You are on page 1of 7

1/ሀገረሰባዊ መደኃኒት በማህበረሰቡ እይታ ምን ማለት ነው? ምን የሚል እሳቤ አለው?

ሀገረሰባዊ ህክምና ጤና ነክ ድርጊቶችን፣ የአቀራረብ መንገድችን፣ ዕውቀትንና እምነቶችን፣ እፀዋትን፣ እንሰሳትን፣ ማዕድናትን፣
መንፈሳዊ ቁሶችንና መንፈሳዊ ክዋኔዎችን መሰረት በማድረግ ህመሞችን የማወቅ፣ የመከላከልና የመፈወስ ስርዓት እንደሆነ
ይታያል ሲቀጥልም ይታሰባል፡፡

በማህበረሰቡ በሕይወት ውስጥ የሚያጋጥሙ የጤና ችግሮች መፍትሄ የማግኘት በሚል የማህበረሰቡ አባላት የሚከውናቸው
አጠቃላይ ድርጊቶች በሀገረሰባዊ ህክምና ውስጥ የሚጠኑ ጉዳዮች እንደሆኑ ይታያል፤ይታሰባል፡፡ እነዚህ ድርጊቶችም
ማህበረሰቡ ስለ ህመምና ጤና ያለው እሳቤ፣ ስለ ህመምተኛው ያለው አመለካከት፣ ስለ ህክምና ባለሙያዎቹ ያለው
አመለካከት፣ አንድን የህመም አይነት ለመለየት የሚጠቀምበት ዘዴ፣ ለበሽታዎቹ መከላከያ ወይም ማጥፊያ የሚሆኑ
መድኃኒቶችን ከምን ከምን እንደሚያዘጋጅ፣ እንዴት እንደሚያዘጋጅ፣ መቼ እና የት እንደያሚዘጋጅ፣ የመደኃኒቶቹ የአወሳሰድ
ስርዓት እና ለህክምናው የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች የመሳሰለትን ነጥቦች ሁሉ እሳቤ ውስጥ ይገባሉ፤ ይታያሉ።

በአጠቃላይ የባህል ሕክምና እውቀት የማህበረሰብን አካባቢያዊ እውቀት፣ እምነት፣ ደንብ፣ ሥርዓት፣ ተግባርና ሙያን ታሳቢ
ያደረገ፤ጥበባዊ ድርጊትን ያካተተ፤ የተለያዩ የበሽታ መንስኤዎችን፣ አውዲዊ ሥርዓቶችን፣ የጤና መጠበቂያና በሽታ
መከላከያ ዘዴዎችን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ (ብርቱካን 2012፣ 6)

2/ሀገረሰባዊ ህክምና መድኃኒት ከመንፈሳዊ ሃይማኖት አንጻር ምን ማለት ነው? ምን አይነት እሳቤ አለ?

ሀገረሰባዊ ህክምና መድኃኒት ከመንፈሳዊ ሃይማኖት አንጻር በጣም ተገቢ እና ተመራጭ እንዲሁም ተመካሪ የሆነ መደሃኒት
ነው፡፡ ምክንያቱም መድኃኒቱን የሚያዘጋጁት በመንፈሳዊ ሃይማኖት የበለጸጉ፡ የበሰሉ አባቶች ናቸውና፡፡ ለዚህም ማስረጃ
መጽሐፈ ሲራክ 38፡1 ላይ እንዲህ ሲል ይገኛል”እሱን እግዚአብሔር ስለመረጠው ጌትነቱ እንደ እጁ ሥራ ነውና ባለ
መድኃኒትን አክብረው”ይላል፡፡አሁንም ከዛው ምእራፍ ቁጥር 3 ላይ እንዲህ የሚል ምስክር ይገኛል”ባለ መድኃኒትን
በጥበቡ ያከብሩታል በመኳንንትም ዘንድ ይመሰገናል” ይላል፡፡ Assefa (1992; P.4)፤ "የኢትዮጵያ ሃይማኖትና አምልኮ
የውጭ አገር ተፅዕኖ አለበት" ይላሉ፡፡ የባህል ሕክምና ዕውቀት ከሃይማኖት፣ ከእምነትና ከአምልኮ ሥርዓትና ተግባር ጋር
እንደሚገናኝ ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ ሃይማኖት፣ አምልኮና እምነት ከጎረቤት አገሮች ጋር የተወራረሰ በመሆኑ፤ የውጭ አገር
ሃይማኖትና ልማድ ተፅዕኖ እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ በተለይ ከግብፅ፣ ከዐረብና ከሱዳን በነበረን፤ የንግድና የሃይማኖት ግንኙነት
የባህል ሕክምና ዕውቀትና ሥርዓት፣ አምልኮና ጥበብ ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ (እንደተዛመተ) አትተዋል፡፡

