You are on page 1of 13

የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

6
www.tlcfan.org 0
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

የእግዚአብሔር የምሕረት ሕግ

ስለሞን የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ ሰርቶ ከጨረሰ በኋላ የምረቃ ስነስርዓት አደረገ።


በመንፈስ ተሞልቶም ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። በጸሎቱም እግዚአብሔር ሃጢያትን በሚያደርጉ ሰዎች
ላይ ፍርድ እንደሚያመጣና ምሕረቱን ፈልገው ንስሃ ሲገቡ ደግሞ ፍርዱ እንደሚያቆም ተናገረ።

“ሕዝብህ እስራኤል አንተን ስለ በደሉ በጠላቶቻቸው ፊት ድል በተመቱ ጊዜ፥ ወደ አንተ


ቢመለሱ፥ ስምህንም ቢያከብሩ፥ በዚህም ቤት ቢጸልዩና ቢለምኑህ፥አንተ በሰማይ ስማ፤
የሕዝብህንም የእስራኤልን ኃጢአት ይቅር በል፥ ለአባቶቻቸውም ወደ ሰጠሃት ምድር
መልሳቸው። አንተን ስለ በደሉ ሰማይ በተዘጋ ጊዜ ዝናብም ባልዘነበ ጊዜ፥ ወደዚህ ስፍራ
ቢጸልዩ፥ ስምህንም ቢያከብሩ፥ ባስጨነቅሃቸውም ጊዜ ከኃጢአታቸው ቢመለሱ፥ አንተ
በሰማይ ስማ፤’’ 1.ነገ.8፥33-36

ሰለሞን ጸሎቱን የወሰደው ከእንቢተኝነት ሕግ ነው። ይህም ሕግ በዘሌዋውያን. 26፥40-42


የሚገኝ ሲሆም ሕጉ እንዲህ ይላል፦ “በእኔም ላይ በእንቢተኝነት ስለ ሄዱብኝ የበደሉኝን በደል፥
ኃጢአታቸውንም፥ የአባቶቻቸውንም ኃጢአት ይናዘዛሉ። እኔም ደግሞ በእንቢተኝነት ሄድሁባቸው፤ ወደ
ጠላቶቻቸውም ምድር አገባኋቸው፤ ነገር ግን በዚያን ጊዜ ያልተገረዘው ልባቸው ቢዋረድ፥
የኃጢአታቸውንም ቅጣት ቢቀበሉ፥እኔ ለያዕቆብ የማልሁትን ቃል ኪዳኔን አስባለሁ፤ ደግሞ ለይስሐቅና
ለአብርሃም የማልሁትን ቃል ኪዳኔን አስባለሁ፤ ምድሪቱንም አስባለሁ።” አለ። እግዚአብሔር በበደሉት
ላይ ሊፈርድ ወደ ጠላት ምድር ማስገባትም አንዱ መንገዱ ነው። ነገር ግን ሃጢያታቸውን ቢናዘዙና
ከሃጢያታቸው ቢመለሱ ወደ ምድራቸው እንደሚመልሳቸው ቃል ይገባል።

እግዚአብሔር ፍርድን የሚያመጣው ሰውን ለማረም ነው። ይሁንና ፍርዱ ሰዎች


ሃጢያታቸውንና አመጻቸውን አምነው ተናዘውና ወደ እርሱ እስኪመለሱ አያበቃም። ለብዙዎች ዛሬ ይህ
ሕግ በሕይወታቸው ፍጻሜን አላገኘም። ምክንያቱም ብዙዎች ስለሚሰሩት ስራ ከልባቸው ተጸጽተው
ንስሃ ስለማይገቡና ወደ እግዚአብሔር ስለማይመለሱ ነው። የፍርድ አላማ አንድና ግልጽ ነው። ይህም
ቀጥቶ እርማትን በንስሃና ምሕረት ማምጣት ነው። ዳዊት ንስሃ ገባ ምንም እንኳን ሃጢያቱ የበዛች
ብትሆንም ከልቡ ንስሃ ገብቷልና እግዚአብሔር ምሕረትን አበዛለት ይቅርም አለው። በመሳፍትን
ዘመንም ሕዝቡ እግዚአብሔር እንደበደለ አውቆ ንስሃ ሲገባ እግዚአብሔር ከተበተኑበት ከጠላት ሃገር
ይሰበስባቸውና በላያቸው ላይ የተሾሙትን ጠላቶቻቸውን ያዋርድላቸው ወይም ያስገዛላቸው ነበር።
መሳፍንትን ዘመን ስናጠና ሕዝቡ ንስሃ ሳይገቡ አንድ ጊዜም የእግዚአብሔር ፍርድ አቁሞ አያውቅም።
ንስሃ በሌለበት የእግዚአብሔር ፍርድ ይኖራል።

ወደ ዘፍጥረት ተመለስን አዳምን ብንመለከት በእግዚአብሔር በማመጹና ትዕዛዙን


ባለመጠበቁ የሞትን ፍርድ ሲቀበል እናገኘዋለን። ይሁንና ወዲያውኑ አለመቀሰፉ እግዚአብሔር
ምሕረቱንና ለንስሃ ጊዜ መስጠቱን ያሳያል። ይህ ሞቱ የሚፈጸምበት ወቅት በሰዓት እረዘመለት ይህም
ጊዜ በመበስበስ በማርጀት ተብሎ ይታወቃል። ይህ የተሰጠው እድሜ ወደ እግዚአብሔር በንስሃ
ለመመለስ የሚያስችል በቂ ጊዜ ነበር። በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ ብሎት ነበር። አንድ ቀን ደግሞ
በእግዚአብሔር ፊት እንደ አንድ ሺ ቀን ነበር። (መዝ.90፥4, 2.ጴጥ.3፥8) ስለዚህ አዳም ወዲያው
አልሞተም። ስለዚህም አዳም ከ930 ዓመት የምድር ቆይታ በኋላ ሞተ። ይህም ለአንድ ሺ አመቱ ሰባ
አመት ብቻ ሲቀረው ነው። ይህ እግዚአብሔር ለአዳም ያሳየው የምሕረትና የንስሃ ዘመን ነበር።

www.tlcfan.org 1
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

“በሁለት ወይም በሦስት ምስክሮች አፍ ሞት የሚገባው ይገደል፤ በአንድ ምስክር አፍ


አይገደል። . . .ማናቸውም ሰው ቢኰራ፥ በዚያም አምላክህን እግዚአብሔርን ለማገልገል የሚቆመውን
ካህኑን ወይም ፈራጁን ለመስማት ባይወድድ፥ ያ ሰው ይሙት፥ ከእስራኤልም ዘንድ ክፋትን አስወግድ፤
” ዘዳ.17:፥6,12 ማንም ካህን የእግዚአብሔርን የሞት ፍርድ ወደ ጎን ማድረግ አይችልም። በምስክር ከጸና
የግድ ሃጢያተኛው የግድ ሞትን ይቀበላል። ነገር ግን ማንኛው አይነት በደለ በሁለት ሰዎች በካከል ቢደረግ
ዳኛው ሆነ ካህኑ ይቅር የማለት መብት አሁንም የለውም ነገር ግን የተበደለው ሰው ብቻ ለበዳዮ
ይቅርታን ወይም ምሕረትን መስጠት ይችላል። ለምሳሌ ብናይ አንድ ሰው ሰርቆ ቢሆንና ዳኛው
ምስክርን ሰምቶ በሌባው ሃጢያተኛ ሰው 80,000 እንዲከፍል ቢያዘው ፍርዱ ይዘጋል። ነገር ግን
የተፈረደለት ሰው ግን ብሩን መቀበል ወይም መማር ይችላል። ወይም ብሩን ለበዳዮ ሊቀንስለት ይችላል።
ንስሃን አይቶ ተበዳዮ በዳዮን ይቅር ማለት ፈጽሞ ይችላል። እግዚአብሔርን ደግሞ ሰዎች ሲበድሉት ይቅር
ማለት መልሶ ወደ ክብሩ በምሕረቱ ማምጣት የእርሱ ብቸኛ መብት ነው።

