You are on page 1of 2

የጣምራ መኖሪያ ቤት ህ/ስ/ማህበር አባላት የስብሰባ ቃለ ጉባኤ

የመሰብሰቢያ ቦታ፦ ባ/ዳ መስቀል አደባባይ


ቀን 2/11/2014 ዓ.ም
እለት፦ ቅዳሜ
ሰአት፦ 4፡00

በስብሰባዉ የተገኙ አባላት

1. አሞኘ በቀለ የኋላ---------------------------አባል


2. ደጀኔ ምትኩ መንገሻ-----------------------አባል
3. ዘላለም በየነ አብተዉ-----------------------አባል
4. ማህሌት ደሳለኝ የስጋት--------------------አባል
5. ፀሃይ ዘለቀ ህብስቱ--------------------------አባል
6. ሽመልስ ጌራ ካሳዉ-------------------------አባል
7. እሸት እናናዉ ከበደ-------------------------አባል
8. ሽመልስ ከበደ ተመስገን ------------------አባል
9. ሁሴን አህመድ እንድሪስ-------------------አባል
10. አበራች ገነት ምናለ-------------------------አባል
11. ዳሳሽ በዉቀት ኪዳኔ------------------------አባል
12. አየለ ላቀዉ አበጀ---------------------------አባል
13. ገነት ባሳዝነዉ ፈንታሁን------------------አባል
14. ስመኝ ጀጀዉ አቦሀይ-----------------------አባል
15. ዮሃንስ ታደሰ ብርሃኑ-----------------------አባል
16. ህይወት ገ/ህይወት በየነ--------------------አባል
17. ዘዉዲቱ ጓንጉል በለጠ--------------------አባል
18. ማየት ደጉ መኮነን-------------------------አባል
19. ጌታቸዉ መኮነን እንግዳ------------------አባል
20. አዛለች ገበየሁ ተገኘ-----------------------አባል

የእለቱ አጀንዳዎች፦

1. ጊዜያዊ አወያይ መምረጥና የማህበሩ አመራሮች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ በመወያየት ግምገማ


ማድረግና ዉሳኔ ማስተላለፍ
2. የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ

ስብሰባዉ አባላቱ ዉይይት በተደጋጋሚ እንዲደረግ ሊቀመንበሩ ቢነገራቸዉም ሊፈጽሙት ባለመቻላቸዉ አባላት
በቴሌግራምና በስልክ በመጠራራት በማህበሩ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ላይ ዉይይት በማስፈለጉ የተደረገ ስብሰባ
ሲሆን አመራሮችን በነጻነት ለመገምገም እንዲቻልና ሊቀመንበሩ ባለመገኘታቸዉ ዉይይቱን በጊዜያዊነት
እንዲመሩ አቶ------------------------------ እና --------------------------------- መርጠን ከላይ የተያዙ አጀንዳዎችን
እንዲታዩ አባላቱ በሙሉ ድምጽ በመስማማት ስብሰባዉ የተጀመረና ሰፊ ዉይይት ከተደረገ በኋላ የሚከተሉትን
ዉሳኔዎች አባላቱ አስተላልፏል።

አጀንዳ 1. የማህበሩ አመራሮች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ በመወያየት ግምገማ ማድረግና ዉሳኔ ማስተላለፍ

Page 1 of 2
አጀንዳ አንድን በተመለከተ ማህበራችን በተለያዩ ጊዜያት ዉይይት እንዲደረግና የፋይናንስ እንቅስቃሴዉን መረጃ
ሪፖርት እንዲቀርብና እንዲያወያዩ በአባላቱ በተደጋጋሚ ለማህበሩ ሊቀመንበሩ ጥያቄ ቢቀርብላቸዉም ሊያወያዩ
ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉና ስራቸዉም ግልጸኝነት የጎደለዉ ከመሆኑ ባሻገር አንዳንድ ዉሳኔዎችን ቃለጉባኤ በማዞር
ብቻ አባላቱ ሃሳብ ሳይሰጥ የሚፈልጉትን ዉሳኔ እያስቀመጡ በአባላቱ የስራ ቦታ በመሄድ በተናጠል አንተ ብቻ ነህ
የቀረህ በማለት እያስፈረሙ ዉሳኔዎችን የሚያስፈጽሙ በመሆኑ፣የማህበር አባላቱ የሚፈለጉ መረጃዎችን
እንዲሰጣቸዉ ሲጠይቁ ባልተገባ ቢሮክራሲ አባላቱን ላልተገባ እንግልትና ወጪ እየዳረጉ መሆኑ፣ የአገልጋይነት
መንፈስን ተላብሰዉ እየሰሩ ባለመሆኑ አባላቱን በእኩል አይን ያለማየት ችግሮች የሚስተዋልባቸዉ በመሆኑ ከጊዜ
ወደ ጊዜ እየባሰባቸዉ የመጣና ሁሉም አባላት የደረሰበትን በከፍተኛ እሮሮ ካቀረበ በኋላ የማህበሩ አባላት ትክክለኛ
አገልግሎት አድሎና ግልጸኝነት ያለዉን አገልግሎት እንዲያገኝ ከማህበሩ አመራሮች መካከል ችግር ያለባቸዉ
ያላቸዉን ማንሳት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ በምትካቸዉ ሌሎች አመራሮችን መቀየር እንዳለባቸዉ በሙሉ
ድምጽ በመታመኑ

1 ኛ. የማህበሩ ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ዮሃንስ ታደሰ ተነስተዉ በምትካቸዉ አቶ/ወ/ሮ------------------------


እንዲተኩና በቀጣይ የማህበሩ ሊቀመንበር ሆነዉ እንዲሰሩ ተወስኗል፡፡

2 ኛ. አቶ ---------------------------------------------------------------------- የነበሩት
በአቶ/ወ/ሮ------------------------------- ተተክተዉ የማህበሩ ---------------------------- ሆነዉ እንዲሰሩ
በሙሉ ድምጽ ተስማምተን የወሰን በመሆኑ የተመረጡ አመራሮች አስፈላጊዉን ሂደት ከማህበራት አደራጅ
ቢሮዎች ጋር በመነጋገር አስፈላጊዉን ሁሉ እንዲፈጽሙ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

አጀንዳ ሁለት፡- የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ማስቀመጥን በተመለከተ

ቀጣይ በማህበሩ መሰራት ያለባቸዉን ጉዳዮች በሰፊዉ አባላቱ ከተወያየ በኋላ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች አስቀምጧል፡፡

 ማህበሩ እስካሁን ከመጀመሪያ ጀምሮ የተከናወኑ ተግባራትንና የወጡ ወጪዎች ሪፖርት ለጠቅላላ አባላት አቅርቦ
ያላስገመገመነ እንደ አስፈላጊነቱ ኦዲት መደረግ የሚገባቸዉ ጉዳዮች ካሉ ለመወሰን እንዲመች በአድስ የተመረጡና ነባር
የቀጠሉ አመራሮች እስከ ነሐሴ 16 ድረስ ሪፖርቱን በማዘጋጀትና በማህበሩ የተከፈቱ የባንክ አካዉንቶችን ባላንስ
ጭምር በማጣራት የስብሰባ ጥሪ በማድረግ ሪፖርቱን እንዲያሰማ ተወስኗል፡፡
 የቀጣይ ስራዎችንና አገልግሎቶችን በተመለከተ በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት አመራሮች በቅንነትና በታማኝነት
ያለአድሎ እንዲያገለግሉ ጠቅላላ ጉባኤዉ አደራ በመስጠት ስብሰባዉ ተጠናቋል፡፡

Page 2 of 2

You might also like