጠ እርምጃ ሲሆን፤ ልዑል ከዚህ በታች
በተዘረዘሩት ሁሉ ላይ በየደረጃው የሚፈፀም ብርቱ ያልታየ እርምጃ ይወስዳል። ይህም ቀድሞ ተወስኗል።
በቀደሙት መልእክቶች የታዘዙት 1ኛ ደረጃ፣ 2ኛ ደረጃ ቅጣቶች ከእርምጃ የሚታቀቡበት ምክንያት በሙሉ
ስላከተመ በሙሉ ኃይላቸው ይፈሳሉ። በመጨረሻ ገጽ ላይ እንደሚገለፀው ከዚህ መልእክት መውጣት በኋላ
የቅጣቶቹ መለቀቂያ ይገለፃል።

በአገራችን በኢትዮጵያና በዓለምም የሚወሰድ ቀዳሚ እርምጃና ብርቱ የቅጣት


ትእዛዞች!!!

ዛሬ ስለቅጣት በምናነሳበት ጊዜ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ለምን የሚለውንም እየመለሰ ሲገለጽ ኖሯል።


በመልእክት 3 /የአፈፃፀም መልእክት/ እንደተገለፀው ኢትዮጵያም ዓለምም በአንደኛ ደረጃ የቅጣት ወንፊት
እንደምትበጠር ያረጋግጣል። በዚህ እርምጃ ውጤት ስላልተገኘ በመልእክት አምስት ቅጣቱ ሁሉ ወደ 2ኛ
ደረጃ ማደጉን በቅጣቱ ዝርዝር የሚካተቱ አገሮችን የእምነት ተቋሞችን፤ በአጠቃላይ መላውን የዓለም ሕዝብ
እንዴት እንደሚዳኝና በቅጣቱ እንደሚጠረግ ይህም በልዑል መወሰኑና በዝርዝር መታዘዙን አረጋግጦ ገልፆአል።
1ኛ ደረጃ ቅጣቱ ከ9 ዓመት በላይ ቢያስቆጥርም እንደገናም ለ7 ዓመት 2ኛ ደረጃ ቅጣቱም ትእዛዙም ወጥቶ
ቢቆይም ልዑል በትእግሥት እንደተገለፀው ወዲያው እርምጃውን ከመውሰድ ለንስሓ ጊዜ በመስጠት እንዲመለሱ
የታሰቡትን በመጠበቅ አሳልፎታል። ዛሬ ላይ ሆነን ግን ውጤቱን እኛ ባናውቀውም ልዑል ያውቀዋል። የሆነ
ሆኖ ጊዜም ቢሰጥ የሰው ልጅ በተሰጠው ጊዜ ከመጠቀም ይልቅ ከድጡ ወደማጡ እንደሚባል የትላንቱን
የኃጢአት ምርቱን በብርቱ ጨመረው አዘመነው ከድብቅነት ወደፍፁም ግልፅነት አወጣው እንጂ አተመለሰም።
ዛሬ መልእክቱ 13 ዓመት ቢያስቆጥርም እንዲያውም እድሜ ሲሰጥ መልእክቱን እንደ ውሸት ቆጠሩት እንጂ
ማንም ትዝም አላለው። በዚህ የተጎዱት ደግሞ ልዑልን ድንግልን ተስፋ ያደረጉና የቅን ፍርዱን መፈጸም
ይጠብቁ የነበሩት ናቸው። እኔም መልእክት አድራሹ ከነቤተሰቤ መልእክቱ ከመውጣቱ ከ13 ዓመት በፊት
ከደረሰብን የጠላት ውጊያ ይልቅ ከ3 ዓመት ወዲህ የደረሰው መከራ ብርቱ ነው። ይህ ደግሞ በሁሉም ወንድም
እህቶቼ ላይ የደረሰም ነው።

41
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ወገኖቼ የእግዚአብሔር ህዝቦች የአዳም ዘሮች!!


ሁሉም በብርቱ ፈተና ላይ እንዳለ ማንም የማይክደው ነው። በመልእክቶቹ አወጣጥ አፈፃፀም ደርሶት
ያነበበው ሁሉ የየራሱን አቋም በመውሰድ በዚያ አቋሙም ሂዶበታል። የናቀው ንቋል፤ ያላመነበት ሳያምንበት
ቀርቶአል። የታመነበት ታምኖበታል በእውነትነቱም ተቀብሎታል። የተዋጋው ሁሉንም መሰናከል በመጠቀም
ስርጭቱን ከመገደብ አንስቶ ይዘው የተገኙትንም እስከማጥቃት ሄዶበታል። በስውር ብዙ ጥፋት ተፈፅሟል።
ዛሬ በዚህ ስምንተኛ መልእክት እንደምትረዱት ቅጣቶች ሁሉ አሰላለፋቸውን በ3 ደረጃ የሚገለፅና የሚፈፀም
እንዲሆን ተደርጓል።
1ኛ/ በደረጃ አንድ የተመደቡ ቅጣቶች በመልእክት 3 እንደተገለፀው እየተከናወኑ ያሉ ሲሆን፤ ዓለምም
አገራችንም በዚሁ ወንፊት እየተበጠሩ ለመሆናቸው ሁሉም የሚያስተውለው ሀቅ ነው። ከማጥፋት ይልቅ ቀጥቶ
ለመመለስ እንዲያግዝ ተደርጎ እየተከናወነ ያለው ይህ የእሳት ወንፊት ዓለምንም ኢትዮጵያንም በሁሉም ዘርፍ
ተሰማርቶ እያበጠረ ይገኛል። ውጤቱ ሁላችንም የምናየው ነው። ከአመፅ ምንም የተመለሰ የለም እንዲያውም
በብዙ እጥፍ አድጎ ተስፋፍቶ ዘምኖ በሁሉም የምድር ገጽ ነግሶ ለበለጠ ጥፋት በመግስገስ ላይ ይገኛል። የዓለሙ
ኃጢአትና አመፅ ከሰው አእምሮ ከሚገምተው በላይ ሆኗል። የአገራችን ደግሞ ከዚህ ቀደም የወጡት መልእክቶች
በሙሉ ቢታወቁም በጣት ከሚቆጠሩ በቀር ሁሉም በሚያስብል ሁኔታ በሁሉም ዘርፍ አመፁን፣ ኃጢያቱን
አዘምነው ቀጥለውበታል። በመሆኑም የመጀመሪያው የቅጣት ወንፊት እንዳለ ሆኖ በስፋትም በጥልቀትም
ሁሉንም በአገሪቱ ያለውን ምልክት አልባ መጥረጉን ይቀጥላል። በዓለምም እንዲሁ የመጀመሪያው ወንፊት
እንዳለ ሆኖ ተጠናክሮ ይቀጥላል 2ኛ ደረጃ፣ 3ኛ ደረጃ ከሚባለው ቀጣይ ከሚዘረዘሩት ጋር ተጣምሮ እርምጃው
ይቀጥላል እንጂ አንዱ አንዱን ተክቶ አይቋረጥም።
2ኛ/ በደረጃ አንድ ያሉት ቅጣቶች እንዳሉ ሆነው: ይህ ሁለተኛ ደረጃ ቅጣት በመልእክት አምስት በሚገባ
የተዘረዘረና ሁሉንም የዓለም ገጽታ ያካተተ በመሆኑ ከደረጃ አንድ ቅጣት ጋር በመጣመር ጉልበቱን በተገለፀው
2ኛ ደረጃ በማሳደግ የሚቀጥል ሲሆን የማያቋርጥም ይሆናል። እስካሁንም ተገትቶ የቆየው ልዑል አምላካችን፤
ድንግል እናታችን አዝነው ምናልባት የሚፀፀት ንስሓም የሚገባ ይኖር እንደሁ በሚል ነበር። ነገር ግን
ጊዜውን የተሰጠውን እድል ከመጠቀምና ከመመለስ ይልቅ፤ ይበልጥ አመፁን ክፋቱም በመጨመር ትእቢቱንም
ግፉንም በብርቱ በማስፋት የማይደፈረውን በመድፈር /እንደዋልድባ ገዳም የመሳሰለውን/ ቀጥለውበት ይገኛል።
መልእክቱንም የቅዠታም ወሬ ነው በማለት አጣጥለውታል። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስንም ሰድበዋል
አራክሰዋል። በመሆኑም ፍርዳቸው አንዳይሻር በራሳቸው አድርገዋል። ስለዚህ በራሳቸው ጥረት ያመጡት እሳት
በመልእክት አምስት የተጠቀሰው ሁሉ በመጨረሻው ገጽ ከሚገለፀው ቀን ጀምሮ በሙሉ ጉልበቱ ሥራ ላይ
ይውላል። የተፈለገው ውጤት እስካልመጣ ድረስ አይቋረጥም። የታዘዙት ጥፋቶች ሁሉ በአንደኛ ደረጃ ካየነው
ይልቅ በሰባት እጥፍ ተባዝተው አልፎም በሰባት ጊዜ ሰባት እጥፍ ይኸውም አርባ ዘጠኝ እጥፍ የሚሆን የጥፋት
ጉልበትን ተግባራዊ ያደርጋሉ።
3ኛ/ደረጃ– ይህ ሶስተኛ ደረጃ ዓለም ከተፈጠረች ጀምሮ ያልታየ ያልተሰማ ጥፋት ነው። ይህ እርምጃ
የሚወስደው! – በአንደኛውም በሁለተኛውም እርምጃ የጠረጋው እሳት እየወረደበት የሚፀናና ከዲያብሎሳዊ
ትእቢቱ የማይገታ ከሆነ እንደአገር፣ እንደአሕጉርም እንደአሕጉሮችም በአንድ ጊዜ ከምድረ – ገጽ እንዲወገዱና
ምድሪቱም ለቀረው የእግዚአብሔር ሕዝብ ብቻ እንዲሆን ይደረጋል። ለቀሪው ሕዝብ የሚጠቅሙ ብቻ ይቀራሉ።
ከእነሱ ወደትቢያነት መቀየር በኋላ ምድር ለቀረው የእግዚአብሔር ሕዝብ ትሆናለች። በምድርም፤በልዑል ኃይል
በመላ ዓለም ላይ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይነግሱባታል። ዓለምም እግዚአብሔር በቀባቸው ባሮቹ ትመራለች።
እግዚአብሔርም ድንግልም ቅዱሳን መላእክትም ቅዱሳን ሃዋርያት ነቢያት ሰማዕታት ሁሉ ይነግሳሉ። በዚህ
ሁሉ የቅጣት ፍሰት ውስጥ የመጀመሪያው ውጤት ኢትዮጵያ ነፃ ትወጣለች በዙሪያዋ ያሉ አገሮችም እንዲሁ
ነፃ ሆነው በሥሯ ይካተታሉ። በ3ኛ ደረጃ መድረስ ማለት የቅጣቱን መጠን ሰባት ጊዜ ሰባት አርባ ዘጠኝ
42
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ከዚያም በሰባት ሲባዛ ሦስት መቶ አሥራ ሦስት እጥፍ እንደማለት ነው። ዓለም እንኳን እዚህ ደረጃ ልትደርስ
ሰባት እጥፍ ቅጣቱን መሸከም ትችላለች ተብሎ አይገመትም። እንኳን ከዚህ ደረጃ በላይ የታዘዘውን ለመሸከም
ፍፁም አስደንጋጭ ነው። ልብ በሉ የልዑል ቁጣ ምን ያህል እንደነደደ እንደ ጤሰ!! እነዳታን የግብፅን ጣኦት
መልሰው አንግሰው ሲያመልኩ፤ያንን ሁሉ የእግዚአብሔርን ታዳጊነት፤ ፈርኦንን ያንበረከከ እርምጃ፤ ቀይ
ባሕርን የሰነጠቀ አምላካዊ እጁን በመናቅ ዳታንና ተከታዮቹ ለሙሴ የሰጡት መልስ እጅግ የሚገርም ነበር።
ያንተ እልቅና በኛ ላይ አይሰራም ነው ያሉት!! የእግዚአብሔር ቁጣ በሙሴ ፊት ነደደ ዳታንና መሳዮቹ ሁሉ
በሕይወት ከነምናምናቸው ምድር ተከፈተች ዋጠቻቸው። ዛሬም ዓለም ሁሉ አገራችንን ጨምሮ በክህደታቸው
በአመፃቸው በከፋና በከረፋ ኃጥያታቸው ከነዳታን በሰባት እጥፍ እየፈፀሙት ይገኛሉ። ይህም ድርጊትና በአመፅ
መፅናት የልዑልንን ቁጣ በጣም በብዙ እጥፍ እንዲነድ አድርጓል።
ወገኖቼ!!
ይህ ስምንተኛው መልእክት በዋናነት የእግዚአብሔርን ሕዝቦች ለማፅናነት እና ስለወቅቱ ሁኔታ ያላቸውን
ብዥታ ለማጥራት ቢታለምም በሁለተኛነት ደግሞ ስለጠቅላላው የመልእክቶቹ አፈፃፀምና ሂደት ለመግለፅ
ቀጣይም የሚሆነውን ለማስረዳት ታስቦ ነው የተገለፀው።
እንግዲህ ሁሉም ሊያውቀው የሚገባው ቢኖር ከእንግዲህ ለሁሉም የአዳም ዘር በሙሉ የመጣው ብርቱ
የእሳት ጠረጋ እጅግ በጣም፤ በጣም ከብዶ ይቀጥላል። የእግዚአብሔር ሕዝብ የተዋህዶ ልጅ ቅን የዋሁ
የልዑል ፈላጊ በዚህ ሁሉ ማዕበል ምንም የሚሆኑት ነገር የለም። በቃ ከእንግዲህ የእግዚአብሔር ቁጣ በልጆች
እግር ሥር በመጀመሪያ ኢትዮጵያና አካባቢዋን አስከትሎም መላውን ዓለም እስኪጥልና እስኪያስገዛ ድረስ
የሚቆም የሚዘገይ ወይም የሚታቀብ ነገር የለም። ከዚህ በታች የሚገለፁት እርምጃዎች በሙሉ ያለውን
የነበረውን የሚገሰግሰውንም እርምጃ ኢላማቸው በይበልጥ የሚያተኩርበትን ለማረጋገጥ ታስቦ የተዘረዘረ ነው።
እንደተጨማሪ ማጠናከሪያ መሆኑን ለማሳወቅም ነው።
1/ የእርምጃው ኢላማዎች /በመጀመሪያ ደረጃ የቅጣት እርምጃ ውስጥ የሚካተቱ፤–
»» በመላው ኢትዮጵያ፤ በዙሪያዋ ያሉ አገሮችን ጨምሮ እርምጃው ይመለከታቸዋል።
»» የሚሰነዘረው ቅጣት ዓይነቱም ብዛቱም ይህ ነው ተብሎ ለመግለፅ የሚያስቸግር ነው። በተናጠል፤
በጥምረት፤ በብዛት፤ በተለያየ መጠን፤ በብዙ ኢላማ በተደረጉ ስፍራዎች የሚወርድ የእሳት ቁጣና
ጠረጋ ነው። በአሁኑ ሰዓት አጥፊና ጠራጊ መላእክት በጥፍራቸው ቆመው የታዘዙትን ለመጥረግ እኔ
ልቅደም እኔ ልቅደም በሚል በታላቅ ጉጉት ላይ ቆመው ያሉ ናቸው።
»» ኢላማዎች ፡ – በኢትዮጵያ፤ በዙሪያዋም ባሉ ነዋሪ ሕዝቦች ላይ ሲሆን፤ እንደግለሰብ እንደማህበረሰብ
እንደሕዝብ፤ እንደ ጎሳ፤ እንደብሔር በአንድ ሆነው በሰፈሩ ሁሉ በውስጣቸውም የተሸከሙትን
እምነታቸውን፤ አስተሳሰባቸውን እስከዛሬ የመጡበት አቋማቸውን ሁሉ መስረት የሚያደርግ ነው።
»» የመጀመሪያ የቅጣት ኢላማዎች፣– መናፍቃን በማንኛውም መልክ አደረጃጀት ቅርፅ በየትኛውም
በአገሪቱ ገጽታ የሰፈሩ ሁሉ፤ በማናቸውም የኑሮ እርከን ያሉ መናፍቃን በሙሉ በመሪነትም ይቀመጡ
በሰባኪነት፤ በመንግሥት ኃላፊነትም ሰራተኝነትም ወይም በግል ሥራ ይሰማሩ የትኛውንም እውቀት
ሀብት ሥልጣን ጉልበት ይጨብጡ አንድም የነሱ የሆነ ቤተሰብ አብሮ ነዋሪ እንስሶቻቸውም ጭምር
ያለምንም ርህራሄ በብርቱ ቁጣ ከኢትዮጵያ ምድር ይጠረጋሉ። ለነዚህ የተተወ ምሕረት፤ ሃዘኔታ
በፍፁም የለም። እነዚህ ተፀፅተናል ቢሉ ቁጣው ከመፍሰሱ በፊት ለሥርጭት በተሰጠችው ጊዜም
ለማምለጥ ቢሞክሩም በመናፍቃን አንፃር አንድም የሚተው መናፍቅ የለም። የለም።

43
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

»» ስለመናፍቃን እንዴት የሚድን ሰው አይኖርም የሚል ሃሳብ ሊኖር ይችላል። መናፍቃን አውቀው፤
ቃሉን አንብበው፤ ቀንሰው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ላይ ያፌዙ፤ በድንግልና በቅዱሳን
መላእክትም ላይ በመናቅ በማቃለል ላይ የተሰማሩ በመሆናቸው ምንም ስፍራ አልተተወላቸውም።
ስለዚህም በትእዛዞቹ መደምደሚያ ላይ የሚጀመርበት ቀንም ይገለፃል።
»» እስላም፤ – የመጀመሪያ የቅጣት ኢላማዎች ናቸው፤ – እስላሞች በውስጣቸው ጥቂት የዋሃን መንገዱ
የጠፋባቸው እስልምና ልዑል የሚገኝበት የመሰላቸው። በተወሰነ ቅጣት ከሚድኑ በስተቀር ሁሉም
ኢትዮጵያና ዙሪያዋ ካሉ አገሮች በብርቱ ቁጣ የሚጠረጉ ናቸው። በጣት የተቆጠሩት የሚድኑትም ስለ
ቅንነታቸው ፡ ስለየዋህነታቸው፤ ስለመንገድ አለማወቃቸው፤ የያዙት እምነት እውነት ስለመሰላቸው
በመሆኑ ነው እኒህ ጥቂቶች የሚድኑት። በመዳናቸው ውስጥ ከእርምጃው ክብደት አንፃር በተጠረጉት
የእምነት አምሳያዎቻቸው አጠፋፍ እጅግ ስለሚደነግጡ፤ ፍርሃቱና ድንጋጤው ቶሎ አይለቃቸውም።
ከሚድኑት እጅግ ጥቂቶቹም ውስጥ ብዙ ጉዳት ገጥሟቸውም ነው የሚተርፉት። ልብ በሉ እስላምም
ነው ዛሬ በቅርቡ በምሥራቁ አገራችን የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችንን ያቃጠሉት ምእመኗንና አገልጋዮቿን
በአሰቃቂ ሁኔታ የፈጁት!! ስለዚህ ነው ቅጣታቸው የበረታ በቅድሚያው ውስጥም የተካተተው።
»» እርምጃው ሂደት እንጂ አንዴ ተከስቶ ወዲያው የሚያቆም አይደለም። ምክንያቱም ጠረጋው በኃጢአት
የጠለመችውን ምድር አፅድቶ ለበረከት ለምሕረት ለትንሳኤው ዘመን ይደርሱ ዘንድ ለተወሰነላቸው
የእግዚአብሔር ሕዝቦች የሚያስረክብም ነው። ልዑል የቀባቸው የሾማቸው አገልጋዮቹ በዚህ የመጀመሪያ
ደረጃ እርምጃም ሆነ በቀጣዩ ሁለተኛ ደረጃ እርምጃ ዓለምም ሆነ በዋናነት በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝም
የሱው ሰራዊትና ተከታይ አምነው ተንበርክከው አልቅሰው ድኸው ያለማቋረጥ ለምነው የተቀቡት
የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሲረከቧቸው ብቻ ነው ቁጣው የቀዘቀዘ ሂደት የሚያሳየው።
»» ካቶሊኮች በኢትዮጵያ – እነዚህም በዋነኛነት ለረጅም ዘመናት በኢትዮጵያ ላይ በእምነቷ በአስተዳደሯ
በመላ ሕይወቷ የማያቋርጥ ዘመቻ ያካሄዱ ናቸው። ዛሬም በዛው አቋማቸው በማጥፋት ላይ ያሉ
ናቸው። ካቶሊክም ሆኑ መናፍቃን በአሁኑ ዘመን እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያ ላይ በተዋህዶ
እምነቷ ላይ በጥፋት ዘመቻው ተጠምደው ያሉ ናቸው። ስልጣኑን ከጨበጡ ፖለቲከኞች ጋር
ሁልግዜም ተጣምረው የሚሠሩ ናቸው። ስለነሱ ብዙ ስለተነገረ በዚህ ጠረጋ ያለርህራሄ ከሚጠረጉት
ዋናዋናዎቹ የአገራችንም የተዋህዶ እምነታችንም መሰረታዊ ጠላቶች በመሆናቸው በአንደኛ ደረጃ
የቅጣቱና የጠረጋው ኢላማዎች ይሆናሉ። ማናቸውም ተቋሞቻቸው በሙሉ ይጠረጋሉ። በኢትዮጵያ
ምድር እንኳን ሊኖሩ ምልክትም አይተውላቸውም።
»» ዋቄ ፈታዎች፤ አባይ ጠንቋዮች ተብታቢዎች መተተኞች አጋንንት ሳቢዎች ባለውቃቢዎች የመጀመሪያው
የእሳት ጠረጋ ኢላማዎች ናቸው። ለነዚህ ምሕረት ምልክት አይተውላቸውም። ዘራቸውም አይቀጥልም።
»» ዘረኞች፤ – እነዚህም የመጀመሪያው የቅጣት የጠረጋ ኢላማዎች ናቸው። ከኢትዮጵያ የተገነጠለችውን
ኤርትራ፤ በኢትዮጵያ ምድር የሚፈሱት ቅጣቶች ሁሉ እንደሥራዋ ያለርህራሔ ይጠርጓታል። ለምና
አንብታና ተንበርክካ ከታላቁ ቁጣ የተረፉትን ጥቂት ሰዎቿን ይዛ በኢትዮጵያ የሚፀናው ብርሃናዊው
የእግዚአብሔር መንግሥት ሲቀብላት ብቻ የማያቋርጥ ጥፋቷ ይገታል። ከዘረኛ በላይ ክፉና ወንድሙን
እጅግ የሚጠላ የዲያብሎስ ፈረስ የለም። ዘረኛ በነገሰበት በየትኛውም የአገራችንም ሆነ የዓለም ሥፍራ
ፍቅር ሰላም የተዋህዶ እምነት ምልክታቸውም አይኖሩም።
በኢትዮጵያ የሠሩት የከፋ ወንጀላቸው ዛሬም ያላረካቸው የትግራይ ምድር ዘረኞች ጨካኞች የዲያብሎስ
ዋንኛ የጥፋት መሳሪያዎች በስውርም በግልጽም የእነሱ እጅና እግር የሆኑ በመላ አገሪቱ ለጥፋት የተሰለፉ
የኢትዮጵያ ጠሎች አንድም ሰው ሳይቀር በታላቅ የቁጣ እሳት ይጠረጋሉ። የሶዶም እሳት በሰባት እጅ ጉልበትና

44
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ጥፋት ይጠርጋቸዋል። እነዚህን በመደገፍ በመታመን ለኢትዮጵያ ጥፋት እየሠሩ ያሉ በየትኛውም የዓለም
ክፍል የመሸጉ ባሉበት የእሳት እራት ይሆናሉ። የዘረኞች ልጆችም እንደቤተሰቦቻቸው ሁሉ ከምድሪቱ ፊት
ሁሉ ይወገዳሉ። በሰሜን በምእራብ በምሥራቅ በደቡብ በማንኛውም ቅርጽ የሚንቀሳቀሱና ታጥቀናል ብርቱ
ነን ጠመንጃውም ታንኩም ጀቱም አለን የሚሉ በብርቱ የቁጣ እሳትና ማዕበል ይበላሉ እነሱም ዘሮቻቸውም
አገልጋዮቻቸውም ከኢትዮጵያ ምድር ከምድሪቱም ገጽታ ያለምንም ርህራሄ ይጠረጋሉ። በአገራችን በራሳቸውም
ክልላችን በሚሉት ምድር የገነቡት ይፈርሳል ያከማቹት ይወረሳል። ለበደሏቸው ሕዝቦች በምርኮ ይሰጣል።
ይህንንም እየጠፉ ባሉበት ሂደት ወስጥ ሆነው ያዩታል።
»» በኢትዮጵያ አገራችን በአሁኑ ወቅት በዘር ተደራጅተው ኢሕአድግ የሚል የዘረኞች መፈልፈያ ውስጥ
መሽገው፤ የእባብነት ቆዳቸውን ቀይረው በኢትዮጵያዊነት ጭንብል ለሚሠሩት እየሠሩ ላሉት ዘርፈ
ብዙ ጥፋት ከዘረኞቹ የማይተናነስ ቅጣት ይጠብቃቸዋል የልባቸውን ክፋት እራሳቸውም ያውቁታልና።
ስልጣናቸውን ለምነው አልቅሰው ተንበርክከው ሲፈቀድላቸው እስካላስረከቡ ድረስ የቁጣው እሳት
ያለማቋረጥ ይጠርጋቸዋል። በየትም ስፍራ ቢመሽጉ ከእሳቱ አያመልጡም።
»» የኢትዮጵያን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ምልክት አልባ ሰንደቅ ዓላማዋን የናቀ የጠላ ያቃለለ ባእድ ምልክት
የጨመረበት፤ የለጠፈበት፤ ስለኢትዮጵያ ግዛትና አንድነት ስለተዋህዶ ቤተ ክርስቲያትን ጥላቻን ያዘለ
ሁሉ በዚች የድንግል እርስት መኖርም ሆነ መቆየት አይችልም ስለዚህ ወደማረፊያው ወደገሃነም
እሳት ይሸኛል። የሚመዘነውም በልቡና በሕሊናው እንጂ በምላሱ ወይም በውጪያዊ ማስመሰሉ
አይደለምና!!
»» በአገራችን በወታደርነት ማለትም በመከላከያነት በደህንነት በፖሊስነት በሚልሺያነት በልዩ ኃይልነት
የተሰማራችሁ ሁሉ ከላይ በተዘረዘሩት ጥፋቶች በአንዱም ሆነ በብዙው ከተገኛችሁ እናንተም በእሳት
ማዕበል ትጠረጋላችሁ። ማንም አይታደጋችሁም።
»» ቅጣቱና ጠረጋውን እንቋቋማለን በሚል ትእቢት የምትገሰሉ በቅድሚያ እሳቱ እናንተን እንዲበላ
ታዟል።
»» ቅጣቱ መፍሰስ ከጀመረ የታሰበውን ሳይፈጽም አይቀዘቅዝም። እንዲያውም በየእለቱ ቅጣቱን
በሚያቃልሉ ወረፋ ጠባቂ ተጠራጊዎች ምክንያት በብርቱ እየጨመረ እጅግም እየተጠናከረ የሚሄድ
ይሆናል።
»» አደጋው እየጨመረና በአእምሮአችሁም ይሆናል ብላችሁ ያላሰባችሁት ጠረጋ ሲነሳ በደመ ነፍስ
የእግዚአብሔር ሕዝቦቹን የተመረጡ ባሮችን ለመጋጨት ወይም ለመጉዳት ካሰባችሁ ማንም ሆንክ
ማን በሃሳቡ መጠንሰስ ውስጥ እያላችሁ ወዲያው ትወገዳላችሁ። የሚመረምራችሁ በፊቱ ምንም
የተሰወረ ነገር የሌለ ልዑል ነውና!! ስለዚህ በስውርም በግልጽም በእጅ አዙርም ወደጥፋት እጅህን
እንዳትሰድ! እሳተ ጎሞራን ጨብጦ የሚድን የለምና!!
»» የመጀመሪያ ደረጃ ትእዛዞች ከላይ የተዘረዘሩትን ሁሉ እንዲጠርጉ እንዲያፀዱ የታዘዙ የልዑል የቁጣ
ሰይፎች ናቸው።
»» ይህ አንደኛ ደረጃ የጠረጋ ትእዛዝ ዋናው ዓላማው የተቀቡት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ጊዜአዊ
ወይም የሽግግር ጊዜ ሕግጋተ ሥላሴን በመደንገግ በመላ የኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ዙሪያ ባሉ
አገሮች ላይ መትከልና ብርሃናዊውን የእግዚአብሔር መንግሥት መፅናቱን ማረጋገጥ ስለአለባቸው
ነው። በኢትዮጵያ ዙሪያ ያሉ ወደመደበኛ ግዛትነት የሚካተቱ የመጀመሪያ ተካታች አገሮች ከዚህ
የሚከተሉት ናቸው። ጂቡቲ፤ ሁለቱም ሱዳኖች፤ ኤርትራ፣ ኬንያ፤ መላው ሱማሊያ፤ ሩዋንዳ፤

45
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ብሩንዲ፤ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፤ ሁለቱም ኮንጎዎች፤ ማእከላዊ አፍሪካን ሪፐብሊክ፤ ቻድ፣ ካሜሮን፤
ግብጽ፣ ጋቦን፣ ጊኒዎች፣ ዛምቢያ፣ አንጎላ ሲሆኑ የመጀመሪያው ደረጃ የቅጣት እርምጃው ይህን
ማረጋገጥ አለበት። ሁለተኛ ደረጃ የቅጣት እርምጃው ደግሞ ይህን ተከትሎ የሚቀጥል ሲሆን፤ ሶስተኛ
ደረጃ የቅጣት እርምጃው ደግሞ የሁለተኛው መጠናቀቅን ተከትሎ የሚቀጥል ይሆናል። ይህ አካሄድ
ለኢትዮጵያ ብቻ የሚወሰን ሲሆን ሌሎቹ የዓለም ሀገራት በየደረጃው የሚካተቱበት በቅንጅት እሳቱ
የሚበላቸው ናቸው። ለዚህም ሁሉም እንዲረዳው በአስፈላጊው ወቅትና ጊዜ ከልዑል አገልጋዮች
አስፈላጊው መመሪያና ትእዛዝ ይሰጥበታል። በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ያላችሁ የወቅቱ መሪዎች
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ባትጋጩ ይጠቅማችኋልና ተዘጋጁበት። በእምነት መታዘዝ ከሁሉም
መስዋእት ይበልጣልና!! ሰውኛ ዘዴና ብልሃቶቻችሁ አይታደጓችሁም!
»» በዚህ የታሪከ መጋጠሚያ ላይ የሰው ልጅ ገጥሞት የማያውቀው የዓለማችንን ቅርፅና ይዘት የድንበር
ቅርዕ የመንግሥት ቅርፅና አስተዳደር የስልጣን ተዋረድና የሕግ ስርፀት ሁሉም አካሂዶች በእግዚአብሔር
ፍቃድና ትእዛዝ መሰረት እንደአዲስ ይዋቀራል። የዲያብሎስ ፈቃድ ፈፃሚዎች ለዘመናት የተከሉት
የቀኝ ግዛት ድንበር በሙሉ ይሻራል። በሁለተኛው እርምጃ ምእራብ አፍሪካ በ3 ይከፈላል። በዓለም
ከሚፀኑት 21 መንግሥታት እንደ አንዱ ይሆናሉ። 2/3 የአፍሪካ ምድር መካከለኛውና የአረብ ገልፍ
ምድሮች በቀጥታ የኢትዮጵያ ልኡአላዊ ግዛት ወይም መደበኛ ግዛት ይሆናሉ። ቀሪው 17 መንግሥታት
በቀሪው ዓለም የሚደለደሉ ይሆናሉ። የዓለም ግፅታ እንዲህ ይሆናል። ዓለም በኢትዮጵያ ትመራለች
ብርሃናዊው የኢትዮጵያ መንግሥት መላውን ዓለም ትገዛለች። ይህ በፊት ቢገለፅም በተጨማሪ ዛሬም
አረጋግጥልሃለሁ። ልዑል የሚበዛውን በራሱ ቀሪውን በባሮቹ አማካኝነት ይፈፅመዋል። ሥላሴ በግልፅ
በሚዳሰስ መልኩ ያህል የቀባቸውን ባሮቹንም ሕዝቡንም ይመራዋል። የትንሳኤው መደበኛ ሕይወትም
እውን ይሆናል። ይህ የልዑል ትእዛዝ በዚህ መልእክት እንደአዲስ ዛሬ አይደለም የታዘዘው በመልእክት
ሦስት በአፈፃፀም ውሳኔ ላይ በጥቅሉ እንደተገለፀው ዓለም በ21 ግዛተ መንግሥት እንደምትጠቀለል
ይገልፃል። መአከሏም ኢትዮጵያ ገዢዋም ኢትዮጵያ እንደሚሆንም ያረጋግጣል። ዛሬም የመጣው
ትእዛዝ ወቅቱ ስለደረሰ ወደተግባር እንዲለወጥ ፈቃደ እግዚአብሔር ስለሆነ ነው፤ ዛሬም ተደግሞ
እየተገለፀ ያለው በዚህ ምክንያት ነው። ጊዜው ስላበቃ!። ስለዚህ ሁላችንም የለመድነው የመንግሥት
አቀራረፅ ስለሚወገድ የዛሬው ውሳኔ ሊያስገርመን ይችላል። ምክንያቱም የሚሆን ስለማይመስለን፤
የሆኖ ሆኖ አንድን ምሳሌ ብንመስል ጥሩ ነው። _ ሰውየው ፀጉሩን ሊስተካከል ከፀጉር አስተካካይ
ዘንድ ሄዶ አስተካካዩ ሥራውን ጀምሮ ሲያስተካክል ተስተካካዩ የፀጉሩ መሸበት አለመሸበት ስላሳሰበው
ለመሆኑ ፀጉሬ ሸብቷል እንዴ አለው እሱም ምን አስቸኮለህ እየቆረጥሁ ከፊትህ እጥልልህ የለም
ወይ ብሎ መለሰለት። እንዴት ይሆናል ለምትሉ አትቸኩሉ እየጠረገ ከፊታችሁ ሲጥለው ታያላችሁ
በምሕረቱ ውስጥ ከሌላችሁ ደግሞ እናንተንም በጥፋት መጥረጊያው ሲጨምራችሁ ታዩታላችሁ።
»» በዚህ የአንደኛ ደረጃ እርምጃ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ሲሰናበት ልናይ እንችላለን።
በሁለተኛው ደረጃ እርምጃ ደግሞ በየቦታው በሀምሳ እና በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር የሰው ልጅ ሲሄድ
ልናይ እንችላለን። በሶስተኛ ደረጃ ከደረስን ግን በእውነቱ እጅግ ከባድ ነው በመቶ ሚሊዮኖችና
ከዚያም በላይ ሲሄድ የምናይ ሲሆን ይህ ሶስተኛ ደረጃ በጥፋቱ በሰው ልጅ ታሪክ ያልታየ ያልተሰማ
ይሆናል። በአብዛኛውም አንድን አገር ሙሉ በሙሉ ጠርጎ ባዶ መሬት የሚያደርግም ነው። አንድን
አገር ብቻ ሳይሆን ከ2ና ሦስት በላይ የሆኑ አገሮችንም የሚያሰናብት ነው። በተለይ ኒዩክለር
መሳሪያን የመሰለ የሰው ዘርን የሚያጠፋ መሳሪያ ታጥቀው ያሉ ሁሉም አገሮች በመሳሪያቸው እነሱ
እንዲጠረጉበት ይደረጋል እንጂ ሌላው ሕዝብ ላይ ምኞታቸውን ወይም ፍላጎታቸውን ማድረግ
አይችሉም። የሚመሩበት የሚተማመኑበት ኤሌክትሮኒክስ፤ ኮምፕዩተር ሳተላይት ጂፒኤስ ሁሉም

46
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

መገናኛዎቻቸው በተፈለገ ጊዜና እነሱም ሊጠቀሙ በወሰኑበት ሰዓት በነሱ አይታዘዙም የሚያዟቸው
የትም ይሁን የት የእግዚአብሔር ሕዝቦች ይሆናሉ። በወሰኑት ሃሳባቸው መሰረት ቃላቸውን ያወጣሉ
ወይም ይናገራሉ እንደተናገሩት ይፈፀማል። የተመረጡት የእግዚአብሔር ባሮች እንደ ነቢያት አለቃ
ሙሴ እጃቸውን በዘረጉ ጊዜ አንደበታቸውም ቃልን ባወጣ ጊዜ በቃሉ መሰረት ይፈፀማል እጃቸው
ወደአመለከተበት በልቡናቸው ያሰቡት ይፈፀማል። ዛሬ ልገልፀው የማይቻል ኃይል ክብር እውቀትና
ጥበብ ማስተዋል ልዑል ያስታጥቃቸዋል። ይህ የሚሆነው እግዚአብሔር ባሮቹን በኃይልም በጥበብም
አልቆ ስለሚያስታጥቃቸውና የዓለምን እውቀት ከንቱ መሆኑን ሊያረጋግጥላቸው ስለወሰነ ነው።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! ዓለም እጅግ ተጠብቤአለሁ ተራቅቄአለሁ እንኳን ምድር ሰማዩንም
እቆጣጠራለሁ ብሎ በርግጥም ያለውን እየፈፀመ ያለበት ዘመን ውስጥ ነን። ዲያብሎስ ምድርን
ተቆጣጥሮ ሰውንም ፍፁም እቃው አድርጎ ጨርሷል። የቀረው የሰማዩን መቀጠልና ልዑልንና ቅዱሳን
መላእክትን መግጠም ነው። ይህን ምኞቱን እሱም የሱም ቀዳሚ ታዛዦች ሁሉ የሚናገሩት ነው።
በመሆኑም የእግዚአብሔርን ትእግሥት ጥንፍፍ ብሎ እንዲያበቃ አድርጓል። የእግዚአብሔር ቁጣ
ምድርም ሰማይም ከተፈጠሩ ወዲህ ያልታየ ሆኖ የመጣውም በዚህ ምክንያት ነው።
»» የታዘዙ የቅጣት አይነቶች ከዚህ በፊት በመልእክቶቹም የተጠቀሱ ቢሆንም ዛሬም ደግሜ ላነሳቸው
ግድ ይለኛል። በአገራችን – እጅግ ከባድ ቋጥኝ ሕንጻን ነቅሎ የሚወስድ አውሎ ነፋስ፤ ከባድ የመሬት
ነውጥና እሳተ ጎሞራ፤ ከባድ ርሃብና ችጋር፤ ተሰምተው የማያውቁ እንደሰደድ እሳት የሚዘምቱ ገዳይ
በሽታዎች፤ ጎርፍ፤ የእርስ በእርስ መተላለቅ፤ ከባድ በረዶ፣ የዘር ፍጅት፤ ከባድ የገንዘብ ቀውስ፤
በሁሉም አደግን በሚሉ ጂ–7 እንዲሁም ጂ–20፤ የኤሽያ፣ የአውስትራሊያ፣ የላቲን አሜሪካ፣ የሰሜን
አሜሪካ፤ የመካከለኛው አረብ አገሮች፣ አውሮፓ፣ የአፍሪካ _ ባንኮች ኢንሹራንሶች፤ ከዋናው መ/
ቤት እስከ ሥር ቅርንጫፍ በማይፈታ በፍፁም በማይቆም የገንዘብ ቀውስ፤ ዴፊሲት የእዳ ክምር
ኢንፍሌሽን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ሪሴሽን ይመታሉ። ጠንካራ ብር የሚባል ቋንቋ ይጠፋል።
ስቶክ ገብያዎች በሙሉ ይፈርሳሉ ዳግምም አይነሱም።
»» 2ኛ ደረጃ የቅጣት እርምጃ፤ – ይህ እርምጃ በቁጥር አምስት የተዘረዘረውን ሁለተኛ ደረጃ የቅጣት
ዓይነት በሙሉ ኃይሉ የሚተገብር ነው። በዚህ እርምጃ የተዘረዘሩት እንዳለ ሆኖ በረዶ መላውን
አውሮፓን አሜሪካንን ደቡብ አሜሪካንንም ኤሺያን በሞላ እስከ ሰሜን አፍሪካ ደቡባዊ አፍሪካንና
ጎረቤቶቿን በታሪክ ባልተመዘገበ ከፍታና እስከ ኔጌቲቭ – 1500 /አንድ ሺ አምስት መቶ/ ሲሊሺየስ
የቅዝቃዜ መጠን የሚጋገርና የሸፈነውን ሁሉ በቅዝቃዜ ክብደት የሚያሟሟ በረዶ ይፈሳል። የበረዶው
ክምር የዛሬ ረጅም በዓለምም ረጅም የሚባሉትን ሕንፃዎች እስከመሸፈን የሚደርስና ክፉውን ሕዝብ
ከጨረሰ በኋላ የሚሟሟ ይሆናል።
»» በምድር ላይ የሰው ልጅ በእውቀቴ በጥበቤ በሃብቴ በጉልበቴ ገነባኋቸው የሚላቸውና ዓለም ሁሉ
የሚያወድሳቸው የሚተርክላቸው ሜጋ ታላላቅ ፕሮጀክቶችና ተጠናቀው የሚሠሩ በሂደት ላይ ያሉ
በየትኛውም አገሮች ውስጥ ያሉ በሙሉ ይመታሉ በከፊልም በሙሉም ይወድማሉ።
»» በመላው ዓለም የተገነቡ የጦር መርከብ የጦር አውሮፕላን ማምረቻ ፋብሪካዎች፤ ታንኮች መድፎች
የጦር ተሽከርካሪዎች በሙሉ ይመታሉ ሽባም ይደረጋሉ። የሚሳኤል /እንደባሊስቲክ፣ ሱፐር ሶኒክ፣
ሃይፐር ሶኒክ፣ የጨረር መሳሪያዎች/ በሙሉ ይመታሉ የማያገለግሉም እንዲሆኑ ይደረጋሉ። በነዚህ
ተቋሞች ውስጥ የሚሠሩ ሰዎችም አብረው የሚጎዱ ይሆናሉ። ብዙ አገር ከአገር የሚያቋርጡ ባቡሮች
የንግድ መርከቦች ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በሙሉ ይመታሉ ይጠረጋሉ። በመላው ዓለም ያሉ በዋናነት
ታላላቅ አምራች በሆኑት አገሮች ውስጥ ያሉት የነዳጅ ማመንጫ ጉድጓዶች፤ በየብስም በውቅያኖስ
በባሕር ላይ የተተከሉት ሁሉ ይደመሰሳሉ።
47
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

»» ዓለም የሚታበይበት ትልቁ ጉልበቴ የሚለው ወታደራዊ ተቋሙ ነው። ይህን ሁሉ አመፅ ትእቢት የገነባው
ልዑልን የናቀው የካደው ትእዛዝና ፈቃዱን ለማጥፋት ሌት ተቀን የሚተጋው በዚሁ ጠመንጃ ታንክ
ጀት መርከብ ሚሳኤል ኒዩክሌርን የመሳሰሉትን ገንብቶ መላውን የዓለምን ሕዝብ የዲያብሎስ ፈረስ ሆኖ
የሚነዳበትም ሆኖ በመገኘቱም ነው። እነዚህን የመሳሰሉ ከነዚህም ወታደራዊ ጉልበቱ ጋር የተጣመረውን
የኢኮኖሚ ጉልበቱ ሁሉ መቅኒው እንዲፈስ ይደረጋል። ወታደራዊውም ኢኮኖሚያዊውም በየትኛውም
ዓለም ውስጥ ይገንቡት ይመሽጉት በብርቱ የማያቋርጥ ምት እንዲፈርሱ እንዲጠፉ ይደረጋል። ለጦርነት
ለፍጅት ሁሉም ረግጦ ለመግዛት ለመንዳት የተዘጋጁ ዘርፈ ብዙ የጦር መሳሪያዎች – አውሮፕላን
ተሸካሚ መርከቦች፤ ክሩዘሮች፤ ዲስትሮየሮች፤ ፍሪጌቶች፤ ስብመሪኖች፤ ባሕር ሰርጓጆች፤ ሁሉም
ተዋጊ ጀቶቻቸው፤ ሄሊኮፕተሮቻቸው፤ ወታደሮቻቸው አዛዦቻቸው ጋር በሙሉ በባሕር በውቅያኖስ
ውስጥ በብርቱ መጥረጊያ ይደመሰሳሉ። በነዚህ የጦር መርከቦች ውስጥ ለጥፋቱ የተተከሉ የተከማቹ
የሚሳኤል ዓይነቶች በሙሉ ይደመሰሳሉ። ሁሉንም አገሮች በተለይም እነዚህን መሳሪያዎች የሰበሰቡ
ኃያል ነን እያሉ የሚገሰሉ፤ የዓለምም ዳኛ ነን የሚሉ ቅድሚያ ይጠረጋሉ። በምድር ላይ ያደራጇቸው
የጦር ከምችቶች፤ የጦር ሰፈሮች የጥፋት ከባድ መሳሪያ አምራቾች፤ ለጥፋት የሚያገለግሉ ኬሚካል
ባዮሎጂካል መሳሪያ ማምረቻዎች የኒዩክለር ክምችቶች፤ የኒዩክሊየር ማብላያዎች ሁሉም ይደመሰሳሉ።
በሕዋ ውስጥ የተተከሉ ሳተላይቶች በተለይም ለወታደራዊ አገልግሎቶች፤ ስለላዎች፤ ማጥቂያዎች
ቋሚ ስቴሽን ብላችሁ የገነባችሁት ሁሉ በቁጣው እሳት ይደመሰሳሉ።
»» በተለይም ኃያል ነን በሚሉ አገሮች ውስጥ የሕዝብ ለሕዝብ ፍጅቶች፤ የሲቭል ጦርነቶች
በጠፉ ልዩነቶች በመመስረት ፍፁም የሰላም ቋንቋ እንዲጠፋ ይደረጋል። ገዢዎች በተገኙበትም
በሚሠሩበትም በሚሄዱበትም የደህንነት ዋስትና ያጣሉ ለአደጋም ይጋለጣሉ። ይወገዳሉም በሚከፉት
ይተካሉ። ጥፋቱም እየበረታ ይሄዳል። ባጠቃላይ ይህ የሁለተኛ ደረጃ ቅጣቱ በመልእክት አምስት
እንደተዘረዘረውና እንደታዘዘው የሚከናወን ሲሆን በዚሁ መልእክት የተዘረዘሩ ያልተዘረዘሩም አገሮች
ሁሉ እንደ ተመዘኑበት ሥራቸው የቅጣቱ ሰለባ ይሆናሉ።
»» 3ኛ ደረጃ ቅጣት_ ይህ ቅጣት ምድሪቱንና የተመረጡ የተወደዱ ለቋሚው የትንሳኤ ዘመን የተጠበቁትን
ወገኖችና ለኋለኛው ዘመን የሚጠቅሙትን ነገሮች ወይም ቁሶች ብቻ ጠብቆ፤ በመላው ዓለም ያሉትን
በአንደኛውም በሁለተኛውም ደረጃ ቅጣት እየተጠረጉም የሚፍረመረሙትን ሁሉ በየደረጃው እንደ
አሕጉርም በአንድ ቅፅበታዊ ድምሰሳ የሚያሰናብት እርምጃ ነው። አገርም ይሁን አሕጉር አንድ ሰዓት
በማይፈጅ ጊዜ ውስጥ ወደታሪክነት የሚቀይር ነው። በዚህ ቦታ በዚህ ሥፍራ እንዲህ የሚባል አገር
ከተማ ነበር ወይ ተብሎ የሚጠየቅበት በቀላሉም የማይገኝበት ይሆናል። በ3ኛ ደረጃ ቅጣት የሚሸኙ
አገሮች በአብዛኛው የምድሪቱ ኃያል ነን የሚሉት ናቸው።
»» በሁለተኛ ደረጃና በሶስተኛ ደረጃ ያለው ቅጣት እንዳለ ሆኖ በመጀመሪያ ደረጃ እርምጃ ከተጠቀሱት
በመላው ዓለም ከተዘረጉት የትእቢት ምንጭ ከሆኑት ከፍ ብሎ ከተዘረዘሩት ወታደራዊ ኢላማዎች
በተጨማሪ በኢኮኖሚው ዘርፍ በመጀመሪያው ምት እንዲካተቱ የተወሰኑ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች
ዝርዝራቸው ከዚህ በታች ከገንዘብ አቅማቸው ጋር ይገለጻል። ይህም ከዚህ በታች በእንግሊዝኛ ስለሚፃፍ
አንባቢዎች ግር እንዳይላችሁ አሳስባለሁ። ከዚህ በታች የተፃፈው ሁሉ በአማርኛው ያነበባችሁት ነው።
የኩባንያዎቹ ስም ዝርዝር ካልሆነ በስተቀር!!

48
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

For those who do not listen or read Amaharic;


All human races of the world I know most of you are not informed of all the past
6 messages : Sorry what happened due to your governments deliberate mistake, as to
me I had done to my capacity. I had sent all messages with respect to all your country
leaders through their Embassies. By paying additional payment with having a receipt I
had sent through the postal office. Today message is the 7th message. In this message
you will hear about the severe punishment that almighty God is going to do, here you
will see the list of main international companies that are going to be targeted by the
first degree and also by the second degree punishment; in this list even though their
correct name is not mentioned it will be listed by its generally known names before
the companies lists, we will also explain those countries that are the main dominant
forces of the world and their military might; and also the ordered punishment they
are going to face. For those new listeners this tremendous force of action is going to
consume uou due to your unseen sins you are commiting. Still you live with your
crimes with out hesitation and repentance. So the time has come to judge you. In
general what will happen; It is clear it had been told 6 times in the past 13 Years.
Todays message is the 7th one. What measure will be taken by Almighty God is clear.
Out of so many measure to tell you some — all forces of nature will erase you from
the faces of the earth; to metion some of their names volcanos, hurricanes, tornados,
cyclons, chaterrinas, tsunamis heat waves stormes of all types etc– in some places all
of them will wipe you in coordination. No escape route you will have every direction
will be sealed off. The action will never halt until you surrender to the order of GOD
Almighty. On this unseen measure particulary the UK USA FRANCE CHINA GERMANY
SAUDI ARABIA THE EMERATES due to their direct action in ETHIOPIA they will be
the imidiate primary target .

LIST OF MILITARY HARDWARES THAT ARE TARGETED IN THE FIRST


DEGREE PUNISHMENT AND OWNER COUNTRIES

USA
1/ A/ All Aircraft carriers , all types of submarines, all types of destroyers, all types
of Crusiers, all types of frigates, all types of corvettes with all their loaded and stored
missiles of all types, all supersonic and hypersonic missiles with all types of military
hardwares, all stuffs and personels overall USA Navy force.
B/ All Ground Forces with their personels equipments — Like tanks artilleries rockets
mortares communication equipment.
C/ All airforces, all types of fighters and bombers, all pilots.

49
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

D/ All space based forces military and intelligence sattlites all neuclear forces neutron
bombs chemical and biological stocks destined to military use.
2/ All military servicemen at large with their high ranking officers all the above
mentioned military forces of USA will be targeted by the first degree punishment, with
coordinated measure; the second degree punishment will additionally take place.
3/ America has a very complex high Tech. Multi faced industrial Technological
laboratories with maximum securities. The place is known by the name SILICON
VALLEY. This place will also be targeted by both degree of punishment. All military
command centers intelligence head command centers will be targeted by both degree
of punishment.
You USA you have 800 military bases and unknown number of intelligence gathering
posts. Almost you are policing the whole world. Remember all your bases and posts,
they will be erased from the faces of the earth. Nothing will be untouched from your
wholeness.

ENGLAND
As is mentioned on USA military forces all 3 lists mentioned will also serve on
England military forces of all sectors and establishments, and it will also be targeted
in both degree of punishment. The same action will be done on England as is going to
be done on USA.

FRANCE
As is mentioned on USA and ENGLAND military forces all 3 lists mentioned
estblishment will also serve on FRANCE military forces of all sectors and establishments
and it will also be targeted in the first degree of punishment. The same action will be
taken on FRANCE as it is going to be done on USA and ENGLAND.

CHINA
As is mentioned on USA, ENGLAND and FERANCE military forces all 3 lists
mentioned will also serve on china military forces of all sectors and military
establishments. And it will also be targeted on the first degree of punishment. The
same action will be taken on CHINA as it is going to be done on USA, ENGLAND and
FRANCE.

RUSSIA
As is mentioned on USA, ENGLAND, FRANCE and CHINA military forces all 3 lists
mentioned will also serve on RUSSIA military of all sectors and military establishments.

50
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

And it will also be targeted on the first degree of punishment. The same action will be
taken on RUSSIA as it is going to be done on USA, ENGLAND, FRANCE and CHINA
All below mentioned 23 countries will also be punished as the 5 super powers get
punished.
INDIA, GERMANY, CANADA, SAUDI ARABIA, TURKS, NORTH KOREA, SPAIN,
PORTUGAL, GREECE, JAPAN, BRAZIL, ARGENTINA, QUATAR, IRAN, ISREAL, EGYPT,
SOUTH KOREA, AUSTRALIA, HOLAND, POLAND, SOUTH AFRICA, NORWAY, FINLAND,
SWEDEN ETC ... Those countries almost numbering 166 will also be punished by their
masters scaled measure because in some points they surpass their symbol masters.
INTERNATIONAL COMPANIES THAT DOMINATES AND CONTROLS THE WORLD
ECONOMY AND ALSO THE POLITICS. ALL OF THEM ARE THE PROPERTY OF DEVIL
who is the master and engineer of all sins and crimes that completely covered the
whole world lets see their lists;

NAMES CAPITAL in NAMES CAPITAL in


billions bilions
Microsoft 750.6 BANK of America 913.5
APPLE 926.9 Alphabet 776.4
AMAZON.COM 771.8 FACEBOOK 541.5
ALIBABA 499.5 TENCENT Holdings 491.3
SEVEN and holdings 389 JP MORGAN CHASE 387.7
BERKSHIRE HATHWAY 491.9 ICBC 311
YUM BRANDS 274 WELLS Fargo 265.3
Royal Dutch Shell 306.5 EXXON mobile 344.1
Samsung Electronics 325.9 Verizom Communication 209.9
CHEVRON 248.1 Walmart 246.2
United Health Group 229 NESTLE 237.7
INTEL 254.8 NOLARTIS 203
HOME DEPOT 219.4 Johnson & Johnson 341.3
VISA 295.1 Master Card 201
CISCO SYSTEMS 221.3 Toyota Motors 200
HSBC Holdings 200. 3 PETRO CHINA 220.2
Ping an insurance group 181.1 AT&T 193.1
Volkswagon group 101.4 BNP parbias 93.3
Allianz 100.4 Royal Bank of Canada 113.4
Banco Santander 106.3 China Mobile 192.6
TOTAL 168 SINO Pec 138.6
China Merchants Bank 112.4 Comcast 146.8
China Life Insurance 104 BP 152.6
Anheuser BuschinBeu 184.3 pfizer 207

51
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

Siemens 112.5 Boieng 199.5


TD bank group 107.9 Procter and Gamble 184.5
British American Tobaco 120 AJA Group 111.4
Pepsico 138.1 Bayer 104.6
Unilever 155.8 ORACLE 191.1
BHP billiton 133.2 Dow du pont 155
Abbvie 165 Medronic 116
Union pacific 109.7 SAP 138
Merk and co 160.6 Philip Moris international 126.6
Broad com 100 Loreal group 134.2
Coca Cola 179 Honey well international 110.1
3M 121.8 Amegon 115.8
Altria group 104.5 Macdonalds 129.9
NIKE 110.3 CITI Group 185.8
General Elictric 126.8 Abbot laboratories 107.4
Kwelchow moutai 142.4 NVIDIA 154 5
Adobe Systems 119.1 novo nordisk 116
Texas Instruments 106.9 Daimler 85.7
A&A Group 64.1 Mitisubuhi uf financial 86.2
Bank of communication 66.6 Soft Bank 84.9
BMW Group 72.3 Gazprom 878
Itali uni banco holdings 87 Nippon Telegraph and tel 96.1
Sber bank 86.3 Morgan Stancly 97.7
Goldman Sachs group 91.8 IBM 132.3
Common wealth bank 93 5 Walt Disney 152.1
ROS net 69 Deutsche Telekom 80.8
BASF 95.3 Reliance Industries 93.1
Equinor 90.2 United Technologies 99.6
AIR BUS 92.1 US Bancorp 84.6
RIO TINTO 99.3 SANOFI 94.9
American Express 87.3 Saudi basic industries 91.8
VALE 77.4 Chiristian Dior 76.4
United Parcel Service 99.7 CNODC 78.8
Time Warner 73.4 Nextra Energy 75.8
Black Rock 86.6 Costco Wholesale 85.9
Gilead Sciences 86 HDFC 77.6
LOWes 72.2 AstraZeneca 90.6
Glaxo Smith Klime 98.6 Thermo Fisher Scientfic 87.1
Danaher 70.1 DiaGEO 89.9
Charles Shwab 80.2 Inditex 99.5
Eliy Lily 89.5 PAYpal 94
Schlumberger 98.5 Conco Philips 81.3

52
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

Quacomm 81.9 Salse force 97


Keyence 75.8 NETFLIX 141.9
Stryker 63.3 Colgate Palmolive 54.4
ASML Holdings 85.4 Vodafone 76
Booking Holdings 99.9 Tata consultancy Services 98.4
Naspers 112.8 Becton Dickinson 60.2
CSL 60 VM Ware 58.4
Bank of Nova Scotia 75 West pac banking group 76.2
Reliance industries 93.1 Saic motor 63.8
Enel 61.6 INg group 62.2
Intesa Sanpaulo 63.1 prudential 67.8
Glencore international 75.5 CUS Health 65.5
ENi 70.7 ROCHE holdings 65.4
Charter communication 64.8 ANZ 61.1
LOYDS banking group 65.4 Kraft Heinz company 72.2
Chubb 63.4 China Shenhua Energy 64.4
Pnc financial services 70.9 KDDI 65.5
Fedex 67 UBS 61.8
Catterpillar 92.6 Tewenty first century fox 70.3
Suncor energy 65.1 Lockheed Martin 92.2
Microm Technology 60.1 Petrobas 92.4
American tower 61.1 walgreens boots alliance 63.6
All the above listed international companies numbring 168 will be targeted in the
first sweeping & punishing actions of ALMIGHTY GOD; Once started the sweeping
actions will not stop. Until the desired target is reached. And also all of them kneel
down and give their hands to the ALMIGHTY GOD servants who are going to rise like
a morning sun in ETHIOPIA.

53
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ከላይ በእንግሊዝኛ ዝርዝራቸውን ያያችኋቸው ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በሙሉ ዋና ዋናዎቹን ለመጥቀስ
ያነሳኋቸው እንጂ ሁሉንም ለመጥቀስ ቢታሰብ ቁጥራቸው ከ2000 በላይ ናቸው። በስም ዝርዝራቸው አኳያ
የተቀመጠው ቁጥር የቢሊየን ቁጥርን የሚገልጽ ሲሆን ከ10 ዓመት በፊት የተያዘ ካፒታላቸው ነው። ዛሬ በብዙ
እጥፍ አድጓል። የሌሎቹን ትቼ የ168 ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ስም እና በቢሊዮን የተቆጠረ ካፒታላቸውን
ገልጨዋለሁ። እነዚህ በሙሉ በመጀመሪያ የልዑል በትር እና እሳት እንዲጠረጉ የተወሰነባቸው ናቸው። ቀሪዎቹ
ያልተገለፁት በቀጣዩ የሁለተኛው ጠረጋ የሚካተቱ ናቸው።

ማጠቃለያ

ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! የታዘዝኩበትን ላጠቃለውና፤ ከዛሬ 13 ዓመት በፊት የመጀመሪያውን


መልእክት ለመፃፍ ስነሳ የእግዚአብሔር ኃይል እንጂ የኔ ፈቃድ እንዳልነበረ በዚህ መልክ ገልጬው ነበር።

እኔ ቃል ተሞልቻለሁና በውስጤም ያለ መንፈስ አስገድዶኛልና በተሃ ጠጅ እንደተሞላና


ሊቀደድ እንደደረሰ አቁማዳ ሊፈነዳ እንደሚችል እንደወይን ጠጅ አቁማዳ እነሆ
አንጀቴ ሆነ ጥቂት እንድተነፍስ እናገራለሁ ከንፈሬን ገልጬ እመልሳለሁ።
መጽሐፈ ኢዮብ 32 ፡ 18 – 20
እንግዲህ እንደቃሉ የታዘዝኩትን ለማድረስ ስጥር ቆይቻለሁ። ዛሬም በዚያው መልክ ግድ ሲሆንብኝ ይህንንም
መልእክት ከ4 ዓመት ቆይታ በኋላ ወደእናንተ እንዳደርስ ሆኗል። ወገኖቼ እኔን አትመልከቱ። እኔ አንድ
መልእክት አድራሽ ፖስተኛ እንደማለት ነኝ። አድርስ የተባልኩትን ማድረስ በቃ ከዚህ የዘለለ ትርጉም የለኝም።

ውኆችን በእፍኙ የሰፈረ ሰማይንም በስንዝር የለካ የምድርንም አፈር በመስፈሪያ ሰብስቦ
የያዘ ተራሮችን በሚዛን ኮረብቶችንም በሚዛኖች የመዘነ ማን ነው? የእግዚአብሔርን
መንፈስ ያዘዘ ወይስ አማካሪ ሆኖ ያስተማረው ማነው? ወይስ ከማን ጋር ተመካከረ?
ወይስ ማን መከረው? የፍርድንም መንገድ ማን አስተማረው? እውቀትንስ ማን
አስተማረው? የማስተዋልንስ መንገድ ግን አሳየው? እነሆ አሕዛብ በገንቦ ውስጥ
እንዳለች ጠብታ ናቸው፤ በሚዛንም እንዳለ ትንሽ ትቢያ ተቆጥረዋል። እነሆ ደሴቶችን
እንደቀላል ነገር ያነሳል። ሊባኖስ ለማንደጃ እንስሶችም ለሚቃጠል መስዋእት አይበቁም
አሕዛብ ሁሉ በፊቱ እንዳልነበሩ ናቸው። ከምናምን እንደሚያንሱ እንደ ከንቱ ነገርም
ይቆጥራቸዋል። እንግዲህ እግዚአብሔርን በምን ትመስሉታላችሁ? ወይስ በምን ምሳሌ
ታስተያዩታላችሁ?
ትንቢተ ኢሳይያስ ም ፥ 40 ፡ 12 – 18
ለዚህ አጠይቆ መልስ አለን፤ በምንም መልኩ አይታሰብም አይታለምም። አመድና ትቢያ ነን! የድፍረት
ሃሳብ ያለን እንጠንቀቅ! ክቡር ስሙን እንኳን ልንመልስ በመድፈር ስለእሱ ስለምንናገረው ሁሉ እንጠንቀቅ!!
ሰውኛነትና ሥጋ ለባሽነት ብርቱ ጠላቶቻችን ናቸውና አርነት አንስጣቸው!! እግዚአብሔርን በመፍራት እናትርፍ
እንጂ በድፍረትና ኃጢአትን በመሥራት፤ በትእቢት፤ አሁን ለእርድ እንደቀረቡት ክፉና አመፀኛ ትውልዶች
እሳት አይብላን!
ወገኖቼ እንግዲህ ምንም ምናምንቴ ታናሽ ብሆንም ከላይ ራሱን በገለጠው ልዑል ኃያል የሰራዊት ሁሉ
ጌታ እግዚአብሔር /ሥላሴ/ አምናለሁ። የአባቶቼን አምላክ እታመንበታለሁ። እኔም ቤተሰቤም እንደኢያሱ
እናመልከዋለን። ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ከሁላችሁም የማንስ ወንድማችሁ ነኝ። እግዚአብሔር ብዙን
ጊዜ የዓለምን እውቀት ማስተዋልና ትልቅነት ከንቱ የሚያደርገው ምናምንቴዎችን ከትቢያ ላይ አንስቶ ሥራውን

54
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ስለሚሠራ ነው። እንደኔ ዓይነቱን ብናኝ አቧራ ማለት ነው። ስለዚህ መልእክቱን ብቻ ተመልከቱ ግራ ቀኝም
አትበሉ። ባላችሀብት ፀንታችሁ ቁሙ!!
እንግዲህ ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! የስምንተኛው መልእክት ይዞልህ የመጣውን በሚገባ ተረድታችሁታል
ብዬ አምናለሁ። ሁሉም የሰማሃቸው ሁሉ ከልዑል የተገለፁልህ ናቸው። እኔ መልእክት ማድረስ እንጂ ሌላ
የምናገረው የለኝም። ይህ መልእክት ከተገለፀበት ከታህሣሥ 21 2011 ዓ.ም ጀምሮ እስከ የካቲት 21 2011
ዓ.ም ድረስ የሚሰራጭበት ጊዜ ስለሆነ ምንም የሚከሰት ነገር አይኖርም። ያው ሁሉም በያለበት እንደሚጠብቀው
ሁሉ ከየካቲት 21 2011 ዓ.ም በኋላ በማናቸውም ጊዜ የቅጣት እርምጃው እንደመልእክቱ አገላለፅ ሥራውን
ይጀምራል። ልብ በሉ ከየካቲት 21 በኋላ ተባለ እንጂ በእለቱ አልተባለም። ከንቱዎች በየትኛውም መልእክቱ
ውስጥ በዚህ ሰዓት በዚህ እለት የሚል የቀን ቀጠሮ ተሰጥቶ አያውቅምና በትእግሥት ተከታተሉ። የተቆረጠች
ቀንና ሰዓት በልዑል እንጂ በማንም አትታወቅም። በእምነት ለምታዩ ወገኖቼ በዚህም በቀደሙትም መልእክቶች
የእግዚአብሔር የሆነውን ለመግለፅ ጥሬአለሁ ለእናተም መልካም መረዳት ይሁንላችሁ። እምነት ለሌላችሁ
ይህንንም ሆነ የቀደሙትን መልእክቶች ባታነቡት ይሻላችኋል። አንብባችሁ እምነት አልባ ናችሁና ማፌዛችሁ
አይቀርም ይህ ድርጊት ደግሞ የማይሻር ሞትን ወልዶላችሁ ይመጣል። ድሮም አሁንም ስለእናንተ ቢነገር
አያልቅም። ለጥፋት የተጻፈ ምን ቢወቅሩት አይሰማም አይለማም። ስለሆነም ከክፉዎች፣ ከአዋቂ ነኝ ባዮች
መራቅ እንጂ ሌላ ምንም ማድረግ አይቻልም።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች የቀደሙትንም የአሁኑንም ምክሮች ተጠቀሙበት ለቅን ፈራጁ አምላክ
ምስጋና አቅርቡ! ሙሉ በሙሉ ደጋግማችሁ አንብቡት! ቁንፅል ንባብ የተዛባ መረዳትን ያስከትላል። መልካም
ንባብና መረዳት ይሁንላችሁ! ደግሜ እላለሁ በማስተዋል በትእግሥት ሁሉንም የተፃፈውን ለማንበብ ሞክሩ!!
በተለይ የቀደሙ መልእክቶችን ብታገኙና ብታነቡ ሙሉ መረዳትን ልትጨብጡ ትችላላችሁ ብዬ አስባለሁ።
– የአባቶቻችን አምላክ የነመልከፄዴቅ የነኢትኤል የነኢቶጵ አምላክ ከዘለዓለም እስከዘለዓለም ስሙ
ይክበር ይመስገን!! የአብርሃሙ ሥላሴ ስሙ ይባረክ።
– ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል እናታችን፤ በሰማይም ንግስት በምድርም ንግስት ስሟ ይመስገን!!
– የከበሩት ሊቃነ መላእክት ሁሉም የተመስገኑ ይሁኑ!!
– ነቢያት ሐዋሪያት ቅዱሳን አባቶቻችን እናቶቻችን የተመሰገኑ ይሁኑ!
– ሰማዕታት አባቶቻችን እናቶቻችን የተመሰገኑ ይሁኑ።
– ሰማእታት አባት እናቶቻችን ልዑል ስለአከበራቸው ስሙ ይከበር!!
– ዛሬም ለተሰዉት

አሜን!!!
የሥላሴ ባሪያ የድንግል ባሪያ
የቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ወዳጅና አገልጋይ
ተፃፈ ታሕሣሥ 21 ቀን 2011 ዓመተ ምሕረት

55
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ስምንት

ማሳሰቢያ

እንግዲህ በሚገባ አንብባችኋል ብዬ አምናለሁ። አንዳንድ ቃሎች የተደጋገሙ ሆነው ያገኛችኋቸው


የተደጋገሙት በምክንያት ነው። እሱም አንድነው። በመልእክቱ የሰፈረው ተደጋጋሚ ቃል አይቀሬ ሁኔታዎችን
የሚገልፅ ስለሆነ ነው።
በተቻላችሁ መልእክቱን ይሰማ ዘንድ ይገባዋል ብሎ ህሊናችሁ ላሳሰባችሁ ሁሉ አድርሱ! በዚህ ምግባራችሁ
ልዑልም ድንግልም ያለበረከት አይተዋችሁም።
መልእክቱን ይገባዋል ብላችሁ ላመናችሁበት ቢያንስ ለ3 ሰው ለመስጠት ብትሞክሩ መልካም ነው። መክሊት
ቀባሪ አትባሉም። እንዲያውም ትጠቀሙበታላችሁ። መክሊት ቀባሪ ለፍርድ መክሊት አትራፊ ግን ለመባረክ
እንደ ዋሉ ሁላችሁም የምታውቁት ስለሆነ በዚህ ቸል አትበሉ።

56
የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት
ደብዳቤ
የደብዳቤዎች ምንነት መግለጫና መሸኛ ለሁሉም የአዳም
ዘር በሙሉ
ይህ ለኢትዮጵያ መንግሥት፤ ለኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን፤ እንዲሁም በዓለም ላይ ሁሉ
ነግሰው ዓለም በእጃችን ናት ብለው የሰውን ዘር በሙሉ ለሚያምሱ ኃያል ነን ባይ መንግሥታት የተፃፈ ደብዳቤ
ታገኛላችሁ። መንግሥትና መንግሥት፤ ድርጅትና መንግሥት፤ድርጅትና ድርጅት በተለያየ ጉዳይ ደብዳቤ
ይለዋወጣሉ። ይህን ደግሞ ከዜጎቻቸው ደብቀውም ወይም በየአጋጣሚው ተገልፆባቸው ሕዝብ ሊያውቀው
ይችላል። ግን ድርጊቱ በመንግሥታት ዘንድ የተለመደ ነው።
እነዚህ ከውስጥ የምታዩአቸው ደብዳቤዎች ለመንግሥታት ለታወቁ ድርጅቶች የተፃፉ ናቸው። እንግዳ
የሚሆንባችሁ እንኳን ለእናንተ ለተፃፈላቸውም የሚገርማቸው የደብዳቤው ጸሐፊዎች ጉዳይ ነው። ምክንያቱም
ከመንግሥት ወይም ከድርጅት የተፃፈ አይደለምና!! ጸሐፊው የሰራዊት ሁሉ፤ የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪና
ጌታ አገልጋይና የታመንኩ ባሪያ ነኝ የሚልና እንደሱም ከሆኑ ወንድሞቹ ጋር እራሱን የሚያስተዋውቅ
ግለሰብ መሆኑ ነው። ለዚህም ነው የእብድ ቃል ነው ብለው የሚያፌዙበት። ወረቀቱ ከሚያወጣው ገንዘብ
ያነሰ ዋጋ የሚሰጡት። ለሁሉም ማንም ይህ ደብዳቤ የደረሰው ሊያውቀው የሚገባው እኛ የእግዚአብሔርና
የድንግል አገልጋዮች የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ልጆቿም ነን። ከፈጠረን አምላክ ከታመንለት
አምላክ የታዘዝነውን በእምነት በተሰጠን ሰማያዊ ስልጣን ተፈፃሚና ወሳኝ ትእዛዞችንና የቅጣት ውሳኔዎችን
በደብዳቤአችን አሳውቀናል። መፈፀም የእግዚአብሔር የከበሩ ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ጉዳይ ነው። ቁጥር
እንደመጨበጡ መጠን የሥራ መጀመሪያችን መሆኑ ነው።
ባጠቃላይ ለ15 ዓመት የዘለቀው የ7 መልእክታት ፍሰት በእናንተ ትርጉም ቢያጣም በልዑል ዘንድ ግን
መቋጫ እንዲበጅለት ግድ ተወሰነ። እርምጃው በምድር ታሪክ ያልታየ ቢሆንም ልዑልም አምላክ ፈራጅ ዳኛ
መሆኑን ይታወቅ ዘንድ፤ ያከበራቸው የወደዳቸው የሾማቸው የምድሪቱን ሥልጣንና አገዛዝ ይረከቡና ፈቃዱንና
ሃሳቡን ብቻ ያፀኑ ዘንድ ስለተደመደመ፤ ከእንግዲህ ለእስትንፋስም እንኳ የሚሰጥ ጊዜ የለም። ስትጨበጡ
እፍኝ የማትሞሉት የዛሬው ሜዳ ሙሉ የጨለማው ኃይላት እወቁ እኛም የልዑል የታመንን ባሮችና አገልጋዮች
የእናንተን ጉዳይ ዘግተን ከድነናል። ለሚመጣው የከፋ ጠረጋ ሁሉ ምክንያት አትደርድሩ ምክንያቱ አንድና
አንድ ብቻ ነው። እሱም እናንተ የጨለማ ኃይላት እድሜና ዘመን መቋጨቱ በምትኩም የብርሃን ዘመን መተካቱ
በመሆኑ ወደዚያ የሚደረግ የመጨረሻ ጉዞ መሆኑን እወቁ!
የእብዶች ቃልም ሆነ የቅዠታሞች፤ ለእናንተም ለጠፊዎች የኮመዲ ሲኒማና ፊልም ያህል ቢያስቃችሁም
ምንም አይደለም። አያት ቅድመ አያቶቻችሁ ከኖኅ ዘመን ጀምሮ ይህንኑ አድርገውታል። ኖኅ በደረቅ ምድር
መርከብ ሲሠራ ለዘመኑ ሕዝብ ስለሃጢያታቸው መጥፋት ሲናገር ዛሬ እናንተ እንደምታሾፉት አልሳቁም?
አላፌዙም? አፊዘዋል። ኖኅ ታንክ ጀት ወታደር ነበረው? አልነበረውም። ቢኖረውማ ይሰሙት ነበር። ዛሬ
በየትኛውም ጉዳይ ከጳጳሱ ጀምሮ እስከ ምእመኑ ሁሉም ዜጋ ሽማግሌው ባልቴቷ ወጣት ሕፃኑ የሚያደምጡት
ዶክተሩን ፕሮፌሠሩን መሪ ተብየውን ነው። በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ይላል ባጠናሁት ጥናት በደረስኩበት
መላ የዲሞክራሲ ስልት መዳኛህ ይህ ነው ይላል ሕዝቡም እየጨፈረ ይቀበላል። ከሱ ሲጠፋ ደግሞ ሌላኛው
ዶክተር ተቀዋሚ ሆኖ ይቀርባል። አይ የሰው ልጅ የተማርኩ ነኝ ባዮች መጫወቻ! የምታምኑት በተጨበጠ
ነገር ነውና! ስለዚህ ባለወታደሩን ባለታንኩን አዳምጥ ሳቅ!! መብትህ ነው!! እኛም መናገር ማስጠንቀቅ
ሲብስም ወሳኙን ቃል በታመንለት በምናገለግለው ልዑል ስም እርምጃችንን ማሳወቅ በመሆኑ፤ ይህን ተፈፃሚ
እርምጃዎችን ማሳወቂያ ደብዳቤ ሕዝቡም ሁሉ እንዲያውቀው አድርገናል። ከእንግዲህ ሰማህ አልሰማህ
አይገደንም። እርምጃው ሲወሰድና ሲከናወን ምን ዓይነት ሽብር ጥፋት ውድመት እንደሚደርስ ብናውቀውም
እናንተ ደግሞ የምታዩትን ስለሆነ የምታምኑት እስኪፈፀም በኛ እያፌዛችሁ መቀጠል ነው። ደግነቱ ጊዜ የለም
እንጂ በጥቅሉ እኛንም እናንተንም ፈጥሮ በዚች ምድር የእንግድነት ጊዜን እንድናከናውን የፈቀደልን አምላካችን
ስሙ የተመሰገነ ይሁን! አሜን በተሰጠን የእጣ ክፍላችን ብንቆምም ለሚሆነው ሁሉ የማስተዋል ልቡና ይስጠን።

ምስጋና እና ክብር ለሥላሴ ይሁን!