“እግዚአብሔር በጸጋው ስጦታና በመጥራቱ አይጸጸትምና።እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር


እንዳልታዘዛችሁ፥ አሁን ግን ከአለመታዘዛቸው የተነሣ ምሕረት እንዳገኛችሁ፥እንዲሁ
በተማራችሁበት ምሕረት እነርሱ ደግሞ ምሕረትን ያገኙ ዘንድ እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም።
እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና
ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ
የለውም።የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው?ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ
ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው? ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ
ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።” ሮሜ.11

“ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ


ዘንድ፥ መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ
ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።”ፊሊ. 2፥10, 11,

ይህን ጥቅስ ጳውሎስ የጠቀሰው ከኢሳያስ 45፥23, ላይ ነው። ሙሉ ጥቅሱ እንዲህ ይላል፦

“እናንተ የምድር ዳርቻ ሁሉ፥ እኔ አምላክ ነኝና፥ ከእኔም በቀር ሌላ የለምና ወደ እኔ ዘወር በሉ
ትድኑማላችሁ። ቃሌ ከአፌ በጽድቅ ወጥታለች፥ አትመለስም፦ ጕልበት ሁሉ ለእኔ
ይንበረከካል፥ ምላስም ሁሉ በእኔ ይምላል ብዬ በራሴ ምያለሁ። ስለ እኔም፦ በእግዚአብሔር ዘንድ
ብቻ ጽድቅና ኃይል አለ፥ ወደ እርሱም ሰዎች ይመጣሉ፥ በእርሱም ላይ የተቈጡ ሁሉ ያፍራሉ።
የእስራኤልም ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር ይጸድቃሉ፥ ይመካሉም ይባላል።”

እግዚአብሔር በራሱ ስም ማለ። ዘሁ. 14፥21, “ነገር ግን እኔ ሕያው ነኝና (AS I LIVE)
በእውነት የእግዚአብሔር ክብር ምድርን ሁሉ ይሞላል።" ብዙዎች ዛሬ ዙሪያቸው የሚሆነውን እያዮ
እግዚአብሔር በራሱ ምሎ የገባውን ቃል ይፈጽመዋል ብሎ ለማመን ይከብዳቸዋል። የሰው ልጆችን ሁሉ
እንደሚያንበረክክና ወደ ንስሃና ምሕረቱ እንደሚያመጣቸው ለማመን ይከብዳቸዋል። ጳውሎስ
እግዚአብሔር በራሱ እንደማለን የእስራኤል ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር እንደሚጸድቁ ሁሉን አልጻፈልንም።
ነገር ግን በሮሜ 11፥31 ላይ “እንዲሁ በተማራችሁበት ምሕረት እነርሱ ደግሞ ምሕረትን ያገኙ ዘንድ
እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም።” እኛ በተማርንበት አይነት ምሕረት ደግሞ እስራኤል ሁሉ ምሕረትን
እንደሚቀበሉ ይነግረናል። እንግዲህ የእስራኤል ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር የሚጸድቁ ከሆነ አሕዛብም ሁሉ
በእግዚአብሔር ይጸድቃሉ። ጉልበት ሁሉ ይንበረከካል የሚለው ትክክለኛ ሃሳቡን ከኢሳያስ ተነስተን
ስንመለከተው እውነቱን በግልጽ እንረዳለን።

www.tlcfan.org 2
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ይህም እንደ የኢሳያስ ትንቢት በነጩ ዙፋን ፊት እንደሚፈጸም አምናለሁ። ይህም ሁሉ


በሸመገለው ፊት ተነስተው እንደ ስራቸው ፍርድን ሲቀበሉ ነው። ከዚያን ቀን በኋላ አንድም የማያምን
ሰው አይኖርም። 1 ቆሮ. 12፥3, ላይ ጳውሎስ እንዲህ ይለናል፦ "ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ
ሲናገር፦ ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፥ በመንፈስ ቅዱስም ካልሆነ በቀር፦ ኢየሱስ ጌታ ነው
ሊል አንድ እንኳ እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ።” እንደ ኢሳያስና ጵውሎስ ትንቢት በዚያን ቀን ሁሉ
ይንበረከካል ኢየሱስ ጌታ ነው ይላል። በነጩ ዙፋን ፊት ኢየሱስ ጌታ ነው ሲሉ በመንፈስ ቅዱስ ነው።
ንስሃ ይገባሉ በሰሩትም ይጸጸታሉ። ሁሉ በዚያን ቀን በፍርድ በኩል ምሕረትን ይቀበላሉ። ያቆብም
እንዳለው ምሕረት በፍርድ ላይ ይመካል የሚለው ለሁሉ ግልጽ ይሆናል።

አንዳንድ ሰዎች በዕብራውያን. 9፥27 ”ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ
እንደ ተመደበባቸው፥” የሚለውን ቃል በተሳሳተ መልኩ በመረዳታቸው የተነሳ ሞት የመለወጥ ወይም
ምሕረትን የመቀበል ማብቂያ እድርገው ያዮታል። ይህም የእግዚአብሔር ቃልና ሕግጋት በትክክል
ካለመረዳት ወይም ካለማወቅ የሚመጣ ነው። እውነት ነው የነጩ ዙፋን ፍርድ የሚመጣው ከሞት
በኋላ ነው። ነገር ግን የትም ቦታ ላይ ቃሉ ሞት ለሰው የምሕረት መቀበያ ዘመን ወም ጊዜ ማብቂያው
እንደሆነ አይነግረንም። ይህ አይነት አስተሳሰብ ከእግዚአብሔር ሳይሆን ከወግና ስርዓት ከሃይማኖት
የመጣ ነው።

ጳውሎስ ይህን ስለሚያውቅና ስለሚያምን ጉልበት ሁሉ እንደሚንበረከክና ምላስ ሁሉ


እየሱስ ጌታ ነው ብሎ እንደሚመሰክር ተናገረ። ይህ ግን የሚሆነው በእግዚአብሔር ክብር እንደሆነም
ነብዮ ኢሳያስ ይተነብያል። ይህም እግዚአብሔር በራሱ ስለማለና ሁሉን በክብሩ ሊሞላ በራሱ ምሎ ቃል
ቃል ስለገባ ነው። ቃሎቹ ደግሞ የታመኑ ናቸው። ሰውን በግድ እንዲያምንና በግድ እንዲለወጥ
በማድረግ ውስጥ ምንም ክብር የለም። ሰውን ኢየሱስ ትክክለኛ እንደሆነ ለማሳየት ማሰቃየት በእሳት
ውስጥ በማቃጠል ምንም ክብር የለበትም። ነገር ግን ሰዎች በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ጽድቅና ኃይል
አለ በማለት ወደ እርሱም ሰዎች ሁሉ ይመጣሉ። ኢሳ.45፥24 እርሱ ጌታ እንደሆነም በፍቃዳቸውም
ይመሰክራሉ። እሳቱም እነርሱን ሳይሆን በእነርሱ ላይ ይህን እንዳያዩ የጋረዳቸውን መጋረጃና ገልባቸውን
ይበላላቸዋል። ይህ ሲሆን እግዚአብሔር በዘሁ.14፥21 ላይ የተናገረው መፈጸሙን እናውቃለን።

ከላይ እንዳየነው ንስሃ የምሕረት ማግኛ ብቸኛ ቁልፍ ነው። በንጉስ ዳዊት ሕይወት ውስጥ
በቃሉ እንደምናየው ምሕረት ፍርድን አይሰርዝም። በፍርድ ቅጣቱን ለሰው በመግለጥ ወደ ቀደመው
ስፍራው ሰውን በምሕረት ይመልሰዋል። በራእይ. 20፥14 " ሞትና ሲኦልም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣሉ።
ይህም የእሳት ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው።”