3/ሀገረሰባዊ መደኃኒት መቸ እንደተጀመረ ከመንፈሳዊ አስተሳሰብ ከክርስትና(መጽሐፍ ቅዱስ ገድላት እና ሌሎች አዋልድ
መጽሐፍት አንጻር )
የባህል ሕክምና እውቀት፣ ልማድና አተገባበር ሥርዓት መቼ ተጀመረ? እንዴት? እና እነማን ጀመሩት? የሚል ጥያቄዎችን በቂ
ምላሽ፣ መረጃና ማስረጃ ማግኘት እንደሚያስቸግር፤ በመስኩ ጥናት ያደረጉ ተመራማሪዎች (አሰፋ፣2008፤ Pankhurst,1996;
Alemayehu,1984) ጠቁመዋል፡፡
Alemayehu (1984) የባህል ህክምና አጀማመር አስመልክተው ሲገልጹ “የሰው ልጅ በሽታን መከላከል፣ መድኃኒትን
መጠቀምና መፈወስ የጀመረው ከጥንተ-ክርስቶስ ልደት 25,000 ዓ.ዓ በፊት ነው” ይላሉ፡፡ በሌላ በኩል (Desta ,2004) እና
(Pankhurst ,2005) በኢትዮጵያ የባህል ሕክምና ታሪክ አጀማመር በቂ የታሪክ ማስረጃ እንደሌለ ገልጸው፤
ስለኢትዮጵያውያን የባህል መድኃኒት አጠቃቀም እውቀት የመጀመሪያ ደረጃና መረጃ የሚሉት የ”Alessandro Zorzi እና
የ Francisco Alvares”ን ዘገባ ነው፡፡

ሃገረሰባዊ መደኃኒት መቼ ተጀመረ ለሚለው ከመንፈሳዊ አስተሳሰብ አንጻር እና ከክርስትና ፤ከመጽሐፍ ቅዱስ፤ከገድላት
እንዲሁም ከአዋልድ መጽሃፍት ተመልክተን ጠቅለል ያለ ሃሳብ ስናቀረብ ገድላት በራሳቸው መድሃኒት ናቸው፡፡ምክንያቱም
እግዚአብሔር ገድሉ የተጻፈለትን ቅዱስ በስምህ ላመነ፤ለተማጽነ፤ለለመነ ፤ባንተ ስም ነደያንን ላበላ ላጠጣ ደዌ ሥጋ ደዌ
ነብስ አያገኘውም ብሎ ቃል ገብቶለታልና አማኞች ይህን አምነው ብያደርጉ ይድናሉ፡፡መጽሃፍ ቅዱስም ይህን ሐሳብ እንዲህ
ሲል (ማቴ 10፡40_42) ያጠነክረዋል፡፡

እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፤ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ
ያገኛል፤ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቅን ዋጋ ያገኛል። ስለዚህ እውነት እላችኋለሁ፣ ማንም ሰው ከእነዚህ
ከታናናሾች ለአንዱ ደቀ መዝሙሬ በመሆኑ አንድ ጽዋ ቀዝቃዛ ውሃ ቢሰጠው ዋጋውን አያጣም።”

4//ሀገረሰባዊ መደኃኒት መቼ እንደተጀመረ ከመንፈሳዊ አስተሳሰብ ከእስልምና(ቁርአና ሌሎችም መጽሃፍት አንጻር)

ቁርአን ደግሞ እንዲህ ሲል የራሱን መድሃኒትነት ይገልጻል፡፡


ቁርአን ወደር የለለው መድሀኒት ነው ፡፡ቁርአን ለአካላዊ ሆነ መንፈሳዊ( ሲህር(ድግምት) ፣ጂኒ፣ቡዳ(አይን) ) መድሀኒት
ነው።አዛኙ አላህ(ሱ.ወ) ቁርአንን እዝነት፣ወደ ቀጥተኛ መንገድ መመሪያ፣ለአማኞች ፈውስ አድርጎ በመጨረሻው ነብዩ
መሀመድ(ሰ.ዐ.ወ) ላይ አውርዷል።በቁርአን መታከም የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሱና፣የሶሀቦች እና ደጋግ የአላህ ባርያዎች መንገድ ነው
አላህ(ሱ.ወ) ቁርአን ፈውስ እንደሆነ በቁርአን ነግሮናል ፡፡ከቁርኣንም ለምእመናን መድኀኒትና እዝነት የኾነን እናወርዳለን፡፡
በዳዮችንም ኪሳራን እንጂ ሌላ አይጨምርላቸውም፡፡ አል ኢስራእ 82

እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ በደረቶች ውስጥም ላለው (የመጠራጠር በሽታ) መድኃኒት ለምእምናንም ብርሃንና
እዝነት በእርግጥ መጣችላችሁ፡፡} ዩኑስ 52

በል እርሱ ለእነዚያ ለአመኑት መምሪያና መፈወሻ ነው፡፡} ፉሲለት 44


ከነዚህ አንቀፆች የምንረዳው ቁርአን መድሀኒት እና ፈውስ  መሆኑ ነው፡፡

5/በክርስትናም ሆነ በእስልምና ሃይማኖቶች የበሽታ መንስኤ እና መፈወሻ ምንድን ነው?

መንስኤው እንዲህ ነው ባይባልም እግዚአብሔር ግን ሳያውቀው ድንገተኛ ችግር ሆን በሽታ በአጋጣሚ አያመጣም፡፡ነገር
ግንእግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሲያዝን ለእርግማት ወይም ለቅጣት በሽታን ሊልክ ይችላል ይባላል፡፡ለዚህ መሰል በሽታ
ፈውስ የሚገኘው ደግሞ በእምነት ላይ በተመሰረተ ህክምና ነው፡፡ለዚሕ ተጠቃሽ ጸበል ነው፡፡መጽህፍ ቅዱስ ላይም
ተጠቅሷል፡፡በቤተ ሳይዳ የነበረው መጠመቂያ ውሃ የእግዚአብሔር መልአክ ሲያንቀሳቅሰው በሽተኞች እየገቡ ይፈወሱ ነበር
ይላል፡፡(ዮሐ 5፤41) በሐገራችንም ሜሮን (ቅብዓ ቅዱስ)ቤተክርስቲያን የምታሰጠው መድኃኒት ነው፡፡ይህም በመጽሐፍ
ቅዱስ ማር 6፡13 ” ብዙ አጋንንትም አስወጡ፤እንዲሁም ብዙ ሕመምተኞችን ዘይት እየቀቡ ፈወሱ።”ይላል፡፡ሌላው
ፈውስ ማግኛ ጸሎት ነው፡፡ለዚህም መጽሃፍ ቅዱስ ማስረጃ አለው፡፡ሐዋ 9፡40_41

በእስልምናም ሙስሊሙ ህብረተሰብ ፈውስ ከፈጣሪ እንደሚገኝ ያምናል፡፡ተአምራዊ ፈውስ የሚል እስላማዊ የህክምና
መጽሃፍ ላይ እንደተጻፈው”ሙስሊም የሆነ ሰው ሁሉ ይህን የአላህ ቃል አምኖ መቀበል እና በአላህ ፈዋሽነትም በመመካት
መለኮታዊ እና ተአምራዊ ኃይል በሆነዉ ተአምራዊ መደሃኒት መጠቀም ብልሃትነት ነዉ ይላል፡፡”

6/ እምነት ምንድን ነው? ሃይማኖትስ?

እምነት (ሰሎሞን 2007፣ 179) ስነልቦናዊ ሁነት( psychological state) ሲሆን አንድ ሰው እምነትነው ብሎ የሚቀበለውና
አማኙም የሚያምንበት ነገር የራሱን ምክንያት ወይም ማብራርያ የሚያቀርብበት ስርዓት ነው። እነዚህን ምክንያቶች ወይም
ማብራሪያዎች በዕምነቱ ዙርያ ያለ ማስረጃዎች፣ መመሪያዎች፣ ህጎች፣ ደንቦች፣ ሰርዓቶች ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። ስነልቦናዊ
ሁነት የሆነው ዕምነት አዕምሮአዊ ውክልና የመስጠት ሂደት ነው። አዕምሮዓዊ ውክልናዉም እምነቱን በሚቀበለው
ማህበረሰብ ወይም በወካዩ(object of belief) መካከል ያለው መንፈሳዊ መስተጋብር ነው።