ምስጋና ለእናታችን ድንግል ማርያም ይሁን!
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር


ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት

ቁጥር፡

ቀን፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ


አሜን!!
ጉዳዩ፡- የኢትዮጵያ መንግሥትና መላው መዋቅሩ በእግዚአብሔር ፊት መሰናበቱን ስለመግለፅ ይመለከታል።
ይህ ደብዳቤ የልዑል የታመኑ ባሮችና አገልጋዮች ውሳኔና ትእዛዝ የተላለፈበት ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
የልዑል ባሮችና አገልጋዮች የመጀመሪያ ተግባራቸውን የጀመሩበት እንደሆነ እንዲታወቅም እናሳስባለን።
አስቀድሜ በቸሩ አምላኬ በሥላሴ ስም ይህ የልዑል የቅጣት እርምጃና ጠረጋው ለሚመለከታቸው ሁሉ
ሰላምታዬን በማስቀደም ከዚሀ በታች ባለው መልክና ይዘቱ እገልፃለሁ።
የዚህን ደብዳቤ መሰረታዊ ምክንያት በጥቅሉ የሚገልፀውን የልዑልን ኃይለ ቃል በማስቀደም ወደዋናው
ጉዳይም አገባለሁ

እግዚአብሔር የበቀል አምላክ ነው የበቀል አምላክ ተገለጠ የምድር ፈራጅ ሆይ ከፍ


ከፍ በል ለትእቢተኞች ፍዳቸውን ክፈላቸው
የዳዊት መዝሙር 931-2
የእግዚአብሔርን መሰዊያ እንወርሳለን የሚሉትን አምላኬ ሆይ እንደትቢያ በንፋስ
ፊትም እንደገለባ አድርጋቸው። እሳት ዱርን እንደሚያቃጥል ነበልባልም ተራሮችን
እደሚያነድድ እንዲሁ በቁጣህ አሳዳቸው በመቅሰፍትህም አስደንግጣቸው።
ፊታቸውንም እፍረት ሙላው አቤቱ ስምህን ይፈልጋሉ ይፈሩ ለዘለዓለምም ይታወኩ
ይጎስቁሉ ይጥፉም ስምህም እግዚአብሔር እንደሆነ በምድር ሁሉ ላይም አንተ ብቻ
ልዑል እንደሆንህ ይወቁ።
የዳዊት መዝሙር 82 ፡ 12 - 18
ለአምላክነቱ የቀናበት የሜዳ ፀብቱን ፈፅሞ ይይዛል ጠላቶቹን ለመበቀል ፍጥረቱን
የሜዳ ፀብት ያደርጋታል። የእውነተኛ ጥሩርርንም ይለብሳል። ማድላት የሌለበት
ቦርቦርቴን ይደፋል የማይሸነፍ የእውነተኛ ጋሻንም ይይዛል። የሚቆርጥ መዓቱ ሰይፍን
ይስላል። ሙሴ ከልዑል ጋር ሆኖ ግብፃውያንን ተጣልቶ ይዋጋል። ፈጥኖ ያገኛቸው
ዘንድ በሳቱ ግብፃውያን ላይ የሚያስፈራ መዓቱ በደል ነጎድ ቀንቶ ይሔድባቸዋል።

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ፃድቃን ግን እንዳማረ ቀስተ ደመና አከባበብ ከበው ረድኤቱን በማግኘት ያመሰግናሉ።


ከመአቱም በደል ነጎድ ድንጊያም ፈጥኖ በረዶ ያወርዳል። የባሕሩም ውኃ በላያቸው
ይበሳጭባቸዋል። ፈሳሾችም ፡ተነዋውጠው ፈጥነው ይከብቡአቸዋል። ኃይል ያለው
ነፋስ ይቀዋወማቸዋል። ነፋስ እንደመሆኑ ድርቅ ያደርጋቸዋል። ኃጢአት ምድሩን
ሁሉ ታጠፋለችና ክፉም መሥራት የኃያላኑን ዙፋን ያጠፋልና ይበትናቸዋል።
መፅሐፈ ጥበብ ፥ም 5 ፡ ከቁ 18 -24
የዚህ ዓለም ነገስታት ስሙ የምድር ዳርቻንም፤ የምትገዙ መኳንንትም ልብ አድርጋችሁ
እወቁ
መጽሐፈ ጥበብ፤ም6፤1
የድሃ ደም፤ የድሃ እምባ፤ የድሃ ለቅሶ፤ ሰቆቃው መከራው ሁሉ ለእናንተ የምቾት ሕይወት የሥልጣን
መደላድል፤ የሆነላችሁ።
የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን ምእመኗና እውነተኛ አገልጋዮቿ ለእናንተ ጨካኝ አውሬዎች የመስቀል
ደመራና የፋሲካ በጎች የሆኑላችሁ፤ የዘመናችን ሄሮድሶች፤ የዘመናችን ጎልያዶች እንደምን አላችሁ? ጨካኝ
ወደር ያልተገኘላችሁ ዘረኞች ጎጠኞች አክራሪ እስላሞች ዋቄ ፈታና መናፍቆች ስለስብእና በጆሯችሁም ደጅ
ያላለፈባችሁ።
እነ ሰው ጤፉ እስኪ አድምጡ! መቼም አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም መልሶ መላልሶ የታመናችሁበት
ዲያብሎስ አደንቁሯችኋልና ትሰማላችሁ ተብሎ አይታሰብም። አሁን ግን ግድህን ትሰማለህ፤ እየተፈጨህ
እየተቆላህ ሞትን እየለመንክ አፍንጫህ ተሰንጎ ትሰማለህ። የእውነትን እውነት ላንተ እሬቱን ትጋታለህ ለምነህም
ተሰቃይተህም ሞትን እንደሽልማት በስተመጨረሻ ትቀበላለህ።
አገሬን ኢትዮጵያን፤ ርስተ ድንግልን፤ የልዑል የክብሩ የቃሉ የፈቃዱ መገለጫን ልታፈርሱ በብርቱ
በመጣር ላይ ያላችሁ የዘመናችን ልቡሰ አጋንንቶች እንዴትስ ተሳካላችሁ? አዎን ወዶና ፈቅዶ፤ እውነትን
በውሸት ለውጦ፤ ሥጋውና ሆዱ በልጦበት ፈጣሪውን ክዶ፤ የውሸት እምነታችሁን ታምኖ የቆመ ትውልድ
ምድሪቱን ሁሉ ስለከደነ በዚህ ተሳክቶላችኋል። እንደ አብርሃም በልዑል ፊት ክርክር ቢደረግ እንኳን ሃምሳ
ፃድቅ ከሚሊዮኖች አምስት ፃድቅ ጠፍቷል።
ዛሬ ወደ እናንተ ከላይ በርእሱ ለተጠቀሳችሁ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ከነአለቃና ጭፍራው፤ የኢትዮጵያ
ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች በየደረጃው ለተሰማራችሁ አገልጋዮች የምፅፈው ደብዳቤ
ለማስተማሪያ ፥ ለማስጠንንቀቂያ ለማሳወቂያ ወይም ሲነገር እንደነበረው መፃኢውን ፍርዳችሁን አፈፃፀሙን
ለመግለፅ አይደለም። ያ መልእክት ይባላል። የዛሬው ደብዳቤያችን በመልእክትነት የሚታሰብ አይደለም። እኛ
የልዑል ባሪያዎችና የታመንን አገልጋዮች እንደ እናንተ ጽ/ቤት፣ ቤተ መንግሥት፣ ሰራዊት ፖሊስ፣ ሰላይ፣
ደህንነት፣ ልዩ ጦር፤ ጀት የጦር መርከብ ሚሳኤል ኒዩክለር የለንም።
የኛ ኃይል እናንተ ከማታዩት እኛ ግን ከምንታመንበት በእምነትም ሁሌ ከምናየው ሰማይና ምድርን
ፍጥረትን ሁሉ እውን ካደረገው ከልዑል እግዚአብሔር ዘንድ ነው። ለዚህ ምሳሌ የሚሆኑን ፡ በእስራኤል
ምድር የነገሱት እነዳዊት፣ እነሙሴ፣ እነእያሱ፣ እነንጉስ ሰለሞን የመሳሰሉት የታመኑ የልዑል ባሮች ናቸው።
እናንተም እንደምታውቁት የእግዚአብሔርን ባሮችና እስራኤል እግባቸው ከመድረስ ምንም አይነት ምድራዊ
ኃይል አላስቆማቸውም። ዲያብሎስ ግን በየዘመኑ የራሱ ባሪያና አገልጋዩ የሆኑ መንግሥታትን እያሰማራ ሕዝበ
እግዚአብሔርን ሲዋጋ ኖሯል። በውጤቱም ተደምስሷል። አማሊቃውያን እያቡሳውያን አሞራውያን ወዘተ

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

የእግዚአብሔርም የሕዝቦቹም ጠላቶች ነበሩና ተደምስሰዋል። ለታሪክም ለትምህርትም ሆነው ዛሬ ይነሳሉ።


እናንተም ዛሬ በግልፅ ስማችሁ ግብራችሁ በዚህ ደብዳቤ የተገለፃችሁ ሁሉ ለታሪክም ለትውልድም ለቀሪው
የእግዚአብሔር ሕዝብም ትምህርት እንድትሆኑ ተደርጎ ትደመሰሳላችሁ። የትላንቱ የነሙሴ፤ የእነዳዊት፤
የነእያሱ፣ የእነኤልያስ፣ የእነአብርሃም፥ ወዘተ ተጋድሎ ተረት የሆነላችሁ የዘመናችን 7.5 ቢሊዮን የክህደት
ሕዝቦች የዲያብሎስ ፈቃድና ሃሳብ ተገዢዎች፤ ልብ በሉ የእግዚአብሔር እውነት ለዘለዓለም እውነት እንጂ
ዘመን ባለፈ ቁጥር የሚያረጅ እንደሰው ታሪክ እንዲህ ነበር እየተባለ የሚጠቀስ አይደለም። የሰው ታሪክ ሰዎች
ሲያልፉ እንዲህ ነበር እየተባለ ይተረካል። የእግዚአብሔር ሥራ ግን ታሪክ ተረት አይደለም።፡ ዘመን ይለፍ
ይሂድ ይምጣ የመጣውም የሄደውም በእግዚአብሔር ተፈቅዶ የተከናወነ ነው ባለቤቱ ዘመንን የሚሽር እሱና
ሥራው ግን በማንም የማይሻር ጌታ ነው። ስለዚህ ዛሬ ዓይናችሁ እያየ የዚሀን ዘመን እነእያሱን እነሙሴን
እነአብርሃምን ክንድ እየቀመሳችሁ፤ የእግዚአብሔር ባሮችን ምንነት በክፉ አጠፋፋችሁ ትመሰክራላችሁ።
ታሪክና ተረት ሆኖ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ቃል የለምና!! ልብ ብለህ አዳመጥከኝ! ግድ የለህም አስተውለህ
ስማኝ እሳት የለበሱ አንደበታቸውም ሃሳባቸውም የሚባላ እሳት ምድርንም ከነጥበቧ ጉልበቷ ከንቱ የሚያደርግ
እንደ ኢያሱ እንደሙሴ ተፈጥሮን በታመኑበት የእግዚአብሔር ኃይል የሚያዝዝ ኃይለ እግዚአብሔር የታጠቁ
የልዑል ባሮች መጡ። ጉድህን ልናየው ነው።
የፍጥረት ሁሉ ጌታ ሥላሴ በቃ ሲሉ በቃ ነው። ተደመደመ ሲሉ ተደመደመ ነው። እውነት እንደጠዋት
ፀሐይ በጨለማ ሥራህ ላይ ሁሉ ልትወጣብህ ነው። የእነዚህ ሦስት ደብዳቤዎች /ብርቱ እሳቶች/ እደጅህ
ከደረሱና ለሕዝብ ከተገለፁ ጀምሮ ሥልጣነ እግዚአብሔርን የጨበጡ የእግዚአብሔርና የድንግል ባሮች ምንነት
ምን እንደሆነ ይከሰትላችኋል። ታውቁታላችሁም።
ከዚህ በኋላ የሚተው የሚሰጥ ወይም ማካካሻ የሚሆን የጊዜ ሽርፍራፊ እንኳን የለም። የለም። እስኪ ደግሜ
እናንት የዲያብሎስ ቀጥተኛ አገልጋዮች እንደምን ሰነበታችሁ ልበላችሁ። ከእንግዲህ እንዲህ የሚላችሁ የለምና!
ምክንያቱም በሁላችሁም አንገት ላይ የልዑል የቁጣው ሰይፍ ሊያርፍ ስንዘራውን ብቻ ይጠብቃልና! የዘመናችን
ጎልያዶች፤ በጋሻና በጦራችሁ የታመናችሁ እናንተኮ የተረጋገጠ የእግዚአብሄርም የሕዝበ ክርስቲያኑም ጠላቶች
ናችሁ እኮ!
ይሁን እንጂ ሚሊዮን ጎልያዶች ሁኑ፤ በዳዊት ወንጭፍ በአንዲት በኃያሉ እግዚአብሔር ስም በተወረወረች
ድንጋይ አናቱ እንደተበረቀሰው ፍልስጤማዊ ጎልያድ፤ የእናንተም ስረ መሰረት ይፈራርሳል ይጠረጋል።
የልዑል ባሮች እንደብላቴናው እረኛ ዳዊት በእግዚአብሔር ስም ታምነው በቃሉ ኃይልን ጨብጠው እነሆ በዚህ
የመጀመሪያ ደብዳቤ ዘልቀዋል።
መግቢያችሁንም መሸሸጊያችሁንም እኛም ልናየው ነው። እስራኤልንና መሪውን ሳኦልን ያስጨነቀውን
ጎልያድን የተካችሁ የዘመናችን ጨካኝ ጎልያዶች! እነሆ መጡላችሁ ፡ እረኞቹ ዳዊቶች በእግዚአብሔር ስም
መጡባችሁ ጎልያድ በልዑል ስም በተወነጨፈችው የዳዊት ድንጋይ አናቱ ተፈርክሶ እንደተገረሰሰ አንገቱም
ተቆርጦ ሬሳው ለአደባባይ እንደዋለ ዛሬም ታሪክ ሊደገም ነው ፡ ዛሬም የዘመኑ ጎልያዶችና ፍለስጤሞች ተዋህዶ
ጠሎች ዘረኞች የአገር ጠላቶች ሬሳቸው ለአደባባይ ይውላል።
ዳዊት ጠላቱን የእግዚአብሔርንም ጠላት ሲገጥም፤ ምንም አስፈሪ ባለትጥቅ ባለጋሻ ባለጥሩር ቢሆንም
በልዑል ስም ገጠመው እንጂ አላመነታም ዛሬም እኛ የልዑል ባሮች በፊታችሁ እጅግ ያነስን ብንሆንም ልክ
ዳዊት እንዳደረገው በእግዚአብሔር ስም መጣንባችሁ።

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ለአንዴና ለማያዳግመው እርምጃ በዘመናችን ጎልያዶች ላይ በኃያሉ እግዚአብሔር ስም ተከሰትንባችሁ።


ምን ይበጃችሁ። ወዴትስ ይመለጣል። ግድ እጣ ፈንታችሁን መቀበል ነው አይነጋ መስሎአት በቋቱ ተፀዳዳች
እንደተባለው፤እናንተም አይመሽ አይነጋ መስሏችሁ በትእቢት በድፍረት ተሞልታችሁ በእግዚአብሔር ሕዝብም
በአገራችንም በባንዲራዋም በአንዲቷ ተዋህዶ ቤተ እምነታችን ላይ የተደራጀ ታስቦበት በውጪ የዲያብሎስ
ኃይላት ሁለንተናዊ ድጋፍ ታምናችሁ እንደጎሊያድ እንደሄሮድስ በጭካኔ ዘመታችሁ። እስካሁንም ዘዴ ብልሃት
ባላችሁት መንገድ ሁሉ ሄዳችሁበት። አንዴ ተደመርን አንዴም ለብልፅግና ተሻገርን፤አገርን በአዲስ መላ ልዩ
በሆነ ዲሞክራሲ ልናስወነጭፋት ነው። ምኑ ቅጡ! ምላስ አንደበት ውሸት እንደልብስ አጥልቃችሁታል።
ትንሽም እንኳን ማፈር ለማን ገደደ! ምናለ አድሜ እንኳን ቢመክራችሁ! ምንም እንኳን ሆድ፤ ገንዘብ፤
ሥልጣን፤ ክብር ውዳሴ ቢያሰክራችሁ እስከዚህ ድረስ በጭካኔ ፍፁም ከመንገድ በወጣ አረመኔነት በዚህ ወገኔ
ላይ መዝመታችሁ የሚያስደምም ነው። የሁሉም ድርጊት ማብቂያ አለው። ለሰማዩም ለምድሩም እውነተኛ ዳኛ
አለውና! አሁን በቃ! በቃ!
የዲያብሎሱ ጣትና ደራሲ የሆነውን ማኪያቬሊያዊ ድርሰት በተግባር የምትመሩበት የመጽሐፈ ጽልመት
ውልዶች ከነሕልማችሁ ከነአቅዳችሁ ከነጌቶቻችሁ እነሱም ከሚያልሙትና ከሚያቅዱት ጋር በፍፁም ሰቆቃ እጅግ
በከበደ ስቃይና ጣር ትወገዳላችሁ ትደመደማላችሁ። ይህ እድሜአችሁን ሁሉ ሁለመናችሁን ያሳረፋችሁበት
ሥልጣንና ክብር እንኳን በኢትዮጵያ ያለው የዓለሙ ሁሉ ሥልጣን ክብርና ሀብት በሙሉ ለታመኑት የልዑል
ባሮች ተሰጥቷል። ለምናችሁ ደም አንብታችሁ በብዙ ጥረት ደክማችሁ ታስረክባላችሁ። ይህ እንዴት ይሆናል
እኛም እናንተም የምናየው ይሆናል።
ድርሰትና ቲያትራችሁ መልክ ብዙ ነው። የዓለም ሁሉ መንግሥታት ገዢአቸው ዲያብሎስ ከዘመናት
በፊት ብዙ ሺ ዘመናትን ሲደክምበት የኖረውን ድርሰቱን /መጽሐፈ - ጽልመትን/ እንደዚህ ዘመን ተሳክቶለት
በተግባር ያዋለበት ዘመን ከዚህ ቀደም አልታየም። ሁሉም የዓለም መንግሥታት፤ በአሁኑ ወቅት ለማናቸውም
የመሪነት ሥራቸው መመሪያም ትእዛዙም አካሄዱም ሁሉ የሚፈስላቸው ከልእለ - ኃያላን አገራት ነው።
የኛው አገር መሪ ወይም ጠ/ሚኒስተር አብይ አህመድ የማንን ትአዛዝ ያስፈፅማል?
በስሩ የተዋቀሩ ካቢኔዎች፤ የፌደራል ባለሥልጣኖች፤ የክልል መዋቅሮች፤ መከላከያ ፌዴራል ፖሊስ፤
መደበኛ ፖሊስ፤ ደህንነት ልዩ ልዩ የየክልል ጦሮች፤ የዘር ቡድኖች ፡ ደምብ አስከባሪዎች፤ ተቃዋሚ ተብየዎች
የማንን ፈቃድ ለመፈፀም የተኮለኮሉ ናቸው። ሲናገሩ ቅዱስ የሚመስሉ በደራሲው የዲያብሎስ ዓለም አቀፍ
ጉዳይ ፈፃሚ በነአሜሪካ፤ በነእንግሊዝ፤ በነጀርመን በነፈረንሳይ በነካናዳ በነሳኡዲ አረቢያ በነቻይና እናም
በሌሎችም የተቀናበረ ትእዛዝ ምክር የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው የማንን ፈቃድ እንዲያስፈፅሙ ነው?
በኛ በልዑል ባሮችና በእናንተ የዲያብሎስ ባሮች መሃል ውጊያው ከተጀመረ 15ኛ ዓመቱን ይዟል። ለ7ጊዜ
መልእክቶች ፈሰዋል ተነግረዋል። ፍርዳችሁ ሲከተላችሁ ኖሯል። ልዑል እንድትመለሱ በናንተ ምክንያት
የጠፋውም እንዲፀፀትና እንዲመለስ፤ የታመኑ ልጆቹ እየተጎዱ፤ የዲያብሎስ መጨዎቻዎች እስከሚሆኑ ድረስ
ታግሷችኋል። አንድ ዓመት የደፈነው መልእክት 8 ምን ያህል ከባድ ውሳኔ እንዳዘለና እንደሚፈጫችሁ
የሰማና ያየው የሚመሰክረው ነው። የጥፋታችሁ ምልክቶች ቢታዩም ማንም አልደነገጠም። እንዲያውም ከበፊቱ
በሚበልጥ የጥፋት ሥራችሁን አራቃችሁ ገፋችሁበት። የሚመራችሁ የሚገፋችሁ በትእቢት የሚሞላችሁ ያው
አባታችሁ ዲያብሎስ ነውና! አይዟችሁ ምንም የሚሆን ነገር የለም እንቆጣጠረዋለን በሳይንሳዊ ዘዴ፤ በረቀቀ
የፖለቲካ /የውሸት ስልታችን/ አካሄዳችን በገነባነው ኃይላችን በሃብታችን በደረስንበት የቴክኖሎጂ ምጥቀታችን
ሁሉንም እንቆጣጠራለን አትጨነቁ የሚሏችሁ እነአሜሪካ እነእንግሊዝ እነቻይና እነሳኡዲ አረቢያና ሌሎችም
አገሮች በርግጥም ስለምትታመኑባቸው ለጊዜው ይረዷችኋል።

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ነገር ግን ይህች የሞት መርዷችሁን የያዘችው ደብዳቤ ታሪክን ልታሳያችሁ እነሆ መጣችባችሁ። አንድ ጊዜ
ለከፋ ጥፋት ተፅፋችኋልና እንኳን በደብዳቤ ከደጃችሁ ነጋሪት ቢጎሰም እንቢልታ ቢነፋ አትሰሙም።
ዛሬም የማይሆን መስሏችሁ በትእቢታችሁ እንደምትዘልቄ ምንም አያጠራጥርም። ተረት ነው እንደምትሉም
ሁሌም ይህንኑ ቃል እንደምትናገሩት የተረጋገጠ ነው። ግን ልታውቁት ይገባል የእግዚአብሔርም የሕዝቡም
የእውነትም ጠላቶች ናችሁና! ተረት የምትሆኑት እናንተ ናችሁ።
እንዲያው ከቀደመው ታሪክ ላስታውሳችሁና የእስራኤልን ሕዝብ ከባርነት ነፃ ከመውጣት፤ ወደተገባላቸው
የቃል ኪዳን ምድር ወደ ከነአን ከመድረስ ያገዳቸው ነበር? በየመንገዳቸው እያደፈጠ የተዋጋቸው ያ ሁሉ
የዲያብሎስ መንጋ፤ በዘመኑ ዲያብሎስ ይተማመንባቸው የነበሩ መንግሥታትና መሪዎች ተዋጊዎች ሕዝቦች
አልተደመሰሱም? ዛሬም ዲያብሎስ ያሰለፋችሁ የአገራችን ጨካኝ ተኩላ መንግሥቶች፤ የውጪ መንግሥታቶች፤
ዓለምአቀፍና አገር አቀፍ ባለሀብት ተብየዎች ምሁር ነን ባዮች ጋዜጠኞች አርቲስቶች ዘረኞች ነጋዴዎች
የተለያየ የእምነት ካባ ያጠለቃችሁ የዲያብሎስ ቀጥተኛ ጉዳይ ፈፃሚዎች በሙሉ ትደመሰሳላችሁ እንጂ በፍፁም
አታመልጡም። ይህን እውነት ደግሞ እኛም የልዑል ባሮች መሆናችንን በሚገባ ታውቁና ትረዱ ዘንድ ይህ
ደብዳቤ እንደደረሳችሁና እንደሚገለፀው ጊዜ ታዩታላችሁ በርግጥም ትፈፀማላችሁም።
ዛሬ ዘመኑ እጅግ በረቀቀ የቁስ እድገት፤ ጥበብ ጉልበትና አቅም የደረጃና ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ
ትእቢትና ክህደት፤ አመፃና ንቀት፤ ምንዝርናና ቅጥፈት፤ ደም አፍሳሽነትና ሶዶምነት፤ ፍፁምም የዲያብሎስ
አሽከርነት የጠለሙ ቢሆንም፤ እርኩሰታችሁ ሰማይንም ምድርንም ቢሸፍንም ከልዑል ፍርድና ቅጣት
የሚያመልጥ አንዳች ነገር የለም።
በትንቢተ ዳንኤል በልዑል ኃይለ ቃል እንዲሀ ይላል፤ ማኔ ቴቄል ፋሬስ፤ ይህም ማለት ምን ማለት ነው?
ይህንን ቃል የፃፈችው የልዑል ጣት ናት። ትርጉሙም ማኔ ማለት እግዚአብሔር መንግሥትህን ቆጠረው፤
ፈፀመውም ማለት ሲሆን ቴቄል ማለት ደግሞ፤ በሚዛን ተመዝነሀ፤ ቀልለህም ተገኘሀ ማለት ነው። ፋሬስ
ማለት ደግሞ፤ መንግሥትህ ተከፈለ፤ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎች ተሰጠ ማለት ነው። እንግዲህ ሁላችሁም
እንደምታውቁት፤ የልዑል ኃይለ ቃል ዘመኑን ሁሉ ይዳኛልና በዘመኑ፤ ቃሉ በሚመጥነው መልኩ እየተተረጎመ
በተግባር የልዑልን ፈቃድና ቃል ይፈጽማል።
የዛሬዎቹ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቁ አመፀኛ ከሃዲ ደም አፍሳሽ መንግሥታት፤ እነሱንም ያነገሰው
አመፀኛ ትውልድ ምድሪቱን ሁሉ፤ አንዲትም ሥፍራ ሳይተው ከድነዋል። ልዑልንም ፍፁም ክዷል። በምትኩም
ዲያብሎስን አንግሷል።
በመሆኑም ይህችው ታሪካዊ ጣት /የልዑል ጣት/ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያና በአካባቢው ሀገሮች ላይ፤
በቀጣይም፤ በመላው ዓለም መንግሥታት ላይ ወጥታለች። በቃሉ መሰረት፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ከነአለቃና
ምንዝሩ ጋር ይወገዳል። ከ8 ዓመት በፊት ይወገድ ዘንድ ተወስኖበት በወቅቱ የነበረውን መሪውንና የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ የጉልበት ፓትርያርክ ቢሰናበቱም፤ ኢሕአድግ አንድ ተለውጦ ኢሕአድግ ሁለትን ብናይም፤ ያም
ሲንገታገት ቆይቶ አሁንም ኢሕአዲግ ሦስትን እያየን ነው። ይሁንና የፈርኦን መንግሥት ከውርደት ሰራዊቱም
ከመደምሰስ ሕዝቡም ከታላቅ ጥፋት አላመለጠም። ፈርኦንም ልኩን አውቆ ለእግዚአብሔር እጁን ሰጠ።
የተረፈውንም ይዞ ቆየ። ከዚያ በኋላ የገጠመውን እጣውን አናውቅም።
ዛሬም የኛው ፈርኦኖች መንግሥታቸው ተቆጠረ። ተፈፀመ። አራተኛ የኢሕአዲግ ጭንብል አጥልቆ ብቅ
ማለት የለም። ውህድ ነኝ፤ ድምር ነኝ፤ ምርጥ ዲሞክራሲ ነኝ፤ የአሜሪካው የእንግሊዙ ዘመናዊ ዲሞክራሲ
ነኝ። የለም አይሰራም። ከሁሉም ምንነታችሁ ጋር ተሰናብታችኋል። አብቅታችኋል። የእግዚአብሔር ብርሃናዊው

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

መንግሥት እንደ ንጋት ፀሐይ ብቅ ይላል። ሲጨንቃችሁ የሽግግር መንግሥት ትሉ ይሆናል። ዲያብሎስና
ምድርን የሸፈኑ ቅራቅንቦዎቹ መንግሥታት ተብዬዎች ደግፎ ከያዛቸው ስርዓት ጋር ተደምድመዋል። ከእንግዲህ
የኛ የምትሉት ዘመን የለም። እቅድ የለ፤ በጀት መበጀት የለ፤ የመጪው አመትን ማየትም የለ። ሩቅ ኣሳቢዎች
አዳራችሁ ቅርብ ነው በቃ!!
የዘመናችን ትውልዶች ዛሬ የመጣውን የልዑል እርምጃ አልተረዳችሁም። ሊገባችሁም አይችልም። ምክንያቱ
ደግሞ አንድና አንድ ብቻ ነው። እሱም ዓለምን የሚያየው እንደዘለቄታ ቤቱ፤ የሚታመነውንም በጨበጠው
ሃብቱ እውቀቱ ሰርቆም ነጥቆም በሚገነባው ንብረቱ ነው። ለሱ ምሳሌው የነጩ ዓለም ሀብት እድገት እውቀት
ዲሞክራሲ ናቸው። ለራሱም ሆነ ለልጆቹ የሚያስበው ተምሮ አስተምሮ ዲግሪ ጨብጦ ሥራ ይዞ በዚች
ምድር ተደስቶ ለመኖር ነው። ስለ ፈጠረው አምላክ አያስበውም አይረዳውም አእምሮው በዓለም እውቀት
ተሞልቶአልና! ለረጅም ዓመታት እግዚአብሔር ቢታገስም የሰው ዘር እንዲህ ሙልጭ ብሎ ለዲያብሎስና
ለዓለም ቢሸነፍም አንድ ቀን ይመጣል እውነቱን ይረዳል በማለት የታመኑ ልጆቹን እየገበረ ከ2000 ዓመታት
በላይ ዓለምን በመጠነኛ ቅጣት ተሸክሟት እዚህ አድርሷታል። አሁን ግን አብቅቷል አመፅና ጥፋቱ ታይቶም
ተሰምቶም የማይታወቅ ደረጃ በመድረሱ ለምድሪቱም ለሰው ዘርም ፍፁም መጥፋት የተደገሰው ድግስ ሊሰየም
ጫፍ በመድረሱ፤ ዲያብሎስም ሃሳብና እቅዱን ሊፈፅመው ጠርዝ በመርገጡ፤ የግድ የልዑል እርምጃ መቅደም
ስላለበት ከአገራችን ኢትዮጵያ የሚጀምረው ሥር ነቀል እርምጃና ጠረጋ ዓለምን በሙሉ አፅድቶ ብርሃናዊው
መንግሥት በኢትዮጵያ ይተከል ዘንድ ከተወሰነ 15 ዓመታት ያህል ቢቆይም ዛሬ ግን ከዚህ በኋላ የሚጠበቅ
ባለመሆኑ በዚህ ደብዳቤ መላው የጨለማ ኃይልና ተገዢው ሁሉ ከምድሪቱ ይሰናበት ዘንድ ታዟል። ስለዚህ
ተደምድማችኋል። እግዚአብሔር ለባሮቹ ለልጆቹ ለታመኑበት አንዳች የሚደብቀው የለምና!! እኛ ያየነውን
የሰማነውን መጪውን ጥፋታችሁን ብታዩት ጥሩ ነበር። ግን ምን ያደርጋል ያለእምነት ዐይን አይታይምና
ዲያብሎስ እንዳወራችሁ የመንፈስ እውራን ስለሆናችሁ ከአንገታችሁ ላይ የቆመውን ሰይፍና እሳት አታዩም።
እንደታወራችሁ ዛሬ ልትጠናቀቁ ነው።
የተቆጠረው ፡የተፈፀመው ፡መንግሥት ነኝ የሚለው፤ የፌዴራሉም የክልሉም መንግሥቶች በማናቸውም ቅርፅና
ይዘት በኢትዮጵያ ምድር ያሉ ተቀዋሚዎችም ሁሉም ተመዝነዋል፤ ተሰፍረዋል፤ተቆጥረዋል፤ እንደመንግሥት
ተብየው የአብይ መንግሥት እነሱም ለሌላ ዙር ጥፋት ለዲያብሎስ ስልት መቀየሪያነት የተዘጋጁ፤ የመንግሥት
መለዋወጫ እቃዎች ናቸውና! ተሰናብተዋል። በጥቅሉ የአብይ መንግሥትም ከነዝግንትሉ ተቃዋሚዎች
ተብየዎችም ነጭ ካሳዘላቸው አጀንዳውና ቅራቅንቧቸው ጋር ለሞት ተሰጥተዋል። ከእንግዲህ እንደእስስት
መልኩን እየቀያየረ በነጮች የእውር ድንብር ሁለንተናዊ ድጋፍ አይቆምም። እነሱ /ሰለጠንን ባዮቹ የዲያብሎስ
ግንባር ቀደም ታማኞች/ ራሳቸው የተደገሰላቸውን የከፋ ሰቆቃና ሞት በጀርባቸው አዝለው፤ ይህንን በኢትዮጵያ
ምድር የተከሉትን አገልጋይ መንግሥታቸውን ለማዳን ሲራወጡ እያየን ነው። ነገር ግን አይቻልም። ሁሉም
ረጂውም ተረጂውም እንደ የቅደም ተከተላቸው ለእሳት ተሰጥተዋል። ከኢትዮጵያ ይጀምራል። በነሱ ደግሞ
ይፈጸማል።
ንጉሥ ሰለሞን እንዳለው ----- ለሁሉም ጊዜ አለው፤ ለማፍረስም ለመገንባትም ለመወለድም ለመሞትም
ለሁሉም ጊዜ አለው።
በመሆኑም ይህን ሁሉ ዘመን ዲያብሎስ ነግሶ፤ የእግዚአብሔር ፈቃድ ተረግጦና ተገስሶ ተክዶም፤ እንደ
እውነት የዲያብሎስ የፅልመት አገዛዝ ሰፍኖ፤ ሁሌም የምትኖሩ መስሏችሁ ነበር። ግን ለሁሉም ማብቂያና
መደመደሚያ አለው።

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

እውነት ነው። ትእቢተኞች ከሃዲዎች፤ ጣኦት አምላኪዎች፤ የውሸት እምነት ተከታዮች በምድሪቱ ነግሰዋል።
ከብረዋል። ምድርን ተቆጣጥረዋል። እውነተኛይቱ እምነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ በብዙ ዘዴና ብልሃት እንትወገድ
በብርቱ እየተጣረ ነው። ዘመቻውም ድብቅ ሳይሆን በግልፅ የሚከናወን ሆኗል። አገሬም እንደአገር መቆም
ተስኗታል የጥፋት ሁሉ ከፍታ ሆነ። መቋጨም አጣ። ዓለም የዲያብሎስ ንብረት መሰለች። ሕዝቡም ዘጠና
ዘጠኝ ከመቶው ለዲያብሎስ ገበረ። አምላኩም አደረገ። ይህንንም ለ15 ዓመታት ሁሉ ተናገርን ምን ዋጋ
አለው! ማንም ከቁም ነገር አልጣፈንም እጅግ በጣት ከሚቆጠሩ በቀር።
በመሆኑም ዲያብሎስ የሰውን ልጅ ሊፈትን በሱ የሚታመኑትን የራሱ ገንዘብ ሊያደርግ እድሉ እስካሁን
አለውና! በዚሁ መሰረት፤ በገነባው /በዘረጋው/ መጠነ ሰፊ የጥፋትና የኃጢአት ባርነት መረቡ የዓለምን ሕዝብ
/በጣት ከሚቆጠሩ በስተቀር/ ተገዢ አድርጎታል። ለሱ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ደግሞ፤ በብርቱ የተፈተኑ፤
የተሰቃዩ፤ ልዑልን የወደዱ እጅግ ተሰቃይተዋል። ታስረዋል፤ ተሳደዋል፤ ታርደዋል፤ ተገድለዋል፤ በታላቅ
ሰቆቃ ተወግደዋል። ለዓለምና ለዲያብሎስ አልተገዙምና!
የቀደመው እባብ /ዘንዶ/ የነገሰባቸው መንግሥታት በሙሉ ገንዘቡ ከሆኑ በሺዎች የተቆጠሩ ዓመታት
አልፈዋል። በምንም መንገድም ሆነ ዘዴ መልካም መንግሥታትን እንኳን ልናያቸው ታሪካቸውም ከጠፋ ብዙ
ዓመታት ነጉደዋል።
በአሁኑ ወቅት ምንም ዓይነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚቀበልና የሚታዘዝ፤ በእውነተኛይቱ ተዋህዶ
እምነት የሚያምን መንግሥት በፍፁም የለም። እንኳን መንግሥታት ድርጅትም ተቋምም የለም። ከግለሰቦች
አእምሮ ይህችን ብርቱ በልዑል የተወደደች የተዋህዶ እምነትን ለመንቀልና ለማጥፋት በብዙ ዘዴና መልኩ
እየሰራችሁ ነው።
እንደምሳሌ የፕሮቴስታንቶችን እምነት ብቻ ብንጠቅስ 50000 ሺ ቤተ እምነት እንገነባለን ብለው /ነጮች/
በዘመነ ኃይለማርያም ከወቅቱ ፕሬዜዳንት ተሾመ ጋር መዋዋላቸው በሚገባ የምናስታውሰው ነው። ያም ውል
በየመንደሩ በየጎጆው የፈሉትን ቸርች ተብየዎችን ማየት ከበቂ በላይ ማስረጃ ነው።
እናንተ ባነደዳችሁት ይህ ሁሉ እሳት ፊት ፀንተው በመቆም ዓለምንና ዝግንትሏን አሸንፈው ወደ አባታቸውና
ወደእናታቸው እቅፍ ወደ ገነት ብዙዎች ፈልሰዋል። እናንተ ግን ለዲያብሎስ በጣላችሁት ግዳይ ተሸልማችሁ
ተወድሳችሁ ዓለም ሁሉ አጎብድዶላችሁ እስከአሁን ዘልቃችኋል። የበዙት ደግሞ በየዘመኑ ሁሉ በጨለማው
ገዢ ሰፊ መረብ ውስጥ ወድቀው ተሸንፈው አልፈዋል። ዛሬም ምድርን ከድነው የአያት የቅድመ አያቶቻቸውን
ክፉ ሥራ አዘምነው ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ጥፋት ውስጥ ወድቀዋል።
ዲያብሎስ ባጠመደላቸው የሀብት የገንዘብ የክብር የሥልጣን ስጦታ ተደልለው በዓለም ቁሳቁስ ተውጠው
በዚህ ዓለም እውቀት ጥበብ ተመክተው ዘለዓለም ነዋሪ የሚሆኑ መስሏቸው ከፈጠራቸው አምላክ ፍፁም
ተካክደው ዲያብሎስን አምላካቸው አድርገው አለእፍረት በግልፅ እግዚአብሔርን እየተገዳደሩ አሉ። በሞትም
ወደተመደበላቸው ሲኦል በብዛት ሲሄዱም ይታያሉ። ያሉትም ሁሉንም የምድር ገጽታ ሸፍነው ሥልጣኑንም
ኢኮኖሚውንም ማናቸውም የማህበራዊ እንቅስቃሴ መረቡንም የእምነት ተቋማትንም ወታደራዊ ተቋማቱንም
የስለላ መረቡንም ጨብጠው የእግዚአብሔር የሆኑትን ጥቂት ሕዝቦች የሚረግጡት የሚጠለሉበት የሚሠሩት
አሳጥተው በጭንቅና በሰቆቃ እንዲኖሩ አሊያም እንዲወገዱ እያደረጉ ይገኛሉ። እንግዲህ ይህን ሁሉ የማነሳው
እናንተ አታውቁትም ብዬ አይደለም። የእግዚአብሔርን ቃልና ትእዛዝ ሁሉም ፍጥረት ያውቀዋል። ነገር ግን
አውቆ ክዷል ንቋል። በተለይም ስሙን ያንጠለጠሉ ካቶሊክ ፕሮቴስታንት አንጀሊካኖች ሌሎችም ክርስቲያን
መሰል ከሃዲዎች ወንጀላቸው እጅግ የከበደ ነው። ቢሊዮኖችን ጠፍረውና አስረው፤ ለዲያብሎስ ምርኮና

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ግዳይ የጣሉ ናቸው። እስላሙ ሺንቶይዝሙ ሂንዱይዝሙ በግልፅና በይፋ ለዘመናት የዘለቀ ጣኦት አቁመው
አምላካቸው አድርገው ልዑልን በቁጣው እንዲነድ አድርገውታል። ቢፀፀቱ ብሎ ሺዎች ዓመታትን ታግሶ
አሳልፏል። ግን ትእግስቱንም የፍቅር እጁንም አፌዙበት እንጂ ለሰከንድ እንኳን አላዳመጡትም። እንግዲህ
ምን ይደረግ ምንስ ማድረግ ይቻላል? ምንም። ምርጫችሁ ነው። የፀናችሁበት አቋማችሁ ነው። እስከሞት
ለዲያብሎስ ታምናችኋል። ስለዚሀ የምድሪቱም የሰማዩም ባለቤት ልዑል አሰናብቷችኋል።
ዛሬ ይህ ደብዳቤ የተፃፈው ከተሰናባቾቹ ግንባር ቀደምና የመጀመሪያው ረድፍ ለተገኛችሁ በአብይ አህመድ
መንግሥት ሥር ላላችሁ፤ ቀጥተኛ የመንግሥቱ እግር እጅ ራስ ዓይን ጉልበት ለሆናችሁ፤ ነው።
እንግዲህ በኔ በአንድ ታናሽ ባሪያው በኩል ለ7ጊዜ ለ15 ዓመታት ተከታታይ መልእክቶችን ወደ እናንተ
የሰው ልጆች ሁሉ በተለያየ መንገድ ሳደርስ ቆይቻለሁ። ዛሬ ይህ አብቅቶ እግዚአብሔር በሰጠን ትእዛዝ፤
ቀጥተኛ ለታቀደላቸው የሚደርስ እንደደረሰም ወደ እርምጃ የሚራመድ ውሳኔና የአፈፃፀም ትእዛዝ ቁጥር ጨብጦ
ወደ ታለመለት እንዲደርስ እነሆ ሆኗል።
ተቀዋሚዎችም አዲስ በእነአሜሪካ በነእንግሊዝ የሚመራ ስልታዊ የእግዚአብሔርን ሕዝብና የተዋሀዶ እምነትን
የማጥፋት ሥራ ከገዢው መንግሥት ጋር በመጣመር እያከናወኑ ይገኛሉ።
የዛሬው ገዢ ከመጀመሪያው እርኩስ የአጋንንት ውላጅ ገዢ ኢሕአድግ አንድ የምንለው የተጠነሰሰ እንደእስስት
መልኩን ቀይሮ ኢሕአድግ ሁለት ሆኖ፤ ከበፊቱ ፍጅትን የዘር ጥቃትን አንግሶ አክራሪ እስልምናን ሊጭን
ሲታገል እየታየ ነው። እንደገና ደግሞ ኢሕአዲግ ሦስትን በውህደት ስም ከነአሜሪካ በደረሰው ቀጥተኛ ትእዛዝ
እስላሞችን መናፍቆችን ዋቄ ፈታዎችን ሆድ አደሮችን አካቶ በተለይ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚያምነውን
አማራውንና ሌሎችንም አግልሎ የብልፅግና ፓርቲ መሰረትኩ ይለናል። በመልእክት ስምንት እንደተገለፀው
የአሁኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አላጋጭ አሿፊ ነህ ክፉ ሞትን ትሞታለህ ይላል።
በመልእክት 8 ስርጭት ወቅት ለሁሉም መንግሥታትና የተለያዩ ድርጅቶች መልእክቱን ስልክ ለአሁኑ
የዲያብሎስ ግንባር ቀደም አገልጋዮች ተሸላሚ፤ አክብሬ በአንቱታ በሸኚ ደብዳቤ ልኬለት ነበር። በሸኚው
ደብዳቤ ከተጠቀሰው ቃል ውስጥ ምክር ነበረበት። ይኸውም፤ የፊተኛው መሪ ጠቅላይ ሚንስትሩና ፓትርያርኩ
የተቀጡበትን ምክንያት እንዲያስታውሱና የፊተኛውን የልዑል እርምጃ አይተው እንዲማሩ መክሬ፤ በዚሀ
ስሕተት እንደማይሄዱ ተስፋዬን ገልጬ ነበር፤ ግን ውጤቱን ሳየው ከበፊቱ እጅግ የከፋና በታሪካችንም
ያላየነውን ያልሰማነውን እልቂትና የቤተ ክርስቲያናችን ጥፋት በዚህ መሪ ስር ተፈፅሟል። የሚገርመው ጥፋቱ
ሁሉ በአንድ ዘር ላይ ሲከናወን፤ ይኸው ዘር ኢላማ የተደረገው ተዋህዶን በማንገሱ አገሩን በመውደዱ፤ ሰንደቁን
አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን በመሸከሙና በመውደዱ፤ ራሱ ጠቅላይ ሚንስትሩና በሥሩ የተዋቀሩት ካቢኔዎች፤
የፀጥታ አካላት ምክር ቤት መከላከያም በመተባበር የተዋሀዶ ቤተ ክርስቲያን እንድትቃጠል እንድትፈርስ፤
በተለይ ኦሮሚያ በሚባል ክልል፤ በሶማሊያ፤ በሲዳማ፤ በቤንሻንጉል በከሚሴ ወዘተ ምእመናኖቿ አገልጋዮቿ
እንዲሰደዱ ንብረታቸው እንዲቃጠል እነሱም እንዲታረዱ እንዲገደሉ እንዲደፈሩ እንዲሰቀሉ እንደእርኩስ
እንዲታዩ ተደርጓል።
የዛሬው የኢትዮጵያችን መሪ ካለፉት /የመለስና የቡድኑ መሪዎች ኃ/ማርያምና የዚሁ ቡድን አጎብዳጅነቱ/
እጅግ የከፋና ከባለፉት አገርና ሕዝብን እንዲሁም ተዋህዶን አጥፊዎች በእጅጉ የሚልቅ ሰው ነው። በታሪክ
የግራኝ መሃመድን ጭካኔ እኛ የዛሬው ትውልዶች በዚህ መሪ ምንነት ውስጥ እያየነው ነው። አልፎም በረቀቀ
የጭካኔ ድርጊት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ ቅጠል ሲረግፍ የዚህ ሰው መንግሥት አንድንም ሰው እንደመንግሥት
ሲከላከል አልታየም አልተሰማም። እንዲያውም በራሱ መዋቅር ሥር ያሉና የሚታዘዙ መከላከያዎች፤ ፌደራሎች፤

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

በየክልሉ ያሉ ልዩ ኃይሎች የደህንነት አባሎች ፖሊሶች ትራፊኮች በይበልጥም በግልፅ ዘረኝነትን ያነገሱ ቄሮ
ተብየዎች ምን እየሠሩ እንዳለ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ ደርሶበት የተመለከተው ነው። በአዲስ አበባ የቀደመውን
ነዋሪ ነቅሎ ከሥራውም ከቤቱም አባሮና ዘርፎ በከንቲባነት ተሰይሞ የራሱን ዘር በቀበሌውም በወረዳውም በክፍለ
ከተማውም በማዘጋጃ ቤቱም በሁሉም የሚኒስቴር መ/ቤቶች፤ በሁሉም ባንኮች ኢንሹራንሶች በማናቸውም
የአገልግሎት መስጫ ተቋማቶች፤ ከከፍተኛ እስከ መዋዕለ ሕፃናት ባሉ የትምህርት ተቋማት ከተወሰነ የኦሮሞ
መኖሪያ አካባቢ የመጡ የፖለቲካው ታማኝ አገልጋዮችን አምጥቶ የቀደመውን ሰራተኛ በተለይም አማራ
ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ያለውን በመንቀል እነዚህኑ ከላይ የገለፅኳቸውን በአብዛኛው አክራሪ እስላሞች
መናፍቆች ዋቄ ፈታዎችን ተክሏል። ማነው የዚህ ሁሉ መሃንዲስ አዎን የጠ/ሚ አብይ ግሩፖች መሆናቸው
ሁሉም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው እውነት ነው። ለነዚሀ አገራችንን እምነታችን ተዋህዶን ኢትዮጵያዊ ወገናችንን
የጨፈጨፉና ያስጨፈጨፉ ጨካኝ ገዢዎችን በብዙ መንገድና በስውርም አንዳንዴም በጭንብልም ሲረዱት
የቆዩ መሰረታዊ ጠላቶቻችን ነጮች የዓለምን ትልቁን ሽልማት ሸለምነው የኛ ፍቅራችን ታዛዣችን ስለሆነ
ተቀበሉ! እንቢ ብትሉም ምንም አታመጡም የሚሉ ያህል ሆነዋል። እንግዲህ ቢነገር የማያልቀውን የዚህን ሰው
ጉድ ገታ ላድርገውና በትግራይ የመሸጉት የዚህ መንግሥት ወላጆች ለ28 ዓመታት የሠሩት ወንጀል ኃጢአት፤
ያፈሰሱት የሚሊዮኖች ደም የዘሩትና ኮትኩተው ያበቀሉት ዘረኝነትና የዘር ፍጅት ከድሃው ኢትዮጵያዊ ጉሮሮ
ነጥቀው እንደሕዝብ ለዘረፋ ለፍጅት ወጥተው ያ ሁሉ ድርጊታቸው ሳይፀፅታቸው ዛሬም ለፍጅትና መልሶ
የቀደመውን እርኩስ ሥራቸውን ለመድገም ዛሬም ያልማሉ። ዶሮ ብታልም ያው ጥሬዋን ነው እንደሚባለው
ማለት ነው። አገራችንን ለዚህ ሁሉ መጠነ ሰፊ ጉዳት የጣሉ እኒህ አርዮሶች ምን ቅጣት ይወሰድባቸዋል
የሚለውን በደረጃውና በዝርዝር ተመልክተን፤ በነማን የወንጀሉ ተዋናዮች ላይ ያርፋል የሚለውን ከዚህ በታች
እንዘረዝረዋለን።
የልዑል ኃይለ ቃል እገዲህ ይላል ፡-

ሰው በልዑል ፊት ለመፈራረድ እንዲመጣ ጊዜ አይወሰንለትም ታላላቆችን ያለምርመራ


ይሰባብራል። በእነርሱም ፈንታ ሌሎችን ያቆማል። ሥራቸውን ያውቃልና እንዲደቅቁም
በሌሊት ይገለባብጣቸዋል። መጽሐፈ ኢዮብ ም፤ 34፡23 -25
የሕያዋን ሁሉ ነፍስ የሰውም ሁሉ መንፈስ በእጁ ናት። መ . ኢዮብ ም ፡ 10፡12
እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ መልካምም ቢሆን ክፉም ቢሆን
ወደ ፍርድ ያመጣዋልና! መ. መክብብ ም፤ 12፡14
የኃጢያተኛ መብራት ይጠፋል፤ የእሳቱም ነበልባል ብልጭ አይልም፤ ብርሃን በድንኳኑ
ውስጥ ይጨልማል፤ መብራትም በላዩ ይጠፋል። የኃይሉም እርምጃ ትጠብባለች፤
ምክሩም ትጥለዋለች፤ እግሩ በወጥመድ ትያዛለች፤ በመረብም ላይ ይሄዳል፤ አሽክላ
ሰኮናውን ይይዛል፤ ወስፈንጥርም ይበረታበታል፤ በምድር ላይ የሸምቆቆ ገመድ፤
በመንገዱም ላይ ወጥመድ ለእርሱ ተሰውራለች። ድንጋጤ በዙሪያው ታስፈራዋለች፤
በስተኋላውም ሆና ታባርረዋለች፤ ኃይሉ በራብ ትደክማለች፤ መቅሰፍትም እስኪሰናከል
ተዘጋጅቶለታል፤ የሰውነቱ ብልቶች ይጠፋሉ፤ የሞትም በኩር ልጅ ብልቶቹን ይበላል፤
ከሚታመንበትም ድንኳን ይነቀላል። ወደ ድንጋጤም ንጉሥ ያስቸኩሉታል። በድንኳኑ
ውስጥ ለእርሱ የማይሆነው ይኖራል፤ በመኖሪያውም ላይ ዲን ይበተናል። ሥሩ ከበታቹ
ይደርቃል፤ ጫፉም ከበላዩ ይረግፋል፤ መታሰቢያው ከምድር ላይ ይጠፋል። በሜዳም
ስም አይቀርለትም፤ ከብርሃን ወደ ጨለማ ያፈልሱታል። ከዓለምም ያሳድዱታል
ዘርም ትውልድም በሕዝቡ መካከል አይሆንለትም፤ በመኖሪያውም ውስጥ የሚቀመጥ

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ሰው አይቀርለትም። የፊተኞች ሰዎች እንደደነገጡ እንዲሁ የኋለኞች ሰዎች ስለ ዘመኑ


ይደነቃሉ፤ በእውነት የኃጢያተኞች ቤት እንዲሁ ናት፤ እግዚአብሔርን የማያውቅ
ሰው ስፍራ ይህ ነው።
መጽሐፈ ኢዮብ ም፤ 18፤ ከቁ 5-21
ከላይ የተጠቀሱት የልዑል ኃይለ ቃሎች በአንደኛ ደረጃ በስምም በኃላፊነት ደረጃም በቡድንም በዘር
ጥላቻ በታወረ ድርጅትም ፓርቲም ተቀዋሚም የጦር ድርጅትም ፖሊስም ደህንነትም የፌደራል መዋቅርም
የክልል መዋቅርም ከቀበሌ እስከመንግሥት በተዋቀረ አካልም ያሉ ሁሉ በዚች በምድራችን በኢትዮጵያ ነግሰው
ጎልብተው በዘረኝነት በጭፍን ጥላቻ ታውረው፤ እግዚአብሔርንና ፈቃዱን ንቀው ክደው፤ ለአጋንንቶች ታዘውና
ታምነው፤ በተለያየ የውሸት እምነቶች ውስጥ ተሰብስበው ያሉ ሁሉ /መናፍቅ እስላም ካቶሊክ ዋቄ ፈታ
ተብታቢ መተተኛ አባይ ጠንቋይ ሰላይ አጋንንት ጎታች/ በዚህ ወቅትም ሆነ በቀደመው ዘረኛ አገዛዝ እጅና
እግር ዐይንና ጆሮ አእምሮና ልብ ሆነው ያገለገሉ በንስሓ ወደ እግዚአብሔር ያልቀረቡ፤ ከሆዳቸው ውጪ ሌላ
የማይታያቸው በጥቅሉ በኢትዮጵያ ምድር በሁሉም አቅጣጫ መንገድ ዘዴ ሥፍራ አቅም ስልጣን ላይ ሆናችሁ
በእምነታችን በተዋህዶ በአገራችን በኢትዮጵያ ሕልውና ላይ በአረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቋ ላይ በስውርም
በግልፅም በሙሉ ሃሳብም የተሳተፋችሁ ሁሉ በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ትወድቃላችሁ። በዚህም መሰረት
ከላይ በልዑል ኃይለ ቃል እንደተገለጸው ከዚሀ በታች በስም የምትዘረዘሩት ሁሉ ከስማችሁ ከኃላፊነታችሁ
በስም ባትታወቁም በስፍራው ላይ ያላችሁ ሁሉ በተጠቀሰው ቅጣት ትካተታላችሁ።።
የስም ዝርዝራችሁ፡ -- በአገራችን በኢትዮጵያ ላላችሁ፤ ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ በዚህ የስም ዝርዝር ያልተካተታችሁ
ነገር ግን በሁሉም ዘርፍ ለአገር ጥፋት፤ የሰራችሁ ሁሉ በስም ከተጠቀሱት ጋር አብራችሁ ትከደናላችሁ።
የሚተው የለም። በምሕረት ከሚታሰብ በስተቀር ስማችሁ፤
1/ አብይ አህመድ ጠ/ሚኒስትር 2/ ደመቀ መኮንን ም/ጠ/ሚኒስትር 3/ ገዱ አንዳርጋቸው ውጪ ጉዳይ
ሚ/ር 4/ ለማ መገርሳ የመከላከያ ሚ/ር 5/ ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት 6/ አዜብ መስፍን ያልተገለፀ
ሥልጣን በሷ ዙሪያ በንግድ በዘረፋ በግንባታ በማናቸውም መንገድ የተባበሯት ሁሉ 7/ ስብሃት ነጋ ከዘረጋው
ሁሉን አቀፍ የፋሽስት መረቡ ጋር ሁሉ 8/ አባይ ፀሐዬ 9/ጌታቸው አሰፋ ከዘረጋው የአፈና የስለላ የዘረፋ
የሽብር ተቋምና መረቡ ሀብትና ገንዘቡ ጋር ሁሉ 10/አርከበ እቁባይ 11/ ደብረ ጺዮን ገ/ሚካኤል 12/ ቴድሮስ
አድሃኖም 13/ ጀዋር መሃመድ በስውር ከዘረጋው አክራሪ እስላም ኦሮሞ ድርጅት አባሎች ጋር 14/ ሙፈሪያት
ካሚል 15/ ብርሃኑ ፀጋዬ 16/አሚር አማን 17/ጌታሁን ሙኩሪያ 18/አህመድ ሸዴ 19/ዳግማዊት ሞገስ 20/
ጥላዬ ጌቱ 21/ ኦመር ሁሴን 22/ ፈትለ ወርቅ ገ/እግዚአብሔር 23/አይሻ መሃመድ ሙሳ 24/ሳሙኤል ሁርቃ
25/ ሂሩት ወ/ማርያም 26/ ኢርጎጌ ተስፋዬ 27/ ያለም ፀጋዬ 28/ ሂሩት ካሳ 29/ አዳነች አቤቤ 3ዐ/ ፍፁም
አሰፋ 31/ሙላቱ ተሸመ 32/አባይ ወልዱ 33/አዲስ ዓለም ባሌማ 34/ ቅዱሳን ነጋ 35/ስዩም መስፍን 36/
ግርማ አመንቴ 37/ነገሬ ሌንጮ 38/አዲሱ አረጋ 39/ ሲሳይ ገመቹ 40/ አባዱላ ገመዳ 41/ወርቅነህ ገበየሁ
42/ሽመልስ አብዲሳ 43/ጠይባ ሃሰን 44/ከፍያለው አያና 45/ጨልቱ ሰኚ 46/ዘቢባ ሲራጅ 47/እልፍነሽ ባየቻ
48/ዘይነባ አደም 49/ለሚ ፈይሳ 50/ፀጋዬ አራርሳ 51/ሕዝቅኤል ገቢሳ 52/በቀለ ገርባ 53/ መለስ ዓለም 54/
መሃመድ ድሪር 55/ ኃ/ማርያም ደሳለኝ 56/ ይበልጣል አሸናፊ 57/ጌታቸው ረዳ 58/ አዲሱ ለገሰ 59/ ተፈራ
ዋልዋ 6ዐ/አሰፋ አብዩም 61/ብርሃኑ ጂላ 62/ አደም መሃመድ 63/ታከለ ኡማ ከነሙሉ ካቢኔው በአዲስ አበባ
ከዘረጋው ሁሉም መዋቅሩ ጋር 64/ካሱ ኢላላ 65/ ንጉሱ ጥላሁን 66/ ዳንኤል ክብረት 67/ዳውድ ኢብሳ
ከነሙሉ የኦነግ አባላቱና መዋቅሩ ጋር 68/የሺዋስ አሰፋ 69/ብርሃኑ ነጋ ኢዜማ በሚል ከዘረጋው አባሉና ሙሉ
መዋቅሩ ጋር 7ዐ/አንዱዓለም አራጌ 71/መራራ ጉዲና የኦሮሞ ኮንግረስ ብሎ ከዘረጋው አባሎቹና መዋቅሩ ጋር

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

72/በየነ ጴጥሮስ መድረክ የደቡብ ህብረት ብሎ ከዘረጋው አባሎቹና መዋቅሩ ጋር 73/ደሳለኝ ጨኔ አብን ብሎ
ከዘረጋው መዋቅሩና አባሎቹ ጋር 74/ ተመስገን ጥሩነሀ ከነሙሉ የስለላ መዋቅሩና ካቢኔው ጋር 75/ዮሐንስ
ቧያለው 76/ ልደቱ አያሌው 77/አብዱል አዚዝ አህመድ 78/ አድማሱ ፀጋዬ 79/ጫኔ ከበደ 80/መዓዛ
አሸናፊ 81/እዮብ ተካልኝ 82/ሽፈራው ጃርሶ 83/ደምመላሽ ገ/ሚካኤል 84/ጄኔራል ሞላ ኃይለማርያም 85/
ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከሚያዛቸው ወታደሮቹ ሁሉ ጋር 86/ ሚልኬሳ ሚደጋ 87/ዓለሙ ስሜ 88/ሌሊሳ ዋቆያ
89/ ካባ ሁንዴ 90/ አበራ ቡኖ 91/ነብዩ ዳበሱ 92/ቦጋለ ሹማ 93/በቃሉ ዘለቀ 94/በልሁ ታከለ 95/ባጫ ገኒ
በባንክ ውስጥ ከዘረጋው መዋቅሩ ጋር 96/መለሰ በየነ 97/ብርቱካን ሚደቅሳ ምርጫ ቦርድ ብላ ካቀፈቻቸው ጋር
98/ አበረ አዳሙ 99/ተመስገን ካሣ 100/ሙስጠፋ ሀሰን 101/እንቃሪ ሃስኔ 102/ ሰማን ሽፋ 103/ ሚኪያስ
እስራኤል 104/ ፈዲላ አደመ 105/ አገኘሁ ተሸገር 106/ተገኝ ተሻገር 107/ ሱልጣን አሊ 108/ መሃመድ
ኑር ሳሊያ 109/ የሺዋስ ዓለሙ 110/ ፍሬሕይወት ደበላ 111/ ዳማርሶ ዶና 112/ ዘርፉ አጥናፉ 113/
ደስታ ዴሌቦ 114/ደሴ ዳልኬ የደቡብ ክልል መሪ ከሁሉም ካቤኔአቸው ምክር ቤታቸው የዞን የወረዳ የቀበሌ
የወጣት የሴት አደረጃጀታቸውና መዋቅራቸው ጋር 115/ሚሊዮን ማትዮስ 116/ ብናልፍ አንዱዓለም 117/
ተሸመ ዋለ 118/ገነት ገ/እግዚአብሔር 119/ጃንጥራር አባይ 120/ ፍርዴ ቸሩ 121/ ፈንታዬ ጥበቡ 122/
ገለታ ስዩም 123/ በድሉ ድንገቱ 124/ይልቃል ከፍያለ አስረስ 125/አበባው ገበየሁ 126/ሞላ ፈጠነ 127/
ፀጋ አራጌ 128/ ፍስሐ ወ/ሰንበት 129/ጥላሁን መሃሪ 130/ ሂሩት ካሳው 131/ሞላ ጀንበሩ 132/መሃመሙድ
አብዱ 133/ በላይነህ አየለ 134/ላቀ አያሌው 135/ ወለላ መብራት 136/ ሌንጮ ለታ 137/ዲማ ነገዎ 138/
ከማል ገልቹ 139/ በተወልደ ወ/ማርያም የሚመራው አየር መንገድ ውስጥ ለተሰገሰጋችሁ ዘረኞች መናፍቆች
አክራሪ ሙስሊሞች ሰላዮች ለአገር ለወገን ለተዋህዶ እምነት ለሰንደቃችን /አረንጓዴ ቢጫ ቀይ/ ቦታ የሌላችሁ
140/በመብራት ኃይል፤ በቴሌ፤ በውኃና ፍሳሽ፤ በመስኖና ኢነርጂ፤ በባንክ በኢንሹራንስ፤ በቤቶች ልማት፤
በውጪና በአገር ውስጥ ላኪና አስመጪዎች፤መንገድ ትራንስፖርት፤ ትምህርት ፍትህ፤ ወዘተ የተሰማራችሁ
አገርጠል ዘረኞች መናፍቃን ዋቄ ፈታዎች አምልኮ ባእድ ተከታዮች ዘራፊዎች ደህንነቶች ሰላዮች አክራሪ
ሙስሊሞች በሙሉ በኢትዮጵያ ምድር በሁሉም የአገሪቱ ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ኮሌጆች ከፍተኛ ሁለተኛ
ደረጃ ት/ቤት፤ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የምታስተምሩ፤ የምትመሩ የምትማሩ ዘረኝነት ዋቄ ፈታነት
መናፍቅነት አክራሪ እስላምነት፤ አገር ጠልነት የተጠናወታችሁ በሙሉ። ለተለያዩ ዘረኛ ቡድኖች ድርጅቶች
አባል ደጋፊ የሆናችሁ በሙሉ ከላይ በሥም የተዘረዘራችሁ ከሥራችሁም መዋቅር ለዘረፋ ለገንዘብ ለሥልጣን
ከዘረጋችሁት መረብ ጋር፤ በውጪም በአገር ውስጥም ከገነባችሁት ካከማቻችሁት ንብረትና ሀብት ጋር በሙሉ፤
ወያኔ የሾማችሁ ጡረታም ወጣችሁ በሥራም ላይ ሆናችሁ ጄኔራሎች ኮሎኔሎች ሻለቆች ሻምበሎች መቶ አለቆች
ወታደሮች፤ በፌደራል ፖሊስ በኮማንደርነት በእንስፔክተርነት ወዘተ ዛሬም ትላንትም ያገለገላችሁ በሙሉ
በፖሊስነት በደህንነት በጡረታም ሆናችሁ አሁንም በሥራ ላይ ሁኑ ሁላችሁም መዓዛ አሸናፊ የምትመራው
የፍርድ ቤት መዋቅር በሙሉ በኣገሪቱ የተዋቀራችሁ የውሸት ክስ የምታደራጁ አቃቢያነ ሕጎች በሙሉ። 141/
ካሳሁን ሙላት 142/ኳንግ ቱትላት 143/ማንደፍሮ ንጉሴ 144/ሶፊያ ካሳ 145/ብዙነሽ መሰረት 146/ ተክሊት
ይመስል 147/ሰለሞን አረዳ 148/አሸነፈች አበበች 149/ፓስተር ፃድቄ አብዶ 150/ ፖስተር ዮናታን አክሊል
151/ተስፋዬ ዳባ 152/ ደምመላሽ ገ/ሚካኤል 153/የሰንሻይን ኮንስትራክሽን ባለቤት ከነሼር ሆልደሮቹ 154/
የኤፈርት የወያኔ ተቋም ከሁሉም ሼር ሆልደሮቹና ቅርንጫፍ አካሎቹ ጋር በሙሉ 155/ አሰር ኮንስትራክሽን
ከሁሉም ሼር ሆልደሮችና ቅርንጫፎቹ ጋር 156/ ሱር ኮንስትራክሽን ከሙሉ ሼር ሆልደሮቹና አካሎቹ ጋር
157/ ተስፋሁን ንጉሴ የጠ/ሚ ደህንነት አማካሪ 158/አብዲ ኤሊ 159/ታዬ ደንዳአ 160/ጋሻው የአብን
የድርጅት ጉዳይ ኋላፊ 161/ መላኩ ፈንታ 162/ሜጀር ጄኔራል ሹሜ አብደታ 163/ብርሃኔ ንጉሴ 164/
ኢሳይያስ ምሕረት 165/ሰይድ አህመድ 166/ አህመዲን ጀበል 167/ኡስታዝ አቡበከር 168/አሚን ጅንዳ

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

169/ ዳንኤል በቀለ 170/ ርስቱ ይርዳው 171/ ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝ 172/ብዙወርቅ ከተተ 173/አዜብ
አስናቀ 174/ ተስፋዬ በልጂጌ 175/ጥላዬ ጌጤ 176/ ኢንጅነር አብርሃም በላይ 177/አምባሳደር ማርቆስ
ተክሌ 178/ መሰረት ዘለዓለም ታደሰ 179/ሜጀር ጄኔራል ተክለ ብርሃን ወ/አረጋይ 180/ዳኛቸው አይጠገብ
181/ ደቻሳ ጉርሙ 182/ ጣሰው ገብሬ 183/ኮሚሽነር እንዳሻው ጣሰው 184/ንጉሴ አክሊሉ 185/ ብዙነሽ
መሰረት 186/እሸቴ አስፋው 187/ ተካ ገ/ኢየሱስ 188/ዮሐንስ ጫላ 189/ብዜና ኤልከድር 190/ነብዩ ባዩ
ከላይ ስማችሁ የተዘረዘረ፤ ሙያችሁ የተገለጠ ነገር ግን አንዳንዶች በስም ያልተጠቀሳችሁ፤ ብትኖሩም በስም
ከተጠቀሱት ይልቅ የእናንተ እጅግ መጥፎ ነው። ለምን ቢባል እናንተ በስም በግብር የተጠቀሳችሁ፤ እድላችሁ
ካልተጠቀሱት የተሻለ ነው። ምክንያቱም በመደንገጥ በፍጥነት በንስሓ በዚያችው ቅፅበት ወደፈጣሪያቸው
ኢምንቶች ሊገቡ ስለሚችሉ ይጠቅማቸዋል። ያልተጠቀሳችሁ ግን አይ እኛን አይመለከትም በሚል ክፉ
ሥራችሁ የማይታይ የተደበቀ መስሏችሁ ራሳችሁን ስትሸነግሉ በክፉ አጠፋፍ ትወገዳላችሁ ማለት ነው።
እንደ እውነቱ ከሆነ፤ ህውአት 3 ሚሊዮን አባል፤ ኦሕዴድ እንዲሁ በሚሊዮኖች አባል፤ ብአዴን እንዲሁ
በሚሊዮኖች አባል፤ ደሕዴግ እንዲሁ በሚሊዮኖች አባል፤ አጋር ድርጅት ተብዬዎች ጋምቤላ፤ ሱማሌ፤ አፋር፤
ቤንሻንጉል በሚሊዮኖች የተቆጠረ አባል ይዛችሁ አገርን ሕዝብን ዘርን ስታጠፉ ኖራችሁ 200 የማይሞላ ሰው
ብቻ ወንጀለኛ አገርና ሕዝብን ተዋህዶ እምነትን አጥፊ ይሆናል? አይሆንም ሁላችሁም በሥራችሁ ልክ ውድ
ዋጋ ትክፍላላችሁ። እውነቱ ይህ ነው። አገረ እግዚአብሔር አገረ ድንግል ፍፁም ትፀዳለች። እግዚአብሔርም
ድንግልም ለወደዷቸው ተባርካ ተሰጥታለች። ለተሰናባቾች መልካም ጉዞ።
በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ትወድቃላችሁ። ከላይ በስምም በጥቅል ስምም ከዚህ በታች በኃላፊነት
በጨበጣችሁት ስምም፤ እንዲሁም ከዋናው የአገሪቱ መሪ አብይ አህመድና ካቢኔው ጋር በማናቸውም የጥቅም
የሥራ የዝምድና የጓደኝነት የእምነት የመረጃ ሰብሳቢና አገልጋይነት የጦር አዛዥና አዝማችነት እንዲሁም
ታዛዥነት በውጪም በአምባሳደርነት በጥቅል ለዚህ መንግሥት እጅ እግር ዐይን ኃይል የሆናችሁ ጠቅላላ
የፌደራል መንግሥት አካሎች ሁሉ
የተወካዮች ምክር ቤት ሁሉም አባሎች፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባሎች በሙሉ በየክልሉ ያላችሁ የክልል
ምክር ቤት አባሎች በሙሉ፤ የአማራ የክልል ምክር ቤት አባሎች ፡ የአዴፓ አባሎች ፡ የአዴፓ የሥራ አስፈፃሚ
የማእከላዊ ኮሚቴ አባሎች ከክልሉ ጀምሮ እስከቀበሌ የተሰበሰባችሁ አስተዳዳሪዎች ከነካቢኔአችሁ፤ በክልሉ
በየደረጃው ተመደባችሁ የክልሉ መንግሥት ፈቃድ ፈፃሚ ታጣቂዎች ሰላዮች በተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን
አናትና መላ አካሏ የተሰገሰጋችሁ ቆብ አጥላቂ የደህንነቱ ሰላዮች በሙሉ በነጋዴነት ስም የምትታወቁ ሥራችሁና
ግብራችሁ ከክልሉ የፖለቲካ ኃይላት ጋር የተቆራኛችሁ ሁሉ፥
የትግራይ ክልል ገዢ ትህነግ /ህውአት/ እንደድርጅት አባሎች በሙሉ፤ በደ/ፂዮን የሚመራው ካቢኔ
በሙሉ፤ የህውአት ሥራ አስፈፃሚ ማእከላዊ ኮሚቴ፤ የወጣቶች አደረጃጀት በሙሉ፤ የሴቶች አደረጃጀት
በሙሉ፤ በክልሉ ያላችሁ ልዩ ኃይል ሚሊሺያ ፖሊስ ደህንነት /ሰላዮች/ የዞን የወረዳ የቀበሌ የጎጥ አመራሮች
ከነካቢኔአችሁ፤ በመላ አገሪቱ ዛሬም ትላንትም ለዘረፋ የተሰማራችሁ ዘርፋችሁም በክልላችሁ በውጪም
በመሃልም የመሸጋችሁ ባለሀብት ተብዬ ነጋዴዎች በሙሉ፤ዘረኝነትን የለበሳችሁ በሙሉ ኢትዮጵያን ባንዲራዋን
/አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን/ የጠሉ ለተዋህዶ እምነትና ቤተክርስቲያን በጥላቻ ለማፍረስ የዘመቱ ያቀዱ ያስተባበሩ፤
ሰንደቃችንን /አረገጓዴ ቢጨ ቀዩን/ በእስልምና እምነት ውስጥ ሆነው ተዋህዶን ኢትዮጵያን ሰንደቋን የጠሉ
ምንፍቅናን ካቶሊክነትን የሚያሰራጩ የሚያምኑ በሙሉ በተለይ በዚህ ክልል በህውሐት አማራውን እንደጠላት
ቆጥረው ከተፈጠሩ ጀምሮ ለጥፋቱ ተሰማርተው መሬት ለማስፋት አቅደው በወልቃይት ጠገዴ በመቶ ሺዎች
የሚቆጠር ሕዝብ የፈጁ በሌሎችም አካባቢዎች ተሰማርተው ብዙን ሕዝብ በዘሩ በእምነቱ ምክንያት ራሳቸው

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

የከፉ ወንጀለኞች ሆነው ዳኛና ፈራጅም ሆነው ሕዝብን የጨረሱ የትላንቶቹም የዛሬዎቹም በሙሉ በጥቅሉ
መላው የህውአት አባል በሙሉ ዐላማውን የደገፉ የረዱ ሁሉ፡
የኦሮሚያ ክልል ገዢ ድርጅት ኦዴፓ በአብይ አህመድ በለማ መገርሳ በሺመልስ አብዲሳ የሚመራ፤ የኦዴፓ
ሥራ አስፈፃሚ፤ ማእከላዊ ኮሚቴና የኦዴፓ መላ አባላት በሙሉ፤ በዚሀ ክልል የሚገኝ ማንኛውም ነጋዴ
ባለሀብት በተለይ በዘሩ ተመክቶ በመዝረፍ ከክልሉም ሆነ ከፌደራል አካላት ጋር በመተባበር የነጠቀ የዘረፈ
ድሃውን ከክልሉ በዘሩ ምክንያት ያባረረ የገደለ ንብረቱን የነጠቀ ያቃጠለ በድርጊቱ የተሳተፈ ያስተባበረ ያቀደ
በታጠቀው ትጥቁ ይህንኑ ዘረኝነትና ጭፍጨፋ የደገፈ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በመዝረፍ በማቃጠል ያቀደ
ያሰማራ ያደረገ ያስተባበረ መረጃ ያሰባሰበ በሙሉ፤ በዋቄ ፈታነት በመናፍቅነት የሚታመን በሙሉ ከነቤተሰቡ
በጠቅላላው ኢትዮጵያን ባንዲራዋን /አረገጓዴ ቢጫ ቀዩን/ የጠሉ ተዋህዶ እምነትን የጠሉ በአምልኮ ባእድ
በውቃቢ በተብታቢ በአጋንንት ጎታች በሰላቢ የሚያምኑ የሚያደርጉ፤ በእስልምና እምነት ውስጥ ያሉ በዚህም
እምነት ተመስርተው ተዋህዶን የጠሉ ኢትዮጵያን የጠሉ እነዚህም ልክ እንደትግሬው ድርጅት ዛሬም ተመሳሳይ
ፍጅት በተለይ በአማራው ላይ በተዋህዶ አማኙ ላይ ያነገሱ በሙሉ
የደቡብ ሕዝቦች ክልል ገዢ ድርጅት በሙፈሪያት ካሚል የሚመራ እንደድርጅት አባሎቹ በሙሉ፤ የክልሉ
ካቢኔ በሙሉ፤ የሥራ አስፈፃሚ ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት በሙሉ፤ በተለይ በቅርቡ ክልል ልሁን ብሎ ለአገር
ጥፋት ድምፁን የሰጠ በሙሉ፤ የየዞኑ ካቢኔ አባላት ከነአስተዳዳሪዎቻቸው በሙሉ የወረዳ የቀበሌ ካቢኔዎች
ታጣቂ ሚኒሻዎች የክልሉ ልዩ ኃይሎች መናፍቆች የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ያቃጠሉ የዘረፉ በሙሉ፤
ኢትዮጵያዊ ዜጋውን በዘሩ ከክልላችን ውጣ ያሉና ያስወጡ የዘረፉ የገደሉ ያስተባበሩ ያቀዱ የመሩ የተሳተፉ
በምንፍቅና የሚያምኑ የሚያስተምሩ በተለያየ ባእድ አምልኮ የተጠመዱ በሙሉ
አፋሮች ሱማሌዎች ሃረሪዎች በምሥራቅ የአገሪቱ ክፍል የሰፈሩ ሙሉ በሙሉ በእስልምና እምነት የሚያምኑ
እነዚሀም ከውስጣቸው ከተቀቀለ ባቄላ ሳይነካ እንደሚወጣ ባቄላ ልዑል በፈቀደው የሚያተርፋቸው ካሉ
በስተቀር ሁሉም በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ይወድቃሉ አጠፋፋቸው በፍጥነት ከመከናወኑ በስተቀር ሁሉም
ቅጣቶች ይፈጸሙባቸዋል።
ጋምቤላ ቤንሻንጉል ጉምዝ እነዚህም ድብልቅልቅ እምነት ያላቸው እስላምም ባእድ አምልኮም እምነት
አልባም ሲሆኑ እነዚህም ልዑል ባወቀ ጥፋታቸው ፈጥኖ የሚጠፋው ጠፍቶ የሚቀረው ይቀራል።
በኢትዮጵያ ምድር እንዲሁም እሷን በተመለከተ በውጪም የተደራጃችሁ ተቃዋሚዎች በየትኛውም ቅርፅና
ይዘት አንዲሁም አላማ ተደራጁ የሁላችሁም ቅኝት ከዲያብሎስ ድርሰት ከመጽሐፈ ጽልመት የሚጠቀስ
የዲሞክራሲ ፍልስፍናና የአገዛዝ ዘዴው የተቀዳ በመሆኑ እንዲሁም እነአሜሪካ እነእንግሊዝ እነሳኡዲ እነአረብ
ኤሜሬትስ እነፈረንሳይ በተቀያሪ ወይም በመለዋወጫነት ያዘጋጇችሁ ሰብአዊ የዘመኑ የነጭ ባሪያዎች በመሆናችሁ
ህዝቡ ወደ ፈጠረው አምላኩ እንዳይመለከት መንገዱን የጋረጣችሁ ስለሆነ በዚሁ በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ
የምትካተቱ ሆናችኋል።
አርቲስቶችና የሚዲያ ሰዎች እንደእናንተ ሕዝብን ወደጥፋት የነዳ የለም። እጅግ የከፋችሁ የአገሪቱ ጠላቶች
የተዋህዶ እምነትንና ስርአቷን የተዋጋችሁ አጥፊዎች ናችሁ። የሚዲያ ሰዎች በየቴሌቪዢኑ በብዙ ቻናል
እየተከሰታችሁ ሕዝብን ለአጥፊ ገዢዎች እንዲንበረከክ የምታደርጉ ለምንዝርና ለክህደት ለዘርፈ ብዙ ጥፋት
ህዝቡን የምትነዱ ክፉ ሆድ አደሮች በየሲኒማ ቤቱ ለሆዳችሁ የተሰበሰባችሁ አርቲስት ተብየዎች እንደጋሪ ፈረስ
የሕዝቡን ዐይንና ጆሮ በዲያብሎሳዊ ሥራችሁ የዘጋችሁ ሌላኛው የዲያብሎስ እጆች በመሆናቸሁ በአንደኛ ደረጃ
ቅጣት ውስጥ ተካታችኋል። በመሆኑም እንደገዢዎቹ ጥፋታችሁ አብሮ ደርሷል።

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

በድሬዳዋ በሃረር በናዝሬት በአዲስ አበባ በመቀሌ በባሕር ዳር በአዋሳ በነቀምት በሻሸመኔ በደሴ በአርባ ምንጭ
በደብረዘይት በጂጂጋ በመቱ በጎሬ በጅማ በወልቂጤ በአክሱም በአድዋ በአዲግራት ወልድያ ሁመራ ሽሬ ጊምቢ
አሶሳ በጥቅሉ በሁሉም የኢትዮጵያ ከተሞች የተሰማራችሁ በማናቸውም ሴክተር መ/ቤት የምትገለግሉ፤በዚህ
ባለው መንግሥት ታምናችሁ ስለሆዳችሁ በሁሉም ዘርፍ አገዛዙን ያቆማችሁ ሁሉ በግልም በተለያየ የንግድ
የግንባታ ሆቴልና ቱሪዝም በትራንስፖርትና መገናኛ በጤና ዘርፍ የተሰማራችሁ በሙሉ ከተዋህዶ ኦርቶዶክስ
እምነት ውጪ የሆናችሁ ሁሉ ከነቤተሰቦቻችሁ በዚሁ በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ተካታችኋል።
በዚህ ደብዳቤ መሰረት ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጋ የሚመዘነው በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ ተመስርቶ ምን አደረገ
በሚል በመሆኑና ቀድሞም ምልክት የተደረገበትና ያልተደረገበት ስለተለየ ሂያጁም ተሸጋሪውም በፈፃሚዎቹ
ስለሚታወቅ ማስረዳት አይጠበቅብኝም።
እንግዲህ ለእናንተ ለክፉዎች ለትእቢተኞች ለከሃዲዎች ለፌዘኞች የሚተው ጊዜ የለም።
በአንደኛ ደረጃ ቅጣት የምትካተቱት ከላይ በስምም በሥራ ኃላፊነትም በድርጅት ተሳትፎም እንደዘርም
እንደቡድንም እንደድርጊታችሁም ታይታችሁና ተመዝናችሁ መሆኑን ልታውቁት ይገባል። ሥራችሁ እምነታችሁ
ድርጊታችሁ በኢትዮጵያዊነታችሁ በተዋህዶ እምነታችሁ ወይም ክህደታችሁ በልባችሁ ቅንነት የዋህነት
እንዲሁም ተፀፅቶ በንስሓ ስለመመለሳችሁ በዚህ ሁሉ በልዑል ሚዛን ተመዘናችሁ ለምሕረት የታሰባችሁ
ምልክትን አግኝታችሁ ወደመሻገሩ ዘልቃችኋል። ቀላችሁ የተገኛችሁ ደግሞ ከላይ እንዳያችሁት ለእሳት
እንዲጥል ለታዘዘው ጥፋት ተጥላችኋል። እንግዲህ ምን ይደረግ እኛም የቀደሙትም የእግዚአብሔር ባሮች
የለፈለፉት የደከሙት የተሰደዱት ያጡት የነጡት የታሠሩት የተገደሉት እናንተን ወደእግዚአብሔር ፍቅር በንስሓ
ለመመለስ ነበር እንደምኞታቸው ባይሆንም ልዑል ድንግል በወሰዱት ሰፊና የማይገመት ትእግስት ለዘር የሚቀር
ምርኮ ተገኝቷል። ልክ እንደኖኅና ቤተሰቡ እንዲሁም እንደሎጥና ልጆቹ የሚሆነው ይህ ነው የቁጥሩ ማነስ
መጨመር ለዚሀ ዘመን ጠፊዎች እንደ ፎርሙላ የሚወሰድ አይደለም። ያው በብዙ አባቶች እንደተረጋገጠው
100 ሚሊዮን ካለፈው የኢትዮጵያ ሕዝብ 7 ወይም ስምንት ወይም 10 ሚሊዮን ቢቀር እንደማለት ነው።
ዛሬ የነገሱት ገዢዎችና አድማቂዎቻቸው ተቃዋሚዎች ምሁሮች ጋዜጠኞች ሁሉም ወዴት ነው የሚያንጋጥጡት?
ወደነጩ ዓለም ወደ አባታቸው ዲያብሎስ ሌላ ምን አላቸው፤በየትኛውም ስብሰባቸው የምሁር ገለፃቸው
ተቃዋሚም በሉት ደጋፊ ጋዜጠኛም ይባል አርቲስት በቋንቋህ ያቅርቡት እንጂ ሱፋቸውን አሳምረው የእንግሊዙ
የአሜሪካው ምሁር እንዲህ ብሎ እኔም እዚያ ሄጄ ባጠናሁት ጥናቴ እያለ ይደረድርልሃል። እንኳን ለሥጋው
የሚደክመው ቀርቶ ጳጳስ ነኝ ካህን ነኝ መንፈሳዊ መምህር ነኝ ዶክትሬቴን የጨበጥኩት ከአውሮፓ መንፈሳዊ
ኮሌጅ ነው የሚለውም ሁሉም መፍትሔ ከአውሮፓ ከአሜሪካ ዲሞክራሲ የሚመነጭ ነው። ትውልዱም በነሱ
መጠነ ሰፊ የሚዲያና የፕሬስ ውሽከታ የደነዘዘ በመሆኑ ፈጣሪውን አስቦም ጠይቆም አምኖትም አያውቅም
ለአፉ ብቻ ለመምሰል ስሙን ይጠራል እንጂ! አንድ ፕሮፌሰር ነኝ የሚል የታወቀ ተቃዋሚ ነኝ ባይ በአንድ
ወቅት ሲናገር ኢትዮጵያ ከዲሚክራሲ ሌላ መፍትሔ የላትም አንዳንድ ሰዎች ስለንጉስ ስለመለኮታዊ አገዛዝ
የሚናገሩ ይህ ከንቱና የማይሆን መታሰብም የሌለበት ነው ሲል በድፍረት ሲናገር ሰምቼዋለሁ እንግዲህ የዚህን
ሰው አስተሳሰብ ሁሉም ገዢውም ተቃዋሚውም በዚህ የሚያምነው መላው ትውልድም የሚሉትና የሚያምኑት
ነው። እርግጥ ነው ስለመንፈሳዊ አገዛዝ በዚህ ስለሚቃኘው ንጉሳዊ ስርዓት አስፈላጊና መጪውም እግዚአብሔር
የወደደውም የሚሆነውም ይህ ነው ብለን ደጋግመን አስረግጠን ስንናገር እንደእብድ የምንታይ ያልተማርን
አክራሪ የተዋህዶ አማኞች ተብለን የምናምቴዎች ስብስብ የሚል ስያሜ ተሰጥቶናል።
መልካም በውኑ እኛ የልዑል ባሮች አስቀድሞ ከእግዚአብሔር የተነገረንን እውነት ስንገልፅ እንደሚታየው
የተነገረው አልተፈፀመም የቀረውስ እየፈጨና እየቆላ ምንም ኃይል ሳያስቆመው እያካተታችሁ አይደለም? አሁን

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

እኛው እብዶች ይኸው ፍርዳችሁን አጠፋፋችሁን የናቃችሁት አይሆንም ቅዠት ነው ያላችሁትን የእግዚአብሔር
ብርሃናዊ አገዛዝ እናንተን ሲያደቃችሁ አይታያችሁም? ጧት ማታ አገር ፈረሰ ተቦደሰ ገደል ጫፍ ላይ ቆመች
እያላችሁ የምትቀባጥሩ እናንተ አይደላችሁም እንዴ? እናንተን እየፈጨ እየቆላ አያነደደ ትቢያ እያደረገ ደም
እንባ አልቅሳችሁ ለምናችሁ ያላችሁን ሁሉ በአደባባይ ገብራችሁ ጌቶቻችሁም አውሮፓ አሜሪካ እንደናንተው
ደም አልቅሰው የታመኑበትን ሁሉ አጥተው ሞትን እንደሽልማት ለምነው እንኳን በኢትዮጵያ ያለውን ስልጣን
የየትኛውም የዓለም ኃያል አገሮችም ሆነ ደካማም መንግሥታት ሁሉም በወረፋ ደጅ ጠንቶ ያስረክባል
እንዴት ይሆናል? ይሆናል የዲያብሎስ ደናቁርቶች በመቃብራችሁ ላይ እውን ይሆናል። እኛ ስንፈርድ ከልዑል
በተሰጠን ስልጣን እንጂ ለናንተ ስልጣን የሰጣችሁ ዲያብሎስ በቸረን አይደለም። ኖኅ በዓለም ፈረደ ኮነነ፤
አብርሃም የወንድሙ ልጅ ሎጥም በዓለም ላይ በፀና እምነታቸው ተለዩ ፈረዱም ፍርዳቸውም ተተገበረ። ሙሴ
በግብፃውያን ላይ፤ እያሱ በአማሊቃውያን በእያቡሳውያን በአሞራውያን ላይ ወዘተ አልፈረደም ተግባራዊስ
አላደረገም? ስለዚህ ዛሬ በሥልጣን ልዑል ባጎናፀፈን መብት እኛም በዚህ ዘመን የከፋ የእግዚአብሔርም
የሕዝቦችም ጠላቶች ላይ ፈርደናል። ይህም ምንም ኃይል ሳያቆመው ይተገበራል።
»» የተቃዋሚ ዲሞክራሲ ሲደመር አሜሪካ ይሆናል ዜሮ
»» የተረኛው ገዢ ዲሞክራሲ ሲደመር የአውሮፓ ዲሞክራሲ ይሆናል ዜሮ
»» የሃይማኖት አባቶች ተብዬ ትምህርት ሲደመር የአሜሪካ ዲሞክራሲ ይሆናል ዜሮ
»» የእስላሙ ዓለም የአረቡ ዓለም ሲደመር የአሜሪካ ዲሞክራሲ ይሆናል ዜሮ
»» የምሥራቁ ዓለም እምነትና አገዛዝ ሲደመር ዲሞክራሲ ይሆናል ዜሮ ስለዚሀ የሁሉም ድምር ዜሮ ነው
ማለት ነው። በመሆኑም ከትውልዱ ሰው ሙሉ ሰው የጠፋው በዚህ ምክንያት ነው። ጠፊው ዘጠና
ዘጠኙን እጅ ይዟል፤ የሚቀረው ደግሞ አንድ እጅ ብቻ መሆኑ ቢያስደነግጥም እውነቱ ይህ ነው።
ይወሰዱባችሁና ተፈፃሚ ይሆኑ ዘንድ በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ለተካተታችሁት ከዚህ የሚከተለው
የቅጣት ትእዛዝ ወጥቶባችኋል።

ፈጥነው የሚፈፀሙ ከልዑል የተወሰኑባችሁ ቅጣቶችና ትአዛዞች

በመልእክት አምስት የተጠቀሰው ቅጣት እንዲህ ይላል፦ ቀጣዩ እርምጃ ኃይልና ጉልበቱ ሁሉ አሁን ከምናየው
በ49 እጥፍ ጨምሮ ተጭኖ መጥቷል። በተለይም እስካሁን እያላገጡ ባሉ መሪዎች /የፖለቲካው የሃይማኖቱም
የጦሩም የፀጥታውም የሃብቱም/ አዛዥ ናዛዞች ከነጭፍሮቻቸው የትም ቦታ ቢወተፉ በማያመልጡበት እሳት
ይጠረጋሉ። ሞትን ይራቧታል ይጠሟታል አያገኟትም ሞት ይሸሸጋቸዋል። ከተገኘላቸውም ብርቱ ስቃይን
አሳይቶ ይወስዳቸዋል።
ሞትን ስላገኙት እድለኞች ናቸው ብለው የቀሩት አምሳያዎቻቸው ይቀኑባቸዋል። የሰበሰቡት ሃብታቸው
ይጠፋል። ቤተሰቦቻቸውም አብረዋቸው ይጠረጋሉ። ለምልክት የሚተውላቸው ነገር በፍፁም አይኖርም።
የገነቡትም ይፈርሳል። የሰበሰቡትም ይበተናል። ወለዱ ዘርም አበዙ ወገን የጎጥ አምሳያቸውንም አደራጁ!
ያመልጣል ብለው ባሰቡበት የዓለም አካል ሁሉ ሸሸጉ የሚያመልጥ የለም እያዩት በብርቱ እሳት ይበላል።
ሁሉንም ጥፋት በቁማቸው ያዩታል። በስተመጨረሻ እነሱም ዘራቸውም የጥፋቱ መደምደሚያ ይሆናሉ። እነሱ
ጠፍተው ፍሬዎቻቸውም ተጠርገው የዲያብሎስ ምልክቱም ሳይቀር ሁሉም በቁማቸው ወደ ምድሪቱ የእሳት
ባሕር ይገባሉ። እንደዳታን ምድር ተከፍታ ወደ እሳት ጉያዋ ትከታቸዋለች። ምልክትም ታሪክም የማያነሳቸው
ይሆናሉ። በዚህ ጥፋታቸው መፈፀም ነፍሳቸው ወደ ሲኦል ለዘለዓለሙ እሳት ወደምትጠበቅበት ትገባለች። ይህ