የመጀመሪያው ሞት በአዳም ላይ መጥቷል ይህም መበስበስን አመጣበት። ይህም ሞት


በእርሱ ወደ ሁላችን መጣ። (ሮሜ.5፥12) ሁለተኛውን ሞት በጳውሎስና በዮሐንስ በቃሉ ውስጥ
ተደጋግሞ ተጠቅሶ እናገኘዋለን። ጳውሎስ ይህን ሁለተኛ ሞት እለት እለት ለአዳማዊው ማንነት መሞትን
ከክፋትና ከአማጽ መመለስ እንደሆነም ያስተምራል። በዚያ በነጩ ዙፋን ፊትም የሚሆነውም
የሚበሰብሰው ድንኳንና መጋረጃ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከሰው ልጆች ሁሉ ላይ ይወገዳል።
በመጀመሪያው ትንሳኤ ያልተነሳ ሰው ሁሉ በዚህ በነጩ ዙፋኑ ፊት ለመቆም የሚይስችለውን
የጠቅላላው ትንሳኤ ይቀበላል። በዚያም ለሁለተኛው ሞት ይታደላል ወይም እድል ይሰጠዋል። ይህም
በእግዚአብሔር ክብር ሰውን ሁሉ በማንበርከክ ነው። “ዳሩ ግን የሚፈሩና የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ
ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው
በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው።” ራእይ.21፥8

www.tlcfan.org 3
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ይህ በሕጉ የሞተውን ሰው በመንካትና ሩቅ ሃገር በመሄድ የመጀመሪያውን ፋሲካ በዓል


ያላደረጉ ሁሉ የሁለተኛውን ፋሲካ በሁለተኛው ወር ሊያደርጉ እድል እንደተሰጣቸው በጥላዊ ትንቢት
የተቀመጠው ዘመኑን ጠብቆ በ8,000 ዓመት በነጩ ዙፋን ፊት ሁሉ ለበጉ ሲንበረከክ የሚፈጸምበት ቀን
ነው። ሙት ከሆነው ከአዳም የተወለደ ሰው ሁሉ የሞተ ሰው ነክቷል። በምድር ላይ የሞተ ሰው ያልነካ
ምንም አይነት ሰው የለም። ርቀው ፋሲካ ያመለጣቸው ደግሞ በተለያያ ሃይማኖትና ባሕል ተጽኖ ውስጥ
ሆነው ስለ ፋሲካው ኢየሱስ ምንም ጭራሽ ያልሰሙትን ወንጌል ለምስማት እድል ያላገቡትን ሁሉ
ይጨምራል። ይህ እድላቸው ሁለተኛው ፋሲካ ነው። በዚያን ቀን የወጉት ሁሉ ሳይቀሩ ያዩታል ያምኑታል
ምህረትም ይቀበላሉ። እርሱ እንደ ገና እንደ ሳሙና አጣቢ በእሳት አጥቦና አንጽቶ ፊቱ ያቆማቸዋል።
ይህም በእሳት እንደሚድን የሚዳንበት የደህንነት ቀን ነው። በትልቅ እሳትና ትኩሳት ፍጥረት ሁሉ
ከታሰረበት እስራት ይፈታል። ምክንያቱ በገዛ ፍቃዱ ስላልተገዛ ነው። “ፍጥረት ለከንቱነት ተገዝቶአልና፥
በተስፋ ስላስገዛው ነው እንጂ በፈቃዱ አይደለም፤” ሮሜ.8፥20 ተስፋውም ሁለተኛው ፋሲካም ነው።

“በመጀመሪያውም ወር በአሥራ አራተኛው ቀን በመሸ ጊዜ በሲና ምድረ በዳ ፋሲካን አደረጉ፤


እግዚአብሔር ሙሴን እንዳዘዘው እንዲሁ የእስራኤል ልጆች አደረጉ። በሞተ ሰው ሬሳ የረከሱ ሰዎችም
ነበሩ፥ ስለዚህም በዚያ ቀን ፋሲካን ያደርጉ ዘንድ አልቻሉም። በዚያም ቀን ወደ ሙሴና ወደ አሮን ቀረቡ።
እነዚያም ሰዎች፦ በሞተ ሰው ሬሳ ረክሰናል፤ በእስራኤል ልጆች መካከል በጊዜው ቍርባን ለእግዚአብሔር
እንዳናቀርብ ስለ ምን እንከለከላለን? አሉት።ሙሴም፦ እግዚአብሔር ስለ እናንተ የሚያዝዘውን እስክሰማ
ድረስ ቈዩ አላቸው። እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፦ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ
ንገራቸው፦ ከእናንተ ወይም ከትውልዶቻችሁ ዘንድ ሰው በሬሳ ቢረክስ፥ ወይም ሩቅ መንገድ
ቢሄድ፥ እርሱ ደግሞ ለእግዚአብሔር ፋሲካን ያድርግ።በሁለተኛው ወር በአሥራ አራተኛው ቀን
በመሸ ጊዜ ያድርጉት፤ ከቂጣ እንጀራና ከመራራ ቅጠል ጋር ይብሉት። ከእርሱም እስከ ነገ ምንም
አያስቀሩ፥ ከእርሱም አጥንትን አይስበሩ እንደ ፋሲካ ሥርዓት ሁሉ ያድርጉት ነገር ግን ንጹሕ የሆነ ሰው
በመንገድም ላይ ያልሆነ ፋሲካን ባያደርግ፥ ያ ሰው ከሕዝቡ ዘንድ ተለይቶ ይጠፋል፤ የእግዚአብሔርን
ቍርባን በጊዜው አላቀረበምና ያ ሰው ኃጢአቱን ይሸከማል።” ዘሁ.9

በእግዚአብሔር ክብር ሰው ወደ ንስሃ ሰለሚመጣ ብዙዎች እንደሚያስቡት ለዘላለም እስከ


ዘላለም የሚሰቃይ ሳይሆን እንደ ሕጉ ሁለተኛውን ፋሲካ ያደርጋል። ይህ የጠቅላላው ሰው ትንሳኤ ብቻ
ሳይሆነ ጠቅላላው ሰው ምሕረት የሚቀበሉበት ቀን ነው። እሳት የእግዚአብሔር ሕግ ምሳሌ ነው።
ዘዳ.33፥2 የእግዚአብሔር ቃልም በእሳት ተመስሏል። (ኤር. 23፥29). ይህ ከዙፋኑና ከፊቱ የሚመነጨው
እሳት የሚያሳየው ከእግዚአብሔር የሚወጣውን ቃልና ሕግ ነው። ዳን. 7፥9,10 ይህ የእሳት ፈሳሽ በራእይ
ላይ የእሳት ባሕር ሆኖ እናየዋለን። ራእይ.20፥14. ይህ የእሳት ፍርድ የእግዚአብሔር ሕግ ፍርድ ሲሆን
የእግዚአብሔር ሕግ ደግሞ ምሕረትን የያዘ ነው። በነጩ ዙፋን ፊት ሁሉም በእሳት ባሕሩ በእግዚአብሔር
ሕግ ሰው ሁሉ የሚፈረድበት ቢሆንም እያንዳንዱ ሰው የሰራውን ስራ ያህል በልኩ ቅጣቱን ይቀበላል።
ነገር ግን ሁላችን ልናውቅ የሚገባው ለዘላለም እስከ ዘላለም የሚቆይ ቅጣት በእግዚአብሔር ሕግ ውስጥ
ፈጽሞ የለም።ከቅጣቱ በላይ አልፎ የሚቀጣ የሚያሰቃይ ምንም አይነት የእግዚአብሔር ሕግ የለም።

