You are on page 1of 14

ነቢዩ ኢሳይያስ

ኦወ 2015 ዓ.ም
የስሙ ትርጉም

 ኢሳይያስ ማለት መድኃኒት ማለት ነው።


 መድኃኒት ለምን ተባለ ቢሉ ተልእኮውን የሚገልጥ ነው።
 በመጽሐፍ ቅዱስ ከሌሎች ተመሳሳይ ስም ካላቸው ለመለየትም "የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ " (ኢሳ 1:1)
ተብሎ ተጠርቷል።
 ልዑለ ቃል ተብሎም ይጠራል።
ትውልድ እና እድገት

 የተወለደው ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመት በፊት ነው።


 አባቱ አሞጽ እናቱ ሶፍያ ይባላሉ። ኢሳ 1:1
ቤተ - ሰብእ

 ኢሳይያስ ባለትዳርና የ 2 ልጆች አባት ነበር የሚኖሩትም በኢየሩሳሌም ነበር።


 ሚስቱም ነቢይት እንደነበረች መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ኢሳ 8፡3
 ልጆቹ “ያሱብ” እና “ማኄር ሻላል ሐሽ ባዥ” ይባላሉ።

 “ያሱብ” = ቅሬታዎቹ ይመለሳሉ። ኢሳ 7:3


 “ማኄር ሻላል ሐሽ ባዥ” = ምርኮ ፈጠነ ብዝበዛም ቸኮለ። ኢሳ 8:3

 በቤተሰቡ ደስተኛ እና የሚመካ ነበር። ኢሳ 8፡18


ኑሮ እና የወቅቱ ፖለቲካ
 ነቢዩ ኢሳይያስ በኢየሩሳሌም ሲኖር በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመነ መንግሥት የቤተ መንግሥት አማካሪ
ነበር፡፡ የነቢይነት ስራውን የጀመረውም ዖዝያን በሞተ በዓመቱ ነው።
 የነገሥታቱን ሃብት፣ የልዑላኑን ለቤተ መቅደስ የሚያቀርቡት መስዋዕት፣ ከሃይማኖት መሪዎች
የሚቀርብላቸውን ከንቱ ውዳሴ፣ ከቤተ መቅደስ መልስ የሚያርጉትን አህዛባዊ ግብር፣ በኣንጻሩ ደግሞ
የችግረኞችን ስቃይ እና ጩሀት በቅርብ ያውቅ ነበር።
“ራስ ሁሉ ለህመም፣ ልብም ሁሉ ለድካም ሆኗል።ከእግር ጫማ አንስቶ
እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም። ቁስልና እበጥ የሚመግልም ነው።አልፈረጠም፣ አልተጠገነም፣ በዘይትም
አልለዘበም” ኢሳ 1፡5-6
 ይኖርበት የነበረው ዘመን ውስብስብ ፖለቲካ ያለበት ጊዜ ነበር።
 እርሱ በነቢይነት በተሾመበት ዘመን ሊቀ ካህናቱ አዛርያስ፣ ንጉሱ ደግሞ ዖዝያን ይባሉ ነበር።
 በነቢዩ ኢሳይያስ ጊዜ የነበረውን ፖለቲካዊ ትኩሳት ስንመለከትም፥ ነቢዩ አገልግሎቱን በዠመረበት ወራት በኹለት ኃያላን
መንግሥታት ማለትም በግብጽና በአሦር መካከል ውጥረት ነግሦ ነበር፡፡ ወደ አገልግሎቱ ማብቂያ አከባቢ ደግሞ በአሦርና
በባቢሎን መካከል የነበረው ፍጥጫ ጣራ የደረሰበት ወራት ነበር፡፡ (2ኛ ነገሥት ከምዕራፍ15እስከ 17 ተመልከት)
 ነቢዩም ይህን ተመልክቶ የተለያዩ ሃገሪቱ ላይ ለሚከሰቱ ሁነቶች ትንቢት ተናግሮኣል። ኢሳ 7 ፣ ኢሳ ኢሳ 39
እግዚብሔርን ስለ መበደሉ እና ስለ ንስሓው