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ይፈፀም ዘንድ በልዑል ፈቃድና ትእዛዝ በኔም በባሪያው በኩል በዚሁ መልእክት እንዲገለፅ ተደርጓል። ይላል
መልእክት 5 በገጽ 13 በአምስተኛው አንቀፅ ላይ ይህ ፍርድ የተገለፀው በ21/1/2004 ዓ.ም ነው።
በመጽሐፈ ኢዮብ በምእራፍ 18 ከቁጥር 5 እስከ 21 የተገለፀው የልዑል ኃይለ ቃል ከላይ የተገለፀውን
ውሳኔ ተግባራዊ ያደርገዋል። የቃሉም ዝርዝር በዚሁ ደብዳቤ ገጽ 11 ላይ ተገልፆአል።
በስምም በስልጣናችሁም በቡድናችሁም በየድርጅቶቻችሁም እናንተው በወደዳችሁት መለኪያ ባደረጋችሁ
የዘር አወቃቀራችሁም በመከላከያችሁም በደህንነታችሁም በኢትዮጵያ በተከላቸሁት ማናቸውም መዋቅሮቻችሁ
ሁሉ ልዑል በሚለየው በ2ኛ ደረጃ የምትቀጡ ደግሞ ሞትን ቶሎ አግኝታችሁ የምትሔዱ ልትሆኑ ትችላላችሁ።
በዚህ ጊዜ ከዚህ ውሳኔና ትእዛዝ በኋላ በፈጣሪ አጅ ለመውደቅ ብትጥሩ ይበጃችሁ ይሆናል በእኛ ግን
የተገለፃችሁት በሙሉ ተሰናብታችኋል። ለክፉው አሟሟትም ተላልፋችሁ ተሰጥታችኋል ፍርዱም ይኸው።
ቁጥር ጨብጦ የወጣው ይህ ደብዳቤም የሥራችን መጀመሪያ የኛንም ምንነት ማረጋገጫ ይሆንላችኋል።
በመከላከያ በደህንነት በፌዴራል በሚሊሽያነት በፖሊስነት በቀደመው በወያኔም ሆነ በዚህ በአብይ መንግሥት
ያገለገላችሁም ሆነ በማገልገል ላይ ያላችሁ በሙሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ እንደአገር እንደአንድ ሕዝብ በአንፃራዊ
ሰላም የነበረውን ሕዝብ ክዳችኋል። አገሪቱን ከዘረኞች ከዘራፊዎች አገርና ሕዝብን ከጠሉና እያፈረሱ ካሉ የዘር
ቡድኖች /ህወሃት፣ ብአዴን፣ ኦሀዴድ፣ ኦነጎች፣ ደሕዴድ የጋምቤላ የጉምዝና ቤንሻንጉል አፋር ሱማሌ/
ስም የተደራጁ ቡድኖች በአገሪቱ ሰልጥነው እስከሚያጠፏት አይታችኋል በናንተው ተጠቅመው ታዛችኋቸው
ገላችኋል አሥራችኋል አሳዳችኋል። አሁንም ይህን በማድረግ ላይ ናችሁ። ጄኔራልም ሆንክ ኮሎኔል ሻለቃ
ሻምበል የመቶ አለቃ እንዲሁም ተራ ወታደር እንደሰራኸው የአገር ክህደትና የወገን ደም ማፍሰስ በአንደኛ ደረጃ
ቅጣት ውስጥ እንድትካተቱ ተደርጓል።
ኤርትራ ፍርዷ ምን አንደሚሆን በመልአክት 1፤ 3፣ 5 የተገለፀ ሲሆን አገር የበተኑ የለዩ በዚህም
ምክንያት ብዙ የኢትዮጵያዊ ደም ያፈሰሱ በመሆናቸው ፍርዳቸውም በራሳቸው ስላለ እነሱንም ኢትዮጵያ
ውስጥ የሚፈፀው ሁሉ ይፈፀምባቸዋል።
ከዚህ ደብዳቤ መውጣት በኋላ በኢትዮጵያ ላይ ከላይ እንደተገለፀው ቅጣቱ ይፈሳል በዚያው ተከትሎ
በኢትዮጵያ መደበኛ ግዛትነት የሚካተቱ በቁጥር ስምንት የተገለፁ በኢትዮጵያ ዙሪያ ያሉ አገሮች የቅጣቱ ፍሰት
ወደነሱም በብርቱ ከብዶ ይቀጥላል የታዘዘው እስከሚፈፀም።
ከላይ በታዘዘውና በተወሰነው መሰረት ጥፋታችሁና መጠረጋችሁ ምንም አይነት ጊዜ ለስርጭትም ይሁን
ለምንም የሚሰጥ ጊዜ የለውም። የፈዴራሉ መንግሥት እጅ እንደደረሰ ቅጣቱ በትእዛዙ መሰረት ያለምንም
ቆያታና ዝግታ መተግበር ይጀምራል። ግዳጁንም እስከሚያጠናቅቅ በብርቱ ከብዶ ይቀጥላል።

ማጠቃለያ

እንግዲህ በጥቅሉ ለመግለፅ ያህል አብይ አህመድ የሚመሩት የከፋ ዘረኛ የእስላምና የመናፍቅ አክራሪ
ቡድን ከወላጆቹ ከወያኔ በሚበልጥ ስልትና ድርቅናም በጭካኔው ወደር ያልተገኘለትን የዘር እና የተዋሀዶ
እምነት ፍጅት አንግሶ አሻግራለሁ የሚል ዐይን ያወጣ ሹፈትና ፌዝ ቀላቅሎበት ዛሬም በዚያው ሊቀጥል
አንባገነንም ሊሆን እየተንደረደረ ነው። የሾሙት የሸለሙት በገንዘብ በሁለንተናዊ መልኩ እየደገፉ ያሉት
ዋናዎቹ ዲያብሎሶች እነአሜሪካ እነእንግሊዝ ወደፊት እንደምናየው የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም የሚለው
ብሂል ተፈፃሚ እንደሚሆን አያጠራጥርም። ጠፊዎች!! መልካም ወደሲኦል ጉዞ ይሁንላችሁ። ይሀ ደብዳቤ
ለእናንተ እንደተላከ ሁሉ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ለራሳቸው የፕሮቶኮል

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ቁጥር ጨብጦ ተልኮላቸዋል። እንዲሁም ለዋናዋናዎቹ ደጋፊዎቻችሁና ሞግዚቶቻችሁ /እነአሜሪካ እነእንግሊዝ


እነፈረንሳይ እነጀርመን እነካናዳ እነ አይ ኤም ኤፍ እነዎርልድ ባንክ እነሳውዲ አረቢያ እነአረብ ኤሜሬትስ
እነግብፅ አነቻይና እና ሌሎችም ለራሳቸውም ፕሮቶኮል ቁጥር የጨበጠ ደብዳቤ ተልኮላቸዋል በጥቅሉ የአንዱ
ደብዳቤ ለአንዱ እንዲያውቀው ስለተፈለገ አባሪ ተደርጎ ተልኮላችኋል።
ሥልጣን የእግዚአብሔር ነው። ለመልካም ሕዝብ መልካም እረኛ እግዚአብሔር ይሰጣል። ለክፉና
ለጠማማ የማያዳምጥ ቢነግሩትም የማይሰማ ትውልድ ደግሞ እንደዚያው ክፉና ጠማማ እረኛ ከእግዚአብሔር
ይታዘዝባችዋል። ልክ እንደኛው ዛሬ እየሆነ እንዳለው። ክፉው መሪ በዚያው ይፀናል ማለት አይደለም መጥረጊያ
ነውና! አገልግሎት እየሰጠ እንደሚያልቀው መጥረጊያ ክፉም መንግሥት ለቅጣት ውሎ እሱም ይወገዳል።
እውነቱ ይህ ነው።
የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ መሪዎች የነሱ ተቀዋሚ መሰል አጃቢና አድማቂዎች ድርጊታቸው ሁሉ እንደ ዝንብ
ነው። ዝንብ የበሽታ ሁሉ መንስኤ የክፉ ነገር ሁሉ ምሳሌ የተውሳክ ማደሪያ ናት። ዝንብ በሁሉም ስፍራ
የምትገባ አዋኪ የጤናም የሰላምም ጠንቅ ናት። ሰውንም እንስሳንም ባለ አካሉ ላይ ሁሉ እያረፈች የምታውክ
በሽታንም የምታሳቅፍ ናት። ስለዚህ ዝንብ ስለምን ትፈለጋለች ስለምንም። በውኃ በበረዶ በእሳት በጭስ
በመሳሰለው ሁሉ ማስወገድ እንጂ! ለምን ዝንብ አለን እንዳትሉ ይልቅስ ሥራችሁንና የዝንቢቱን ተግባር
አወዳድሩ ምንነታችሁን ከዚያው ታገኛላችሁ። እንዲያውም እንደእውነቱ ከሆነ አለቆቻችሁ ትልቁ እናንተ ታናሽ
ዝንብ ናችሁ። ከተማ የለመደው ዝንብ እሽ! ሲሉት ይሄዳል ለማስወገዱም ይቀላል። የበረሃው ዝንብ ንብን
የሚያክለውን፤ ገንዲን ከብት ጨራሹን በሽታ አምጭውን ተናዳፊውን ወጊውን አይነቱ የማይታወቀውን ገዳይ
ዝንብ ወይም የዝንቦች በኩር የሆነውን ዝንብ ናችሁ። ሕዝብን ለመጨፍጨፍ ምን እንዳደረጋችሁ ታውቁት
የለ! በገጠርና በከተማ የፈሰሰውን ጋጠ ወጡን እንደእንስሳ የሚያስበውን ከሚበላው ከሚጠጣው በቀር ስለምንም
የማይጨንቀውን እንደመንጋ የሚነዳውን አደራጅታችሁ አስታጥቃችሁ ገንዘብ አፍስሳችሁ ፍጅ ግደል ቤተ
ክርስቲያንን አቃጥል ዝረፍ ድፈር እረድ ብላችሁ በጦራችሁ አጅባችሁ የምታሰማሩ ጉዶች እኮ ናችሁ።
አገር አለኝ መንግሥት አለኝ ብሎ እንደቀደምት መንግሥት መስሎት ለሥራ ለትምህርት ለአምልኮ ለተለያየ
ጉዳዩ የሚሰማራውን ሕዝብ ያሳረዳችሁ ያስገደላችሁ የዝንብም ክፉው ዝንብ ናችሁ። የመንግሥት ስም ሥራ
ኃላፊነት በጉልበታችሁ ጨብጣችሁ መንጋ ያሰማራችሁ ሌላ ምን ስም ይሰጣችሁ አጥቼ እንጂ በደረብኩላችሁ።
ለማንኛውም ክብራችሁ በነውራችሁ በቅሌታችሁ ነውና! ለእናንተ የታዘዘው የሞት ሁሉ በኩር ነው። እያንገላታ
እያሰቃየ አሳር እያሳዬ ለተመልካቹ የሚዘገንን መከራን እያወረደ ሞትን በብርቱ እንድትፈልጓት እያደረገ
ስትገኝላችሁም የሽልማት ያህል እንዲቆጠር እያደረገ ይጨርሳችኋል። አለን እምትሉትን ሥልጣን እንኳን እናንተ
የናንተም ኃያል ጌቶች አምላኮቻችሁ፤ እነባቢሎን እነአንግሊዝ እነቻይና አነጀርመን እነፈረንሳይ እነአረብ
እስላም ሁሉም ኢትዮጵያ ጠሎች ተዋህዶ እምነትን ናቂዎች እንደናንተው ከእናንተም በሚከፋ ተሰቃይተው
ሞትን ለምነው ደም አልቅሰው ወርቅ እንቋቸውን ብራቸውን ገብረው ስልጣንን ሁሉ እግር ልሰው ያስረክባሉ።
እናንት አስገባሪዎች አስጨንቃችሁ አስጠብባችሁ ግብሩን ሁሉ ጭናችሁ የምታስወልዱ እናንተም ላይ ይህ
ሲፈፀም ለቀሪው ትምህርት ይሆናል።
በዚህ ደብዳቤ መሰረት ቁጥር የጨበጠ ትእዛዝና ውሳኔ መሆኑን ከላይ ገልጫለሁ። የሥራችንም መጀመሪያ
ይህ ደብዳቤ የጨበጠው ትእዛዝና ውሳኔ መተግበር መሆኑን አረጋግጥላችኋለሁ።
ከዚህ ደብዳቤ ጋር በልዑል ፊት ከከበሩት ዋና ዋና ሊቃነ መላእክቶች --- ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፤
ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል፤ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ትእዛዙንና ውሳኔውን ለመፈፀም በኃያል
ሙላት ተነቃንቀዋል።

17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

በስተመጨረሻ እንደ ልዑል ፍላጎት እንደ ድንግል ምኞትም መሻትም ሁሉም የሰው ዘር በእቅፋቸው
ቢሰበሰብ ፍፁም ፈቃዳቸው ነበር። ይህን ሁሉ ዘመናት በታላቅ ትእግሥት የጠበቁትም በዚሁ ለሰው ባላቸው
ፅኑ ፍቅር ነበር። አልሆነም እንጂ፤ አንደሰማችሁት እንደተረጋገጠው ተራፊው አንድ እጅ ጠፊው ዘጠኝ አጅ
/ለኢትዮጵያ/ መሆኑን፤ ስለ ቀሪው ዓለም ግን ወገኖቼ ልገልፀው ስለሚከብድ መተው የተሸለ ነው።
እኛም ታናሽ የልዑል ባሮች ምኞታችን ሰው ሁሉ ቢድን ነበር፤ ግን ምኞት ሆነብን እንጂ እንደ ኖኅ ዘመን
ልዑል ጥቂቶችን እንደባረከ ከቁጣውና ከመቅሰፍቱ ከጠረጋው የተረፉትን ይባርካቸው።
እናንት ተሰናባቾችም በምርጫችሁ ነውና መልካም ስንብት በምንም መልኩ ወደ እኔ ለመምጣት አትሞክሩ።
ይህን ደብዳቤ ሳዘጋጅ በጎጆ መጥታችሁ አውካችኋል በመሆኑም ቀይ መስመር አልፋችኋል ለዚህ ደግሞ
በየቀበሌው የኮለኮላችኋቸው ደካሞች ገቢ ነን፤ ደንብ ነን ፖሊስ ነን አደረጃጀት ነን የሚሉ ሁሉ ዘወትር
የሰውን ቤት ሲደፍሩና ሲያውኩ ይታያል። ፊታችሁን ለማየት የሚያስችል ትእግሥት የለኝምና በ3ኛ ወገን
ሃሳብ ካላችሁ እሰማዋለሁና!! አትድረሱብኝ የመጨረሻው ማስጠንቀቂያዬ ነው። እጅ ለመስጠት፤ ለመንበርከክ
ስትገደዱ ያኔ አደምጣለሁ! የልዑልም የድንግልን ፈቃድ ጠይቄ ስታዘዝ ሊሆን የሚገባውን ሁሉ እንደታዘዝኩት
አከናውናለሁ። እኔም ሆንኩ ወንድም እህቶቼ የልዑልና የድንግል አገልጋዮች ሙሉ በሙሉ አሰናብተናችኋል።
ማዳን መማር የእግዚአብሔርና የድንግል ሥልጣን ነው። አንዳንዶችን ለኛ መቀበሉ ቢከብደንም እንደበላየሰብ
ሊድኑ ይችሉ ይሆናል። ግድ ነውና እንቀበላለን። እግዚአብሔር የማረውን ድንግልም የተቀበለችውን ማንም
መኮነን አይችልምና!
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን
ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል እናቴ ስሟ የተመሰገነ ይሁን!
ቅዱሳን ሊቃነ መላእክቶች ሁሉም ስማቸው የተመሰገነ ይሁን ሰማዕታት ቅዱሳን አባቶቼ እናቶቼ ስማቸው
ይባረክ አሜን!!
ከሰላምታ ጋር

ፊርማ
ታናሽ የሚሆን የሥላሴ ባሪያና የታመነ አገልጋይ
የድንግል የታመነ አገልጋይ የቅዱሳን ሊቃነ መላእክት አገልጋይ

18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር


ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት

ቀን፡

ቁጥር፡

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ


አሜን!!
ጉዳዩ፡- የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እረኞች በልዑልና በድንግል ፊት ተመዝነው
ስለተሰጣቸው ኃላፊነትና የእረኝነት ተግባር በጣት ከሚቆጠሩ በቀር ፍፁም አንሰው በመገኘታቸው መሰናበታቸውን
ስለማሳወቅ ይመለከታል። በነሱ ምትክ ልዑል የታመኑ ባሮቹንና እረኞችን መቀባቱንና መሾሙን ይታወቅ ዘንድ
በተጨማሪ ማሳወቅን ይመለከታል።
የተከበራችሁ አባቶቼ አስቀድሜ በትህትና በልዑልና በወላዲተ አምላክ ስም የአክብሮት ሰላምታዬን በትህትና
ጎንበስ ብዬ አቀርባለሁ።፡ አስቀድሜ ስለማንነቴ ብገልፅ መልካም እንደሆነ ይሰማኛል።
እኔ አንድ ድሃ ምስኪን ከጎስቋላ ቤተሰብ የተገኘሁ ከስረ መሰረቴም የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ
ምእመን ነኝ። እናንተ ጨዋ እንደምትሉት ማለት ነው። ይህን ደብዳቤ እንድፅፍላችሁ የሆነው ከልዑል ኃያል
ጌታ በመታዘዜ እንደሆነ በቅንነት እንድትረዱልኝ በአክብሮት እገልፅላችኋለሁ።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በሚል ከመልእክት አንድ እስከ መልእክት ስምንት እንዲሁም አዋጅን የያዘ
ለሕዝብ ያልተገለፀ መልእክት 7 ሲቀር ለሕዝብም ለመላው የሰው ዘርም ለ15 ዓመታት ሳደርስ ቆይቻለሁ።
ለእናንተም በአደራ ፖስታ እንዲደርሳችሁ አድርጌአለሁ። ግን ማንም አባት ጉዳዬ ብሎ የገለፀ ወይም እውነት
ነው ወይ አይደለም ብሎ ከፈጣሪው ጠይቆ ያስተማረም የመከረም የለም። እንዲያውም በአንዳንድ የክብረ በአል
ቦታ ወረቀት የሚበትን ሃሰተኛ ሰው አለና እንዳትሰሙ ተብሎም ሲነገር እንደነበር አረጋግጫለሁ። ለማንኛውም
እኔም ተሰደብኩ ተነቀፍኩ አንድ ተራ ሰው ነኝ መልእክቱ ግን ከልዑል ዘንድ የመጣ በመሆኑ ያቃለላችሁት
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ነበርና አውቆ አጥፊ ሆናችኋል። ብዙ አባቶች እየተላኩ ሊመክሯችሁ ከልዑል
የተላከውንም ሊነግሯችሁ ሞክረዋል። አልተቀበላችኋቸውም።፡ ዛሬም ይህ ቁጥር ጨብጦ ወደ እናንተ የደረሰው
መልእክት አይደለም ደብዳቤ እንጂ! ከእግዚአብሔር የታመኑ ባሮች የተላከ ደብዳቤ። ምክር ተግሳፅ ቅጣት
ከእግዚአብሔር የሚመነጩ እረኞች በአግባቡ በጎቹን እንዲያሰማሩ ለማድረግ የሚሰነዘር የልዑል እግዚአብሔር
የፍቅር በትር ነበር፤ ግን እናንተ በምክሩ በተግሳጹ ከመጠቀም ይልቅ መልእክት አድራሹን በመናቅ በማጣጣል
በመስደብ ተጠመዳችሁ። ስለኔ ያላችሁትን ሁሉ መናገር ባያስፈልግም ያልተሰጠኝ ስም የለም። ለመሆኑ
ሰው ሁሉ የእግዚአብሔር ፍጡር አይደለም እንዴ ምናምንቴ ቢሆን ቢደኸይ ቢያጣ ቢነጣ እግዚአብሔር

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

በአንደበቱ ሊናገር የሚከለክለው አለን? የበለአም አህያ የነብዩን እብደት ለማገድ አንደበት ብታወጣ ብትናገር
ስለመደብደቧም በትህትና ብትናገር ነብዩ ሰማትን አልሰማትም እንዲያውም ዱላውን አከበደባት እንጂ! በሰው
አንደበት መናገሯም አላስደነገጠውም። እኔኮ ሰው ነኝ። እርግጥ በእውቀቱ በትምህርቱ በሥልጣኑ በክብሩ
በሁሉም እጥጋችሁ የማልደረስ አንድ የእግዚአብሔር ድሃ ነኝ። ምስኪን ድሃ ጠላት ዲያብሎስ በብርቱ
ያደቀቀኝ። ይሁን ጨዋውን ምእመን፤ እንደበለኣም አህያ የሚቆጠረውን እንደኔ አይነቱን ሰው በሰውነቴ
ከምታዩ ይልቅ ለምን ቃሉን አትሰሙም ነበር? ከየት የመጣ ነው ከኛ ያለፈ ቃል የሚናገረው እያላችሁ ሁሉንም
ከምትነቅፉና ከምትንቁ በውኑ ይህ እውነት ነውን? ይህ ሰው የሚናገረው እውነትነት አለወይ? ብላችሁ ልዑልን
ለምን አትጠይቁም? አንዴ ደቂቀ ኤልያስ ነው አንዴም የንቡረእድ ኤርሚያስ ተከታይ ነው / ከሳቸው የዓለሙ
መፋረጃ ከሚለው ስእል መልካም የመሰለኝን ስለተጠቀምሁ/ ቅዝታም ነው ሰላይ ነው ምን ስፍር ቁጥር አለው
የማልባለው የለም። ይሁን እንጂ እኔ የምትሉትን ሁሉ አይደለሁም። ጆሯችሁን ኮርኩሩና አዳምጡ እኔ ድሃ
ያልተማርኩ ተራ የኢትዮጵያ ተዋሀዶ ኦርቶዶክስ እምነት አማኟና ተከታይ ነኝ።
ከልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ የሚልን ቃል እናገኘለን! እናንተን በአሁኑ ሰዓት እንድትመዘኑ የተደረገበት
የእግዚአብሔር ቃል ነው። ከዚህም በላይ በዋናነት የተመዘናችሁበት የልዑል ቃል በትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ
ሰላሳ አራት በሙሉ የተገለፀው ኃይለ ቃል ነው። የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፡

ለኢዮሳፍጥም ብዙ ብልጥግናና ክብር ነበረው። ለአክአብም ጋብቻ ሆነ። ከጥቂት


አመት በኋላም ወደ አክአብ ወደ ሰማርያ ወርደ አክአብም ለእርሱና ከእርሱ ጋር
ለነበሩት ሕዝብ ብዙ በጎችንና በሬዎችን አረደ። ከእርሱም ጋር ወደ ሬማት ዘገለአድ
ይሄድ ዘንድ አባበለው። የእስራኤልም ንጉስ አክዓብ የይሁዳን ንጉሥ እዮሳፍጥን
ከኔ ጋር ወደ ሬማት ዘገልአድ ትሔዳለህን? አለው። እርሱም -- እኔ እንዳንተ ነኝ
ሕዝቤም እንደ ሕዝብህ ናቸው፤ በሰልፍም ከአንተ ጋር እንሆናለን ብሎ መለሰለት።
ኢዮሳፍጥም የእስራኤልን ንጉሥ የእግዚአብሔርን ቃል አስቀድመህ ትጠይቅ ዘንድ
እለምንሃለሁ አለው። የእስራኤልም ንጉስ ነቢያቱን አራት መቶ ሰዎች ሰብስቦ ወደሬማት
ዘገለአድ ለሰልፍ ልሂድን? ወይስ ልቅር አላቸው።፡ እነርሱም -- እግዚአብሔር
በንጉሥ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ውጣ አሉት። እዮሳፍጥ ግን -- እንጠይቀው ዘንድ
የእግዚአብሔር ነብይ የሆነ ሌላ ሰው በዚህ አይገኝምን አለ። የእስራኤልም ንጉሥ
እዮሳፍጥን እግዚአብሔርን የምንጠይቅበት አንድ ሰው አለ ነገር ግን ሁልጊዜ ክፉ
እንጂ ከቶ መልካም ትንቢት አይናገርልኝምና እጠላዋለሁ ፡ እርሱም የይምላ ልጅ
ሚኪያስ ነው አለው። -- ኢዮሣፍጥም -- ንጉሥ እንዲህ አይበል አለው። የእስራኤልም
ንጉሥ አንድ ጃንደረባ ጠርቶ -- የይምላን ልጅ ሚኪያስን ፈጥነህ አምጣው አለው።
የእስራኤል ንጉሥና የይሁዳ ንጉሥ እዮሣፍጥ ልብሰ መንግሥት ለብሰው በሰማርያ
በር መግቢያ አጠገብ በአደባባይ በዙፋኖቻቸው ላይ ተቀምጠው ነበር። ነቢያትም ሁሉ
በፊታቸው ትንቢት ይናገሩ ነበር። የክንዓና ልጅ ሴዴቅያስም የብረት ቀንዶች ሰርቶ
-- እግዚአብሔር እንዲህ ይላል -- ሶርያውያንን እስኪጠፉ ድረስ እንደዚህ ትወጋለህ
አለ። -- ነቢያትም ሁሉ እግዚአብሔር በንጉሥ እጅ አሳልፎ ይሰጣታልና ወደ ሬማት
ዘገለአድ ሂድና ተከናወን እያሉ እንዲሁ ትንቢት ይናገሩ ነበር። ሚኪያስንም ሊጠራ
የሄደ መልእክተኛ -- እነሆ ነቢያት በአንድ አፍ ሆነው ለንጉሥ መልካም ይናገራሉ
፡ ቃልህም እንደቃላቸው እንዲሆን መልካም እንድትናገር እለምንሃለሁ አለው።-
- ሚኪያስም ሕያው እግዚአብሔርን አምላኬ የሚለውን እርሱን እናገራለሁ አለ።
ወደ ንጉሡምም በመጣ ጊዜ ንጉው -- ሚኪያስ ሆይ ወደሬማት ዘገለአድ ለሰልፍ
እንሂድን? ወይስ እንቅር? አለው። እርሱም ውጣ ተከናወን በእጅህም አልፈው ይሰጣሉ

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

አለ። ንጉሥም -- በእግዚአብሔር ስም ከእውነት በቀር እንዳትነግረኝ ስንት ጊዜ


አምልሃለሁ? አለው። እርሱም እስራኤል ሁሉ ጠባቂ እንደሌላቸው በጎች በተራሮች
ላይ ተበትነው አየሁ ፡ እግዚአብሔርም--- ለእነዚህ ጌታ የላቸውም እያንዳንዱም
በሰላም ወደ ቤቱ ይመለስ አለ። ብሎ ተናገረ። የእስራኤልም ንጉሥ እዮሳፍጥን ፡
- - ክፉ እንጂ መልካም ትንቢት አይናገርልኝም አላልሁህምን? አለው። ሚኪያስም
አለ ፡-- እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር በዙፋኑ ተቀምጦ
የሰማይ ሰራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ። እግዚአብሔርም፤-- ወጥቶ
በሬማት ዘገለአድ ይወድቅ ዘንድ የእስራኤልን ንጉሥ አክዓብን የሚያታልል ማነው?
አለ ፡ አንዱም እንደዚሀ ሌላውም አንደዚያ ያለ ነገር ተናገረ። መንፈስም መጣ
በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ ፡ -- እኔ አታልለዋለሁ አለ ፡ -- እግዚአብሔርም
በምን አለው። እርሱም ወጥቼ በነቢያቱ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ እሆናለሁ አለ።
እግዚአብሔርም ታታልለዋለህ ይቀናሃል ውጣ እንዲሁም አድርግ አለ። አሁንም እነሆ
እግዚአብሔር በእነዚህ በነቢያት አፍ ሐሰተኛ መንፈስን አድርጓል እግዚአብሔርም
በአንተ ላይ ክፉ ተናግሮብሃል። የከንዓንም ልጅ ሴዴቂያስ ቀረበ ሚኪያስንም በጥፊ
መታውና -- የእግዚአብሔር መንፈስ ከአንተ ጋር ይናገር ዘንድ በምን መንገድ ከኔ
አለፈ አለ። ሚኪያስም እነሆ በዚያ ቀን ልትሸሸግ ወደ እልፍኝህ ስትሄድ ታያለህ
አለ። የእስራኤልም ንጉሥ -- ሚኪያስን ውሰዱ ወደከተማይቱም አለቃ ወደ አሞን
ወደ ንጉሠም ልጅ ወደ ኢዮአስ መልሳችሁ -- ንጉስ እንዲህ ይላል -- በደህና
እስክመለስ ድረስ ይህን ሰው በግዞት አኑሩት የመከራም እንጀራ መግቡት የመከራም
ውኃ አጠጡት በሉ አለ። ሚኪያስም በደህና ብትመለስ እግዚአብሔር በኔ የተናገረ
አይደለም አለ። ደግሞም እናንተ ሕዝብ ሁሉ ስሙኝ አለ። ------ መጽሐፈ ዜና
መዋዕል ካልእ ምእራፍ 18 ከቁ 1 --- 26
ይህን ታሪክ ለእናንተ ልጠቅስ ያስገደደኝ ምክንያት በዚህ ነው። አባቶቼ እናንተ በእምነታችን በተዋህዶ
ቤታችን በቤተ ክርስቲያናችን ትልቁን ሥፍራ የያዛችሁ ናችሁ። በጵጵስና ማእረግ በሲኖዶስ ሁሉን ታዩ ዘንድ
እግዚአብሔር ከራሱ ቀጥሎ በታላቅ ሥፈራ ያስቀመጣችሁ የታላቁ የእግዚአብሔርም የድንግልም ሕዝብ የሆነው
ምእመን እረኛ ናችሁ። ይህን ሁሉም ያውቀዋል። ታዲያ ስታጠፉ ማን ይውቀሳችሁ አዎን እግዚአብሔር ነው።
እግዚአብሔር እንዴት ይናገራችሁ በመረጠው በፈቀደው መንገድ አይደለም? አዎን ነው። ወደ እናንተ እየተላኩ
የሚመጡ ብዙ የልዑል መልእክተኞች ከአውደ ምሕረት ከየባእታችሁ ያባረራችኋቸውን በዘበኛ የተቀጠቀቱን
ለአሳሪ መንግሥት ተላልፈው የተሰጡትን አታስታውሷቸውም እግዚአብሔር ሥራችሁን መዘነ ወቀሰ፤ ገሰፀ፤
አስጠነቀቀ ፤ አልሰማችሁም ። ከላይ በእግዚአብሔር ቃል እንዳያችሁት፤ ስንት ሚኪያሶችን በጥፊ በሚበልጥ
መታችሁ።
ከኛ በምን አልፎ አይደል እንዴ የምትሉት። ያለውን ዘረኛ መንግሥት የምትመርቁ አይደላችሁም እንዴ
ሕዝበ ክርስቲያኑ ሲፈጅ ቤተ ክርስቲያን ሲቃጠል አገልጋዮች ሲታረዱ ምን አደረጋችሁ። ለይምሰል
ውግዘት ምን ትርጉም አለው።፡ ወዲያው ከእስላሟ ከመናፍቁ የመንግሥት ተብዬ ልኡካን ጋር የምትደራደሩ
አልፋችሁም በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር ለከተማው አስተዳደር የምትለግሱ በስልት የተዋህዶን ሕዝብና ቤተ
ክርስቲያንን የሚያስፈጀውን መሪ እንኳን ተሸለምክልን ደስ ብሎናል የምትሉ ከሚኪያስ ተፃረው እንደቆሙት
400 ነቢያት የመንግሥትን የተቀናበረ ጥፋት ፈፃሚዎችን ከመመረቅ አልፋችሁ የምእመኑን ገንዘብ ዝቃችሁ
የምትሰጡ ከእናንተ በተቀበሉት ገንዘብ ቄሮ ዘረኛ አጥፊ መንጋ አደራጅተው እንዲዘምቱብን ያገዛችሁ። በውኑ
የምትሠሩትን ውጤቱንስ አውቃችሁታል? መቼም ይህ ይጠፋችኋል ብዬ አላስብም። ሚኪያስ እንደተናገረው
የእስራኤል ንጉሥ ሞተ እንጂ ተመልሶ በሕይወት አልመጣም እሬሳው እንጂ። ዛሬ የምትመርቋቸው ገዢዎች

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ነገ አታይዋቸውም እናንተም በግብር መስላችኋቸዋልና የልዑል ፍርድ መጥቶባችኋል። እግዚአብሔር እውነትን


የሚያፀድቁ እሱንም የሚፈሩ የሚታዘዙትን አገልጋይ ባሮቹን መርጧል። በእስራኤል መልካም ዘመን የቤተ
ክህነቱ ዋና የነበረው ሊቀ ካህን ኤሊ ረጅም ዘመን ከ40 ዓመታት በላይ ቤተ ክርስቲያንን ያገለገለ ነበር።
ይሁንና ቀደም የነበረው ትጋቱ መታመኑ ጠፍቶ ልማዳዊ ሕይወትን አነገሰ። አፍኒንና ፊንሐስ የሚባሉ ሁለት
ልጆች ነበሩት ሁለቱም ምናምነቴዎች ነበሩ በቤተ እምነቱ ከጋለሞቶች ጋር ይተኙ ነበር። ኤሊም ይህንን
ክፉ ሥራቸውን ሰምቶ አልገሰፃቸውም ብርቱም እርምጃ አልወሰደም። እግዚአብሔርም በአባትም በልጆችም
አዝኖ ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ ፍልስጤምና የእስራኤል ሕዝብ ውጊያ ገጥመው ነበር።፡ የእስራኤል ታቦተ
ጽዮን ወደ ውጊያው ዘምታ ነበር። አጅበው የሔዱት ደግሞ አፍኒንና ፊንሃስ ነበሩ። ውጊያው በረታ አፍኒንና
ፊንሐስ ሞቱ። ታቦተ ጽዮን ተማረከች። ኤሊም የልጆቹን ሞትና የጽዮንን በፍልስጤም መማረክ ሲሰማ ደንግጦ
ከተቀመጠበት ወንበር ወደቀ ሞተም።
ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን የነገሰው ማነው? ስንቶች አፍኒንና ፊንሃሶች አሉ? ስንቶቻችሁ የኤሊን እጣ
ትጠብቁ ይሆን? የእናንተ እረኝነት ከዚህ በታች በማሰፍረው የልዑል ኃይለ ቃል ተመዘነ። ፍርዳችሁም ወጣ።
የእግዚአብሔር ኃይለ ቃል ወደ እኔ እንዲሀ ሲል መጣ! ይላል የታመነው የልዑል ባርያ ሕዝቅኤል በትንቢት
ቃሉ በምእራፍ 34

የሰው ልጅ ሆይ ትንቢት ተናገር በእስራኤል እረኞች ላይ ትንቢት ተናገር፤----


እረኞችንም እንዲህ በላቸው፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እራሳቸውን
ለሚያሰማሩ ለእስራኤል እረኞች ወዮላቸው! እረኞች በጎችን ያሰማሩ ዘንድ
አይገባቸውምን? ጮማውን ትበላላችሁ ጠጉሩንም ትለብሳላችሁ የወፈሩትን
ታርዳላችሁ በጎቹን ግን አታሰማሩም። የደከመውን አላፀናችሁትም፣ የታመመውንም
አላከማችሁትም የባዘነውንም አልመለሳችሁትም የጠፋውንም አልፈለጋችሁትም
በኃይልና በጭቆናም ገዛችኋቸው። እረኛንም በማጣት ተበተኑ ለምድርም አራዊት
ሁሉ መብል ሆኑ ተበተኑም። በጎቼ በተራሮች ሁሉና በረዘሙ ኮረብቶች ሁሉ ላይ
ተቅበዝብዘዋል በጎቼም በምድር ፊት ሁሉ ላይ ተበትነዋል። የሚሻም የሚፈልግም
አልነበረም። ስለዚሀ እረኞች - ሆይ! የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ -- ጌታ እግዚአብሔር
እንዲህ ይላል ፡ -- እኔ ሕያው ነኝና እረኛ ስለሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ
እረኞችም እራሳቸውን እንጂ በጎቼን ስላላሰማሩ በጎቼ ንጥቂያ ሆነዋልና በጎቼም
ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆነዋልና! ስለዚህ እረኞች ሆይ የእግዚአብሔርን ቃል
ስሙ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ በእረኞች ላይ ነኝ በጎቼንም ከእጃቸው
እፈልጋለሁ በጎቼንም ከማሰማራት አስተዋቸዋለሁ። ከዚያም ወዲያ እረኞች እራሳቸውን
አያሰማሩም በጎቼንም ከአፋቸው አድናለሁ። ሙብልም አይሆኑላቸውም።፡ ጌታ
እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና ፡ -- እነሆ እኔ እራሴ በጎቼን እሻለሁ እፈልግማለሁ
እረኛ በተበተኑት በጎች መካከል ባለ ጊዜ መንጋውን እንደሚፈልግ እንዲሁ በጎቼን
እፈልጋለሁ። በደመናና በጨለማ ቀን ከተበተኑበት ሥፍራ ሁሉ አድናቸዋለሁ።
ከአሕዛብም ዘንድ አወጣቸዋለሁ። ከአገሮችም እሰበስባቸዋለሁ። ወደ ገዛ አገራቸውም
አመጣቸዋለሁ። በእስራኤልም ተራሮች ላይ በፈሳሾችም አጠገብ በምድርም ሰዎች
በሚኖሩበት ሥፍራ ሁሉ አሰማራቸዋለሁ ፡ በመልካም ማሰማሪያ አሰማራቸዋለሁ።
ጉሮኗቸውም በረጅሞቹ በእሥራኤል ተራሮች ላይ ይሆናል። በዚያም በምልጃም ጉሮኖ
ውስጥ ይመሰጋሉ ፡ በእስራኤል ተራሮችም ላይ በለመለሙ ማሰማሪያ ይሰማራሉ። እኔ
እራሴ በጎቼን አሰማራለሁ አስመሥጋቸዋለሁ ይላል ጌታ እግዚአብሔር የጠፋውንም
እፈልጋለሁ የባዘነውንም እመልሳለሁ ፡ የተሰበረውንም እጠግናለሁ። የደከመውንም

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

አፀናለሁ። የወፈረውንና የበረታውንም አጠፋለሁ። በፍርድም እጠብቃቸዋለሁ። ጌታ


እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ፡-- እናንተም መንጋዬ ሆይ እነሆ በበግና በበግ መሃከል
በአውራ በግና በአውራ ፍዬልም መካከል እፈርዳለሁ። የቀረውን ማሰማሪያችሁን
በእግራችሁ የረገጣችሁትን በመልካሙ መሰማሪያ መሰማራታችሁ ባይበቃችሁ ነውን?
የቀረውንስ ውኃ በእግራችሁ ያደፈረሳችሁት ጥሩውን ውኃ መጠጣታችሁ ባይበቃችሁ
ነውን? በጎቼም በእግራችሁ በረገጣችሁት ይሰማራሉ። በእግራችሁ ያደፈረሳችሁትን
ይጠጣሉ። ስለዚሀ ጌታ እግዚአብሔር እንዲሀ ይላቸዋል፦- እነሆ እኔ በወፈሩት
በጎችና በከሱት በጎች መካከል እፈርዳለሁ እስክትበትኗቸው ድረስ በእንቢያና በትከሻ
ስለምትገፏቸው የደከሙትን ሁሉ በቀንዳችሁ ስለምትወጓቸው ስለዚህ መንጋዬን
አድናለሁ። ከእንግዲህ ወዲህ ንጥቂያ አይሆኑም በበግና በበግ መሃከልም እፈርዳለሁ።
በላያቸውም አንድ እረኛ አቆማለሁ። እርሱም ያሰማራቸዋል። እርሱም ባሪያዬ
ዳዊት ነው። ያሰማራቸዋል እረኛም ይሆናቸዋል። እኔም እግዚአብሔር አምላክ
እሆናቸዋለሁ። ባሪያዬም ዳዊት በመካከላቸው አለቃ ይሆናል። እኔ እግዚአብሔር
ተናግሬአለሁ። የሰላምን ቃል ኪዳን ከእነርሱ ጋር አገባለሁ። ክፉዎችንም አራዊት
ከምድር አጠፋለሁ። ተዘልለውም በምድረ በዳ ይኖራሉ። በዱርም ውስጥ ይተኛሉ።
እነርሱንና በኮረብታዬ ዙሪያ ያሉትን ስፍራዎች ለበረከት አደርጋቸዋለሁ። ዝናቡንም
በጊዜው አወርዳለሁ የበረከት ዝናብ ይሆናል። የምድረበዳም ዛፍ ፍሬውን ይሰጣል።
ምድርም ቡቃያዋን ትሰጣለች። በምድራቸውም ተዘልለው ይኖራሉ። የቀንበራቸውንም
ማነቆ በሰበርሁ ጊዜ ከሚገዟቸውም እጅ ባዳንኋቸው ጊዜ እኔ እግዚአብሔር
እንደሆንሁ ያውቃሉ። እንግዲህም ለአሕዛብ ንጥቂያ አይሆኑም፤ የምድርም አራዊት
አይበሏቸውም፤ተዘልለውም ይቀመጣሉ። የሚያስፈራቸውም የለም። የዝናን ተክል
አቆምላቸዋለሁ። እንግዲህም ከራብ የተነሳ በምድር አያልቁም። የአህዛብንም ስድብ
ከእንግዲህ ወዲህ አይሸከሙም። እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው ከእነርሱ ጋር እንዳለሁ
እነርሱም የእስራኤል ቤት ሕዝቤ እንደሆኑ ያውቃሉ። ይላል ጌታ እግዚአብሔር።
እናንተም በጎቼ የማሰማሪያዬ በጎች ሰዎች ናችሁ። እኔም አምላካችሁ ነኝ ይላል ጌታ
እግዚአብሔር። ትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ 34 በሙሉ።
ከላይ በእግዚአብሔር ቃል እንደተገለፀው የዛሬው አባቶቻችን ምን ይመስላሉ? የሚለውን ብናይ ፡-- ዛሬ
በየገጠሩ በየበረሃው ያሉ ቤተ ክርስቲያናት ገዳማት በነሱ ሥር ያሉ የአብነት ትምህርት ቤቶችስ እምን ላይ ናቸው?
እውነት ነው የገጠሩ ቤተ ክርስቲያናችን እንዲሁም ገዳማት በፍፁም ማጣት ውስጥ የወደቁ አገልጋዮቻቸው
የተበተኑ ቢኖሩም አልፎ አልፎ ከምእመኑ በሚደረግላቸው ምፅዋት ለመሰንበት የሚታገሉ ናቸው። ገዳማት
ለከተማ የቀረቡ እንደደብረ ሊባኖስ አይነት ካልሆኑ የተቀሩት በእጦት የተበተኑ ተማሪዎቻቸው መምህራኖቻቸው
የተሰደዱባቸው ናቸው። ጥሬና አቡጀዲ የሚሰጣቸው አጥተው የተዘጉ ብዙዎች ናቸው። በከተሞች ያሉ ቤተ
ክርስቲያናት በአብዛኛው በቅጥራቸው ዙሪያ ሕንፃ ገንብተው የሚያከራዩ ከከተማው ሕዝብም በተለያየ መንገድ
ገቢ የሚያገኙ ናቸው። የተለያየ ንግድም ውስጥ የገቡ ናቸው። አባቶች ጳጳሳት ካህናት ዲያቆናት በተለያየ
መንገድ ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ሕንፃ የገነቡ የሚያከራዩ በዘመኑ መኪና የሚንፈላሰሱ ትልልቅ ባለሃብቶችን በንስሓ
ልጅነት ይዘው የበለፀጉ ናቸው። ይህም አንሷቸው በለበሱት ካባ በሚጠሩበት ከፍተኛ መንፈሳዊ ማእረጋቸው
የክህደት ትምህርትን ኑፋቄን ተሃድሶን ቅባትን ካቶሊክነትን ያለሃፍረት በማስፋፋት ላይ ያሉ መሆናቸው አንዱ
የጨለማው ገዢ አገልጋይነታቸው ማረጋገጫ ነው። ከመናፍቃን ከካቶሊኮች ከእስላሞች ጋር ከሌሎችም ፍፁም
የተዋህዶ ተፃራሪዎች ጋር ሕብረት ፈጥረው የፖለቲካው ስውርም ግልፅም መሳሪያ ሆነው ተገኝተዋል። በየቤተ
ክርስቲያኑ የመንግሥት የደህንነት ቢሮ እንዲቋቋም አድርገው ሕዝብ እንዲሰለል ያደርጋሉ ዛሬም እያደረጉ ነው።
እውነተኛ የተዋህዶ እምነት አገልጋይ ካህናትን መምህራንን ዓይናማ ሊቃውንትን አባረውና አጥፍተው ከውጪ
የመናፍቅና የካቶሊኮች ኮሌጆች ድግሪ የሰበሰቡትን በጵጵስና ኮልኩለው ተገኝተዋል። ቤተክርስቲያን ለሚያፈርስ

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ለሚያቃጥል መንግሥት የበጀት ድጋፍ አድርገዋል። የክህነት የጵጵስና ሹመቶች በገንዘብ እንዲሰጡ አድርገዋል።
በፖለቲካው ኃይል እየታዘዙ ሹመትንም ሰጥተዋል። ዛሬ ስለናንተ ምንነት መዘርዘር መጽሐፍ የመፃፍ ያክል
በመሆኑ ልግታው። እንግዲህ ቤተክርስቲያንን ከእናንተ የበለጠ ያፈረሳት ከዶክትሪኗ ከቀኖናዋ ያወጣት አለ
ወይ? እነአቡነ ተክለሃይማኖት እነአቡነ ሃብተ ማርያም ሌሎችም ታላላቅ አባቶች ሁለመናቸውን የከፈሉባትን
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምን ላይ አደረሳችኋት? ዛሬማ ጆሮ አይሰማ የለው ጉድ እየሰማን ነው።
ፓትርያርኩ አባ ማትያስ ወይም አዘናጊው ፓትርያርክ በአደባባይ ወጥተው ቤተ ክርስቲያናችን ታወቀች በዩኔስኮ
ተመዘገበች ከእንግዲህ ቱሪስቱ ይፈሳል ዶላሩም ይፈስልናል። ዓለም ሁሉ እኛን ያየናል አሉ። ልብ በሉ ይህ
ሁሉ ፈንጠዝያ በዓለም አቀፉ ድርጅት የዲያብሎስ አንዱ ድርጅት ተመዘገብን ይሉናል። የእግዚአብሔር ሕዝብ
የዲያብሎስ ማሕበርተኛ አይደለም። ቤተ እምነታችን በመድኃኒዓለም ከተመዘገበች 2000 አመታት አለፉ።
መመዝገብ በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ እንጂ ዲያብሎስ ባደራጀው በሚመራው ድርጅት ውስጥ አይደለም። ካባ
ያጠለቃችሁ የዘረኛው ፖለቲካ ጉዳይ ፈፃሚዎች በነማን ጫማ ውስጥ እንክተታችሁ በጥቅሉ አሳፋሪ ናችሁ።
በመምህርነት የተሰማሩ ግልገል ተተኪዎቻችሁ በተቃጠለ ቤተ ክርስቲያን በተጨፈጨፉ አገልጋይ ዲያቆናትና
ምእመናን ስም በውጪም በአገር ውስጥም በማህበራዊ ሚድያው አብዝተው የሚጮሁ እውን ከልብ ቤተ
እምነታችንን ለመገንባት ነው ገንዘብ የሚያሰባስቡ? ሁሉንም የምናየው ነው። ከእንግዲህ የእግዚአብሔር ቤት
መነገጃ መሸቀጫ የፖለቲካ ጉዳዮች ማቀናበሪያ የዘረኞች መናኸሪያ አትሆንም። የእናንተም መዝገብ ተዘግቷል
በጨለማ የሰራችሁት በአደባባይ ይገለጣል። በውርደት በሃፍረት በክፉ ቅጣት ትወገዳላችሁ።
ልዑል የታመነ እረኛ ነው። ሕይወትን ያህል ውድ ዋጋ የከፈለበትን፤ ሥጋና ደሙን የቆረሰበትን
የተጨፈጨፈበትን የተቀጠቀጠበትን እውነት፤ የተዋህዶ እምነት ማፍረስ የወንጀል ሁሉ ወንጀል ነው። እንደዓይኑ
ብሌን የሚያያቸውን በጎቹን ለአውሬ መስጠት ምን እንደሚያስከፍል አሁን ታዩታላችሁ። በየበረሃው የወደቁት
አባቶች የወቅቱ ሁኔታ ቢያሳስባቸው ለዚህም መሳሪያቸው ጾም ጸሎት ነውና ህዝቡ ሁሉ እንዲጾም ቢያውጁ
ምን ክፋት ተገኘበት? እኛ ያላዘዝነው ጾም አይሆንም፤ ሲኖዶስ ማወጅ አለበት ብላችሁ በቴሌቪዥን መስኮት
ተከስታችሁ ስትናገሩ ስሰማ እጅግ ደንቆኛል። የናንተን ሥራ ስለሠሩ ሊከበሩ ሲገባቸው ውግዘት! አሁን ፍርዱ
ስለመጣ ወዴት እንደምትሸሸጉ እናያችኋለን። መነኮሰ ሞተ የሚለውን ቃል ፈፅመናል። ለዓለምም ሞተናል
ያላችሁ። እግዚአብሔርም ከፍተኛውን የእረኝነት ሥራ የሰጣችሁ፤ ሥጋ የዚህ ዓለም ቅራቅንቦ አያሸንፋችሁም
ለልጆቼ ለበጎቼ ጥሩ እረኛ ይሆናሉ ብሎ ያመነባችሁ። እያጠፋችሁም እድሜአችሁን ሁሉ በትእግሥት
የጠበቃችሁ። ቤተ እምነታችን ተዋህዶ እምነታችን በጠራራ ፀሐይ በመንግሥት ተቀናብሮ የከሱ በጎች ሁሉ
በአውሬው መንግሥት ተብዬ ሲታረዱ ሲዘረፉ የአፍ ውግዘት ብቻ፤ ይብስ ድርድር አልፎም መሸለም ገንዘብ
መለገስ። ታዲያ ከዚህ በላይ ምን ወንጀል አለ። ለመሆኑ በመተረየስ የተረሸኑት አቡነ ጴጥሮስ ስለበጎቻቸው
አደራ አይደለም እንዴ የተዋጉ? ከጣሊያን ተስማምተው መነገድ ሕንፃ መገንባት መወፈር ብር ማከማቸት
አይችሉም ነበር እንዴ? እውነተኛ እረኛ ስለበጎቹ ነፍሱን ይሰጣል። እናንተ እንኳን ነፍሳችሁን በወደቀበት
በደቀቀበት ስፍራ እንኳን ብቅ ብላችሁ አላያችሁትም። ተመዘናችሁ ቀለላችሁ። ተፈረደባችሁ። ግብራችሁ
ተከተላችሁ። አብራችሁ የምትሞዳሞዱበት መንግሥት ይታደጋችሁ። እናንተ ለምትፈሩት ለምትታመኑበት
ለምትለማመጡት ዓለምን ሁሉ እያጠፋ ያለው በነአሜሪካ፤ እንግሊዝ፤ ቻይና፤ ሳኡዲ አረቢያ፤ በነግብፅ
በነአውሮፓ የሚደገፈውን የአብይ የእስላምና የመናፍቅ መንግሥት ፍፃሜውን እናንተም እየተፈፀማችሁ
የምታዩት ይሆናል። ትላንት ለወያኔ ዛሬም ለከፋው ዘረኛ ጭምብል ለባሽ የምትታዘዙ ለሥጋ ትርፋችሁ ስትሉ
በአገሪቱ የተበተኑትን የተዋህዶ ልጆች ሲበሉና ለአውሬ ንጥቂያ ሲሆኑ እያያችሁ፣ ለአውሬው የምትሰግዱ
ከሆነ፣ ጠባችሁ ግጭታችሁ ከማን ነው? አዎን ከልዑል ነው። ካከበራችሁ፤ የከበረውን ኃላፊነት የእረኝነት
ሥራ ከሰጣችሁ ከኃያሉ እግዚአብሔር ጋር መሆኑን በተግባራችሁ አረጋግጣችኋል። እግዚአብሔር ፈራጅ
አምላክ ነው። በጎቹን ለአውሬ የሰጣችሁ የወፈረውን የበላችሁ የከሳውን የጣላችሁ የወፈሩትን በጎች /
ባለፀጋ ክርስቲያኖች ምእመኖች/ የበላችሁ። እግዚአብሔር ፈርዶባችኋል። ከእረኝነቱም ተሰናብታችኋል።

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ፍርዳችሁም ይክተላችኋል። በጣት የተቆጠሩ እውነተኞች እረኞች ነፍሳቸውን ሥጋቸውን አስጨንቀው በእናንተ
እየተሳደዱ ያሉ፤ በየገደሉ በየምናምቴው ስፍራ ወድቀው ስለሕዝባቸውም ስለአገሪቷም ስለእናንተም መክፋት
ወደፈጣሪያቸው የሚጮሁ ተመርጠዋል ተሹመዋል። እውነተኛ የተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን እረኞች ይሆናሉ።
በእናንተም ፈንታ ሥልጣነ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ሁሉ ይረከባሉ። ይህም ተወስኗል ታዟል።
ይፈፀማልም። በፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የምትመራው ቤተ ክርስቲያናችን፤ ሲኖዶስ፤ የዋናውም የየክልሉም
የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መዋቅር ከፓትርያርኩ ጀምሮ እስከአጥቢያ ያሉ አገልጋዮች፤ ካህናት ዲያቆናት ጳጳሳት
ሰባኪዎች መምህራን ዘማሪዎች ሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች አስተማሪዎች ወዘተ --- በተመዘናችሁበት
መሰረት የተወሰነላችሁን እጣችሁን ታገኛላችሁ ይሀ ደብዳቤ እናንተ ጋ ከደረሰ ጀምሮ በተከታታይ እርምጃው
ይቀጥላል። መድኃኔዓለም አባታችን መድኃኒታችን ከእናታችን ከእናቱ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ጋር
ጎብኝተዋችኋል። ሥራችሁንም መዝነው በጣት ከሚቆጠሩ በስተቀር ቀላችኋል። ፍርዳችሁን የታዘዘውን ሁሉ
ለመተግበር ሊቀ - መላእክት ቅዱስ ሚካኤል፤ ሊቀ - መላእክት ቅዱስ ገብርኤል፤ ሊቀ - መላእክት ቅዱስ
ሩፋኤል ፤ ሊቀ - መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል በማይቆጠረው ኃይላቸውና ክብራቸው ውሳኔውን ለመተግበር
ተነቃንቀዋል።
ራሳችሁን አዘጋጁ የሚሰጥ ምንም ጊዜ የለም።
ልብ በሉ በእግዚአብሔር ቤት የሰለጠኑ ናቸው ልዑልን የናቁና ያቃለሉ። ዛሬም ይህ ደብዳቤ የመዝገብ
ቁጥር ጨብጦ ሲደርሳችሁ፤ እንደለመዳችሁት ልትነቅፉ ትነሱ ይሆናል። ይህን እንደምታደርጉ ደግሞ አስቀድሞ
ተነግሮናል። ደግሜና አስረግጬ ልንገራችሁ። ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ናት። ኢትዮጵያ የዓለም ሁሉ ገዢ
ትሆናለች። በእናንተ ትችት ነቀፋ የድፍረት ኃጢአት ራሳችሁ ለብርቱ ፍርድ ትጣላላችሁ እንጂ እግዚአብሔር
በወደዳቸው፣ ባከበራቸው፣በሾማቸው ላይ የምታመጡት አንዳች ነገር የለም። ይልቅስ እንደ ክፉዎቹ ፈሪሳውያን
ሰዱቃውያን ስለአውቀናል ባይነታችሁ ባትታበዩ ይበጃችኋል። ሚስኪኖች ምንም እውቀት ጥበብ የሌላቸው
በየዋህነት በስብከት ሞኝነት መድኃኒያለምን ያመኑ ድንግልን የወደዱ ፈርተው በደጁ ተሸቆጥቁጠው እናንተንም
አክብረው ስትገፏቸው ተገፍተው ስትንቋቸው ተንቀው ያሉት ናቸው ዛሬ ባለድል የሆኑት። ስለዚህ ትችት
አውቃለሁ ባይነት መታበይ ይጎዷችኋል እንጂ አይጠቅሟችሁም። ስለኔ ያሻችሁን በሉ አልሸከመው ምን
ይገደኛል። ስለእናንተ አትርፎ መክሰር ልዘን እንጂ፤ ቅን ፈራጁ በፍርዱ የማያዳላ የሁሉ ፍጥረት አስገኝ፣ጌታና
ፈጣሪ መድኃኔዓለም ስሙ ይባረክ!!!
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ ስሙ የተመሰገነ
ይሁን!!!
እናታችን አማላጃችን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል እናቴ በሰማይም ንግሥት በምድርም ንግሥት ስሟ የተመሰገነ
ይሁን!! ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ስማቸው የተመሰገነ ይሁን! ሰማዕታት ቅዱሳን አባቶች እናቶች ስማቸው
የተመሰገነ ይሁን! አሜን!

በትሕትና ከማክበር ሰላምታ ጋር

የታመነው የሥላሴ ባሪያና አገልጋይ


የድንግል ባሪያና አገልጋይ

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር


ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት

Date:

Number:

IN THE NAME OF ALMIGHTY GOD


IN THE NAME OF OUR MOTHER VIRGIN MARRY
The reason to issue this letter of executive order, by the Almighty God trusted
servants and slaves is; to inform all today super powers /USA, UK, FRANCE, CHINA,
RUSSIA/ and also the Saudi Arabia, Egypt, United Arab Emirates, INDIA, GERMANY,
CANADA, NORWAY, NORTH KOREA, SOUTH KOREA, IRAN, all companies whose
names and capitals were mentioned in message 8 international organizations like ; IMF,
WORLD BANK, are going to be the first target to face the most destructive actions,
annihilation and termination of all their beingness. After the release of this letter of
executive order every measures that had been told to you in messages, 1, 2, 3, 5,
6, and 8 will be effective as soon as you are informed. In the face of Almighty God
your all beingness, all your power, governance with all your men and women under
your command and service are scraped and thrown to the molten inferno of fire for
unstoppable duration of time.
Before you go reading these letter, first read the words of Almighty GOD from
PSALMS 83:

Rest not, O GOD; O GOD, be neither silent nor still, for thy
enemies are making a tumult, and those that hate thee carry their
heads high, they devise cunning schemes against thy people. And
conspire against those thou hast made thy treasure; come away with
them, they cry, let them be a nation no longer, let Isreal name be
remembered no more. With one mind they have agreed together to
make a league against thee; the families of Edom, the Ishmaelites,
Moabites and Hagarenes, Gebal, Ammon and Amalek, Philistia and
the citizens of Tyre, Asshur too their ally, all of them lending aid

1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

to the descendants of Lot, deal with them as with Sisera, as with


Jabin, by the torrent of kishon, who fell vanquished as Midian fell
at En-harod, and were spread on the battle field like dung. Make
their princes like Oreb and Zeeb, make all their nobles like Zebah
and Zalmunna; for they said, we will seize for ourselves all the
pastures of God’s people. Scatter them, O God, like thistledown,
like chaff before the wind. Like fire raging through the forest or
flames which blaze across the hills, hunt them down with thy
tempest and dismay them with thy storm wind. Heap shame upon
their heads, O Lord, until they confess the greatness of thy name.
let them be abashed, and live in perpetual dismay; let them feel
their shame and perish. So let them learn that thou alone art Lord,
God most High over all the earth.
As you are seeing the words of Almighty God above, who are today’s enemies of
the Almighty God? It should be clear; you are the most arc enemies of Almighty God,
in which You surpasses 1000 times of your ancestors, the Amalek, the Ammons, the
Philistia and Lot.
This letter could be referred as an executive order of The Almighty God trusted slaves
and servants.
As it is well known by all concerned states of the world at large. | had sent messages
that are affecting your future destiny and fate for almost 15 years. As you did every
crimes and sins knowingly as your ancestors the Lot and Sodomite did, all the messages
/1,2,3,5,6,and 8/ had told you tirelessly, but nothing positive could be seen. The
messages tried to advise and warn you, of your deeply rooted sins. you had done and
still doing that is the hated sin. Neglecting and breaking the Almighty God advise and
warnings, you still live by your own wills. You also accepted and practiced the laws
and wills of the Devil, by doing this forbidden crimes and sins, you never regretted
and repented by kneeling before Almighty GOD.
Almost 2000 years passed away by waiting you. But still you never repented. Rather
you still do and practice the most hated sins and crimes in the faces of Almighty GOD.
As you know very well in the past 15 years, all messages 1,2,3,5,6,8 had been sent to
you, through your Embassy in Addis Ababa Ethiopia. I am sure you had got all of the
messages. But you never had done as the messages advised you. But on the contrary
you did the negative or the opposite way. By neglecting the messages continuous advise
and warnings, you showed your arrogance and hatred to Almighty God. He patiently
waited you for so many years, but for no avail. All nations, governments, the so called
international communities, the world leading G-8, G-20, EU, Arab League, all in all
the whole world above 200 countries, with all your populations; and your loved faiths

2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

like catholic, protestant, Islam, shintoizm, Hinduism, and so many demonized faiths
and cultures that are incubation machines of demonized faiths almost had covered and
controlled the whole faces of the earth. It is crystal clear every lay man can witness it.
In the past 15 years those messages clearly had told you what you have done and
still doing in the faces of Almighty God. Neglecting him you spoiled the whole world
by your most ugliest sins of sins. /you made Sodom legal, adultery as a right of every
human kind, you completely erased the true faith the Tewahedo Orthodox from every
corner of the earth, you demonized the whole world and imposed the demonized laws
and traditions in every daily life of the human kind/. Your eyes, ears,mind and hearts
always accept the enemy of the Almighty God. that is the devil. You obeyed the devil
commands and orders with no hesitation. All in all you worshiped the most hated
enemy of Almighty God and his sons, that is the demon.
Let’s remind you again this letter you are going to receive is not a message that
may warn you, rather this is a letter of command and decisions from the Almighty
God trusted servants and slave, which will act immediately when it reaches in your
hands. Today is not yesterday, all things will pass away. Before you become history,
you should have saved yourself from being dead in soul and flesh eternally. You should
have had used them by the time of advise and warnings.
As you know very well about us, we live in Ethiopia. Though we do not have an
office or army or security apparatus to act like you are doing as a government, but we
do have a power which will not be seen by your eyes or being heard by your ears. The
hand of Almighty God that measures scales and judges you cannot be seen. But when
it acts you could sense it by the results. When we speak, what we want to say we say
it by His Name it will be done as we said. Because we are trusted and entitled slaves
and servants of Him. You may be biased by our words and executive orders, when you
face the devastating and erasing actions, remember, we are the trusted servants of the
Almighty God. He authorized, assigned, given us power to do his wills, orders, and
commands and decisions to be put into deeds.
Based on this raw truth and facts, the whole world is subjected to obey our orders,
commands and decisions, in which we are issuing on behalf of the Almighty God
name. Still I believe your manner in which you had grown up will never let you to do
positively. So if you neglect, or try to obstruct or make obstacle, you must know that,
you will never be left without severe punishment that the most annihilating inferno of
fire will consume you. When I was preparing these letter of executive order, I heard the
USA president Donald trump speaking to the world at large. Due to his military action
and killing against the IRAN general, IRAN also took counter measures by missiles
barrages. Based on this actions he said the general is a monster and a terrorist, it is

3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

not surprising to call another person a monster, but to me who is the most arrogant
monster of our world. It is true you USA and your brothers in arms like UK, France,
CANADA, GERMANY, and a lot others are unseen monsters criminals mass murderers.
Why do not see your self as you see others?
REMEMBER---- The actions and punishing hands of Almighty God, that are going to
happen on Ethiopia soon, will be a good sign that tells you, what will be the next step
concerning you. The devastating, annihilating actions which are going to consume you
will never be seen in human kind history. After this letter appearance you will see what
it means. Today is not yesterday, of course we had tried to convey what Almighty God
ordered us to tell you. As all human kinds witness, the whole words and commands of
Almighty God had been discarded and buried, by all nations governments institutions
international organizations, medias presses that covers all faces of the earth. The whole
world is almost sunk by the sins of sins like Sodom, adultery and many nameless crimes
and sins.
Everything has a limiting point. Your sins and crimes are never seen in the world, it
surpasses your ancestors who had lived on Noah, and Sodom time. That is the reason
the Almighty God decided to terminate you, and bury you in the molten inferno of
fire once and forever. As I mentioned above; seven messages had been issued and
distributed for almost 15 years. You did nothing but the time elapsed. So you wasted
your time of repentance and still stood against the will of almighty God. You kindled
his anger. It is clear that you are going to pay dearly. The Almighty God words says
as follows;

PSALMS 94:
O Lord, thou God of vengeance, show thyself. Rise up, judge of
the earth; punish the arrogant as they deserve. How long shall
the wicked, O Lord, how long shall the wicked exult? Evil doers
are full of bluster, boasting and swaggering; they beat down thy
people, O Lord, and oppress thy CHOSEN NATIONS; they murder
the widow and the stranger and do the fatherless to death; they
say, the Lord does not see, the God of Jacob pays no heed, pay
heed yourselves, most brutish of the people; you fools, when will
you be wise? Does He that planted the ear not hear, He that
moulded the eye not see? Shall not He that instructs the nations
correct them? The teacher of mankind has He no knowledge? The
Lord knows the thoughts of man, that they are but a puff of wind.
As you see the words of Almighty God which scaled, measured judged you, who
could save you? No one, now you are going to pay the dearest price that had never
been done before.

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

In the messages 1,2,3,5,6 and 8 the measures that are going to be taken are clearly
written, they were halted till now to make you repent. But you neglected laughed
and discarded it. So everything has its own limit, and now the following orders and
commands are issued.
Orders commands and decisions of Almighty god trusted servants and slaves; that
are going to be effective as they arrived in the hands of your representative here in
ADDIS ABABA ETHIOPIA.

THE REVELATION OF JHON 18 / read it for your reference /


»» All decisions, repeatedly had been told and given to all concerned countries in
messages 1,2,3,5,6, and 8 which must be put into implementation. Because you
never accepted them as an advise and warning of Almighty God. Beyond that
you neglected even laughed and had thrown them as a dirty matter. Due to
your repeated, demonized acts, you tested the almighty God patience. So the
time has come to decide and implement all measures as had been told in all
messages. That is the reason, we the trusted servants and slaves of the Almighty
GOD issued this letter of command and orders to be put in to effect.
»» Primary targets of countries that are going to face the punishing hands of The
Almighty God soon are as follows :-
»» USA, UK, CHINA, FRANCE, GERMANY ,CANADA, SAUDI ARABIYA, RUSSIA,
EGYPT, INDIA, NORTH KOREA, PAKISTAN, POLAND, ROMMANIA, BULGARIA,
VEITNAM, UNITED ARAB EMIRETES, AUSTRALIA JAPAN, IRAN, ISRAEL,
SWIZERLAND, SPAIN, BELGIUM, SOUTH KOREA, AUSTRIA, UKRAINE,
NORWAY, SWEDEN, FINLAND, BRAZIL, NEWZLAND, TURKEY, PHILIPINES,
INDONESIA, DUBAI, OMAN, QUETE, SOUTH AFRICA, ITALY ETC.......
»» Those nations or states that had developed, stock piled mass destruction weapons
/like nuclear, neutron, chemical, biological/ and also heavy conventional mass
destructive bombs are going to be primary targets. Who are these states?
- 1/ United States of America:- this country in which every person, in every corner of
the world knows her, she is the most and the first nation that stood against the words,
wills, orders, and commands of Almighty God from the beginning of her creations as
a state. USA is seen as the leader or police of the whole world states. It is true she is
almost God to every nations of the world. She destroyed the world by imposing the will
of demon /devil/. She still is doing and also forcing the rest of countries in the whole
world to follow suit as she do. For almost 200 years she had been judged, and in the
past 15 years she had been told repeatedly about her unseen sins of sins and crimes
of mass destruction, in every states of the world she installed her puppet governments.

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

She is the mother of wars, adultery, Sodom, every states of the world willingly or
forcefully did and doing what she orders him, so in all her statehoodness the following
actions will be taken;
The Senate, the Congress with all their representative, the so called republicans and
democrats the Trump administration with all its stuffs, all armed forces that serve her
interest, all security apparatus like CIA, FBI, NSC, all coast guards, all military bases
with in its boundary and aboard all installations of intelligence gathering posts, all
warships, warplanes all its international banks insurances will be eradicated and being
destroyed without any mercy. Her complete annihilation by every natural forces will
be unlimited. The whole world is going to witness it. All the rest of nations states
governments when you see this measures happening on your master USA, you must
be sure of your fate. It will tell you that; you too will be done as your God USA got.
And remember what will be the result to kindle the anger of Almighty God and also
neglect the messages and an executive order of the Almighty God trusted slaves and
servants mean. Unless they ask their Almighty God for His mercy, no one will stop
your complete destruction and erasing from the faces of the earth.
2/UNITED KINGDOM :- the united kingdom is the most demonized states of the
world. She almost colonized most of the world states, so many states of today got their
boundary from her. UK is the most arc enemy of Almighty God. She is real picture of
demon in its real physical existence. Even the USA, FRANCE, GERMANY, all EU core
members were directed in clandestine structure by Lucifer installed queen ELZABIETH
the second. Her state structure is the house of commons, the prime minister either
labour or conservative party representative, UK the most hated nations on earth is going
to pay a dear price unseen in the history of mankind, nothing will be left untouched
from UK state and states under her umbrella. She will be completely destroyed with
nothing to be left as remaining symptoms. The rest of nations governments when you
see these things occur the next step will be you yourself. UK royal families the queen
the princes and princesses all will go to their final departure of this world, they will
become history. When this happens let it be a symptom to all of you who are going
to follow suit.
UK, house of commons, all labour and conservative party members, all judiciary
infrastructures, all international and local banks, all insurance company, all administrative
installation, all security forces/like MIS, MI6, Scotland Yard etc --/ all UK armed forces,
all international companies, and its sodommite and demonized populations will be pri-
mary target. All UK and its offshoots like Australia will be eliminated and be consumed
by unseen inferno of fire. And also by all forces of nature, her and USA suffering will
be unstoppable it will make them to beg for death. This action will start soon after you

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

get this letter of executive order and command of The Almighty God trusted servants
and slaves.
3/ CHINA:- this completely demonized and dragon worshipers will be counted as
USA, and UK, these nations are the most populated state of our earth. China as a whole
will never be left to exist as a country, never at all. The Chinese people assembly, the
state apparatus led by her president LI Ping are responsible for all its destruction.
She is equally seen as USA, and UK. Russia, France, Germany, Saudi Arabia, Egypt,
Arab Emirates will be measured, scaled and be seen as USA, UK are seen. So their
punishment is as the same as of USA and UK.
4/ FRANCE, RUSSIA, INDIA, ISREAL, PAKISTAN, NORTH KOREA, IRAN /on the way
of possessing nuclear/. As I mentioned above you will be eliminated, terminated, and
will become history.
»» All religious domains either they be small or large they already are screened
and evaluated by Almighty GOD. Based on the result, they are going to pay
the highest price, that means they are going to be erased from the faces of the
earth. The only faith that is going to reign on all faces of the earth will be the
TEWAHEDO ORTHODOX FAITH. THE TEWAHEDO ORETODOX CHURCH OF
ETHIOPIA will be the only religion that will guide the whole world to their true
father Almighty God, and will be the governing religion of the earth.
»» The whole world and all the human kinds will face the historic measures of
Almighty God soon, After seeing severe punishment all nations of the earth
must give their hands to servants and slaves of Almighty God, who are living
and soon are going to reign in Ethiopia. To get something, or any solutions
you must kneel down and beg for their mercy. You should know and be sure
that without their prayer and quest to Almighty God merciful hand, no one on
earth could save you.
»» When all severe measure starts taking you down, remember why it happened.
The only reason you should know is that the judgment of Almighty God that |
conveyed to youfor almost 15 years will be the only reason. Do not cheat your
nations by making artificial cover up. which never helps you.
»» The overall devastating and annihilation of the world will emanate from all
messages 1,2,3,5,6 and 8, everything is described and clearly noted. The messages
scaled, measured and evaluated you. Based on the result obtained from your
lasting deeds, todays actions are coming to terminate you. After that the whole
world will be given to the trusted servants and slaves of Almighty God.

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ

»» This letter of command and order came to decide your fate of existence or non-
existence. This makes it clear, what this letter of executive order of Almighty
God trusted servants and slaves mean.
»» When the process of Your destruction starts and resumes you must have to think
twice, before you try so many ways of resistance. It is natural I too expect it,
but it never halts your complete destruction. I repeat it again the only solution
available to you, as nations, governments and leader of your countries are to
beg, kneel down, and pour your tears in the face of Almighty God trusted
servants and slaves who are living in their homeland Ethiopia.
»» They may or may not accept you, but you must have to do it untill they show
their mercy.
»» Remember the Almighty God trusted servants and slaves are his loved sons.
He hears them, He accepts their prayer and gives them His answer. So as the
punishment came on their request the solutions also will come on their mercy
request to the Almighty God /their father/

When will the Almighty God sweeping, devastating, erasing action halts?

It must be clear to all of you, the whole world will not go as business usual. Today
all nations, governments and the population at large live and serve by the will and
order of devil. This you too will never deny. All your constitutions, laws, orders, the
so called democracy were given to all of you by your master demon /the snake/; so
from the appearance of this letter of executive order issued by Almighty god trusted
servants and slaves, everything you installed must be erased, and the will, order and
commands of Almighty God be planted. Every power on earth must be transferred to
the trusted servants and slaves of Almighty God. Unless this will of LORD Almighty is
achieved, your complete annihilation will never be stopped. This must be clear to all
nations of the earth.
Though you will neglect this letter of command and order, thank you for just reading
it.
With do you respect and sincerity

The trusted servant and slaves of The Almighty God


The trusted servant and slaves of Virgin Marry

8
መልእክት ዘጠኝ
ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም.

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!

የአብርሃሙ ሥላሴ ስምህ የተመሰገነ ይሁን!


ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል እናቴ – በሰማይም ንግስት በምድርም ንግስት እምዬ
ስሟ የተመሰገነ ይሁን!
የተጉ ሊቃነ መላእክት ስማቸው የተመሰገነ ይሁን!
ሰማዕታት አባቶቻችን እናቶቻችን ስማቸው ይክበር! ቅዱሳን አባቶቻችን
ሰማዕታት እናቶቻችን አባቶቻችን ስማቸው የተመሰገነ ይሁን
አሜን! አሜን! አሜን!

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር!


ኢትዮጵያ ርሥተ – ድንግል ማርያም! ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን!
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ!!

ይድረስ ለመላው የአዳም ዘር በሙሉ!!!

ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ


መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት!!
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!


እንደምን ከረማችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የተሰበሰባችሁ የትጉሃን መማክርት
የፅዋ ማህበራት እንዲሁም በመልእክታቱ ተረድታችሁ አምናችሁበት በንስሓም ራሳችሁን ከዚህ ዓለም ጉድፍ
የጠበቃችሁ። የተመዘገባችሁም ያልተመዘገባችሁም ቅኖች የዋሆች እንኳን ለዚህ ወቅት አደረሳችሁ!!!
ለመላው የአዳም ዘር ሁሉ! ሁሉንም የሰው ዘር የሚመለከተውን ይህን ዘጠነኛ መልእክት ከንቀትና ከመታበይ
ተቆጥባችሁ አንብቡት! ምናልባት በአለቀውም ሰዓት ቢሆን እግዚአብሔር ልብ ቢሰጣችሁ ማን ያውቃል ከሱ
በስተቀር መልካም መረዳት ይሁንላችሁ! አሜን!

እግዚአብሔር ነገሠ ምድር ሐሤትን ታድርግ፤ ብዙ ደሴቶች ደስ ይበላቸው፤ ደመና


ጭጋግም በዙሪያው ናቸው፤ ጽድቅና ፍርድ የዙፋኑ መሰረት ናቸው። እሳት በፊቱ
ይሄዳል፤ ጠላቶቹንም በዙሪያው ያቃጥላል፤ መብረቆቹ ለዓለም አበሩ፤ ምድር አየችና
ተናወጠች፤ ተራሮችም ከእግዚአብሔር ፊት፤ ከምድር ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም
ቀለጡ፤ ሰማያት የእርሱን ጽድቅ አወሩ፤ አሕዛብም ሁሉ ክብሩን አዩ ለተቀረፀ ምስል
የሚሰግዱ ሁሉ፤ በጣኦታተቻቸው የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ፤ መላእክት ሁሉ ስገዱለት፤
አቤቱ ስለፍርድህ፤ ጽዮን ሰምታ ደስ አላት የይሁዳም ሴት ልጆች ደስ አላቸው፤
አንተ እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና! እግዚአብሔርን የምትወድዱ
ክፋትን ጥሉ፤ እግዚአብሔር የቅዱሳኑን ነፍሶች ይጠብቃል ፡ ከኃጥአንም እጅ
ያድናቸዋል ብርሃን ለፃድቃን፤ ደስታም ለልበ ቅኖች ወጣ፤ ጻድቃን በእግዚአብሔር
ደስ ይበላችሁ፤ ለቅድስናውም መታሰቢያ አመስግኑ!!
መዝሙረ ዳዊት 56(57)
እግዚአብሔር የበቀል አምላክ ነው፤ የበቀል አምላክ ተገለጠ፤ የምድር ፈራጅ ሆይ
ከፍ ከፍ በል፤ ለትእቢተኞችም ፍዳቸውን ክፈላቸው፤ አቤቱ ኃጢአተኞች እስከ መቼ
ይጓደዳሉ ይከራከራሉ አመፃንም ይናገራሉ፤ አመፃንም የሚያደርጉ ሁሉ ይናገራሉ
አቤቱ ሕዝብህን አዋረዱ፤ ርስትህንም አስቸገሩ፤ ባልቴቷን ድሃ አደጉን ገደሉ፤
ስደተኛውንም ገደሉ፤ እግዚአብሔር አያይም፤ የያዕቆብ አምላክ አያስተውልም አሉ፤
የሕዝብ ደንቆሮች ሆይ አስተውሉ፤ ሰነፎችማ መቼ ይጠበባሉ፤ ጆሮህን የተከለው
አይሰማምን፤ ዐይንን የሰራው አያይምን አሕዛብንስ የሚገስፀው ለሰውም እውቀትን
የሚያስተምረው እርሱ አይዘልፍምን፤ የሰዎች ሃሳብ ከንቱ እንደሆነ እግዚአብሔር
ያውቃል፤ ለኃጢአተኛ ጉድጓድ እስኪቆፈር ድረስ፤ ከክፉዎች ዘመናት ይወገድ
ዘንድ፤ አቤቱ አንተ የገሰፅኸው ሕግህንም ያስተማርኸው ሰው ምስጉን ነው።
እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤ ርስቱንም አይተውምና፤ ፍርድ ወደ ጽድቅ
እስከሚመለስ ድረስ፤ ልበ ቅኖችንም ሁሉ ይከተሉታል፤ በክፉዎች ላይ ለኔ የሚቆም
ማነው፤ ዓመፅንስ በሚያደርጉ ላይ ለእኔ የሚከራከር ማን ነው?
መዝሙረ ዳዊት 93(94) 1—16
አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ፤ የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ፤ ኢየሩሳሌምንም
እንደመደብ አደረጉት፤ የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፤
የፃድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት፤ ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ
አፈሰሱ፤ የሚቀብራቸውም አጡ፤ ለጎረቤቶቻችንም ስድብ ሆንን በዙሪያችንም ላሉ
ሳቅና ዘበት፤ አቤቱ እስከ መቼ ለዘለዓለም ትቆጣለህ፤ ቅንዓትህም እንደ እሳት
ይነድዳል፤ ስምህን በማይጠሩ ነገሥታት ላይ፤ በማያውቁህም አሕዛብ ላይ መዓትህን
አፍስስ፤ ያዕቆብን በልተውታልና፤ ስፍራውንም ባድማ አድርገዋልና፤ የቀደመውን
በደላችንን አታስብብን፤ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፤ እጅግ ተቸግረናልና፤ አምላካችንና
1
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

መድኃኒታችን ሆይ እርዳን፤ ስለስምህ ክብር አቤቱ ታደገን፤ ስለስምህም ኃጢያችንን


አስተሰርይልን፤ አሕዛብ –– አምላካቸው ወዴት ነው እንዳይሉ፤ የፈሰሰውን
የባሪያዎችህን ደም በቀል፤ በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ይወቁ፤ የእስረኞች ጩኸት
ወደ ፊትህ ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት ሊገደሉ የተፈረደባቸውንም አድን ፡
አቤቱ የተዘባበቱብህንም መዘባበታቸውን ለጎረቤቶቻችን ሰባት እጥፍ በብብታቸው
ክፈላቸው፤ እኛ ሕዝብህ ግን የማሰማሪያህም በጎች ለዘለዓለም እናመሰግንሃለን!
ለልጅ ልጅም ምስጋናህን እንናገራለን!!
መዝሙረ ዳዊት 78 (79) በሙሉ
ከላይ በሶስቱ የልዑል ኃይለ ቃል እንደ ሰማችሁት እግዚአብሔር ስለሕዝቦቹ ሲል ቅን ፍርዱን እንደሚያስከትል
የሕዝቦቹም የፍረድልን ጩኸት ዝም ብሎ እንደማይታገስ ሁሉም ቃሎች ይገልፁልናል። ልብ በሉ እግዚአብሔር
እውነት ነው በመሆኑም ጽድቅና ፍርድ የዙፋኑ መሰረት ናቸው። በምንም መንገድም ሆነ ዘዴ የልዑል መሰረት
ቅን ፍርድ ነው። እሳት በፊቱ ይሄዳል አዎን! ልዑል የሚባላ እሳት ነው። ሥላሴን ተፃረው የቆሙ ሁሉ በእሳቱ
ይበላሉ ይቃጠላሉ። መብረቆቹም ለዓለም አበሩ ዓለም ከአሁን በኋላ የሚወሰደውን እርምጃ እንደ ፀሐይ ሲያበራ
የሚያዩት ይሆናል። ስለ እግዚአብሔር እውነት የሚከራከር ማነው፤ አዎን እጅግ ጥቂቶች ስለልዑል እውነት
ይከራከራሉ። በዋናነት የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት ጥረታቸው የነበረው እውነትን መግለፅ ነበር።
ይህም ለ15 ዓመታት ተካሂዷል። ከላይ ባለው የልዑል ኃይለ ቃል በየእንዳንዳንዱ ቃል ያለውን አንድምታ
በሚገባ አስተውሉ ተረዱ ወደ እርስትህ ገቡ ሲል ምን ማለት ነው። ይህን በሚገባ እያያችሁት ነው። ዛሬ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲያብሎስ ዘማቾች መወረሯን ልትጠራጠሩ አይገባም። የዛሬው መሪያችን የማንን
አጀንዳ ነው የሚያስፈፅሙት፤ አዎን የዓለም አቀፉን የዲያብሎስ አገዛዝ ዘመቻ አስፈፃሚ ናቸው። የእንግሊዝ
የስለላ ተቋም፤ የአሜሪካ የስለላ ተቋም፤ የአረብ ኤሜሬትስ የሳኡዲ አረቢያ መንግሥታት የስለላ ተቋም፣ የቻይና
የስለላ ተቋም፣ የአውሮፓ የስለላ ተቋም ስለምን ብራቸውን ያፈሳሉ ጧት ማታ ሰላዮቻቸው ይመላለሳሉ።
ለመሆኑ በኢትዮጵያ ምድር ይህን ያህል ሕዝበ ክርስቲያን የተዋህዶ አማኝ ሲያልቅ ሲሰደድ በጅምላ ሲፈረጅ
አይታችኋል። አልታየም የሚል ሰው የለም። ዘረኛው የትግሬው ኃይል ኢትዮጵያን ሲበትን ሲገል ሲያሳድድ
ለ29 ዓመታት አካሂዷል። ከሱ ማሕፀን የወጣው የአሁኑ መንግሥት ደግሞ መልኩን የቀየረ እባብ ማለት
ነው። በመልእክት ስምንት በሚገባ ተገልጧል። ቤተ ክርስቲያናችንን የተዋህዶ እምነታችንን ለማጥፋት ወያኔ
የጀመረችውን የተቀናጀ ዘመቻ ይህም መንግሥት አጠናክሮ እያካሄደ ነው። የሱ አባት ወያኔ ቤተ ክርስቲያናችን
ገዳማትን፤ ታላላቅ አባቶችን በብዙ ዘዴ አጥፍታለች። የዛሬው መንግሥት ደግሞ በአዲስ ጥርስ መልኩን
ቀይሮ የመጣ ነው በነእንግሊዝና በአሜሪካ እቅድ መሰረት የቆመም ነው። በእነቻይናም ፍፁም የሚደገፍ ነው።
ይህ የአብይ መንግሥት ሥልጣን ከጨበጠ ጀምሮ ቤተክርስቲያን ፈርሳለች ተቃጥላለች፤ ምእመናኖቿ ሁሉ
በእቅድና በስልት ብቻ ሳይሆን በግልፅ በሚታይ የተዋህዶ ጥላቻ ይህንን እምነት በጨበጠው የአማራ ሕብረተሰብ
ላይ ጦርነትና ዘሩን የማጥፋት ዘመቻ እያካሄደ ይገኛል። ይህኛው አገዛዝ መሰረቱን ያደረገው /እንደበፊተኛው
የትግሬን ሕዝብ መሰረት እንዳደረገው/ የኦሮሞን ሕዝብ ሲሆን፣ ሁሉንም የኦሮሞ ሕዝብ ሳይሆን በይበልጥ
የምሥራቁንና የምእራቡን የኦሮሞ ክፍል ነው። በእምነቱም መናፍቁንና እስላሙን መሰረት ያደረገ ነው።
በሁለት አመት ተኩል ጊዜ እጅግ ብዙ ሕዝብን አስፈጅቷል። ለረጅም ጊዜ ይህንኑ ለመፈፀም የሚያስችለው
ዝግጅትና ጥረት እያደረገም ይገኛል። ምኞት ቢሆንም። የሆነ ሆኖ የእግዚአብሔርን እርስት አጥፍቷል።
የቅድስናህንም መቅደስ አፈረሱ ይላል የልዑል ቃል ይህንን አይተናል። ቤተ ክርስቲያንን በማቃጠል በማፍረስ
አሳይቶናል። ስለዚህ ፍርዱ እጅግ የከበደ መሆኑን ሁሉም የመልእክቱ አንባቢዎች እንድትረዱ አስገነዝባለሁ።
ገና ወደ ዋናው መልእክት ሳትገቡ በመግቢያው በር ላይ የልዑልን ኃይለ ቃል ያስቀመጥኩት በምክንያት ነው።
የመጣው ጠረጋ የሰው ልጅ በታሪኩ ያላየው የእግዚአብሔርም ቁጣ ምን ያህል ብረቱና የማይመለስ እንደሆነ
ያረጋግጣል። ከዚህም መግቢያ ቃል ቀጥሎ የምታገኙት ከራእየ ዮሐንስ ከምእራፍ 16፣ 18፣ 19፤ የተገለፀውን
2
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ኃይለ ቃል ሲሆን የቁጣውን ፍሰት የሚያመላክት ክብደቱንም የሚያሳይ ግቡም በራእይ ዮሐንስ 20 የተጠቀሰው
የልዑል ኃይለ ቃል መፈፀም መሆኑን እንድትገነዘቡ አሳስባችኋለሁ።

የመልእክቱ መሠረታዊ ይዘትና ዓላማ!