በፍርዱ ቀን በጠቅላላው ትንሳኤ እለት አንዳዶች እግዚአብሔርን የሚያውቁት ሰዎች ሲገኙ


አንድ አንዶች ደግሞ እግዚአብሔርን አያውቁም። ንጹ የሆኑ ሰዎች ነገር ግን የሚገባቸውን ያላደረጉ
ይገኛሉ። እነርሱ ደግም ሃጢያታቸውን ስለሚሸከሙ በዚያን ፍርድ ቀን እጅግ ይገረፋሉ። ይህም ማድረግ
የሚገባቸውም ዘሁልቁ ላይ እንዳየነው በጊዜው ስላላደረጉ ነው። በጊዜው አድርገው ቢሆን
የመጀመሪያውን ፋሲካ ካደረጉት ጋር በአንድነት በመጀመሪያው ትንሳኤ ተነስተው ከኢየሱስ ክርስቶስ
ጋር በምድር ላይ ለአንድ ሺ አመት ይነግሱ ነበር።

www.tlcfan.org 4
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

“የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤ ያላወቀ ግን
መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ
ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል። በምድር ላይ እሳት ልጥል
መጣሁ፥ አሁንም የነደደ ከሆነ ዘንድ ምን እፈልጋለሁ? “(ሉቃ.12፥47,48)

በመጨረሻው ፍርድ ዘመን ቀድመው የማያምኑ የነበሩ ሰዎች በሙሉ ጽድቅን ይማራሉ።
“ፍርድህን በምድር ባደረግህ ጊዜ በዓለም የሚኖሩ ጽድቅን ይማራሉና ነፍሴ በሌሊት ትናፍቅሃለች፥
መንፈሴም በውስጤ ወደ አንተ ትገሠግሣለች።”(ኢሳ. 26፥9) ይህም ወደ እግዚአብሔር ልጅነት ክብር
በፍጥረት ኢዮቤልዮ እስከሚገቡ ድረስ የሚቀጥል ነው። በዚያም ቀን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆናል።
(1.ቆሮ.15፥28).

“የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ይጠባበቃልና። ፍጥረት ለከንቱነት


ተገዝቶአልና፥ በተስፋ ስላስገዛው ነው እንጂ በፈቃዱ አይደለም፤ተስፋውም ፍጥረት ራሱ ደግሞ
ከጥፋት ባርነት ነፃነት ወጥቶ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት (ኢዮቤልዮ)
እንዲደርስ ነው። ፍጥረት ሁሉ እስከ አሁን ድረስ አብሮ በመቃተትና በምጥ መኖሩን
እናውቃለንና።”(ሮሜ.8፥19-22)

ሰው ያሰቃያል እግዚአብሔር ግን ይቀጣል ደግሞም በጽድቅ ፍርድን ይፈርዳል። በሮም


የሕግ ስርዓት ውስጥ ጽድቅን ማስተማር አይገኝበትም። የሮም ሕግ ያጠፋውን ሁሉ አንስቶ በመስቀል
ይሰቅላል። ከሁለት ክፍለ ዘመን በፊት በእንግሊዝ ሃገር ውስጥ የዳቦ ቁራሽ የሰረቀ ይሰቀልም ነበር። የከፋ
ቅጣት የሰዎች ችግርን አመጽን የማስወገድ የሙከራ መንገድ ነው። የእግዚአብሔር ሕግ ጽድቅን ማድረግ
የመጀመሪው አላማው ሲሆን ማረም፣ ስርዓት ማስያዝ፣ አመጽ መልሶ እንዳይደረግ ማድረግ ደግሞ
የሁለተኛ ክፍል ነው። (Justice is primary, and deterrence is secondary)

ሰው በሰው ልጆች ሕግና ስርዓት መሰረት ሲቀጣ ወይም ብዙ ይቀጣል ወይም ጥቂት ይቀጣል
እንጂ ትክክለኛ ቅጣት ማስተላለፍ ሰው ፈጽሞ አይችልም። እግዚአብሔር ግን ማንንም አሳንሶም ሆነ
አስበልጦ አይፈርድም። ሁሉ እንደሚገባው ቅጣቱን ይቀጣል ወይም ይፈረድበታል። የእግዚአብሔር
ፍርድ የተሰራውን ሃጢያት ልክ ያህል ብቻ የሚቀጣ ነው። እግዚአብሔር ቅጣቱን አያንስም ወይም
አይጨምርም። ሰው 1000 ብር ቢሰርቅ በሰረቀው ፋንታ ሁለት እጥፍ እንዲከፍል እግዚአብሔር በሕጉ
ያዛል። ይህ ሰው ከፍርድ ቅጣት ውስጥ ላለመውደቅ አስር ሳንቲም ሳያጎድል ሊከፍል ይገባዋል። ሃጢያቱ
በልኩ ቅጣቱን ያገኛል። ከዚህ በላይ ለዘላለም ሲከፍል እንዲኖር እግዚአብሔር አያዝም። ይህ ሰው
እዳውን ሲጨርስ ነጻ ይመጣል። ለዚህ ነው ኢየሱስ ወደ ውጭ ጣሉት የመጨረሻውን ሳንቲም እስኪከፍል
ድረስ የሚለው። ይህ ሰው ከፍሎ ሲጨርስስ? እንደ እግዚአብሔር ሕግ ነጻ ይወጣል ወይም በጸጋው ስር
ይሆናል።

ከዚህ ሁሉ ያለፈ የእግዚአብሔር ታላቁ የምሕረቱ ሕግ ደግሞ የኢዮቤልዮ ሕግ ነው።


የኢዮቤልዮ ሕግ የእግዚአብሔር የመጨረሻውና የጸጋውን ጣራ የሚያሳይበት ታላቁን ምሕረቱ ማሳያ
ሕግ ነው። ያቆብ ኢዮቤልዮን ሲረዳ ምሕርት በፍርድ ላይ ይመካል ብሎ አስቀመጠው። ምክንያቱም
ኢዮቤልዮ ይቅር የማይለው ሃጢያት የለምና ነው። የኢዮቤልዮ ሕግ ሃጢያቱ እዳው ትልቅ ቢሆን ትንሽ፣
ሰውየው ሊከፍለው ባይችል እኳን የሚበዠው ቢያጣ ወይም የሚቤዠውን በእልከኝነት አልቀበልም ቢል
ኢዮቤልዮ ሕግ በሚፈጸምበት ቀን ግን ነጻ መውጣቱ ግድና የማይቀር ጉዳይ ነው። ዘዳ.25፥1-3
አልፈልግም እንኳን ቢል ነጻ ፍቃድ የሚባል ነገር ቢኖር እንኳን ይህ ኢዮቤልዮ ሕግ ከሰውየው ይህን የነጻ
ፍቃድ መብቱን ይነጥቀዋል።

www.tlcfan.org 5
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ከሃጢያተኞች ዋንኛ የሆነው ሳኦልን በደማስቆ አግኝቶ ያበረከከው አይነት ብርሃን ነው።
ጳውሎስ ይህን የመጣውን ጌታ ወዶ ሳይሆን በግዱ ተቀበለ። ጌታ ለዚህ ጥላ እንዲሆን በክብሩ ተገልጦ
አንበረከከው። (ሐዋ.9) ይህም የኢዮቤልዮ ሕግ አሰራር የገለጥበት ዘንድ ነው። ይህ ሕግ ስለ ጌታ ምንም
ሳያዉቁ የሞቱትንና እያወቁም በራሳቸው ምርጫ በእርሷ ላይ እንደ ሳኦል አምጸው በሃጢያት ባርነት
ሊኖሩ የወደዱትን ሁሉ መጨረሻቸውን የሚያሳይ ሕግ ነው። ይህ አይነት ሰው ከእግዚአብሔር ነጻነትን
በመቀበል ወደ እርስቱ መመለሰን የግድ ይሰጠዋል። በኢዮቤልዮ ሕግ መዳን ወይም ወደ እርስታችን
መመለስ ተፈቅዶልናል መጥፋትና መሰቃየት በባርነትም ለዘላለም ለመኖር ብትፈልግም የለም። ሰውን
ለማሰቃየትና መሰቃየሁን የምትሰብኩ ካላችሁ እኔና እኔ የማመልከው እግዚአብሔር እንዲ አይነት ሰውን
ስለ ሃጢያቱ ማሰቃየት የለንም። ሰው ስለ ሃጢያቱ ቅጣትን ይቀበላል። ቅጣቱም የሃጢያቱን ልክ ያህል
ይሆናል። ቅጣቱ ሲፈጸም ከእስራቱ ወይም ከተጣለበት ቅጣት ይፈታል። ይህ የእግዚአብሔር የምሕረት
ሕግና አሰራር ነው። ይህ ማለት ግን እንደ ፈለግን በሃጢያት እንጨማለቅ ወይም እንኑር ማለት
አይደለም። ምክንያቱም ሁሉ ሃጢያት ቅጣትና ፍርድ አለው። ይህ ባይሁን ኢየሱስ በመስቀል ላይ
መሞት አያስፈልገውም ነበርና ይህን አርነታችንን ለስጋችን ምክንያት አንስጥበት።