‘ዕምነት’ የሚለውን ቃል የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ተቋም ባዘጋጀው


የአማርኛ መዝገበ ቃላት ‘ሀይማኖት፣ አምልኮ፣ እርግጠኝነት፣ ሀላፊነት፣ ታማኝነት’ የሚል
ፍቺዎችን ተሰጥተውታል (1993፡ 305)፡፡

እምነት ማለት “ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው፡፡ ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል
እንደተዘጋጁ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን (ዕብ 11፡1-3)፡፡” ለምሳሌ መንግስተ
ሰማያትን (የዘላለም ሕይወትን) ተስፋ እናደርጋለን፡፡እምነትም ይህንን ተስፋ ያረጋግጥልናል፡፡ የእግዚአብሔርን (የሰማዩን)
መንግስት አላየነውም፡፡ እምነት ይህንን ያላየነውን ነገር ያስረዳናል፡፡ ሳይንስ ይህንን ሊያደርግ አይቻለውም። እምነት በፍጹም
እውነት (absolute truth) ላይ እንጂ እንደ ሳይንስ በአንጻራዊ እውነት (relative truth) ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡
የመፅሃፌ ቅደስ መዜገበ ቃሊት ዯግሞ ሇቃለ

የሚከተለትን ሁሇት ፌቺዎች ያስቀምጣሌ፡- እምነት ሁሇት ነገሮችን ይይዚሌ፡፡


1415
1. ስሇ አምሊክ ወይም ስሇሰው ዕውቀት ወይም አሳብ፡፡
2. በአምሊክ ወይም በሰው ፌፁም ተስፊ ማዴረግ (1980፡178)፡፡
ዯስታ ተክሇ ወሌዴም በበኩሊቸው ቃለ ሃይማኖት፣ ማመን፣ መታመን የሚለ ትርጓሜዎች
እንዲለት ባ዗ጋጁት መዜገበ ቃሊት ውስጥ ጠቁመዋሌ፡፡ ‘ማመን’ የሚሇውንም ቃሌ
መቀበሌ፣ መውዯዴ፣ ማክበር፣ እውነት ነው ብል መቀበሌ ነው በማሇት ይፇቱታሌ
(1962፡108-109)፡፡
በጥቅለ ዕምነት ማሇት ሰዎች በዕሇት ተዕሇት ህይወታቸው ውስጥ የሚተገብሩት ሲሆን
ይፇፀምሌናሌ ወይም ይከሰትብናሌ ብሇው በማሰብ በጎ የሚለትን ነገር እንዱፇፀምሊቸው
የሚጠይቁበት ክፈ ነገር ዯግሞ እንዲይከሰትባቸው የሚከሊከለበት (የሚሇማመኑበት)
መንገዴ ነው፤ ቃለ ሂዯትን የሚያሳይ ሲሆን በሚታመነው አካሌ እና በአማኙ መካከሌ
የሚዯረግ መንፇሳዊ ግንኙነት ነው፡፡
ከእነዙህ ፌቺዎች መገን዗ብ የሚቻሇው ዕምነት አንዴ ነገር ይሆናሌ ወይም ይፇፀማሌ ብል
ማሰብ እንዱሁም አምሊክን ወይም ሰዎችን ከጥርጣሬ ነፃ ሆኖ አስተሳሰባቸውን ወይም
ዴርጊታቸውን መከተሌ ነው፡፡ በዙህ ጥናትም ተጠኝው ማህበረሰብ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር
የተያያዘ እምነቶችን የሚተገብረውና ከትውሌዴ ወዯ ትውሌዴ የሚያስተሊሌፇው በምን
መሌኩ እንዯሆነ ተፇትሿሌ፡፡
2.1.6 ሀይማኖት
ሰልሞን (2007፣174) ሀይማኖት የባህሌ፣ የስርዓት፣ የእምነትና የዓሇማዊ ማንፀባረቂያ
ስብስብ ሲሆን ማህበረሰቡን ከመንፇሳዊነት ስሜት ጋር የሚያገናኝ፣ በእሇት እሇት የህይወት