መልእክቱ የወጣው እንደቀደሙት መልእክቶች በልዑል ባሪያ በሚል ብቻ የተገለፀ ወይም የተላለፈ
አይደለም። ይልቅስ በመንግሥትነት ሥልጣን በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ መልእክት
መሆኑን በግልፅ ያረጋግጣል። የመልእክቱንም ክብደትና በብርቱው የሥላሴ ፈቃደ ኃይል ተፈፃሚ የሚሆን
መሆኑን ያረጋግጥልናል።
መልእክቱ ብዙ ነገሮችን የሚዳስስ፤ የሚገልፅ፤ በንፅፅርም የሚያመላክት ተፈፃሚነቱንም በተጨባጭ
የሚያስረግጥ፤ፍንትው ያለውን እውነትና ፍርድን /ቅን ፍርድን/ የሚያሳይና የሚያረጋግጥም ነው። የትላንቱን
ቅን የሥላሴን ፍርድና የተፈፀመውንና በሂደትም የሚፈፀመውን በአፅንኦት እያፀና በቀጣዩ የመጣውን ታላቁንና
በሰው ልጅ ታሪክ ያልታየውን ጠረጋና እርምጃ የሚገልፅም ነው። ከሁሉም የሚከብደው በውስጡ ብርቱ ተፈፃሚ
መመሪያ ያዘለ፤ የከበዱ በዘመኑ ሰው ይሆናሉ ተብለው በፍፁም የማይታሰቡ ከባድ ውሳኔዎች የተላለፉበት፤ ፅኑ
ትእዛዞች የፀኑና ብርቱ እርምጃዎች የታወጁበት ሲሆን ከዚህ በላይ እስከዛሬ ያልተገለፁ ምስጢር ሆነው የቆዩ
አማኙንም የማያምነውንም ሲያወዛግቡ፤ ለክፉዎችም ለዲያብሎስ አገልጋዮችም እንደማደናገሪያ ሲያገለግሉ
የነበሩ አንድምታዎችን ምንነታቸው በግልፅ የሚገለፅበት ይሆናል።
ከሥላሴ በተሰጡ መለኮታዊ ሥልጣን በልዑል ባሮችና አገልጋዮች ቀጥተኛ ትእዛዝ ተፈፃሚ የሚሆኑ ውሳኔና
ትእዛዞች የወረዱበት፤ አስቸኳይና ብርቱ ትእዛዞች የሰፈሩበትና የተገለጡበት መልእክት ነው።
ሁሉም የአዳም ዘር ቢያነበው ቢያደምጠው እጅግ የሚጠቅመው ነው። ማንም የአዳም ዘር በየትኛውም ዓለም
ይኑር በሥላሴ ቅን ፍርድ የማይዳኝ የለምና ይስማ! የቀደመው እባብ፤ የቀደመው ዘንዶ፤ ሃሰተኛው ነብይ፤
የተከሏቸው መንግሥታት፣ ድርጅቶች፣ የእምነት ተቋሞች፣ ተሰሚ ነን የሚሉ የዘመኑ የፖለቲካ ቁማርተኞች፣
ባለጠጎች በጠቅላላው ለዲያብሎስ የሰገዱ ምልክቱንም በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ የተቀበሉና ለሥጋ ትርፋቸው
ነፍሳቸውን የሸጡ ሁሉ በብርሃናዊው ቅን ፍርድ የሚካተቱበት ስለሆነ ይስሙ እንላለን። ባይሰሙም ቢሰሙም
ቢያነቡም ባያነቡም የኛ ተልእኮ መርዶ ለሆነበት መርዶውን፤ ብሥራት ለሆነለት ብሥራቱን መግለፅ ብቻ ነው።
እስከዛሬ ከ7 ያላነሱ መልእክቶች ለአዳም ዘር በሙሉ እንዲደርሱ ተደርጓል። ከ2011 ዓመተ ምሐረት ጀምሮ
በቴሌግራም ቻናል /በዋናነት /፣ የዮሐንስ ራእይ 20 በሚል በልጃችን በብሩክ የተከፈተ ቻናል የኢትዮጵያ
የዓለም ብርሃን መልእክታትን፣ መግለጫዎችን፣ ትምህርቶችን፣ ምክሮችን፣ ትእዛዞችን በተከታታይ ለመላው
የአዳም ዘር እንዲደርስ ተደክሞበታል። ቸሩ መድኃኔዓለምና ድንግል ባተጋቻቸው የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
በተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ሁሉም የሰው ዘር በሙሉ እንዲሰማው፣ እንዲደርሰው ተደርጓል። እንደኔና
እንደመልእክቱ አገላለፅና የልዑል ውሳኔ እስከዛሬ እንኳን ልትኖሩ ምልክታችሁንም ማየት ባልተገባን ነበር።
ይሁንና እስከዛሬ በንቀታችሁ፣ በትእቢታችሁ ፀንታችሁ፣ ከቀደመው ወንጀላችሁና ክህደታችሁ፣
ግብረሶዶምነታችሁና ምንዝርናችሁ፣ በምድር ታሪክ ታይቶም ተሰምቶም ባልታየ የአመፃ የኃጢአት የትእቢት
ድርጊታችሁ፤ እኛ የልዑል ባሮች እንኳን ልንታገሳችሁ፤ እስከዛሬ በመቆየታችሁ በአምላካችን በአብርሃሙ ሥላሴ
በድንግልም ስለትእግስታቸው ብዛት ተከፍተናል ተሟግተናል ውሳኔው ፍርዱ በሙላት በፍጥነት ባለመፈፀሙ
አዝነናል። ይሁንና እኛ ሰው ነን ትእግስታችንም በሰው እሳቤ ልክ ነው የመድኃኔዓለም ትእግሥት ግን እጅግ
ከአእምሮ በላይ ነው። እስከዛሬም የቆያችሁት በዚህ ነው።
አሁን ግን የልዑልንም የድንግልንም ትእግሥት አጠንፍፋችሁ ስለተጠቀማችሁበት ከእንግዲህ የሚሰጥ ጊዜ
በፍፁም የለም። ሊኖርም አይችልም። ይህም መልእክት የመጣው የመፈፀሚያችሁን ደወል ለማብሰር ብቻ
3
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ነው። በእስካሁኑ ትእግሥት በፍፁም ሊከፈል የማይገባ ብርቱና ውድ ዋጋ ተከፍሏል። ፅዋው ሞልቶ ስለፈሰሰ
ማብቂያችሁንና መደምደሚያ የሆነውን ድግስ ትታደማላችሁ።
ሁሉም የአዳም ዘር ቢያነበው ቢያደምጠው መልካምና የሚበጀው ነው። የሕይወቱ ቆይታም ሆነ ስንብቱ
የሚበሰርበት የፍትሃዊ ሚዛናዊነትንም ምንነት የሚረዳበት ነውና! በማስተዋል ያንብቡ።
ከዚህ በኋላ በእግዚአብሔርም በድንግልም የተመረጡት ባለሟሎቹ /የተመረጡ እቃዎቹ/ ምንነት መጠነኛ
መግለጫ የሚሰጥበትም ነው። ይህም የሆነው ከ15 ዓመት ቆይታ በኋላ በሥላሴ በተሰጠ መለኮታዊ ትእዛዝ
መሰረት ነው።
ለትንሳኤው ዘመን ተሻጋሪዎች ብሥራት! ለከንቱዎች ለዚህ ዓለም ሰዎች፣ የኃጢአት ባለፀጎች፣ የዲያብሎስ
ታማኞች ክፉ ትውልዶች የሞትና የመጠረጊያቸው መርዶ ነው።
በቃ! በቃ! በቃ! ተፈፀመ! የሚል ድምፅ ብርቱ ነጎድጓድም – የሁሉ ፍጥረት አስገኚ ከሆኑት ሥላሴ
መንበር፣ ከፀባኦት ወጣ! አዎን ደግሜና ደጋግሜ ልንገርህ የመፈፀሚያህ ትእዛዝ ወጣ!። የአዳም ዘር ስማ
አድምጥ ብርቱው ጥፋትህ የዘመን ጉዞውን ጨርሶ ሊያጠፋህና ሊያበጥርህ ሞትን ሊያስለምንህ እነሆ መጣ!
የልዑል ኃይለ – ቃል እንዲህ ይለናል።

ለሰባቱም መላእክት ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን የቁጣ ፅዋዎች በምድር ውስጥ አፍስሱ


የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ /ከመንበሩ/ ሰማሁ። ፊተኛውም ሄዶ ፅዋውን በምድር
ውስጥ አፈሰሰ። የአውሬውም ምልክት ባለባቸው ለምስሉም በሚሰግዱ ሰዎች ክፉኛ
የሚነዘንዝ ቁስል ሆነባቸው። ይህ ሲሆን እግዚአብሔርን የካዱ በተለያየ የውሸት
እምነት ማለትም ዲያብሎስ የፈጠራቸው እምነቶች /መናፍቅ፣ ካቶሊክ፣ እስላም፣
ሺንቶይዝም፣ ቡዲሂዝም፣ ሂንዱይዝም፣ ቅባት ፀጋ፣ ዋቄ ፍታ፣ ወዘተ –––/
በሙሉ አውሬውን ያስመለኩ ለእሱም ያሰገዱ ስለሆነ ማንም ከኢትዮጵያ ተዋህዶ
ኦርቶዶክስ እምነት ውጪ የሆነ ሁሉ የሚመታበት ይሆናል። ቁስሉ ብርቱና የማይድን
ሞትን የሚያስመኝና የሚያስለምን ነው።
ሁለተኛውም ፅዋውን በባሕር ውስጥ አፈሰሰ። እንደሞተም ሰው ደም ሆነ፣ በባሕርም
ከሚኖሩት ሕይወት ያለበት ነፍስ ሁሉ ሞተ። ልብ እንበል የዚህ ቁጣ መፍሰስ
የባህሩን ሕይወት ያለበትን ሁሉ ካጠፋ ሃምሳ ከመቶ የሚሆነውን የሰው ምግብ
የሚሸፍኑ አሳዎች በሙሉ ይጠፋሉ፣ እንዲሁም ወደ መጥፎ ጠረንና ሽታ ባሕሩ ሁሉ
ሰለሚለወጥ የመጥፎ በሽታዎች ሁሉ ምንጭ ሆነ ማለት ነው፤ በትኩሳት ተቃጠሉ።
ሶስተኛውም ፅዋውን በወንዞችና በውኃ ምንጮች ውስጥ አፈሰሰ፣ እነርሱም ደም
ሆኑ፤ የውኃውም መልአክ ያለህና የነበርክ ጌታ ሆይ! ቅዱስ ሆይ! እንዲህ ስለፈረድህ
ፃድቅ ነህ፣ የቅዱሳንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ፣ ደምንም ደግሞ አጠጥተሃቸዋል።
የሚገባቸው ነውና! ብሎ ሲናገር ሰማሁ። ከመሰዊያውም አዎን ሁሉን የምትገዛ ጌታ
አምላክ ሆይ ፍርዶችህ እውነትና ፅድቅ ናቸው። ብሎ ሲናገር ሰማሁ። የዚህ አንድምታ
ደግሞ ስንረዳው በምድር ላይ ያሉ ወንዞችና ምንጮች ደም ከሆኑ የሚከሰተው እንደ
ግብፅ ሕዝብ በውኃ ጥም ማለቅ ማለት ነው። መላው የሰው ልጅ ውኃን ካጣ እድሜው
ለሳምንትም አትቆይም፣ ባሕሩ ጨው ሰለሆነ አይጠጣም።
አራተኛውም መልአክ ፅዋውን በፀሐይ አፈሰሰ። ሰዎችንም በእሳት ልታቃጥል
ተሰጣት፣ ሰዎችም በታላቅ ትኩሳት ተቃጠሉ፤ በነዚህም መቅሰፍቶች ላይ ሥልጣን
ያለውን የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ፣ ክብርንም እንዲሰጡት ንስሓ አልገቡም።
እንግዲህ ከቁስሉም ከውኃ ጥማቱም በላይ ብርቱ የሚያቃጥልና የሚያነድ እሳት

4
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ክፉው ሰው ሁሉ ሲወርድበት ሞትንም ፈልጎ ሞት ሲሸሸግበት ልዑልን መሳደብ


ይጀምራል ማለት ነው። እንደአባቱ እንደ ዲያብሎስ።
አምስተኛውም መልአክ ፅዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፣ መንግሥቱም ጨለማ
ሆነች። ከሥቃያቸውም የተነሳ ምላሳቸውን ያኝኩ ነበር፤ ከሥቃያቸውና ከቁስላቸውም
የተነሳ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ ከሥራቸውም ንስሓ አልገቡም። ይህ እርምጃ ከፊትህ
የመጣ ነው፣ ብርቱና የሚነዘንዝ ቁስል እማያስተኛ የማያስቀምጥ፣ ቃጠሎ እጅግ
ብርቱ እሳት ከብርታቱ የተነሳ ጥርስን የሚያሳኝክ መቆሚያ የሌለው ለማረፍ ሞት
ቢፈለግ የማይገኝበት ይህ ነው የመጣልህ።
ስድስተኛውም መልአክ ፅዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፣ ከፀሐይም
መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲሰናዳላቸው ውኃው ደረቀ፣ ከዘንዶውም
አፍና፣ ከአውሬው አፍ ከሃሰተኛው ነብይ አፍ ጓጉንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኩሳን
መናፍስት ሲወጡ አየሁ፣ ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና –––
በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደሚሆነው ጦር እንዲያስከትቷቸው
ወደ ዓለም ነገሥታት ሁሉ ይወጣሉ።
እነሆ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፣ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ
ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው፣ በእብራይስጥም አርማጌዶን ወደሚባል ሥፍራ
አስከተቷቸው። ይህም ከፊታችን የሚጠብቅ በምድር ያልታየ ዓለምን ሁሉ የሚስብና
የሚያካትት አብዛኛውን የዓለም ሕዝብ የሚፈጅ ጦርነት ይሆናል ማለት ነው።
ሰባተኛውም መልአክ ፅዋውን በአየር ውስጥ አፈሰሰ፣ ከመቅደሱም ውስጥ ተፈፅሟል
የሚል ታላቅ ድምፅ ከዙፋኑ ወጣ! መብረቅና ድምፅም ነጎድጓድም ሆኑ! ትልቅም
የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ መናወጥ
ከቶ አልነበረም፤ ከሁሉ በለጠ፤ ታላቂቱም ከተማ በሦስት ተከፋፈለች፤ የአሕዛብም
ከተማዎች ወደቁ! ታላቂቱም ባቢሎን የብርቱ ቁጣው ወይን ጠጅ የሞላበትን ፅዋ
እንዲሰጣት በእግዚአብሔር ፊት ታሰበች። ደሴቶችም ሁሉ ሸሹ፤ ተራራዎችም
አልተገኙም፤ በሚዛንም አንድ ታላንት /አንድ ታላንት 3 ፈረሱላ ነው / የሚያህል
ታላቅ በረዶ በሰዎች ላይ ከሰማይ ወረደባቸው። ሰዎችም ከበረዶው መቅሰፍት የተነሳ
እግዚአብሔርን ተሳደቡ፣ መቅሰፍቱ እጅግ ታላቅ ነውና!
ከዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 16 ያለውን ቃል ነው የተመለከትነው።
ከላይ ከልዑል ቃል እንደሰማችሁት በጌታችን በመድኃኔዓለም አባታችን ይወደድ የነበረው ለእግዚአብሔር
ምስጢርም ቀራቢ የነበረው ሐዋሪያው ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት እያለ ከልዑል ዘንድ የተገለጠለትን ፅኑ ራእይ
ነበር። ከዚህ ቀደም በትምህርታችን እንደገለፅኩላችሁ፤ልዑል ምንግዜም ለወዳጆቹ አስቀድሞ ሊያደርግ ያሰበውን
የሚሆነውን ሳይናገር አንዳች ነገር አያደርግም። በዚህም ምክንያት እጅግ ይወደው ለነበረ ለሐዋርያው ዮሐንስ
የመጪውን ሁኔታ በዓለም የሚከናወነውን ሁሉ የልዑል የቅን ፍርዱን አፈፃፀም ሁሉ አስረግጦ ነግሮት ነበር፤
እነሆ ቃሉን የሚያፀናው መድኃኔዓለም ቃሉን ይተገብር ዘንድ በሊቃነ መላእክት ታጅቦ መጣ!! ፅዋው ሞልቷልና
የአዳም ዘር የሆንክ ሁሉ ስማ አድምጥ! የናቅኸው፣ ያቃለልከው፣ የካድከው፣ አልፈህም የተዋጋኸው፣ የዘመን
ትእግሥቱን የጨረሰው የአብርሃሙ ሥላሴ በፍርዱ ሊያካትትህና ሊደመድምህ መጣ!
ወገኔ የሆንከው የሰው ዘር በሙሉ ስማኝ! የእስከዛሬው ያየኸው ሁሉ ምክር አዘል ቅጣት ነበር ምናልባት
ብትመለስ ተብሎ የተደረገ ጥረት! አልሆነም ይብስ ከድጡ ወደ ማጡ ሆነ! ምናልባት የሚፀፀት ቢገኝ ተብሎ
የተደረገው ጥረት ሁሉ በትእቢትህና በክህደትህ ሳቢያ ከንቱ ሆነ። በፍፁም አጥፊነትህ ገፋህ እንጂ ለተዘረጋልህ
የምሕረት እጅ ቅንጣት ዋጋም አልሰጠኸው! በቀደመው እባብ ተማምነህ ሃሰተኛውን ነብይ የቀደመውን እባብ

5
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

አምላክህ አድርገህ በክህደትህ ፀናህ እንጂ አልተፀፀትክም በተሰጠህ እድሜ ንስሓ አልገባህም። በክህደትህ
ተደሰትክ! በመሆኑም የመድኃኔዓለምን ትእግሥት በትእቢትህ በክህደትህ ረገጥከው!
ዛሬ የሚታየው የምድሪቱ እውክታና ረሃብ፣ በሽታና ጦርነት፣ የእርስ በእርስ ፍጅትና ሰላም መጥፋት፣
የዘርና የሃይማኖት ጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋው፣ የምድር መናወጥ፣ በሽታ እነዚህ ሁሉ ካላስደነገጡህ ወደፈጣሪ
ጉያ እንድትሰበሰብ ካላደረጉህ አባታዊ ቅጣቱን ሁሉ ካቃለልህ ጭርሱን አምላክነትህን አላውቅም ካልክ ሌላም
አምላክ /ጣኦት/ ካቆምክ የእግዚአብሔርም የሰውም ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ካመለክህና ካነገሥህ ከዚህ
በኋላ ምን ይደረግ? ምንስ ይጠበቅ? ዘመን ተትረፍርፎ ቢሰጥህ ዲያብሎስን ለማንገስ አዋልከው። እጅግ
በከበደው ክህደትህ የማይመለሰውን የልዑል ቁጣ አመጣህ! እነሆም የመፈፀሚያህ ድምፅ ከልዑል ዘንድ
ከፀባኦት /ከመንበሩ/ ወጣ! ተፈፀመ አለ!
ሰባቱም መላእክት የቁጣውን ፅዋ ሁሉ ሊያፈሱት በፍጥነት ወደ ምድራችን ገሰገሱ። እንግዲህ ወዴት መሸሸግ
ይቻልሃል? የመከርነው የዘከርነው የጮህነው ከዚህ እቶን ላይ ወድቀህ ከነዘር ማንዘርህ እንዳትጠፋ ነበር፣
አልሆነም! እኔም ምናምንቴው በፊቱ የታመንሁ የሥላሴ ባሪያ ለ15 ዓመታት ጮኬ ለፍልፌ አቅሜን ሁሉ
ጨረስኩ ዛሬ የምነግርህ የሥላሴ ብርቱ ትእዛዝ ሆኖብኝ እንጂ ዳግም ወደእናንተ መድረስ አልሞክረውም ነበር።
ስለ አባቴ ፍቅር ስለአባታዊ ትእዛዙ ስል ስለእናቴ ድንግል ስል መርዶህን እነግርሃለሁ።
እንግዲህ ተፈፅሟልና ስማ! ስማ! ያለችህ ጊዜ የመስሚያና የመሰናበቻ ጊዜ ብቻ ናት። ሌላ ጊዜ የለህም
አብቅቶልሃና!

እነማናቸው የአውሬው አምላኪዎች? ይህንን በግልፅ ልታውቁ ይገባል።

እምንበዛው ሕዝበ ክርስቲያን የዮሐንስ ራእይን የትንቢት ቃል መረዳት ይቸግረናል። ምክንያቱ ደግሞ ልዑልን
ጠይቀን የራእዩን ፍቺ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ምሪት ስለማናነበው ነው። ብዙ የዘመኑ ምሁራን ነን የሚሉ
በዲያብሎሳዊ መነፅራቸው እየተነዱ ለሱ ክፉ ሃሳብ እንደሚመች አድርገው የሚተረጉሙ ሞልተዋል። እዚሁ
አገራችን ያሉ በድፍረት በሰዎች አእምሮ ላይ የጥርጥር መንፈስ ለመዝራት ለሸክም የከበደ መጽሐፍ ጠርዘው
አውጥተዋል። ይህን ያደረጉት ደግሞ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በቁጥር አምስት በ2004 የወጣው መልእክት
ላይ የተገለፀውን ለመፃረር ተብሎና ታስቦ ነበር። የነዚህን ፀሐፊዎች ምንነት በሚገባ ስለማውቀው ፍርዳቸውም
ስለተከተላቸው ውጤታቸውን የምናየው ይሆናል።
ወደ ዋናው ጉዳያችን እንመለስና እነማናቸው የአውሬው አምላኪዎች ሰጋጆችና ምልክቱን የተቀበሉ?
የመጀመሪያው ረድፍ ላይ የምንገልፃቸው መናፍቃን ሲሆኑ ቀጣዩ የነሱ እናት የሆነችው ካቶሊክ ከነዚህ ቀጥሎ
ደግሞ እስላም ዋናዎቹ ሲሆኑ ከኤሺያ በቻይና በታይላንድ በኮሪያዎች በቬይትናም በካምቦዲያ በሞንጎሊያ
በሌሎችም ሺንቶኢዝም ቡዲሂዝም ኮንፊሺያን የመሳሰሉ እምነቶች በሕንድም ሂንዱስታን ሲኪዝም የመሳሰሉት
ሲደመሩ ዘጠና ከመቶ የሚጠጋውን የዓለም ሕዝብ ያካለሉ ናቸው። ከነዚህም ውጪ በተለያየ ጣኦት የሚያመልኩ
ጭርሱኑ እምነት የሌላቸው የሚሸፍኑት ነው። ማነው የአውሬውን ምልክት ያልጨበጠው የማያመልከው
የማይሰግደው? አዎን ግልፅ ነው የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እውነተኛ አማኞችና በእርግጥም ሥላሴን በእውነትና
በመንፈስ የሚያመልኩ በ40 ቀናቸው ተጠምቀው የልጅነት ክብርን የጨበጡ በእምነታቸውም የተለያየ ባእድ
አምልኮ ሳያዳብሉ በቅድስና እምነታቸውን ጠብቀውና ጨብጠው በልዑልም በድንግልም ፊት የሚመላለሱ
እነዚህ ብቻ ናቸው ለአውሬው ያልሰገዱ ምልክቱንም ያልወሰዱ የማያመልኩ በቃ እውነቱ ይህ ነው። እንግዲህ
ከጠረጋው ቁጣ ማን ይተርፋል? ማንስ ወደትንሳኤው ዘመን ይሻገራል? ግልፅ ነው ደግሜ እላለሁ ለአውሬው
ያልሰገደ ምልክቱንም ያልወሰደ ያላመለከ ተሻጋሪ ነው። ሀብትንም እውቀትንም ጉልበትንም ማምለክ ሌላው
የአውሬው አምልኮትም እንደሆነ እንወቅ።

6
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ማስታወሻ፡ በዛሬው ዘመን አሁን ባለንበት ሰዓት የአውሬው ዋንኛ ተጠሪዎች ወይም ማዘዣ ጣቢያዎች
እነማናቸው?
በአገርነታቸው እንጥቀሳቸው። እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እስራኤል፣ ሳኡዲ
አረቢያ፣ ቱርክ፣ ኢራን፣ ኮሪያዎች፣ አውስትራሊያ፣ ብራዚል፣ ሕንድ፣ ስፔን፣ ካናዳ፣ ደቡብ አፍሪካ፣
ጃፓን፣ ጀርመን፣ ጣሊያን ወዘተ እነዚህና ሌሎችም አነስ ያሉ አገሮች እንደማዘዣና እንደማስተባበሪያ ተደርገው
ለዲያብሎስ የሚያገለግሉ ናቸው።
ባቢሎን /አሜሪካ / በድሃ እምባና ደም ታጥባበትና ተነክራበት የተመሰረተች የአውሬው ዋንኛ መገለጫ
ናት። እንግሊዝም የዓለምን ግማሽ በቅኝ ለመግዛቷ ሁሉም የሚያውቀው ሲሆን ይህን የቅኝ ግዛት ማስፋፋት
ሲያከናውኑ ነዋሪዎቹን ጨፍጭፈው በማጥፋት ስለነበር የብዙ ሚሊዮኖች ንፁሕ ደም በእጃቸው ይገኛል።
በዚህች ምድራችን ለተፈፀመው የደም ማፍሰስ ማሃንዲሶች እንግሊዞች ፈረንሳዮች ፖርቹጋሎች እስፔኖች
ጣሊያኖች ጀርመኖች ዋንኞቹ ናቸው። በኤሽያ ያሉት እነቻይና ራሽያ ጃፓን ኮሪያዎች ሌሎችም የአውሬው
መገልገያና የሕልሙና የውጥኑ ፈፃሚዎች ነበሩ። ዛሬም ይህንኑ አምልኮታቸውን አዘምነውት በዚያው እየሄዱ
ያሉ ናቸው።
ለአውሬው የማይሰገድ ምልክቱንም ያልጨበጡ መንግሥታትና ሕዝቦች የሉም። ከኛው አገር መንግሥት
ጭምር ትልቅም ትንሽም መንግሥታት በሥራቸው ያሉ አለቃና ምንዝሮቻቸው በሙሉ ለአውሬው የሚሰግዱ
ምልክቱንም የያዙ ናቸው።
አውሬውን የሚያመልኩና የሚሰግዱ ምልክቱም ያለባቸው ከምንላቸው ከመናፍቃን ከካቶሊኮች ቀጥለው
ያሉት ደግሞ ከዚህ በታች ያሉ ናቸው።

እስላም
ይህ እምነት የቀደመው እባብ የደረሰው ከመፅሐፈ ፅልመቱ ያወጣው ተረትን የተሞላ የውሸት እምነት
ነው። ይህ እምነት ለ 1400 አመት በላይ ሰውን ሁሉ ያጠፋና ከሕይወት መንገድ ያወጣ እውነተኛ ነቢያትንና
ፃድቃንን /ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን / በዋናነት የፈጀና ያስፈጀ ደማቸውን ያፈሰሰ እምነት ነው። ይህ
እምነት የሚጨበጥ ነገር የለውም በተረትና ምሳሌ የተሞላ ነው። መነሻውን ዛሬ ሳኡዲ አረቢያ ከምንላት አገር
የተነሳ ነው። የዛሬ ከቢሊዮን በላይ የሚገመት እስላም በመካ መዲና እየተገኘ ዲያብሎስ የነገሰበትን ሥፍራ
ይሳለማል። ይሰግዳል። ለአውሬውም ሰግደዋል አምልከዋል ምልክቱንም ተቀብለው ኖረውበታል።
በእስላሞች ዘንድ በተለይም በዚሁ በመካ መዲና ዙሪያ እስላሞች ባሉበት ሁሉ የሚታመንና የሚነገር አንድ
አባባል ወይም ትንቢት አለ። እሱም እንዲህ ነው። ወደፊት በኢትዮጵያ ምድር የሚነሳ አንድ መላጣ የሆነ ንጉስ
ይመጣል /ይነግሳል / ይህ ሰው እስልምናንና እንዲሁም ዋናውን ሥፍራ መካ መዲናን ያፈርሳል ጥቂት ሰው
ብቻ ነው የሚተርፈው የተቀረው ይጠፋል ብለው ያምናሉ። ይህን አባባል የቀደሙ በእድሜያቸው የገፉ አባት
እስላሞች ባብዛኛው የሚያውቁት ነው። ወጣቱ እስላም ብዙም ቦታ አይሰጠውም ነገሩ ግን እውነት ነው። መቼም
በየዘመኑ እግዚአብሔር የሚወደው አንዳንድ የዋህ ሰው ከየትኛውም ሥፍራ አይጠፋምና አንዱ የዋህ እስላም
ተገልጦለት ይሆናል። የሆነ ሆኖ እስልምና እጅግ ብዙ የንፁሃንን ደም ያፈሰሰ በመሆኑ በእርግጥም ይጠፋሉ
ይጠረጋሉ። በኢትዮጵያ የሚነግሰው ንጉሥ ደግሞ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ነው። ይረዱት ጊዜውም አልቆ
እደጃቸው የደረሰ ነው። የሚያጠፋቸውም እሱው ነው። በልዑል የታመነ የተወደደ በልዑል ኃይል የተሞላ፣
ምንም ምድራዊ ኃይል የማይቋቋመው ነው። የታመነ የሥላሴ ባሪያ! ስለዚህ እውነት በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
መልእክታት ለ15 ዓመታት ሲገለፅ የቆየ ነው። መቼም ይህች ምድራችንና ነዋሪው እውነትን ለመቀበል እሬትን
እንደመጠጣት ያህል የሚመረው ነውና አይቀበልም። አትቀበል እየሞትክ ትቀበለዋለህ!

7
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት 15 ዓመታትን ሁሉ ለሁሉም የአዳም ዘር ሲፈስ ሲነገር ኖሯል፤
አልሰማም ብሎ ጆሮውን የደፈነ ትውልድ ምድሪቱን ስለሞላ ምን ይደረግ? በትእቢታቸው በክህደታቸው
ከሚታወቁትና ምድርን ካጠፉት ውስጥ እስልምና አንዱ የዲያብሎስ መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው። ቢመከሩ
የማይሰሙ በጥላቻና በንቀት የተሞሉ ከእስላም ውጪ ሌላው ሰው የማይመስላቸው ናቸው። ለንስሓ እንዲበቁ
ከማንም በላይ እድል ተሰጥቷቸዋል ግን አልተጠቀሙበትም። ስለዚህ በዚህ መልእክት መሰረት እጣቸው
የሚቀበሉት ፅዋ እንደመናፍቃን እንዲሆን ተወስኗል። ይህ መርዶ ይድረሳችሁ። ከዚህ በኋላ እድል የለም
በራሳችሁ ትእቢት ተቀብሯል። እስልምና የሌለበት የምድር ገጽታ የለም፣ በሁሉም ዓለም አሉ። በቁጥር ከአንድ
ቢሊዮን ተኩል በላይ ቁጥር የያዙም ናቸው። ከላይ እንደገለፅኩላችሁ ለቀደመው እባብ ለዘንዶው ለሃሰተኛው
ነብይ የተገዙ የአመለኩት የሚሰግዱለት ምልክቱንም የተቀበሉ በመሆናቸው ሰባቱም መላእክት የሚያፈሱት
መቅሰፍት ሁሉ የሚፈስባቸው ናቸው።

የቻይናዋ እና መሰሎቿ እምነቶች


ታኦኢዝም፣ ኮንፊሺያኒዝም፣ ቡድሂዝም፣ ሺንቶኢዝም እነዚህ እምነቶች በሙሉ፣ ሙሉ በሙሉ ሥላሴን
የካዱ ጣኦትን ፍልስፍናን ድራጎንን የሚያመልኩ ናቸው። ለቀደመው እባብ ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ
የሚሰግዱ ምልክቱንም የጨበጡ መሆናቸውን ከማንም በላይ በግልፅ የሚያሳዩን እነዚህ እምነቶች ናቸው።
አመቶቻቸውን ሲዘክሩ የውሻ ዓመት፣ የአይጥ ዓመት የዘንዶ ዓመት፣ የዝንጀሮ ዓመት፣ የድራጎን ዓመት እያሉ
የሚያከብሩም ናቸው። ይህ እምነት ከቻይና አልፎ ቬይትናም፣ ታይላንድ፣ ኔፓል፣ ካምቦዲያ፣ ኮሪያዎች፣
ጃፓን ድረስ የዘለቀ ነው ። እነዚህም ራሳቸውን ለመትከል በዘመን ሁሉ ለረጅም ጊዜ የንፁሐንን ደም
በምድራቸው ያፈሰሱ ናቸው። ስለዚህም በልዑል ቅን ፍርድ የሚካተቱ ናቸው። የሚጠፉና የሚጠረጉ ናቸው።
የሕዝባቸው ብዛት አንድ ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ይሆናሉ

ሕንድ
ሂንዱኢዝም ዋናው የሕንዶች እምነት ነው ሰማኒያ ፐርሰንቱን የህንድ ሕዝብ ይይዛል። 14 ፐርሰንቱ ደግሞ
እስላም ነው። ከዚህ የተረፈው ሲኪዝም እና ሌሎችም ሽርፍራፊ የጣኦት እምነቶች ያሉባት ናት። በዚች ሀገር
ጀግና የነበሩ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ነበሩ። ዛሬ የሉም በሚባል ደረጃ ደርሰዋል። እነዚህ
ከላይ የተጠቀሱት የዲያብሎስ ውልድ እምነቶች ተዋህዶዎችን አጥፍተዋቸዋል። የብዙ ንፁሕ ደም ፈሶባታል።
1.3 ቢሊዮን ሕዝብ ያቀፈች አገር ናት። ለአውሬው በግልፅ የሰገዱና ዛሬም በዚያው የፀኑ ናቸው። በሙሉ
የሚጠረጉና የሚጠፉ ናቸው።
ከላይ የዘረዘርናቸውን የእምነት አይነቶች በቁጥር ስንዘረዝራቸው
»» መናፍቅ፣ ካቶሊክ፣ ሌሎችም ክርስቲያን መሰል እምነቶች ወደ ሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን
»» ሺንቶኢዝም፣ ቡድሂዝም፣ ታኦኢዝም፣ ኮንፊሺያኒዝም በድምሩ ወደ ሁለት ቢሊዮን
»» ሂንዱኢዝም ሲኪዝም እና ሌሎችም አንድ ነጥብ ሦስት ቢሊዮን
»» ኦርቶዶክስ የሚለውን እምነት የጨበጡ ወደ ግማሽ ቢሊዮን የሚጠጉ ሲሆን
»» ተዋህዶ ኦርቶዶክስን የሚያምኑ አንድ መቶ ሚሊዮን ይደርሳሉ።
»» እምነት የሌላቸው፣ ልማዳዊ ወጎችን የሚያመልኩ አንድ ቢሊዮን ይገመታሉ በድምሩ ከተዋህዶ
ኦርቶዶክስ ውጪ ያሉ ወደ 7 ቢሊዮን አምስት መቶ ሚሊዮን ይደርሳሉ።

8
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንግዲህ ከተዋህዶ ውጪ ያለው በሙሉ የአውሬውን የቀደመውን እባብ፣ የቀደመውን ዘንዶ፣ ሃሰተኛውን
ነብይ የሚያመልኩ፣ የሚሰግዱ፣ ምልክቱንም የወሰዱና ገንዘባቸው ያደረጉ በመሆናቸው፣ ንሳሃም ባለመግባታቸው
ከላይ በራእይ ዮሐንስ ምእራፍ 16 የተገለፁት መቅሰፍቶች ሁሉ ይወርዱባቸዋል ይጠረጋሉ ከምድረ ገጽ በታላቁ
የሥላሴ ቁጣ ይወገዳሉ።
በጥቅሉ በአለማችን 205 የሚጠጉ አገሮች አሉ። ሁሉም ከላይ በዘረዘርናቸው እምነቶች ውስጥ ያሉ ናቸው።
እንደ ተገለጠው እንደተወሰነው ፍርድ መሰረት በእጣ ክፍላቸው ቆመው ከሥላሴ በተሰጠውና በታዘዘው ፍርድ
መሰረት በቅርቡ በመለኮታዊው ቁጣ ይጠረጋሉ።
የዮሐንስ ምእራፍ 18 ምን ይነግረናል?

ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። ከክብሩም
የተነሣ ምድር በራች። በብርቱም ድምፅ ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፤ ወደቀች፤
የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች። የርኩሳን መናፍስትም ሁሉ መጠጊያ የርኩሳንና
የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች አህዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቁጣ ወይን ጠጅ
የተነሳ ወድቀዋልና ይላል የልዑል ኃይለ ቃል!
አሜሪካንን የማያውቅ አለ? የለም ሁሉም ያውቋታል ጡጦ የጨበጠው ሕፃንም ያውቃታል። አሜሪካ
ያላገለሞተችው ግብረሶዶም ያላደረገችው ያላዘዘችው አለ ወይ? ደፍሮስ ያልታዘዛት አለ ወይ? እሷ የማታዘው
የማትመፀውተው የማትቀጠቅጠው አገር ሆነ ድርጅት አለ ወይ? ይህን ሁሉ አመጿን አይተናል ሠምተናል።
ፍርዷ ከወጣ 15 ዓመታት ተቆጥረዋል። ከሷው ጋር በባለሟልነት በእኩል ደረጃ በአመጿ በግልሙትናዋ
በቀደመው እባብ አምልኮዋ በእኩል የሚታዩ እነእንግሊዝ እነፈረንሳይ እነቻይና እነራሺያ እነኢራን እነቱርክ
እነሳኡዲ እኒህ ሁሉ በግምባር ለዲያብሎስ ቀዳማይ ታማኝ አገልጋይ የሆኑ የእግዚአብሔር ጠላቶች አይደሉም
እንዴ? አዎ ናቸው።
በዮሐንስ ምእራፍ 19 ደግሞ የልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ ይነግረናል።

ሃሌሉያ! በዝሙትዋ ምድርን ያጠፋችይቱን ታላቂቱን ጋለሞታ ስለፈረደባት


የባሪያዎቹንም ደም ከእጅዋ ስለተበቀለ ፍርዶቹ እውነትና ፅድቅ ናቸውና ማዳንና
ክብር ኃይልም የአምላካችን ነው። ብሎ ሲናገር እንደብዙ ሕዝብ ታላቅ ድምፅ
ያለ ድምፅ ሰማሁ! ደግመውም ሃሌሉያ አሉ። ጢሷም ከዘለዓለም እስከዘለዓለም
ይወጣል። ሃያ አራቱም ሽማግሌዎችና አራቱ እንስሶች በፊታቸው ተደፍተው በዙፋኑ
ለተቀመጠው ለእግዚአብሔርም አሜን ሃሌሉያ እያሉ ሰገዱለት! ድምፅም –––
ባሪያዎችም ሁሉ እርሱን የምትፈሩት ሁሉ ታናናሽና ታላላቆች ሆይ አምላካችንን
አመስግኑት! ሲል ከዙፋኑ ወጣ! እንደ ብዙ ሕዝብም ድምፅ እንደ ብዙ ውኃዎችም
ድምፅ እንደ ብርቱም ነጎድጓድ ድምፅ ያለ ድምፅ ሰማሁ። እንዲህ ሲል! –––
ሃሌሉያ ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላካችን ነግሦአልና የበጉ ሰርግ ስለደረሰ፣ ሚስቱም
እራሷን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን! ሐሴትም እናድርግ ክብርንም ለሱ እናቅርብ፣
ያጌጠና ቀጭን የተልባ እግር ልብስ እንድትጎናፀፍ ተሰጥቷታል። ቀጭኑ የተልባ እግር
የቅዱሳን የፅድቅ ሥራ ነውና! እርሱም ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁአን ናቸው
ብለህ ፃፍ አለኝ ––– ደግሞም ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው አለኝ።
የዮሐንስ ራእይ ም 19 ከ 1—9
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! አዎን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች!
እንዲሁም ይህን መልእክትም ሆነ የቀደሙትን ሰባት መልእክታት ለመስማት እድሉ የገጠማችሁ ይህን ታላቅ
ምስጢር የእግዚአብሔርን እውነት ለመገንዘብ የሚያስችል ልቡና ይስጣችሁ! መቼም እግዚአብሔር ልቡናችሁን

9
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ካላበራው የቀደመው እባብ ሃሰተኛው ነቢይ ዘንዶው ያላደነቆረው፣ ወደራሱም ያላካተተው የአዳም ዘር
የለምና! ጥቂቶቹ በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ የተመረጣችሁ የከበራችሁ ታላቁን መከራ የታገሳችሁ ልትፅናኑ
ይገባችኋል። ዛሬ ቀናችሁ ሊሆን ነውና! ብርሃናችሁ ሊበራ ድካማችሁ ሊታይ ሸክማችሁ ሊራገፍ መድኃኔዓለም
ሊክሳችሁ ነውና! አመስግኑ! እናንተ እርኩሳን የቀደመው እባብ አምላኪዎች የሃሰተኛው ነብይ ታማኞች፣
የዘንዶው ሰጋጆች ወየው በሉ! ወዴት ታመልጣላችሁ? ቀኑ አያልፍ! ደቂቃው አይረዝም ሰከንዷም አትዛነፍ!
አታመልጡም! አሜሪካ! እንግሊዝ! ፈረንሳይ! ቻይና! ራሺያ! ሕንድ እስራኤል ፓኪስታን ሰሜን ኮሪያ
ኢራን የኒኩለር ባለቤቶች የዲያብሎስ እልፍኝ አስከልካዮች ለጥፋት የሰውን ዘር ለዲያብሎስ ጭዳ ልታደርጉ
የተዘጋጃችሁ! ያ ሁሉ የድሆች ደም እንደጅረት ውኃ ያፈሰሳችሁት አንሷችሁ ለሌላ ታላቅ ደም ማፍሰስ
የተሰናዳችሁ። የንፁሐንን ደም ለዘንዶው ለቀደመው እባብ ዘወትር የምታፈሱ ፈጣሪያችሁን የናቃችሁ የካዳችሁ
የማትፀፀቱ የትእቢትን ጥግ የለበሳችሁ አታመልጡም ከነጭራዎቻችሁ መንግሥታት ጭምር ሁሉም መቅሰፍቶች
ከምድር እስክትጠፉ ድረስ ይፈሱባችኋል ያጠፏችኋል።
በመልእክት አንድ የዛሬ 15 ዓመት በወጣው የመጀመሪያው መልእክት የባቢሎን ፍርዷ ተገልጧል። ዛሬ
ይፈፀማል። እውነቱ ይህ ነው።
እንግዲህ ከላይ ከዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 16፣ 18፣ 19 ውስጥ የተገለፁትን የልዑል ኃይለ ቃሎች በተግባር
የሚገለጡ የእግዚአብሔር ፈቃድና ተፈፃሚ ውሳኔዎቹ ናቸው።

እስራኤል ዘሥጋ እነማናቸው? ምንስ ማለት ነው? ለምንስ እነዲህ ተባሉ?

ይህንን ልንረዳ ካልቻልን የእግዚአብሔርን ፈቃድ፣ ሃሳብ ተፈፃሚነቱ ለምን ነበር የሚለውን ልንረዳ
አይቻለንም።
እስራኤል ዘሥጋ ዛሬ የምናያት አገር ብትሆንም በቀደመው ታሪኳ ደግሞ ለሰው ልጅ በሙሉ እግዚአብሔር
ፈቃዱን ትእዛዛቶቹን እሱን ልናመልክ ልንፈራው ከሱ ውጪ ሌሎችን አማልእክት እንዳንከተል ያስተማረበት
ለዛም የተከላቸው ሕዝቦች ነበሩ። እግዚአብሔር ከእሥራኤሎች መፈጠር በፊት የተከላቸው በፊቱም በልቡናቸው
ላይ በታተመው ሕገ ልቡና በፊቱ ሲመላለሱና ሲኖሩ ሲያመልኩትም የነበሩ ሕዝቦች እንደነበሩ ያልተገለፁ
የተደበቁ ታሪኮች ይነግሩናል። በታላቅነት በዓለም ሁሉ ገነው መርተው የነበሩ ሕዝቦችም ነበሩ።
በመልእክት ስምንት ላይ እንደሰፈረው የዓለምን ሕዝብ ከ150 ያላነሱ መንግሥታትን ኤል ብለው በሚያመልኩት
በእግዚአብሔር ታምነው በፈቃዱ ግዛታቸውን አስፍተው የኖሩ ከየትኛውም የዓለም መንግሥታት የከበሩ
በልዑልም የተወደዱ ነበሩ! ኢትዮጵያውያኖች። ምሳሌ ብንወስድ ንጉሠ ነገሥት ሰንደቅ አልማ ከክርስቶስ
ልደት በፊት 4500 ዓመተ ዓለም ወቅት የነበረ ንጉሠ ነገሥት ነበር። አጼ ሰንደቅ አልማ በዘመኑ አፍሪካን
በሙሉ፣ ሩቅ ምሥራቅን፣ ኤሽያን ጨምሮ በከፊል አውሮፓን በመያዝ ከ150 ያላነሱ መንግሥታትን ወይም
አገሮችን ይገዛ የነበረ ንጉሥ ነበር። ከዚህ ቀደም በወጣው መልእክት ስምንት ገጽ 25፣ 26 ላይ እንደተገለፀው
በዚያ ዘመን ልዑል ራሱን ይገልፅላቸው የነበረው እጅጉን በጥቂቱ ነበር። በዛችው ጥቂት የብርሃን ብልጭታ
አባቶቻችን እጅግ በመደነቅ አብዝተውና በታላቅ ድካም ተሞልተው እግዚአብሔርን ሊያገኙት ይደክሙ ነበር።
እግዚአብሔርን ሳያዩት የጠነከረ ምስጢር ሳይገልፅላቸው እነሱ ግን እጅግ ኢምንት በሆነችው መገለጡ ወደውት
አምነውት ታምነውበት በመፍራትና በፍቅር ታምነው ፍትህን ቅን አገዛዝን አፅንተው በመጓዛቸው ልዑልም
ወዶአቸውና አክብሯቸው ነበር። ንጉሠ ነገሥት ሰንደቅ አልማ 400ዓመት በላይ የገዛ መንግሥት ነበር። ልጁም
አፄ አፍላስ ከአባቱ በሚበልጥ ግዛቱን አስፍቶ ኤል ብሎ የሚጠራውን አምላክ ልክ እንደአባቱ አክብሮና ወዶ
የኖረ የዓለም አባት እስከመባል የደረሰ፣ 450 ዓመት የነገሰ ነበር። ይህ ሁሉ ሲሆን እስራኤል አልነበረችም።
እስራኤል ዘሥጋ ስትፈጠር የሰው ልጅ ከሕገ ልቡና ወደ ተፃፈ ሕገ እግዚአብሔር የተሸጋገረችበት ወቅት ነበር።

10
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ሙሴ የእስራኤልን ሕዝቦች ከግብፅ ባርነት ነፃ እንዲያወጣ ሲታዘዝ ልዑል ለአባቶቻቸው ለነአብርሃም የገባውን
ቃል በማሰብ ነበርና! እግዚአብሔር ራሱን ለሰው ልጅ የሚበጀውን ትእዛዙን በግልፅ በመግለፅ ክብሩንም በሰው
የመቀበልና የመሸከም አቅም ልክ በመግለፅ እሥራኤሎችን ለታላቅ ክብር መርጦ ነበር። ታሪካቸውን በግልፅ
እንደምትረዱት በታላቅ ኃይል፣ በታምራት የእስራኤልን ሕዝቦች ህዝቤ ብሎ በመጥራት ፈርኦንን ሕዝቤን ልቀቅ
ያገለግለኝ ዘንድ ብሎ ነበር ያዘዘው።
ይሁንና ትእዛዙን የናቀው ያልተቀበለው ፈርኦን በእድሜው በታሪኩም ያልገጠመውን መቅሰፍት አሳርፎበት
ጉልበቴ የሚለውንም ሰራዊት በባሕር ውስጥ አስጥሞ በኃይል እስራኤላውያንን ነፃ አወጣ። እስራኤላውያን እጅግ
ልበ ደንዳኖች በመሆናቸው ገና ከጅምሩ ጀምሮ እየካዱት ጣኦት እያመለኩ በጉዟቸው ሁሉ እያስቆጡት፣
እየፈተኑት ቃል ወደተገባላቸው ስፍራ ልጆቻቸው ሊደርሱ ችለዋል። እነሱ ግን በየበረሃው ወድቀው ቀርተዋል።
ወገኖቼ! እስራኤላውያንን ስታስቡ ሙሉውን የብሉያት /ሕገ ኦሪትን / ከመጽሐፍ ቅዱስ ከዘፍጥረት ጀምሮ
አስከ ወንጌሉ ድረስ የምታዩት በእስራኤል ሕዝቦች የሕይወት ውጣ ውረድ መሞላቱንና በዚህ ሕይወታቸው
ውስጥ እግዚአብሔር በወደዳቸው ርቀት ልክ ሳይሆን እጅግ በሚበልጥ ሲፈታተኑት ሲዳፈሩት ሲክዱት
ጣኦትን ሲያነግሱበት አሳልፈዋል። ምንም እንኳን ልዑል እጅግ የተወደዱ የታመኑ ነቢያትን ቢያስነሳም እነሱ
አልተጠቀሙባቸውም ከነሱ በሚሻል አሕዛብ ተጠቅመውባቸዋል። ነቢይ በገዛ ሀገሩ አይከበርም የተባለውም
በነዚሁ ጠማማነትን በሚያነግሡና በሚተገብሩ እስራኤላውያን የመጣ አባባል መሆኑን ልንረዳ ይገባናል።
እግዚአብሔር እነሱን ሕዝቦቼ ብሎ መጥራቱ ምን ያህል እንደፀፀተው በሲና ተራራ ላይ ሙሴን ጠርቶ አሰርቱ
ትእዛዛትን ሲሰጠው በክህደታቸው እጅግ መቆጣቱን ገልፆለት ነበር። በዚያ ሙሴ የቆየው 40 ቀን ቢሆንም
ለአርባ ቀን ሙሴ ባለመታየቱ እስራኤላውያን ፈጥነው ነበር የካዱት። ጣኦት ሰርተው አመለኩ፣ ግብፅን ተመኙ
በዚህ ጊዜ ነበር እግዚአብሔር ለሙሴ –– ባሪያዬ ሙሴ ሕዝቦችህ ፈጥነው ካዱኝ! ተወኝ ላጥፋቸው አንተን
ግን ለተወደደና ታላቅ ለሆነው ሕዝብ መሪ አድርጌ ልሹምህ አለ። ሙሴ ርህሩህ ነበርና በስምህ ያወጣሀቸውን
በድንቅ የመራሃቸውን ሕዝቦችህን በረሃ ላይ ወስዶ ጨረሳቸው ትባላለህና ይህ አይደረግ ብሎ ልዑልን ለመነ።
ልዑልም ተለመነው። እንግዲህ የእስራኤል ሕዝቦች ሥጋቸውን ያነገሡ እንጂ ልዑልን የሚታመኑ እንዳልነበር
ያረጋግጥልናል። እግዚአብሔር በቃሉ እንደተናገረው በዚያ ዘመን ታላቅ ሕዝብ ብሎ የመሰከረላቸው የምድያም
ሕዝቦች ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ከዚያም በፊት ለረጅም ዓመታት በፊቱ የተወደዱ ነበሩ። እግዚአብሔርን ከብዙ
ሺዎች ዓመታት ጀምሮ በእውነትና በመንፈስ ከልባቸው ሲፈልጉት በጥቂቷም መገለጡ አብዝተው ይወዱትና
ይታመኑበት እንደነበር ታሪክ አስቀምጦታል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለይም በተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት የፀና
ሕዝብ በመሆኑ ዛሬም እግዚአብሔር አብዝቶ ይወደዋል። እንደአባቶችህ በእምነትህ በመወደድህ የአባቶችህን
ከፍታ በብዙ በረከትና መወደድ ዛሬም ሊያጎናፅፍህ በስሙ በከበረው ስሙ ከማለና ቃል ከገባ ቆየ። እኔም
ይህንኑ እውነት በታዘዝኩት መሰረት ከዛሬ 15 አመት ጀምሮ በ7 ተከታታይ መልእክቶች ገለፅኩልህ።

እስራኤል ዘሥጋ ለምን አነሱ? ለምንስ ለትንሳኤው ሳይታመኑ ቀሩ?

መልሱ ቅርብ ነው። በምሕረት ዘመን፣ በተወደደው ሰዓት ጌታ በገባው ቃል የሰውን ዘር ሊያድን ከዲያብሎስ
እሥራት ሊፈታ ሲመጣ ወደ ወገኖቹ ወደእስራኤላውያን ነበር የመጣው። አልተቀበሉትም። እነሱ የሚጠብቁት
ዓለምን ሁሉ በጦር ኃይሉ በሥልጣኑ ጨፍልቆ እንዲያነግሳቸው ነበር። በበረት የተወለደ ለነሱ ሰውም
አልነበረም። አሳልፈውም ለሞት ሰጡት። ሰቀሉት ገደሉት። ሞትን ድል አድርጎ ቢነሳም እንኳ አላመኑበትም
የሱን ደቀ መዝሙሮች አሳደዱ ገደሉ። ሥሌታቸው ሥጋ ነውና በዚህም እስራኤል ዘሥጋ ተባሉ። ክብራቸውም
መወደዳቸውም ወደኢትዮጵያ ፈለሰ። ታቦተ ፅዮን ወደኢትዮጵያ የፈለሰችው የእስራኤል ክብራቸው ወደታመኑት
ወደኢትዮጵያውያን ስለሔደ ነው። እስራኤል ዘሥጋ ዛሬም ከባቢሎን /አሜሪካ/ ጋር ሆነው ተጣምረውና

11
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ተዋህደው የቀደመው እባብ፣ የቀደመው ዘንዶ የሃሰተኛው ነብይ አምላኪ ሰጋጅ ምልክቱንም የጨበጡ ሆነው
እነሆ ዛሬም በክህደት በግልጽ የምታዩአቸው ናቸው። እስራኤል ዘሥጋ እንግዲህ እነዚህ ናቸው።

እስራኤል ዘነፍስ /ኢትዮጵያውያን/ ለምን ተባሉ?

ከላይ እንደተመለከትነው ኢትዮጵያውያን ቀድመውም በሕገ ልቡና በልዑል ዘንድ በእምነታቸው ተወደው
የነበሩ ነበሩ። እግዚአብሔርም በምድር ላይ እጅግ የገነኑ መንግሥታትን ሰጥቷቸው አክብሯቸው ኖረዋል።
ብዙ ሺ አመታትን በፅናት ታምነውበታል። ወንጌልን በፍቅር ተቀብለው ሳያዩት በቃሉ ብቻ አምነው ወደውት
ኖረዋል። ዛሬም በመከራ እቶን እየተጠበሱ ብሉይን ከሃዲስ አፅንተው እግዚአብሔር የተከላትን ተዋህዶ እምነትን
እንደጨበጡ ዘልቀዋል። በዚህ በምሕረት ዘመን ከዛሬ 700 ዓመታት ጀምሮ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው
ነብይ አልቆረጠም ያለችውን ተዋህዶን ያፀናችውን ኢትዮጵያን ለማጥፋት ዘመተ። ዛሬም ያልተቋረጠ ጥፋትን
እያካሄደ ይገኛል። መላው ዓለም ለቀደመው እባብ ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ ሰግዷል፣ አምልኳል ምልክቱንም
ተቀብሎ ኖሮበታል። አልንበረከክ ያለችው ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትና አማኞቿ ብቻ ናቸው። ወገኖቼ ሰባት
መቶ ዓመታት ሰባት ቀኖች ወይም ወሮች አሊያም ዓመቶች አይደሉም። ሰባት ትውልድ ያለፈባቸው ዘመኖች
እንጂ! አባቶቻችን እጅግ ድንቆች ነበሩ። ዛሬ በየትኛው የዓለም ገጽታ መድኃኔዓለም፤ ድንግል፣ ቅዱሳን
ሰማዕታት፣ ሊቃነ መላእክት ሲከበሩ ሲወደሱ ሲመሰገኑ ታያላችሁ። በሌላው ዓለም ይህ የለም። ሌቱን
ቀኑን ቅዳሴው፣ ማህሌቱ፣ ኪዳኑ፣ ሰአታቱ ከወር እስከ ወር ያሉ ክብረ በአላት፤ ሁለት ሶስተኛውን የዓመት
ክፍል በከባድ ጾም የሚያሳልፍ ሕዝብ ኃጢያቱን ለእግዚአብሔር አገልጋዮች እየነገረ ንስሓ የሚገባ አምላኩን
የሚፈራ፤ በሕብረት የሚመገብ ፡ የሚዘክር ፍቅርን የሚያነግሥ ሕዝብ ወዴት አለ? ጠላት በከፈተበት ሁሉን
አቀፍ ዘመቻ እየተመታና እየደቀቀ እየተሳደደ የዓለም ቁጥር አንድ ርሃብተኛ ተብሎ የተቆጠረ ሕዝብ፣ ሁሉም
አገሮች በዚችው በተወደደች እምነቱ ምክንያት እጅግ የጠሉት ሕዝብ ኢትዮጵያዊው የተዋህዶ ኦርቶዶክስን
ያፀናው ሕዝብ ነው።
እስራኤል ዘነፍስ ኢትዮጵያ ሁሉም ጠላቷ ነው። እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ጀርመን፣ መላው
አውሮፓ፣ ኤሺያ፣ አውስትራሊያ፣ ኢራን፣ ቱርክ፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ አረብኤሜሬትስ፣ ኳታር፣ ግብጽ፣ ካናዳ፣
እስራኤል፣ ሁሉም ላቲን አሜሪካ በጥቅሉ ሁሉም ዓለም ብትጠፋለት የሚወድ ቁጥር አንድ ጠላቱ አድርጎ
የሚቆጥራት ናት። ስለምን ይህ ሆነ? አዎን ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነቷን ስላፀናች ብቻ ነው። ይህንን እምነት
የጨበጠው ደግሞ በዋናነት አማራው በመሆኑ ዛሬ በገዛ ሀገሩ የሚጨፈጨፍ የሚሳደድ የሚገደል ሕዝብ ሆኗል።
እያያችሁት ስለሆነ ደግሜ መንገሩ ትርጉም የለውም። ይህ እምነቱ ያስከፈለው ውድ ዋጋ መሆኑን ጠላትም
ወዳጅም ሊያውቅ ይገባል። ወገኖቼ እስራኤል ዘነፍስ የተባልነው በሥላሴ በድንግል እጅግ የተወደድነው
እኛ ኢትዮጵያውያን የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት አፅንተን በእውነትና በመንፈስ የምናመልክ የእግዚአብሔር
የታመንን ልጆች ነን።
ዓለም እወቅ እውነቱ ይህ ነው። መላው የዓለም ሕዝብ የሆንክ የአዳም ዘር አልሰማሁም አላወቅሁም እንዳትል
ዛሬ እወቅ ገዢዎቼ አታለሉኝ የእምነት ድርጅቶቼ አጠፉኝ እንዳትል ስማ! ዲያብሎስን አንግሰሃል!የቀደመው
እባብ እንዲሁም ዘንዶውን አምልከሃል በሃሰተኛው ነቢይ እባቡ ታምነሃል አምልከኸዋል ምልክቱንም ወርሰሃል
ከአያት ከቅድማያትህ ተወራርሰሀል። እውነቱ ይህ ነው። የተወደደችው እምነትን ተዋህዶ ኦርቶዶክስን የጨበጡ
ቁጥራቸው ከየትም ቢሰበሰቡ 50 ሚሊዮን አይሞሉም። አንተ ግን ምድርን ሁሉ የሸፈነው 7ቢሊዮን አምስት
መቶ ሚሊዮን ሕዝብን አሰግደሃል ገንዘብህ አድርገሃቸዋል። እውነቱ ይህ ነው። በቃ! የመዋቀሻ ጊዜ አይደለም!
የፍርድ ሰዓት ነው። እንደ ክህደትህ እንደትእቢትህ እንዳፈሰስከው ንፁህ ደም እንደከረፋው ኃጢአትህ ምድርን
እንዳጠፋው ኃጢአትህ ልትከፈል ታሰብህ። የብዙ ሺ ዘመናት ግፎችህ ተገለጡ! እስራኤል ዘነፍስ የናቅሃት
የጨፈጨፍካት ኢትዮጵያ፤ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ሰንደቋ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ታሰቡ ተወደዱ በምርኮ

12
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ተላልፈህ ተሠጥተሃል። ቀድመህ ግን ፍርድህ ነውና ትፈጫለህ ትጠበሳለህ ሞትን በሚያስለምን እቶን ቁስል
ትጠበሳለህ እውነቱ ይህ ነው።
ወደ ኁዋላ ገጾች ላይ የሚገጥምህን ሁሉ የመደምደሚያህን ስለምትበሰር ሁልህም አስተውለህ ተከታተለው።
ኢትዮጵያውያን እንዲሁ አይደለም እስራኤል ዘነፍስ የተባሉት ብዙ ወገኖቻቸውን ገብረው እንጂ!
እምነታቸውን አፅንተው በምግባራቸው የልዑልን ፍቅር አሸንፈው ነው! እንደ እስራኤል ጥላ ሳይሆኑ እውነት
ሆኑ አላሳዘኑትምና ወደውታልና ታዘውታልና ሳይታክቱ ስለስሙ ስለቃሉ መከራውን ሁሉ ጠጥተዋል። በዚህ ቸሩ
አምላክ መረጣቸው፣ ወደዳቸው አፀደቃቸው አከበራቸው። የምሕረቱን ዘመን አዋልደው በእምነት የሚገኘውን
ቃሉን በመስማትና በማመን በመንፈስ መፅናትን በመቀጠላቸው እንደ ፈቃዱ በመመላለሳቸው ወደዳቸው።
ይበልጥም የነጠሩ የእምነት አርበኞች የተዋህዶ ጀግኖች ይሆኑ ዘንድ በታላቅ የመከራ ውጣ ውረድ ለ700
ዓመታት በጋለው እሳት ላይ በመድኃኔዓለም ታምነው ተዋህዶን አፅንተው መከራውን ሁሉ ጠጥተው በተግባር
እምነት ኖሩበት። በመሆኑም የሁሉ አስገኝ እግዚአብሔር በዚህ የዘመን መካተቻ ተዋህዶን፣ ኢትዮጵያን፣
ኢትዮጵያዊነትን፣ የባሪያው የኖኅን ቃል ኪዳን ምልክት /አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ሰንደቅ/ የጨበጡትን ደማቸውን
የገበሩትን በታላቅ ሰማዕትነት የፀኑትን የተዋህዶ ኦርቶዶክስ አማኞችን አፀደቀ። መረጣቸው፣ ለመጪው
የትንሳኤው ዘመን ለበረከቱ ለመፅናናቱ ለፊተኛው ትንሣኤ ተከላቸው። ዓለም ነግሬህ ነበር ገና በመጀመሪያው
መልእክቴ አመላክቼህ ነበር። አልሰማህም፤ ጆሮህንም ወደመልእክቱ አላዘነበልክም! ናቅኸው አቃለልከው፤
ዛሬም ያው ነህ፤ 15 ዓመት አለፈ ዛሬ ይህንኑ እውነት ቢመርህም እውነት ነውና ተጋተው። የልዑል ቃል
አይሻርምና! እውነቱ ይኸው ነው።
ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ሕዝቦች! ከላይ እንደገለጥኩላችሁ እውነቱ መጣ! ከዘመናት በፊት እግዚአብሔር
አፅንቶ የተናገረው ቃል ኪዳኑን ያፀና ዘንድ ሰዓቱ ሞላ። ለቀደመው እባብ፣ ለዘንዶው፣ ለሃሰተኛው ነብይ
የሰገድህ ያመለክህ ምልክቱንም የጨበጥህ ታምነህ የኖርክበት መናፍቅ፣ ካቶሊክ፣ እስላም፣ ዘረኛ፣ ዋቄ ፈታ፣
ሺንቶኢዝም፣ ታኦኢዝም፣ ኮንፊሺያኒዝም፣ ሂንዱኢዝም፣ ሲኪዝም፣ ጣኦት አምላኪ፣ ተብታቢ፣ አባይ ጠንቋይ
ኮኮብ ቆጣሪ፣ ቅባት፣ ፀጋ፣ ግብረ ሶዶም አመንዛሪ እንዲሁም ተምሬአለሁ የምትል እውቀትህን ወረቀትህን
የምታመልክ፣ ሀብት ንብረትህን የምታመልክ ሁሉ ይህ አካሄድህና መታመንህ ሁሉ ያረፈው ዲያብሎስ ባደራጀው
መንገድ ላይ ነውና! ይህንንም ሰምተህ ስትወቀስ ስትመከር ስትጠበቅ በንስሓ እንደመመለስ በክህደትህና
በጥፋትህ በከፋ ኃጢአትህ ስለዘለቅህ የፈጠረህን እጁን ዘርግቶ በፍቅር የጠራህን ስለኃጢአትህ የሞተልህን
መድኃኔዓለምን ስለካድክ በምትኩም የቀደመውን እባብ ዘንዶውን ሃሰተኛውን ነብይ ስላመለክህ በቁጣው
የነደደው እግዚአብሔር እቶን ሆኖ ሊያነድህ መጣ! ገና ከጅምሩ የተፃፈውን ትእዛዝ አሰርቱ ትእዛዛትን በሙሴ
አማካኝነት ሲሰጥህ የመጀመሪያይቱ ትእዛዝ ምን እንደምትል ላስታውስህ –– ከኔ በቀር ሌላ አምላክ አታምልክ፣
በሰማይም በምድርም ካለው ማናቸውንም ምስል ጣኦት አታምልክ አትስገድ እኔ አምላክህ የፈጠርኩህ የምቀና
በብርቱም የምባላ እሳት ነኝ፣ ተጠንቀቅ! አላለህም? ማንን ፈርተህ! መካድህና ማምለክህ ብቻ በሆነ! ጭርሱኑ
ተዋጋኸው፤ በስሙ የታመኑትን እውነተኞቹን አጠፋህ ገደልክ፣ አረድህ ደማቸውን እንደጉድፍ አፈሰስህ
ለቀደመው እባብ ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ ግብር አደረግሃቸው። ስለዚህ ፍርድህ ተጭኖ መጣ!
በዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 16፣ 18፣ 19፣ የተገለፀው የፍርድ ቃል ትእዛዝ ባንተ ላይ ይፈፀም ዘንድ
ከመንበሩ ከልዑል ትእዛዝ ወጣ! ውጤቱንም ልንገርህ ከምድር በታላቅ ቁጣና መቅሰፍት ዘርህም እንኳን ሳይቀር
ትጠረጋለህ በእሳት ትበላለህ! ለዘለዓለም እስከዘለዓለም ምልክትህም አይገኝም! ቢመርህም እውነቱ ይኸው።
በቃ! ተፈፀመ!!!
የእግዚአብሔር ወገኖችና ቤተሰቦች በታላቁ መከራ ታምናችሁ በታመነው አምላክ በሥላሴ ፀንታችሁ ውድ
ዋጋ ከፍላችሁ፤ ስለመታመናችሁ ተጨፍጭፋችሁ ዘወትር ተርባችሁ ተጠምታችሁ ታሥራችሁ ተገድላችሁ

13
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ተሳዳችሁ የኖራችሁ ሁሉ ስለ ተዋህዶ እምነታችሁ ዛሬም በዚሁ ሰዓት የስቃይ ዓይነት እየፈሰሰባችሁ ያላችሁ
ወገኖቼ ኢትዮጵያዊነትን ተዋህዶ ኦርቶዶክስን አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ሰንደቃችሁን ምልክታችሁ ያደረጋችሁትን
በመላው ዓለም በዚሁ እምነታችሁ በየዋህነታችሁ የፀናችሁት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! ዓለምን በእምነታችሁ
በፅናታችሁ አሸንፋችኋል። ጀግኖች በእሳት የነጠራችሁ የተዋህዶ አርበኞች እንኳን ደስ አላችሁ። ዘመንን
ዲያብሎስ ያነገሰውን የጨለማ ወቅትን ሳትፈሩ በመድኃኔዓለም አባታችሁ በድንግል እናታችሁ ታምናችሁ
በፅናት ቆማችሁ ለድል በቅታችኋል። ልዑል አምልካችሁ ሊባል ይገባል አላሳፈራችሁትም ሊክሳችሁ አብዝቶ
ሊወዳችሁ ይገባል። በእሳት የተፈተናችሁ ወርቅ ልጆቹ ናችሁና!

እስራኤል ዘነፍስ ወይም ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት ነው?

ኢትዮጵያ ውስጥ የተካተቱ፣ በኢትዮጵያዊነት ስም እንደዜጋ የተቆጠሩ ሁሉ እስራኤል ዘነፍስ አይባሉም


ተብለውም አይቆጠሩም። እስራኤል ዘነፍስ የሚባሉት የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትን አፅነተው የያዙ፣ ኢትዮጵያ
የድንግል እርስት መሆኗን የሚያምኑ፣ ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመሥገኛ ምድር መሆኗን
የሚያምኑ፣ በተገባላት የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን መሰረት ከፊታችን በሚመጣው ጊዜ ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መሆኗን የሚቀበሉና የሚታመኑ ሁሉ እስራኤል ዘነፍስ ወይም የቃል ኪዳኗ ተቀባይ
የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። ትክክለኛ ኢትዮጵያዊ። ኤሳው የአሕዛብ አባት፣ ለእስራኤል ዘሥጋ ምሳሌ ሆኖ
የሚቆጠር እንደሆነ ሁሉ ያዕቆብ ደግሞ በይስሃቅ የተመረቀ በእናቱ በርብቃ የተወደደ ስለነበር የእስራኤል ዘነፍስ
ምሳሌ ሆኖ የሚቆጠር ነው። ዛሬም እኛ ኢትዮጵያውያን ከላይ እንደገለፅኩት መስፈርቱን የምናሟላ ከሆንን
እውነተኛ ኢትዮጵያውያን የትንሳኤው ሙሽሮች ነን ማለት ነው። ኢትዮጵያዊነትን የማያሟሉ እነማናቸው?
በፖለቲካው ስያሜ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ነገር ግን ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ ተቆርጠው የወደቁ ነገም ደርቀው
የሚወገዱና በእሳት የሚበሉትን እንይ!
መናፍቅ፦ እነዚህ ሕዝቦች የነጩን እምነት የወረሱ ከተዋህዶ እምነት ጋር ፍፁም የተጋጩ ኢትዮጵያዊነት
ስሜቱም ፍቅሩም የሌላቸው የዲያብሎስ አምላኪዎች ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ሰንደቋ ፀረ ተዋህዶ ናቸው። ለአገር
መፍረስ በውጪ ኃይሎች እየተገፉ የሚሠሩም ናቸው። ካቶሊኮችም በተመሳሳይ እንደመናፍቃን ናቸው።
እስላሞች፦ እነዚህ ኢትዮጵያዊነትን የማይቀበሉ በተረቱ እምነታቸው ለክተው የሚያዩ፤ ሁሉን አጥፍተው
እስልምናን እናነግሳለን ብለው ንፁህ ደም የሚያፈሱ ናቸው ኢትዮጵያዊነትን ከመካ መዲና ከአረብ የሃይማኖት
አምሳዮቻቸው አሳንሰው የሚያዩ ናቸው።
ዘረኞች ዋቄ ፈታዎች፦ እነዚህም በግልፅ ኢትዮጵያዊነትን የሚጠሉ አረንጋዴ ቢጫ ቀዩን ሰንደቃችንን
አምርረው የሚጠሉና እስከማቃጠል የደረሱ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ብለው በግልፅ የተናገሩ ናቸው። በኢትዮጵያ
ምድር ከተዋህዶ ኦርቶዶክስ ውጪ የሆኑት ሁሉ ፀረ ኢትዮጵያ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት ለኢትዮጵያ፤ ለእውነተኛ ክብሯ የቆሙ እነማን ናቸው? ከመሪው ጀምሮ ሁሉም የፖለቲካ
ቁማርተኞች ማን ምን እንደሚሠራ ምን እንደወጠነ የማን ጉዳይ ፈፃሚ እንደሆነ ለማወቅ የፈለገ ሁሉ በሚሠሩት
ሥራ ሊያውቃቸው ችሏል። መንግሥታችን ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን ለእንግሊዝና አሜሪካ በዋናነት፣
ለአረብ ኤሜሬትስና ለሳውዲ በቀጣይነት ለቻይና በተጨማሪነት ፍላጎታቸውን እያሟላ ያለ መንግሥት ነው።
በሥልጣን ላይ ለመቆየት በማሰብ። በየትኛውም የዓለም ገጽታ እንደ አገር እንደ ሕዝብ የቆመ መንግሥት በሙሉ
የኃያላኑ መንግሥታት ታዛዥ ነው። የነሱንም ፈቃድ ፈፃሚ ነው።
ከላይ መጪውን እርምጃ ተረድታችኋል የማይቀር ውሳኔ ነው። በኢትዮጵያ ተደጋግሞ እንደተነገረው
የሚቀሩት እውነተኞቹ የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሕዝቦች ብቻ ናቸው። በኢትዮጵያ ጥላቻ የተሞሉ፣
ሰንደቋን የጠሉና የናቁ፣ አገርነቷንም ሊያፈርሱ የሚደክሙ እየጣሩ ያሉ ሁሉ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥም

14
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በህዝቡ ውስጥም በፖለቲካው መዋቅር አናትና ውስጥም ያሉ አገርን በሆዳቸው የሚለኩ፤ ለከርሳቸው ስብናቸውን
የሸጡ ሲጋልቧቸው የሚጋለቡ የጥፋት አጀንዳ ሲያሸክሟቸው ያለምንም ማንገራገር የሚሸከሙ፣ እንደ አህያይቱ
የሚነዱ ሁሉ፣ በገዛ ወገናቸው ላይ ለሆዳቸው ተገዝተው የሕዝባቸውን ደም የሚያፈሱ የሚያስገድሉ የሚያሳድዱ
የሚያስሩ ሁሉ ፀረ ኢትዮጵያ ናቸው። ፍርዳቸው የማይሻር ነው። ከነዘራቸው የሚጠፉ ናቸው።
በመላው ኢትዮጵያ ተበትነህ የምትኖር ወገኔ በኢትዮጵያዊነትህ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትህ ይችንም
እምነት በጨበጠው ዘርህ /አማራነትህ / የምትጨፈጨፍ የእግዚአብሔር ድሃ ልምክርህ ስማ! አባቶችህን አስብ!
ጥንካሬአቸውን እንዴት እንደነበር ተረዳ። አንተም ከነሱ አብራክ ነው የወጣኸው እምነትህን ተዋህዶን አጥብቀህ
ያዝ በእምነትህ አትደራደር ራስህን አደራጅ አስታጥቅ! ማንም የሚረዳህ የለም ከምትታመንበት እግዚአብሔር
በስተቀር። መንግሥት አልደረሰልህም! ስትታረድ ስትጨፈጨፍ መግለጫ እንኳን አላወጣልህም፤ መንግሥት
መንግሥት የሆነው ዜጎቹን ሊጠብቅ ነው ይህ መንግሥት ግን ፍፁም ጨካኝ የሆነ ስለሥልጣኑ ብቻ የሚጨነቅ
ነው፤ ለዚህ ደግሞ የማይክደው ተግባሩን ስናነሳ በመላው የአዲስ አበባ የመንግሥት ተቋማት ውስጥ ከአንድ
የኦሮሞ አካባቢ በወጡ ዘሮቹ መሙላቱ ሲሆን ለዚህ ምንም የሰጠው የጥፋት ምክንያት የለም በቃ እኛ ተራችን
ነው ውጡ እያለ ከሥራ ገበታቸው እያባረረ አይኑን በጨው አጥቦ ተቀምጧል፤ ደግሞም አያፍርም ለእድገት
ለሰላም ለእኩልነት ነው የምደክመው ይላል። የምታየው መንግሥት ግን አንተን ንፁህ ኢትዮጵያዊውን እጅግ
ነው የሚጠላህ ምክንያቱም እምነቱ በእግዚአብሔር የተጠላ መናፍቅነት እስልምና ነውና አይፈልግህም። በገዛ
ሀገርህ እሱ መወገድ ሲገባው በቤትህ በሀገርህ ያንተን ሕልውና የሚወስን ሆኖ እያሰቃየህ ነው። ለዚህ ሁሉ
ግን ጥፋቱ የራስህ ነው። እየሞትክ እግሩ ሥር ነህ ምን እንዲያደርግልህ ከሚገልህ ውጪ! ስለዚህ ከወገንህ
በእምነት ከሚመስልህ አገሩን በእውነት ከሚወድ ጋር ተደራጅ ታጠቅ እራስህን እምነትህን አገርህን ጠብቅ።
ትጥቅህን ለማንም አትስጥ! ራስህን ሁሌ ዝግጁ አድርግ የአባቶችህ ወኔ ይሽተትህ! በአማራነትህ ብቻ አይደለም
የተዘመተብህ በዋናነት በእግዚአብሔር እጅግ በተወደደቸው ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነትህ ምክንያት ነው። ልብ
በል! በተዋህዶ እምነት ላይ ሁሉም ዓለም ዘማች ነው። ሊያጠፉህ! ምክንያትም የሆኑት ከተዋህዶ ውጪ የሆኑ
እምነቶች ሁሉ ናቸው። የቀደመው እባብ፣ የዘንዶው፣ የሃሰተኛው ነብይ የደረሳቸው የክህደት ትምህርቶቹም
ናቸው። ሁሉም እሱን የሚያመልኩ የሚሰግዱለት፣ ምልክቱንም የተቀበሉ ናቸው። ስለዚህ በታላቅ ቁጣና
መቅሰፍት በቅርቡ ከፊትህ የሚጠረጉ ናቸው። ስለዚህ ወገኔ የእግዚአብሔር ሕዝብ ተዋህዶነትህን አጠንክር
እምልህ ለዚህ ነው።
የዮሐንስ ራእይ 20 ስለፊተኛይቱም ትንሳኤ ምን እንደሚል! የቀደመው እባብ የዘንዶው የሃሰተኛው ነብይ
እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን በግልፅ የተቀመጠበት መልእክት በመስከረም 21 2004 ዓ.ም ወጥቶ በሚገባ
ተገልጦበታል። ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሐዋሪያው ዮሐንስ እጅግ አብዝቶ ከሚወደው ከመድኃኔዓለም
እሱም /ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ/ ከሐዋሪያት ሁሉ አብዝቶና የልብ ወንድሙና ልጁ አድርጎ
ይወደው የነበረ ዮሐንስ ያልተገለጠለት ሚሥጥር የለም። የልብ ፍቅሩን በግልፅ ያሳየው ዮሐንስ በጌታችን መከራ
ከጅምሩ እሰከፍፃሜው ሳይለይ በነፍሱም በሥጋውም ከፍተኛ ሃዘንን ለብሶ የዘለቀ ነበር። ሐዋሪያው ዮሐንስ
በእምነት ፅናቱ ቅንጣት መዋዠቅ ያልታየበት ነበር። ጌታም ዮሐንስን እናቱን እናታችንን እነሆ ብሎ አደራ
የሰጠው ለሱ ነበር። ወገኖቼ ሐዋሪያው ዮሐንስ የጌታ የልብ ወዳጅ ነበርና በራሱ ቃል ስለሰማው ስለተረዳው
ሲናገር ሁሉንም በመጽሐፍ ለመግለፅ የማይቻል ብዙ ሚሥጥርን እንደተረዳ ገልፆታል። ይህ ሐዋሪያ የፃፈውን
እውነት ከጌታ የተገለጠለትን የዓለም መፃኢ እጣ ፈንታ የዮሐንስ ራእይ በሚል በመጽሐፍ ቅዱስ መጨረሻ
ላይ አስቀምጦልን በክብር ወደጌታው ሄዷል። በእውነቱ ለመናገር በእምነት ስትመላለሱ እንደሐዋሪያው ዮሐንስ
በእምነታችሁ የማትዋዥቁ፤ በማናቸውም ውጣ ውረድ መከራ ፀንታችሁ የምትቆሙ ልትሆኑ ይገባል። እንደሱ
በእምነታችሁ በእውነታችሁ በምግባራችሁ ሁሉ ሥላሴን በፍፁም ልባችሁ በፍፁመም ሃሳባችሁ በፍፁም

15
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ነፍሳችሁ ልትወድዱት ይገባል። ይህን ስል የሌሎቹን ታላላቅ ሐዋሪያት ተጋድሎና ታላቅነት ሰማዕትነት ማሳነሴ
አይደለም። ሁሉም በእግዚአብሔር ፊት ከብረዋል የእምነታችንም አምድ ሆነዋል።
ወገኖቼ! ዛሬም ደግሜ ላንሳልህና ሊፈፀም ከፊትህ እየታየ ባለው ሁኔታ ላይ ነሀና የዮሐንስ ራእይ 20 ምን
ይላል የሚለውን እንይ!!

የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ።
የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው ሺ
ዓመትም አሰረው። ወደጥልቁም ጣለው፤ አሕዛብንም ወደፊት እንዳያስት፤ ሺህ
ዓመትም እስኪፈፀም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማህተም አደረገበት፣ ከዚህም በኋላ
ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።
ከዚህ በኋላ ዙፋኖች ተዘርግተው የሰው ልጅ በላያቸው ተቀምጦ አየሁ። ስለ ኢየሱስና
ስለ እግዚአብሔር ቃል ስለሞቱ ሰዎች ነፍስ ቅን ፍርድን ፈረደላቸው። ለአውሬውና
ለምስሉ ያልሰገዱትን ምልክቱንም በግንባራቸው በእጃቸውም ላይ ያልተቀበሉትን
አየሁ። ከክርስቶስም ጋር ሺህ ዓመት ኖሩና ነገሱ። የቀሩት ሙታን ግን ይህ ሺህ
ዓመት እስኪፈፀም ድረስ በሕይወት አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሳኤ ነው።
በፊተኛው ትንሳኤ እድል ያለው ብፁእና ቅዱስ ነው። ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ
ስልጣን የለውም። ዳሩ ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ። ከእርሱም
ጋር ይህን ሺህ ዓመት ይነግሳሉ።
ሺሁም ዓመት ሲፈፀም ሰይጣን ከእሥራቱ ይፈታል። በአራቱም በምድር ማዕዘን
ያሉትን አሕዛብ ጎግንና ማጎግን እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያስከትታቸው
ይወጣል። ቁጥራቸውም እንደ ባሕር አሸዋ የሚያህል ነው። ወደ ምድርም ስፋት ወጡ
የቅዱሳንንም ሰፈርና የተወደደችውን ከተማ ከበቡ፣ እሳትም ከሰማይ ከእግዚአብሔር
ዘንድ ወርዳ በላቻቸው። ያሳታቸውም ዲያብሎስ አውሬውና ሃሰተኛው ነብይ ወደ
አሉበት ወደእሳቱና ወደዲኑ ባሕር ተጣለ። ለዘለዓለም እሰከ ዘለዓለም ቀንና ሌሊት
ይሰቃያሉ።
ታላቅና ነጭ ዙፋን በእርሱም ላይ የተቀመጠውን አየሁ ምድርና ሰማይም ከፊቱ
ሸሹ። ሥፍራም አልተገኘላቸውም። ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ
ፊት ቆመው አየሁ፣ መጽሐፍት ተከፈቱ ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት
መጽሐፍ ነው። ሙታንም በመጽሐፍት ተፅፎ እንደነበረ እንደሥራቸው መጠን
ተከፈሉ። ባሕርም በሱ ውስጥ ያሉትን ሙታን ሰጠ። ሞትና ሲኦልም በእነርሱ ዘንድ
ያሉትን ሙታን ሰጡ። እያንዳንዱም እንደሥራው መጠን ተከፈለ። ሞትና ሲኦልም
በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣሉ። ይህም የእሳት ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው። በሕይወትም
መጽሐፍ ተፅፎ ያልተገኘው ማንኛውም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣለ።
የዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 20 በሙሉ
በመልእክት አምስት መስከረም 21 ቀን 2004 ዓ.ም. የዚህን /የዮሐንስ ራእይ 20ን/ አንድምታ በአግባቡ
ለመግለፅ ሞክሬአለሁ።
ይህንን የዮሐንስ ራእይ ብዙ ምሁራን በተለያየ መልኩ ተርጉመውታል።
»» በትርጓሜአቸውም ሁሉም ማለት ይቻላል። ሁለት ትንሳኤ የለም። ስንጠመቅ የመጀመሪያው ትንሳኤ
ነው፤ ሁለተኛውን በመጨረሻው ከፍርድ በኋላ ያለው ትንሳኤ ነው ይላሉ።

16
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

»» ሁለተኛው ደግሞ ክርስቶስ ሺውን ዓመት ይነግሳል የሚለውንም አይሆንም ያው በመጨረሻ ፍርድ
ትንሳኤ ሲሆን ከነሱ ጋር ይነግሳል። ብለው ይደመድማሉ። እንግዲህ የቀደመው እባብ፣ ዘንዶው፣
ሃሰተኛው ነብይ ሁሉንም የምድር አለቆች ስለተቆጣጠራቸው በምሁር መነፅራቸው የሚሰጡት
ትርጉም ነው። ሃሰተኛው ነብይ ሥራው ሃሰትን እንደእውነት ማስረፅ ስለሆነ፣ በታላላቅ የስነ መለኮት
ዩኒቨርሲቲዎች ኮሌጆች የሚሰጠው ትምህርትም ከላይ እንደገለፅኩላችሁ ሃሰተኛው ነብይ በሁሉም ስነ
መለኮት ትምህርቶቹ እውነት መሰል የተጣመሙ ትምህርቶችን ስላስጨበጣቸው በምድራችን የሚከሰት
ትንሳኤ የለም። ስንሞት ያው ምድር ስታልፍ የመጨረሻው ፍርድ ሲሰጥ የሚሆን ትንሳኤ ነው ያለው
ሌላ የለም ብለው ደምድመዋል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያን ትንሳኤ እንደተረት የሚቆጥሩ ሆነዋል።
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት የተገለፀውን የእግዚአብሔር እውነት አሁንም በዚህ ዘጠነኛ መልእክት
ከዚህ በታች ባለው መልኩ በድጋሚ እንገልፀዋለን።
ሺው ዘመን በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገላጭነት እንዲህ እንረዳዋለን፦
ቃል በቃል ስንሄድበት የመጀመሪያው ቃል እንዲህ ይላል፤ –– የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት
በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። ይህን ቃል ከማየታችን በፊት፤ ሺው ዘመን ስንል ምን ማለታችን
ነው? እግዚአብሔር ዘመንን ፈጣሪ ነውና ስለ አቆጣጠሩም ምስጢር የተገለጠለት ሐዋሪያው ጴጥሮስ ሲገለጠው
አንድ ቀን በእግዚአብሔር ዘንድ እንደ ሺህ ዓመት ይቆጠራል እንዲሁም ሺው ዘመን እንደ አንድ ቀን ይቆጠራል
ብሎናል። ስለዚህ ዘመንን በቁጥር መለካት ለኛ እንጂ በእግዚአብሔር ዘንድ በማናቸውም ጊዜና ሰዓት ዘመን
ፈቃዱን አይገድብም እሱ በወሰነው ሰዓት ያለቀጠሮ ፈቃዱ ተፈፃሚ ይሆናል። በመሆኑም ሺው ዘመን ሊያንስም
ሊጨምርም ወይም በግማሽ ሊፈፀምም ይችላል። እግዚአብሔር እኔ እንደሌባ እመጣለሁ አለ እንጂ በዚህ ቀን
በዚህ ሰዓት በዚህ ደቂቃ እመጣለሁ አላለም። በመሆኑም በቁጥር መወዛገቡ አስፈላጊ አይደለምና! ፈቃደ
እግዚአብሔር ሲፈፀም ሊያጥርም ሊረዝምም፤ በተገለፀው ቁጥርም ሊሆን ስለሚችል በእምነት መጠበቅ ዋናው
ተግባር ነው። ሰንሰለቱንና የጥልቁንም መክፈቻ የያዘው መልአክ ከልዑል በታዘዘው መሰረት ዲያብሎስና
ሰይጣን የተባለውን ያዘው ሺህ ዓመትም አሰረው። ወደጥልቁም ጣለው አሕዛብንም ወደፊት እንዳያስት ሺው
ዓመትም እስኪፈፀም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማህተም አደረገበት። እንግዲህ ወገኖቼ ታላቅ ሰንሰለት እንዲሁም
የጥልቁን መክፈቻ የያዘው መልአክ ከሰማይ ወዴት ወረደ? ወደ ምድር የታዘዘውን ለመፈፀም ማንን አሰረ ማንን
ወደ ጥልቁ ጣለ? የቀደመውን እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን። ለአውሬው ለቀደመው
እባብ፣ ዘንዶና ሃሰተኛው ነብይ ያልሰገዱ ያላመለኩ ምልክቱንም ያልተቀበሉ በእግዚአብሔር ቅን ፍርድ
ነፃነታቸውን ሲጎናፀፉና የተጠቀሰውን ሺህ ዘመን ሲፅናኑ፤ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ በጥልቁ
ውስጥ ታስሮና ተጥሎ ሺውን ዘመን ያሳልፋል። ከዚህ መፈፀም በኋላ ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል። ይህ
የመጨረሻው የፍርድ ሰዓት የሚያመላክት ነው።
እንግዲህ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ከተከረቸመ በኋላ ምን ይከናወናል? ከዚህ በኋላ ዙፋኖች
ተዘርግተው የሰው ልጅ በላያቸው ተቀምጦ አየሁ። ይላል የራእዩ ቃል። የሰው ልጅ መድኃኔዓለም ነው።
ዙፋኖች ከአንድ በላይ መሆናቸውን ስለሚያሳይ ሶስቱም አካል ሥላሴ መኖራቸውን በፈቃዳቸው የሚከናወን
መሆኑን ያረጋግጣል።
ሲቀጥል ደግሞ! ስለ ኢየሱስና ስለ እግዚአብሔር ቃል ስለሞቱ ሰዎች ነፍስ ቅን ፍርድን ፈረደላቸው።
አዎን ስለ እግዚአብሔር ቃል ስለእውነቱ ስለተዋህዶ ብዙ ወገኖች ተጨፍጭፈዋል ተሰውተዋል በሰማዕትነት
አልፈዋል። ዛሬ እንኳን የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት የጨበጡ ኢትዮጵያውን በተለይም አማሮች ዓለም
በተስማማበት ከበስተኋላ ሆኖ በሚደግፈው እቅድ እየተጨፈጨፉ እያየን ነው እየሰማን ነው። ዛሬ ሆኖ
የምታዩት ከብዙ መቶ አመታት ጀምሮ ሲከናወን የመጣ የቀደመው እባብ፣ የቀደመው ዘንዶ፣ ሃሰተኛው ነብይን

17
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የሚያመልኩ የሚሰግዱለት ምልክቱንም ያስጨበጣቸው በተለያየ ዘዴና መልኩ እየፈፀሙት የሚገኝ ያልተሸፈነ
ተግባር ነው። ስለዚህ ቢሰዉም ስለነፍሳቸው ዋጋ በገነት በአፀደ ነፍስ ሆነው የሥላሴን ቅን ፍርድ ያያሉ። ስለቅን
ፍርዱም ሥላሴን ያመሰግናሉ።
ለአውሬውና ለምስሉ ያልሰገዱትን ምልክቱንም በግምባራቸው በእጃቸውም ላይ ያልተቀበሉትን አየሁ፤
ከክርስቶስም ጋር ሺህ አመት ኖሩና ነገሱ። ይህ ቃል ዋናው መሰረታዊው ነጠብ ነው። በዛሬው ዘመን ያለውን
እንይ! የቀደሙት የሆኑትን ሆነው አልፈዋል። የዛሬው ምን ይመስላል። ለአውሬው የሰገዱ እነማናቸው?
መላው ዓለም ለአውሬው ሰግዷል ማለት ይቻላል። ምክንያቱም ያልሰገዱት ቁጥራቸው ኢምንት ነውና!
ኢምንቶቹ ያልሰገዱት እነማን ናቸው?
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችና እውነተኞቹ አማኞች ናቸው። ባጭሩ መልሱ ይህ ነው። ሁሉም
ኦርቶዶክስ ይህን አያሟላም ምክንያቱም፤ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሆኖ፤ በልማድ ብቻ ስሙን አንጠልጥሎ ተብታቢ፣
ጠንቋይ፣ ኮኮብ ቆጣሪ እንዲሁም ከተለያዩ እምነቶች ጋር የተዳበለ ንስሓ ሳይገባ ዘወትር የሚሰርቅ የሚነጥቅ
የሚዋሽ የሚያመነዝር ትእቢተኛ አታላይ ክፉ ጨካኝ ባሕሪ ይዞና ተሸክሞ ያልንስሓና መፀፀት የሚመላለስ፤
ተሃድሶ ቅባት ፀጋ እያለ ቤተ ክርስቲያንንና መሰረታዊ ሕጓን ያፈረሰ እረኞች ሆነው ከመናፍቁም ከካቶሊኩም
ከእስላሙም ለውሸት አላማቸው ሲሉ፤ ለፖለቲካው ለገዢው መሳሪያ የሆኑና ምእመኑንም እንደዚያው ያደረጉ፤
ለካሃዲዎች ለአውሬው መንግሥታት ሹመኞች በታማኝነት የሚያገለግሉ ሁሉ ለአውሬው የሰገዱ ናቸው።
ለአውሬው የሰገዱ ያመለኩ ምልክቱንም በግምባራቸው በእጃቸው የጨበጡ እነዚህ ናቸው፤ –– እስላም፣
መናፍቅ፣ ካቶሊክ፣ አንግሊካን፣ ፐሬስባይቴሪያን፣ ሰባተኛው አድቬንትስት፣ ጂኦቫ፣ ፕሮቴስታንት የሆኑ
በሙሉ፣ሺንቶኢዝም፣ ታኦኢዝም፣ ኮንፊሺያኒዝም፣ ሂንዱኢዝም፣ ሲኪዝም፣ እንዲሁም በቁጥር ለመገመት
የሚያስቸግሩ የልማድ እምነት የጨበጡ ከዚህም በላይ ባለእውቀቶች እውቀታቸውን ጥበባቸውን ወረቀታቸውን
የሚያመልኩ፣ ሃብታቸውን የሚያመልኩ ሁሉ ለአውሬው የሰገዱ የሚያመልኩ ምልክቱንም የተሸከሙ ናቸው።
እነዚህ ዛሬ የምናያቸው የአውሬው ልጆች ሲጠረጉ የሚቀሩት ለአውሬው ያልሰገዱት ያላመለኩት ስለሆነ
ከክርስቶስ ጋር የሚነግሱ ናቸው። ወደትንሳኤው የሚሻገሩ ናቸው። እውነቱ ይህ ነው። ክርስቶስ እንዴት
ይነግሳል? አዎን ይነግሳል። በመረጣቸው ባሮቹ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በላያቸው ያርፋል። ክርስቶስን
ይለብሱታል። በነዚህ ቀዳማይ አገልጋይ ባሮቹ ላይ ያረፈው ክርስቶስ ከቀሩት ሕዝቦቹም ላይ ቅዱስ መንፈሱን
ስለሚያሳርፍ አብሮ ነገሰ ማለት ሚስጥሩ ይኸው ነው። የሚወድደውን ያደርጋሉ፣ የሚጠላውን ይጠላሉ።
መሪያቸው አስተማሪያቸው ሁሉንም የሚያከናውነው በእነሱ ያደረው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና።
የቀሩት ሙታን ግን ይህ ሺው ዓመት እስከሚፈፀም ድረስ በሕይወት አልኖሩም። ዓለም ከተፈጠረች ጀምሮ
በምድር ላይ ከአዳምና ሔዋን የተፈጠረ በሞት የተከደነ ሁሉ በዚህ የመጀመሪያው ትንሳኤ አይነሳም። የሚነሱት
ለመጨረሻው ፍርድ ዓለምም በምታበቃበትና በምትሰናበትበት ጊዜ ብቻ ነው።
በፊተኛው ትንሳኤ እድል ያለው ብፁእና ቅዱስ ነው። ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም።
እንግዲህ ቃሉ ግልጽ ነው። በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት ግልፅ ተደርጓል። የትንሳኤው ባለቤት
የተዋህዶ እምነትን ያፀናችው ኢትዮጵያ ናት። ዓለም በሙሉ እየጨፈጨፋት ፀንታ የቆመችው እሷው ናት።
የክርስቶስ ካህናትም የሚሆኑት የተዋህዶ አርበኞቹ ናቸው። ረጅሙን ዘመን በምድር የሚነግሡትም እነሱ
ናቸው። ከዚህ በኋላስ?
ሺውም ዓመት ሲፈፀም ሰይጣን ከእሥራቱ ይፈታል። በአራቱም በምድር ማእዘን ያሉትን አሕዛብ ጎግንና
ማጎግን እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያስከትታቸው ይወጣል። ቁጥራቸው እንደ ባሕር አሸዋ የሚያህል ነው።
ወደ ምድርም ስፋት ወጡ የቅዱሳንንም ሰፈርና የተወደደችውን ከተማ ከበቡ፤ እሳትም ከሰማይ ከእግዚአብሔር
ዘንድ ወርዳ በላቻቸው። ያሳታቸውም ዲያብሎስ አውሬውና ሃሰተኛው ነብይ ወደ አሉበት ወደ እሳቱና
18
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ወደ ዲኑ ተጣሉ። ከመጀመሪያው ትንሳኤ መጀመርና መፈፀም ጀምሮ የታሰረው ዲያብሎስ ለአጭር ጊዜ


ተፈቶ፤ በመጀመሪያው የትንሳኤ ዘመን ልዑልን ስታከብር ስታመሰግን የቆየችውን ከተማ፣ በእግዚአብሔር
የተወደደችውን ከተማ ለማጥፋት ይከባል፤ በዚህ የዲያብሎስ ድርጊት መነሻነት የእግዚአብሔር ፍርድ ይገለጣል
እሳት ትወርዳለች ዲያብሎስንና ዝግንትሉን ትበላለች።
ያሳታቸውም ዲያብሎስ አውሬውና ሃሰተኛው ነብይ ወደ አሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ። ይኸው
በድፍረት የዘመተው ዲያብሎስ አለቆቹ ወደ አሉበት ወደ እሳት ባሕር ተከተተ። ለዘለዓለም እስከዘለዓለም
ቀንና ሌሊት ይሰቃያሉ። ይህ እንግዲህ የቀደመው እባብ የአውሬው የሃሰተኛው ነብይ የዲያብሎስ መደምደሚያ
ነው። ታላቅና ነጭ ዙፋን በእርሱም ላይ የተቀመጠውን አየሁ ምድርና ሰማይም ከፊቱ ሸሹ። ሥፍራም
አልተገኘላቸው። ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ። ይህ ማለት የሰው ፍጥረት
ሁሉ በሕይወት ያለውም የሌሉት ሙታንም ለመጨረሻው ፍርድ በልዑል ፊት ይቆማሉ። ወደገሃነም የሚገባው
ወደዚያው ይሰናበታል። ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚገባውም በልዑል ተባርኮና ተመስግኖ ወደእዚያው ይገባል።
መፃሕፍት ተከፈቱ ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው። ሙታንም በመጻሕፍት ተፅፎ
እንደነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈለ። ባሕርም በእርሱ ውስጥ ያሉትን ሙታን ሰጠ ሞትና ሲኦልም
በእነርሱ ዘንድ ያሉትን ሙታን ሰጡ። እያንዳንዱም እንደሥራው መጠን ተከፈለ። ሞትና ሲኦልም በእሳት ባሕር
ውስጥ ተጣሉ። ይህም የእሳት ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው። በሕይወት መጽሐፍ ተፅፎ ያልተገኘው ማንኛውም
በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣለ።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! እውነቱ ከላይ የገለፅኩላችሁ ነው። የኢትዮጵያ ትንሳኤ የለም ለሚሉ ሁሉ
ከላይ ገልፀናል። እኛ መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ ነው የምንሰማው ይላሉ። ሁሉም መናፍቅ ይህንኑ ይላል። ዛሬም
የኛው ሰባኪ ነን የሚሉ ከመናፍቅ መፈልፈያው ኮሌጅ ተመርቀናል ይላሉ በየመድረኩ እየዘለሉ በድፍረት
ዲያብሎስ በሰጣቸው ትእቢት ተሞልተው የቀደሙት አባቶቻችንን ገድል መንፈሳዊ ተጋድሎ ይንቃሉ።
ያቃልላሉ። በተጋድሎአቸው ዘመናቸውን ሁሉ ለእምነታቸው ለተዋህዶ ተንከራተው ተቀጥቅጠው ተሳደው
ተርበው ተጠምተው ሲብስም ታስረው ተገርፈው እንዲሁም በሰማዕትነት ያለፉትን ሁሉ ያቃልላሉ። በዚህ ሁሉ
ዋጋ ያፀኑትን ድንበር ያፈርሳሉ። እነዚህ የዘመናችን ጉዶች በእነሱ የክህደት አንደበት ሊነሱ ቀርቶ ሊታሰቡ
ያልተገባቸውን የተዋህዶ አርበኞችን ከልዑል ተገልጦላቸው የተናገሩትን የትንቢት ቃል ሲክዱና ምንፍቅናን
ሲያፀኑ እየተመለከትን ነው። ሰማዕቱ ፊቅጦር በገድሉ ላይ ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ ያስቀመጠውን ሲክዱ፤ በሊቀ
መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ድርሳን በግልፅ የተቀመጠውን ሁሉ ሲሽሩ እነሆ እየሰማን ነው። ነጭ የፈለፈላቸው
ጉዶች እራሳቸው የቀደመው እባብ የዘንዶው የሃሰተኛው ነብይ ደቀ መዝሙር ሆነው እውነትን የሚገለፅበትን
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታትን ሲተቹና ሲነቅፉ ሲሳደቡም እየተመለከትን ነው። እነዚህ ዲያብሎስ
የተላበሳቸው ደቀመዝሙሮቹ፤ በሉ የተባሉትን እንደበቀቀን የሚያስተጋቡ ናቸው። የሆነ ሆኖ እነዚህ ፍርዳቸውን
ሊያገኙ የሚገባ ስለሆነ ወደፊት ውሳኔያችን የሚያርፍባቸው ይሆናል።
ከላይ ወደተነሳንበት ጉዳይ ተመልሰን እናጠቃለው ፡– እንግዲህ በሰፊው ለመግለፅ እንደተሞከረው በሐዋሪያው
ዮሐንስ የተገለፀው የዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 16፣ 18፣ 19፣ እንዲሁም መጠቅለያውና ማሰሪያው ምእራፍ
20 ምን አንደሚል በዝርዝር ለመግለፅ ሞክሬአለሁ። ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ሕዝቦች የእግዚአብሔርን ቃል
ለመረዳትም ሆነ ለማስረዳት ለማስተማርም በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ምስጢር ገላጭነት የሚመራ ሕይወት
በፈቃዱም የሚመራ እምነት በእውነተኛይቱ ተዋህዶ የፀና ሰው ልንሆን ይገባል። ማንም መናፍቅ፣ የኮሌጅ
ምሩቅ ነኝ የሚል የሥነ መለኮት ተመራማሪ የእግዚአብሔርን ቃል እንዳሻው ሊገልጠው አይችልም። ልብ በሉ!
ቀድሞ የተከደነበት ነውና! ያጠለቀው የዚህ ዓለም የእውቀት መነፅር አውሮታልና ሊረዳው አይቻለውም።
እንግዲህ ለዘመኑ ተችዎች ነቃፊዎች ዛሬ ልንገራችሁ። ትንሳኤ ኢትዮጵያ የለም ብላችሁ በድፍረት ለምትናገሩና
ለምታስተምሩ ሁሉ ይህ መልእክት ከወጣ ጀምሮ በምትተቹም ሆነ በምትነቅፉ ላይ ቅጣት ተላልፎባችኋል።
19
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ቅጣቱም ለሰይጣንና ለሰራዊቱ ተሰጥታችኋል በሥጋችሁ ላይ እንዲሰለጥንም ሆኗል፤ ትንሳኤ ኢትዮጵያን ሳታዩ
በሞት እንድትከደኑ ተወስኖባችኋል። ይህም በምንም መንገድ የማይሻር ሆኖ ፀንቷል። እስኪ ከዚህ ፍርድ
ስታመልጡ እንይ። ያ በድፍረት እንድትተቹ እንድትነቅፉ የነዳችሁ ዲያብሎስ ይታደጋችሁ።
እውነትን ጨብጣችሁ፤ እግዚአብሔርን ጠይቃችሁ መልስም አግኝታችሁ የተረጋገጠ ተስፋን ጨብጣችሁ
ያላችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ባለድል ናችሁ። እውር ዓይናማውን ቢተቸው እኔ ልምራህ ቢለው ምንኛ ፌዝ
እንደሚሆን ትረዳላችሁ። ስለዚህ ማንም ተነስቶ በሚደረድረው ከንቱ ቃል ልባችሁን አታስቱ! በቅርቡ ሁሉንም
እንደቃሉ ሲፈፀም ታያላችሁ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የተገለፁ የልዑል የፍርድ ቃሎች መልእክቶች
ሲፈፀሙ አላያችሁም? የቀሩትስ ለመፈፀማቸው ምልክታቸውን እየሰጡ የሰውን ልጅ በእግዚአብሔር የፍርድ
ሚዛን ተለክተው ሲካተቱ እንደምታዩት አልተረዳችሁምን? የጥርጥር ችግር ካለባችሁ ልዑልን ጠይቁ ከሰው
ይልቅ ከሱ የሚሰጣችሁ ማረጋገጫ ይበልጣልና መጠየቅ መብታችሁ ስለሆነ ጠይቁ ተረዱ ተዘጋጁ በቃ! ስላበቃ
ሁሉም የምታዩት የሚያስቷችሁ የአውሬው የዘንዶው የሃሰተኛው ነብይ ደቀ መዝሙሮች ቅጥረኞች ሆድ አደሮች
በሙሉ በቅርብ በክፉ መከራና ስቃይ ሲወገዱ ታዩአቹዋላችሁ።

የቀደሙ አባቶች የእምነት አካሄድና ትምህርታቸው

በቀደመው ዘመን በአባቶቻችን ጊዜ እምነት እምነት ነው። ለድርድር የማይቀርብ ሕይወት የሚሰዋበት።
አምልኮት በእውነትና በመንፈስ በመታመን ነው። ዛሬ ያ የለም። አመልካለሁ የሚለውም ልማድ አድርጎት
መመላለስን እንደ ትክክል የሚቆጥር መሰረቱን ያላጠበቀ ነው። እንደምታዩት እንደምትሰሙት የሚበዛው ወጣት
የዘመኑ እውቀት ሰለባ የሆነ በዚያው እውቀቴ በሚለው የተንሸዋረረ ምልከታው የአባቶቹን እምነት ንቆ የነጩን
እምነት የወረሰ በመሆኑ ለዛሬው የአገራችንም ጥፋት ለትውልዱም በቁም መሞት አድርሶታል። እሱ ሙታን
ሆኖ ድቁቅና ደካማ በመጠጥ በጫት በምንዝርና ደቆና ወድቆ የቤተሰቦችን የተዋህዶ እምነት ይንቃል።
ከአባቶቹ ስለእምነት አይጠይቅም፤ የመናፍቃንን በማር የተለወሰ እሬት እንደእውነት ይጠጣል። አንዴ
ጠፍቷልና ተመለስ ቢሉት አይመለስም።
አባቶቻችን የእውነት ሰዎች ነበሩ። እውነትን እውነት ሃሰትን ሃሰት የሚሉ የግንባር ሥጋ ነበሩ አምልኮታቸውም
ከልብ የመነጨ ሽንገላ የሌለበት በእውነት የፀና ነበር። በአንፃሩ የዛሬው ትውልድ ለሥጋው የሞተ ራስ ወዳድ
ነው። እውቀት ጥበብ የቁሳቁስ እድገት ምድርን ሸፍኗል። ሁሉ ነገር እረቋል። ሳይንስ ያልፈጠረው የለም።ሁሉ
ነገር አፍ ተእጅ ሆኗል።
የጦር መሣሪያው ዘመናዊነት ብዛት ዓይነት እጅግ ብዙ ነው። አውሮፕላኑም እንዲሁ የተዋጊው የሰው
ማመላለሻው መርከቡ በአንዴ ጭኖት የሚሄደው ቁስ ብዛት መኪናው ሚሳየሉ፤ ፋብሪካው ቤቱ የዘመነው
ህንፃ መገናኛው ስልኩ ቴሌቪዥኑ ሳተላይቱ መድኃኒቱ ሆስፒታሉ፤ የዘመነው ሆቴል የምንዝርና ጣቢያው፤
የግብረሶዶሙ ምድርን ማጥለቅለቅ መጠጡ አርቴፊሻል ምግቡ እኒህን ሁሉ ሰው ስለጨበጠ ሳይንስና ውጤቱ
አምላኩ ሆኑ ዛሬ ስለእምነት ስንነግረው ይስቃል ይሳለቃል። ለሱ አምላኩ የሚያየው ቁሳቁስ ነውና! የትኛውም
ሰው በማሕበራዊ ሚዲያ /በፌስ ቡክ፣ በዩቲዩብ፣ በቴሌግራም፣ በኢሞ፣ በዋትስ አፕ፣ በመሳሰሉት የሚለቀቁ
ማናቸውንም ነገሮች ስለሚያይ ፍፁም ውሉ የጠፋ ልቃቂት ሆኗል። እኛ እራሳችን ለትውልዱ መልእክታትን
ለማድረስ በፅሑፍ ያዘጋጀነውን እጅግ ጥቂቶች አነበቡት እንጂ የሚበዛው ወጣትም ሆነ ጎልማሳ አላነበበም። ነገር
ግን እግዚአብሔር እንደመከረን በተጉ ልጆቻችን በኩል በቴሌግራሙ በፌስቡኩ በመሳሰለው በድምፅ እንዲደርስ
በመሞከሩ የተሸለ ሰው ሊያደምጠው ችሏል።
ከላይ ከመጀመሪያው ገጽ ጀምሮ ለመግለፅ እንደሞከርኩት መልእክታቶቹ በብዙ ቋንቋ ተተርጉመው በመላው
ዓለም ደርሰዋል። የአዳም ዘር አልሰማሁም ብትል የሚሰማህ የለም። ንቀህ ተውከው እንጂ! የምትሰማው

20
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የመናፍቅ አለቆችህን ትምህርት ነው። የካቶሊኩን የእስላሙን የጣኦት አምላኪዎቹን የነሺንቶኢዝም ታኦኢዝም
ኮንፊሺያኒዝም ሂንዱኢዝም ሲኪዝም ሌሎችንም ድምፅ ነው የምትሰማው፤ ምንዝርናውን የጭፈራውን
የፖለቲካው ቅጥፈትን ክህደቱን ማጭበርበሩን ማታለሉን ነው የምትሰማው፤የዓለም ሕዝብ ቁጥር ወደ 8
ቢሊዮን ተጠግቷል ዘጠና ዘጠኝ ከመቶው የሚሆነው ሕዝብ የሚሄደው በዲያብሎስ መንገድ በሰፊው መንገድ
ችግር በሌለበት ምቾት በሞላበት ክህደት አምልኮ ባእድ በሞላበት በዚያ ነው የምትነጉደው ክርስቲያን መሰል
የዲያብሎስ ድርሰቶች እነመናፍቅ እነካቶሊክ ቀፍድደው ይዘውሃል ስለዚህ እኛን የተዋህዶ አርበኞችን ድምፅ
ብርሃናዊውን ቃል አትሰማም። እንዲያውም ትተቻለህ ትንቃለህ። በክህደት ውስጥ ያለውን ሕዝብ ስናየው
ሁሉም የዓለም ሕዝብ ነው ማለት እንችላለን። አሁንም ልትረዱ ይገባል የቅጥፈት የቀደመው እባብ የዘንዶው
የሃሰተኛው ነብይ ድርሰቶች የሆኑትን መናፍቃንን ካቶሊኩን እስላሙን የሩቅ ምሥራቁን እምነቶች ደምሩ
ከሃዲውን ደምሩ ግብረሶዶሙን ተብታቢው ኮኮብ ቆጣሪውን ደምሩት፤ ከሆዱ ውጪ አምላክን የማያውቀውን
ደምሩት እኔ ያላስታወስኳቸውን ሁሉ ደምሩ ስንት ለእግዚአብሔር በእውነት ያደረ ሰው ታገኛላችሁ? በግልፅ
ነው የማረጋግጥላችሁ። የለም እኮ ነው የሚያስብለው።
»» በኢትዮጵያ በእግዚአብሔር ቸርነት ተጠብቀው ከታላቁ መከራ ያመለጡ በእውነትና በመንፈስ
እግዚአብሔር ያመለኩ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ አርበኞች የደከመውንም የበረታውንም የተመረጠውንም
ጨምረን በእግዚአብሔር ፍቅር ተወደው ለትንሳኤው የታጩትን ቁጥር ብነግራችሁ መቼም
እንደምትደነግጡ ይገባኛል። እውነት እውነት ነውና ግልፅ ይሁንላችሁ ከ10 ሚሊዮን የማይበልጥ
ሕዝብ ነው በኢትዮጵያ ይድናል ተብሎ የሚጠበቀው። እግዚአብሔር ቸርነቱ ብዙ ነውና ጥቂቶችን
በምሕረቱ ከልሎ ጉድለታቸውን ከድኖ የፈቃዱን ቁጥር ቢጨምርበት ለኔ ድል ነው ብዬ እቆጥረዋለሁ።
ከተቀረው አፍሪካ ቢተርፍ ወይም ቢገኝ ከ3 ሚሊዮን የማይበልጥ ነው። ሁሉም እምነታቸው ጣኦትና
እስልምና ካቶሊክ መናፍቅ ነውና ከዚህ የዘለለ እምነት የለሽ ስለሆኑ የሚተርፍ የለም።
»» አውሮፓ /ሙሉ በሙሉ በተለይ እንግሊዝ ፈረንሳይ ጀርመን/ ሰሜን አሜሪካ ካናዳ አውስትራሊያ
ቻይና ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ እጃቸውን ከሚሰጡና ከሚያመልጡ እጅግ ጥቂቶች፤ በእግዚአብሔር ባሪያ
ቅን ችሎት ለፍርድ ከሚቀርቡ በስተቀር ሁሉም የሚጠረጉ ናቸው። በዚያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን
የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጆች የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች ባለምልክቶች የትጉሃን መማክርት
አባሎች የፅዋ ማህበር አባሎች፣ እንዲሁም በተጉት በአንደኛው ዙር ምዝገባ በዋናነት አምነው
ያስጠለሏቸው እንዲሁም በሁለተኛው ዙር ተመዝግበው በእነሱ የተጠለሉ ቤተሰቦቻቸው፣ ከሚድኑ
በቀር የተቀረው በሁሉም መቅሰፍቶች የሚጠፉ ናቸው።
»» መካከለኛው ምሥራቅ፦ በዚህ ክልል ብዙ የአረብ አገሮች /ሳኡዲ አረቢያ፣ አረብ ኤሜሬት፣
ኩዌት፤ ባህሬን፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ኢራቅ፣ ኢራን፣ የመን፣ ሊባኖን፣ እስራኤል፣ ዮርዳኖስ፣ ሶሪያ
ቱርክ፣ በሙሉ የሚጠረጉ ይሆናል። ምናልባት ትንሽ ቁጥር ምናልባትም በሺህ ብቻ የሚቆጠር ሰው
ይድን ይሆናል።
»» ኤሺያ፦ ጃፓን፣ ሁለቱም ኮሪያዎች፣ ቬትናም፣ ፊሊፒንስ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ኔፓል፣ ማይማር፣
ኪርጊስታን፣ ኡዝቤክስታን፣ ተረኪሚስታን፣ አዘርባጃን፣ ሜቄዶኒያ፣ ክሮሺያ፣ ላትቪያ፣ ኢስቶኒያ፣
ኖርዌይ፣ ፊንላንድ፣ ስዊድን፣ አየርላንድ፣ ስኮትላንድ፣ ግሪንላንድ ከጥቂት ልበ ንፁህ እግዚአብሔር
በምሕረቱ ከሚመለከታቸው በስተቀር በሙሉ የሚጠፉ /የሚጠረጉ/ ናቸው።
»» ራሺያ፣ አርመኒያ፣ ሰርቢያ፣ በእግዚአብሔር ምሕረት ከሚታዩ እጅግ ጥቂቶች በስተቀር እንዲሁ
የሚጠፉ ናቸው። በተለይ ራሺያ በመልእክት 3 መላሽ ቅጣት እንደሚጠብቃት አውቃ የተሠጣትን
ጊዜ ባለመጠቀሟ እንደሌሎቹ ሁሉ ልትመዘን ሆኗል።

21
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

»» ላቲን አሜሪካ /ደቡብ አሜሪካ / በሷ ዙሪያ ያሉ አገሮች እነኩባ፣ እነካራጉዋ፣ ፓናማ በሙሉ
የካቶሊክ ዋናዎቹ ተከታዮች በሙሉ የሚጠረጉ ሲሆን ጥቂት የዋሃንና ቅኖች በእግዚአብሔር ምሕረት
የታሰቡ ሊተርፉ ይችላሉ።
»» ባጠቃላይ ሁሉም የአዳም ዘር አገሩ በሥም ባይጠቀስ እንኳን ከሚመጣው ፍርድ ጠረጋ ከታላላቅ
መቅሰፍቶችና ጠረጋዎች ሊያመልጥ አይችልም።
»» በዚህ ሁሉ መቅሰፍቶችና ቅጣቶች በእሳት የሚጎበኙ ለአውሬው ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ የሰገዱ ሁሉ
ናቸው። ማንም ሆነ ማንም ሁሉም የአዳም ዘር አለቃም ምንዝርም ቄስም ሼክም ምሁሩም መሪውም
ወታደሩም ነጋዴውም ገበሬውም ፓስተሩም ሰላዩም ፖሊሱም ሕፃኑም ወጣቱም ሽማግሌውም ሴቱም
ወንዱም ሁሉም በተመዘኑበትና ከመጀመሪያው ጀምሮ በተከተላቸው ፍርዳቸው መሰረት የሚሰናበቱ
ይሆናሉ።
»» የሚቀሩት ደግሞ የዋህ ቅኖች እግዚአብሔርን ስለቅን ፍርዱ ስለገባው ቃል ኪዳን በተስፋ በፅናት
ሲጠብቁ የቆዩ ስለቀናችው ሃይማኖት ስለተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ዋጋን የከፈሉ የተገባቸው
ስለሆነ ነጩን ልብስ የለበሱ፤ ሻማቸውን ያበሩ፤ ዘይታቸው ያላለቀባቸው፤ ለበጉ እራት የተጠሩ፤
በግምባራቸው ምልክት የተደረገባቸው ከዚህ ሁሉ መቅሰፍቶች ይድናሉ። በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ
መንግሥት ሥር ደምቀውና ከብረው በሥላሴም በድንግልም ተባርከው መልካሙን ዘመን ትንሳኤውን
ይነግሱበታል። እግዚአብሔርም ጧትም ቀንም ማታም ሌሊትም ምንም በማያቋርጥ ዜማ ቅዳሴ ማህሌት
ሳእታት ኪዳን እንደማያቋርጥ ጅረት ከልጆቹ በፍቅር ይፈስለታል። በሁሉም የትንሳኤው ታዳሚዎች
ላይ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስለሚያርፍ ክርስቶስም በላያቸው ስለሚነግሥ የተባረከ የተወደደ
በፍፁም መፅናናት የተሞላ በረጅም እድሜ የሚባረኩበት፤ ዛሬ ያለችውን እድሜ በአሥር እጥፍ
የሚቀዳጁበት፤ እግዚአብሔር በየትኛውም ዘመን ያላደረገውን ምሕረት ቸርነት በረከት እንደ ወራጅ
ውኃ የሚያፈስበት ይሆናል። እናታችን ድንግል የምትከብርበት ዘወትር የምትመሰገንበት ቅዱሳን
ሰማዕታት ሁሉም በሥላሴ ፊት የከበሩት ሊቃነ መላእክት የሚመሰገኑበት ቅዱሳን ሁሉ የሚመሰገኑበት
ዘመን ይሆናል። በዮሐንስ ራእይ 20 የተገለፀው ምስጢር ይኸው ነው። ፊተኛው ትንሳኤ፤ ሺው ዘመን
ክርስቶስ የሚነግሥበት ከካህናቱ ጋር በምላት ዘወትር የሚገኝበት ይሆናል።
እንግዲህ ወገኖቼ ይህ እንደሚሆን የቀደመው እባብም አውሬውም ሃሰተኛው ነቢይም ያውቃሉ። ወደታላቁ
እሳት ገብተው እንደሚጠፈሩ ያውቃሉ፤ ለነሱ አልገዛም ያሉ ቢፈጯቸው ቢቆሏቸው አልጠፋ ያሏቸው የትንሳኤው
ሙሽሮች ባለምልክቶች የሥላሴም የድንግልም ምርጦች እንደሚደርሱ እንደተነገረው ሁሉም በእግዚአብሔር ቅን
ፍርድና ኃይል ተፈፃሚ እንደሚሆን በጥንቃቄ በሚገባ ያውቃል። የሚገርመው ግን ዛሬ የምታዩአቸው ይህንን
እውነት የሚክዱ ሁሉ ዛሬ ዲያብሎስ ያከበራቸው የምሁር የሊቅነት የምሁርነት የጳጳስነት የካህንነት የጠበብትነት
ስልጣን ያጎናፀፋቸው አንደበተ ርቱዕ ያደረጋቸው በሁሉም ሥፍራ የክብር ቦታ ሀብት ንብረት የሰጣቸው
በሙሉ የሚጠፉ መሆናቸው ነው። እነሱንም እንደ እርድ በሬ ወፍረውና ተብተው ሳይ በእውነቱ ይገርመኛል።
እግዚአብሔርን እያወቁት እንደ እግዚአብሔርነቱ ያላከበሩት ሐዋሪያው ጳውሎስ እንደነገረን በገዛ እውቀታቸው
የተመኩ በታላላቅ ቃላት ተሞልተው የሚገሰሉ እነዚህ ለማይረባ አእምሮ ተላልፈው የተሰጡ ናቸው። በቤተ
ክርስቲያናችን እግርና እጇን ተብትበው ይዘው ካባ አጥልቀው ሊቅ ሊቃውንት መምህር መሪጌታ ተብለው ከኛ
በላይ ማንም አይደመጥ እኛ ነን መምህር እኛን ብቻ ስሙ የሚሉ በትእቢት የተሞሉ ስለሆዳቸው የእግዚአብሔርን
እውነት የሸጡ እንደፀሀፍት ፈሪሳውያን ክርስቶስን የካዱ፤ የሰቀሉ ያስገደሉ የዛሬዎቹም እንዲሁ እኛ ከምንለው
ውጪ ቃሉም ቢነገር እኛ ያላፀደቅነው አይሆንም የሚሉ የኢትዮጵያን ትንሳኤዋን የሚክዱ፤ በተለያዩ ማህበራት
ፍርፋሪ እየተወረወረላቸው በካባ ተከልለው ምሁር መምህር ተባብለው የእግዚአብሔርን ተስፋ የሚያጨልሙ፤

22
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ዓይናቸው እያየ ፍርድ እየተከናወነ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን እንደተነገረው እግዚአብሔር ሥራውን እያከናወነ
በበቁ አባቶች ያለማቋረጥ እየተነገረ እየተመሰከረ እየሰሙ ስውር አጀንዳ ይዘው ለዲያብሎስ አድረው በማህበረ
ቅዱሳን በሰንበት ት/ቤት ውስጥ መሽገው የምንፍቅናን ትምህርት የሚያስፋፉ ደፋሮች ይህንን ከሚክዱ ነጮች
ካቶሊኮች መናፍቃን እስላሞች በምንድነው የሚለዩት? አዎን ቀድሚያ ዋጋቸውን የሚያገኙ እነዚህ ለከርሳቸው
ያደሩ ናቸው።

የጥንት አባቶቻችን ሃይማኖት በአጭሩ ምን ነበር?

ይህ ርእስ ሰፊ በመሆኑ በቅርብ የነበሩ ጥቂት አባቶችን ብቻ እንደምሳሌ አንስተን ከአሁኑ አባቶች ጋር
ለማነፃፀር እንሞክራለን።

ሐዋሪያት በእውነት ያስተማሩ የሚሥጢረ ሥጋዌን የሚሥጢረ ሥላሴን ነገር


በተናገሩበት በዲዲስቅልያ በአሥራ ሁለቱ ሐዋሪያት፤ ጳውሎስ የጌታችን ወንድም
የተባለ ያዕቆብ ሰባቱ ዲያቆናት ሰባ ሁለቱ አርድእት እንዲህ አሉ። የእግዚአብሔር
አገልጋዮች፣ የሰላም ልጆች፣ እኛም በእውነት ጸንተው ለሚታዘዙ ይህን የከበረ
ትምህርት እናስተምራለን።
ሃይማኖተ አበው ገጽ 8 ምእራፍ 6 ክፍል አንድ
»» ዓለም ሳይፈጠር የተወለደ የጌታችን የፈጣሪያችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ እግዚአብሔር
አብ አንድ ነው። ወልድ ዋህድ ከእርሱ ጋር ትክክል የሚሆን የባሕርይ አምላክ ነው።
»» ሠራዊትን ሢመታትን ሥልጣናትን ሁሉ የፈጠረ በኋላ ዘመን ሰው ይሆን ዘንድ የወደደ። ያለዘርአ
ብእሲ ንጽሕት ድንግል ከምትሆን ከእመቤታችን ማርያም ሥጋን የነሳ። ገላ።
»» ከሥጋ ጋር የማትሞት የማትለወጥ /የማትፈርስ የማትበሰብስ/ ነፍስ በሥጋችን እንዳለች ፈፅመን
እንወቅ። ሃይማኖትን የካዱ የመናፍቃን ሥራቸው ሁሉ መለየትን ሁሉ ሕግ መለወጥንም፤ እነርሱ በኛ
ዘንድ የተጠሉ ናቸውና!
»» አባቶቻችን ቀድመው የመሰከሩባቸው መናፍቃን ከሃዲዎች የእግዚአብሔርን ቃል የሚቀንሱ የሚደልዙ
የሚለውጡ እንደሆነ ከላይ ባለው ቃላቸው መስክረውባቸዋል። እነዚህ መናፍቃን በእምነታቸው
የወለዷቸው ዛሬም አብዝተውና አዘምነው የመሰሏቸው ልጆቿቸው ዛሬ በግልጽ ዲያብሎስን አንግሰው
ዓለምን ሁሉ አጥፍተው ለመጨረሻው ፍርድ አብቅተዋል።
አሁንም ቀጥለው አባቶቻችን እንዲህ አሉ፣

ዳግመኛም የሞቱ የኃጥአንን የፃድቃንን ትንሳኤ እናምናለን። ዳግመኛም ክርስቶስ ሰው


ከመሆኑ የተነሣ ምን ምን ሕፀፅ እንደሌለበት እናምናለን። በእውነት ሰው የሆነ አርሱ
እግዚአብሔር ቃል ነው። ሊቀ ካሕናት እርሱ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስታረቀ።
ከንፅሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ሥጋን ፈጥሮ የተዋሃደ እርሱ ነው። ሰውን
ሁሉ የፈጠረ እርሱ ነው። ከሙታን ተለይቶ የተነሳ ሙታንንም ሁሉ የሚያስነሳ እርሱ
ብቻ ነው።
ኤጲስ ቆጶስ ሄሬኔዎስ እንዲህ አለ

ኦሪት ነቢያት ወንጌል ክርስቶስን አስተማሩ፤ ከድንግል እንደተወለደ፤ በመስቀልም


መከራ እንደተቀበለ እንደሞተ እንደተቀበረ ከሙታንም ተለይቶ ተነስቶ እንደ አዩት
ወደ ሰማይ እንዳረገ በእግዚአብሔር አብ ምስክርነት እንደተገለጠ ለዘለዓለም እንደነገሰ።
ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ሁሉን የፈጠረ ሰውን የፈጠረ በሥራ ሁሉ ያለ በአበው
23
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

አለቆች ዘንድ የአበው አለቃ እርሱ ነው። ሕግን በመሥራት ጊዜ ሕግን የሠራ እርሱ
ነው።
ካህናትን የሚሾም ሊቀ ካህናት ነው። ነገሥታትን የሚገዛ እርሱ ነው። በነቢያት አድሮ
የሚናገር እርሱ ነው። በሰው ባሕርይ ሰው የሆነ እርሱ ነው። ከአብ የተወለደ ከባሕርይ
አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ የዘለዓለም ንጉሥ እርሱ ነው። ኖኅን የጠበቀው እርሱ
ነው። አብርሃምን የመራው ከይስሐቅ ጋር የታሰረ፣ ከያዕቆብ ጋር እንግዳ የሆነ ከዮሴፍ
ጋር የተሸጠ እርሱ ነው።
ሌላው አባታችን ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናሲዮስ እንዲህ ተናገረ

ለመላእከት ሁሉ እውቀት ከእነርሱ ዘንድ የሚገኝባቸው ሥላሴን እናመሥግናቸው


ከመጻሕፍትም እንደመላእክት እውቀትን በእኛ ላይ እንደማሳደራቸው መጠን አካል
ከሌለው ካለመኖር ወደመኖር በሰማይ በምድር ያለውን ፍጥረት ሁሉ ያመጡ
ናቸውና! እውቀትን የሚገልፁ ብርሃናት ናቸው። የምእመን ከእግዚአብሔር መወሃዱ
ፍፁም በሚሆን ገንዘብ ፍፁም የሚያደርጉት እነርሱ ናቸው። ኄራን መላእክትን ሁሉ
የሚሾሙ ናቸው። ለሚገባቸው ረቂቅ ጸጋን የሚሰጡ ናቸው።
አባቶቻችን ሥላሴን አመሥጥረው ሲገልፁ እንዲህ ነው። የመለኮትን ነገር ከሚናገሩ መጻሕፍት ይህንን
ተምረናል። ዳግመኛም የሚያመሰግኑ ምእመናንም በመለኮት አነጋገር እርሱ አምላክ እንዲባል አማልእክት ሲባሉ
አገኘናቸው። እናንተ አማልእክት ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ። ተብሎ እንደተፃፈ አምላክ መባል ለሥላሴ
ባሕርይ የሚገባው እንደመሆኑ፣ ስለዚህ በመለኮት የሚናገሩ እሊህን ሦስቱን አካላት ያመሰግናሉ፣ የማይመረመር
የማይለይ አንድነታቸውን እየተናገሩ እነርሱን ብቻ ያገለግላሉ። ከፍጡራን ሁሉ በላይ ልዑል ነው፣ አንድ ኃይል
ናቸውና!
ባሕሪያቸው አንድ ስለሆነ አንድ ይባላሉ። የሥላሴ ገጻት በየአካላቸው ልዩ ሲሆኑ በመለኮት አንድነት
ፀንተው ይኖራሉ። አንድ ሲሆኑ ሦስት አካላት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ስለመገለጣቸው ሦስት ናቸውና!
አመሥግኗቸው።
አብ ብርሃን ነው ከአብ የተወለደ ቃሉ ወልድም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው፤ እንዲሁም ከአብ የሰረፀ
መንፈስ ቅዱስም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው። ከአብ የወልድ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ መሥረፅ በዕጹብ
ይወሰናል እንጂ እንዲህ ነው ተብሎ አይነገርም። ከሕሊናት ሁሉ በላይ ነው፣ አይመረመርም።
በዚህ ዓለም ገዥ አለቃ የሚባል ሁሉ ከእርሱ ተሹሞ ነው ሁሉን የፈጠሩ የሁሉ መገኛ ናቸውና! ሁሉም
በቸርነታቸው ለመፈጠር በቅቷልና!
ከአካሎቻቸው በአንዱ አካል በውነት ተዛምደውናልና በሰው ማደርን መረጡ በአብ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ
ወልድ ዋህድ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ለመሆን በቃ! በንፅሕት ድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ። ድንቅ በሆነ
ሚሥጥር ከእርሷ ተወለደ።
ጥንት የሌለው ዘለዓለም የሚኖር እርሱ ከማእረጋት ሁሉ በላይ ከፍጡራንም ሁሉ በላይ በሚሆን ተዋህዶ የኛን
ባሕርይ ነስቶ ዘመን ተቆጠረለት፣ ያለመለወጥ ያለመቀላቀል በእውነት ሰው ሆነ። በባሕርየ መለኮቱም ሕፀፅ
የለበትም በሦስትነቱ ያመንበትን እኛን በአምላክነቱ በሠራው ሥራ እንድናውቀው አደረገን።
አምላክ ከሾማቸው ከመምህራን ይሕን ረቂቅ ትምህርት ተምረናል። እርሱን አስተማሩን ይህም ትምህርታችን
ለማያምኑ የተሠወረ ነው። ለምናምን ግን የተገለፀ ነው። ፃድቃን ያውቁታል። ኃጥአን ግን አያውቁትም።

24
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እኛስ ይህን ትምህርት ተምረናል። ካህናት ተብለን እንደመጠራታችን፣ በማዕረገ ክህነት እንደ አእምሮአችን
መጠን ተገለጠልን።
ሌላው አባታችን ከሐዋሪያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ በኋላ ሦስተኛ ሆኖ የተሾመ የአንፆኪያ ሊቀ ጳጳሳት
ሰማዕት አግናጥዮስ በመልእክቱ እንዲህ አለ።
ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር የፍጥረቱን ሁሉ ሹመትና መአረግ መስጠት የሚቻለው በመልክ
በገጽ ፍፁም በሚሆን በሦስት አካል በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ሁሉን የሚገዛ ነው። ከሶስቱ አካላት አንዱ አካል
በእመቤታችን በንፅሕት ድንግል ማርያም ማሕፀን አደረ። ስለ መለኮት ተዋሃደ፣ በዚህ የምንናገርም በወልድ
ያለውን ነው። ስለአብ ስለመንፈስ ቅዱስ አይደለም። ፈፅሞ አብ መንፈስ ቅዱስ ሰው ለመሆን በድንግል ማሕፀን
አደሩ አንልም። ከሶስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ብቻ ከእርሷ ተወለደ እንላለን እንጂ!
አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ሕልው እንደሆነ፣ ወልድም በአብ በመንፈስ ቅዱስ ሕልው እንደሆነ መንፈስ
ቅዱስም በአብ በወልድ ሕልው እንደሆነ እናምናለን ይህች ሦስትነት ያለመለየት ያለመለወጥ በሦስት አካላት
በአንድ መለኮት የተካከለች ናት።
አንዲት አገዛዝ አንዲት ፈቃድ አንዲት ኃይል አንዲት መንግሥት አንዲት ስግደት አንዲት ምስጋና አንዲት
ክብር አንድ ጽንዕ ለሥላሴ ይገባል። አንዲት ምክር አንዲት ሥልጣን አንድ ክብር አንዲት ጽንዕ አንድ አኗኗር
አንድ ፈቃድ ለሥሉስ ቅዱስ ነው።
አብም አብ ነው እንጂ ወልድን መንፈስ ቅዱስን አይደለም። ወልድም ወልድ ነው እንጂ አብን መንፈስ
ቅዱስን አይደለም። መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ አብን ወልድን አይደለም። አብ ወልድን
መንፈስ ቅዱስን ወደመሆን አይለወጥም። ወልድም አብን መንፈስ ቅዱስን ወደመሆን አይለወጥም መንፈስ
ቅዱስም አብን ወልድን ወደመሆን አይለወጥም። እሊህ ሦስቱ አካላት በጌትነት በክብር ፍጹማን ናቸው። በአንድ
መለኮት አንድነትም አንድ ናቸው።
ይኸውም ሦስትነት ከእርሱ የሚገኝ አንድ ብርሃን ነው። በዓለሙ ሁሉ መሉዕ ነው። ከምድር በታች ላሉትም
ያበራል። በሰማይ በምድር ምሉ ነኝ እኮ! በሲኦልም ያሉ ጌትነቱን አዩ ተብሎ እንደተፃፈ።

ምንፍቅናና የኛ አባቶች መልስ

መለኮት በባሕርዩ ታመመ ሞተ የምትል አንተ የኛን ነገር ሰምተህ እፈር። እኛ ግን የባሕርይ አምላክ
ክርስቶስ ሰው እንደመሆኑ በሥጋ እንደታመመ በመለኮት እንዳልታመመ እናምናለን። በሥጋ ሞተ በመለኮት
አልሞተም። እግዚአብሔር ቃል ስለኛ እንደታመመ እግዚአብሔር ለእኛ ቤዛ ሆኖ እንደሞተ ብትሰማ! እኛ
መለኮትን ከትስብእት ጋር አንድ አካል አንድ ባሕርይ አድርገን ለእግዚአብሔርነቱ በሚገባ በዚህ ባንድ ስም
ክርስቶስን እንደምንጠራው እወቅ!
ዳግመኛ አንተም ከሁለት ባሕርያት አንድ ሆነህ ከነፍስና ከሥጋ ተገኝተህ ለሰው በሚገባ በዚህ ሥም አንድ
ተብለህ ትጠራለህ። ያንተ ነፍስ እንኳ መለኮትን ሳትሆን በባሕርይዋ አትሞትም። ለነፍሳችንም ክብርን ልንሰጥ
የምንወድ የማትሞት ስለሆነ ነው።
እንዲህ ከሆነ በወልድ ዋህድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላለ ለአንዱ ሥላሴ ባሕርይ ክብር ልትሰጠው
እንደምን አትወድ! መለኮት ሞተ ካልክ ሦስቱ ሞቱ እንዲያሰኝብህ የጌታችንም ሥጋ በመቃብር ውስጥ
እንደሙታን በድን እንዳደረግኸው ከመለኮትም እንደለየኸው አታውቅምን! የሥላሴ ባሕርይ አንድ ነውና!
ይኸውም አንድ መለኮት ነው።

25
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንዲህ ከሆነ ሞትን ድል የነሳው ሲኦልን የማረከው ወዴት አለ! አንተስ ኃይል እንደሌለው እንደ አንድ ሰው
አደረግኸው! ጽንዕ አጥተው ከማይንቀሳቀሱ ሙታንም ጋር ቆጠርኸው!
ይልቁንም ሌሎቹን መናፍቃንን ታኦማጎሊስ ሲባሉ እነሆ እናገኛቸዋለን። ይኸውም የእግዚአብሔር ጠላቶች
ማለት ነው። ፈጣሪ እንደመሆኑ እርሱ እንዳወቀ ከንጽሕት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ከነፍስዋ እግዚአብሔር
ፈጥሮ በተዋሃደው ሥጋ፣ ሥጋ ነፍስ የሌለው እንደሆነ እንዲህ ያስባሉ። መለኮትም ስለነፍስ ፈንታ ሆነው ይላሉ።
በውኑ መለኮት ከሥጋ ፈጽሞ ተለየን ሥጋስ ለዘለዓለም ፈርሶ በስብሶ ቀረን ነፍስ አልነሳም የሚል እንዲህም
የሚክድ ሰው ነፍሴ እሰከሞት ድረስ አዘነች ያለውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ሰምቶ እንዲህ ይፈር!
አቤቱ ይህን መናገሩ በማን ላይ ነው! በሚጠፋ ወገን ላይ ነው እንጂ!
ሊቀ ጳጳስ የከበረ ሰማዕት አግናጢዮስ በአሥራ ሦስተኛው መልእክቱ እንዲህ አለ!

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእውነት ተወለደ በእውነት አደገ በእውነት በላ ጠጣ


በእውነት ተሰቀለ በእውነት ታመመ ሞተ ተቀበረ ከሙታንም ተለይቶ ተነሳ!
ይህንን እንዲህ ያመነ ብፁእ ነው። ይህንን የካደ ግን እኛ ተስፋ ከምናደርጋት ከተመሰገነች ሕይወት የተለየ
ነው። ወልድ ዋህድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚከፍሉት አንድ አካል አንድ ባሕርይ ከሆነ በኋላ ሁለት
አካል ሁለት ባሕርይ የሚያደርጉት ሰው ስትሆን ራስህን እግዚአብሔር ታደርጋለህና! ስለመሳደብህ ነው እንጂ
ስለበጎ ሥራህ ልንጣላህ የምንወድ አይደለም ብለው በአመፃቸው ከሚናገሩ አምላክን ከሰቀሉ ከአይሁድ ጋር
ይቆጠራሉ።
በወልደ እግዚአብሔር ድካም ሕፀፅ አለበት የሚሉ ሁለት አካል ሁለት ባሕርይ የሚያደርጉትም እድል
ፈንታቸው ከካሕድያን አይሁድ ጋር የተካከለ ነው።
የወልድ አካል ግን ከእኛ ጋር ተዛምዷል። ከተዋሃዱ ከመለኮትና ከትስብት ከሁለቱ አንድ ሆኗልና ሁለቱንም
አንድ አድርገዋቸዋልና!
በመለኮት የአካል አራተኛ የባሕርይ ሁለተኛ ሆኖ የተጨመረ አይደለም። በአካል ሦስት ናቸው እንጂ! የሥላሴ
አካላቸው ተቀድሞ ስማቸው ከአካላቸው በኋላ የተገኘ አይደለም። ጥንት ሳይኖራቸው ዘመን ሳይቀድማቸው
ከዘመን አስቀድሞ የነበሩ ናቸው እንጂ! ነገር ግን ከሰው ወገን ማንም አያውቃቸውም ነበር የእግዚአብሔር ልጅ
ወልድ ዋህድ ሰው ሆኖ አባቴ እነሆ ስምህን ለሰው ሁሉ ገለጥኩ እኔንም የባሕርይ ልጅህ እንደሆንኩ ያውቁ
ዘንድ ዓለም ሳይፈጠር በነበረ ጌትነትህ ግለጠኝ ብሎ ከአስረዳ በኋላ ነው እንጂ!
አብም እንዲሁ በደብረታቦር የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ ከመሰከረ በኋላ እንዲሁም ሦስቱ በቅድምና
የነበሩ ቀዳማውያን መበላለጥ የሌለባቸው ፅሩያን እንደሆኑ ያስረዱን ዘንድ በዮርዳኖስ መንፈስ ቅዱስን ከሰደደ
በኋላ ነው እንጂ!
የወልድ ከአብ መወለዱ የማይመረመር ሊናገሩትም የማይቻል ነው። የማይመረመር ረቂቅ ስለሆነ ግዙፉ
ረቂቁን መርምሮ ማወቅ የማይቻለው ነውና! የነርሱንም ነገር ይመረምር ዘንድ አይቻለውምና! ከሰው ባሕርይ
ጋር አይመሳሰልምና ልደቱም እንደ ሰው ልደት አይደለምና ረቂቅ ምስጢር ነው። አይመረመርም።
እንግዲህ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ልብ ብላችሁ የተዋህዶ እምነታችሁን መሰረት በሚገባ ትረዱና ታስተውሉ
ዘንድ፣ ማስተዋላችሁን መረዳታችሁን ታጎለምሱ ዘንድ እጅግ ጥቂት ለመንደርደሪያ የሚያገለግሏችሁን የአበው
የቀና የተዋህዶ እምነታቸውና ሚሥጢረ – ሥላሴን እንዴት እንደሚያመሰጥሩት /እንደሚገልፁት/ እንድትረዱ
ለማድረግ የጣርኩበት መጠነኛ ማስረጃ ነው። ይበልጥ እንድትረዱ የእምነታችሁንም መሰረት እንድታጠብቁ

26
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የጥንት አባቶቻችንን የተዋህዶ እምነት መሰረትን እንዴት እንደአፀኑት የሚገልፀውን ሃይማኖተ አበው መጽሐፍ
እንድታነቡ እመክራችኋለሁ።
በዚህ አስተማሪና መካሪ መሰረታዊ የእምነታችን አካሄድ የተገለፀበት ስለሆነ አንብቡት ተረዱት፤ ብዙ
ጥያቄዎቻችሁን ይመልሳል። የጠላቶችን አመጣጥና የጥፋት አካሄዳቸውን በሚገባ ትረዱበታላችሁ። በዚሁ
የአበው መፃህፍት ውስጥ እጅግ የተከበሩ የተወደዱ የተዋህዶ እምነታችን መሰረቶችና መንፈሳዊ ተዋጊዎች
ጥቂቶቹን በዚሁ የሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ውስጥ ስለምታገኟቸው ብንጠቅስ፤ ቅዱስ አትናቴዎስ፣ ባስሊዮስ፤
ጎርጎሪዮስ፤ አቡሊዲስ፤ ኤፍሬም፤ ኤራቅሊስ፤ አፍሮስዮስ፤ ዮሐንስ፤ ቴዎዶጦስ፤ ኤጲፋንዮስ፤ ዮሐንስ አፈ
ወርቅ፤ ቄርሎስ፤ ቴዎዶስዮስ፤ ሳዊሮስ፤ ኪራኮስ፤ ዲዮናሲዮስ፤ አባ ገብርኤል፤ መቃርስ፤ እና ሌሎችም
ስለቦታ ውስንነት ያልጠቀስኳቸውን ሁሉ በዚሁ የአበው መፀሐፍ ውስጥ ታገኟቸዋላችሁ።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የእነዚህን አባቶቻችን ተጋድሎ ስትረዱ አሁን ያሉትን የአባቶችን ስም
ወርሰው የማእረግ ስማቸው ያደረጉ ዛሬ የምታዩአቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን መሪዎች
/እረኞች/ ስለበጎቻቸው ምን እያደረጉ ነው! ብላችሁ ልትረዱ ትችላላችሁ። ዛሬ ይህ መልእክት የመጣው
ለመምክር አይደለ።ም ሰባት ጊዜ ሲተላለፍ የነበረውን የእግዚአብሔር የፍርድ ቃል ተግሳፅ ማስጠንቀቂያ ቤተ
ክርስቲያንም ምእመኑም ከዚያም በላይ መላው የዓዳም ዘር በሙሉ የመጣበትን በአመፁ ምክንያት የተፈረደበትን
ፍርድ ሊያደምጥና ሊሰማ ሊፀፀት ባለመቻሉ፤ በመናቁ፤ በምትኩ የቀደመውን እባብ፣ ዘንዶውን፣ ሃሰተኛውን
ነብይ በመከተሉ የመጣ ብርቱ የእሳት ጠረጋ ለመግለፅ ነው። ይህም ብቻ አይደለም ትእግሥትም ተሟጦ
የመጨረሻው ምድር ከተፈጠረችበት ጊዜ አንስቶ ያላየችው ተደራራቢና ተከታታይ የእሳትና የማዕበል የቸነፈር
የምድር ነውጥ እሳተ ጎሞራ ፍጅት ብርቱ አውዳሚ በረዶ ጎርፍ የመጣበትና የሚወርድበት መሆኑን ለማሳወቅ
የመጣ ነው።

በእውነትና በመንፈስ በማምለክና መንፈሳዊ ምሪት በተዋህዶ እምነት ተከታዮች


ዘንድ ምን ይመስላል?

የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የድንግል ለልጆች በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መመራትን መማርን መፅናናትን
ምን እንደሆነ ልንረዳ ይገባናል።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፤ መድኃኔዓለም አባታችን ለሐዋሪያት የመጨረሻ የሥራ /የአገልግሎት/
ስምሪት ትእዛዝን ከመሥጠቱ በፊት ያላቸው አንድ ትልቅ ትእዛዝ ነበር ––– እሱም ኃይል እስከምትቀበሉ
ከእየሩሳሌም ከባእታችሁ እንዳትወጡ፤ እኔ ወደአባቴ አርጋለሁ አፅናኙን መንፈስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን
እልክላችኋለሁ ነበር ያለው። ለምን ይህን አለ! አዎን በእውነተኛይቱ በቀናችቱ በአንዲቱ የተዋህዶ እምነት ያሉ
በእግዚአብሔርም በድንግልም የሚወደዱና የሚታመኑ ልጆቹ ሁሉ ውድ ዋጋ የከፈለባቸው መሰረታዊው የሰው
ልጅ ጠላት ዲያብሎስ ከሚፈጥርባቸው አደጋ ዘወትር እንደዓይኑ ብሌን የሚጠብቃቸው በብርሃናዊው መንገድ
ዘወትር በመምራት ሌትም ቀንም ይጋርዳቸዋል። እንዲሁም በእውነት ይመራቸዋል ፤ፈቃዱን ያሳውቃቸዋል፤
እንዲጠነቀቁ ይመክራቸዋል፤ የተዘጋጀላቸውን መልካም ሁሉ እያመላከተ ያፅናናቸዋል። ቃሉን ይረዱ ዘንድ
ማስተዋልን መረዳትን መገንዘብን መንፈሳዊ መረዳትንም ሁሉ እንደ ቸርነቱ ያድላቸዋል። ታዲያ ይህ ሁሉ
ሲሆን የእግዚአብሔር መናገሪያው መንገድ ብዙ ነው። በዚህ ዘመን የብዙዎችም ጥያቄ ከእግዚአብሔር እንዴት
እንደሚገናኙና በሱም መንፈሳዊ ምሪት እንደሚያገኙ አለመረዳታቸው ነው። ለዚህ ጥያቄአቸው ብዙ የዘመኑ
ሰባኪያን መምህራን በቃሉ ነው የምንመራው ብለው ከምእመኑ ለሚቀርብላቸው የአመላክቱን ጥያቄ ይመልሳሉ።
ቃሉ መሰረታዊው እምነታችን የተመሰረተበት ዋናው የእምነታችን አምድ ነው። ነገር ግን በየእለቱ በየዘመኑ
በምንኖረው የሕይወት ምልልስ ስለምንሄድበት አቅጣጫ ስለምንታቀብበት አካሄድ ስለሚሰጠን በጎ ነገር

27
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ስለጠየቅነው ስለምንሻው ነገር ምላሽ ለመስማት ከእግዚአብሔር ድምፅን ምልክትን ምክርን ማግኘት አለብን።
በዚህ ስንጓዝ ብቻ ነው የእግዚአብሔርን ቃል ያለ ሕፀፅ ጠብቀን ልንጓዝ የምንችለው።
በእግዚአብሔር ቃል በመጽሐፈ ኢዮብ ምእራፍ 33 ቁጥር 12 – 33 እንዲህ ይናገረናል

እግዚአብሔር ከስው ይበልጣል ብዬ እመልስልሃለሁ፤ አንተ ለቃሌ ሁሉ አይመልስልኝም


ብለህ ስለምን ከእርሱ ጋር ትከራከላለህ፤ እግዚአብሔር በአንድ መንገድ በሌላም
ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም በሕልም በሌሊት ራእይ አፍላ እንቅልፍ በሰዎች
ላይ ሲወድቅ በአልጋ ላይ ተኝተው ሳሉ በዚያን ጊዜ የሰዎችን ጆሮ ይከፍታል፤
በተግሳፁም ያስደነግጣቸዋል። ሰውን ከክፉ ሥራው ይመልሰው ዘንድ ከሰው ትእቢትን
ይሰውር ዘንድ፤ ነፍሱን ከጉድጓድ፤ በሰይፍም እንዳይጠፋ ሕይወቱን ይጠብቃል።
ደግሞ በአልጋ ላይ በደዌ ይገስፀዋል አጥንቱንም ሁሉ ያደነዝዘዋል። ሕይወቱም
እንጀራን ነፍሱም ጣፋጭ መብልን ትጠላለች፤ ሥጋው እስከማይታይ ድረስ ይሰለስላል።
ተሸፍኖ የነበረውም አጥንት ይገለጣል ነፍሱ ወደ ጉድጓድ ሕይወቱም ወደ ሚገድሏት
ቀርባለች፤ የቀናውን መንገድ ለሰው ያሳውቀው ዘንድ ከሺህ አንድ ሆኖ የሚተረጉም
መልአክ ቢገኝለት እየራራለት፤ ቤዛ አግኝቻለሁና ወደጉድጓድ እንዳይወርድ አድነው
ቢለው፤ – ሥጋው እንደ ሕፃን ሥጋ ይለመልማል። ወደጉብዝናውም ዘመን ይመለሳል።
ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል እርሱም ሞገስን ይሰጠዋል ፊቱንም በደስታ ያሳየዋል።
ለሰውም ፅድቁን ይመልስለታል። እርሱም በሰው ፊት እየዘመረ፤ –– እኔ በድያለሁ
ቅኑንም አጣምሜአለሁ፤ የሚገባኝንም ብድራት አልተቀበልኩም ነፍሴ ወደ ጉድጓድ
እንዳትወርድ አድኗታል ሕይወቴም ብርሃን ታያለች ይላል። እግዚአብሔር ይህን ሁሉ
ሁለት ጊዜና ሦስት ጊዜ ከሰው ጋር ያደርጋል፤ ይህም ነፍሱን ከጉድጓድ ይመልስ
ዘንድ በሕያዋንም ብርሃን ያበራ ዘንድ ነው።
ይላል በመጽሐፈ ኢዮብ የምናገኘው የልዑል ኃይለ ቃል
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! ከላይ በእግዚአብሔር ቃል እንደተረዳችሁት እግዚአብሔር በቅንነት
በእውነት ከፈለግነው እንደምናገኘው መልስም እንደሚሰጥ እንደሚገሥጽ እንደሚያስተምር ቃሉ ያስተምረናል።
ወገኖቼ! ዛሬ የገጠመን ጠላት እጅግ የተራቀቀ የዘመነ በዘመኑ የክፋት አይነት የተሞላ ትውልድ የሞላበት ጊዜ
በመሆኑ ብዙ የእግዚአብሔር ሰዎች ዓይኖቻቸው ከሰው ምሪትን ስለሚፈልጉ እግዚአብሔር በሕልምም በራእይም
ሲነግራቸው ሄደው የሚያማክሩት በእምነቱም በቅንነቱም በእውነተኝነቱም በቦታው የሌለውን ሰባኪ መምህር
ካህን ነው። እሱ ደግሞ ፈጣሪውን ስለገንዘብ የሸጠ በጎችን አርዶ የሚበላ ስለሆነ ቀና ነገር ከሱ አይገኝም።
እኛ ራእይን ህልምን አንሰማም አናምንም የምናምነው በቃሉ የተፃፈውን ብቻ ነው ብለው አሳንሰውና ከንቱ
አድርገው ሰዎቹን ያስታሉ። ልብ በሉ እነሱ መናፍቅ፣ ካቶሊክ፣ ተሃድሶ፣ ቅባት፣ ፀጋ፣ በቤተ ክርስቲያናችን
የመሸጉ አርዶ በሊታዎች እግዚአብሔር ከሌቦች ከካሃዲዎች ከጨለማ ሰራተኞች ምን ሕብረት አለው? ምንስ
ሊረቡ ክደውታል ለፍርፋሪ ለውጠውታል የፈለገውን ያህል ቢጮሁ በአል ሆይ ስማን ቢሉ እንደ አክአብ እና
ኤልዛቤል የእስራኤልን አምላክ የካዱ! ማን ሰማቸው ስለዚህ እነዚህም ልዑል ስለማይሰማቸው ይህንን በሚገባ
ስለሚያውቁ በኤልያስ እንደተጠረጉ የዛሬዎቹም የበአል ካህናት መምህር ሰባኪ በሙሉ በቤተ ክርስቲያናችን
ውስጥ የበቀሉ አረሞች ናቸውና ብዙም ሳይርቅ በቅርቡ ታጭደው ለእሳት ይጣላሉ። እግዚአብሔርን በሚናገርበት
አግባብ አትስሙ የተፃፈውን እኛ የምንለውን ብቻ ስሙ ይላሉ። ነገ ታየዋለህ! እየሸቀጡ መኖር እግዚአብሔርን
መድፈር ቃሉን መቀነስ መደለዝ ቅኖችን ማሰናከል ወደ እውነት እንዳይቀርቡ ሰውን እንዲያመልኩ ማድረግ
ተግባራችሁ ስለሆነ እንደበአል ነቢያት እንደጉድፍ ትጣላላችሁ እሳትም ይበላችኋል። ለዘለዓለም ትከደናላችሁ
ከነዘር ማንዘራችሁ፤ ይህ ደግሞ የታመናችሁበት ዲያብሎስና መንገዱ አያድኗችሁም። የአህያ ባል ከጅብ
አያስጥልም።

28
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ዛሬ ራእይ ሕልም አላቅም የምትል ቃሉንም በአግባቡ የማታውቅ ሰባኪ መምህር ስለምንፍቅናህ
ስለድፍረትህ ስለካቶሊክነትህ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ስለመናቅህ ተፈርዶብሀል። ምእመናን ስላዩት
ራእይ ስለተመለከቱት ሕልም በቃሉ ተረድተው ፀልየው ፆመው ላገኙት መልስ ቀንተህ እኔ በህልም በራእይ
አልመራም የምትል ከሆንክ ለእግዚአብሔር መናገሪያ መንገድ መራጩ አንተ ከሆንክ ራስህን ከእግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስ በላይ አድርገሃል ማለት ነው። በዚህም የምረዳው ዲያብሎስ እኔ አምላክ ነኝ ብሎ በድፍረት
እንደተናገረ ሁሉ በዚህ አቋም ውስጥ ያለ ሰው ቢያውቅም ባያውቅም የቀደመው እባብ የዘንዶው የሃሰተኛው
ነብይ ሰለባ ነው። እሚፈፅመውም የዲያብሎስን ፈቃድ ነው። ከላይ በቃሉ እንደገለፅኩት እነዚህ እውነትን
የማያውቁ ነጋዴዎች፣ የኮተለኩ፣ መናፍቅ የሆኑ፣ የተሃድሶ የቅባት የፀጋ ግሪሳዎች ለሆዳቸው ሲሉ የሚኖሩ
ጌታን ከሰቀሉት ፈሪሳውያን በላይ እያጠፉ ያሉ ናቸውና! ሁልህም ሕዝበ ክርስቲያን ተጠንቀቅ! የተፈረደበት
ከጥፋት አይመለስም ይዞህ እንዳይጠፋ ራስህን ጠብቅ!
ዛሬም ንስሓ የማያውቃቸው፤ የማይመልሳቸው አስደንጋጭ በተራ ወንጀል የማይታይ በአካል ዲያብሎስ
ከሚሰራው በላይ ወንጀልን የሚፈፅሙ እንደ ሥራም ያደረጉት ስለሞሉ የጠመጠመውን ሁሉ፤ ሰባኪ ነኝ
መምህር ነኝ ምሩቅ ነኝ የሚል ካባ አጥልቀው ግብራቸው ግን ከዲያብሎስም በላይ የሆኑ ሁሉንም መንገድ
ስለሸፈኑ አብዝታችሁ ተጠንቀቁ። ጉባኤያቸው እንዲበተን ቢደረግም በማህበረ ቅዱሳን ካባም ሊመጡ ችለዋል።
ስለዚህ በተለይ ወጣት ሴቶች እንድትጠነቀቁ እንመክራችኋለን።
በአንድ ወቅት ሙሴ የእግዚአብሔርን ሕዝቦች የቀይ ባሕርን እንደተሻገሩ ሕዝቡን ሲመክር ሲመራ ማርያም
የምትባል እህቱ ትጋጨዋለች /ትቃወመዋለች/ አልፋም እኛም ነብይ ነን አንተ ከማን በልጠህ ነው ትላለች።
እግዚአብሔርም ሁለቱንም ወደ መቅደሱ ወደ ድንኳኑ እንዲመጡ ያዛል! ይቀርባሉ። ጌታም ከመቅደሱ ሆኖ
እንዲህ ይላል ማርያም አንቺም ሌሎችም ነብይ እንደሆናችሁ እኔም በህልም በምሳሌ አድርጌ እንደማነጋግራችሁ
እንደምገልጽላችሁ ልክ ነው፤ ሙሴ ባሪያዬ ግን እንደእናንተ አይደለም እኔ አፍ ለአፍ ነው የማነጋግረው ብሎ
ከመሰከረ በኋላ የሙሴን እህት በለምፅ መታት ስለምን ስላላከበረችው። ይህን ያነሳሁት እግዚአብሔር በሕልምም
አፍ ለአፍም በራእይም ከዚህም በላይ በብዙ መንገድ ይናገራል።
እግዚአብሔር ታላቁ የእስራኤል ካህን ኤሊ ብዙ ጥፋት በመፈፀሙ ናቀው ከክብሩም ሊያሰናብተው ወሰነ።
በወቅቱ በቤተመቅደስ የሚያገለግለው ሳሙኤል ገና ትንሽ ነበርና ምንም የሚያውቀው አልነበረም ሥራው ደግሞ
ለካህኑ ኤሊ ረድ ሆኖ ማገልገል ነው። በዚያው በቤተ መቅደስ ተኝቶ ሳለ በሌሊት ሳሙኤል ሳሙኤል ብሎ
የሚጣራ ድምፅ ሰማ፤ ደንግጦ ተነስቶ ካህኑ ኤሊ የጠራው መስሎት አቤት እነሆኝ አባቴ መጥቻለሁ ይለዋል
ኤሊም እኔ አልጠራሁህም ይሁንና ድጋሚ ከጠራህ እነሆን ባሪያህ ይሰማል ተናገር በል አለው። እግዚአብሔርም
ተናገረው በኤሊና በነውረኛ ልጆች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ገለፀለት ይህንንም ወስዶ ለኤሊ ነገረው።
እንደተነገረውም የኤሊ ልጆች ታቦተ ፅዮንን ተከትለው ከፍልስጤማውያን በሚደረገው ውጊያ ላይ ተገኝተው
ስለነበር በዚያው ወጊያ ሁለቱም የዔሊ ልጆች ሲሞቱ የእነሱን ሞት ለኤሊ ሲነገረው ደንግጦ ከመቀመጫው
ወድቆ አንገቱ ተጠምዝዞ ሞተ። እግዚአብሔር ለሳሙኤል እንደተናገረው። እግዚአብሔር በዚህም በዚያም በብዙ
መንገድ ይናገራል ያልነውም ቃሉም የነገረን ይህ ነው።
ወገኖቼ! ዮሴፍ ገና ብላቴና ሳለ እግዚአብሔር በሕልሙ እንደሚነግሥ ታላቅም እንደሚሆን ሲነግረው
ለወንድሞቹ ሲነግራቸው እጅግ እንደጠሉት በቃሉ ተነግሯል። በኛ ላይ ልትነግሥ ነው ወይ ብለው ተከፉበት
ድጋሚም ጨረቃና ፀሐይ ሲሰግዱልኝ አየሁ ብሎ ለአባቱም ጭምር ተናገረ አባትም ተቆጣው እኔና እናትህ
እንሰግድልህ ይሆን አለ ማን? ያዕቆብ ታዲያ ቀረ አልቀረም የተነገረው ተፈፀመ።

29
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ልብ በሉ ከሔኖክ ጀምሮ ኖኅ አብርሃም ይስሐቅ ያዕቆብ ሙሴ ኢያሱ ኢሳይያስ


ሕዝቅኤል ኤርሚያስ ሁሉም ነቢያት፤ በአዲስ ኪዳንም ሁሉም ሐዋሪያት ከይሁዳ በስተቀር በራእይ በሕልም
በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመሩ ነበሩ ስለዚህ ይህን ከማያምኑና ከከሃዲዎች ራቁ እንላለን።

ኢትዮጵያና ዓለም በንፅፅር! ዓለም ለምን ኢትዮጵያን ይጠላል? ይዋጋል? በአንድ


ሃሳብ ቆሞ ይገዳደራል? ሊያጠፋትም ይጥራል?

ኢትዮጵያ ዛሬ ስናያት እጅግ የደከመች በብርቱም የተጎዳች በብዙ የጠላት ሴራ የተከፋፈለች፤ ልባቸው
ሃሳባቸው የተለያየ የዲያብሎስ አጀንዳ ተሸክመው በገዛ ሃገራቸው ላይ ለጥፋት የተሰማሩ ትውልዶች የተከሰቱባት
አገር ሆናለች። አባቶቿ በፀና የተዋህዶ እምነታቸው በአንድነታቸው በፍቅር ኖረው ጠላታቸውን በሕብረትና
በአንድነት መክተው በሺ የተቆጠሩ ዘመናትን አሳልፈዋል። ኢትዮጵያ ከሁሉም የሚለያት ብዙ ጠላትም
እንዲነሳባት ያደረገው እምነቷና እግዚአብሔርን ስትፈልግ በቅን ልቧ ስለነበር ነው። ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር
እንድትወደድ ያደረጋት በቅንነት በፍፁም ልብ አምላኳን ትፈልግና በፈቃዱ ለመኖር ትጥር ስለነበር ነው።
ዓለም ፈጣሪውን ሳያውቅ በፊት እሷ በሕገ ልቦና እንደፈቃዱ ለመጓዝ ትጥር ነበር። ለዚህ ምስክር የሚሆነን
የቅርቡን ብናነሳ እንኳን ሙሴ እስራኤላውያንን ወደ ነፃነት የማውጣት ጉዞ ውስጥ እያለ ከገዛ ሕዝቦቹ በገጠመው
ተግዳሮትና ክህደት እግዚአብሔር ለታላቅ ሕዝብ መሪ ላድርግህ እነዚህ የካዱኝን ያስመረሩኝን ላጥፋ ባለው ጊዜ
ታላቅ ሕዝብ ተብላ በእግዚአብሔር የተመሰከረላት ኢትዮጵያ ነበረች። ዛሬም በወንጌሉ ዘመን ገና ከመነሻው
ጌታን ተቀብላ ብሉይን ከሃዲስ አስማምታና አዋህዳ እውነትን ከነምልክቱ አስርፃ ታቦታትን ቀርፃ በብዙ
ሰማዕትነት ተዋህዶን አፅንታ ለረጂም ዘመን በታላቅ ተጋድሎ እየተፈጨች እየተሳደደች እንደገናም እየተሰራች
በተጉ በፀኑ አባቶቻችን ተጋድሎ በእግዚአብሔር እርዳታ መወደድና ፍቅር እዚህ ደርሳለች። ቀሪው ዓለም
ያደገውም ያላደገውም ፈጣሪውን ክዶ ጣኦት አንግሶ የዲያብሎስ ድርሰት የሆኑ እምነቶችን ተሸክሞ እራሱን
እንደ እውነተኛ አድርጎ በመቁጠር የእውነት ባለቤት የሆነችውን በእግዚአብሔር ፀጋና ቸርነት የቆመችውን
ተዋህዶንና ኢትዮጵያን ጠዋትና ማታ ሲያሴርባት ሊያጠፋት ሲደክም ይውላል ያድራል። ለዚህ ምስክሩ ደግሞ
ይህ ያለው ትውልድ በራሱ የሚያየው ስለሆነ ግልፅ የሆነ የዓለምን ሴራ ሁሉም ቅን አእምሮ ያለው መላው
የዓለም ፍጥረት ይረዳል።
ኢትዮጵያ ከዚህም በላይ ባለቃል ኪዳን መሆኗና በዚህም የእግዚአብሔር ቃል ታምነው ተስፋ አድርገው
የተዋህዶ እምነትን ያፀኑ ሕዝቦች አቅፋ በመያዟ በብዙ የጠላት የረቀቀ ዘመቻ ስትፈጭ ስትቆላ ትታያለች።
የሚደንቀው ሁሉም ጠላቶች የሚመነጩት ከሁሉም አቅጣጫና ማእከልም ነው። የበለፀጉ ዓለምን በኢኮኖሚያቸው
በጦራቸው እያስጨነቁ ያሉ አገሮች /እነአሜሪካ እነእንግሊዝ እነፈረንሳይ እነጀርመን እነቻይና እነራሺያ እነቱርክ
እነሳኡዲ አረቢያ እነግብፅ እነሕንድ እነጃፓን እነካናዳ ወዘተ/ ናቸው። ብዙዎቹ አገሮች የመናፍቃን የካቶሊኮች
የእስላም የምሥራቁ ጣኦት አምላኪዎች ስለሆኑ፤ ሁሉም የዲያብሎስ መልከ ብዙ በይዘት ግን አንድ የሆኑ
እምነቶች ስለሆኑ ወደዚች ወደ ኢትዮጵያችን ሲመጡ ከነሱ የማይገናኝ በእግዚአብሔር የምትወደድ አገር
መሆኗን ከአባታቸው ከዲያብሎስ ስለተረዱና ከአባቶቻቸውም ይኸው ታሪክ ሲዘከርላቸው ስለኖረ የዛሬዎቹ
ልጆቻቸውም ይህንኑ ወርሰው በኢትዮጵያ ላይ የተቀናበረ ዘመቻ ያካሂዳሉ።
ዛሬ በኢትዮጵያ ዙሪያ የመላው ዓለም ኃያል ነን የሚሉ መንግሥታት ሰፍረው ኢትዮጵያን ሁለመናዋን
በመቆጣጠር ላይ ይገኛሉ። በጂቡቲ ትላልቅ የጦር ሰፈር የመሰረቱ አገሮች ምን ፍለጋ መጡ ስንል ይህችኑ
ቅድስት አገር ሊገዳደሩ በማሰብ መሆኑ ግልፅ ነው። እነዚህ በዙሪያችን የሰፈሩ የአጋንንት ውልዶች ጭንቀታቸው
ትልቅ ነው። ያጋንንት ውላጅ የዲያብሎስ ልጆች መሆናቸው በሚገባ የሚያውቁና በሱ የሚመሩ ስለሆነ ትእዛዙ
ሁሉ የሚወርደው ከዚሁ ከሚነዳቸው ዲያብሎስ ነው።

30
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እነዚህ በኢትዮጵያ ዙሪያ የሰፈሩ አገሮች እነማናቸው?

