You are on page 1of 3

መልስ

1. የተቸገሩ ሰዎች የምትያቸው ምን የጎደላቸው ናቸው? ለእነዚህ ሰዎች ምን አድርገሽ ታውቂያለሽ ?

የተቸገሩ ሰዎች የምትያቸው ምን የጎደላቸው ናቸው?

 የተቸገሩ ሰዎች የምላቸው በኑሮዋቸው ማለትም በገቢያቸው ዝቅተኛ ሆኖ መሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎት
የምንላቸውን (ምግብ፣መጠለያ፣ልብስ…) ማሟልት የማይችሉ፣
 የተደላደለ ኑሮ ኖሯቸው በቤታቸው ደስታ እና ፍቅር የሌላቸው፣
 በህይወታቸው ተስፋ የሌላቸው ፣
 እውቀት የጎደላቸው ያላቸውን እና የተሰጣቸውን ነገር እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ የማያውቁ

ለእነዚህ ሰዎች ምን አድርገሽ ታውቂያለሽ ?

 በብር የተቸገሩ ሰዎች ከሆኑ ከተረፈኝ ላይ በብር ወይም በአይነት እረዳቸዋለሁ


 በህይወታቸው ተስፋ ከቆረጡ እግዜአብሄርን ተስፋ እንዲያደርጉ እመክራቸዋለሁ፣
2. ሃይማኖትሽን በፍቅር ገልጠሽ ታውቂያለሽ እንዴት? መቼ? የት? ለማን?

 ሃይማኖቴን በፍቅር ለመግለፅ እሞክራለው ነገር ግን ከእግዜአብሄር ምላሽ አገኛለው ብዬ ስለማስብ ነው፣

እንዴት?

 ለተቸገረ ሰው በመስጠት
 ሰው በማክበር
 ሰው በመውደድ (በገደብ) ሰውን ያለ ምክንያት አልወደውም ያለምክንያት ግን ልጠላው እችላለው

የት

 በእምነት ቦታ
 በቤት ውስጥ
 በአካባቤ
 በስራ ቦታ ….
ለማን
 ለቤተሰቦቼ
 ለስራ ባልደረቦቼ
 ለነድያን
3. እየቆረብሽ ነው ?ካልቆረብሽ ለምን?መቼ ታስበሻል?

እየቆረብሽ ነው ?
 አልቆረብኩም

ካልቆረብሽ ለምን?

 መቁረብ እፈልጋለው ነገር ግን በህይወቴ ብዙ ያልተሟሉልኝ ነገሮች አሉ ብዬ ስለማስብ እና እነዛን ነገሮች


ለማግኘት ስል ፈጣሪዬን አስቀይማለሁ ከመንገዱ እወጣለሁ የሚል ፍርሃት ስላለኝ ስጋ እና ደሙን መቀበል
እፈራለሁ
 በመቁረብ ውስጥ ብዙ ገደብ ( በአለባበስ፣በአመጋገብ፣በንግግር፣….) አለ ብዬ ስለማስብ ፍርሃት ያድርብኛል
 እምነት ይጎለኛል ብዬ ስለማስብ መቁረብ ማለት ወደ ሞት መጠጋት ማለት ነው የሚል ፍርሃት
ስላለኝ
 ገና ነኝ ብዬ ስለማስብ ( ጊዜአለኝ)

መቼ ታስቢያለሽ?

 መቁረብ ማለት ምን ማለት እንደሆነ በደንብ ሲገባኝ፣


4. በስራ እየተረጎምኩት ነው ብለሽ የምታስቢው ሃይማኖታዊ ትእዛዝ የቱ ነው?የማትፈጽሚውስ? ለምን?

በስራ እየተረጎምኩት ነው ብለሽ የምታስቢው ሃይማኖታዊ ትእዛዝ የቱ ነው? ፍጹም አከብራቸዋለሁ ብዬ ባላስብም ግን በስራ
ለመተርጎም የምሞክራቸው

 ከእኔ በቀር ሌሎች አማልክት አይሁኑልህ


 አትስረቅ
 አትግደል
 አታመንዝር

የማትፈጽሚውስ?

 አትዋሽ
 ባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር
 የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ
 የባልንጀራህን ቤት አትመኝ
 አባትህንና እናትህን አክብር
ለምን?
 በወቅቱ ልክ የሆንኩ ስለሚመስለኝ
 ልክ እንዳልሆንኩ ባውቅም ባለማድረጌ የማገኘው ነገር በልጦ ስለሚታየኝ
 ስተቶችን በተደጋጋሚ ከመፈጸሜ የተነሳ ልማድ ሆኖ በመቅረቱ

5. በአካባቢይሽ እምነታቸውን በሥራ የሚገልጹ የምታስቢያቸው ሰዎች አሉ? ምሳሌ ይሰጥበት?


