Professional Documents
Culture Documents
10 3&4
10 3&4
ምዕራፍ አራት
1
ድርሰት
ድርሰት በአዕምሯችን የሚመላለስን ጉዳይ በጽሑፍ የማስተላለፍ /የማንጸባረቅ/ ስልት ነው፡፡ በውስጡም ፈጠራዊ
እና ፈጠራዊ ያልሆኑ ገዳዮች እየተነሱ ሊብራሩና ትንታኔ ሊቀርብባቸው ይችላል፡፡ አጠቃላይ ድርሰት ልቦለዳዊ ወይም
ኢልቦለዳዊ ተብሎ በሁለት ይከፈላል፡፡ ልቦለዳዊ ድርሰት የምንለው ፈጠራዊ ሥራን የሚያመለክት ሲሆን በውስጡም
ኪናዊ ለዛ ያላቸውን ሥነጽሑፋዊ ሥራዎች ያካትታል፡፡
ኢልቦለዳዊ ድርሰት ደግሞ እውነተኛ የሆኑ ኩነቶችን በጽሑፍ የምናስተላልፍበት መንገድ ነው፡፡ ከተከሰተው ኩነት
ዘርፋዘርፍ ሳንጨምር ማለትም ሳንከልስና ሳንበርዝ እንዳለ ማቅረብ ነው፡፡
ድርሰት በምንጽፍበት ጊዜ ልንከተላቸው የሚገባን (ሊያግዙን የሚችሉ) መርሆች አሉ፡፡ እነርሱም ድርሰት ከመጻፋችን
በፊት እንዲሁም በምንጽፍበት ጊዜ የምንከተላቸው ናቸው፡፡
፩. ድርሰት ከመጻፋችን በፊት (ቅድመ ድርሰት ተግባር) ቀጥለን የምንዘረዝራቸው ተግባራት ድርሰት ከመጻፋችን
በፊት የምንፈጽማቸው ናቸው፡፡
1.1 ራሳችንን ድርሰት ለመጻፍ ማነሳሳት፡- በዚህ ተግባር ሥነልቦናችሁን ዝግጁ የማድረግ ተግባር የሚፈጸምበት ነው፡፡
1.2 ድርሰት የመጻፍ ዓላማ፡- ድርሰት የመጻፍ ዓላማ የምንለው ለማን፣ ለምን እንዴት እጽፋለሁ የሚለውን ቀድመን
መመለስ የሚገቡን ጥያቄዎች የምንመልስበት ተግባር ነው፡፡
1.3 ርዕስ መምረጥ፡- የሚመረጠው ርዕስ ሳቢ፣ ግልጽና አጭር መሆን አለበት፡፡
1.4 ርዕስ ማጥበብ/መወሰን/፡- የምንጽፈው ድርሰት ሊዳስስ የሚችላቸውን ነጥቦች የምንወስንበት ነው፡
1.5 አስተዋጽኦ /ቢጋር/ ማዘጋጀት፡- የምንጽፈው ድርሰት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ፍሰቱን ጠብቆ እንዲጻፍ
የሚያግዘን ትልም ወይም መንገድ ቀያሽ ነው፡፡
1.6 መረጃ ማፈላለግ፡- በርዕሱ መሰረት ከሰዎች፣ ከመጻሕፍት ወይም ከመገናኛ ብዙሀን ልንፈልግ እንችላለን፡፡
1.8 የተደራሲ ዓውድ፡- የምንጽፈው ድርሰት በሰዎች ተቀባይነት እንዲያገኝ የምናደርግበት ነው፡፡
2.1 ረቂቅ መጻፍ፡- በተነደፈው ቢጋር መሰረት መጀመሪያውን የመጣልን ሀሳብን ማስፈር ነው፡፡
2.2 አርትኦት /እደታ/፡-የፊደል፣የቃል ወይም የዓረፍተ ነገር ግድፈት እንዳይኖር ሙሉ ጥንቃቄ ተደርጎ የሚታረምበት
ነው፡፡
2.3 የመጨረሻ ረቂቅ መጻፍ፡- ፀሀፊው ማድረግ የሚገባውን ሁሉ መፈፀሙን ባመነ ጊዜ ተከታዩ ተግባር በተፃፈበት