አሜሪካ፣ ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ጀርመን፣ ጃፓን፣ ቱርክ፣ አረብ ኤሜሬትስ፣ ሌሎችም በደቡብ ሱዳን እንግሊዝ
በሰሜን ሱዳን ራሺያ ግብጽ ትንሽ ራቅ ብለው የተቀሩ የአውሮፓና የኤሺያ ሌሎች አገራትም ሰፍረዋል።
እንደምትረዱት ይህን ያህል የሚያስፈሩ እንደነሱ የጠነከሩ በኢኮኖሚውም በወታደራዊ አቅምም የደረጁ አገሮች
የሉም። ያለችው ይህችው በኢኮኖሚም በወታደራዊ አቅሟም ከሌሎች ጋር ሲታይ ምንም በሆነ ደረጃ ላይ
ያለችው ኢትዮጵያ ናት። የተቀሩት የነዚሁ የከባቢዎቹ ኃያል አገራት ተገዢና ተጠዋሪ አገሮችና መንግሥታት
ናቸው። ሁሉም በነጮችና በአረቦች የሚደጎሙ አገሮች ናቸው። ጂቡቲ፤ ሱዳን፣ ሁለቱም ሱማሊያ፣ ኤርትራ
በችሮታ ያሉ አገሮች ናቸው። እነሱ ዓላማውን ሊያውቁም ላያውቁም ይችላሉ ይሁን እንጂ መጠቀሚያ ናቸው።
እንደነገርኳችሁ ኢትዮጵያን ለምን ፈሯት ለምንስ ጠሏት ስንል መልሱ አንድና አንድ ነው። የአብርሃሙ ሥላሴ
ያሰበውና ያዘጋጀው ምን እንደሆነ ለኢትዮጵያም ያለውን ፍቅር ጠላት ዲያብሎስ በሚገባ የሚያውቅ ስለሆነ፤
ይህም ብቻ አይደለም እነሱን ከምድረ ገጽ ሊያጠፋቸው የሚችልና የሚያደርግ እግዚአብሔር የቀባቸው ባሮች
የሚነሱት ከዚሁ ከኢትዮጵያ መሆኑ ግልጥ ስለሆነ ያንን የሚቋቋሙ መስሏቸው የሚያደርጉት የደመ ነፍስ
መወራጨት ነው። ሌላ ምን ያድርጉ ምንስ ያምጡ? ያላቸውን ቢሰራም ባይሰራም ጀታቸውን ሚሳኤላቸውን
መርከባቸውን ታንክና ጠመበንጃቸውን ይዘው መሰለፍ ነው። ያደረጉትም ይህንኑ ነው።
ሰባት መልእክታት በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ስም ወጥቶ ለመላው ዓለምም ለአገራችን ለኢትዮጵያም
ሲሰራጭ የዓለም ኃያላን መንግሥታት ሁሉም ስለደረሳቸው ያደረጉት የመጀመሪያ እርምጃ መልእክቱ
በሕዝባቸው መሃል እንዳይሰራጭ፣ ሚዲያዎች እንዳይዘግቡት ማድረግ ነበር። በተለይ የእንግሊዙ ቢቢሲ የዜና
ክፍል በኢሜይል ቁጥር ሦስትን /በእንግሊዝኛ የተፃፈውን/ ሲደርሰው ወዲያው የሠጠኝ መልስ እኛ መገለፅ
አንችልም ቦርዶች አሉ ለነሱ ላክ ብለው የኢሜይል አድራሻቸውን ይገልፁልኛል። ወዲያው ላኩኝ ግን ምንም
መልስ የለም አልወጣም። በሁለተኛም እንዲሁ ዘ ኢኮኖሚስት ለተባለ ዓለም አቀፍ መፅሔት አዘጋጅ እንዲሁ
በኢሜይል ላኩኝ። እነዚህ ደግሞ መድረሱን ገልፀው ነገር ግን እኛ ቀንሰንና አስተካክለን አርመን እናውጣው
ብለው ጠየቁኝ አይ አይሆንም አይቀነስም አይደለዘም አይጨመርም ከቻላችሁ እንዳለ አውጡት አሊያ ተውት
አልኳቸው፤ ተውት። እንግዲህ የነጩ ዓለም ሊመጣ ያለውን የእግዚአብሔር ፍርድ የማያውቅ አይደለም በሚገባ
ጠንቅቆ ያውቃል። በተለይ መሪዎች እንደቀላል ጉዳይ አላዩትም መሪያቸውን ዲያብሎስን ጠይቀው እውነቱን
ስለገለፀላቸው፣ ሊያደርጉ የሚገባቸውንም ስለመከራቸው ያዋጣናል ያሉትን እርምጃ ወስደዋል። ቀድመውም
ስለኢትዮጵያ ምንነት ከአባታቸው ዲያብሎስ የተረዱ በመሆናቸው ሕዝቡንና ተዋህዶ እምነትን የማጥፋት ዘመቻ
ማካሔድ ጀምረው ነበር።የተቀናጀ ዘመቻ ሲያካሂዱ 700 ዓመታት ተቆጥረዋል። የኛ ህዝበ – ክርስቲያን ግን
አጠገቡ ይህ ሁሉ ፍልሚያ ሲካሄድ ምንም ጉዳዬ ሳይል ልማዳዊ ሕይወትን ይዞ ይቀጥላል። በሚገባ ይረዳ ዘንድ
ኢትዮጵያ ማን እንደሆነች ያውቅና ይጠነቀቅ ዘንድ የተሳሳተውም ንስሓ ገብቶ ራሱን እንዲያስተካክል፣ በመላው
ዓለም ላይ ከመጣው ፍርድ ቁጣ ጠረጋ ያመልጥ ዘንድ ኖኅ አባታችን እንደጮኸው በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
7 መልእክታት እንዲደርሱት እነዲሰማቸው ተደረገ። ከዚህም በላይ በዘመኑ መገናኛ በማሕበራዊ የትስስር ገጾች
ራእይ ዮሐንስ 20 በሚል የቴሌግራም ገጽ ተከፍቶ ከሁለት ዓመት ላናነሰ ጊዜ ሁሉም መለእክቶች እንዲደርሱ
ተደረገ። ይህም ብቻ አይደለም ሁሉም የአዳም ዘር ቢሊዮኖች በሚገለገሉበት እነ ፌስ ቡክ ዩ ቲዩብ ዋትስ አፕ
ኢሞ በግልፅ በተለያየ ቋንቋ ተሰራጨ ዛሬም እየተሰራጨ ይገኛል። ማን ሰማ! እጅግ የሚያሳዝን የሚደንቅም
ነው የሰው ልጅ እጅግ ሞገደኛ ትእቢተኛ ከሃዲ የሚንቅ በእውቀቱ የሚታበይ ነው። በኢትዮጵያም ሆነ በመላው
ዓለም ከሚከታተሉት የቴሌግራም ተጠቃሚዎች 116 ሺ ሰዎች ሲከታተሉት ብናይም የኑ ተመዝገቡ ጥሪ
ስናደርግ አምነው የተመዘገቡትን ብንገልፅላችሁ እጅግ ትገረማላችሁ። ለታሪክ አቆይተነዋል። ብቻ የተመዘገቡት
እድል ነውና ባለድል ሆነዋል።

31
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንግዲህ ከላይ እንደገለፅንላችሁ የዓለም መንግሥታት ዝም ብለው አልተቀመጡም የሚችሉትን የጥፋት


ዘመቻ በኢትዮጵያ ላይ ማካሄዳቸውን ቀጠሉ። ዛሬም አልታከቱም የሚጋልባቸው ዲያብሎስ እስከፍፃሜ ድረስ
ይነዳቸዋል እንጂ! ለዚህም ነው በተቻላቸው መጠን ሁሉ የኢትዮጵያ አሻንጉሊት መንግሥታትን እየተከሉና
እያቀያየሩ ከዚህ ያለውን የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንዲሁም ምእመኑን ለመቆጣጠር ሲቻልም
ከእምነቱ በተለያየ የጨለማ እምነታቸው በማጥመድ በራሳቸው ቁጥጥር ስር ሊያደርጉት የሚጥሩት። የመናፍቁን
ስምሪትና ስፋት የእስላሙን መስፋፋት የዘረኛው መስፋፋት የከሃዲው ብዛት የሆድ አደሩ ብዛት እውቀቱን
የሚያመልከው ብዛት ይህ ሁሉ ዘመቻ በነጮች የሚቀናበር ሁለገብ ጥቃት ነው። ያውቃሉ ወገኖቼ! ኢትዮጵያ
እንደምትነሳ ዓለምን በተዋህዶ እምነት እንደምትመራ፤ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት እንደሚነግሥ
በሚገባ ያውቃሉ። የጨነቃቸው እንዴት እንቋቋመው የሚለው ብቻ ነው። እግዚአብሔር እንደሚያደርገው
ቃሉም እንደማይቀር ዲያብሎስ ጠንቅቆ ያውቃል። ግን ምንም መንገድ የለም ያለው ዘዴ ኢትዮጵያን ማዳከም
ምእመኑን ማጥፋት ትንሳኤዋን አለ ብሎ እንዳይቀበል ማድረግ እንደ አገር እንደ ሕዝብ እንዳይቆም ማድረግ
ዋናውና እያደረገ ያለው ተግባሩ ነው። ከዚህ ቢዘልና የመጨረሻው ውጊያ ቢገጥመኝ ብሎ ሁሉንም ታላላቅ
መንግሥታት በማንቀሳቀስ ያላቸውን ጦር መርከብ ሰራዊት ጀት ሚሳኤል በዙሪያችን ኮልኩለዋል። መቃብራቸው
እዚሁ እንደሚሆን በዚሁ አጋጣሚ ላበሥራቸው እወዳለሁ። እንኳን በደጃችን ቀርቶ በተመሰረትክበት አገርህ
የሚጠብቅህ ትቢያ መሆን ብቻ ነው። የኛ ጉልበት የሚመነጨው ከሥላሴ ከመለኮት ነው። ጉልበታችን ኃይላችን
ልዑልና ድንግል ናቸው። አንተንም የጨለማውን ኃይል መላውን ፍጥረት የፈጠሩ ያስገኙ ራሳቸው ናቸው።
ፈቃዳቸው በሞላ ጊዜ ቅን ፍርዳቸው በተገለጠ ጊዜ ምን እንደምትሆን ታየዋለህ ከነቅራቅንቦህ ትቀበራለህ።
ዛሬ ኢትዮጵያ እንደ ሥጋው እይታ ድሃ ናት። እንደመንፈሳዊው ግን ባለፀጋ ናት። ያዕቆብ አባታችን በእምነት
ጉዞው በቤተል የገጠመው ምን እንደሆነ በትምህርታችን ወቅት ገልፀንላችኋል። መሰላል ከምድር ወደሰማይ
ተዘርግቶ ቅዱሳን መላእክት ሲወጡበት ሲወርዱበት በአናቱም ልዑል ተቀምጦበት ነበር ያየው። እጅግ በመደነቁ
ይህ ቦታ እጅግ የተከበረ የእግዚአብሔር ሥፍራ ነው በማለት የድንጋይ ሃውልት አቁሞ ዘይት ቀብቶ አፍስሶበት
ነበር፣ ወደእናቱ ወገኖች የተሰደደው። በቦታው እግዚአብሔር በግልፅ ነበር ለአብርሃም የገባውን ቃል ከሱም ጋር
እንደሚያፀና የነገረው! ሲመለስም 20 ዓመታትን በአጎቱ ቤት ሲያሳልፍ እግዚአብሔር አልተለየውም ነበር።
ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር ተመልሰህ ወደአባትና እናትህ ሂድ ስላለው ቃሉን በመጠበቅ ወደዚያው ሲጓዝ
በቤተል ድጋሚ እግዚአብሔር ተገልጦለት ቃሉን እንደሚያፀና! ለአብርሃም ለይስሃቅ የገባውን ቃል ከሱም ጋር
እንደሚያፀና አረጋግጦለታል።

በቤተል ለያዕቆብ የተገለፀው መሰላል የት ነው የተተከለው?

እግዚአብሔር በዚህ ዘመን ቃሉን ያፀናው ከማን ጋር ነው? ቀደም ሲል ስለ እስራኤል ዘነፍስና ስለ እስራኤል
ዘሥጋ እንደገለፅነው ዛሬ ልዑል ቃል ኪዳኑን ያጸናው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ጋር ነው።
ኢትዮጵያን የሚወዳትን አገር ለእናቱ ለእናታችን ርስት አድርጎ ሰጥቷል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ የክብሩ
መገለጫና መመሥገኛ ምድር መሆኗን አረጋግጧል።
በቤተል የተገለፀው መሰላልም በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ምድር ፀንቶ ነው ያለው። ቅዱሳን መላእክት
ለተሰጣቸው ተልእኮ ሲወጡ ሲወርዱ ብዙ አባቶቻችን /በቅድስና ያሉ/ እያዩት ነው። እንግዲህ በዚህ እውነት
መሰረት ዛሬም በኛ ምስኪን አገር ዙሪያ ጦራቸውን ቢኮለኩሉ ልንገረም አይገባንም።
ዛሬ ያለው መንግሥት ምን እየሠራ እንዳለ ብዙዎቻችን እንደምንረዳው የቀደመውን የዓለም አቀፍ ወንጀለኞች
ማሕበር የቀደመው እባብ ማሕበርና ማሕበርተኛ ትእዛዝ ማስፈፀም መሆኑን በግልፅ የምንመለከተው ነው።
ቀዳማይ የዲያብሎስ ተዋጊ መሆኑን ልንጠራጠር አይገባም።

32
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች! ልብ ብላችሁ አንብቡ ተረዱ! ዛሬ ባቢሎን አሜሪካ በኢትዮጵያ የገነባችውን
ኤምባሲ እንዴት እንደተገነባ ምንስ ማስፈፀሚያ እንደሆነ ታውቃለህ?! አታውቀውም። የአሜሪካ ኤምባሲ
ሲገነባ 250 ሚሊዮን ዶላር የፈጀ ሲሆን ይህም አንሶ የተጨመረበት ነው። ወደ ምደር የሚወርድ ምድር ቤት
ያለው እጅግ ግዙፍ በምሥራቅም በደቡብም ያለውን የአፍሪካ ምድር የሚያዝዝ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ ያለው
ሁሉንም የአፍሪካ ቀጠና የሚዳስስ የሚሸፍን የተራቀቀ መገናኛ ያለው፤ በኢትዮጵያ በሁሉም ሥፍራ የሚደረጉ
ማናቸውም የስልክ የኢንተርኔት የሌሎችም ኤሌክትሮኒክስ የመገናኛ ዘዴዎች የሚለዋወጡትን መረጃ በሙሉ
የሚከታተል፤ እራሳቸው ጠቅላይ ሚንስተሩ የሚያደርጉትን የመረጃ ልውውጥ በሙሉ የሚከታተል የሚያውቅ፤
ቅርንጫፍ የሲአይ ኤ የተሟላ ቢሮና ማዘዣ ጣቢያ ያለው መሆኑን ልታውቅ ይገባሃል። ከኢትዮጵያ ውጪ
በመላው ዓለም ያሉ ኃያላን እንደምታውቀው ትልቅ ፍልሚያ ያደርጋሉ። በኢኮኖሚ ይዋጋሉ እነቻይና ራሺያ
ከአሜሪካ ጋር በሁሉም መልኩ እነሱ እንደሚጠሩት በቀዝቃዛ ጦርነት ውስጥ ነው ያሉት። አሜሪካ ከወዳጆቿ
ከአውሮፓ በኢኮኖሚ ይፋጫሉ። በተለያዩ እቃዎች ላይ ታሪፍ ይጥላሉ ሌላውም መልሶ የመልስ ምት ይሰጣል።
በወታደራዊ ግንባታም ሁሌ አንዱ አንዱን ለመብለጥ ትግል ያደርጋሉ። ይህ ሁሉ ፍጭታቸው ግን በኢትዮጵያ
ጉዳይ ሲሆን አንድ ይሆኑና ይቆማሉ። ያሁሉ ጠባቸውን ወደጎን አድርገው በጋራ አንዲት ትንሽ አገር ጅቡቲ
ውስጥ ሳይጣሉ የየራሳቸውን የጦር ካምፕ አቋቁመው የኢትዮጵያን እስትንፋስ ያዳምጣሉ። ይህችን ምስኪን
ድሃ አገር አምነው አይተዋትም። አንድ ቀን ድንገት ትቆረጥመናለች ብለው ይፈሯታል። በምን ጉልበቷ ነው
እንዲህ የሚፈሯት የሚጨነቁባት?
እውነት ነው የአንድ ቀበሌ የነጭ ወታደር የያዘውን ዘመናዊ መሳሪያ እንኳን የለንም። የኛ ሰራዊት ዘመን
የጣለውን ክላሽ መድፍ ከ40 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ታንክ ራሺያ የረሳችው ሚግ23፣ እንዲሁም በአሁኑ
ሰዓት እየተተወ ያለ የራሺያ ሱ 27 ጀት ይዛ በምን አቅሟ ነው ኒዩክለር አሕጉር አቋራጭ ሚሳየል የጨበጡ
አገሮች ጫፍ የምትደርሰው? ወገን ተረዳ ጉዳዩ የጉልበት የጦር መዘመን በኢኮኖሚ የመበልፀግ አይደለም።
ጉዳዩ እምነት ነው። እውነተኛውን እምነት ማነው የጨበጠው እግዚአብሔርስ ከማን እምነት ጋር ነው የቆመው?
ይህ ነው ዓለምን እየነዳ ያለው ዲያብሎስንም ያስጨነቀው እውነቱ ይህ ነው ሌላው ሁሉ ተቀፅላ ምክንያት
ነው። ይህንን ደግሞ በሚገባ የተረዳው ስለሆነ የሞት የሽረት ትግል እያካሄደ ነው። ኢትዮጵያ ድሃዋ! ኢትዮጵያ
ለጠላት የጉሮሮ አጥንት የሆነችበት ኢትዮጵያ! ለዲያብሎስ ብርቱ ዳገት የሆነችበት ኢትዮጵያ አስፈርታዋለች
በርግጥም የሞቱን ደብዳቤ የጨበጠችው ይህችው የኛይቱ ማንም ሥፍራና ቦታ ያልሰጣት ኢትዮጵያ ነች።
እግዚአብሔር በግልፅ ከዚቸው ምስኪን አገር ጋር መቆሙን ካሳወቀ ቆየ። እውነቱ ይህ ስለሆነ በተለይ የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት የጨበጥክ ኢትዮጵያዊ እንድትፀና እመክርሃለሁ። እርግጥ ከመቶ ሚሊዮን በላይ
የሕዝብ ቁጥር በኢትዮጵያ አለ። ምን ዋጋ አለው በእግዚአብሔር ፊት ተወዶ የቆመው ከ10 ሚሊዮን የማይበልጥ
ሕዝብ ነው። እኔ ኢትዮጵያ እስራኤል ዘነፍስ እያልኩ ስጠራ ምድረ መናፍቅ፤ ምድረ ካቶሊክ ምድረ ዘረኛ
ምድረ እስላም ምድረ ተብታቢ አባይ ጠንቋይ ኮኮብ ቆጣሪ ዘራፊ ነጣቂ ነፍሰ ገዳይ ጨካኝ ሁሉ ኢትዮጵያዊ
ነህ አላልኩም። አታታልል ኢትዮጵያዊ ነኝ አትበል አይደለህምና! በእግዚአብሔር መዝገብ ውስጥ እንደ
ኢትዮጵያዊ አትቆጠርምና! በዚህ የራስህ ምርጫ ነውና ኢትዮጵያዊ አይደለህም። አንተ የቀደመው እባብ
ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ አምላኪና የሱ ልጅ ሰጋጅ ምልክቱንም የተቀበልክ ነህ። እግዚአብሔር እውነት ነው
ሥራህን አንተ ማነህ የሚለውን በግልፅ ይነግርሃል እንጂ ስለምን ይሸፍንልሃል? አዎን ለረጂም ዘመናት ከአያት
ቅድማያቶችህ ጀምሮ ባለመታከት ለንስሓ ጠርቶሃል። አያት ቅድማያቶችህ እንዳልሰሙ ሁሉ አንተም የነሱ ፍሬ
ስለሆንክ በነሱ መንገድ ሄደህ በክፋታቸው ወርሰሃቸዋል። ስለዚህ የዲያብሎስ ልጅ የሆነ በክፉ ሥራው የፀና ሁሉ
የታመነበት ዲያብሎስ ወደሄደበት መሄድ ግድ ሆኗል። ስለዚህ አንተ ከሃዲ የተዋህዶ ጠላት የእውነት ጠላት
የሰንደቋ ጠላት ዛሬ ልንገርህ ወደመቃብርህ በብርቱ ቁጣ ትወርዳለህ በቃ!

33
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ያለው መንግሥት የአብይ መንግሥት ለዚሁ ጉዳይ ተብሎ /ኢትዮጵያን ለማፍረስ ተዋህዶን ለማጥፋት ይህን
የእግዚአብሔር እውነት የተሸከመውን ሕዝብም ለመጨፍጨፍ /በእንግሊዝና አሜሪካ ይሁንታ አግኝተው በአረብ
አገራት የገንዘብ ድጋፍ ተደግፈው በዋናነት ተዋህዶ ኦርቶዶክስን በማስከተልም ይህንኑ እምነት እንደሕብረተሰብ
የጨበጠውን አማራውን ለማጥፋት በግልጽ ዘመቻ የከፈቱ ሰው ናቸው። ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ውጪ
ታሳድራለች እንደሚባለው በጌቶቻቸው ስለታመኑ ለፍጅቱም ለእልቂቱም በአማራው ላይ ለሚሰራው ሁለገብ
ጥፋት ዋንኛ መሪ ሆነው ተገኝተዋል። ሙሉ በሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳሉ። ቀድሞም በፍርድ ውስጥ ያሉ
መሆናቸው ግልፅ ቢሆንም ፅዋውን እስኪሞሉት ሲጠበቁ ነበር። አሁን ግን ከመሙላትም አልፎ ስለፈሰሰ
የእግዚአብሔርን ቁጣ ይጋቱታል።
በጥቅሉ ኢትዮጵያ ማናት ለሚለው መጠነኛ መረዳት እንዲኖራችሁ ሞክሬአለሁ። ልብ በል ወገኔ! ይህ
መልእክት እንደወጣ በመላው የዲያብሎስ ተጠዋሪዎች እጅ እንደደረሰ ምን እንደሚያደርጉ ቀድሜ ልንገርህ!
በዚህ መልእክት ውስጥ የተጠቀሰው እውነት እንዳልሆነ በተለያዩ የምሁር ካባ የተሸከፉ ሆድ አደሮች የዲያብሎስ
ምርጥ እቃዎች ሁሉ በእጃቸው ስለሆነ በሚዲያው ሁሉ ተፃራሪ ፕሮፓጋንዳ መንዛት ይጀምራሉ። ከዚያም
እጅግ አሳሳች የሃይማኖት ትንታኔና ዲያብሎሳዊ ስልቶች እያቀናበሩ በግለሰብም በድርጅትም እንደመንግሥትም
በመላው ዓለም ያሉ ሰዎቻቸውን በውስጥ መስመራቸው የማጠንከር ሥራ ይሰራሉ። ምናልባትም አሁን ከምናየው
የሚበልጥ ሴራ አደራጅተው በጭካኔ ለጥፋት ይነሳሉ። እነሱ ይህን የሚያደርጉት ያቆየናል እንሰነብታለን ከሚል
የዘወትር ህልማቸው በመነሳት ነው። የሚሆነው ይህ ነው። ግን ጊዜ የለም። ጊዜ የለም፤ ደጋግሜ ልንገርህ ምንም
ጊዜ የለም ፍርዱ ሁሉ ተጭኖ መጥቶ በምድሪቱም በሰማዩም ሞልቷል። ትእዛዝ ብቻ ነው የሚጠብቁት ይህ
ደግሞ ከዚህ መልእክት መውጣት በኋላ ከፀባኦት ከልዑል ዘንድ ትእዛዝ ይወጣል። መፈፀሚያህም ይጀምራል።
ዲያብሎስ ያነገሳቸው ምርጥ እቃዎች አሉት የዛሬዎቹ አሜሪካ እንግሊዝ ፈረንሳይ ጀርመን ቻይና ራሺያ
እስራኤል ሕንድ ቱርክ ስፔን ካናዳ አውስትራሊያ ሌሎችም እኒህ ሁሉ እንደ የደረጃቸው ዲያብሎስ ኮልኩሎ
ያነገሳቸው ምርጥ እቃዎቹ ናቸው። እነዚህ ደግሞ በድሃው አገር ላይ አለቃና አዛዥም ናቸው። የአንድ ታዛዥ
አገር መሪ ትእዛዝ መፈፀም ሲሳነው ሲደክም ፈረስ ነውና ሌላ ፈረስ እንዲተካ ዋናው አዛዥ ዲያብሎስ ትእዛዝ
ይሰጣል። በተዋረድ ስልጣን የሰጣቸው ታዛዦቹ አለቆች የደከመውን ፈረስ እንደትእዛዙ ይቀይራሉ ሌላ ፈረስ
ትኩስ ጉልበት ያለው ይተካል። የተሰጠውንም አጀንዳ ተሸክሞ ይበራል። ሂደቱ እንዲህ ነው። ወያኔ ከመድከሙ
በፊት አይዞህ በርታ እየተባለ በገንዘብ በፖለቲካው በወታደራዊ አቅም በሁሉም ሲደገፍ ነበር። ወደ ሁዋላ
መለስ በሉና ያሳለፈውን ዘመን ቃኙት። ሕዝቡ ሸክሙ ሲከብደው ለማመፅ ሲነሳ አለቃ ዲያብሎስ ለነአሜሪካ
ለነእንግሊዝ ትእዛዝ ሰጠ ይህ ፈረስ ደክሟል ፈጥናችሁ ቀይሩ አለ። የኢትዮጵያ ጉዳይ ደግሞ ለኔም ለናንተም
ሕልውና አስጊና አደጋ ስለሆነ ፈጥነን ፈረስ መቀየር ይገባናል አለ። እንደምታዩት የነመለስ /ትግሬው/
ፈረስ በመድከሙ፤ በምትኩ የኦሮሞ ፈረስ አብይ አሕመድ ተተካ። እሱም ካቃተው ሌላ ፈረስ ለመቀየር
ዲያብሎስ አያቅማማም። ግን ዛሬ ችግሩ ጊዜ የለም። አብቅቷል። በመላው ዓለም ደርጅቶና ተንሰራፍቶ የኖረው
የጨለማው ገዢ ዲያብሎስ የሺዎች ዘመናት ጉዞውና ንግሰቱ ተጠናቋል። አብቅቷል። ጊዜ የለም። እንደ ቼዝ
በሰው ልጅ ደም መንቦጫረቅ በቅቷል። የፍጥረት ሁሉ ጌታ ለሺዎች ዘመናት ፈቅዶለት ዲያብሎስ የነገሰበት
ዘመን ስላበቃ ፍርዱም እንደሥራው ሊበየን ስለሆነ ጊዜ የለም። ቅን ፈራጁ እግዚአብሔር ምድርን በቅን ፍርዱ
ያካትታል። የማፅናናት ጊዜ ይመጣል ይወለዳል። የተገፉ የተፈጩ የተቆሉ ለረጅም ዓመታት ዘመናት የተዋረዱ
በልዑል ታምነው የተፈጩ የተቆሉ የሚካሱበት በሰማዕትነት ያለፉትም የሚታሰቡበት ዘመን ይሆን ዘንድ
ከልዑል በመወሰኑ ይህም ውሳኔ ወደመተግበሩ ከመሄዱ በፊት ለአንዳንዶችም ለንስሓ በመታሰቡ ለ15 ዓመታት
ቆይቷል። አሁን ግን ጊዜው ተደምድሟል። ሌላ ጊዜ የለም። ያው በፍርድ ተካቶ ወደ ሲኦል መውረድ ብቻ
ነው።

34
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርሰቲያን ዛሬ እምን ላይ ነች?

የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበት ሁኔታ እጅግ አስከፊ በዘመኗም ያላየችው
ፈተና እያመሳት እያጠፋት ባለበት ሁኔታ ውስጥ ነው ያለችው።
በኢትዮጵያ ታሪክ እጅግ የከፋ የሚባለው የግራኝ መሃመድና የጉዲት የጥፋት ዘመን ቢሆንም በቤተ
ክርስቲያን ላይ ብርቱ ጉዳት ደርሶ ሕዝብ ቢፈጅም እንደ እምነት ሕዝቡ በእምነቱ ጠንካራ ነበር። ጥፋቱም
ያው ዲያብሎስ ያደራጀው ቢሆንም ብዙ አልዘለቀም። ሕዝቡ /ምእመኑ / ወደ ፈጣሪው ጮኸ እግዚአብሔርም
በፍጥነት አስወገዳቸው። ነጮች እንግሊዝ ቱርክ ጣሊያን ፖርቹጋል እነዚህ በአንድም በሌላ እንዲሁም በቀጥታ
በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ ይገቡ ነበር። የራሳቸውንም ተፅኖ ፈጥረው ጉዳት ማድረሳቸው በታሪክ ተመዝግቦ
ይገኛል። የዛሬው ግን ለየት ያለ ዘመቻ ነው።
የአሁኑ የቤተ ክርስቲያን ጥፋት ከውስጥም ከውጪም እየተካሄደ ያለ በመሆኑ ጥፋቱን እጅግ ያከብደዋል።
በተለይ ደርግ ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን ላይ ዘመቻው በይፋ የተከፈተ ነበር። ቤተ ክርስቲያን
ባትፈርስም በውስጧ ያሉ አገልጋዮች በስፋት ባይገደሉም። ደርግ ይመራ የነበረው በኮሚዩኒዝም ስለነበር።
ብዙን ወጣትም ሆነ ሕብረተሰብ ወደቤተ ክርስቲያንም ሆነ ወደመስጊድ መሄድን እጅግ እንዲፈራ ያደረገ ሁኔታ
ፈጥሮ ነበር። በውቅቱ ቀይ ሽብር የነገሰበት ወቅት ስለነበር ሰው ሁሉ በሥጋት ውስጥ የወደቀበትና በየቤቱ
ተከቶ በጭንቅ የሚያሳልፍበትም ወቅት ነበር። ተረጋግቶ ወደቤተ ክርስቲያን ለመሄድ የሞከረው ኢሰፓኮ
የሚባል ፓርቲ ከተመሰረተና በደርግ ውስጥ ያለው የውስጥ ትግል በመንግሥቱ ኃይለማርያም የበላይነት
ከተጠናቀቀ በኋላ ነበር የተሞከረው። ይሁንና ቤተ ክርስቲያን በትምህርቱም በጣም የተዳከመችበት ነበር።
በተለይ በከተሞች አካባቢ የጎላ ነበር። አብዛኛው በሰሜን ያለው የአገራችን ክፍል የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ተከታይ
ስለነበር መተዳደሪያውም መሬት ስለነበር ይህ መሬት በመወረሱ የቤተ ክርስቲያን ገቢ በእጅጉ የተመታና ገቢዋ
ሁሉ ተመናምኖ የወደቀበት ጊዜ ነበር። በተለይ የአብነት ትምህርት ቤቶች በእጅጉ ተመትተዋል። የደርግ
አስተዳደር በፈጠረው ተፅእኖ የየኔታ ትምህርት ቤቶች የመጥፋት ያህል ሆነዋል። በዚህ ሂደት የቀጠለው ጉዞ
በተለይ የቤተ ክርስቲያናችንን ፓትሪያርክ እስከመግደል በመሄዱ ብዙ አባቶች ወደውጪ አገር እስከመሰደድ
ደርሰዋል። ይህ ሁኔታ እስከደርግ ውድቀት ድረስ ቢላላም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያረፈው መድቀቅ ቀጥሎ ነበር።
ከደርግ ውድቀት በኋላ ወያኔ ስልጣን እንደያዘ የመጀመሪያ ዘመቻው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን ላይ ነበር። በቤተ ክርስቲያናችን በቀጥታ ጣልቃ በመግባት በወቅቱ የነበሩትን ፓትሪያርክ
መርቆሪዮስን ከአገር እንዲባረሩ አድርጎ በምትካቸው ወያኔ ያዘጋጃቸው ካቶሊኩ አባ ጳውሎስ በጉልበት
እንዲቀመጡ አደረገ። በዚህ ድርጊት ስለእምነታቸው መሟገት ሲገባቸው በመስማማት 33 ጳጳሳት ፊርማቸውን
በማሳረፍ የካቶሊኩን ጳጳስ አባ ጳውሎስን ተቀበሉ። አባ ጳውሎስ ወዲያው ብዙም ሳይቆዩ የቤተ ክርስቲያኒቱን
ሥርአተ አምልኮ ለመናድ በማሰብ ከካቶሊክ የተሰጣቸውን ትእዛዝ ለማስፈፀም ወስነው የቤተ ክርስቲያኒቱ
የበላይ የሆነውን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚገለጥበትን ሕግ ለመለወጥ ወሰኑ። ቀደም የነበረው ትክከለኛው
ሕግ የቤተ ክርስቲያናችን የበላይ ሲኖዶስ ሲሆን የሲኖዶሱ የበላይ ደግሞ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነበር።
ጉባኤ ሲኖዶስ ሲጀመር ሁሉም ጳጳሳት በክብ ይቀመጣሉ በመሃላቸው ከፍ ባለ ጠረጴዛ ሰማኒያ አሃዱ መጽሐፍ
ቅዱስ ይቀመጣል። ጉባኤው ሲከፈት በጸሎት ጉባኤውን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እንዲረከብ ይደረጋል።
ከዚያ በኋላ ጉባኤው ይከናወናል። ፓትሪያርኩ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መሪነት በሲኖዶሱ የተላለፈውን
ውሳኔ ሥራ ላይ ያውላል። ፓትሪያርኩ ተጠሪነቱ ለሲኖዶስ በመሆኑ ሥራው ሁሉ የሚመራው በሲኖዶሱ
ውሳኔ ላይ በመመስረት ነበር። ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ ቤተ ክርስቲያናችንም ቀኖናዋ ከተለወጠ በኋላ የቀደመው
ትክክለኛው ሕግ ተሸሮ አባ ጳውሎስ የሲኖዶሱ መሪ እንዲሆኑ ተደረገ። ይህም ማለት ሲኖዶሱ ለአባ ጳውሎስ
ተጠሪ ሆነ። ይህ ጣኦትን ያነገሰ፤ አባ ጳውሎስ በሲኖዶስ ቦታ እራሳቸውን ስለሾሙ ቤተ ክርስቲያን የጣኦት

35
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ቤት ሆነች። ይህ ሕግ እስከአሁንም ያልተሻረ ሆኖ በአቡነ ማትያስም ቀጥሎ ይገኛል። የተሰደዱት ፓትሪያርክ


ተመልሰው ቢመጡም በዚህ ሕግ ላይ የተደረገ ለውጥ የለም። አባታችን ሊቀ – ሊቃውንት አያሌው ታምሩ
በወቅቱ ባደረጉት ሙግት ትክክለኛውን የቤተ ክርስቲያን ስርዓት የለወጡትን አባ ጳውሎስ ከጥፋት ሥራቸው
እንዲገቱ ለማድረግ ከፍተኛ ትግል ቢያደርጉም ራሳቸው ጳጰሳቱም ስላልደገፏቸው ጭርሱኑ ከሥልጣናቸውም
ከቤተ ክርስቲያን ታገዱ። እሳቸውም በከበረው የክህነት ሥልጣናቸው ሲኖዶሱንም አባ ጳውሎስንም የአባ
ጳውሎስን ስም የሲኖዶስ አባላትን ስም በቅዳሴውም በአገልግሎቱም የምትጠራ ቤተ ክርስቲያን ካህን አገልጋይ
ሁሉ በግዝት እንዲታሰር አደረጉ። ትክክለኛም ሥራ ሠሩ። ይህ ግዝት የሚነሳው ቤተ ክርስቲያን እሳቸው
የገዘቱበትን በቂ ምክንያት ተረድታ ከጥፋቷም በመፀፀት ተመልሳ የትክክለኛውን አባት ግሣፄ ተቀብላ ስትታረም
ብቻ ነው። የቤተ ክርስቲያን ሕይወት የሚመለሰውም በዚህ መንገድ ብቻ ነው። ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ከዚህና
ከመሳሰሉ ጥፋቶች ከመመለስ ይልቅ በጥፋቷ ገፍታ ትገኛለች። ዛሬ ቤተ ክርስቲያን የተሃድሶ የቅባት የፀጋ
መታጎሪያ ሆናለች።
ቤተክርስቲያን ነጋዴ ከመሆንም አልፋ የሚበዙት እረኞቿ ሚሊዮነሮች ሆነው ቤተ ክርስቲያንን የንግድ
ማእከል አድርገዋል። ይህም ብቻ አይደለም የሚበዙት ጳጳሳት ዝቅም ባለ ማእረግ ያሉ አገልጋዮች ሁሉ
የመንግሥት ሰላይ ሆነው ለመናፍቁና የእስላም አስተዳደሩ የአብይ መንግሥት አገልጋይ ሆነው ለቀደመው እባብ
ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ ተሸንፈዋል አምልከውታል በዚህም ድርጊታቸው ምልክቱን ወስደዋል።
ወገኖቼ እውነት እውነት ነው። እንዲህ ብለን እውነትን የተጨበጠችውን ቤተ ክርስቲያናችንን ያፈረሱትን
በግልፅ ማንነታቸውን ልንገልፅ ይገባል። በእምነትህም ልደራደር የምትል፣ ከፖለቲካውም ከካሃዲ እምነቶችም
ጋር በምንም መንገድ የምትተባበር እምነትህን አታውቀውም። ከሃዲም ነህ። እንደምትረዱት ቤተ ክርስቲያን
እረኛ የላትም ሁሉም ማለት ይቻላል እራሳቸውን ያሰማሩ የካዱ ምንፍቅናን ያነገሱ ሆነዋል። ስለዚህ ፍርዱም
የመጣው እነዚህን ተዋህዶ እምነትን ከውስጥ ተቀምጠው እያፈረሱ ያሉትን ለማጽዳትም ነው። በአፍ ተዋህዶ
ነኝ ይላሉ በተግባር ግን ቅባቶች፣ መናፍቆች ተሃድሶዎች ሰላዮች ናቸው። ማንም ሰው በምላሱ በፕሮፓጋንዳው
ከጠቀሙት ሊደግፋቸው ይችላል። በእግዚአብሔር ዘንድ ግን በማንነታቸው ላይ ለውጥ አያመጣም። ያው
የዲያብሎስ ልጆች ናቸው ፍርዳቸውም ወደ አደባባይ ይወጣል።
ቤተ ክርስቲያን በዚህ ብቻ አይደለም እየተመታች ያለችው። የነጩ ዓለም በዚች የእውነት ቤት ላይ ዘመቻ
ከከፈቱ እረጅም ዘመን ያስቆጠሩ ቢሆንም እንደአሁኑ ጊዜ ከፍቶ አያውቅም። ለዚህ ደግሞ ዋናው ምክንያት
የዛሬ 15 አመት ጀምሮ እየተገለፀ የመጣው እውነት ፈተና ውስጥ ስለከተታቸው ነው። ያደፈጡት ሁሉ በስውር
ቤተ ክርስቲያንን ሲገሉ የነበሩ በግልፅ ማጥፋት የጀመሩት በዚሁ ምክንያት ነው።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በሚል ኃይለ ቃል የመጣው መልእክት ከልዑል በተሰጠን ዓይነ – ልቡና
እየተገለገልን እውነቱን ወደ አደባባይ ስላደረስን መሸፈኛ ዘዴ ስላጡለት ጭፍን ውግዘትን በየስርቻው ሲያካሂዱ
እንሰማለን።
እግዚአብሔር አምላካችን በባሕርዩ እውነት ነው። በመሆኑም እውነትን ብቻ ነው የሚያጸድቀው። የውሸት
ባለቤት ደግሞ ዲያብሎስ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ነው። ሃሰትን ክህደትን ምንፍቅናን ያነገሱ
የቤተ ክርስቲያናችንን የተዋህዶ እምነት የካዱ በላያችን ነግሰው እየተመለከትን ዝም የምንል ከሆነ እግዚአብሔርን
እንዴት እያመለክነው ነው እንላለን? እንዴትስ እውነትን አንግሰናል እንላለን? በመሆኑም ቤተ ክርስቲያናችንን
አፍርሰዋል የምንለው እየሠሩ ባሉት ምግባርና አካሄዳቸው ነው። በአንድ ወቅት መልካም ለመሥራት በመልካም
የተዋህዶ ልጆች የተመሰረተው ማህበረ ቅዱሳን የሚባል ተቋም በወቅቱ በጎ ሥራ ቢሰራም ቀስ በቀስ የመንግሥት
ሰላዮች ስለተሰገሰጉበት ስሙ እንጂ ግብሩ የጠፋ እንዲሆን አድርጎታል። ፀጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል

36
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንደሚባለው ይህም ድርጅት በግልፅ ወጥቶ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃንን ሲቃወም ሰምተናል ይህንንም ያደረገው
ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ስርጭቱ ላይ ባቀረባቸው ሁለት እንግዶች አማካኝነት ነው።
እንግዶቹ መምህር ኃይለማርያም ዘውዱ እና መምህር ገብረ መድህን እንየው ይባላሉ። የፕሮግራም አዘጋጁና
ጠያቂው ስማቸውን ስላልገለፁ ስማቸውን ባንጠቅስም የድርጊቱ ዋናው አቀናባሪ እንደሆኑ ተረድተናል።
በዚህ ዝግጅቱ ሁለቱ መምህሮች ነን የሚሉ ካባና ጥምጥም ያደረጉ አዋቂ ነን የሚሉ የኢትዮጵያ ትንሳኤ
የለም። እንዲያውም መጽሐፍ ቅዱስን እንጂ አዋልድ ብለው የሚጠሯቸውን ገድላተ ቅዱሳን እንደከንቱ ሲቆጥሩ
ሰምተናል። እንግዲህ ልብ ልንል ይገባል እነዚህ በግልፅ እንደ ፕሮቴስታንቶቹ ዓይነት አቋም ይዘው ሲናገሩ
ሰምተናቸዋል። ቤተ ክርስቲያናችንን ለማፍረስና ምንፍቅናን ለማንገስ ምን ያህል ማህበራት ቤተ ክህነትና አመራሩ
እንደተሸጡ እየተረዳን ነው። ይሁንና እየደከሙ ያሉት ላለው የመናፍቅና የእስላም ጥምር መንግሥት እራሳቸውን
የሸጡ በመሆናቸው ካባውንና ጥምጥሙን የሚጠቀሙበት ውስጣዊ ማንነታቸውን ለመሸፈንና የጠመጠመ ሁሉ
የተማረ ካህን ነው በሚል ሕዝበ ክርስቲያኑ ይቀበለናል በሚል የሠሩት ስልታዊ የምንፍቅና ዘመቻ ነው። መምህር
ኃይለማርያም ዘውዱ በአብዛኛው ፌስ ቡክን ቴሌግራምን ዩቲዩቡን በመተቸት ተጠምደው ነበር ያሳለፉት።
በሌላ በኩል በተለያዩ አባቶችም እሳቸው እንደሚሉት በከተማ የሚኖሩ አባቶች መናገር እንደውሸት ተናጋሪ
አድርገው ቆጥረው ነበር ሲተቹ የነበረው። ይህም ብቻ አይደለም ስለትንሳኤ ምንነት የሚነግሩን በማቲዎስ 24
የተፃፈ ስለሆነ የሚነግረን አያሻም ነበር ያሉት። እንግዲህ እኝህ ሰው ራሳቸው በቴሌቪዥን ቀርበው እየተናገሩ
ማህበራዊ ገጾችን በሙሉ እንደማይጠቅሙ ከንቱዎች እንደሆነ ተናግረዋል። እሳቸው የለፈለፉበት ቴሌቪዥንም
የኤሌክትሮኒክስ ውጤት መሆኑን እረስተዋል። ለሳቸው ንገግር ሲሆን ትክክል ለሌላው ግን ውሸት ነው ባይ
ናቸው። ከኔ ውጪ አይሰማ ባይ ናቸው። ቀጥሎም ስለትንሳኤው ያነሱት ማቴዎስ 24 የሚነግረን የልዑልን
መምጣት ለመጨረሻው ፍርድ ይህንንም የሚያሳዩ ምልክቶች እንደሚከሰቱ ጌታ የተናገረበት ነው። እኛው
እንንገራቸውና ለመምህሩ ማቴዎስ 25 ስለዚሁ በግልፅ የሚያስረዳ ቃለ እግዚአብሔር ነው። ይሁንና የሳቸው
ንግግር ከኛ አባባል ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም። እኛ ያልነው በምድር እግዚአብሔር ስለሚያመጣው
የትንሳኤ ዘመን በራእየ ዮሐንስ የተነገረውን ሲሆን ወደዚያም እንዴት እንደምንጓዝ በዚሁ በራእይ ዮሐንስ
ምዕራፍ 16፣ 18፣ 19 የተጠቀሰውን ቃል በመግለፅና ኢትዮጵያም የትንሳኤው መሪ መሆኗን በመግለፅ ነው።
እንግዲህ መምህር ስለንጉሥ ቴዎድሮስም ልጨምርሎት ትንቢተ ኢሳይያስ ምእራፍ 49ን ያንብቡ! ይቅርታ
የአዲስ ኪዳን መምህር ኖት። ብሉይን አያውቁትም ስለዚህ እርስዎ ብሉይን ከሃዲስ አዋህዳና እስማምታ
የተመሰረተችውን ተዋህዶ የሚያውቋት አይመስለኝም። ምንፍቅናዎን በሚገባ ያሳብቅቦታል።
ሁለተኛው መምህር ገብረመድህን እንየው የተባሉ ደግሞ አዲስ ነገር ያወራሉ። አንድም ንግግራቸው
በእግዚአብሔር ቃል ያልተደገፈ ተራ ስድብና ትችት ነበር። ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃንን በመተቸት መታወቂያ
ያድላሉ በመርከብ ግቡ ይላሉ ብለው እንደወንጀል እንደአጋንንት መንፈስ ቆጥረውናል። መሰደብ መናቅ ለኛ
ልብሳችን ነው። እኛ ቃሉን በመሸምደድ እንደድርሰት አናነበንብም። በእምነት እንኖርበታለን እንጂ! ለመሆኑ
እኛን የት ያውቁናል? የትኛውን መልእክታችንን አንብበዋል አያውቁትም መሽሩፍ አገኙ ወጥተው ደነፉ።
መልካም ነው። ከዚህም ሲያልፉ 3ት ትንቢት አይነት አለ አሉ አንዱ የመረጃ ትንቢት ሁለተኛው የአጋንንት
ትንቢት ሶስተኛው የመንፈስ ቅዱስ ትንቢት ብለው ከፋፍለዋል። ለማንኛውም ይህ አባባል በአንድና በሁለት
ስለጠቀሷቸው በእግዚአብሔር ቃል አስደግፈው ቢነግሩን መልካም በሆነ ነበር። መረጃም በሉት አጋንንትም
በሉት ሁለቱም ትንቢት አይባሉም ቅዠት ይባላሉ። ጥምረታቸው ከእርኩስ መንፈስ ጋር ነውና! እግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስ ስለሚገልጠው እውነት ግን በሕልምም በራእይም በብዙ መንገድም ሥላሴ ለልጆቻቸው
መንፈሳዊ ምሪትን ይሰጣሉ። መምህር ጎረምሳ ኖት እንደተመለከትኮት ከ30 አይበልጡም ጓደኛዎም እንዲሁ
ናቸው። በእድሜ ብዙ ያለፉትን አባቶች ለመንቀፍ ስትደፍሩ ማንነታችሁንና መሰረታችሁን ያሳያል። እናንተ
መምህር የተባላችሁበትን አዲስ ኪዳን ለኛ ያሳለፉልን ሐዋርያት ራሳቸው የፃፉትን ወንጌል ነበር እናንተም

37
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

የጠቀሳችሁት /ማቴዎስ24/ ግን ጌታ ከእየሩሳሌም እኔ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እስክልክላችሁ ተቀመጡ


እኔ ካረግሁ በኋላ እሱን /እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን/ እልክላችኋለሁ እሱ ይመራችኋል ይመክራችኋል
ያስተምራችኋል ነው ያለው። እንዴት ነበር የመራቸው በራእይ በሕልም እየተገለጠ የፀናውን መሰረታዊ ቃሉን
ብሉይ ከሃዲሱን ዘመኖችን በየጊዜው እንዴት እንደሚዳኝ የሚገልፅበት መንገድ መሆኑን እያሳወቀ እዚህ
እንዳደረሰን አታውቁምን ለማንኛውም እኛ መታወቂያ ሰጠን ስለምን ዓለማ ሠጠን የወሰዱት ይንገሯችሁ
ግን ምን ያደርግላችኋል ብትመኙትም አታገኙትም። የእምነት መርከብ ድንግል ናት። የታመኑት የትንሳኤው
ሙሽሮች ናቸው የሚሳፈሩባት። ቃሉን ማነብነብ አይደለም ይግባችሁ በእምነት ነው እግዚአብሔርን ማስደሰት
የሚቻለው። እሺ! እናንተ መምህሮች የዘመናችን ፈሪሳውያን አዋቂዎች መምህር መምህር አትበሉ መምህራችሁ
እኔ ነኝ ያለው ጌታችን ወዴት ሄዶ ነው እናንተ የዘመናችን ፈሪሳውያን መንገድ የምትዘጉ አታልፏትም።
በመጀመሪያ የመጣው እሳት እናንተን መንገድ ዘጊዎችን አጥፊ እረኞችን ነው የሚጠርገው። ስለማታውቁት
ባታወሩ በተሻላችሁ ነበር። ስለእናንተ ትንቢተ ሕዝቅኤል ምእራፍ 34 በሙሉ አንብቡ። እናንተ ማረፊያችሁ
ከዚያ ነው። የተጠበቃችሁትም ለፍርድ ስለሆነ በነፍሳችሁ ብትድኑ እንዲሆን ሥጋችሁን ግን ለሰይጣን መሰልጠን
ሰጥተናል።
የኢትዮጵያን ትንሳኤዋን ስለካዳችሁ እንኳን ልትሻገሩ ለዋዜዋም አትደርሱም። ይህ እውነት ይድረሳችሁ።
ሞት ይቀድማችኋል።
በማጠቃለያ ቤተ ክርስቲያናችን በታላቅ አደጋ ውስጥ እንደሆነች መረዳት ያስፈልጋል። የአባቶችን ሕግ አፍርሳ
በአባ ጳውሎስ /በጉልበተኛው ጳጳስ / የተከለችውን የጣኦትነት ሕግ ስላላስተካከለች አገልጋዮቿ ሁሉ በውግዘት
ውስጥ ናቸው። በነሱ መባረክ ማናቸውም አገልግሎት ማድረግ አይቻልም። የሚያደርግ ደግሞ በተግባራቸው
ተካፋይ ስለሚሆን ውግዘቱ ያገኘዋል ማለት ነው። በመሆኑም የምንመክረው የእግዚአብሔርን እርምጃ በትእግሥት
መጠበቅ ግድ ሲሆን። ወደ ፊት በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የተሰበሰቡ ቤተ ክርስቲያኖች ሲጠናከሩና በርከት
ሲሉ የነዚህ ውገዘቱን የተቀበሉና ትእዛዙን አክብረው ራሱን ለማረም ለማስተካከል ያልፈቀደውን ሲኖዶስ ስም
በማናቸውም ሥርአተ አምልኮ ባለማንሳት የተለዩ ሲሆኑ በእነሱ መገልገል ይቻላል ብለን እናስባለን። በጥቅሉ
ጊዜው ቅርብ ስለሆነ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንዳትታወኩ እንመክራችኋለን። ሌላው የምንመክራችሁ ቤተ
ክርስቲያን የመንግሥት ፖሊሲ አስፈፃሚ ከሆነች ቆየች። ስለዚህ ለመንግሥት ሌላው ምላስ ከሆነች ልትሰሙ
አይገባም እንላለን። ከዚህ የሚልቀው ትልቁ ምንፍቅናዋና ክህደቷ የሚመነጨው ከአባ ጳውሎስ ጊዜ ጀምሮ
እየተተገበረ ያለው የሃይማኖቶች ሕብረት የሚባል ስብስብ ውስጥ አባል ስትሆን በቅርቡ የኮረና በሽታን
ተከትሎ በቴሌቪዥን በተላለፈ የጋራ ፀሎታቸው የቤተ ክርስቲያናችን መሪዎች ባዘዙት መሰረት ከመናፍቃን፣
ከካቶሊኮች፣ ከእስላሞች ጋር የጋራ ጾም ጸሎት ለ1 ወር አውጀው አከናውነውታል። ስለዚህ አውሬውን
ለተቀበሉ እሱም ለፈጠራቸው እምነቶች ምንፍቅና ኩትልክና እስልምና ጋር አንድነታቸውን አረጋግጠዋል።
ስለዚህ ለቀደመው እባብ፣ ለዘንዶው፣ ለሃሰተኛው ነብይ ሰግደዋል አምልከዋል፣ ምልክቱንም ተቀብለዋል።
የዚሁ የዲያብሎስን መንግሥት ፈቃድና ሃሳብ ተግብረዋል። በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን ራሷ መዳን መፈወስ
ይገባታል እንጂ ሌላውን ምእመን ልታድንና የእረኝነት ግዴታዋን ልትወጣ አትችልም። በእንደዚህ አይነት
ክህደት ውስጥ እስከወደቀች ድረስ!!
በእውነትና በመንፈስ በፍፁም ልብ በፍፁም ሃሳብ በፍፁም ነፍስ በሥላሴና በድንግል ለምንታመን የእግዚአብሔር
ቤተሰቦች በእምነት ዐይናችሁ አስተውላችሁ እንድትመለከቱና የሚሆነውን በትእግስትና በፅሞና እንድትከታተሉ
እየገለፅኩ ከዚህ በታች የምገልፅላችሁ መሰረታዊ ክንዋኔዎች የሚፈጸሙና በቶሎ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ
የሚተገበሩ ናቸው።

38
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ንቅለ ተከላ

እነማን ይነቀላሉ አዎን በመላው ዓለም ያሉ በመግቢያው እንደተገለፀላችሁ ለቀደመው እባብ ለዘንዶው
ለሃሰተኛው ነብይ የሰገዱ ያመለኩ ምልክቱንም የተቀበሉ ሁሉ መሪም ተመሪም ሁሉም የሰው ዘር በየትኛውም
የምድር ገጽታ ያለ ሁሉ ከዚች ምድር በታላቅ ቁጣ በታላቅ እሳትና መቅሰፍት እንዲጠረግ ይደረጋል። የትኛውም
ኃያል አገር፣ ምንም አይነት አቅምና ጉልበት ይኑረው እንደ ትእቢቱ በሚመጥን እሳት ፍፁም ይጠረጋል።
በተለይ ታላላቅ ነን የሚሉ አገሮች ኒዩክለር ጨብጠናል ሚሳየል ጀት የጦር መርከብ አለን ሁሉን እንገጥማለን
የሚሉ የዲያብሎስ አለቆች በታላቅ ቁጣ ምድርም ሰማይም አይተውትም ተመልክተውም በማያውቁት ከባድ
እሳት ሙሉ በሙሉ ከዜጎቻቸው ጋር ይጠረጋሉ። እነማን ይድናሉ ለሚለው በመልእክት 3 እንደተገለፀው፤
በመልእክት ስምንት በመልእክት አምስት እንደተገለፀው ይሆናል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከፈረሰችበት ከተቃጠለችበት፤ በመናፍቅ በካቶሊክ
በደህንነት ሰላይ በካድሬ ቄስ ከተተበተበችበት ከአጥፊዎቿ የተላቀቀችበት ሁኔታ ይፈጠራል። እነዚህ ሁሉ
ጠላቶቿ በእግዚአብሔር ፍርድ ተጠርገው ለእሳት ይጣላሉ። እግዚአብሔር የወደዳቸው የመረጣቸው ያፀደቃቸው
አገልጋዮች ስፍራውን ይረከባሉ።

እነማን ይተከላሉ?

አዎን እግዚአብሔር ወደትንሳኤው ይሻገሩ ዘንድ የወደዳቸው ሁሉ በመላው ዓለም ይተከላሉ። የሚበዙ
የምድራችን ከተሞች ሁላችሁም እንደምታውቁት ሰንበትን በመጣስ የተገነቡ፤ ዲያብሎስን በአንድም በሌላም
መንገድ ለማንፀባረቅና ለማስረፅ የተሠሩ ናቸውና ሙሉ በሙሉ ይጠረጋሉ በምትካቸውም በተቀደሱ
እግዚአብሔርን ባከበሩ ቅድስናቸውን በጠበቁ ሰንበትን በሚያከብሩ የልዑልን ሕግ በሚያከብሩ የእግዚአብሔር
አገልጋዮች በአስደናቂ ሁኔታ መልሰው ይገነባሉ።
በሁሉም የምድር ገጽ እንዳስፈላጊነቱ ጊዜያዊ አስተዳደሮች በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ሥርና
ገዢነት ይዋቀራሉ። የመጀመሪያው የመንግሥት አወቃቀር በኢትዮጵያችንና በዙሪያዋ ባሉ አገሮች /በመልእክት
ስምንት እንደተገለፀው/ ይመሰረታል። ዓለም በግልፅ ልዑልም ድንግልም የሚከብሩባትን ኢትዮጵያን፤
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ሥር ደምቃና በተወደዱት በተመረጡት ለትንሳኤው በታጩት ልጆቸቿ
አብርታ ያያሉ።
ከተዋህዶ ኦርቶዶክስ ውጪ የሆኑ እምነቶች ተቋሞች የጣኦት ቤቶች የነካቶሊክ የነመናፍቅ የእስላም የነቻይና
የነሕንድ የሌሎችም የጣኦት ማምለኪያዎች በዲያብሎስ ለረጂም ዘመን በምድር ላይ ተኮልኩለው የሰውን ልጅ
ለእሳት ለሲኦል የዳረጉ ሁሉ በታላቅ ቁጣ ከምድረ ገጽ ከነተከታዮቻቸው ከነአገልጋቻቸው ይጠረጋሉ።
ዛሬ እንደምናየው የዓለም መንግሥታት ሕብረት፤ የአውሮፓ ሕብረት፤ የአፍሪካ ሕብረት የኤሺያ ትብብር
የላቲን ሕብረት የአረብ ሊግ የመሳሰሉት ሁሉ ከምድረ ገጽ ይጠፋሉ። መሰብሰብም መወሰንም መነጋገርም
አይቻልም እስትንፋስ አይሰጠም። የማያቋርጥ እሳት ይፈሳልና! ልጠግነው ላክመው ልሽሽ ላምልጥ እከሌን
ልርዳው ማለት ፍፁም አይቻለም። የደበቁትን ማንሳት በዚህ ተደብቄ ጊዜ ላሳልፍ ማለት አይቻልም።
ሁሉም ስፍራ እያሰቃየ የሚፈጅ ሞት ይነግሥበታል። ምድር ያላየችው ሰውም ያላየው በታሪኩም ያልዘገበው
ያልተነገረው ቁጣ ይወርዳል። በዚህ ወቅት እነማን ከነሰላማቸው ይቆማሉ እነማን ይንቀሳቀሳሉ? አዎን
የተመረጡት የእግዚአብሔር ሕዝቦች በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት እውቅና ያገኙ ግለሰቦች አገሮች
ብቻ መንቀሳቀስ ይችላሉ። እጃቸውን ለምነው ጮኸው የሰጡ እንደ ሁኔታው እየታየ ልዑል በፈቀደው መሰረት
በሰላም ይኖራሉ። ከቁጣው የተረፉት መልሰው በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ሥር እንደ ሕግጋተ
ሥላሴ ሕግ መሰረት ይተከላሉ።
39
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ተከላም ነቀላም በጥፋቱ ውስጥ ይካሄዳል። በመላው ዓለም በየትኛውም ገጽ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ
መንግሥት ተዋቅሮ ፀንቶ እስከሚተከል ድረስ ዓለም ባልቋረጠ የእሳት ጠረጋ ውስጥ ትቆያለች። ለጥፋት
ሰዎች ሺዎችን ዘመናት ምድርን ያጠፉ የዲያብሎስ አገልጋዮች በሙሉ ተጠርገው ትቢያ ይሆናሉ። የኢትዮጵያ
ትንሳኤ የለም ሲሉ የነበሩ እየሞቱ ኢትዮጵያ በአስፈሪነት በታላቅ ክብር ምድርንና የጥጋበኞችን ዓለም በአምላኳ
እየጠራረገች እየቀበረች በታላቅ ግርማ ስትነሳ ዓይናቸው ያያል። እያዩ እየሰሙ ነው ወደሞታቸው የሚሄዱት።
ለእግዚአብሔር ሕዝብ ለኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ አማኝ ሲሰፍሩ የነበሩትን መከራ በብዙ መቶ እጥፍ
እየተሰፈረላቸው የእግዚአብሔርን ሕዝብ ክብር በሞታቸው ውስጥ ሆነው እያዩ ወደ መቃብራቸው ይወርዳሉ።
ከፊትህ የሚፈፀመው ይህ የዘረዘርኩልህ ክንዋኔ አሁን የሚከናወን ነው። ረጅም ጊዜ አለ እያልክ እንድታላግጥ
የሚያስችል ነገርና ጊዜም የለም። መልእክቱ እንደወጣ በውሳኔውና በትእዛዙ እንደሚገለጠው ወቅት ጀምሮ
እርምጃው ይከናወናል።
አንዳንዶች በእርግጥም እርምጃው ሲጀምራቸው ሲጠርጋቸው ወይም እሳቱ እነሱን ለመብላት ሲገሰግስ
የሚደነግጡና ለካ እውነት ነው እንዴ ወዴት እናምልጥ የሚሉ እንደሚበዙ እርግጥ ነው። ምንም ዋጋ የለውም።
አስቀድሞ ነበር መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ ይላሉ አባቶቻችን ስትመከር ስትገሰፅ
በአባታዊ ቅጣት ስትቀጣ መመለስ ለማን ገደደ። ያኔ የታመንክበት ጥበብህ ያደራጀሃቸው ዲያብሎስ ያስጨበጠህ
ድንቅ በሆኑ ሕንፃዎች ውስጥ የኮለኮልካቸው ማምለኪያዎችህ ጣኦቶችህ አስጥሉኝ በላቸው። ልክ ፈርኦን
በእግዚአብሔር ቁጣ ሲመታ የሚያመልከውን ሶካር የሚባል ጣኦቱን ታቅፎ ነበር አድነኝ ያለው። አንተም
ጆሮሕን የደፈንክ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት ለ15 ዓመታት በአጠገብህ ሲፈሱ መች ሰማሃቸው።
በየፌስ ቡኩ በቴሌግራሙ በዩቲዩቡ ጧት ማታ ተጥደህ የምትውል ትውልድ፤ በቢሊዮኖች የምትቆጠረው
መልእክታቶቹ ሁሉ በፊትህ አልነበሩም እንዴ? ስቀህና ንቀህ እያፌዝክ አልተውካቸውም? በታላላቅ ቋንቋዎች
በሙሉ ተፅፈው በድምፅም ተዘጋጅተው ደርሰውሃል። ለምነውሃል ያለመታከት ጮኸዋል ስለዚህ ዛሬ በፍርድ
ስትያዝ ማን ያስጥልሃል ማንም አያስጥልህም የተጣላኸው ከሥላሴ ነውና።
በዚህ ታላቅ ቁጣ ሱሪ ለባሽ ሴቶች የተጠላ ተግባር እየፈፀማችሁ ነውና አትድኑም ትጠረጋላችሁ።
እስካሁን ምድርን እየቀጡ ያሉ ቅጣቶች ሁሉ በመልእክት ሦስት እንደተገለፀው የመጀመሪያ ደረጃ ቅጣቶች
ናቸው። አሁን ደግሞ የሁለተኛው እርምጃ ጅማሮ ምልክት የሆኑ በታሪክ ያልተመዘገቡ የምትሏቸው አውሎ
ንፈስ ጎርፍ የመሬት መንሸራተት የትራንስፖርት አደጋ የዘር ፍጅት የሃይማኖት ጦርነት የድንበር ጦርነት
የሲቭል ጦርነት የሕዝብ አለመገዛት እነዚህ ሁሉ በመጀመሪያ ደረጃ ቅጣት ውስጥ የታዘዙ ነበሩ። ዛሬ ኮሮና
ኢቦላ እያልክ የምትጠራቸው በሽታዎች በተለይም ኮሮና እያልክ የምትጠራቸው በሽታ በእኛ አጠራር መቅሰፍት
ምን ያህል እንዳናወጠህ አይተሃል እያየህም ነው። ይህም ከመጀመሪያው እርምጃ የዘለለ አይደለም።
ከዚህ መልእክት መለቀቅ በኋላ የሚመጣው ሁሉንም ዓይነት መቅሰፍት ጠረጋ በሙላት የሚከናወንበት
ነው። ጉልበቱም በምድርም በሰማይም ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ይሆናል። በሰባት ጊዜ ሰባት እጥፍ
49 እጥፍ /መጠን/ የሆነና ከዚያም የሚልቅ ጥፋት ታያለህ። በመላው ዓለም ኮረና መጣ ብለህ ቤት ዘግተህ
እጅህን በሳኒታይዘር ታጥበህ ከሰው ተለይተህ ለመከላከል ስጥር ትታያለህ ይህ ቀላል ነው። ምን ያህል ጎዳህ?
ታውቀዋለህ። ይኸው እንደምናየው ወደፈጣሪህ ደንግጠህ ከመመለስ ይልቅ ክትባት አደረስኩልህ እያልክ ሰው
ወደፈጣሪው ከመመለስ ይልቅ አሁንም አንተን እንደ አዳኝ እንዲያይህ እያደረግህ ትገኛለህ። ሰው እንዳይፀፀት
ወደፈጣሪውም እንዳይመለስ ትግል ገጥመሃል። እንደ ለመድከው እንደቀደመው ሥራህ ዛሬም እኔኑ አምልክ
እኔ መፍትሄ አምጭህ ነኝ እያልክ ነው። ስለዚህ ልክ እንደፈርኦን ትእቢትህን አንግሰሃልና ሞት መላውን
ግብፅ ከድኖ እንደጠረጋቸው ሁሉ፤ በብዙ መቅሰፍቶች ሁሉ ፊት ልቡን ያደነደነው ፈርኦን፤ ሞት በሱም ቤት
በመላው ግብፅ ምድር በሁሉም ባለሟሎች ዘንድ ሲነግሥ ያኔ ወዴት ይግባ? ያሁሉ ትእቢትስ ያሁሉ ንቀትስ

40
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ትችትስ ፌዝስ ወዴት ሄዱ? እባክህ ሂድልኝ የፈለግኸውን ወስደህ ሂድ ብሎ አጅሬ ትእቢተኛው ፈርኦን በሙሴ
እግር ስር ወደቀ። አሁንም የሚሆነው ይኸው ነው። ታያታለህ።
በየትኛውም የዓለም አገሮች ባለ የሰው ዘር በሙሉ በሁሉም ቤት ሞት ይነግሳል ይቆርጣል ይፈልጣል
ማንም ከልካይ የለውም። በቤትህ ሰቆቃ ነው ብትወጣ የሚብስ ነው ወዴት ትሄዳለህ ይህ ነው የሚሆነው።
ልብ በል እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦች የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች በምንታመንበት የአብርሃሙ ሥላሴ
በምንታመንባት ድንግል በእሳት ታጥረን ያለጭንቀት ያለሃሳብ ፈጣሪያችንን እያመሰገንን የነፃነት በዓላችንን
እናከብራለን። በደስታ እንዘምራለን። እኛ ጋ ለመለመን እንኳ በቤትህም በደጁም በሁሉም ስፍራ የነገሰውን ሞት
/የሞት ባሕር/ እንዴት ትሻገራለህ። እግዚአብሔር የወደዳቸው የታደጋቸው ያከበራቸው የትንሳኤው ሙሽሮች
ሲፈነጥዙ ታያለህ ግን ወደእነሱ መድረስ አትችልም። በመሃል አይምሬው ሞት በሁለመናህ ነግሷልና! የሚሆነው
ይህ ነው ምን ይበጅህ አላጋጩ የዛሬው ትውልድ! ብርህ አያድን፤ ሕንፃህ ዋሻህ ግንብህ ዘበኛህ ጠመንጃህ
ታንክህ ጀትህ መርከብህ እኒህ ሁሉ አቧራ ይሆናሉ። ማን ያድንሃል?
የሚሆነውን ሁሉ እየነገርኩህ ነው። ጊዜው ተፈፅሟልና! ጉደኛው ትውልድ ዛሬ ይህ መልእክት እየተዘጋጀ
ቀድመን በተለያዩ መግለጫዎቻችን እንድሁም ትምህርቶቻችን ሳንታክት አልመከርንህም? አልነገርንህም? እኛ
ለልጆቻችን ለአድማጮቻችን የተዘጋጁ ምክር ስናስተላልፍ አንተ ትእቢተኛው አባትህ ዲያብሎስን የቀደመውን
እባብ ዘንዶውን ሃሰተኛው ነብይን ተማምነህ በኛ እያፌዝክ ከመሪ እከተመሪ ከሃይማኖት መሪ እስከ ምእመን
ሁልህም አላላገጥክም? እኛም እንዲሁ ሞት ሲከድንህ ነፍስህን አውጥቶ ለመውሰድ ሲያስጨንቅህ እያየን
የሥራህ ውጤት ነውና ከመገረም በላይ፤ ስለ እግዚአብሔር ቅን ፍርድ ከመደመም በቀር ምንም እንደማንረዳህ
እወቅ። እነዚህ እንግዲህ ዛሬ ከፊትህ የመጡ ሳይውሉ ሳያድሩ የሚፈፀሙ መሆናቸውን እናረጋግጥልሃለን።
ፅናቱን ይስጥህ!
በምድር የሚቀሩ ምንና ምን ናቸው! አንተ ሂያጁ ይጠቅሙኛል ለዘር ማንዘሬም ይተላለፋሉ ብለህ ያሰብከው
ይሆኑኛል ለዘለዓለም ይረዱኛል ብለህ ያደራጀሀቸው ለሰው ሕይወት የሚጠቅሙ መንፈሳዊ ሕይወትን የማይጎዱ
በትንሳኤው ዘመን ለበጎ አገልግሎት ይጠቅማሉ የተባሉ ሁሉ ትተሃቸው ስለምትሄድ ለቀሪው የትንሳኤው ዘመን
ሰው ምድሪቱንም የደከምክበትንም ሁሉ ይወርሳሉ።

41
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ንጉሥ – ነገሥት ቴዎድሮስ ማነው? ስለምን ዓላማ በእግዚአብሔር ታሰበ? የት ነው


ያለው? ምንስ ይፈፅማል? የት ነው የሚነግሰው? የትኛውን ግዛት ይገዛል? ይህ እውነት
በማን ተገለፀ? አባቶችስ ስለዚህ ንጉስ ምን አሉ?

በፍካሬ ኢየሱስ፣ በመፅሐፈ ፊቅጦር፣ በድርሳነ ዑራኤል፣ በሳቤላ ትንቢት፣ በመፅሐፈ ሽኖዳ፣ በሌሎችም
ስለ ንጉሠ – ነገሥት ቴዎድሮስ ተገልፆአል። በእግዚአብሔር ቃል እስከዛሬ ብዙዎች ባላስተዋሉት እንዲሁ
ተገልፆአል።
ዛሬ በዩ ቲዩቡ፣ በፌስ ቡኩ፣ በሌሎችም ማሕበራዊ ገጾች በተለያየ መልኩ የሚያነሱት እጅግ በዝተዋል።
በድፍረትም እንዲህ የሚባል ንጉሥ የለም ብለው የሚቃወሙ በአብዛኛው ከምንፍቅና ጋር የተጋቡ ይናገራሉ።
ለሁሉም በመጀመሪያ የልዑል ኃያለ ቃል በትንቢተ ኢሳይያስ ምእራፍ 49 የተጠቀሰውን ቃል ተመልክተን
የተቀረውን ሃሳብ እንመጣበታለን።
የልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ ይላል –––

ደሴቶች ሆይ ስሙኝ፣ እናንተም በሩቅ ያላችሁ አሕዛብ አድምጡ፣ እግዚአብሔር


ከማሕፀን ጠርቶኛል። ከእናቴም ሆድ ጀምሮ ስሜን አንስቷል። አፌንም እንደተሳለ
ሰይፍ አድርጓል። በእጁ ጥላ ሰውሮኛል። እንደ ተሳለ ፍላፃም አድርጎኛል። በሰገባውም
ውስጥ ሸሽጎኛል። እርሱም ––––– እስራኤል ሆይ አንተ ባሪያዬ ነህ በአንተም
እከብራለሁ አለኝ። እኔ ግን በከንቱ ደከምሁ ምንም ጥቅም ለሌለውና ለከንቱ ጉልበቴን
ፈጀሁ፣ ፍርዴ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋዬም በአምላኬ ዘንድ ነው አልሁ።
አሁንም በእግዚአብሔር ዓይን ከብሬአለሁና አምላኬም ጉልበት ሆኖኛልና ያዕቆብን
ወደ እርሱ እንድመልስ እሥራኡልንም ወደ እርሱ እንድሰበስብ ባሪያ እሆነው ዘንድ
ከማሕፀን ጀምሮ የሰራኝ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እርሱም ––––– የያዕቆብን
ነገዶች እንድታስነሳ ከእስራኤልም የዳኑትን እንድትመልስ ባሪያዬ ትሆን ዘንድ እጅግ
ቀላል ነገር ነውና እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን
አድርጌ ሰጥቼሃለሁ ይላል። የእስራኤል ታዳጊ ቅዱሱም እግዚአብሔር ሰዎች ለሚንቁት
ሕዝብም ለሚጠላው ለገዢዎች ባሪያ እንዲህ ይላል። ስለ ታማኙ ስለ እግዚአብሔር
ስለመረጠህም ስለ እስራኤል ቅዱስ ነገሥታት አይተው ይነሳሉ። መሳፍንትም አይተው
ይሰግዳሉ።
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ––– በተወደደ ጊዜ ሰምቼሃለሁ፣ በመድኃኒትም ቀን
እረድቼሃለሁ፣ እጠብቅህማለሁ፤ ምድርንም ታቀና ዘንድ ውድማ የሆኑትንም እርስቶች
ታወርስ ዘንድ የተጋዙትንም ውጡ በጨለማም የተቀመጡትን ተገለጡ ትል ዘንድ ቃል
ኪዳን አድርጌ ለሕዝቡ ሰጥቼሃለሁ። በመንገድም ላይ ይሰማራሉ ማሰማሪያቸውንም
በወና ኮረብታ ሁሉ ላይ ይሆናል። የሚራራላቸውም ይመራቸዋልና፤ በውኃም
ምንጮች በኩል ይወስዳቸዋልና አይራቡም አይጠሙም፣ ትኩሳት ወይም ፀሐይ
አይጎዳቸውም። ተራሮቼንም ሁሉ መንገድ አደርጋለሁ ጎዳኖቼም ከፍ ከፍ ይላሉ።
እነሆ እነዚህ ከሩቅ፣ እነሆም እነዚህ ከሰሜንና ከምእራብ፣ እነዚህም ከሲንም አገር

42
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ይመጣሉ። እግዚአብሔር ሕዝቡን አጽናንቷልና ለችግረኞችም እራርቷልና ሰማያት


ሆይ ዘምሩ፣ ምድር ሆይ ደስ ይበልሽ ተራሮችም ሆይ እልል በሉ።
ፅዮን ግን –––– እግዚአብሔር ትቶኛል ጌታም እረስቶኛል አለች። በውኑ ሴት
ከማሕፀንዋ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕፃንዋን ትረሳ ዘንድ ትችላለችን?
አዎን እርስዋ ትረሳ ይሆናል እኔ ግን አልረሳሽም። እነሆ እኔ በእጄ መጻፍ ቀርጬሻለሁ
ቅጥሮችሽም ሁልጊዜ በፊቴ አሉ። ልጆችሽ ይፈጥናሉ ያፈረሱሽና ያደሙሽ ከአንቺ
ዘንድ ይወጣሉ። ዓይንሽን አንስተሸ በዙሪያሽ ተመልከቺ፣ እነዚህ ሁሉ ተሰብስበው
ወደ አንቺ ይመጣሉ። እኔ ሕያው ነኝና እነዚህን ሁሉ እንደጌጥ ትለብሻቸዋለሽ፣ እንደ
ሙሽራም ትጎናፀፊያቸዋለሽ ይላል እግዚአብሔር። ባድማሽና ውድማሽ ወናም የሆነው
ምድርሽ ከሚኖሩብሽ የተነሳ ዛሬ ጠባብ ትሆናለችና፣ የዋጡሽም ይርቃሉና፣ የወላድ
መካን ከሆንሽ በኋላ የተወለዱልሽ ልጆችሽ በጆሮሽ ––– ሥፍራ ጠብቦኛልና እቀመጥ
ዘንድ ቦታ እስፊልኝ ይላሉ። አንቺም በልብሽ –––– የወላድ መካን ሆኛለሁና እኔም
ብቻዬን ተሰድጃለሁና ተቅበዝብዤአለሁምና እነዚህን ማን ወለደልኝ? እነዚህንስ ማን
አሳደጋቸው? እነሆ ብቻዬን ቀርቼ ነበር እነዚህስ ወዴት ነበሩ? ትያለሽ።
ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል –––– እነሆ እጄን ወደ አህዛብ አነሳለሁ ዓላማዬንም
ወደ ወገኖቼ አቆማለሁ። ወንዶች ልጆችሽንም በብብታቸው ያመጧቸዋል፣ ሴቶች
ልጆችሽንም በጫንቃቸው ላይ ይሸከሟቸዋል። ነገሥታትም አሳዳጊ አባቶችሽ
ይሆናሉ። እቴጌዎቻቸውም ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ። ግምባራቸውንም ወደ ምድር
ዝቅ አድርገው ይሰግዱልሻል፣ የእግርሽንም ትቢያ ይልሳሉ፣ እኔም እግዚአብሔር
እንደሆንሁ ታውቂአለሽ፣ እኔን በመተማመን የሚጠባበቁ አያፍሩም።
በውኑ ብዝበዛ ከኃያል እጅ ይወስዳልን? ወይስ የጨከኙ ምርኮኞች ያመልጣሉን?
እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል –––– በኃያላን የተማረኩ ይወሰዳሉ የጨካኞችም
ብዝበዛ ያመልጣል። ከአንቺ ጋር የሚጣሉትን እጣላቸዋለሁ ልጆችሽንም አድናለሁ ፡
አስጨናቂዎችሽንም ሥጋቸውን አስበላቸዋለሁ። እንደ ጣፋጭም ወይን ጠጅ ደማቸውን
ጠጥተው ይሰክራሉ፡ ሥጋ ለባሹም ሁሉ እኔ እግዚአብሔር መድኃኒትሽና ታዳጊሽ፣
የያዕቆብ ኃያል እንደ ሆንሁ ያውቃል።
ትንቢተ ኢሳይያስ ምእራፍ 49 በሙሉ ከላይ እንደ ተመለከታችሁት ስለኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት
ቴዎድሮስ፤ ስለኢትዮጵያ ትንሳኤ፤ እንዲሁም ስለ እስራኤል ዘሥጋ መታሰብ ቁልጭ አድርጎ ይነግረናል።
ቃሉንም በዝርዝር እንተነትነዋለን። በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ያለውን የቅኖች አለመረዳት ችግር ይወገዳል። የጥፋታቸው
የክህደታቸው ማምታቻ እውነትን አጥፍቶ ማወዛገቢያ ያደረጉ የቀደመው እባብ የዘንዶው የሃሰተኛው ነብይ ደቀ
መዛሙርቶችና በቢሊዮኖች የተቆጠረው መላው የዓለም ሕዝብ ሁሉ በክህደትህ ታፍራለህ። ትላንት አዋልድ
መጽሐፍ አልከተልም የኢትዮጵያ ትንሳኤ የለም ትል የነበርክ፤ ነብዩ ዳንኤል እንዳለው –– በመጨረሻው ዘመን
እውቀት ይበዛል ሰው በጥበብ የእግዚአብሔርን እውነት ለመመርመር ይነሳል ዳንኤል ሆይ አንተ ግን መፅሐፉን
አትም ዝጋ እንደአለው ልዑል ስለዚህ እናንተ ሥልጣንም ብርሃናዊ ዓይንም የላችሁም። የእግዚአብሔርን
እውነት ልትገለፁ የሚያስችል እምነትም ስለሌላችሁ ይኸው እኛ የሥላሴ ባሮች መርዷችሁን እንንገራችሁ።
አንዱ የማምታቻ ቋንቋችሁ እኛ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ አናምንም ትሉ ነበር። የሃሰተኛው ነብይ ፍጡሮች
ናችሁና እናምነዋለን ካላችሁት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በግልፅና በማያሻማ መንገድ የተቀመጠውን የትንቢት
ቃል አስቀመጥኩላችሁ። የሌሎች የካዳችሁትን የአባቶች ትንቢት እንዳለ ሆኖ፤ ወደአንድምታው ገብተን እንየው
––

43
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ደሴቶች ሆይ ስሙኝ፣ እናንተም በሩቅ ያላችሁ አሕዛብ አድምጡ! ––– /ቃሉ/


ደሴቶች ማለት አገሮች መንግሥታት እንደማለት ነው በምድር ሁሉ ተበትነህ ያለህ መላው የአዳም ዘር
ይመለከትሃልና ስማ ነው የሚልህ ልዑል እግዚአብሔር።

እግዚአብሔር ከማሕፀን ጠርቶኛል ፡ ከእናቴም ሆድ ጀምሮ ስሜን አንስቷል፣ አፌንም


እንደተሳለ ሰይፍ አድርጓል ፡ ––– /ቃሉ/
አንድምታው –––– እግዚአብሔር እያንዳንዱን ፍጥረት ለክብሩ ለወደደው ምግባርና የሕይወት ምልልስ
ፈጥሮ እንደ እጣ ፈንታው በየስፍራው አድርጎታል። ሰውንም ቢያልቀውም እሱም እንዲሁ እንደተወሰነለት
የልዑል እጣ ፈንታ በምድር እንዲመላለስ አድርጎታል። እኛም ስንፈጠር ለፈቃዱ እንድንገዛ በምድሪቱም
እንድንኖር ሲፈቅድልን በወደድነው እንድንሄድ ጨለማና ብርሃን ክፉውንና ደጉን በፊታችን አስቀምጦልናል።
መርጠን ወደ ወደድነው እጃችንን እንድንሰድ ፈቃዱ ሆኗል። እንዲህም ሲሆን በጎ ስንመርጥ ወደበጎ የሚመራንን
መልካሙን መልአክ ያዝልናል። መልካሙን መርጠናልና እግዚአብሔር በወደደው መንገድ እንድንማር ያደርጋል።
እግዚአብሔርን ምርጫው አድርጎ የሚመላለስ ሰው የሚማረው በእግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር ለአሰበው
ለፈቀደው ዓላማ ከሰዎች መሃል ለይቶ ለአገልግሎቱ ሰውን ይመርጣል። ንጉሥ ዳዊት እግዚአብሔር መርጦት
ላሰበው አላማ እንዲሆን ካደረገው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳቡ ምን እንደሆነ የተረዳው ንጉሥ ዳዊት
ይህንን አለ –––– ገና በናቴ ማሕፀን ሳለሁ፣ አጥንትና ደም ሆኜ ሳልዋደድ በአንተ ዘንድ ታወቅሁ አለ።
እግዚአብሔር ከማሕፀን የጠራው የለየው ላሰበው ዓላማ ነው። በመሆኑም የእግዚአብሔር ምርጫ ገና ሳይፈጠር
ነው ያሰበው። ሁሉም ነቢያቶች ሐዋሪያት ገና በእናታቸው ማሕፀን ሳይዋደዱ በፊት ላቀደው ተግባር አስቀድሞ
ተመርጠዋል። የመረጣቸውን እንደተሳለ ሰይፍ አድርጓቸዋል። በተናገሩት ሁሉ ዓለምን አንቀጥቅጠዋል፤
ምክንያቱም በእነሱ እቃነት በእነሱ አንደበት ሥራውን የሚሠራው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና!