 በንጉሡ እና በሊቀ ካህናቱ መሃከል በተነሳ ጸብ ንጉሡ የበላይነቱን ለማሳየት ሃብተ ክህነት ሳይኖረው
ቤተመቅደስ ለማጠን ገብቶ ነበር።
 ኢሳይያስም ሊገስጸው ሲገባ ዝም በማለቱ እግዚኣብሔር ከንፈሩ ላይ በለምጽ መትቶታል።
 ዖዝያንንም በለምጽ መትቶታል።
 እርሱንም ወስደው ጨለማ ቤት ዘጉበት:: ሃብተ ትንቢቱንም ተቀማ::
 በዚያው ሆኖ ንስሃ ገባ: ጾመ: ጸለየ::
 እግዚአብሔርም ንስሓውን ተመለከተለት:: ከዚያም ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት ኢሳይያስ
እግዚአብሔርን በረዥም [ልዑል] ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ: ኪሩቤል ተሸክመውት: 24ቱ ካህናተ ሰማይ
"ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ሲያመሰግኑት ተመለከተ:: ኢሳ (6:1)
 ያን ጊዜ እግዚአብሔር "ወደ ሕዝቤ ማንን እልካለሁ?" አለ:: ኢሳይያስም "ጌታዬ! እኔ ከንፈሮቼ የረከሱ
አለሁ" አለው:: እግዚአብሔርም ሱራፊን ላከለት:: መልአኩም ፍሕም [እሳት] በጉጠት አምጥቶ ከንፈሩን
ቢዳስሰው ነጻ:: ሃብተ ትንቢቱም ተመለሰለት:: ይኸውም የሥጋ ወደሙ ምሳሌ ነው::
 ከዚህች ቀን በኋላ ግን ኢሳይያስ የተለየ ሰው ሆነ:: ማንንም የማይፈራ እውነተኛ የልዑል ወታደር ሆነ::
ከዖዝያን በሁዋላ በየዘመናቸው 4ቱንም ነገሥታት ገሰጸ:: እነዚህም ኢዮአታም: አካዝ: ሕዝቅያስና ምናሴ
ናቸው::
ትንቢት ወ ተአምራት

 ደረቅ ሐዲስ (የኢሳይያስ ወንጌል)


 ጌታ በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና እንደሚወለድ ኢሳ (7:14)
 አምላክነቱን /ኢሳ.9፡6/፣ የነገደ እሴይ ስር መኾኑ /ኢሳ.11፡1/፣ መንፈስ ቅዱስ እንደሚያርፍበት
/ኢሳ.11፡2/፣ ለአሕዛብ ፍርድን እንደሚያመጣ /ኢሳ.42፡1/፣ ትሕትናው /ኢሳ.42፡2/፣ ለኹሉም ተስፋ
ድኅነትን እንደሚያመጣ /ኢሳ.42፡3/፣ ወደ ግብጽ እንደሚሰደድ /ኢሳ.19/፣ መከራውና ስቅለቱ /ኢሳ.53/፣
በትንሣኤው ለኹሉም ተስፋ ትንሣኤን እንደሚሰጥ /ኢሳ.35፡8-10/፣
 “ትንቢተ ኢሳይያስን ሳነብ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት የሚተርክ ወንጌላዊን አገኛለኹ፤ ከዚኹ
ጐን ለጐንም ስለ መፃእያት የሚናገር ነቢይን አገኛለኹ” ቅዱስ ጀሮም
 ኢሳይያስ ፀሐይን ዓለም እያየ ፲ [10] መዓርጋትን ወደ ሁዋላ መለሳት::