በአካባቢይሽ እምነታቸውን በሥራ የሚገልጹ የምታስቢያቸው ሰዎች አሉ?
 አዎ

ምሳሌ ይሰጥበት?

በአካባቢዬ የእውነት የሚያመልኩ እና ትእዛቱንም የሚያከብሩ ሰዎች አውቃለው ሰውን የሚወዱ የማይዋሹ፣
አዛኝ፣ ለተራበ የሚያበሉ፣ ሰውን ማማት የሚጸየፉ,፣የእግዚአብሄርን ትዕዛዝ በፍርሃትና በንጽህና
የሚፈጽሙ ፣በማንኛኛም ሁኔታ በሃዘንም በደስታም እግዚያብሄርን የሚያመሰግን ሰው አውቃለሁ፡፡
6. ስለገነት እና ሲኦል ፣መንግስተ ሰማያት እና ገሃነመ እሳት….ያለሽ ኅሊናዊ ስዕል ምንድነው›

ገነት
 በምድር ላይ ሳሉ የእግዚአብሄርን ትእዛዝ ሲፈፅሙ የኖሩ ሰዎች ሲሞቱ የእግዚያብሄር ዳግም መምጫው
እስኪደርስ ድረስ በጊዜያዊነት ነብሳቸው የምትቆይበት ቦታ ፣
 አረንጓዴና ለም ቦታ፣ መላክቶች እያሸበሸቡ ፍጠሪያቸውን የሚያመሰግኑበት ቦታ አድርጌ እስለዋለሁ፣
 ችግር ረሃብ በሽታ የሚባል ነገር የሌለው እና ነብሳችን በጣም የምትደስትበት ቦታ ይመስለኛል፣
 የመንግስተ ሰማያት ተምሳሌት

ሲኦል
 በምድር ላይ ሳሉ የእግዛብሄርን ትእዛዝ ሳይፈጽሙ የኖሩ ሰዎች ሲሞቱ የእግዚያብሄር ዳግም መምጫው
እስኪደርስ ድረስ በጊዜያዊነት ነብሳቸው የምትቆይበት ቦታ
 የሚያቃጥል እሳት፣ሰውነት የሚሰነጣጥቅ ብርድ አጋንንት ተሰብስበው የሰውን ነብስ የሚያሰቃዩበት ቦታ
አድርጌ እስለዋለሁ
 ችግር ረሃብ በሽታ ያለበት እና ነብሳችን የምትሰቃይበት ቦታ ይመስለኛል፣
 የገሃነም ተምሳሌት

መንግስተ ሰማያት

 እግዚአብሄር ወደ ምድር ሲመጣ እና ሲፈርድ ገነት ያሉ ነብሶች ለዘላለም በደስታ የሚኖሩባት የእግዚአብሄር ከተማ
ትመስለኛለች

ገሃነም

 እግዚአብሄር ወደ ምድር ሲመጣ እና ሲፈርድ ሲኦል ያሉ ነብሶች ሁላ በስቃይ ለዘላለም የሚኖሩባት ትመስለኛለች
7. ጽድቅና ኩነኔን እንዴት ታስቢያቸዋለሽ?

ጽድቅ

 ጽድቅ ሰዎች በምድር ላይ እግዚአብሄር የሚወደውን ስራ በመስራት ወደ መንግስተ ሰማያት መግቢያ


መንገድ ናት

ኩነኔ

 ኩነኔ ሰዎች በምድር ላይ እግዚአብሄር የማይወደውን እና ያልፈቀደውን ስራ በመስራት ወደ ገሃነም


መግቢያ መንገድ ናት
8. እግዚአብሄር በአንቺ እየተደሰተ ይመስልሻል?ለምን ?ምን ብታደርጊ ይደሰታል ብለሽ ታስቢያለሽ?
እግዚአብሄር በአንቺ እየተደሰተ ይመስልሻል?
 አይመስለኝም

ለምን ?

 ምክንያቱም እኔ ሁሌ ጥቅሜን ነው የማስቀድመው ፈጣሪን የማመሰግነው በምክንያት ነው ሲደረግልኝ


ብቻ ነው ባለኝ እና በሚኖረኝ ነገር እግዚአብሄርን አላመሰግነውም እግዚአብሄር የሚያስፈልገኝንና
የጠየቁትን ነገር ሁላ ያደርግልኛል በተጨነኩ ሰዓት ይደርስልኛል ብዙ ለሰው የማልነግረው ነገር ፈጣሪዬ
አድርጎልኛል ግን እኔ እምነቴ ጎዶሎ ነው ፣

ምን ብታደርጊ ይደሰታል ብለሽ ታስቢያለሽ

 የፀና እምነት ቢኖረኝ


 ሃይማኖታዊ ትእዛዛቶችን ባከብር

You might also like