በእጁ ጥላ ሰውሮኛል፣ እንደ ተሳለ ፍላፃም አድርጎኛል፣ በሰገባውም ውስጥ ሸሽጎኛል።


––– /ቃሉ/
ዛሬ የእግዚአብሔርን የፍርድ ቃል፣ ተግሳፁን በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት አማካኝነት እየሰማችሁ
ነው። ነገር ግን በአካል እኔን የልዑል ባሪያ አላያችሁም። ለምን ሰዓቱ እስኪሞላ ድረስ ሸሽጎኛልና ከ15
ዓመታት በላይ እንደሸሸገኝ ነውና! በዚህ የእግዚአብሔርን አሰራር ልታውቁ ይገባል።

እርሱም –––– እስራኤል ሆይ፣ አንተ ባሪያዬ ነህ፣ በአንተም እከብራለሁ አለኝ፣ እኔ
ግን ––– በከንቱ ደከምሁ ምንም ጥቅም ለሌለውና ለከንቱ ጉልበቴን ፈጀሁ፣ ፍርዴ
ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋዬም በአምላኬ ዘንድ ነው አልሁ። /ቃሉ/
እግዚአብሔር ለመረጠው በግልፅ ይናገራል አንተ ባሪያዬ ነህ ይላል። በዚህ በመረጠው እቃ ስለሚገለገልበት
በጎ ፈቃዱ ሁሉ በዚህ በመረጠው ሰው ላይ አድሮ ስለሚከናወን ልዑል ይከብርበታል። ወገኖቼ ይህን ቃል
ስገልፀው በእውነት ያስገርመኛል፤ በልቤ የነበረውን በሃሰቤም ሳመላልሰው የነበረው ቃል ቢኖር ይህ ቃል
ነው ፡––– በከንቱ ደከምሁ፣ ምንም ጥቅም ለሌለውና ለከንቱ ጉልበቴን ፈጀሁ፣ ፍርዴ ግን በእግዚአብሔር
ዘንድ ዋጋዬም በአምላኬ ዘንድ ነው አልሁ። ይህን እውነት ስገልፀው እኔው ቃሉን ያሰፈርኩት ያህል ይሰማኝ
ነበር። በዚህ መልእክት ውስጥ ስለራሴ የሕይወት ምልልስና የመከራ ዓይነት መግለፅ ስለማልፈልግ የፈለገ
ልዑልን ይጠይቅ፣ ካልቸኮላችሁ ሁሉም ስለሚገለፅ ወደብርሃን የማይወጣ ስለሌለ ትሰሙታላችሁ። በግሌ ግን
የመጣሁበትን ጎዳና ማሰብ አልፈልግም እሱን ሳስብ መቋቋም የሚያቅተኝ እውክታ ውስጥ ስለምገባ ብዘለው
መልካም ነው። አሁንም ዋጋዬም ፍርዴም በእግዚአብሔር እጅ ነው። ሁላችሁም እንደምትረዱት በመላው
ዓለም ነግሶ ዓለምን እንዳሻው በሚነዳው የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ጋር የተደረገው ውጊያ
እጅግ ብዙ ከልጅነቴ ጀምሮ ነበር። ብዙም ነፍስን ሳላውቅ እኔን ለማጥፋት ዲያብሎስ ያላደረገው ጥረት

44
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

አልነበረም። ፈቅጄ መከራን አልጠጣሁም። ሌላውን ሁሉ ልተወውና መልእክታቱ ወደ እናንተ አደርስ ዘንድ
ከታዘዝኩበት ጀምሮ በእያንዳንዱ መልእክት መውጣት ወቅት እንዲሁ ወደ እናንተ የሚደርስ አልነበረም። ዛሬ
የማልገልፀው ከባድ ዋጋ ተከፍሎበታል። ዲያብሎስ የማጥቂያ ስልቱ እጅግ ብዙ ነው። በእግዚአብሔር ኃይል
ብናልፈውም ሳንጎዳበት ቀርተን አይደለም። እንደግሌም እንደቤተሰብም ውድ ዋጋ ከፍየበታለሁ። እድሜዬን
ሰፍሬበታለሁ። ብዙዎች ክብርን ማእረግን ሀብትና ክብረትን መወደስን ይሻሉ። ይህ በሥጋው ዓለም ለሚኖሩ
እጅግ የሚመኙት ነው።
እውነትን ለተረዱ እግዚአብሔርን ለሚወዱ ግን ይህ ትርጉም የለውም። ፍላጎታቸው ሁሉ የሚያርፈው
የዚችን ምድር ክፉ ውጣ ውረድ ቶሎ አልፎላቸው ወደ አባቶቻቸው ወደ ገነት መሄድን ነው። እኔም በሕይወት
ዘመኔ ካየሁት ፍዳና መከራ አንፃር በዚች ምድር ላይ መኖር እጅግ ያስመረረኝ ነው። ብቆይ እንኳን ለፈጠረኝ
አምላክ ፍቃድ ለክብሩ ለከበረው ስሙ እስከጠቀምኩና በአገልግሎቴ እስካስደሰትኩት ድረስ ብቻ ነው። ዛሬ
እኔ የሥላሴ ባሪያ እምኖረው ላገለግለው ልታዘዘው ፈቃዱን ልፈፅም እናቴንም ፍቃዷን ልፈፅም ብቻ ነው።
ከዚህ ውጪ ምንም የምሻው የሚያረካኝ የለም። ሩጫዬን ጨርሼ በአካሄዴ የወደደኝን አምላኬን አስመልኬ
ፈቃዱ ተፈፅሞ ከብሮ ዘወትር ተመሥግኖ ካየሁ ለኔ ካሳዬ እሱ ብቻ ነው። ከዚች ምድር ላይ እምሻው ለሥጋዬ
ብዬ እማስበው የለም። እርግጥ ለምትሰሙት እጅግ ሊያስደነግጣችሁ ይችላል። ዓለምን ሁሉ በአንድ ውዳቂ
ምናምንቴ በሆንኩት ከሁሉ እጅግ ባነስኩት በቸርነቱ በምሕረቱ ሸፍኖኝ ነውሬን ኃጢያቴን ከድኖ ውድ ዋጋ
ከፍሎልኝ እንደገናም እጅግ ከአእምሮ በላይ በሆነ ሥፍራ ላይ ሊያስቀምጠኝ መወሰኑን ከተነገረኝ ጀምሮ ለረጅም
ዓመታት ይህ ከኔ እንዲያልፍ እኔም ለዚህ እንደማልመጥን በመግለፅ ከፈጣሪዬ ከመድኃኔዓለም ጋር በብርቱ
ተከራክሬአለሁ። አልሆነም እናቴንም ድንግልን ጠይቄአለሁ አልሆነም። ይሁንና ሁሉንም ጊዜ ስለሚገልጠው
ብዙ ባልል መልካም ነው። ወደ ቀጣዩ ቃል እንሂድ።

አሁንም በእግዚአብሔር ዓይን ከብሬአለሁና አምላኬም ጉልበት ሆኖኛልና! ያዕቆብን


ወደ እርሱ እንድመልስ እስራኤልንም ወደ እርሱ እንድሰበስብ ባሪያ እሆነው ዘንድ፣
ከማህፀን ጀምሮ የሰራኝ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል –– እርሱም የያዕቆብን ነገዶች፤
እንድታስነሳ፣ ከእስራኤልም የዳኑትን እንድትመልስ ባሪያዬ ትሆን ዘንድ እጅግ ቀላል
ነገር ነውና! እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌ
ሰጥቼሃለሁ ይላል። የእስራኤል ታዳጊ ቅዱሱም እግዚአብሔር፣ /ቃሉ/
እንደምትመለከቱት የልዑል ቃል ዛሬ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ማነው እያላችሁ ለምትታወኩ! እንዲሁም
የለም ሃሰት ነው ለምትሉ እውነቱ ይህ ነው። እርሱም ለምን እንደተጠራ ማን እንደጠራው ማን እንደሾመው
እወቁ! ለሱ የከበደው እንደገደል የታየው ለእግዚአብሔር እጅግ ቀላል እንደሆነ ጌታችን መድኃኔዓለም
ሲያበረታው ያው እየሰማችሁት ነው።
ቃሉ ይቀጥላል ––––– ለገዢዎች ባሪያ እንዲህ ይላል ––––– ስለታማኙ ስለ እስራኤል ቅዱስ
ነገሥታት አይተው ይነሳሉ መሳፍንትም አይተው ይሰግዳሉ። ––– መላው ዓለም ለገዢዎች ባሪያ የሆንክ ሁሉ
ስለእግዚአብሔር ቅን ፍርድ እግዚአብሔር ስለ ሚገልጠው እውነት አንተ የምትንቀጠቀጥላቸው የምትገዛለቸው
መንግሥታት መሳፍንቶች ሁሉ ለንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ወደው ሳይሆን በግዳቸው እየተጠረጉ እየተፈጩ
ይንበረከካሉ ይሰግዳሉ። ቃሉ የሚነግርህ ይህንን እውነት ነው።

እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ––– በተወደደ ጊዜ ሰምቼአለሁ በመድኃኒትም ቀን


ረድቼአለሁ፣ እጠብቅህማለሁ፣ ምድርንም ታቀና ዘንድ፣ ውድማ የሆንትንም ርስቶች
ታወርስ ዘንድ፣ የተጋዙትንም –––– ውጡ በጨለማም የተቀመጡትን –– ተገለጡ
ትል ዘንድ ቃል ኪዳን አድርጌ ለሕዝቡ ሰጥቼሃለሁ። ––– /ቃሉ/

45
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንግዲህ እግዚአብሔር ባሪያውን እንደጠበቀው በብርቱ መከራም ውስጥ እንዳዳነው እንደሰማው እንደሚጠብቀው
አረጋግጦለታል። ልብ በሉ ምድርንም ታቀና ዘንድ ማለት የፈረሰውን የጠፋውን እንደ ቀደመው ይመልስ ዘንድ
ባሪያውን አዟል። የተጋዙትንም ውጡ በጨለማም የተቀመጡትን ተገለጡ ትል ዘንድ ––– ይላል ቃሉ ––
ንጉሡ የተሰጠው ቀዳሚ ተግባር የታሠሩትን የተሳደዱትን በዲያብሎስ ዓይን የተዘመተባቸውን ስለቀናችው
የተዋህዶ እምነታቸው የተሰቃዩትን ሁሉ ይገለጡና ወደ ብርሃን ይመጡ ዘንድ ያደርጋል። እግዚአብሔር
ቀጥሎም እንዲህ ይላል –– ቃል ኪዳን አድርጌ ለሕዝቡ ሰጥቼሃለሁ። እንግዲህ ለህዝቡ እግዚአብሔር በገባው
ቃል መሰረት ንጉሱን ለሕዝቦቹ ሰጥቷል።

በመንገድም ላይ ይሰማራሉ ማሰማርያቸውም በወና ኮረብታ ሁሉ ላይ ይሆናል።


የሚራራላቸውም ይመራቸዋልና በውኃም ምንጮች በኩል ይነዳቸዋልና አይራቡም
አይጠሙም ትኩሳት ወይም ፀሐይ አይጎዳቸውም። ተራሮቼንም ሁሉ መንገድ
አደርጋለሁ። /ቃሉ/
እግዚአብሔር በመጪው መልካም ዘመን በትንሳኤው ዘመን በባሮቹ በኩል ሕዝቦቹን እንዴት እንደሚመራ
መልሶም እንደሚተክል አብሯቸውም እንደሚሆን መሰናክሉንም እንደሚያስወግድ ይነግረናል። ከተራራ የገዘፈ
የለም እሱን ሁሉ አስወግዶ መንገድ እንደሚያደርግ ልዑል ቃሉን ሰጥቷል። የዛሬ ተራሮች መንግሥታት
ኃይላት ሃሰተኛ እምነቶች ሕዝብን ያጠፉ ሁሉ ይወገዳሉ እውነቱ ይህ ነው።

ጎዳኖቼም ከፍ ከፍ ይላሉ። /ቃሉ/


እግዚአብሔር የሚወስዳቸው ቅን ፍርዶቹ ሁሉ በዚያ ዘመን ለትንሳኤው ለታጩት ሁሉ መንገዶች ሁሉ ሰላም
በረከት ፍቅር ደስታ የሚሆንበት እግዚአብሔርም በፍፁም ልብ በፍፁም ሃሳብ በፍፁም ነፍስ የሚመለክበት
የከበረ ከፍ ከፍ ያለም የብርሃን ዘመን ይሆናል።

እነሆ እነዚህ ከሩቅ እነሆም እነዚህ ከሰሜንና ከምእራብ፣ እነዚህም ከሲንም አገር
ይመጣሉ። እግዚአብሔር ሕዝቡን አፅናንቷልና ለችግረኞችም ራርቷልና ሰማያት ሆይ
ዘምሩ፣ ምድርም ሆይ ደስ ይበልሽ፣ ተራሮችም ሆይ እልል በሉ። /ቃሉ/
በመጪው ዘመን በትንሳኤው ዘመን ከሁሉም የምድር ገጽታ ወደ ኢትዮጵያ ለመፅናናት ለመዳን ይመጣሉ።
እግዚአብሔር ከታላቁ ቁጣ የተረፈውን የተቸገረውን ሁሉ ያፅናናል። ለሕዝቡ እራርቷልና እግዚአብሔርን ስለቅን
ፍርዱ ስለሕዝቡ እርህራሄ ሰማያትም ምድርም መንግሥታትም እልል ይላሉ። የሚሆነው ይህ ነው።

ፅዮን ግን –––– እግዚአብሔር ትቶኛል፣ ጌታም እረስቶኛል፣ አለች። በውኑ ሴት


ከማሕፀንዋ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕፃንዋን ትረሳ ዘንድ ትችላለችን?
አዎን እርስዋ ትረሳ ይሆናል። እኔ ግን አልረሳሽም። እነሆ እኔ በእጄ መፃፍ
ቀርጬሻለሁ፣ ቅጥሮችሽንም ሁልጊዜ በፊቴ አሉ። ልጆችሽ ይፈጥናሉ፣ ያፈረሱሽና
ያወደሙሽ ከአንቺ ዘንድ ይወጣሉ። /ቃሉ/
ይህ ቃል ሰለእስራኤል ዘሥጋ የሚናገር ነው። በመልእክት ሦስት እንደተገለፀው እስራኤል በመጪው የትንሳኤ
ዘመን በኢትዮጵያ ብርሃናዊ መንግሥት ሥር የራሷ የውስጥ አስተዳደር መብት ተሠጥቷት ከቁጣው የተረፉትን
ሕዝቦቿን ይዛ እንደ ታናሽ የኢትዮጵያ እህት ሆና በመንፈሳዊ አስተዳደር በኢትዮጵያ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ
ብርሃናዊ አመራር እየተመራች ተፅናንታ ትኖራለች። እግዚአብሔር ስለ ቀደሙት ነቢያት ሐዋሪያት በፊቱ
ታምነው ስላሳለፉት ሕይወት እግዚአብሔር እንደ ሕዝቦቹ አምጦ የወለዳቸው የወደዳቸው ነበሩ። ምንም እንኳን
ቢክዱትም ወደ ሕዝቦቹ ቢመጣም ባይቀበሉትና በታላቅ ክህደት ለሞት አሳልፈው ቢሰጡትም፣ እስከአሁኑ
ድረስም ከጥፋታቸው ባይመለሱም እሱ ግን እነሆ በመጨረሻው ሰዓት በፍርድ ዓለምን ሲጎበኝ ለቅሬቶቹም

46
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ሕዝቦች እራራ አሰባቸውም። የቀደመውን የነአብርሃምን የይስሐቅን የያዕቆብን የመሰረቱ አባቶችን የነሙሴን
የነኤልያስን የነዳዊትን የፍቅር ዘመን አሰበ። እስራኤልም በዚህ ነው እድሉ የገጠማት።

ዓይንሽን አንስተሽ በዙሪያሽ ተመልከቺ፣ እነዚህ ሁሉ ተሰብስበው ወደአንቺ


ይመጣሉ። እኔ ሕያው ነኝና እነዚህን ሁሉ እንደ ጌጥ ትለብሻቸዋለሽ እንደ ሙሽራም
ትጎናፀፊአቸዋለሽ ይላል እግዚአብሔር። ባድማሽና ውድማሽ ወናም የሆነው ምድርሽ
ከሚኖሩብሽ የተነሳ ዛሬ ጠባብ ትሆናለችና የዋጡሽም ይርቃሉና የወላድ መካን
ከሆንሽ በኋላ የተወለዱልሽ ልጆችሽ በጆሮሽ –––– ሥፍራ ጠብቦኛልና እቀመጥ
ዘንድ ቦታ አስፊልኝ ይላሉ። አንችም በልብሽ የወላድ መካን ሆኛለሁና እኔም ብቻዬን
ተሰድጃለሁና ተቅበዝብዤአለሁምና እነዚህን ማን ወለደልኝ እነዚህንስ ማን አሳደጋቸው
እነሆ ብቻዬን ቀርቼ ነበር፣ እነዚህስ ወዴት ነበሩ ትያለሽ። /ቃሉ/
እግዚአብሔር የታመነ አምላክ ነው በቃሉ የፀና ነው። ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር ፊት ስትታሰብ በሁለመናዋ
ነው የምትጠገነው ያጣችውን ተስፋ የቆረጠችበትን የተሰደዱባትን ሁሉን እግዚአብሔር ይመልሳል። ባድማው
ሁሉ ይለመልማል ኢትዮጵያ የሁሉ ምደር መፅናኛ ትሆናለችና ስፍራ እስከሚጠብ የትንሳኤው ሙሽሮች
የሚደምቁባት ትሆናለች፤፤ ግዛቷም እጅግ ይሰፋል። መካን ሆንኩ ሁሉን አጣሁ እንደ ጠላት ተቆጠርኩ
ልጆቼም ጠፉ ብላ ተስፋ የቆረጠችው ኢትዮጵያ ከመላው ዓለም ሁሉ የሰው ዘር እንደ አዲስ በተዋህዶ ተወልዶ
ለክብሯ ጌጥ ይሆናል።

ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ––––– እነሆ እጄን ወደ አሕዛብ አነሳለሁ


ዓላማዬንም ወደ ወገኖቼ አቆማለሁ፣ ወንዶች ልጆችሽንም በብብታቸው ያመጧቸዋል።
ሴቶች ልጆችሽንም በጫንቃቸው ላይ ይሸከሟቸዋል። ነገስታትም አሳዳጊ አባቶችሽ
ይሆናሉ። እቴጌዎቻቸውም ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ። ግምባራቸውንም ወደ ምድር ዝቅ
አድርገው ይሰግዱልሻል። የእግርሽንም ትቢያ ይልሳሉ እኔም እግዚአብሔር እንደሆንሁ
ታውቂአለሽ። /ቃሉ/
እግዚአብሔር እጄን ወደ አሕዛብ አነሳለለሁ አላማዬንም ወደ ወገኖቼ አቆማለሁ ሲል በመልካሙ ዘመን
በመጠገኛው ዘመን አህዛብን ወደ አላማው ወደ እውነት መገለጫው ወደ እሚከብርበት ምድር ወደ ኢትዮጵያ
የሚጠራበት እንደሚሆን ያመለክታል።

እኔንም በመተማመን የሚጠባበቁ አያፍሩም!! /ቃሉ/


እኔንም በመተማመን የሚጠባበቁ አያፍሩም!! በውኑ ወገኖቼ የዚህን ቃል አንድምታ በሚገባ ታስተውላላችሁን
አዎን ሕሊናው ያልተከደነ ማስተዋሉ ያልተጋረደ ይረዳል በዬ አምናለሁ። ኢትዮጵያ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት
ምድር በእግዚአብሔር የተወደደች እምነትን ያፀኑ ወገኖች ምድር ፈጣሪዋን አዳኟን ታዳጊዋን መድኃኔዓለምን
እናቷን ድንግልን ለረጅም ዘመናት እንደተገባላት ቃል ኪዳን ታምና ተስፋ አደርጋ ስትጠባበቅ ኖራለች።
አባቶች እናቶች ይህንን እውነት ለልጆቻቸው አውርሰው በተስፋ ተሳልመው ወደ እረፍታቸው ሄደዋል።
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የድንግል ልጆች ታላቁ ነብይ ኢሳይያስ የኖረው ከጌታችን መወለድ በፊት ነው። ስለ
ኢትዮጵያ ታላቅነት ወደፊት ስለሚጠብቃት የፀና ታላቅ ተስፋ ከልዑል ተገልጦለት እሱም የአምላኩን ቃል
ኪዳን በትንቢት መፅሐፉ አስፍሮልን አልፏል። ሰዓቱ ሲደርስ እነሆ እግዚአብሔር ቃሉንና ሚስጥሩን እየገለጠ
መጣ! ኢትዮጵያ የቃል ኪዳን ምድር እንደሆነች ይህንን እውነት ያመኑና የተረዱ እጅግ ጥቂት ወገኖች
ተስፋ ሳይቆርጡ ሲጠባበቁ ኖረዋል ። እግዚአብሔር አንድ ቀን እውን ያደርገዋል ብለው ታምነው ቆመዋል።
እኛም የመልእክቱ አድራሾች እንዲሁ በተስፋ ፀንተን ስንጠብቅ ቆይተናል። እግዚአብሔር ኃያል የታመነ ጌታ
በመተማመን የሚጠብቁትን አያሳፍርም። እውነቱ ይህ ነው። ዛሬም የምነግርህ ተስፋህ እነሆ እውን ይሆናል
ደርሰህበታል። የካዱትም የናቁትም ያቃለሉትም ተስፋን የማይሰጥ የማይፈርድ የማይታደግ አድርገው የቆጠሩት

47
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ሁሉ እነሆ ያዩታል በቅን ፍርዱም እየጠረገ ይሸኛቸዋል። በቃሉ አላግጠዋል፣ እውነትን በውሸት ለውጠዋል።
የሃሰት እምነትን ታምነዋል። በእውነት የቆሙትን አጥፍተዋል። ለዲያብሎስ ለዘንዶው ለሃሰተኛው ነብይ
ትምህርት ተንበርክከዋል።
በዮሐንስ ራእይ 20 የተገለጠውን እውነት ክደዋል። የእውነት ሰዎችን የተዋህዶ አርበኞችን ተፈታትነዋል
አሳደዋል። የኢትዮጵያን የፀና ተስፋ የገለጥነውን ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታትን በድፍረት ተቃውመዋል።
ዛሬስ የትንቢተ ኢሳይያስ ምእራፍ 49 /በሙሉ/ ከላይ እንደገለፅነው ይህን ደግሞ እንዴት ታስተባብሉ ይሆን
መቼም ደፋሮች ናችሁና የሃሰተኛው ዲያብሎስ ልጆች ናችሁና ውሸት ልብሳችሁ ስለሆነ የድፍረት ኃጢአትን
ለመሥራት ትሞክሩ ይሆናል ግን በአንድ ነገር እርግጥ እንደሆነ ላረጋግጥላችሁ፣ ––– ጊዜ የለም አብቅቷል
መሽቶባችኋል። አሁን ከፊታችሁ ሁሉም ነገር ተጭኖ መጥቷል። መግቢያ የለም። መደበቂያ በፍፁም የለም
አበቃ!!

በውኑ ብዝበዛ ከኃያል እጅ ይወስዳልን? ወይስ የጨካኙ ምርኮኞች ያመልጣሉን?


እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል ––––– በኃያላን የተማረኩ ይወሰዳሉ፣ የጨካኖችም
ብዝበዛ ያመልጣል፣ ካንቺ ጋር የሚጣሉትን እጣላቸዋለሁ፣ ልጆችሽንም አድናለሁ።
አስጨናቂዎችሽንም ሥጋቸውን አስበላቸዋለሁ፤ እንደ ጣፋጭም ወይን –ጠጅ
ደማቸውን ጠጥተው ይሰክራሉ። ሥጋ ለባሹም ሁሉ እኔ እግዚአብሔር መድኃኒትሽና
ታዳጊሽ የያዕቆብ ኃያል እንደ ሆንሁ ያውቃል። /ቃሉ /
ዛሬ ዓለም በትእቢቷ የተሞላች ናት አትሰማም። እንኳን እኛን ድሃዎችን የተናቅነውን የተሻሉትን እንኳን
አይሰሙም። ምክንያቱም የዘመኑ ኃያላን ናቸው። ከአሜሪካ እጅ ወይም ከራሽያ አሊያም ከእንግሊዝ እጅ አንድ
ድሃ አገር የሚሻውን በጉልበት ይወስዳልን? አይታሰብም አይሞከረም። ሁሉም የሦስተኛ ዓለም ሀገር ከአውሮፓ
ተዋግቼ ከሁሉም የምድሪቱ ኃያላን ተዋግቼ ምርኮ እወስዳለሁ የሚል የአፍሪካ አገር በሕሊናችን ልናስበው
አንችልም። ነገር ግን ይህ እውነት ሁሉም የዘመኑ ሰው የሚያምንበት እንደሆነ ግልጽ ነው። ተገረሙ እንጂ ይህ
እውነት ይገለበጣል። እንዴት ይሆናል? አዎን ይሆናል አይሆንም የምትሉት በእግዚአብሔር ይቻላልና። ልብ
በሉ በኃያላን የተማረኩ ይወሰዳሉ። ከኃያላኑ እጅ በግድ ነፃ ይወጣሉ። ጨካኞች የዚህ ዘመን ኃያሎች ያጎሯቸው
ያመልጣሉ /ነፃ ይወጣሉ/። እውነቱ ይህ ነው።
ወገኖቼ ልብ በሉ ከፊታችሁ የደረሰው እውነት በተግባር ሲፈፀም ታያላችሁ። የእግዚአብሔር ቃል ተረት
የሆነባችሁ የዘመኑ አለቆች ኃያላን ፈራጆች የምድሩ ነገሥታቶች ሁሉ ከነትምክህታችሁ በእሳት ትጠረጋላችሁ።
የዓለማችን ኃያላን ወዳችሁ አይደለም በምድር የምታሳቃዩአቸውን የምትለቁት በቁማችሁ እሳት ሲበላችሁ ሞትን
ስትለምኑ ያኔ በራሳችሁ ለምናችሁ ይደረግ የተባላችሁትን ሁሉ ከሚፈለገው በላይ ሁሉ ታደርጋላችሁ።
ከተመሰገነችው ከተወደደችው በፊታችሁ ሁሉ ትከብር ዘንድ በኃያሉ እግዚአብሔር በታሰበችው ኢትዮጵያ
ፊት ትቢያ ትሆናላችሁ፤ ምናምንቴና የተዋረዳችሁ ትሆናላችሁ። የተመካችሁበት ሁሉ የትምክህታችሁ ምንጭ
የሆነው ሁሉ በቅፅበት ከፊታችሁ እንደ ጭስ ይተናል። የተጣላችሁት ከኢትዮጵያ ነውና! ይህ ድርጊት ደግሞ
ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት ነው።
መከራችሁ ምን ያህል እንደሚከብድ የሚገልፀው የፍርድ ቃል ሥጋችሁን ያስበላችኋል ደማችሁን እንደ
ወይን ጠጅ ያስጠጣችኋል። በዚህም ሥጋ ለባሽ ሁሉ የሚያየው ይሆናል። የኢትዮጵያ ታዳጊ መድኃኒት ኃያሉ
እግዚአብሔር እንደሆነ ያኔ ታውቃላችሁ።
ወገኖቼ ንጉሠ – ነገሥት ቴዎድሮስ የኢትዮጵያ ትንሳኤ ምን እንደሚመስል እንዴትስ እንደሚከናወን በሚገባ
በትንቢተ ኢሳይያስ ተረጋግጦ ተገልጦላችኋል። ከፊታችሁ ደግሞ ሊከናወን በደጃችሁ ቆሟል። ከዚህ መልእክት
መውጣት በኋላ ሁሉም ድርጊት ይከናወን ዘንድ ከልዑል ዘንድ ታዟል።

48
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ዛሬ ባለንበት በዚህ ሰዓት ምድር በውሸት ወሬ ጧትም ማታም በምትናጥበት ወቅት፤ ወጣቱም ሽማግሌውም
የቴሌቪዥን ሱሰኛ በሆነበት ዘመን የማህበራዊ ድረ ገጾች እስረኛና በእነሱ እስትንፋስ የሚኖር ያህል በተቆጠረበት
ዘመን፤ ዩ – ቲዩቡን፣ ፌስ – ቡኩን፣ ሌሎችንም ገጾች የሸፈነው አንዱ የወቅቱ ጉዳይ ስለ ኢትዮጵያ ትንሳኤ
የሚፃፈው ሲሆን፣ ከዚሁ ጋር ተጣምሮ የሚነሳው ደግሞ የንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ መነሳትና የመምጣት ጉዳይ
ዋናው ሆኗል። አንዳንዱ ወቅቱንና ያለውን የዓለም ነውጥ በመመልከት ከኢትዮጵያ ትንሳኤ ጋር መያያዙን
የሚቃወም ሲሆን፣ አንዳንዱም ስለትንቢት ቃሉ በመፃረር የዘመኑን ገዢዎች ለማስደሰትና ፍርፋሪ ለመልቀም
ይለፋሉ። አንዳንዱ ደግሞ የጣፈጠ ተደማጭ እንግዳ ነገር በማቅረቡ ብዙ አንባቢ በማግኘት ከዩ ቲዩብ ሳንቲም
ለማግኘት የሚደክም ነው። የሚበዙት ደግሞ የዲያብሎስ ታዛዦች በመሆናቸው መፈፀሚያቸው መድረሱን
ከጌታቸው ስለሰሙ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብተው ሕዝቡን እንዳይሰማ ለማድረግና ከእውነቱ መንገድ
ለማሳት የሚጥሩ ናቸው። ንጉሱ በዚህ ነው የሚሉ እንዳሉ ሁሉ የተለያዩ የትንቢት መፃሕፍትን በመጥቀስ
ስለትውልድ ሀረጉ ስለሚመጣበት አቅጣጫ ስለተወለደበት ሁሉ የሚናገሩ ገጾች እጅግ በዝተዋል። ብዙዎቹ
የሚያነሱት እንግሊዝ አገር ስለሚገኘው ፍካሬ ኢየሱስ ሲሆን እንዳሻቸው እየተረጎሙ እንዲህ ይላል እንዲያ
ይላል እያሉ ሕዝቡን ሁሉ ሲያሳክሩት ይታያል። የዘመኑ ሰው ወሬ ቀለቡ ነውና ውሸቱንም ከጥቂት እውነት
የተቀላቀለውንም ማሳሳቻውንም ሁሉንም ሳይመርጥ ያዳምጣል። በዚህም ግራ ይጋባል።
የዘመናችን የዲያብሎስ አለቆችና መንግሥታት እንዲሁም የዲያብሎስ የሃሰተኛው ነብይ ድርሰት የሆኑ
እምነቶች ከሃዲዎች ይህን እውነት በማዛባት በማግነን የተሳሳተ ትርጉም በመስጠት በጥርጥርም መንፈስ
በሙሙላት እንደተረት እንዲታይ ብዙ ጥረት ያደርጋሉ። በብርቱ የሰጋው ዓለማችን፤ የሚነዳትም ዲያብሎስ
የቀደመው እባብ፣ ዘንዶው፣ ሃሰተኛው ነብይ ይህንን እውነት ጠንቅቀው ያውቃሉ። እውነትነቱንም በሚገባ
የተረዱ ናቸው። ልብ በሉ እግዚአብሔርን የካደ የልዑልን መንግሥት ሊገለብጥ እሱ ፈጣሪ ሊሆን የተመኘ
ይህንንም ህልሙን ለመፈፀም እስከመዋጋት የሄደ ዲያብሎስ በምድር ያቆማቸው አለቆችና ሹሞች ናቸው።
በመሆኑም ዛሬም በውጊያ ላይ ናቸው። በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም። ተሸንፈው ተጠቅልለው ወደ ምድር
ተጥለዋል። ዛሬ ደግሞ የምድር ምሽጋቸውም ሊደረመስ ነው። እግዚአብሔርም በታመኑ ባሮች አገልጋይነት
በምድሪቱም በሙላት ሊከብርባት ሊመሰገንባት ነው። ታዲያ ይህ እውነት ሊውጠው ስለመጣ እነሆ በከባድ
ውጊያ ላይ ተጠምዶ እናያለን። ግድ ነውና ይህ እውነት እውን እንዳይሆን ይመኛሉ። ምክንያቱም የህልውናቸው
ማብቂያ ነውና!። ይህም ብቻ አይደለም የካዱት እየተዋጉ ያሉት እኛንም እነሱንም የፈጠረ አምላክን ነውና!
በታላቅ ድንጋጤ ቢዋጡ አይገርምም። በነሱ ግብአተ መሬት ላይ እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ ይከብራልና!
ይህ እውነት ምድርን በከደነ ጨለማ ላይ ሁሉ ያበራል። የሁሉ ፍጥረት ጌታ በቅን ፍርዱ በምድርም በሰማይም
ሊከብር ሊመሰገን ይገባዋል። ቅን ፈራጅ አምላክ ነውና!
ታዲያ የዚህ ጨለማ ገዢዎች ሕልውና የሚያጠፋ ንጉሠ – ነገሥት ቴዎድሮስ በእግዚአብሔር ኃይል
ተቀብቶና ተሸሞ ሲመጣ እንዴት ይቀበሉታል። ቄጠማ ጎዝጉዘው እንደማይቀበሉት እሱም ጠንቅቆ ያውቃል።
ጨለማና ብርሃን ምን ሕብረት አላቸውና! ንጉሡ የመጣው የፈጠረውን አምላክ ፈቃድ ሊያስፈፅም ሊያስመልክ
በሁሉም ነገር በምድር ስለ እግዚአብሔር ክቡር ስም ስለ ከበረው ቃሉ ዘብ ሊቆም የመጣ ነው። ስለዚህ
ሊያጠፉት ቢመኙ ከእነሱ ዐይን ሲታይ ግድ የሚላቸው ነው። ብቻ ትግላቸው በቀላል የተገነባ አይደለም።
ዲያብሎስ ጥበቡን አልተነጠቀምና ለጥፋቱ ብዙ ዘዴ እንደሚፈበርክ ግልፅ ነው። ስለዚህ በምታዩት ትርምስ
አትደነቁ። የእግዚአብሔር እውነት ከተገለፀ ሁሉም የጨለማ ኃይል ሥፍራና መቆሚያ የለውምና ጠላት በብርቱ
ታውኳል። ወገኖቼ በጨለማ ያለን ሰው ያሻቸውን ቢያደርጉት ቢጎትቱት ምን ያውቃል። ምንም አያውቅም
ያሻቻውን ያደርጉታል። እውነቱ ይህ ነው። ዛሬ እንደምታዩት ዓለምን ዲያብሎስ ፍፁም አጨልሟት በኃጢአት
ባሕር ውስጥ እንድትዋጥ አድርጓታል።

49
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ፍጅት ጦርነት እርስ በእርስ በዘር መፋጀት በድንበር በእምነት መተላለቅ፣ እኔ ነኝ የበላይ፣ የለም እኔ ነኝ
በሚል እየተላለቀ ይገኛል። ሁሉም ሰው እንደሚያውቀው ዓለም በሁለት ጎራ ተለይቶ የሚቋላው ዲያብሎስ
በአደራጀለት እቅዱ መሰረት ነው። የፈቃዱ ተገዢዎች ስለሆኑ የታዘዙትን ያደርጋሉ። የሁሉም መንግሥት
ምኞት እኔ የተሻለ ሰላምን ብልጽግናን ደስታን ፈንጠዝያን ዲሞክራሲን /የሰይጣን ፍትህን/ አመጣለሁ የሚል
ነው። ይህንንም ለማድረግ ያንተ ዘዴ የተሻለ ነው፣ አይ የዚያኛው የተሻለ ነው በሚል ዘዬ ዲያብሎስ
ስላደራጃቸው፣ ሺዎችን ዘመናት እየተቋሉ እዚህ ደርሰዋል። የዲያብሎስ ሕልምና ኑሮ የሚደምቀው በዚህ
የጨለማ ኑሮ እየተፋጨ እየተቋላ የሚዳክር፣ መጨበጫ የሌለው ዓለም በመፍጠር ስለሆነ ይህ ሕልሙም
ተሳክቶለት ቢሊዮኖችን እየነዳ ይገኛል።
ሰው ፈጣሪውን ካወቀ እንደፈቃዱ ከሄደ ትእዛዙን ከወደደና ካከበረ፣ ወደ ብርሃን ዓለም ገባ ማለት ነው።
መዝኖና አስተውሎ የሚጓዝ እግዚአብሔርና ፍቃዱ የተረዳ በሱ ሲኖር ምን እንደሚያተርፍ ስለሚያውቅ፣
በእውነትም ተደሳች ለመጪውም ዘመን ወደ ብርሃን ተሸጋሪ እንደሚሆን፣ እንደሚፅናናም ዲያብሎስ ስለሚያውቅ
ይህንንም እውነት ሰው እንዳያውቅና ወደ እግዚአብሔር ጉያ ተሰብስቦ፣ በምድርም በረከት ለወዲያኛውም ዓለም
የመንግሥቱ ወራሽ እንዳይሆን ታላቅ ተጋድሎ አድርጓል እያደረገም ነው።
አመፁ በዝቶ ––– ዛሬ የሰው ዘር እንደቅጠል እየረገፈ፣ ዲያብሎስ ባደራጀውና ባቀደው መልክ የሰው ደም
እንደ ጎርፍ እየፈሰሰ ነው። መቋረጫ የለውም። እዚህ አገራችን ስንት ንፁህ ደም ፈሰሰ ስንት ድሀ አለቀ፤ ስንት
ቤት ፈረሰ ስንቱ በረሃብ በጦርነት ረገፈ፤ ስንቱ በዘሩ ተፈጨ፣ ስንቱ ስለተዋህዶ እምነቱ ተጨፈጨፈ። ዛሬ
በግልፅ፣ ባልተሸፈነ መልኩ እያያችሁት አይደለም እንዴ?
ዲያብሎስ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ያነገሰው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዲያብሎስን ፍላጎት
ለማርካት፣ የእውነትን መንገድ ሊያጠፋ ምን እየሠራ እንዳለ የምታዩት አይደለም ወይ! ዓይኑን በጨው ያጠበ
አፍረት የማይሰማው ውሸትን እንደልብስ ያጠለቀ፣ማጭበርበርን ማታለልን እንደስልትና እውቀት አእምሮው
የተቀበለ፤ አፉ ቅቤ ልቡ ጩቤ እንደሚባለው ዓይነት መሪ ለኛ መጥፋት የሚተጋው ዲያብሎስ ተክሎብን
ስንት የኢትዮጵያ ድሃ ስለ ዘሩ ስለ ተዋህዶ እምነቱ ተፈጨ፤ ስንት ቤተ ክርስቲያናችን ፈረሰ ተቃጠለ፣ ስንቱ
ተሳደደ፣ ስንቱ የአረብ መጫወቻ ሆነ፣ አገራችንን ለማፍረስ ስንት ጥረት ተደረገ። የጥፋት ሁሉ ማእከል
ኢትዮጵያ ለምን ሆነች፣ ግልፅና የማያሻማ ነው። የቀደመው እባብ፣ ዘንዶው፣ ሃሰተኛው ነብይ ተጠዋሪዎች
ሕልማቸውንና ሩጫቸውን የሚያጦፉት እግዚአብሔር ኃይልን ያስታጠቃቸው የሥላሴ ባሮች የሚነሱት ከዚች
ከድንግል ርስት ኢትዮጵያ ስለሆነ ነው። የጠላታችን ሞትም ከነዝግንትሉ መጠረጉም የታወጀው ከዚች እጅግ
አብዝቶ ከሚጠላት ኢትዮጵያ ነው።
ኢትዮጵያ የተወደደች የተመረጠች በዘመን ጉዞዋ አምላኳን ያከበረች፣ ያንንም አምልኮ ከልቡ የሚፈፅም
ሕዝብ በውስጧ እስከዛሬ ይዛ የዘለቀች ናት። ይህ እውነት ይህ ብርሃን ዲያብሎስን ያለ እረፍት የሞት መርዶውን
ተሸክሞ እንዲዞር አድርጎታል።
»» ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መመሥገኛና መገለጫ ምድር ናት። ይህን ስንል ምን ማለታችን ነው?
አዎን አምላካችን ሥላሴ የፍጥረት ሁሉ አስገኝ ፈጣሪ፤ የምድሩም የሰማዩም የሚታየውም የማይታየውም
ረቂቅ ፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ በፈቃዱ ሁሉን ያፀና እኛንም ወዶንና ፈቅዶ በአምሳሉ የፈጠረን ጌታ በሰማይ
ሁሉም ፍጥረት ያላማቋረጥ ያመሰግነዋል ሌትም ቀንም፤ ምድርም ልታመሰግነው ይገባታል። በላይዋ
ያለ ፍጥረት ሁሉ ሲያመሰግን ሰው ብቻ አምፆ ቆሟል። ይኸውም በሰማይ ክብሩንና ማእረጉን በገዛ
ትእቢቱ የጣለው ዲያብሎስ ወደ ምድር ስለተጣለ ሰው ደግሞ ይሕን በፈጣሪው ያመፀውን ክፉ ጠላት
ከመካድና ከማውገዝ ይልቅ ፈጣሪውን ክዶ የሱ ተገዥ ሆኖ በመገኘቱና ቢመከርም ቢገሰፅም አልሰማ
ስላለ ብርቱ ፍርድ ሊጠርገው እነሆ በደጁ ደርሷል። ይህ ከተፈፀመ በኋላ የተዋህዶ እምነታችን አሸንፋ

50
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

እንደ ፀሐይ ስለምታበራ እግዚአብሔር የአብርሃሙ ሥላሴ ድንግል እናታችን ቅዱሳን አባቶቻችን
እናቶቻችን ሰማዕታት ቅዱሳን ሁሉ የሚነግሱባት ዓለም የግድ ትፈጠራለች። መሪዋም እግዚአብሔር
መንፈስ ቅዱስ ይሆናል። እንደማያቋርጥ ጅረት የልዑል ስም ሌትም ቀንም ይመሰገናል ይከብራል።
የሥላሴ ክብርም ምድርን ይከድናል። አገልጋይ ባሮቹ ሁሉ የወደዳቸው ከታላቁ መከራ ያወጣቸው
ልጆቹ ነጭን ልብስ ለብሰው አብረውት ይከብራሉ። ይህ እውን ይሆናል። ለዚህም ነው ከላይ ያለውን
ቃል አስቀድመን የምናነሳው በሁሉም ነገራችን ላይ የምናፀናው።
»» ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም ናት። /አዎን ቅድስተ ቅዱሳን እናታችን በሰማይም ክብሯ የላቀ
የመድኃኒተ ዓለም እናት ንግሥት በምድርም ንግስት የተወደደችው ኢትዮጵያም ልዑል አክብሮ
የሰጣት የሷም የክብር መገለጫ ናት። ዓለም ሁሉ ያለሷ ምልጃና እናትነት የማይድን መሆኑ በግልፅ
የተመሰከረበት መሆኑን የሚያረጋግጥ። ሥላሴ በረከትን ምሕረትን ጤናና እድሜን ሁሉ የሰጠው በሷ
የፍቅር ምልጃ መሆኑን ያወቀ ትውልድ ስለከበረ ይህ አሸናፊ ትውልድ ደግሞ የተዋህዶ አርበኛና
ሲጠራትም እምዬ እናቴ የሚላት መሆኑ ክብሯን በሚገባ ጠንቅቆ ስላወቀ መሆኑን ከላይ ያለው ቃል
ያረጋግጥልናል /
»» ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ናት። አዎን ናት። ዓለም ንቀህ ነበር ተዋህዶን ንቀህና አቃልለህ ነበር
የታመነችቱን እምነት ሐዋርያት ነቢያት በደማቸው በአጥንታቸው የተፈጩላትን እምነት ልዑል
የወደዳትን ያከበራትን እምነት ተዋህዶን ጠልተህ ተዋግተህ ነበር ጠላታችን ዲያብሎስ ሁሉን ምድር
ብትቆጣጠርም ኢትዮጵያን የተዋህዶን መሰረት ብትፈጫትም ልትጠፋልህ አልሆነም። በመሆኑም
ባነደድከው የእሳት ደጅ በፅናት ቆማ አምላኳን ተማምና ይህን ሁሉ ዘመን በመዝለቋ አሸናፊ ሆናለች።
ዓለም ሁሉ በምርኮ ተሰጥቷታል። በፅናቷ ለዓለም ብርሃን እንድትሆን ልዑል ከመረጣት በእኔ መረዳት
እንኳን 15 ዓመታት ተቆጥሯል። ስለዚህ ይህ እውነት ይታወቅ ዘንድ ዘወትር በሁሉም ድርጊታችን
እንገልፀዋለን።
»» ኢትዮጵያ የዓለም ገዢ ናት፣ ––– አዎን ናት። ድል ያደረገችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን ናት። ወገኖቼ እግዚአብሔር ወደዚህ ምድር ፈጥሮ እንድንኖርባት እንድንመላለስባት
በእንግድነት እንድንኖርባት ለሱ ለፈጠረን ባስቀመጠልን ስርዓትና የአምልኮት ሕግ ታምና ዘመናትን
በሞት ጥላ ውስጥ ፀንታ በመገኘቷ በልዑል ዘንድ አስወደዳት አስከበራት አሸለማት። በመሆኑም ዓለም
በምርኮ ተሰጣት። ኢትዮጵያን ማእከሏ አድርጋ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥትነት ዓለምን
ሁሉ ትገዛለች።
»» ከላይ የተገለፀው እውነት በዲያብሎስና በሚነዳቸው ጭፍሮቹ መቃብር ላይ እውን ይሆናል። ይህ
በመሆኑ ይህን እውነት በሚገባ ስላወቀና ስላረጋገጠ ዲያብሎስ ከነምንዝሩ ታውኳል። ይህ ደግሞ ግድ
ነው። መፈፀም አለበት የእግዚአብሔር እውነት ነውና ይፈፀማል። ዲያብሎስና ምንዝሩ ወደመቃብሩ
የእግዚአብሔር ሕዝብም በድል አድራጊነት ወደ ትንሳኤው ዓለም መሸጋገር ግድ ይሆናል ማለት ነው።
ይህን ለማስቀረት ዲያብሎስ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ አለኝ የሚለውን በክህደት የገነባውን
እምነቶች /መናፍቅ ካቶሊክ እስላም ምሁር የኤሺያው የጣኦት እምነት ወዘተ ––/ በሙሉ የማስተባበል
እንዳይሰማ ማድረግ ሌሎችንም ይጠቅሙኛል ያለውን ዘዴ በሙሉ ያንቀሳቅሳል። በዚች ምድራችን ለዲያብሎስ
ፍላጎት ለሆዱ ነፍሱን ያልሸጠ የለምና የሚበዛው በዚህ አባዜ የተለከፈ ነው። የሚታዘዘው ስለሞላለት ነው።
ይህን ደሞ የግድ ያደርጋል።
በመሆኑም እግዚአብሔር በምድራችን ላይ ፈቃዱንና ትእዛዙን የሚያስፈፅሙ ባሮቹን መርጦ ወድዶ አክብሮ
እንዲሁም ቀብቶና ሹሞ ጨርሷል። ለዚህ አላማው የተመረጡት ምርጥ እቃዎቹም ይህንን አውቀውና ተረድተው

51
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በየባእታቸው ተቀምጠዋል። የሚሠጣቸውንም ትእዛዝ በመጠባበቅ ላይ ናቸው ሁላችሁም እንደምታውቁት


መድኃኔዓለም አባታችን ሐዋሪያትን ራሳቸውን ችለው እንዲሰማሩ ለማድረግ በወሰነና እሱም ወደአባቱ
ቀኝ ሊያርግ ሰዓቱ በደረሰ ጊዜ ለሐዋርያት እነዲህ ነበር ያላቸው ከእየሩሳሌም ኃይልን እስክትቀበሉ ድረስ
እንዳትንቀሳቀሱ ኃይልን ትለብሳላችሁ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አፅናኙን አስተማሪውን እልክላችኋለሁ ነበር
ያለው። ዛሬም የተቀቡት የተሸሙት የእግዚአብሔር ቀዳማይ አገልጋዮች ይህንኑ ትእዛዝ አክብረው እየተጠባበቁ
እንዳለ ሁልህም የሰው ልጅ እወቅ!
በንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ የሚመሩ 39 ንጉሶች እንዳሉ ልታውቁ ይገባል። ከነሱም በመቀጠል እንዲሁ
በተዋረድ በልዑልና በመሥፍንነት ማእረግ የሚያገለግሉ እንደተሾሙ ልታውቁ ይገባል።
የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩ በቀዳማይ አባት የሚመሩ ከ300 ያላነሱ አባቶች
ተመርጠው የከበረውን የክህነት ሥልጣን ጨብጠው እንደ ሐዋሪያት ኃይልን እስከሚቀበሉ ድረስ በባእታቸው
ተዘጋጅተው ተቀምጠዋል።
ዓለም እወቅ ምትሻገረው ወገኔ ተረዳ አስተውል እውነቱ እንግዲህ ይህን ይመስላል። በተለይ ተሻጋሪ የሆንከው
የእግዚአብሔር ቤተሰብ ለትንሳኤው ዘመን ትደርስ ዘንድ የተወደድህ ወገኔ እድለኛ ነህና በትእግስት ተጠባበቅ!
በጥርጥር ተሞልተህ የዲያብሎስን የማያቋርጥ ቱልቱላ እያዳመጥክ አትሳሳት የተሰጠህንም እድል እንዳታመክን።
የፈሰሰ ውኃ አይታፈስምና ተታለህ ወደ ጠላት ጉያ ከገባህ መልሰህ በምንም መልኩ አታገኘውምና ተጠንቀቅ
ብዬ እመክርሃለሁ።
ወደትንሳኤው ከተሸጋገርክ በኋላ ምድር ትፈወሳለች። የተሰው ሰማዕታት አባቶቻችን እናቶቻችን ስለ ፈሰሰው
ደማቸው ስለደረሰባቸው ሰቆቃ ሁሉ በልጆቻቸው ይነግሳሉ። በአፀደ ገነት ሆነው ሁሉንም ክንዋኔ ያያሉ።
ስለታመነው ስለቅን ፈራጁ አምላካቸው ስለ ቅን ፍርዱ ይደሰታሉ ያመሰግኑታልም።
ልዑልም ይከብራል ይነግሳል። ባሮቹ አገልጋዮቹ ይለብሱታል። በልባቸው በሃሳባቸው በነፍሳቸው ይላበሱታል።
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ልባቸው መቅደሰ ሥላሴ ነውና ይመራቸዋል። ወደ እውነት ሁሉ መንገድ
እንዲጓደዱ ያደርጋል። በምድር ላይ በአንዲቷም ቀዳዳ ዲያብሎሳዊ ተግባር አይኖርም። ተነቅሎ ይጣላል።
በየትኛውም የምድር ገጽታ እግዚአብሔር ያለማቋረጥ ይመሰገናል። ይመለካል። ይሰገድለታል። ይከብርበታል።
ድንግል ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ቅዱሳን ሰማዕታት የከበሩ አባቶች እናቶች ሁሉ ይመሰገናሉ ዘወትር። ወገኖቼ
ይህ እውነት ስለመጣ ዲያብሎስ ወዴት ይግባ! የከፋውን መርዶውን እየሰማ ወዴት ይድረስ!
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በተሰጣችሁ ተስፋ የፀናችሁ ወገኖቼ!
ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ማነው በሚለው ጥያቄ ዙሪያ ብዙ ነገሮች ተነስተዋል። በብዙ ፀሐፍቶች ዘንድ
ታሪኩ እየተዛባ በመፃፍ ላይ ይገኛል። ይህ ደግሞ የሚሆነው ጠላት በሚያንቀሳቅሳቸው እቃዎቹ አማካኝነት
ነው። ተአማኒነትን ለማጥፋት የሰውን ልቡና በጥርጥር መንፈስ ለመሙላት የሚያደርገው ተግባሩ ነው። በዚህ
መልክ በዚህ ዘመን በዚህ ፅሁፍ ተገለፀ ከሚባል በቀር በተጨባጭ እዚህ ነው ያለው ለማለት የቻለ የለም።
አንድ ወንድማችን /ተክለኪዳን/ ካለው በስተቀር።
ብዙዎች በቅንነትም ወይም ከጉጉታቸው የተነሳ አግንነው ይናገራሉ። ከሰውም በላይ የመላእክትን ያህል
የሚያደርጉትም አሉ። ወገኖቼ እነሙሴ እነኤልያስ እነዳዊት ሌሎቹም ሰው ነበሩ በነሱ ሕይወት የነገሰው
እግዚአብሔር ግን በነሱ አድሮ ምን እንደሠራ ሁላችሁም የምታውቁት ነው። አሁንም እግዚአብሔር በመረጣቸው
በወደዳቸውና በሾማቸው ምርጥ እቃዎቹ ላይ አድሮ የፈቃዱን ሥራ ይሰራል ማለት ነው። እግዚአብሔር
በየዘመኑ የታመኑ ባሮችን አስነስቷል። ሐዋሪያት ነቢያት ሰማዕታት ሁሉም መገልገያዎቹ ምርጥ እቃዎቹ

52
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ሆነው አክብረውት ስለእውነት ቆመው አስከብረውት በክብር አልፈዋል። በሰጣቸው መንፈሳዊ ኃይል ጠላትን
ተዋግተዋል ለእኛ ደግሞ የተጋድሎአቸውን አሻራ አትመው አልፈዋል።
ዛሬስ! ይህ ዘመን ምን ይመስላል! አዎን ምድር ከቀደሙት ዘመናት በእጅጉ ተለውጣለች። በስልጣኔዋ
ገስግሳለች ምድር መንደር ሆናለች እውቀት እጅግ በዝቷል። ምድራችን በሕንፃዋ በመንገዷ በመኪናው በመብራቱ
በንግዱ በአውሮፕላኑ በመርከቡ ተሞልታለች። በመገናኛው ረቃለች። በህክምናው እንዲሁ ዘምናለች፤ ምድር
ጠቧት ሕዋውን ታስሳለች። ለዚህ ሁሉ ክንዋኔ የተጠቀመችበት እውቀትና ጥበብን የሚያፈልቀው አእምሮዋ
ቀድሞም ለሰው ዘር የሰጠው እግዚአብሔር ነው። ሥላሴ ሰው ስለሰራው በጎ ነገር ቅር አላላቸውም፤ ነገር
ግን አስገኝ የሆነው ሁሉን የፈጠረ ጌታ ሊመሰገን ሊከብር ሲገባው፣ በፈቃዱ ላፀናው ምድር ይሁን ብሎ
ወዶ ለክብሩ የፈጠረው በአምሳሉ ያነፀው ሰው የወደደው የሰው ልጅ ካደው። ፍጡሩን ዲያብሎስን አነገሰ።
ቢወቅሰው ቢመክረው ቢገስፀው አልሰማ አለ። ጥንት ገና ከመጀመሪያው ሕግን ሲሰጠው አበክሮ ያስጠነቀቀው
ቢኖር እኔ አምላክህን ትተህ ክደህ ሌላ አማልእክት እንዳታቆም እኔ ቀናተኛ አምላክ ነኝ የምባላ እሳት ነኝ
ተጠንቀቅ እንዳትስት ነበር ያለው። ይህንን እንዳይረሳ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር በየዘመኑ የታመኑ የወደዱትን
የሚታዘዙትን ባሮቹን አገልጋዮቹን እያስነሳ ወቅሷል። በንስሓ እንዲመለስ ጠርቷል። ሲብስም ገስፆአል።
እንደምትመለከቱት ሰው ግን አልሰማም።
የሰው ትእቢት ክህደት ይበልጥ ከፋ በእውቀቱ በሃብቱ በቴክኖሎጂ ውጤቱ በዘመነ ቁሳቁሱ፣ ቤቱ፣
ኮምፕዩተሩ፣ መኪናው፣ ለሥጋው የገነባው ምቾቱ፣ በሰማይ የሰቀለው ሳተላይቱ፣ የጦር ጀቱ፣ መርከቡ፣
ጠብመንጃው፣ ታንኩ፣ የአየር መንገዱ፣ አውሮፕላኑ እኒህ ሁሉ ዓለምን መንደር ስላደረጉለት በቃ እግዚአብሔር
የለም አላውቀውም አለ። ምድር ተበላሸች። ለሰው ያልተገባ ተግባር እግዚአብሔር ያወገዘው ድርጊት ሁሉ /
ሶዶማዊነት ምንዝርና ምድርን አለበሰ/ እነዚህ ሁሉ ተደማምረው እግዚአብሔርን የካደው ዲያብሎስ ምኞት
በሰው ልጅ ዘንድ ቦታና ስፍራ ጨበጡ እግዚአብሔር ተረሳ በምትኩ በሰው ልብም ሃሳብም ተግባርም
የጨለማው ገዢ ዲያብሎስ ነገሰ።
እግዚአብሔር ተንቋል ተክዷል ተጠልቷል፤ የለምም ተብሏል። ስሙንም የሚያነሳ የመጥፋት ያህል ሆኑል።
በመላው የሰው ሕይወት ውስጥ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ተወደዋል ተደምጠዋል ተሰግዶላቸዋል
ተመልከዋል። ምልክታቸውም ለሰው ሁሉ እንዲወስድና እንዲያደርገው ሆኗል።
ይህን ሁሉ እየተመለከተ ያለው የአብርሃሙ ሥላሴ የግድ አምላክነቱን ቅናቱን የሚባላ እሳት መሆኑን
ምድርም ሰማይም በፊቱ ብናኝ ኢምንት መሆናቸውን ይታወቅ ዘንድ ግድ ነውና! ይህ ሊረጋገጥ ስለሚገባው
ዛሬ ፍርዱ ወደተግባር ሊለወጥ ሆኗል።
ጌታ ገና ዓለም እዚህ ደረጃ ሳትደርስ አሁን ወደአለችበት ዘመን ሳትቀርብ እንኳን በውኗ በህልሟም ይሆናል
ብላ ባላሰበችበት ሰዓት የሰው ልጅ እጅግ እንደሚያጠፋ እሱንም እንደሚክድ ገልፆ ተናገሮታል። ያለው
አልቀረም የሰው ትእቢት ገንፍሎ ፈሰሰ። አባቶችም ይህ እንደሚሆን ከእግዚአብሔር እንደተነገራቸው ልክ
እውነቱን ሲመሰክሩ ኖረው አልፈዋል። ዛሬም ይኸው በመመስከር ላይ አሉ። የእውነት መንገድ፤ የፅድቅ ጎዳና
እጅግ ጠባብ ናት በዚችው በጠበበችው መንገድ ለመግባት ታገሉ ነበር ልዑል ያለው። ሰፊው መንገድ እጅግ
ሰፊ ነው። እጅግ ብዙ ሕዝብ ይሄድበታል። ያ ደግሞ ወደጨለማ የሚወስድ የዲያብሎስ መንገድ ነው። ታዲያ
ይህ አልሆነም ሆኗል ወገኖቼ!
በመሆኑም ዛሬ ፅዋው በመሙላቱ በጠላት ሰፈር እውክታ ሆኗል። ምድር ታውካለች ሰላም ጠፍቷል። በሽታ
ጦርነት ፍጅት ግጭት ነግሷል። የተፈጥሮ አደጋ አዘወትሮ መምጣት ጀምሯል። ሰው ግን እነዚህ ምልክቶች
ሁሉ አላስደነገጡትም። አብሶት ወደጥፋቱ ገፍቷል።

53
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ለ15 ዓመታት የወቅቱን ሁኔታ በግልፅ በመግለፅ የንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ
መምጣት ኢትዮጵያም ዓለምን በእምነቷ ማሸነፏን በማብሰር፣ ዓለም ከጥፋቱ እንዲመለስ ንስሓ እንዲገባ
በኢትዮጵያ ለሚፀናው ብርሃናዊ የዓለም መንግሥት እጁን ለመስጠት እንዲዘጋጅ፣ ፈጣሪውን ይቅርታ እንዲጠይቅ
ተመክሯል። አልሰማም! በትእቢቱ ገፋ! እንግዲህ ምን ይደረግ ለነገር መጀመሪያም መጨረሻም ስላለው፣ ዛሬ
የመጨረሻው መጀመሪያ መግለፅ ግድ ሆነ።
እስከዛሬ ዲያብሎስ መልካሙን ነገር በማጣመም በተቻለው መጠን የእግዚአብሔርን እውነት መላው የሰው
ልጅ እንዳይቀበለው እንደተረት እንዲቆጥረው /እንዲያየው/ ብርቱ ጥረት አድርጓል። በእርግጥም ተሳክቶለታል።
የሰው ብርቱና ደካማ ጎኑ ሥጋው ነውና ይህንን የሥጋ ፍላጎቱን ለመሙላት የማያደርገው ጥረት የለምና ይህንን
ድክመቱን በመጠቀም ዲያብሎስ ወደ ጨለማው መንገድ ሲነዳውና ከፈጠረው አምላክ ሕግና ስርዓት እንዲወጣ
እንዲክድም ሊያደርገው ችሏል።
በረጅም ዘመን የፕሮፓጋንዳ የውሸት ትርክት የማይጨበጥ ተስፋ የተፋለሰ ታሪክ ደርቶ በሳይንስና በፍልስፍና
የታጀለ ብርዝ ታሪክ እንደእውነት ሲሰብክ በመኖሩ፣ የሚበዛው የአዳም ዘር በእውቀት ጭንብል ተጠቅልሎ
እውነትን ሳያውቃት እስከወዲያኛው ተሰናብቷል።
የጠላት ትግል የማያምን፣ የእግዚአብሔርን እውነት የማይፈልግ፣ በሥጋ ፍላጎቱ የታሰረ፣ አላማ ቢስ
ትውልድ፣ ፈጥሮ መንዳት ነበርና ይህንንም አሳክቷል።
እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥር አልቆ በአምሳሉ አድርጎ ነው። የፈጠረው ሰው የሚያስብ የሚመዝን የሚረዳ
የሚያስረዳ የሚያስተውል የሚገነዘብ አእምሮ ሰጥቶ ነው የፈጠረው። እንደ እንስሶቹ ግራና ቀኝ እንደማያዩት
አድርጎ አልፈጠረውም። አክብሮ አልቆ ፈጠረው እንጂ። ክፉና በጎ የሚለይ ጨለማን ከብርሃን የሚለይ አስተውሎ
የሚያይ አእምሮ አጎናፀፈው በአምሳሉም ፈጠረው። ሲያዘውም የምድርን ፍጥረት ሁሉ አስገዝቶለታል።
እንዲህም ብሎ አዘዘው! ––– ክፉንና በጎውን፣ ጨለማና ብርሃኑን፣ ለይተህ ወደ ወደድከው፣ አእምሮህ
አውጥቶ አውርዶ ወደ ወሰነው እጅህን ስደድ! አለው። በውጤቱም ደግሞ ኃላፊነቱን ትወስዳለህ። እንደምርጫህ!
በዚያም ተንተርሶ እንደተከተልከው ውሳኔ በውሳኔህም እንደተገበርከው ተግባር ትዳኛለህ። በዚህም ውስጥ
ስህተትህን ተረድተህ ንስሓ ከገባሕ ባደረግኸው ከተፀፀትክ እምርሃለሁ። በሌላ መልኩ በብርሃን በመልካሙ
ከሄድክ፣ ተመሥግነህ ተወደህ ተባርከህ፣ በኔ ታምነሃልና እኔንም ትፈራለህና፣ እውነትንም አፅንተሃልና፣
እኔን አምልከሃልና፣ ከክፉ ምግባር እርቀሃልና፣ የካደኝን ክደሃልና፣ ያልተገዛልኝን አንተም አልተገዛህለትም
አውግዘኸዋልና በዚህም ምክንያት የታመንክ ባሪያዬ ነህ። ስለዚህ ወድጄሃለሁ፤ እክስሃለሁ፣ አፀድቅሃለሁ፣
አከብርሃለሁ አለው።
ከዚህ ተፃራሪ ከቆምክ ደግሞ ምክሬን ጠልተህ እኔን ክደህ በትእቢት ተሞልተህ፣ ጨለማን አንግሰህ፣ የዚህን
ዓለም ገዢ አምላክህ አድርገህ ለጥፋት ቆመህ፣ ክፋትን አንግሰህ፣ ፈጣሪን አላውቅም ነፍሴ በዚህ ምድር
ተደሰቺ ብለህ ከሆዳቸው ውጪ እንደማያስቡ እንስሶች ሆድህን አምላክ አድርገህ፣ በምድር ጥበብ ተመክተህ
አምልከህ፣ እኔን የፈጠርኩህን ንቀህ ትእዛዜን አቃለህ በገዛ ምኞትህ ሄደህ፣ መፀፀትን ጠልተህ ከዲያብሎስ
ተቆራኝተህ ስለፀናህ ፍርዴ ይከተልሃል ያካትትሃል። እኔ ቅን ፈራጅ ነኝና እንደልብህ ድንዳኔ እፈርድብሃለሁ
አለው።
እውነቱ ይህ ነው። ይህን እውነት ለመላው የአዳም ዘር በዚህ ክፉ ዘመን ከዛሬ 15 ዓመታት ጀምሮ
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት ተገለፀልህ። ተነገረህ። አልሰማህም ናቅህ፣ ልትድን አልወደድክም።
ከዚህ በላይ ምን ይደረግ?

54
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በዓለማችን ያለው ሕዝብ ወደ 8 ቢሊዮን ተጠግቷል። ከዚህ ውስጥ በኔ እሳቤ 100 ሚሊዮን የማይሞላ
ሕዝብ ነው ለፈጣሪው ፈቃድ በመገዛት ላይ ያለው ተብሎ ይታመናል። ይህ ሁሉ ምድርን የሸፈነ የሰው ዘር
ከዲያብሎስ ጋር ተጣብቆ ጠፍቷል። ላይመለስ ሆኗል።
በእግዚአብሔር ቃል በግልፅ እንደተቀመጠው የመዳን መንገድ፣ የእውነት መንገድ እጅግ ጠባብ ነው።
በዚህ በጠበበው መንገድ ለመግባት ተጋደሉ ይላል። የጨለማው መንገድ ግን እጅግ ሰፊ ነው። ብዙዎችም
ይሄዱበታል። ግን ይጠፉበታል። ይከስሩበታል። እውነቱም ይኸው ነው። እንግዲህ ወገኖቼ እግዚአብሔር
ቀጠሮ አክባሪ ነው። የተናገረውን የገባውንም ቃል ኪዳን አክባሪና ፈፃሚ ነው። እነሆ ዛሬም ቃሉን ለመፈፀም
ከብዙ ሺህ ዘመናት ትእግሥት በኋላ ምድርንና መላውን ነዋሪ የአዳም ዘር ከእናቱ ከእናታችን ከድንግል ጋር
በመሆን ጎብኝቶ የሰውን ዘር ልማትና ጥፋት አክራሞቱን ሁሉ መዝኖ አጠናቀቀ። ከላይ እንደገለፅኩት የሰው
ልጅ እንደምርጫው ተሰማርቶ ስለጠበቀው፣ በዚያው መሰረት እንደመፀፀቱ እንዲሁም እንዳለመፀፀቱ እንደልቡ
ጥንካሬና እንደ ቅንና የዋህነቱ ፍርዱን አፀና። በዚህም መሰረት ለቅዱሳን ሊቃነ መላእክት የአፈፃፀም ትእዛዝ
ሰጠ።
ከዚህ ውሳኔና ትእዛዝ አዘል መልእክት መውጣት በኋላ የመላውን ዓለም ሁኔታ ታየዋለህ። ምን ዓይነት
የዓለም ጥፋት እንደሚከናወን በእርግጥ ታየዋለህ።
ትንቢት የተነገረላቸውን፣ ለበጎው ቀን ያተማቸውን የወደዳቸውን፣ ያፀደቃቸውን ያከበራቸውን ሁሉ
በግምባራቸው አተመ። ለአገልግሎቱ በግምባር ለሚሰለፉት በብርሃናዊ ሕጉ ለሚያገለግሉት ሹመትን ሰጠ፣ ቀባ
የገዥነት የመምራት ስልጣንና የግርማ ሞገሥን ፀጋ ሰጠ። ዘውዳቸውንም ከቀዳማይ አገልጋይ ባሪያው ንጉሠ
–ነገሥት ቴዎድሮስ ጀምሮ በተዋረድ ለተሸሙትና ለተቀቡት ሁሉ ጫነላቸው። ኃይላቸውም እንዲሁ ተዘጋጀ።
ሲገለጡ አብሮ የሚነግሥ ብርቱ ኃይላቸውም ተዘጋጀ። አበቃ!! ተፈፀመ!!
ይህን የንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስን ምንነትና ሁኔታ የተመለከተውን ርእስ ስናጠቃልል –––– በመልእክት
3 በመጋቢት 19 ቀን 2001 ዓ.ም. ከገጽ 87 – 88 ከዛሬ 12 ዓመታት ጀምሮ ተገልፆአል። ይሁን እንጂ
ላላስተዋለውም ላላነበበውም ዛሬ ደግሜ ገልጬዋለሁ። እንኳን ስለ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ስለ ሁሉም ስርአተ
አገዛዝ በግልፅ በዚሁ መልእክት 3 ተገልፆአል።
ዓለም 21 ግዛተ አስተዳደር 21 ገዢ ንጉሶችም እንደሚኖሩ አንድ /1/ ንጉሠ ነገሥት 18 ንጉሦች በተለያየ
ከፍተኛ የአገልግሎት ስፍራ እንደሚሰየሙ ዛሬም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ። ሁሉም መንግሥታት፣ ሁሉም
ቀዳማይ እረኞች /አባቶች/ ማእከላቸው መቀመጫቸው መንበራቸው እዚህ ኢትዮጵያ ይሆናል። ማእከላቸውም
እዚህ ይገነባል።
ዓለምን የምትመራው ኢትዮጵያ የተወደደች፣ የተባረከች ምድር፣ የመፅናኛ አገር ትሆናለች። ዓለም
ለኢትዮጵያ ይገዛል። ይገብራል። በብርሃናዊ አገዛዟ ጥላ ውስጥ ያርፋል። ኢትዮጵያዊነት በታላቅ መንፈሳዊ
ተጋድሎ የሚጨብጡት ታላቅና ውድ ዋጋ የሚያስከፍል ስጦታ ይሆናል።
ንጉሠ – ነገሥት ቴዎድሮስ ኢትዮጵያዊ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጅ ነው። በመልእክቶቹ ሁሉ እንደተናገረው
ድሃ ጎስቋላ ሊቅ ያልሆነ ምናምንቴ ሰው ነው። ስለሱ መመረጥ የታወኩ ነውም ብለው ለመቀበል የተቸገሩ
እንዳሉ ግልፅ ነው። በቁጥር ቀላል ያልሆኑ በብዙ ምክንያቶች እራሳቸውን ቴዎድሮስ ነን ብለው አምነው የቆሙ
ሰዎች አሉ። ይህ ምንም አይደለም ሁሉ ወደፊት ስለሚገለጥ ወደ ብርሃንም ስለሚወጣ እንደዚህ ያሰቡበትንና
ያመኑበትን መንገድ ስለሚገለፅ ብዙም ከዚህ በላይ መግለፁ ወቅታዊ አይሆንም።
ንጉሡና ሌሎችም አባቶች እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ያሉት። ከዋናው ከተማ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ
ክልል በተለያየ ጉዳይ እየተንቀሳቀሱ ሁሉንም ድርጊት ይከታተላሉ። በመገለጡ ሰዓት በቀዳማይ ምክትልነትና

55
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በምክትልነት በግራና በቀኝ የሚሆኑ በንጉሥ ማእረግ ያሉ ዛሬም አብረውት በሥራው ሁሉ እያገዙትና አብረውም
እየሠሩ ነው። ሌሎች 37 የሚሆኑ በንጉሥ ማእረግ ያሉ በየባእታቸው ሆነው፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
ሕብረትና አንድነት በሁሉም እያገዙ የሚገኙ ናቸው። ሁሉም ሊያውቀው የሚገባው ቢኖር ዘመናዊ መገናኛ
እስካለ ድረስ፤ በቴሌግራም የዮሐንስ ራእይ 20 ቻናል ላይ ስለሁሉም ሁኔታ በቀጥታ የሚገለፅበት ይሆናል።
የንጉሠ ነገሥቱም፣ የንጉሦቹም ድምፅ የምትሰሙበት የሚገለጥበት ነው። ከዚህ በተረፈ በኢትዮጵያ የዓለም
ብርሃን መልእክታት በግልፅ የምታገኙት ነው። ቴሌግራሙም እስካለ ድረስ ነው የሚያገለግለው። ከዚህ ውጪ
የሚመጣ ነገር የለም። ተስፋ የምታደርጉት የኢትዮጵያ ትንሳኤም ሆነ የንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስና አብረውት
የሚገለጡት ንጉሦች እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ታላላቅ አባቶች መላውን ዓለም በተዋህዶ እምነት
የሚመሩት በይፋ የሚገለፅበት የሚታወቅበት ይኸው መንገድ ብቻ ነው። ከዚህ በዘለለ ሌላ እውነት አለን ካላችሁ
በርቱ ቀጥሉበት እንላለን። ዳኛው በሰማይ በመንበሩ ሆኖ ሁሉንም ስለሚመለከት እንደየታመንበት ፍርዱም
ትእዛዙም አብረው ይገለጣሉ። በሌላ በኩል እንደ እውነቱ ከሆነ እኔን ለምትቃወሙ ቅሬታም የለብኝ እኔ ዛሬም
ነገም የምለው የማምነው የምረዳው አምላኬም ያስተማረኝ እውነትና እውነትን ብቻ መግለፅ ነው። ስለዚህ እኔ
ከሁሉ የማንስ ነኝ። በሁሉም ገጽታ ከኔ ትበልጣላችሁ ብዬ አስባለሁ። ግን በምን መስፈርት እኔን እንደመረጠ
እኔም ስለማልረዳ እናንተ ቅር የተሰኛችሁ ሁሉ መድኃኔዓለምን ድንግልን ጠይቁ መልስን ታገኛላችሁ። ይህን
ያልኩት በዚህ ምክንያት እንዳትሰናከሉ በማሰብ ነው።
ንጉሥ ዳዊትን ልዑል ሲመርጠው ታላላቅ ወንድሞቹን እንዳላስደሰተ ሁሉ ሳሙኤልንም ግራ አጋብቷል። ጌታ
ግን ለሳሙኤል መልስ ሰጥቶታል መልሱም እግዚአብሔር ልብን እንደሚያይ ውጪያዊ ገጽታን እንደማይመለከት
አረጋግጦለታል። ነቢያትን በተለይም ሐዋሪያትን ጌታ የመረጠው ከተናቀው ሥፍራ እንደሆነ ሁሉም የሚያውቀው
ነው። በሥራዬ ለእግዚአብሔር ምንም የሠራሁት በምግባሬም ያስደሰትኩበት ሥራ የለኝም። በአንድ ነገር ብቻ
አስቦኝ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ። እሱም የፈጠረኝን አምላኬን ከከፋው ኃጢያቴ ያዳነኝን እንደሰው የቆጠረኝን
አምላኬን ውዳቂ ነው ብላ ያልተወችኝን እናቴን ድንግልን አብዝቼና በፍፁም ልቤ እወዳቸዋለሁ። ሌላ
የማውቀው ሰርቼ ያስደሰትኩበት ምንም የለኝም። እውነቱ ይህ ነው።
እንግዲህ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ማነው ለምትሉ ሁሉ፣ ለወዳጅም ለጠላትም፤ ግራ ገባን ለምትሉ ከላይ
ምንነቱን በመጠኑ እንድታውቁት ለማድረግ ጥሬአለሁ። ጊዜው ሲደርስ የሱንም የሌሎችንም ማንነት በግልፅ
የምታዩበት ጊዜ ይመጣል። መታገሥ ነው።
አንድ ነገር እርግጥ እንዲሆንላችሁ የምፈልገው ሁሉንም እውነት መገለፅም ቢሆን በራእይ ዮሐንስ 20 ቻናል
ላይ በልጃችን በተከፈተው ገጽ ላይ የምትሰሙት ይሆናል። መልእክታቱም ሁሉ አንዱ የኛ መግለጫ መስመር
ናቸው። እነዚህም ሁሉ በመከራው ክብደት ቢዘጉ ሌላ መንገድ እናዘጋጃለን። በዚያን ሰዓት መነቃነቅ ቀርቶ
መደበቂያ የሚያጣው ከሃዲው ትውልድ ይጨነቅ እንጂ! እኛ እውክታ የለብንም።
ሌላው ጉዳይ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ እኔ ነኝ የሚሉ እጅግ ብዙ ሰዎች እንዳሉ ይገመታል። ብዙም ሲናገሩ
እየተሰሙ ናቸው። እኔም እየሰማሁ ነው፤ ከመገረም ውጪ ምን ይባላል። እርግጥ ነው ሁሉም ወደ ብርሃን
ሲወጣ ማን ምን እንደሆነ ልዑልና ድንግል ስለሚገልጡት መታገሥና መጠበቁ መልካም ነው ብዬ አምናለሁ።
እንግዲህ እውነቱን ለናፈቃችሁ ይኸው እውነቱን ገልፀናል። በኛ ዘንድ ትመዘገቡ ዘንድ ባስታወቅነው መሰረት
የተመዘገባችሁ፤ ስለአመንበት መዝግበናል። መታወቂያ የወሰዳችሁ መልካም አድርጋችኋል። ለአገልግሎት ስለሆነ
የወሰዳችሁት በሰዓቱ ትጠቀሙበታላችሁ። በመታወቂያው ላይ ያለው ፊርማ የኔው መሆኑን ላረጋግጥላችሁ
እወዳለሁ።
ይህ ዘጠነኛ መልእክት ከምታውቁት የኔ ፊርማ በተጨማሪ የሁለት ወንድሞቼን ፊርማ ታገኙበታላችሁ። ይህ
የሆነው የወጣው መልእክት በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ሥር መሆኑን እንድታውቁና ላረጋግጥላችሁ

56
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ስለ ወደድሁ ነው። ሁለቱም ወንድሞቼ በንጉሥ ማእረግ በ2ኛና በ3ኛ ማእረግ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው
በ3ታችንም ስምምነትና በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይሁንታና ትእዛዝ የወጣ መሆኑን አረጋግጥላችኋለሁ።
እንግዲህ ዛሬ በሰዎች አእምሮ ሲጉላላ የነበረውን እውነትን የማወቅ ጉዳይ ገልፀናል። ንጉሡ ማነው ለሚለው
የእውነት ፈላጊዎች መልሱን ሰዓቱ በመሆኑ ልንገልፅ ሞክረናል። በኛ ግልፅ አድርገናል። መቼም ያለንበት
ዘመን የጨለማ ዘመን ነውና! ስለብርሃን ሲነገረው መልሶ ስለኖረበት ጨለማ ታላቅነት የሚሰብክ ትውልድ
ነውና! ምድርንም የሸፈነው ይኸው ትውልድ ነው። እኛ እውነትን ልንነግረው ጥረናል። ይሁንና አውቆ የተኛን
ቢቀሰቅሱት አይሰማም። ስለሆነም ላለቀ ጉዳይ አይገደንም። ካልሞተ የማይገባው ከሆነ ዝምታን እንመርጣለን ፡
ቀኑም ሰዓቱም ከፊታችን ያለ ስለሆነ፤ እሳቱ ሲከድንህ የት ተቁሞ እንደሚከራከር፤ ወዴትስ ሄዶ በትእቢት
እንደሚገሰል እሱ ራሱ ይወቀው።
በመጨረሻም በዚህ ጉዳይ በእኔነት ወይም በክህደት ባለማመን ወይም በግነት ብቻ ዛሬ ከገለፅልናችሁ ውጪ፤
እውነት አለን የምትሉ ሁሉ እንደፈቀዳችሁ ቀጥሉበት። እርግጡ ሲገለጥና ስታየው እንደአለመታዘዝህ ልክ
የሚመጥን ፍርድ ከልዑልም ከድንግልም እንደሚያስከትል በእርግጥ ልትረዱ ይገባል።
መልካም መረዳት ይሁንላችሁ።

በሰው የሚታመን ሥጋ ለባሹን ክንዱ የሚያደርግ ወዳቂ ሰው ነው። ነገር ግን ቀኑን


ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት ኑር በእውነት ፍፃሜ አለህና! ተስፋህም አይጠፋምና!
መጽሐፈ ምሳሌ 23 ፡ 17 – 18
እውነትን የሚጠብቅ ፃድቅ ሕዝብ ይገባ ዘንድ፣ በሮችን ክፈቱ፤ በአንተ ላይ
ታምናለችና! በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈፅመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። ጌታ
እግዚአብሔር የዘለዓለም ዓምባዋ ነውና! ለዘለዓለም በእግዚአብሔር ታመኑ
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 26ን በሙሉ አንብቡ
ይህ ሕዝብ በአፉ ወደኔ ይቀርባልና በከንፈሮቹም ያከብረኛልና ልቡ ግን ከኔ የራቀ
ነውና! በሰዎች ሥርአትና ትምህርት ብቻ ይፈራኛልና!
ትንቢተ ኢሳይያስ ም፡ 29 ፡ ቁ 13
ከላይ በሦስቱም የልዑል ኃይለ ቃል እንደተመለከታችሁት ዛሬ ለያዥ ለገራዥ ያስቸገሩ ቢነግሯቸው
የማይሰሙ ከቃሉ ይልቅ እከሌ አባት፣ እከሌ ጳጳስ፣ እከሌ መምህር፣ እከሌ ሊቃውንት፣ እከሌ የቤተ ክርሰቲያን
አባት አዘውኛል ነግረውኛል ብለው የሚመፃደቁ ለመልካም ሰዎች እንቅፋት ሆነዋል። አንዳንድ አባት ነን
የሚሉ ስለእኛ ምንም ሳያውቁ መልእክታቱን ሳያነቡ በሚገባ መረጃና እውነትን አጥርተው ሳይረዱ የራሳቸውን
ጥፋት በካባቸው ከልለው እኛን ስለእውነት በግልፅ ስለነገርናቸው ያወግዛሉ፤ ይፈክራሉ። አልፈውም ምኑንም
በአግባቡ ያልተረዱ ወጣቶችን አውግዘው ከእውነት እንዳወጧቸው ተረድተናል። በኛ ዘንድ ተመዝግበው
ለወደፊት በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ስር እንዲያገለግሉ የሚያበቃቸውን መታወቂያ የወሰዱትን
እንዲመልሱ እስከማስገደድ ደርሰዋል ። እንዲህ ያደረጉት አባት ተብዬ ለሰይጣንና ለሰራዊቱ ተላልፈው
እንዲሰጡ ወስነንባቸዋል። ስለማንታገስ! መታወቂያውን የመለሱትም ወጣቶች ዳግም ለአገልግሎቱ ስለማይበቁ
መታወቂያው መልሶ እንዳይሰጣቸው ተወስኗል። ከኛ ዘንድ የተመዘገቡ እንደመሆናቸው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ
ከምዝገባውም ሊሰረዙ ስለሚችል በንስሓ ወደፈጣሪ አመልከተው ለኛም በምዝገባችን እንቆይ የሚል ጥያቄ
በሰጠነው የአንድ ወር የጊዜ ገደብ ውስጥ ካላመለከቱ የምንሰርዝ መሆኑን ሊያውቁ ይገባል።

57
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ፖለቲካና እምነት የተደበላለቀባችሁ አማኝ ትሆኑ አስመሳይ ውላችሁ የማይታወቅ ጨለማውን ብርሃን ብርሃኑን
ጨለማ ለምትደርጉ ልብ በሉ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ የዲስኩር ማጣፈጫ
አይደለም። እውነት እውነት ማለትን ትተው የእንቻቻል ስልትን ለሚከተሉ የእምነት ድሃዎች እግዚአብሔርን
ስሙን እንጂ ፈቃዱን አያውቁም። በእምነት ድርድር የለም። ስልጣነ ክህነታቸውን ያለነውርና ነቀፋ የጠበቁ
አለቃ አያሌው በመጨረሻ ጊዜአቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ
ሰብሳቢ ነበሩ። ይህን ሁላችንም እናውቃለን። እኝህ አባት ስለእምነታችን አምድ /ዶክትሪን/ እና እንዲሁም
ዶግማ /ስርአተ ቤተ ክርስቲያን/ ጠንቅቀው የሚያውቁ ስለነበሩ በወቅቱ ባዶ ቤት አግኝተው የተሾሙት አባ
ጳውሎስ ሕገ ሲኖዶሱን ገልብጠው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ፈንታ የሲኖዶሱ የበላይ የሚያደርጋቸውን
ሕግ አፀድቀው ሲሰየሙ፣ በወቅቱ የቤተ ክርስቲያንን መሰረት መናጋት የተመለከቱት ሊቀ–ሊቃውንት አያሌው
ታምሩ ፓትሪያርኩንም ሕጉን በፊርማቸው ያፀደቁትን ጳጳሳት የሲኖዶስ አባላት አወገዙ፤ ሥልጣናቸውንም
እንዲታሰር አደረጉ። ለምን ኮትልከዋልና፣ መንፍቀዋልና፣ ጣኦት ሆነዋልና። በመሆኑም በማውገዛቸው በትክክል
መንፈሳዊ ግዴታቸውን ተወጥተዋል። ታዲያ ሕጉም ሳይሻር ውግዘቱን የሚያስነሳ እርምጃ ሳይወሰድ እንዴት
ተብሎ ነው ቤተ ጣኦት የሆነችው ቤተ ክርስቲያናችን የምትፈወሰው። በወቅቱ ፓትሪያርኩ የወሰዱት እርምጃ
አለቃ አያሌው ታምሩን ማባረርና ማገድ ነበር። እንደ እውነቱ ከሆነ መታገድም መባረር የነበረበት ፓትሪያርኩ
አቡነ ጳውሎስ ነበሩ። የፖለቲካው ሹመኛ ስለሆኑ እውነተኛውን አባት አባረሩ። ያ ጥፋት እስካሁንም ሥራ
ላይ ነው አልተለወጠም። በዚህም ማናቸውም የቤተ ክርስቲያናችን ካህናት አገልጋዮች በግዝቱ ውስጥ የታሠሩ
ናቸው። ጥፋታቸውን አውቀው አልታረሙምና፤ ስለዚህ ማንንም መፍታት መባረክ አይችሉም። ይህንን እውነት
እያወቁ ምንአለበት ለሚሉ ሁሉ ውጤቱን ወደፊት ያዩታል።
በዲያብሎስ ከተፈጠሩ እምነቶች /ካቶሊክ፣ መናፍቅ፣ እስላም፣ ዋቄ ፈታ፣ ሺንቶኢዝም፣ ታኦኢዝም፣
ኮንፊሺያን፣ ሂንዱኢዝም፣ ሲኪዝም፣ ተብታቢ፣ ኮከብ ቆጣሪ፣ ሰላቢ፣ ሁሉም አምልኮ ባእድ አምላኪ፣ ፀጋ፣
ቅባት / በሙሉ የቀደመው እባብ የዘንዶው የሃሰተኛው ነብይ እምነቶች ስለሆኑ ሁሉም የተፈረደባቸው ናቸው።
በምንም መልኩ ከነዚህ ጋር የተቀራረበ ከነሱ ተለይቶ የሚታይበት መንገድ የለም። ሁሉም እግዚአብሔርን
ክደዋል። እምነትን ከፖለቲካው አካሄድ ጋር አመሳቅሎ መስበክ ትልቅ ጥፋት ነው።
በዚህ ዘጠነኛ መልአክት መሰረት ከታች በሚገለፁት ውሳኔዎች፣ ትእዛዞች፣ መመሪያዎች፣ ቅድመ ሁኔታዎች
በአንደኛ ደረጃ በርቱ ቅጣት ውስጥ እንደሕዝብም እንደመንግሥትም እንደ ግለሰብም የሚያርፉትን፤ በሁለተኛ
ደረጃ ብርቱ ቅጣት ውስጥም እንዲሁ እንደመንግሥትም እንደግለሰብም እንደሕዝብም የሚያርፉትን በሦስተኛ
ደረጃ በብርቱ ቅጣት ውስጥ እንደሕዝብም እንደ መንግሥትም እንደ ግለሰብም የሚያርፉትን አገሮች በሦስት
ከፍለን እንዘረዝራቸዋለን።

በአንደኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ


አሜሪካ /ባቢሎን/፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ቻይና፣ ግብጽ፣ ጀርመን፣ ሕንድ፣ ኢራን፣ ሳኡዲ አረቢያ፣
ጣሊያን፣ ሁለቱም ኮሪያዎች ፣ እስራኤል፣ ራሺያ፣ ፓኪስታን፣ ካናዳ፣ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ፣
አውስትራሊያ፣ ስፔን፣ ቱርክ፣ ጃፓን፣ ኢንዶኔዢያ፣ ዱባይ እንዲሁም በመልእክት ስምንት እንደተጠቀሰው
በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ በፍጥነት ከሚጠረጉትና ከሚፀዱት ውስጥ ጅቡቲ፣ ሁለቱም ሱዳኖች፣ ኤርትራ፣
ኬኒያ፣ መላው ሱማሊያ፣ ሩዋንዳ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሁለቱም ኮንጎዎች፣ ማእከላዊ አፍሪካ፣
ቻድ፣ ካሜሮን፣ ግብፅ፣ ጋቦን፣ ጊኒዎች፣ ዛምቢያ፣ አንጎላ እነዚህም ከላይ በአንደኛ ደረጃ ከተጠቀሱት አገሮች
ጋር በቅድሚያ የሚፀዱ አገሮች ናቸው።

58
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በሁለተኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ


ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ አርጀንቲና፣ ሊባኖስ ፣ ኢራቅ፣ አፍጋኒስታን፣ በርማ፣ ታይላንድ፣ ካምቦዲያ፣
ቬትናም፣ ላኦስ፣ ኔፓል፣ ሲንጋፖር፣ ማሌዢያ፣ ታይዋን፣ ሲሪላንካ፣ ናይጄሪያ፣ ኒጀር፣ ኩባ፣ ኒካራጉዋ፣
ጓቲማላ፣ ኤልሳልቫዶር፣ ኮስታሪካ፣ ሆንዱራስ፣ ጃማይካ፣ ፓናማ፣ ሃይቲ፣ በሃማስ፣ ኩዌት፣ ኳታር፣ ኦማን፣
ባሕሬን፣ ቬንዙዋላ፣ ኮሎምቢያ፣ ሱማትራ፣ ፍሬንች ጉዩና፣ ኢኳዶር፣ ፔሩ፣ ፓራጓይ፣ ኡራጋይ፣ ቺሊ
ቦሊቢያ፣ ታጂኪስታን፣ ኪርጊስታን፣ ኡዝቬክስታን፣ ተርኪሚስታን፣ ጆርጂያ፣ ካዛኪስታን፣ ቤላሩስ፣
አዘርባጃን፣ አርመኒያ፣ ሶሪያ፣ ፊሊፒንስ፣ አልጄሪያ፣ ምእራብ አፍሪካ በሙሉ።

በሶስተኛ ደረጃ ውስጥ የሚካተቱ


በዚህ ውስጥ የሚካተቱ አገሮች ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት በአንደኛ በሁለተኛ ደረጃ ከተመለከቱትና ስማቸው
ከተዘረዘረው ውስጥ ያልተጠቀሱ ቢሆንም የሌሎችን ጥፋት ዕያዩ በስተመጨረሻም የሚካተቱና የሚጠረጉ
ናቸው።
ልብ በሉ በመልእክት 3 በመልእክት 5 በመልእክት 8 የተጠቀሱ አገሮች፣ በመላው ዓለም እንደአገር
የተቆጠሩ ሁሉ በፍርድ የሚካተቱ እንጂ የሚቀር አገር የለም። እንደሁኔታው ልክ ኮሮና ቫይረስ ዓለምን
እንዳዳረሰው የጠረጋውም ሆነ የቁጣው ትኩሳት የማይጎበኘው የማይጠርገው ምድር የለም። እርግጥ ብርቱ ነን
የሚሉ በኢኮኖሚውም በጦር ኃይልም በሁሉም ቀዳሚ ነን የሚሉ በቅድሚያ የሚጠረጉና ታይቶም ተሰምቶም
በማይታወቅ ጥፋት የሚበሉ ናቸው። አንዳንዶቹ ሙሉ በሙሉ ታሪክ እንኳ ሆነው የማይታሰቡና ቅሬት
የማይተውላቸው ሆነው ይጠፋሉ።
በዚህ መልእክታችን ስትረዱት ነገሮች የተደጋገሙ ሊመስላችሁ ይችላል። ነገር ግን አይደለም። የተደጋገመው
ብዙ አዳዲስ ፍርዶችንም ያካተተው አደጋ ስለመጣ ከዚያ አደጋ እንድታመልጡ ነበር። ስለ አጠፋፋችሁ
አስፈሪነት ስለሚያስጨንቅም ነው። በታሪክ እንደሰማችሁት የአንደኛ የዓለም ጦርነት የፈጀው ሕዝብና ንብረት
ትምህርት ሆኖ ሰው ጦርነትን እንዲተው አላደረገውም። በሁለተኛም 2ኛው የዓለም ጦርነት ሲከሰት ዓለም
ወዶትና ፈቅዶት ያመጣው አይደለም። አንድ ዲያብሎስ የጋለበው ሂትለር የለኮሰው ጦርነት ነው። በወቅቱም
ሁሉም አገሮች ጦርነቱን ሊያመልጡት አልቻሉም። ገቡበት። በመቶ ሚሊዮን የተቆጠረ ሕዝብም አለቀበት
ብዙ ንብረትም ወደመበት። ከዚያም ወዲህ ያነሱ ቢመስለንም ብዙ ጦርነቶች በየቦታው ተደርገዋል። እነዚህ
ሁሉ ቅጣቶች ሲመጡ ያለ ምክንያት አይደለም። ሰው ከፈጣሪው ጋር ያለውን ግንኙነት በማበላሸቱ፤ከዚያም
አልፎ ምድር ፍፁም በመጥፋትዋ ታላቁ ቁጣ ከመገለፁ በፊት ምናልባት ተፀፅቶ ንስሓ ገብቶ ሰው ቢድን
ተብሎ የተሰጠ እድል ነበር። ጠፊው ትውልድ ግን መልእክታቱን ሁሉ እንደተረት እንዲቆጥሩት ሆነ። መታገሥ
መምክር፣ መናቅን መካድን ካስከተለ፤ ፍቅርና ትእግሥት ፍሬ ካላፈራ ማጥፋት ምን ይከብዳል። እንደተሰራኸው
እንዲሁም ትፈርሳለህ። ባለቤቱን ንቀሃል አጥሩንም ነቅንቀሃል። በመሆኑም ተነቃቅለህና ተጠርገህ ወደ ትቢያነት
ትለወጣለህ። እውነት ይህ ነው። ብትወደው ስማው ባትወደው ደግሞ በግድ እየሰማህ ወደማይቀረው ክፉ ሞትህ
ትሄዳለህ!!
ሌላው በአንዳንድ ወገኖች በኩል ከኛ ዘንድ የሚሰጡ ቃሎችን አጣሞ ፖለቲካዊ ትርጉም በመሥጠት
የእግዚአብሔርን ሕዝቦች ለማሳሳት ሲጥሩ ይታያል። ከነዚህም አባባሎች ውስጥ ––– እግዚአብሔር የሥጋ ድጋፍ
አይፈልግም የሚል ቃል ከኛ ዘንድ በእርግጥ ተገልጧል። በሌላ በኩል ደግሞ በኦዲዮ በሰጠነው ትምህርት
በተዋህዶ እምነቱ በአገሩ ለሚደቀንበት የጠላት አደጋ ራሱንም አገሩንም እዲከላከል መክረናል። ዛሬም በዚህ
መልእክታችን ደግመን ገልፀናል። ለምን?