ልዩ ስብእናዎች
 ነቢዩ እውነትን የማይሸፋፍን፣ ለማንም የማያዳላ መምህር ወመገስጽ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ከሊቅ እስከ
ደቂቅ እንዲኽ ቢገስጻቸውም የድኅነት ተስፋም ይሰጣቸው ነበር፤ ተስፋውም ለእነርሱ ብቻ ሳይኾን
ለደቂቀ አዳም በሙሉ የሚኾን ተስፋ ድኅነትን ነበር፡፡
 ታላቅ ነቢይ ነው፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ካደረጋቸው ግብሮችና ከጻፈው መጽሐፍ ይዘት አንጻር ታላቅ ነቢይ
ልንለው እንችላለን፡፡
 እግዚአብሔር በሦስት መንገድ ኢሳይያስን አናግሮታል፡፡ በሚያስደንቅ ግርማ /ኢሳ.6/፣ በጽኑ እጅ
/ኢሳ.8፡11/፣ እንዲኹም በአባታዊ ንግግር /ኢሳ.20፡2/ አናግሮታል፡፡ እርሱም ይኽ ከእግዚአብሔር
የተቀበለውን መልእክት በሦስት መንገድ አስተላልፎታል፡፡ በአደባባይ በሚደረግ ግልጽ ትምህርት፣
ለምልክትና ለተአምራት ሊኾን ራቁቱንና ባዶ እግሩን በመሔድ፣ እንዲኹም በጽሕፈት፡፡
 ከቤተ ክህነቱ እስከ ቤተ መንግሥቱ ድረስ ኹሉም ሕይወቱ በተበላሸና አምልኮው ኹሉ ግብዝ በኾነበት
ሰዓት ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ግሩም የኾነውን መለኮታዊ ምስጢር ይካፈል ነበር፡፡ በዚኽም እግዚአብሔር
አፍቃሬ ኃጥአን እንደኾነ፣ ድካማቸውን እንደሚረዳ፣ ድኅነታቸውንም አብዝቶ እንደሚሻ ይሰብክ ነበር፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን
 ነቢዩ ኢሳይያስንና ኢትዮጵያውያን ነጣጥሎ ማየት ከባድ ነው።
 ኢትዮጵያውያን በሌላ ሃገር ሲሔዱም ከልብሳቸውና ከስንቃቸው ጋር ይዘዉት እየሔዱ ያነቡት
እንደነበር ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ምስክር ነው። /ሐዋ.፰፡፳፮-፵/
 በዘወትር ጸሎታችን ውስጥ፡- “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ጸባዖት ፍጹም ምሉዕ ሰማያተ ወምድረ
ቅድሳተ ስብሐቲከ” የምንለውም ከትንቢተ ኢሳይያስ በቀጥታ የተወሰደ ነው /ኢሳ.፮/፡፡
 በየቀኑ ለእግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን በሚቀርበው የቅዳሴ፣ የሰዓታት፣ የማኅሌት ምስጋናና ጸሎት
ትንቢተ ኢሳይያስን ሳያነሣ አያልፍም፡፡
ዕረፍቱ

 ልዑለ ቃል ቅዱስ ኢሳይያስ ለ 70 ዘመናት ሕዝቡን አስተምሮ: ነገሥታቱን ገስጾ: 68 ምዕራፎች ያሉትን
ሐረገ ትንቢት ጽፎ አረጀ::
 በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ምናሴ ግን ይባስ ብሎ ጣዖትን አቆመ: ለጣዖትም ሰገደ:: ቅዱሱ ይህንን
ሲያደርግ ዝም አላለውም:: በአደባባይ ገሰጸው እንጂ::
 በዚህ የተበሳጨ ምናሴም ሽማግሌውን ነቢይ በእንጨት መጋዝ ለሁለት አሰነጠቀው:: ቅዱስ ኢሳይያስ
በዚህ ዓይነት በጐ ሕይወት መስከረም ፮ [6] ቀን ሩጫውን ፈጸመ::
 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይኹን፤ እኛንም በጸሎቱ ይማረን፤ በረከቱም ከኹላችን ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ
አሜን!!!

“ ሰላም ለኢሳይያስ ነቢየ ሥርዓቱ ለዕብኖዲ።


ቅቡዐ ከናፍር ወአፍ እም አፍሐመ እሳት ነዳዲ።
እንዘ ይብል አስምዐ በእንተ ክርስቶስ የማነ ወላዲ።
ይፀነስ በከርሠ ድንግል ወይትወለድ ዓዲ።
ውስተ ግበ አርዌ ሕጻን እዴሁ ዘይወዲ።”
ስብሐት ለእግዚአብሔር!!!

You might also like