ርዕሰ ጉዳይ ላይ ሙያ ያላቸው ሰዎች አንብበው ተገቢ ማስተካከያ፤ አስተያየትና ምዘና እንዲሰጡ ማድረግ ነው፡፡
የቃል ክፍሎች
2
፩. የቃል ክፍሎች የሚባሉትን በመዘርዘር ለእያንዳንዳቸው ምሳሌ ስጡ፡፡የቃል ክፍሎች በአምስት ይከፈላሉ፡፡
በአምስት ለመክፈል በመስፈርትነት የሚያገለግሉን ሶስት ነጥቦችን መሰረት በማድረግ ነው፡፡ እነርሱም፦ቅርፅ፣
አገባብና ፍቺ/ትርጉም ናቸው፡፡
ፍቺ /ትርጉም/፡- ቃሉ የሚሸከመው መሰረታዊ ትርጉም ወይም ፍቺን የሚመለከት ጽንሰ ሃሳብ ነው፡፡ በእነዚህ
ሶስት መሰረታዊ ነጥቦች መነሻ በማድረግ የቃል ክፍሎች በአምስት ይከፈላሉ፡፡ በዚህም መሠረት ስም፣ ግስ፣ ቅፅል፣
ተውሳከ ግስና መስተዋድድ ናቸው፡፡
ሀ. ስም፡- የሰዎች፣ የእንስሳት፣ የእጽዋትና የማንኛውም ግኡዝና ረቂቅ ነገሮች መጠሪያ በመሆን የሚያገለግል ቃል
ነው፡፡ ስሞች፡- ተውለወጠ፣ የተጸውኦ ወዘተ… ሁሉ ያጠቃልላሉ፡፡ በዓረፍተ ነገር ውስጥ መዋቅር የባለቤነት፣
የተሳቢነት እና የዘርፍነት ሙያ ይወጣሉ፡፡
እንደ /-ኦች/ እና /-ዎች/ የመሳሰሉትን አብዢ ምዕላድን ይወስዳሉ፡፡ መጠን፣ አይነትና ባህሪ የሚጠቁሙ ቃላትን
ይወስዳሉ፡፡ ምሳሌ፡- ልጅ፣ ተራራ፣ ሰው፣ በግ፣ ውሃ፣ ቤት፣ አንበሳ ወዘተ
ለ. ቅፅል፡- ከስም በፊት እየገባ የስሙን ባህሪ፣ ቅርጽ፣ መጠን፣ ቀለም፣ ወገን ወዘተ የሚገልፅ ሲሆን የስም ገላጭ
በመባልም ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ከስም በፊት የመጣ ቃል ሁሉ ቅጽል ሊሆን አይችልም፡፡ ቅጽሎች በጣም የሚለውን
ሐ. ግስ፡- በአገባቡ የዓረፍተ ነገር መቋጫ በመሆን ድርጊትን ወይም ሁነትን ያመለክታል፡፡ በቅርጹ ደግሞ የአረፍተ
ነገር ባለቤት አመልካች ቅጥያዎችን ያስከትላል፡፡
መ. ተውሳከ ግስ፡- ማለት የግስ ጭማሪ ማለት ሲሆን ከግስ በፊት እየገባ ግሱን ከመጠን፣ ከሁኔታ፣ ከጊዜ፣ ከቦታ ወዘተ
አንፃር የሚገልፅ ነው፡፡ ምሳሌ፡- ግምኛ፣ ምንኛ፣ ጅልኛ፣ ክፉኛ፣ ቶሎና ገና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ሠ. መስተዋድድ፡- ማለት ቃልን ከቃል፣ ሀረግን ከሀረግ እና ዓረፍተ ነገርን ከዓረፍተ ነገር ጋር የሚያዋድድ ወይም
የሚያስማማ ማለት ነው፡፡ መስተዋድዶች የሚከተሉትን ባህሪያት የሚያሳዩ ቃላት ናቸው፡፡
ሀ. ልጁ በችኮላ ይናገራል፡፡
3
ሐ. የጤና ጥበቃ ባለሙያዎች ዛሬ ተመረቁ፡፡
ሀ. ቶሎ ሠ. ጎበዝ
ለ. ብርሃን ረ. ፈጣን
ሐ. እንደ ሰ. ኮሮና
መ. መረመረ ሸ. አሁን