59
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ልዑል የሥጋ ድጋፍ አይፈልግም ስንል ምን ማለታችን ነው? ሰው በጦር በትጥቅ በውጊያ ተነስቶ እግዚአብሔር
ለሕዝቦቹ የገባውን ቃል – ኪዳን ለመፈፀም በራሱ የሥጋ ዝግጅት እግዚአብሔርን ሊረዳ አይችልም ማለት
እንደሆነ ልብ በል። ለዚህ ምሳሌ የሚሆነን እንግለፅ – እሥራኤሎች በአመፁ ጊዜ የእግዚአብሔር ታቦት
ፂዮንን ይዘው ከእግዚአብሔር እርቅን ሳይፈፅሙ ከፍልስጤሞች ጋር ውጊያ ገጠሙ። በውጊያ ወቅት ታቦተ
ፅዮንን ይዘው ዘምተው ነበር። እግዚአብሔር ሊረዳህ የሚፈቅደው ስትታመንበት ቅድስናህን ስትጠብቅ ንስሓም
ገብተህ ስለውጊያህም ፍቃዱን ጠይቀህ ቢሆን በእርግጥ ይረዳሃል ጠላትህንም ታሸንፋለህ። ይህንን የሚያውቁት
እስራኤላውያን ለተለምዶው ታቦቱን ይዘው ወጡ እንጂ ከጥፋታቸው አልተመለሱም፤ ከነውራቸውም አልራቁም
ብቻ በትእቢት ወጡ በፍልስጤሞች ተመቱ። ታቦተ ፅዮንም ተማረከች። ፅዮን በሄደችበት ማንም እስራኤላዊ
በሌለበት በፍልስጤሞች ጣኦት ቤት ቢከቷትም የነሱ ጣኦት እየወደቀ ሲሰግድ ፍልስጤሞች አዩ፤ ይህም ብቻ
አይደለም የፍልስጤምን ምድር በታላቅ በሽታና መቅሰፍት መታ። ፍልስጤሞች ታወኩ ደነገጡ ታቦተ ፅዮንን
ሊመልሱ ወስነው በሚያጠቡ ላሞች የሚጎተት ሰረገላ አዘጋጅተው ታቦቱን በዚያ አድርገው ወደ እስራኤል
ምድር ሸኙ። ታቦቷም ወደ እስራኤል ምድር ስትደርስ ይህ ሁኔታ በወቅቱ ለነበረው ንጉስ ዳዊት ዜናው
ደረሰው። በመንገድም ሰረገላውን የሚጎትቱት ላሞች ይፋንኑ ስለነበር ታቦቱን የሚጥሉት ያህል ይመስል ነበር።
በዚህ ጊዜ ነበር ኦዛ የሚባል ገበሬ ታቦቱን ሊደግፍ ወደታቦቱ እጁን የሰደደው፣ ወዲያው የእግዚአብሔር
መንፈስ ቀሰፈው። ወገኖቼ እግዚአብሔር የሥጋ ለባሽን ድጋፍ እንደማይፈልግ በዚህ ልንረዳ ይገባናል። እኛ
ድጋፍ እንጠይቃለን ርዳታውን እንሻለን እንጂ ጌታ ከኛ የሥጋ ድጋፍ አይፈልግም። እኛ ግን የሱን ድጋፍ
ስንሻ ማድረግ ያለብንን ቅንነት በንስሓ የቀና ሕይወት በሱ የሚታመን ልብ ይዘን በፊቱ አርዳታውን ከጠየቅን
ይረዳናል።
ራሳችንንም ለመከላከል እምነታችንን ለመጠበቅ አገራችንን ሰንደቃችንን ለመጠበቅ መብቱ አለን። በግፍ
ለሚዘምትብን ለሚዘርፈን አገራችንን እምነታችን የሚፃረር የሚያጠፋ ጠላት ልክ እንደጣሊያን ሲመጣ የፈጣሪን
ድጋፍ በመጠየቅ ለመከላከል ልንቆም ይገባናል። ዛሬ ነጭ ጠላት ባይመጣብንም እሱ ይዞብን የመጣውን
ተግባር በውክልና የገዛ አገራችን ዜጎች እየፈፀሙና ለጠላት ግዳይ እየጣሉ በመሆኑ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ልንዋጋ
ይገባናል። አቡነ ጴጥሮስ ጠመንጃ ይዘው ተዋጉ ሲያዙ በክህነት ሥልጣናቸው አወገዙ። ስለእውነታቸው ደግሞ
ሰማዕት ሆኑ። የኛ እምነት እንዲህ ናት። ዛሬ ያለ ትውልድ አገሩን እምነቱን ሰንደቁን ሸጦ የበላ መናፍቅ ካቶሊክ
እስላም የዲያብሎስ አጀንዳ ተሸካሚ ፈሪ የምላስ ጀግና ቀጣፊ ውሸታም አታላይ ዘረኛ ተብታቢ መተተኛ ነጭ
አምላኪ በመሆኑ ዛሬ ለመጣው ፍርድ እርድ ሆኖ ቀርቧል። የሚገርመው እኛን ሊነቅፈን መሞከሩ ፡ እኛና
የዛሬ እምነቱና አገሩን ሰንደቁን የጣለ ትውልድ በምን መስፈርት ነው በኛ ላይ ምላሱን የሚያላቅቀው? ቤተ
ክርስቲያንን ያፈረሰ ለዲያብሎስ አሳልፎ የሸጠ፣ ፍርድህን ታየዋለህ። በምላስህ በመለፍለፍህ ብዛት አትድንም።
ልበ አምላክ ያውቅሃል። ስለዚህ ማንኛውም እውነተኛ የተዋህዶ ልጅ ስለእውነት ስለተዋህዶ እምነቱ ስለአገሩ
ስለሰንደቁ ዘብ ሊቆም ይገባዋል። ነጣ ጠቆረ ዜጋ ሆነ አልሆነ በእምነትህ በአገርህ በሰንደቅህ ላይ በጠላትነት
ከዘመተ የተፈጥሮ መብትህ ነውና ልትከላከለው ትችላለህ።
ድሮ ትምህርት ቤት ስንማር የእስፖርት መምህራችን አንድ አሸናፊ የሌለው ውድድር ያወዳድሩን ነበር።
ውድድሩ በሾርባ ማንኪያ ላይ እንቁላል ይቀመጥና የማንኪያውን እጀታ በጥርሱ ነክሶ መሮጥ ሲሆን ማንም ሰው
እንቁላሉን በሰላም ሩብ መንገድ እንኳን ማድረስ አይችልም። ይዞ የሚዘልቅ የለም። ገና ትንሽ እንደሄደ እንቁላሉ
ይወድቃል ይሰበራል። ይህን ምሳሌ ያመጣሁት በአንድ ምክንያት ነው። ሁሉም እንደሚያውቀው የዛሬው
መሪያችን መናፍቅ፤ እስልምናንም እንዲሁ የሚመስሉት ቁራጭ ኢትዮጵያዊነት የሌላቸው እጅግ አስመሳይ
ተዋኝ የማይጨበጥ ሕልም ይዘው ያሉ እንደመለስ ዜናዊ ሥልጣኔን የሚያቆይ ዘዴ ብቻ ልከተል ብለው
የሚደክሙ ሰው ናቸው። ሥልጣናቸው በማንኪያ ላይ እንደተቀመጠው እንቁላል በጥርሳቸው ይዘው የሚሮጡት
እንደሆነ እነሆ እያየነው ነው። አይድከሙ እሩቅ አሳቢው ቅርብ ነው አዳሮ። በቅርቡም የሚያዩት ይሆናል።

60
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ያም ሲያማ ይህም ሲያማ ለኔ ብለህ ስማ እንደሚባለው ወያኔ ወደቀ ተፈረካከሰ አዎን እግዚአብሔር ሲፈርድ
እንደዚህ ነው። እርስዎ ፈቅደው ወደ ውጊያው አልገቡም ቢሆንሎት እየተለማመጡ ስልጣኖን አስጠብቀው
ለመጓዝ ነበር። እነሱ ግን በግድ ጦርነቱን አመጡሎት። ይኸው መከረኛ አማራ የሚጠሉት ስለ እምነቱ ስለአገር
ወዳድነቱ ስለሰንደቁ የጸና ዜጋ ስለሆነ ብቻ የተገፋው ሥልጣኖን ለጊዜውም ቢሆን ታደጎት። ነገም ሌላው አደጋ
መጥቷል ከኢትዮጵያ ከተዋህዶ እምነት ከሰንደቋ የተጣላ አይጠራጠሩ በውርደት ይሰናበታል። ይህንንም ደግሞ
ልቦ የሚያምንበትን ልዑል እንደሚያውቅ ካልናቁት በስተቀር ይረዱታል። ሁሉም ከሚያውቀው ጮሌ ምላስዎ
ተመስርቶ የሚመጣ ውሳኔ የለም። በልቦ በሚያመላልሱት እምነቶ ላይ ተመስርቶ ዋጋ የሚከፍሉበት ይሆናል።
ትእቢትና ክፋት ክህደትና ንቀት ዘረኝነትና ሴራ ከሥልጣን ጋር ሲደመሩ በዚህ ለሚሄድ ሰው የሚጠፋው
ወዲያው ነው ብለን እናምናለን። ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ ነው።
በአሁኑ ጊዜ አከራካሪ ሆኖ እየተነሳ ያለ አንዳንድ ነጥቦችን ለማንሳት እንወዳለን።
በ1988 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከወቅቱ የፖለቲካ ለውጥ ጋር የመጣ
አዲስ ነገር ተፈጥሮ ነበር። ይኸውም በወቅቱ የቤተ ክርስቲያኗ ፓትሪያርክ አባ መርቆሪዮስ በመንግሥት /
በወያኔ/ ትእዛዝ ከመንበረ ሥልጣናቸው ተባረው አገር ጥለው ሲሄዱ በትእዛዝም በማስፈራሪያም አባ ጳውሎስ
ከውጪ ተጠርተው መጥተው የፓትርያርክነቱን ስልጣን ጨበጡ። ስልጣናቸውን ካደላደሉ በኋላ የቀደመውን
የአባቶችን ድንበር በመጣስ የቤተ ክርስቲያንን የሲኖዶስ መመሪያ ሕግን አፍርሰው በእግዚአብሔር መንፈስ
ቅዱስ ፈንታ እራሳቸውን በመሾማቸው ሲኖዶሱ ተጠሪነቱ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው የሚለውን ሽረው
ሲኖዶሱ ተጠሪነቱ ለእሳቸው ለፓትሪያርኩ እንዲሆን አደረጉ። ይህ ሕግ ዛሬም ሳይሻር በሥራ ላይ አለ። አለቃ
አያሌው ታምሩ በወቅቱ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ ነበሩ። ሥራቸውም እንዲህ አይነቱን ሕፀፅ
መከለላከልና ቤተክርስቲያንን ከተዋህዶ እምነቷ አባቶች ካስቀመጡት ድንበር እንዳትወጣ መከላከል ስለነበር፤
በወቅቱ ብዙ ታግለው ሰሚ በማጣታቸው ፓትሪያርኩንም የሳቸው ተባባሪ የሆነውን የአገር ቤቱን ሲኖዶስ
በውግዘት አሠሩት። አቡነ ጳውሎስም ከሥራቸውም ከሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢነታቸውም አባረሯቸው። ውግዘቱ
የሚለውን ቃሉን ስናየው እንዲህ ይላል።
»» ምናልባት የሕጉን ጽሑፍ አንብቦ መረዳት የተሳነው ግን በልዩ ልዩ ደጋፊዎቻቸው ተጭበርብሮ
በቸልታ የሚመለከተው ከዚያም አልፎ በሥልጣናቸው እየተመኩ ለቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ጆሮአችንን
አንሰጥም ብለው ይሕንን በደል ያደረሱትን ፓትሪያርክ አባ ጳውሎስንና በሦስት የሹመት ስም
የሚንቀባረሩትን አባ ገሪማን ለእነርሱም ድጋፍ የሚሰጡትን ሁሉ –– ጌታዬ አምላኬ በምድር
ያሰራችሁት በሰማይም የታሰረ ይሆናል ሲል በሰጠው ቃል በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስም
ሥልጣን በቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ በቅዱስ ማርቆስና በአባ ቄርሎስ በአባ ባስልዮስና በአባ
ቴዎፍሎስ በፃድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ዘደብረ ሊባኖስም ቃል –– ኃጥእ ደካማም በምሆን በእኔም
በቀሲስ ወልደ ጊዮርጊስ ቃል አውግዣለሁ።
»» ይህን ሕግ የተቀበሉና ከሥራ ላይ ያዋሉ ሁሉ እንደአርዮስ እንደ መቅዶንዮስ እንደ ንስጥሮስ እንደ
ፍላብያኖስ እንደኬልኬዶን ጉባኤና ተከታዮቹ እሱራን ውግዛን ይሁኑ። በማይፈታው በእግዚአብሔር
ሥልጣን አስሬአለሁ። ለአብና ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን አሜን ይላል። አምላኬ ሒድ
ተናገር ያለኝን ትእዛዝ ለእናንተ አድርሼአለሁ። ሩጫዬንም ጨርሻለሁ ከእንግዲህ ተጠያቂነቱ የእናንተ
የምእመናንና ታሪክ ተጠያቂ ያደረገው የመንግሥት ነው። ለዚህም ምስክሬ ራሱ እግዚአብሔርና
ቅዱሳን መላእክት ሰማይና ምድር ናቸው።
»» ይህ ውግዘት እስካሁን አልተነሳም። ቤተክርስቲያን ያፈረሰችውን የአባቶች ድንበር በመፀፀት
አላስተካከለችም። ዛሬም አባ ጳውሎስ በደነገጉት ሕግ ትጓዛለች። ስለ ውግዘቱ አንድ ወንድም

61
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

በአሳተመው – ያልተፈታው ውግዘት የሚል መጽሐፍ ገዝታችሁ አንብቡ። እኛ እውነትን መግለፅ


የታዘዝንበት ሥራችን ነው። ሸፍነን አቻችለን አንጓዝም። ሚሊዮኖች ይቀየማሉ አንልም ይልቅስ
እውነቱን ብርሃኑን እንናገራለን። ቁጥር ለእግዚአብሔር የሚገድ አይደለም። ስለእውነት ለቆመው ግን
እግዚአብሔር ግድ ይለዋል። አስተውሉ የተጠራነው ስማችንም እንደሚገልፀው /ኢትዮጵያ የዓለም
ብርሃን / እንደሚለው ነን። አትቸኩሉ ነብዩን ኤልያስን አስታውሱ ብቻውን ስለእውነት ቆመ።
የእስራኤል ሕዝብ መሪዎቹ አክአብና ኤልዛቤል መላው ካህናት ቡኤል ዘቡኤልን ሲያመልኩ ቁጥራችሁ
ብዙ ነው እና ለነሱ ልፍረድ አላለም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ለማንኛውም ማንኛውም የሥላሴና
የድንግል ቤተሰብ ስለውግዘቱም ሆነ ስለሌላ ጥያቄዎቹ ጾም ይዞ ሱባኤ ገብቶ ከልብ በመነጨ ጸሎት
ከፈጣሪው ከመድኃኔዓለም ይጠይቅ። የጥፋት መንገድ ሰፊ ነው ሂያጁም ብዙ ነው። የእውነት መንገድ
ጠባብ ነው የሚሄዱበትም እጅግ ጥቂቶች ናቸው። በጠባቡ መንገድ ለመግባት ተጋደሉ ነው የሚለው
ቃሉ።
»» እኛ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን የተሰበሰብን ሁሉ በስሜት በደመ ነፍስ
አንመራም። የሚመራን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው። የሚመራን ቃሉ ነው። የሚመራን
አባቶቻችን ያፀኑት በእውነትነት የሄዱበት ሰማዕት የሆኑበት ተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነታችን ነው።
ስለዚህ አንዳንዶች የማቻቻል ጨለማን ከብርሃን አደበላልቆ የመሄድ ስልት ለምትከተሉ ራሳችሁን
መርምሩ ከፈጣሪያችሁ ጠይቁ እንላለን።
»» ማህበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ስለገለጽነው እውነት ማንም ሊያስተባብልን ሊነግረን ሳይሆን በውስጣቸው
የነገሰውን የጨለማ ሥራቸውን እንዲያርሙ መንገር ከእውነተኞች ምእመን ይጠበቃል። በማናቸውም
መግለጫችንም ሆነ በመልእክታችን መረጃን ሳንይዝ አንናገርም። በውስጣቸው መልካሞች ሊኖሩ
ይችላሉ። እኛ የሉም አላልንም። የቀደሙት የተጉት መልካም ሰርተዋል። ይህንንም እናውቃለን የዛሬዎቹ
በእርግጥ በእነሱ ጫማ ውስጥ ናቸው ወይ! እግዚአብሔር ያውቃቸዋል እኛም በተረዳነው እውነት
እናውቃቸዋለን። ሌላው የተመረጡ በእግዚአብሔር ለበጎው ቀን የተጠበቁ የት እንዳሉ የሚያውቃቸው
እግዚአብሔርና ራሳቸው የተጠሩት ባሮቹ ናቸው። አሁን የሚያስጨንቀን ጉዳይ አይደለም። ከፊታችን
የእሳት ወንፊቱ ስለመጣ ሁሉም ወደ ብርሃን ስለሚወጣ ያኔ የሁሉንም እጣ እናየዋለን።
»» ውግዘቱ ማንን ያሥራል ለሚለው ግልፅ ነው በቅዳሴው በሁሉ ስርአተ ፀሎቱ የአባ ጳውሎስ፣
የአባ ማትያስ፣ በአሁኑ ሰዓት ውግዘት ያስከተለውን ሕግ የሚገለገልበት ሲኖዶስ እሱራን ስለሆኑ
ስማቸውን በቅዳሴውም በስርአተ ጸሎቱም የሚያነሳ ካህን ዲያቆን ክህነቱ የታሰረ ነው ማለት ነው።
እኛ እውነቱን መግለፅ ግድ ይለናል። የዕረኝነት ሥራችን ነውና! እኛ የቆረብነው ክርስትና የተነሳነው
ዛሬም ይህንን የምናደርገው ክርስቲያን አይደለንም ወይ የሚል ጥያቄ ይነሳል። እኛ ምንረዳው ሳያውቅ
ሳይረዳ የሄደውን ወይም እየተጓዘበት ያለውን ስለምን አላወቅህም አላልንም አንልም። እንደአለማወቁ
ዳኝነቱ የመድኃኔዓለም ነው። ዛሬ የተሸፈነውን እውነት ገልፀናል። ይህን ካወቀ በኋላ ለሚጓዝበት
እሚመለከተው አድራጊውን እራሱን ነው። እኛ መፍትሔ ዛሬ ልንሰጥ አንችልም። በቤተ ክርስቲያን
የእረኝነት ኃላፊነት መንበር ላይ አይደለንም። ስንደርስበት ምንም ጥርጥር የለውም የአባቶች ሕግ
ወደነበረበት ይመለሳል። መመለስ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራት አገልጋዮቿ
ሁሉ ከሱ ፈቃድ የማይወጡባት ፍፁም ለእግዚአብሔር ምክር፣ ትእዛዝ ምሪት አስተምህሮ የምትገዛ
የአባቶቻችን የተዋህዶ እምነታችን ያለ ሕፀፅ የምትፀናባት ትሆናለች።
»» ስለትጉሃን መማክርትና ስለፅዋ ማህበራት ብዙ አስተያየቶችን እንሰማለን። በቅንነት ባለማወቅ ልምድም
ከማጣት ስሕተት ሊሠሩ ይችላሉ። ሐዋሪያትን ጌታ ሲመርጥ ልባቸውን አይቶ ስለነበር ሁሉም
የናቃቸው ነበሩ። መራጩ መድኃኔዓለም ያውቃቸዋል። እርግጥ አንዳንድ የዲያብሎስ አገልጋዮች የሉም
62
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

አይባልም እንዳሉ እናውቃለን። ቢቆዩም ለጥፋታቸው ነው። ቢሄዱም እጣቸው ነው። ስለድፍረታቸው
ግን ዋጋ መክፈላቸው አይቀርም። ስለ ቅኖቹ ግን በጊዜ ሂደት በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ
አስተምህሮና መሪነት ሙሉ ሰው እንደሚሆኑ አይጠረጠርም።
ወገኖቼ የእግዚአብሔር ሕዝቦች!!
የዛሬው ዘጠነኛ መልእክት የመጣው ለምንድነው የሚል ለሚለው የሕሊና ጥያቄ መልእክቱን አንብባችሁ እዚህ
ከደረሳችሁ በሚገባ ትረዳላችሁ ብዬ አስባለሁ። ከሌሎች መልእክታት ለየት የሚያደርገው ቢኖር መልእክታትን
በስፋት ከማንሳቱም በላይ እጅግ የበረታ ውሳኔንም፣ ቅድመ ሁኔታን መመሪያን ትእዛዝን መጨበጡ ነው።
መልእክቱን ደጋግማችሁ ስሙ በአንድ ጊዜ ንባብ ልትረዱት ይቸግራል። ለሰውም ለማስረዳት የሚቻለው
በሚገባ በማንበብና በመረዳት ነው።
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በዚህ መልእክት ያልተረዳችሁትን ይበልጥ እንግዳ የሆናችሁ፣ እስከዛሬ ያልሰማችሁ
በመዘግየታችሁ ባዝንም የእግዚአብሔርን ጥሪ ማንም አያውቀውምና ከልባችሁ ወደፈጣሪ ቀርባችሁ ሁለመናችሁን
ለእግዚአብሔር ሰጥታችሁ ከልባችሁ ተፀፅታችሁ በእንባ ለድንግል ለመሰላችሁ ሊቃነ መላእክቶች ለቅዱሳን
ሰማዕታት እንዲሁም ለከበሩት ሁሉ ምልጃቸውን ተገን አድርጋችሁ ቶሎ ከጥፋት ዓለም ውጡ። እንደ መናፍቃን
ካቶሊኮች ተብታቢዎች አባይ ጠንቋዮች እስላሞች የምሥራቅ ጣኦት አምላኪዎች ቅባቶች ፀጋዎች ግብረ ሶዶሞች
ዘረኞች ሁሉ እናንተም በኔ ተሰናብታችኋል። በእግዚአብሔር ቸርነትና ፈቃድ ኢምንቶች ከንፍር እንደወጣው
ባቄላ ትወጡ እንደሆነ አላውቅም።
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰብነት ታምናችሁ ተመዝግባችሁ ያላችሁም ሆነ ያልተመዘገባችሁ በትጉሃን
መማክርት የተሰባሰባችሁ በፅዋ ማህበር የተሰባሰባችሁ የተመዘገባችሁም ያልተመዘገባችሁም የታዘዛችሁትን
በጠረጋው ሰዓት ልታደርጉ የሚገባችሁን ምልክቶች አሟልታችሁ ተዘጋጅታቸሁ ንስሓ ገብታችሁ በአቅማችሁ
ልክ ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ። ገንዘብ ያላችሁ በገንዘባችሁ መልካም በማድረግ አትርፉበት የሌላችሁም በአቅማችሁ
ልክ ብቻ ተዘጋጁ እግዚአብሔር ድንግል ስለእናንተ ጉድለት ያሟላሉ!!
በየበረሃው ያላችሁ አባቶቼ እናቶቼ ወንድም እህቶቼ ልጆቼም እግዚአብሔር እንደመከራችሁ ራሳችሁን
አዘጋጁ። ከዚህ በኋላ ሌላ የእውነት መገለጫ መንገድ አለ ብላችሁ አታስቡ ሁሉንም ባይሆን መሰረታዊውን
እውነት አስጨብጠናችኋል። ከእግዚአብሔር ከድንግል ከሊቃነመላእክት ከቅዱሳን ከሰማዕታት ጋር በፍቅር
አንድነት ተጣበቁ! በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጣችሁ። ቀጣዩ ርእስ በመላው ዓለም ይፀና ዘንድ የታወጀውን
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ታያላችሁ። ይህም አዋጅ በሥላሴዎች ትእዛዝ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ
መንግሥት ሥርና ሥልጣን የታወጀ አዋጅ መሆኑን እንድታውቁት እንላለን።
»» ሁሉም የአዳም ዘርን ስለሚመለከት ቢያነበው፣ ቢያደምጠው መልካም ነው።
»» በማናቸውም ቋንቋ ቢተረጎም ሁሉም እንዲሰማው ለማድረግ ስለሚቻል የዚህ እድሉ ያላችሁ
ተርጉሙት። ነገር ግን ይህን ስታደርጉ የተረጎማችሁትን ለልጃችን ለራእይ ዮሐንስ 20 መሥራች
ላኩለት። እናየዋልን ከዚያ ታወጡታላችሁ። ጊዜው አጭር ስለሆነ እድሉ ያላችሁ ቶሎ ብታገርጉት
ይመረጣል። ስርጭቱንም እንዲሁ ለሁሉም አድርሱት ገደብ የለበትም። ከዚህ በታች የምታገኙት
አዋጁን ነው።
የልዑል ኃይለ ቃል እንዲህ ይለናል።

ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፣ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፣


በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ፣ ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፣
ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል፣ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደተተከለች፣

63
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት ዘጠኝ

ፍሬዋን በየግዜው እንደምትሰጥ፣ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፣


የሚሰራውም ሁሉ ይከናወንለታል፣ ክፉዎች እንዲህ አይደሉም፣ ነገር ግን ነፋስ ጠርጎ
እንደሚወስደው ትቢያ ናቸው፣ ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ፣ ኃጢአተኞችም በፃድቃን
ማህበር አይቆሙም፣ እግዚአብሔር የፃድቃንን መንገድ ያውቃልና! የክፉዎች መንገድ
ግን ትጠፋለች።
መዝሙረ ዳዊት ምእራፍ 1 ከቁጥር 1 – 6

የአብርሃሙ ሥላሴ ስማቸው ይክበር ይመስገን! ድንግል እናታችን ስሟ ይክበር ይመስገን!!


መልእክት ዘጠኝ ከዚህ ተፈፀመ

የሥላሴና የድንግል ባሪያ!

64
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ቁጥር፡ ኢብመ/4/2013 ዓ.ም


ታህሣሥ 21 ቀን 2013 ዓ.ም

ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ


የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ!!
አዋጅ! አዋጅ! አዋጅ!
ሁሉም የሰው ዘር በእግዚአብሔር ቅን ፍርድ የሚጎበኝበትና ፍርድን የሚቀበልበት ሰዓት እነሆ ደረሰ!
የተዘጋጁ! ንስሓ የገቡ! በተዋህዶ እምነታቸው የፀኑ ከዚህ ዓለም ጉድፍ የተጠበቁ ታሰቡ የአባቶቻቸውን ዋጋ
በዚህ ምድር ተክሰው ተወደው ሊፅናኑ ለእራት ተጠርተዋልና ስማ! ኢትዮጵያ ታሰበች! በታላቅ ተጋድሎዋ
ድልን ነሳች! ስማ! የአዳም ዘር ሁሉ ስማ! አድምጥ!

መግቢያ

በዚህ ምድር ላይ ለረጅም ዘመናት በሺዎች የተቆጠሩ ጊዜያት በመንግሥትነት የዓለምን ሕዝብ ሲነዱ ሲገዙ
የነበሩ ነገሥታት ለሥልጣናቸው፤ ግዛቴ ለሚሉት በመቆም በአብዛኛው ለዲያብሎስ ሃሳብና እቅድ በመገዛት
ሲጨፈጭፉ ሲዋጉ ሲገድሉ ሲጋደሉ ኖረዋል። ይህ ሁሉ እየሆነ ዛሬ ላይ ደርሰናል።
በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ ከጥቂት የእግዚአብሔር አገልጋይ ገዢዎች በስተቀር ሁሉም መንግሥታት
የእግዚአብሔርን ሕዝብ፣ ቤተ ክርስቲያንን እውነተኛ እምነትን ሲያጠፉ ሲገሉ፣ ሲያስገድሉ ሲጨፈጭፉ
ኖረው ታሪክ ሆነዋል። በእግዚአብሔር ዘንድ ዛሬ በገነት ያሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ስለፈሰሰው ደማቸው ሁልጊዜ
የእግዚአብሔርን ቅን ፍርድ እየጠየቁ ቆይተዋል አሁንም እየጠየቁ ነው። ጌታም ይቆዩ ፅዋው ይሙላ ብሎ በቆይታ
አስቀምጧቸዋል። ዛሬ ግን ፅዋው ሞላ። ጌታም ቅን ፍርዱን ዛሬ በዚህ መልእክት ገለፀ። በዚህም መሰረት
የዓለም የምናየው ገጽታዋ በውስጧም ያለው ይዘት በዋናው ተዋናይ የሰው ዘር፤ ክፉና የረከሰ የማይጠገን ጥፋት
ምክንያት፣ ፍፁም እንዲለወጥ፤ የነበረው እንዳልነበር እንዲሆን በተለይም ሰው የዘራው የኃጢአት የክፋትና
የትእቢት የክህደት አዝመራ፣ ምድርን ፍፁም ስላበላሸ በእሳት እንዲጠረግ ተወሰነ። በምትኩም መላው ዓለም
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ሥር እንድትገዛና ለእግዚአብሔር ሕዝቦች የተፈቀደው በሐዋሪያው
ዮሐንስ ራእይ ምእራፍ 20 የተጠቀሰው በምድር ላይ ይፈፀም ዘንድ የተነገረው ለሺ ዘመን የመፅናናት ጊዜ
እውን እንዲሆን ተወሰነ።
ዛሬም እያየን ያለው ያላባራው እንዲያውም ታይቶም በማይታወቅ ሁኔታ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ፍጅት
ፅዋውን እንዲሞላ ካደረጉት ምክንያቶች የሚጨመር ሆኗል።

65
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ስማ የሰው ዘር! ስማ የአዳም ዘር! ስሙ ምድርን የከደናችሁ መንግሥታት! ስሙ የዓለም ታላላቅ ሃይማኖት
ተቋሞች! ስሙ ጣኦት አምላኪዎች ዘረኞች! ተብታቢዎች አጋንንት ሳቢዎች ጠንቋዮች ስሙ! ዛፍን ወንዝን
አምላኪዎች ስሙ! የፍጅትና የእልቂት ባለቤቶች ስሙ! ስሙ የእምነት ነጋዴዎች ካባ አጥልቃችሁ ጥምጥም
ጠምጥማችሁ መምህር መምህር እየተባባለችሁ ያላችሁ አሰናካዮች ስሙ! ቃሉን ለንግድ ለሆድ የለወጣችሁ
ስሙ! እውቀታችሁን የምታመልኩ ምእመንን የምትንቁ ስሙ! ከእኛ አልፎ ማንም ስለእግዚአብሔር አይናገር
የምትሉ ስሙ! ዛሬም የጌታን ቁስል የምትወጉ ከኛ ውጪ እግዚአብሔር አይተንፍስ አይናገር የምትሉ ስሙ!
እግዚአብሔርን የማዘዝ ያህል በድፍረት የሰውን አንደበት ለመዝጋት የምትታገሉ ስሙ! ቀጣፊዎች፣ አታላዮች፣
ትእቢተኞች፣ ጨካኞች፣ ሁላችሁም ስሙ! እስላም መናፍቅ ካቶሊክ ቅባት ፀጋ ተሃድሶ ጣኦትን በልብህ
ያነገስክ ሁሉ ስማ! ግብረ ሶዶማውያን ስሙ፣ አዎን ስሙ ምንዝራናን ያነገሳችሁ ስሙ! በግልጽም በስውርም
የቀደመውን እባብ ዘንዶውን ሃሰተኛው ነብይን የምትታመኑ የምታመልኩ የምትሰግዱለት ሁሉ ስሙ! እንግዲህ
ስማ በምድር ያለህ ቆይታ አብቅቷል። ተደምድሟል። ስማ የሰው ዘር አድምጥ ፍርድህ ተከትሎህ መጥቶ
ዛሬ ሊፈፀምብህ ነው። ምንም ጊዜ የለህም። ይግባኝም የለም ሁሉም እድልህ ጥንፍፍ ብሎ አልቋል። ዘመነ
ዲያብሎስ፤ ለሺዎች ዘመናት የነገሰበት ዘመንም አለቀ ተጠናቀቀ፤ የሱ ተጠዋሪ እሱን አንግሰህ የነኖርክ የአዳም
ዘር ሁሉ ቅኑ ብርሃናዊው የእግዚአብሔር ፍርድ እንዲፈፅምህም ተወሰነ። ስለዚህ ዓለምን የከደነ ጨለማ ሁሉ
ተጠርጎ ምድር በብርሃን እንድትሸፈን ታዘዘ። ከፊትህ የመጣው ይህ ነው።
ምድርም ልትፈወስ፣ እውነተኞች የእግዚአብሔር ሕዝቦች፣ በዚህ ጨለማ በነገሰበት ታላቅ የመከራ ዘመን
ፀንተው የተገኙ የሚፅናኑባት ልትሆን ነው። ያለፉት አባት እናቶቻችን በገነት ሆነው በልዑል ቅን ፍርድ ሊደሰቱ
ነው። በመንፈስ አንድነት በልጆቻቸው ሊከብሩ ነው። አንዲቷ እምነት የተወደደችው የፀናችው የተቀጠቀጠቸው
እምነት የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ፀናች አሸነፈች፣ ተተከለች። እውነተኛ ልጆቿን ይዛ በምድር ላይ ሁሉ ትነግሥ
ዘንድ ለቅሬት የታሰቡትን የትንሳኤው ተሸጋሪዎችን አቅፋ ደግፋ በብርሃናዊ አገልግሎቷ ምድርን ልትከድን
እነሆ ታሰበች። ስማ! እየሰማህ ሂድ! ልብ ብለህ አድምጥ አባትህ ዲያብሎስ የቀደመው እባብ ዘንዶው
ሃሰተኛው ነብይ ምድርን ከከደናችሁት ከእናንተ ወዳጆቹ ጋር ወደ ሲኦላችሁ ሂዱ። እሱም ወደ እሥራቱ
አንተም ለመጨረሻው ፍርድ ወደ ምትጠበቅበት ሲኦል ልትሰናበት ተወሰነ ስማኝ! አድምጥ የዲያብሎስ
ተጠዋሪ ሁሉ ደህና ሰንብት!! ከመፅናናት በኋላ በመጨረሻው የፍርድ አደባባይ አንተም ከሲኦልህ እኛም
የተሰጠንን የመፅናናት ጊዜ ጨርሰን ከገነት ከአባቶቻችን ጋር ከአባታችን ከመድኃኔዓለም እንዲሁም ከእናታችን
ከድንግል ጋር ከምንወዳቸው በዘመናችን ሁሉ ሲራዱን ከኖርት ቅዱሳን ሊቀ መላእክት ጋር በእግዚአብሔር
የፍርድ ወንበር ከቀኝ በኩል ቆመን ታየናለህ! ስማ እየሄድክም ቢሆን ለመጨረሻ ልንገርህ! ምን ይደረግ
አንተንም ከጌታ የፍርድ ዙፋን /ወንበር/ ከግራ ቆመህ ለእሳት ልትጣል ልትሰናበት ስትል እናይሃለን ከዘለዓለም
እስከዘለዓለም ከዚያ ወዲያ አንተያይም። አንተም ወደታላቁ የገሃነም እሳት ለዘለዓለም ስቃይ መሄድ ግድ ነው።
እኛ ደግሞ የሚወደን አባታችን የናፈቅነው የአብርሃሙ ሥላሴ ወደአዘጋጀልን መንግሥተ ሰማይ በፈንጠዝያ
እንገባለን። ከዘለዓለም እስከዘለዓለም እንደ ክዋክብት እናበራለን። ለዘለዓለም ክብሩን እያወደስን እያመሰገንን
እንደመላእክት እንሆናለን። መቼም አታምንምና አታዳምጥም ልብህ በጥርጥር ተሞልቷልና ይህንን ስንነግርህ
እንደምታፌዝ ለሌላ ጥፋት እንደምትዘጋጅ እርግጥ ነው። ግን ስማ! አብቅተሃል! ተደምድመሃል! አዋጁም
የመጣው አንተንና አባትህ ዲያብሎስን ሊደመድም ነው።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስንል ምን ማለታችን ነው!

በመላው ዓለም በአሁኑ ሰዓት ፀንተው ቆመው የምናያቸው 205 ገደማ አገሮች አሉ። ሁሉም እንደ
የአቅማቸው ሕገ መንግሥት ደንግገው ሕዝባቸውን ይገዛሉ። እኛም የኢትዮጵያ ሕዝብ በዓለም እንግዳ በሆነ
ሕገ መንግሥት ለ30 አመት እስከአሁኑ ስአት ድረስ እየተገዛንበት ነው። በጉልበተኛ የተጫነ ሕግ። እነ አሜሪካ

66
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

እነ እንግሊዝ በወቅቱ ዲያብሎስ በመረጣቸው ፈረሶቹ በወያኔዎች እንድንገዛ እንዲያደርጉ ለሁለቱም ኃያላን
አሽከሮቹ በሰጠው ትእዛዝ መሰረት እነሱ በተከሉት ሰይጣናዊ አገዛዞች እየተሰቃየን አለን።
እነሆ ሁሉም እንደሚያውቀው በዚህ ሕገ መንግሥት አገራችን እንድትፈርስ በተደረገ ሴራ እየታመሰች
ትገኛለች። መላው ዓለም ተስማምቶ አሁን እየኖረበት ያለው ህገ መንግሥት ሁሉም አገር ለኔ ይሆነኛል
ብሎ ቀርፆ እየኖረበት ነው። ይሁንና የቆመው መንግሥት ለማንሳት አንዳንድ የሕዝብ አመፆች ሲከሰቱ
ወይም በተለያዩ ጠላቶች መንግሥት ሊያፈርሱ ከተነቃነቁ መንግሥት እራሱን ለመከላከል የነበረውንም አገዛዝ
ለመመለስ የሚወስደው የመጨረሻው እርምጃ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅና ባለው ጦር፣ ፖሊስ፣ የደህንነት
ኃይል ሁሉንም ተፃራሪ ኃይል ተቆጣጥሮ ወይም ደምስሶ የያዘውንም ለፍርድ አቅርቦ በአደጋ ውስጥ የወደቀውን
ስርአቱን የሚታደግበት መንገድ ነው።
ዛሬ ግን በዚህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የምታየው ከተለመደውና ከምታውቀው ለየት ያለ ነው። የአዳም ዘር
አድምጥ! ምንድነው የተለየው በል! አንተ የምታውቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሁሌም የምትሰማው አገር
በችግር በተፈጥሮ አደጋ በአመፅ ስትታመስ ወይም መቋቋም አቅቷት ሥርአተ አገዛዟ ሊፈርስ ሲዳዳው ባለው
መንግሥት የሚታወጅ አገርንና ስርአተ አገዛዙን የማዳን እርምጃ ነው። ያኔ መብት ማስጠበቅ የለም። መላወስ
መንቀሳቀስ የለም ሁሉም የተገደበና በቁጥጥር ውስጥ ሆኖ የሚያከናውኑት ሕይወት ይሆናል። ይህ ነው በአንተ
እውቀት ውስጥ ያለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ።
ዛሬ የምትሰማው የኛ አዋጅ ግን ይለያል። አዋጁ የመነጨው ወይም የታወጀው ከማታየው ከማትዳስሰው
በአንተ ክህደትና ንቀት ከረሳኸው እግዚአብሔር የመነጨ ነው። አንተን ፈጥሮ ምድርንም ሰማይንም እንዲሁ
ፈጥሮ የሚታየውንም የማይታየውንም ሕልው አድርጎ፤ በምድርም አንተን የአዳምን ዘር በአምሳሉ ፈጥሮ፤
ከዚች ምድር ቆይታህ በኋላ ደግሞ በክብሩ ዙሪያ እንደ ክዋክብት አንድትደምቅ የስሙ አወዳሽ ቀዳሽ እንድትሆን
በፍፁም ፍቅሩ ወዶህ ተክሎህ ነበር። አንተ ምን መለስክለት ስለፍቅሩ ጥሪ ስለመዳንህ ስለከፈለው የሕይወት
ዋጋ አንተ ምን መለስክለት ምን ከፈልከው ባኖረህና በደገፈህ በረዳህ ለችግርህ ለደረሰለህ ከጥፋት ሁሉ
ለታደገህ በፍፁም ፍቅር ወደ ፍቅሩ ሊሰበስብህ ብዙ ሺ ዘመናትን የጠበቀህን አምላክ ምን መለስክለት አዎን
አይካድ አንተም አትክድ። ያፀናኸውን አቋምና የተመላለስክበትን ሕይወት ታውቀዋለህ። ንቀትህን ክህደትህን፤
አለመፀፀትክን አመፅህን አልፈህም እሱ የፈጠረውን ዲያብሎስን አምላክህ ማድረግህን ታውቀዋለህ። ትእግስቱን
አጠንፍፈህ በልተህ ጨርሰሃል ። በመሆኑም እሱን ባታየውም እኛ ደግሞ ፈልገነው በእምነት አይተነው በፍቅሩ
ኖረናል። ፍርዱ እንደሚገለጥ እኛም በእምነታችን እንደምናተርፍ ተረድተን ጠብቀነዋል። ለኛ እንግዳ አይደለም
የታመነ አምላክ በመሆኑ ይህ እንደሚሆን በእምነት አሻግረን ተመልክተናል። ዛሬም እነሆ ሆኗል። ይህ አዋጅ
በጆሮህ ደርሶም እንኳ አሁንም አታምንም። ይህ መልእክት በመላው ዓለም እንደሚደርስ እርግጥ ነው። አንተ
የጠፋህ ትውልድ አትሰማም። ኮረና አንድ የበሽታ ዘር ምን ያህል አሳርህን እንዳሳየህ አይተኸዋል። አሁንም
ቫክሲን እያልክ ትራወጣለህ። ቁጥር አምስት መልእክት ላይ ምን እንደሚል አስታውስ ገና ብዙ ቫይረስ ይፈላል
አለ እንጂ ኮረና ብቻ ይመጣል አላለም። ስለዚህ መከራህ ምልክት ሰጠ እንጂ መቼ መጣ?
ከላይ እንደተገለፀው ይህ አዋጅ ምድራዊ ገዢዎችህ ካለማመዱህ በፍፁም ይለያል። በምን በምን ይለያል።
በመጀመሪያ የአዋጁ ባለቤት በሥልጣኑ ያወጣው አካል ምድርና ሰማይን የዘረጋው የፈጠረው ኃያሉ እግዚአብሔር
ነው። አዋጁን እንዲገልፁ እነማን ታዘዙ አዎን የታመኑ ባሮቹ። ብርሃኑን በቅርብ ሲፈነጥቅ የምታየው ኢትዮጵያ
የዓለም ብርሃናዊው መንግሥት የሚመሩት የሥላሴ ቀዳማይ ባሮች በፊርማቸው በደማቸው አፅድቀው አተሙበት።
የኛ አዋጅ ይለያል ከለመድከው ጋር አይመሳሰልም ያልንህ በዚህ ነው። አንተና መሰሎችህ የምታውቁት
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመንግሥታት የሚታወጅ ኃይልና ጉልበት ያላቸው በጦር ኃይል ፍላጎታቸውን
ለመፈፀም የሚችሉበትም የሚያደርጉትም ነው። ከላይ እንደገለፅኩት የኛ ይለያል። ከማታየው ከማትዳስሰው

67
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ከፈጠረህ ከእግዚአብሔር ፈቅዶም ፈጥሮም በዚች ምድር እንድትኖር ከፈቀደልህ የወጣ አዋጅ በመሆኑ ይለያል።
የሚያኖርህም በቃ ካለ የሚወስድህም በሁሉ ነገር ላይ በሞትም ጭምር ላይ ሥልጣን ያለው አምላክ ያፀናው
አዋጅ ነው።
እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብፅ ምድር ከፈርኦን የጭካኔ አገዛዝ ቃል በገባው መሰረት ነፃ ሊያወጣቸው
መጣ። ቃሉን አክባሪው ልዑል በታመነ ባሪያው አማካኝነት እስራኤላውያንን ነፃ ለማውጣት ሲንቀሳቀስ የላከው
ሙሴንና አሮንን ነበር። ይሁንና በተከታታይ ከአሥር ያላነሱ መቅሰፍቶች በግብጽ ሕዝብ ላይ ሲወርድበት ፈርኦን
ልቡን አደነደነ እንጂ አልሰማም። የእግዚአብሔርን ቃል በሙሴ በኩል ሲናገር ሕዝቤን ልቀቅ ያገለግለኝ ዘንድ
ነበር ያለው። በእንቢታው የፀናው ፈርኦን በተደጋጋሚ በትእቢቱ ቢገሰልም የመጨረሻው ክፉ አስደንጋጭ ቁጣ
መጣ። የግብፅ ምድር በኩራት ሁሉ የሰውም የእንስሳውም በሞት ተከደነ። ራሱ የፈርኦንም ቤት ሞት ነገሠበት።
ያኔ መቋቋም ያቃተው ፈርኦን ወርቅና እንቁን ገብሮ እስራኤላውያንን እጅግ ፈርቶ ተንቀጥቅጦ ለቀቀ።
ዛሬም እግዚአብሔር ደጋግሞ በተለያዩ ቅጣቶች ዓለምን ቢመክር ቢገስፅ ሕዝቤንና የምወደውን የተዋህዶ
ኦርቶዶክስ እምነት ከጨበጠው ሕዝቤ ጋር ያገለግለኝ ዘንድ ልቀቅ ብሎ በባሪያው በኩል ከ15 አመታት ላላነሰ
ጊዜ ደጋግሞ እርምጃ በመውሰድ ፈቃዱን ግልፅ አደረገ። ነገር ግን በመላው ዓለም ስሩን የተከለው ዲያብሎስ
ሁሉንም ዓለም ሁሉንም የአዳም ዘር በቁጥጥሩ ሥር ስላደረገ አልሰማም። ኢትዮጵያን ተዋህዶ እምነትን
አልለቅቅም አለ። ጭራሽም መከራዋን እጅግ አከበደ። በመሆኑም ዓለም ያላየውን ያልሰማውን ይሆናልም ብሎ
በፍፁም በሕልሙም የማያየውን መከራ እነሆ ተጭኖ መጣ!! በዚህም መሰረት እነሆ ከፀባኦት ትእዛዝ ወጣ!!
»» አዋጁ ምን ያስፈፅማል!
»» ከየት ይመነጫል!
»» እነማን ያስፈፅሙታል!
»» ግቡስ ምንድነው!
1 – ይህ አዋጅ በመላው ዓለም ያለው የአመፃ ትውልድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን የካደ የማይሰማ የማይለማ
ትውልድን የሚያስወግድ ሲሆን በምትኩም ለሥላሴ የታመነችው እምነት ተዋህዶና በሷ ሥር ሆነው ታላቅ
መከራና ስቃይን ለብዙ ዘመናት የተቀበሉትን በፈጣሪያቸው የታመኑትን ምድርን እንዲወርሱ እንዲተከሉ
ያደርጋል። ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ትሆናለች። ምድር ከዚህ በታች ባሉ የከበሩ የኪዳኑ ቃሎችና በአረንጓዴ
ቢጫ ቀዩ የቃል ኪዳን ሰንደቅ ትሸፈናለች። የሚከብሩት ቃሎች
ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመሥገኛ ምድር
ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ
እነዚህ ኃይለ ቃሎች በየትኛውም የምድር ገጽታ ላይ ከፍ ብለው ይነግሳሉ ይከብራሉ። የእግዚአብሔር ስም
ያለማቋረጥ በምድር ሁሉ ላይ ይመሰገናል። እንዲሁም ድንግል ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት፤ ቅዱሳን ሰማዕታት
አባቶቻችን እናቶቻችንም እንዲሁ ይከብሩባታል።
2 – አዋጁ ከየት ይመነጫል? ይህ አዋጅ የልዑልን ፈቃድ ይገልፁና ያሳውቁ ዘንድ በታመኑ የልዑል ባሮችና
እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ ይነግሥ ዘንድ ፈቃዱ በሆነው በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በኩል
እንዲገለፅ በወሰነው መሰረት የተገለፀ ነው። ምንጩም የልዑል ፈቃድ ነው።

68
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

3 – አዋጁን እነማን ያስፈፅሙታል? ይህንን አዋጅ ያስፈፅሙ ዘንድ እጅግ የከበሩት ቅዱሳን ሊቃነ
መላእክት
ሀ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል
ለ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል
ሐ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል
መ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል
ሰ/ ሊቀ መላአክት ቅዱስ ራጉኤል
ረ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል
ሠ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሳቁኤል
ሸ/ ሊቀ መላአክት ቅዱስ አፍኒንኤል
ቀ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሰዳክኤል
በ/ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሱርያል
ተ/ ሊቀ መላእክት ሰላትያል
ከነሠራዊቶቻቸው ሙሉ በሙሉ ምድርን ያጠፉትን በኃጢአት ባሕር ተነክረው ንስሓን ንቀው እግዚአብሔርን
ክደው ምክርን ተግሳፅን ንቀው በትእቢት ተሞልተው በዲያብሎስ በቀደመው እባብ በዘንዶው በሃሰተኛው ነብይ
ተማምነው እየተገሰሉ ያሉትን ነገሥታት ከነሕዝባቸው በታላቅ ቁጣ የሚጠረጉ ናቸው።
4 – ግቡስ ምንድነው? አዎን ግቡ ቀደምም ተገልጿል። አሁንም ግልፅ እንዲሆን እግዚአብሔር ከዘመናት
በፊት ጀምሮ በስሙ የታመኑ ሕዝቦችን ይመለከትና በልቡም ሲያኖራቸው ቆይቷል። ከህገ ልቡና ጀምሮ በሕጉም
ዘመን አሁንም በወንጌሉ ዘመን በታላቅ ፈተና የፀናችውን ተዋህዶንና የፀኑ ሕዝቦቿን ወደደ። መረጠ አፀደቀ።
አከበረም። በመሆኑም ዓለምን በሙሉ በምርኮ ለዚችው ለተናቀችው ኢትዮጵያ ለከበረችውም የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሰጠ። በመሆኑም ይህ ይፈፀም ዘንድ ግድ ሆነ። ግቡም ይኸው ነው።
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በመላው ዓለም ላይ ማንገሥ ነው።
5 – ለትንሳኤው ዘመን የተመረጠውን ስንዴውን ከገለባው መለየት፤ ገለባውን ለእሳት መስጠት፤ ለቀደመው
እባብ፣ ለዘንዶው፣ ለሃሰተኛው ነብይ የሰገዱትን፣ ያመለኩትን፣ ምልክቱን የተቀበሉትን ወደ ሲኦል እንዲሰናበቱ
ማድረግ ነው።
6 – ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ፡ አገራችን ኢትዮጵያ ቅድሚያ ነፃ የምትወጣ አገር ናት።
በመሆኑም የሚወሰደው እርምጃ ፈጣንና ቶሎ የሚፈፀም ነው። ያለው የኢትዮጵያ መንግሥትም በዚህ አዋጅ
መሰረት ተሰናብቷል። በቀደሙት መልእክታት የታዘዘው ቅጣት ሁሉ ይፈፀምበታል።
7 – አፍሪካ እንዲሁ እንደ ኢትዮጵያ ከሚፈጠረው ሁኔታ ጋር አብራ ትፀዳለች። በቅድሚያም የኢትዮጵያ
አካል መሆኗ ይረጋገጣል። መካከለኛው ምሥራቅም እንዲሁ በተፃመር ይፀዳል ይጠረጋል። በከፊልም የኢትዮጵያ
አካል ይሆናል። በኢትዮጵያም ሆነ ወደ ኢትዮጵያ በግዛትነት የሚካተቱ የአፍሪካ አገሮች በመላው ዓለም
እንደሚፀናው አዋጅ በኢትዮጵያም የፀና ይሆናል። ያለኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃናዊ መንግሥት ማረጋገጫ
ሰነድ ማንኛውም እንቅስቃሴ የተከለከለና ወዲያው ለቅጣት የሚያበቃ ነው። መንቀሳቀስ የሚቻለው ከኢትዮጵያ
የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ማረጋገጫ በማግኘት ብቻ ነው። በሁሉም የኢትዮጵያም የአፍሪካም የመላው
ዓለም ሕዝብ ላይ የሚፈፀም ነው። በመላው ዓለም ያሉ እንዲሁም በአገር ውስጥ ያሉ የትጉሃን መማክርት የፅዋ
69
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ማህበራት ከዚህ ከኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃናዊ መንግሥት በሚሰጣችሁ መመሪያ መሰረትና ቀድሞም በተረዱት
አግባብ በተሰጣቸው መታወቂያ መሰረት እየተንቀሳቀሱ መንፈሳዊ አገልግሎትን ይሰጣሉ።
8 – የተቀረው ዓለም እነእንግሊዝ፣ እነአሜሪካ፣ መላው አውሮፓ፣ መላው ኤሺያ፣ መላው አፍሪካ፣ መላው
ላቲን አሜሪካ፣ መላው አውስትራሊያና ዙሪያዋ ያሉ አገሮች በጠቅላላው መላው ዓለም በታላቅ መቅሰፍት
በታላቅ ቁጣ በታላቅ እሳት ይመታል ይጠረጋል። አንዳንድ ኃያል ነን የሚሉ አገሮች ከነካቴውም ከምድረ ገጽ
ይጠፋሉ።

የሚፈሱት ቁጣዎች በምድር ላይ ምንን ያስከትላሉ –

1 – በመላው ዓለም ባሉ ሁሉም አገሮች ላይ በብዙ መቶ እጥፍ የሚበልጥ በፈርኦንና በግብፅ ሕዝብ ላይ
የነገሰው ሞት ዛሬም ባለው መላው የሰው ዘር ላይ ይነግሳል። ሞት የማይነግሥበት አንድም ቤት፣ ሥፍራና ቦታ
የለም። በግንባሩ ላይ ምልክት ካለውና በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በተሠጠው መመሪያ መሰረት
ምልክቱን የሚጠቀሙ ከኛ ዘንድ የተመዘገቡ እኛ ባንመዘግባቸውም በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በየባእታቸው
የተመዘገቡ ለአገልግሎት መታወቂያ የወሰዱ በጥቅሉ በእኛ ወገኖች ከተሰበሰቡ ካልሆነ በስተቀር ከሞት ጋር
የማይገናኝ የለም።
2 – ከታላቁ ቁጣ ፍሰት መጀመር ጀምሮ በመላው ዓለም በቤቱም በደጁም በውጪውም በምድሩም
በጫካውም በገደሉም በተራራውም በዋሻውም በአየሩም በሰማዩም ሞት ይነግሳል። ለጥፋት ሲተጉ የኖሩትን
የምድር ኃይላት በሙሉ ይጠርጋል። ያስጨንቃል ይጠርጋል፣ ያሰቃያል። አስጨንቆና አስጠብቦ ተለምኖም
ይወስዳል። ይህ ሁሉ በሰው ልጅ ላይ በምሕረት ከታየው በስተቀር ይፈፀማል። እንስሶችንና ተክሎችን
አይጎዳም። ከላይ እንደገለፅኩት ትሁት ቅን የዋህ ሰው ይድናል።
3 – ማንኛውም ሰው በምሕረት ከታየው በስተቀርና እንዲንቀሳቀስ ከተፈቀደለት በስተቀር ማንም ሆነ ማንም
ለመንቀሳቀስ አይችልም። ፈቃጁ ደግሞ ማነው ለሚለው የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት መሪዎች
ሲሆኑ የነሱ ፊርማ ያረፈበት መታወቂያ ወይም ደብዳቤ ያለው ሰው መንቀሳቀስ ይችላል። ፈቃድ ለመጠየቅ
ምሕረት ለመጠየቅ እጅ ለመስጠት ለሌሎችም ጉዳዮች የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥትን መሪዎች
እንዴት ማግኘት ይቻላል ለሚለው ደግሞ፤ በመላው ዓለም የተቋቋሙ የትጉሃን መማክርቶች እንዲሁም የፅዋ
ማህበር አባላትን ማግኘትና መጠየቅ ይቻላል። እነሱ ከኛ ጋር የሚገናኙ /የሚያገናኙ/ ድልድዮች ስለሆኑ
መፍትሄው ይህ ነው።
4 – ማናቸውም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች የተመዘገባችሁም ባትመዘገቡም በኛ ዘንድ የምትታወቁም እንዲሁም
እግዚአብሔር ከሁሉ ከልሎ /ደብቆ /ያቆያችሁ ሁሉ ባላችሁበት ባእታችሁ የኢትዮጵያን ሰንደቅ /አረንጋዴ
ቢጫ ቀዩን/ በደጃችሁ መስቀል ግዴታ ነው። አብሮትም ከስሩ የሚጠቀሱ የከበሩ የኪዳኑን ቃሎችን ፅፋችሁ
አብራችሁ ትሰቅላላችሁ። ስማችሁንና የተመዘገባችሁበትን ቁጥርም ታሰፍራላችሁ። ላልተመዘገባችሁ እምነቱ
አለኝ የምትሉ፣ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክታት በእርግጥ የምታምኑበት፣ በትክክል የተዋህዶ ኦርቶዶክስ
ልጆች የሆናችሁ፣ በንስሓ እራሳችሁን ከዓለም ጉድፍ የጠበቃችሁ በእምነት ልክ እንደተመዘገቡት አድርጉ
ማን ያውቃል እግዚአብሔር ስለእምነታችሁ ስለቅን ልባችሁ ስለ የዋህነታችሁ ቀደምም ስለአለመስማታችሁ
እራርቶላችሁ መድኃኔዓለም ድንግል ሊታደጓችሁ ይችላሉና በዚህ ምክራችን ይህ ነው።

70
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ቃሎቹ
ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመሥገኛ ምድር
ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ
የሚሉ ናቸው።
5 – በታላቁ የቁጣ ፍሰት በመላው ዓለም ያለ ማናቸውም የትራንስፖርት /አውሮፕላን፣ መርከብ፣ መኪና፣
የእንስሳም ማጓጓዣ ሁሉ / አገልግሎት በሙሉ ይቆማል። ቢንቀሳቀስም ወዲያው ይጠረጋል። ማናቸውም
ማምረቻዎች፣ ፋብሪካዎች አገልግሎት ሰጪዎች የጤና ተቋሞች የግልም የመንግሥትም ድርጅቶች መሥሪያ
ቤቶች ዓለም አቀፍ ተቋሞች ድርጅቶች በሙሉ ይከረቸማሉ። የሚጠፉትም ይጠፋሉ። ለመንቀሳቀስም
ለመሥራትም ለሁሉም በመላው ዓለም የፀናው ያለመንቀሳቀስ ትእዛዝ ሲነሳ ብቻ ነው ለመንቀሳቀስ የሚቻለው።
ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በሚሰጥ ጊዜያዊም ሆነ ቋሚ የፈቃድ ትእዛዝ ብቻ ነው ለመንቀሳቀስ
የሚቻለው።
6 – በኢትዮጵያ የሚተከለው የሚነግሰው ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት እዚህ በኢትዮጵያ
በፈቀደው ጎጆ ወይም ማናቸውም አናሳ ቤት ሆኖ አመራሩን ውሳኔውን ትእዛዙን ፍርዱን ያከናውናል። ቤተ
መንግሥት ያማረ ሕንፃ አያስፈልገውም። ዓለም በእግዚአብሔር ፊት ኢምንት ብናኝ አቧራ እንደሆንክ በእርግጥ
ታውቅና ትመሰክር ዘንድ በእኛ በድሆች፣ በተናቅን፣ በተጠላን፣ እውቀትም ሀብትም ጥበብም ክብርም በሌለን
ኃጢአተኛ ደካማ የመድኃኔዓለምና የድንግል ልጆች ፊት ቀርበህ ትዳኛለህ ትታዘዛለህ ግዴታህንም ፈቅደህ
ወይም ተገደህ ትፈፅማለህ። ሁን የተባልከውን ትሆነለህ
7 – በኢትዮጵያ እንደመኖራችን መጠን እኛንም ለማግኘት ሆነ ወይም በግል ጉዳይ ለመንቀሳቀስ
ወደውጪም ለመውጣት ለመግባት የግድ መጓጓዣ ስለሚያስፈልግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ በመላው
ዓለም እንዲንቀሳቀስ ይደረጋል። አየር መንገዱ ከኛ የተሰጠውን የቃል ኪዳን ምልክት ሰንደቁንም የቃል ኪዳን
ቃሉንም በውጪ አካሉ ላይ በሚታይ መልኩ መለጠፍ አለበት። ይህም ብቻ አይደለም ከኛ ዘንድ የተፈረመበትን
ደብዳቤ መያዝ አለበት። የሌሎች አገሮች የትልቆቹም የትንሾቹም አየር መንገዶች በሙሉ በራሳቸው አርማ
ወይም ሰንደቅ መንቀሳቀስ አይችሉም። በራሳቸው አገር ውስጥም መንቀሳቀስ አይችሉም። ለመገልገልም ቢሆን
የሚችሉት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ይሆናል። የነሱ አየር መንገድ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሥር
ሆኖ በሱው እየታዘዘ በሚሰጠው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደብዳቤና የቃል ኪዳኑ ምልክት ብቻን በማድረግ
መንቀሳቀስ ይችላል። ታምኖበት ሲፈቀድለት ብቻ ነው ይህም የሚሆነው። ፈቃጁም የኢትዮጵያ የዓለም
ብርሃናዊ መንግሥት ብቻ ነው።
8 – በመላው ዓለም የአየር የየብስ የባሕር ጉዞና መገናኛ ሁሉ ይቆማል። በማናቸውም የራሱ መንገድ
መንቀሳቀስ አይቻልም። ሁሉም ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ኢንዱስትሪዎች ማምረቻዎች የኤሌከትሮኒክስ
መገናኛዎች በሙሉ ይቆማሉ። ደጋግመን እንደገለፅነው ሰው ሁሉ ለመነቃነቅ አይቻለውም ከኛ ፈቃድ ካላገኘ
በስተቀር። አንዱ አንዱን አይረዳም። በሁሉም ስፍራ ሞት ይነግሳል። ደጋግመን እንደገለፅነው በእያንዳንዱ
የአዳም ዘር በትኛውም የዓለም ስፍራ ይኑር በማናቸውም ባለበት ስፍራ ሁሉ ሞት ይነግሳል። ከባለምልክቶች
በስተቀር። እነሱም በቁሶቹም ለመገልገል ይችላሉ ለራሳቸው ብቻ!
9 – በመላው ዓለም የየትኛውም አገር መንግሥት መንቀሳቀስ አይችልም። እንደመንግሥትም መሆን
አይችልም። በጠቅላላው ሁሉም የሰው ዘር በማናቸውም የኢኮኖሚ የማህበራዊ የወታደራዊ እንቅስቃሴ መሳተፍም
71
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ማድረግም አይችሉም። በአገር ውስጥም በውጪም በማናቸውም ጉዳይ ያለ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ወይም
እራሱ ፈቅዶ ከወከለው ሰው ፊርማና መታወቂያ ወይም ሰነድ ውጪ መንቀሳቀስ አይቻልም። ሁሉም የአዳም
ዘር መዳንም ከመጣው ቁጣ መትረፍም የሚችለው እግዚአብሔር ትረፍ ካለው ብቻ ነው። ተርፎም ቢሆን
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት መሆኗን መሪዎቿም የሥላሴ ባሮች መሆናቸውን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አንዲቷ እውነተኛይቱ እምነት አሸናፊዋ እምነት መሆኗን ከልቡ አምኖ መቀበልና
መፀፀት ይገባዋል። በንስሓም እራሱን ሊያስተካክል ግድ ይለዋል። የዳነውም በእግዚአብሔር ቸርነት መሆኑን
አውቆ ሥላሴን ድንግልን ሊያመሰግን ይገባዋል።
10 – በኢትዮጵያ አገራችንና በጎረቤት አገሮች ሁሉ አዋጁ መተግበር ሲጀምር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ
ማድረግ አይቻልም። እንቅስቃሴ ለማድረግ ከኢትዮጵያ የዓለሙ ብርሃናዊ መንግሥት የሚሰጥ ሰነድ ግዴታ
ያስፈልጋል። ደጋግመን የምናነሳው ግድ መሆኑን ሁሉም እንዲያውቀው ስለፈለግን ነው።
11 – በመላው ዓለም ያሉ የየብስ መገናኛዎች ባቡር፣ ከባድ የጭነት መኪኖች፣ ትላልቅ የሕዝብ ማመላለሻዎች፣
ማናቸውም የተቋማት የትርንስፖርት አገልግሎት ሰጪ መኪናዎች፣ የግል የንግድ ትናንሽ መኪናዎች ሁሉም
ተሸከርካሪዎች በምንም መንገድ ያለ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ፍቃድ ወይም ትእዛዝ መንቀሳቀስ
በፍፁም አይቻልም። የባሕር ትራንስፖርትም በሙሉ መንቀሳቀስ አይችልም። ከተንቀሳቀሰ ወዲያው ይወገዳል።
በባሕር ላይና ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ለወታደራዊ አላማ የተሰማሩ በሙሉ ይወገዳሉ።
12 – በሕዋው ውስጥ የተሰቀሉ ማናቸውም ሳተላይቶች ለወታደራዊ መረጃ፣ ለስለላ፣ ለአጥቂነት ለሌላም
አጥፊ ስምሪት ያላቸው ሳተላይቶች፣ ቋሚ ስቴሽኖች በሙሉ ይወገዳሉ።
13 – በመላው ዓለም ካሉ አገሮች ውስጥ ኃያል ነን የሚሉ ኒዩክለር ኬሚካል፣ ኒውትሮን፣ ባዮሎጂካል
መሳሪያ የታጠቁ አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፤ ቻይና፣ ራሺያ፣ ሕንድ፣ ፓኪስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኢራን፣
እስራኤል እነዚህ በግልፅ ዓለም ያወቃቸው ኒዩክለር ታጣቂዎች በመጀመሪያ በከባድ ጠረጋ ውስጥ የሚወድቁ
ናቸው። እድሜም ጊዜም ፋታም የማይሰጣቸው ናቸው።
14 – ቅድመ ሁኔታ ––
ማናቸውም አገር ኃያል ይሁን ደካማ ወይም መካከለኛ ጠረጋው ሲጀምረው ለመተንፈስ፣ እጅንም
ለመስጠት፣ ፈቃደኛ ሲሆን /ሕዝቡን አማክሮና በገዛ አገሩና በዓለም አቀፍ ሕግ አለኝ በሚለው/ አስወስኖ
ያስወሰነበትን ሰነድ ይዞ ልኡክ አዘጋጅቶ ለትጉሃን መማክርቶች በማሳወቅ እጁን ለመስጠት የሚንቀሳቀስበት
ፈቃድ ይሰጠዋል። መጥቶ ማረፍ የሚቻለው በጎረቤት አገር በኬንያ፣ በጅቡቲ ብቻ ይሆናል። እዚያ ሆኖ
የመግቢያ ትእዛዝ እስከሚሰጠው ይጠብቃል። አሊያም እዛው ባለበት ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መንግሥት
የተላኩ መልስ ይሰጡታል። በተሰጠው መልስ መሰረት የሚሰጠውን ግዴታ ሲፈፅም ቀጣዩ እርምጃ ምን
እንደሚሆን ይገለፅለታል። በዚህ መልክ የተከላ የነቀላ የሽግግር ተግባሮች ይከናወናሉ። ፈቃደኛ ላልሆነ አገርና
ሕዝብ አገሩ ባዶ እስከሚቀር ድረስ ፍፁም ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ ይደረጋል።
ማናቸውም አገር ውስጥ ያለ የዚያ አገር ዜጋ በግሉ እጁን ለመስጠት ወደ ፍርድም ለመቅረብ ሲሻ
ባለበት አገር ካለው በኛ የተወከለ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሄዶ ማመልከቻውን ፅፎ ወረፋ ማስያዝ ግድ ይለዋል።
ኤምባሲዎች በትክክል የማያስተናግዱ ከሆነ በዚያ አገር ወይም በዚያው አገር ካሉ የኢትዮጵያ ወይም የሌላ አገር
ዜጋ የትጉሃን መማክርት ዘንድ ማመልከቻን አቅርቦ ወረፋ አሲዞ ውሳኔውን መጠበቅ ይችላል። እንደ ድርጅትም
እንደ ማህበረሰብም ተወካይ በማዘጋጀት ይህንኑ አካሄድ መከተል ይቻላል።
የአብርሃሙ ሥላሴ ስም ይክበር ይመስገን! ድንግል ስሟ ይክበር ይመስገን
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በ ታህሣሥ 21 ቀን 2013 ዓ.ም ታወጀ!! ከየካቲት 21 ቀን 2013

72
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

ዓ.ም በኋላ በማናቸውም ጊዜና ወቅት ሥላሴዎች ብቻ በሚያውቁት ማንም በማያውቀው ጊዜ እርምጃውና
ጠረጋው ይጀምራል። የታለመለትን ግብ ሳይፈጽም በምንም መልኩ አይቆምም። ይህም በሥላሴ ባሮች ወይም
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ቀዳማይ አገልጋዮች ተማፆኖና ልመና ብቻ ሊቆም ይችላል። ከዚህ
ያለፈ ምንም አይነት መፍትሄ የለም።
በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ከሥላሴ በተሰጠ ሥልጣን መሠረት በታህሣሥ 21 ቀን 2013 ዓ.ም
ታወጀ ቀዳማይ አገልጋይ የሥላሴ ባሮች

1 – ስም ገብረ መድህን፤ ፊርማ –––––––––––––––––፤ የጣት አሻራ ––––––––––––––––––

2 – ስም ሰይፈ ሥላሴ፤ ፊርማ –––––––––––––––––፤ የጣት አሻራ –––––––––––––––––––

3 – ስም ፍሬ ሰንበት፤ ፊርማ ––––––––––––––––––፤ የጣት አሻራ ––––––––––––––––––

ለእኔም –– ዘመኑ ቀርቧልና የዚህን መጽሐፍ የትንቢት ቃል በማህተም አትዝጋው፤


አመፀኛው ወደፊት ያምፅ እርኩሱም ወደፊት ይርከስ፤ ጻድቁም ወደፊት ጽድቅ
ያድርግ ቅዱሱም ወደፊት ይቀድስ አለ። እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም
እንደሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከኔ ጋር አለ። አልፋና ኦሜጋ ፊተኛውና
ኋለኛው መጀመሪያና መጨረሻው እኔ ነኝ።
ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆቿም ወደ ከተማይቱ
እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው። አምስቱ ውሾች ግን ከዚያች
አገር ወጥተው ይሄዳሉ። እልሂም ሥራይን የሚያደርጉ፣ ሴሰኞች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣
ጣኦትን የሚያመልኩና የሃሰትን ሥራ የሚወዱት ሁሉ ናቸው። እኔ ኢየሱስ በአብያተ
ክርስቲያናት ዘንድ ይህን እንዲመሰክርላቸው መልአኬን ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርና
ዘር ነኝ። የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ። መንፈሱና ሙሽራይቱም ና ይላሉ።
የሚሰማም ና ይበል! የተጠማም ይምጣ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው
ይውሰድ። የዮሐንስ ራእይ ም፣ 22 ፡ 10 –– 17

በስተመጨረሻ ጥብቅ ማሳሰቢያዬና ምክሬ /ለሁሉም የአዳም ዘር/ ይህ ነው። ከላይ የተመለከታችሁት ቁርጥ
ያለው ፍርድ መጥቷል። ሊፈፅምህም ደጅህ ቆሟል። ማንም ሆንክ ማንም ከሚጠርግህ ሞት አታመልጥም።
ምናልባት ትንሽ ጭላንጭል ሆና ብትረዳህ የምልህ ይህንን ብቻ ነው። ስማኝ!! ምንም አይነት ሰውኛ ዘዴህን
እንደለመድከው አታልም። እንኳን አንተ የነዳህም ዲያብሎስ አያመልጥም። ስለዚህ እሚጠቅምህ ብዬ በግሌ
የምመክርህ –– ራስህን በእግዚአብሔር እጅ ጣል ራስህን ዝቅ አድርግ ከልብህ ተፀፀት ታደገኝ በለው። ቃልም
ግባ እውነትህን ብቻ እሰማለሁ እታዘዝህማለሁ ቅን ባሪያህም እሆናለሁ። ማረኝ አሻግረኝ ስለድንግል ስትል
ስለከበሩት ሊቃነ መላእክት ስትል ብለህ ተንበርከክ ለምነው! በብርቱ ለምነው! ቁጣው የገነፈለ ብርቱ እሳት
ነውና ከፊትህ ያለው! እምመክርህ ይህንን ነው። ወገኔ! እንደኛው ብትሻገር ብዬ በመመኘት ነው የምነግርህ!
እኛ የእግዚአብሔር ባሮች የድንግል አገልጋዮች የተዋህዶ ኦርቶዶክስ አርበኞች ዛሬም ምኞታችን ብትድን ነው።
በዚች አጭር የስርጭት ጊዜ ተጠቀምባት። መናፍቃን ካቶሊኮች፣ ቅባቶች ፀጋዎች ዘረኞች እናንተ በምንም
73
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ

መንገድ ምሕረት የላችሁም። ይሕንን ደግሜ አረጋግጥላችኋለሁ። እስላሞች ቀደም ይህ መልእክት እስከወጣ
ድረስ ለንስሓ እንድትበቁ ተጠብቃችሁ ነበር። የተጠቀሙበት ተጠቅመውበታል። ነገር ግን በዛው በተረታችሁ
ውስጥ ታምናችሁ አሁንም ለቆማችሁ ከየካቲት 21 ቀን 2013 በኋላ ሙሉ በሙሉ እንደመናፍቁ እንደካቶሊኩ
የምትታዩና የነሱ እጣም የናንተም እንደሚሆን አረጋግጥላችኋለሁ።

እግዚአብሔር ለሁሉም ልበ ቅን የዋህ ደግ ሰው ማስተዋልን ይስጠው። አሜን!!


የአብርሃም የይስሐቅ የያዕቆብ አምላክ ስሙ ይባረክ ድንግል እናቴ ስሟ ይባረክ!!
አሜን!!

74

You might also like