ሉቃስ 12 ላይ ያለውን ከላይ እንደተመለከትነው። ሃጢያት የሰራው ሰው ሁሉ አማኝ ቢሆን


የማያምን ሰው መገረፍ የሚገባውን ግርፊያ በመጨረሻው ዘመን እንደሚቀበል የእግዚአብሔር ቃል
ይናገራል። የዚህን ግርፊያ መልክና እንዴት እንደሚሆን ለማየት የግድ ኢየሱስ ይህን ተነስቶ የተናገረበትን
የእግዚአብሔርን ሕግ ወደኋላ ተመልሰን ልናጠናና ኢየሱስ ምን እያለ እንደሆነ ልናውቅ ይገባናል።

“1. በሰዎች መካከል ጠብ ቢሆን፥ ወደ ፍርድም ቢመጡ፥ ፈራጆችም ቢፈርዱባቸው፥ ጻድቁን።


ደኅና ነህ፥ የበደለውንም። በደለኛ ነህ ይበሉአቸው። 2. በደለኛውም መገረፍ ቢገባው
እንዲገረፍ ፈራጁ በፊቱ በምድር ላይ ያጋድመው፤ የግርፋቱም ቍጥር እንደ ኃጢአቱ
መጠን ይሁን። 3. ግርፋቱም አርባ ይሁን፤ ከዚህ በላይ ጨምሮ ብዙ ግርፋት
ቢገርፈው ወንድምህ በፊትህ ነውረኛ ይሆናልና ከዚህ በላይ አይጨመርበት።” ዘዳ.25

ኢየሱስ ይህን ሕግ በሉቃስ.12፥42-49 ላይ የጠቀሰው ነው። እግዚአብሔር ታማኝ ባሪያዎቹን


ባለው ሁሉ ይሾማቸዋል” (12፥44) ነገር ግን ጌታዮ ይዘገያል ብሎ የተለያዮ የክፉ ነገሮችን የሚያደርግ
አውቆ የሚያጠፋው አውቆም ፋሲካን ያላደረገ ባሪያ ግን ስላጠፋው ነገር ብዙ ይገረፋል። ነገር ግን
ባለማወቅ የሚያጠፏ ጥቂት ይገረፋሉ እንጂ አላወቁም ተብሎ እነርሱም ከግርፊያም አያመልጡም።
ይህም ግርፊያ በሕጉ መሰረት እስከ አርባ ጅራፍ የሚደርስ ነው እንጂ ለዘላለም እስከ ዘለዓለም አይደለም።

እዚህ ላይ ትልቁ ከኢየሱስ ትምህርት የምንረዳው ሃጢያተኛ ፍርድን እንደሚቀበልን ፍርዱን


ሲጨርስ እንደ ሚለቀቅ እንጂ በሲኦል ለዘላለም እንደማይቃጠል ነው። ኢየሱስ ግን ምሳሌውን ሲጨርስ
ይህ የእግዚአብሔር ሕግ ራሱ የፍርድ እሳት እንደ ሆነ ነግሮናል። ቁጥር.49, ኢየሱስ ሰዎች ያሰቃያል በእሳት
(torture) ያደርጋል ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የእግዚአብሔርን ባሕሪ የሚጻረር ነው። የእርሱ ምኞትና ፍላጎት
ግን ምድርንም ሆነ ሰዎችን በሕጉ በእሳቱ መመለስ ደግሞም መልሶ ማቆም ወይም ማደስ ነው። ነገር
ግን ይህ የነጩ ዙፋን ፍርድ ገና አልመጣም ወይም አልተፈጸመም። ከታላቁ ፍርድ በፊት ክርስቶስ ዳግም
ሊመለሰና ድል የነሱ ጻድቃን ደግሞ በመጀመሪያው ትንሳኤ ተነስተው ከእርሱ ጋር ለ1,000 ዓመት
ሊነግሱ ይገባል።ራዕይ.20፥1-6 ይህ 1,000 ዓመት ሲያልቅ በ8,000 መጀመሪያ ላይ እግዚአብሔር
በኢየሱስ የተናገረውን ይህ የነጩ ዙፋን ፍርድ ያከናወናል።

www.tlcfan.org 6
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ኢየሱስ በሉቃስ 12 እንደ ተናግረው ይህ የነጩ ዙፋን የፍርድ እሳት ለማያምኑ ብቻ እንዳል
ሆነ የእርሱ የሆኑ ባሪያዎቹም የሚፈረዱት በዚሁ እሳት እንደ ሆነ ያስረዳናል። ኢየሱስ ይህ እሳት በእርሱ
ዘመን ቢነድ ኖሮ ፍርድን ወዲያው ከትንሳኤው በኃላ ያደርግ ነበር። ኢየሱስ እሳትን ሊጥል መጥቷል ይህ
እሳት የእግዚአብሔር ሕግ ነው። ይህ እሳት ግን ያን ጊዜ በሁሉ ላይ አልነደደም ነበር። ምክንያቱም ፍርድ
ለሁሉ የሚሰጥበት ዘመኑ አልነበረምና ነው። ኢየሱስ ይህ እሳት ቢነድ ኖሮ ኢየሱስ ሌላ ምንም ማድረግ
አያስፈልገውም ነበር። የተናገረውም ይህንን ነው። ነገር ግን እሳቱ ለፍርድ ከእግዚአብሔር ዙፋን
የሚወጣበትን ቀንን ይቀጥራል። ደግሞ ይህ እሳት በፍርድ የሚወጣበት ዘመን ገና እንደ ሆነ መንፈስ
ቅዱስ ያስረዳል። ይህም ፍርድ ለእኛ እንዲሆን ኢየሱስ ቀድሞን በፍርድ ማለፍ በእሳቱ ውስጥ እራሱ
መጠመቅ ነበረበት። ስለዚህም ኢየሱስ እንደ ሕጉ በመስቀል ላይ ፍርድን በመቀበል እንደ ሕጉ በእሳት
መስዋዕት ሆነ። የእሳትን ጥምቀት ሰለ ሁሉ ተቀበለ በዚያም የእግዚአብሔርን ፍርድ አፈጻጸሙን አሳየ።