እንቅስቃሴዎቹ የሚያምነውና የሚተገብረው ስርዓት ነው፡፡ ሀይማኖት ያሇውን የአስተምሮ
ፅንሰ ሀሳብ መነሻ በማዴረግ በተምሳላታዊ፣ በዴርጊታዊ፣ በገሇፃዊና በታሪካዊ ሁነቶች
ሇህይዎትና ስሇ ህይዎት አፇጣተር፣ ስሇዓሇም፣ ስሇዓሇም አፇጣጠር፣ ስሇስነ
ፇሇግ
ወ዗ተ
ሂዯቶችን የሚያሳይና ትርጉም የሚሰጥ ነው፡፡ በመሆኑም በዙህ ጥናት በማህበረሰቡ ዗ንዴ
ያሇው ሀይማኖታዊ አስተምሮ ሇእፅዋት ሆነ ሇደር እንስሳት ሇመጠበቅ እና በአጠቃሊይ
ሇአካባቢ ጥበቃ ሌማዴ ምን ፊይዲ ሉኖረው እንዯሚችሌ ሇመመርመር ተሞክሯሌ፡፡
ሃይማኖት ማለት ደግሞ እምነትና አምልኮን በአንድ ላይ አጣምሮ የያዘ  የእምነትና የአምልኮ ሥርዓት ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔርን አምነን የምናመልክበት ሥርዓት (system) ሃይማኖት ይባላል፡፡ የዚህም አስተምህሮ ትምህርተ ሃይማኖት
ይባላል፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔርን እናምናለን፡ እርሱንም እናመልካለን፡፡ እርሱን ምን ብለን እንደምናምንና እንዴት
እንደምናመልክ (የአምልኮ ሥርዓት እንደምንፈጽም) የሚገልጽ ሃይማኖት ነው፡፡ ስለዚህ የእምነት መገለጫው ሃይማኖት
ነው፡፡
 አንዲት ሃይማኖት/እምነት ማለት ምን ማለት ነው? ኤፌ 4፡5.
የዚህ መነሻው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ብሎ ያስተማረው ነው (ኤፌ 4፡4-
5)፡፡ ይህንን የጻፈበትም ዓላማ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ይተጉ ዘንድ (በመካከላቸው መለያየትን
ያስወግዱ ዘንድ) ነበር።  በዚህ አገላለጽ መሠረት አንዲት ሃይማኖት ማለት የሚከተሉትን ትርጉሞች እንሚይዝ ሊቃውንት
ያስረዳሉ፡
 አንዲት ሃይማኖት ማለት በአንድ አምላክ ማመን ነው፡፡
የአዳም አምላክ የአብርሀምም አምላክ ነው፡፡ ያው የአብርሀም አምላክ የይስሐቅም የያዕቆብም የሙሴም የዳዊትም
የጴጥሮስም የእኛም አምላክ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ያመነውን አምላክ እርሱ እንዳመነው አድርገን ካመንን እርሱ
እንዳመለከውም አድርገን ካመለክን ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በሃይማኖት አንድ ነን፡፡ ልጆቻችንም እንደዚህ ካመኑ እንደዚህም
ካመለኩ አንዲት ሃይማኖት ተጠብቃ ኖረች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አንዲት ሃይማኖት ማለት በአንድ (በቁጥርም በባህሪም)
አምላክ ማመንንና እርሱንም በአንድ አይነት አምልኮ ማምለክ ነው፡፡በብሉይም በሐዲስም ያለው አምላክ አንድ ነው፡፡
ሐዋርያው አንዲት ሃይማኖት ያለው ስለአንዱ አምላክ የሚሰብክ መሆኑን ለማስረገጥና ክርስትናም ቀደም ከነበረው
ሃይማኖት በገሃድ በመገለጥ የቀጠለ ነው እንጅ ክርስትና አዲስ መጥ ሃይማኖት አይደለም ለማለት ነው፡፡