እግዚአብሔር ሃጢያት ላይ ፈረደ እንጂ ጸጥ ብሎ አላለፈውም ወይም አልደመሰሰውም።


ኢየሱስ እግዚአብሔር በሕጉ ከፈረደበት በኃላ እዳችችን ከፍሎ ለዘላለም እስከ ዘላለም በሲኦል በእሳት
እየተቃጠለ አልተሰቃየም። ነገር ግን እግዚአብሔር የሞትን ጣር አጥፍቶ በሦስተኛው ቀን በኃላ ከሞት
አስነሳው። ስለዚህ የአለም ሁሉ ሃጢያት የተሸከመው ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ
ስለ ሃጢያታችን ለዘላለለም እስከ ዘላለም አልተሰቃየም። ምክንያቱም የእግዚአብሔር የፍርድ አሰራር
ለዘላለም እስከ ዘላለም ማሰቃየት አይደለምና ነው። ስለዚህ የእዳችንን ልክ ከፍሎ ስለጨረሰ ሕያው ሆኖ
ተነሳ። እግዚአብሔር ለዘላለም እስከ ዘለዓለም ሰዎችን በእሳት ያቃጥል ያሰቃያል የሚሉ ካሉ ኢየሱስ እኛ
ሕያዋን እንድንሆን ስለ እኛ እስከ አሁን እየተሰቃየ ነው እያሉ ወይም ባሪያው እንዳለው ኢየሱስን
ደግመው ደግመው እየሰቀሉት ይገኛሉ። ኢየሱስ ግን አንዴ ስለ ሃጢያት ፍርድን ተቀብሎ እዳችንን ከፍሎ
አሁን በነጻነት በክብር አርጎ በአባቱ ቀኝ ተቀምጧል። ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪገዛለትም ይጠብቃል።

እግዚአብሔር ፍርድ እንዳንገባ ቀድመን እንዴት መታረም እንዳለብንም ጳውሎስ


አስተማረን። ጳውሎስ የቆሮንጦስን ሰዎች በራሳችን ብንፈር ባልተፈረብን ይላቸዋል። ይህም በጊዜ
እራሳችን ከክፋት፣ ከዓመጽ ከሕግ የለሽ ኑሮ አላቆ እግዚአብሔር በሁሉ ወደ መምሰል በማደግ ነው። ይህ
ካልሆነ ሉቃስ ላይ እንዳየነው ከማያምኑ ጋር እድላችን ይሆናል። ከቅዱሳን ማሕበር ተሰንጥቀን
ከአመጸኞች ጋር በነጹ ዙፋን ፊት በእግዚአብሔር ሕግ እሳት ፍርድን እንቀበላለን። “ቅዱሳን እራሳቸው
ሳይቀር በእሳት ውስጥ የሚድኑ አሉ ብሎ ቃሉ ያስተምረናል። “saved, yet so as through fire”
(1.ቆሮ. 3፥15)

በራእይ ሃያ መሰረት በመጀመሪያው ትንሳኤ የሚነሳ ብፁዕ እና ቅዱስ የሆነ ከተቀበለው


መከራ መታዘዝን የተማረ የተቀደሰ አማኝ ወይም ድል ነሺ አማኝ ብቻ ነው። በሁለተኛው ትንሳኤ
በጠቅላለው በነጩ ዙፋን ፊት በሚሆነው ትንሳኤ ግን ድል ያልነሱ አማኞችና ክፉ ያደረጉ ሰዎች ሁሉ
በጠቅላላ የአዳም ዘር ሁሉ ይነሳሉ። ዮሐ.5፥28-29 ይህ እንደ ሆነ የነጩ ዙፋን ፍርድ እሳት በሆነው
በእግዚአብሔር ሕግ ይጀምራል። እግዚአብሔር ያን ጊዜ እሳት በሆነው በሕጉ ሁሉን እንደ ሥራው መጠን
ይከፍለዋል። እንደ ሕጉም እንደ ሃጢያቱም መጠን ሁሉ ቅጣቱን ይቀበላል። ስለዚህ ከእነዚህ ጋር
በሁለተኛው ትንሳኤ ላለመነሳት በቅድስና የምንኖር ድል ነሺ የተዘጋጀን ስንተጋ የምንገኝ አማኞች ልንሆን
የገባናል።

www.tlcfan.org 7
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ኢይሱስ በዮሐንስ 5 ላይ የሚናገረው ጥቂቶች ብቻ ስለሚነሱበት በመጀመሪያው መለከት


መነፋት የሚፈጸመውን የመጀመሪያውን ትንሳኤ አይደለም። ራዕ.20፥6 እየሱስ ይናገር የነበረው ስለ ሁሉና
ስለ ጠቅላላው ሰው ትንሳኤ ነው። ጳውሎስም ሆነ ዳንኤል ስለዚህ ትንሳኤ ተናግረዋል። ዳን.12፥2, ሐዋ.24፥
14-15 ይህ ደግሞ ሲኦልን የነፍስን የንቅልፍ ስፍራ (Hades)ን ባዶ ያደርገዋል።

ኢየሱስ እንዳለው በዚያን ቀን አንዳዶች ሕይወትን አለመበስበስን (immortality)


ይቀበላሉ። ሌሎቹ ደግሞ በእግዚአብሔር ፍርድን ይቀበላሉ። ይህም የእሳት ባሕር ነው። (the lake of
fire) ጳውሎስ በፊሊክስ ፊትም የመሰከረው ይህን የሁለተኛውን ትንሳኤ ነው። የመጀመሪያውና
የሚበልጠው ትንሳኤ ተብሎ በዕብ.11 የተጠቀሰው ትንሳኤ ግን ለጥቂቶች ለድል ነሺዎች ብቻ የሚሰጥ
ትንሳኤ ነው። እንደ ቀደዱና መረን የወጣ ሕይወት ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ከመጀመሪያም ትንሳኤና ሊገለጥ
ወዳለው ክብሩና መንግሥቱ ፈጽሞ አይገቡን። ሺው አመት እስኪፈጸም ከበር ውጭ ይቀራሉ።

ክርስቲያኖች አማኝ የሆኑ በሁለተኛው ትንሳኤ ሕይወትን የሚቀበሉ ወደ እሳት ባሕር


አይጣሉም። ነገር ግን በእሳት (በሕጉ) ይድናሉ። ማለት እሳት በሆነው በእግዚአብሔር ሕግ እንደሚገባው
መጠን ይፈረዳሉ። ሕጉ ስንል የኢየሱን ስራ ጠቅልሎ ነው። ፋሲካ እግዚአብሔር ሕግ ሲሆን የፋሲካ
መካከለኛ በጉ ኢየሱስ ነው።

ስለዚህ ሕግ ስንልን ኢየሱስ የሕጉ መካከለኛና ሰጪና ፈጻሚ መሆኑን መዘንጋት የለብንም።
የሚያምኑ ድል ያልነሱ ክርስቲያኖችና የማያምኑ ሁለቱም የሚፈረዱት በሕጉ ስለ ሆነ የክርስቲያኖችም
ፍርድ ሆነ የማይምኑ ፍርድ በእሳት ነው። ለማያምኑ ግን የእሳት ባሕር የሆነበት ምክንያት ብዙ ቁጣን
የሚቀበሉ ሰለሆነ ሳይሆን እነርሱም የሚቀበሉት ቅጣትና ፍርድ እንደየሥራቸውን መጠን ብቻ ነው።
የሚቀበሉት ነገር ግን እሳቱ ወይም በእነርሱ ላይ የወጣው የሕግ ፍርድ ባሕር መሆኑ የማያምኑት በፍርድ
ፊት እንደሚበዙ ብዛታቸውን በራእይ ለዮሐንስ እና ለእኛ የሚያመለክት ነው። ምክንያቱም በአመጸኞች
የሚደረገው ፍርድ በክርስቲያኖቹ ከሚደረገው ፍርድ ይልቅ ጊዜ የሚወስድ መሆኑን ብዙ መሆኑን
ለማመልከትም ጭምር ነው።

ይህ እሳት በኢዮቤልዮ ብቻ የሚፈጸም ብዙ የፍርድ ሂደትንና ዘመንን የሚወስድ ፍርድ


ነው። ይህ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነጻነት ቀን የኢዮቤልዮ ዘመን እስከሚደርሱ ድረስ
የሚቆይ ነው። ኢዮቤልዮን የሚያልፍ ግን ምንም አይነት እዳ ሆነ ሃጢያት ስለሌለ ያን ጊዜ
በመጀመሪያው አዳም ውስጥ የሰው ልጆች ወደ ነበራቸው እኩልነት በሁለተኛው አዳም ውስጥ
በእግዚአብሔር ምሕረት በኩል ይመጣሉ። ይህ የእግዚአብሔር የምሕረት ሕግ ነው። ሁሉ እንደ ገና
የእግዚአብሔር ልጆች ይሆናሉ። ወደ መጀመሪያው እርስታቸው በበለጠ ክብር ይመለሳሉ።
የእግዚአብሔር ቃል እንደሚያስተምረን የእግዚአብሔር ሕግ መጀመሪያ አላማ ለተበደለው ሰው በጽድቅ
ለመፍረድ ሲሆን ሁለተኛው አላማ ደግሞ በበዳዮ ላይ ፍርድን በመፍረድ ምሕረትን ማድረግ ነው። ይህ
ፍርዱን ሲጨርስ የሚሆነው ተሃድሶ ነው። የእግዚአብሔር በዳይ ካጠፋው ነገር በላይ እንዲቀጣና
እንዲሰቃይ አይፈቅድም። ነገር ግን እዳውን ሲከፍል ወደ ምሕረት ይመጣል። የእግዚአብሔር ሕግ
ሁለተኛው አላማው ሃጢያተኛውን በምሕረት ማደስ ነው።

www.tlcfan.org 8
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ነገር ግን ዛሬ ሰዎች ሰዎችን የመቅጣትና የማሰቃየተ ፍላጎት ጥልቀት በልባቸው ከሞላው


ክፋትና ራስ ወዳድነት የተነሳ ይህ የእግዚአብሔር ምሕረት ሕግ ከሰው አዕምሮ ተወስዷል። አለማችን
ይህንን የእግዚአብሔር የምሕረት ሕግ ብታውቅና እንደ እግዚአብሔር መፍረድ ብትችል አለማችን አሁን
ያለችበት ችግር ውስጥ አትወድቅም ነበር። ይህን እውነትን የሰው ልጆች ከአዕምሯቸው ተነጥቀውታል።
መዝሙር.103፥3-8 ላይ ዳዊት ይህ ስለገባው እንደ ሰዎች እግዚአብሔር “ ሃጢያትን ብትጠባበቅ ማን
ይቆማል? ይቅርታ ካንተ ዘንድ ነውና፣ አቤቱ ስለ ስምህ ተስፋ አደረግሁህ ነፍሴም በሕግህ ታገሰች”
ይላል። ስንቶቻችን ሕጉ ገብቶን በሕጉ ሁሉ ታግሰን የእግዚአብሔርን ፍርድ እንጠባበቃለን?

ልጆችን የወለዱ ሰዎች ይህን ቅጣት መመልከት አያቅታቸውም። ቅጣት ለልጅ መልካሙንና
ክፉውን ለይቶ ልጅ ያድግ ይበስል ዘንድ ወሳኝና አስፈላጊ ነው። ዕብ.12፥5-11 ሕግ ልክ እንደ ሞግዚት
(schoolmaster) ወደ ክርስቶስ መልክና ባሕሪ የሚቀርጸንና የሚጠርበን ጥሩ ምዶሻና መሮ ነው።
በእያንዳንዱ ቅጣት መጨረሻ ይቅርታ ከአባት ዘንድ አለው። ከቅጣት በኃላ ያለ ምሕረት ልጅ አባቱን
እዲያከብር ያደርገዋል። ይህ እውነተኛ የሆነ የእግዚአብሔር ፍርሃትን በልጁ ላይ ያመጣል። ያልተገባ
ቅጣት ወይም መጠን ያለፈ ቅጣት ተቀጪውን መራራ ከማድረጉ በላይ ተቀጪው ትክክለኛ ያልሆነ
ፍርሃት ውስጥ እንዲወድቅ ያደርገዋል። ይህ አይነት ቅጣት የሚያደርጉ አባቶች ልጆችን ከማጣታቸው
ባሻገር መከበርን ያጣሉ።

እግዚአብሔር ልጆቹን ይቀጣል። ለዚህም ነው ያመንን የእግዚአብሔር ልጆች የምንባለው።


ከዚህ የተነሳ እርሱ ብቸኛ አባታች ነው። እርሱ ፍጹምና ቅዱስ የሆነ አባትና አሳዳጊ ነው። እግዚአብሔር
በዕብራውያን አስራ ሁለት እንደምናገኘው ልጆቹን ይቀጣል። ነገር ግን ከሚገባን በላይ የሚቀጣን አባት
አይደለም። ለገዛ ጥቅምችን ከፍቅር የተነሳ ይቀጣናል፣ ይገርፈናልም። ይህም ከቅድስናው እንድንካፈል
እንድንቀደስ ነው። ይህን ቅጣት የለምዱ ልጆቹ ደግሞ ሰላም የበዛላቸው የጽድቅን ፍሬ የሚያፈሩ
በቅድስና የሚኖሩ ናቸው።

“5-6 እንደ ልጆችም ከእናንተ ጋር። ልጄ ሆይ፥ የጌታን ቅጣት አታቅልል፥ በሚገሥጽህም ጊዜ
አትድከም፤ ጌታ የሚወደውን ይቀጣዋልና፥ የሚቀበለውንም ልጅ ሁሉ ይገርፈዋል ብሎ የሚነጋገረውን
ምክር ረስታችኋል። 7 ለመቀጣት ታገሡ፤ እግዚአብሔር እንደ ልጆች ያደርግላችኋልና፤ አባቱ
የማይቀጣው ልጅ ማን ነው? 8 ነገር ግን ሁሉ የቅጣት ተካፋይ ሆኖአልና ያለ ቅጣት ብትኖሩ ዲቃላዎች
እንጂ ልጆች አይደላችሁም። 9 ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤
እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን? 10 እነርሱ
መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል
ለጥቅማችን ይቀጣናል። 11 ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ
ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።”

ሰዎች ስለ እግዚአብሔር ቅጣትና ፍርድ ሲያስቡ ጤነኛ የሆነ ፍርሃት እንደሌላቸው


እመለከታለሁ። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከሚገባው በላይ እንደሚቀጣና እንድሚያሰቃይ ሰዎች ስለ
ተማሩ ነው። አንዳን የሃይማኖት ድርጅቶች ድሮ ኢየሱስ እሳት ነው በጣም ያለ ልክ ከቀረብነው በሕይወት
ያቃጥለናል ብለው ያስተምሩ ነበር። ይህም ሰው ወደ እርሱና ወደ ቃሉ ቀርቦ እውነቱን እንዳያውቅና
የሚሰሩት ስራና የሚያስተምሩት ትምህርት ትክክል አለመሆኑን እንዳያውቅባቸው ነው።

www.tlcfan.org 9
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

ከዚህም የተነሳ ስንጸልይ እንኳን ወደ እርሱ በቀጥታ ከመሄድ ይልቅ በጻድቃን በኩል
አስቀድሞ መቅረብ ፍርድ ያቀላል በእነርሱ ስም መጸለይና ምጽዋት መቅረብ ይገባናል ይህም ምሕረትን
ፍትሃትን ያመጣልናል ይላሉ። ይህም እነሱን ስለ እኛ እንዲለምኑልን እንደሆነ ሕዝብን ያስተምራሉ።
ሰዎች ከክርስቶስ በፍርሃት መራቃቸውን ከተመለከትኩበት ቀን ጀምሮ አርነት በሚያወጣው
በእግዚአብሔር እውነት ቃሉ ሕዝቡ ነጻ ይወጣ ዘንድ ጸሎቴም ፍልጎቴም ነው። እባካችሁ የምትማኑት
እውነት እንደሆነ በእግዚአብሔር ቃል ፈትኑ መርምሩ። የሰውን ስብከት ወይም ትምህርት በአንድ
ሃይማኖት ዶክትሪን ወይም እምነት መፈተን ሞኝነትና ስሕተት ነው። ትክክለኛ የሆነ መፈተን
በእግዚአብሔር ቃል ብቻ የሆነ ምንም አይነት ሃይማኖተዊ ወገንተኝነት ካለው ማንነት ነጻ ወጥቶ
መፈተሽ ነው።