 አንዲት ሃይማኖት ማለት በአንዲት ጥምቀት መወለድ ነው፡፡


የሃይማኖት መግቢያ በር በአንድ አምላክ አምኖ መጠመቅ ነው፡፡ ጥምቀትም ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድና የክርስቶስን
ቤተሰብን መቀላቀል ነው፡፡ እያንዳዳችን የምንጠመቃት ጥምቀት አንዲት (በቁጥር) ናት፡፡ አትደገምም፡፡ ልጅ ከተባልንና ወደ
እቅፉ ከገባን በኋላ ደግሞ ሌላ ስም ስለማይሰጠን ፣ ዳግመኛ ልጅነትም ስለማይኖር ፣ ጥምቀታችን አንዲት ብቻ ናት እንላለን
፡፡  ሁላችንም የተጠመቅናት የልጅነት ጥምቀት ዓላማዋ አንድ ነው፡፡ ይህም ልጅነትን ማግኘት ነው፡፡ በመጠመቃችን
ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድነትን ፣ ኀብረትን እንፈጥራለን ፤ ሞትና ትንሣዔውን እንጋራለን ፤ መንፈሳዊ የጸጋ ልጅነትንም
እናገኛለን ፡፡  ያ የልጅነት ጸጋም አንድ ነው (አይለያይም)፡፡ ስለዚህ ይህችን አንዲት ጥምቀት ተጠምቆ ልጅነትን አግኝቶ
ከአንድ ከክርስቶስ ቤተሰብ የተቀላቀለ አንዲት ሃይማኖት ነው የሚከተለው ለማለት አንዲት ሃይማኖት አለ፡፡

 አንዲት ሃይማኖት ማለት በአንድና ለአንድ ተስፋ መጠራት ነው፡፡


በአንድ አምላክ አምኖ አንዲት ጥምቀትን የተጠመቀ የሚጠባበቀው አንድ ተስፋ ነው፡፡ እርሱም ተስፋ መንግስተ ሰማያት
(የዘላለም ሕይወትን) ነው፡፡ ለአንዱ ሌላ ለሌላው ሌላ ተስፋ የለም፡፡ አንድ ተስፋ እንጂ፡፡ ለአንድ ተስፋ የተጠራ በተላያየ
ሃይማኖት ሊሆን አይችልም፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ ስለአንዲት ተስፋ ሰብከውላቸው ያመኑ ክርስቲያኖች አንድ
ሃይማኖት ነበሩ፡፡ ጴጥሮስ ለተገረዙት ፣ ጳውሎስ ደግሞ ለአሕዛብ ቢያስተምርም ፣ ሃይማኖታችን አሁንም አንዲት ናት ፡፡
ስለዚህ ነው አንዲት ሃይማኖት ያለው፡፡

 አንዲት ሃይማኖት ማለት አንድ አካል መሆን ነው፡፡


አንዲት ሃይማኖት ማለት አንድ አካል አንድ መንፈስ መሆን ነው፡፡ ሐዋርያው ይህንን ሲገልፅ “አካልም አንድ እንደ ሆነ
ብዙም ብልቶች እንዳሉበት ነገር ግን የአካል ብልቶች ሁሉ ብዙዎች ሳሉ አንድ አካል እንደ ሆኑ፥ ክርስቶስ ደግሞ እንዲሁ
ነው፤ አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ
አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና… አካል ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና…እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ
እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።  (1 ቆሮ 12፡27)።” ጌታም “እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ ዮሐ 15፡
5።” እንዳለ በአንዱ ግንድ ላይ የተመሠረትን ነን፡፡ የተለያየ ጸጋ ቢኖረንም የአንዱ የክርስቶስ አካል ስለሆንን አንድ ሃይማኖት
ነን እንጂ ብዙ ሃይማኖቶች አይደለንም፡፡
 አንዲት ሃይማኖት ማለት በአንድ መንፈስ መመራት ነው፡፡
ክርስቶስ ካረገ በኋላ ቤተክርስቲያንን የሚመራት በሐዋርያት ላይ የወረደው መንፈስ ቅዱስ ነው (ሐዋ 2፡1)፡፡ ዛሬም
ቤተክርስቲያንን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል የሚመራት መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ”ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል እንዲል
(1 ቆሮ 12፡27)።”  በአንድ መንፈስ ቅዱስ የምንመራ አንድ እምነት አንድም ሃይማኖት እንጂ ብዙ እምነት ወይም ብዙ
ሃይማኖት ሊኖረን አይችልም፡፡ ስለዚህም አንዲት ሃይማኖት ማለት አንድ መንፈስ ቅዱስ የሚመራት ማለት ነው፡፡