እንደ ኢያሱ ዛሬም እኔ በዚህ ምድር በሕይወት እስካለሁ ድረስ ይህ ሕዝብ የፈራውን
ታላቁን የእግዚአብሔር እረፍት ያለበትን እውነት ለመስለል እንደ እግዚአብሔር እይታ ነገሮችን ለማየት
ከዮርዳኖስ ባሕር ማዶ ርቆ ያለውን ለሕዝቡ የተገባውን የምድሪቱን ፍሬ ለሕዝቡ ይዤ ለመምጣት
ማንኛውንም ዮርዳኖስ ለማቋረጥ ቆርጫለሁ። ካሌብና ኢያሱ ነኝ ያለ አብሮኝ ይህን እውነት ይዞ
ይሰለፍ። ይህ እውነት በኢያሱና ካሌብ ላይ ድንጋይ እንዳስነሳ ድንጋይ እደሚነሳብን አውቀን ዋጋችንን
ተምነን ከእግዚአብሔርና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ብቻ እንወግን። የፈራና የደነገጠ ደግሞ ይመለስ።
እውነት ግን አንድ ነው። እውነት ደግሞ አይበሰብስም። የእውነት እውቀት ደግሞ አርነት ያወጣል።

ሰው እንደ ሆነ ኢየሱስ ባልጠበቀውም መንገድ ሲመጣበት ሲያይ ምትሃት እንደሚሆንበት


ከቃሉ አይቻለሁ። ነገር ግን አምላኬን አባቴን እግዚአብሔርን ያልሆነውን ነገር ነው ሲሉት ግን ዝምልል
ከቶ አልችልም። አላዋቂዎችን ዝም ታሰኝ ዘንድ የእግዚአብሔር ፍቃድ ነው። የሚለውን ቃል አስቡ።
ለተገለጠ ፍቃድ መገለጥ አያስፈልገውም ተነስቶ የሰነፍ አፍ ዝም ማሰኘት ነው።

ፍሬውንም ከዮርዳኖስ ማዶ ሰው ሰው ሰምቶ ከማያውቀውና ቀምሶት ከማያቀው


የእግዚአብሔር ያለፈ ክብር ስናመጣ። ሰው መናውን ይዞ የሙጥኝ ሊል እንደሚችል እርግጠኛ ነኝ። እንቢ
ብሎ በምድረበዳ ከመናው ጋር ቢጣበቅ እንደ ጉበኛ ቅጥር ጠባቂ ወደ ከፍታ ወጥተን የተመለከትነውን
በመናገር ከማንኛው ሰው ደም ራሳችንን ነጻ እናደርጋለን ደግሞ ከንቱ የሆነን ፍርድ በሰዎች ላይ ከመናገር
እንድናለን።

እስቲ ልጆች ያላችሁ አባትና እናቶች ሁሉ ፍረዱኝ ልጆቻችሁ አባታቸውና እናታቸው እንዲ
ክፉ የሆነ አባትና እናት ናቸው ተብለው ቢማሩ ምን ይሰማችኃል? እውነትስ እንደ አባትስ ልጆቻችሁን
በማይጠፋ እሳት እያቃጠላችሁ ማየት ይሆንላችኃልን? እናንተ በዳቦ ፋንታ እባብ ካልሰጣችሁ የሰማይ
አባታችሁስ? ይህን ሊያደርግ አይችልምን? እኔም ዛሬ ሁላቹን ጳውሎስ እንዳለ እንደ ባለ አዕምሮ አስቡ
ብዮ ከሕሊናችሁና የእግዚአብሔር ቃል በዚች መጣጥፍ ትቼላችሁ አልፋለሁ።

ዛሬ አቢያተ ክርስቲያናት የአባታችንን የእግዚአብሔርን ባሕሪ አላወቀችም። ስለዚህም


የምታስተምረው ትምሕርት ከሁሉም የእምነት ድርጅቶች የማይለይ ሰቆቃና ጭንቀት የሞላበት ነው።
የሚያሳዝነው ግን ማንኛውንም የሃይማኖት ድርጅትን እግዚአብሔር ፈጽሞ እለማወቁ ነው።
እግዚአብሔር ሁሉን ሰው በመጀመሪያው ወይም በሁለተኛው አዳም ውስጥ ብቻ ይመለከተዋል።

www.tlcfan.org 10
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

እግዚአብሔር የየትኛውም እምነትና ሃይማኖት አባል፣ አማኝና ተከታይ ስለሆንክ ብሎ


ላንተ የሚሰጥህ የተለየ ነገር የለም። እግዚአብሔር ሁሉን በአንዱ አዳም ወይም በኢየሱስ ክርስቶስ
ያያል። ሁላችን ከአንዱ አዳም መምጣታችንን አንዘንጋ። የሰውን ስርዓትና የሰው ስራሽን ሃይማኖት
እንተውና በአንዱ አብታችን ሕብረት ውስጥ ገብተን ከምግዜው በላያ እንድነታችን እናጎልብት። አንዱና
ብቸኛውን የምሕረት አባታን የሆነው እግዚአብሔር ብቻ እንፈልግ።

ሰዎች እንዲፈሩ ለመሪዎቻቸው እንዲገዙ ለማድረግ ወይም ሕዝቡ ነጻነትና የእግዚአብሔር


ጥበቃና ፍቅር እንዳይገባው በዚህ አይነት ትምህርት ብዙዎችን ጠፍረው ያሰሩ ብዙ ሃይማኖቶች በምድር
ላይ አሉ። ዛሬ ሃይማኖት ሳይሆን የሚያስፈልገን በእግዚአብሔር ቃል ላይ ትክክለኛ እምነት ነው።
ኢየሱስም ወደ ምድር ሲመጣ ሊያይ የሚናፍቀው እምነትን እንጂ የየትኛው ሃይማኖት ድርጅት አባል
መሆናችንን አይደለም። አይሁድ የለም ግሪክ የለም ሴት የለም ወንድ የለም። የሚለውን ቃል በደንብ
አስተውሉ።

የልጆች ልብ ወደ አባቶች የአባቶችም ልብ ወደ ልጆች በማስፈራራትና በተሳሳተ ትምህርት


ያልሆነውን የእግዚአብሔር ባሕሪ በማስተማር ፈጽሞ አይመጣም። እውነተኛ የአባትነትን ባሕሪ
ማስተማር ሆነ በእርሱ በአባትነት ባሕሪ መገለጥ ግን መከበርንም ሆነ መፈቀርን ያመጣል። የውሸትን
ፍራትና ያልተገባን አይነት ፍርሃትን ያስወግዳል። ሰው ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን በእውነተኛ መፍራት
የሚገባው ክርስቶስን ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር በምሕረቱ በሚመኩትና በሚታመኑት ደስ ይሰኛልና።
መዝ.147፥11 ይህ እውነት ገብቶን ካመን እግዚአብሔር ደስ እንዳሰኛችሁት እመሰክርላችኋለሁ።
የእግዚአብሔር የምሕረት ሕግ እንግዲህ ፍቅርን ክብርን ነጻነትን የተሞላ ነው። ከእግዚአብሔር ጋርና
ከቃሉ ጋር መወገን እንዲሆንላችሁ ጸሎቴ ነው።

በሚቀጥለው ቁጥር ሰባት እትማችን ለዳዊት እግዚአብሔር እንዴት ምሕረትን


እንደ ሕጉ እንዳደረገለት እንመለከታለን

www.tlcfan.org 11
የእግዚአብሔር መንግስት ሕጎች #6

www.tlcfan.org 12

You might also like