 አንዲት ሃይማኖት ማለት አንድ ጊዜ የተሰጠች ማለትም ነው፡፡


ሃይማኖት አንድ ጊዜ የተሰጠች አንዲት ናት፡፡ ይህንንም “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ
ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ
(ይሁዳ 1፡3)።” ይህችም ሃይማኖት ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ሆኗት በአለት ላይ የመሠረታት ናት (ማቴ 16፡16)፡፡ በዚህ
መሠረት ሃይማኖት ደግማ ደጋግማ የምትሰጥ አይደለችም፡፡ ለሐዋርያት የተሰጠችው ያችው ሃይማኖት ናት ዛሬም በእኛ
ዘመን መኖር ያለባት፡፡ በዚህም መሠረት ሃይማኖት የምትጠበቅ (conservative) እንጂ በየጊዜው የምትሻሻል
(progressive) አይደለችም፡፡ ስለዚህ ሃይማኖት አንዲት ናት፡፡

 አንዲት ሃይማኖት ማለት አንዱን ክርስቶስን መምሰል ማለት ነው፡፡


ከአንዱ ከክርስቶስ እርሱን (ክርስቶስን) መምሰል እንዳለብን ተምረናልና ሃይማኖት አንዲት ናት፡፡ ስለዚህ ነገር ሐዋርያው
“ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን
አታውቁምን? … ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር
እንተባበራለን (ሮሜ 6፡4-5)” ብሏል፡፡  ጌታችንም “መምህራችሁ፣ ሊቃችሁ፣ አባታችሁ አንድ ነው (ማቴ 23፡8)፡፡” ብሎ
አስተምሯል፡፡ እኛ ክርስቶስን መምሰል እንዳለብንም ሲናገር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እናንተ
እኔን ምሰሉ (1 ኛ ቆሮ 11፡1)” ብሏል፡፡ ጌታችንም “ከእኔ ተማሩ (ማቴ 11፡29)” “እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ (1 ኛ
ጴጥ 1፡16)” ብሎ ገልጾታል፡፡  እንግዲህ በሃይማኖት መኖር ማለት አንዱን ክርስቶስን መምሰል ከሆነ ሃይማኖትም አንዲት
ናት ማለት ነው፡፡

7 በአጠቃላይ ከሃገረሰባዊ መድሃኒት ጋር ተያይዞ ያለው ታሪካዊ ዳራ በአፍሪካ በኢትዮጵያ ምን ይመስላል


በተጨማሪ ንባብ ማዳበር ግለጽ።
ባህላዊ መድኃኒት በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ 85% የሚሆነው የማህበረሰብ ክፍል የሚኖረው
በገጠር ነው፡፡ በመሆኑም የጤና እንክብካቤው ሽፋን አናሳ በመሆኑ አመራጭ የጤና መጠበቂያ ዘዴ ይገለጻል፡፡ ከዚህ አንጻር
80% የሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል ባህሊዊ መድሀኒት እንደ ዋና የጤና መጠበቂያ ተቋም ይመለከተዋል
(Franklin,W,2011,P,32) በማለት ይገልጻል፡፡ አያይዘውም አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሰው ልጅ ጤና፤ የፈጣሪ ስጦታ
ነው የሚል እምነት ሲሆን ከዚህ እምነት የተነሳ ባህላዊ ሀኪሞች የሰውን ልጅ ጤና ለመፈወስ የተላኩ የፈጣሪ ስጦታዎች
ናቸው የሚል አመለካከት ሲኖራቸው፤ ባህሊዊ ህክምናው ከዘመናዊው ህክምና ይልቅ ተቀባይነት ማግኘቱን
(Franklin,W,2011,P,33) ያስረዳል፡፡ ይሁን እንጂ የባህላዊ ሕክምና ሙያተኞች እውቀት በብሔራዊ የጤና ስርዓት ዘርፍ ችላ
መባልን እና አንዳንዴ ባህላዊ ሀኪሞች በባህሊዊ መድሃኒቶች እና ልምድቸው ላይ በመመርኮዝ በቂ ሳይንሳዊ እና የስነ ዘዴ
ዕውቀት አለመኖሩ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የባህላዊ ህክምና አሰራሮችን የሙያ ብቃት ለማጎልበት ያለው ቁርጠኝነት ዝቅተኛ
መሆን፣ የባህላዊ ህክምና ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም ዓይነት ድጋፍ አለማግኘታቸው፣ የባህላዊ መድኃኒት
ምዝገባ ሂደት በኢትዮጵያ ውስጥ ግልፅ ፖሊሲና ስትራቴጂ ተቀርጾ አለመቀመጡ የኢትዮጵያ ባህልዊ መድሃኒት እውቅና
አንዳይኖረው አድርጓል (Franklin,W, 2011)።

You might also like